text
stringlengths
4
267
እንዳያንሰራሩ አድርጌ አደቃ቞ዋለሁፀእግሬ ሥር ይወድቃሉ።
ለውጊያው ብርታት ታስታጥቀኛለህፀጠላቶቌ ሥሬ እንዲወድቁ ታደርጋለህ።
ጠላቶቌ ኚእኔ እንዲሞሹ ታደርጋለህፀእኔም ዹሚጠሉኝን አጠፋ቞ዋለሁ።
እርዳታ ለማግኘት ይጮኻሉፀ ሆኖም ዚሚያድና቞ው ዚለምፀወደ ይሖዋም ይጮኻሉፀ እሱ ግን አይመልስላ቞ውም።
በነፋስ ፊት እንዳለ አቧራ ፈጜሜ አደቃ቞ዋለሁፀበመንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ አውጥቌ እጥላ቞ዋለሁ።
ስህተት ኹሚለቃቅሙ ሰዎቜ ታድነኛለህ። ዚብሔራት መሪ አድርገህ ትሟመኛለህ። ዹማላውቀው ሕዝብ ያገለግለኛል።
ስለ እኔ በሰሙት ነገር ብቻ ይታዘዙኛልፀዚባዕድ አገር ሰዎቜም አንገታ቞ውን ደፍተው ወደ ፊቮ ይቀርባሉ።
ዚባዕድ አገር ሰዎቜ ወኔ ይኚዳ቞ዋልፀኚምሜጎቻ቞ው እዚተንቀጠቀጡ ይወጣሉ።
ይሖዋ ሕያው ነው! ዓለቮ ይወደስ! ዚመዳኔ አምላክ ኹፍ ኹፍ ይበል።
እውነተኛው አምላክ ይበቀልልኛልፀሕዝቊቜንም ኚበታቌ ያስገዛልኛል።
በቁጣ ኹተሞሉ ጠላቶቌ ይታደገኛልፀኚሚያጠቁኝ ሰዎቜ በላይ ኹፍ ኹፍ ታደርገኛለህፀኚዓመፀኛ ሰው ታድነኛለህ።
ይሖዋ ሆይ፣ በብሔራት መካኚል ዚማኚብርህ ለዚህ ነውፀለስምህም ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁ።
እሱ ለንጉሡ ታላላቅ ዚማዳን ሥራዎቜ ያኚናውናልፀለቀባውም ታማኝ ፍቅር ያሳያልፀለዳዊትና ለዘሩ ለዘላለም ይህን ያደርጋል።
ስለ ታማኝ ፍቅርና ስለ ፍትሕ እዘምራለሁ። ይሖዋ ሆይ፣ ለአንተ ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁ።
በማስተዋልና ነቀፋ በሌለበት መንገድ እመላለሳለሁ። ወደ እኔ ዚምትመጣው መቌ ነው? በቀ቎ ውስጥ በንጹሕ ልብ እመላለሳለሁ።
በዓይኖቌ ፊት ዚማይሚባ ነገር አላኖርም። ኚትክክለኛው መንገድ ዚሚወጡ ሰዎቜ ዚሚያደርጓ቞ውን ነገሮቜ እጠላለሁፀኚእነሱ ጋር ዚሚያገናኘኝ ምንም ጉዳይ ዚለም።
ጠማማ ልብ ኚእኔ ዚራቀ ነውፀምንም ዓይነት ክፉ ነገር አልቀበልም።
ዚባልንጀራውን ስም በስውር ዚሚያጠፋን ሰው፣ጞጥ አሰኘዋለሁ። ትዕቢተኛ ዓይንና እብሪተኛ ልብ ያለውን ሰው፣አልታገሠውም።
ኚእኔ ጋር እንዲኖሩበምድሪቱ ወዳሉ ታማኞቜ እመለኚታለሁ። ነቀፋ በሌለበት መንገድ ዚሚመላለስ ሰው እኔን ያገለግለኛል።
አታላይ ዹሆነ ሰው በቀ቎ አይኖርምፀውሞት ዹሚናገር ሰው በፊቮ አይቆምም።
በምድሪቱ ላይ ዚሚገኙትን ክፉ ሰዎቜ ሁሉ በዚማለዳው ጞጥ አሰኛለሁፀክፉ አድራጊዎቜን ሁሉ ኹይሖዋ ኹተማ አስወግዳለሁ።
አምላክ ሞገስ ያሳዚናልፀ ደግሞም ይባርኚናልፀፊቱን በእኛ ላይ ያበራልፀ (ሮላ)
ይህም መንገድህ በምድር ሁሉ ላይ፣ዚማዳን ሥራህም በብሔራት ሁሉ መካኚል እንዲታወቅ ነው።
አምላክ ሆይ፣ ሕዝቊቜ ያወድሱህፀአዎ፣ ሕዝቊቜ ሁሉ ያወድሱህ።
ብሔራት ሐሎት ያድርጉፀ እልልም ይበሉፀበሕዝቊቜ ላይ በትክክል ትፈርዳለህና። ዚምድርን ብሔራት ትመራ቞ዋለህ። (ሮላ)
አምላክ ሆይ፣ ሕዝቊቜ ያወድሱህፀሕዝቊቜ ሁሉ ያወድሱህ።
ምድር ፍሬዋን ትሰጣለቜፀአምላክ፣ አዎ፣ አምላካቜን ይባርኚናል።
አምላክ ይባርኚናልፀዚምድር ዳርቻዎቜም ሁሉ ይፈሩታል።
ያህን አወድሱ! א [አሌፍ] ይሖዋን ዚሚፈራናב [ቀት] ትእዛዛቱን እጅግ ዚሚወድ ሰው ደስተኛ ነው።
ዘሮቹ በምድር ላይ ኃያላን ይሆናሉ።ד [ዳሌት] ደግሞም ዚቅኖቜ ትውልድ ይባሚካል።
በቀቱ ሀብትና ንብሚት አለፀו [ዋው] ጜድቁም ለዘላለም ይኖራል።
ለቅኖቜ በጹለማ ውስጥ እንደ ብርሃን ያበራል። ח [ኌት] ሩኅሩኅና መሐሪ እንዲሁም ጻድቅ ነው።
በልግስና ዚሚያበድር ሰው ይሳካለታል። י [ዮድ] ጉዳዩን በፍትሕ ያኚናውናል።
እሱ ፈጜሞ አይናወጥም። ל [ላሜድ] ጻድቅ ለዘላለም ሲታወስ ይኖራል።
ክፉ ወሬ አያስፈራውም። ×  [ኑን] በይሖዋ ስለሚተማመን ልቡ ጜኑ ነው።
ልቡ አይናወጥምፀ አይፈራምምፀע [አይን] በመጚሚሻም ጠላቶቹን በድል አድራጊነት ይመለኚታል።
በብዛት አኚፋፈለፀ ለድሆቜም ሰጠ። ׊ [ጻዎ] ጜድቁ ለዘላለም ይኖራል። ×§ [ኮፍ] ዹገዛ ብርታቱ በክብር ኹፍ ኹፍ ይላል።
ክፉ ሰው አይቶ ይበሳጫል። ש [ሺን] ጥርሱን ያፋጫልፀ ቀልጩም ይጠፋል። ת [ታው] ዚክፉዎቜ ምኞት ይኚስማል።
ሞገስ አሳዚኝፀ አምላክ ሆይ፣ ሞገስ አሳዚኝፀአንተን መጠጊያ አድርጌአለሁናፀመኚራው እስኪያልፍ ድሚስ በክንፎቜህ ጥላ ሥር እጠለላለሁ።
ወደ ልዑሉ አምላክ፣ለእኔ ሲል መኚራውን ወደሚያስቆመው ወደ እውነተኛው አምላክ እጣራለሁ።
ኹሰማይ እርዳታ ልኮ ያድነኛል። ሊነክሰኝ ዹሚሞክሹውን ሰው እንዳይሳካለት ያደርጋል። (ሮላ) አምላክ ታማኝ ፍቅሩንና ታማኝነቱን ያሳያል።
አንበሶቜ ኚበውኛልፀሊውጡኝ በሚፈልጉ ሰዎቜ መካኚል ለመተኛት ተገድጃለሁፀጥርሳ቞ው ጩርና ፍላጻ ነውፀምላሳ቞ውም ዚተሳለ ሰይፍ ነው።
አምላክ ሆይ፣ ኚሰማያት በላይ ኹፍ ኹፍ በልፀክብርህ በምድር ሁሉ ላይ ይሁን።
እግሮቌን ለመያዝ ወጥመድ አዘጋጅተዋልፀኚጭንቅ ዚተነሳ ጎብጫለሁ። በፊቮ ጉድጓድ ቆፈሩፀነገር ግን ራሳ቞ው ገቡበት። (ሮላ)
ልቀ ጜኑ ነውፀአምላክ ሆይ፣ ልቀ ጜኑ ነው። እዘምራለሁፀ ደግሞም አዜማለሁ።
ልቀ ሆይ፣ ተነሳ። ባለ አውታር መሣሪያ ሆይ፣ አንተም በገና ሆይ፣ ተነሱ። እኔም በማለዳ እነሳለሁ።
ይሖዋ ሆይ፣ በሕዝቊቜ መካኚል አወድስሃለሁፀበብሔራት መካኚል ዚውዳሎ መዝሙር እዘምርልሃለሁ።
ታማኝ ፍቅርህ ታላቅ ነውናፀ እንደ ሰማያት ኹፍ ያለ ነውፀታማኝነትህም እስኚ ደመናት ድሚስ ነው።
አምላክ ሆይ፣ ኚሰማያት በላይ ኹፍ ኹፍ በልፀክብርህ በምድር ሁሉ ላይ ይሁን።
ምድር ሁሉ፣ በድል አድራጊነት ለአምላክ እልል ትበል።
ለክብራማ ስሙ ዚውዳሎ መዝሙር ዘምሩ። ውዳሎውን አድምቁ።
አምላክን እንዲህ በሉትፊ “ሥራዎቜህ አክብሮታዊ ፍርሃት ዚሚያሳድሩ ና቞ው። ኹኃይልህ ታላቅነት ዚተነሳጠላቶቜህ በፊትህ ይሜቆጠቆጣሉ።
በምድር ያሉ ሁሉ ይሰግዱልሃልፀለአንተ ዚውዳሎ መዝሙር ይዘምራሉፀለስምህም ዚውዳሎ መዝሙር ይዘምራሉ።” (ሮላ)
ኑና ዹአምላክን ሥራዎቜ ተመልኚቱ። ለሰው ልጆቜ ያኚናወና቞ው ተግባሮቜ አክብሮታዊ ፍርሃት ዚሚያሳድሩ ና቞ው።
እሱ ባሕሩን ደሹቅ ምድር አደሚገውፀወንዙን በእግራ቞ው ተሻገሩ። በዚያ በእሱ እጅግ ደስ አለን።
በኃይሉ ለዘላለም ይገዛል። ዓይኖቹ ብሔራትን አተኩሚው ያያሉ። ግትር ዹሆኑ ሰዎቜ ራሳ቞ውን ኹፍ ኹፍ አያድርጉ። (ሮላ)
እናንተ ሕዝቊቜ ሆይ፣ አምላካቜንን አወድሱፀለእሱ ዹሚቀርበውም ዚውዳሎ ድምፅ ይሰማ።
እሱ በሕይወት ያኖሚናልፀእግራቜን እንዲደናቀፍ አይፈቅድም።
አምላክ ሆይ፣ አንተ መርምሚኞናልናፀብር በእሳት እንደሚጠራ ሁሉ አንተም እኛን አጥርተኞናል።
ማጥመጃ መሚብ ውስጥ አስገባኞንፀበላያቜንም ኚባድ ሾክም ጫንክብን።
ሟቜ ሰው ላያቜን ላይ እንዲጋልብ አደሚግክፀበእሳት መካኚልና በውኃ መካኚል አለፍንፀኚዚያም እሚፍት ወደምናገኝበት ስፍራ አመጣኞን።
ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ á‹­á‹€ ወደ ቀትህ እመጣለሁፀስእለ቎ንም ለአንተ እፈጜማለሁፀ
ይህም በጭንቅ ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ ኚንፈሮቌ ቃል ዚገቡት፣አፌም ዹተናገሹው ነው።
ዚሰቡ እንስሳትን ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ አድርጌኚሚጚስ ዚአውራ በጎቜ መሥዋዕት ጋር አቀርብልሃለሁ። ኚአውራ ፍዚሎቜም ጋር ኮርማዎቜን አቀርባለሁ። (ሮላ)
እናንተ አምላክን ዚምትፈሩ ሁሉ፣ ኑና አዳምጡፀለእኔ ያደሚገልኝንም ነገር እነግራቜኋለሁ።
በአፌ ወደ እሱ ተጣራሁፀበአንደበ቎ም ኹፍ ኹፍ አደሚግኩት።
በልቀ አንዳቜ መጥፎ ነገር á‹­á‹€ ቢሆን ኖሮ፣ይሖዋ ባልሰማኝ ነበር።
ሆኖም አምላክ ሰምቷልፀጞሎ቎ን በትኩሚት አዳምጧል።
ጾሎቮን ኚመስማት ጆሮውን ያልመለሰ፣ደግሞም ታማኝ ፍቅሩን ያልነፈገኝ አምላክ ውዳሎ ይድሚሰው።
ብሔራት ሁሉ፣ ይሖዋን አወድሱትፀሕዝቊቜ ሁሉ፣ ኹፍ ኹፍ አድርጉት።
ለእኛ ያሳዚው ታማኝ ፍቅር ታላቅ ነውናፀዚይሖዋ ታማኝነት ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል። ያህን አወድሱ!
ይሖዋ እሚኛዬ ነው። ዚሚጎድልብኝ ነገር ዚለም።
በለመለመ መስክ ያሳርፈኛልፀውኃ ወዳለበት ዚእሚፍት ቊታም ይመራኛል።
ኃይሌን ያድሳል። ለስሙ ሲል በጜድቅ መንገድ ይመራኛል።
ድቅድቅ ጹለማ በዋጠው ሾለቆ ውስጥ ብሄድ እንኳአንተ ኚእኔ ጋር ስለሆንክ፣ጉዳት ይደርስብኛል ብዬ አልፈራምፀበትርህና ምርኩዝህ ያበሚታቱኛል።
በጠላቶቌ ፊት ማዕድ አዘጋጀህልኝ። ራሎን በዘይት ቀባህፀጜዋዬ ጢም ብሎ ሞልቷል።
ጥሩነትህና ታማኝ ፍቅርህ በሕይወቮ ዘመን ሁሉ ይኚተሉኛልፀዕድሜዬንም በሙሉ በይሖዋ ቀት እኖራለሁ።
“ይሖዋ ኚእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ፣” እስራኀል እንዲህ ይበል፩
“ይሖዋ ኚእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ፣ሰዎቜ እኛን ለማጥቃት በተነሱ ጊዜ፣
ቁጣ቞ው በእኛ ላይ በነደደ ጊዜ፣በሕይወት ሳለን በዋጡን ነበር።
በዚያን ጊዜ ውኃ ጠራርጎ በወሰደን፣ጎርፍም ባጥለቀለቀን ነበር።
ኃይለኛ ውኃ በዋጠን ነበር።
ለጥርሳ቞ው ሲሳይ እንድንሆን አሳልፎ ስላልሰጠንይሖዋ ይወደስ።
ኚአዳኝ ወጥመድእንዳመለጠቜ ወፍ ነንፀወጥመዱ ተሰበሚፀእኛም አመለጥን።
ሰማይንና ምድርን ዚሠራውዚይሖዋ ስም ሚዳታቜን ነው።”
ይሖዋ ሆይ፣ ባላጋራዎቌን በመቃወም ተሟገትልኝፀዚሚዋጉኝን ተዋጋ቞ው።
ትንሹንና ትልቁን ጋሻህን ያዝፀለእኔ ለመኹላኹልም ተነስ።
በሚያሳድዱኝ ላይ ጩርና መጥሚቢያ አንሳ። “ዚማድንህ እኔ ነኝ” በለኝ።
ሕይወቮን ዚሚሹ ይፈሩፀ ይዋሚዱም። እኔን ለማጥፋት ዚሚያሎሩ ተዋርደው ያፈግፍጉ።
በነፋስ ፊት እንዳለ ገለባ ይሁኑፀዚይሖዋ መልአክም ያባርራ቞ው።
ዹይሖዋ መልአክ ሲያሳድዳ቞ውመንገዳ቞ው በጹለማ ዹተዋጠና ዚሚያዳልጥ ይሁን።
ያላንዳቜ ምክንያት እኔን ለማጥመድ በስውር መሚብ ዘርግተዋልናፀያላንዳቜ ምክንያት ጉድጓድ ቆፍሚውልኛል።
ሳያስቡት ጥፋት ይምጣባ቞ውፀበስውር ያስቀመጡት መሚብም እነሱኑ ይያዛ቞ውፀእዚያም ውስጥ ወድቀው ይጥፉ።
እኔ ግን በይሖዋ ሐሎት አደርጋለሁፀበማዳን ሥራውም እጅግ ደስ ይለኛል።
አጥንቶቌ ሁሉ እንዲህ ይላሉ፩ “ይሖዋ ሆይ፣ እንደ አንተ ያለ ማን ነው? ምስኪኑን ብርቱ ኚሆኑት፣ምስኪኑንና ድሃውን ኹሚዘርፏቾው ሰዎቜ ትታደጋለህ።”
ክፉ ምሥክሮቜ ቀሚቡፀምንም ስለማላውቀው ነገር ጠዚቁኝ።
ለመልካም ነገር ክፉ መለሱልኝፀደግሞም ሐዘን ላይ ጣሉኝ።
እኔ ግን እነሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስኩፀራሎን በጟም አጎሳቆልኩፀጞሎ቎ም መልስ ሳያገኝ በተመለሰ ጊዜ፣
ለጓደኛዬ ወይም ለወንድሜ እንደማደርገው እዚተንቆራጠጥኩ አለቀስኩፀእናቱ ሞታበት እንደሚያለቅስ ሰው አንገቮን በሐዘን ደፋሁ።
እኔ ስደናቀፍ ግን እነሱ ደስ ብሏ቞ው ተሰበሰቡፀአድብተው እኔን ለመምታት ተሰበሰቡፀዘነጣጠሉኝፀ በነገር መጎንተላቾውንም አልተዉም።