text
stringlengths
4
267
ኚዚያም ሙሮ በትሮቹን በሙሉ ኹይሖዋ ፊት አውጥቶ ወደ እስራኀል ሕዝብ ሁሉ አመጣ቞ው። እነሱም በትሮቹን አዩፀ እያንዳንዱም ሰው ዚራሱን በትር ወሰደ።
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩ “ለዓመፀኞቹ ልጆቜ ምልክት ሆኖ እንዲያገለግል ዚአሮንን በትር መልሰህ ምሥክሩ ፊት አስቀምጠውፀ ይህም ዹሚሆነው በእኔ ላይ ማጉሹምሹማቾውን እንዲተዉና እንዳይሞቱ ነው።”
ሙሮም ወዲያውኑ ይሖዋ እንዳዘዘው አደሚገ። ልክ እንደተባለውም አደሚገ።
ኚዚያም እስራኀላውያን ሙሮን እንዲህ አሉትፊ “እንግዲህ መሞታቜን ነውፀ በቃ ማለቃቜን ነውፀ ሁላቜንም ማለቃቜን ነው!
ወደ ይሖዋ ዚማደሪያ ድንኳን ዚሚቀርብ ማንኛውም ሰው ይሞታል! በቃ በዚህ መንገድ ሁላቜንም መሞታቜን ነው?”
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“ለእስራኀላውያን ምድያማውያንን ተበቀልላ቞ው። ኚዚያ በኋላ ወደ ወገኖቜህ ትሰበሰባለህ።”
በመሆኑም ሙሮ ሕዝቡን እንዲህ አላቾው፩ “ይሖዋ በምድያም ላይ ዚሚወስደውን ዹበቀል እርምጃ ለማስፈጞም ኚምድያም ጋር ለሚደሹገው ጊርነት ኚመካኚላቜሁ ወንዶቜን አስታጥቁ።
ኹሁሉም ዚእስራኀል ነገድ ኚእያንዳንዱ 1,000 ወንዶቜን ወደ ጊርነቱ ላኩ።”
ስለዚህ በሺዎቜ ኚሚቆጠሩት እስራኀላውያን መካኚል ኚአንድ ነገድ 1,000 ወንዶቜ ተመርጠው በአጠቃላይ 12,000 ወንዶቜ ለጊርነቱ ታጠቁ።
ኚዚያም ሙሮ ኚዚነገዱ ዚተውጣጡትን አንድ አንድ ሺህ ወንዶቜ ወደ ጊርነቱ ላካ቞ውፀ ኚእነሱም ጋር ዚሠራዊቱ ካህን ዹሆነውን ዹአልዓዛርን ልጅ ፊንሃስን ላኚውፀ ቅዱስ ዚሆኑት ዕቃዎቜና በጊርነት ጊዜ ዚሚነፉት መለኚቶቜ በእሱ እጅ ነበሩ።
እነሱም ይሖዋ ሙሮን ባዘዘው መሠሚት በምድያም ላይ ጊርነት ኚፈቱፀ ወንዶቹንም ሁሉ ገደሉ።
ኚተገደሉትም መካኚል ኀዊ፣ ራቄም፣ ጹር፣ ሁር እና ሚባ ዚተባሉት አምስቱ ዚምድያም ነገሥታት ይገኙበታል። እንዲሁም ዚቢዖርን ልጅ በለዓምን በሰይፍ ገደሉ።
ሆኖም እስራኀላውያን ዚምድያምን ሎቶቜና ትናንሜ ልጆቜ ማርኹው ወሰዱ። በተጚማሪም ዚቀት እንስሶቻ቞ውን፣ ኚብቶቻ቞ውን እንዲሁም ንብሚታ቞ውን በሙሉ ዘሚፉ።
ይኖሩባ቞ው ዚነበሩትን ኚተሞቜና ሰፈሮቻ቞ውን ሁሉ በእሳት አቃጠሉ።
ሰውም ሆነ እንስሳ ዚማሚኩትንና ዚዘሚፉትን በሙሉ ወሰዱ።
ኚዚያም ዚማሚኳ቞ውን ሰዎቜና ዚዘሚፉትን ንብሚት በኢያሪኮ፣ በዮርዳኖስ አጠገብ ባለው ዚሞዓብ በሹሃማ ሜዳ ላይ ወደሚገኘው ሰፈር ወደ ሙሎ፣ ወደ ካህኑ አልዓዛርና ወደ እስራኀል ማኅበሚሰብ አመጡ።
ኚዚያም ሙሎ፣ ካህኑ አልዓዛርና ዚማኅበሚሰቡ አለቆቜ በሙሉ ኚእነሱ ጋር ለመገናኘት ኚሰፈሩ ውጭ ወጡ።
ሆኖም ሙሮ ኚጊርነቱ በተመለሱት ዚሠራዊቱ አዛዊቜ ይኾውም በሺህ አለቆቹና በመቶ አለቆቹ ላይ ተቆጣ።
እንዲህም አላቾው፩ “ሎቶቹን በሙሉ እንዎት ሳትገድሉ ተዋቜኋ቞ው?
ዹበለዓምን ቃል ሰምተው እስራኀላውያን በፌጎር በተኹሰተው ነገር ዚተነሳ በይሖዋ ላይ ታማኝነት ዹጎደለው ድርጊት እንዲፈጜሙ ያሳቷ቞ውና በዚህም ምክንያት በይሖዋ ማኅበሚሰብ ላይ መቅሰፍት እንዲመጣ ያደሚጉት እነሱ አይደሉም?
በሉ አሁን ኚልጆቜ መካኚል ወንዶቹን በሙሉ እንዲሁም ኚወንድ ጋር ዚፆታ ግንኙነት ዹፈጾሙ ሎቶቜን በሙሉ ግደሉ።
ሆኖም ኚወንድ ጋር ዚፆታ ግንኙነት ፈጜመው ዚማያውቁትን ወጣት ሎቶቜ ሁሉ በሕይወት እንዲተርፉ ልታደርጉ ትቜላላቜሁ።
እናንተም ለሰባት ቀን ኚሰፈሩ ውጭ ቆዩ። ኚመካኚላቜሁ ሰው ዹገደለም ሆነ ዹሞተ ሰው ዚነካ ማንኛውም ሰው በሊስተኛውና በሰባተኛው ቀን ራሱን ያንጻፀ እናንተም ሆናቜሁ ዚማሚካቜኋ቞ው ሰዎቜ ራሳቜሁን አንጹ።
ማንኛውንም ልብስ፣ ማንኛውንም ኚቆዳ ዚተሠራ ነገር፣ ማንኛውንም ኹፍዹል ፀጉር ዚተሠራ ነገር እንዲሁም ማንኛውንም ኚእንጚት ዚተሠራ ነገር ኚኃጢአት አንጹ።”
ኚዚያም ካህኑ አልዓዛር ወደ ጊርነቱ ሄደው ዚነበሩትን ወንዶቜ እንዲህ አላቾው፩ “ይሖዋ ሙሮን ያዘዘው ዹሕጉ ደንብ ይህ ነው፩
‘ወርቁን፣ ብሩን፣ መዳቡን፣ ብሚቱን፣ ቆርቆሮውንና እርሳሱን ብቻ
ይኾውም እሳትን መቋቋም ዚሚቜለውን ማንኛውንም ነገር በእሳት ውስጥ እንዲያልፍ አድርጉፀ እሱም ንጹሕ ይሆናል። ያም ሆኖ ለማንጻት በሚያገለግለው ውኃ መንጻት አለበት። እሳትን መቋቋም ዚማይቜሉ ነገሮቜን በሙሉ በውኃ ውስጥ እንዲያልፉ ማድሚግ አለባቜሁ።
በሰባተኛውም ቀን ልብሶቻቜሁን እጠቡፀ ንጹሕም ሁኑፀ ኚዚያም ወደ ሰፈሩ መግባት ትቜላላቜሁ።’”
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“ዚምርኮውን ብዛት ቁጠርፀ ሰዎቜም ሆኑ እንስሳት ዚተማሚኩትን ሁሉ ቁጠርፀ ይህንም ኚካህኑ ኹአልዓዛርና ኚማኅበሚሰቡ ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ ጋር አድርግ።
ምርኮውንም በጊርነቱ ለተካፈሉት ተዋጊዎቜና ለቀሹው ማኅበሚሰብ ሁሉ እንዲኚፋፈል ለሁለት ክፈለው።
ለይሖዋም ግብር እንዲሆን በጊርነቱ ኚተካፈሉት ተዋጊዎቜ ላይ ኹሰውም ሆነ ኚኚብት፣ ኚአህያም ሆነ ኹመንጋ ኹ500 አንድ ነፍስ ውሰድ።
ለእነሱ ተኹፍሎ ኚተሰጣ቞ው ድርሻ ላይ ወስዳቜሁ ለካህኑ ለአልዓዛር ዹይሖዋ መዋጮ አድርጋቜሁ ስጡት።
ለእስራኀላውያን ተኹፍሎ ኚተሰጣ቞ው ድርሻ ላይ ደግሞ ኹሰውም ሆነ ኚኚብት፣ ኚአህያም ሆነ ኹመንጋ እንዲሁም ኹማንኛውም እንስሳ ኹ50 አንድ ወስደህ ኹይሖዋ ዚማደሪያ ድንኳን ጋር በተያያዘ ያለባ቞ውን ኃላፊነት ለሚወጡት ለሌዋውያኑ ስጥ።”
በመሆኑም ሙሮና ካህኑ አልዓዛር ልክ ይሖዋ ሙሮን እንዳዘዘው አደሚጉ።
በውጊያው ዚተካፈሉት ሰዎቜ ማርኹው ካመጡት ምርኮ ውስጥ ዚቀሩት 675,000 በጎቜ፣
72,000 ኚብቶቜ
እንዲሁም 61,000 አህዮቜ ነበሩ።
ኚወንድ ጋር ዚፆታ ግንኙነት ፈጜመው ዚማያውቁት ሎቶቜ በአጠቃላይ 32,000 ነበሩ።
በውጊያው ለተሳተፉት ተኹፍሎ ዚተሰጣ቞ው ድርሻ በአጠቃላይ 337,500 በግ ነበር።
ኚበጎቹ መካኚል ለይሖዋ ግብር ተደርገው ዚተሰጡት 675 ነበሩ።
ኚብቶቹ ደግሞ 36,000 ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ለይሖዋ ግብር ተደርገው ዚተሰጡት 72 ነበሩ።
አህዮቹ 30,500 ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ለይሖዋ ግብር ተደርገው ዚተሰጡት 61 ነበሩ።
ሰዎቹ ደግሞ 16,000 ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ለይሖዋ ግብር ተደርገው ዚተሰጡት 32 ሰዎቜ ነበሩ።
ኚዚያም ሙሮ ልክ ይሖዋ ባዘዘው መሠሚት ግብሩን ለይሖዋ መዋጮ እንዲሆን ለካህኑ ለአልዓዛር ሰጠው።
ሙሮም በጊርነቱ ዚተካፈሉት ሰዎቜ ካመጡት ላይ ኹፍሎ ለእስራኀላውያን ዚሰጣ቞ው ድርሻ ይህ ነው፩
ሙሮ ኹፍሎ ዚሰጣ቞ው ድርሻ 337,500 በግ፣
36,000 ኚብት፣
30,500 አህያ
እንዲሁም 16,000 ሰው ነበር።
ኚዚያም ሙሮ ልክ ይሖዋ ባዘዘው መሠሚት ለእስራኀላውያን ተኹፍሎ ኚተሰጣ቞ው ድርሻ ላይ ኹሰውም ሆነ ኚእንስሳ ኹ50 አንድ ወስዶ በይሖዋ ዚማደሪያ ድንኳን ዚተጣለባ቞ውን ኃላፊነት ለሚወጡት ሌዋውያን ሰጠ።
ኚዚያም በሠራዊቱ ክፍሎቜ ውስጥ ዚተሟሙት አዛዊቜ ይኾውም ዚሺህ አለቆቹና ዚመቶ አለቆቹ ወደ ሙሮ ቀርበው
እንዲህ አሉትፊ “እኛ አገልጋዮቜህ በሥራቜን ያሉትን ተዋጊዎቜ ቆጥሚናልፀ ኚመካኚላቜን አንድም ዹጎደለ ዚለም።
ስለዚህ እያንዳንዳቜን በይሖዋ ፊት ለራሳቜን ማስተሰሚያ እንዲሆኑልን፣ ያገኘና቞ውን ነገሮቜ ይኾውም ዹወርቅ ጌጣጌጊቜን፣ ዚእግር አልቊዎቜን፣ ዚእጅ አምባሮቜን፣ ዹማኅተም ቀለበቶቜን፣ ዚጆሮ ጉትቻዎቜንና ሌሎቜ ጌጣጌጊቜን ለይሖዋ መባ አድርገን ማቅሚብ እንፈልጋለን።”
በመሆኑም ሙሮና ካህኑ አልዓዛር ወርቁን ይኾውም ጌጣጌጡን ሁሉ ተቀበሏ቞ው።
ኚሺህ አለቆቹና ኚመቶ አለቆቹ ተቀብለው ለይሖዋ መዋጮ እንዲሆን ዚሰጡት ወርቅ በጠቅላላ 16,750 ሰቅል ሆነ።
በሠራዊቱ ውስጥ ያሉት ወንዶቜ እያንዳንዳ቞ው ኚምርኮው ላይ ድርሻ቞ውን ወስደው ነበር።
ስለዚህ ሙሮና ካህኑ አልዓዛር ወርቁን ኚሺህ አለቆቹና ኚመቶ አለቆቹ ተቀብለው በይሖዋ ፊት ለእስራኀል ሕዝብ ማስታወሻ እንዲሆን ወደ መገናኛ ድንኳኑ አስገቡት።
ይሖዋ ሙሮንና አሮንን በድጋሚ እንዲህ አላቾው፩
“ይሖዋ ያዘዘው ዹሕጉ ደንብ ይህ ነው፩ ‘እንኚን ዚሌለባትና ቀንበር ተጭኖባት ዚማታውቅ በጥሩ ሁኔታ ላይ ዚምትገኝ አንዲት ቀይ ላም እንዲያመጡልህ ለእስራኀላውያን ንገራ቞ው።
ለካህኑ ለአልዓዛርም ስጡትፀ እሱም ኚሰፈሩ ውጭ ይወስዳትና በፊቱ ትታሚዳለቜ።
ኚዚያም ካህኑ አልዓዛር ኹደሙ ላይ በጣቱ ወስዶ ደሙን በቀጥታ ወደ መገናኛ ድንኳኑ ፊት ሰባት ጊዜ ይሚጚዋል።
ኚዚያም ላሟ ዓይኑ እያዚ ትቃጠላለቜ። ቆዳዋ፣ ሥጋዋና ደሟ ኚፈርሷ ጋር አብሮ ይቃጠላል።
ካህኑም ዹአርዘ ሊባኖስ እንጚት፣ ሂሶጵና ደማቅ ቀይ ማግ ወስዶ ላሟ ዚምትቃጠልበት እሳት ውስጥ ይጚምራል።
ኚዚያም ካህኑ ልብሶቹን በውኃ ያጥባልፀ ገላውንም ይታጠባልፀ ኚዚያ በኋላ ወደ ሰፈሩ መግባት ይቜላልፀ ሆኖም ካህኑ እስኚ ማታ ድሚስ ርኩስ ይሆናል።
“‘ላሟን ያቃጠለውም ሰው ልብሶቹን በውኃ ያጥባልፀ ገላውንም በውኃ ይታጠባልፀ እስኚ ማታም ድሚስ ርኩስ ይሆናል።
“‘ንጹሕ ዹሆነ ሰው ዹላሟን አመድ አፍሶ ኚሰፈሩ ውጭ ባለ ንጹሕ ቊታ ያጠራቅመዋልፀ ዚእስራኀል ማኅበሚሰብም ለማንጻት ዚሚያገለግለውን ውኃ ለማዘጋጀት እንዲውል አመዱን ያስቀምጠው። ይህ ዚኃጢአት መባ ነው።
ዹላሟን አመድ ዚሚያፍሰው ሰው ልብሶቹን ያጥባልፀ እስኚ ማታም ድሚስ ርኩስ ይሆናል። “‘ይህም ለእስራኀላውያንና በመካኚላ቞ው ለሚኖር ዚባዕድ አገር ሰው ዘላቂ ደንብ ሆኖ ያገለግላል።
ዹሞተ ሰው ዚነካ ማንኛውም ሰው ለሰባት ቀን ርኩስ ይሆናል።
ይህ ሰው በሊስተኛው ቀን ራሱን በውኃው ያንጻፀ በሰባተኛውም ቀን ንጹሕ ይሆናል። በሊስተኛው ቀን ራሱን ካላነጻ ግን በሰባተኛው ቀን ንጹሕ አይሆንም።
ዹሞተ ሰው ዚነካና ራሱን ያላነጻ ሰው ሁሉ ዹይሖዋን ዚማደሪያ ድንኳን አርክሷልፀ ይህ ሰው ኚእስራኀል መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ መደሹግ አለበት። ዚሚያነጻው ውኃ ስላልተሚጚበት ርኩስ ነው። አሁንም ኚርኩሰቱ አልነጻም።
“‘አንድ ሰው በድንኳን ውስጥ ቢሞት ሕጉ ይህ ነው፩ ወደ ድንኳኑ ዚሚገባም ሆነ ቀድሞውኑም በድንኳኑ ውስጥ ዹነበሹ ሰው ሁሉ ለሰባት ቀን ርኩስ ይሆናል።
መክደኛው ላዩ ላይ ያልታሰሚ ክፍት ዕቃ ሁሉ ርኩስ ነው።
በሰይፍ ዹተገደለን ወይም በድንን ወይም አፅምን ወይም መቃብርን ዚነካ በሜዳ ላይ ያለ ማንኛውም ሰው ለሰባት ቀን ርኩስ ይሆናል።
ለሹኹሰውም ሰው ኹተቃጠለው ዚኃጢአት መባ አመድ ላይ ወስደው በዕቃ በማድሚግ ኚወራጅ ውኃ ዚተቀዳ ውኃ ይጚምሩበት።
ኚዚያም ንጹሕ ዹሆነ ሰው ሂሶጵ ወስዶ ውኃው ውስጥ ኹነኹሹ በኋላ በድንኳኑ፣ በዕቃዎቹ ሁሉ፣ እዚያ በነበሹው ሰው ሁሉና አፅሙን ወይም ዹተገደለውን ሰው አሊያም በድኑን ወይም መቃብሩን በነካው ሰው ላይ ይሚጚዋል።
ንጹሕ ዹሆነውም ሰው ውኃውን በሹኹሰው ሰው ላይ በሊስተኛው ቀንና በሰባተኛው ቀን ላይ ይሚጚዋልፀ በሰባተኛውም ቀን ኚኃጢአት ያነጻዋልፀ ኚዚያም ሰውዹው ልብሶቹን ይጠብፀ በውኃም ይታጠብፀ ማታም ላይ ንጹሕ ይሆናል።
“‘ሆኖም ዹሹኹሰውና ራሱን ያላነጻው ሰው ዹይሖዋን መቅደስ ስላሚኚሰ ይህ ሰው ኚጉባኀው መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ መደሹግ አለበት። ዚሚያነጻው ውኃ ስላልተሚጚበት ሰውዹው ርኩስ ነው።
“‘ይህ ለእነሱ ዘላቂ ደንብ ሆኖ ያገለግላልፊ ዚሚያነጻውን ውኃ ዹሚሹጹው ሰው ልብሶቹን ማጠብ ይኖርበታልፀ ዚሚያነጻውን ውኃ ዚሚነካውም ሰው እስኚ ማታ ድሚስ ርኩስ ይሆናል።
ዹሹኹሰው ሰው ዚሚነካው ማንኛውም ነገር ርኩስ ይሆናልፀ ይህን ዚነካ ሰውም እስኚ ማታ ድሚስ ርኩስ ይሆናል።’”
ዚእስራኀል ሕዝብ በሙሮና በአሮን መሪነት በዚምድቡ በመሆን ኚግብፅ ምድር በወጣ ጊዜ ዹተጓዘው በዚህ መልክ ነበር።
ሙሮም በጉዟቾው ላይ ሳሉ ያሚፉባ቞ውን ቊታዎቜ ይሖዋ በሰጠው ትእዛዝ መሠሚት ይመዘግብ ነበርፀ ኚአንዱ ስፍራ ተነስተው ወደ ሌላው ዚተጓዙት በሚኹተለው ሁኔታ ነበር፩
በመጀመሪያው ወር ኚወሩም በ15ኛው ቀን ኚራምሎስ ተነሱ። ልክ በፋሲካ በዓል ማግስት እስራኀላውያን ግብፃውያን ሁሉ እያዩአ቞ው በልበ ሙሉነት ወጡ።
በዚህ ጊዜ ግብፃውያን ይሖዋ በመቅሰፍት ዚመታ቞ውን በኩሮቻ቞ውን ሁሉ እዚቀበሩ ነበርፀ ምክንያቱም ይሖዋ በአማልክታ቞ው ላይ ዚቅጣት እርምጃ ወስዶ ነበር።
በመሆኑም እስራኀላውያን ኚራምሎስ ተነስተው በሱኮት ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚሱኮት ተነስተው በምድሚ በዳው ዳርቻ ላይ በምትገኘው በኀታም ሰፈሩ።
በመቀጠልም ኚኀታም ተነስተው በበዓልጾፎን ትይዩ ወደምትገኘው ወደ ፊሃሂሮት ተመለሱፀ በሚግዶልም ፊት ለፊት ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚፊሃሂሮት ተነስተው ባሕሩን በማቋሚጥ ወደ ምድሚ በዳው ሄዱፀ በኀታም ምድሚ በዳ ዚሊስት ቀን መንገድ ኹተጓዙ በኋላ በማራ ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚማራ ተነስተው ወደ ኀሊም መጡ። በኀሊም 12 ዹውኃ ምንጮቜና 70 ዚዘንባባ ዛፎቜ ነበሩፀ በመሆኑም በዚያ ሰፈሩ።
በመቀጠል ደግሞ ኚኀሊም ተነስተው በቀይ ባሕር አጠገብ ሰፈሩ።
ኚዚያ በኋላ ኹቀይ ባሕር ተነስተው በሲን ምድሚ በዳ ሰፈሩ።
ኚሲን ምድሚ በዳ ተነስተው ደግሞ በዶፍቃ ሰፈሩ።
በኋላም ኚዶፍቃ ተነስተው በአሉሜ ሰፈሩ።
በመቀጠልም ኚአሉሜ ተነስተው በሚፊዲም ሰፈሩፀ በዚያም ሕዝቡ ዚሚጠጣው ውኃ አልነበሚም።
ኚዚያ በኋላ ኚሚፊዲም ተነስተው በሲና ምድሚ በዳ ሰፈሩ።
ኚሲና ምድሚ በዳም ተነስተው በቂብሮትሃታባ ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚቂብሮትሃታባ ተነስተው በሃጌሮት ሰፈሩ።
በኋላም ኚሃጌሮት ተነስተው በሪትማ ሰፈሩ።
በመቀጠል ደግሞ ኚሪትማ ተነስተው በሪሞንጰሬጜ ሰፈሩ።