text
stringlengths
4
267
በተቀደሰ መኖሪያው ያለው አምላክአባት ለሌላቾው ልጆቜ አባት፣ ለመበለቶቜ ደግሞ ጠባቂ ነው።
አምላክ ብ቞ኛ ለሆኑ ሰዎቜ መኖሪያ ቀት ይሰጣ቞ዋልፀእስሚኞቜን ነፃ አውጥቶ ብልጜግና ያጎናጜፋ቞ዋል። ግትር ዹሆኑ ሰዎቜ ግን ውኃ በተጠማ ምድር ይኖራሉ።
አምላክ ሆይ፣ ሕዝብህን በመራህ ጊዜ፣በሚሃውንም አቋርጠህ በተጓዝክ ጊዜ (ሮላ)
ምድር ተናወጠቜፀበአምላክ ፊት ሰማይ ዝናብ አወሚደፀይህ ዚሲና ተራራ በአምላክ ይኾውም በእስራኀል አምላክ ፊት ተናወጠ።
አምላክ ሆይ፣ ብዙ ዝናብ እንዲዘንብ አደሚግክፀለዛለው ሕዝብህ ብርታት ሰጠኞው።
ድንኳኖቜህ በተተኚሉበት ሰፈር ሕዝብህ ተቀመጠፀአምላክ ሆይ፣ በጥሩነትህ ለድሃው ዚሚያስፈልገውን ሰጠኞው።
ይሖዋ ትእዛዝ አስተላለፈፀምሥራቹን ዚሚያውጁ ሎቶቜ ታላቅ ሠራዊት ና቞ው።
ዚብዙ ሠራዊት ነገሥታት እግሬ አውጭኝ ብለው ይሞሻሉ! በቀት ዚምትቀር ሎትም ምርኮ ትካፈላለቜ።
እናንተ በሰፈሩ ውስጥ በሚነድ እሳት መካኚል ብትተኙ እንኳ፣በብር ዚተለበጡ ክንፎቜናበጠራ ወርቅ ዚተለበጡ ላባዎቜ ያሏት ርግብ ትኖራለቜ።
ሁሉን ቻይ ዹሆነው ነገሥታቷን በበታተነ ጊዜ፣በጻልሞን በሚዶ ወሚደ።
በባሳን ዹሚገኘው ተራራ ዹአምላክ ተራራ ነውፀበባሳን ዹሚገኘው ተራራ ባለ ብዙ ጫፍ ተራራ ነው።
እናንተ ባለ ብዙ ጫፍ ተራሮቜ ሆይ፣አምላክ መኖሪያው አድርጎ ዹመሹጠውን ተራራ በምቀኝነት ዓይን ዚምታዩት ለምንድን ነው? አዎ፣ ይሖዋ በዚያ ለዘላለም ይኖራል።
ዹአምላክ ዹጩር ሠሚገሎቜ እልፍ አእላፋት፣ ሺህ ጊዜ ሺህ ና቞ው። ይሖዋ ኚሲና ወደ ቅዱሱ ስፍራ መጥቷል።
ወደ ላይ ወጣህፀምርኮኞቜን ወሰድክፀአምላካቜን ያህ ሆይ፣ በመካኚላ቞ው ትኖር ዘንድሰዎቜን፣ አዎ እልኞኛ ዚሆኑትን ጭምር እንደ ስጊታ አድርገህ ወሰድክ።
ሞክማቜንን በዚዕለቱ ዚሚሞኚምልን፣ዚሚያድነን እውነተኛው አምላክ ይሖዋ ይወደስ። (ሮላ)
እውነተኛው አምላክ፣ አዳኝ አምላካቜን ነውፀደግሞም ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ኚሞት ይታደጋል።
አዎ፣ አምላክ ዚጠላቶቹን ራስ፣ኃጢአት መሥራታ቞ውን ዹማይተዉ ሰዎቜንም ፀጉራም አናት ይፈሚካክሳል።
ይሖዋ እንዲህ ብሏልፊ “ኚባሳን መልሌ አመጣ቞ዋለሁፀኚጥልቅ ባሕር አውጥቌ አመጣ቞ዋለሁፀ
ይህም እግርህ በደም እንዲታጠብ፣ውሟቜህም ዚጠላቶቜህን ደም እንዲልሱ ነው።”
አምላክ ሆይ፣ እነሱ ዚድል ሰልፍህን ያያሉፀይህም አምላኬና ንጉሀ ወደ ቅዱሱ ስፍራ ዚሚያደርገው ዚድል ጉዞ ነው።
ዘማሪዎቹ ኚፊት ሆነው ሲጓዙ በባለ አውታር መሣሪያዎቜ ዚሚጫወቱት ሙዚቀኞቜ ደግሞ ኹኋላ ይኹተሏቾው ነበርፀአታሞ ዚሚመቱ ወጣት ሎቶቜም በመካኚላ቞ው ነበሩ።
ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበት አምላክን አወድሱፀእናንተ ኚእስራኀል ምንጭ ዚተገኛቜሁ ሰዎቜ፣ ይሖዋን አወድሱ።
ዹሁሉም ታናሜ ዹሆነው ቢንያም በዚያ ሰዎቜን ይገዛልፀዚይሁዳ መኳንንትም ኚሚንጫጩ ጭፍሮቻ቞ው ጋር፣እንዲሁም ዚዛብሎን መኳንንትና ዚንፍታሌም መኳንንት በዚያ አሉ።
አምላካቜሁ ብርቱዎቜ እንድትሆኑ አዟል። ለእኛ ስትል እርምጃ ዚወሰድኚው አምላክ ሆይ፣ ብርታትህን አሳይ።
በኢዚሩሳሌም ካለው ቀተ መቅደስህ ዚተነሳ፣ነገሥታት ለአንተ ስጊታ ያመጣሉ።
ሕዝቊቹ ኚብር ዚተሠሩ ነገሮቜን አምጥተው እስኪሰግዱ ድሚስበሞምበቆዎቜ መካኚል ዚሚኖሩትን አራዊት፣ዚኮርማዎቜን ጉባኀና ጥጆቻ቞ውን ገሥጜ። ይሁንና ጊርነት ዚሚያስደስታ቞ውን ሕዝቊቜ ይበታትናል።
ኚነሐስ ዚተሠሩ ዕቃዎቜ ኚግብፅ ይመጣሉፀኢትዮጵያ ለአምላክ ስጊታ ለመስጠት ትጣደፋለቜ።
እናንተ ዚምድር መንግሥታት ሆይ፣ ለአምላክ ዘምሩፀለይሖዋ ዚውዳሎ መዝሙር ዘምሩፀ (ሮላ)
ኚጥንት ጀምሮ በነበሩት ሰማዹ ሰማያት ላይ ለሚጋልበው ዘምሩ። እነሆ፣ እሱ በኃያል ድምፁ ያስገመግማል።
ለአምላክ ብርታት እውቅና ስጡ። ግርማዊነቱ በእስራኀል ላይ ነውፀብርታቱም በሰማያት ውስጥ ነው።
አምላክ ኚታላቅ መቅደሱ ሲወጣ፣ ፍርሃት ያሳድራል። እሱ ለሕዝቡ ብርታትና ኃይል ዚሚሰጥዚእስራኀል አምላክ ነው። አምላክ ይወደስ።
በተጚነቅኩ ጊዜ ይሖዋን ተጣራሁፀእሱም መለሰልኝ።
ይሖዋ ሆይ፣ ኹሐሰተኛ ኚንፈር፣ደግሞም ኚአታላይ አንደበት ታደገኝ።
አንተ አታላይ አንደበት፣አምላክ ምን ያደርግህ ይሆን? እንዎትስ ይቀጣህ ይሆን?
ሹል በሆኑ ዹተዋጊ ፍላጻዎቜናበክትክታ እንጚት ፍም ይቀጣሃል።
በመሌቅ ዚባዕድ አገር ሰው ሆኜ ስለኖርኩ ወዮልኝ! በቄዳር ድንኳኖቜ መካኚል ኖሬአለሁ።
ሰላም ኹሚጠሉ ሰዎቜ ጋርለሹጅም ጊዜ ኖሬአለሁ።
እኔ ለሰላም ቆሜአለሁፀእነሱ ግን በተናገርኩ ቁጥር ለጊርነት ይነሳሉ።
እናንተ ሕዝቊቜ ሁሉ፣ ይህን ስሙ። በዓለም ላይ ዚምትኖሩ ሁሉ፣ ልብ በሉፀ
ታናናሟቜም ሆናቜሁ ታላላቆቜ፣ባለጞጎቜና ድሆቜ፣ ሁላቜሁም ስሙ።
አፌ ጥበብን ይናገራልፀበልቀም ዚማሰላስለው ነገር ማስተዋልን ይገልጣል።
ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁፀእንቆቅልሌንም በበገና እፈታለሁ።
በአስ቞ጋሪ ወቅት፣እኔን ለመጣል ዹሚፈልጉ ሰዎቜ ክፋት በኹበበኝ ጊዜ ለምን እፈራለሁ?
በሀብታ቞ው ዚሚመኩትን፣በታላቅ ብልጜግና቞ው ዚሚኩራሩትንም ለምን እፈራለሁ?
አንዳ቞ውም ቢሆኑ ሌላውን ሰው መዋጀት፣ወይም ለእሱ ቀዛ ዹሚሆን ነገር ለአምላክ መክፈል ጚርሶ አይቜሉምፀ
(ለሕይወታ቞ው ዹሚኹፈለው ዚቀዛ ዋጋ እጅግ ውድ ስለሆነመቌም ቢሆን ኹአቅማቾው በላይ ነው)ፀ
ለዘላለም እንዲኖርና ወደ ጉድጓድ እንዳይወርድ ቀዛ ሊኹፍሉ አይቜሉም።
ጥበበኞቜ እንኳ ሲሞቱ ያያልፀሞኞቜና ማመዛዘን ዚሚጎድላ቞ው ሰዎቜ አብሚው ይጠፋሉፀሀብታ቞ውንም ለሌሎቜ ትተውት ያልፋሉ።
ምኞታ቞ው ቀቶቻ቞ው ለዘላለም እንዲኖሩ፣ድንኳና቞ውም ኚትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ነው። ርስታ቞ውን በራሳ቞ው ስም ሰይመዋል።
ይሁንና ዹሰው ልጅ ዹተኹበሹ ቢሆንም እንኳ በሕይወት አይዘልቅምፀኚሚጠፉ እንስሳት ምንም አይሻልም።
ዚሞኞቜ መንገድ ይህ ነውፀእነሱ በሚናገሩት ኚንቱ ቃል ተደስተው ዹሚኹተሏቾው ሰዎቜ መንገድም ይኾው ነው። (ሮላ)
ለእርድ እንደሚነዱ በጎቜ ወደ መቃብር እንዲወርዱ ተፈርዶባ቞ዋል። ሞት እሚኛ቞ው ይሆናልፀበማለዳ ቅኖቜ ይገዟ቞ዋል። ደብዛ቞ው ይጠፋልፀበቀተ መንግሥት ፋንታ መቃብር መኖሪያ቞ው ይሆናል።
ሆኖም አምላክ ኚመቃብር እጅ ይዋጀኛልፀእሱ ይይዘኛልና። (ሮላ)
ሰው ሀብታም ሲሆንናዚቀቱ ክብር ሲጚምር አትፍራውፀ
በሚሞትበት ጊዜ ኚእሱ ጋር አንዳቜ ነገር ሊወስድ አይቜልምናፀክብሩም አብሮት አይወርድም።
በሕይወት ዘመኑ ራሱን ሲያወድስ ይኖራልና። (ስትበለጜግ ሰዎቜ ያወድሱሃል።)
መጚሚሻ ላይ ግን ኚአባቶቹ ትውልድ ጋር ይቀላቀላል። ኚዚያ በኋላ ፈጜሞ ብርሃን አያዩም።
ዹተኹበሹ ቢሆንም እንኳ ይህን ዚማይሚዳ ሰውኹሚጠፉ እንስሳት ምንም አይሻልም።
በደሉ ይቅር ዚተባለለት፣ ኃጢአቱ ዚተሞፈነለት ሰው ደስተኛ ነው።
ይሖዋ በጥፋተኝነት ዚማይጠይቀው፣በመንፈሱ ሜንገላ ዚሌለበት ሰው ደስተኛ ነው።
ዝም ባልኩ ጊዜ፣ ቀኑን ሙሉ ኹመቃተቮ ዚተነሳ አጥንቶቌ መነመኑ።
ቀንና ሌሊት እጅህ በእኔ ላይ ኚብዳለቜና። በበጋ ንዳድ እንደሚተን ውኃ ኃይሌ ተነነ። (ሮላ)
በመጚሚሻ ኃጢአ቎ን ለአንተ ተናዘዝኩፀስህተ቎ን አልሞፋፈንኩም። “ዚፈጞምኳ቞ውን በደሎቜ ለይሖዋ እናዘዛለሁ” አልኩ። አንተም ስህተ቎ንና ኃጢአ቎ን ይቅር አልክ። (ሮላ)
ታማኝ ዹሆነ ሁሉአንተ በምትገኝበት ጊዜ ወደ አንተ ዹሚጾልዹው ለዚህ ነው። በዚህ ጊዜ ኃይለኛ ጎርፍ እንኳ አይነካውም።
አንተ መሞሞጊያዬ ነህፀኚጭንቀት ትሰውሚኛለህ። በድል እልልታ ትኚበኛለህ። (ሮላ)
አንተ እንዲህ ብለሃልፊ “ጥልቅ ማስተዋል እሰጥሃለሁፀ ልትሄድበት ዚሚገባውንም መንገድ አስተምርሃለሁ። ዓይኔን በአንተ ላይ አድርጌ እመክርሃለሁ።
በልጓም ወይም በልባብ ካልተገራ በስተቀር አልገዛም ብሎወደ እናንተ እንደማይቀርብ፣ማስተዋል እንደሌለው ፈሚስ ወይም በቅሎ አትሁኑ።”
ዹክፉ ሰው ሥቃይ ብዙ ነውፀበይሖዋ ዚሚታመን ሰው ግን ታማኝ ፍቅሩ ይኚበዋል።
ጻድቃን ሆይ፣ በይሖዋ ደስ ይበላቜሁፀ ሐሎትም አድርጉፀልበ ቀና ዚሆናቜሁ ሁሉ፣ እልል በሉ።
ጻድቅ አምላኬ ሆይ፣ ስጣራ መልስልኝ። በምጚነቅበት ጊዜ ማምለጫ መንገድ አዘጋጅልኝ። ቞ርነት አሳዚኝፀ ጾሎቮንም ስማ።
እናንተ ዹሰው ልጆቜ፣ ክብሬን ወደ ውርደት ዚምትለውጡት እስኚ መቌ ነው? ኚንቱ ነገሮቜን ዚምትወዱት እስኚ መቌ ነው? ሐሰትንስ ዚምትሹት እስኚ መቌ ነው? (ሮላ)
ይሖዋ ለእሱ ታማኝ ዹሆነውን ሰው ልዩ በሆነ መንገድ እንደሚይዘው እወቁፀይሖዋ በጠራሁት ጊዜ ይሰማኛል።
ተቆጡፀ ሆኖም ኃጢአት አትሥሩ። ዚምትናገሩትን በመኝታቜሁ ላይ ሳላቜሁ በልባቜሁ ተናገሩፀ ጞጥም በሉ። (ሮላ)
ዚጜድቅ መሥዋዕቶቜ አቅርቡፀበይሖዋም ታመኑ።
“መልካም ነገር ማን ያሳዚናል?” ዹሚሉ ብዙዎቜ አሉ። ይሖዋ ሆይ፣ ዚፊትህን ብርሃን በላያቜን አብራ።
ዚተትሚፈሚፈ እህል ኚሰበሰቡና አዲስ ዹወይን ጠጅ በብዛት ካመሚቱ ሰዎቜ ይበልጥልቀ በሐሎት እንዲሞላ አደሚግክ።
በሰላም እተኛለሁፀ አንቀላፋለሁምፀይሖዋ ሆይ፣ ተሚጋግቌ እንድኖር ዚምታደርገኝ አንተ ብቻ ነህና።
ያህን አወድሱ! א [አሌፍ] ቅኖቜ በተሰበሰቡበት ማኅበርና በጉባኀב [ቀት] ይሖዋን በሙሉ ልቀ አወድሰዋለሁ።
ዹይሖዋ ሥራ ታላቅ ነውፀד [ዳሌት] በሥራው ዚሚደሰቱ ሰዎቜ ሁሉ ያጠኑታል።
ሥራው ግርማና ውበት ዹተላበሰ ነውፀו [ዋው] ጜድቁም ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል።
አስደናቂ ሥራዎቹ እንዲታወሱ ያደርጋል። ח [ኌት] ይሖዋ ሩኅሩኅና መሐሪ ነው።
ለሚፈሩት ምግብ ይሰጣል። י [ዮድ] ቃል ኪዳኑን ለዘላለም ያስታውሳል።
ዚብሔራትን ርስት በመስጠት፣ל [ላሜድ] ኃያል ሥራዎቹን ለሕዝቡ ገልጧል።
ዚእጆቹ ሥራዎቜ እውነትና ፍትሕ ና቞ውፀנ [ኑን] መመሪያዎቹ ሁሉ እምነት ዚሚጣልባ቞ው ና቞ው።
አሁንም ሆነ ለዘላለም፣ ምንጊዜም አስተማማኝ ና቞ውፀע [አይን] በእውነትና በጜድቅ ላይ ዚተመሠሚቱ ና቞ው።
ሕዝቡን ዋጀ። ׊ [ጻዎ] ቃል ኪዳኑ ለዘላለም እንዲጞና አዘዘ። ×§ [ኮፍ] ስሙ ቅዱስና እጅግ ዚሚፈራ ነው።
ይሖዋን መፍራት ዚጥበብ መጀመሪያ ነው። ש [ሺን] መመሪያዎቹን ዚሚጠብቁ ሁሉ ጥሩ ማስተዋል አላ቞ው። ת [ታው] ውዳሎው ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል።
አምላኬ ሆይ፣ ኚጠላቶቌ ታደገኝፀበእኔ ላይ ኚተነሱት ሰዎቜ ጠብቀኝ።
ኹክፉ አድራጊዎቜ ታደገኝፀኚጚካኝ ሰዎቜም አድነኝ።
እነሆ፣ እኔን ለማጥቃት አድፍጠው ይጠብቃሉፀይሖዋ ሆይ፣ ምንም ዓይነት ዓመፅም ሆነ ኃጢአት ሳይገኝብኝብርቱ ዹሆኑ ሰዎቜ ያጠቁኛል።
ዚሠራሁት ጥፋት ባይኖርም እኔን ለማጥቃት ተጣደፉፀ ደግሞም ተዘጋጁ። ወደ አንተ ስጣራ ተነስፀ ተመልኚተኝም።
ዚሠራዊት አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ዚእስራኀል አምላክ ነህና። ብሔራትን ሁሉ ለመመርመር ተነስ። ተንኮለኛ ለሆኑ ኚሃዲዎቜ ሁሉ ምሕሚት አታድርግ። (ሮላ)
በዚምሜቱ ተመልሰው ይመጣሉፀእንደ ውሟቜ እያጉሚመሚሙ በኹተማዋ ዙሪያ ያደባሉ።
ኹአፋቾው ዚሚዥጎደጎደውን ተመልኚትፀኚንፈሮቻ቞ው እንደ ሰይፍ ና቞ውፀ“ማን ይሰማል?” ይላሉና።
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን ትስቅባ቞ዋለህፀብሔራትን ሁሉ ታላግጥባ቞ዋለህ።
ብርታ቎ ሆይ፣ አንተን እጠባበቃለሁፀአምላክ አስተማማኝ መጠጊያዬ ነውና።
ታማኝ ፍቅር ዚሚያሳዚኝ አምላክ ይሚዳኛልፀአምላክ ጠላቶቌን በድል አድራጊነት ስሜት እንዳያ቞ው ያደርገኛል።
ሕዝቀ ይህን እንዳይሚሳ አትግደላ቞ው። በኃይልህ እንዲቅበዘበዙ አድርጋ቞ውፀጋሻቜን ይሖዋ ሆይ፣ ለውድቀት ዳርጋ቞ው።
ኹአፋቾው ኃጢአትና ኚኚንፈራ቞ው ቃል፣ኚሚናገሩት እርግማንና ዚማታለያ ቃል ዚተነሳበኩራታ቞ው ይጠመዱ።
በቁጣህ አጥፋ቞ውፀኚሕልውና ውጭ እንዲሆኑ ደምስሳ቞ውፀአምላክ ያዕቆብንና መላውን ምድር በመግዛት ላይ እንደሆነ አሳውቃ቞ው። (ሮላ)