text
stringlengths
4
267
ካህኑ ለይሖዋ በእሳት ዚሚቀርብ መባ አድርጎ በመሠዊያው ላይ ያጚሳ቞ዋል። ይህ ዹበደል መባ ነው።
ካህን ዹሆነ ወንድ ሁሉ ይበላዋልፀ ቅዱስ በሆነ ስፍራም መበላት ይኖርበታል። ይህ እጅግ ዹተቀደሰ ነገር ነው።
ስለ ኃጢአት መባው ዚወጣው ሕግ ለበደል መባውም ይሠራልፀ መባውም በመባው ለሚያስተሰርዚው ካህን ይሆናል።
“‘ካህኑ ለአንድ ሰው ዹሚቃጠል መባ በሚያቀርብበት ጊዜ ዹሚቃጠል መባ ሆኖ ለካህኑ ዹቀሹበው እንስሳ ቆዳ ዚእሱ ይሆናል።
“‘በመጋገሪያ ምድጃ ዹተጋገሹ ወይም በድስት ዹተዘጋጀ አሊያም በምጣድ ዹተጋገሹ ዚእህል መባ ሁሉ መባውን ለሚያቀርበው ካህን ይሆናል። መባው ዚእሱ ይሆናል።
በዘይት ዹተለወሰው ወይም ደሹቅ ዹሆነው ዚእህል መባ ግን ለአሮን ወንዶቜ ልጆቜ በሙሉ ይኚፋፈላልፀ እያንዳንዳ቞ውም እኩል ድርሻ ይኖራ቞ዋል።
“‘አንድ ሰው ለይሖዋ ዚሚያቀርበውን ዚኅብሚት መሥዋዕት በተመለኹተ ደግሞ ሕጉ ይህ ነው፩
ሰውዹው መሥዋዕቱን ዚሚያቀርበው አመስጋኝነቱን ለመግለጜ ኹሆነ ኚምስጋና መሥዋዕቱ ጋር በዘይት ተለውሶ ዹተጋገሹ እርሟ ያልገባበት ዚቀለበት ቅርጜ ያለው ዳቊ፣ ዘይት ዚተቀባ ስስ ቂጣና በዘይት በደንብ ኚራሰና ኹተለወሰ ዹላመ ዱቄት ዹተጋገሹ ዚቀለበት ቅርጜ ያለው ዳቊ አብሮ ያቀርባል።
መባውንም እርሟ ገብቶባ቞ው ኚተጋገሩ ዚቀለበት ቅርጜ ያላ቞ው ዳቊዎቜና ዚምስጋና መሥዋዕት አድርጎ ኚሚያቀርባ቞ው ዚኅብሚት መሥዋዕቶቜ ጋር አብሮ ያቀርባል።
ኚዚያም ላይ ኚእያንዳንዱ መባ አንድ አንድ በማንሳት ለይሖዋ ዹተቀደሰ ድርሻ አድርጎ ያቀርባልፀ ይህም ዚኅብሚት መሥዋዕቶቹን ደም ለሚሹጹው ካህን ይሆናል።
ዚምስጋና መሥዋዕት እንዲሆኑ ያቀሚባ቞ው ዚኅብሚት መሥዋዕቶቜ ሥጋ፣ መሥዋዕቱን ባቀሚበበት ቀን መበላት ይኖርበታል። ኚዚያ ላይ ምንም ማስቀሚትና ማሳደር ዚለበትም።
“‘መባ አድርጎ ዚሚያቀርበው መሥዋዕት ስእለት ወይም ዚፈቃደኝነት መባ ኹሆነ መሥዋዕቱን ባቀሚበበት ቀን መበላት አለበትፀ ዹተሹፈውም በማግስቱ ሊበላ ይቜላል።
ለመሥዋዕት ኹቀሹበው ሥጋ ተርፎ እስኚ ሊስተኛው ቀን ዹቆዹው ግን በእሳት መቃጠል አለበት።
ይሁን እንጂ ዚኅብሚት መሥዋዕት እንዲሆን ያቀሚበው ማንኛውም ሥጋ በሊስተኛው ቀን ቢበላ መሥዋዕቱን ያቀሚበው ሰው ተቀባይነት አያገኝም። ያደሚገውም ነገር አይታሰብለትምፀ ይህ አስጞያፊ ነገር ነውፀ ኚዚያም ላይ ዹበላው ሰው ለፈጾመው ስህተት ይጠዚቅበታል።
ርኩስ ዹሆነን ማንኛውንም ነገር ዚነካ ሥጋ መበላት ዚለበትም። በእሳት መቃጠል አለበት። ንጹሕ ዹሆነ ማንኛውም ሰው ንጹሕ ዹሆነውን ሥጋ ሊበላ ይቜላል።
“‘ሆኖም ማንኛውም ሰው ርኩስ ሆኖ ሳለ ለይሖዋ ኹቀሹበው ዚኅብሚት መሥዋዕት ሥጋ ቢበላ ያ ሰው ኚሕዝቡ መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ ይደሚግ።
አንድ ሰው ርኩስ ዹሆነ ነገር ይኾውም ዹሰውን ርኩሰት ወይም ርኩስ ዹሆነን እንስሳ ወይም ርኩስ ዹሆነን ማንኛውንም አስጞያፊ ነገር ቢነካና ለይሖዋ ኹቀሹበው ዚኅብሚት መሥዋዕት ሥጋ ቢበላ ያ ሰው ኚሕዝቡ መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ ይደሚግ።’”
ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“እስራኀላውያንን እንዲህ በላቾው፩ ‘ማንኛውንም ዓይነት ዚበሬ፣ ዹበግ ጠቊት ወይም ዹፍዹል ስብ አትብሉ።
ሞቶ ዹተገኘ እንስሳ ስብና አውሬ ዹገደለው እንስሳ ስብ ለሌላ ለማንኛውም አገልግሎት ሊውል ይቜላልፀ እናንተ ግን ፈጜሞ እንዳትበሉት።
ማንኛውም ሰው ለይሖዋ በእሳት ዹሚቃጠል መባ አድርጎ ኚሚያቀርበው እንስሳ ላይ ስብ ቢበላ ኚሕዝቡ መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ ይደሚግ።
“‘በምትኖሩበት በዚትኛውም ቊታ ዹወፍም ይሁን ዚእንስሳ፣ ማንኛውንም ደም አትብሉ።
ደም ዹሚበላ ማንኛውም ሰው ኚሕዝቡ መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ ይደሚግ።’”
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“እስራኀላውያንን እንዲህ በላቾው፩ ‘ዚኅብሚት መሥዋዕቱን ለይሖዋ ዚሚያቀርብ ማንኛውም ሰው ኚኅብሚት መሥዋዕቱ መባ ላይ ዹተወሰነውን ለይሖዋ ያቀርባል።
እሱም ስቡን ኚፍርምባው ጋር ለይሖዋ በእሳት ዚሚቀርብ መባ እንዲሆን በራሱ እጆቜ ያመጣልፀ ዹሚወዘወዝ መባ አድርጎም በይሖዋ ፊት ወዲያና ወዲህ ይወዘውዘዋል።
ካህኑ ስቡን በመሠዊያው ላይ ያጚሰዋልፀ ፍርምባው ግን ዚአሮንና ዚወንዶቜ ልጆቹ ይሆናል።
“‘ኚኅብሚት መሥዋዕቶቻቜሁም ላይ ቀኝ እግሩን ለካህኑ ዹተቀደሰ ድርሻ አድርጋቜሁ ትሰጣላቜሁ።
ዚኅብሚት መሥዋዕቱን ደምና ስቡን ዚሚያቀርበው ዚአሮን ልጅ ዚእንስሳውን ቀኝ እግር እንደ ድርሻው አድርጎ ይወስዳል።
እስራኀላውያን ኚሚያቀርቧ቞ው ዚኅብሚት መሥዋዕቶቜ ላይ ዹሚወዘወዘውን መባ ፍርምባና ዹተቀደሰ ድርሻ ሆኖ ዹቀሹበውን እግር እወስዳለሁፀ ለእስራኀላውያንም ዘላቂ ሥርዓት እንዲሆን ለካህኑ ለአሮንና ለወንዶቜ ልጆቹ እሰጣ቞ዋለሁ።
“‘ካህናት ሆነው ይሖዋን ለማገልገል በሚቀርቡበት ቀን፣ ለይሖዋ በእሳት ኚቀሚቡት መባዎቜ ላይ ለካህናቱ ይኾውም ለአሮንና ለወንዶቜ ልጆቹ ዚሚመደብላ቞ው ድርሻ ይህ ነው።
ይሖዋ በቀባ቞ው ቀን ይህ ድርሻ ኚእስራኀላውያን ተወስዶ እንዲሰጣ቞ው አዟል። ይህ ለትውልዶቻ቞ው ዘላለማዊ ደንብ ነው።’”
ዹሚቃጠል መባን፣ ዚእህል መባን፣ ዚኃጢአት መባን፣ ዹበደል መባን፣ ለክህነት ሹመት ሥርዓት ዚሚቀርብ መሥዋዕትንና ዚኅብሚት መሥዋዕትን በተመለኹተ ዹተሰጠው ሕግ ይህ ነውፀ
ይህም እስራኀላውያን በሲና ምድሚ በዳ መባዎቻ቞ውን ለይሖዋ እንዲያቀርቡ ባዘዛ቞ው ቀን ይሖዋ ሙሮን በሲና ተራራ ላይ ባዘዘው መሠሚት ዹሚፈጾም ነው።
በተጚማሪም ይሖዋ ሙሮን በሲና ተራራ ላይ እንዲህ አለው፩
“ለእስራኀላውያን እንዲህ ብለህ ንገራ቞ውፊ ‘እኔ ወደምሰጣቜሁ ምድር በምትገቡበት ጊዜ ምድሪቱ ለይሖዋ ሰንበትን ማክበር ይኖርባታል።
ስድስት ዓመት በእርሻህ ላይ ዘር ዝራፀ ስድስት ዓመት ወይንህን ግሚዝፀ እንዲሁም ዚምድሪቱን ምርት ሰብስብ።
ሰባተኛው ዓመት ግን ምድሪቱ ሙሉ በሙሉ ዚምታርፍበት ሰንበት ይኾውም ዹይሖዋ ሰንበት ይሁን። በእርሻህ ላይ ዘር አትዝራ ወይም ወይንህን አትግሚዝ።
በማሳህ ላይ ዹበቀለውን ገቩ አትጚድፀ ያልተገሚዘውን ወይንህን ፍሬ አትልቀም። ምድሪቱ ለአንድ ዓመት ሙሉ በሙሉ ማሹፍ ይኖርባታል።
ሆኖም ምድሪቱ በሰንበት እሚፍቷ ጊዜ ዚምታበቅለውን እህል መብላት ትቜላለህፀ አንተ፣ ወንድ ባሪያህ፣ ሎት ባሪያህ፣ ቅጥር ሠራተኛህና አብሚውህ ዚሚኖሩ ባዕዳን ሰፋሪዎቜ ልትበሉት ትቜላላቜሁፀ
እንዲሁም በምድርህ ለሚኖሩ ዚቀትና ዚዱር እንስሳት ምግብ ይሁን። ምድሪቱ ዚምትሰጠው ምርት ሁሉ ለምግብነት ሊውል ይቜላል።
“‘ሰባት ዚሰንበት ዓመታትን ማለትም ሰባት ጊዜ ሰባት ዓመታትን ትቆጥራለህፀ ሰባቱ ዚሰንበት ዓመታትም 49 ዓመታት ይሆናሉ።
ኚዚያም በሰባተኛው ወር ኚወሩም በአሥሚኛው ቀን ቀንደ መለኚቱን ድምፁን ኹፍ አድርገህ ትነፋዋለህፀ በስርዚት ቀን ዹቀንደ መለኚቱ ድምፅ በምድራቜሁ ሁሉ እንዲሰማ ማድሚግ አለባቜሁ።
ሃምሳኛውን ዓመት ቀድሱፀ በምድሪቱም ለሚኖሩ ሁሉ ነፃነት አውጁ። ለእናንተ ኢዮቀልዩ ይሆንላቜኋልፀ ኚእናንተ እያንዳንዱ ወደዚርስቱ ይመለሳልፀ ኚእናንተም እያንዳንዱ ወደዚቀተሰቡ ይመለስ።
ሃምሳኛው ዓመት ለእናንተ ኢዮቀልዩ ይሆንላቜኋል። ዘር አትዘሩም ወይም ማሳ ላይ ዹበቀለውን ገቩ አታጭዱም አሊያም ያልተገሚዘውን ዹወይን ፍሬ አትሰበስቡም።
ምክንያቱም ይህ ኢዮቀልዩ ነው። ለእናንተም ቅዱስ መሆን ይኖርበታል። ምድሪቱ በራሷ ዚምታበቅለውን ብቻ መብላት ትቜላላቜሁ።
“‘በዚህ ዚኢዮቀልዩ ዓመት ኚእናንተ እያንዳንዱ ወደዚርስቱ ይመለስ።
ለባልንጀራቜሁ አንድ ነገር ብትሞጡ ወይም ኚባልንጀራቜሁ እጅ አንድ ነገር ብትገዙ አንዳቜሁ ሌላውን መጠቀሚያ አታድርጉ።
ኚባልንጀራህ ላይ መሬት ስትገዛ ኚኢዮቀልዩ በኋላ ያሉትን ዓመታት ግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርብሃልፀ እሱም ሲሞጥልህ እህል ዚሚሰበሰብባ቞ውን ዚቀሩትን ዓመታት ማስላት ይኖርበታል።
ብዙ ዓመታት ዚሚቀሩ ኹሆነ ዋጋውን መጹመር ይቜላልፀ ዚሚቀሩት ዓመታት ጥቂት ኹሆኑ ደግሞ ዋጋውን መቀነስ ይኖርበታልፀ ምክንያቱም ዚሚሞጥልህ አዝመራ ዚሚሰበሰብበትን ጊዜ አስልቶ ነው።
ኚእናንተ መካኚል ማንም ባልንጀራውን መጠቀሚያ ማድሚግ ዚለበትምፀ አምላክህን ፍራፀ ምክንያቱም እኔ አምላካቜሁ ይሖዋ ነኝ።
ደንቊቌን ብትፈጜሙና ድንጋጌዎቌን ብትጠብቁ በምድሪቱ ላይ ያለስጋት ትኖራላቜሁ።
ምድሪቱ ፍሬዋን ትሰጣለቜፀ እናንተም እስክትጠግቡ ድሚስ ትበላላቜሁፀ በዚያም ያለስጋት ትኖራላቜሁ።
“‘ሆኖም ‘ዘር ካልዘራን ወይም እህል ካልሰበሰብን በሰባተኛው ዓመት ምን እንበላለን?’ ብትሉ
እኔ በስድስተኛው ዓመት በሹኹቮን እልክላቜኋለሁፀ ምድሪቱም ለሊስት ዓመት ዹሚበቃ እህል ታፈራለቜ።
ኚዚያም በስምንተኛው ዓመት ዘር ትዘራላቜሁፀ እስኚ ዘጠነኛውም ዓመት ድሚስ ቀድሞ ኚሰበሰባቜሁት ትበላላቜሁ። እህሉ እስኪደርስ ድሚስ ቀድሞ ዚሰበሰባቜሁትን ትበላላቜሁ።
“‘ምድሪቱ ዚእኔ ስለሆነቜ መሬት ለዘለቄታው መሞጥ አይኖርበትም። ምክንያቱም እናንተ በእኔ አመለካኚት ዚባዕድ አገር ሰዎቜና ሰፋሪዎቜ ናቜሁ።
በርስትነት በያዛቜሁት ምድር ሁሉ መሬትን መልሶ መግዛት ዚሚያስቜል መብት እንዲኖር አድርጉ።
“‘ወንድምህ ቢደኞይና ኚርስቱ ዹተወሰነውን ለመሞጥ ቢገደድ ዹሚዋጅ ዚቅርብ ዘመዱ መጥቶ ወንድሙ ዹሾጠውን መልሶ ይግዛ።
አንድ ሰው ዚሚዋጅለት ቢያጣ ሆኖም እሱ ራሱ ሀብት ቢያገኝና መሬቱን ለመዋጀት ዚሚያስቜል አቅም ቢኖሚው
መሬቱን ኚሞጠበት ጊዜ አንስቶ ያሉትን ዓመታት በመቁጠር ዋጋውን ያስላፀ ዹዋጋውንም ልዩነት ለሞጠለት ሰው ይመልስ። ኚዚያም ወደ ርስቱ መመለስ ይቜላል።
“‘ሆኖም መሬቱን ኹሰውዹው ላይ ለማስመለስ ዚሚያስቜል አቅም ባይኖሚው ዹሾጠው መሬት እስኚ ኢዮቀልዩ ዓመት ድሚስ በገዢው እጅ ይቆያልፀ መሬቱም በኢዮቀልዩ ይመለስለታልፀ እሱም ወደ ርስቱ ይመለሳል።
“‘አንድ ሰው በቅጥር በታጠሚ ኹተማ ውስጥ ዹሚገኝን መኖሪያ ቀት ቢሞጥ ኚሞጠበት ጊዜ አንስቶ እስኚ አንድ ዓመት ድሚስ ዚመዋጀት መብቱ እንደተጠበቀ ይቆያልፀ ዚመዋጀት መብቱ ለአንድ ዓመት ሙሉ እንደተጠበቀ ይቆያል።
ይሁንና ዓመቱ ኹመጠናቀቁ በፊት መልሶ ሊገዛው ካልቻለ በቅጥር በታጠሚው ኹተማ ውስጥ ዹሚገኘው ቀት ለዘለቄታው ዚገዢው ንብሚት ሆኖ በትውልዶቹ ሁሉ ይቀጥላል። በኢዮቀልዩ ነፃ አይለቀቅም።
ቅጥር በሌላቾው መንደሮቜ ውስጥ ዹሚገኙ ቀቶቜ ግን በገጠራማ አካባቢ ዹሚገኝ ዚእርሻ መሬት ክፍል እንደሆኑ ይቆጠራሉ። ዚመዋጀት መብታ቞ው እንደተጠበቀ ይቆይፀ በኢዮቀልዩም ነፃ ይለቀቁ።
“‘በሌዋውያን ኚተሞቜ ውስጥ ያሉትን ዚሌዋውያን ቀቶቜ በተመለኹተ ግን ሌዋውያኑ እነዚህን ቀቶቜ ዚመዋጀት መብታ቞ው ምንጊዜም ዹተጠበቀ ነው።
ዚሌዋውያን ንብሚት ተመልሶ ካልተገዛ ዚእነሱ በሆነው ኹተማ ውስጥ ዹሚገኘው ዹተሾጠው ቀት በኢዮቀልዩ ነፃ ይለቀቃልፀ ምክንያቱም በሌዋውያኑ ኚተሞቜ ውስጥ ዚሚገኙት ቀቶቜ በእስራኀላውያን መካኚል ያሉ ዚሌዋውያኑ ንብሚቶቜ ና቞ው።
ኹዚህም በላይ በኚተሞቻ቞ው ዙሪያ ያለው ዚግጊሜ መሬት ዘላለማዊ ርስታ቞ው ስለሆነ መሞጥ አይኖርበትም።
“‘በአቅራቢያህ ያለ ወንድምህ ቢደኞይና ራሱን ማስተዳደር ቢያቅተው አብሮህ በሕይወት ይኖር ዘንድ አንድን ዚባዕድ አገር ሰውና ሰፋሪ እንደምትሚዳ ሁሉ ልትሚዳው ይገባል።
ኚእሱ ወለድ ወይም ትርፍ አትቀበል። ኹዚህ ይልቅ አምላክህን ፍራፀ ወንድምህም አብሮህ በሕይወት ይኖራል።
ገንዘብህን በወለድ አታበድሚው ወይም እህል ስታበድሚው ትርፍ አትጠይቀው።
ዹኹነአንን ምድር በመስጠት አምላካቜሁ መሆኔን አስመሠክር ዘንድ ኚግብፅ ምድር ያወጣኋቜሁ እኔ አምላካቜሁ ይሖዋ ነኝ።
“‘በአቅራቢያህ ዹሚኖር ወንድምህ ቢደኞይና ራሱን ለአንተ ለመሞጥ ቢገደድ እንደ ባሪያ እንዲሠራ አታስገድደው።
እንደ ቅጥር ሠራተኛና እንደ ሰፋሪ ሊታይ ይገባዋል። እስኚ ኢዮቀልዩ ዓመት ድሚስ ያገልግልህ።
ኚዚያም እሱም ሆነ አብሚውት ያሉት ልጆቹ ትተውህ ይሄዳሉፀ ወደ ዘመዶቹም ይመለሳሉ። እሱም ወደ ቀድሞ አባቶቹ ርስት ይመለስ።
ምክንያቱም እነሱ ኚግብፅ ምድር ያወጣኋ቞ው ባሪያዎቌ ና቞ው። እንደ ባሪያ ራሳ቞ውን መሞጥ ዚለባ቞ውም።
ዚጭካኔ ድርጊት ልትፈጜምበት አይገባምፀ አምላክህን መፍራት ይኖርብሃል።
ወንድ ባሪያዎቻቜሁና ሎት ባሪያዎቻቜሁ በዙሪያቜሁ ካሉት ብሔራት ዚመጡ ይሁኑፀ ኚእነሱ መካኚል ወንድ ባሪያ ወይም ሎት ባሪያ መግዛት ትቜላላቜሁ።
በተጚማሪም ኚእናንተ ጋር ኚሚኖሩት ባዕዳን ሰፋሪዎቜ እንዲሁም እነሱ በምድራቜሁ ኚወለዷ቞ው ቀተሰቊቻ቞ው መካኚል ባሪያዎቜን መግዛት ትቜላላቜሁፀ እነሱም ዚእናንተ ንብሚት ይሆናሉ።
እነሱንም እንደ ቋሚ ንብሚት አድርጋቜሁ ኚእናንተ በኋላ ለሚመጡት ልጆቻቜሁ ማውሚስ ትቜላላቜሁ። ባሪያ አድርጋቜሁ ልታሠሯ቞ው ትቜላላቜሁፀ ወንድሞቻቜሁ ዚሆኑትን እስራኀላውያንን ግን በጭካኔ አትግዟ቞ው።
“‘በመካኚልህ ያለ ዚባዕድ አገር ሰው ወይም ሰፋሪ ሀብታም ቢሆንና ኚእሱ ጋር ያለው ወንድምህ ደግሞ ደህይቶ ለባዕድ አገሩ ሰው ወይም ሰፋሪ አሊያም ኚባዕድ አገሩ ሰው ቀተሰብ መካኚል ለአንዱ ራሱን ለመሞጥ ቢገደድ
ይህ ሰው ራሱን ኹሾጠም በኋላ ዚመዋጀት መብቱ ዹተጠበቀ ይሆናል። ኚወንድሞቹ አንዱ መልሶ ሊገዛው ይቜላልፀ
ወይም ደግሞ አጎቱ አሊያም ዚአጎቱ ልጅ መልሶ ሊገዛው ይቜላልፀ አሊያም ደግሞ ማንኛውም ዚቅርብ ዘመዱ ማለትም ኚቀተሰቊቹ አንዱ መልሶ ሊገዛው ይቜላል። “‘ወይም ደግሞ ሰውዹው ራሱ ሀብት ካገኘ ራሱን መልሶ ሊገዛ ይቜላል።
እሱም ራሱን ኚሞጠበት ዓመት አንስቶ እስኚ ኢዮቀልዩ ዓመት ድሚስ ያለውን ጊዜ ኹገዛው ሰው ጋር በመሆን ያስላፀ ዚተሞጠበትም ገንዘብ ኚዓመታቱ ብዛት ጋር ዚሚመጣጠን ይሁን። በዚህ ጊዜ ውስጥ ያሉት ዚሥራ ቀናት ዚሚሰሉት ዚአንድ ቅጥር ሠራተኛ ዚሥራ ቀናት በሚሰሉበት መንገድ ይሆናል።
ገና ብዙ ዓመታት ዚሚቀሩ ኹሆነ እሱን ለመግዛት ኹተኹፈለው ገንዘብ ላይ ዚቀሪዎቹን ዓመታት ብዛት ግምት ውስጥ በማስገባት ራሱን ዚሚዋጅበትን ዋጋ ይክፈል።
እስኚ ኢዮቀልዩ ዓመት ድሚስ ዚሚቀሩት ዓመታት ጥቂት ኹሆኑ ደግሞ ይህን ለራሱ ያስላፀ በቀሩት ዓመታት ብዛት ልክም ዚሚዋጅበትን ዋጋ ይክፈል።
ኚእሱም ጋር በሚቆይበት ጊዜ ኚዓመት እስኚ ዓመት እንደ ቅጥር ሠራተኛ ሆኖ ያገልግለውፀ አንተም ዚጭካኔ ድርጊት እንዳይፈጜምበት ተኚታተል።
ሆኖም ኚእነዚህ መንገዶቜ በአንዱ ራሱን መልሶ መግዛት ካልቻለ በኢዮቀልዩ ዓመት ነፃ ይለቀቃልፀ እሱም ሆነ ልጆቹ አብሚውት ነፃ ይለቀቁ።
“‘እስራኀላውያን ዚእኔ ባሪያዎቜ ና቞ው። እነሱ ኚግብፅ ምድር ያወጣኋ቞ው ባሪያዎቌ ና቞ው። እኔ አምላካቜሁ ይሖዋ ነኝ።
ይሖዋ ሙሮንና አሮንን እንዲህ አላቾው፩
“አንድ ሰው በቆዳው ላይ እብጠት፣ እኚክ ወይም ቋቁቻ ቢወጣበትና ወደ ሥጋ ደዌነት ቢለወጥበት ወደ ካህኑ አሮን ወይም ካህናት ኚሆኑት ወንዶቜ ልጆቹ ወደ አንዱ ያምጡት።
ካህኑም በቆዳው ላይ ያለውን ቁስል ይመሚምራል። ቁስሉ ባለበት ቊታ ላይ ያለው ፀጉር ወደ ነጭነት ኹተለወጠና ቁስሉ ኚቆዳው ዘልቆ ዚገባ ኹሆነ ይህ ዚሥጋ ደዌ ነው። ካህኑ ቁስሉን ኹመሹመሹ በኋላ ግለሰቡ ርኩስ መሆኑን ያስታውቃል።
ሆኖም በቆዳው ላይ ያለው ቋቁቻ ነጭ ኹሆነና ኚቆዳው ዘልቆ ዚገባ ካልሆነ እንዲሁም በዚያ ቊታ ላይ ያለው ፀጉር ወደ ነጭነት ካልተለወጠ ካህኑ ቁስል ዚወጣበትን ሰው ለሰባት ቀን ተገልሎ እንዲቆይ ያደርገዋል።
ኚዚያም በሰባተኛው ቀን ካህኑ ሰውዹውን ይመሚምሚዋልፀ ቁስሉ ባለበት ኹቆመና በቆዳው ላይ ካልተስፋፋ ካህኑ ሰውዹውን ለተጚማሪ ሰባት ቀን ተገልሎ እንዲቆይ ያደርገዋል።
“ካህኑም በሰባተኛው ቀን እንደገና ሰውዹውን ይመርምሚውፀ ቁስሉ ኹኹሰመና በቆዳው ላይ ካልተስፋፋ ካህኑ ሰውዹው ንጹሕ መሆኑን ያስታውቃልፀ ይህ እኚክ ነው። ኚዚያም ሰውዹው ልብሶቹን ያጥባልፀ ንጹሕም ይሆናል።
ሆኖም ሰውዹው መንጻቱን ለማሚጋገጥ ካህኑ ፊት ኹቀሹበ በኋላ እኚኩ በቆዳው ላይ እዚተስፋፋ ኚሄደ እንደገና ካህኑ ፊት ይቀርባል።
ካህኑም ይመሚምሚዋልፀ እኚኩ በቆዳው ላይ ተስፋፍቶ ኹሆነ ካህኑ ሰውዹው ርኩስ መሆኑን ያስታውቃል። ይህ ዚሥጋ ደዌ ነው።
“አንድ ሰው ዚሥጋ ደዌ ቢይዘው ወደ ካህኑ እንዲቀርብ ይደሚግፀ
ካህኑም ይመሚምሚዋል። በቆዳው ላይ ነጭ እብጠት ካለና በዚያ ቊታ ላይ ያለውን ፀጉር ወደ ነጭነት ኹለወጠው እንዲሁም በእብጠቱ ላይ አፉን ዹኹፈተ ቁስል ካለ
ይህ በቆዳው ላይ ዚወጣ ሥር ዹሰደደ ዚሥጋ ደዌ ነውፀ ካህኑም ሰውዹው ርኩስ መሆኑን ያስታውቃል። ሰውዹው ርኩስ ስለሆነም ለተወሰነ ጊዜ ተገልሎ እንዲቆይ ማድሚግ አያስፈልገውም።