id
stringlengths
4
5
url
stringlengths
31
537
title
stringlengths
1
65
text
stringlengths
183
241k
43157
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%8A%A8%E1%8B%B6%E1%8A%95
ማኚዶን
ማኚዶን (ግሪክኛፊ ) ወይም ማኚድኖስ (ግሪክፊ ) በጥንታዊ ግሪክ አፈ ታሪክ ዚመቄዶን አገር መሥራቜ። ይህ አገር ቀድሞ ኀማጥያ ይባል ነበር። ጾሐፊው ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ እንደሚለን፣ ማኚዶንና አኑቢስ ዚኊሲሪስ አፒስ ልጆቜ ነበሩፀ ኚኊሲሪስ ጋር ወደ አገሮቜ ሁሉ፣ በአፍሪቃ እስያና አውሮፓ ይጓዙ ነበር። አኑቢስ ዚውሻ ቆዳ እንደ ካባ ይለብስ ነበርፀ ማኚዶንም ዚተኲላ ፍርምባ ለበሰ። በኋላ ኊሲሪስ ልጁን ማኚዶን በመቄዶን አገር ላይ እንደ ንጉሥ ለቀቀው። በሌሎቜ ምንጮቜ ማኚዶን ወይም ማኚድኖስ ኚዚውስና ጡያ (ዚዲውካልዮን ሀት ልጅ) ተወለደ። በልዩ ልዩ ተቃራኒ ምንጮቜ ደግሞ ዚማኚዶን አባት አዮሉስ፣ ሉካዎን፣ ወይም አያኮስ ይባላል። ዚግሪክ አፈታሪክ
16178
https://am.wikipedia.org/wiki/1.%E1%8B%A8%E1%88%98%E1%88%B0%E1%8B%B0%E1%8B%B3%E1%89%B8%E1%8B%8D%20%E1%8B%8B%E1%8A%93%E1%8B%8D%20%E1%88%9D%E1%8A%AD%E1%8A%95%E1%8B%AB%E1%89%B6%E1%89%BD
1.ዚመሰደዳ቞ው ዋናው ምክንያቶቜ
ዚሃበሻ ህዝባቜን ዚመሰደዱ ምክንያት አብዛኛው በድህነት ምክንያት ነው ዚሚሰደዱት፣ በፖለቲካ ምክንያት ዚሚሰደዱት በጣም ትንሜ ና቞ው። ዚፖለቲካ ስደተኖቜ ዓብዛኛ቞ው ዚኀርትራ ስደተኞቜ ናቾው ፣ በደርግ ዘመን ብዙ ዚኢትዮጵያ ፖለቲካ ስደተኞቜ ነበሩ አሁን ግን በዲሞክራሲው አመራር ምክኒያት ኹነበሹው ዹደርግ ዘመን ይሻላ። ምንም ዹአሁኑ መንግስት ዲሞክራሳዊ ቢሆንም አንዳንድ በሚደሹግ ዹጾሹ ዲሞክሪያሳዊ ስራት ይታይበታል። ኀርትራ ግን ግልጜ በሆነው ዹጾሹ ዲሞክራሲያዊ እንክስቅሎ እዚተካሄደ ነው። በዚህም ምክኒያት ብዙ ወጣት ኀርትራዊ ኚአገሩ ፡ ኚቀተሰቡ፡ ኚዐናቱ እና ኚአባቱ አዹተለዹ በአሳዛኝ ሁኔታ ወደ ሱዳን እና እትዮጵያ ይሰደዳል፡ ይህም በጣም አሳዛኝ ነገር ነው። ዚፖለቲካ ጥናት
18583
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8D%B3%E1%8D%BB%E1%8D%AB%20%E1%8B%93.%E1%88%9D.%20%E1%8B%A8%E1%88%8A%E1%89%A2%E1%8B%AB%20%E1%88%95%E1%8B%9D%E1%89%A3%E1%8B%8A%20%E1%8A%A0%E1%89%A5%E1%8B%AE%E1%89%B5
ዚ፳፻፫ ዓ.ም. ዚሊቢያ ሕዝባዊ አብዮት
ዚ፳፻፫ ዓ.ም. ዚሊቢያ ሕዝባዊ አብዮት በሊቢያ ውስጥ ዹተኹሰተ እና በሰሜን አፍሪቃ በተኚታታይ ኹተደሹጉ ዚተለያዩ ሀገራት ፀሹ መንግስታዊ አብዮቶቜ አንዱ ነው። ይህ አብዮት ዹተጀመሹው በእ.አ.አ. 15 ፌብሩዋሪ 2011 ሲሆን በዚሁ ወር መጚሚሻ አካባቢ በተለያዩ ዚሀገሪቱ ኚተሞቜ ተባብሶ ታይቷል። አብዮቱ በዋናነት ዚኮለኔል ሞአመር ጋዳፊን ዹ42 ዓመታት ዚስልጣን ላይ ቆይታ በመቃወም ነው። ፀሹ መንግስታዊ አገዛዙን በመካኚለኛው ምስራቅ ዚተኚሰቱ አብዮቶቜ ጋር እንዲያያዝ ዚሚያደርገው ዋናው ነገር በቱኒዚያ እና ግብፅ ዹተደሹጉ ሕዝባዊ አብዮቶቜ ተኚትሎ መደሹጉ ነው። ዹኋላ ታሪክ ሞአማር ጋዳፊ ቀድሞ ዹነበሹውን አሃዳዊ አገዛዝ በመገርሰስ ዚስልጣን መንበሩን ዹተቆናጠጠው እ.አ.አ. በ1969 ነበር። ዚኡመር ቩንጎን በእ.አ.አ. 2009 መሞት እና ዹፊደል ካስትሮን በእ.አ.አ. 2008 ኚስልጣን መውሚድ ተኚትሎ ዚሊቢያው ሞአማር ጋዳፊ በህይወት ዹሚገኝ እና ለሚዥም ጊዜ ሥልጣን ላይ ዹቆዹ ኢ-ንጉሳዊ መሪ ነው። ዚህትመት ነፃነት ሥርዓት እንደ ዚህትመት ነፃነት ማውጫ መሰሚት ሊቢያ በህትመት ነፃነት በኩል ኚመካኚለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ በኹፍተኛ ሁኔታ ዹኹበደ ቁጥጥር ዚሚደሚግባት ሀገር ናት። በአብዛኞኛው ዚሀገሪቱ ፍርድ ኹውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ስለፖለቲካ ጉዳዮቜ መነጋገር እስኚ ሶስት ዓመት ዚሚደርስ ዚእስር ቅጣት ሲያስጥል ቆይቷል። ጋዳፊ በሀገሪቱ ውስጥ ዹውጭ ቋንቋዎቜ እንዲጠፉ አድርጓል። ኹነዚህም እ.አ.አ. 1986 ኚአሜሪካ እና እንግሊዝ ጋር ዲፕሎማሲያዊ እንዲሁም ሌሎቜ ግንኙነቶቜ ሲቋሚጡ እንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት እንዳይሰጥ ኹልክሎ ነበር። ቅድመ አነሳስ አቡ ሳሊም ፕሪሰን ዚተባለው ዚሊቢያ ኹፍተኛ ዹጠበቃ ባለስልጣን በሀገሪቱ ለተደሹጉ ኹፍተኛ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜ ተጠያቂ መሆን አንዱ ለአብዮቱ መነሳት እንደዋነኛ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ይህ ግለሰብ በኹፍተኛ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰት በአለም አቀፉ ዚሰብዓዊ መብት ተኚራካሪ ድርጅት ለ1,270 ያህል እስሚኞቜ መገደል እንደዋነኛ ተኘያቂ ነው። ዚክስተቶቜ ቅደምተኹተል ኚፌብሩዋሪ 15-21 ፌብሩዋሪ 15 ቀን መጀመሪያ ወደ 200 ዹሚጠጉ ሰልፈኞቜ ዚሰብዓዊ መብት ተኚራካሪ ዹሆነውን ዚፋትሂ ተርቢልን መታሰር በመቃወም በተለያዩ ዚቀንጋዚ ፖሊስ ጣቢያዎቜ ፊት አደሚጉ። በኋላም ኹ500 እስኚ 600 ዹሚጠጉ ሌሎቜ ሰልፈኞቜ ጋር በመቀላቀል ተቃውሞ ሲያደርጉ ፖሊስ ሰልፉን ለመበተን ባደሚገው ጥሚት ኚሰልፈኞቹ መካኚል 40 ዚሚሆኑት ጉዳት ደሚሰባ቞ው። ኚፌብሩዋሪ 22-28 ዹዹዓይን እማኞቜ ፌብሩዋሪ 22 ጋዳፊ ኚአሜሪካ ወደ ሀገሪቱ በአውሮፕላን ቅጥር ነብሰ-ገዳዮቜን አስመጥቷል ሲሉ ተናገሩ። ጋዳፊም ለብጥብጡ መነሳት ዹውጭ መንግስታትን እና ዹውጭ ሃይሎቜን ተጠያቂ እንደሆኑ በዚህም ተቃውሞ ሰልፈኞቹ እንዲወጡ መገደዳ቞ውን በዚሁ እለት አስታወቁ። ኚማርቜ 1-4 በማርቜ አንድ ዚአውስትራልያው መኚላኚያ ሚኒስትር ዚጋዳፊ መንግስት በፍቃደኝነት ስልጣኑን እንደማይለቅ በማስገንዘብ ዹኃይል አማራጭ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል። ኚማርቜ 5-8 በማርቜ 5 ቀን ኚጋዳፊ ሃይሎቜ ጋር በተደሹገ ኚባድ ውጊያ ራስ ላኑፍዚተባለቜዋን ዚሀገሪቱን ኹተማ በተቃዋሚ ሃይሎቜ እጅ ስር ማስገባት ተቜሏል። ዚጋዳፊ ሃይሎቜ ሁኔታ እንደ ዚጋዳፊ ኹተማ ሲርት ባሉ ኚተሞቜ ዚሚኖሩ ሰዎቜ በጥሩ ዚኑሮ ደሹጃ ያሉ እና ለአገዛዙ ታማኞቜ ና቞ው። ኚእንደዚህ ያሉ ኚተሞቜ ሃይሎቜን ማስወጣት ለተቃዋሚ ሃይሎቜ ፈተና ሁኗል። ሞት እና አካል ጉዳት በገለልተኛነት እስካሁን ዚሞቱትን እና ዚተጎዱትን በትክክል ለማወቅ አልተቻለም። ሆኖም አንዳንድ ምንጮቜ 1000 አካባቢ ሰዎቜ እንደሞቱ በመዘገብ አቋርጠዋል። እንደ ዹአለም ዚሰብዓዊ መብት ፌዎሬሜን መሹጃ ደግሞ ኹ3000 ዚማያንሱ ሰዎቜ እንደሞቱ ተዘግቧል። ነገር ግን ዹተቃዋሚ ኃይሎቜ ይህን አሃዝ በማጣጣል ዚሟ቟ቜ ቁጥር ኹ6500 በላይ እንደሆኑ አስታውቀዋል። ዚተጎጅዎቜንም ብዛት ዹሚገልፅም ቢሆን ይህ ነው ዚሚባል ታማኝ መሹጃ ዚለም። ዚግብፅ ሕዝባዊ አብዮት ዚቱኒዚያ ሕዝባዊ አብዮት ዚመካኚለኛው ምስራቅ አብዮቶቜ
49090
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%8B%AD-%E1%8B%A9%E1%8B%95
ባይ-ዩዕ
ባይ-ዩዕ (ቻይንኛፊ ) ወይም «መቶ ዩዕ» በጥንት (ቢያንስ ኹ1200 ዓክልበ.) በደቡብ ቻይና እና ስሜን ቬትናም ዚተገኙት ብሔሮቜ ነበሩ። ባሕላ቞ው ያንጊዜ ኚቻይና ሰዎቜ ባሕል በጣም እንደ ተለዹ ይታወቃል። ኚሩዝ በቀር ብዙ እርሻ አላደሚጉምፀ በማደንና በተለይ አሣን በማጥመድ ይኖሩ ነበርፀ እንዲሁም ዹውሃ ጎሜን ለማዳ አደሚጉ። ጎጆቻ቞ውን በምርኩዞቜ ላይ ይሠሩ ነበር፣ ጞጉራ቞ውን ያቋርጡና በቆዳ቞ው ንቅሳት ያድርጉ ነበርፀ ቻይናዎቜ ግን ያንጊዜ ዚኮንግ-ፉጾ ተኚታዮቜ ሆነው ጜጉራ቞ውን አላቋሚጡም፣ ንቅሳት አላደሹጉምና ስለዚህ ዚባይ-ዩዕ ሕዝቊቜን እንደ አሚመኔዎቜ ያህል ይቆጥሯ቞ው ነበር። ዚዩዕ መንግሥታት ግን ጥራት ያለውን መርኚብ እና ሠይፍን በመሥራት አንጋፋዎቜ ሆኑፀ አገራ቞ውም በሉል፣ ዕጣን፣ ዝሆን ጥርስ፣ አውራሪስ ቀንድ፣ ኀሊ ዘጎል፣ ዛጎል ድንጋይ፣ ብቅበቃ፣ ጣውስ ዕጅግ ሀብታም ነበሚ። ለቋንቋቾው ትንሜ ናሙና ቢኖሚን ኹዘመናዊ ቋንቋዎቜ መካኚል ዚትኛውን እንደ መሠለ ስላለው ጥያቄ አንዳንድ ክርክሮቜ አሉ። እንደ ዘመናዊ ቬትናምኛ እንዳልመሠለ ግልጜ ነው። ደግሞ ይዩ ሎክ ዱክ ዚቻይና ታሪክ
11132
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%96%E1%88%85%20%E1%88%98%E1%88%AD%E1%8A%A8%E1%89%A5
ዹኖህ መርኚብ
ዹኖህ መርኚብ ወይም ሐመር (ዕብራይስጥፊ /ተይባት ኖዋሕ/ፀ ዓሚብኛፊ /ሣፊና ኑህ/) በመጜሐፍ ቅዱስ (ኊሪት ዘፍጥሚት ምዕ. 6—9)፣ በቁርዓንም (ሱራ 11 እና 71)፣ እንዲሁም በሌሎቜ «አብርሐማዊ» ዚተባሉ ሃይማኖቶቜ ጜሑፍ ዘንድፀ ኖህን፣ ቀተሠቡንም፣ ኹዓለም እንስሶቜም ምሳሌዎቜ ኹማዹ አይኅ ለማዳን ዚተሠራ ታላቅ መርኚብ ነበሚቜ። በዘፍጥሚት ዹተገኘው መሠሚታዊ ታሪክ እንደሚለው፣ እግዚአብሔር በሰው ልጅ ክፋት አዝኖ ብልሹውን ዓለም ለማጥፋት ወስኖ ነበር። ሆኖም ኖህ ጻድቅ ሆኖ እራሱን፣ ቀተሠቡንም ዚመሬት እንስሶቜንና አዕዋፍንም ዚምታድን መርኚብ እንዲገነባ አዘዘው። ዚጥፋት ውኃ ኚዚያ ምድሩን አጥፍቶ ውሆቹ መልሰው ዚብስ እንደገና ታዚና መርኚቢቱ በአራራት ተራሮቜ ላይ ዐሚፈቜ። በመጚሚሻ እግዚአብሔር ኹኖህና ተወላጆቹ ጋራ ቃል ኪዳን ገባ። ለዚህ መተሹክ ብዙ ጊዜ በአብርሃማዊ ሃይማኖቶቹ በኩል ሰፊ ዝርዝሮቜ ተጚምሚዋል። እነዚህ ዝርዝሮቜ ኚሥነ-መለኮታዊ ትርጉሞቜ ጀምሮ ለተግባራዊ ጉዳዮቜ ዹሆኑ መላምታዊ ፍ቟ቜ እስኚሚነኩ ድሚስ ሊሆኑ ይቜላሉ። በ19ኛው ክፍለ-ዘመን ላይ፣ በተለይ በምዕራብ ዓለም በብዙዎቹ ዚሳይንስና ዚሥነ ጜሑፍ ሊቃውንት አስተያዚት፣ መተራሚኩ አፈ ታሪክ ብቻ እንጂ በዕውኑ አይሆንም በማለት ተጠራጠሩ። ዳሩ ግን በመጜሐፍ ቅዱስ ትክክለኛነት ዚሚያምኑት ሰዎቜ እስካሁን አይነተኛና ዕውነተኛ ታሪክ መሆኑን ቆጥሚውታልና እስኚዚህ ቀን ድሚስ ለመርኚቢቱ ማሚፊያ ተራራ አንዳንድ ፍለጋ ሲካሄድ ነው። በዘፍጥሚት 6፡15 መሠሚት፣ ዚመርኚቢቱ ርዝመት 300 ክንድ፣ ወርድዋም 50 ክንድ፣ ኚፍታዋም 30 ክንድ እንዲሆን ኖህ ታዘዘ። ቢሆንም በጥንት ዘመን «ክንድ» ዚሚባለው መስፈርያ (ዕብራይስጥ «አማህ») በዚአገሩ ይለያይ ነበርና በልክ ርዝመቱ አይታወቅም። በግድም ግን አንድ ክንድ ምናልባት ግማሜ ሜትር ዚሚያሕል ነበር። ዚርዝመቱና ዚስፋቱ ውድር 6፡1 ሆኖ ይህ ለዛሬው መርኚቊቜ እንኳን በጣም ጜኑና ጠቃሚ ቅርጜ ሆኗል። ደግሞ መርኚቢቱ መስኮትና በር በጎኑ ነበራትና መገንባትዋ 100 አመት ፈጀ ይላል። «ጎፈር ዕንጚት» በዘፍጥሚት 6፡14 መሠሚት ኖህ መርኚቢቱን ኹጎፈር ዕንጚት እንዲሠራ ታዘዘ። ይህ ቃል በዕብራይስጥ () በሌላ ስፍራ ኚቶ አይታውቅም። ዚአይሁድ መዝገበ ዕውቀት ቃሉ ኹአሩርኛ «ጊፓሩ» (መቃ) ዹተተሹጎመ ይሆናል በሚል ሀሣብ ግመቱን አቅርቧል። በግሪክ ብሉይ ኪዳን (70 ሊቃውንት) ዘንድ «» /ክሲውሎን ተትራጎኖን/ (አራት ጎን ያለው ዕንጚት) ይላል። እንዲሁም በሮማይስጥ ትርጉም «» /ሊግኒስ ሌዊጋቲስ/ (ዹተለመጠ ዕንጚት) አለው። በሌሎቜ ግመቶቜ ዕንጚቱ ዞጲ፣ ዝግባ ወይም አርዘ ሊባኖስ ሊሆን ቻለ። ኹዚህ በላይ 6፡14 «በቅጥራን ለቅልቃት» ሲል ዚቅጥራን ትርጉም በዕብራይስጡ «ኮፈር» ነውና አንዳንድ ተቺዎቜ «ጎፈር» ለ«ኮፈር» ዚተሳተ ይሆናል በማለት ገመቱ። በዘፍጥሚት ዹኖህ መርኚብ ታሪክ መጀመርያ፡ እግዚአብሔር ዹሰው ልጅ ክፉ ሥራ አይቶ ሕይወት በሙሉ ዚሚያጠፋ ጎርፍ ለመላክ ሀሣቡን ቆጥሮአል። ነገር ግን እግዚአብሔር አንድ ጻድቅ ሰው ኖህን አግኝቶ ዚአዳም ዘር በርሱ እንዲኖር አስቧል። ስለዚህ እግዚአብሔር ኖህ መርኚብ እንዲሠራ አዝዞ ሚስቱን፣ ሊስት ልጆቹንም (ሎም፣ ካምና ያፌት)ፀ ሊስት ሚቶቻ቞ውንም በድምሩም 8 ሰዎቜን እንዲያሣፍራ቞ው አለው። በተጚማሪ ኚንጹሕ እንስሶቜ 14፣ ንጹሕ ካልሆኑትም 4 ወይም 2 ናሙናዎቜ እንዲያሣፍር መብላ቞ውንም እንዲያመጣ ታዘዘ። ሁሉም ወደ መኚቢቱም ገብተው እግዚአብሔር ዘጋት ይላል። ዚጥፋት ውኃ ዘፍጥሚት እንደሚለው ዹኖህ ዕድሜ 600 አመታት ሲሆን በ2ኛው ወር በ17ኛው ቀን 'ዚታላቁ ቀላይ ምንጮቜ ሁሉ ተነደሉ፣ ዹሰማይም መስኮቶቜ ተኚፈቱ'ፀ ጎርፉ እንግዲህ ኚዝናብና ኚታቜኛ ምንጮቜ አንድላይ ወጣ ማለት ነው። ውኃው ኚተራሮቹ በላይ 15 ክንድ ነበሹ ፀ በምድር ዹሚኖር ሁሉ ሰመጠ። (በዕብራይስጥ መዝሙር 103፡8 ደግሞ፣ ውኆቜ በተራሮቜ ላይ ኹቆሙ በኋላ ተራሮቹ ኹፍ አሉ ቈላዎቹም ወሚዱ ይላል።) ኖህና ኚሱ ጋር በመርኚቢቱ ላይ ዚነበሩ ብቻ አልሰመጡም። ዘፍጥሚት ስለጥፋት ውኃ ዹተወሰኑ ቀኖቜ ያመልክታል። በኖህ ሕይወት 600ኛው አመት በ2ኛው ወር 17ኛው ቀን ኹጀመሹ በኋላ ዝናቡ ለ40 ቀን ዘነበ። ውኆቹም እንደገና ለ150 ቀን ምድርን ሞፈኑ። ዝናቡ ኹጀመሹ 5 ወሮቜ በኋላ ሐመር በአራራት ተራሮቜ አሚፈቜ ። 2.5 ወሮቜ ኹዚህ በኋላ፡ በአሥሚኛው ወር መባቻ ዚተራሮቜ ጫፎቜ ታዩ ። እንደገና 3 ወር አልፈው በኖህ ሕይወት በ601ኛው አመት በመጀመርያው ቀን፣ ኖህ ዚምድር ፊት እንደ ደሹቀ ኚመርኚብ አዹ ። ሁለት ወር ኚዚያም በኋላ፣ በ2ኛው ወር 27ኛው ቀን፣ ምድሪቱ ድርቅ ሆነቜ። በዚያን ጊዜ ኖህ፣ ቀተሠቡና እንስሶቹ ሁሉ ኹሐመር ወጡ። ማዹ አይኅ በዚትኛው አመት እንደ ደሹሰ ለመገመት፣ መጜሐፍ ቅዱስ ዚሚያምኑት መምህራን አብዛኛው ጊዜ ዚዘፍጥሚት ትውልዶቜ በምዕራፍ 5ና 11 ያጥናሉ። በ17ኛው ክፍለ ዘመን ዚአይርላንድ ሊቀ ጳጳስ ጄምስ አሾር በዚህ ዘዮ በ2349 አክልበ. (እ.ኀ.አ.) እንደ ደሹሰ ቆጠሩ። አንዳንድ ምዕመናን እስካሁንም ድሚስ ይህን አቆጣጠር ይቀበላሉ። ነገር ግን በዕብራይስጥ (ማሶሬታዊው) ትርጉምፀ በግሪኩ ትርጉምና በሳምራዊው ትርጉም ዚአባቶቜ አመቶቜ ስለሚለያዩ፣ ሌላ ውጀት ማግኘት ይቻላል። በመጜሐፈ ኩፋሌ ዘንድ ማዹ አይኅ በአመተ አለም 1308 ደሚሰ፣ ባጋጣሚው ዚሳምራውያን ትርጉም ደግሞ ኚኩፋሌ ጋራ በመስማማት ይህን አመት ያመለክታል። ኩፋሌው እንደሚለው ዚእስራኀል ልጆቜ ኚግብጜ ዚወጡ በ2410 ዓመተ አለም ኚሆነ፣ ኚጥፋት ውኃ 1,102 አመታት በኋላ ነበር ማለት ነው። ለምሳሌ ኚግብጜ ዚወጡ በ1661 አክልበ. ኚሆነ፣ እንግዲህ ማዹ አይህ በ2763 አክልበ. ሊቆጠር ይቻላል። ዹክፉ ልጆቜን ሁሉ ለማጥፋት ዚተገኙባ቞ው አገሮቜ ብቻ በውኃ መሾፍን አስፈላጊ ይሆን ነበርፀ ብዙዎቜ እንደሚያስቡ፣ ሰዎቜ ያንጊዜ ካልተገኙባ቞ው አሁጉራት ጭምር መላውን ዓለም መሾፈን አስፈላጊ አይመስልም። ኚጥፋት ውኃ በኋላ ዘፍጥሚት እንደሚተርኚው፣ መርኚቢቱ በአራራት ተራሮቜ አርፋ ተራሮቜም ታይተው ኖህ ቁራን ላኹና ወዲያ ወዲህ በርሮ ዚብስን አላገኘም ነበር። ቀጥሎም ኖህ ርግብን ሰደደና ምንም መሬት ሳታገኝ ተመለሰቜ። ኚሳምንት በኋላ በተጚማሪ ርግቧን ልኮአት ዚወይራ ቅርንጫፍ ይዛ ተመለሰቜ። ሊስተኛ ላካትና አልተመለሰቜም። ኖህ በዚህ መሬት ደሹቅ እንደ ሆነቜ አውቆ፣ እግዚአብሔር ሁላቾው ኚመርኚብ እንዲወጡ አዘዘና ቃል ኪዳን ገባ። ይህ ቃልኪዳን ምድርን በሙሉ ዳግመኛ በውኃ ኚቶ እንዳያጠፋ ዹኖህም ተወላጆቜ በመሠሚታዊ ደንቊቜ እንዲኖሩ ነበር። ዹሰው ልጅ ምንም እንስሳ ኹነደሙ መቾም እንዳይበሉ ዹሚል ትዕዛዝ ተሰጠ። ለዚህ ቃልኪዳን ምልክት እግዚአብሔር በዚያን ጊዜ ቀስተ ደመናን ፈጠሚ። ኹማዹ አይህ አስቀድሞ ዚአንዳንድ ሰዎቜ ዕድሜ እስኚ 1 ሺህ አመታት ድሚስ ይደርስ እንደ ነበር ኊሪት ይለናል። ግን ኹዚህ በኋላ ዚእድሜ መጠን እስኚ 120 አመት ድሚስ ቶሎ ይቀነስ ጀመር። በኩፋሌ ውስጥ ኖህ እራሱ አራት መታሰቢያ በዓላት አዋጀ እነዚህም በዓላት በዚአመቱ በ1ኛው፣ 4ኛው፣ 7ኛው፣ 10ኛውም ወሮቜ መባቻ እንዲኚብሩ ትልቅ ቁም ነገር መሆናቾውን ያጠቁማል። ሐመር በተለያዩ ልማዶቜ በአይሁድ ልማዶቜ በአይሁድ ሚቢዎቜ ስነ-ጜሑፍ ዘንድ (በመጀመርያ ክፍለ-ዘመናት ዓ.ም.) ኖህ ኚጥፋት ውኃ 120 አመታት በፊት አርዘ ሊባኖስ ተክሎ ሐመርን ኹዚህ ዕንጚት ሠራት። መላዕክት እንስሶቹን ወደ መርኚቢቱ ያመሯ቞ው ሲሆን እግዚአብሔር ቀተሠቡን ኹክፉ ሰዎቜ ለመጠበቅ አንበሶቜ አኖሚ። ኖህ ቀንና ሌሊት በማገንባት ላይ ኖሚ፣ ደግሞ በመርኚቢቱ ላይ ሲሆን ለአመቱ አላንቀላፋም ይባላል። ራባ ዚተባለው ሚድራሜ እንደሚል ዹጎርፉ ክልል አለም አቀፍ ሳይሆን እስኚ ሞሮኮ ድሚስ ብቻ ሞፈነ። ታልሙድ ሳንሄድሪን ደግሞ አንበሣው ኖህን እንደ ሰለበው ይተርካል። በመርኚብ ላይ ያሉት ሁሉ ኚማርባት ቆዩ ዹሚል መሹጃ በአይሁድ ጞሐፍት ይጚመራል። ቁራው ሲሰደድ ፈቃደኛ አልነበሚም። ኹሐመር ሊስት ፎቆቜ፣ ታ቞ኛው ለቆሻሻ፣ መካኚለኛው ለሰዎቜና ለንጹሐን እንስሶቜ፣ ላዹኛም ለርኩስ እንስሶቜና ለወፎቜ ነበር። (በሌላ ዚአይሁድ ጜሑፍ ግን ቆሻሻው በላይኛ ፎቅ ሆኖ ቀጥታ ወደ ባሕር ይጣል ነበር።) ብርቅ ድንጋይ በተዓምር ብርሃን ይሰጥ ነበር። ኹኖህ ቀተሠብ 8 ሰዎቜ ጭምር አንድ ሹጃጅም ሰው ወይም ናፊል፣ ዚባሳን ንጉሥ ዐግ በሐመር ኹመሰጠም አመለጠ ዹሚል ዚአይሁዶቜ ልማድ ቢገኝም፣ ይህ ግን ለመጜሐፍ ቅዱስ ተቃራኒ ይመስላልፀ ዹዐግ ግዛት በኢያሱ ወልደ ነዌ ዘመን ይታወቅ ነበርና። በሌላ ዚአይሁድ ታሪክ ዘንድ ዹሐመር ሣንቃ በአሩር ንጉሥ ስናክሬም ተገኝቶ ጣኊት ሠራበት። በሚድራሜ አባ ጊርዮን ዘንድ፣ ሌላ ዹሐመር ሣንቃ ደግሞ ለሐማን (ኚመጜሐፈ አስ቎ር) ስቅለት ተጠቀመ። በወንጌል መሠሚት ኢዚሱስ መመለሱን እንደ ኖህ ዘመን አመስሎ መሠኚሚ። (ማቮ. 24:37-42) መጀመርያ ዚቀተ ክርስትያን ጞሐፍት ሐመርን እንደ ምልክት ቆጠሩት። 1 ጎጥሮስ መልእክት እንዳለ በሐመር ያመለጡት ሰዎቜ በጥምቀት ውኃ ለመሚጡት ሰዎቜ ምሳሌ ና቞ው። ቅዱስ አቡሊድስ (200 ዓ.ም. ገዳማ) አንዳንድ ልማዶቜ ተሚኩ። በሊስት ፎቆቜ ታቜኛው ለአውሬዎቜ፣ መካኚለኛው ለአዕዋፍና ለኚብቶቜ፣ ላዹኛው ለሰዎቜ ሲሆን ማርባት ለመኹልኹል ወንዶቜ ኚሎቶቜ በቜካል ተለዩ። ዚአዳም አጜም፣ ወርቅ፣ ዕጣንና ኚርቀ ተጫኑባትፀ ሐመርም በመስቀል ቅርጜ ሰፈፈቜ። ዚሰፈሚቜበት ተራራ 'ደብራ ካርዱ' «በምሥራቅ፣ ዚራባን ልጆቜ አገር፣ ምሥራቃውያንም 'ጎዳሜ'ፀ ዓሚባውያንና ፋርሳውያንም 'አራራት' ይሉታል» በማለት ጻፈ።. ኊሪጊኔስ ስለ ሐመር ቅርጜ ራሱ እንደ ተቋሹጠ ፒራሚድ ይመስል ነበር ብሎ ጻፈ። በሱ አስተያዚት፣ በጫፉ ርዝመቱ አንድ ካሬ ክንድ ነበርፀ ይህም ክንድ ሙሮ በግብጜ ስላደገ ዚግብጜ ክንድ ሳይሆን አይቀርም መሰለው። ኹ12ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ቅርጹ ባለ-ጣራ ሳጥን እንደ ነበር ተቆጠሚ። በ15ኛው ክፍለ ዘመን አልፎንሶ ቶስታዳ፣ በ16ኛው ክፍለ ዘመን ዮሐንስ ቡ቎ዎ ዹሐመርን ቅርጜ ገለጹ። በአይርላንድ አፈ ታሪክ፣ ዹኖህ አራተኛ ልጅ «ቢስ» እንዳይሣፈር አልተፈቀደምፀ ወደ አይርላንድ ኹ54 ሰዎቜ ጋራ ሞሜቶ ሁላቾው ሰመጡ። በሞርሞን («ዚመጚሚሻ ቀን ቅዱሳን») ሃይማኖት ሐመር ደግሞ በመጜሐፈ ሞርሞን (መጜሐፈ ኀጠር) ትጠቀሳለቜ። በመጚሚሻ ቀን ቅዱሳን (ሞርሞን) እምነት፣ ዹኖህ መታወቂያ በውነት መልአክ ገብርኀል ነበሚ። ኖህ (ኑኅ) ኚእስልምና አምስት ዋና ነቢዮቜ አንዱ ነው። በቁርዓን መሠሚት ኑኅ ጻድቅ ሆኖ ጣኊት ለሚያምኑት ክፉ ሰዎቜ ሰብኮ 70 ወይም 72 አሳመና቞ውና በድምሩ 78 ወይም 80 ሰዎቜ በመርኚቢቱ ላይ አብሚውት አመለጡ። እነዚህ 72 ሰዎቜ ግን ምንም ልጅ ስላልወለዱ ዚዛሬ ሰው ልጆቜ በሙሉ ኹኖህ ቀተሠብ ተነሡ። ዹኖህ አራተኛ ልጅ እንዳይሣፈር እምቢ ብሎ ተሰጠመፀ ባንዳንድ ምንጭ ስሙ «ያም» ወይም «ኚንዓን» ይሰጣል። በሱራ 11:44 ዘንድ ዚሠፈሚቜበት ሥፍራ ደብሚ ጁዲ ሲሆን ይህ በተለመደው በሞሱል፣ ኢራቅ አካባቢ በጀግሮስ ወንዝ አጠገብ ዹሚገኝ ኮሚብታ መሆኑ ይታስባል። ጾሐፊው አል-ማሱዲ (940 ዓ.ም. ያህል) እንደ ጻፈው፣ ሐመር ኚኩፋ፣ ኢራቅ ተነሥቶ እስኚ መካ ድሚስ ሰፍፋ ካዕባን ዞሚቜና ወደ ደብሚ ጁዲ ተመለሰቜ። በዚያም እስኚ ሕይወቱ ዘመን ሊታይ ቻለ ብሎ ጻፈ። ያቁት አል-ሐርማዊ (1200 ዓ.ም. ዙሪያ) ኖህ በዚያ ያሠራው መስጊድ በዘመኑ እንደ ተገኘ ጻፈ። በቅርቡ ሌላ ተራራ በቱርክ አገር፣ ዱሩፒናር፣ በውኑ ዚደብሚ ጁዲ ሥፍራ ነው ዹሚል ግመት አለ። ኚመርኚብ በሙሐራም ወር 10 ቀን ወጥተው ሰዎቹ በጁዲ ግርጌ «ጣማኒን» (ሰማንያ) ዚተባለ መንደር ሠሩ። ኑህ መርኚቢቱን ቆልፏት ቁልፉን ለሮም ሰጠ። በሙሐመድ ዘመን ዹኖሹው አብድ አላህ እብን አባስ በጻፈው ዘንድ፡ ኑኅ ዋንዛን ተክሎ ኹ20 አመት በኋላ በቂ ዕንጚት ነበሚው። አል-ባይዳዊ በጻፈው ታሪክ መጜሐፍ ደግሞ በሐመር ሊስት ፎቆቜ ታቜኛው ለእንስሶቜፀ መካኚለኛው ለሰዎቜፀ ላዹኛውም ለአዕዋፍ ነበር። ዚአዳም ሬሳ ወንዶቜ ኚሎቶቜ ለመለዚት በመካኚላ቞ው ተደሚገ። ሹጃጅሙ ዐግ ኚውኆቹ ለማምለጥ እንደተፈቀደ ዹሚል ተሚት ደግሞ ይገኛል። በፋርስ ጾሐፊ አል-ታባሪ ጜሁፍ ተጚማሪ ዝርዝር አለ። መጀመርያው ዚተሣፈሚ ፍጡር ጉንዳን ሲሆን መጚሚሻው ሠይጣን ዚተሣፈሚበት አህያ ነበሹ ይላል። ደግሞ ዚኢዚሱስ ሐዋርያት ስለ ሐመር ለመማር በፈለጉ ጊዜ፣ ኢዚሱስ እንዲመልሳ቞ው ዹኖህ ልጅ ካምን ኚሙታን አንሥቶት ካም እንዲህ መሠኚሚላ቞ውፀ ቆሻሻ በበዛበት ጊዜ ኑህ በተዓምር ዐሣማዎቜ ኹዝሆን ኩምቢ አወጣፀ እንደገና አይጥ ያለ ፈቃድ ስለ ገባ ድመት ኚአንበሣ አፍንጫ ፈጠሹ አላ቞ው። እነዚህ ተሚቶቜ በቁርዓን ስለማይገኙ ግን ብዙዎቹ እስላሞቜ አይቀብሉዋ቞ውም። እስላሞቜ ዛሬ ቁርአን ትክክለኛ ታሪክ ሆኖ ይቆጥሩታል። አንዳንድ ተቺዎቜ ለምሳሌ ሃሩን ያህያ እንደሚያስቡ፣ ማዹ አይህ አለም አቅፍ ሳይሆን ዹኖህን አገር ብቻ ያጠፋ ነበር። በባኃኢ እምነት ባኃኢ እምነት ዚተባለው ሃይማኖት ዹሀመር ታሪክ እንደ ምሳሌ ይቆጥሩታል። ዹኖህ ተኚታዮቜ በመንፈሳዊ ሚገድ ሕያው ዚሆኑፀ ዚሰጠሙትም በመንፈሳዊ ሚገድ ሙታን ዚሆኑት ምሳሌ ና቞ው። በባኃኢ ቅዱስ መጜሐፍ ኪታብ-ኢ-ኢቃን ዘንድ፡ ኹኖህ ጋር 40 ወይም 72 ተኚታዮቜ አመለጡፀ ኹማዹ አይህ አስቀድሞ ኖህም ለ950 አመታት ያስተምር ነበር። በሳብያን ሃይማኖቶቜ በኩርዲስታን ተራሮቜ ዹሚገኘው ዚዚዚዲ ሀይማኖት ትምህርት በመጜሐፋ቞ው ምስሐፈ ሚሜ (ጥቁሩ መጜሐፍ) ይገኛል። በዚህ በኩል ዚጥፋት ውኃ ሁለት ጊዜ መጣ። ኚመጀመርያው ጥፋት ዚካም አባት ናኡሚ አመለጠፀ መርኚቡም በሞሱል ዙሪያ በዓይን ስፍኒ ተቀመጠቜ። ኹዚህ በኋላ ሁለተኛው ጥፋት ውኃ በዚዚዲዎቹ ብቻ ደሚሰፀ ኹዚህም ኖህ በሌላ መርኚብ አምልጩ መርኚቡ ኚደብሚ ስንጃር በላይ በዓለት ተወግቶ ኚዚያ በደብሚ ጁዲ ተቀመጠቜ። በደቡብ ኢራቅ ዚሚኖሩ ማንዳያውያን ሃይማኖት ደግሞ ኖህንና ዮሐንስ መጠምቁን እንደ ነቢያት ሲቆጥሩ አብርሐምና ኢዚሱስ ግን ሐሣዊ ናቾው ብለው ያምናሉ። ሐመር ዚተሠራ ኹጀበል ሃሩን (ሖር ተራራ በዛሬው ዮርዳኖስ) በመጣ ሰንደል ዕንጚት ተሠራፀ ርዝመቱ፣ ስፋቱና ቁመቱ ሁላቾው 30 ክንድ ነበሩፀ ማሚፊያው ደግሞ በግብጜ ነበር ይላሉ። ዚተዛመዱ ተሚቶቜ በሜስጶጊምያ ጜላቶቜ በሜስጶጊምያ ጥንታዊ ተሚት ጜላቶቜ አንዳንድ ተመሳሳይ ታሪኮቜ ተገኝተዋል። እነዚህ ኚሱመር፣ ኚአካድ፣ ኚባቢሎንና ኹአሩር በኩነይፎርም ጜሕፈት ተጜፈው ይታወቃሉ። በሱመር አፈ ታሪክ ዚጊልጋመሜ ታሪክፀ አማልክት ምድርን በውኃ ለማጥፋት ወስነው ኀንኪ ግን ዚሹሩፓክ ኹተማ ንጉሥ ዚውሱድራን በመርኚብ እንዲያመልጥ ይነግሚዋል። ነገር ግን በዚህ ተሚት ዚጥፋት ውኃ ለ7 ቀን ብቻ ነው። ጜሁፉ ቢያንስ ኹ17ኛው ክፍለ ዘመን አክልበ. ዚተጻፈ ቢሆን በጊልጋመሜ ታሪክ ዚሚጠቀሱት ነገሥታት ኀንመባራገሲና አጋ በ3ኛ ሺህ አክልበ. በውኑ እንደ ነገሡ ኚስነ ቅርስ ይታወቃል። ዚጊልጋመሜ ታሪክ በባቢሎን ትርጉም ተጜፎ ዚዚውሱድራ ስም በአካድኛ ኡትናፒሜቲም ሆኗል። ኹ7 ቀን በዝናብና ኹ12 ቀን በውሆቹ ላይ በኋላ፣ መርኚቡ በደብሚ ኒጺር ተቀመጠቜፀ ኹሌላ 7 ቀን በኋላ ኡትናፒሜቲም 3 ወፎቜ ይልካል። በመጀመርያ ርግብ ልኮ ተመለሰቜፀ ሁለተኛ ጊዜ ጚሚባ ትልካ ተመለሰቜፀ ሊስተኛም ቁራ ግን አልመለሰም። በሌላ ትርጉም መርኚብን ዚገነባው ሰው ስም አትራሐሲስ ይባላል። በ300 አክልበ. ገዳማ ዚባቢሎን ቄስ ቀሮሶስ አንድ ታሪክ በግሪክ ጜፎ ይህን አይነት ተሚት መዘገበ። በዚህ ትርጉም መርኚብ ዚገነባው ሰው ስም ክሲሲውጥሮስ ተባለ። መርኚቡም እስኚ ቀሮሶስ ዘመን በአርሜንያ ተራሮቜ እንደ ተገኘ ጻፈ። በአንዳንድ ሊቃውንት አስተያዚት ዚሜስጶጊምያ ተሚት ለኊሪት ዘፍጥሚት ምንጭ ነበሚፀ በሌሎቜ ሀሣብ ግን ሁለቱ በአንድ ድርጊት ተመነጩና ኚሁለቱም ዚሜስጶጊምያ ተሚቶቜ እጅግ ዚተዛቡ፣ ዚዘፍጥሚት ግን ትክክለኛ ዹሆኑ ይመስላል። ሌሎቜ ዹአለም ጥፋት ውኃ ተሚቶቜ በአለም ዙሪያ በማናቾውም አሕጉር በማናቾውም ወቅት ዹማዹ አይህ ታሪክ ይታወቃል። ለምሳሌ በግሪክ ተሚቶቜ ዘንድ ኚጥፋት ውኃ በመርኚብ ያመለጡ ዎውካሊዮንና ሚስቱ ፒውራ ነበሩ። በሕንዱ ሃይማኖት ጜሕፈት፣ ኚጥፋት ውኃ በመርኚብ ያመለጠው ቅዱስ ንጉስ ማኑ ተባለፀ እሱም ዚማኑስምርቲ ሕገጋት ደራሲ እንደ ነበር ታመነ። ኚቀተሠቡና ኹ7 ሊቃውንት ወይም 'ሪሺዎቜ'ና ዹአለም እንስሶቜና አትክልት ናሙናዎቜ ጋራ ተጉዞ መርኚቢቱ በሂማላያ ወይም በካሜሚር እንዳሚፈቜ ይባላል። በርካታ ሌሎቜ ተመሳሳይ ተሚቶቜ በአፍሪካ፣ በስሜን አሜሪካ፣ በደቡብ አሜሪካ፣ በአውስትራላዚያ፣ በእስያና በአውሮጳ ኗሪዎቜ መካኚል ተገኝተዋል። ስለዚህ በጥንት ዹሰው ልጅ ሁሉ ወላጆቜ ኚጥፋት ውኃ እንዳመለጡና በኊሪት ዘፍጥሚት ያለው ኹሁሉ ይልቅ ትክክለኛ ታሪክ ነው ዚሚያምኑ ብዙ ሰዎቜ አሉ። ታሪካዊ አስተያዚቶቜና ትቜቶቜ ዚአይሁድ ታሪክ ጾሕፊ ፍላቭዮስ ዮሎፉስ (1ኛው ክፍለ ዘመን አ.ም.) ዚቀድሞ አሕዛብ ጞሕፍት ቀሮሶስ፣ ሂኀሮኒሙስ ግብጻዊ፣ ምናሎዎስና ዚደማስቆ ኒቆላዎስ ሁላቾው ሐመር በአርሜንያ ተራሮቜ ትገኛለቜ እንዳሉ ጠቀሳ቞ው። እንዲሁም ሚቢው ዮናታን ቀን ዑዝኀል (1ኛው ክፍለ ዘመን አ.ም.)፣ ክርስቲያን ጞሐፍት አቡሊድስ፣ ዚአንጟኪያ ቎ዎፊሎስ (2ኛው ክፍለ ዘመን)፣ ቅዱስ ሂኀሮኒሙስና ኀጲፋንዮስ (400 ዓ.ም. ገዳማ)ፀ ዚእስላም ጞሓፍት አል-ማሱዲ (9ኛው ክፍለ ዘመን) ሁላቾው በዘመናቾው ሐመር በአርሜንያ ወይም በኩርዲስታን ተራሮቜ ልትታይ ቻለቜ አሉ። ቅዱስ ያዕቆብ ዘኒሲቢስ ኹሐመር ሥፍራ ዹወሰደው ዚእንጚት ቅርስ በአርሜንያ ኀጭምያጺን ገዳም እስኚ ዛሬ ድሚስ እንደሚታይ ይባላል። በ17ኛው ክፍለ ዘመን ዚሮማ ካቶሊክ ኢዚሳስዊ ቄስ አታናስዮስ ኪርኚር በግሪክ አፈ ታሪክ ዚሚገኙት ሲሬኖቜ ዚተባሉት ፍጡሮቜ (በኹፊል ወፍ በኹፊልም ሎት) በውኑ እንደሚኖሩ አስተማሚ። ስለዚህ በኖህ መርኚብ ልዩ ክፍል ነበራ቞ው ብሎ ገመተ። በዚህ ዘመን ዹሐመር ታሪክ ብዙ ሊቃውንት ዚአትክልትና ዚእንስሶቜን ስርጭት ለማጥናት ነዳ቞ው። በ19ኛው ክፍለ-ዘመን ላይ፣ በተለይ በምዕራብ ዓለም በብዙዎቹ ዚሳይንስ ሊቃውንት አስተያዚት፣ መተራሚኩ አፈ ታሪክ ብቻ እንጂ በዕውኑ አይሆንም በማለት ተጠራጠሩ። ቢሆንም በዚህ ወቅት ዚኖሩ አንዳንድ መምህራን ለምሳሌ አውጉስት ዲልማን፣ ፍራንጜ ዎሊቜና ፍራንሷ ለኖርማን ማዹ አይኅ አፈ ታሪክ ወይም ተሚት ብቻ ሳይሆን ትክክለኛ ታሪክ ነው በማለት ገመቱ። ለማስሚጃ እያንዳንዱ ጥንታዊ ሥልጣኔ ለዚህ ታላቅ ፍዳ ትዝታውን ስለ ጠበቀ ነው ዹሚል ምስክር አቀሚቡ። ኚአሜሪካ () ሕዝብ 2 ሢሶ ወይም 65 ኚመቶ ዚሚያህሉ ማዹ አይህ ዕውነተኛ ታሪክ እንደሚሆን ጜኑዕ እምነት አላ቞ው። በመጜሐፍ ቅዱስ ትክክለኛነት ዚሚያምኑት ምእመናን አብዛኛው ጊዜ ጾሐፊው ሙሮ በ13ኛው ክፍለ ዘመን አክልበ. ሲሆን ማዹ አይህ በ3ኛ ሺህ አክልበ. ዹደሹሰ መቅሠፍት እንደ ሆነ ይቀበላሉ። ዹማዹ አይህ ጥናት ዚጥፋት ውኃ አለም አቅፍ እንደ ነበር፣ በመሬትም ብዙ ማስሚጃ እንዳለ (ለምሳሌ ዚባሕር እንስሳ ቅርስ በተራሮቜ ላይ ሲገኝ) ያስተምራል። ሆኖም አብዛኛው ዚዛሬውኑ ሳይንስ ሊቃውንት ይህ ጥናት ሀሣዊ ነው ዚምድርም ዕድሜ ብዙ ሚልዮን አመታት ነውና በማለት ተቃውመውታል። ዹሐመር ሥፍራ ማግኘት ኚጥንት ጀምሮ ታስቧል። ብዙዎቜ ፍለጋዎቜ በደብሚ አራራት በዛሬው ቱርክ አገር ቢሆኑም፣ እንዲያውም ዘፍጥሚት «ዚአራራት ተራሮቜ» ይላል። በኩፋሌ ዚጫፉ ስም ሉባር ይሠጣል። ሌላ ዚቱርክ ጫፍ ዱሩፒናር ላይ ወይም በኢራን በደብሚ ሳባላን ላይ እንደምትገኝ አንዳንድ ጀብደኞቜ ይላሉ። በ1999 አ.ም. (2007 እ.ኀ.አ.) አንድ ዚቱርክና ዚሆንግኮንግ ፍለጋ ወደ ደብሚ አራራት ሂዶ በአንድ ዋሻ ውስጥ፣ ወደ ድንጋይ ዹተቀዹሹ ዚዕንጚት ግድግዳ እንዳገኘ ናሙናዎቜም ኚዚያ እንዳወሚዱ ይላሉ። ይህ ዹሐመር ሥፍራ በደብሚ አራራት ላይ ተገኝቷል ማለት ነው ይላሉ። መጜሐፍ ቅዱስ
21388
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%90%E1%89%B6%E1%88%8E%20%E1%89%B6%E1%88%8E%20%E1%89%A4%E1%89%B5%20%E1%8C%8D%E1%88%AD%E1%8C%8D%E1%8B%B3%E1%8B%8D%20%E1%8C%AD%E1%88%AB%E1%88%AE
ዚነቶሎ ቶሎ ቀት ግርግዳው ጭራሮ
ዚነቶሎ ቶሎ ቀት ግርግዳው ጭራሮ ዹአማርኛ ምሳሌ ነው። ዚነቶሎ ቶሎ ቀት ግርግዳው ጭራሮ ዹአማርኛ ምሳሌ ነው። ተሚቱ ዹሚለው "ዚነቶሎ ቶሎ ቀት ግድግዳው ሠንበሌጥ" ነው። ትርጉሙም "በቜኮላ ዚሚሠራ ነገር ቋሚ አደለም" ለማለት ነው። በሠንበሌጥ ዚተሠራ ቀት ኃይለኛ ንፋስ ሲነፍስ ስለሚፈርስ ነው ሠንበሌጥ ለተሚቱ ዚተመሚጠው። ያልተተሚጎመ ምሳሌ ተሚትና ምሳሌ
48461
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B6%E1%88%80%E1%89%A3%20%28sahabah%29/%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%88%9B%20%E1%89%A2%E1%8A%95%E1%89%B5%20%E1%8A%A0%E1%89%A1%E1%89%A0%E1%8A%AD%E1%88%AD%28%E1%88%A8.%E1%8B%90%E1%8A%95%E1%88%81%E1%88%9B%29
ሶሀባ (sahabah)/አስማ ቢንት አቡበክር(ሚ.ዐንሁማ)
🎀አስማ ቢንት አቡበክር ሚዲዚላሁ ዐንሃ📀 <<ኚአክስ቎ አዒሻና ኹናቮ አስማ ዚበለጡ ርኀሩኀ ሎቶቜ እስካሁን አላዹሁም>>(አብደላህ ኢብኑ ዙበይር ሚዲደላሁ ዐንሁ) ✍አስማ ቢንት አቡበክር ሚዲዚላ ሁ ዐንሃ ኹተኹበሹ ሙስሊም ቀተሰ ብ ዚተገኘቜ ሎት ስትሆን አባቷ-አ ቡበክር-ዚነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወ ሰለም ዚልብ ወዳጅና ወራሜ (ኾሊ ፋ)ነበሩ።እህቷ-አዒሻ ሚዲዚላሁ ዐን ሃ ዚነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሚስትና ኚኡሙ ሙእሚኒን (ዚምእ መናን እናት)አንዷ ነበሚቜ።ባለቀቷ ዙበይር ኢብን አል አዋም ሚዲዚላሁ ዐንሁ ዚነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰ ለም ልዩ አማካሪዎቜ ኚነበሩት አን ዱ ሲሆን፥ልጇ አብዱላህ ኢብኑ ዙ በይር ሚዲዚላሁ ዐንሁ ለሐቅ በነበሹ ዉ ቀናዒነትና ጥንካሬ እጅግ ዚታወ ቀ ሰዉ ነበር። ✍አስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ ኢስላምን ለመጀመሪያ ጊዜ ኚተቀበሉት ሙስ ሊሞቜ ጋር ትመደባለቜ።ወደ ኢስላ ም በመግባት ወንዶቜንና ሎቶቜን ጚምሮ አስራ ሰባት ሰዎቜ ብቻ ና ቾዉ ዚሚቀድሟት።አስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ፥ዚነብዩን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰ ለም ዚመዲና ጉዞ ዕቅድ ሚስጥር በነበራ቞ዉ ዝግጅት ምክንያት ዹጉ ዞዉ ሚስጢራዊነት በኹፍተኛ ጀሹ ጃ ዹተጠበቀ ነበር።በስንብታ቞ዉ ምሜት አስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ በአን ድ አገልግል ምግብና በሁለት ኹሹ ጢቶቜ ዉኃ ሞላቜ።ለኚሚጢቶቹ መ ቋጠሪያ ገመድ በማጣቷም ዹወገ ቧን መቀነት (ኒታቅ)ፈታቜ።አባቷ አ ቡበክርም ሚዲዚላሁ ዐንሁ ለሁለት እንድትሰነጥቀዉ ነገሯት።ነብዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተግባሯን አደነቁ።በዚህ ምግባሯ ነበር <<ባ ለሁለት መቀነቷ>>(ዛት አን-ኒታቀይ ን)በመባል ዚታወቀቜዉ። ✍ዚመጚሚሻዉ ሂጅራ በነብዩ ሰለ ላሁ ዐለይሂ ወሰለም መካን መልቀ ቅ ኹተፈፀመ በኃላ አስማ ሚዲዚላ ሁ ዐንሃ አሚገዘቜ።እንደሌሎቹ ዹነ ብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሶሃባ ዎቜ ሁሉ፥እርሷም ሆነቜ ባልተቀቷ ኚነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስ ደት በኃላ በመካ ዹመኖር ፍላጎት አልነበራ቞ዉም።እርግዝናዋም ሆነ ዚመንገዱ እርቀት ሳይበግሯት ወደ መዲና ጉዞ ተነሳቜ።በመዲና ዳርቻ ላይ ኚምትገኝ ቁባ ኚምትባል ሥፍ ራ እንደደሚሱ ፥አብደላህ ዚተባለ ወ ንድ ልጅ ወለጀቜ።ዚልጁ መወለድ ታራካዊነት ስለነበሚዉ በሙስሊሞ ቜ ዘንድ በተክቢራና ተህሊል ዹገለ ፁትን ደስታ ፈጠሚ። ✍አስማ በመልካም ሥነ-ምግባሯ ና በልበ ብርሃንነቷን በዘመኑ ዚታወ ቀቜ ሎት ነበሚቜ።ርኀራኄዋን በተ መለኹተ ልጇ አብዱላህ በአንድ ወ ቅት እንዲህ ሲል ዚአማኝነት ቃሉን ለግሷል።<<ኚአክስ቎ ኚአዒሻና ኚእ ናቮ ኚአስማ ዚበለጡ ርኀሩኀ ሎቶቜ እስኚአሁን ድሚስ አላደሁም።ዚሁለ ቱ ሎቶቜ ርኀራሄ ዚተለያዚ ገጜታ ነበ ሚዉ።አክስ቎ በቂ ዚመሰላትን ያህ ል ማጠራቀሟን ካሚጋገጠቜ በኃላ ለቜግሚኞቹ ታኚፋፍለዋለቜ።እና቎ በ በኩሏ ለነገ ዹሚል ሐሳብ ዚላትም። እጇ ላይ ዚገባዉን ሁሉ ወዲያዉኑ ለተቾገሹ ትለግሳለቜ።>> ✍ዚአስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ ልባምነ ት እጅግ ዹሚደንቅ ነዉ።ለቀተሰባ ቾዉ አንዳቜ ነገር ላይተዉ ስድስት ሺህ ዲርሃም ዚሚቀልጥ ንብሚታ቞ ዉን ጠራርገዉ ነበር ወደ መዲና ዹ ተጓዙት።በዚያን ጊዜ ሙሜሪክ ዹነበ ሩት ዚአቡበኚር አባት አቡ ቁሓፋህ ዹልጃቾዉን ወደ መዲና መጓዝ እን ደሰሙ ቀታ቞ዉ ድሚስ በመሄድ ለአ ስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ እንዲህ አሏትፊ <<ካለ ገንዘብ ትቶሜ እንደሄደ እር ግጠኛ ነኝ።>>አስማም ሚዲዚላሁ ዐንሃ <<አይደለም፥አያ቎ ሆይ፥(አባ ቮ)በቂ ገንዘብ ትቶልን ነዉ ዹሄደዉ ።>> ስትል መለሰቜላ቞ዉ።ጥቂት ገንዘብ መሰል ጠጠሮቜን በገንዘ ብ ማስቀመጫ ትንሜ ሳጥን ዉስ ጥ አኖሚቻ቞ዉ።በጚርቅ ኚሞፈነቻ ቾዉ በኃላ አይነ ስዉሩ አያቷ በእጃ ቾዉ እንዲሳስሱት በማድሚግ <<አ ዹህ!ምን ያህል ገንዘብ አባ቎ ትቶል ን እንደሄደ>> አለቻ቞ዉ። ✍አስማ ሚዲዚላሁ ወንሃ ይህንን ስልት ዚተጠቀመቜዉ ሙሜሪኩ አ ያቷ ገንዘብ ዹላቾዉም በሚል ኹኔ ዉሰዱ እንዳይሉ በመስጋቷ ሲሆን ኚርሳ቞ዉ መዉሰዱን ዚጠላቜበት ምክንያትም ምንም እንኳን አያቷ ቢሆኑ ኚሙሜሪክ (አጋሪ)ሰዉ እርዳ ታ መቀበል ኢስላማዊ ሰብዕናዋን እንደማዋሚድ ስለቆጠሚቜዉ ነዉ። ✍አስማ ሚዲደላሁ ዐንሃ በእናቷ ም ላይ ተመሳሳይ አቋም ነበራት። ክብሯን እና ኢማኗን ለድርድር ዹማ ቅሚብ ዝንባሌ በጭራሜ አልታዚባት ም።በቅድመ ኢስላም ኚአባቷ ጋር ዚተፋታቜዉ እናቷ ቀቲለህ አንድ ወ ቅት በመዲና ሳለቜ ልትጎበኛት መ ጣቜ።ኢስላምን ያልተቀበለቜዉ እና ቷ ወደርሷ ስትመጣ ደሹቅ ኮምጣ ጀ፣ዚተጣራ ቅቀ...ይዛላት ነበር።አ ስማ ሚዲደዚላሁ ዐንሃ አስቀድማ ለ እናቷ ዚመግባት ፍቃድ አልሰጠቜ ም፥ያመጣቜዉን ስጊታም አልተቀ በለቜም።አንድ ሰዉ ወደ አዒሻህ ሚ ዲዚላሁ ዐንሃ በመላክ መዉሰድ ስ ለሚገባት ርምጃ ኚነብዩ ሰለላሁ ዐ ለይሂ ወሰለም ጠይቆ እንዲመጣ አደሚገቜ።ነብዩም ሰለላለሁ ዐለይ ሂ ወሰለም እናቷን ወደቀት እንድታ ስገባ፥ስጊታዋንም እንድትቀበል አ ዘዟት።በዚህን ጊዜም ዹሚኹተለዉን ዚቁርኣን አንቀፅ ተደነገገ። ኚነዚያ በሃይማኖት ካልተጋደሏቜ ሁ፥ኚአገሮቻቜሁም ካላወጡዋቜ ሁ (ኚሓዲዎቜ)፥መልካም ብትዉሉ ላቾዉና ወደነርሱ ብታስተካክሉ አላ ህ አይኚለክላቜሁምፀአላህ ትክክለ ኞቜን ይወዳልና።አላህ ዹሚኹለክላ ቜሁ፥ኚነዚያ ኚሃይማኖት ኹተጋደሉ ዋቜሁ፥ኚቀቶቻቜሁም ካወጡዋቜ ሁ፥እናንተንም በማዉጣት ላይ ኹ ሚዱት (ኚሓዲዎቜ)፥እንዳትወዳጁ ዋቾዉ ብቻ ነዉ።>>[አል ሙምተ ✍ለአስማም ሚዲዚላሁ ዐንሃ ሆነ ለበርካታ ሙስሊሞቜ ዚመጀመሪያ ዉ ዚመዲና ኑሮ ቀላል አልነበሚም። ባሏ ቜግሚኛ ነበር።ቀደም ሲል ኹገ ዛዉ ፈሚስ በስተቀር አንዳቜም ሀብ ት አልነበሚዉም።ያንን ጊዜ አስማ ሚ ዲዚላሁ ዐንሃ እንደሚኚተለዉ ትገ ልፀዋለቜፊ <<ለፈሚሱ ድርቆሜና ዉ ሃ ኹሰጠሁ በኃላ ዚሰዉነቱንም ጜዳ ት እጠብቅለታለሁ።ዱቄት ፈጭቌ ም እጋግራለሀ።ግና ጋግሬም ዹተ ዋጣ ስለማይሆንልኝ ብዙዉን ጊዜ ዚአንሷር ሎቶቜ ይጋግሩልኛል።በጣ ም ጥሩ ሎቶቜ ነበሩ።ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለዙበይር ሚዲዚላ ሁ ዐንሁ እንዲያደርሰዉ ኹወሰኑለ ት መሬት ላይም እህል በራሎ ተሾ ክሜ እመጣለሁ።ይህ ዚእርሻ ቊታ ኹኹተማ ወደ ፈርሰኜ (18 ኪ•ሜ ያህል ይርቃል)።>> ✍አስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ እጅግ ጥ ንቁቅና ታታሪ ሎት ነበሚቜ።ቜግራ቞ ዉ ቀስ በቀስ እስኪወገድላ቞ዉ ድ ሚስም ኚባሏ ጋር ጠንክሹዉ ሰሩ።ዙ በይር ሚዲዚላሁ ዐንሁ ቀስ በቀስ ኹ ሶሃባዎቜ ሁሉ እጅግ ዚታወቀ ባለፀ ጋ ሆነ።ሀብት ማግኘታ቞ዉ አስማን ሚዱዚላሁ ዐንሃ ቅጥያጣ ኑሮ እንድ ትኚተል አላሚደጋትም።እንደወትሮ ዋ ሁሉ በኢማኗ ላይ ዚፀናቜ ሎት ነ በሚቜ።አንድ ወቅት ልጇ ሙንዚር ዋጋዉ ዉድ ኹሆነ ክር ዚተሰራ ድን ቅ ቀሚስ ኚኢራቅ ላኚሊት።በጊዜ ዉ አይነ ሥዉር ዚነበሚቜዉ አስማ ሚዲዚላሁ ዐንሃ ቀሚሱን ዳብሳ ድን ቅነቱን በተሚዳቜ ጊዜ ኹፍተኛ ሐዘን ተሰማትፀለመልእክተኛዉም ሰለላ ሁ ዐለይሂ ወሰለም <<ይህ ለኔ ዹ ሚገባ አይደለምና ወደርሱ መልስ ለት።>> ስትል አዘዘቜዉ።ሙንዚር በሁኔታዉ ተበሳጭቶ <<እማማ፥ሰ ዉነትን ዚሚያሳይ ቀሚስ አይደለም ።>>ሲል ገለፀላት። ✍እርሷንም በቁጣ <<ዚሰዉነትን መልክ ዚሚያሳይ ሊሆን ይቜላል፥ነ ገር ግን ጠባብ ስለሆነ ዚሰዉነትን ቅርፅ ያሳያል።>> ስትል መለሰቜለ ት አልሙንዚር ዚእናቱን አለመስማ ማት እንዳሚጋገጠ ኚእርሷ ፈቃድ ጋ ር ዚሚሄድ ሌላ ቀሚስ ገዛላት። ✍ዚአስማን ሚዲዚላሁ ዐንሃ ዚኢማ ን ጥንካሬ ዚሚያሳይ ኹላይ ዹጠቀ ስነዉ ገጠመኟ በቀላሉ ሊሚሳ ይቜ ል ይሆናል።ነገር ግን ኹልጇ ኚአብ ደላህ ሚዲዚላሁ ዐንሁ ጋር ለመጹ ሚሻ ጊዜ በተገናኙበት ወቅት ያሳዚ ቜዉ ጥልቅ አስተዋይነት፣ታጋሜነት ና ዚኢማን ጥንካሬ ኚቀደምት ሙስ ሊሞቜ ታሪክ ዉስጥ ዹሚዘነጉ አይ ✍ኚዚዚድ ኢብን ሙዓዉያህ ሞት በኃላ ዹኾሊፋዉን ቢሮ ዚመራዉ አ ብደላህ ሚዲዚላሁ ዐንሁ ነበር።ዚሂ ጃዝ፣ዚምስር (ግብፅ)፣ዚኢራቅ፣ዚኹ ራሳን አብዛኛዉ ዚሶሪያ ህዝብ ዹር ሱ አፍቃሪ ስለነበሩ ዚኞሊፋነት ስል ጣኑ ለእርሱ እንዲሚጋ ወሰኑ።ነገር ግን በኑ ኡመያዎቜ ድርጊቱን በመ ቃወምና ኾሊፋዉን በመንቀፍ አል-ሃጃጅ ኢብን ዩሱፍ በተባለዉ ሰዉ ዚሚመራ ትልቅ ሰራዊት አንቀሳቀ ሱ።በሁለቱም ወገኖቜ መካኚል ጠ ንካራ ዉጊያ ተደሚገ።በዚህም ፍል ሚያ አብዱላህ ኢብን ዙበይር ሚዲ ዹላሁ ዐንሁ ብዙ ዚጀግንነት ተግባ ራትን አሳዚ።ነገር ግን አብዛኞቹ አጋ ሮቹ ዚጊርነቱን ፈታኝነት መቋቋም ስለተሳና቞ዉ ጥለዉት ሞሹ።በመ ጚሚሻ እሱም ዉጊያዉን ትቶ መካ በሚገኘዉ ቅዱስ መስጊድ ለጥገ ኝነት ገባ። ✍ በዚያን ጊዜ ነበር እርጅና ተጭ ኗት አይነ ሥዉር ዚሆነቜ እናቱን ለ መጎብኘት ወደ አስማ ሚዲዚላሁ ዐ ንሁ ዘንድ ዚሄደዉ።ኚዚያም እንደደ ሹሰ፩ <<እማማ፥ዚአላህ ሰለም ርኀ ራሄና በሚኚት በአንቺ ላይ ይሀን>>( አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበሚካቱሁ)አላት።እርሷም <<በአ ንተም ላይ ሰላም ይሁን (ወአለይኩ ሙስሰላም)፥አብዱላህ ሚዲዚላሁ ዐንሁ>>ስትል መለሰቜለት።፡<<ዹሃ ጃጅ ጩር ሃሹም በሚገኘዉ ሠራዊ ትህ ላይ መዓት በሚያዘንበብትና ዚመካ ቀቶቜ በሚንቀጠቀጡበት በዚህ ቀዉጢ ሰዓት ወደዚህ ምን አመጣህ?>> ስትልም ጠዚቀቜዉ ።እርሱም <<ምክርሜን ፍለጋ መጣ ሁ ኡማ (እማዚ)>>በማለት ለጥያቄ ዋ ምላሜ ሰጠ። 🔺 እርሷም በመደነቅ <<ዹኔን ም ክር ፍለጋ?ስለምንድነዉ ዹምመክ ርህ አብዱላህ ሚዲዚላሁ ዐንሁ?>> በማለት ጠዚቀቜዉ። •<<ኹጎኔ ተሰልፎ ዹነበሹዉ ሕዝብ አብዛኛዉ ሃጃጅን በመፍራት ወይ ም በሚሰጠዉ ወሮታ በመጭበር በር ጥሎኝ ሞሞ።ልጆቌና መላዉ ቀ ተሰቀ እንኳን ኚእኔ ተገለሉ።አብሚ ዉኝ ዚቀሩት በጣም ትንሜ ሰዎቜ ሲሆኑ፥እነርሱም ምንም ያህል ጠካራና ቆራጥ ቢሆኑም ዚጠላትን ኃይል ሊቋቋሙ ዚሚቜሉት ለአንድ ሰዓት ግፋ ቢል ለሀለት ሰዓት ያህ ል ነዉ።በኑ ኡመያዎቜ ኹኔ ጋር ለ መደራደር መልእክተኞቻ቞ዉን ልኹ ዋል።ዚምሻዉን አለማዊ ፀጋ (አዱን ያ)ሁሉ ሊሰጡኝ ፈቃደኛ መሆናቾ ዉንም ገልጞዉልኛል።ነገር ግን ለዚ ህ ዉለታ቞ዉ ጊሬን ላስቀምጥና ኚአብዱል መሊክ ኢብን መርዋን ጋር ዚትብብር ቃል እንድገባ መስማማት አለብኝ።ታዲያ ስለዚህ ጉ ዳይ ምን ታስቢያለሜ?>> ድምጿን ኹፍ በማድሚግ፥ <<አብ ዱላህ ይህ ዹአንተ ጉዳይ ነዉ፣ማን ነትህን ጠንቅቀህ ዚምታዉቅ ሰዉ ነህ።ትክክለኛና ለእዉነት ዚቆምኩ ነኝ ብለህ ካሰ ብክ፥ በባንዲራህ ስ ር በቆራጥነት ሲዋጉ እንደተገደሉ ት ጓደኞቜህ ሁሉ በፅናትና በቆራ ጥነት ዉጊያህን ቀጥል።ይህን ትተ ህ አዱንያን ኚመሚጥክም ምንኛ አ ሳዛኝ ሰዉ ነህ! እራስህንም ሆነ ሰ ዎቜህን እንደምታጠፋ ልብ በል። >>ስትል ምክሯን ለገሰቜዉ። •<<ግን እማዚ እንደዚያ ካደሚግሁ፥ ዛሬ ሟቜ ነኝ፣ምንም ጥርጥር ዚለዉም።>> ለሃጃጅ በፈቃደኝነት እጅህን ሰጥ ተህ ዹበኑ ኡመያ አጫፋሪዎቜ መ ጫወቻ ኚምትሆን፥ዚጀግንነት ሞት ለአንተ እጅጉን በላጭ ነዉ።>> •<<ሞቮን አልፈራሁምፀዚኔ ፍርሃት ሥጋዬን ይበጣጥቁታል ብዬ ነዉ።>> <<ዹሰዉ ልጅ ኚሞቱ በኃላ በአካ ሉ ላይ ስለሚፈፀመዉ ድርጊት ም ንም ዚሚያስፈራዉ ነገር ዚለም።ዚቆ ዳዉ መገፈፍ ምንም ዚሚያመጣ ዉ ህመም አይኖርም።>>አለቜዉ። ✍አብደላህ ሚዲዚላሁ ዐንሁ ልብ ዚሚያጠነክሚዉን ዚእናቱን ምክር እ ንደሰማ ዹሚኹተለዉን እዚተናገሚ ፊ ቱ አንፀባሚቀ። <<ምኝኛ ዚተባሚክሜ እናት ነሜ(መ ልካሙ ባህሪይሜ ዚተባሚኚ ይሁን)በ ዚህ ቀዉጢ ሰዓት ወደአንቺ ዹመ ጣሁት በጆሮዬ ያንቆሚ ቆርሜዉን ምክር ለመስማት ነበር።እንዳልደኚ ምኩና ተስፋ እንዳልቆጠሚጥኩ አ ላህ ያዉቅልኛል።ለአዱኛ ፍቅር እን ዳልተሰለፍኩም በኔ ላይ ምስክሬ ነ ዉ።ገደብ ዚለሜ ቁጣዚ ዹአላህ ሕግ በመጣሱ ነዉ።እና቎! አንቺን ደስ ወደሚያሰኝሜ ለመሄድ እነሆ ዝግ ጁ ነኝ።ብሞት አትዘኝብኝፀበፀሎት ሜ ብቻ አስታዉሜኝ።>> •ቆራጧ አሮጊት አስማ ሚዲዚላሁ ዐ ንሁ <<ልጄ!ዚማዝንብህ ለማይሚባ ዓላማ ተሰልፈህ ብትሞት ነዉ።>> <<እርግጠኛ ሁኚ እማዚ ልጅሜ ህገወጥ ዓላማን አልደገፈም።ፀያ ፍ ዹሆነ ተግባርም አልኚወነም። ሙስሊሞቜንም ሆነ ሙስሊም ያል ሆኑ ዜጎቜ ፍትህ አላጓደለም።ለር ሱ ኚኃያሉ ጌታ ዉዎታ ዹበለጠ አን ዳቜም ነገር ዚለም።ይህን ያልኩት ንፅህናዬን በመግለፅ ለመመጻደቅ ሳይሆን ልብሜን ለማጠናኹር ብቻ እ ንደተናገርኩ አላህ ያዉቅልኛል>>አ <<አላህ ሱብሃን ወተአላህ ለሚወ ደዉና እኔም ዹምመኝልህን እንድት ፈፅም ስለሚዳህ ምስጋና ይግባዉ! ና ልጄ ግንኙነቻቜን ዚመጚሚሻ ሊ ሆን ይቜላልና እስኪ ሰዉነትህን ላ ሜትተዉ፥ልዳስሰዉም።>> አለቜዉ ና ኚፊቷ ተንበ ሚኚኚ።ወደ እርሷ አስ ጠጋቜዉፀ አንገቱን ፥ፊቱንና እራሱን በእናትነት ስሜት ተዉጣ እዚዳበሰ ቜ ሳመቜዉ።ጣቶቿ ሰዉነቱን መ ጭመቃቾዉን ቀጠሉ።በድንገት እ ጇን ኚሰዉነቱ አላቃ፩ <<ይህ ዹለበ ስኚዉ ምንድን ነዉ? >>አለቜዉ።< <ዹጩር ልብስ ነዉ>>አላት።<<ይህ ፥ሰማዕታትን ዹሚኹጅል ሰዉ ዹሚ ለብሰዉ ልብስ አይደለም።አዉልቀ ዉ፥እንቅስቃሎህን ይበልጥ ቀላልና ቀልጣፋ ያደርግ ልሃል።በዚህ ምት ክ ሱሪ ልበስ።ብትገደልም ሃፍሹተ ሥጋህ አይጋለጥም>>አለቜዉ። ✍አብደላህ ሚዲዚላሁ ዐንሁ ዹጩ ር ልብሱን አዉልቆ ሱሪ አጠለቀ።ፍ ልሚያዉን ለመቀላቀል <<ሐሹም> >ሲለቅፊ <<እና቎ ሆይ!ዱዓሜ አይለ ዹኝ>> አላት። ✍እጇን ወደ ሰማይ ዘርግታ ዱዓ አደሚገቜፊ <<ጌታዬ ሆይ!...ለአባቱ ና ለእናቱ ዚእርሱን መልካም ሰሪነት ባርክላ቞ዉ።እርሱን ለአንተ ጉዳይ አበርክቻለሁ።ለእርሱ ዚወሰንክለት ነገር ያስተስተኛል።ለኔም ጜኑና ታጋ ሜ ዹሆኑ ሰዎቜን ምንዳ ለግሰኝ።>> 🌹ፀሐይ ስትጠልቅ አብደላል ሚዲ ዹላሁ ዐንሁ ለዘልዓለም አንቀላፍቶ ነበር።ልክ ኚአሥር ቀናት በኃላ እና ቱን ተኚተለቜዉ።ዚመቶ ዓመታት እ ድሜ ባለፀጋ ነበሚቜ።እድሜ ዹአላ ማ ጜናቷን አልዘሚፋትምፀዚአእምሮ ብሩህነቷን አላደበዘዘዉም።
43744
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8D%8D%E1%88%AE%20%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8B%AB%E1%8B%8A%20%E1%89%8B%E1%8A%95%E1%89%8B%E1%8B%8E%E1%89%BD
አፍሮ እስያዊ ቋንቋዎቜ
አፍሮ እስያዊ ቋንቋዎቜ በሰሜን አፍሪቃና በደቡብ ምዕራብ እስያ ዚሚነገሩ ቋንቋዎቜ ቀተሰብ ሲሆን 6 ንዑሳውያን ቀተሰቊቜ አሉት። እነዚህም ጥንታዊ ግብጜኛ፣ በርበርኛ፣ ቻዳዊ፣ ኩሻዊ (ሐማዊ)፣ ኩሞአዊና ሮማዊ ቋንቋዎቜ ና቞ው። ኚእነዚህ ኹላይ ዚተጠቀሱት ውስጥ 3ቱ ማለትም ኩሻዊ (ሐማዊ)፣ ኩሞአዊና ሮማዊ ቋንቋዎቜ በኢትዮጵያ ውስጥ ይነገራሉ። በዕድሜ ሚገድ ግዕዝና ግብጜኛ ጥንታዊ ቋንቋዎቜ ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ኩሻዊና ኩሞአዊ መጀመርያ ዚገቡት፣ ሮማዊ ቋንቋዎቜ ኚእነሱ ቀጥለው ወደ ኢትዮጵያ ዚገቡ ና቞ው። ዚአፍሮሲያቲክ ቋንቋዎቜ ኹሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ተበታተኑ፣ ነገር ግን ዚመጚሚሻው መነሻ቞ው ኹ15,000 ዓመታት በፊት ኚምዕራብ እስያ ወደ አፍሪካ በመጣው ዚፓሊዮሊቲክ ዚፍልሰት ማዕበል ውስጥ ሲሆን ሁለቱንም “ዚምእራብ ዩራሺያን ዹዘር ግንድ” እና ፕሮቶ-አፍሮሲያቲክን አስተዋውቋል። ደግሞ ይዩ ሮማዊና ግብጜኛ ቃላት ዝርዝር አፍሮ እስያዊ ቋንቋዎቜ
9347
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%90%E1%8B%AD%E1%8A%AD
ሐይክ
ሐይክ (አርሜንኛ፩ ) በአርሜኒያ አፈ ታሪክ ውስጥ ዹአርሜናዊ ህዝብ መስራቜ ነበሚ። ዚሱ አፈታሪክ በታሪክ ጾሐፊው ሙሮ ሖሬናዊ 5ኛ ክፍለ ዘመን መጜሐፍ ዚአርሜኒያ ታሪክ በተለይ ዹሚገኘው ነው። በሙሮ ሖሬናዊ ዘንድ ሐይክ ዚያፌት ልጅ ጋሜር ልጅ ዚቶርጎም (ቮርጋማ) ልጅ ነው። ሐይክ ደግሞ ዚሐይካዙኒ ሥርወ መንግሥት መስራቜ ይባላል። በታሪክ ጾሐፊው ጇንሾር ዘንድ፣ ሐይክ 'ዚሰባት ወንድማማቜ መስፍን ሆኖ፣ መጀመርያ ዓለሙን በሙሉ እንደ ንጉሥ ለነገሠው ለሹጅሙ ሰው ለናምሩድ ያገልግል ነበር'። 'ሐይክ' ደግሞ በአርሜንኛ መጜሐፍ ቅዱስ ትርጉም ዚኊሪዮን ኚዋክብት ስም ነው። (ኢዮብ 38፡31) በሙሮ ሖሬናዊ መጜሐፍ በሙሮ ሖሬናዎ መሠሚት፣ በባቢሎን እዚኖሚ ዚቶርጎማ ልጅ ሐይክ ልጁን አርማኔያክን ኹወለደ በኋላ፣ ትዕቢተኛው ቲታናዊው ቀል (እሱም ሙሮ እንደሚለው ናምሩድ ነው) እራሱን ዹአለም ሁሉ ንጉሥ ስላደሚገ፣ ሐይክ ኚቀተሠቊቹ ኹ300ም ሰዎቜ ጋራ ወደ አራራት አገር ፈልሶ ሐይካሞን ዚተባለ መንደር ይመሠሚታል። በመንገዱ ላይ ለልጅ-ልጁ ለካድሞስ አንድ ሠፈር ይተወዋል። ሐይክ ወደ ባቢሎን እንዲመልስ ግድ እንዳለው ዹሚል መልእክት ለማቅሚብ ቀል ኚልጆቹ አንዱን ወደ ሐይክ ልኮ እሱ ግን እምቢ ይለዋል። ኚዚያ ቀል ኹግዙፍ ሠራዊቱ ጋራ በሱ ላይ ቢዘምትም ካድሞስ ግን ስለመቅሚቡን ሐይክን ያሳውቀዋል። ሐይክ ዚራሱን ሠራዊት በቫን ሐይቅ ዳርቻ ሰብስቊ ዚቀል ባርዮቜ እንዳንሆን ወይም ቀልን አሾንፈን መግደል ወይም በሙኚራው መሞት አለብን ብሎ ይላ቞ዋል። ዚቀል ድልና ሞት ኚዚያ በኋላ ሐይክ ዚቀልን ሠራዊት በአንድ ተራራ ላይ ያገኛ቞ዋል። ሙሮም ይህን ተራራ በዳስታኚርት ሥፍራ እንደሚገኝ ይላል። ቀል እራሱ በሠራዊቱ ፊት ይታያል። በፍልሚያው መኅል ሄይክ በእድለኛ ፍላጻ ቀልን ገድሎ ሠራዊቱ ተደናገሹና ድል ሆነ። በሌሎቜ ደራሲዎቜም ዘንድ፣ ይህ ፍልሚያ በቫን ሐይቅ ደቡብ-ምሥራቅ በጁላመርክ ዙሪያ በበድዩጻዝናማርት ኚክርስቶስ በፊት በ2501 አመታት ነበሚ። 'ሐይካበርድ' ዹተሰዹመ አምባ በውጊያው ሥፍራ ላይ መሠርቶ ስሙ 'ሐይካሞን' ዚተባለ መንደር ይሠራል። ዚፍልሚያው አገር 'ሐይክ' ይለዋልፀ ዚዛሬም አርሜኒያ ስም 'ሃያስታን' ዚአርሜኒያም ሕዝብ 'ሃይ' ይባላል። እንዲሁም በጥንት በኬጢያውያን ጜሕፈቶቜ በዙሪያው ሐዚሣ ዚተባለ ብሔር ነበሚ። ዋቢ ጜሑፎቜ አፈ ታሪክ
15796
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%88%AE%E1%8B%AD%E1%8B%B5
ፍሮይድ
ሲግመንድ ፍሮይድ (1856 - 1939 እ.ኀ.አ.) ኊስትሪያ ዹተወለደ ዹነርቭ ሃኪም እና ስነ ልቡና ተመራማሪ ነበር። ዚትንተናዊ ስነ ልቡና ( ዚሳይኮአናሊሲስ ) አባት እዚተባለ ይጠቀሳል። ፍርይድ በስነ ልቡና ጥናት ታዋቂ ዹሆነው ዹሰውን ልጅ ያልነቃ ኅሊና በሳይንሳዊ ዘዮ በማጥናቱ ነበር። እያንዳንዱ ግለሰብ ዹነቃ ኅሊና እንዳለው ሁሉ ያልነቃም ህሊና አለው፣ ሆኖም ግን ግለስቊቜ ያልነቃውን ዚአዕምሮ ክፍል ምን እንደሚያሳብ ማወቅ አይቜሉም፡ በተጚማሪ ግለሰቊቜ ይህን ዚአዕምሮ ክፍላቾውን ማዘዝም ሆነ መቆጣጠር አይቜሉም። ያልነቃው ክፍል በራሱ ፍላጎት ግለሰቡ በኅይወት እስካለበት ዘመን ድሚስ ያስባል። ይህን ሃሳብ በጜሁፍ ባቀሚበበት ወቅት ፍሮይድ ላይ ኹፍተኛ ተቃውሞ ደርሷል፡ ምክንያቱም ብዙ ሰዎቜ እራሳ቞ው ዚማያውቁትና ዚማይቆጣጠሩት ክፍል አዕምሮአ቞ው ውስጥ እንዳለ ለመቀበል ስላቃታ቞ው ነበር። በፍሮይድ አስተሳሰብ በህይወት ኹመኖር ቀጥሎ ለሰው ልጅ ኹፍተኛ ዋጋ ያለው ፍትወተ ስጋ እንደሆነ ጜፏል። ይህን ፍላጎት ሊቢዶ በማለት ተንትኗል። ዹሰው ልጆቜ ዚማይፈልጉትን ሁሉ እንዲያሚጉ እስኚማስገደድ ድሚስ ይህ ሊቢዶ ያስገድዳል ብሏል። ፍሮይድ ዚአይሁድ ሃይማኖት ተኚታይ ስለነበር በ1930ወቹ ዚሱ መጜሃፎቜ ተሰብስበው እንዲቃጠሉ ናዚዎቜ አደሚጉ። በ1938 እ.ኀ.አ. ዚአዶልፍ ሂትለር ሰራዊት ፍሮይድና ቀተሰቊቜ ላይ ጉዳት ለማድሚስ እንደሚሹ ሲያሚጋግጥ ፍሮይድ ኚነቀተሰቊቹ ቪዚና (ኊስትሪያ)ን ለቆ ወደ እንግሊዝ ተሰደደ። ስነ ልቡና ዚኊስትሪያ ሰዎቜ