verse_id stringlengths 8 8 | book stringclasses 66
values | chapter stringclasses 151
values | verse int64 1 176 | verse_text stringlengths 0 495 | text stringlengths 13 511 |
|---|---|---|---|---|---|
000_0008 | ኦሪት ዘፍጥረት | 8 | 17 | ከአንተ ጋር ያሉትን አራዊት ሁሉ፥ ሥጋ ያላቸውን ሁሉ፥ ወፎችንና እንስሶችን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ከአንተ ጋር አውጣቸው፤ በምድር ላይ ይርመስመሱ፥ ይዋለዱ፥ በምድርም ላይ ይብዙ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 8:17] ከአንተ ጋር ያሉትን አራዊት ሁሉ፥ ሥጋ ያላቸውን ሁሉ፥ ወፎችንና እንስሶችን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ከአንተ ጋር አውጣቸው፤ በምድር ላይ ይርመስመሱ፥ ይዋለዱ፥ በምድርም ላይ ይብዙ። |
000_0008 | ኦሪት ዘፍጥረት | 8 | 18 | ኖኅም ልጆቹንና ሚስቱን የልጆቹንም ሚስቶች ይዞ ወጣ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 8:18] ኖኅም ልጆቹንና ሚስቱን የልጆቹንም ሚስቶች ይዞ ወጣ፤ |
000_0008 | ኦሪት ዘፍጥረት | 8 | 19 | አራዊት ሁሉ፥ ተንቀሳቃሾች ሁሉ፥ ወፎችም ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚርመሰምሰው ሁሉ በየዘመዳቸው ከመርከብ ወጡ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 8:19] አራዊት ሁሉ፥ ተንቀሳቃሾች ሁሉ፥ ወፎችም ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚርመሰምሰው ሁሉ በየዘመዳቸው ከመርከብ ወጡ። |
000_0008 | ኦሪት ዘፍጥረት | 8 | 20 | ኖኅም ለእግዚአብሔር መሠውያውን ሠራ፥ ከንጹሕም እንስሳ ሁሉ ከንጹሐን ወፎችም ሁሉ ወሰደ፥ በመሠውያውም ላይ መሥዋዕትን አቀረበ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 8:20] ኖኅም ለእግዚአብሔር መሠውያውን ሠራ፥ ከንጹሕም እንስሳ ሁሉ ከንጹሐን ወፎችም ሁሉ ወሰደ፥ በመሠውያውም ላይ መሥዋዕትን አቀረበ። |
000_0008 | ኦሪት ዘፍጥረት | 8 | 21 | እግዚአብሔርም መልካሙን መዓዛ አሸተተ፤ እግዚአብሔርም በልቡ አለ። ምድርን ዳግመኛ ስለ ሰው አልረግምም፥ የሰው ልብ አሳብ ከታናሽነቱ ጀምሮ ክፉ ነውና፤ ደግሞም ከዚህ ቀድሞ እንዳደረግሁት ሕያዋንን ሁሉ እንደ ገና አልመታም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 8:21] እግዚአብሔርም መልካሙን መዓዛ አሸተተ፤ እግዚአብሔርም በልቡ አለ። ምድርን ዳግመኛ ስለ ሰው አልረግምም፥ የሰው ልብ አሳብ ከታናሽነቱ ጀምሮ ክፉ ነውና፤ ደግሞም ከዚህ ቀድሞ እንዳደረግሁት ሕያዋንን ሁሉ እንደ ገና አልመታም። |
000_0008 | ኦሪት ዘፍጥረት | 8 | 22 | በምድር ዘመን ሁሉ መዝራትና ማጨድ፥ ብርድና ሙቀት፥ በጋና ክረምት፥ ቀንና ሌሊት አያቋርጡም። a | [ኦሪት ዘፍጥረት 8:22] በምድር ዘመን ሁሉ መዝራትና ማጨድ፥ ብርድና ሙቀት፥ በጋና ክረምት፥ ቀንና ሌሊት አያቋርጡም። a |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 1 | እግዚአብሔርም ኖኅንና ልጆቹን ባረካቸው እንዲህም አላቸው። ብዙ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:1] እግዚአብሔርም ኖኅንና ልጆቹን ባረካቸው እንዲህም አላቸው። ብዙ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 2 | አስፈሪነታችሁና አስደንጋጭነታችሁ በምድር አራዊት፥ በሰማይም ወፎች፥ በምድር ላይ በሚንቀሳቀሱትም፥ በባሕር ዓሦችም ሁሉ ላይ ይሁን፤ እነርሱም በእጃችሁ ተሰጥተዋል። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:2] አስፈሪነታችሁና አስደንጋጭነታችሁ በምድር አራዊት፥ በሰማይም ወፎች፥ በምድር ላይ በሚንቀሳቀሱትም፥ በባሕር ዓሦችም ሁሉ ላይ ይሁን፤ እነርሱም በእጃችሁ ተሰጥተዋል። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 3 | ሕይወት ያለው ተንቀሳቃሽ ሁሉ መብል ይሁናችሁ፤ ሁሉን እንደ ለመለመ ቡቃያ ሰጠኋችሁ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:3] ሕይወት ያለው ተንቀሳቃሽ ሁሉ መብል ይሁናችሁ፤ ሁሉን እንደ ለመለመ ቡቃያ ሰጠኋችሁ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 4 | ነገር ግን ነፍሱ ደሙ ያለችበትን ሥጋ አትብሉ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:4] ነገር ግን ነፍሱ ደሙ ያለችበትን ሥጋ አትብሉ፤ |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 5 | ነፍሳችሁ ያለችበትን ደማችሁን በእርግጥ እሻዋለሁ፤ ከአራዊት ሁሉ እጅ እሻዋለሁ፤ ከሰውም እጅ፥ ከሰው ወንድም እጅ፥ የሰውን ነፍስ እሻለሁ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:5] ነፍሳችሁ ያለችበትን ደማችሁን በእርግጥ እሻዋለሁ፤ ከአራዊት ሁሉ እጅ እሻዋለሁ፤ ከሰውም እጅ፥ ከሰው ወንድም እጅ፥ የሰውን ነፍስ እሻለሁ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 6 | የሰውን ደም የሚያፈስስ ሁሉ ደሙ ይፈስሳል፤ ሰውን በእግዚአብሔር መልክ ፈጥሮታልና። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:6] የሰውን ደም የሚያፈስስ ሁሉ ደሙ ይፈስሳል፤ ሰውን በእግዚአብሔር መልክ ፈጥሮታልና። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 7 | እናንተም ብዙ፥ ተባዙ፤ በምድር ላይ ተዋለዱ፥ እርቡባትም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:7] እናንተም ብዙ፥ ተባዙ፤ በምድር ላይ ተዋለዱ፥ እርቡባትም። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 8 | እግዚአብሔርም ለኖኅና ለልጆቹ እንዲህ ብሎ ተናገረ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:8] እግዚአብሔርም ለኖኅና ለልጆቹ እንዲህ ብሎ ተናገረ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 9 | እኔም እነሆ ቃል ኪዳኔን ከእናንተና በኋላ ከሚመጣው ከዘራችሁ ጋር አቆማለሁ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:9] እኔም እነሆ ቃል ኪዳኔን ከእናንተና በኋላ ከሚመጣው ከዘራችሁ ጋር አቆማለሁ፤ |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 10 | ከእናንተ ጋር ላሉትም ሕያው ነፍስ ላላቸው ሁሉ፥ ከእናንተ ጋር ከመርከብ ለወጡት ለወፎች፥ ለእንስሳትም ለምድር አራዊትም ሁሉ፥ ለማንኛውም ለምድር አራዊት ሁሉ ይሆናል። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:10] ከእናንተ ጋር ላሉትም ሕያው ነፍስ ላላቸው ሁሉ፥ ከእናንተ ጋር ከመርከብ ለወጡት ለወፎች፥ ለእንስሳትም ለምድር አራዊትም ሁሉ፥ ለማንኛውም ለምድር አራዊት ሁሉ ይሆናል። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 11 | ቃል ኪዳኔንም ለእናንተ አቆማለሁ፤ ሥጋ ያለውም ሁሉ ዳግመኛ በጥፋት ውኃ አይጠፋም፤ ምድርንም ለማጥፋት ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይሆንም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:11] ቃል ኪዳኔንም ለእናንተ አቆማለሁ፤ ሥጋ ያለውም ሁሉ ዳግመኛ በጥፋት ውኃ አይጠፋም፤ ምድርንም ለማጥፋት ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይሆንም። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 12 | እግዚአብሔርም አለ። በእኔና በእናንተ መካከል፥ ከእናንተም ጋር ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል፥ ለዘላለም የማደርገው የቃል ኪዳን ምልክት ይህ ነው፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:12] እግዚአብሔርም አለ። በእኔና በእናንተ መካከል፥ ከእናንተም ጋር ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል፥ ለዘላለም የማደርገው የቃል ኪዳን ምልክት ይህ ነው፤ |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 13 | ቀስቴን በደመና አድርጌአለሁ፥ የቃል ኪዳኑም ምልክት በእኔና በምድር መካከል ይሆናል። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:13] ቀስቴን በደመና አድርጌአለሁ፥ የቃል ኪዳኑም ምልክት በእኔና በምድር መካከል ይሆናል። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 14 | በምድር ላይ ደመናን በጋረድሁ ጊዜ ቀስቲቱ በደመናው ትታያለች፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:14] በምድር ላይ ደመናን በጋረድሁ ጊዜ ቀስቲቱ በደመናው ትታያለች፤ |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 15 | በእኔና በእናንተ መካከል፥ ሕያው ነፍስ ባለውም ሥጋ ሁሉ መካከል ያለውን ቃል ኪዳኔን አስባለሁ፤ ሥጋ ያለውንም ሁሉ ያጠፋ ዘንድ ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይሆንም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:15] በእኔና በእናንተ መካከል፥ ሕያው ነፍስ ባለውም ሥጋ ሁሉ መካከል ያለውን ቃል ኪዳኔን አስባለሁ፤ ሥጋ ያለውንም ሁሉ ያጠፋ ዘንድ ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይሆንም። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 16 | ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:16] ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 17 | እግዚአብሔርም ኖኅን። በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው ሁሉ መካከል ያቆምሁት የቃል ኪዳን ምልክት ይህ ነው አለው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:17] እግዚአብሔርም ኖኅን። በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው ሁሉ መካከል ያቆምሁት የቃል ኪዳን ምልክት ይህ ነው አለው። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 18 | ከመርከብ የወጡት የኖኅ ልጆችም እነዚህ ናቸው፥ ሴም፥ ካም፥ ያፌት፤ ካምም የከነዓን አባት ነው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:18] ከመርከብ የወጡት የኖኅ ልጆችም እነዚህ ናቸው፥ ሴም፥ ካም፥ ያፌት፤ ካምም የከነዓን አባት ነው። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 19 | የኖኅ ልጆች እነዚህ ሦስቱ ናቸው፤ ከእነርሱም ምድር ሁሉ ተሞላች። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:19] የኖኅ ልጆች እነዚህ ሦስቱ ናቸው፤ ከእነርሱም ምድር ሁሉ ተሞላች። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 20 | ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:20] ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 21 | ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:21] ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 22 | የከነዓን አባት ካምም የአባቱን ዕራቁትነት አየ፥ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:22] የከነዓን አባት ካምም የአባቱን ዕራቁትነት አየ፥ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 23 | ሴምና ያፌትም ሸማ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉ፥ የኋሊትም ሄደው የአባታቸውን ዕራቁትነት አለበሱ፤ ፊታቸውም ወደ ኋላ ነበረ፥ የአባታቸውንም ዕራቁትነት አላዩም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:23] ሴምና ያፌትም ሸማ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉ፥ የኋሊትም ሄደው የአባታቸውን ዕራቁትነት አለበሱ፤ ፊታቸውም ወደ ኋላ ነበረ፥ የአባታቸውንም ዕራቁትነት አላዩም። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 24 | ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:24] ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 25 | እንዲህም አለ። ከነዓን ርጉም ይሁን፤ ለወንድሞቹም የባሪያዎች ባሪያ ይሁን። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:25] እንዲህም አለ። ከነዓን ርጉም ይሁን፤ ለወንድሞቹም የባሪያዎች ባሪያ ይሁን። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 26 | እንዲህም አለ። የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:26] እንዲህም አለ። የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 27 | እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር፤ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:27] እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር፤ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 28 | ኖኅም ከጥፋት ውኃ በኋላ ሦስት መቶ አምሳ ዓመት ኖረ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:28] ኖኅም ከጥፋት ውኃ በኋላ ሦስት መቶ አምሳ ዓመት ኖረ። |
000_0009 | ኦሪት ዘፍጥረት | 9 | 29 | ኖኅም የኖረበት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ አምሳ ዓመት ሆነ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 9:29] ኖኅም የኖረበት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ አምሳ ዓመት ሆነ፤ ሞተም። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 1 | የኖኅ ልጆች የሴም የካም የያፌት ትውልድ ይህ ነው፤ ከጥፋት ውኃም በኋላ ልጆች ተወለዱላቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:1] የኖኅ ልጆች የሴም የካም የያፌት ትውልድ ይህ ነው፤ ከጥፋት ውኃም በኋላ ልጆች ተወለዱላቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 2 | የያፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዴ፥ ያዋን፥ ይልሳ፥ ቶቤል፥ ሞሳሕ፥ ቴራስ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:2] የያፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዴ፥ ያዋን፥ ይልሳ፥ ቶቤል፥ ሞሳሕ፥ ቴራስ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 3 | የጋሜርም ልጆች አስከናዝ፥ ሪፋት፥ ቴርጋማ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:3] የጋሜርም ልጆች አስከናዝ፥ ሪፋት፥ ቴርጋማ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 4 | የያዋንም ልጆች ኤሊሳ፥ ተርሴስ፥ ኪቲም፥ ሮድኢ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:4] የያዋንም ልጆች ኤሊሳ፥ ተርሴስ፥ ኪቲም፥ ሮድኢ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 5 | ከእነዚህም የአሕዛብ ደሴቶች ሁሉ በየምድራቸው በየቋንቋቸው በየነገዳቸው በየሕዝባቸው ተከፋፈሉ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:5] ከእነዚህም የአሕዛብ ደሴቶች ሁሉ በየምድራቸው በየቋንቋቸው በየነገዳቸው በየሕዝባቸው ተከፋፈሉ። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 6 | የካምም ልጆች ኩሽ፥ ምጽራይም፥ ፉጥ፥ ከነዓን ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:6] የካምም ልጆች ኩሽ፥ ምጽራይም፥ ፉጥ፥ ከነዓን ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 7 | የኩሽም ልጆች ሳባ፥ ኤውላጥ፥ ሰብታ፥ ራዕማ፥ ሰበቃታ ናቸው። የራዕማ ልጆችም ሳባ፥ ድዳን ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:7] የኩሽም ልጆች ሳባ፥ ኤውላጥ፥ ሰብታ፥ ራዕማ፥ ሰበቃታ ናቸው። የራዕማ ልጆችም ሳባ፥ ድዳን ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 8 | ኩሽም ናምሩድን ወለደ፤ እርሱም በምድር ላይ ኃያል መሆንን ጀመረ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:8] ኩሽም ናምሩድን ወለደ፤ እርሱም በምድር ላይ ኃያል መሆንን ጀመረ። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 9 | እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ ነበረ፤ ስለዚህም። በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ እንደ ናምሩድ ተባለ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:9] እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ ነበረ፤ ስለዚህም። በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ እንደ ናምሩድ ተባለ። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 10 | የግዛቱም መጀመሪያ በሰናዖር አገር ባቢሎን፥ ኦሬክ፥ አርካድ፥ ካልኔ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:10] የግዛቱም መጀመሪያ በሰናዖር አገር ባቢሎን፥ ኦሬክ፥ አርካድ፥ ካልኔ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 11 | አሦርም ከዚያች አገር ወጣ፤ ነነዌን፥ የረሆቦትን ከተማ፥ ካለህን፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:11] አሦርም ከዚያች አገር ወጣ፤ ነነዌን፥ የረሆቦትን ከተማ፥ ካለህን፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 12 | በነነዌና በካለህ መካከልም ሬሴንን ሠራ፤ እርስዋም ታላቂቱ ከተማ ናት። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:12] በነነዌና በካለህ መካከልም ሬሴንን ሠራ፤ እርስዋም ታላቂቱ ከተማ ናት። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 13 | ምጽራይምም ሉዲምን፥ ዐናሚምን፥ ላህቢምን፥ ነፍታሌምን፥ ፈትሩሲምን፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:13] ምጽራይምም ሉዲምን፥ ዐናሚምን፥ ላህቢምን፥ ነፍታሌምን፥ ፈትሩሲምን፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 14 | ከእነርሱ የፍልስጥኤም ሰዎች የወጡባቸውን ከስሉሂምን፥ ቀፍቶሪምንም ወለደ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:14] ከእነርሱ የፍልስጥኤም ሰዎች የወጡባቸውን ከስሉሂምን፥ ቀፍቶሪምንም ወለደ። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 15 | ከነዓንም የበኵር ልጁን ሲዶንን፥ ኬጢያውያንንም፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:15] ከነዓንም የበኵር ልጁን ሲዶንን፥ ኬጢያውያንንም፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 16 | ኢያቡሳውያንንም፥ አሞራውያንንም፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:16] ኢያቡሳውያንንም፥ አሞራውያንንም፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 17 | ጌርጌሳውያንንም፥ ኤዊያውያንንም፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:17] ጌርጌሳውያንንም፥ ኤዊያውያንንም፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 18 | ዐሩኬዎንንም፥ ሲኒንም፥ አራዴዎንንም፥ ሰማሪዎንንም፥ አማቲንም ወለደ። ከዚህም በኋላ የከነዓናውያን ነገድ ተበተኑ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:18] ዐሩኬዎንንም፥ ሲኒንም፥ አራዴዎንንም፥ ሰማሪዎንንም፥ አማቲንም ወለደ። ከዚህም በኋላ የከነዓናውያን ነገድ ተበተኑ። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 19 | የከነዓናውያንም ወሰን ከሲዶን አንሥቶ ወደ ጌራራ በኩል ሲል እስከ ጋዛ ድረስ ነው፤ ወደ ሰዶምና ወደ ገሞራ፥ ወደ አዳማና ወደ ሰቦይም በኩልም ሲል እስከ ላሣ ድረስ ነው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:19] የከነዓናውያንም ወሰን ከሲዶን አንሥቶ ወደ ጌራራ በኩል ሲል እስከ ጋዛ ድረስ ነው፤ ወደ ሰዶምና ወደ ገሞራ፥ ወደ አዳማና ወደ ሰቦይም በኩልም ሲል እስከ ላሣ ድረስ ነው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 20 | የካም ልጆች በየነገዳቸውና በየቋንቋቸው፥ በየምድራችውና በየሕዝባቸው እነዚህ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:20] የካም ልጆች በየነገዳቸውና በየቋንቋቸው፥ በየምድራችውና በየሕዝባቸው እነዚህ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 21 | ለሴምም ደግሞ ልጆች ተወለዱለት፤ እርሱም የያፌት ታላቅ ወንድምና የዔቦር ልጆች ሁሉ አባት የሆነ ነው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:21] ለሴምም ደግሞ ልጆች ተወለዱለት፤ እርሱም የያፌት ታላቅ ወንድምና የዔቦር ልጆች ሁሉ አባት የሆነ ነው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 22 | የሴምም ልጆች ኤላም፥ አሦር፥ አርፋክስድ፥ ሉድ፥ አራም ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:22] የሴምም ልጆች ኤላም፥ አሦር፥ አርፋክስድ፥ ሉድ፥ አራም ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 23 | የአራምም ልጆች ዑፅ፥ ሁል፥ ጌቴር፥ ሞሶሕ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:23] የአራምም ልጆች ዑፅ፥ ሁል፥ ጌቴር፥ ሞሶሕ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 24 | አርፋክስድም ቃይንምን ወለደ፤ ቃይንምም ሳላን፥ ሳላም ዔቦርን ወለደ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:24] አርፋክስድም ቃይንምን ወለደ፤ ቃይንምም ሳላን፥ ሳላም ዔቦርን ወለደ። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 25 | ለዔቦርም ሁለት ልጆች ተወለዱለት፤ የአንደኛው ስሙ ፋሌቅ ነው፥ ምድር በዘመኑ ተከፍላለችና፤ የወንድሙም ስም ዮቅጣን ነው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:25] ለዔቦርም ሁለት ልጆች ተወለዱለት፤ የአንደኛው ስሙ ፋሌቅ ነው፥ ምድር በዘመኑ ተከፍላለችና፤ የወንድሙም ስም ዮቅጣን ነው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 26 | ዮቅጣንም ኤልሞዳድን፥ ሣሌፍንም፥ ሐስረሞትንም፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:26] ዮቅጣንም ኤልሞዳድን፥ ሣሌፍንም፥ ሐስረሞትንም፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 27 | ያራሕንም፥ ሀዶራምንም፥ አውዛልንም፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:27] ያራሕንም፥ ሀዶራምንም፥ አውዛልንም፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 28 | ደቅላንም፥ ዖባልንም፥ አቢማኤልንም፥ | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:28] ደቅላንም፥ ዖባልንም፥ አቢማኤልንም፥ |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 29 | ሳባንም፥ ኦፊርንም፥ ኤውላጥንም፥ ዩባብንም ወለደ፤ እነዚህ ሁሉ የዮቅጣን ልጆች ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:29] ሳባንም፥ ኦፊርንም፥ ኤውላጥንም፥ ዩባብንም ወለደ፤ እነዚህ ሁሉ የዮቅጣን ልጆች ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 30 | ስፍራቸውም ከማሴ አንሥቶ ወደ ስፋር ሲል እስከ ምሥራቅ ተራራ ድረስ ነው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:30] ስፍራቸውም ከማሴ አንሥቶ ወደ ስፋር ሲል እስከ ምሥራቅ ተራራ ድረስ ነው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 31 | የሴም ልጆች በየነገዳቸውና በየቋንቋቸው፥ በየምድራቸውና በየሕዝባቸው እነዚህ ናቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:31] የሴም ልጆች በየነገዳቸውና በየቋንቋቸው፥ በየምድራቸውና በየሕዝባቸው እነዚህ ናቸው። |
000_0010 | ኦሪት ዘፍጥረት | 10 | 32 | የኖኅ የልጆቹ ነገዶች እንደ ትውልዳቸው በየሕዝባቸው እነዚህ ናቸው። አሕዛብም ከጥፋት ውኃ በኋላ በምድር ላይ ከእነዚህ ተከፋፈሉ። a | [ኦሪት ዘፍጥረት 10:32] የኖኅ የልጆቹ ነገዶች እንደ ትውልዳቸው በየሕዝባቸው እነዚህ ናቸው። አሕዛብም ከጥፋት ውኃ በኋላ በምድር ላይ ከእነዚህ ተከፋፈሉ። a |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 1 | ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:1] ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 2 | ከምሥራቅም ተነሥተው በሄዱ ጊዜ በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:2] ከምሥራቅም ተነሥተው በሄዱ ጊዜ በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 3 | እርስ በርሳቸውም። ኑ፥ ጡብ እንሥራ፥ በእሳትም እንተኵሰው ተባባሉ። ጡቡም እንደ ድንጋይ ሆነላቸው፤ የምድርም ዝፋት እንደ ጭቃ ሆነችላቸው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:3] እርስ በርሳቸውም። ኑ፥ ጡብ እንሥራ፥ በእሳትም እንተኵሰው ተባባሉ። ጡቡም እንደ ድንጋይ ሆነላቸው፤ የምድርም ዝፋት እንደ ጭቃ ሆነችላቸው። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 4 | እንዲህም። ኑ ለእኛ ከተማና ራሱ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንሥራ፤ በምድር ላይ ሳንበተንም ስማችንን እናስጠራው አሉ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:4] እንዲህም። ኑ ለእኛ ከተማና ራሱ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንሥራ፤ በምድር ላይ ሳንበተንም ስማችንን እናስጠራው አሉ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 5 | እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:5] እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 6 | እግዚአብሔርም አለ። እነሆ፥ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፥ ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት አይከለከሉም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:6] እግዚአብሔርም አለ። እነሆ፥ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፥ ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት አይከለከሉም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 7 | ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:7] ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 8 | እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተዉ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:8] እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተዉ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 9 | ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ፥ እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ ሁሉ ደባልቋልና፤ ከዚያም እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እነርሱን በትኖአቸዋል። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:9] ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ፥ እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ ሁሉ ደባልቋልና፤ ከዚያም እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እነርሱን በትኖአቸዋል። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 10 | የሴም ትውልድ ይህ ነው። ሴም የመቶ ዓመት ሰው ነበረ፥ አርፋክስድንም ከጥፋት ውኃ በኋላ በሁለተኛው ዓመት ወለደ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:10] የሴም ትውልድ ይህ ነው። ሴም የመቶ ዓመት ሰው ነበረ፥ አርፋክስድንም ከጥፋት ውኃ በኋላ በሁለተኛው ዓመት ወለደ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 11 | ሴምም አርፋክስድን ከወለደ በኋላ አምስት መቶ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:11] ሴምም አርፋክስድን ከወለደ በኋላ አምስት መቶ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 12 | አርፋክስድም መቶ ሠላሳ አምስት ዓመት ኖረ፥ ቃይንምንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:12] አርፋክስድም መቶ ሠላሳ አምስት ዓመት ኖረ፥ ቃይንምንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 13 | አርፋክስድም ቃይንምን ከወለደ በኋላ አራት መቶ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። ቃይንምም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ሳላንም ወለደ፤ ቃይንምም ሳላን ከወለደ በኋላ ሶስት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:13] አርፋክስድም ቃይንምን ከወለደ በኋላ አራት መቶ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። ቃይንምም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ሳላንም ወለደ፤ ቃይንምም ሳላን ከወለደ በኋላ ሶስት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 14 | ሳላም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ዔቦርንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:14] ሳላም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ዔቦርንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 15 | ሳላም ዔቦርን ከወለደ በኋላ ሦስት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:15] ሳላም ዔቦርን ከወለደ በኋላ ሦስት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 16 | ዔቦርም መቶ ሠላሳ አራት ዓመት ኖረ፥ ፋሌቅንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:16] ዔቦርም መቶ ሠላሳ አራት ዓመት ኖረ፥ ፋሌቅንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 17 | ዔቦርም ፋሌቅን ከወለደ በኋላ አራት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:17] ዔቦርም ፋሌቅን ከወለደ በኋላ አራት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 18 | ፋሌቅም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ራግውንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:18] ፋሌቅም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ራግውንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 19 | ራግውንም ከወለደ በኋላ ፋሌቅ ሁለት መቶ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:19] ራግውንም ከወለደ በኋላ ፋሌቅ ሁለት መቶ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 20 | ራግውም መቶ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ፥ ሴሮሕንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:20] ራግውም መቶ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ፥ ሴሮሕንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 21 | ራግውም ሴሮሕን ከወለደ በኋላ ሁለት መቶ ሰባት ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:21] ራግውም ሴሮሕን ከወለደ በኋላ ሁለት መቶ ሰባት ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 22 | ሴሮሕም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ናኮርንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:22] ሴሮሕም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ናኮርንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 23 | ናኮርንም ከወለደ በኋላ ሴሮሕ ሁለት መቶ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:23] ናኮርንም ከወለደ በኋላ ሴሮሕ ሁለት መቶ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 24 | ናኮርም መቶ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፥ ታራንም ወለደ፤ | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:24] ናኮርም መቶ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፥ ታራንም ወለደ፤ |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 25 | ታራንም ከወለደ በኋላ ናኮር መቶ ሃያ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:25] ታራንም ከወለደ በኋላ ናኮር መቶ ሃያ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፥ ወንዶችንም ሴቶችንም ወለደ፤ ሞተም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 26 | ታራም መቶ ዓመት ኖረ፥ አብራምንና ናኮርን ሐራንንም ወለደ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:26] ታራም መቶ ዓመት ኖረ፥ አብራምንና ናኮርን ሐራንንም ወለደ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 27 | የታራም ትውልድ እነሆ ይህ ነው። ታራ አብራምንና ናኮርን ሐራንንም ወለደ፤ ሐራንም ሎጥን ወለደ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:27] የታራም ትውልድ እነሆ ይህ ነው። ታራ አብራምንና ናኮርን ሐራንንም ወለደ፤ ሐራንም ሎጥን ወለደ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 28 | ሐራንም በተወለደበት አገር በከለዳውያን ዑር በአባቱ በታራ ፊት ሞተ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:28] ሐራንም በተወለደበት አገር በከለዳውያን ዑር በአባቱ በታራ ፊት ሞተ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 29 | አብራምና ናኮርም ሚስቶችን አገቡ፤ የአብራም ሚስት ስምዋ ሦራ ነው፤ የናኮር ሚስት የሐራን ልጅ ሚልካ ናት፤ ሐራንም የሚልካና የዮስካ አባት ነው። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:29] አብራምና ናኮርም ሚስቶችን አገቡ፤ የአብራም ሚስት ስምዋ ሦራ ነው፤ የናኮር ሚስት የሐራን ልጅ ሚልካ ናት፤ ሐራንም የሚልካና የዮስካ አባት ነው። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 30 | ሦራም መካን ነበረች፤ ልጅ አልነበራትም። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:30] ሦራም መካን ነበረች፤ ልጅ አልነበራትም። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 31 | ታራም ልጁን አብራምንና የልጅ ልጁን የሐራንን ልጅ ሎጥን የልጁንም የአብራምን ሚስት ምራቱን ሦራን ወሰደ፤ ከእርሱም ጋር ወደ ከነዓን ምድር ይሄዱ ዘንድ ከከለዳውያን ዑር ወጡ፤ ወደ ካራንም መጡ፥ ከዚያም ተቀመጡ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:31] ታራም ልጁን አብራምንና የልጅ ልጁን የሐራንን ልጅ ሎጥን የልጁንም የአብራምን ሚስት ምራቱን ሦራን ወሰደ፤ ከእርሱም ጋር ወደ ከነዓን ምድር ይሄዱ ዘንድ ከከለዳውያን ዑር ወጡ፤ ወደ ካራንም መጡ፥ ከዚያም ተቀመጡ። |
000_0011 | ኦሪት ዘፍጥረት | 11 | 32 | የታራም ዕድሜ ሁለት መቶ አምስት ዓመት ሆነ፤ ታራም በካራን ሞተ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 11:32] የታራም ዕድሜ ሁለት መቶ አምስት ዓመት ሆነ፤ ታራም በካራን ሞተ። |
000_0012 | ኦሪት ዘፍጥረት | 12 | 1 | እግዚአብሔርም አብራምን አለው። ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ። | [ኦሪት ዘፍጥረት 12:1] እግዚአብሔርም አብራምን አለው። ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.