category
large_stringclasses
7 values
headline
large_stringlengths
10
171
text
large_stringlengths
1
26.4k
url
large_stringlengths
13
180
lang
large_stringclasses
16 values
business
የናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ተቆልፎባቸው እንዲሰሩ የተገደዱ 300 ሰራተኞችን ነፃ ማውጣቱን ገለፀ
የናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ውስጥ ተቆልፎባቸው የነበሩ 300 ሰራተኞችን ነፃ ማውጣቱን ገልጿል። ሰራተኞቹ ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ ከፋብሪካው እንዳይወጡ እግድ ተጥሎባቸውና ተቆልፎባቸው ይሰሩ ነበር ተብሏል። በሰሜናዊ ናይጄሪያ ግዛት በምትገኘው ካኖ በሚገኝ ፋብሪካ ውስጥ የሚሰሩት ሰራተኞች የኮሮናቫይረስ አስገዳጅ የቤት መቀመጥ አዋጅን ተከትሎ ወደቤታቸው እንዳይሄዱና በየወሩም ከሚያገኙት 2 ሺህ 600 ብር ደመወዝ በተጨማሪ 500 ብር እንደሚጨመርላቸው የፋብሪካው አስተዳዳሪዎች ቃል ገብተውላቸው ነበር። ወ...
https://www.bbc.com/amharic/news-53127360
amh
business
ኢትዮጵያ፡ በደረሰው የጎርፍ አደጋ 130 ሺህ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል
በኢትዮጵያ እስከ ነሐሴ ወር አጋማሽ ድረስ የጣለው ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የተነሳ 170 ሺህ ያህል ነዋሪዎች ጉዳት ሲደርስባቸው 130 ሺህ ሰዎች ደግሞ ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክትል ኮሚሽነር ለቢቢሲ ገለፁ። ኮሚሽነሩ አቶ ዳመነ ዳሮታ ከዚህ በፊት የነበረውን ልምድ ከግንዛቤ በማስገባት በዚህ ዓመት ክረምት ወቅት በጎርፍ ምክንያት ወደ 2 ሚሊየን ያህል ሰዎች ሊጎዱ እንዲሁም 434 ሺህ ያህሉ ደግሞ ሊፈናቀሉ ይችላሉ ተብሎ ግምት መያዙን ተናግረዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ ...
https://www.bbc.com/amharic/news-53852369
amh
business
አየር መንገዶች ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን እንዳያበሩ ዳግም ታገዱ
ከሁለት የመከስከስ አደጋ በኋላ ዳግም እንዲበር ፍቃድ አግኝቶ የነበረው የቦይንድ 737 ማክስ አውሮፕላን ዳግም አጣብቂኝ ውስጥ ገባ። የኢትዮጵያ እና የኢንዶኔዢያው ላየን አየር መንገድ ንብረት የሆኑት የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች የመከስከስ አደጋ ካጋጠማቸው በኋላ በመላው ዓለም አውሮፕላኑ እንዳይበር እግድ ተጥሎበት እንደነበረ ይታወሳል። ከስድስት ወራት በፊት ግን የአሜሪካ የበረራ ደህንነት ተቋማት አውሮፕላኑ ዳግም እንዲበር ፈቃድ ሰጥተው ነበር። ይሁን እንጂ አውሮፕላኑ ሌላ የኤሌክትሪክ ችግር እንዳ...
https://www.bbc.com/amharic/news-57075420
amh
business
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ500 ቢሊዮን ብር በላይ ዓመታዊ በጀት አዘጋጀች
የኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀትን ለመጀመሪያ ጊዜ ከ500 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያደርግ ረቂቅ በጀት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸደቀ። የመጪው ዓመት የኢትዮጵያ መንግሥት በጀት ከዘንድሮው በ85 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያዘጋጀው ረቂቅ በጀት አመልክቷል። ምክር ቤቱ የቀጣዩ ዓመት የፌደራል መንግሥቱ በጀት 561 ቢሊዮን ብር በላይ በላይ እንዲሆን የወሰነ ሲሆን በ2013 ካለው የ476 ቢሊዮን ብር በጀት በ18 በመቶ ከፍ ብሏል። ይህም የየ85 ቢሊዮን ብር ጭማሪ ታይቶበታል። የሚኒስትሮች ምክር ...
https://www.bbc.com/amharic/news-57372163
amh
business
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ስዊፍት ምንድን ነው?
ስዊፍት የአገራት ድንበሮች ሳይገድቡት በተመቸ እና በፈጣን ሁኔታ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት ዓለም አቀፍ የገንዘብ ማስተላላፊያ ሥርዓት ነው። ስዊፍት [Swift] ሶሳይቲ ፎር ኢነትረባንክ ፋይናንሻል ቴሌኮምዩኒኬሽን [Society for Worldwide Interbank Financial Telecommunication] የሚለው ስያሜ አህጽሮተ ቃል ነው። በሥርዓቱ የተካተቱ በዓለም ዙሪያ ያሉ ባንኮች ያለምንም ተጨማሪ ውጣ ውረድ ገንዘብ ይላላኩበታል። ስዊፍት እንደ አውሮፓውያኑ በ1973 የተጀመረ ሲሆን መሰረቱ ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60630455
amh
business
የሳምሰንግ ትርፍ ከ50 በመቶ በላይ አሽቆለቆለ
የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች አምራቹ ሳምሰንግ በሁለተኛው ሩብ ዓመት የምርቱ ትርፋማነት እንዳሽቆለቆለበትና ይህም ወደፊት ተግዳሮቶች ሊያጋጥሙት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ እንደሆነ አስታወቀ። • የአዲሱ ሳምሰንግ ጋላክሲ S9 በካሜራ ብቃት ላይ አተኩሯል •ሳምሰንግ እንደ መጽሐፍ የሚገለጥ ስልክ አመረተ የዓለማችን ትልቁ ዘመናዊ ስልኮችንና የኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን አምራቹ ኩባንያ- ሳምሰንግ እንዳለው ትርፋማነቱ ከዚህ ዓመት ቀድሞ ባለው የበጀት ዓመት በ56 በመቶ ቀንሷል። ለዚህም በአሜሪካና በቻይና መካከል እየተካሄደ...
https://www.bbc.com/amharic/news-49174785
amh
business
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስካሁን አንድ ቢሊየን ዶላር ያህል ገቢ አጥቷል
ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ በኮሮናቫይረስ ምክንያት በአየር ትራንስፖርት ዘርፉ ላይ በተፈጠረው መስተጓጎል ሳቢያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንዳጣ ተገለጸ። የኮሮናቫይረስ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ በአየር መንገዶች ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ቀውስ ማምጣቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ይናገራሉ። ከ90 በመቶ በላይ የመንገደኛ በረራዎች መቆማቸውን ለቢቢሲ የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፣ ያንን ተከትሎ ደግሞ ከየካቲት እስከ ሰኔ መጨረሻ ድርጅቱ ...
https://www.bbc.com/amharic/53075791
amh
business
ዚምባብዌ የዋጋ ንረትን ለመግታት የወርቅ ሳንቲሞችን አስተዋወቀች
የዚምባብዌ ማዕከላዊ ባንክ ከአገሪቱ ኢኮኖሚ ማሽቆልቆል ጋር ተደምሮ እየናረ የመጣውን የዋጋ ንረት ለመግታት የወርቅ ሳንቲሞችን በመገበያያነት ለመጠቀም ይፋ አድርጓል። የአገሪቱ ዓመታዊው የዋጋ ግሽበት ከ190 በመቶ በላይ ማደጉን ተከትሎ የማዕከላዊ ባንቡ በያዝነው ወር የወለድ ተመኑን ከእጥፍ በላይ በማሳደግ 200 በመቶ አድርሷል። እያንዳንዱ ሳንቲም በዓለም አቀፍ ገበያ አንድ አውንስ ወርቅ የሚኖረውን ዋጋ ብሎም 5 በመቶ ሳንቲሙን ለማምረት የወጣውን ተጨምሮ ያወጣል። ባሳለፍነው አርብ አንድ አውንስ ወርቅ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cx0qqnwwevxo
amh
business
ቢትኮይንን ለሁሉም አገልግሎትና ግብይት የምትጠቀመው አገር
የቢትኮይን ዋጋ ከሌላው ጊዜ በተለየ በእዚህ ሳምንት በጣም ቀንሷል። የኤል ሳቫዶር መንግሥት ግን ቢትኮይንን ሕጋዊ መገበያያ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል። ይህንን ለማበረታታትም በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው። ይህ ውሳኔ ከተወሰነ ከ9 ወር ወዲህ መንግሥት 200 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለቢትኮይን ፈሰስ አድርጓል። አሁን ደግሞ የውሻ ባለቤቶች በቢትኮይን የሚከፍሉ ከሆነ በጣም በርካሽ እንዲታከሙ አንድ ሆስፒታል አመቻችቷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgr9yx339elo
amh
business
የአርሶ አደሮችን ሕይወት ለማቅለል ዘመናዊ ጎተራ የሠራችው ወጣት
ደራርቱ ደረጀ በጅማ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ውስጥ የባዮ ሜዲካል ትምህርት ክፍል መምህርት ናት። እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪዋን ባዮ ሜዲካል ኢሜጂንግ በሚባል የትምህርት ዘርፍ እየተማረች ሲሆን፣ ከትምህርቷ ጎን ለጎን ፈጠራዎች ላይ ተሰማርታለች። ከሥራዎቿ መካከል አንዱ የሆነው ደግሞ አርሶ አደሮችን መሠረት በማድረግ የሠራችው ዘመናዊ ጎተራ ነው። "ገበሬዎቻችን የሚጠቀሙበት ጎተራ ከጭቃ አልያም ከአፈር ስለሚሠራ የታፈነ ነው። በዚህም ምክንያት እህሉ በነቀዝ እንዲበላ ይሆናል" ትላለች ደራርቱ። ደራርቱ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60906496
amh
business
ቤይሩት ውስጥ በመሳሪያ አስገድዶ ገንዘቡን ከባንክ የወሰደው ጀግና ተባለ
መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው የሊባኖስ ዜጋ በሕዝቡ ጀግና ተብሎ ተወደሰ። ሊባኖስ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ባንኮች ደንበኞቻቸው ወጪ በሚያደርጉት ገንዘብ ላይ ገደብ ጥላለች። ይህ ግለሰብ ግን መሳሪያ ታጥቆና ባንክ ውስጥ ነዳጅ አርከፍክፎ ለሆስፒታል ክፍያ ለመፈጸም የሚያስፈልገው ገንዘቡ እንዲሰጠው በኃይል መጠየቁን ኤኤፍፒ ዘግቧል። በግለሰቡ እና በባንኩ መካከል ለስድስት ሰዓታት ከቆየ ፍጥጫ በኋላ ግለሰቡ የጠየቀውን ገንዘብ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c4n30811d2no
amh
business
ኬንያ ገንዘብ ከመቀየሯ ጋር ተያይዞ ከሰባት ቢሊዮን ሺልንግ በላይ ጥቅም አልባ ሆነ
የኬንያ ማዕከላዊ ባንክ እንዳሳወቀው ኬንያ የመገበያያ ገንዘብ ከመቀየሯ ጋር ተያይዞ ከ95% በላይ የሚሆነው የአንድ ሺ ሺልንግ ተመልሶ በአዲሱ ተተክቷል። በዚህ መካከል ግን መሃል ላይ ተንሳፎ የቀረ ገንዘብ እንዳለም ተገልጿል። "ይህ ማለት 7.3 ቢሊዮን ሺልንግ ጥቅም አልባ ሆኗል፤ እንደ ወረቀት ነው የሚቆጠረው" በማለት የባንኩ አስተዳዳሪ ፓትሪክ እንጆሮጌ ለጋዜጠኞች አስረድተዋል። •የኢትዮጵያ ሙዚቃ- ከመስከረም እስከ መስከረም •ከአንደኛ ክፍል ዲግሪ እስኪጭኑ ከልጃቸው ጋር የተማሩት አባት ባንኩ እንዳሳ...
https://www.bbc.com/amharic/49916629
amh
business
"ለ15 ዓመታት ኮንዶሚኒየም እየጠበቅኩ ሁለት ልጆች ወልጃለሁ" የአዲስ አበባ ነዋሪ
"ለ15 ዓመታት ኮንዶሚኒየም እየጠበቅኩ ሁለት ልጆች ወልጃለሁ" ይህ የተሰማው ስሜ አይጠቀስ ካሉ አንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ ነው። ቤት የመኖር ተስፋቸውን ሰንቀው የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ይደርሰኛል ብለው የተመዘገቡት በ1997 ዓ.ም ነበር። የጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲሰጣቸው በማህበር ተደራጅተው ከተመዘገቡት የመጀመሪያው ዙር ተመዝጋቢም መካከል ናቸው። ለአስራ አምስት ዓመታትም ያህል ቤት ይደርሰኛል ብለው ጠብቀዋል። በእርሳቸው ማህበር ውስጥ ከሚገኙት ከሃያ አባላቱ በላይ በሙሉ የቤት ባለቤት ቢሆኑም እርሳቸው...
https://www.bbc.com/amharic/53996764
amh
business
ፈረንሳዊው ቢሊየነር በፓሪስ ተደብድበው ተዘረፉ
የፈረንሳዩ ቢሊየነር በርናንድ ታፒ በፓሪስ ኩምላቪል መኖርያ ቤታቸው ውስጥ ሳሉ ነው ዘራፊዎች ገብተው የደበደቧቸው፡፡ ባለቤታቸውም ክፉኛ ተጎድተዋል፡፡ ቢሊየነሩ በርናንድ ታፒ የዝነኛው የአዲዳስ የስፖርት ትጥቅ አምራች የቀድሞ ባለቤት ናቸው፡፡ የቢሊየነሩን ቤት የደፈሩት ዘራፊዎች ቁጥርና ማንነት እስከአሁን አልታወቀም፡፡ ዘራፊዎቹ ቢሊየነሩን በርናንድ ታፒ እና ባለቤታቸው ሌሊት ላይ ከእንቅልፋቸው ቀስቅሰው በኤሌክትሪክ ገመድ ካሰሯቸው በኋላ ነበር ጠቀም ያለ ገንዘብ ለመዝረፍ የሞከሩት፡፡ ሆኖም በቢሊየነሩ ቤ...
https://www.bbc.com/amharic/news-56636712
amh
business
የሲዳማ ቡና በኪሎ ለምን እስከ አርባ ሁለት ሺህ ብር ተሸጠ?
ያለፉት ሦስት ዓመታት ለሲዳማ ቡና ‘ቡናማ’ ዓመታት ናቸው። ወርቃማ እንዳይባሉ ቡና ከወርቅም በላይ ነኝ ያለባቸው ዓመታት ናቸው። ከዚህ ጀርባ ደግሞ ሦስት ስሞች ቀድመው ወደ አዕምሮ ይመጣሉ። ንጉሤ ገመዳ፣ ታምሩ ታደሠ እና ለገሠ በጦሳ ናቸው። ሦስቱም የሲዳማ ቡናን ይዘው ለውድድር ቀርበው አላፈሩም። ይህ የቡና ውድድር ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ይባላል። ውድድሩ ቡናን በጥራት ይለያል። ቀጥሎ በዓለም አቀፍ ጨረታ ለገበያ ያቀርባል። ንጉሴ አንድ ኪሎ ቡናውን በ407 ዶላር ሸጠዋል። የታምሩ ቡና ደግሞ 330 ዶላር...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c28wxj81xveo
amh
business
"በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ፈርተው ዛሬ መደብር አልከፈቱም"
የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የጃኮብ ዙማን እስር ተከትሎ በአገሪቱ ሰላማዊ ሰልፎችና ነውጥ መቀስቀሱን ተከትሎ በጆሀንስበርግ የሚሠሩ ኢትዮጵያውያን ዛሬ መደብራቸውን ዘግተው እንደዋሉ በከተማዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊን ለቢቢሲ ተናገሩ። በንግድ ሥራ የተሰማራው ዳዊት ተወልደመድኅን፤ በጆሀንስበርግ በተለይም ጂፒ ጎዳና እና ብሪ ጎዳና በሚባሉት አካባቢዎች በርካታ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ጥቃት እንዳይደርስባቸው ፈርተው ዛሬ ሐምሌ 5/2013 ዓ.ም. መደብራቸውን ዘግተው ለመዋል መገደዳቸውን ተናግሯል። ትላንት ...
https://www.bbc.com/amharic/news-57808849
amh
business
ኮሮናቫይረስ፡ አፍሪካ በወረርሽኙ ሳቢያ ከተጎዳው ምጣኔ ሐብት ለማገገም 1.2 ትሪሊየን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ
አፍሪካ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ካጋጣት የኢኮኖሚ ውድቀት ለማገገም እንዲሁም የጤና ወጪ 1.2 ትሪሊየን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ዓለም አቀፉ ገንዘብ ተቋም [አይኤምኤፍ] አስታወቀ። ገንዘቡ ያስፈልጋታል የተባለው ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት መሆኑ ተገልጿል። የተቋሙ ዳሬክተር ክርስታሊና ጆርጂቫ እንዳሉት ዓለም አፍሪካ ከገባችበት ቀውስ እንድታገግም ለመደገፍ ዓለም ብዙ መስራት አለበት ብለዋል። በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ እንዲሁም የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከሌሎች አህጉራት ያነሰ ነው፤ ነገር ግን የዓለም ባንክ በወ...
https://www.bbc.com/amharic/news-54498317
amh
business
የወቅቱ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ተግዳሮቶች
የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ምርት እድገት (ጂዲፒ) ባለፉት 10 ዓመታት በየዓመቱ በአማካኝ 9.4 በመቶ እያደገ መሆኑን ይናገራል። ኢትዮጵያ ከጥቅምት 24/2013 ጀምሮ በትግራይ ክልል የቀሰቀሰው ጦርነት፣ በቅርቡ የተከሰተው ከፍተኛ ሆነ የምንዛሬ እጥረት እንዲሁም ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት ኢኮኖሚውን እየተፈታተነው ይገኛል። ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ አንድ ዶላር በጥቁር ገበያው ከ64 እስከ 68 ብር ድረስ በመመንዘር ላይ እንደሚገኝ እና በተለያዩ ሁኔታዎች ይህ ዋጋ እስከ 72 ብር ድረስ ከፍ እ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58185460
amh
business
እሷ ማናት? #4፡ ከሒሳብ ጋር በአጋጣሚ ነው የተዋደድነው
በሒሳብ ትምህርት የዶክትሬት ዲግሪዋን (ፒኤች ዲ) ለማግኘት እየሰራች ነው። ሰዎች እምብዛም ገፍተው በማይሄዱበት የትምህርት ዓይነት እንዴት ውጤታማ ልትሆን እንደቻለች አጫውታናለች። ስሜ ኤቢሴ አዱኛ ይባላል። ተወልጄ ያደኩት በነቀምት ከተማ ነው። የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርቴን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪ ደግሞ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተምርያለሁ። በአሁን ሰዓት ደግሞ የሦስትኛ ዲግሪ ትምህርቴን በዴንማርክና በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች እየተከታተልኩ ነው። • የኮምፒዩተር ትምህርት ለኬኒያ ሴት እስረኞች ሁለተኛ ...
https://www.bbc.com/amharic/news-50218736
amh
business
ሲም ካርድ ያለው ሁሉ ገንዘብ መበደር የሚችልበትን ዕድል የፈጠረው ቴሌብር
ከአስራ አራት ወራት በፊት ወደ አገልግሎት የገባው ቴሌብር የተሰኘው የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለፈው ሳምንት አርብ ከቁጠባ እና ብድር ጋር የተያያዙ አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት ጀምሯል። ከቢቢሲ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አዳዲሶቹ አገልግሎቶች በፋይናንስ ሥርዓት ያልተሸፈነውን 60 በመቶ የሚሆን የኅብተረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል። የነዳጅ ድጎማ እና የግብር ክፍያን ጨምሮ ባለፉት 14 ወራት ገንዘብ ለመላላክ፣ የግብይትና የ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy0xj34y9l7o
amh
business
ቻይና ዝናብ ለማዝነብና የተፈጥሮ ሂደትን ለመቆጣጠር የምታደርገው ጥረት
እንደ ቻይናዋ ቤይጂንግ የአየር ብክለት የሚፈትነው ከተማ የለም። የቤይጂንግ ሰማይ በመጠኑም ቢሆን ጠርቶ ፀሐይ የምትታየው በከተማዋ የሚካሄድ ዓለም አቀፍ ውይይት ሲኖር ነው። ይህ የሚሆነው በተፈጥሯዊ ሂደት ሳይሆን መንግሥት በቀየሰው ስልት አማካይነት ነው። የቻይና መንግሥት የአገሪቱን የአየር ሁኔታ ለመለዋወጥ ሰው ሠራሽ መንገድ መጠቀም ጀምሯል። ይህ ሰው ሠራሽ ሂደት በጥቂት የቻይና ከተሞች ብቻ ይተገበር ነበር። ከጥቅምት ወዲህ ግን አገር አቀፍ እንደሚሆን ተነግሯል። ሂደቱ በሰው ሠራሽ መንገድ ዝናብ እን...
https://www.bbc.com/amharic/news-56099470
amh
business
ፓኪስታን ፡ በካርቱን ስዕል ምክንያት የፈረንሣይ ምርቶችን መጠቀም ልታቆም ነው
አንድ የፓኪስታን እስላማዊ ቡድን የጠራውን የፀረ-ፈረንሳይ ተቃውሞን የፓኪስታን መንግሥት የፈረንሳይ ምርቶችን ላለመጠቀም በመወሰኑ ማቋረጡን አሳወቀ። ሰልፎቹ የተጠሩት ፈረንሳይ የነቢዩ ሙሐመድን ካርቱን የማሳየት መብትን በመደገፏ ነበር። አንድ መምህር በክፍል ውስጥ በነበረ ውይይት ወቅት የነቢዩ መሐመድን ካርቱን ካሳዩ በኋላ መገደላቸውን ተከትሎ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን አገራቸው በሐይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አትገባም ሲሉ በጥብቅ ተከላክለዋል። ይህም በሙስሊሙ ዓለም ቁጣን ቀስቅሷል። የአክራሪው ተህሪክ ኢ-...
https://www.bbc.com/amharic/news-54970898
amh
business
እየበረታ በመሄድ ላይ ያለው የዋጋ ንረት አዙሪት
ባለፉት ጥቂት ወራት የሸቀጦች የዋጋ ንረት እና አጠቃላይ የኑሮ ዋጋ መወደድ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ የብዙሃን መገናኛዎች ተደጋግመው የሚወሱ ጉዳዮች ሆነዋል። የመንግሥት ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶችም የችግሩን አሳሳቢነት ከመቀበል በዘለለ እየተወሰዱ ናቸው የሚሏቸውን እርምጃዎች ሲናገሩ ተስተውለዋል። በወርሃ ግንቦት 2011 ዓ.ም መገባደጃ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ኢንጂነር እንዳወቅ አብጤ በመዲናዋ በግንባታ ዕቃዎች...
https://www.bbc.com/amharic/news-49922350
amh
business
የአንድ ቢትኮይን ዋጋ 2.4 ሚሊዮን ብር ገባ
የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ60 ሺህ ዶላር ወይም 2.4 ሚሊዮን ብር በላይ በመግባት ክብረ ወሰን ሰብሯል። ቢትኮይን መመንደግ የጀመረው በተለይ ደግሞ ከባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት መገባደጃ አንስቶ ነው። ይህንን የማይጨበጥ የማይዳሰስ መገበያያ ገንዘብ በርካታ ግዙፍ ድርጅቶች እንቀበለዋለን ማለታቸው ለዋጋው መናር ምክንያት ሆኗል ተብሏል። በዘርፉ ጥርስ የነቀሉ ግን የቦትኮይን ዋጋ እንዲህ ያሻቀበው የአሜሪካ መንግሥት በኮሮናቫይረስ ኪሳቸው ለተጎዳ ዜጎች የሰጠውን ድጎማ ተከትሎ ነው ይላሉ። የቢትኮይ...
https://www.bbc.com/amharic/news-56391321
amh
business
ከኮሮናቫይረስ በኋላ ኢኮኖሚያቸው በቶሎ ሊያገግም የሚችል አምስት አገራት
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ አገራት ከበሽታ ጋር በሚያደርጉት ትግል በዓለም ምጣኔ ሃብት ላይ አለመረጋጋትን ፈጥሯል። ከዚህ አንጻር ከወረርሽኙ በኋላ የትኞቹ አገራት በተሻለ ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው እንደሚመለሱ ባለሙያዎች ለመገምገም ሞክረዋል። ይህንን በተሻለ ለመረዳት የኢንሹራንስ ኩባንያ የሆነው ኤፍ ኤም ግሎባል የ2019 ዓለም አገራት የምጣኔ ሃብት ፈተናን የመቋቋም አቅም አመላካች ደረጃን ተመለከትን። በዚህም አገራት ለቫይረሱ የሰጡትን የመጀመሪያ ምላሽ ከግምት በማስገባት ቀውሱን በተረጋጋ መንገድ የሚወጡበትን ሁ...
https://www.bbc.com/amharic/news-52217125
amh
business
ላይቤሪያ 4 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ አሮጌ የገንዘብ ኖቶችን አቃጠለች
የላይቤሪያ ማዕከላዊ ባንክ ያረጁ እና የተበላሹ የገንዘብ ኖቶችን በአዲስ ለመተካት በሚል አራት ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ አሮጌ የገንዘብ ኖቶችን አቃጥሏል። በአገሬውም የመገበያያ ገንዘብም የተቃጠለው 600 ሚሊዮን የላይቤሪያ ዶላር ነው። የገንዘብ ኖቶቹ እንዲወገዱ የተደረጉትም መንግሥት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ አዳዲስ ኖቶችን ቢያትምም አሮጌዎቹ በስርጭት ላይ ይገኛሉ የሚለውን ስጋት ተከትሎ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በአውሮፓውያኑ 2018 ከፍተኛ መጠን ያለው የመንግሥት ገንዘብ ጠፍቷል የተባለ ሲሆን እንዲሁም ከ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60229480
amh
business
ምጣኔ ሐብት ፡ ከብር ለውጡ በኋላ የወርቅ ዋጋ ለምን ጨመረ?
ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ መደብሮች የወርቅ ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን ነጋዴዎችና ገዢዎች ለቢቢሲ ገለጹ። ቢቢሲ በመሐል አዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ በሚገኙ የወርቅ መሸጫ መደብሮች ተዘዋውሮ እንደተረዳው የወርቅ መግዣ እና የመሸጫ ዋጋዎች ላይ ጭማሪዎች ታይተዋል። በተለይ ኢትዮጵያ የብር ኖቶቿን መቀየሯን ይፋ ካደረገችበት ከመስከረም ወር መጀመሪያ አንስቶ ጭማሪው በተለይ ከፍ ማለቱን በአዲስ አበባ ከተማ በወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እና ሠራተኞች ለቢቢሲ ተናግረዋል። ቢቢሲ አዲስ አ...
https://www.bbc.com/amharic/news-54333190
amh
business
የነዳጅ ድጎማ መነሳትና ሊያስከትል የሚችለው ጫና
የኢትዮጵያ መንግሥት የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ ጭማሪ ማድረጉን አሳውቋል። በዚህም አስካሁን ከታዩት የዋጋ ጭማሪዎች ሁሉ ከፍተኛው እንደሆነ ተነግሯል። መንግሥት እንደሚለው የነዳጅ ምርቶችን ለመደጎም በወር በአማካይ 10 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ በመግለጽ፣ በአሁኑ ወቅት 146 ቢሊየን 624 ሚሊየን 248 ሺህ 889 ብር የነዳጅ ድጎማ ዕዳ አለበት ተብሏል። ቀደም ሲል መንግሥት በየወሩ በሚያደርገው የነዳጅ ዋጋ ክለሳ ላይ ጭማሪው ከ10 በመቶ የሚበልጥ አልነበረም። አሁን ግን ይህንን የመንግሥት ድጎማው...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cyd3yjlr0rgo
amh
business
ሱዊዝ ቦይ በመዘጋቱ በየቀኑ የ9.6 ቢሊዮን ዶላር ምርት መተላለፍ አልቻለም
የግብጹ ሱዊዝ የባሕር ላይ ማቋረጫ ቦይ በመዘጋቱ በየቀኑ 9.6 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶች መተላለፍ እንዳልቻሉ ተገለጸ። በሱዊዝ መተላለፊያ ላይ አንድ ግዙፍ የጭነት መርከብ ባሕሩን ዘግቶ ከማክሰኞ ዕለት ጀምሮ በመቆሙ ምክንያት እንቅስቃሴ መገታቱ ይታወሳል። ሎይድስ ሊስት የተባለው የመርከብ ጉዞ ድርጅት እንደሚለው፤ በቀን ውስጥ ከምዕራብ አቅጣጫ ይመጡ የነበሩ 5.1 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶች መጓጓዝ አልቻሉም። ከምሥራቅ አቅጣጫ ይመጡ የነበሩና የተስተጓጎሉ ምርቶች ደግሞ 4.5 ቢሊዮን ዶላር የሚያ...
https://www.bbc.com/amharic/56534020
amh
business
ኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍን ለውጭ ባለሐብቶች ክፍት ለማድረግ ወሰነች
የኢትዮጵያ መንግሥት ካቢኔ ለአስርታት ለውጭ ባለሐብቶች ዝግ ሆኖ የቆየውን የባንክ ሥራ ዘርፍ ክፍት ለማድረግ የቀረበለትን ረቂቅ ፖሊሲ አጸደቀ። በአገሪቱ ብሔራዊ ባንክ አማካይነት ተዘጋጅቶ የቀረበው ረቂቅ ለዘመናት ለኢትዮጵያውያን ብቻ ተትቶ የነበረውን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ባንኮችም ክፍት እንዲሆን የሚፈቅድ ነው። ይህም በዘርፉ ታዋቂ የሆኑ ዓለም አቀፍ ባንኮች በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ላይ እንዳይሰማሩ አድርጎ የቆየውን የአገሪቱን የፋይናንስ ፖሊሲ የቀየረው ውሳኔ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ይፋ ሆ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6px7z4zg45o
amh
business
የኬንያው ፕሬዝዳንት በአገራቸው ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች እንዳይሸጡ አገዱ
የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በአገሪቱ ከግንባታዎች ላይ የተነሱ፣ ያገለገሉ እንዲሁም የተጣሉ ብረታ ብረቶች ሽያጭ እንዳይካሄድ አስቸኳይ እገዳ ጣሉ። ይህ የፕሬዝዳንቱ ድንገተኛ እገዳ ይፋ የተደረገው መንግሥት እየጨመረ ነው ያለውን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ የሕዝብ ንብረቶች ላይ የሚፈጸም ዝርፊያና ውድመትን ለመከላከል ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። ይህ የወዳደቁና አሮጌ ብረቶች ሽያጭ እገዳ ተግባራዊ የሚሆነው የኬንያ መንግሥት የእነዚህን ብረታ ብረቶች ምንጭ፣ ንግድና ወደ ውጭ የሚላኩበትን ሁኔታ በ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60082636
amh
business
ቦይንግ 20 በመቶ ሰራተኞቹን ለመቀነስ ማቀዱን አስታወቀ
ቦይንግ በቅርቡ 7 ሺህ የሚሆኑ ሰራተኞቹን እንደሚቀንስ ይፋ አድርጓል። በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተጎዳው የአሜሪካኑ አውሮፕላን አምራች ቦይንግ በከፍተኛ ሁኔታ የሰራተኞቹን ቁጥር ለመቀነስ እንዳሰበ ያሳወቀ ሲሆን በመጪው አውሮፓውያኑ አመት መጨረሻም 20 በመቶ የሚሆኑትን ወደ 30 ሺህ ሰራተኞቹን እንደሚቀንስ አስታውቋል። ከቀውሱ በፊት ኩባንያው የነበሩት የሰራተኞች ቁጥር 160 ሺህ ነበር። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በተጨማሪ ከ337 ማክስ የደህንነት ስጋቶች ጋር ተደራርቦ ኩባንያውን ለኪሳራ ዳርገውታል። እስከ...
https://www.bbc.com/amharic/news-54748697
amh
business
በቀጣዩ ስምንት ዓመት ቻይና በምጣኔ ሃብት አሜሪካን ትበልጣለች ተባለ
ቻይና በፈረንጆቹ 2028 በዓለም ትልቁ የምጣኔ ሃብት ባለቤት በመሆን አሜሪካን ልትቀድማት እንደምትችል ተገምቷል። ከዚህ ቀደም ቻይና አሜሪካን በ2033 ነበር ትቀድማታለች ተብሎ የተገመተው። መቀመጫውን ዩናይትድ ኪንግደም ያደረገው የምጣኔ ሃብት እና ቢዝነስ ጥናት ማዕከል ነው ይህን የገመተው። ማዕከሉ እንደሚለው ቻይና ኮቪድ-19ኝን የተቋመመችበት መንገድ ዕድገቷን ሊያፋጥን ይችላል። በተቃራኒው አሜሪካና አውሮፓ በኮሮናቫይረስ ክፉኛ መደቆሳቸው ጉዳት አለው ተብሏል። በሌላ በኩል ሕንድ በ2030 ከዓለም ሦስተ...
https://www.bbc.com/amharic/news-55457811
amh
business
ከጂቡቲ ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ ሲከፈት የባቡር መስመሩ እንደተዘጋ ነው ተባለ
ከቀናት በፊት በተቃዋሚዎች ተዘግቶ የነበረው ከጂቡቲ ወደ መሃል አገር የሚወስደው መንገድ መከፈቱ ተገለጸ። ጂቡቲን ከአዲስ አበባ የሚያገናኘው የባቡር መስመር ግን አሁንም ዝግ ሆኖ እንደሚገኝ የሶማሌ ክልል ኮምዩኒኬሽን ምክትል ኃላፊ መሐመድ ሮብሌ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ካሳለፍነው እሁድ ጀምሮ መንገዱና የባቡር መስመሩ በሶማሌ ተወላጆች ላይ የደረሰውን ጥቃት በሚቃወሙ የአካባቢው ወጣቶች ተዘግቶ ነበር። መንገዱ ከጂቡቲ ወደብ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ የተለያዩ ሸቀጦች ዋነኛ መተላለፊያ መስመር ነው። ባለፈው ቅዳ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58022659
amh
business
ንግድ፡ በኢትዮጵያ አንድ ግለሰብ ብቻውን ኩባንያ እንዲያቋቁም ተፈቀደ፤ አዲሱ የንግድ ሕግ ምን ይዟል?
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 16/2013 ዓ.ም ላለፉት 62 ዓመታት ሲያገለግል የቆየውን የአገሪቱን የንግድ ሕግ በመሻር በአዲስ እንዲተካ በሙሉ ድመጽ ወስኗል። ይህን አዲሱ የንግድ ሕግ ከዚህ በፊት ከነበረው አንጻር በርካታ ለውጦች የተደረጉበት እንደሆነ ይነገራል። ለማዘጋጀትም ረጅም ጊዜ የወሰደና በርካታ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ነበር። ከቢቢሲ ጋር ቆይታ የነበራቸውና አዋጁን በማርቀቅ ሂደት የተሳተፉት ከፍተኛ የሕግ አማካሪ ታደሰ ሌንጮ (ዶ/ር) የሕጉ መውጣት የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ...
https://www.bbc.com/amharic/56547521
amh
business
በኢትዮጵያ ይጀመራል የተባለው ክሬዲት ካርድ ምንድነው? አገልግሎቱን ለማግኘት ከእርስዎ ምን ይጠበቃል?
አዋሽ ባንክ በኢትዮጵያ የክሬዲት ካርድ አገልግሎት በመስጠት የመጀመሪያው ባንክ ለመሆን መቃረቡን አሳውቋል። ባንኩ በቅርቡ ይፋ እንዳደረገው ‘ዴቢት ካርድ’ ከተሰኘው አገልግሎት በተጨማሪ፣ የክሬዲት ካርድ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል። በዚህም ሁለት ዓይነት የክሬዲት ካርድ አገልግሎት እንደሚጀምር በገለጸበት ወቅት አንደኛው ሙሉ በሙሉ በአንድ ጊዜ የሚመለስ፣ ሌላኛው ደግሞ ተከፋፍሎ የሚመለስ ነው ብሏል። የኢትዮጵያ ባንኮች ከዴቢት ካርድ አገልግሎት በቀር ሌሎች የካርድ አገልግሎቶች ለደንበኞቻቸው አይሰጡም። ከ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c9805q1yq39o
amh
business
ኮቪድ-19፡ ቤት የመቀመጥ ገደብ ጉግልን ትርፋማ አድርጓል ተባለ
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የተጣለው ቤት ውስጥ የመቀመጥ ገደብ ለጉግል ትርፋማነት አስተዋጽኦ አድርጓል ተባለ። የጉግል ባለቤት ድርጅት የሆነው አልፋቤት ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ 17 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ያገኘ ሲሆን ይህም የ162 በመቶ ጭማሪ መሆኑ ተገልጿል። ለትርፋማነቱም ሰዎች በወረርሽኙ ሳቢያ እንቅስቃሴያቸው ሲገደብ የጉግልን አገልግሎቶች መጠቀማቸው በምክንያትነት ተቀምጧል። ያለፉት ሦስት ወራትም በድርጅቱ ታሪክ ከፍተኛ ትርፍ የተመዘገበበት ነው ተብሏል። ጉግል ይህን የትርፍ መጨመር "ደ...
https://www.bbc.com/amharic/news-56884833
amh
business
"የዓለም አስር ባለ ጸጎች ሀብት ቢደመር ለሁላችንም ክትባት ይገዛል"
ኦክስፋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተው፤ በወረርሽኙ ወቅት ሀብታቸው የናረ አስር ወንዶች ሀብት ንብረት ሲደመር 540 በሊዮን ዶላር ይጠጋል። ይህ ሀብት የዓለም ሕዝቦችን ከድህነት የሚያወጣ እንዲሁም ለሁሉም ሰው ክትበት መግዛት የሚያስችል እንደሆነ የተራድኦ ድርጅቱ ኦክስፋም ጠቁሟል። በዓለም ላይ ያሉ ቢሊየነሮች ጠቅላላ ሀብት፤ የጂ-20 አገራት ወረርሽኙ ካሳደረው ጫና ለመላቀቅ ከሚያወጡት ወጪ እኩል መሆኑ በኦክፋም ሪፖርት ተመልክቷል። ኦክስፋም ይህንን ሪፖርት ተመርኩዞ መንግሥታት ባለ ጸጎች ላይ ከፍተ...
https://www.bbc.com/amharic/55798217
amh
business
በከተማ ግብርና የተለወጡት የአዲስ አበባ ዙሪያ አርሶ አደሮች
በከተሞች ውስጥና በዙሪያቸው የሚኖሩ አርሶ አደሮች የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለነዋሪዎች ያቀርባሉ። ይም በተወሰነ ደረጃ የከተማ ነዋሪዎችን ፍላጎት ሲያሟላ ለእነሱም የገቢ ምንጭ ይሆናል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cp639zpjxrgo
amh
business
የምንፈልገውን ሥራ እና እድገት ለማግኘት ራሳችንን እንዴት እንግለጽ?
ስለራስ መናገር ምቾት አይሰጥም፤ አይደለም ለአለቃ ለወዳጅ እንኳ ቢሆን 'ምን ጉራህን ትቸረችራለህ' ሊያስብል ያስችላል። የሰው ጀማ ተሰብስቦ ስለራስ 'ጥሩንባ መንፋት' የተለመደ አይደለም፤ ይህ ግን የኢትዮጵያውያን ችግር ብቻ ሳይሆን ፈረንጆቹም እዚህ ላይ ትንሽ ቆንጠጥ ያደርጋቸዋል። ስለራሳቸው ለመናገር ጀምረው ድምጻቸው የሰለለባቸው፣ እጃቸውን ያላባቸው፣ አፋቸውን የፈቱበት ቋንቋ የጠፋቸውን የየመሥሪያ ቤቱ ደጃፍ ይቁጠራቸው። ለስቴፋኒ ስዎርድ ዊሊያምስ ግን "ይህ ክህሎት ሁለቴ ማሰብ የማያስፈልገው ሁሉም ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58676398
amh
business
በአሜሪካ ማዕቀብ ምክንያት ፊቱን ወደ አሳማ እርባታ ያዞረው ሁዋዌ
ሁዋዌ በአሜሪካ ዘመናዊ ስልኮቹ ላይ ከባድ ማዕቀቦችን በመጣሉ ምክንያት ፊቱን ለአሳማ ገበሬዎች ቴክኖሎጂ ወደ ማቅረብ አዙሯል። ግዙፉ የቻይናው የቴሌኮም ኩባንያ የትራምፕ አስተዳደር ለአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት አስጊ ነው ተብሎ በመፈረጁ አስፈላጊ ዕቃዎችን እንዳያገኝ ተደርጓል፡፡ ሁዋዌ የገጠመውን የስማርት ስልክ ሽያጭ ሊያካክስ በመፈለጉ ለቴክኖሎጂው ሌሎች የገቢ ምንጮችን እየተመለከተ ነው፡፡ ለአሳማ ገበሬዎች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጅ ከመሥራት በተጨማሪ ሁዋዌ የከሰል ማዕድን ኢንዱስትሪ ጋርም ይሠራ...
https://www.bbc.com/amharic/news-56121975
amh
business
ዩናይትድ አየር መንገድ ቦይንግ 777 አውሮፕላኖችን ከበረራ አገደ
የአሜሪካው ዩናይትድ አየር መንገድ 24 ቦይንግ 777 አውሮፕላኖችን ከበረራ አገደ። አየር መንገዱ አውሮፕላኖቹን ከበረራ ያገደው ባሳለፍነው ቅዳሜ ከአውሮፕላኖቹ አንዱ ሞተሩ ላይ አደጋ ካጋጠመው በኋላ ነው። አውሮፕላኑ 231 መንገደኞችንና አስር የበረራ አስተናጋጆችን አሳፍሮ የነበረ ሲሆን በዴንቨር አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ ተገዷል። እስካሁን በአደጋው የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል። የአውሮፕላኑ ስብርባሪዎችም በአቅራቢያው ባሉ የመኖሪያ ቦታዎች ወዳድቀው ተገኝተዋል። ይህንንም ተከትሎ ጃፓን ተመሳሳይ ፕራት...
https://www.bbc.com/amharic/56151142
amh
business
ስንዴ፣ ዘይት፣ ስኳር እና ሩዝ ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ
የተወሰኑ መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላልተወሰነ ጊዜ ከቀረጥና ታክስ ሙሉ ሙሉ ለሙሉ ነጻ መደረጋቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ እንዳሳወቁት የመሰረታዊ የምግብ ሸቀጦችን የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያው ከነሐሴ 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ተግባራዊ ይሆናል። በዚህም መሠረት የምግብ ዘይት፣ ስኳርና ሩዝ ከውጭ ሲገቡም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምባቸው ከቀረጥና ታክስ ሙሉ በሙሉ ነፃ ሲሆኑ ስንዴ ከውጭ ሲገባ ከቀረጥና ታክስ ነፃ እንዲሆን ተወስኗል።...
https://www.bbc.com/amharic/news-58437093
amh
business
ካፒታሊዝም፡ የአፕል ኩባንያ ሀብት ዋጋ ግምት ሁለት ትሪሊዮን ዶላር ደረሰ
የቴክኖሎጂው ኩባንያ አፕል በስቶክ ገበያ የሀብት ምጣኔ ግምት ከቢሊዮን ዶላሮች አልፎ በትሪሊዮን ዶላር የተገመተ ሁለተኛው የዓለም ኩባንያ ሆኗል፡፡ በአሜሪካ በ2 ትሪሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብት ያለው ኩባንያ የለም፡፡ አፕል የመጀመርያው ሆኗል፡፡ ከዚህ ቀደምም አንድ ትሪሊዮን ዶላር ለመድረስ የመጀመርያው ሆኗል፤ በ2018 ዓ.ም መጀመርያ፡፡ አሁን የአፕል የአንድ ሼር ዋጋ ግምቱ $467.77 ዶላር ደርሷል፡፡ ትናንትና ረቡዕ በነበረው የስቶክ ገበያ የኩባንያው ጥቅል ሀብት 2ሚሊዮን ዶላር መድረሱ ተበስሯል...
https://www.bbc.com/amharic/news-53846118
amh
business
ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት ከምታደርገው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ምን ያህል ተጠቃሚ ናት?
በያዝነው ወር ግንቦት 2003 ዓ.ም ነበር ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገር ጂቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የጀመረችው። በአፍሪካ የልማት ባንክ በ95 ሚሊዮን ዶላር የብድር ድጋፍ በተገነባው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር የመጀመሪያው ዓመታዊ 22 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለጅቡቲ በመሸጥም የኃይል ወጪ ንግድ ከአስራ አንድ ዓመታት በፊት ተበሰረ። የግልገል ጊቤ ሁለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በመዘጋቱ ከታቀደው አንድ አመት ዘግይቶ ነበር የተጀመረው። በወቅቱ የነበረው ...
https://www.bbc.com/amharic/news-61587303
amh
business
የኮሮናቫይረስ ተጽዕኖ በቻይናና በዓለም ምጣኔ ሃብት ላይ
ቻይና በኮሮናቫይረስ በርካታ ዜጎቿን በሞት ከመነጠቋም በተጨማሪ፤ በምጣኔ ሃብቱ ረገድም በዋናነት እየተጎዳች ያለችው ቻይና ስትሆን ሌሎች አገራትም የችግሩ ገፈት ቀማሽ ሆነዋል። የመጣኔ ሃበቱ ጉዳት በቀጥታ ቫይረሱ በቀጥታ ያስከተው ብቻ ሳይሆን ቫይረሱን ለመከላከልም ከፍተኛ ወጭ ጠይቋል። 11 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርባት የዉሃን ከተማ ነዋሪዎች እንዳይንቀሳቀሱ የከተማዋ መግቢያ መውጫ በሮች ተዘግተዋል። በሁቤይ ግዛት በሚገኙ ሌሎች ከተሞችም የሰዎችና የሸቀጦች ዝውውውር እንዲገደብ እየተደረገ ነው። ይህም ለከተሞ...
https://www.bbc.com/amharic/news-51403845
amh
business
የዓለም ምግብ ፕሮግራም በሰሜን ኢትዮጵያ ያሉ የእርዳታ ሥራዎቹ ሊገቱ እንደሚችሉ አስጠነቀቀ
በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት ነዳጅና ምግብ መተላለፍ ባለመቻሉ የነፍስ አድን የምግብ እርዳታ አቅርቦት ሥራው ሊቆም መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስጠነቀቀ። ከአንድ ዓመት በላይ በሆነው ጦርነት ምክንያት ከታህሣሥ ጀምሮ የዓለም ምግብ ፕሮግራም የእርዳታ ጭነት መኪኖች መቀለ ሊደርሱ እንዳልቻሉ ድርጅቱ ዛሬ ጥር 6/2014 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስፍሯል። በተጨማሪም ምግብ፣ ነዳጅና የገንዘብ ድጋፍ ዕጥረት እንዳጋጠመው የገለጸው ድርጅቱ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ላለባቸው ህጻና...
https://www.bbc.com/amharic/news-59977324
amh
business
ለከብቶቻችን የምንሰጠውን ያደረ ዳቦ ለራሳችንም አጥተናል፡ አፍጋኒስታናውያን
አፍጋኒስታናውያን ናን የሚሉት ዳቦ አላቸው። ናን አምባሻ የሚመስል በእስያ ተወዳጅ ምግብ ነው። አፍጋኒስታናውያን ‘የዕለት እንጀራዬን አትንፈገኝ’ የሚሉት ይህን ዳቦ እያሰቡ ነው። መሃል ካቡል ሰማያዊ መስጂድ ይገኛል። በአቅራቢያው አነስተኛ ጉልት አለች። በዚህች ገበያ ትልልቅ ብርቱካናማ ከረጢቶች በደረቁ የናን ዳቦዎች ተሞልተዋል። ከዚህ ቀደም በየቦታው የሚተራርፉ ዳቦዎች ለእንስሳት ምግብነት ይውሉ ነበር። አሁን ግን ነገሮች ተቀይረዋል። ብዙ አፍጋኒስታናውያን ረሃባቸውን ለማስታገስ ወደ እነዚህ ዳቦዎች ፊታ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c0w7nnv9p24o
amh
business
አይኤምኤፍ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገትን መተንበይ እንዳልቻለ አመለከተ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በአውሮፓውያኑ 2022 አስከ 2026 ባለው ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ የሚኖራትን አጠቃላይ አገራዊ ምርት እድገትን (ጂዲፒ) መተንበይ እንዳልቻለ ገለጸ። ድርጅቱ ለዚህ እንደምክንያት ያስቀመጠው በምጣኔ ሀብቱ ውስጥ "ባልተለመደ ሁኔታ ከፍተኛ እርግጠኛ ያለመሆን" በመኖሩ እንደሆነ ገልጿል። ይህ የድርጅቱ አስተያየት የተገለጸው በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ አስራ አንድ ወራትን ያስቆጠረው ግጭትን ተከትሎ ነው። አይኤምኤፍ የዓለም ምጣኔ ሀብት ገጽታ ባሳየበት ሪፖርቱ ላይ በያዝነ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58858523
amh
business
የኬንያው ሳፋሪኮም ኩባንያ ሠራተኞቹን ከኢትዮጵያ አስወጣ
የኬንያው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ የፖለቲካ እና የፀጥታ ሁኔታ በአገሪቱ ለሚያካሂደው ኢንቨስትመንቶች አደጋ መደቀኑንና የሚፈጠሩት ክስተቶች የወደፊት የንግድ ውሳኔዎች ላይ ተዛማጅነት እንዳለው ለቢቢሲ ገለጸ። ኩባንያው በቅርቡ የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ሠራተኞቹንና ተቋራጮችን ከአገሪቱ ማስወጣቱን አስታውቆ፤ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞቹ ደግሞ ከቤታቸው ሆነው እንዲሰሩ እንደሚደረግ ገልጿል። በምሥራቅ እና በመካከለኛው አፍሪካ ትልቁ እና ትርፋማ የሆነው የቴሌኮም ኩባንያ፣ ሳፋሪኮም ኢት...
https://www.bbc.com/amharic/news-59235392
amh
business
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት የሚያስችል የጉምሩክ ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ መሆኑ ተገለፀ
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገውን ጥረት በበለጠ ለመደገፍና ለማሳካት የሚያስችል የጉምሩክ ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ የግብርናና የአምራች ዘርፉን በመደገፍ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በአገር ውስጥ ለመተካት የሚያስችል የሸቀጦች አመዳደብ ስርዓትን ያለመ ነው የጉምሩክ ታሪፍ ማሻሻያው። የቀረጥና ታክስ ማሻሻያው እስከ 8 ሺ የሚሆኑ የታሪፍ መስመሮች የሚያካትት ሲሆን ማሻሻያው ትኩረት ያደረገው በጥሬ እቃዎች፣ በከፊል የተመረቱ ግብአ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58089454
amh
business
ኮሮናቫይረስ፡''አፍሪካ ሁለተኛ ዙር ወረርሽኝ ይከብዳታል'' የዓለም ጤና ድርጅት
የዓለም ጤና ድርጅት ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለአፍሪካ በእጅጉ አስጊና ከባድ ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቋል። ድርጅቱ አክሎም ወረርሽኙ በተለይ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ አስጊ እንደሆነ አስታውቋል። የዓለም ጤና ድርጅት ይህንን ያለው በርካታ አገራት የእንቅስቀሴ ገደቦችንና ሌሎች የጥንቃቄ እርምጃዎችን ማላላት መጀመራቸውን ተከትሎ የቫይረሱ ስርጭት እንደገና ማንሰራራት በመጀመሩ እንደሆነ ተጠቁሟል። የአፍሪካ አገራት ኢኮኖሚያቸውን ለማነቃቃት በማሰብ ወደቀደመው እንቅስቃሴያቸው መመለስ መጀመራቸው ቫይረሱ ከ...
https://www.bbc.com/amharic/news-54574582
amh
business
ከጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ምርት አቋርጦ የነበረው የፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ ወደ ሥራ ተመለሰ
በአካባቢው ባለው ጸጥታ ችግር ምክንያት የነዳጅ አቅርቦት በመስተጓጎሉ የስኳር ምርቱን አቋርጦ የነበረው የፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ ዳግም ወደ ሥራ መመለሱን የስኳር ኮርፖሬሽን የኮሙዩኒኬሽን ተጠባባቂ ሥራ አስፈፃሚ ለቢቢሲ ገለጹ። ፋብሪካው ለሰባት ቀናት ያህል ከየካቲት 02፣ 2014 ዓ.ም ሥራ አቁሞ የነበረ ሲሆን የካቲት 8 ዳግም ወደ ሥራ መግባቱን የኮርፖሬሽኑ የኮሙዩኒኬሽን ተጠባባቂ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ረታ ደመቀ ተናግረዋል። በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የነዳጅ ጫኝ አሸከርካሪዎች ስጋት አድሮባ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60413928
amh
business
የአሜሪካን የአቪዬሽን ንግድ ሚስጥርን ሰርቋል የተባለው ቻይናዊ ተቀጣ
ቻይናዊው የስለላ ሠራተኛ የአቪዬሽን ኩባንያዎችን ምስጢር ለመስረቅ አሲሯል በሚል በአሜሪካ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ መባሉን የአሜሪካ የፍትህ መሥሪያ ቤት አስታወቀ። ዡ ያንጁን የተባለው ይህ ግለሰብ ከኢኮኖሚ ስለላ እና ከንግድ ምስጢር ስርቆቶች ጋር በያያዘ በቀረቡበት አምስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን የ60 ዓመት እስራት እና ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ቅጣት ይጠብቀዋል። ዡ ለመጀመሪያ ጊዜ በቁጥጥር ስር የዋለው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2018 ቤልጂየም ውስጥ ሲሆን ምናልባትም ለአሜሪካ ተላልፎ የተሰጠ የ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59188531
amh
business
የናይጄሪያ አየር መንገዶች በአውሮፕላን ነዳጅ ጭማሪ ምክንያት የሀገር ውስጥ በረራዎችን ሊያቆሙ ነው
የናይጄሪያ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ ጭማሮን በመቃወም ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የሃገር ውስጥ በረራዎችን ሊያቆሙ ነው። በተያዘው አመት ብቻ አራት እጥፍ ገደማ መጨመሩን ያስታወቀው የናይጄሪያ አየር መንገድ ኦፕሬተሮች (ኤኦኤን) ይህንም ሁኔታ መቋቋም አልተቻለም ብሏል። "በአለም ላይ ያለ የትኛውም አየር መንገድ ቢሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲህ አይነት አስደንጋጭ አጨማመርን ሊቋቋም አይችልም። ከዚህ ማገገም አይቻልም" ብሏል። ለጭማሬው ዋነኛ ምክንያት የሆነው ሩሲያ በየካቲት ወር ዩክሬንን መውረሯ ነው።...
https://www.bbc.com/amharic/news-61369465
amh
business
የዓለማችን ለኑሮ ምቹ የሆኑ 10 ከተሞች ይፋ ሆኑ
በዓለማችን ለኑሮ ምቹ የሆኑ 10 ከተሞች ይፋ ሆኑ። ከተሞቹ ምርጥ የተባሉት ለኑሮ ባላቸው ምቹነት መሠረት ነው። አውሮፓዊቷ አገር የኦስትሪያ ዋና ከተማ ቪዬና ቀዳሚዋ የዓለማችን ምቹ ከተማ ተብላለች። በተከታይነት ደግሞ የዴንማርክ ኮፐን ሃገን እና የስዊትዘርላንድ ዙሪክ ከተሞች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘዋል። የካናዳ ከተማ የሆኑት ካልጋሪ እና ቫንኩቨር ደግሞ በአራተኝነት በቀጣይ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ሲሆን፤ የስዊትዘላንዷ ጄኔቫ፣ የጀርመኗ ፍራንክፈርት፣ የካናዳዋ ቶሮንቶ፣ የኔዘርላንድስ አምስተርዳም፣...
https://www.bbc.com/amharic/articles/clw4zjvpljjo
amh
business
የትኞቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በሩሲያ ያላቸውን ስራ አቋረጡ?
ሰላሳ ዓመት ወደኋላ! ከሰላሳ ዓመታት በፊት በሶቭየት ኅብረት ኮምዩኒዝም ሲንኮታኮትና የሩሲያ በሮች ለኢንቨስትመንት እና ንግድ ሲከፈቱ ይህንን ዕድል ለመጠቀም የምዕራባውያን ኩባንያዎችን የቀደመ አልነበረም። ያኔ እንደ ኮካ ኮላ እና ማክዶናልድስ ያሉ ታዋቂ ኩባንያዎች በሩሲያ ስራ ሲጀምሮ የሩሲያ አዲሱ ጊዜ መጣ እስከመባል ደርሶ ነበር። የተለያዩ ምርት አቅራቢዎች፣ ማዕድን አውጪዎች፣ የህግ አማካሪዎችና በርካታ ድርጅቶች ቀስ በቀስ በሩሲያ ተስፋፉ። ሩሲያውያንም በሌዊ ጂንስ መዘነጥ እና የምዕራብያውያኑ ቅንጡ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60598954
amh
business
ሕይወት ከመሠረታዊ አቅርቦቶች ውጪ በሆነችው ትግራይ
ኑሮውን ሱዳን ካርቱም ያደረገው እና ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ግለሰብ በቅርቡ መቀለ ለሚገኙ ቤተሰቦቹ የዕለታዊ ፍጆታ መግዣ ገንዘብ መላኩን ይናገራል። የባንክ አገልግሎት ከተቋረጠ ወራት ወደ ተቆጠረባት መቀለ 40 ሺህ ብር መላክ ማሰቡን ያወቁ እና ከክልሉ ውጪ የሚኖሩ ግለሰቦች፣ ገንዘቡን ለቤተሰቦቹ ለማድረስ 20 ሺህ 800 ብር እንዲከፍላቸው እንደጠየቁት ለቢቢሲ ገልጿል። ምንም እንኳ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ውስጥ በሕጋዊነት የሚሰራ አንድም የፋይናንስ ተቋም ባይኖርም፣ መቀለ ለሚገኙ ቤተሰቦቹ ገንዘ...
https://www.bbc.com/amharic/news-60735701
amh
business
የእስራኤሏ ቴልአቪቭ በዓለም ላይ በጣም ውድ ከተማ ተብላ ተሰየመች
የእስራኤሏ ከተማ ቴልአቪቭ በዓለም ካሉ ውድ ከተሞች የአንደኛነቱን ሰፍራ ያዘች። እየጨመረ ያለው ግሽበትና የአቅርቦት ሰንሰለት ችግር በዓለም አቀፍ ደረጃ ንረትን ከፍ ባደረገው ወቅትም ነው ቴልአቪቭ ለሰው ልጅ መኖሪያነት ውድ ከሆኑ ከተሞች የቁንጮነቱን ስፍራ የያዘችው። የእስራኤሏ ከተማ በአንደኛነት ስፍራ ስትቀመጥ የመጀመሪያ ሲሆን ፓሪስና ሲንጋፖር ተከታታዩን ስፍራ እንደያዙ ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት ያደረገው ጥናት ይፋ አድርጓል ። በዚሁ ተቋም መረጃ መሰረት ቴልአቪቭ ባለፈው አመት አምስተኛ ስፍራ ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59493433
amh
business
ዛምቢያ፡ ድሮኖች ቀረጥ ያልከፈሉ ተሽከርካሪዎችን እያደኑ ነው
የዛምቢያ የግብር ባለሥልጣናት ቀረጥ ሳይከፍሉ እቃዎችን የሚያዘዋውሩ ከባድ መኪናዎችን ለመቆጣጠር ድሮኖችን መጠቀም ጀመሩ። ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ የዛምቢያ ገቢዎች ባለሥልጣን በድሮኖች በመታገዝ ከዋናው መንገድ በመውጣት ተደብቀው የነበሩ ሰባት ተሽከርካሪዎች መያዛቸውን አስታውቀዋል። • ያለአብራሪ በሚበረው የሰማይ ታክሲ ይጠቀማሉ? • ሥራ ቀጣሪና አባራሪ እየሆነ የመጣው ሮቦት " ድሮኖቹ የፍተሻ ሠራተኞች በማይደርሱባቸው እንዲሁም አደጋ ባለባቸውና ጥንቃቄን በሚጠይቁ ቦታዎች ድረስ በመግባት አሰሳ ያደርጋ...
https://www.bbc.com/amharic/news-49404009
amh
business
በኢትዮጵያ በምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት መመዝገቡ ተገለጸ
በኢትዮጵያ በምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ ከፍተኛው የዋጋ ግሽበት እየተመዘገበ መሆኑን የአገሪቱ ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ምክር ቤት ገለጸ። ምክር ቤቱ የዘጠኝ ወራት የምጣኔ ሀብት አፈጻጸምን ገምግሞ ባወጣው በዛሬው ግንቦት 2፣ 2014 ዓ.ም መግለጫ ላይ እንዳመለከተው የኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብት ከፍተኛ ፈተና እየገጠመው ያለው ከዋጋ ግሽበት አንጻር መሆኑን ጠቁሟል። በዚህም የዋጋ ግሽበቱ በዋናነት በምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መመዝገቡን ጠቅሶ፤ ይህም ካለፈው ዓመት የሚያዝያ ወር ጋር ሲነጻጸር የዋጋ ግ...
https://www.bbc.com/amharic/news-61394971
amh
business
"የቱሪስት ማግኔት" የሆነችው ቬኒስ ከተማን ጎርፍ እያስጨነቃት ነው
በዓለም አቀፍ ደረጃ የቱሪስት ማግኔት አላት የምትባለው የጣልያኗ ቬኒስ ከተማ በጎርፍ እየተፈተነች ነው። ጎርፉ ቬኒስን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር አሳጥቷታል ተብሏል። በጎርፉ ምክንያት የውሃ መተላለፊያ የሆነው የከተማዋ ዋና አደባባይ ሴንት ማርክ ፣ትምህርት ቤቶችና ንግድ ቤቶች ተዘግተዋል። የጣልያን መንግስሥትም በዩኔስኮ ድረ ገፅ ላይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁን አስታውቋል። • ከባድ ዝናብና የጎርፍ አደጋ በአንዳንድ አካባቢዎች ጉዳት አስከተለ • ጎርፍ ባጠቃቸው የምሥራቅ አፍሪካ አገራት ተጨማሪ ዝናብ ሊ...
https://www.bbc.com/amharic/news-50437271
amh
business
ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልን የሚወስነውን ቦርድ ልታቋቁም ነው
በኢትዮጵያ የዝቅተኛ የደመወዝ መጠንን የሚወስነው የደመወዝ ቦርድ ሊቋቋም መሆኑን ቢቢሲ ከሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ካገኘው መረጃ መረዳት ችሏል። በአሁኑ ወቅት የዝቅተኛ ደመወዝ ወለልን የሚወስነው የደመወዝ ቦርድ ማቋቋሚያ ደንብ የተረቀቀ ሲሆን በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የበላይ ኃላፊዎች ምክክር ሲደረግበት ቆይቶ ደንቡ ወደሚፀድቅበት ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ለመላክ በዝግጅት ላይ ነው ተብሏል። ይህ ቦርድ በኢትዯጵያ እስካሁን ድረስ ሲሰራበት የ...
https://www.bbc.com/amharic/news-57340391
amh
business
ከወለድ ነጻ ባንክ ሥርዓት ለሚሰጠው 'ብድር' እንዴት ትርፍ ያገኛል?
የሼሪያ ሕግን መሰረት አድርጎ ሥራውን የሚያከናውነው እስላማዊ ወይም ከወለድ ነጻ የባንክ ሥርዓት ገንዘብ ሰጥቶ፣ አትርፎ መቀበልን ያወግዛል። ይህም በባንኩ ሥርዓት ብቻ ሳይሆን በቅዱስ ቁርዓንም የተከለከለ በመሆኑ በቀዳሚነት የእስልምና እምነት ተከታዮችን ያገለግላል። ሆኖም የእምነቱ ተከታዮች ላልሆኑ ደንበኞችም ክፍት ነው። በተቃራኒው መደበኛው የባንክ ሥርዓት፣ የቁጠባ ሂሳብ ለሚከፍቱ ወለድ እየከፈለ ገንዘባቸውን ሲያስቀምጥ፣ ለሚያበድረው ገንዘብ ደግሞ ወለድ ይቀበላል። ይህም የመደበኛ ባንኮች ዋነኛ የትርፍ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59521754
amh
business
የሊባኖስ ባንኮች ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቆሙ
የሊባኖስ ባንኮች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች አስፈላጊውን ጥበቃ አላደረጉልንም በሚል ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ የአገሪቱ ባንኮች ማኅበር ገለጸ። ደንበኞች ባለፈው ሳምንት እንዳይንቀሳቀስ የተደረገውን የቁጠባ ሂሳባቸውን ለማግኘት በኃይል ታግዘው ገንዘባቸውን የመውሰድ ድርጊቶች መበራከታቸውን ተከትሎ ነው የሊባኖስ ባንኮች ማኅበር አገልግሎት መቆሙን ያስታወቀው። በአገሪቱ የሚገኙ ባንኮች ውስጥ የሚያገለግሉ ሠራተኞች መፍትሄ ማግኘት ያልቻሉ የደኅንነት ስጋት ገጥሟቸዋል ሲልም ማኅበሩ ገልጿል። ባሳለፍነ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c99pqg8j2v8o
amh
business
በጥሬ ገንዘብ ዝውውር ላይ የተጣለው ገደብ ለምን አስፈለገ?
በኢትዮጵያ ከባንኮችና ከማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በሚወጣ የጥሬ ገንዘብ ላይ የተጣለው እገዳ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል። ብሔራዊ ባንክ ያወጣው መመሪያ ተቋማትና ግለሰቦች ከባንኮች በቀንና በወር ውስጥ በሚያወጡት የጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ገደብ ጥሏል። በዚህም መሰረት አንድ ግለሰብ በቀን እስከ 200 ሺህ ብር እንዲሁም በወር እስከ 1 ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ ከባንኮች ማውጣት የሚችል ሲሆን፤ ተቋማት ደግሞ በቀን እስከ 300 ሺህ ብር እና በወር እስከ 2.5 ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ ማንቀሳቀስ እንደሚችሉ ...
https://www.bbc.com/amharic/news-52734564
amh
business
ኢትዮጵያ ግሽበትን ለመግታት የባንኮች የመጠባበቂያ የገንዘብ መጠን በእጥፍ እንዲያድግ ወሰነች
በከፍተኛ ሁኔታ እያንሰራራ ያለውን የዋጋ ግሽበት ለመግታት ባንኮች ከሚሰበስቡት የተጣራ ቁጠባ በኢትዮጵያ ብሔራዊ እንዲያስቀምጡት የሚጠበቅባቸውን የመጠባበቂያ የገንዘብ መጠን ወደ አስር በመቶ ከፍ እንዲያደርጉት ተወስኗል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዳስታወቀው ከዚህ ቀደም 5 በመቶ የነበረውን የመጠባበቂያ የገንዘብ መጠን ከፍ እንዲል የወሰነው በኢኮኖሚው ውስጥ የሚዘዋወረውን የገንዘብ መጠን ለመቀነስ ቁጥብ የገንዘብ ፖሊስ ለማድረግ ከመወሰኑ ጋር ተያይዞ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ባንኮች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58391135
amh
business
የቢትኮይን ዋጋ በ50 በመቶ በከፍተኛ ሁኔታ አሽቆለቆለ
ዋጋው እያሽቆለቆለ ያለው ቢትኮይን፣ በአሁኑ ጊዜ ከፍተኛ ቅናሽ በማሳየት አንድ ቢትኮይን 34ሺህ የአሜሪካ ዶላር እየተሸጠ ነው። የክሪፕቶከረንሲ አሻሻጩ ኮይንቤዝ ከስድስት 6 ወራት በፊት ጣራ ነክቶ የነበረው ቢትኮይን በአሁኑ ወቅት ዋጋው 50 በመቶ ቀንሷል ብሏል። በክሪፕቶከረንሲዎች የገበያ ድርሻ ቀዳሚ የሆነው ቢትኮይን ዋጋው መቀነሱ የተሰማው በመላው ዓለም የድርሻ ገበያዎች [ስቶክ ገበያ] መቀነሳቸውን ተከትሎ ነው። የክሪፕቶካረንሲዎች ዋጋ ከዓለም የስቶክ ገበያ ጋር ተያይዞ ዋጋቸው ከፍ እና ዝቅ ሲል ይ...
https://www.bbc.com/amharic/news-61375822
amh
business
ኤሎን መስክ የግል ጀቱን የሚከታተለውን የትዊተር ገጽ ባለቤት ሊከስ ነው
ኤሎን መስክ በግል ጀቱ የት እንደተጓዘ የሚከታተለውን የትዊተር ገጽ ባለቤት ሊከስ ነው። የግል ጀቱ እንቅስቃሴ @ElonJet account በሚባለው ገጽ ለሕዝብ ይፋ መደረጉ የልጁን ደኅንነት አደጋ ላይ እንደሚጥለው መስክ ተናግሯል። ይህ የትዊተር ገጽ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ተከታዮች አሉት። በዚህ ሳምንት ገጹን ትዊተር አግዶታል። የገጹ ባለቤት የ20 ዓመቱ ጃክ ስዊኒ ነው። በረራ የሚከታተሉ መተግበሪያዎችን ተጠቅሞ ነው የመስክን የግል ጀት የሚከታተለው። የመስክለ ጀት ሲነሳና ሲያርፍ ትዊተር ገጹ ላይ ይጽፋ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgl1m1yn2p4o
amh
business
ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ከነጮች ባነሰ ሁኔታ የሚኖሩባት ደቡብ አፍሪካ
ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ከነጭ አቻዎቻቸው በሦስት እጥፍ ያነሰ ገቢ እንደሚያገኙ አንድ ጥናት ይፋ አደረገ። ጥናቱ በደቡብ አፍሪካውያን መካከል ያለውን ያልተመጣጠነ ገቢን የተመለከተ ሲሆን፤ ከአገሪቱ 80 በመቶ የሚሆኑት ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን የወር ገቢያቸው በአማካኝ 13000 ብር ገደማ ሲሆን፤ የነጭ ደቡብ አፍሪካውያን ግን 38 ሺህ ብር አካባቢ እንደሆነ ተቀምጧል። • “ከብሔርም ከሐይማኖትም በላይ ሰውነት ከሰሃራ በረሃ ስቃይ አውጥቶኛል" • ፓርቲዎች በክልላቸው ባሉ ዩኒቨርስቲዎች የሚታየው ግጭት እን...
https://www.bbc.com/amharic/50443851
amh
business
በኢንተርኔት መቋረጥ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ቀጥሎ በአፍሪካ ከፍተኛ ገንዘብ አጥታለች - ሪፖርት
ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት በኢንተርኔት መቋረጥ ከሰሃራ በታች ከሚገኙ የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ በመቀጠል ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንዳጣች አንድ ሪፖርት አመለከተ። ባለፈው ዓመት በዓለም ዙሪያ ሆን ተብለው የተፈጸሙ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጦች በአገራት ላይ ያስከተሉትን ኪሳራ በተመለከተ ቶፕ ቴን ቪፒኤን ባወጣው ሪፖርት ላይ በአፍሪካ ናይጄሪያ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን በቀዳሚነት ተቀምጠዋል። በመላው ዓለም መንግሥታት በአገራቸው ውስጥ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በማቋረጣቸው በአጠቃ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59988907
amh
business
የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ፍለጋና የዋጋ መናር በአዲስ አበባ
አዲስ አበባ ውስጥ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በከፍተኛ ገንዘብ ሲሸጥ እንደነበረና በመደብሮች ውስጥ ማግኘት እንዳልቻሉ ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገለጹ። አርብ ዕለት አዲስ አበባ ላይ የጤና ጥበቃ ባለስልጣናት የመጀመሪያው የተረጋገጠ የኮሮናቫይረስ ታማሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ከተገኘ በኋላ ስጋት የገባቸው ሰዎች የፊት ጭንብልና ፈሳሽ የእጅ ማጽጃ ውህዶችን በመግዛት ላይ ናቸው። የቢቢሲ ያናገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንዳሉት በሽታው አሳሳቢ ከመሆኑ የተነሳ ሊከላከለው ይችላል ...
https://www.bbc.com/amharic/news-51894637
amh
business
ኮሮናቫይረስ፡ የአሜሪካ ታችኛው ምክር ቤት ጆ ባይደን ያቀረቡትን የ1.9 ትሪሊየን ዶላር ድጎማ አፀደቀ
የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት አሜሪካዊያንን ለመርዳት ያቀረቡት የ1.9 ትሪሊየን ዶላር የኢኮኖሚ ማነቃቂያ ማዕቀፍ በተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ። የድምፅ አሰጣጥ ሁኔታው ከፓርቲ ወገንተኝነት ጋር የተያያዘ ነበር። ሁሉም ሪፐብሊካኖች ተቃውመውታል። ሁለት ዲሞክራቶችም ገንዘቡ በጣም ብዙ ነው ሲሉ በመቃወም ሪፐብሊካኖችን ተቀላቅለዋል። ማዕቀፉ በሚቀጥለው ሳምንት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዲሞክራቷ ካማላ ሃሪስ ሰብሳቢ በሆኑበት የሕግ መወሰኛው ምክር ቤት ይቀርባል። ይህ ምክር ...
https://www.bbc.com/amharic/news-56221851
amh
business
የተሰናባቹ 2013 ዓመት ዓበይት ምጣኔ ኃብታዊ ክስተቶች
ኢትዮጵያ 2013ን ተሰናብታ አዲሱን ዓመት ልትቀበል የቀራት ጥቂት ቀናት ናቸው። ተሰናባቹን ዓመት ዘወር ብለን በምናይበት ወቅት አገሪቷ በጦርነት ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿ የተቀጠፉበት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቤት አልባ ሆነው በችግር ውስጥ የሚገኙበት፣ ከፍተኛ የዋጋ ንረት የብዙዎችን ናላ እያዞረ ባለበት ነው ያሳለፉት። ፈታኝ በሚባል የታሪክ ሂደት ውስጥ ያለችው አገሪቷ በምትሸኘውም ዓመት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጸጥታ ምክር ቤት ዋነኛ ርዕሰ ጉዳይ፣ የኃያላኑ መንግሥታት መነጋገሪያ፣ በባለስልጣ...
https://www.bbc.com/amharic/news-58489178
amh
business
በኬንያ ከኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ የሚሰረቅ መርዛማ ዘይት ለምግብ ማብሰያነት እየተሸጠ ነው ተባለ
የኬንያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ድርጅት ከሃይል ማስተላላፊያ ወይም ትራንስፎረመር ላይ እየተሰረቀ እንደ ማብሰያ ዘይት የሚሸጠው ፈሳሽ መሰረተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት በማድረስ በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር ኪሳራ እያስከተለ እንደሆነ ገለጸ። የኬንያ ኤሌክትሪክ ሃይል ወንጀለኞች ፈሳሹን ከትራንስፎርመሮቹ ውስጥ በማውጣት ለሬስቶራንቶች እና በመንገድ ዳር ምግብ ለሚያዘጋጁ በሽያጭ ቀርቦ ምግብ ለማብሰል እና ለመጥበስ እንደሚሸጥ አስታውቋል። ከምግብ ዘይት ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስፋፋ የመጣው ይህ ድ...
https://www.bbc.com/amharic/61020009
amh
business
‘እጅ የበዛበት’ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ
ከሰሞኑ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ጋር ተያይዘው በተከሰቱ ችግሮች ምክንያት ዕጣው ውድቅ እንዲሆን ውሳኔ ተላልፏል። በበርካቶች ዘንድ መነጋገሪያ የሆነውና ውዝግብ ባስከተለው ዕጣ ውስጥ መሳተፍ የነበረባቸው 79 ሺህ የሚሆኑ ተመዝጋቢዎች ቢሆኑም፣ በድብቅ የተዘጋጁ 172 ሺህ ያህል ሰዎች በዕጣው ውድድር ተሳታፊ እንዲሆኑ ተደርገዋል ተብሏል። በዚህም 93 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች ተገቢ ባልሆነ መንገድ የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት በተዘጋጀው ዕጣ ውስጥ መካተታቸው ተገልጿል። ከአስራ አምስት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/ckvn7zepvp3o
amh
business
የዋነኛው ክሪፕቶከረንሲ ዋጋ እያሽቆለቆለ ያለው ለምንድን ነው?
ያለፉት ጥቂት ቀናት ለቢትኮይንም ሆነ ለክሪፕቶከረንሲ አስከፊ ጊዜ ነው። አሁን ላይ የአንድ ቢትኮይን ዋጋ 21 ሺህ 974 ዶላር ነው። ቢትኮይን ቀድሞ ከነበረው ዋጋ ጋር ሲነጻጸር ባለፉት አምስት ቀናት ብቻ 25 በመቶ አሽቆልቁሏል። ይህም ባለፉት 18 ወራት የተመዘገበው ዝቅተኛው ዋጋው ነው። ቢትኮይን በዘመኑ ያወጣው ከፍተኛ ዋጋ ባለፈው ኅዳር ወር ላይ የተመዘገበ ሲሆን፣ ይህም ዋጋው 70 ሺህ ዶላር የሚጠጋ ነበር። ባለሙያዎች እንደሚሉት ለዚህ ምክንያቱ በዓለም ላይ ያለው ሁኔታ ነው። በእርግጥ በዓለማችን ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c4nzzqv8ljgo
amh
business
ክትባትና ውሃ አምራቹ ከእስያ ቁጥር አንድ ሀብታም ሆነ
ዞንግ ሻንሻን የእስያ ሀብታሞች ዝርዝርን በግንባር ቀደምነት መምራት ጀምሯል። ክትባት እና የታሸገ ውሃ ማምረቻ ባለቤት የሆነው ዞንግ፤ በዚህ ዓመት ሀብቱ ሰባት ቢሊየን ዶላር ጨምሯል። የሕንዱን ሙከሽ አምባኒ እና የቻይናውን ጃክ ማ በልጦም የእስያ ቁጥር አንድ ባለ ጸጋ ሆኗል። አጠቃላይ ሀብቱ ወደ 77.8 ቢሊየን ዶላር ይጠጋል። ይህም የዓለም 11ኛው ሀብታም እንደሚያደርገው የብሉምበርግ ቢሊየነር ኢንዴክስ ያሳያል። “ብቸኛው ተኩላ” በሚል ቅጽል ስሙ የሚታወቀው ባለ ሀብት በጋዜጠኛነት፣ በእንጉዳይ እርሻና ...
https://www.bbc.com/amharic/news-55495983
amh
business
አርጀንቲና በወረርሽኙ የተጠቁትን ለመደጎም የናጠጡ ኃብታሞቿ ላይ ግብር ጣለች
አርጀንቲና አገሯ በሚገኙ የናጠጡ ኃብታሞች ላይ ለየት ያለ ግብር ጥላለች። ግብሩ ለኮሮናቫይረስ የሚያስፈልጉ የህክምና ቁሳቁሶች ግብዓትና በወረርሽኙ ምክንያት ክፉኛ ለተጠቁት ኑሯቸውን መደጎሚያ እንዲሆን ነው። የምክር ቤቱ አባላት "የሚሊዮነሮች ግብር" ብለው የጠሩት በአንዴ የሚከፈል ገንዘብ ሲሆን በዚህ ሳምንት አርብም 42 ለ 26 በሆነ የድምፅ ብልጫም ፀድቋል። በዚህም መሰረት ከ200 ሚሊዮን ፔሶ (2.5 ሚሊዮን ዶላር) ኃብት ያከማቹ ግለሰቦች መክፈል አለባቸው። በአገሪቱ ይህ የገንዘብ መጠን ያላቸውም ወ...
https://www.bbc.com/amharic/news-55191619
amh
business
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናውያን ግላዊ መረጃ ተሰርቆ ለሽያጭ መቅረቡ አነጋጋሪ ሆኗል
አንድ የበይነ መረብ መረጃ ሰርሳሪ ከቻይና የፖሊስ ተቋም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን መረጃ መዝብሮ ለሽያጭ ማቅረቡን ተከትሎ ጉዳዩ መነጋገሪያ ሆኗል። ይህ አንድ ቢሊየን ይደርሳሉ የተባሉ የቻይናውያን ግላዊ መረጃ ስርቆት ዜና ይፋ ከሆነ በኋላም የአገሪቱ ፕሬዝዳንት የሕዝቡ መረጃ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግለት አሳስበዋል። የበይነ መረብ መረጃ ሰርሳሪዎች (ሃከርስ) ሰርቀነዋል ያሉትን የቻይናውያንን መረጃ የሚገዛቸው ካለ ለመሸጥ ማስታወቂያ ካወጡ በኋላ ነው፣ ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ሕዝባዊ ተቋማት “የመረጃ ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cp42eek8x71o
amh
business
ቦይንግ ከ737 ማክስ ጋር በተያያዘ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ
ቦይንግ ስለ 737 ማክስ አውሮፕላኑ ዲዛይን ከአሜሪካ የደኅንነት እና ጥንቃቄ ባለሙያዎች መረጃዎችን በመደበቅ ለተመሰረተበት የወንጀል ክስ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ቅጣት ለመክፈል ተስማማ። የአሜሪካ ፍትህ ቢሮ እንዳለው ከሆነ ኩባንያው "ከግልጽነት ይልቅ ትርፍን" አስቀድሟል። ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን በኢትዮጵያ እና በኢዶኔዢያ ተከስክሶ የ346 ሰዎች ህይወት አልፏል። ቦይንግ ለመክፈል ከተስማማው ገንዘብ ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላሩ በአውሮፕላኑ አደጋ ቤተሰቦቻቸውን ላጡ የሚከፋፈል ይሆናል። ቦይንግ እንዳለ...
https://www.bbc.com/amharic/news-55570801
amh
health
ዘግታችሁ የወጣችሁትን በር እንዳልተዘጋ የሚያሳስባችሁ የአእምሮ ሕመም - ኦሲዲ
ምሥራቅ* ለዚህ ታሪክ ሲባል ስሟ የተቀየረ “ለሦስት ዓመታት የማስበውን ሁሉ እንድጽፍ አእምሮዬ ያስገድደኝ ነበር” ትላለች። እንቅልፍ እና እርሷ ተፋትተው ነበር የከረሙት። “ዝም ብዬ መጻፍ ነው። ደብተር፣ ወረቀት፣ ሞባይል ሁሉ ነገር ላይ እጽፋለሁ።” የምትጽፈው ነገር ለሚያነበው ሰው ትርጉም ላይሰጥ ይችላል። ማንኛውንም ነገር በአእምሮዋ ውስጥ ሰንዳ የያዘቸውን ወይም የመጣላትን ጥቃቅን ነገር ሁሉ ካልጻፈች ሰላም ይነሳታል። “ፀጉሬ ላይ ቅባት ተቀብቼ ጥሩ ነው ብዬ ካሰብኩኝ እጽፈዋለሁ።” ይህ የመጻፍ ጉትጎ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6pqpg24lvno
amh
health
'ባሌ አጫሽ ነበረ፣ በእሱ ምክንያት ካንሰር ያዘኝ'
“በአፍንጫዬ መተንፈስ አልችልም። የምተነፍሰው ‘ስቶማ’ በሚባልና አንገቴ ላይ በሚገኝ ቀዳዳ አማካይነት ነው’’ ይላሉ የ75 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋዋ ናሊኒ ሳትያናርያን። ናሊኒ በህይወታቸው እንድም ቀን ሲጋራ አጭሰው አያውቁም። ነገር ግን ላለፉት 33 ዓመታት ባለቤታቸው ከሚያጨሱት ሲጋራ የሚመጣ ጭስ ሲተነፍሱ ኖረዋል። ባለቤታቸው ሕይወታቸው ካለፈ ከአምስት ዓመታት በኋላ በአውሮፓውያኑ 2010 ላይ ናሊኒ ካንሰር እንዳለባቸው ተነገራቸው። “ባለቤቴ አጫሽ ነበር። የእሱ ሲጋራ ማጨስ እኔን ይሄን ያክል ይጎዳኛል ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6p914npjevo
amh
health
የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ካንዬ ዌስት “ሳትጠራ እና ሳታሳውቅ” መጥተሃል ተብሎ ከስኬቸርስ ቢሮ እንዲወጣ ተደረገ
ስኬቸርስ የተባለው የጫማ አምራች ኩባንያ ራፐሩ ዬ፣ በቀድሞ ስሙ ካንዬ ዌስት፣ “ሳያሳውቅ እና ሳይጋበዝ” መጥቷል በሚል ከኩባንያው ሕንጻ እንዲወጣ እንዳደረገው ገለፀ። ድርጅቱ አክሎም ከራፐሩ እና ዲዛይነሩ ዬ ጋር በጋራ የመስራት “ምንም ዓይነት ፍላጎት” የለኝም ብሏል። ይህ ዜና የተሰማው የጀርመኑ ስፖርት ትጥቅ አምራች አዲዳስ፣ ዬ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሰጠውን ፀረ አይሁዳዊ አስተያየት ተከትሎ ያለውን ግንኙነት ካቋረጠ በኋላ ነው። ቢቢሲ የዬን ወኪሎች አስተያየት ቢጠይቅም ምላሽ ማግኘት አልቻለም። ስኬ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cj5z15d3g61o
amh
health
አንድ ውሻ በዝንጀሮ ፈንጣጣ መያዙን የአለም የጤና ድርጅት አስታወቀ
አንድ ውሻ ከባለቤቱቶቹ በተላለፈ የዝጀሮ ፈንጣጣ ቫይረስ መጠቃቱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። ይህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የበሽታው ስርጭት ሰዎች በቫይረሱ ከተያዙ በኋላ ራሳቸውን ከቤት እንስሳቶቻቸውም ጭምር ማግለል እንዳለባቸው የሚያሳይ እንደሆነም የጤና ሃላፊዎቹ አስታውቀዋል። ሌሎች እንስሳትን የመበከል አደጋን ለመቀነስ ቆሻሻን በጥንቃቄ ማስወገድ እንደሚያስፈልግ የዓለም ጤና ድርጅት አስጠንቅቋል። ውሾች በሽታውን ወደ ሌሎች ውሾች ወይም ወደ ሰዎች ያስተላልፉ እንደሆነ የሚያረጋግጥ መረጃ እስካ...
https://www.bbc.com/amharic/articles/cqlk1nd5877o
amh
health
“ስለ አዕምሮ ጤና በግልፅ መነጋገር ለሁላችንም ጤንነት ነው” ያዕቆብ ተክዔ
ያዕቆብ ተክዔ (ዶ/ር) በአሜሪካው ፔንሲልቬንያ ዩኒቨርሲቲ የሥነ አዕምሮ ባለሙያ ነው። ያዕቆብ በትምህርቱ ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት፣ በሥራው ቴራፒስትና የሙሉ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ አስተማሪ ነው። ያዕቆብ ተውልዶ ያደገው በኤርትራ ሲሆን የድህረ ምረቃ ትምህርቱን ለመከታተል ከበቃበት ጊዜ አንስቶ የሥራ ዓለሙን እስኪቀላቀል ድረስ ኑሮው በአሜሪካ ነው። የያዕቆብ ሥራ የሚያተኩረው በስደትና በስደተኞች ላይ ሲሆን በተለይም ደግሞ ከአፍሪካ፣ አብልጦም ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ለተሰደዱ ሰዎችን የአዕምሮ ጤና ድጋፍ እና ክትት...
https://www.bbc.com/amharic/news-58552208
amh
health
ኮሮናቫይረስ፡ የአስትራዜንካን ክትባት ተጠቀሙ- የዓለም ጤና ድርጅት
በርካታ የአውሮፓ ሃገራት የኮሮናቫይረስ መከላከያ የሆነውን አስትራዜንካ ክትባት ማገዳቸውን ተከትሎ የዓለም ጤና ድርጅት ክትባቱን እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርቧል። ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያንና ስፔይንን ጨምሮ ሌሎች አገራት የኦክስፎርዱ አስትራዜንካ ክትባት ደም መርጋት በተያያዘ ችግር አለበት በሚል ክትባቱ እንዳይሰጥ አግደውታል። የዓለም ጤና ድርጅት በበኩሉ ደም መርጋት ስለማስከተሉ ምንም አይነት ማስረጃ የለም ይላል። የድርጅቱ የክትባት ደህንነት ልሂቃንም በዛሬው ዕለት ተሰብስበው ስለ ክትባቱ ይመክራሉ ተብሏል።...
https://www.bbc.com/amharic/news-56411232
amh
health
ዓለም ተስፋ የጣለበት የኦክስፎርድ የኮሮና ክትባት ምርምር እንዲቆም ተደረገ
የመጨረሻ የክሊኒካል ሙከራ ላይ የነበረውና ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት የቆየው የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ከመድሃኒት አምራቹ አስትራዜኔካ ኩባንያ ጋር እያበለጸጉት የነበረው የኮሮና ክትባት ነበር። ምርምሩ ለጊዜው ባለበት ይቁም ተብሏል። ምክንያቱ ደግሞ የክትባት ቅንጣቱን የወሰዱ በጎ ፍቃደኛ ተሳታፊዎች ህመም ስላጋጠማቸው ነው። ይሁን እንጂ ግዙፉ የመድኃኒት አምራች አስትራዜኔካ ይህ የሚያደናግጥ ሳይሆን የሚያጋጥም ነው ይላል። ህመም የተሰማቸው ተሳታፊዎች ለምን ህመም እንደተሰማቸው ለማወቅ ጊዜ ይፈልጋል። የኦክስትፎ...
https://www.bbc.com/amharic/54078490
amh
health
ሕንድ ፡ በአንድ ሆስፒታል ላይ በተከሰተ የእሳት አደጋ 10 አራስ ሕፃናት ሞቱ
ዛሬ ቅዳሜ ጠዋት በሕንድ አንድ ሆስፒታል ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የሆስፒታሉ ሠራተኞች ህይወት ለማትረፍ የቻሉትን ቢያደርጉም አስር አራስ ሕፃናት ህይወት ማለፉ ተነገረ። የእሳት አደጋ ተከላካዮች በምዕራባዊው ማሃራሽትራ ግዛት ወደምትገኘው የብሃንዳራ አካባቢ ሆስፒታል እሳቱን ለመቆጠጠር ከመድረሳቸው በፊት ሰባት ሕፃናትን ከእሳት አደጋው ማትረፍ ተችሏል። የሕንድ ጠቅላይ ሚንስትር ናሬንድራ ሞዲ "ልብ የሚያቆስል አሳዛኝ ክስተት" ሲሉ አደጋውን ገልጸዋል። የእሳት አደጋው የተከሰተው አርብ ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢ...
https://www.bbc.com/amharic/news-55581634
amh
health
ኮሮናቫይረስ፡ ኒውዚላንድ ከወራት በኋላ በቫይረሱ የተያዘች ሴት አገኘች
ከሁለት ወራት በላይ የኮሮናቫይረስ የማህበረሰብ ስርጭት ያልታየባት ኒውዚላንድ ከሰሞኑ በቫይረሱ የተያዘች ሴት አግኝታለች። የጤና ባለሙያዎች ከሰሞኑ ከአውሮፓ የተመለሰች የ56 አመት ሴት ቫይረሱ ተገኝቶባታል። ግለሰቧ ከሌላ አገራት ለሚመጡ አስገዳጅ የሆነውን የሁለት ሳምንት ለይቶ ማቆያ ጊዜ ጨርሳ ቤቷ ከሄደች ከቀናት በኋላ ነው ቫይረሱ እንደተገኘባት የታወቀው። ከሴትዮዋ ጋር የቅርብ ግንኙነት ያላቸውን እንዲሁም የጎበኘቻቸውን ስፍራዎች ዝርዝር ባለስልጣናቱ እየተከታተሉ ነው ተብሏል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን...
https://www.bbc.com/amharic/news-55785138
amh
health
የዓለም ጤና ድርጅት ክትባቶች ኦሚክሮንን መቋቋም አለባቸው አሉ
የኮሮናቫይረስን ለመከላከል በአሁን ላይ በጥቅም ላይ እየዋሉ የሚገኙት ክትባቶች በአዲሱ ኦሚክሮን የቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ከባድ የጤና እክል እንዳይገጥማቸው መከላከል እንደሚችሉ የዓለም ጤና ድርጅት ከፍተኛ ኃላፊ ተናገሩ። ኃላፊው ይህን ያሉት በደቡብ አፍሪካ በተደረጉ ሙከራዎች ይህ ቫይረስ በተለይ የፋይዘር ክትባትን ማሸነፍ እንደሚችል ምልክቶች አሉ መባላቸውን ተከትሎ ነው። ተመራማሪዎች እንደሚሉት ሰዎች በአዲሱ ቫይረስ ሲያዙ የኮሮናቫይረስ ክትባቶች በሰውነታችን የሚፈጥሩ የመከላከል አቅም በእጅጉ ይቀንሳል።...
https://www.bbc.com/amharic/news-59574506
amh
health
ወላጆቻቸው የሚያጨሱ ልጆች አጫሽ የመሆን ከፍተኛ ዕድል እንዳላቸው ጥናት አመለከተ
ወላጆቻቸው የሚያጨሱ ታዳጊዎች እነሱም አጫሽ የመሆን አራት እጥፍ ዕድል እንዳላቸው በዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት አማካይነት የተሰራ አንድ አዲስ ጥናት አመለከተ። በዚህም ምክንያት ዶክተሮች ሲጋራ የሚያጨሱ ወላጆችንና አሳዳጊዎችን ማጨስ እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። የፀረ ሲጋራ ማጨስ ዘመቻ እንቅስቃሴ እንዳለው ወላጆቻቸው የሚያጨሱ ታዳጊዎች 4.9 በመቶ እነሱም አጫሽ የመሆን ዕድል ሲኖራቸው፣ ወላጆቻቸው የማያጨሱ አቻዎቻቸው ግን የማጨስ ዕድላቸው 1.2 በመቶ ብቻ እንደሆነ አመልክቷል። የዩናይትድ ኪንግደም ብ...
https://www.bbc.com/amharic/59802873
amh
health
ለሁለት ዓመት ድንበሯን ዘግታ የቆየችው ኒው ዚላንድ በሯን ልትከፍት ነው
በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ከሁለት ዓመታት በላይ ድንበሯን ዘግታ የቆየችው ኒው ዚላንድ በስተመጨረሻ በሮቿን ልትከፍት እንደሆነ ይፋ አድርጋለች። ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ አውስትራሊያዊያን ምንም ዓይነት በለይቶ ማቆያ መቆየት ሳያስፈልጋቸው በነፃነት መግባት ይችላሉ። ከ60 ሃገራት የሚመጡ ሙሉ በሙሉ የተከተቡ ሰዎች ደግሞ ከግንቦት ወር ጀምሮ መግባት እንዲችሉ ይፈቀድላቸዋል። ከእነዚህ ሃገራት መካከል ዩናይትድ ስቴትስ እና ዩናይት ኪንግደም ይገኙበታል። ሁሉም ወደ ኒው ዚላንድ የሚመጡ ተጓዦች ከኮቭድ ነፃ ...
https://www.bbc.com/amharic/60761357
amh
health
ኮሮናቫይረስ : አዲሱ የቫይረስ ዝርያ በመላው ዓለም ሊሰራጭ ይችላል ተባለ
አዲሱ የኮሮናቫይረስ ዝርያ በመላው ዓለም ሊሰራጭ ይችላል ተባለ። ኬንት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው የኮሮናቫይረስ ዝርያ በዓለም ላይ በስርጭቱ ቀዳሚው ሊሆን ይችላል ሲሉ የዩናይትድ ኪንግደም የዘረ መል ክትትል መርሃ ግብር ኃላፊ ገልጸዋል። ኃላፊው ፕሮፌሰር ሻሮን ፒኮክ ለቢቢሲ እንደተናገሩት አዲሱ ዝርያ "በአገሪቱ የተሰራጨ" ሲሆን "በመላው ዓለም የመሰራጭ ዕድሎችም" አሉት ብለዋል፡፡ በኬንት የተገኘው ዝርያ ከ50 በላይ በሆኑ አገራት ውስጥ ተሰራጭቶ ይገኛል። የኮሮናቫይረስ ዝርያ በደቡብ ምስራቅ እንግ...
https://www.bbc.com/amharic/news-56027521
amh
health
ኢኳዶር ለሁሉም ዜጎቿ የኮቪድ-19 ክትባትን መውሰድ ግዴታ አደረገች
ኢኳዶር እየተባበሰ የመጣውን የኮሮናቫይረስ ስርጭት ለመግታትና እንደ ኦሚክሮን ያሉ ዝርያዎችን ጉዳት ለመቀነስ በሚል አብዛኛው የኅብረተሰብ ክፍል የኮቪድ-19 ክትባት እንዲወድ የሚያስገድድ መመሪያ አወጣች። የአገሪቱ የጤና ሚኒስቴር እንዳለው አጠቃላይ ሕዝቡን ለመከተብ የሚያስችል የክትባት ክምችት ያለ ሲሆን፣ የሕክምና ማስረጃ ያላቸው ሰዎች ብቻ ያለመከተብ መብት ይኖራቸዋል። ከአገሪቱ አጠቃላይ ሕዝብ ውስጥም ማንኛውም ዕድሜው ከአምስት ዓመት በላይ የሆነ ሰው በሙሉ ክትባቱን ይወስዳል ተብሏል። እስካሁን ድረስ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59778546
amh
health
ጣልያናዊቷ ለ10 ወራት 'ኮማ' ውስጥ ከቆየች በኋላ ነቃች
ጣልያን ውስጥ አንዲት ሴት እራሷን ስታ በሕይወት እና በሞት መካከል ውስጥ ለአስር ወራት ከቆየች በኋላ መንቃቷ ተዘገበ። የ37 ዓመቷ ክሪስቲና ሮሲ ባሳለፍነው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ የሰባት ወር ነፍሰ ጡር እያለች ነበር የልብ ድካም አጋጥሟት እራሷን የሳተችው። ሴት ልጇ ካተሪና በወቅቱ በድንገተኛ ሕክምና እንድትወለድ የተደረገ ሲሆን ክሪስቲና ግን ላለፉት ዘጠኝ ወራት ኮማ ውስጥ ቆይታለች። ለህመሟ ምክንያቱ አንጎሏ ውስጥ የደረሰ ጉዳት ሊሆን ይችላል ተብሎ ነበር። በአሁኑ ሰአት ከኮማ ነቅታ የመጀመሪያ ቃሏን...
https://www.bbc.com/amharic/news-57431084
amh
health
ኮቪድ -19፡ ሰሜን ኮሪያ የኮቪድ ወረርሽኝ በመከሰቱ ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደብ እንዲጣል አዘዘች
ሰሜን ኮሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ በኮቪድ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎ ጥብቅ ብሔራዊ የእንቅስቃሴ ገደብ እንዲጣል አዘዘች። የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን በዋና ከተማዋ ፕዮንግያንግ የኦሚክሮን ወረርሽኝ መከሰቱን የዘገበ ሲሆን ምን ያህል ሰዎች በቫይረሱ እንደተያዙ ግን አልገለጸም። ኮሪያ ሴንትራል ኒውስ ኤጀንሲ ( ኬሲኤንኤ) የወረርሽኙን መከሰት የአገሪቷን የለይቶ ማቆያ ሕግ የጣሰ "ትልቅ አደጋ " ነው ያለ ሲሆን፣ የአገሪቷ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ለብሔራዊው አደጋ ምላሽ ለመስጠት አስቸኳይ ስብሰባ እያደረ...
https://www.bbc.com/amharic/news-61418838
amh
health
የኮቪድ-19 ማጠናከሪያ ክትባት ሆስፒታል የመግባት መጠንን እንደሚቀንስ ጥናት አመለከተ
የኮቪድ-19 ማጠናከሪያ ሦስተኛ ክትባት ሰዎች በቫይረሱ ተይዘው ወደ ሆስፒታል እንዳይገቡ ለመከላከል 88 በመቶ በማገዝ ውጤታማ ነው ሲል የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) የጤና ጥበቃ ኤጀንሲ አዲስ ጥናት አመለከተ። አስትራዜኒካ፣ ፋይዘር ወይም ሞደርና ክትባቶችን ሁለት ዙር የወሰዱ ሰዎች በኦሚክሮን እንዳይያዙ እምብዛም ባይጠብቃቸውም በጠና ከመታመም እንደሚከላከል ጥናቱ ያሳያል። የጤና ኃላፊዎችም ይህ ጥናት ሦስተኛ ዙር ወይም የማጠናከሪያ ክትባት አስፈላጊነትን ያጎላዋል ሲሉ ተናግረዋል። የዩኬ የጤና ፀሐፊው ሳጂ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59845459
amh
health
በዋግ ኽምራ ዞን ሰዎች በረሃብ እየሞቱ መሆኑን ነዋሪዎችና ኃላፊዎች ገለፁ
በአማራ ክልል በሚገኘው የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በርካታ ሰዎች በረሃብ ምክንያት እየሞቱ መሆኑን ከአካባቢው ወደ ባሕር ዳር እና እብናት የመጡ ነዋሪዎች እንዲሁም የአካባቢው ኃላፊዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተስፋዬ ገብሬ የአካባቢው ማኅበረሰብ ላለፉት አራት ወራት ምንም ዓይነት እርዳታ አግኝቶ እንደማያውቅ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ዋና ከተማ ሰቆጣን ጨምሮ ሌሎች የዞኑ ከተሞች በህወሓት አማፂያን ቁጥጥር ሥር በመሆናቸው በብዛት ኑ...
https://www.bbc.com/amharic/news-59161562
amh
health
ኮሮናቫይረስ፡ በአሜሪካ በአንድ ቀን ብቻ 94 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ ተያዙ
በአሜሪካ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 94 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ለማካሄድ ቀናት በቀሯት አሜሪካ በተለያዩ ግዛቶችም በኮሮናቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር አሻቅቧል ተብሏል። በዚህ ሳምንት ሃሙስ 91 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ከፍተኛ ቁጥር ነው በማለት ሪፖርት አድርጋ የነበረቸው አሜሪካ በተከታታይ ባሉት ቀናትም እንዲሁ ከዚህ በላይ ያለው ቁጥር በየቀኑ ተመዝግቧል። ወረርሽኙ ከተከሰተ ጀምሮም እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 9 ሚሊዮን መድረሱን ከጆንስ ሆፕኪንስ ...
https://www.bbc.com/amharic/news-54752422
amh