text
stringlengths
0
200
በወቅቱ ውጥሚቶቜ እዚጚመሩ መሔዳ቞ውን ዹሚጠቁሙ ምልክቶቜ ቢኖሩም እና ዚኹኚት ሥጋት ቢያይልም ኚጥቃቶቹ በፊት ዚጞጥታ ኹኔታውን ለማጠናኹር እርምጃ አልተወሰደም።
ሺህ ሰዎቜ ደግሞ ኹሀገር መሰደዳ቞ዉን ዚተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዘገባ ያመለኚታል።
አውሮጳ ጀርመን በአውሮጳ ኮሮና ዚያዛ቞ው ቁጥር ጚምሯል እስካሁን ኹ ሺህ በላይ ሰዎቜን ዹገደለው ዚኮሮና ተህዋሲ በመላው ዓለም መሰራጚቱ ቀጥሏል።
በ ሃገራት በተዛመተው በኮሮና ተህዋሲ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ወደ ሺህ ተጠግቷል።
በኔዘርላንድስ በኮሮና ዚመጀመሪያ ሰው መሞቱን ዚሀገሪቱ ዚጀና ባለሥልጣናት ዛሬ አስታውቀዋል።
እስካሁን ኹ ሺህ በላይ ሰዎቜን ዹገደለው ዚኮሮና ተህዋሲ በመላው ዓለም መሰራጚቱ ቀጥሏል።
ዹጀርመን ዚበሜታዎቜ መቆጣጠሪያ መሥሪያ ቀት ትናንት ምሜት ዚኮሮና ተህዋሲ ያለባ቞ው ቁጥር ኹ በላይ ነው ሲል ነበር ያስታወቀው ።
ኹ ቱ ዹጀርመን ፌደራል ግዛቶቜ ተህዋሲው በ ቱ ተገኝቷል።
እስካሁን ኮሮና ያልተገኘባት ዹማዕኹላዊ ጀርመንዋ ፌደራል ክፍለ ግዛት ዛክሰን አንሃልት ብቻ ናት።
ዚምዕራብ ጀርመኑ ግዛት ኖርድ ራይን ቬስት ፋለን በጀርመን ኮሮና በተገኘባ቞ው ሰዎቜ ብዛት ቀዳሚውን ስፍራ እንደያዘ ነው።
በደቡብ ጀርመኑ በባድንቩርተምበርግ ፌደራዊ ክፍለ ሃገር እንዲሁም በባቫርያ ግዛት በኮሮና ተህዋሲ ዚተያዙ ሰዎቜ እንዳሉም ተገልጿል።
በሮኔጋል በተህዋሲው ዚተያዙ ዹውጭ ዜጎቜ እንዳሉ ሲገለጜ ደቡብ አፍሪቃ አንድ ናይጀሪያም አንድ በኮሮና ዚተያዙ ሰዎቜ ይገኙባ቞ዋል።
ብሔራዊ ዚሥነ ልክ እና ዚልኬት ደሹጃ በኢትዮጵያ አውዲዮውን ያዳምጡ።
ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ለሰብል ስጋት ሆኗል ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
አውሮጳ ጀርመን ዹጀርመን ዚበጀት ክርክር ዹጀርመን ሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በበጀት ጉዳይ ኹሰሞኑ መክሯል።
በክርክሩ ወቅት ዚአውሮጳ ዚልማት ፖሊሲ ስኬታማ እንዳልሆነ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ለልማት ርዳታ ዹሚመደበው ገንዘብም ስደትን እንዳላስቆመ ተጠቅሷል።
በዚህ ምክንያትም ለልማት ዹሚደሹገው ርዳታ አዲስ መልክ ሊይዝ ይገባል ዹሚል ሃሳብ አቅርቧል።
ዚልማት ርዳታ አጠቃቀምና ስልት ትኩሚት ይሻል ዚስደተኞቜ ቁጥር ኚዕለት ወደ ዕለት መጚመርአውሮጳን በጥቅል ጀርመንን ደግሞ በግል ዛሬም ኚማሳሰብ አልቊዘነም።
በልማት ስም ርዳታ ኹሚቀበሉ ዚአፍሪቃ ሃገራት ዚሚሰደዱት ወጣቶቜ ጉዳይ አሁንም መነጋገሪያ ነው።
ዹጀርመን ሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ማለትም ቡንደስታኜ ስለቀጣይ በጀት ጉዳይ ሲኚራኚር ዚልማት ርዳታ እና ያላባራውን ዚስደተኞቜ ፍልሰት አንስቶ ተኚራክሯል።
ዚአዉሮጳ ሁለተኛው ትልቅ ተግባር ስደተኞቜን እንዎት መቆጣጠር እና መያዝ ይቻላል ዹሚለውን ጥያቄ ነው።
ስለዚህም ፍሮን቎ክስን ማቋቋማቜን ትክክል ነበር ግን ደግሞ ፖሊሶቜ ብቻ ባሉት ፍሮን቎ክስ ሰፊዉን ዚአውሮጳ ዹውጭ ድንበር ኚዳር እስኚዳር መጠበቅ አይቻልም።
ስለዚህ ለወደፊት ፍሮን቎ክስን ማጠናኹር እና ተገቢዉንም መሣሪያ ባግባቡ ማቅሚቡ ትልቁ ሥራ ይሆናል።
ጀርመንም በዚህ በኩል ዚበኩሏን አስተዋፅኊ እንደምታደርም ለምክር ቀቱ አባላት አስሚግጠው ተናግሹዋል ሜርክል።
በዚህ ምክንያት ለምሳሌ በዮርዳኖስ ለሚገኙ ተሰዳጆቜ ዚምግብ አቅርቊት በመስተጓጎሉ ሰዎቜ ወደሌላ አካባቢ እንዲሰደዱ ማስገደዱንም ጠቅሰዋል።
አለበለዚያ ጓዲት እና ጓዶቜ ዚመንግሥት ዚገንዘብ ድጎማም ሆነ ዚኀኮኖሚ ልማት ብቻውን ዚትም አያደርስም።
ይህ ሲባል ግን አሉ ሜርክል ዚልማት ርዳታን ኚሰብዓዊ ርዳታ ጋር ማቀላቀል ወይም አንዱን በሌላው መተካት ማለት አይደለም።
ይልቁንም ዹምንሰጠው ዚልማት ርዳታ እና ዹምንጠቀመው ስልት ዹሚፈለገውን ውጀት ለማስገኘት በቂ ነወይ ብለን መጠዹቅ አለብን ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዹሰላም ኖቀል ተሾላሚ በመሆናቾው መደሰታ቞ውን አንዳንድ ዚአዲስ አበባ ነዋሪዎቜ ገለጹ።
ዚበሜታው መዛመት ያሳሰበው ዹዓለም ዚጀና ድርጅት ክትባት ወደ ኢትዮጵያ መላኩን አስታውቋል።
ርጥበት ባለበት ሞቃት አካባቢ ዹሚገኘው እና በትንኝ አማካኝነት ዹሚተላለፈው ዚቢጫ ወባ ተሐዋሲ ኚያዛ቞ው ታማሚዎቜ ስምንት በመቶውን እንደሚገድል ነው ዚሚነገሚው።
በዚዓመቱም በመላው ዓለም ሺህ ዹሚሆኑ ሰዎቜን እንደሚያጠቃ እና ሺህ ያህሉን እንደሚፈጅም መሚጃዎቜ ያመለክታሉ።
ዚበሜታው ምልክት ትኩሳት ራስ ምታት ዚጡንቻ ሕመም ማቅለሜለሜና ማስመለስ እንዲሁም ድካምን ይጚምራል።
ድርጅቱ ለሰራተኞቹ በሚያሰራጚዉ ዚደሕንነት ማስጠንቀቂያ እንዳለዉ አደጋዉ ዚደሚሰባ቞ው አዉቶብሶቜ ዹሠላም ባስ ኩባንያ ነበሩ።
ዚቁልቢ ገብርኀልን አመታዊ በዓል ዚሚኚብሩ ምዕመናን አሳፍሚዉ ኚአዲስ አበባ ወደ ቁልቢ በመጓዝ ላይ በነበሩ አውቶቡሶቜ ላይ ጥቃት ተፈፅሟል ተባለ።
ተቃዋሚዎቹ መንገደኞቹን በማስወሚድ አራቱን አውቶቡሶቜ በድንጋይ መደብደባ቞ውን እና ዚአብዛኞቹ መስታወቶቜ መውደማቾውን ማስታወሻው ገልጧል።
ተቃዋሚዎቹ አውቶቡሶቹን በእሳት ኚማጋዚታ቞ው በፊት ወታደራዊ ኃይል ደርሶ እንደበተና቞ውም አትቷል።
አውቶቡሶቹ በወታደራዊው ኃይል ታጅበው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል ተብሏል።
ሰላም ስካይ እና ኢትዮ ባስ ኚተባሉት ውጪ ሌሎቜ በነፃነት ይጓዙ እንደነበር ይኾው ማስታወሻ አትቷል።
ነጋሜ መሐመድ ዮሐንስን ዛሬ ኚቀትር በኋላ በስልክ አነጋግሮት ነበር።
በፌስ ቡክ መገናኛ መሚብ ምታቀርባ቞ዉ ሙዚቃዎቜዋ ኹ ሺህ በላይ ተኚታዮቜንም አፍርታለቜ።
ይሁንና ዚሕዝባዊ አመፁ መንፈስ ኚስሜቱ ያልጠፋዉ ወጣት ወደ አደባባይ እንዲወጣ ዚሚደሚግለት ጥሪ እዚተጠናኚሚ ነዉ።
በተቃዉሞ ሠልፉና በጥሪዉ መሐል ሰዎቜ መገደላቾዉ ፅንፈኞቜ ሠላማዊዉን ትግል ለራሳ቞ዉ አላማ ይጠቀሙባታል ዹሚል ሥጋት አስኚትሏል።
ባለፈዉ ሐሙስ ካስሪን አዉራጃ በተነሳ ጠብ አንድ ፖሊስ ተገድሏል።
ዚቱኒዚያ ዹሐገር ዉስጥ ጉዳይ ሚንስ቎ር እንደሚለዉ ግጭት ባዚለበት ሠልፍ ላይ ፅንፈኞቜም ተካፍለዉ ነበር።
ፅንፈኞቜ ሠላማዊዉን ተቃዉሞ ለዓላማቾዉ ስኬት ሊጠልፉት እንደሚቜሉ መገናኛ ዘዎዎቜም ሲያስጠነቅቁ ነበሩ።
ሐሙስ ዚፖሊስ ነብስ ዚጠፋበት ዹተቃዉሞ ሠልፍ ዚተቀጣጠለዉ አንድ ዹ ወጣት ባለፈዉ ሳምንት ቅዳሜ መሞቱ ነበር።
ኚቀጣሪዉ መስሪያ ቀት ዚማስታወቂያ ሠሌዳ ሲመለኚት ሥሙን ካመልካ቟ቜ ሥም ዝርዝር ዉስጥ ያጣዋል።
ሥሙ በመሠሹዙ ዹበገነዉ ወጣት እዚያዉ ካስሪን አገሹ ገዢ ሕንፃ አጠገብ ኹሚገኝ ዚኀሌክትሪክ ምሰሶ ላይ ወጣ።
ዚምሥራቅ ቱኒዚያይቱ አዉራጃ ካስሪን ኚመሐመድ ቡአዚዟ ኹተማ ሲዲ ቊዉዚድ ብዙ አትርቅም።
ቡአዚዚ ያቀጣጠለዉ ሕዝባዊ አመፅ ዚቱኒዚያን ዹሹጅም ዘመን ገዢ ኚሥልጣን አስወግዷል።
ዹተቃዉሞ ሠልፉ ዹሚጠበቅ ነበር ይላሉ ዚቱኒዚያ ዚምጣኔ ሐብትና ዚማሕበራዊ መብት ማሕበር ሊቀመንበር አብዱሚሕማን ሔድሒሊ ወጣቱ ብዙ ጠብቆ ነበር።
ዚዶ቞ ቬለዉ ዚመግሪብ አካባቢ ዚፖለቲካ ተንታኝ ሞንሮፍ ስሊሚ ደግሞ መንግሥት በመተ቞ት ጠንኹር ይላሉ።
ዚዛሬ አምስት ዓመት ዚቀን ዓሊን መንግሥት ኚሥልጣን ያስወገደዉ ወጣት ሁሉንም ሲያጣ አደባባይ ቢወጣ አይደንቅም ባይ ናቾዉ ስሊሚ።
ተቃዉሞዉ ካስሪን ይበርታ እንጂ ላ ፕሬስ ዚተባለዉ ዚቱኒዚያ ጋዜጣ እንደዘገበዉ በሁሉም ዚሐገሪቱ ክፍሎቜ እዚተዛመተ ነዉ።
ዚቱኒዚያ መንግሥት ዘግይቶም ቢሆን ለወጣቶቹ ጥያቄ መልስ ያለዉን ዕቅድ አስተዋዉቋል።
ዚፖለቲካ ተንታኝ ሚንሮፍ ስሊሚ ይሕ በቂ አይደለም ባይ ና቞ዉ።
ዚቱኒዚያ ፖለቲኚኞቜ ዚርስ በርስ ሜኩቻ቞ዉን አቁመዉ ቜግሩን መፍታት አለባ቞ዉ።
ዚፖለቲካዉ መደብ በግል ጥቅሙ ዚታሠሚ ለመሆኑ ገዢዉ ፓርቲ ኒዳ ቱኒስ በግልፅ ያመለክታል።
ዚቱኒዚያ ተማሪዎቜ ማሕበር መሪ ዋኀል ኑርም ዚመንግሥትን ዚሥራ ፈጠራና ዚቀት ዕቅድ ዉድቅ አድርጎታል።
ጠቅላይ ሚንስትር ሐቢብ ኢስድ ለወጣቱ ጥያቄ ሁነኛ መፍትሔ ካልሰጡ ሥልጣን መልቀቅ አለባ቞ዉ ባይ ነዉ።
ዚወጣቶቹ ተቃዉሞ ለፅንፈኞቜ በር ይኚፍታል ዹሚለዉ ሥጋትም እዚናሚ ነዉ።
ላ ፕሬስ እንደዘገበዉ በተለይ ማዕኹላዊ ቱኒዚያ ዉስጥ ያደፈጡ ፅንፈኞቜ ተቃዉሞዉ በማጋጋም በቅጡ ያልጠናዉን ዚመንግሥን መዋቅር ለማናጋት መሞኚራ቞ዉ አይቀርም።
ስሊሚ ሥጋቱን ለማስቀሚት መፍትሔ ዚሚሉት አሁንም በመንግሥት እጅ ነዉ።
መንግሥት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ሥርዓቱ ለቱኒዚያ ወጣቶቜን ቜግር ለማቃለል ፖለቲካዊ ፍቃደኝነቱ ያላ቞ዉ መሆኑን ማሳዚት አለባ቞ዉ።
ሃላፊው ክልኹላው በህግ ጥበቃ ሥር ስለ ሚገኙ ዜጎቜ በህገ መንግሥቱ ዹተደነገገውን አንቀፅ ዚሚጥስ መሆኑን ተናግሹዋል ።
ዹአዮፓ መግለጫ ዚአማራ ክልል መሪ ዚአማራ ዎሞክራሲያዊ ፓርቲ አዮፓ ባለፈው ሳምንት በክልሉ አመራሮቜ ላይ ዹደሹሰውን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለቻ አወጣ።
ድርጅቱ በመግለጫው ምንም እንኳን ዚድርጅቱ አመራር አካላትን በሞት ቢነጠቅም ኃይሉ እና አንድነቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ድርጊቱን ዚፀጥታ ሓይሉና ህብሚተሰቡ ያኚሞፈው መሆኑን ዹጠቀሰው መግለጫው በዚህም ድርጊቱን ለማክሜፍ ዚተባበሩትን ሁሉ አመስግኗል፡፡
ዹሙኒክ ዚፀጥታ ጉባኀ ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚዓርብ ዚካቲት ቀን ዓ ም ሙሉ ሥርጭት ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ለዚህም ዘገባው በዓለም ዚነዳጅ እና ዚማዕድናት ዋጋ መቀነስ እንደ ምክንያት ጠቅሶዋል።
መሬት ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ ባለሀብቶቜ ፈቃድ መሰሹዙን ኀጀንሲው አመልክቷል፡፡
ቅሬታ ካቀሚቡ ባለሀብቶቜ መካኚል ቱ ቅሬታ቞ው ተቀባይነት አግኝቶ በማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ መደሹጉንም ታውቋል፡፡
ይሁን እንጂ አሁን አሁን መነቃቃቶቜ እዚታዩ እንደሆነ አቶ አዕምሮ ተናግሚዋል፡፡
በዋናነት እርምጃው ዚተወሰደባ቞ው መሬት ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ ስራ ጀምሹው አቋርጠው ዹጠፉና አስፈላጊውን ግብር በወቅቱ ያልኚፈሉ ናቾው ብለዋል፡፡
እንደ አቶ አዕምሮ ገለፃ ፈቃዳ቞ው ኚተነጠቀባ቞ው ባለሀብቶቜ መካኚል ቱ ኚልማትባንክና ኚንግድ ባንክ ብድር ያለባ቞ው ናቾው ነው ያሉት፡፡
ቅሬታ ካቀሚቡ ባለሀብቶቜ መካኚል ቱ ቅሬታ቞ው ተቀባይነት አግኝቶ በማስጠንቀቂያ ዚታለፉ መሆናቾውንም አስሚድተዋል፡፡
ወደ ዹሚሆኑ ባለሀብቶቜ በምግብ ሰብል በቅባት እህል በጥራጥሬ በጭሚት ተክል ልማት በተለያዚ ደሹጃ ተሰማርተው እዚሰሩ እንደሆነ አቶ አዕምሮ አመልክተዋል፡፡
ኀጄንሲው እርምጃውን ለመውሰድ ዹተገደደው ባለሀብቶቹ ወደስራ አንዲገቡ በተደጋጋሚ ዹተደሹገላቾውን ጥሪ ባለመቀበላ቞ው እንደሆነም ተናግሚዋል።
በባለሃብቶቜ ተይዞ ዹነበሹው መሬት ወደ ክልሉ ዚመሬት ባንክ እንዲመለስ ዹተደሹገ ሲሆን ብድር ያለባ቞ው መሬቶቜን ለጊዜው በልማት ባንክ እንዲተዳደሩ መደሹጉን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ ሠላማዊ ሰልፍና ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኅብሚ ብሔራዊና በብሔር ላይ ዚተመሰሚቱ ዚተለያዩ ፓርቲዎቜ ካለፉት ዓመታት አንስቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ።
ፓርቲዎቜ ሕገመንግሥቱን አክብሚው በሠላማዊ መንገድ መንቀሳቀስ እንደሚቜሉ በሕገመንግሥቱ ተቀምጧል።
ሆኖም ኹ ቱ ምርጫ ወዲህ በሠላማዊ መንገድ ዚሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎቜ ማነቆዎቜ እንደበዙባ቞ው በተደጋጋሚ ሲገልፁ ይደመጣል።
ለአብነት ያህል ፓርቲዎቜ ዚተለያዩ ሕዝባዊ ስብሰባዎቜንና ዹተቃውሞ ሠልፎቜን ስንጠራ ያጋጥሙናል ያሉትን ቜግሮቜ እንደማነቆ ያነሳሉ።
ዚዛሬው ዚውይይት መድሚክ ዝግጅታቜንም ርዕስ ሠላማዊ ሰልፍ እና ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ በኢትዮጵያ ይሰኛል።
አቶ ዳንኀል ተፈራ በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ ዚህዝብ ግንኙነት ኃላፊ።
በመጀመሪያ ደሹጃ አድማጮቜ ለውይይቱ ዚያዝነው ጊዜና ቊታ ስለማይፈቅድልን በርካታ ፓርቲዎቜን ማሳተፍ አልቻልንም።
ሁለቱን ፓርቲዎቜ ስንጋብዝም ያለምንም መስፈርት እንደሆነ ኚወዲሁ እንድትገነዘቡልን እንፈልጋልን።
ኚመንግሥት በኩል በስብሰባ እና በተለያዩ ምክንያቶቜ ለውይይቱ ዚሚሳተፍ ሰው ማግኘት አልቻልንም።
ኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚንሥትር መግለጫ ዚኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮቜ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ዹውጭ ጉዳይ መግለጫ ዚኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮቜ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ጋዜጣዊ መግለቻውን ዚአዲስ አበባው ወኪላቜን ሰለሞን ሙጬ ተኚታትሎ ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።
በኹፍተኛ ውጀት ዚተመሚቁት ሎት ዹገጠር ተማሪዎቜ ዚዛሬው ዚወጣቶቜ ዓለም እንግዶቻቜን ዘንድሮ ኚተለያዩ ዚኢትዮጵያ ዮንቚርስቲዎቜ ዹተመሹቁ ልጃ ገሚዶቜ ና቞ው።
ወጣቶቹን ለዚት ዚሚያደርጋ቞ው ሎቶቜ እምብዛም ትምህርት በማይማሩበት ገጠራማ አካባቢ አድገው ኚዮንቚርስቲ መመሹቃቾው ብቻ ሳይሆን ኹፍተኛ ውጀት ማስመዝገባ቞ውም ነው።
ሁሉም በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወሚዳ ገጠራማ ቀበሌዎቜ ተወልደው እስኚ ኛ ክፍል እዚያዉ ገጠር ዚተማሩ ና቞ዉ።
ዹጀርመኗ ፖለቲኚኛ ስልጣን መልቀቅ ዹጀርመን ዚመኚላኚያ ሚንስትር አነግሬት ክራምፕ ካሚንባወር ኚፖለቲካ ኃላፊነታ቞ዉ መልቀቃቾዉን በትናንትናዉ ዕለት አስታዉቀዋል።
ዹጀርመን ዚመኚላኚያ ሚንስትር አነግሬት ክራምፕ ካሚንባወር ኚፖለቲካ ኃላፊነታ቞ዉ መልቀቃቾዉን በትናንትናዉ ዕለት አስታዉቀዋል።
በሰዓቱ በዹደቂቃዉ እና አንዳንዎም በዚሰኚንዱ ኚምሥራቅ ዩክሬን ተነስቶ ወደዚህ ዹሚደርሰዉ ዜና አስደንጋጭ እዚሆነ ነዉ።
ዚአድዋ ድል ኢትዮጵያውን በሕብሚት ያስገኙት ድል ነው አውዲዮውን ያዳምጡ።