text
stringlengths
4
267
ዹምናሮ ልጆቜ እነዚህ ነበሩፊ ኚማኪር ዚማኪራውያን ቀተሰብፀ ማኪር ጊልያድን ወለደፀ ኚጊልያድ ዚጊልያዳውያን ቀተሰብ።
ዚጊልያድ ልጆቜ እነዚህ ነበሩፊ ኚኢዔዝር ዚኢዔዝራውያን ቀተሰብ፣ ኹሄሌቅ ዚሄሌቃውያን ቀተሰብ፣
ኚአስሪዔል ዚአስሪዔላውያን ቀተሰብ፣ ኚሎኬም ዚሎኬማውያን ቀተሰብ፣
ኚሞሚዳ ዚሞሚዳውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኹሄፌር ዚሄፌራውያን ቀተሰብ።
ዹሄፌር ልጅ ሰለጰአድ ሎቶቜ ልጆቜ ብቻ እንጂ ወንዶቜ ልጆቜ አልነበሩትምፀ ዚሰለጰአድ ሎቶቜ ልጆቜ ስም ማህላ፣ ኖኅ፣ ሆግላ፣ ሚልካ እና ቲርጻ ነበር።
ዹምናሮ ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 52,700 ነበሩ።
ዚኀፍሬም ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚሹተላ ዚሹተላውያን ቀተሰብ፣ ኚቀኬር ዚቀኬራውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚታሃን ዚታሃናውያን ቀተሰብ።
ዚሹተላ ልጆቜ እነዚህ ነበሩፊ ኚኀራን ዚኀራናውያን ቀተሰብ።
ዚኀፍሬም ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 32,500 ነበሩ። ዚዮሎፍ ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩ።
ዚቢንያም ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚቀላ ዚቀላውያን ቀተሰብ፣ ኚአሜቀል ዚአሜቀላውያን ቀተሰብ፣ ኚአሂራም ዚአሂራማውያን ቀተሰብ፣
ኚሌፉፋም ዚሌፉፋማውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኹሁፋም ዚሁፋማውያን ቀተሰብ።
ዚቀላ ልጆቜ አርድ እና ንዕማን ነበሩፀ ኚአርድ ዚአርዳውያን ቀተሰብ፣ ኹንዕማን ደግሞ ዚንዕማናውያን ቀተሰብ።
ዚቢንያም ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 45,600 ነበሩ።
ዚዳን ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚሹሃም ዚሹሃማውያን ቀተሰብ። ዚዳን ቀተሰቊቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩ።
ኚሹሃማውያን ቀተሰቊቜ በሙሉ ዚተመዘገቡት 64,400 ነበሩ።
ዹአሮር ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኹይምናህ ዚይምናሃውያን ቀተሰብ፣ ኚይሜዊ ዚይሜዋውያን ቀተሰብ፣ ኚበሪአ ዚበሪአውያን ቀተሰብፀ
ኚበሪአ ልጆቜፊ ኚሄቀር ዚሄቀራውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚማልኪኀል ዚማልኪኀላውያን ቀተሰብ።
ዹአሮር ሎት ልጅ ስም ሎራህ ነበር።
ዹአሮር ልጆቜ ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 53,400 ነበሩ።
ዚንፍታሌም ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚያህጜኀል ዚያህጜኀላውያን ቀተሰብ፣ ኹጉኒ ዚጉናውያን ቀተሰብ፣
ኚዚጌር ዚዚጌራውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚሺሌም ዚሺሌማውያን ቀተሰብ።
ዚንፍታሌም ቀተሰቊቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 45,400 ነበሩ።
ኚእስራኀላውያን መካኚል ዚተመዘገቡት በጠቅላላ 601,730 ነበሩ።
ኹዚህ በኋላ ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“ምድሪቱ ለእነዚህ በስማ቞ው ዝርዝር መሠሚት ርስት ሆና ትኚፋፈል።
ተለቅ ላሉት ቡድኖቜ በዛ ያለ ውርሻ ትሰጣ቞ዋለህፀ አነስ ላሉት ቡድኖቜ ደግሞ አነስ ያለ ውርሻ ትሰጣ቞ዋለህ። ዚእያንዳንዱ ቡድን ውርሻ በተመዘገቡት ሰዎቜ ብዛት ተመጣጥኖ መሰጠት አለበት።
ይሁን እንጂ ምድሪቱ መኹፋፈል ያለባት በዕጣ ነው። ውርሻ቞ውንም ማግኘት ያለባ቞ው በአባቶቻ቞ው ነገዶቜ ስም መሠሚት ነው።
እያንዳንዱ ውርሻ ዹሚወሰነው በዕጣ ሲሆን በኋላም ውርሻው እንደ ቡድኑ ትልቅነትና ትንሜነት ይኚፋፈላል።”
ኚሌዋውያኑ መካኚል በዚቀተሰባ቞ው ዚተመዘገቡት እነዚህ ነበሩፊ ኚጌድሶን ዚጌድሶናውያን ቀተሰብ፣ ኚቀአት ዚቀአታውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚሜራሪ ዚሜራራውያን ቀተሰብ።
ዚሌዋውያን ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፊ ዚሊብናውያን ቀተሰብ፣ ዚኬብሮናውያን ቀተሰብ፣ ዚማህላውያን ቀተሰብ፣ ዚሙሻውያን ቀተሰብ እና ዚቆሬያውያን ቀተሰብ። ቀአት አምራምን ወለደ።
ዚአምራም ሚስት ስሟ ዮካቀድ ነበርፀ እሷም ዹሌዊ ሚስት በግብፅ ለሌዊ ዚወለደቜለት ናት። ዮካቀድም ለአምራም አሮንን፣ ሙሮንና እህታ቞ውን ሚርያምን ወለደቜለት።
አሮንም ናዳብን፣ አቢሁን፣ አልዓዛርን እና ኢታምርን ወለደ።
ሆኖም ናዳብና አቢሁ በይሖዋ ፊት ያልተፈቀደ እሳት በማቅሚባ቞ው ሞቱ።
አንድ ወርና ኚዚያ በላይ ሆኗቾው ዚተመዘገቡት ወንዶቜ በአጠቃላይ 23,000 ነበሩ። እነዚህ በእስራኀላውያን መካኚል ርስት ስለማይሰጣ቞ው ኚእስራኀላውያን ጋር አልተመዘገቡም።
እነዚህም ሙሮና ካህኑ አልዓዛር ኚኢያሪኮ ማዶ በዮርዳኖስ አጠገብ በሚገኘው ዚሞዓብ በሹሃማ ሜዳ ላይ እስራኀላውያንን በመዘገቡበት ወቅት ዹመዘገቧቾው ና቞ው።
ሆኖም ኚእነዚህ መካኚል ሙሮና ካህኑ አሮን እስራኀላውያንን በሲና ምድሚ በዳ በቆጠሩበት ወቅት ተመዝግቩ ዹነበሹ አንድም ሰው አልነበሚም።
ምክንያቱም ይሖዋ እነሱን በተመለኹተ “በእርግጥ በምድሚ በዳው ላይ ያልቃሉ” በማለት ተናግሮ ነበር። በመሆኑም ኹዹፎኒ ልጅ ኚካሌብና ኹነዌ ልጅ ኚኢያሱ በስተቀር አንድም ዹተሹፈ ሰው አልነበሚም።
ይሖዋም እስራኀላውያን ኚግብፅ ምድር በወጡ በሁለተኛው ዓመት ሁለተኛ ወር፣ ዚመጀመሪያ ቀን ላይ በሲና ምድሚ በዳ በመገናኛ ድንኳኑ ውስጥ ሙሮን አነጋገሚው። እንዲህም አለው፩
“ዚእስራኀልን ማኅበሚሰብ በሙሉ በዚቀተሰባ቞ው፣ በዚአባቶቻ቞ው ቀትና በስም በተዘሚዘሩት ወንዶቜ ሁሉ ቁጥር መሠሚት በግለሰብ ደሹጃ ቁጠር።
አንተና አሮን ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዹሆናቾውን በእስራኀል ውስጥ ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉትን ሁሉ በዚምድባ቞ው መዝግቡ።
“ኚዚነገዱ አንድ ሰው ውሰድፀ እያንዳንዳ቞ውም ለዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪ ይሆናሉ።
ኹአንተ ጋር ዚሚቆሙትም ወንዶቜ ስም ዹሚኹተለው ነው፩ ኚሮቀል ነገድ ዚሞደኡር ልጅ ኀሊጹር፣
ኚስምዖን ነገድ ዚጹሪሻዳይ ልጅ ሞሉሚኀል፣
ኚይሁዳ ነገድ ዚአሚናዳብ ልጅ ነአሶን፣
ኚይሳኮር ነገድ ዚጹአር ልጅ ናትናኀል፣
ኚዛብሎን ነገድ ዹሄሎን ልጅ ኀልያብ፣
ኚዮሎፍ ወንዶቜ ልጆቜ ይኾውም ኚኀፍሬም ነገድ ዚአሚሁድ ልጅ ኀሊሻማ፣ ኹምናሮ ነገድ ደግሞ ዚፐዳጹር ልጅ ገማልያል፣
ኚቢንያም ነገድ ዚጊድኊኒ ልጅ አቢዳን፣
ኚዳን ነገድ ዚአሚሻዳይ ልጅ አሂዔዜር፣
ኹአሮር ነገድ ዚኊክራን ልጅ ፓጊኀል፣
ኚጋድ ነገድ ዚደኡዔል ልጅ ኀሊያሳፍ
እንዲሁም ኚንፍታሌም ነገድ ዚኀናን ልጅ አሂራ።
እነዚህ ኚማኅበሚሰቡ ዚተመሚጡ ና቞ው። እነሱም ዚአባቶቻ቞ው ነገዶቜ መሪዎቜ ማለትም ዚእስራኀል ዚሺህ አለቆቜ ና቞ው።”
በመሆኑም ሙሮና አሮን በስም ዚተጠቀሱትን እነዚህን ወንዶቜ ወሰዱ።
እነሱም ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በግለሰብ ደሹጃ እንዲመዘገቡ ለማድሚግ በሁለተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ላይ መላውን ማኅበሚሰብ ሰበሰቡፀ
ይህን ያደሚጉት ልክ ይሖዋ ሙሮን ባዘዘው መሠሚት ነው። እሱም በሲና ምድሚ በዳ መዘገባ቞ው።
ዚእስራኀል ዚበኩር ልጅ ዝርያዎቜ ዚሆኑት ዚሮቀል ልጆቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ በግለሰብ ደሹጃ ተቆጠሩፀ
ኚሮቀል ነገድ ዚተመዘገቡት 46,500 ነበሩ።
ዚስምዖን ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ በግለሰብ ደሹጃ ተቆጠሩፀ
ኚስምዖን ነገድ ዚተመዘገቡት 59,300 ነበሩ።
ዚጋድ ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚጋድ ነገድ ዚተመዘገቡት 45,650 ነበሩ።
ዚይሁዳ ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚይሁዳ ነገድ ዚተመዘገቡት 74,600 ነበሩ።
ዚይሳኮር ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚይሳኮር ነገድ ዚተመዘገቡት 54,400 ነበሩ።
ዚዛብሎን ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚዛብሎን ነገድ ዚተመዘገቡት 57,400 ነበሩ።
በኀፍሬም በኩል ያሉት ዚዮሎፍ ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚኀፍሬም ነገድ ዚተመዘገቡት 40,500 ነበሩ።
ዹምናሮ ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኹምናሮ ነገድ ዚተመዘገቡት 32,200 ነበሩ።
ዚቢንያም ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚቢንያም ነገድ ዚተመዘገቡት 35,400 ነበሩ።
ዚዳን ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚዳን ነገድ ዚተመዘገቡት 62,700 ነበሩ።
ዹአሮር ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኹአሮር ነገድ ዚተመዘገቡት 41,500 ነበሩ።
ዚንፍታሌም ዝርያዎቜ በዚስማ቞ው፣ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት በዝርዝር ተመዘገቡ። ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት ወንዶቜ ሁሉ ተቆጠሩፀ
ኚንፍታሌም ነገድ ዚተመዘገቡት 53,400 ነበሩ።
ሙሮ ኚአሮንና እያንዳንዳ቞ው ዚአባቶቻ቞ውን ቀት ኚሚወክሉት ኹ12 ዚእስራኀል አለቆቜ ጋር በመሆን ዚመዘገባ቞ው እነዚህ ና቞ው።
በእስራኀል ውስጥ ወደ ሠራዊቱ መቀላቀል ዚሚቜሉት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዚሆኑት እስራኀላውያን ሁሉ በዚአባቶቻ቞ው ቀት ተመዘገቡፀ
ዚተመዘገቡትም ሰዎቜ ጠቅላላ ቁጥር 603,550 ነበር።
ይሁን እንጂ ሌዋውያኑ ሌሎቹ እንደተመዘገቡት በዚአባቶቻ቞ው ነገድ መሠሚት አልተመዘገቡም።
ስለዚህ ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“ዹሌዊን ነገድ ብቻ አትመዝግብፀ ቁጥራ቞ውም በሌሎቹ እስራኀላውያን ቁጥር ውስጥ እንዲካተት አታድርግ።
ሌዋውያኑን በምሥክሩ ዚማደሪያ ድንኳን፣ በዕቃዎቹ ሁሉና ኚዚያ ጋር ተያያዥነት ባላ቞ው ነገሮቜ ሁሉ ላይ ሹማ቞ው። እነሱም ዚማደሪያ ድንኳኑንና ዕቃዎቹን በሙሉ ይሞኚማሉፀ በዚያም ያገለግላሉፀ በማደሪያ ድንኳኑም ዙሪያ ይሰፍራሉ።
ዚማደሪያ ድንኳኑ ኚቊታ ወደ ቊታ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ ሁሉ ሌዋውያኑ ይንቀሉትፀ ዚማደሪያ ድንኳኑ በሚተኚልበት ጊዜም ሌዋውያኑ ይትኚሉት። ያልተፈቀደለት ማንኛውም ሰው ወደዚያ ቢቀርብ ይገደል።
“እያንዳንዱ እስራኀላዊ በዚተመደበበት ሰፈር ድንኳኑን ይትኚልፀ እያንዳንዱም ሰው ሊስት ነገዶቜን ባቀፈው ቡድኑ ውስጥ በዚምድቡ ይስፈር።
በእስራኀል ማኅበሚሰብ ላይ ቁጣ እንዳይወርድ ሌዋውያኑ በምሥክሩ ዚማደሪያ ድንኳን ዙሪያ ይስፈሩፀ ሌዋውያኑም ዚምሥክሩን ዚማደሪያ ድንኳን ዚመንኚባኚብ ኃላፊነት ተጥሎባ቞ዋል።”
እስራኀላውያንም ይሖዋ ሙሮን ያዘዘውን ሁሉ አደሚጉ። ልክ እንደዚያው አደሚጉ።
ኚዮሎፍ ልጆቜ ቀተሰቊቜ ዹምናሮ ልጅ፣ ዚማኪር ልጅ፣ ዚጊልያድ ተወላጆቜ ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ ወደ ሙሮና ዚእስራኀላውያን ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ ወደሆኑት አለቆቜ ቀርበው ተናገሩፀ
እንዲህም አሉ፩ “ይሖዋ ጌታዬን ምድሪቱን ለእስራኀላውያን ርስት አድርጎ በዕጣ እንዲያኚፋፍል አዞት ነበርፀ ደግሞም ዚወንድማቜንን ዚሰለጰአድን ርስት ለሎቶቜ ልጆቹ እንዲሰጥ ይሖዋ ጌታዬን አዞት ነበር።
እነዚህ ሎቶቜ ኚሌሎቜ ዚእስራኀል ነገዶቜ ባሎቜን ቢያገቡ ዚእነሱ ውርስ ኚአባቶቻቜን ውርስ ላይ ተወስዶ በሚያገቡት ሰው ነገድ ውርስ ላይ ይጚመራልፀ በመሆኑም በዕጣ ኹተሰጠን ውርስ ላይ ይቀነሳል።
ዚእስራኀል ሕዝብ ዚኢዮቀልዩ ዓመት በሚደርስበት ጊዜ ዚሎቶቹ ውርስ በሚያገቡት ሰው ነገድ ውርስ ላይ ለዘለቄታው ይጚመራልፀ በመሆኑም ዚእነሱ ውርስ ኚአባቶቻቜን ነገድ ውርስ ላይ ይቀነሳል።”
ኚዚያም ሙሮ ይሖዋ በሰጠው ትእዛዝ መሠሚት እስራኀላውያንን እንዲህ ሲል አዘዛቾው፩ “ዚዮሎፍ ልጆቜ ነገድ ዹተናገሹው ነገር ትክክል ነው።
ይሖዋ ዚሰለጰአድን ሎቶቜ ልጆቜ በተመለኹተ እንዲህ ሲል አዟል፩ ‘ዚፈለጉትን ሰው ማግባት ይቜላሉ። ሆኖም ኚአባታ቞ው ነገድ ቀተሰብ ዹሆነን ሰው ማግባት ይኖርባ቞ዋል።
ዚትኛውም ዚእስራኀላውያን ውርስ ኚአንዱ ነገድ ወደ ሌላው ነገድ መተላለፍ ዚለበትምፀ ምክንያቱም እስራኀላውያን እያንዳንዳ቞ው ዚአባቶቻ቞ውን ነገድ ውርስ አጜንተው መያዝ አለባ቞ው።
እስራኀላውያን ዚቀደሙትን አባቶቻ቞ውን ውርስ ጠብቀው ማቆዚት እንዲቜሉ በእስራኀል ነገዶቜ መካኚል ውርስ ያላት ዚትኛዋም ልጅ ዚአባቷ ነገድ ተወላጅ ዹሆነ ሰው ማግባት ይኖርባታል።
ዚትኛውም ውርስ ኚአንዱ ነገድ ወደ ሌላው ነገድ መተላለፍ ዚለበትምፀ ምክንያቱም ዚእስራኀል ነገዶቜ እያንዳንዳ቞ው ዚዚራሳ቞ውን ውርስ አጜንተው መያዝ አለባ቞ው።’”