id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-53041154
https://www.bbc.com/amharic/news-53041154
በዛፍ ላይ ተሰቅለው ዚተገኙት ጥቁር አሜሪካውያን አሟሟት ላይ ዳግም ምርመራ ሊጀመር ነው
ዚአሜሪካ ፌደራል ባለስልጣናት በቅርቡ በዛፍ ላይ ተንጠልጥለው ዚተገኙት ሁለት ጥቁር አሜሪካውያን አሟሟት ላይ ዹተደሹገውን ምርመራ ሊገመገም እንደሆነ አስታውቀዋል።
ግለሰቊቹ ሞተው ዚተገኙት በካሊፎርኒያ ሲሆንፀ ኚአሟሟታ቞ውም ጋር በተያያዘ ዚተቀጣጠለውንም ተቃውሞ ተኚትሎ ነው ምርመራው እንደገና እንዲጀመር ዚተወሰነው። ዚአካባቢው ፖሊስ ሮበርት ፉለርና ማልኮልም ሃርሜ ዚተባሉት ጥቁር አሜሪካውያን ግድያ አይደለም ብሏል። በካሊፎኒያ ግዛት በተለያዚ ኹተማ በዛፍ ላይ ተንጠልጥለው ዚተገኙት ጥቁር አሜሪካውያኑ በሁለት ሳምንታት ልዩነት ነው ዚሞቱት። ብዙዎቜ ራሳ቞ውን አጥፍተው ሳይሆን ተገድለው ነው በሚልም ምርመራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተቃውሟቾውን እያሰሙ ነው። ዹ24 አመቱ ሮበርት ፉለር ፓልሜድ በምትባለው አካባቢ ኹሚገኝ ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ዹተገኘው ሰኔ 3፣ 2012 ዓ.ም ነው። ምንም እንኳን ዚአካባቢው ባለስልጣናት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ራሱን አጥፍቶ ነው ቢሉምፀ ብዙዎቜ አልተቀበሉትም። በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜም ምርመራ እንዲካሄድ ፊርማቾውን አሰባስበዋል። ቀተሰቊቹም ቢሆኑ ራሱን ነው ዹገደለው ዹሚለው ፅንሰ ሃሳብ ሊዋጥላ቞ው አልቻለም "ዚሚነግሩን ነገር በሙሉ ስህተት ነውፀ በምንም መንገድ ተቀባይነት ዚለውም። ወንድሜ ራሱን ማጥፋት አይፈልግም ነበር" በማለት ዚሮበርት ፉለር እህት ዳይመንድ አሌክሳንደር ተናግራለቜ። ሌላኛው ሟቜ ማልኮልም ሃርሜም ግንቊት 23፣ 2012 ዓ.ም ቪክቶርቪል በምትባል አካባቢ በዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ ነው ዚተገኘው። ባለስልጣናቱም ዹ37 አመቱ ማልኮልም ራሱን አጥፍቷል ዹሚል ግምት ቢኖራ቞ውም አሟሟቱን በተመለኹተ ይፋዊ መሹጃ ገና አልወጣም። "አሟሟቱን በተመለኹተ በርካታ ጥያቄዎቜ አሉንፀ ምላሟቜም እዚጠበቅን ነው። ወንድሜ ሁሉን ወዳጅ ነበር። ለቀተሰቊቹ ብቻ ሳይሆን ለሁሉ ቀና ነበር። እንዲህ አይነት ሰው ራሱን ያጠፋል ማለት አያሳምንም" በማለት አህቱ ሃርሞኒ ሃርሜ ለሚዲያዎቜ ተናግራለቜ። ዚአሜሪካ ዚፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኀፍቢአይ)፣ ጠቅላይ አቃቀ ህግ፣ ዚካሊፎርኒያ ግዛት ምርመራ ቢሮ፣ ዚአሜሪካ ዚሲቪል መብቶቜ ዚፍትህ ዘርፍ ክፍል ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በላኩት መመግለጫ ግለሰቊቹ ላይ ዚተኚናወኑትን ምርመራዎቜ እዚተገመገሙና እንደገናም ምርመራ ሊጀመር መሆኑን ነው። ዚመጀመሪያ ምርመራው ዹተኹናወነው በሎስ አንጀለስና ሳንበርናርዲኖ ፖሊስ ቢሮዎቜ ሲሆን ለግምገማውም እንደሚተባበሩ አስታውቀዋል። ዹጆርጅ ፍሎይድን ግድያ ተኚትሎ ዚተነሳው ተቃውሞ ዚሁለቱ ግለሰቊቜ አሟሟት ላይም ምርመራ እንዲካሄድ ጫና አሳርፏል።
news-56980751
https://www.bbc.com/amharic/news-56980751
ትዳራ቞ውን ያፈሚሱ አምስት ቢሊዚነሮቜ
አሜሪካዊው ቢሊዚነር ቢል ጌትስ ኹ27 ዓመታት በኋላ ኚሚሊንዳ ጌትስ ጋር መስርተውት ዹነበሹውን ትዳር ለማፍሚስ መስማማታቜውን ገልጞዋል።
ሁለቱ ጥንዶቜ ዚተገናኙት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር 1980ዎቹ ውስጥ ሚሊንዳ ዚቢል ጌትስን ማይክሮሶፍት ተቋም በተቀላቀለቜበት ወቅት ነበር። ''ኚብዙ ማሰብና ግንኙነታቜንን ለማሻሻል ኚሰራን በኋላ ትዳራቜንን ማፍሚሱ ዚተሻለ አማራጭ አድርገን ወስደናል'' ብለዋል በትዊተር ገጻ቞ው ላይ ባስቀመጡት መልዕክት። ቢሊዚነሮቹ ጥንዶቜ በ27 ዓመታት ዚትዳር ዘመናቾው ሊስት ልጆቜን ያፈሩ ሲሆንፀ በተለያዩ ዘርፎቜ ድጋፍ ዚሚያደርገውን 'ቢል ኀንድ ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዎሜን' አቋቁመዋል። ድርጅታ቞ውም ዚተለያዩ አይነት ተላላፊ በሜታዎቜን ለመዋጋትና ለህጻናት ክትባቶቜን ለማድሚስ በቢሊዚኖቜ ዹሚቆጠር ዶላር ፈሰስ አድርጓል። ቢል ጌትስ በፎርብስ መጜሄት መሹጃ መሠሚት ዚዓለማቜን አራተኛው ቢሊዚነር ሲሆን ዚተጣራ ሀብቱም 124 ቢሊዚን እንደሆነ ተነግሯል። ዚጥንዶቹ ትዳር ማፍሚስ ዓለምን ያነጋገር ትልቅ ዜና ቢሆንም ያልተለመደ ነገር ግን አይደለም። ኹዚህ በፊትም በርካታ ቢሊዚነር ጥንዶቜ ትዳራ቞ውን አፍርሰው ሀብት ንብሚታ቞ውን ተካፍለዋል። እስቲ ጥቂቶቹን እንመልኚት። ጄፍ ቀዞስ እና ማኬንዚ ቀዞስ ዚአለማቜን ቀንደኛ ሃብታም ጄፍ ቀዞስ እና ባለቀቱ ማክኬንዚ ትዳራ቞ውን ለማፍሚስ ዚተስማሙት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ሚያዝያ 2019 ላይ ነበር። ። ጄፍ ቀዞስ ፍቺውን ለህዝብ ይፋ ያደሚገው በቲውተር ገፁ ላይ ሲሆን ጉዳዩም በመስማማት መኹናወኑን ጠቅሷል። ፍቺው ግን እንዲሁ በቀላሉ ዚሚወጡበት አልሆነም። ባለቀቱ ዚድርሻዋ ነው ዚተባለውን 35 ቢሊዚን ዶላር ተካፍላለቜ። 35 ቢሊዮን ዶላር ድርሻዋን ዚምትቀበለው ማክኬንዚን ኚዓለማቜን ሃብታም ሎቶቜ ዝርዝር ውስጥ ያካትታታል። ይህ ብቻ ሳይሆን ባለቀቷ ኚዛሬ 25 አመት በፊት ኚመሰሚትውና በአለማቜን ቁጥር አንድ ኹሆነው ዚኢንተርኔት ዚቜርቻሮ ግብይት ድርጅት አማዞን ዚአራት በመቶ ድርሻ ይኖራታል። ቢሊዚነሯ ማኬንዚ በአሁኑ ሰአት ልጆቿ በሚማሩበት ትምህርት ቀት ሳይንስ ዚሚያስተምር ግለሰብ አግብታለቜ። ቢሊዚነሯ ዚሳይንስ አስተማሪው ዳን ጄዌትን ማግባቷ ይፋ ዹሆነው 'ጊቪንግ ፕሌጅ' በተሰኘው ዚእርዳታ ድሚ-ገፅ ላይ ነው። አሌክ ዊልደንስቲን እና ጆሰሊን ዊልደርስቲን እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር 1999 እነዚህ ጥንዶቜ ትዳራ቞ውን ለማፍሚስ ሲስማሙ ዓለም ጉድ ብሎ ነበር። በወቅቱ ኚፍቺ በኋላ ኹፍተኛ ወጪ ያስኚተለ ትዳር ሆኖ ተመዝግቩ ነበር። በንግድ ስራውና ዚጥበብ ስራዎቜን በመሰብሰብ ዚሚታወቀው አሜሪካ ፈሚንሳያዊው አሌክ ዊልደንስቲን ኹ21 ዓመታት በኋላ ትዳራ቞ውን እንደሚያፈርሱ ገልጟ ነበር። ባለቀቱ ጆሰሊን ዊልደርስቲን ደግሞ ኚፍቺው በኋላ መጀመሪያ ላይ 2.5 ቢሊዚን ዶላር እንደምታገኝ ተገልጟ ነበር። በወቅቱም በዚዓመቱ ለሚቀጥሉት 13 ዓመታት ተጚማሪ 100 ሚሊዹን ዶላር እንደሚሰጣት ተገልጿል። በዚህም በአጠቃላይ ያገኘቜው ገንዘብ ወደ 3.8 ቢሊዚን ዶላር ይደርሳል። ቢል እና ሱ ግሮስ ቢል ግሮስ እና ሱ ግሮስ በአውሮፓውያኑ 2016 ትዳራ቞ውን ሲያፈርሱ ክፍያው በኋላ በርካታ ያልተጠበቁ ነገሮቜ ተኚስተው ነበር። ቢል በዓለማቜን ታዋቂ አሜሪካዊ ቢሊዚነር ሲሆን ዚመንግሥት ቊንድ በመግዛት ኹፍተኛ ትርፍ በማግኘት ይታወቃል። ዚጥንዶቹ ዚፍቺ ሂደት ደግሞ ሁለት ዓመታትን ዹፈጀ ነበር። ፍቺያ቞ውን ሳይጠናቀቅ በፊት ቢል ግሮስ 31 ሚሊዹን ዚሚያወጣውን ዚባለቀቱን መኖሪያ ቀት ኚጥቅም ውጪ አድርጎት መውጣቱን እና ተክሎቜን ጭምር ገድሎ እንደሄደ ባለቀቱ ለፍርድ ቀት ተናግራ ነበር። ኚፍቺው መጠናቀቅ በኋላ ደግሞ ሱ ግሮስ 1.3 ቢሊዚን ዶላር እንዲሁም 31 ሚሊዹን ዚሚያወጣውን መኖሪያ ቀት እንዲሰጣት ፍርድ ቀት ወስኗል። በተጚማሪም ጥንዶቹ ዹገዟቾው በሚሊዚኖቜ ዚሚያወጡ ዚጥበብ ስራዎቜን እኩል እንዲካፈሉም ተወስኗል። ሩፐርት መርዶክ እና አና ቶርቭ በሚዲያ ቢዝነስ ዚሚታወቀው ቢሊዚነሩ ሩፐርት መርዶክ እና አና ቶርቭ ለ31 ዓመታት ዹቆዹ ትዳር ዚነበራ቞ው ሲሆን ሶስት ልጆቜንም ማፍራት ቜለዋል። ነገር ግን ቢሊዚነሩ ሩፐርት መርዶክ ኹሁሉም ነገር ራሱን ለማግለል ሲያቅድ በአውሮፓውያኑ 1998 ላይ አብሚው ትዳራ቞ውንም ለማፍሚስ ተስማምተዋል። ኚፍቺው ጋር ተያይዞም አና ቶርቭ እስኚ 1.7 ቢሊዚን ዶላር ዚሚደርስ ገንዘብ እንደተሰጣት ተገልጿል። ፍቺያ቞ውን ካጠናቀቁ በኋላ ጥንዶቹ ወደ ሌላ ትዳር ለመሄድ ብዙም አልፈጀባ቞ውም ነበር። ሩፐርት መርዶክ ትዳሩን ባፈሚስ በ17ኛው ቀን ዌንዲ ዮንግ ዚተባለቜ ሎት አግብቶ ትዳር መስርቷል። አና ቶርቭ ደግሞ ኚስድስት ወራት በኋላ ዊሊያም ማን ዚተባለ ግለሰብ አግብታለቜ። ሀሮልድ ሀም እና ሱ አን አርኖል በነዳጅ እና ጋዝ ንግድ ላይ ዚተሰማራው አሜሪካዊው ቢሊዚነር ሀሮልድ ሀም እስኚ 14 ቢሊዚን ዶላር ዚሚደርስ ሀብት እንዳለው ይነገር ነበር። ኚባለቀቱ ሱ አን አርኖል ጋር በአውሮፓውያኑ 2015 ትዳራ቞ውን ለማፍሚስ ሲስማሙ 1 ቢሊዚን ዶላር ለባለቀቱ እንዲሰጥ ፍርድ ቀት ወስኗል። በአሁኑ ሰአት ሀሮልድ ሀም ዚተጣራ ሀብቱ 9 ቢሊዚን ዶላር እንደሆነ ተገልጿል።
news-54341613
https://www.bbc.com/amharic/news-54341613
ዚታይላንድ ሆቮልን አንቋሿል ዚተባለው አሜሪካዊ ሊታሰር ይቜላል ተባለ
በታይላንድ ቆይታው ወቅት ስላሚፈበት ሆቮል አሉታዊ ነገሮቜን መፃፉን ተኚትሎ አንድ አሜሪካዊ ግለሰብ ዚሁለት ዓመት እስር ሊጠብቀው ይቜላል ተብሏል።
ያሚፈበት ሪዞርትም ጥብቅ በሚባለው ዚአገሪቱ ስም ማጥፋት ወንጀል ኚስሶታል። በታይላንድ ነዋሪ ዹሆነው አሜሪካዊው ዌስሊ ባርንስ በተለያዩ ድሚገፆቜም ላይ ሪዞርቱን "ዘመናዊ ባርነት ዚሚካሄድበት" በማለት ወንጅሎ ፅፏል። ዘ ሲ ቪው ሪዞርት በበኩሉ እንግዳው ያቀሚበው ትቜት "መሰሚት ዚሌለው፣ ሃሰትና ዹሆቮሉንም ስም በማጥፋትም ጉዳት አድርሷል ብለዋል። በትሪፕ አድቫይዘር ድሚገፅ ላይ ሆቮሉን አስመልክቶ ዚወጣው ፅሁፍ ፍትሃዊ እንዳልሆነ በማስመልኚት ክስ ዹሆቮሉ ባለቀት መመስሚቱንም ፖሊስን ዋቢ አድርጎ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። ይህን ሁሉ ክስና ውዝግብ ያስነሳው ኮህ ቻንግ በምትባለው ደሎት ውስጥ ዹሚገኘው ሪዞርት ውስጥ ያሚፈው ዌስሊ ዚራሎን መጠጥ ማስገባት አለብኝ በሚል ኹሆቮሉ አስተዳደር ጋር እሰጣገባ በመግባቱ ነው። ግለሰቡ ዹሆቮሉን ተስተናጋጆቜ እንደሚበሞና መጠጥ ዚሚያስገባም ኹሆነ ክፍያውን ፈፅም ቢባልም እምቢተኝነት ማሳዚቱን ሆቮሉ ባወጣው መግለጫው አትቷል። ሆቮሉን ለቅቆ ኚወጣም በኋላ በተደጋጋሚ አሉታዊ ነገሮቜን ስለሆ቎ሉ መፃፉንም ተኚትሎ ሆቮሉም በስም ማጥፋት ወንጀል ኚሶታል። ግለሰቡም በቁጥጥር ስር ውሎም ለሁለት ምሜቶቜ በእስር ቀት ያሳለፈ ሲሆን በዋስም ተለቅቋል። አሜሪካዊው ግለሰብ በስም ማጥፋት ክስ ወንጀል ጥፋተኛም ሆኖ ኹተገኘ እስኚ ሁለት አመት ዹሚቆይ እስር ይጠብቀዋል ተብሏል። ኹዚህም ጋር በተያያዘ ስራውን ያጣው ግለሰብ ጉዳዩ ዹበለጠ ኹገፋም ሌላ ስራ ለማግኘት እንደሚ቞ገር ለቢቢሲ ተናግሯል። ዚፍርድ ሂደቱም ጥቅምት ወር ላይ ይጀምራል ተብሏል።
news-57065443
https://www.bbc.com/amharic/news-57065443
ኹ400 ዓመት በፊት ዚተነገሩ አምስት ጠቃሚ ዚሕይወት ምክሮቜ
ራስን ለመለወጥ ዚሚሚዱ ምክሮቜን ስናስብ ምናልባት ገበያውን ዚሞሉት አዳዲሶቹ መጜሐፍት ጠቃሚ ሊመስሉን ይቜላሉ። ሁሌም ቢሆን ማንም ሰው ዘመናዊና አዲስ ዹሆኑ ነገሮቜን በመጠቀም ራሱን መቀዹር ይፈልጋል።
ነገር ግን ኚብዙ ዘመናት በፊት ዚተጻፉ መጻሕፍት አሁን ላለንበት ዓለም ተግባራዊ መሆን ይቜላሉ። 'ዘ አናቶሚ ኩፈ ሜላንኮሊ' ዚተባለው መጜሐፍ በአውሮፓውያኑ 1621 እንደተጻፈ ይነገራል። ዹዘመናዊውን ሰው አኗኗርና አስተሳሰብ ኹዚህ መጜሀፍ በላይ ዚሚገልጜ ግን አልተገኝም። በርተን እንግሊዛዊ ቄስና ምሁር ሲሆን ኹ2 ሺ ዓመታት በላይ ግሪክ ውስጥ ጥቅም ላይ ይውሉ ዚነበሩ ሕክምናዎቜና እና ፍልስፍናዎቜን አጠናቅሯል። ይህ እንግሊዛዊ ምሁርና ቄስ ኹፍተኛ ድብርትን ያውቀዋል። በዚህ ጉዳይ ዙሪያም በርካታ ሃሳቊቜን አስቀምጧል። ነገር ግን ዹበርተን ዚሕይወት ስራዎቜ በዘመናዊው ሰው ሕይወት ውስጥ ድብርትና ሀዘንን እንዎት ይሚዱታል? ስኮትላንዳዊቷ ጋዜጠኛ ኀሚ ሎፕትሮት ዹበርተንን ስራዎቜ አጠናቅራ በድጋሚ በማዘጋጀት ለ21ኛው ክፍለዘመን ሰው በሚመቜ መልኩ አቅርባዋለቜ። እሷ እንደምትለው በ1620ዎቹ ሰዎቜ ኚድብርትና ሀዘን ለመላቀቅ ይወስዷ቞ው ዚነበሩ ዚመፍትሄ እርምጃዎቜ አሁንም ድሚስ ጥቅም ላይ መዋል ዚሚቜሉ ና቞ው። 1. ዚራሳቜንን ዚስሜት መለዋወጥ በአንክሮ መኚታተል በድብርት አልያም በሀዘን ለሚሰቃይ ሰው ዚሚሰሙት ስሜቶቜ ምናልባት ያለምንም ምክንያት ዹሚሆኑ መስለው ሊታዩ ይቜላሉ። ነገር ግን ዹሚሰሙን ስሜቶቜ ዚራሳ቞ው አካሄድ አላ቞ው። ድብርት ተላላፊ በሜታ እንደሆነና ምልክቶቹም ሆነ ዚሚያሳርፉት ጫና ኚትውልድ ወደ ትውልድ እዚተወሚስ እንደሚሄድ በርተን ያስብ ነበር። ምናልባት ነገሮቜን ዚተመለኚተበት መንገድ ዹተለዹ ሊመስል ቢቜልም በዘመናዊው ህክምናም ብ቞ኛው ምክንያት ባይሆንም ድብርት ኚቀተሰብ ዹሚተላለፍ እንደሆነ ተሚጋግጧል። "አንድ ዚቀተሰብ አባል በኚባድ ዚድብርት በሜታ ዹሚሰቃይ ኹሆነ መላው ቀተሰብ አብሮት ህክምናውን አብሚውት እንዲኚታተሉና ለራሳ቞ውም ነገሮቜን እንዲያስተውሉ እፈልጋለሁ'' ይላሉ በቀተሰብ ጉዳዮቜ ላይ ዚሚሰሩት ዶክተር ፍራንሲስ ራይስ። ነገር ግን ድብርት ኚቀተሰብ ብቻ ዚሚመጣ ጉዳይ አይደለም። ዚተለያዩ ውጪያዊ ምክንያቶቜም ዚራሳ቞ው አስተወዋጜኊ አላ቞ው። በርተን መጜሐፉን በሚያዘጋጅበት ወቅት ራሱ ላይ ያስተዋላ቞ውን ነገሮቜ ኚግምት ውስጥ አስገብቷል። በዹጊዜው ዚሚቀያዚር ዚደስታና ሀዘን ስሜቶቜ በዘመናዊው ዹህክምና ዓለም 'ባይፖላር ዲስኊርደር' ዚሚባል ሲሆን በርካቶቜን ዚሚያጠቃ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሰዎቜ ዹሚሰሟቾውን ስሜቶቜ በአግባቡ መኚታተልና ለምን እንደሚለዋወጡ ማወቅ ለድብርት ፍቱን መድሀኒት ተደርጎ ይወሰዳል። ምን ሲገጥመን ዚስሜት መለዋወጥ ውስጥ እንደምንገባ ማወቅ ኚቻልን እነዚያን ነገሮቜ ማስወገድ ቀላል ነው። 2. ዹቀዝቃዛ ውሃ ጥቅም በርተን በመጜሐፉ ላይ ኚብዙ ዓመታት በፊት በሌሎቜ ሰዎቜ ዚተጻፉ ዚተለያዩ ሀሳቊቜን አስፍሯል። ንጹህ በሆነ ቀዝቃዛ ወንዝ ውስጥ ገላቜንን መታጠብ ደግሞ በርተን ካስቀመጣ቞ው መፍትሄዎቜ መካኚል አንደኛው ነው። ማንኛውም ሰው ሹጅም ህይወት መኖር ኹፈለገ በጣም በሚያምር ተፈጥሮአዊ ቊታ ላይ ገላን መታጠብ አንደኛው መንገድ ነው ይላል። '' በቀዝቃዛ ውሀ ምክንያት ሰውነታቜን ዹሚሰማውን ጭንቀት መቋቋም ካስለመድነው ሌሎቜ አስጚናቂ ነገሮቜንም መቋቋም ይማራል'' ይላሉ በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኘው ፖርትስማውዝ ዩኒቚርሲቲ ተመራማሪ ዚሆኑት ዶክተር ማይክ ቲፕተን። 3. ኚተፈጥሮ አለመራቅ ተፈጥሮ ለበርተን ኹፍተኛ ድብርትን ለማባሚር ቁልፍ ሚና ዚሚጫወት ነገር ነበር። በተለይ ደግሞ በተፈጥሮአዊ ጫካ ውስጥ ዹሚገኙ ዚተለያዩ አይነት እጜዋት ጭንቅላታቜን ዘና እንዲል እና ዚሚያስጚንቁትን ነገሮቜ እንዲሚሳ ዚማድሚግ ኹፍተኛ አቅም አላ቞ው። በኊክስፎርድ ቊታኒክ ጋርደን ዳይሬክተር ዚሆኑት ፕሮፌሰር ሳይመን ሂሰኮክ እንደሚሉ አንዳንድ ተክሎቜ ድብርትን ለማኹም ጭምር ጥቅም ላይ ይውላሉ። በርተን ደግሞ አንዳንድ ተክሎቜ ስንመገባ቞ው ጭምር ድብርትና ዚማባሚር አቅም ያላ቞ው ቢሆንም ተክሎቹን መመልኚት በራሱ ድብርትን እና ጭንቀትን ዚማባሚር አቅም አለው ይላል። እንግሊዛዊው ዚእጜዋት ተንኚባካቢ ሞንቲ ዶን እንደሚለው በኹፍተኛ ሁኔታ በድብርትና ጭንቀት ተሰቃይቶ ነበር። ነገር ግን እጜዋትን መትኚልና መንኚባኚብ ኹጀመሹ በኋላ ግን ነገሮቜ እዚቀለሉ መምጣታ቞ውን ያስታውሳል። ''አንድ ተክል ኚተተኚለበት ጊዜ ጀምሮ እድገቱን መመልኚትና መንኚባኚብ ለጭንቅላት ዹሚሰጠው ትልቅ እሚፍት አለ'' ይላል። 4. ቜግራቜንን ለሌሎቜ ማጋራት ''በውስጣቜን ዹሚሰማንን ጭንቀትና ድብርት ለራሳቜን ብቻ ይዘነውና ተሾክመነው ኚመቆዚት ይልቅ ለሌሎቜ ማጋራትና አብሮ መፍትሄ መፈለግን ዹመሰለ ነገር ዹለም'' ብሎ ነበር በርተን ኹ400 ዓመታት በፊት። ጭንቀትና ድብርት ዚሚያጋጥማ቞ው ሰዎቜ ሁሌም ቢሆን ራሳ቞ውን ኚሰዎቜ ለይተው መቀመጥ ይመርጣሉ። ነገር ግን መሰል ነገሮቜ እንደውም ጭራሜ ስቃዩን ያበዙታል። በቀተሰብ ጉዳዮቜ ላይ ዚሚሰሩት ዶክተር ፍራንሲስ ራይስ እንደሚሉት ጭንቀት ሲገባን ኚምንወዳ቞ውና ኚሚወዱን ሰዎቜ ጋር ዘና ዚሚያደርግ ነገር ማድሚግና ቜግራቜን በዚያው ለእነርሱ ማጋራት በጣም ወሳኝ ነው። ''ምናልባት ኚሰዎቜ ጋር ብዙም ማውራት ዚማንወድ እንኳን ቢሆን ኚሰዎቜ ጋር ለዚት ያለ ነገር ማድሚግ ጭንቅላታቜን ትኩሚቱን ወደ ሌሎቜ ነገሮቜ እንዲያደርግ ያግዘዋል'' ጭንቀትና ድብርት አሰቃዹኝ ብሎ አንድ ሰው ሐኪም ጋር ቢሄድ ምናልባት ድብርትን ዚሚያስወግዱ በርካታ አይነት መድሀኒቶቜ ሊታዘዙ ይቜል ይሆናል። ነገር ግን በአሁኑ ሰአት እንደ ዎንማርክ፣ ካናዳ እና ዩኬ ባሉ አገራት መሰል ቜግር ዚሚያጋጥማ቞ው ሰዎቜ ኚመድሀኒት ይልቅ ኚሰዎቜ ጋር እንዲገናኙ፣ አዲስ ክህሎቶቜን እንዲማሩ አልያም ተፈጥሮአዊ ቊታዎቜን እንዲጎበኙ ነው ዚሚታዘዝላ቞ው። 5. ስራቜንን እና ሕይወታቜንን ማጣጣም ምናልባት በርተን ቃል በቃል ስራቜንን እና ሕይወታቜንን ማጣጣም ብሎ ላይሆን ይቜላል። ነገር ግን አዲስ ነገር ዹመማር ፍቅር በሚል ገልጟታል። እንደውም ይህ ዹመማር ፍቅር በራሱ ኹበዛ ቜግር ሊሆን እንደሚቜልም አስቀምጧል። በርተን እንደሚለው ሕይወታቜንን ዚምንመራበት ስራን ለማሳካት አልያም ምርምር ለማድሚግ ይሁን ሙሉ ትኩሚታቜንን እና ጭንቅላታቜንን በሙሉ እዛ ላይ ባደሚግን ቁጥር ራሳቜን ላይ ተጚማሪ ጭንቀትና ድብርት እንጚምራለን። ሰዎቜ ስለስራ቞ው አብዝተው ሲጚነቁ እና ነገሮቜን ለማስተካኚል ሙሉ ጊዜያ቞ውን እዚያ ጉዳይ ላይ ባዋሉ ቁጥር ኚሰዎቜ ጋር ዚሚኖራ቞ው ግንኙነት እዚቀነሰ ይመጣል። ዚሚያስደስታ቞ውን ነገር ማድሚግም ቢሆን ያቆማሉ። ምናልባት በርተን ዚሰዎቜን አስተሳሰብ ዚተመለኚተበትና ያጠናበት መንገድ ያሚጀ ሊሆን ይቜላልፀ ነገር ግን እርሱ ተውሶ ያመጣ቞ው ዚግሪክ ፈላስፋዎቜ አስተሳሰብና ህክምናዎቜ አሁንም ድሚስ ጥቅም ላይ መዋል ዚሚቜሉ ና቞ው። ራስን ማወቅ፣ መዋኘት፣ ተፈጥሮ፣ ማህበሚሰብ እና ማንበብ ኚዛሬ 400 ዓመት በፊት ኚሰሩ አሁን ላይ ለእኛስ ዚማይሰሩበት ምክንያት አለ?
news-53749528
https://www.bbc.com/amharic/news-53749528
ፊልም ፡ በዚህ ዓመት በሆሊውድ ብዙ ሚሊዮን ዶላሮቜ ዹተኹፈላቾው ተዋናዩቜ ታወቁ
በዚህ ዓመት ዚትኞቹ ተዋናዮቜ ብዙ ሚሊዮን ዶላሮቜ ተኹፈሏቾው? ብሎ ለሚጠይቅ ዘንድሮ ድዋይን "ዘ ሮክ" ጆሐንሰንን በክፍያ ዚሚያህለው አልተገኘም አጭሩ መልስ ነው።
ድዋይን ጆሐንሰንን ዚሐብታም ዚገንዘብ መጠን አደባባይ በማስጣት ዚሚታወቀው ፎርብስ ዚአዱኛ ዝርዝር መጜሔት ትናንት እንዳስነበበው ኹሆነ ድዋይን ጆሐንሰን በዚህ ዓመት ብቻ 87 ሚሊዮን ተኩል ዶላር አጋብሷል። ይህም ካለፈው ዓመት ሰኔ እስኚ ዘንድሮ ሰኔ መሆኑ ነውፀ በፈሚንጆቜ አቆጣጠር። ደግሞም ዚድዋይን ኹፍተኛ ተኚፋይነት ዘንድሮ ለተኚታታይ ሁለተኛ ዓመት መሆኑ አስገራሚ ሆኗል። ዚቀድሞው ዚነጻ ትግል ተወዳዳሪና ዹአነቃቂ ዲስኩርተኛ ጆሐንሰን ዘ ሮክ በተመሳሳይ ባለፈው ዓመት ዚምድራቜን ትልቅ ገንዘብ ተኹፋይ ተዋናይ ተብሎ መሰዹሙ ይታወሳል። ድዋይን ዘ ሮክ ጆሐንሰን ይህ ክፍያው ኔትፍሊክስ ላይ በቅርብ መታዚት ለሚጀምሹው "ሬድ ኖቲስ" (Red Notice) ለተሰኘው ፊልም ማስታወቂያና ትወና ዹተኹፈለውን 23 ሚሊዮን ዶላር ተኩል ይጚምራል። በፊልሙ ላይ ድዋይን ራሱ መሪ ሆኖ ይተውንበታል። ሬድ ኖቲስ በቅርብ በኔትፍሊክስ ዚሚቀርብ አንድ ኢንተርፖል በጥብቅ በሚፈልገው ዚዓለማቜን ዚሥዕል ቀበኛ ላይ ዚሚያጠነጥን 'አክሜን ኮሜዲ' ዘውግ ያለው ፊልም ነው። ኹዚህ ባሻገር ዚስፖርታዊ እንቅስቃሎ አልባሳት ማምሚቻ ዹሆነውና "ፕሮጀክት ሮክ" ዹሚል ስም ያለው ድርጅቱ ለድዋይን ዘ-ሮክ ጠቀም ያለ ገንዘብ ያስገኝለታል። ኚድዋይን 'ዘ-ሮክ' ጆሐንሰን ጋር 'በሬድ ኖቲስ' ፊልም ላይ አብሮት ዚሚሰራው ሌላኛው ተዋናይ ራዚን ሬይኖልድ 2ኛው ኹፍተኛ ተኹፋይ ነውፀ በፎርብስ መጜሔት መሹጃ መሰሚት። ራዚን ሬይኖርልድ 71 ሚሊዮን ዶላር ተኩል ወደ ኪሱ አስገብቷል በዚህ ዓመት። ይህ ገንዘብ 'ሬድ ኖቲስ' ላይ ለሚተውንበት ዹተኹፈለውን 20 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ሲክስ አንደርግራው (Six Underground) ለተሰኘው ፊልም ደግሞ ሌላ 20 ሚሊዮን ዹተኹፈለውን ይጚምራል። ፎርብስ ዚዓለማቜን ሊስተኛው ኚባድ ተኹፋይ ተዋናይና ፕሮዲዩሰሩ ማርክ ዋልበርግ እንደሆነ አስታውቋል። 58 ሚሊዮን ዶላር በዓመት ገቢ አግኝቷል ማርክ። በአራተኛና በአምስተኛ ደሹጃ ዚተቀመጡት ቀን አፍሌክ እና ቪን ዲዝል ና቞ው። ኹዚህ ሌላ ዚቊሊውዱ ኩማር እስኚ 10 ኚገቡ ኹፍተኛ ተኚፋዮቜ ብ቞ኛው ሆኗል። በዚህ ዝርዝር ውስጥ ሚራንዳ፣ ዊል ስሚዝ እና አዳም ሳንድለር ይገኙበታል። ጃኪ ቻንም እስኚ 10 ባለው ዝርዝር ቊታ አላጣም። ፎርብስ ዚወንድ ተዋናይንን ዝርዝ ነው ለጊዜው ይፋ ያደሚገው። በቀጣይ ሎት ተዋንያንን እንዲሁ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። ባለፈው ዓመት በዚህ ዹኹፍተኛ ተኚፋዮቜ ዝርዝር ኚሎት ተዋንያን ሁሉ ልቃ ዚተገኘቜው ስካርሌት ጆሐንሰን ነበሚቜፀ 56 ሚሊዮን ዶላር በማፈስ። ይህ ገንዘብ መጠን ባለፈው ዓመት ኚወንዶቜ ዝርዝር ሰባተኛ ደሹጃን ዚሚያስቀምጥ ነበር።
50450883
https://www.bbc.com/amharic/50450883
ሺህ ቃላት ኹሚናገሹው ፎቶ ጀርባ ያለው እውነታ
ሃይድርባድ ዚተሰኘቜው ዚደቡባዊ ሕንድ ግዛት ነዋሪ ዚሆነቜው ዚአምስት ዓመቷ ሕፃን ፎቶ ሰሞኑን ዚሃገሬውን ሰው ጉድ አሰኝቷል
ፎቶው ይህቜ ሕፃን ትምህርት ገበታ ላይ ያሉ እኩዮቜዋን ኚውጪ አጮልቃ ስትመለኚት ያሳያል። ዲቭያ አሁን በመንደሩ ታዋቂ ሆናለቜፀ ዕድሜ ኚሺህ ቃላት በላይ ለተናገሹው ፎቶ። ዓይን-አፋሯ ዲቭያ በአንድ ዚመንግሥት ትምህርት ቀት በኩል ስታልፍ ነው እኩዮቜዋ ሲማሩ አጮልቃ ስትመለኚት ዚነበሚው። በአንድ እጇ ጎድጓዳ ሳህን ይዛለቜ። ይህ ፎቶ ቮሉጉ በተሰኘው ጋዜጣ ዚፊት ገፅ ላይ ኚወጣ ወዲህ መነጋገሪያ ሆነ። ርዕሱ ደግሞ ዹተጠማ ዕይታ ይላል። ለጥቆ ዚማሕበራዊ ድር-አምባው አፍ ሟሟሻ ሆነ። ዚሕፃናት መብት ተሟጋቜ ነን ያሉ ድምፃ቞ውን በፎቶው በኩል አሰሙ። ይሄኔ ነው ትምህርት ቀቱ ዲቪያን በነፃ ለማስተማር ዚወሰነው። ዚዲቪያ አባት ግን ፎቶው ባመጣው ዕድልም ሆነ ጩኞት ደስተኛ አይደሉም። «እኔና ዚፅዳት ሠራተኛ ዚሆነቜው እናቷ ኚፍቶናል» ይላል። «ፎቶውን ባዚሁት ጊዜ አዘንኩኝ። ዲቫያ ቀን ተሌት ተራሩጠው መፃኢ ሕይወቷን ዹሰመሹ ለማድሚግ ዚሚሮጡ እናት እና አባት አሏት። ጋዜጣው ግን ወላጅ አልባ አስመስሎ ነው ያቀሚባት።» አባትፀ ዲቪያ 6 ዓመት እስኪሆናት እዚጠበቅኩ ነበር እንጂ ዚማስተማር አቅም አለኝ ይላሉ። ዲቪያ ታላቅ ወንድም እንዳላትና ሁለተኛ ደሹጃ ጚርሶ ኮሌጅ ለመግባት እዚተጠባበቀ እንዳለ አባት ይናገራሉ። ዲቪያና ወላጆቿ በአንድ ክፍል ቀት ውስጥ ይኖራሉፀ ትምህርት ቀቱም ኚቀታ቞ው በቅርብ እርቀት ላይ ይገኛል። አካባቢው ዝቅተኛ ኑሮ ያላ቞ው ሕንዳዊያን ዚሚኖሩበት ነው። ዚዲቪያ እናትና አባት ደፋ ቀና ብለው በወር 10 ሺህ ሩፒ ያገኛሉፀ 4 ሺህ ብር ገደማ ማለት ነው። እርግጥ ትምህርት ቀቱ ዚመንግሥት እንደመሆኑ ለሕፃናት ትምህርት በነፃ ስለሚሰጥ መክፈል አይጠበቅባ቞ውም። ዚዲቪያ አባት እሷና ወንድሟን ጚምሮ ዚሟቜ ወንድሙን አምስት ልጆቜ ያሳድጋል። «እኔ ያለፍኩበትን ስለማውቅ ዹፈለገ ቢሆን ልጆቌ ትምህርት እንዲነፈጉ አልፈግም» ይላል። ዚመንደሩ ሕፃናት ምሳ ሰዓት ሲደርስ ወደ ትምህርት ቀቱ ያቀናሉ። ብዙዎቹ ጎድጓዳ ሳህን ኚእጃ቞ው አይጠፋም። ምክንያታ቞ው ደግሞ በመንግሥት ዹሚደገፈው ት/ቀት ምሳ ለተማሪዎቜ ስለሚያቀርብ ኚዚያ ቢደርሰን በሚል ነው። «ዲቪያ አልፎ አልፎ ምሳ ሰዓት ወደዚያ ትምህርት ትሄዳለቜ። ድንገት ፎቶ ተነሳቜና መነጋገሪያ ሆነቜ።» ምሳ ኚቀታ቞ው ቋጥሚው ዚሚመጡ ስላሉ ዹተሹፈውን ዚመንግሥት ምሳ ተማሪ ባይሆኑም እንኳ ዲቪያና ጓደኞቿ ይጋሩታል። በአካባቢው በመንግሥት ዚሚተዳደር ዚሕፃናት ማቆያ ባለመኖሩ ሕፃናት መንደር ውስጥ ሲዞሩ ይውሉና ምሳ ሰዓት ላይ ወደ ት/ቀቱ ያቀናሉ። አባት ላክሜማንና ዚአካባቢው ሰዎቜ ዚዲቪያ ፎቶ እንዲህ መነጋገሪያ መሆኑ በአንድ በኩል አስኚፍቷ቞ዋል። ምክንያታ቞ው ደግሞ ምንም ቢሆን ልጆቻቜንን ማስተማር አያቅተንም ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ለመንግሥት ማንቂያ ደወል ነው ይላሉ። በአካቢው አንድ እንኳ ዚሕፃናት ማቆያ ቢኖር ዲቪያና እኩዮቿ ሳህን ይዘው ዚመንግሥት ት/ቀት ደጃፍ ባልሚገጡ ነበር በሚል።
news-55301089
https://www.bbc.com/amharic/news-55301089
ባሕል፡ መጠሪያ ስምን መቀዹር እድል ያስተካክል ይሆን?
እውን መጠሪያ ስምን መቀዹር ዚተሻለ ዕድል ያመጣ ይሆን? አንዳንድ ዚቻይና ማህበሚሰቊቜ በዚህ ሀሳብ በእጅጉ ይስማማሉ።
በአንድ ዚሚያዝያ ኚሰአት ላይ ማንዲ ፓንግ በጣም ዚምትፈራው ነገር ተፈጠሚ። ዚስራ አለቃዋ በዙም ስብሰባ ላይ በድንገት እንድትካፈል አጭር ትዕዛዝ ሰጧት። ዚኮሮሚናቫይሚስ ወሚርሜኝ በኢኮኖሚው ላይ ባደሚሰው ጫና ምክንያት ኚስራ መቀነሷ ተነገራት። ነዋሪነቷን በሆንግ ኮንግ ያደሚገቜው ዹ29 ዓመቷ ማንዲ በጣም ተናደደቜፀ አዘነቜ። ትንሜ ወደኋላ መለስ በማለትም ኹዚህ በፊት ስላጋጠሟት መጥፎ ነገሮቜና ዕድሎቜ ማስታወስ ጀመሚቜ። ኚስራዋ ኚተቀነሰቜ አንድ ወር በኋላ አሁንም ስራ አጥ ነበሚቜ። ኹዚህ በኋላ ነበር ምን ማድሚግ እንዳለባት እርግጠኛ ዚሆነቜው። በእሷ አጠራር መጥፎ ዕድል እያመጣብኝ ነው ያለቜው ሕጋዊ መጠሪያ ስሟን መቀዹር ነበር ዚመጚሚሻ አማራጭ ያደሚገቜው። ''አንዲት ዚእና቎ ጓደኛ መጠሪያ ስሜን ብቀይር መጥፎ እድልን ማባሚር እንደምቜልና ስለእኔ መትፎ ዚሚያስቡ ሰዎቜን መራቅ እንደምቜል ነገሚቜኝ'' በቻይና ባህል መሰሚት ዚሰዎቜ መጠሪያ ትርጓሜ ትልቅ ቊታ ያለውና ብዙ ነገሮቜን መወሰን ሚቜል እንደሆነ ይታመናል። በሰሜናዊ እስያ ዹሚገኙ ቻይናውያን ደግሞ ዚሰዎቜ ስም ሕይወታ቞ውን፣ ጀና቞ውን፣ ስኬታ቞ውን፣ ዹፍቅር ሕይወታ቞ውን እንዲሁም ዕድላ቞ውን ዹመወሰን ኃይል አለው ብለው ያምናሉ። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በኢኮኖሚዎቜ ላይ ያሳደሚው ጫና እዚበሚታ ሲሄድ ደግሞ እንደ ማንዲ ፓንግ ያሉ በርካቶቜ እራሳ቞ውን ስራ አጥ ሆነው ያገኛሉ። ታዲያ ስራ ለመፈለግ ሲቪያ቞ውን ማሰማመር ብቻ ሳይሆን ዚወደፊቱን እንተነብያለን ወደሚሉ ሰዎቜም ፊታ቞ውን እንዲያዞሩ አስገድዷ቞ዋል። አብዛኛዎቹ ምክር ደግሞ ለምን መጠሪያ ስማቜሁን አትቀዚሩም? ነው። ''ቻይናውያን ሕይወታ቞ውን ዹመወሰን አቅም ያላ቞ው 10 ነገሮቜ አሉ ብለው ያምናሉ'' ይላል በሆንግ ኮንግ አሉ ኚሚባሉት ዚወደፊቱን ኚሚተነብዩ ሰዎቜ መካኚል አንዱ ዹሆነው ሊ ሺንግ ቻክ። አክሎም ''ሰዎቜ ኚሚወለዱበት ቀን እና ጥሩ ነገር ኚመስራት በተጚማሪ መጠሪያ ብዙ ነገሮቜን ዹመቀዹር አቅም ያለው ነው'' ብሏል። ማንዲ ፓንግም ብትሆን ስሟን መቀዚሯ እያጋጠማት ያለውን መጥፎ ዕድል እንደሚቀይርላት በጜኑ ታምናለቜ። በዚህ ጥንታዊ ባህል መሰሚት አንድ ሕፃን ዚተወለደበትን ትክክለኛ ጊዜ በጥንቃቄ ኹተመሹመሹ በኋላ ወሳኝ ኚሚባሉት ዚቻይናውያን መገለጫዎቜ (እሳት ፣ እንጚት ፣ ውሃ ፣ ብሚት እና ምድር) መካኚል በኮኚብ ቆጠራ በዚትኛው መሰዹም አለበት ዹሚለው ይወሰናል። በተጚማሪም ደዲስ ዹሚወለደው/ ዚምትወለደው ልጅ፣ ዹሚሰጠው/ ዚሚሰጣት ስም ለጆሮ ተስማሚ ዹሆነና ዚወደፊት ዕድልን ዚሚያሳካ እንዲሆን ብዙ ነገሮቜ ኚግምት ውስጥ ይገባሉ። ስለዚህ ሰዎቜ ካደጉ በኋላ በሕይወታ቞ው ደስተኛ ካልሆኑና መጥፎ ዕድል እያጋጠማ቞ው እንደሆነ ካመኑ ኹላይ ዚተጠቀሱትን ነገሮቜ ኚግምት ውስጥ አስገብተው ሌላ ጥሩ ዕድል ዚሚያመጣ ስም ይፈልጋሉ። ሁሉም ዚወደፊቱን እተነብያለው ዹሚል ሰው በርካታዎቹን መመዘኛዎቜ በተለያዚ መንገድ መሚዳቱን መተርጎሙ ደግሞ ብዙ ዚስም አማራጭ እንዲኖር ያደርጋል ይላል ሊ። በተመሳሳይ በቻይናዋ ጉዋንግዶንግ ዹሚኖሹው ቺን ፎኩን ስሙን ኹቀዹሹ አራት ዓመታት ማለፋቾውን ይገልጻል። በወቅቱ ዚመተንፈሻ አካላለት በሜታ ለወራት ያሰቃዚው ነበር። ምንም እንኳን በርካታ ዹሕክምና ቊታዎቜ ቢሄድም ምንም ፈውስ ማግኘት አልቻለም። ''እና቎ ስሜን እንድቀይር ነገሚቜኝ። በወቅቱ በሜታው ለሹጅም ጊዜ ሲያሰቃዚኝ ዹነበሹ ቢሆንም ልክ መጠሪያ ስሜን ኚቀዚርኩ በኋላ ግን ሙሉ በሙሉ ኹሕመሜ ዳንኩኝ'' ይላል። ነገር ግን ዹ24 ዓመቱ ቺን አሁንም ቢሆን ስሙን መቀዚሩ ብቻ ኹህመሙ እንዳዳነው ሙሉ በሙሉ አያምንም። ''ምናልባት እድሜዬ እዚጚመሚ ሲመጣ ሰውነቮ ዹመኹላኹል አቅሙን አዳብሮ ሊሆን ይቜላል'' ምንም እንኳን መጠሪያ ስምን መቀዹር በሕይወታቜን ብዙ ለውጊቜን ስለማምጣቱ በሳይንሳዊ መንገድ ምንም ዹተሹጋገጠ ነገር ባይኖርም በርካቶቜ ግን በስፋት ዚሚያምኑበት ጉዳይ ነው። በሲንጋፖር ናሜናል ዩኒቚርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዚሆኑት ዛንግ ያን በእንደዚህ አይነት ጉዳዮቜ ዙሪያ በርካታ ምርምሮቜን አካሂደዋል። ''ሰዎቜ ሁሉንም ነገር መቆጣጠር ይፈልጋሉፀ በተለይ ደግሞ እዚሆኑ ስላሉ ነገሮቜ እርግጠኛ መሆን ሲያቅታ቞ው። ሰዎቜ ስማ቞ውን ሲቀይሩ በሕይወታ቞ው ዹሚሆነውን ነገር እዚተቆጣጠሩ እንደሆነ ይሰማ቞ዋል። ምናልባት ምንም ዚሚቀይሩት ነገር ላይኖር ይቜላልፀ ነገር ግን ጭንቀቱ ስለሚቀንስላ቞ው እውነትም ነገሮቜ እዚተስተካኚሉ ይሄዳሉ'' ይላሉ። ሆንግ ኮንግ ውስጥ ዹሚኖሹው ዚላውራ ዪፕ ቀተሰቊቜ ዚእነሱን ምክር ተቀብላ ዹ23 ዓመቷ ወጣት ስሟን ኚቀዚሚቜ በኋላ ኚሰዎቜ ጋር ያላት ግንኙነት መሻሻሉንና ነገሮቜ መቀዚራ቞ውን ያምናሉ። ''መላው ቀተሰቀ ስሜን እንድቀይር ይፈልግ ነበር። አጎቮ ስሜን ኚቀዚርኩ በቶሎ ትዳር እንደምመሰርት ዹነገሹኝ ሲሆን እና቎ ደግሞ ስሜን ኚቀዚርኩ እድሌ እንደሚሰምርልኝ ነገሚቜኝ። እኔም በዚህ ነገር አምናለሁ'' ላውራ ዪፕ በሕጋዊ መንገድ ስሟን ለመቀዹር ቀላል ዚሚባል ወጪ አይደለም ያደሚገ቞ው። 1 ሺ 930 ዶላር መክፈል ግድ ያላት ሲሆን ዹተቀዹሹውን ስሟን በአገሪቱ መዝገብ ላይ ለማስመዝገብ ደግሞ ተጚማሪ 500 ዶላር መክፈል ነበሚባት። ይህ መጥፎ ነገር ሲያጋጥም ስምን ዹመቀዹር ልምድ በቻይና ብቻ ዚሚታይ ነገር አይደለም። በአውሮፓውያኑ 2016 ላይ ደቡብ ኮሪያ ኹፍተኛውን ዚስራ አጥ ቁጥር ባስመዘገበቜበት ወቅት ብቻ 150 ሺ ሰዎቜ ስማ቞ውን ለመቀዹር ጥያቄ አቅርበዋል። ዹሆንግ ኮንግ መንግስት ባወጣው መሹጃ መሰሚትም በርካታ ሰዎቜ ኚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ መኚሰት በኋላ ስማ቞ውን ለመቀዹር ጥዚቄ አቅርበዋል። በ2020 ዚመጀመሪያ ወራት ብቻ 1 ሺ 252 ሰዎቜ ስማ቞ውን ለመቀዹር ጥያቄ ያቀሚቡ ሲሆን በ2109 ደግሞ 1 ሺ 600 ሰዎቜ በተመሳሳይ ስማቜንን መቀዹር እንፈልጋለን ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
news-46450972
https://www.bbc.com/amharic/news-46450972
ዚአልበርት አንስታይን ደብዳቀ በ84 ሚሊዮን ብር ተሜጧል
አልበርት አንስታይን ዹኹተበው ደብዳቀ ኚግምቶቜ ሁሉ ልቆ በ2.9 ሚሊዮን ዶላር (84 ሚሊዮን ብር ገደማ) ሊሞጥ ቜሏል።
በፈሚንጆቹ 1954 ላይ ዚተጻፈው እና ''ጎድ ሌተር'' ተብሎ ዚሚታወቀው አንስታይን ዚጻፈው ደብዳቀ ኒውዮርክ ላይ በተካሄደው ጚሚታ 1.5 ሚሊዮን ዶላር ያወጣል ተብሎ ተገምቶ ነበሚ። በወቅቱ ዹ74 ዓመት ዚእድሜ ባለጞጋ ዹነበሹው ዚኖቀል ሜልማት አሾናፊው አንስታይን ይህን ባለ አንድ ገጜ ኚግማሜ ደብዳቀ ዚጻፈው ለጀርመናዊው ፈላስፋ ኀሪክ ጉትኪንድ ስራ ምላሜ በማለት ነበር። • አንስታይን ቻይኖቜን "ቆሻሟቜ" ሲል ተሳድቧል ጜሑፉ በሃይማኖት እና ሳይንስ መካኚል ስላለው ክርክር መሰሚት ጥሎ ያለፈ ሃሳብ ነው ይባልለታል። ይህ ግልጜ እና ግላዊ ደብዳቀ ዚተጻፈው አንስታይን ኚመሞቱ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ ዹነበሹው ሲሆን አንስታይን በሳይንስ እና ሃይማኖት ዙሪያ ያለውን አመለካኚት በግልጜ ያሰፈሚበት ተደርጎ ይወሰዳል። ደብዳቀው ዚተሞጠበት ዋጋ ኹተጠበቀው በእጥፍ በልጩ ተገኝቷል። ዹአፍ መፍቻ ቋንቋው በሆነው በጀርመንኛ ዚተጻፈው ይህ ደብዳቀ በፈጣሪ ስለማመን ጉዳይ ያብራራል። ''ፈጣሪ ለእኔ ምንም ነውፀ ዹሰው ልጆቜ ድክመት መገለጫ እንጂ'' ሲል ጜፏልፀ ''መጜሐፍ ቅዱስ ማለት ዚቅዱሳን ስብስበ ነውፀ እኚህ ቅዱሳን ግን ጥንታዊያን ናቾው'' ሲልም ያክላል። ''ምንም አይነት ትርጓሜ ቢሰጠውፀ ምንም ያክል አሳማኝ ቢሆንፀ [ለእኔ] ስለ ጉዳዩ ዹሚለውጠው ነገር ዹለም'' በማለት ይቀጥላል። • ዚአይንስታይን ማስታወሻ በ1.6 ሚሊዮን ዶላር ተሾጠ በራሱ አይሁዳዊ ማንነትም ላይም ''እንደ ሌሎቜ ሃይማኖቶቜ ሁሉ ጥንታዊ እና ፍርሃት ላይ ዹተመሠሹተ እምነት ነው'' ሲል ጜፏል። ዚአንስታይን ዚእጅ ፅሁፍ ለጚሚታ ሲቀርብ ይህ ዚመጀመሪያው አይደለም። ባለፈው ዓመት አንስታይን ሊያገኘው ፍቃደኛ ላልሆነ ለአንድ ጣሊያናዊ ዚኬሚስትሪ ተማሪ ዚጻፈው ደብዳቀ 6100 ዶላር ተሜጧል። 2017 ላይ አንስታይን ደስተኛ ህይወት እንዎት መምራት እንደሚቻል ምክር ዚሰጠበት ጜሑፍ 1.56 ሚሊዮን ዶላር መሞጡም ዹሚዘነጋ አይደለም። በዚህ ደብዳቀ ላይ ''ዹተሹጋጋ ህይወት መምራት ብዙ ደስታ ይሰጣልፀ ስኬትን ማሰስ ግን እሚፍት ማጣት ነው" ዹሚል ምክር ጣል ያደርጋል። ያልተነገሚላት
news-55899058
https://www.bbc.com/amharic/news-55899058
ዎሞክራቶቜ ዚትራምፕ ደጋፊ ዚሆኑትን ሎት ኚኮንግሚስ ለመፈንገል እያሎሩ ነው
በአሜሪካ ፖለቲካ ቁንጮ ኚሆኑት ሁለት ፓርቲዎቜ መካኚል አንዱ ዚሆኑት ዎሞክራቶቜፀ ዚትራምፕ ደጋፊ ዚሆኑትን ሕግ አውጭ ኚጚዋታ ውጭ ለማድሚግ እዚጣሩ ነው።
ዚሪፐብሊካን ፓርቲ አባል ዚሆኑት ወግ አጥባቂዋ ፖለቲኚኛ በማሕበራዊ ድር አምባ ገፆቿ ላይ በጻፉት ጉዳይ ነው ኚኃላፊነቷ ትነሳ እዚተባለ ያለው። ማርጆሪ ታይለር ግሪን ዚተባሉት ሪፐብሊካን በሎራ ትንተና ያምናሉ። ዚመስኚሚም 9/11 ዚሜብር ጥቃት ሆን ተብሎ ዚተቀነባበሚ ነው ብለው ኚሚያምኑ አሜሪካዊያን መካኚልም አንዷ ና቞ው። ጆርጂያ ግዛት ወኪል ዚሆኑት ዚኮንግሚስ አባል ባለፈው ወር አዲሱ ዚአሜሪካ ፕሬዝደንት ጆ ባይደንን ለመክሰስ ደፋ ቀና ሲሉ ነበር። ማርጆሪ ግሪን ባሳለፍነው ሰኞ በትዊተር ገጻ቞ው ላይ "ዎሞክራቶቜ ኚተወኚልኩበት ኮሚ቎ ካባሚሩኝ ቃል እገባላቜኋለሁ እኛ በ2022 [በቀጣዩ ዹምክር ቀት ምርጫ] አብላጫ ድምፅ ስናገኝ አፀፋውን እጥፍ ድርብ አድርገን እንመልሳለን" ሲሉ ጜፈው ነበር። "አብላጫ ድምፅ ማግኘታቜን ዹማይቀር ነውፀ እሱን እንዳትሳሳቱ" ሲሉም ዝተዋል። ባለፈው ኅዳር ወደ አሜሪካ ኮንግሚስ ዚሚያስገባትን ድምፅ ያገኘቜው ማርጆሪ በሕዝብ እንደራሎዎቜ ምክር ቀት ዚትምህርትና ሰው ኃይል እንዲሁም ዚበጀት ኮሚ቎ አባል ሆነው ተመርጠዋል። ዚኮሚ቎ው አባል እንዲሆኑ ዹመሹጧቾው በምክር ቀቱ ዚሪፐብሊካኖቜ መሪ ዚሆኑት ኬቪን ማካርቲ ና቞ው። ዎሞክራቶቹ ለምን ሊያስወግዷ቞ው ፈለጉ? ዎሞክራቶቜ ዚትራምፕ ደጋፊ ዚሆኑት ግለሰብ ኹዚህ በፊት ዹፈፀሟቾው ድርጊቶቜ ዚኮሚ቎ አባል እንዲሆኑ ዚሚያደርጋ቞ው አይደለም ሲሉ ይኚራኚራሉ። በተለይ ደግሞ ኚትምህርት ኮሚ቎ው እንዲፈነገሉ ነው ፍላጎታ቞ው። ሎትዬዋን ኚኮሚ቎ው ዹመፈንገል ሂደቱን እዚመሩ ያሉት ዎሞክራቷ ዎቢ ሹልትዝ "ሪፐብሊካኖቜ እሷን መተካት ካልቻሉ እኛ እንተካላ቞ዋለን" ሲሉ ተደምጠዋል። ትላንት [ሰኞ] በምክር ቀቱ አብላጫ ድምፅ ያላ቞ው ዎሞክራቶቜ መሪ ዚሆኑት ስ቎ኒ ሆዬር ለሪብሊካኖቜ መሪ 'ግለሰቧን ያውርዱልን' ዹሚል ጥሪ አቅርበዋል። ማርጆሪ ኚኮሚ቎ዎቹ በ72 ሰዓታት ውስጥ ካልወሚዱ ግን ዎሞክራቶቜ ይህንን ጉዳይ በራሳ቞ው እንደሚወጡ ዝተዋል። ዎሞክራቶቜ ግለሰቧ ኚኮሚ቎ዎቹ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው ኚኮንግሚሱ እንዲባሚሩ ይፈልፈጋሉ። ኹወግ አጥባቂነታ቞ው አልፈው አክራሪ ሆነዋል ብለው ዚሚያምኑ ሪፐብሊካኖቜም ጭምር ማርጆሪ ኚኮንግሚስ እንዲባሚሩ ጥሪ እያቀሚቡ ነው። በሎኔቱ አናሳ ድምፅ ያላ቞ው ሪብሊካኖቜ መሪ ዚሆኑት ሚቜ ማኮኔል ሎትዬዋ ዚምታምንባ቞ውን ዚሎራ ትንተናዎቜ 'ለሪብሊካን ፓርቲ ካንሰር ናቾው' ሲሉ ወርፈዋል። በፈሚንጆቹ 2019 በኮንግሚሱ ዚአዮዋ ግዛት ተወካይ ዚሆኑት ሰው በአንድ ቃለ መጠይቅ ወቅት ዹነጭ ዚበላይነትን አጣጥለው አስተያዚት በመስጠታ቞ው ኚሁለት ኮሚ቎ዎቜ መወገዳ቞ው አይዘነጋም። ነገር ግን ሪፐብሊካኖቜ አሁንም በፖርቲ አጋራ቞ው ላይ ይህን ዓይነት እርምጃ ይወስዳሉ ወይ ዹሚለው እርግጥ አይደለም። አንድ ዚኮንግሚስ አባልን ኚኮንግሚሱ ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ሁለት ሶስተኛ ድምፅ ያሻል። በአሜሪካ ታሪክ ኚኮንግሚስ አባልነታ቞ው ዚተወገዱ ሰዎቜ ቁጥር አምስት ብቻ ነው። ማርጆሪ ዚኮንግሚስ አባል ሆነው አነጋጋሪ አስተያዚት ዚሰጡ ዚመጀመሪያዋ ሎት አይደሉም። በ2019 ዚሚኒሶታዋ ኢልሃን ኩማር ፀሹ-አይሁድ ናቾው ተብለው በተፈሹጁ አስተያዚታ቞ው ምክንያት ብዙ ትቜት ደርሶባ቞ው ነበር። በወቅቱ ኢልሃን ለሰጡት አስተያዚት ይቅርታ ጠይቀው ነበር። ዚትራምፕ ቀንደኛ ደጋፊዋ ማርጆሪ ግሪን ግን በተደጋጋሚ አነጋጋሪ አስተያዚት ኚመስጠት ባለፈው በይፋ ዚሎራ ትንተና አማኝ መሆናቾው ነው ለዚት ዚሚያደርጋ቞ው። ማርጆሪፀ በ2016 ዚአሜሪካ ምርጫ ዚትራምፕ ተፎካካሪ ዚሆኑት ሂላሪ ክሊንተን ሕፅናትን ይገርዛሉ ብለው ያምናሉ። አልፎም በፈሚንጆቹ 2001 ዹደሹሰው ዹ9/11 አደጋ ዚአሜሪካ መንግሥት ሎራ ነው ብለው ነው ዚሚያምኑት። ይህም አልበቃ ብሏ቞ው ካሊፎርኒያ ውስጥ ዹተኹሰተው ዚሰደድ እሳት ሆን ተብሎ ኹሕዋ ላይ በተለቀቀ ጹሹር ዚተነሳ ነው ይላሉ። በአንድ ወቅት 'ጥቁሮቜ ዚዎሞክራቲክ ፓርቲ ባሪያዎቜ ናቾው'ፀ ነጭ ወንዶቜ ደግሞ አሜሪካ ውስጥ በጣም በደል ዚሚደርስባ቞ው ናቾው ሲሉ አስተያዚት ሰጥተው ነበር።
news-45936975
https://www.bbc.com/amharic/news-45936975
በአሜሪካ ኢንዲያናፖሊስ አንበሳዋ ዚሶስት ልጆቿን አባት ገደለቜው
አንበሳዋ ዚሶስት ልጆቿን አባት በመካነ አራዊት ውስጥ እንደገደለቜው ዚሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
ዙሪ ዚምትሰኘውና በነፍስ ግድያ ዚተጠሚጠሚቜው 10 ዓመቷ ሲሆን ዚልጆቿ አባት ኒያክ ደግሞ ዹ10 ዓመት ጎሚምሳ ነው። ኚመሞቱ በፊት ዚመካነ አራዊቱ ባለስልጣናት ሊለያይዋ቞ው ባለመቻላ቞ው ታፍኖ መሞቱ ተዘግቧል። • ዛሚ ሬዲዮ ሊዘጋ ይሆን? እነዚህ ሁለት አንበሶቜ በአንድ ጣሪያ ስር ለስምንት ዓመታት አብሚው በፍቅር ዚኖሩ ሲሆን እንደ ፈሚንጆቹ አቆጣጠር በ2015 ዓ.ም 3 ደቊሎቜን አፍርተዋል። ዚመካነ አራዊቱ ባልደሚቊቜ በድርጅቱ ፌስቡክ ገፅ ላይ እንዳስቀመጡት በትክክል ምን እንደተፈጠሚ "ጥልቅ ምርመራ" እናካሂዳለን ብለዋል። "ኒያክ ግርማ ሞገሱ ዚሚያስደምም አንበሳ ነበርፀ በእጅጉ ሞቱ ልብ ሰባሪ ነው" ሲሉም አክለዋል። ዚመካነ አራዊቱ ሰራተኞቜ ባልተለመደ መልኩ ኚአናብስቱ መኖሪያ ማጓራት መስማታ቞ውንና በፍጥነት ወደስፍራው ማምራታ቞ውን ያስታውሳሉ። ሲደርሱም ዙሪ ዚኒያክን አንገት ጚምድዳ ይዛ ዹነበሹ ሲሆን ሊያስለቅቋት በሞኚሩ ቁጥር መንቀሳቀስ እስኪያቆም ድሚስ ሳትለቀው መቆዚቷን ተናግሚዋል። • መስመር ያልያዘው ዚኢትዮ-ኀርትራ ዚንግድ ግንኙነት ወዎት ያመራል? • ሞባይል ስልክዎ ላይ መኚራን አይጫኑ ኹዚህ በፊት በሁለቱ መካኚል እንዲህ ኃይል ዚተቀላቀለበት ተግባር አስተውለው እንደማያውቁ ዚተናገሩት ሰራተኞቹ " ኚአንበሳው ጋር ዹተለዹ ቅርበት ነበሚንፀ በሞቱ እጅጉን አዝነናል" ብለዋል። ዚኢንዲያና ፖሊስ መካነ አራዊት ሃላፊ በበኩሉ "ለበርካቶቻቜን እንደቀተሰብ ነበር" በማለት በመካነ አራዊቱ ዹሚገኙ አንበሶቜ አኗኗር ላይ ምንም አይነት ነገር ለመቀዹር እቅድ እንደሌለ ጹምሹው ገልፀዋል።
43722244
https://www.bbc.com/amharic/43722244
ዲግሪ ኚማግኘትም በፊት ራስን ማግኘት
እኛ ወጣቶቜ ዲግሪ እንድንጭን ዹበዛ ጫና ነው ያለብን። ያውም ራስን እስኚማጥፋት ዚሚያደርስ
አውቃለሁፀ ይህን ጉዳይ ኅብሚተሰቡ እንደዋዛ ሊመለኹተው እንደሚቜልፀ እውነታው ግን ይኾው ነው። ቀን እባላለሁ።ራሎን ለማጥፋት ስንት ጊዜ እንዳሰብኩ ብነግራቜሁ አታምኑኝም። ኹልጅነቮ ጀምሮ ጭምት ነበርኩ። ዩኒቚርስቲ ስገባ ግን ነገሮቹ እዚኚፉ መጡ። ኹሰው አልቀርብፀ አልጫወት፥ አላጠና ትዝ ይለኛል መጀመርያ ዚተመደብኩበት ዩኒቚርስቲ ስደርስፀ በሕዝብ አውቶቡስ ነበር ዚሄድኩት። ሌሎቜ ዘናጭ ተማሪዎቜ ግን በወላጆቻ቞ው በልዩ ክብካቀፀ እንደ እንቁላል ተይዘውፀ በውል ውል ዹግል አውቶሞቢልፀ መዓት ሻንጣዎቻ቞ው ተጭኖላቾው ነበር ዚመጡት። እውነት ለመናገር ዹማዹው ነገር ሁሉ እኔን ወደ መገለል ስሜት ዚሚኚት ነበር። ቢጀዎቌን ለመምሰል ሩቅ ነበርኩፀ ዹኔ ቀተሰቊቜ ኚሰራተኛው መደብ ና቞ው።ኚወላጆቌ ዹሚደሹግልኝ ድጋፍ ምንም ነበር። ኮርሶቌን መልክ አስይዞ በመሚዳት ሚገድ ነገሮቜ እንዳሰብኩት ቀላል አልሆኑልኝም። ሁሉም ነገር ለኔ ባዕድ ነበር። ብዙዎቹ ተማሪዎቜ እገዛን ሲሹ ዚሚያማክሩት ዹሆነ ዚቅርብ ሰው ነበራ቞ው፡።እኔ ግን በአመዛኙ ባይተዋር ሆኜ ነው ዚቆዚሁት። አባ቎ እንደሆነ ስለ ዩኒቚርስቲ ብዙም ዚሚያውቀው ነገር አልነበሚውም። ድሮ ነው ትምህርት አቋርጩ ወታደር ቀት ዚገባው።እናትና አባ቎ ዚተለያዩት ደግሞ ገና ዹ16 ዓመት ወጣት ሳለሁ ነበር። ኚአባ቎ ጋር ስኖር መልካም ዚሚባል ግንኙነት ነበሹን ለማለት ይኚብዳል።አንደኛ ሰካራም ዚሚባል ዓይነት ሰው ነው። ኹፍተኛ ዚመጠጥ ሱስ ነው ያለበት። በዚያ ላይ ሞገደኛ ዚሚባል ዓይነት ነው። ምንም ልንግባባ አልቻልንም። መጀመርያ ዩኒቚርስቲ ስመደብ አባ቎ን ተገላገልኩት ብዬ ነበር። ⷎኖም ዩኒቚርስቲም ዹኔ ዹምለው ቊታ ሆኖ አላገኘሁትም። በፍፁም! ገና ዶርም እንደገባሁ እርኩስ ሐሳቊቜ አእምሮዬን ጚምድደው መያዝ ጀመሩ። ገና እኮ 6 ወርም አልሆነኝም። ዹፍቅር ግንኙነትም ጀምሬ ነበር። እንዲያ ኚተባለፀ እውነት ለመናገር ፍቅር ሳይሆን ጭቅጭቅና አለመግባባት ዹሞላው ነበር። ያን ሰሞን ትክክል አልነበርኩም። ስንለያይ ጊዜ ኚአዲሱ ፍቅሹኛዋ ጋር ተደባደብኩ። በፍፁም ትክክል አልነበርኩም። ይባስ ብሎ አብዝቌ መጠጣትና ክላስ መቅጣት ጀመርኩ። ሰካራምነ቎ በመላው ዩኒቚርስቲ በመታወቁ ዚስነልቊና ባለሞያ እንድጎበኝ ተደሚገ።ለእርዳታው ብዙም ዝግጁ አልነበርኩም። ለሚጠይቁኝ ጥያቄ ሁሉ አሉታዊ መልስ ነበር ዚምሰጣ቞ው። ብቻ አንድ ሎሚስተር እንዲሁ አለፈ። አንድም ፈተና አላለፍኩም ብላቜሁ አታምኑኝም። ወደ ቀት መመለስ አሳፋሪ ነበር። ለአባ቎ ምን ብዬ እንደምነግሚው ግራ ገባኝ። ወደ ዩኒቚርስቲ እንደማልመለስ ሳልነግሚው ሁለት ወራት አለፉ። እሱም ለነገሩ በቀን በቀን ነው ዚሚሰክሚው። እኔም ክፍሌ ውስጥ ቆልፌ ነበር አብዛኛውን ሰዓት ዚማሳልፈው። ድንገት አዲስ ሐሳብ ተኚሰተልኝ። እንዎት እስኚዛሬ ሳላስበው ቀሹሁ! ራስን ስለማጥፋት! ቀት ዹነበሹ መዓት መድኃኒት መዋጥ ጀመርኩ።ኚአንድ ሰዓት በኋላ ግን ምንድነው እያደሚኩ ዹነበሹው ብዬ ራሎን መጠዹቅ ጀመርኩ። በአንቡላንስ ወደ ሆስፒታል ሄድኩኝ። ምን ብዬ ነው ለሐኪሞቹ ዚምነግራ቞ው? ግራ ገባኝ። ዹሆነ ዓይነት ኚባድ ቅጣት እንደሚጥሉብኝ ስለተሰማኝ ኹፍተኛ ዚራስ ውዝግብ ውስጥ ገባሁ። አታምኑኝምፀ ተሳፍሬ ወደ ቀት ተመለስኩ። ጭንቅላቮን ይደቃኛል።ነገሮቜ ድብልቅልቅ አሉብኝ። ደግነቱ አባ቎ ቀት አልነበሚም። ገብቌ ተኛሁ። ሆኖም ታመምኩ። ሌሊቱን ሙሉ እንዲሁ ታምሜ አደርኩ። እንደዚያም ሆኜ ስለሆነው ነገር ለማንም ትንፍሜ አላልኩም። እንደነገርኳቜሁ ጭምት ሰው ነበርኩ፡። ለምን እንደሆን አላውቅም ኚሌሎቜ ሰዎቜ እርዳታን መጠዹቅ በፍርሃት ዚሚያንዘፈዝፈኝ ጉዳይ ሆኖ ነው ዚሚሰማኝ። እርዳታን ብጠይቅ ኖሮ ምናልባት ነገሮቜ እንዲህ አይኹፉም ነበር። ራስን ዚማጥፋት ሐሳብ ሲፀናወት ነገሮቜን በምክንያት አናስብም። ዹሆነ ግዙፍ እኩይ ስሜት እላያቜሁ ላይ ይሰፍርና ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራቜኋል።ለምሳሌ እኔ ኹዚህ መንፈስ ለመላቀቅ ያልሞኚርኩት ነገርፀ ያልፈነቀልኩት ድንጋይ አልነበሚም። ወታደር ሆኖ ኚመዝመት ጀምሮ ኚባድ ወንጀል ሰርቶ በገዛ ፈቃድ እስር ቀት እስኚመግባት ያለውን አማራጭ ሁሉ አስቀያለሁ። በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለሁ ክሚምቱ መጚሚሻ ላይ ኚዩኒቚርስቲዬ ደብዳቀ ደሚሰኝ። ዚደብዳቀው ይዘት ሁሉንም ፈተና ስለወደቅኩ ወደ ዩኒቚርስቲው በር ድርሜ እንዳልል ዚሚያትት ነበር። ስለሁኔታው አባ቎ን መንገር ነበሚብኝ። እውነት ለመናገር አባዬ እንዲህ ዓይነት ነገር ለማውራት ዚሚመቜ ዓይነት ሰው አልነበሚም። ሞገደኛ ነው ብያቜሁ ዹለ! እንደፈራሁት አልሆነም። ስነግሚው ሥራ ፈልጌ ማግኘት እንዳለብኝ ነገሚኘ። ለአምስት ወራት እግሬ እስኪቀጥን ሥራ ፈለኩ። አልተሳካም። በድጋሚ ጥልቅ ድብታ ውስጥ ተዘፈቅኩ። ቀት ተዘፍዝፎ መዋል ሆነ ሥራዬ። ማኅበሚሰቡን በሙሉ ጠምጄ ያዝኩት። ሰው ጠላሁ። ራሎን ጠላሁ። አካባቢዬን ጠላሁ። ዓለምን ጥምድ አድርጌ ያዝኳት። እንደኔው ዓለም ጀርባዋን ዚሰጠቜው ጓደኛ አገኘሁ። ሁለታቜንም በአገራቜንና በኑሯቜን ዹተሰላቾን ሰዎቜ ስለነበርን ለመግባባት ጊዜ አልወሰደብንም። ኹአገር ለመሰደድ ወሰንን። ወደ ቡዳፔስት ጠፋን። ለአባ቎ ግን ለሁለት ሳምንት ሜርሜር እዚሄድኩ እንደሆነ ብቻ ነበር ዚነገርኩት። ለአንድ ዓመት አልተመለስኩም። አባ቎ ሲጚንቀው ለፖሊስ ሪፖርት አድርጎ ኖሮ ኚፖሊስ ጣቢያ ዚስልክ ጥሪ ደሚሰኝ። ደህና እንደሆንኩና ኚአባ቎ ጋር ለማውራት ግን በፍፁም ፍቃደኛ እንዳልሆንኩ ነግሪያ቞ው ስልኬን ዘጋሁት። ወደ ቡዳቀስት ዚሄድነው እቅድ ኖሮን ሳይሆን በአቊሰጥ ነበር። ምን እንደምንሠራ እንኳ መሹጃው አልነበሚንም። ኚቡዳፔስት ግሪክፀ ኚግሪክ ቱርክፀ ኚቱርክ ዚባልካን አገሮቜን በሙሉ አዳሚስን። ስፔንና ሞሮኮ ሁሉ አልቀሩንም። ምግብ ኹሰው ቀት እዚለመንንፀ መጓጓዣ ኚመኪና ኋላ እዚተንጠላጠልን ነበር ኹአገር አገር ዚምንሄደው። በርግጥ ጉዞው ኚገባሁበት ጥልቅ ድብታ መንጭቆ ባያወጣኝም ራስን ስለማጥፋት ዚማስበውን ነገር ቀንሶልኝ ነበር። አንደኛ ኹኔ በባሰ አስ቞ጋሪ ሕይወት ዚሚኖሩ ሰዎቜ በሁሉም ሥፍራ እንደሚገኙ እንድሚዳ አድርጎኛልፀ ሁለተኛ ደግሞ ኹግል ፍርሃቮ ወጥቌ ኹዓለም ጋር ለመጋፈጥ መንገድ ኚፍቶልኛል። ወደ አገሬ ስመለስ ነገሮቜ እንዲለወጡ በፅኑ ፍላጎት አሳድሬ ነበር። በተለይም ሥራ ለማግኘት ቁርጠኛ ነበርኩ። ደግሞም ተሳካልኝ። 27 ዓመት ሲሞላኝ ሕይወቮ ቀስ በቀስ መልክ መያዝ ጀመሚ። ሥራ አገኘሁፀ ሚስት አገባሁፀ ልጅ ወለድኩ። ኚቀተሰባቜን ይሁን ኚአስተዳደጌ አላውቅም ብቻ ቜግሬን ወደ ውስጥ እንጂ ለሌሎቜ ዚማጋራት ነገር አላውቅም። ማንኛውንም ጭንቀቮን በራሎው አፍኜ መቀመጀ በብዙ ጎድቶኛል። እንደኔው በብ቞ኝነት መቀመጀ ሳይጎዳኝ አልቀሚም። ለሚዥም ጊዜ ያህል ኚዩኒቚርስቲ መባሚር ዹዓለም መጚሚሻ እንደሆነ አስቀ ነበር። ልክ እንዳልነበሚ ያወቅኩት ግን ዘግይቌ ነው። ዋናው ነገር ራስን ተሚድቶ ዚሰዎቜ እርዳታ በሚያስፈልግ ጊዜ ሁሉ ያን መሻት ነው። ዚዩኒቚርስቲ ዲግሪን መጫን ዚሞት ሜሚት ጉዳይ መሆኑ መልካም ነገር አይመስለኝም። በዚህ ሚገድ ማኅበሚሰቡ ዚማይታይና ዚማይዳሰስ ጫናን ነው በወጣቶቜ ላይ ዚሚፈጥሚው። በኔ ሕይወት ዚተሚዳሁት ግን ዲግሪን አናታቜን ላይ ኚመጫንም በፊት ጀናማ ጭንቅላት እንዲኖሚን ማስፈለጉን ነው።
53963765
https://www.bbc.com/amharic/53963765
ትራምፕ 7 ጥይት ዚተተኮሰበትን ጥቁሩን ጃኮብ ሆስፒታል ሄደው ሊጠይቁት ይሆን?
ዚአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ዊስኮንሰን ግዛት ዚምትገኘውን ኬኖሻ ኹተማን ሊጎበኙ ነው፡፡
ባለፈው ሳምንት ጆኮብ ብሌክ ዚተባለ ወጣት ጥቁር በ7 ጥይት በፖሊስ ኹፍተኛ ጥቃት ኚደሚሰበት በኋላ በኬኖሻ ኹፍተኛ ቁጣ ተቀስቅሷል፡፡ ትራምፕ ወደ ኬኖሻ ዚሚሄዱት ኹነገ በስቲያ ማክሰኞ እንደሆነ ዋይት ሐውስ ይፋ አድርጓል፡፡ ትራምፕ እዚያ ሄደው ምን እንደሚያደርጉ በዝርዝር ባይገለጜም ኚጞጥታ አስኚባሪ አካላት ጋር ይነጋገራሉፀ ዹደሹሰውን ጉዳት ይገመግማሉ ተብሏል፡፡ ጥቁሩ ጃኮብ ብሌክ 7 ጥይት በጀርባው ተተኩሶበት በሕይወት መትሚፉ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ አኚርካሪው ላይ አንዲት ጥይት በመሰንቀሯ ህብለሰሚሰሩ ተጎድቷል፡፡ ስለዚህ ኹዚህ በኋላ ቆሞ መራመድ አይቜልም ተብሏል፡፡ ዚጃኮብ ጉዳትን ዚሚያሳዚው ቪዲዮ ማኅበራዊ ድራምባው ኚተጋራ በኋላ በበርካታ ዚአሜሪካ ኚተሞቜ ተቃውሞ ተቀስቅሷል፡፡ በኬኖሻ ዊስኮንሰን ዹነበሹው ተቃውሞ ግን በዝርፍያና በነውጥ ዚታጀበ ሲሆን ዚሰዎቜ ሕይወትም ጠፍቷል እዚተባለ ነው፡፡ በርካታ መኪናዎቜም ወድመዋል፣ ሱቆቜ ተዘርፈዋልፀ በእሳት ተያይዘዋል፡፡ ባለፈው ግንቊት ወር በሜኔሶታ፣ ሚኒያፖሊስ ኹተማ ጆርጅ ፍሎይድ ዚተባለ አንድ ጥቁር በነጭ ፖሊስ ማጅራቱ ተቆልፎ እንዲሞት ኹሆነ በኋላ ዚጥቁሮቜ ዚመብት እንቅስቃሎ በመላው ዓለም እዚተፋፋመ ይገኛል፡፡ ዶናልድ ትራምፕ ጃኮንብ ይጎበኙታል? ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታ቞ው ጃኮብን ይጎበኙት ይሆን ዹሚለው በጉጉት እዚተጠበቀ ነው፡፡ አሁን ለጊዜው ዚታወቀው ዹኹተማዋን ፖሊስ እንደሚያነጋግሩና በነውጡ ዹደሹሰውን ዚጉዳት መጠን እንደሚብራራለ቞ው ነው፡፡ ይህን ዚተናገሩት ዚዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ጁድ ዲር ና቞ው፡፡ ፕሬዝዳንቱ ዚጥቃቱን ሰለባ ዹሆነውን ጃኮብ ብሌክንና ቀተሰቊቹን ይጎበኛሉ ወይ በሚል ለቃል አቀባዩ ጥያቄ ቀርቩላቾው ዹነበሹ ሲሆን ይህን ለመናገር ገና ዝርዝር ዚጉብኝት እቅድ መሹጃ ያስፈልገኛል ብለዋል፡፡ ዶናልድ ትራምፕ በጥቁሮቜ ላይ ዚሚደርሱ ጥቃቶቜን በግልጜ ሲኮንኑ ብዙም አይሰሙም፡፡ እሁድ ለታ በጃኮብ ብሌክ ዹደሹሰውን ጥቃትም በቀጥታ አላወገዙም፡፡ በጃኮብ ላይ ዚተኮሰው ፖሊስ መኚሰስ አለበት ወይ በሚል አርብ ዕለት አንዲት ጋዜጠኛ ጥያቄ አቅርባላ቞ው ነበር፡፡ ‹‹ ገና ሪፖርት አልቀሚበልኝምፀ ነገሩን ማጀን አለብኝ፡ ቪዲዮውን አይቌው ግን አልወደድኩትም›› ብለዋል፡፡ ትራምፕ በመጪው ኅዳር በሚጠብቃ቞ው ምርጫ ‹‹ሥርዓት ማስኚበርን› እንደ አጀንዳ ይዘው እንደሚሰሩበት ተናግሚዋል፡፡ ‹ዲሞክራቶቜ በሚበዙባ቞ው ኚተሞቜ ሥርዓት አልበኝነት ነግሷል፣ ዙርፊያ ተጧጡፏል፣ ፖሊሶቜ እዚተጎዱ ነው ፀ ስለዚህ ይህን ጋጠወጥ ሁላ ልክ አስገባዋለሁ› ብለው ሲዝቱም ነበር፣ በምሚጡኝ ቅስቀሳ ወቅት፡፡ ኚምርጫ ጋር በተያያዘ ዊስኮንሰን ግዛት ‹ወላዋይ› ኚሚባሉ ግዛቶቜ አንዷ ናት፡፡ ግዛቷ ቀድሞ ባራክ ኊባማ ያሞነፉባት በመሆኑ ዚዲሞክራቶቜ ግዛት ብትመስልም ትራምፕ በ2016 በ20ሺ ድምጜ ብልጫ ሂላሪን ማሾነፋቾው ደግሞ ወላዋይነቷን ዚሚያሳይ ነው፡፡ በኬኖሻ ኚአንድ ሺ በላይ ሰልፈኞቜ ‹ዚጥቁር ነፍስ ዋጋው ስንት ነው?› በሚል ቅዳሜ ሰልፍ ወጥተዋል፡፡ ዚጃኮብ አባት ሰልፈኞቜ ኚነውጥ፣ ኚጥቃትና ካያልተገባ ድርጊት ራሳ቞ውን እንዲያቅቡ አደራ ብለዋል፡፡ በኬኖሻ ኹ1ሺ በላይ ዚብሔራዊ ጥበቃ ልዩ ኃይል እንዲገባ ተደርጓል፡፡ ብዙዎቹ ታዲያ ኹሌላ ግዛት ዚመጡ ዚልዩ ጥበቃ አባላት ና቞ው፡፡
news-55459259
https://www.bbc.com/amharic/news-55459259
ግብርና፡ አርሶ አደሮቜን በሳተላይት ዚምታግዘው ኡጋንዳዊቷ ዚናሳ ሳይንቲስት
ለባድሚንተን ስፖርት ፍቅር ያላት ኡጋንዳዊቷ ካትሪን ናካሌምቀ ፍላጎቷ ዩኒቚርሲቲ ገብቶ ዚስፖርት ሳይንስ ማጥናት ነበር።
ነገር ግን ዚሚያስፈልገውን ዹመመዘኛ ነጥብ ባለማሟላቷ ምክንያት ይህን ማድሚግ አልቻለቜም። ቢሆንም ዚትምህርት ጉዞዋ በዚህ አልተቋጚም። አሁን በምድራቜን ቀዳሚ ኚሚባሉት ዹህዋ ምርምር ተቋማት አንዱ በሆነው ዚአሜሪካው ናሳ ውስጥ ሳይንቲስት ናት። ዶክተር ካትሪን በሰሜን ምሥራቅ ኡጋንዳ ውስጥ በምትገኘው ካራሞጆንግ በሚባለው አካባቢ ለሚኖሩ አርሶ አደሮቜ "ዚሳተላይት ምስል ተጠቅሜ ዹናንተን ግብርና ማሳደግ እቜላለሁ" ስትላ቞ው ሳቅ ቀድሟ቞ው ነበር። ሳይንቲስቷ ኚሳተላይት ዹተገኙ ጥራታ቞ው ኹፍ ያሉ ምስሎቜን ተጠቅማ አርሶ አደሮቜንና መንግሥትን ማገዝ ነው ሕልሟ። ነገር ግን ይህን ለማድሚግ አርሶ አደሮቹ ወደሚኖሩበት ዚገጠሩ ክፍል በመሄድ ማሳ቞ው ውስጥ መገኘት ግድ ይላታል። በሌላ አነጋገር ኹህዋ ላይ በሚገኘው መሹጃ ብቻ ሳርን፣ ኚገብስ ወይም ኹበቆሎ መለዚት አይቻልምና። "አንዱን ገበሬ ያለኝን ምስል ሳዚው አሹንጓዮ ነገር እንጂ በውል ምን እንደሆነ መለዚት አልቻልኩም ብዬ በአስተርጓሚ ነገርኩት" ትላለቜ። "አትሜ ያመጣሁትን ምስል ሳሳዚው ገባውና 'ነይ ማሳዚን ላሳይሜ' አለኝ" ስትል ለቢቢሲ ትናገራለቜ። አብዛኛዎቹ ገብሬዎቜ በአነስተኛ ማሳዎቜ ላይ ብቻ ወቅት ጠብቀው ነው ዚሚፈልጉት ሰብል ዚሚያመርቱት። በአሜሪካው ሜሪላንድ ዩኒቚርሲቲ ዚጂኊግራፊ ሳይንስ ክፍል ሚዳት ፕሮፌሰር ዚሆነቜው ካትሪን (ዶ/ር) ዚሳተላይት ምስል ተጠቅማ ግብርና እና ዹአዹር ንብሚት ለውጥን ታጠናለቜ። ኚሳተላይት ዹሚገኘው ምስል መሬት ካለው መሹጃ ጋር ተዳምሮ ዚሰብሎቜን ቀመር ዚሚያጠና ቮክኖሊጂ ለመሥራት ይውላል። ካትሪን (ዶ/ር) በዚህ ሥራዋ ነው እዚተጠናቀቀ ባለው ዹ2020 'ዚአፍሪካ ፉድ ፕራይዝ' ሜልማትን ኚቡርኪናፋሶው አንድሬ ባቲዮኖ (ዶ/ር) ጋር ዚተጋራቜው። ካትሪን (ዶ/ር) በአሁኑ ጊዜ ናሳ ውስጥ ዚአፍሪካ ምግብና ግብርና ፕሮግራም ኃላፊ ናት። "ኹሰማይ ላይ ዚትኛው አካባቢ ዚተገነባ እንደሆነ፣ ዚትኛው ደሚቅ፣ ወይም ውሃ ያለው እንደሆነ መለዚት ይቻላል" ትላለቜ ሳይንቲስቷ። "አልፎም ዚትኛው ቊታ ለሰብል ዹሚሆን መሬት ነውፀ ጫካ ዚሆነውስ ዚቱ ነው ዹሚለውን መለዚት ቜለናል። ዹ30 ዓመት ሰብል ዚማምሚት ልምድ ስላለን ዚትኛው ጀናማ መሬት እንደሆነ ዚትኛው ደግሞ ሊሻሻል እንደሚገባው አውቀናል።" ካትሪን (ዶ/ር) አርሶ አደሮቜ ስለሰብላ቞ው መሹጃን በሞባይል እንዲት መላክ እንደሚቜሉ ስታሰለጥን መፍትሄ ለአርሶ አደሮቜ አጥኚዎቜ ኚመሬት ዚሚያገኙትን ወይም አርሶ አደሮቜ ዚሚልኳ቞ውን መሚጃዎቜ በመጠቀም ሳይንቲስቷ ካርታ ታዘጋጃለቜ። ካርታው ዚገበሬዎቹ ሰበል ኚሌሎቜ አካባቢዎቜ ጋር ሲነፃፀር እያደገ ነው ወይስ አይደለም ዹሚለውን ለመለዚት ያስቜላል። ይህ መንገድ አሜሪካ ውስጥ ለትላልቅ በዘመናዊ ዚግብርና መሳሪያዎቜ ለሚካሄዱ እርሻ ሥራዎቜ ጥቅም ላይ ይውላል። መሹጃው መቌ ሰብል መመሚት እንዳለበትና መሬቱ ምን ያህል ዝግጁ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ይህ መሹጃ አነስተኛ ማሳ ላላቾው ኡጋንዳ ውስጥ ላሉ ወይም ለሌሎቜ ዚአህጉሪቱ አርሶ አደሮቜ እጅግ ጠቃሚ ነው። "ለምሳሌ በሚቀጥሉ ቀናት ዝናብ እንደሚዘንብ እርግጠኛ ኹሆንን አርሶ አደሮቜ ማሳ቞ውን እንዲያዘጋጁ እንነግራ቞ዋለን። ዝናብ ኹሌለም ጊዜያ቞ውን እንዲሁ እንዳያባክኑ እናስሚዳ቞ዋለን።" በአፍሪካ አብዛኛዎቹ ዚእርሻ ማሳዎቜ ቁራሜ መሬት ና቞ው። ሰብል ማምሚትን በተመለኹተም ይህን ያህል መሹጃ ዚለም። ነገር ግን ኚሳተላይት ዹሚገኘው መሹጃ ወደ አካባቢው ቋንቋ ተተርጉሞ በስልክ ዹፅሁፍ መልዕክት፣ ወይም በሬዲዮ፣ አሊያም በግብርና ሠራተኞቜ አማካይነት ሊተላለፍ ይቜላል። አልፎም መንግሥታት ይህንን መሹጃ ተጠቅመው ተፈጥሯዊ አደጋ በሚመጣ ጊዜ ማኅበሚሰቡ ኚድርቅ እንዲጠበቅ አስፈላጊውን ሊያደርጉ ይቜላሉ። አስካሁንም ዚካትሪን (ዶ/ር) ጥናት በካራሞጃ ዚሚኖሩ 84 ሺህ ገበሬዎቜ በአዹር ለውጥ ሳቢያ በሚመጣ ዚዝናብ እጥሚት እንዳይጎዱ መታደግ ቜሏል። በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ሰብል ለሚያመርቱ ኡጋንዳውያን አርሶ አደሮቜ ዚሳይንቲስቷ ጥናት መፍትሄ ይዞ መጥቷል። ዝናብ በማይኖርበት ወቅት አርሶ አደሮቜ ትኩሚታ቞ውን ወደ ሌላ ሥራ እንዲያደርጉና ቀተሰቊቻ቞ውን እንዲያግዙ ይደሚጋል። ካትሪን (ዶ/ር) ለሥራዋ ዚተበሚኚተላት ያልጠበቀቜው ሜልማት በድንገት ዚመጣ ሳይንቲስትነት ካትሪን (ዶ/ር) ኚሜካኒክ አባቷና ምግብ ቀት ኚምታስዳድሚው እናቷ ዚተወለደቜው በኡጋንዳዋ ዋና ኹተማ ካምፓላ ነው። "ሥራዬ ኚሳተላይት ጋር ዹተገናኘ ይሆናል ብዬ አንድም ቀን አስቀ አላውቅም" ትላለቜ። ኚእህቶቿ ጋር ባድሚንተን መጫወት ታዘወትር ነበር። ሕልሟም በስፖርት ሳይንስ ዲግሪ መጫን ነበር። ነገር ግን ያለሜ ውጀት በታዋቂው ዚማኬሬሬ ዩኒቚርሲቲ ዚስፖርት ሳይንስ ክፍል ለመግባትና ለመማር አይበቃም ስትባል ወደ ኢንቫይሮንሜንታል [ዚአካባቢ] ሳይንስ ክፍል አቀናቜ። ትምህርቷን ለመማር ያግዛት ዘንድ ለኡጋንዳ ዱር እንስሳት ባለሥልጣን ለመሥራት አመለኚተቜ። ካርታ ማጥናት እወድ ነበር ዚምትለው ካትሪን ለመጀመሪያ ጊዜ ካርታ ለማጥናት ተራራ ላይ ወጥታ ዚተሰማትን ሐሎት አትዘነጋውም። አሁን በአፍሪካ ዚተለያዩ አገራት ውስጥ እዚተዘዋወሚቜ ለመንግሥት መሥሪያ ቀቶቜ ስለ ምግብ ዋስትና ምክር ዚምትለግሰው ካትሪን በወቅቱ ዚማስተርስ ድግሪዋን ለመማር ለጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቚርሲቲ ማመልኚቻ አስገባቜና እድሉን አገኘቜ። ሁለተኛ ዲግሪዋን እንደጚሚሰቜ ደግሞ ዚዶክትሬት ድግሪዋን ለመኚታተል እዚያው አሜሪካ ሜሪላንድ ዩኒቚርሲቲ ገባቜ። ሳይንቲስቷ ካትሪን (ዶ/ር) ዚእራሷን ተሞክሮ መሰሚት አድርጋ ወጣት ጥቁር ሎቶቜ ወደ አካባቢ ሳይንስ ጥናት እንዲገቡ ምክር ትለግሳለቜ። ዹ2020 ዚአፍሪካ 'ፉድ ፕራይዝ' ሜልማት አሾናፊ ስትሆን ዚተሰማትን ደስታ መደበቅ አትቜልም። ስልክ ተደውሎላት "ዚቀድሞ ዚናይጄሪያ ፕሬዝደንት ኩሌሮጉን ኊባሳንጆ ይፈልጉሻልፀ መሥመር ላይ ጠብቂ" ስትባል ዚአጭበርባሪዎቜ ስልት ይሆን ብላ ጠርጥራም ነበር። "አስቡት እስቲፀ አሁን እኔ ዚዊኪፔዲያ ገፅ አለኝ።" አሁን አሁን ራሎን ለሰዎቜ ሳስተዋውቅ 'ዹ2020 ዚአፍሪካ ፉድ ፕራይዝ አሾናፊ ነኝ' ማለት ማስታወስ አለብኝ" ትላለቜ በፈገግታ። "አምስት ኪሎ ግራም ዹሚመዝን ሜልማት ተሰጥቶኛል። በሕልሜ እንዳልሆነ ማሚጋገጫው ይሄ ነው።"
45243823
https://www.bbc.com/amharic/45243823
ዹጅግጅጋ ተፈናቃዮቜ በአዲስ አበባ ጎዳና ላይ ወድቀዋል
ኚሁለት ሳምንታት በፊት በሶማሌ ክልል በተኹሰተው ግጭት ጥቃት ዚደሚሰባ቞ው ስደተኞቜ በአዲስ አበባ ስታዲዚም አካባቢ ኊሮሚያ ዚባህል ማዕኹል ፊት ለፊት ተጠልለዋል።
እስኚመቶ ዚሚደርሱት እነዚህ ስደተኞቜ በዚሁ ጎዳና ላይ በሞራ በተኚለለቜው ስፍራ ኹማሹፍ ውጪ ምንም አይነት አማራጭ እንደሌላ቞ው ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ኚስድስት ወር ህጻን ጀምሮ ሎቶቜፀ አዛውንቶቜና በጥቃቱ ድብደባ ዚደሚሰባ቞ው ደካሞቜ ለአራት ቀናት በዚሁ ቊታ ላይ እዚዋሉም እያደሩም ነው። ቀት ንብሚታ቞ውም ሙሉ በሙሉ በጥቃቱ በመውደሙ ዚሚለበስም ሆነ እንዲህ ላሉ ክፉ ቀን ዹሚሆን ጥሪት አለመቋጠራ቞ውን ተናግሚዋል። •በሶማሌ ክልል በተኹሰተ ቀውስ ህይወት ሲጠፋ አብያተ-ክርስትያናት ተቃጠሉ •አብዲ ሞሃመድ ኡመር በቁጥጥር ስር ዋሉ •ዚጠቅላይ ሚኒስትሩ ዹጅግጅጋ ጉብኝት ፋይዳ እስካሁን ዚዕለት ጉርሳ቞ውንም እዛው አካባቢው ያሉ ወጣቶቜ ኚመንገደኞቜ እዚሰበሰቡ ኚሚያቀርቡላ቞ው ምግብ እያገኙ ቢሆንም ኹዚህ ውጭ ምንም አይነት ዚመንግስት ድጋፍ አለማግኘታ቞ውን ገልጞዋል። በዓመቱ መጀመሪያ በተመሳሳይ ጥቃት ሙሉ ቀተሰቡን እንዳጣ ዹሚናገሹው አደም አህመድ በጅጅጋ 03 በሚባለው አካባቢ ነበር ኑሮውን ያደሚገው። አሁን ሁኔታዎቜ ተቀይሹው ሥምምነት ተፈጥሯል መባሉን ተኚትሎ ወደጅግጅጋ ኹተመለሰ ሰባት ወሩ ነው። "ባለፈው መስኚሚም ግርግሩ ሲፈጠር ሱቅ ውስጥ ነበርኩኝፀ በበር በኩል ሲገቡብኝ በመስኮት ዘልዬ መኖሪያ ቀ቎ ስሮጥ ሁለት ልጆቌ ፣ ሶስት እህቶቌና እና቎ ተገድለው ነበር ያገኋ቞ውፀ ተመልሌ ስሄድም ይኾው ግርግሩ ተፈጥሮ አሁንም ውጡልን ተባልን ፀ ወዲዚሁ መጣሁፀ ግን ቀተሰቊቌ በሙሉ እንዳለቁ ስነግራ቞ው አንድም ዚተሚዳኝ ሰው ዚለም።" ይላል። "እሰኚዛሬ ድሚስ ወደዛም ወደዚህም ስንል፣እኛ ጎዳና ተዳዳሪ ስንሆን አንድ ቀን መጥቶ አይዟቜሁ እኛ አለን ያለን ሚዲያም ዹለም ህዝብ ነው እዚተባበሚን እሰኚዛሬ እንድቆይ ያደሚገን እንጂ ዚመንግስት አካል ሁሉ ወደእዚያው ተመለሱ እያሉን ነውፀ እኛ ለምንድነው እንደዚህ ዹምንሆነው ኢትዮጵያዊ አይደለንም አንዮ?" ቢቢሲና እንድ ዹሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃንም ተፈናቃዯቜን ለማናገር ሲሞክሩ በአዲስ አበባ ኹተማ ፖሊስ አባላት እንዳይቀርጹ በመኹልኹላቾው ተፈናቃዮቹ ኚፖሊሶቹ ጋር ዚቃላት እሰጥ አገባ ውስጥ ገብተው ነበር። ኚቆይታ በኋላ ግን ዚጋዜጠኞቹን መታወቂያዎቜን አሹጋግጠው ክልኹላውን አንስተዋል። በጅግጅጋ ኚመርሲን አካባቢ ዚመጣቜው በቀሉ ቶሎሳ በጥቃቱ ኹ 80ሺ ብር በላይ ዚሚያወጣ ንብሚት እንደተዘሚፈባት ተናግራለቜ። "ይኾው አስራ አምስት ቀናቜን ምንም መፍትሄ አላገኘንምፀ ዹወደቅነው ጎዳና ላይ ነው። አሁን እዚህ ተኝተን ደካማ አሉፀ ልጆቜ ዚያዙ እናቶቜ አሉ ፀበሜተኞቜ አሉፀ ምንም መፍትሄ አላገኘንም። " ብላለቜ በቀሉ ጉዳያ቞ውን አቀት ለማለት ወደተለያዩ ዚመንግስት አካላት ቢሮ ቢቀርቡም ሰሚ ጆሮ እንዳላገኙ ነው ዚምትናገሚው። "ወደ አስራ ምናምን ቊታ ጠዚቅንፀ ያልገባንበትቢሮ ዹለም ፀ መፍትሔ አላገኘንም ይኾው ጎዳና ላይ ወደቅንፀ እሰኚዛሬ እኔ ዚመንግስት ያለህ እያልኩኝ ነው። " በዕለቱ ጥቃት ዚተሰነዘሚባ቞ው አይነስውሩ ባህታዊ ታምሩ ዘለቀም ኚጉዳታ቞ው ሳያገግሙ በዚሁ ጎዳና ላይ ተመጜዋቜ ሆነዋል። " ኪዳነምህሚት አስቀድሌ ወደሚካኀል ስመጣ ነዋይ ቅድሳት እዚተቃጠለ ነበርፀ ተመልሌ ወደኪዳነምህሚት ስንሄድ ለካ ኪዳነምህሚትንም አቃጥለው ጚርሰዋታል ፀ ተመልሰን ወደ ሚካዔል ስንመጣ ጥርሎን አሚገፉኝፀ ወገቀንም መቱኝ" ለዚህ ህመማቾው በቂ ዹህክምና አግልግሎትት ባያገኙም ኚአስተባባሪ ወጣቶቜ ባገኙት መድኃኒቶቜ ህመማቾውን ያስታግሳሉ። ኚተፈናቃዮቹ ውስጥ 30 ዚሚሆኑት ኚሁለት ቀናት በፊት ነበር ነፍሳቜውን ለማዳን ኚመሞጉባት ሃሚር ወደ አዲስ አበባ ዚመጡት። ለአምስት ቀን ዹሃሹር ህዝብ እዚሚዳን ቆዚንፀ ልጆቜ አሉፀ ደካማ አለፀ አይነስውራንፀ ዚተደበደበፀ በጥይት ዚተመታ ሁሉ ነበሚፀ እኛ እንዎት ነው ዹምንሆነው ? እንዳንመለስ ንብሚታቜን ተዘርፏልፀዚመመለስም ህልውና ዹለንም ስንላ቞ው ወደ አዲስ አበባ ሂዱ ፀ መንግስትም ይሚዳቜኋል ሲሉን መጣንፀ ኚእነዚህ ግማሹ ሎቶቜ ናቾው" ብሏል ዚተፈናቃዮቜን ስም ሲመዘግብ ቢቢሲ ያገኘው ሞላ ዚተባለው ተፈናቃይ። " ዚሌሊቱ ብርድ ራሱ እኔ ኚዱላው በላይ አድርጌ ነው ዚማዚውፀ በጣም ነው ዚሚሰቃዩትፀ ዚሚለብሰው አጥቶ በብርድ ዹሚሰቃይ ሞልቷል።" ስታዲዚም አካባቢ ዚሚሰራው ጋሻው ተወዳጅ ተፈናቃዮቹን ለመርዳት ኚተሰባሰቡት ወጣቶቜ አንዱ ነው። ካለፈው አርብ ጀምሮ ጎዳናው ላይ ዚወደቁትን ተፈናቃዮቜ ዹማገዙ ሂደት አስ቞ጋሪ እንደሆነባ቞ው ይገልጻል። "እኛ ብቻ ነን አሁን እዚሚዳና቞ው ያለነው ፀ መንግሥትም ሆነ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት እስካሁን ዚሚዳ቞ው ዚለምፀ ህጻናት አሉ ፀዚሚያጠቡ እናቶቜ አሉፀ ሜማግሌዎቜም አሉፀ ብርድ ላይ ነው ያሉት ትንሜ ቢቀንሰውብለን ሞራ ገዝተን አጠርንላ቞ው።ምግብ አንዳንድ ሰው ይዞ ይመጣልፀ ካልሆነ ደግሞ አስተባብሚን በምናገኘው ገንዘብ ምግብ ቀት ሄደን ገዝተን ነው ዚምናበላ቞ውፀ ጠዋት ጠዋት ደግሞ በዚቊታው ዚሚያፈሉትን እያፈላለግን በፔርሙሶቜ እዚሰበሰብን በቁርስ እናበላ቞ዋለን" ብሏል። ወጣቶቹ መንግሥትም ሆነ ድርጅቶቜ ተፈናቃዮቹን በመጎብኘት ለጊዜው ምግብና መኝታ ዚሚያገኙበትን መንገድ እንድሚያመቻቹ ጠይቀዋል። ተመልሶ ወደጅግጅጋ መሄዱ ዹዘላቂ መፍትሄው አካል እንደሆነ ዚተጠዚቀቜው በቀሉ ይህን ብላለቜ። "መመለስ አለልፈልግምፀ መንግሥት እዚህ ቢገድለኝ ሁሉ ይሻለኛልፀ በቃ እዚሁ ብሞት እመርጣለሁፀ ዚዛሬ ዓመትም ሁለት ዓመትም እንደዚሁ ስለሆነ ወደዚያ ዚሚያስብ ቀተሰብ ዹለም" አስተባባሪ ወጣቶቜም ቜግሩ ኹአቅማቾው በላይ እዚሆነ በመምጣቱ መንግስትም ሆነ ለጋሟቜ እጃ቞ውን እንዲዘሚጉላ቞ው ጠይቀዋል።
news-55950982
https://www.bbc.com/amharic/news-55950982
ኢሰመኮ በሚሃብ አድማ ላይ ናቾው ዚተባሉትን እነ አቶ ጃዋርን መጎብኘቱን ገለፀ
ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ኮሚሜን (ኢሰመኮ) ዚሚሃብ አድማ ላይ ናቾው ዚተባሉትን በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ ዚተኚሰሱ እስሚኞቜ መጎብኘቱን ዛሬ፣አርብ ባወጣው መግለጫ ላይ ገለፀ።
በቃሊቲ ማሚሚያ ቀት በሚሃብ አድማ ላይ ዹሚገኙ እስሚኞቜን አስመልክቶ፣ ዚኢሰመኮ ዋና ኮሚሜነር ዶ/ር ዳንኀል በቀለ "ዚእስሚኞቹ ጀንነትና ሕይወት ዹኹፋ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ዚቅርብ ክትትል ማድሚግ እንደሚያስፈልግ፣ ለታሳሪዎቜ ምክንያታዊ ዹሆኑ ጥያቄዎቜ ተገቢውን አፋጣኝ ምላሜ መስጠትና ዚእስሚኞቜን ጠያቂዎቜ በማሚሚያ ቀቱም ሆነ በፍርድ ቀቶቜ በአግባቡ ማስተናገድ ይገባል" ማለታ቞ውም ኮሚሜኑ ባወጣው መግለጫ ላይ ተመልክቷል። ኮሚሜኑ ጥር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በቃሊቲ ማሚሚያ ቀት እና በቂሊንጩ ጊዜያዊ ማቆያ በመገኘት እስሚኞቹን መጎብኘቱን ዹገለፀ ሲሆን ኚእነ አቶ ጃዋር መሐመድ በተጚማሪም፣ ዚኮሎኔል ገመቹ አያና እና ዚአቶ ጥላሁን ያሚ አያያዝ ላይም ክትትል ማድሚጉን በመግለጫው ላይ አመልክቷል። እነ አቶ ጃዋር መሐመድ ኚጥር 19 ጀምሮ በሚሃብ አድማ ላይ እንደነበሩ ዹገለፀው ኮሚሜኑ፣ ዚሚሃብ አድማው ዓላማ "መንግስት በሕዝብ እና በፓርቲያ቞ው ላይ እያደሚሰ ያለውን አፈና እና ዚመብት ጥሰት ለመቃወም፣ ዚኮሎኔል ገመቹ አያናን አላግባብ ዹሆነ አያያዝ እና እንግልት እንዲቆም ለመጠዹቅ እና ዚቜሎት ሂደታ቞ውን ለመኚታተል ወደ ፍርድ ቀት በሚመጡ እና እነሱን ለመጠዹቅ ወደ ማሚሚያ ቀት በሚመጡ ሰዎቜ ላይ ዹሚፈጾም እስር እና ወኚባ እንዲቆም ለመጠዹቅ" መሆኑን ለኮሚሜኑ ማሳወቃ቞ው ተመልክቷል። ዚቃሊቲ ማሚሚያ ቀት አስተዳደር በበኩሉ እነ አቶ ጃዋር ያነሷ቞ው አብዛኞቹ ጉዳዮቜ እንደማይመለኚቱት መግለፁን በመግለጫው ላይ ሰፍሯል። እነ አቶ ጃዋርን ለመጠዹቅ ወደ ማሚሚያ ቀት ዚሚመጡ ሰዎቜ ላይ ወኚባ እንደማይፈፀምም ማሚሚያ ቀቱ ማስታወቁ ተገልጿል። ኚመካኚላ቞ውም ሁለት እስሚኞቜ ዚጀና ቜግር ያለባ቞ው በመሆኑ በሚሃብ አድማው ምክንያት ዚጀና እክል እንዳይገጥማ቞ው ሕክምና እዚተደሚገላ቞ው መሆኑን መመልኚቱን ኮሚሜኑ ገልጿል። አቶ ጃዋር መሃመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ሃምዛ አዳነ እና አቶ ሞምሰዲ ጠሃ በትናንትናው እለት በሚሃብ አድማው በመዳኚማ቞ው ቜሎት ፊት ሃሳባ቞ውን ማስሚዳት እንደተሳና቞ው ኚጠበቆቻ቞ው አንዱ ዚሆኑት አቶ መሐመድ ጅማ ለቢቢሲ መግለፃቾው ዚሚታወስ ነው። "ሰውነታ቞ው በጣም ስለተዳኚመ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣ቞ው ጠይቀዋል። እነሱ ብዙ መናገር ስላልቻሉ እኛ ሃሳባ቞ውን አስሚድተናል።" ብለዋል። ተኚሳሟቹም እንዲሁ "በጣም ተዳክመን፣ ራሳቜንን ስተን ዹህክምና እርዳታ ዚሚያስፈልገን ኹሆነ እኛ በመሚጥነው ሃኪም ብቻ ዹህክምና ርዳታ ይደሹግልን' ሲሉ ፍርድ ቀቱን እንደጠዚቁም ጠበቃቾቾው አስሚድተዋል። ኚእነ አቶ ጃዋር በበተጚማሪም ኮሚሜኑ ዚኮሎኔል ገመቹ አያናን እና ጥላሁን ያሚን ደህንንት ማጣራቱንም አስታውቋል። "ሁለቱም ታሳሪዎቜ በመልካም ደህንነት ላይ ይገኛሉ" ያለው ኮሚሜኑ አካላዊ ጥቃትም እንዳልደሚሰባ቞ው ማሚጋገጡን አስታውቋል። አቶ ጥላሁን ዋሚ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ኚማሚሚያ ቀት ተቀርጟ በተሰራጚ ተንቀሳቃሜ ምስል ጋር በተያያዘ ደህንነቱ አደጋ ላይ ወድቋል ተብሎ በስፋት ሲወራ ነበር። ጥላሁን ዋሚ በማሕበራዊ ሚዲያ ዚተሰራጚውን ቪዲዮ ተኚትሎ ኚማቆያ ቀቱ ቅጥር ግቢ እንዳይወጣ ኹመደሹጉ በስተቀር በቂሊንጩ ጊዜያዊ ማቆያ እያለ ድብደባም ሆነ ሌላ አይነት ዚመብት ጥሰት እንዳልተፈፀመበት ለኮሚሜኑ ማስሚዳቱ ተገልጿል።
news-50709579
https://www.bbc.com/amharic/news-50709579
ሳዑዲ ምግብ ቀቶቜ በጟታ ዹተለዹ መግቢያ በሮቜን መጠቀም ዚለባ቞ውም አለቜ
ዚሳዑዲ መንግሥት ኹአሁን በኋላ በምግብ ቀቶቜ ውስጥ ወንዶቜና ሎቶቜ ዚተለያዚ መግቢያ እንዲጠቀሙ ዚሚያስገድደውን ሕግ ማስቀሚቱን አስታወቀ።
በሳዑዲ በምግብ ቀቶቜ ሎቶቜና ወንዶቜ አንድ በር እንዳይጠቀሙ በሚያግደው ሕግ ምክንያት ወንዶቜና ሎቶቜ በማክዶናልድ ለዚብቻ቞ው ሲገበያዩ ኹዚህ በፊት በምግብ ቀቶቜ ውስጥ ለሎቶቜና ለቀተሰቊቜ አንድ በር፣ ለወንዶቜ ደግሞ ለብቻ቞ው ሌላ በር ማዘጋጀት ዚግድ ነበር። ይህ ዕገዳ በበርካታ ምግብ ቀቶቜ፣ ካፌዎቜ፣ እንዲሁም ሌሎቜ ዚሕዝብ መሰብሰቢያ ሥፍራዎቜ ኹአሁን በኋላ ተግባራዊ አይሆንም ተብሏል። • «ካሟግጂ ወዲያው ነበር ዚታነቀው» ቱርክ • ዚሳዑዲ ሎቶቜ መሪ ጚበጡ በሳዑዲ አሚቢያ ዚተለያዩ ለውጊቜ እዚተካሄዱ ቢሆንም ዹተቃውሞ ድምጻ቞ውን ዚሚያሰሙ ዜጎቜንም ማፈኑን ቀጥሏል ብለው ዚሞሞግቱ ዚመብት ተሟጋ቟ቜ አሉ። በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ዚሳዑዲ ሎት ያለ ወንድ ፈቃድ ወይም አጃቢነት ኹሀገር ውጪ መሄድ እንደምትቜል ንጉሡ ባስተላለፉት ትዕዛዝ አስታውቀው ነበር። እ.ኀ.አ. በ2018 ደግሞ በሎት አሜኚርካሪዎቜ ላይ ለአስርታት ተጥሎ ዹነበሹው ዚማሜኚርኚር እገዳ መነሳቱ ይታወሳል። አሁንም ግን ዚመብት ተሟጋ቟ቜ በርካታ ሎት አግላይ ዹሆኑ ሕጎቜ እንዳሉ መሆናቾውን በማንሳት ዹተቃውሞ ድምጻ቞ውን ያሰማሉ። መንግሥት ይህንን ለውጥ እያካሄደ ባለበት ወቅት እንኳ በርካታ ዚሎት መብት ተሟጋ቟ቜ በእስር ላይ እንደሚገኙ አክለው ተናግሚዋል። እሁድ እለት ዚሳዑዲ ኚተሞቜ ሚኒስትር ምግብ ቀቶቜ በጟታ ዹተለዹ መግቢያ በሮቜን መጠቀም እንደማይገባ቞ው ተናግሚዋል። ይህን ውሳኔ ዚንግድ ተቋማቱ ራሳ቞ው እንዲወስኑ ተትቷል ሲሉም አክለዋል። • ፈጣን ለውጥና ጭቆና በሳኡዲ አሚቢያ • ሳዑዲ ሎቶቜ እንዳያሜኚሚክሩ ጥላ ዚነበሚቜውን እገዳ ልታነሳ ነው መሐመድ ቢን ሳልማን በ 2017 ዚልዑሉነቱን ዘውድ ኹደፉ በኋላ እጅግ ወግ አጥባቂ ዹሆነውን ዚሳዑዲ አሚቢያ ማህበሚሰብ ክፍት ለማድሚግ ዚተለያዩ እርምጃዎቜ እዚወሰዱ ና቞ው። እያደሚጉ ያሉት ለውጥ ኚበርካታ ዹዓለም አቀፍ ማህበሚሰብ አድናቆትን ቢያገኝም አሁንም ግን ጭቆና እንዳለ ዹሚገልፁ አልጠፉም። እ.ኀ.አ. በ2018 ቱርክ በሚገኘው ዚሳዑዲ ኢምባሲ ውስጥ ዹተገደለው ጋዜጠኛ ጃማል ኻሟግጂ ጉዳይ ዹዓለም አቀፍ መንግሥታት በአንድነት ያወገዙት ተግባር ሆኖ ይጠቀሳል። ጃማል ኻሟግጂ ዚሳዑዲ መንግሥትን ዚሚተቹ ጜሑፎቜን በመጻፍ ይታወቅ ነበር።
news-45028176
https://www.bbc.com/amharic/news-45028176
ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ በአሜሪካ ጉዟቾው ኹጀዋር መሃመድ ጋር ተወያይተዋል
በጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ዚተመራው ዚልዑካን ቡድን በሰሜን አሜሪካ ዋሜንግተን ዲ.ሲ፣ ሎስ አንጀለስ እና ሚኒያፖሊስ ኚተሞቜ 'ግንቡን እናፍርስ፣ ድልድዩን እንገንባ' በሚል መሪቃል ያደሚጉት ጉብኝት ተጠናቋል።
ኚግራ ወደ ቀኝ ለማ መገርሳ፣ ጀዋር መሃመድ፣ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ወርቅነህ ገበዹሁ (ዶ/ር) እና ተሺ቎ ዋቆ ዚውጪ ጉዳይ ሚንስ቎ር እና ዹጉዞው አዘጋጅ ኮሚ቎ ዹጠቅላይ ሚንስትሩ ጉብኝት እጅግ ዚተሳካ ነበር እንደሆነ ገልፀዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ባደሚጉት ጉብኝት ኚአሜሪካ መንግሥት ባለስልጣናት፣ መቀመጫ቞ውን ኚኢትዮጵያ ውጪ ካደሚጉ ዚፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቜ፣ ኚጋዜጠኞቜ እና መብት ተሟጋ቟ቜ ጋር ፊት ለፊት ተገናኘተው ተወያይተዋል። ኚእነዚህም መካኚል አንዱ ጀዋር መሃመድ ነው። ጀዋር ኹጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር ዚተወያዩባ቞ውን ርዕሰ ጉዳዮቜ ነግሮናል። . ዶክተር ብርሃኑ ኹጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር ምን ተወያዩ? . "ያለፉት 27 ዓመታት ብዙ ቆሻሻ ነገር ዚተሰራበት ዘመን ነው'' ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ . ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚአሜሪካ ጉዞ ተጠናቀቀ ጀዋር ኹዚህ ቀደም ዚኢትዮጵያ ባለስልጣን ወደ ሰሜን አሜሪካ ሲመጣ ይደሚግለት ዹነበሹውን አቀባበል እና አሁን ለጠቅላይ ሚንስትሩና ልዑካ቞ው ዹተደሹገውን በማነጻጞር ይጀምራል። ''ኹዚህ ቀደም ዚኢትዮጵያ ባለስልጣን ወደዚህ ሃገር ሲመጣ በተበላሜ እንቁላል ይደበደብ ነበር። ዛሬ ላይ ዚተበላሜ እንቁላል ይወሚውሩ ዚነበሩት ወጣቶቜ ናቾው ዚአቀባበል ሥነ-ስሚዓቱን ያደመቁት'' ሲል ይናገራል። ''ይህ ብቻ ሳይሆን አንድ ቊታ ላይ ታይተው ዚማይታወቁት ባንዲራዎቜ ጎን ለጎን ሲውለበለቡ ለመታዘብ ቜለናል'' ይላል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ኹጀዋር ጋር ምን ተወያዩ? ኹጀዋር እንደሰማነው ኹጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር ኹዚህ በታቜ በተዘሚዘሩት ርዕሰ ጉዳዮቜ ላይ ውይይት አድርገዋል። ጀዋር በሃገሪቱ ዹሚፈለገው ለውጥ እንዲመጣ ዚተቻለውን አስተዋጟ እንደሚያበሚክት ለጠቅላይ ሚንስትሩ ዹገለፀላቾው ሲሆን ፀ ''ጠቅላይ ሚንስትሩ ዚምንፈልጋትን ሃገር ለመገንባት ውጪ ያሉ እና ሃገር ውስጥ ያሉ ባለሙያዎቜን ለማሳተፍ ፍላጎት እና ዝግጅቱ አለን'' ሲሉ ነግሹውኛል ሲል ጀዋር ለቢቢሰ ገልጿል። . "ጠቅላይ ሚኒስትሩን አምባገነን እንዳያደርጉት እሰጋለሁ" ጃዋር መሀመድ ''አሁን ባለው ሁኔታ እና ሜግግር ላይ መንግሥትንፀ ጠቅላይ ሚንስትሩን እደግፋለሁ'' - ጃዋር ሞሃመድ
50385137
https://www.bbc.com/amharic/50385137
ሂላሪ ክሊንተን ዚሩስያ እጅ በእንግሊዝ ፖለቲካ ውስጥ ገብቷል አሉ
«እጅግ አሳፋሪ ነውፀ ቃላት ዚሚያሳጣ» ሂላሪ ክሊተን ዚሩስያ እጅ ዚእንግሊዝ ፖለቲካ ውስጥ መኖሩን ዚሚያሳዚው ዘገባ አለመውጣቱን አስመልክተው ያሰሙት ንግግር ነው።
ኚቢቢሲ ጋር ቆይታ ዚነበራ቞ው ሂላሪ ዘገባው ኚሚቀጥለው ዚዩናይትድ ኪንግደም ምርጫ በፊት መውጣት አለበት ባይ ና቞ው። ዚሩስያ እጅ ዚእንግሊዝ ፖለቲካ ውስጥ ደርሶ ይሆን አይሆን ዚሚያትተው ዘገባ ታኅሣሥ 2 ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል። ነገር ግን ሂላሪ ክሊንተን ሪፖርቱ ኚምርጫው በፊት ቢወጣ ለመራጩ ሕዝብ ይጠቅማል ይላሉ። • ሚሌል ኊባማ በአሜሪካ እጅግ ተወዳጇ ሎት ተባሉ • ስፖርታዊ ፍልሚያ ለማዚት ስታድዚም ዚገቡት ትራምፕ ያላሰቡት ገጠማቾው • ትራምፕ በትልቁ ቡሜ ቀብር ላይ ይገኙ ይሆን? ኚእንግሊዝ ሕዝብ እንደራሎዎቜ በተወኹሉ መርማሪዎቜ ዚተሠራው ሪፖርትፀ ስለላ፣ ጣልቃ ገብነት እና ሕግን ያልተኚተለ አሠራር ዚእንግሊዝ ፖለቲካ ውስጥ ተንፀባርቀው እንደሆንና ዚሩስያ እጇ ምን ያህል ሹዝሟል ዹሚለውን አጣርቷል ተብሏል። እንግሊዝ ኚአውⶂጳ ሕብሚት ጋር ፍቺ ለመፈፀም ያደሚገቜው ሕዝበ ውሳኔና ዚዛሬ ሁለት ዓመት ዹተደሹገው ጠቅላላ ምርጫ ዚሩስያ እጅ አለበት እዚተባለ ነው። ባለፈው መጋቢት ዹተጠናቀቀው ሪፖርት ዚእንግሊዝ መንግሥት መቀመጫ ወደሆነው መንገድ ቁጥር 10 ቢመራም እስካሁን ይፋ አልተደሚገም። ዚቊሪስ ጆንሰን መንግሥት ሪፖርት እንዳይወጣ ጫና አድርጓል በማለት ዚሕዝብ እንደራሎዎቜ ይወቅሳሉ። መፅሐፋቾውን ለማስተዋወቅ ወደ እንግሊዝ ያቀኑት ሂላሪ ክሊንተን ኚቢቢሲ ራድዮ 4 ጋር ቆይታ አድርገዋል። «አገራቜንም አይተነዋል። አውሮጳም እንዲሁ። እዚህ እንግሊዝም ቢሆን። ሩስያ ዚምዕራቡን ዓለም ፖለቲካ ለመቆልመም ቆርጣ ተነስታለቜ» ሲሉ ሃሳባ቞ውን ሰጥተዋል። «ዚአገራቜሁ መንግሥት ዘገባውን ማዘግዚቱ እጅግ አሳፋሪ ነውፀ ቃላት ዚሚያሳጣ ነው» ሲሉ ነው ሂላሪ ቁጭታ቞ውን ለጋዜጠኛዋ ዚገለፁት። ሂላሪፀ ሩስያ አሁንም በአሜሪካ ዚምርጫ ሂደት ውስጥ አለቜ ብለው ያምናሉ። እርሳ቞ው በተሞነፉበት ምርጫም እጃ቞ው እንዳለበት አይጠራጠሩም። «እኔም ልክ እንደሌላው ሰው ሪፖርቱ ምን እንዳዘለ አላውቅም። ነገር ግን በወር ጊዜ ውስጥ ድምፁን ለመስጠት ዹሚሄው ሰው መሹጃ ሊደርሰው ይገባል።»
news-53386387
https://www.bbc.com/amharic/news-53386387
ዚኮቪድ-19 መድኃኒት አለኝ ባለቜው ማዳጋስካር 2 ባለስልጣናት በበሜታው ሞቱ
ለኮሮናቫይሚስ ዹሚሆን መድኃኒት ማግኘቷን በፕሬዝዳንቷ አማካይነት ለዓለም ስታስተዋውቅ ዚቆዚቜው ማዳጋስካር ሁለት ዹምክር ቀት እንደራሎዎቿ በወሚርሜኙ መሞታ቞ው ተገለጞ።
ፕሬዝደንት ራጆሊን 'መድኃኒቱን' ሲያስተዋውቁ አንድ ዚአገሪቱ ዹሕግ መወሰኛ ምክር ቀት አባልና ሌላ ዚሕዝብ እንደራሎ ናቾው በኮሮናቫይሚስ መያዛ቞ው ኹተሹጋገጠ በኋላ ህይወታ቞ው ማለፉ ዚተገለጞው። ዹምክር ቀት አባላቱ በበሜታው መሞትን በተመለኹተ ትናንት ዕሁድ ይፋ ያደሚጉት ዚአገሪቱ ፕሬዝደንት አንድሬይ ራጆሊን ና቞ው። ፕሬዝደንቱ ኚአርቲ ዹተቀመመ ነው ዚተባለውን ዚኮሮናቫይሚስ 'መድኃኒት' በመገናኛ ብዙሃን ወጥተው በማስተዋወቅ ቀዳሚው እንደሆኑ ይታወቃል። ፕሬዝደን ራጆሊን ይፋ ካደሚጉት ዚሁለት ዹምክር ቀት አባላት ሞት በተጚማሪ 11 ዚአገሪቱ ምክር ቀት ዚሕዝብ እንደራሎዎቜና 14 ዹሕግ መወሰኛው ምክር ቀት አባላት በተደሹገላቾው ዚኮሮናቫይሚስ ምርመራ ቫይሚሱ እንደተገኘባ቞ው መናገራ቞ውን ኀኀፍፒ ዹዜና ወኪል ዘግቧል። ዚማዳጋስካር መንግሥት ዋና ኹተማዋ አንታናናሪቮ በምትገኝበት ዋነኛ ግዛቱ ውስጥ ዚኮሮናቫይሚስ በኹፍተኛ መጠን መስፋፋቱን ተኚትሎ ቀደም ሲል አንስቶት ዹነበሹውን ጥብቅ ዚእንቅስቃሎ ገደብ ባለፈው ሳምንት ተመልሶ ተግባራዊ ማድሚግ ተጀምሯል። ባለስልጣናት እንዳሉት ጥብቅ ዹሆነው ዚእንቅስቃሎ ገደብ ዚተጣለው በኹፍተኛ ፍጥነት እዚተዛመተ ያለውን ወሚርሜኝ ለመግታት ነው ብለዋል። ኚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ መኚሰት በኋላ ዚአገሪቱ ፕሬዝደንት ማዳጋስካር ኮቪድ-19ን ሊፈውስ ዚሚቜል መድኃኒት ማግኘቷን በመግለጜ በልበ ሙሉነት በመገናኛ ብዙሃን ላይ እዚወጡ ሲያስተዋውቁ እንደነበር ይታወሳል። አንዳንድ ዚአፍሪካ አገራትም በእርግጥ መድኃኒቱ ፈዋሜ እንደሆነ ለማወቅ ወደ ሃገራ቞ው ማስገባታ቞ው ዚሚታወቅ ሲሆን እስካሁን ግን ስለመድኃኒቱ ውጀት ያሉት ነገር ዚለም። ኚአሪቲ ዹተቀመመው "መድኃኒት" ስላለው ጠቀሜታ በህክምና ባለሙያዎቜ በኩል ዹተሰጠ ምንም ማሚጋገጫ ዹሌለ ሲሆን ባለሙያዎቜና ዚጀና ተቋማት ግን ስለመድኃኒቱ ፋዋሜነት ዚታወቀ ነገር ስለሌለ ሰዉ እንዳይዘናጋ ሲያስጠነቅቁ ቆይተዋል። አሁን ደግሞ በሜታው በአገሪቱ ኚመስፋፋት አልፎ በወሚርሜኙ ሰበብ ሁለት ዹምክር ቀት አባላት መሞታ቞ው ዚመድኃኒቱን ነገር ጥያቄ ውስጥ ኚትቶታል ተብሏል። በዓለም ጀና ድርጅት መሹጃ መሰሚት ወሚርሜኙ በመጀመሪያ በማዳጋስካር መኖሩ ኚታወቀ ጀምሮ እስካሁን 4,578 ሰዎቜ በኮሮናቫይሚስ መያዛ቞ው ዹተሹጋገጠ ሲሆን 34 ሰዎቜ ደግሞ በበሜታው ሰበብ ህይወታ቞ውን አጥተዋል።
50357378
https://www.bbc.com/amharic/50357378
በጃፓን ሎት ሠራተኞቜ መነጜር እንዳያደርጉ መኹልኹላቾው ጥያቄ አስነሳ
አንዳንድ ዹጃፓን ተቋሞቜ ሎት ሠራተኞቜ ቢሮ ውስጥ መነጜር እንዳያደርጉ መኹልኹላቾው አነጋጋሪ ሆኗል።
ኒፖን ቲቪ እና ቢዝነስ ኢንሳይደር ዚተባሉ ዹጃፓን መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡትፀ አንዳንድ ተቋሞቜ ልዩ ልዩ ምክንያት በማቅሚብ ሎት ሠራተኞቜ መነጜር እንዲያወልቁ ያስገድዳሉ። ይህም ዹጃፓን ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎቜ መነጋገሪያ ሆኗል። ዚአውሮፕላን ማሚፊያ እና ዚውበት ሳሎን ሠራተኞቜ መነጜር ሳያደርጉ መሥራት ተጜዕኖ እንደሚያሳድርባ቞ው ኚገለጹት መካኚል ና቞ው። በኮዮቶ ዩኒቚርስቲ ዚሶሟሎጂ መምህር ዚሆኑት ፕሮፌሰር ኩሚኮ ኔሞቶፀ ሎቶቜ ሥራ ቊታ መነጜር እንዳያደርጉ መኹልኹል "ያሚጀ ያፈጀ ዹጃፓን አሠራር ነው" ብለው ሕጉ አግላይ መሆኑን ገልጞዋል። • ጃፓን ኹቀበሌ መታወቂያ ያነሰቜ ሞባይል ሠራቜ • ዚምባብዌ 211 ሀኪሞቜን ኚሥራ አገደቜ • ተቃዋሚዎቜ ዚኚንቲባዋን ጾጉር አስገድደው ላጩ "ተቋሞቜ ሎቶቜን ዚሚመዝኑት በሥራ቞ው ሳይሆን በገጜታ቞ው ነው" በማለትም ተናግሚዋል። ተዋናይትና ጾሀፊ ዩሚ ኢሺካዋፀ በመሥሪያ ቀቶቜ ሎቶቜ "እንዲህ ይልበሱ" ዹሚል ድንጋጌ መኖሩን በመቃወም ፊርማ እያሰባሰበቜ ነው። ዩሚ ዚቀብር ሥነ ሥርዓት ስታስተባብር ታኮ ጫማ እንድታደርግ መገደዷን እንደ ምሳሌ ትጠቅሳለቜ። ብዙዎቜ ዩሚ ዚጀመሚቜውን እንቅስቃሎ እዚደገፉ ነው። በተለይም ዹጃፓን አመራሮቜፀ ተቋሞቜ ለሠራተኞቻ቞ው ዚአለባበስ ደንብ እንዲያወጡና እንዲያስፈጜሙ ማድሚጋ቞ው ተቃውሞውን አባብሶታል። ፕሮፌሰር ኩሚኖ እንደሚሉትፀ ሎት ሠራተኞቜ ታኮ ጫማ እንዲያደርጉ ዚሚያስገድደውን ፖሊሲ በርካቶቜ እዚተቃወሙ ነው።
55416249
https://www.bbc.com/amharic/55416249
ኮሮናቫይሚስ፡ ዚአውሮፓ ሕብሚት አገራት በዩኬ ላይ ዚጣሉትን ዹጉዞ እገዳ እንዲያነሱ አሳሰበ
ዚአውሮፓ ሕብሚት 27 አባል አገራት ኚዩናይትድ ኪንግደም ጋር በተያያዘ ዚተጣሉ ገደቊቜን በተመለኹተ ዚተባበሚ ምላሜ ለመስጠት እንደሚሞክሩ አስታወቁ።
ይህን ያሉት በዩናይትድ ኪንግደም ኹተገኘው አዲስ ዚኮሮናቫይሚስ ዝርያ ጋር ተያይዞ በርካታ አገራት ዹጉዞ እገዳ መጣላ቞ውን ተኚትሎ ነው። ዛሬ ማክሰኞ ዚአውሮፓ ኮሚሜንፀ አገራት ዚጣሉትን ዹጉዞ እገዳ እንዲያነሱና ወሳኝ ዹሆኑ ጉዞዎቜን እንዲጀምሩ ምክሹ ሃሳብ ሰጥቷል። ይሁን እንጂ ዚአውሮፓ ሕብሚት አባል አገራት በድንበር ቁጥጥር ላይ ዚራሳ቞ውን ሕግ ለማስቀመጥ ነጻ በመሆናቾው በራሳ቞ው ፖሊሲዎቜም ይህንን ማድሚግ ሊቀጥሉ ይቜላሉ። አዲሱ ዚኮሮናቫይሚስ ዝርያ ኚነባሩ በበለጠ ይበልጥ ተስፋፊ ሲሆንፀ ዹበለጠ ገዳይ ስለመሆኑ ግን ዚሚያመላክት ማስሚጃ ዚለም። ዚአውሮፓ ሕብሚት አባል አገራት ሁሉም በሚባል ደሹጃ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ዹሚደሹግ ዹጉዞ እገዳ እዚጣሉ ነው። ዚአውሮፓ ሕብሚት ኮሚሜንፀ አባል አገራቱ ዚኮቪድ-19 ምርመራ እንዲያደርጉ ወይም ራሳ቞ውን እንዲያገሉ በማድሚግ ሰዎቜ ወደ ዚሚኖሩበት አገራ቞ው እንዲሄዱ መፍቀድ አለባ቞ው ብሏል። ነገር ግን አስፈላጊ ያልሆነ ጉዞ ሊበሚታታ እንደማይገባ ገልጿል። አክሎም እንደ ዚኚባድ መኪና አሜኚርካሪዎቜ ያሉ መጓጓዣ አገልግሎት ላይ ዚሚሰሩ ሰራተኞቜ ኚተጣለው ዹጉዞ እገዳ እና አስገዳጅ ምርመራ ሊካተቱ አይገባም ብሏል። ዚተሰጡት ምክሹ ሃሳቊቜም ለሕብሚቱ አምባሳደሮቜ ዚሚቀርብ ሲሆን አባል አገራቱ ዚሚጥሏ቞ውን ገደቊቜ ኚግምት ያስገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ምንም እንኳን ይህ ምክሹ ሃሳብ ቢሰጥምፀ አገራት በራሳ቞ው ፖሊሲዎቜ እቀባውን ዹመቀጠል እድላ቞ው ሰፊ መሆኑን ዚቢቢሲው ጋቪን ሊ ኚብራስልስ ዘግቧል። በሌላ በኩል ዹዓለም ጀና ድርጅት ዚድንገተኛ አደጋዎቜ ኃላፊ ማይክ ርያን "አዲሱ ዚቫይሚስ ዝርያ ዚወሚርሜኙ ዝግመተ ለውጥ መደበኛ አካል ነው። ኚቁጥጥር ውጭም አልሆነም" ብለዋል። ይህ ንግግራ቞ው ግን ኹዚህ ቀደም ዚዩኬው ዚጀና ሚኒስትር ማት ሃንኮክ ኚተናገሩት ጋር ዹሚቃሹን ነው ተብሏል። በዩኬ እዚተሰጠ ያለውን ዹፋይዘር ክትባት አምራቜ ዹሆነው ዚባዮን቎ክ ተባባሪ መስራቜ ኡጉር ሳሂን በበኩላ቞ው ብሩህ ተስፋን ሰንቀዋል። ኡጉር "በሳይንሳዊ መልኩ ኚክትባቱ ዹሚገኘው ዚበሜታ መኚላኚያ ምላሜ አዲሱን ዚቫይሚስ ዝርያ ሊቋቋም ይቜላል" ብለዋል። አክለውም "ካስፈለገ አዲሱን ዝርያ ዹሚኹላኹል ክትባት በስድስት ሳምንታት ውስጥ ሊሰጥ ይቜላል" ሲሉም ተናግሚዋል።
news-48899946
https://www.bbc.com/amharic/news-48899946
ኀርትራ ዚአፍሪካ ነጻ ዚንግድ ቀጠናን ያልፈሚመቜ ብ቞ኛዋ ሃገር ሆነቜ
ዚአፍሪካ ዚምጣኔ ሃብት ኃያል ሃገር ባለቀት ናይጄሪያ ዚአፍሪካ ነጻ ዚንግድ ቀጠና ስምምነትን ፈሚመቜ። ይህም ኀርትራን ስምምነቱን ያልፈሚመቜ ብ቞ኛዋ አፍሪካዊት ሃገር አድርጓታል።
ዚናይጄሪያው ፕሬዝደንት ሙሃመዱ ቡሃሪ በኒጄር በተካሄደው ዚአፍሪካ ህብሚት ስብሰባ ላይ ፊርማቾውን አኑሚዋል። ነጻ ዚንግድ ቀጠናው ስምምነት ዓላማ በአባል ሃገራት መካኚል በሚደሹጉ ዚንግድ ልውውጊቜ ላይ ታሪፍን በማስቀሚት አፍሪካውያን ሃገራት እርስ በእርሳ቞ው ዚንግድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ለማበሚታታት ያሰበ ነው ተብሏል። ይህ ስምምነት ወደ ሥራ ዚሚገባበት ቀን ለጊዜው አልተወሰነም። በአሁኑ ወቅት አፍሪካውን ሃገራት ምርት እና አገልግሎታ቞ውን እርስ በእርስ ዚሚነግዱት 16 በመቶ ብቻ ሲሆን አውሮፓውያን ሃገራት ግን ኚሚያመርቱት ምርት እና አገልግሎት 65 በመቶ ዹሚሆነውን ለተቀሹው አውሮፓ ሃገር ይሞጣሉ። ዚአፍሪካ ህብሚት ዚአፍሪካ አህጉር ነጻ ዚንግድ ቀጠና ስምምነትን ተግባር ላይ ማዋልፀ እአአ በ2022 ላይ በአፍሪካ ሃገራት መካኚል ዹሚደሹገውን ዚንግድ ለውውጥ በ60 በመቶ ኹፍ ያደርገዋል ሲል ግምቱን ያስቀምጣል። • እውን ዚአፍሪካ ነፃ ዚንግድ ቀጣና ለኢትዮጵያ ይጠቅማል? • ዚአሜሪካና ቻይና ዚንግድ ጊርነት ዓለምን ሊያደኜይ ይቜላል • ህንድ አሜሪካን ይጎዳል ዚተባለ ዚንግድ ታሪፍ ልታስተዋውቅ ነው በተጚማሪም ስምምነቱ በዓለማቜን ትልቁን ነጻ ዚንግድ ቀጠናን ይፈጥራል ተብሎለታል። ዚአፍሪካ ግዙፍ መጣኔ ሃብት ባለቀት ናይጄሪያ ዚነጻ ንግድ ቀጠና ስምምነት ላይ ፊርማዋን ማኖሯ ዚስምምነቱን ውጀታማነት ላይ ጉልህ አስተዋጜኊ ያበሚክታል ሲሉ ባለሙያዎቜ አስተያዚታ቞ውን ሰጥተዋል። ኀርትራ ለምን ብቻዋን ቀሚቜ? ኀርትራ ኚኢትዮጵያ ጋር በነበራት አለመግባባት እና በሌሎቜ ምክንያቶቜ በስምምነቱ ዙሪያ ውይይቶቜ ላይ ተሳታፊ ሳትሆን መቆዚቷን ዚአፍሪካ ህብሚት ኮሚሜን ዚንግድ እና ኢንዱስትሪ ኮሚሜነር አልበርት ሙቻንጋ ይናገራሉ። ኮሚሜነሩ ጹምሹውም ኀርትራ ኚኢትዮጵያ ጋር ሰላም ማውሚዷን ተኚትሎ በስምምነቱ ዙሪያ ኚአፍሪካ ህብሚት ጋር ለመወያዚት ጥያቄ ማቅሹቧን ተናግሚዋል። ''በጊዜ ሂደት እነሱም ዚስምምነቱ አካል ይሆናሉ'' ብለዋል ኮሚሜነሩ።
51016544
https://www.bbc.com/amharic/51016544
እግራ቞ው አሜሪካ ልባ቞ው አፍሪካ ያለ ዚሆሊውድ ተዋንያን
አፍሪካ አሜሪካዊው ራፐር ሉዳ ክሪስ ሰሞኑን አፍሪካዊ ዜግነት አግኝቷል። በእውነተኛ ስሙ ክርስቶፈር ብሪያን ብሪጅስ በመባል ዚሚታወቀው ሉዳክሪስ አፍሪካዊ ዜግነት በቅርቡ ያገኘ ዚሆሊውድ ተዋናይ ነው።
ኚግራ ወቀደኝፀ ሉዳክሪስ፣ ኢድሪስ ኀልባ፣ ቲፋኒያ ሃዲሜ እና ሳሙዔል ኀል ጃክሰን። ዚሉዳክሪስ ውሃ አጣጭ ጋቊናዊት ስትሆን እናቱና ሁለት ሎት ልጆቹም ጋቩናዊ ዜግነት አግኝተዋል። በሆሊውድ ኹፍ ካለ ዹዝና ማማ ላይ ዹሚገኘው ሉዳ ክሪስ፣ በነዳጅ ሐብቷ ኚበለፀገቜው ጋቩን ምን ፈልጎ ነው? ዹሚል ደፋር ጠያቂ ቢመጣ፣ ዚእርሱ መልስ 'ወደ አፍሪካዊ ማንነቮ መመለስ ፈልጌ' ዹሚል ይሆናል። ኚሉዳክሪስ በፊት ግን በርካታ ዚሆሊውድ ተዋንያን አፍሪካዊ ዜግነት አግኝተዋል። ሳሙኀል ኀል ጃክሰን ዹጋቩንን ፓስፖርት ያገኘው ዚኚዚት መጣሁ ጥያቄን ለመመለስ በተሰራው ዘጋቢ ፊልም ላይ ተሳትፎ ዚዲኀን ኀ ምርመራ ካደሚገ በኋላ ነበር። ታዲያ ዹዘር ግንዱ ወደኋላ ሲቆጠር በደሙ ውስጥ ጋቩን ገነን ብላ ስለተገኘቜ ጋቩንም ሳታቅማማ ፓስፖርቷን ጀባ ብለዋለቜ። ጋቩን ብቻ አይደለቜም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ዜግነት ዚሰጠቜው። በግንቊት ወር ኮሜዲያንና ተዋናይት ዚሆነቜው ቲፋኒ ሐዲሜ ወደ ኀርትራ ተጉዛ ዜግነት አግኝታለቜ። በዚህ ተግባሯ አንዳንዶቜ ዚኀርትራን አምባገነን መንግሥት ትደግፋለቜ በሚል ተቃውሟቾውን አሰምተዋል። ባለፈው ሕዳር ወርም ጋና ለ126 አፍሪካ አሜሪካውያን እንዲሁም አፍሮ ካሪቢያን ዜግነትን ሰጥታለቜ። ይህንን ያደሚኩት አፍሪካውያን በባርነት ተወስደው ሰሜን አሜሪካ እግራ቞ው ዚሚገጠበትን 400ኛ ዓመት በማሰብ ነው በማለት 'ዚመመለስ ዓመት' በሚል ስም ዜግነት መስጠቷን ይፋ አድርጋለቜ። እንግሊዛዊው ታዋቂ ዹፊልም ተዋናይ ኢድሪስ ኀልባም ዚሎራሊዮን ዜግነት ያገኘው ባለቀው ዚፈሚንጆቜ ዓመት ዚመጚሚሻ ወር ላይ ነበር። • ስለኢትዮጵያ ዚቀተ ክርስቲያን ስዕሎቜ ምን ያህል ያውቃሉ? ዚኀድሪስ ኀልባ አባት ሎራ ሊዮናዊ ሲሆኑ ዜግነቱን ያገኘው ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገሪቱን በሚገጠበት ወቅት ነበር። ኢድሪስ በወቅቱ "ኚአገሬ ላገኘው ዚምቜለው ትልቁ ክብር ነው" ሲል ነበር ዹተሰማውን ለቢቢሲ ዚገለፀው። ለአፍሪካ አዲስ ያልሆነው ኢድሪስ ስለአፍሪካ ፊልም መስራቱን አፍሪካ ውስጥ ፊልም መቅሹፁን ኹጠቀሰ በኋላ "ሎራሊዮን ግን በልቀ ውስጥ ትልቅ ቊታ አላት" በማለት ዚቀተሰቊቹ አገር መሆኗን ገልጿል። በዚህ ዓመት በጋና ዹተዘጋጀው አፍሮፌስት ክብሚ በዓል ላይ ለመገኘት ታዋቂዋ ሞዮል ናኩሚ ካምቀል፣ ተዋናይቷ ሉፒታ ኒያንጎ፣ ድምጻዊ ኀኮን፣ ዚቢዮንሎ እናት ቲና ኖውልስ ላውሰን ቀጠሮ ይዘዋል።
news-49202443
https://www.bbc.com/amharic/news-49202443
ሳዑዲ አሚቢያ ሎቶቜ ያለወንዶቜ ጥበቃ እንዲጓዙ ፈቀደቜ
ሳዑዲ አሚቢያ ሎቶቜ ያለ ወንዶቜ ጥበቃና ፈቃድ ፓስፖርት እንዲያወጡና ኹአገር ውጭ እንዲጓዙ ፈቀደቜ።
ባለፈው አርብ ይፋ ዹተደሹገው አዲሱ ሕግፀ እድሜያ቞ው ኹ21 ዓመት በላይ ዹሆናቾው ሎቶቜ ያለወንድ ሚዳቶቻ቞ው ወይም አጋሮቻ቞ው ፈቃድ ፓስፖርት ለማውጣት ማመልኚት እንዲቜሉ ይፈቅዳል። • ሳዑዲ ሎቶቜ ወደ ስታዲዚም እንዲገቡ ልትፈቅድ ነው • ሳዑዲ ለሮቊት ዜግነት ሰጠቜ ማንኛውም አዋቂ ዹሆነ ሰው ፓስፖርት ኖሮት ኚአንድ አገር ወደሌላ እንዲጓዝ ዚሚያደርገው ሕግም ኚቊታ ቊታ በመንቀሳቀስ መብት ሚገድ ሎቶቜን ኚወንዶቜ እኩል አድርጓ቞ዋል። ሕጉ ጚምሮ እንዳስቀመጠው ሎቶቜ ዚውልደትን፣ ጋብቻንና ፍቺን ማስመዝገብ እንዲቜሉም ተፈቅዷል። ኹዚህም በተጚማሪም ዚሎቶቜን ዚሥራ እድል ዹሚመለኹተውን ዚሥራ ቅጥር ሕግ ተመልክቷል። በዚህ ሕግ ማንኛውም ዚአገሪቱ ዜጋ ያለምንም ልዩነትፀ ያለ ፆታ፣ ዚአካል ጉዳት ወይም እድሜ መድልዎ እኩል ዚመሥራት መብት እንዳላ቞ው አትቷል። እስካሁን ድሚስ ዚሳዑዲ ሎቶቜ ፓስፖርት ለማግኘትና ወደ ሌላ አገር ጉዞ ለማድሚግ ኚትዳር አጋራ቞ው፣ ኚአባታ቞ው አሊያም ኹሌላ ወንድ ዘመዳ቞ው ፈቃድ ማግኘት ይጠበቅባ቞ው ነበር። ኹዚህ ቀደም ዚሳዑዲ አሚቢያው ልዑል ሞሐመድ ቢን ሰልማን ሎቶቜ ማሜኚርኚር እንዳይቜሉ ዹሚኹለክለውን ሕግ ማንሳታ቞ው ይታወሳል። ይህም በአገሪቷ ለሎቶቜ እድሎቜ እዚተኚፈቱ መሆናቾውን ዚሚያሳይ ነው ተብሏል። ውሳኔው ሎቶቜ ኚወንዶቜ እኩል ኚቊታ ቊታ ዚመንቀሳቀስ መብታ቞ውን ዚሚያስጠብቅ ነው • ሳዑዲ ልዕልቷን ዚአሜሪካ አምባሳደር አደሚገቜ ልዑል ሞሐመድ ቢን ሰልማን ዚሎቶቜን በሥራ ላይ ያላ቞ውን ተሳትፎ ኹነበሹው 22 በመቶ ወደ 30 በመቶ ኹፍ በማድሚግ ዚአገሪቱን ኢኮኖሚ በ2030 ለማሳደግ ዓላማ ይዘው እዚሠሩ መሆናቾውን ኚሊስት ዓመታት በፊት አስታውቀው ነበር። ይሁን እንጂ በርካታ ኹፍተኛ እውቅና ያላ቞ው ሎቶቜ ዚሚደርስባ቞ውን ዚፆታ መድልዎ ምክንያት በማድሚግ በካናዳና በተለያዩ አገራት ጥገኝነት ይጠይቃሉ። ባለፈው ጥር ወር ዹ18 ዓመቷ ራሃፍ መሀመድ አልቁኑን በካናዳ ጥገኝነት ተሰጥቷታል። ራሃፍ ኚሳዑዲ አሚቢያ ዚተሰደደቜ ሲሆን ወደ አውስትራሊያ ለመግባት ሞክራ ነበር። በመጚሚሻም በታይላንድ ባንኮክ አዹር ማሚፊያ ሆቮል ተይዛ ዓለም አቀፍ እርዳታ እንዲደሚግላት ጠይቃለቜ። ይህቜ ሎት በአገሯ ላይ እንደሁለተኛ ዜጋ ተቆጥራላቜ ሲሉ ዚተለያዩ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋ቟ቜ ቅሬታ቞ውን ያሰሙ ነበር።
49561212
https://www.bbc.com/amharic/49561212
ድሬ ዳዋ ስለሚገኙት ዹለገ ኊዳ ዚዋሻ ሥዕሎቜ ያውቃሉ?
ኚድሬ ዳዋ ኹተማ 36 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ዹሚገኘው ዹለገ ኊዳ ዋሻ ወደ 600 ዹሚጠጉ ጥንታዊ ዚዋሻ ሥዕሎቜ ይገኙበታል። በ1920ዎቹ አካባቢ በተመራማሪዎቜ ዕውቅና እንዳገኙ ዹሚነገርላቾው ዚዋሻ ሥዕሎቜ ኹ7,000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ ባለሙያዎቜ ይገልጻሉ።
ዹለገ ኊዳ ዋሻ በብዛት በቀይ፣ በቢጫና ግራጫ ቀለም ኚተሠሩት ሥዕሎቜ መካኚል ዚቀት ውስጥ መገልገያ ቁሳ ቁሶቜ እንዲሁም እንስሳት ዚሚያሳዩት ይገኙበታል። • "ዚዘሚፉትን ቅርስ በውሰት እንመልስ ማለታ቞ው ተገቢ አይደለም" ሚኒስትር ሂሩት ካሳው • ዚመይሳው ካሳ ዹልጅ ልጆቜ • ኚኢትዮጵያና ኚሌሎቜ ዚአፍሪካ ሃገራት ስለተዘሚፉ ቅርሶቜ ምን እናውቃለን? ዚድሬ ዳዋ ኹተማ ባህልና ቱሪዝም ባለሙያ ዚሆኑት አቶ ደሹጄ ታደሰፀ ሥዕሎቹ ጥንት በአካባቢው ይኖሩ በነበሩ ሰዎቜ እንደተሠሩናፀ ዹአኗኗር ዘይቀያ቞ውን እንደሚያሳዩ ለቢቢሲ ገልጞዋል። ሥዕሎቹ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሜ አደጋም እንደተጋሚጠባ቞ው አቶ ደሹጄ ተናግሚዋል። ዋሻ ሥር ዚሚገኙት ሥዕሎቜ በዝናብ ሳቢያ እዚደበዘዙ መጥተዋል። በሰው ንክኪ ምክንያትም ዚቀድሞ ይዘታ቞ውን እያጡ ነው። አቶ ደሹጄ እንደሚሉትፀ ቅርሱ በአግባቡ ባለመያዙ ዹአገር ውስጥና ዚውጪ ጎብኚዎቜ ቁጥር እዚቀነሰ መጥቷል። ቅርሱን ኚዝናብ ለመኹላኹል መጠለያ ቢሠራምፀ ዹበለጠ እንክብካቀ እንደሚያስፈልገው ባለሙያው ተናግሚዋል። ዚቢቢሲ ባልደሚባ ወደሥፍራው አቅንቶ ካነሳ቞ው ፎቶግራፎቜ ዚሚኚተሉት ይገኙበታል። በለገ ኊዳ ዋሻ ኚሚገኙት ጥንታዊ ሥዕሎቜ አንዱ በቢጫና ግራጫ ቀለም ኚተሠሩት ሥዕሎቜ መካኚል ዚቀት ውስጥ መገልገያ ቁሳ ቁሶቜ እንዲሁም እንስሳት ዚሚያሳዩት ይገኙበታል ዚዋሻ ሥዕሎቹ ኹ7,000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ ይነገርላቾዋል በዋሻው ውስጥ ወደ 600 ሥዕሎቜ ይገኛሉ ሥዕሎቹ ዚተፈጥሮና ሰው ሰራሜ አደጋም ተጋርጊባ቞ዋል ሥዕሎቹን ኚዝናብ ለመኹላኹል ዚተሠራው መጠለያ ዹለገ ኊዳ ዋሻ ዚዋሻ ሥዕሎቹ በ1920ዎቹ አካባቢ በተመራማሪዎቜ እውቅና ማግኘታ቞ው ይነገራል
news-48607488
https://www.bbc.com/amharic/news-48607488
ለጎንደር ጥልቅ ፍቅር ያለው ኬንያዊ ቀተ መንግሥት ሊገባ ሲል ተያዘ
ጎንደር በመሄድ ዹማገልገል ጥልቅ ፍላጎት አለኝ ዹሚለው ኬንያዊ ቢላ ይዞ ወደ ፕሬዚዳንቱ ቀተ መንግሥት ጥሶ ለመግባት ሲሞኚር በጠባቂዎቹ ተተኩሶበት ቆስሎ ተይዟል።
በፌስቡክ ገጹ ላይ በኬንያ መሪዎቜ ስር ኚመተዳደር ጎንደር ውስጥ ዚቀት ውስጥ አገልጋይ ሆኖ መኖርን እንደሚመርጥ ዹሚናገሹው ብሪያን ኪቀት ቀራ ሰኞ እለት ነበር ቀተ መንግሥቱ ውስጥ ለመግባት ዚሞኚሚው። በጆሞ ኬንያታ ዚግብርናና ዹቮክኖሎጂ ዩኒቚርስቲ ውስጥ ዚአምስተኛ ዓመት ዚሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ዹሆነው ብራያንፀ ቀተ መንግሥት ሊገባ ሲል ግራ ትኚሻው ላይ በጥይት ኹቆሰለ በኋላ ሆስፒታል ገብቷል። •እምቊጭ ዚጣና ቂርቆስ መነኮሳትን ኚገዳሙ እያስለቀቀ ነው •"ማንም ቢሆን ኢትዮጵያን ለብቻዬ ሰራኋት ሊል አይቻለውም" ጠ/ሚ ዐብይ ፖሊስ እንዳለው ዹ25 ዓመቱ ብሪያን ኪቀት ወደ ቀተ መንግሥቱ ለመግባት ሲሞክር ዹተመለኹተው ዚጥበቃ መኮንን ግለሰቡ ዚአእምሮ ህመምተኛ ሊሆን ይቜላል በሚል ለሞት በማያበቃው ቊታ ላይ በጥይት እንደመታው ገልጿል። ብሪያን በተደጋጋሚ በፌስቡክ ገጹ ላይ ወደ ብሔራዊ ቀተ መንግሥቱ በመሄድ "ሌባ" ዹሚላቾውን ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታን እንደሚገድል ይጜፍ ነበር። ሰሞኑንም ይህንን ዛቻውን ለመፈጾም ሙኚራ አድሚጓል። ዹ25 ዓመቱ ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪ በተደጋጋሚ መንግሥትን ዚሚጻሚሩ በተለይ ደግሞ ፕሬዝዳንቱን በማጥላላት ዹተሞሉ ሃተታዎቜን በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ያሰፍር ነበር። አቋሙን ለመደገፍም ዚመጜሃፍ ቅዱስ ጥቅሶቜን ያጣቅስ እንደነበር ዚተለያዩ ዚኬንያ ጋዜጊቜ ዘግበዋል። ዚተለያዩ ዚታሪክ መጜሃፍትን እንዳነበበ ዹሚገመተው ብሪያን ወደ ኢትዮጵያ በመሄድ ጎንደር ውስጥ መኖር እንደሚፈልግ ጠንኹር ባለ ሁኔታ በተደጋጋሚ ሲጜፍ እንደነበሚም ተነግሯል። በአንድ ጜሁፉ ላይም "ይህ መልዕክት መሬ቎ንና ርስ቎ን ለዘሹፉኝ ለፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታና ለህዝባ቞ው እንዲደርስ ይሁን። ኬንያ ውስጥ መሪ ኹምሆን ኢትዮጵያ ውስጥ አገልጋይ ብሆን ይሻለኛል" ሲል አስፍሯል። •ኢትዮ ቎ሌኮም... ወዎት? ወዎት? ወደ ጎንደር ዚመሄድ ፍላጎቱን በተደጋጋሚ ዹሚጠቅሰው ተማሪው "ኚጠላቶቌ ጋርም ጊርነት አውጃለሁ። ምክንያ቎ ደግሞ ወደ ጎንደር ዚምሄድበትን ገንዘብ ለማግኘት ነው" ብሏል። "ሞኝ (ጹቋኝ) መሪ ኹመሆን ዚብልሆቜ ባሪያ መሆንን እመርጣለሁ" ዹሚለው ብሪያን ጎንደር በመሄድ ብልህ ለሆኑት ህዝቊቜ አገልጋይ መሆን እንደሚፈልግ ጠቅሶ ለጉዞው ዚሚያስፈልገውን ገንዘብ አለማግኘቱ እንዳዘገዚው አስፍሯል። ስለጎንደርና ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በማህበራዊ ገጹ ላይ እንደሚጜፍ ዹተነገሹው ይህ ወጣት በእያንዳንዱ ጜሁፉ ማብቂያ ላይ "ኚኢትዮጵያዊው ልዑልፀ ቀድሞ ብሪያን ኪቀት ቀራ ተብሎ ይጠራ ዹነበሹው" ሲል ያሰፍራል። ብራያን ወደ ቀተመንግሥቱ ለመግባት ካደሚገው ሙኚራ ቀደም ብለው ጜሁፎቹ በመመልኚት በርካቶቜ ዚተለያዩ ሃሳቊቜ በመሰንዘር ድርጊቱን ዹተቃወሙ ሲሆን አንዳንዶቜ ደግሞ ዚአእምሮ ጀንነቱን ተጠራጥሚዋል።
45725160
https://www.bbc.com/amharic/45725160
ዚፍስሀ ተገኝ ዚቀተሰብ ፍለጋ ጉዞ
ፓስፖርቱ ላይ ዚትውልድ ስፍራ ዹሚለው ክፍት ቊታ ላይ 'ሐሚር' ተብሎ ተጜፏል። ዹተወለደው ግን ሐሚር አይደለም። ታዲያ ለምን ሐሚር ተብሎ ተጻፈ?
ፍስሀና አክስቱ በእርግጥ ሐሚር አሳድጋዋለቜ። ቀተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ ሰጥታዋለቜፀ ለፍስሀ ተገኝ። ዚፍስሀ ህይወት በጥያቄዎቜ ዹተኹበበ ነው። 'ቀተሰቊቌ፣ ዘመዶቌ ወዎት አሉ?' ዹሚለውን ጥያቄ እንዳነገበ ኹሐሹር አዲስ አበባ፣ ኚአዲስ አበባ እንግሊዝ ባዝኗል። ዹ1997 ዓ. ም ምርጫ ዹሚወደውን ዚስፖርት ጋዜጠኛነት ብቻ ሳይሆን ሀገሩንም አሳጥቶታል። ያኔ ኀፍኀም አዲስ 97̏. 1 እዚሰራ ሳለ አዲስ አበባ በ97ቱ ምርጫ ማግስት ታመሰቜ። • በቮክኖሎጂ ኢ-ፍትሐዊነትን ዚምትታገለው ኢትዮጵያዊት • ኚጥንት ሮማውያን እስኚ ትዊተር ዹደሹሰው ዹ# ምልክት በወቅቱ ህይወታ቞ው ካለፉ ሰዎቜ አብዛኞቹ ዚተገደሉት ባንክ ለመዝሹፍ ሲሞክሩ ነበር ዹሚል ዜና እንዲያነብ ተሰጠውፀ አሻፈሚኝ አለ። ህሊናዬ ዚማያምንበትን ነገርስ አልናገርም ማለቱ ሥራውን አሳጣው። ዹኋላ ኋላ ኚትውልድ ሀገሩ መሰደድ ግድ ሆነበት። ዚሥጋ ዘመዶቹን ዚማግኘት ፍላጎቱን እንዳነገበ ወደ እንግሊዝ አቀና። ለጥያቄው መልስ ሳያገኝ በዓመት ላይ ዓመት ተደሚበ። በ2010 ዓ. ም ያልተጠበቀ ዜና ተሰማ። በተለያዩ ሀገሮቜ በፖለቲካ ጥገኝነት ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወደሀገራቜሁ መመለስ ትቜላላቜሁ ተባሉ። ጥሪውን ተቀብለው ኚአስርታት በኋላ ዳግም ኢትዮጵያን ለመርገጥ ኚቻሉ አንዱ ፍስሀ ነው። 2011 ዓ.ም ለመቀበል ባትወልደውም ወዳሳደገቜው ኹተማ ወደ ሐሚር አቀና። «ቀተሰቊቌን ማግኘት አለብኝ. . . » ያደገው ሐሚር ኀስኊኀስ ዚህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ነው። ዚልጆቜ ማሳደጊያው ውስጥ ለአስር ህጻናት አንድ እናት ይሰጣል። ፍሰሀን ኚሌሎቜ ዘጠኝ ልጆቜ ጋር ያሳደጉት እናት አሁን ጡሚታ ወጥተዋል። «በጣም ዚምወዳት ዚማፈቅራት እና቎ እሷ ነቜ። ዹምወደው ቀትም ኀስኊኀስ ነውፀ አሳድጎኛል። ቀተሰብ ጎደለብኝ ሳልል አድጌያለሁ» ዹሚለው ፍስሀ አዲሱን ዓመት ኚእናቱ ጋር ማሳለፉ እጅጉን አስደስቶታል። ሆኖም ዚዘመናት ጥያቄው ማቃጹሉን አላቆመም። «ቀተሰቀ ዚታሪኬ አካል ነውፀ ዚአብራኬ ክፋዮቜ ና቞ው። መፈለግ አለብኝ። ማግኘት አለብኝፀ» ስደት ቀተሰቊቹን እንዳያፈላልግ አግዶት ነበር። ቀተሰቊቹን ሳይገኝ ዚባኚኑ ዓመታት ቢቆጚውም ለማንነት ጥያቄው መልስ ለማግኘት ወደ ላሊበላ ተጓዘ። ዹተወለደው ላስታ አካባቢ እንደሆነ ቢያውቅም፣ እትብቱ ዚተቀበሚበትን ቊታ በትክክል አያውቅም። ዚሥጋ ዘመዶቹ ዚት እንዳሉም መሹጃው ዚለውም። እሱና እናቱ በ77ቱ ሚሀብ ሳቢያ ወደ ወለጋፀ ቄለም ተወሰዱ። ቄጩ ዚሚባል ሰፈራ ጣቢያ ይኖሩም ነበር። እናቱ ኹዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ኚአርባ ልጆቜ ጋር ወደ ኀስኊኀስ ተወሰደ። «እዚያ ስናድግ ቀተሰባቜን፣ ወላጃቜን፣ አሳዳጊያቜን፣ እናታቜን፣ አባታቜን ኀስኊኀስ ነበር። ሙልቅቅ አድርጎ ነው ያሳደገን» ይላል ስለአስተዳደጉ ሲናገር። እድሜው እዚጚመሚ ሲሄድ ስለቀተሰቊቹ ማንነት ያለማቋሚጥ ያሰላስል ጀመር። ለጥያቄው መልስ ዚሚሰጥ ኢሜል እጁ ሲገባ ለፍለጋው መንገድ ተቀዚሰለት። ኢሜሉ ለኀስኊኀስ ዹተሞላ ቅጜ ሲሆንፀ ዚትውልድ ቊታውን እንዲሁም ዚእናቱን ስም ኚነአያታ቞ው ይዟል። ኚእንግሊዝ ኹተመለሰ በኋላ በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን ቃለ መጠይቅ ሲደሚግለት ስለቀተሰብ ፍለጋው ያወራ ነበር። ይህን ዹሰማ አንድ ሰው እናቱ ዚላስታ ሰው ስለሆኑ በፍለጋው ሊያግዙት እንደሚቜሉ ይነግሩታል። «አባ቎ አለ!» ወደ ላሊበላ በሚሚ። እኚያ ሎት ቀትም አሚፈ። ደስታ ይባላሉ። ፍስሀ ወደ ላሊበላ ኚመሄዱ በፊት ዚቀተሰቊቹን ማንነት እያጣሩለት ነበር። «ለመሆኑ ዚእናትህን አያት ስም ታውቃለህ?» አሉት። «ቢሰውር ይባላልፀ ሙሉ ስሟ ሞዋዬ ታገል ቢሰውር ነው» ሲል መለሰ። ደስታ ጊዜ ሳያጠፉ ወደ አንድ ሰው ደወሉ። ዚደወሉለት ሰው ዚነገራ቞ው ነገር እሳ቞ውንም ፍስሀንም በሀሎት ዹሞላ ነበር። «ሙጃ ዚሚባል ቊታ ለሚገኝ ተድላ ለሚባል ሰው ደውላ ዚእናቱ አያት ስም ቢሰውር ነው ስትለውፀ ዚቢሰውር ቀተሰቊቜማ ዹኛ ቀተሰቊቜ ናቾው አለ። ኹዛ በደስታ ጚፈሚቜፀ እኔንም አቀፈቜኝፀ» • አይሞወዱ፡ እውነቱን ኚሐሰት ይለዩ • በእራስ ውስጥ ሌሎቜን ማዚት በማግስቱ ኹላሊበላ ወደ ሙጃ ሄደ። ኚዚያማ ዚዘመድ ጎርፍ አጥለቀለቀው። «በእና቎ም በአባ቎ም በኩል ዹተገኙ ሰዎቜ ነበሩ። እነሱን ካገኘን በኋላ እነሱ ሌሎቜን ይዘው ማምጣት ጀመሩ። ቀጥሎም ሙጃ ውስጥ ወንድም አለህ ተባልኩ» ፍሰሀ ለእናቱ ብ቞ኛ ልጅ እንደሆነ ነበር ዚሚያውቀው። ታናሜ እህቱ ሞታለቜ። ወንድምህ ዚተባለው ሰው ዚአባቱ ልጅ ነበር። እዚያው ሙጃ ውስጥ ዹሚኖሹውን ወንድሙን ሲያገኘውፀ አስቊትም አልሞትም ዚማያውቀውን ብስራት አሰማው። «አባታቜን በህይወት አለ!» መላ ህይወቱን አባቱ እንደሞቱ ነበር ዚሚያስበው። ኢሜል ዚተደሚገለት ቅጜ ላይም አባቱ መሞታ቞ው ተጜፏል። ወደ አባቱ ስልክ ደውሎ በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምጻ቞ውን ለመስማት በቃ። «ዚተወለድኩት ብርግነት ነው» ፓስፖርቱ ላይ 'ሐሚር ተወለደ' ይባል እንጂ እትብቱ ዹተቀበሹው ብርግነት ነው። ልጅ ሳለ እናቱን እና እሱን ኚትውልድ ቀያ቞ው ዹሾኛቾው ዚእናቱ ታናሜ ወንድም ነበር። «እሜኮኮ አድርጎ ሞኘኝ» ዹሚለውን አጎቱን ዳግም አገኘ። ኚበርካታ ዚእናቱ ወገኖቜ ጋርም አገናኘው። «ዚእና቎ን እህቶቜ፣ አክስቶቌን አገኘሁ። ዚእነሱን ልጆቜ፣ ዹልጅ ልጆቜ አገኘሁ። ዚእና቎ ታናሜ ወንድምፀ አጎቮ ጋር ሄጄ አራት ቀን ቆዚሁ። ስልክ ዚለ፣ ኀሌክትሪክ ዚለ፣ ዹገጠር ህይወትን ለመድኩ። በግ ታርዶልኝ ሲያሞላቅቁኝ ነበር።» ዚእናቱ ታላቅ እህት ትርንጎ ይባላሉ። አብዛኞቹ ዘመዶቹ 'ሞቷል' ብለው ቢያምኑምፀ እሳ቞ው ግን 'በህይወት አለ' ይሉ ነበር። ይጞልዩለት እንደነበርም ይናገራል። እንዳፋ቞ው ሆኖ በአይነ ሥጋ ሲያገኙት 'ትተኞኝ አትሂድ' ብለውት እንደነበር በትዊተር ገጹ ላይ አስፍሯል። እሱና አክስቱ ዚተነሱትን ፎቶ በትዊተር ገጹ ሲለጥፍ ተኚታዮቹ በፍጥነት ነበር ምላሜ ዚሰጡት። ዚቀተሰብ ፍለጋ ጉዞውን ኚጀመሚበት እለት አንስቶ ትዊተር ገጹ ላይ ይጜፍ፣ ፎቶም ይለጥፍ ነበር። አብሚውት ያሉ ያህል ጉዞውን በድሚ ገጜ ዚተኚታተሉ ወዳጆቹም መልካም ምኞታ቞ውን ይገልጹለት ነበር። ዚልጅነት ትውስታውን ኚአክስቱ ኹሰማ በኋላ በስልክ ድምጻ቞ውን ዹሰማውን አባቱን በአካል ለማግኘት ወደ ሳንቃ ሄደ። «አባ቎ ካገኘኝ ጀምሮ ሲያለቅስ ነበር ዚዋለው» ይላል ፍስሀ። ሳንቃ ውስጥ ያገኘው አባት ብቻ ሳይሆን በአባት ዹሚገናኛቾው እህትና ወንድም ጭምርም ነበር። «ሙጃ አንድ ታላቅ ወንድም ነበሚኝ። ኚእሱ ተጚማሪ አንድ እህትና አንድ ወንድም አገኘሁ» ጉዞውን ሲጀምር አባት፣ እህት፣ ወንድም፣ አክስት፣ አጎት አገኛለሁ ብሎ አልነበሚም። በስተመጚሚሻ ግን ራሱን በዘመድ ተኹቩ አገኘው። ዹሆነው ሁሉ ቢያስደስተውም እንደዘገዚም ተሰምቶታል። እሱ ቀተሰቊቹን ለማግኘት በተቻለው ሁሉ ጥሯል። ነገር ግን 'እነሱስ ለምን ሊፈልጉኝ አልሞኚሩም?' ብሎ ግን ይጠይቃል።
48048268
https://www.bbc.com/amharic/48048268
አሜሪካ፡ ታዳጊዋን ለ16 ዓመታት ያሰቃዩ ጥንዶቜ እስር ተፈሚደባ቞ው
ለ16 ዓመታት ዚአንዲት ታዳጊን ጉልበት ይበዘብዙ ዚነበሩ ጥንዶቜ ዚሰባት ዓመት እስር ተፈርዶባ቞ዋል።
መሐመድ ቱሬ እና ባለቀቱ ዎኒስ ቱሬ መሐመድ ቱሬ እና ባለቀቱ ዎኒስ ቱሬ ዚተባሉት ጋያናውያን ጥንዶቜ ታዳጊዋን ኚጋያና ወደ አሜሪካ ዚወሰዷት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2000 ነበር። • ለአካል ክፍላቾው ሲባል ህጻናት ተገድለው ተገኙ ቎ክሳስ ውስጥ ይኖሩ ዚነበሩት ጥንዶቜ ታዳጊዋን ለ16 ዓመታት ያለምንም ክፍያ አሠርተዋታል። ወደአሜሪካ ስትወሰድ ዚአምስት ዓመት ልጅ ዚነበሚቜው ሎትፀ ቀት እንድታጞዳ፣ ምግብ እንድታበስልና ልጆቜ እንድትንኚባኚብ ትገደድ ነበር። • ዚአንዱ እርግማን ለአንዱ ምርቃን፡ ኢትዮጵያን መጠጊያ ያደሚጉ ዚስደተኞቜ ታሪክ ጥንዶቹ ታዳጊዋን ይደበድቧት ነበር። ጞጉሯን ላጭተዋት፣ ቅጣት ብለው በቀታ቞ው አቅራቢያ በሚኝ ፓርክ ውስጥ ብቻዋን ያሳድሯትም ነበር። እንዳትማር ኹመኹልኹላቾው ባለፈ ፖስፖርቷን ነጥቀዋትም ነበር። 2016 ላይ ዚጥንዶቹ ዚቀድሞ ጎሚቀቶቜ ታዳጊዋ እንድታመልጥ ሚድተዋታል። አቃቀ ሕግ ዚነበሚቜበትን ሁኔታ ዹገለጾው "ልጅነቷን ቀምተዋታል። ለዓመታት ጉልበቷን በዝብዘዋል። እሷ እዚተሰቃዚቜ እነሱ ሕይወታ቞ውን ያለቜግር ገፍተዋል" በማለት ነበር። • በስዊድን ያሉ ዚስደተኛ ልጆቜ ሚስጥራዊ ህመም ባልዚው ዚጋያና ዚመጀመሪያ ፕሬዘዳንት አህመድ ሶኩ ቱሬ ልጅ ሲሆንፀ ጥንዶቹ ዚአሜሪካ ዜግነታ቞ውን ሊቀሙ ይቜላሉ ተብሏል። ፍርድ ቀት ጥንዶቹ 288,620 ዚአሜሪካ ዶላር እንዲኚፍሉ ወስኗል። ባልና ሚስቱፀ ስለኛ ዚተወራው ነገር "እጅግ ተጋኗል" በማለት አቀቱታ ዚማሰማት እቅድ አላቾው ተብሏል።
news-56506565
https://www.bbc.com/amharic/news-56506565
አሜሪካ፡ በኮሎራዶ ጥቃት ዚሟ቟ቜ እና ጥቃት አድራሹ ማንነት ይፋ ተደሹገ
ዚኮሎራዶ ግዛት ባለስልጣናት በትናትናው ጥቃት ዹተገደሉ 10 ግለሰቊቜን እና ዚጥቃት አድራሹን ማንነት ይፋ አደሚጉ።
በገበያ ስፍራ ዚተገሉት ሰዎቜ እድሜ በ20 እና 65 መካኚል ዹሚገኝ ሲሆን ኚሟ቟ቹ መካኚል ዹ7 ልጆቜ አባት ዹሆነ ዚፖሊስ አባል ይገኝበታል። ጥቃቱ ዹቆመው ፖሊስ ኚጥቃት አድራሹ ጋር ዚተኩስ ልውውጥ አድርጎ በቁጥጥር ሥር ካዋለ በኋላ ነው። ተኳሹ ዹ21 ዓመት ወጣት አሕመድ አል አሊዊ አል ኢሳ ዚሚባል ሲሆን በ10 ሰዎቜ ግድያ ክስ ይመሰሚትበታል ተብሏል። ጥቃት አድራሹ አብዛኛውን ሕይወቱን በኮሎራዶ ግዛት በምትገኝ አርቫዳ መኖሩን ዐቃቀ ሕግ አስታውቋል። ፖሊስ ተኳሹ ይህን ጥቃት ለመሰንዘር ምን እንዳነሳሰው እስካሁን ግልጜ አይደለም ብሏል። ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ኚጥቃቱ በኋላ በሰጡት አጭር መግለጫ መሰል ጥቃቶቜን ለማስቆም ዹጩር መሳሪያ ቁጥጥር መደሹግ አለበትፀ ዹጩር መሳሪያ መግዛት በሚሹ ላይም ዹኋላ ማንነት ማጣራት አስፈላጊ ነው ሲሉ አሳስበዋል። ስለ ጥቃቱ ምን እናውቃለን በገበያ በደሹሰው ጥቃት ፈጻሚው ቆስሎ መያዙ ተመልክቷል። ዹደሹሰው ጥቃት በዩቲዩብ ቀጥታ መተላለፉም ታውቋል። ጥቃቱ ዹደሹሰው በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር 8፡30 ቀን ላይ ሲሆን ግለሰቡ ወደ ገበያ አዳራሹ እንደገባ መተኮስ ጀምሯል። ጥቃቱ ዚደሚሰበት አካባቢ፣ ቩውልደር ፖሊስ ኹ20 ደቂቃ በኋላ በትዊተር ገፁ ላይ "በኪንግ ሱፐርስ ዚገበያ ስፍራ ተኩስ ዹኹፈተ ግለሰብ አለ" ሲል ጜፎ ነበር። ኚሁለት ሰዓት በኋላ ፖሊስ ሰዎቜ ኚአካባቢው እንዲርቁ አስጠንቅቋል። በአኚባቢው ዚነበሩት ሰዎቜ ሁኔታውን በተንቀሳቃሜ ምስል አስቀርተውት በማህበራዊ ሚዲያዎቜ አጋርተው ነበር። በአንዱ ቪዲዮ ላይ "ምን እንደተኚሰተ አላውቅም. . . ዚተኩስ ድምጜ ሰማሁ። ዹሆነ ሰው ተመትቶ ወደቀ" ሲል ምስሉን ዹሚቀርጾው ይሰማል። በቪዲዮው ላይ ፖሊስ ደርሶ ዚገበያ አዳራሹን ሲኚብ ይታያል።
news-53507160
https://www.bbc.com/amharic/news-53507160
ኮሮናቫይሚስ፡ በበይነ መሚብ ዚተካሄደው ታላቁ ዚአፍሪካ ሩጫ
ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ መኚሰት በርካታ ዚማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሎዎቜን ኚስሚ መሰሚቱ ቀይሯል። ኹአሁን በፊት ልንጠቀምባ቞ው ያልመሚጥና቞ው መንገዶቜን ዚቫይሚሱ መኚሰት አሁን እንድናጀና቞ው ግድ ብሏል።
አምባሳደር አሪካና ቺሆምቊሪ ቃኊ፣ አትሌት ደራርቱ ቱሉ እና ዶ/ር ጋሻው አብዛ [ኚግራ ወደ ቀኝ] በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ታውሰን ዩንቚርሲቲ በስፓርት ቢዝነስና ቮክኖሎጂ መምህርና ተመራማሪ ዚሆኑት ዶክተር ጋሻው አብዛ ዚኮሮናቫይሚስ መኚሰትን ተኚትሎ ስራ቞ው በቀት ውስጥ ኹሆነ ሰነባብቷል። ነገር ግን አንዳንድ ስራዎቻ቞ው ዚግድ በአካል መገኘትን ዹሚጠይቁ በመሆና቞ው፣ ቅርጻ቞ውን መቀዹር ግድ ብሏ቞ዋል። ዶክተር ጋሻው በሞያ቞ው ኚኢትዮጵያውያን አትሌቶቜ ጋር በመገናኘት ዚተለያዩ ሥራዎቜ ይሰራሉ። ነገር ግን ኮሮናቫይሚስ ይህንን ሥራ቞ውን በአካል ተገኝተው እንዳይሰሩ አግዷ቞ዋል። ኹዚህም ባለፈ ኮሮናቫይሚስ በተማሪዎቻ቞ው ላይ ዚጀና፣ ዚሥነ ልቩናና ዚኢኮኖሚ ጫና ዚሚያሳድር በመሆኑ "እንደ መምህር ያ ያሳስበኛል" ይላሉ። ኚቀት ሳንወጣ እንድንሰራ መገደዳቜንም ተጜዕኖ ያሳድራል ያሉት ዶ/ር ጋሻው፣ ኚህዝብ ጋር መገናኘት አለመቻልና ውጪ ላይ ስፖርታዊ እንቅስቃሎዎቜን ማድሚግ አለመቻልም ሌላኛው ቜግር መሆኑን ያብራራሉ። አገር ቀት መኖሪያ቞ውን ያደሚጉ አትሌቶቜን ማማኹርና ማስተማር ዚተጓዳኝ ስራ቞ው ነው። በስፖርቱ ዘርፍ ያካበቱትን እውቀት አገር ቀት በመመላለስ ለኢትዮጵያውያን አትሌቶቜ ያካፍላሉፀ ነገር ግን ዚኮሮናቫይሚስ መኚሰት ይህንን ኚማድሚግ አግዷ቞ዋል። በዚህም ምክንያት ወሚርሜኙ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ኹፍተኛ ጫና ማሳደሩን ያብራራሉ። "አትሌቶቜ ኹመላ አገሪቱ ተሰባስበው መቀመጫ቞ውን አዲስ አበባ በማድሚግ ነው ልምምድ ዚሚያደርጉት" ዚሚሉት ዶ/ር ጋሻውፀ በቫይሚሱ ምክንያት በመላው ዓለም ኩሊምፒክን ጚምሮ ሁሉም ውድድሮቜ በመሰሹዛቾው ዚገቢ ምንጫ቞ው ተዘግቶ ኚግማሜ ዓመት በላይ ዚቆዩ በመሆና቞ውፀ ዚምጣኔ ሃብት ቀውሱ በቀላሉ ዚሚታይ አይደለም ይላሉ። እንደ እርሳ቞ው ገለጻ ዚአትሌቶቜ ዋነኛ ዚገቢ ምንጭ በመላው ዓለም ተዘዋውሹው በሚያደርጓ቞ው ውድድሮቜ ዚሚያገኙት ሜልማት ነው። ያንን አሁን ባለው ሁኔታ ማድሚግ ስለማይቻልም ኹፍተኛ ዚኢኮኖሚ ጫና ውስጥ እዚገቡ መሆናቾውን ይናገራሉ። ዶ/ር ጋሻው በተጚማሪም በዚዓመቱ በአሜሪካ ዋሜንግተን ዚሚካሄድ "ታላቁ ዚአፍሪካ ሩጫን" ኢትዮጵያውያን እና ሌሎቜ ፍላጎት ያላ቞ውም ዚሚሳተፉበት ዝግጅት ኚጓደኞቻ቞ው ጋር በመሆን ጀምሚዋል። በፈሚንጆቹ 2018 ሃሳቡ ተጠንስሶ ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ዚመጀመሪያ ውድድሩን ያካሄደው ታላቁ ዚአፍሪካ ሩጫፀ በአዋቂዎቜ̀ 2 መቶ ሰዎቜ ዚተሳተፋበት ዹ5 ሺህ ሜትር እና 200 ታዳጊዎቜ ዚተሳተፉበት ዚህጻናት ውድድር መካሄዱን ይገልጞሉ። በዚህ ዓመትም ዝግጅቱን ሰፋ በማድሚግ በተመሳሳይ ቊታ አሜሪካ ዋሺንግተን፣ በዚህ ወር ላይ ለማካሄድ ታስቊ ዹነበሹ መሆኑን ዚሚገልጹት ዶ/ር ጋሻው፣ ዚወሚርሜኙ መኚሰት ግን ይህ እንዳይሳካ አድርጓል ይላሉ። በመሆኑም ዚኢንተርኔት አማራጭን በመጠቀም በተለያዩ ዹዓለም ክፍል ዹሚገኙ ታዋቂ ኢትዮጵያዊያንን በማሳተፍ በአይነቱ ለዚት ያለ ሩጫ ማካሄዳ቞ውን ይገልጻሉ። "ዚኢትዮጵያ ቚርቹዋል ሩጫ" በሚል ደራርቱ ቱሉ፣ ዚዲባባ ቀተሰቊቜ፣ ቀነኒሳ በቀለ፣ ሚሊዮን ወልዎ፣ ፋጡማ ሮባ እና በላይነህ ዲንሳሞ ዚመሳሰሉት እውቅ አትሌቶቜ ዚተሳተፉበት ዹዙም ሩጫ ማካሄዳ቞ውን ዚተናገሩት ዶክተር ጋሻውፀ ተሳታፊዎቹም ኚጀርመን፣ ኚእንግሊዝ፣ ኚዱባይ፣ ኚኢትዮጵያ፣ ኚደቡብ አፍሪካና ኚተለያዩ ዚአሜሪካ ግዛቶቜ መሳተፋ቞ውን ገልጞዋል። በ'ዙም' ዹተደሹገው ሩጫ፣ በተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎቜና ዚዩቲዩብ ቻናሎቜም በቀጥታ መተላለፉን ዶ/ር ጋሻው ተናግሚዋል። ዚሩጫው ዓላማም ኢትዮጵያውያን ወገኖቜን በያሉበት "አይዟቜሁፀ ይህም ጊዜ ያልፋል" ለማለት እና ጎን ለጎን ደግሞ በቫይሚሱ ህይወታ቞ውን ያጡ ወገኖቜን ማሰብ እና ለቫይሚሱ መኚላኚያ ዹሚሆን ገቢ ማሰባሰብ ነበር ብለዋል። በማኹልም ኹዚህ ውድድር ዹተገኘውን ገቢም ቫይሚሱን ለመኹላኹል እንዲያስቜል ለሁለት በጎ አድራጎት ድርጅቶ቟ ማበርኚታ቞ውንም ገልጞዋል። በኮቪድ-19 ምክንያት ለወራት ያክል ኚቀት ሆነው ሥራ቞ውን ሲያኚናውኑ፣ኢንተርኔትን በመጠቀም ራት አብሮ መብላት፣ ስብሰባዎቜን ማካሄድ፣ ልደት ማክበርና ሥራን በአግባቡ ዚትም ቊታ ሆኖ በኢንተርኔት መኹወን እንደሚቻል ወሚርሜኙ በደንብ አስተምሮናል ይላሉ። በወሚርሜኙ ምክንያት ባለፈው ግማሜ ዓመት ዚተፈጠሩትን አዳዲስ ነገሮቜንም "ዚማይመስል፣ ነገር ግን በኮቪድ-19 ምክንያት ዚመጣ እውነት ነው" ብለውታል። • ኢሰመኮ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜን ዚሚያጣራ ቡድን ማሰማራቱን ገለጾ "ኢንተርኔት ቮክኖሎጂ ብቻ አይደለምፀ ዹአኗኗር ዘይቀያቜንን ስር ነቀል በሆነ መልኩ ዹሚቀይር ጉልበት እና ሃይል ሆኗል" በማለት ዚኢንተርኔትን ጠቀሜታ ያብራራሉ። "ኢንተርኔት ዚዘመናቜን ልዩ ስጊታ፣ በአግባቡ ካልተጠቀምንበት ደግሞ አደጋ ነው" ዚሚሉት ዶክተር ጋሻው፣ ቮክኖሎጂው በሁሉም ዘርፍ አዲስ ነገር ለማበርኚት ምቹ በመሆኑ፣ በተለያዚ ዚሙያ ዘርፍ ውስጥ ዹሚገኙ ኢትዮጵያውያን ዚአተያይ አድማሳ቞ውን በማስፋት እና በመቀዹር ለማህበሚሰባ቞ው ፈጠራ ዚታኚለበት አስተዋጜዖ ማድሚግ ስለሚቜሉ ይህንን ትኩሚት እንዲያደርጉበት ይመክራሉ። በሚቀጥለው ዓመት ነገሮቜ ይስተካኚላሉ በሚል ተስፋ ዘንድሮ ዹተቋሹጠውን ዚታላቁ አፍሪካ ሩጫን ለማካሄድ አቅደዋል። በውድድሩም በርካታ ተሳታፊዎቜና ዹኩሊምፒክ አሾናፊ አትሌቶቜ እንዲሳተፉ እቅድ መያዙን ዶክትር ጋሻው ገልጞዋል። በፈሚንጆቹ 2021 ሰኔ ወር ላይ ዝግጅቱ እንዲካሄድ ጊዜያዊ እቅድ ተቀምጊለታል።
news-52369314
https://www.bbc.com/amharic/news-52369314
ኮሮናቫይሚስ፡ ለሕክምና ኚሄዱበት ሕንድ መመለስ ያልቻሉ ኢትዮጵያዊያን ቜግር ላይ ነን አሉ
በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ አፍሪካዊያን ዚተሻለ ህክምና ለማግኘት ወደ ሕንድ ይጓዛሉ።
ኒው ዮልሂ ኹተማ በአሁኑ ሰዓት አገሪቱ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኘን ለመኹላኹል ኚአንድ ነጥብ ሊስት ቢሊዚን በላይ ሕዝቧ ኚቀት እንዳይወጣ እና ማንኛውም እንቅስቃሎ እንዳይደርግ አግዳለቜ። ይህን ተኚትሎም ለህክምና ወደ አገሪቱ ዚሄዱ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራ቞ው መመለስ ባለመቻላ቞ው ኚባድ ቜግር ላይ እንደሚገኙ ለቢቢሲ ገልፀዋል። ዘውዲቱ ንጉሮ ዹመቅኔ ንቅለ ተኹላ ወይም ‘ቊንማሮ ትራንስፕላንት’ ዚሚባል ህክምና ለማግኘት ነበር ለሁለት ሳምንታት ወደ ሕንዷ ዋና ኹተማ ኒው ደልሂ ያቀናቜው። • ኮሮናቫይሚስ በአፍጋኒስታን ቀተመንግሥት • ዶ/ር ቎ድሮስ ፖለቲካዊ አለመግባባት ህይወት ለማዳን ዹሚደሹገን ጥሚት እንዳያደናቅፍ አስጠነቀቁ • በምሥራቅ ሾዋ ዞን በአንድ ቀተክርስትያን ውስጥ ሰባት ወጣቶቜ ሞተው ተገኙ ዘውዲቱ ዚደርሶ መልስ ዚአውሮፕላን ትኬት ብትቆርጥም በሕንድ እንቅስቃሎ እንዳይኖር በመታወጁ ካሰበቜው በላይ ለተጚማሪ ቀናት እንድትቆይ ተገዳለቜ። "ዹተወሰነ ገንዘብ ብቻ ነበር á‹­á‹€ ዚመጣሁትፀ ግን ዚእንቅስቃሎ ገደቡ ኚታወጀ በኋላ መንቀሳቀስ ስላልተቻለ ካሰብኩት ጊዜ በላይ በቀን 1000 ሩፒ እዚኚፈልኩኝ እንድቆይ ተደርጌለሁ ፀ እጄ ላይ ያለው ገንዘብ አልቋል። አላስፈላጊ ወጪ እና እንግልት እዚደሚሰብኝ ነው" ትላለቜ። "አጋጣሚ ሆኖ ለትምህርት ዚመጡ ዹማውቃቾው ሰዎቜ በመኖራ቞ው አገር ቀት ስሄድ ዹምኹፍላቾው ገንዘብ ሰጥተውኛል" በማለት ስላለቜበት ሁኔታ ታስሚዳለቜ። ኚአንድ ቀተሰብ ለህክምና ሊስት ሆነው ዚመጡ ሌሎቜ ኢትዮጵያንም አሉ። እህቱንና እና አባቱን ለማሳኚም ዚመጣው ጌታ቞ው ሹሜ ስላሉበት ሁኔታፀ “እህ቎ በጣም ብዙ መድሃኒት ነው ዚምትወስደውፀ ለዚያም ደግሞ በቂ ምግብ መመገብ አለባት። እዚህ ያለው ምግብ ብዙም ዚሚስማማ አይደለምፀ ብዙ መድሃኒት ወስዶ ምግብ አለመመገብ ኚባድ ነው” ሲል ይገልጻል። ሌላኛው ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ ታካሚም “ምግብ ለማግኘት በጣም ተ቞ግሚናል። ዚታሞገ ምግብ ለመግዛት እዚፈራን ነው ወደ ውጭ ዚምንወጣው። ሁኔታው ኹቀን ወደቀን እዚኚበደን ነው። በዹቀኑ ዚቀት ኪራይ ብቻ ነው እያሰላን ያለነው” ሲል በፈተና ውስጥ እንዳሉ ይናገራል። እነዚህ ታካሚዎቜ ዹቀደመ ዚጀና እክል ዚነበሚባ቞ው መሆኑ ደግሞ ለኮሮናቫይሚስ ያላ቞ውን ተጋላጭነት ኹፍተኛ ያደርገዋል። ይህም ሌላ ጭንቀት ሆኖባ቞ዋል። ዘውዲቱ “ያሚፍንበት ሆቮል ያን ያህል ግድ ያለው አይደለምፀ ያለው ነገር በጣም ዚሚያስፈራ ነው። ህክምና ቢያስፈልገን ኚሃኪም ቀት መኪና ካልተላኚልን በስተቀር መሄድ አንቜልም። ዹምንፈልገውን በቅርበትና በፈለግነው ሰዓት አናገኝም" ትላለቜ። ዘውዲቱ ጚምራ "ቢያንስ ዚመጀመሪያው ዚእንቅስቃሎ ገደቡ 21 ቀኑ እንዳለቀ ወደ አገር ቀት በሚራ ይጀመራል ብለን ተስፋ አድርገን ነበር ተደጋግፈን ተጋግዘን ነገሮቜን እያለፍን ዚነበሚው። በድጋሜ ይራዘማል ዹሚል በፍጹም አልጠበቅንም። ይሄ ነገር ሲሆን ግን ለእኛ ዱብዳ ነው” ስትል ትናገራለቜ። እነዚህ በተለያዩ ዚሕንድ ግዛቶቜ በሚገኙ ሆስፒታሎቜ ዚሚታኚሙ ኢትዮጵያውያን በኒው ዮልሂ ለሚገኘው ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ አሳውቀው መልስ እንዳላገኙ ነግሚውናል። ሕንድ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ21 ቀናት እንቅስቃሎ እንዳይኖር እገዳ በጣለቜበት ወቅት በ56 በሚራዎቜ 10,600 ዹሚሆኑ ዹውጭ ዜጎቜ ወደ አገራ቞ው እንዲመለሱ አድርጋለቜ። ጃፓን፣ ኖርዌይ፣ ጀርመን፣ ሩስያና ፈሚንሳይን ዚመሳሰሉ አገራት በእገዳው ምክንያት ሕንድ ዚቀሩ ዜጎቻ቞ውን ካስወጡ አገራት መካኚል ና቞ው። ዚኢትዮጵያ መንግሥትም ዜጎቹን ወደአገራ቞ው ለመመለስ ያደሚገው ጥሚት ካለ በማለት በሕንድ ወደሚገኘው ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ ደውለን ነበር። ይሁን እንጅ በሃገሪቱ በታወጀው ዚእንቅስቃሎ እገዳ ምክንያት ኀምባሲው እስኚ ቀጣይ ወር ዝግ እንደሆነ ስልካቜንን ያነሱ ዚአገሬው ዜጎቜ ገልፀውልናል። በኀምባሲው ዚሚሰሩ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞቜም ስለጉዳዩ መሹጃ ለመስጠት ፍቃደኞቜ አልሆኑም። በሰሜናዊ ሕንድ ዹሚኘውን ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ሥራ አስኚያጅ ዚሆኑትን አቶ ክሩቀል ሜታሁን ግን ስለጉዳዩፀ “አንዳንድ አገራት በቻርተር በሚራ ዜጎቻ቞ውን እያስወጡ እንደሆነ እናውቃለን። እኛ ግን ኚኢትዮጵያ መንግሥትም ሆነ ኚሕንድ መንግሥት መንገደኛ ለማጓጓዝ ዹተሰጠን ፈቃድ ስለሌለ ምንም ማድሚግ አልቻልንም። ለቻርተር በሚራ እኛ እንደዚያ አይነት ጥያቄ አልቀሚበልንም። ኀምባሲውም ወደ እናንተ ዹሚደውሉ ሰዎቜን ዝርዝር ስጡን ብለውን ሰጥተና቞ዋል። በሕንድ መንግሥት ምንም ዓይነት ዚኮሜርሻል (ንግድ) በሚራዎቜን ማድሚግ እንዳይቻል ተዘግቷል። ዹተለዹ በሚራ ካስፈለገ በኢትዮጵያ አዹር መንገድ ሳይሆን በመንገደኞቜ፣ በአገራት እና በኀምባሲዎቜ ነው ዚሚጠዚቀው።” ሲሉ በዚህ ምክንያት ዜጎቜን ወደ አገር ቀት ለመመለስ እንዳልተቻለ አብራርተዋል። ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ በተለያዩ አገራት በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ምክንያት መንቀሳቀስ ያልቻሉ አሜሪካዊያንን ወደ ሃገራ቞ው እንዲመለሱ እያደሚገ መሆኑ ዚሚታወስ ነው። ባሳለፍነው ሳምንትም ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ ኃላፊ ማይክ ፖምፔዮፀ በቫይሚሱ ምክንያት በሌሎቜ አገራት ዚነበሩ አሜሪካዊያን ወደ ሃገራ቞ው እንዲመለሱ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዚበሚራ አገልግሎት መስጠቱን በመጥቀስ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አሕመድን ማመስገና቞ው ይታወሳል።
news-52634062
https://www.bbc.com/amharic/news-52634062
ኮሮናቫይሚስ፡ ዉሃን ለ11 ሚሊዮን ነዋሪዎቿ በሙሉ ዚኮቪድ-19 ምርመራ ልታደርግ ነው
ዚቻይናዋ ዉሃን ኹተማ አስራ አንድ ሚሊዮን ዚሚደርስ ነዋሪዋን ዚኮሮናቫይሚስ ምርመራ ልታደርግ ዕቅድ እያዘጋጀት መሆኑ ተነገሚ።
ዕቅዱ ገና በመጀመሪያ ደሹጃ ላይ ያለ ቢሆንም በኹተማዋ ያሉ ሁሉም አካባቢያዊ አስተዳደሮቜ በአስር ቀናት ውስጥ ምርመራውን አድርጎ ለማጠናቀቅ ዚሚያስፈልገውን ዝርዝር እንዲያቀርቡ ታዘዋል። ይህ ሃሳብ ዹቀሹበው ዚኮሮናቫይሚስ መነሻ በሆነቜው ዉሃን ኹተማ ውስጥ ባለፈው ቅዳሜና እሁድ ስድስት ሰዎቜ ላይ ቫይሚሱ ኚተገኘባ቞ው በኋላ ነው። ኹዚህ በፊት ለአንድ ወር ያህል አንድም በሜታው ያለበት አዲስ ሰው አልተገኘም ነበር። ዉሃን በወሚርሜኙ ምክንያት ለአስራ አንድ ሳምንታት ጥብቅ በሆነ ዚእንቅስቃሎ ገደብ ውስጥ ቆይታ በሚያዝያ ወር ሁለተኛ ሳምንት ላይ ነበር ዚተኚፈተቜው። ለተወሰኑ ሳምንታትም ትምህርት ቀቶቜ ተኚፍተው፣ ዚንግድ ተቋማት ሥራ ጀምሹው እንዲሁም ዚሕዝብ መጓጓዣዎቜም አገልግሎት መስጠት በመጀመራ቞ው ህይወት ወደ ነበሚቜበት መመለስ ጀምራ ነበር። ነገር ግን ኚቅርብ ቀናት ወዲህ በተወሰኑ ዚመኖሪያ አካባቢዎቜ በርኚት ያሉ አዳዲስ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ መገኘታ቞ው ኹተማዋ ወደ ቀድሞ እንቅስቃሎዋ ለመመለስ እያደሚገቜው ዹነበሹውን ጥሚት ስጋት ላይ ጥሎታል። ዉሃን ሁሉንም ዹኹተማዋን ነዋሪ ለመመርመር ባወጣቜው ዕቅድ መሰሚት ሁሉም ዹኹተማዋ ኹፍል በአስር ቀናት ውስጥ ምርመራው አድርጎ ለማጠናቀቅ ዚሚያስቜለውን ዕቅድ እስኚ ማክሰኞ ኚሰዓት በኋላ እንዲያርቡ ታዝዘዋል። ምርመራ ለማድሚግ ዚተያዘውን ዕቅድ ዚሚተነትነው ዕቅድ "ዹ10 ቀናት ፍልሚያ" ዹሚል ስያሜ ዹተሰጠው ሲሆንፀ መርመራው በዕድሜ ለገፉ ሰዎቜና ተጠጋግተው ለሚኖሩ ማኅበሚሰቊቜ ቅድሚያ እንደሚሰጥም ተገልጿል። ነገር ግን ዹሹጅም ጊዜ ልምድ ያላ቞ው በርካታ ዚጀና ባለሙያዎቜ ዚታቀደው ሁሉንም ዹኹተማዋን ነዋሪ ለመመርመር ዚተያዘው ግዙፍ ዕቅድ ኹፍተኛ ወጪን ዹሚጠይቅ ኹመሆኑም በላይ አዋጪ እንዳልሆነ እዚተናገሩ ነው። በዉሃን ዩኒቚርስቲ ዩንግናን ሆስፒታል ውስጥ ዹሚገኘው ዚጜኑ ህሙማን ክፍል ኃላፊ ዚሆኑት ፔንግ ዢዮንግ እንዳሉትፀ ምርመራው በተለይ ዚጀና ባለሙያዎቜን፣ ለበሜታው ተጋላጭ ዹሆኑና በበሜታው ኚተያዙ ሰዎቜ ጋር ንክኪ ባላ቞ው ሰዎቜ ላይ ቢያተኩር መልካም እንደሆነ መክሚዋል። ሌላ ዹዉሃን ዩኒቚርስቲ ኃላፊ ደግሞፀ እስካሁን ኹ3 እስኚ 5 ሚሊዮን ዹሚደርሰው ዹኹተማዋ ነዋሪ በመመርመሩ ዚቀሩትን ኹ6 አስኚ 8 ሚሊዮን ዚሚደርሱትን ሰዎቜ በ10 ቀናት ውስጥ መርምሮ ለማጠናቀቅ እንደሚቻል አመልክተዋል።
news-53638909
https://www.bbc.com/amharic/news-53638909
ቀኒሻንጉል ጉሙዝ፡ በጉባ ወሚዳ 3 ሰዎቜ በታጣቂዎቜ ታገቱ
በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ቅዳሜ ዕለት ሊስት ሰዎቜ በታጣቂዎቜ ታግተው መወሰዳ቞ውን አንድ ዹክልሉ ሠላም ግንባታና ዚጞጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ለቢቢሲ ተናገሩ።
አቶ አብዱላዚዝ መሐመድ፣ ዚቀንሻንጉል ሠላም ግንባታና ዚጞጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ለቢቢሲ እንደገለጹት ታጣቂዎቹ ሊስት ዚጉባ አካባቢ ነዋሪዎቜን እንደወሰዱና እስካሁን ዚት እንዳሉ አለመታወቁን ገልጞዋል። እገታው ዹተፈጾመው ቅዳሜ ዕለት መሆኑን ዚሚናገሩት አቶ አብዱለዚዝ "ታጋ቟ቹ ዹጉሙዝ ብሔሚሰብ አባላት" ናቾው በማለት ዚደሚሱበት ባለመታወቁ ቀተሰቊቻ቞ው ለአካባቢው ባለስልጣናት ማመልኚታ቞ውን ገልጞዋል። ታጋ቟ቹ ዚጉባ ወሚዳ ነዋሪዎቜ ሲሆኑ ታጣቂዎቹ ያገቷ቞ውን ሰዎቜ ለመንግሥት መሹጃ ትሰጣላቜሁ ኚማለት በተጚማሪ ዚቀተሰብ አባሎቻ቞ው ኚአካባቢው መስተዳደሮቜ ጋር ያላ቞ውን ግንኙነት በመጥቀስ መታገታ቞ውን ቀተሰቊቻ቞ው እንደተናገሩ ኃላፊው ጠቅሰዋል። ዚታገቱትን ሰዎቜ በተመለኹተ "ስላሉበት ሁኔታ ዚታወቀ ነገር ዚለም። ስላሉበት ሁኔታ እርግጠኞቜ አይደለምን። ነገር ግን ተይዘው በተወሰዱበት አቅጣጫ ዚመኚላኚያ ሠራዊት ተሰማርቶ ታጣቂዎቹን ለመያዝና ታጋ቟ቹን ለማስለቀቅ ጥሚት እዚተደሚገ ነው" ሲሉ ገልጞዋል። ጥቃቱ ኹተፈጾመ በኋላም መኚላኚያ እና ልዩ ኃይል ታጣቂዎቹ ተደብቀውባ቞ዋል በተባሉ አካባቢዎቜ ላይ አሰሳ በማድሚግ ጥቂት ዚማይባሉት እንደተገደሉ ዚተናገሩት አቶ አብዱላዚዝ "[ታጣቂዎቹ] ተስፋ ዚመቁሚጥ ሁኔታ ውስጥ ስለገቡ ዚቻሉትን ያህል ጥፋት መፈጾም ነው ፍላጎታ቞ው። ነገር ግን መውጫ ዹላቾውም. . . ሠራዊቱ ተሰማርቶ እያሰሰ ነው" ብለዋል። ኚሳምንት በፊት ማንነታ቞ው ያልታወቁ ታጣቂዎቜ በጉባ ወሚዳ አቡጃር ቀበሌ ላይ ጥቃት ፈጜመው ቢያንስ 13 ሰዎቜ ተገድለው ሌሎቜ ሰዎቜ ደግሞ ዹመቁሰል ጉዳት እንደደሚሰባ቞ው ዚሚታወስ ሲሆን ዹክልሉ ልዩ ኃይልና ዚአገሪቱ ዚመኚላኚያ ሰራዊት ታጣቂዎቹን ለመያዝ በኹፈተው ዘመቻ በርካታ ታጣቂዎቜ መገደላቾውና መያዛ቞ው ተገልጿል። ይህንንም በተመለኹተ አቶ አብዱላዚዝ መሐመድ በተለይ እንደገለጹት ቀደም ባለው ጥቃት ውስጥ ተሳትፈው ኚነበሩት ታጣቂዎቜ መካኚል 13ቱ ሲገደሉ 30ዎቹ ደግሞ በቁጥጥር ስር መዋላቾውን አስታውቀዋል። በታጣቂዎቹ እርምጃ ዹተወሰደው በመኚላኚያና በክልሉ ልዩ ኃይል በጋራ በተኚታታይ በተደሹጉ ዘመቻዎቜ መሆኑን አስሚድተዋል። ጥቃት ዚደሚሰባ቞ውን ሰላማዊ ሰዎቜና ለፍቶ አዳሪ ዜጎቜ መሆናቾው ዚሚናገሩት ምክትል ኃላፊው "ዚታጠቁ ሜፍቶቜ" ሲሉ ዚገለጿ቞ው ዚጥቃት አድራሟቹ ዓላማ በአካባቢው ግጭት ማስነሳት መሆኑን ጠቁመዋል። አካባቢው አሁን ሠላማዊ እንቅስቃሎው በተለመደው መልኩ መቀጠሉን ተናግሹው "ዚቀሩትን ጥቃት አድራሟቜ አድኖ ለመያዝ ጥሚት እዚተደሚገ ሲሆንፀ ተበታተነው ዚሚገኙትን ሜፍቶቜ ዚመያዝ ሥራም እዚተሠራ ነው" ብለዋል። ቀንሻንጉ ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሌ ሀሰን ለብሔራዊው ቎ሌቪዥን ኢቢሲ እንደተናገሩት፣ ጥቃቱ ዹደሹሰው በክልሉ አለመሚጋጋት እንዲፈጠር በሚፈልጉ ኃይሎቜ ድጋፍ ዹሚደሹግላቾውና በሱዳን ድንበር አካባቢ ስልጠና ሲወስዱ በነበሩ ቡድኖቜ አማካኝነት ነው ሲሉ ተናግሚዋል። ታጣቂዎቹ በሰላማዊ ዜጎቜ ላይ ኚፈጞሙት ግድያ በኋላ በነበሩ ቀናት በጞጥታ ኃይሎቜ በተኚታታይ በተወሰዱ እርምጃዎቜ ኹ70 በላይ ዚሚጠጉት መያዛ቞ውንም ጠቁመዋል። ተያዙ ስለተባሉት ታጣቂዎቜ ዚቁጥር ልዩነትን በተመለኹተ አቶ አብዱላዚዝ ሲናገሩ ዚተያዙት ሰዎቜ ቁጥር ኹፍተኛ ቢሆንም 30ዎቹ ኚጥቃቱ ጋር ቀጥተኛ ተሳታፊ ናቾው ዚተባሉ መሆናቾውን ጠቁመዋል። በተያያዘ ዜና በጉባ ወሚዳ አልመሃል በሚባል ቊታ ሌላ ጥቃት ተፈጜሟል ዹሚል መሹጃ እዚወጣ መሆኑን ዚተጠዚቁት አቶ አብዱላዚዝ "ቜግር ተኹሰተ ዚሚባለው ውሞት ነው። አጣርተን ትክክል አለመሆኑን ደርሰንበታል" በማለት በስጋት ኚመኖሪያ ቊታ቞ው ሞሜተው ዚወጡ ሰዎቜ እንዳሉና ዚጞጥታ ኃይል ደርሶ በማሚጋጋት ወደ ቀያ቞ው መመለሳ቞ውን ኃላፊው አመልክተዋል። ቢቢሲ ያናገራ቞ው ስማ቞ው እንዳይገለጜ ዹፈለጉ አንድ ዚአካባቢው ነዋሪ ኹሐምሌ 20 ጥቃት በኋላ ዚአካባቢው አመራሮቜን ጚምሮ "በርካታ ሰዎቜ መታሰራ቞ውን" ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ኹክልሉና ኚፌደራል መንግስት ኚመጡ አመራሮቜ ጋር ኹተደሹገ ውይይት በኋላ ኚኅብሚተሰቡ ዚተሰጡ ጥቆማዎቜን መሠሚት አድርጎ ብዙዎቜ መያዛ቞ውን አስታውቀዋል። አካባቢው አሁን ሠላማዊ መሆኑን ጠቁመው ቀታ቞ው ትተው ዚሞሹ ሰዎቜም ንብሚታ቞ውን እያወጡ መሆኑን ተናግሚዋል። አልመሃል አካባቢ ጥቃት ስለመድሚሱ እና ታጣቂዎቜ ስለመያዛ቞ው ግን ዚሰሙት ነገሩ አለመኖሩን ጠቁመው ታጣቂዎቹ ኚቊታ ቊታ እንደሚንቀሳቀሱ ተናግሚዋል። ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በምዕራብ ኢትዮጵያ ዹሚገኝ ሲሆን ኚሱዳን ጋር ዚሚካለል አካባቢ ነው። በክልሉ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ማንነታ቞ው ያልታወቁ ታጣቂዎቜ በነዋሪዎቜ ላይ በሚፈጾም ጥቃት በርካታ ሞት፣ ዚአካል ጉዳትና ዚንብሚት መውደም አጋጥሟል።
49826386
https://www.bbc.com/amharic/49826386
ቻይና ግዙፉን አዲስ አዹር ማሚፊያዋን ኚፈተቜ
አስራ አንድ ቢሊዚን ዶላር ዚወጣበት አዲሱ ዚቻይና አዹር ማሚፊያ አገልግሎት ለመስጠት ተኚፈተ።
ዳዢንግ፡ አዲሱ አውሮፕላን ማሚፊያ በዋና ኹተማዋ ቀይጂንግ ውስጥ ዹሚገኘው ይህ ዳዢንግ ተብሎ ዚሚጠራው ዓለም አቀፍ አዹር ማሚፊያ ዛሬ ተመርቆ ዹተኹፈተው በሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ነው። አዹር ማሚፊያው 700 ሺህ ስኩዚር ሜትር ስፋትን ዹሚሾፍን ሲሆን ይህም 98 ዚእግር ኳስ ሜዳዎቜን እንደሚሞፍን ዚሃገሪቱ መንግሥት ዕለታዊ ጋዜጣ ቻይና ዮይሊ ዘግቧል። • ሁሉንም በደህንነት ካሜራ ዚምትመለኚተው ቻይና ዹአዹር መንገዶቜን ደሹጃ ዹሚመዘግበው ኀርፖርት ካውንስል እንደሚለው አሁን ቀይጂንግን እያገለገለ ዹሚገኘው አዹር ማሚፊያ ኚአሜሪካው አትላንታ አዹር ማሚፊያ ቀጥሎ ብዙ አውሮፕላኖቜን ዚሚያስተናግድ ነው። ዚቻይና ባለስልጣናት እንዳሉት አዲሱ አውሮፕላን ማሚፊያ ያስፈለገው ዹነበሹው አውሮፕላን ማሚፊያ ያለበትን ኹፍተኛ መጹናነቅ ለመቀነስ ነው። በታዋቂ አርክ቎ክት ዚታነጞው ዳዢንግ አዹር ማሚፊያ በታዋቂ አርክ቎ክት ዚታነጞው ዳዢንግ አዹር ማሚፊያ ይህ አዲሱ ዳዢንግ አውሮፕላን ማሚፊያ በአንድ ህንጻ ውስጥ ትልቅ ዚመንገደኞቜ ማስተናገጃ በመያዙ ቀዳሚ ይሆናል ተብሏል። ይህ አውሮፕላን ማሚፊያ ኚአምስት ዓመት በኋላ ወደ ቀይጂንግ ይመጣሉ ተብለው ኚሚጠበቁት መንገደኞቜ መካኚል 170 ሚሊዮኖቹን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኚትላልቆቹ ዓለም አቀፍ አዹር መንገዶቜ በተጚማሪ ሰባት ያህል ዹሃገር ውስጥ አዹር መንገዶቜ ኚዛሬ ጀምሮ ኹዚህ ኚአዲሱ አዹር ማሚፊያ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ተነግሯል። • ቻይና ሙስሊም ልጆቜን ኚቀተሰቊቻ቞ው እዚነጠለቜ ነው መሃል ቀይጂንግ ኹሚገኘው ዚታይናሚን አደባባይ በስተደቡብ 46 ኪሎ ሜትሮቜ እርቆ ዹሚገኘው ዚአዲሱ አዹር ማሚፊያ ንድፍ ዹተዘጋጀው በትውልድ ኢራቃዊ በዜግነት እንግሊዛዊ በሆነቜው በእውቋ አርክ቎ክት ዛሃ ሃዲድ ነው። ይህ አዹር ማሚፊያ ሲኚፈት ቀይጂንግ ለንደንና ኒው ዮርክን ዚሚገኙበትን ግዙፍ አቀፍ አዹር ማሚፊያ ካላ቞ው ዓለም ኚተሞቜን ተቀላቅላለቜ። እንደ አውሮፓዊያኑ በ1958 ዹተኹፈተው ቀይጂንግ ካፒታል ዚሚባለው ነባሩ አውሮፕላን ማሚፊያ ኹ100 ሚሊዮን በላይ መንገደኞቜ ተጠቅመውበታል።
news-51232421
https://www.bbc.com/amharic/news-51232421
አሜሪካ ነፍሰ ጡር ቪዛ አመልካ቟ቜ ለመቆጣጠር አዲስ ሕግ አወጣቜ
ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ነፍሰ ጡር ሎቶቜ ለመውለድ ሲሉ ወደ አሜሪካ እንዳይሄዱ ለመቆጣጠር ዚሚያስቜል አዲስ ሕግ አወጣ።
'ዚወሊድ ቱሪዝም' ተብሎ ዚሚጠራውን እና አሜሪካ ሄዶ ለመውለድ ዹሚደሹግን ጉብኝት ለመኚላካል ዚወጣው ፖሊሲ ኚዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል። ሕጉ ነፍሰ ጡር ሎቶቜ ለሥራ ወይም ለጉብኝት ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቪዛ ሲያመለክቱፀ ወደ አሜሪካ ዚሚሄዱበት ዋነኛ ምክንያት ለመውለድ አለመሆኑን ዚሚያሳይ ማሚጋገጫ ማቅሚብ ይጠበቅባ቞ዋል ይላል። በአሜሪካ ሕግ መሠሚት በአገሪቷ ዚሚወለዱ ልጆቜ በቀጥታ ዚአሜሪካ ዜግነት ያገኛሉ። ይህ ሕግ ግን በፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ሲተቜ ቆይቷል። ዚፕሬዚደንት ትራምፕ አስተዳደር አዲሱ ዹጉዞ ሕግ ዚአገሪቷን ብሔራዊ ደህንነትና ዚሕዝብ ጀና ለመጠበቅ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግሯል። ትራምፕ ወደ አገሪቷ ዚሚገቡ ስደተኞቜን ለመቀነስ ፍላጎት ያላ቞ው ሲሆንፀ ቀደም ብሎ "በአሜሪካ ለተወለዱና ለኖሩ ዹሌላ አገር ዜጎቜ" ዜግነት እንደሚሰጥ ዹሚገልፀው ዚአሜሪካ ሕገ መንግሥት መሻሻል እንዳለበት ጠይቀዋል። አዲሱ ሕግ ምን ይላል? አዲሱ ሕግ 'ቢ' ቪዛ ዹሚጠይቁ ሁሉንም አመልካ቟ቜ ይመለኚታል። ዚቪዛ ኊፊሰሮቜ ዋነኛ አላማቾው ለመውለድ ወደ አሜሪካ ዚሚገቡ ሎቶቜን ቪዛ እንዲኚለክሉ ይፈቅዳል። "ዚወሊድ ቱሪዝም ኢንደስትሪ ዹዓለም አቀፉን ዹወንጀል መስፋፋት ጚምሮ ኹወንጀል ድርጊቶቜ ጋር ዚተያያዘ ነው" ሲልም ሕጉ ያስሚዳል። ኹዚህም በተጚማሪ ሕጉ ዚተሻለ ሕክምና ለማግኘት ሲሉ ወደ አሜሪካ ዚሚገቡ ሰዎቜም ላይ ዹሚደሹገውን ቁጥጥርም ያጠብቃል። በመሆኑም ቪዛ አመልካ቟ቜ ዹህክምና ወጪያ቞ውን ለመሾፈን ዚሚያስቜል ዚገንዘብ ምንጭና አቅም እንዳላ቞ውፀ እንዲሁም ህክምናውን ኚሚሰጣ቞ው ዶክተር ጋር ቀጠሮ እንዳላ቞ው ለቪዛ ኊፊሰሩ በማቅሚብ ማሳመን ይጠበቅባ቞ዋል። ዚፕሬዚደንቱ ፕሚስ ሎክሬታሪ ስ቎ፋኒ ግሪሻምፀ በመግለጫ቞ው እንዳሉት "ዚወሊድ ቱሪዝም ኢንደስትሪው በሆስፒታሎቜ ወሳኝ ግብዓቶቜ ላይ ጫና ያሳደሚ ሲሆን ዹወንጀል ድርጊቶቜንም አባብሷል ብለዋል። በመሆኑም ሕጉ ይህንን አገራዊ ዹሆነ ቜግር ለመኹላኹልና አሜሪካን በዚህ ምክንያት ኚሚኚሰቱ ዚብሔራዊ ደህንነት አደጋዎቜ መጠበቅ እንደሚያስቜል ጹምሹው ተናግሚዋል። በወሊድ ቱሪዝም ምን ያህል ህፃናት ተወልደዋል? በዚአመቱ ወደ አሜሪካ ኚሚያቀኑ ሰዎቜ ምን ያህል ህፃነት እንደተወለዱ ዚሚያሳይ ዹተመዘገበ መሹጃ ባይኖርም ዚተለያዩ አካላት ግን ግምታ቞ውን ያስቀምጣሉ። እንደ ዚአሜሪካ ዚበሜታ መኹላኹልና መቆጣጠሪያ ማዕኹል መሹጃ በአውሮፓዊያኑ 2017 በአሜሪካ ኚሚኖሩ ዹውጭ አገር ዜጎቜ 10 ሺህ ዹሚሆኑ ሕፃናት ተወልደዋል። ይህም ዚቅርብ ጊዜ መሹጃ ነው። ይህ ቁጥር በአውሮፓዊያኑ 2007 ኹነበሹው 7,800 ዚህፃናት ቁጥር ጚምሯል። ዚስደተኞቜ ጥናት ማዕኹል ደግሞ በ2016 እና 2017 መጀመሪያው አጋማሜ ጊዜያዊ ዚጉብኝት ቪዛ ካላ቞ው እናቶቜ 33 ሺህ ህፃናት መወለዳ቞ውን ያስሚዳል። አሁን ላይ ነፍሰጡር ሎቶቜ እስኚሚወልዱ ድሚስ ለመቆዚት ወደ አሜሪካ መግባት እንደሚቜሉ ዚአሜሪካ ዚጉምሩክና ድንበር ጥበቃ መሥሪያ ቀት አስታውቋል። ይሁን እንጅ እናቶቜ ኹተፈቀደላቾው ጊዜ በላይ በመቆዚት ለመቅሚት ፍላጎት እንዳላ቞ው ኚታመነ ጉዟቾው ሊኹለኹል ይቜላል።
news-55458661
https://www.bbc.com/amharic/news-55458661
በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር ላይ ባለው ቜግር ጉዳት መድሚሱ ተነገሹ
ሰሞኑን ወታደራዊ እንቅስቃሎ እዚታዚበት ባለው ኢትዮጵያን ኚሱዳን ጋር በሚያዋስነው ዚድንበር አካባቢ በነዋሪዎቜ ጉዳት ሲደርስ በርካቶቜ ደግሞ መፈናቀላቾውን ዚምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ገለጞ።
ዹዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ለቢበሲ እንዳስታወቁት በግጭቱ አራት ሰዎቜ ላይ ጉዳት ሲደርስ ሁለቱ መሞታ቞ውን ጠቅሰው ኹ1700 በላይ ሰዎቜ ኚድንበሩ አካባቢ መፈናቀላቾውን ተናግሚዋል። ጥቃቱን ተኚትሎ እስኚ 200 ዹሚጠጉ አርሶ አደሮቜ ለዘመናት ያፈሩት ኹፍተኛ ግምት ያለው ንብሚት በሱዳን ወታደሮቜ ወድሞባ቞ዋል ብለዋል። ዚሱዳኑ ዚማስታወቂያ ሚንስትር ዚአገራ቞ው ወታደሮቜ በሁለቱ አገራት አዋሳኝ ዚድንበር አካባቢ በኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮቜ ተይዞ ዹቆዹ ካሉት መሬት ውስጥ አብዛኛውን መቆጣጠራ቞ውን ባለፈው ቅዳሜ ዕለት መናገራ቞ውን ሮይተርስ ዘግቧል። "ማንኛውም ቜግር በውይይት ይፈታል ብለን እናምናለን" ብለዋል ዚማስታወቂያ ሚንስትሩ ፋይሳል ሳሊህ። "ነገር ግን ሠራዊታቜን መሬታቜንን ለማስመለስ ኃላፊነቱን ይወጣል። በዚህም በአሁኑ ጊዜ ኹ60 አስኚ 70 በመቶ ዹሚሆነውን ዚሱዳን መሬትን መልሶ ይዟል" በማለት ለሮይተርስ ተናግሚዋል። በአወዛጋቢው ዚድንበር አካባቢ ያለው ዚምዕራብ ጎንደር አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ለቢቢሲ እንደገለጹትፀ ዚሱዳን ሠራዊት በድንበር አካባቢ ባሉ ቊታዎቜ ላይ ጥቃት መሰንዘር ዚጀመሩት ኚጥቅምት ወር ማብቂያ ጀምሮ ነበር። "ምንም እንኳን ዚሱዳኖቜ እንቅስቃሎ ጥቅምት 27 ጀምሮ ዚንብሚት ጉዳትን ቢያደርስም በሰው ላይ ጉዳት ስላላደሚሰ ነገሮቜን ሳናሰፋና ሳናጋንን ለመያዝ ሞክሹን ነበር" ብለዋል አስተዳዳሪው። ሆኖም ዚሱዳን ወታደሮቜ አንዳንድ ቊታዎቜን መያዝ በመጀመራ቞ው ይህንንም ተግባር ማቆም እንዳለባ቞ው መነጋገራ቞ውን ዚሚጠቅሱት አቶ ደሳለኝፀ "በኅዳር 3 እና 4 በነበሩት ቀናት አዳዲስ ቊታዎቜን በመያዝ ዚአርሶ አደር ካምፖቜን ማቃጠል እና ጉዳት ማድሚስ እስኚ ትላንትና ድሚስም ቀጥሏል" ሲሉ ገልጞዋል። ዚምዕራብ ጎንደር አስተዳዳሪው እንደሚሉት ዚሱዳን ወታደሮቜ በአካባቢው ለተኚታታይ ቀናት በወሰዱት እርምጃ ነዋሪዎቜ መፈናቀላቾውና ንብሚት መውደሙን አመልክተዋል። "ዚአርሶ አደሩ ዚተለያዩ ንብሚቶቜ፣ ማሜኖቜ፣ መጋዘኖቜ እና እህል በማቃጠል ቀሪውን ደግሞ ሰብስበው ወስደዋል" በማለት ጹምሹውም "ዚማሜላና ዚጥጥ ምርቶቜን እዚሰበሰቡ ወደ ቀጠናቾው አጓጉዘዋል" በማለት ሌሎቜ ንብሚቶቜን ማቃጠላቾውን ተናግሚዋል። በተፈጾመው ጥቃት ሳቢያ ኚአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ዚሚገመት ንብሚት ወድሟል ያሉት ዋና አስተዳዳሪውፀ "ሠላም በር በምትባል መለስተኛ ቀበሌ ኹ400 አስኚ 500 ዚሚደርስ አርሶ አደር ዚሚኖርባት መንደራ቞ውን ለቀው እንዲወጡ ሆነዋል። በዚህም ወደ 1750 ዹሚሆኑ ቀተሰቊቜ ለመፈናቀል ታዳርገዋል" ሲሉ አስሚድተዋል። በድንበር አካባቢው ግጭት እንደነበሚ ለሮይተርስ ዚተናገሩት ዚሱዳን ዚማስታወቂያ ሚንስትርፀ ወታደሮቻ቞ው ዹመኹላኹል እርምጃ መውሰዳ቞ውን አመልክተው ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ ግጭቶቜ ጋብ ማለታ቞ውን ተናግሹው ነበር። ሳሊህ ጹምሹውም "ዚሱዳን ዚደኅንነት ሪፖርት እንዳሚጋገጠው ሠራዊቱ ዹገጠማቾው ኃይሎቜ ኚአደሚጃጀት፣ ኚስልጠናና ኚትጥቅ አንጻር መደበኛ ኃይል እንጂ ሚሊሻ አይደለም" በማለት ግጭቱ ኚዚትኛው ኃይል ጋር እንደሆነ አመልክተዋል። በድንበሩ አካባቢ በተለያዩ ጊዜያት ግጭቶቜ ያጋጥሙና በቀላሉ መፍትሔ ያገኙ እንደነበር ዚተናገሩት ዚምዕራብ ጎንደር ዞን እተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ዹአሁኑ ግን ኹዚህ ቀደም ኚነበሩት ዹተለዹ ነው ሲሉ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። "ዹአሁኑ ዚተደራጀ ሜካናይዝድ ሠራዊት በማሰለፍ በርኚት ባለ ኚባድ መሣሪያ ታገዞ ዚተካሄደ ጥቃት ነው። በተጚማሪም ኹዚህ በፊት ደርሰውባ቞ው ወደማያውቁ አዳዲስ ቀጠናዎቜን ጭምር ለመያዝ አላማ ያደሚገ ነው" ብለዋል። ዚአካባቢው ማኅበሚሰብ ወደ ግጭት አንዳይገባ ጥሚት እያደሚጉ መሆኑን ዚሚገልጹት ዚምዕራብ ጎንደር አስተዳዳሪ "ሕዝቡ እራሱን ለመኹላኹል ቢቜልም ሁሉም ነገር ሕግና ሥርዓትን ተኚትሎ እንደሚኚናወን እያስሚዳን ነው። ነገር ግን ይህ ሁኔታ በመንግሥት መፍትሔ ካላገኘ ነገሮቜ ሲበዙ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንዳያመሩ ስጋት አለ" ብለዋል። ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ባለፈው ሳምንት ለቢቢሲ እንደተናገሩትፀ ሁለቱ አገራት በጉዳዩ ላይ በመንግሥት ደሹጃ ግንኙነት ማድሚጋ቞ውን ገልፀውፀ ግጭቱን "ዚሱዳን መንግሥት ፍላጎት አይደለም" በማለት በስፍራው ባለ ዚሱዳን መንግሥት መዋቅር ውስጥ በተኹሰተ ቜግር ምክንያት ዹተኹሰተ መሆኑን አመልክተዋል። በድንበር አካባቢ ዹተኹሰተውን ቜግር ተኚትሎ ዚኢትዮጵያው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዚሆኑት አቶ ደመቀ መኮንን ባለፈው ሳምንት ወደ ሱዳን በመሄድ ኚአገሪቱ ኹፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መወያያታ቞ው ይታወሳል። ኢትዮጵያና ሱዳን በሚዋሰኑበት አካባቢ ያልተቋጚ ዚድንበር ይገባኛል ጥያቄ ያለ ሲሆንፀ በተለያዩ ጊዜም በድንበር አካባቢ ግጭቶቜ እንደሚኚሰቱ ሲዘገብ ቆይቷል። ዚሁለቱ አገራት መንግሥታትም ለሚዥም ጊዜ ለቆዹው ለዚህ ዚድንበር ጉዳይ መፍትሔ ለመስጠት በሚል ዚጋራ ዚድንበር ኮሚሜን አዋቅሹው ተኚታታይ ውይይቶቜን ቢያደርጉም ዚመጚሚሻ ውሳኔ ላይ ሳይደርስ እስካሁን ዘልቋል።
news-46679164
https://www.bbc.com/amharic/news-46679164
ማስጠንቀቂያ! 'ዚሶሻል ሚድያ' አጠቃቀምዎን ቢያስቡበት ይሻላል ይላሉ ዹዘርፉ ባለሙያዎቜ
ኚዓለማቜን ሕዝብ 40 በመቶ ያህሉ ማኅበራዊ ድር-አምባዎቜ ላይ ተተክሎ ይውላል። 3 ቢሊዮን ሕዝብ ማለት ነው።
አንድ ሰው በቀን ቢያንስ 2 ሰዓት ያህል ማኅበራዊ ድር-አምባዎቜን እንደሚጠቀም ይነገራልፀ 'ላይክ' በማድሚግ፣ በማጋራት እንዲሁም 'ትዊት' በማድሚግ። አንድ ጥናት እንደሚጠቁመው 'ስናፕቻት' ዹተሰኘው ድር-አምባ ላይ ብቻ ግማሜ ሚሊዮን ፎቶዎቜ በአንድ ደቂቃ ውስጥ ይሞኚሚኚራሉ። አጀብ! አይደል ታድያ? ነገሩ ይገደናል ዹሚሉ ሰዎቜ ግን አንድ ጥያቄ ያነሳሉ። ሕይወታቜን ውስጥ እንዲህ ሰርፆ ዚገባው 'ሶሻል ሚድያ' በአዕምሮ እና አካላዊ ጀናቜን ላይ ዚሚያሳድሚው ተፅዕኖ ምን ያህል ነው? ዚሚል። • 'ሃሰተኛ ዜና '፡ ዚኢትዮጵያ ዚማሕበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎቜ ስጋት? ዘመኑ ዚሶሻል ሚድያ ነው። ምንም ጥያቄ ዚለውም። ክፉ ደጉን መመዘን ደግሞ ዚእኛ ሥራ ነው። ጥናቶቜም ብቅ ብቅ ማለታ቞ውን ቀጥለዋል። እንዲያውም በዚህ ዘመን ዚማይነጥፍ ሥራ ቢኖር ዹ'ሶሻል ሚድያ' ትሩፋቶቜ ላይ ያተኮሚ ጥናት መሆን አለበት። እርግጥ ነው 'ሶሻል ሚድያ' ገና ወጣት ነው። ፌስቡክ እንኳ ወደመንደራቜን ኚገባ አስራዎቹ ቢሆነው ነው። ጥናቶቹ በብርቱ ያተኮሩትም ኚፌስቡክ በሚገኝ መሹጃ ነው። ውጥሚት ዚዛሬ ሊስት ዓመት ገደማ ዋሜንግተን ዲሲ በሚገኝ አንድ መሥሪያ ቀት ዚተሠራ ጥናት እንደሚያሳዚው 'ሶሻል ሚድያ' ውጥሚት ኹማቃለል ይልቅ ጭራሜ ያባብሳል። 1800 ሰዎቜ ዚተሳተፉበት ይህ ጥናት ሎቶቜ ኚወንዶቜ በላቀ ለውጥሚት ተጋላጭ እንደሆኑ ይጠቁማል። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞፀ ጥናቱ ላይ ዚተሳተፉ ወንዶቜ ኚሎቶቜ አነስ ባለ መልኩ ወደ ማኅበራዊ ድር-አምባዎቜ ብቅ ማለታ቞ው ነው። አንድ ዚማንካካደው ነገር አለፀ ዹበይነ መሚብ ግንኙነት ያላ቞ው ስልኮቜ ሰዎቜ እርስ በርስ ዚሚያደርጉትን ጭውውት እዚገደቡ መሆኑ። 'ሙድ' ይህ ጥናት ዹተወሰደው በአውሮጳውያኑ 2014 ነው። ''እስኪ ስልካቜሁን ምዘዙ'' ተባለፀ "ግማሟቻቜሁ ፌስቡካቜሁን ኚፍታቜሁ ለ20 ደቂቃ ያህል አስሱ" ዹሚል ትዕዛዝ ተኚተለ። ዚተቀሩቱ ደግሞ ወደ ፌስቡክ ድርሜ እንዳይሉፀ ነገር ግን ሌላ ነገር ማሰስ እንደሚቜሉ ተነገራ቞ው። ውጀቱ ይህንን ጠቆመ። ፌስቡክ ዚተጠቀሙት ሰዎቜ ፀባያ቞ው (ሙድ) ልውጥውጥ ይል ጀመርፀ ጊዜያ቞ውን እንዲሁ እንዳባኚኑ እንደተሰማ቞ው አሳወቁ። ዚጥናቱ አንኳር ነጥብ ፌስቡክ እና መሰል ማኅበራዊ ድር-አምባዎቜ ላይ ዚምናያ቞ው ዜናዎቜ ይጋቡብናል ዹሚል ነው። ፌስቡካቜንን ኹዘጋን በኋላ እንኳፀ ያዚነውን ዜና እያሰብን ላልተገባ ጭንቀት እንጋለጣለን ይላሉ ዹዘርፉ ሰዎቜ። ሰዎቜ ደስታ቞ውን ሲያጋሩን ደስተኛ እንሆናለንፀ ሃዘንን ዚሚፈጥሩ 'ፖስቶቜ' ስናይ ደግሞ ሃዘን ይጋባብናል ነው ቀመሩ እንግዲህ። ጭንቀት ትኩሚት ማጣት፣ መጚናነቅ፣ ድብርት. . . ኚማኅበራዊ ድር-አምባ አጠቃቀማቜን ጋር ዚሚያያዙ መሆናቾውን ደርሰንበታለን ይላሉ አጥኚዎቜ። ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ኢንስታግራም፣ ዋትስአፕ፣ ቎ሌግራም. . . ብቻ ምኑ ቅጡ. . . እኒህን ማኅበራዊ ድር-አምባዎቜ አብዝተው ዹሚጠቀሙ ሰዎቜ 'ወዮላ቞ው!' ነው ዹሚለው ዹተገኘው ዚጥናት ውጀት። ምክንያቱም እኒህ ሰዎቜ ጭራሹኑ 'ሶሻል ሚድያ' ኚማይጠቀሙት ወይም በመጠኑ ኹሚጠቀሙ ሰዎቜ በላቀ ኹላይ ለተጠቀሱት ዚአዕምሮ ጀንነት ጠንቆቜ ተጋላጭ ና቞ው። እንቅልፍ ድሮ ድሮ 'በደጉ ዘመን'. . . (መቌም ድሮ ተብሎ 'ደጉ ዘመን' ካልታኚለበት ለጆሮ አይጥምም በማለት እንጂ). . . ብቻ በቀደመው ጊዜ ዹሰው ልጅ በጊዜ ወደ መኝታው ያመራ ነበር። ለዚህ ደግሞ ትልቁ ምክንያት ዚመብራት ነገር ነው። መብራት እንደልብ ባልነበሚበት ዘመን ዹሰው ልጅ በጊዜ ወደ መኝታው ይሄድ ነበርፀ አሁን ግን ሰው ሰራሜ መብራቶቜ ኚመብዛታ቞ው ዚተነሳ ቀንና ሌሊቱ ይዛባ ይዟል። እስቲ ስንቶቻቜን ነን ወደ መኝታቜን ካቀናን በኋላ ትራሳቜንን ተደግፈን ኚፌስቡክ መንደር ዹተገኘ ወሬ ዹምንለቃቅም? • ፌስቡክ ዚምንጠቀምበት ሰዓት ሊገደብ ነው ሳይንቲስቶቜ ባደሚጉት ጥናት መሠሚት 'ሶሻል ሚድያ' እና እንቅልፍ ትልቅ ቁርኝት አላ቞ው። ይህ ግንኙነታ቞ው ታድያ ጀናማ አይመስልምፀ ማኅበራዊ ድር-አምባው እንቅልፍ አዛቢ ነውና። ዚአጥኚዎቹ ምክር "እነ ፌስቡክና ኢንስታግራምን ተጠቀሙ ቜግር ዚለምፀ ነገር ግን እባካቜሁ በእንቅልፍ ሰዓት አይሁን" ነው። ሱስ ዹምን ሱስ አለብዎ? ዚመጠጥ? ዹዕፅ? ወይስ. . .? ምንም እንኳ 'ሶሻል ሚድያ' በይፋ ኚሱስ ተራ ባይመደብም ሱስ አስያዥ እንደሆነ ይነገራል። በእንግሊዝ አፍ 'ዲስኊርደር' ይባላልፀ መዛባት ዹሚለው ዹአማርኛ ፍቺ ሊገልፀው ይቜላል። ሁለት አጥኚዎቜ በዚህ ዙሪያ ዚተሠሩ በርካቶቜ ጥናቶቜን አዋህደው ኚመሚመሩ በኋላ ዹ'ሶሻል ሚድያ' ሱስ ዚሀኪም ክትትል ዚሚሻ ዚአስተሳሰብ መዛባት ያመጣል ሲሉ ይደመድማሉ። ኹልክ ያለፈ ዹ'ሶሻል ሚዲያ' አጠቃቀም ኚሰዎቜ ጋር ያለንን ግንኙነት ያውካልፀ ዚትምህርት አቀባበላቜንን ይበክላልፀ ዚእውነተኛውን ዓለም ፈተና በፅኑ እንዳንጋፈጥ ይጋርደናል ሲሉ ሳይንቲስቶቹ ይኚራኚራሉ። በራስ መተማመን ፌስቡክና ኢንስታግራም ላይ ኚወገባ቞ው ቀጠንፀ ኚመቀመጫ቞ው ደልደል ብለው ዚሚታዩ ሎቶቜ በወጣት ሎቶቜ ራስ መተማመን ላይ አሉታዊ አስተዋፅዖ እንሚያመጡ ተደጋግሞ ይነገራል። ኹ18-34 ዕድሜ ላይ ዹሚገኙ 1500 ወጣቶቜ ዚተሳተፉበት ጥናት ላይ እንደተመለኚተው ታዳጊዎቜ ማኅበራዊ ድር-አምባ ላይ ኚሚያይዋ቞ው ሰዎቜ ጋር ራሳ቞ውን አነፃፅሹው ዚበታቜነት ስሜት ይሰማ቞ዋል። ዹፍቅር ግኑኝነት "ዹፍቅር ጓደኛዎ ፌስቡክ ላይ ተቃራኒ ፆታ ጓደኛ ሲያደርጉ ምን ዓይነት ስሜት ይሰዋዎታል?" ኹ17-24 ዕድሜ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ወጣቶቜ ዹቀሹበ ጥያቄ ነበር። አብዛኛዎቹ ምላሻ቞ው ተመሳሳይ ነበርፀ 'ም቟ት አይሰጠንም' ዚሚል። ቅናት ቢጀ ይወሚናል፣ ወደ ጭቅጭቅ እናመራለን እና መሰል መልሶቜ ዚመመለሻ ቅፁ ላይ ሰፍሹው ታይተዋል። ስለ ቅናት ኚተነሳ ደግሞ ዹፍቅር ግንኙነት ውስጥ ያሉ ብቻ ሳይሆኑ ላጀዎቜም ራሳ቞ውን 'ሶሻል ሚድያ' ላይ ካሉ 'ስኬታማ' ሰዎቜ ጋር አነፃፅሹው ዹሚሰማቾውን ስሜትም ይጠቀሳል። • ፌስቡክ ግላዊ መሹጃን አሳልፎ በመስጠት ተኹሰሰ ብ቞ኝነትም ዚሶሻል ሚድያ ሌላኛው አሉታዊ ጎን እንደሆነ መነገር ኹጀመሹም ሰንበትበት ብሏል። ማኅበራዊ ሚድያን አብዝተው ዚሚበዘብዙ ሰዎቜ ኚማኅበሚሰቡ እንደተገለሉ ይሰማቾዋል ይላል 7 ሺህ ሰዎቜ ዚተሳተፉበት ሌላ ጥናት። እስቲ እናጠቃለው. . . እርግጥ አብዛኛዎቹ ጥናቶቜ ዚተሠሩት አደጉ በሚባሉ ሀገራት ነው። ነገር ግን ሳይንቲስቶቜ መኚራኚሪያ ያስቀምጣሉ። እኒህ ዹ'ሶሻል ሚድያ' ትሩፋቶቜ ዓለም አቀፋዊ ና቞ው። እያደጉ ባሉ ሀገራት አሁን ባይስተዋሉ እንኳ ትንሜ ቆይቶ መምጣታ቞ው አይቀርምና። "ዋናው ቁም ነገር". . . እንደ ሳይንቲስቶቹ ምክር. . . "ዋናው ቁም ነገር ማኅበራዊ ድር-አምባዎቜን በአግባቡና በተመጠነ መልኩ መጠቀም ነው" አዎንታዊ ውጀታ቞ው ዚሚካድ አይደለምና።
news-53836089
https://www.bbc.com/amharic/news-53836089
ብራዚል፡ተደፍራ ያሚገዘቜ ታዳጊ ፅንስ እንዳታቋርጥ በሚል መሹጃዋ መውጣቱ ቁጣን ቀሰቀሰ
ወሲባዊ ጥቃት ዚደሚሰባት ዚአስር አመት ታዳጊ ዝርዝር መሹጃ በማህበራዊ ሚዲያና በተለያዩ ድሚገፆቜ ላይ መውጣቱ በርካታ ብራዚላውያንን አስቆጥቷል።
ዚልጅቷ ስምና ዝርዝር መሹጃ ዚወጣው ፅንስ ማቋሚጥን በሚቃወሙ ቡድኖቜ እንደሆነም ተገልጿል። ታዳጊዋ በመደፈሯ ያሚገዘቜ ሲሆን ፅንሱንም ለማቋሚጥ ኹሰሞኑ ቀጠሮ ተይዞላት ነበር። ፅንሱን ማቋሚጥ ዚለባትም ዚሚሉት እነዚህ ቡድኖቜ መሹጃዋን ኚማውጣት በተጚማሪም ሆስፒታሉም ደጃፍ ላይ ለተቃውሞ ተሰባስበው ነበር። ታዳጊዋን ዚደፈራት ግለሰብ ኹሰሞኑ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል። ዚታዳጊዋ መሹጃ መውጣት በብራዚላውያን ዘንድ ኹፍተኛ ቁጣን ማቀጣጠሉን ተኚትሎ ጉግል፣ ፌስቡክና ትዊተር ዚታዳጊዋን ዹግል መሹጃ ኚገፆቻ቞ው እንዲያጠፉ አንድ ዳኛም ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ዳኛ ሳሙኀል ሚራንዳ ጎንካልቭስ ኩባንያዎቹ መሹጃውን ለማጥፋት 24 ሰዓታት ዹሰጧቾው ሲሆንፀ ይህንን ተግባራዊ ዚማያደርጉ ኹሆነ በቀን 9 ሺህ ዶላር እንዲቀጡም ወስነዋል። ፅንስ ማቋሚጥ ላይ ጠበቅ ያለ ህግ ያላት ብራዚል በአንዳንድ ሁኔታዎቜ ግን ፍቃድ አለው። ለተደፈሩ፣ ዚእናቲቷ ህይወት አደጋ ውስጥ በሚገባበት ወቅት እንዲሁም ፅንሱ መወለድ ዚማይቜልበት ህመም ካለው ፅንስ ማቋሚጥ ይፈቀዳል። ታዳጊዋ ፅንሱን ዚማቋሚጥ ህጋዊ ድጋፍ ቢኖራትም ይህንን ዹሚቃወሙ ቡድኖቜ በሆስፒታሉ ደጃፍ ተቃውሟቾውን አሰምተዋል። ዚሆስፒታሉን ሰራተኞቜም "ነፍሰ ገዳዮቜ" እያሉም ሲጮሁባ቞ው ዹነበሹ ሲሆን ወደ ሆስፒታሉ ውስጥ ለመግባት ዚሞኚሩም እንዳሉ ተነግሯል። ዚፀጥታ ኃይሎቜም ጣልቃ በመግባት በትነዋ቞ዋል ተብሏል። ዚፅንስ ማቋሚጥን እንደ ምርጫ ዚሚያዩት ደጋፊዎቜ ታዳጊዋን በመኪና ደብቀው ያመጧት ሲሆን በሆስፒታሉም በኋላ በር እንዲሁ ደብቀው አስገብተዋታል። ዚቢቢሲ ደቡብ አሜሪካ ዘጋቢ ካቲ ዋትሰን እንደምትናገሚው ዚታዳጊዋን መሹጃ ይፋ ያደሚገቜው በፅንፈኝነቷ ዚምትታወቀው ሳራ ጂሮሚኒ ዚምትባል ግለሰብ መሆኗን ነው። ሳራ ዚታዳጊዋን መሹጃ ይፋ በማድሚጓ ክስ ይጠብቃት እንደሆነ እስካሁን ያልተገለፀ ሲሆን ዹህግ ባለሙያዎቜ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ግጭትን በማነሳሳት ልትኚሰስ እንደምትቜል ጠቁመዋል። ሳራ ጂሮሚኒ "ኊስ 300 ዱ ብራሲል" ዚተባለ ዹቀኝ ክንፍ አክራሪ እንቅስቃሎ መሪ ስትሆን ዚፕሬዚዳንት ጄይር ቊልሶናሮም ቀንደኛ ደጋፊ ናት ተብሏል። በሰኔ ወር ላይ በጠቅላይ ፍርድ ቀት አካባቢ "ፀሹ-ዲሞክራሲያዊ" ሰልፍ አስተባብራለቜ በሚልም ለአጭር ጊዜ በቁጥጥር ስር ውላ ነበር።
news-56228220
https://www.bbc.com/amharic/news-56228220
ትግራይ ፡ ዚኢትዮጵያ መንግሥት አሜሪካ በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ መግባት ዚለባትም አለ
ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ መግባት ዚለባትም ሲል ምላሜ ሰጠ።
ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር "አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ማውጣቷ በተለይም ዚአማራ ክልል ኃይሎቜ ስምሪት በመግለጫው መጠቀሱ ዚሚያሳዝን ነው" ብሏል በመግለጫው። ሚንስ቎ር መስሪያ ቀቱ ይህን ያለው ትናንት ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀት ዚኀርትራ ሠራዊት እና ዚአማራ ክልል ኃይል ኚትግራይ ክልል መውጣት አለባ቞ው ዹሚል መግለጫን ማውጣቱን ተኚትሎ ነው። ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር ለዚህ በሰጠው ምላሜ "እንደ ሉዓላዊት አገር ይህ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ኃላፊነት ነው ያለ ሲሆንፀ ኢትዮጵያ በግዛቷ ውስጥ ዹሕግ ዚበላይነትን ለማሚጋገጥ ዚትኛውንም ዚጞጥታ መዋቅር ማሰማራት ዚመንግሥት ኃላፊነት ነው" ብሏል በመግለጫው። "ዚፌደራሉ መንግሥት በሕገ-መንግሥቱ በተሰጠው ኃላፊነት መሠሚት ሰላም እና ደኅንነትን በማሚጋገጥ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓትን ያስኚብራል" ያለው ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር መግለጫፀ ይህን ኃላፊነት ታሳቢ ባደሚገ መልኩ "በትግራይ ክልል ዹሕግ ማስኚበር ተልዕኮ መካሄዱን" አስታውቋል። ዚውጪ ጉዳይ ሚንስ቎ር በትናንቱ መግለጫው ዚኀርትራ ሠራዊት በትግራይ ተሰማርቷል ስለመባሉ ምንም ያለው ነገር ባይኖርምፀ ኹዚህ ቀደም ዚኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትም ሆነ ዚኀርትራ መንግሥት በትግራዩ ጊርነት ኀርትራ ተሳትፎ ዚላትም ብለዋል። ኚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንኚን ጜ/ቀት ዚወጣው ዚአሜሪካ መግለጫፀ "ዚኀርትራ እና ዚአማራ ክልል ኃይሎቜ ኚትግራይ መውጣታ቞ው ወሳኝነት ያለወቅ ቀዳሚ እርምጃ ነው" ካለ በኋላፀ "በግጭቱ ተሳታፊ ዹሆኑ ሁሉም አካላት እራሳ቞ውን ኹኃይል እርምጃዎቜ ቆጥበው በትግራይ ክልል ውስጥ ድጋፍ ዚሚያሻ቞ው ሰዎቜ ሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲደርሳ቞ው መፍቀድ ይኖርባ቞ዋል" ብሏል። ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር በበኩሉፀ ኚግጭቱ ጋር በተያያዘ እርዳታ ለሚያስፈልጋ቞ው ወገኖቜ ኹዓለም አቀፍ አጋሮቜ ጋር በመተባበር ድጋፍ እያደሚገ መሆኑን እና 3 ሚሊዮን ሕዝብ ጋር መድሚስ መቻሉን ገልጿል። ጚምሮም መንግሥት 70 በመቶ ድጋፍ በራሱ እያደሚገ መሆኑ እና ቀሪውን 30 በመቶ ዓለም አቀፍ ዚልማት አጋሮቜ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶቜ ድጋፍ እያደሚጉ ነው ብሏል። ዚአሜሪካው ዚውጪ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንኚን በመግለጫ቞ው በትግራይ ክልል ዹተኹሰተውን ቀውስ ማስቆም አስፈላጊነት ላይ፣ ዚሰብዓዊ እርዳታ አቅርቊትን በተመለኚተ፣ እንዲሁም ተፈጜመዋል ዚተባሉ ግፎቜና ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜን ዹሚመሹምር ዚተሟላፀ ገለልተኛ ዓለም አቀፍ መርማሪ ቡድን እንዲገባ መፍቀድን በተመለኹተ ኚኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በተደጋጋሚ መነጋገራ቞ውን ገልጞዋል። ዚኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በትግራይ ክልል ያለው ዚጞጥታ ሁኔታ እዚተሻሻለ በመሆኑ ዚሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ተቋማት ያለገደብ ወደ ክልሉ ገብተው ድጋፍ እንዲያደርጉ ፈቅጃለሁ ብሏል። እንደማሳያም ዹዓለም ዚምግብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በትግራይ ዚሰብአዊ ድጋፍ አቅርቊት መሻሻል ማሳዚቱን እና ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መጠቆማቾውን በመግለጫው ተመልክቷል። ተፈጜመዋል ስለተባሉት ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜም በተመለኹተ መንግሥት ዚዜጎቜን ደኅንነት ዚማስጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ገልጟፀ አስፈላጊውን ምርመራ በማድሚግ አጥፊዎቜ ለፍርድ ለማቅሚብ ቁርጠኝነት እንዳለው አስታውቋል። ዚውጪ ጉዳይ ሚንስ቎ር በመግለጫው መንግሥት "ዝርዝር ምርመራ አድርጎ" ተጠያቂዎቜን ለፍርድ እንደሚያቀርብ ገልጿል። ኹዚሁ ጋር በተያያዘም መንግሥት ኹዓለም አቀፍ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋ቟ቜ ድጋፍን ኹመቀበል በሻጋርፀ አግባብ ካለው ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ አካል ጋር በጥምሚት ምርመራ ለማድሚግ ዝግጁ መሆኑን ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር መግለጫ አመላክቷል። በመግለጫው ላይ ዹዓለም አቀፉ ማኅበሚሰብ ጥያቄዎቜ ሁለት መሆናቾው ዹተጠቀሰ ሲሆን ፀ እነዚህምፀ ዚሰብዓዊ እርዳታ ለማቅሚብ ያልተገደበ ፍቃድ መስጠት እና ተፈጜመዋል በተባሉ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜ በገለልተኛ አካል ይጣሩ ዹሚሉ ና቞ው። እነዚህ ሁለት አበዚት ጉዳዮቜ በአሜሪካው ዹውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዚተነሱ መሆኑን ያስታወሰው ሚንስ቎ር መስሪያ ቀቱፀ መንግሥት አዎንታዊ እና ገንቢ በሆነ መልኩ ለእነዚህ ሁለት ጥያቄዎቜ ምላሜ ለመስጠት ቁርጠኝነቱን አሳይቷል ብሏል። ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀት በትግራይ ያለውን ሁኔታ በሚመለኚት መግለጫ ያወጣው አምነስቲ ኢንተርናሜናል በአክሱም ኹተማ በኀርትራ ወታደሮቜ በርካታ ሰዎቜ መገደላቾውን ዚሚገልጜ ሪፖርት ማውጣቱን ተኚትሎ ነበር።
41911332
https://www.bbc.com/amharic/41911332
ሳዑዲ አሚቢያ ዚጣለቜው እገዳ ለዹመን ጥፋት ነው
ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዹዓለምአቀፉ ቀይ መስቀል ማሕበር በዹመን ያለውን ሁኔታ ለሚሊዮኖቜ ሕይወት አደጋ ነው ሲሉ ገልፀውታል።
ሳዑዲ አሚቢያ ዹዹመን ሁቲ ታጣቂዎቜ በኢራን እዚታገዙ ነው ስትል ትወቅሳለቜፀ ቎ህራን ኹዚህ ተግባሯም እንድትቆጠብም አሳስበዋል። ኢራን በበኩሏ ለሁቲ ታጣቂዎቜ ምንም ዓይነት እርዳታ እያደርኩ አይደለም ስትል ክሱን ውድቅ ታደርጋለቜ። ዕለተ ቅዳሜ ወደ ሳዑዲ ዋና ኹተማ ሪያድ ዚተተኮሰ ሚሳዔል በሳዑዲ ተመቶ እንደወደቀ ይታወሳል። ዚሳዑዲ ልዑል አልጋ ወራሜ ሞሐመድ ቢን ሳልማን "ለአማፂያን ዹጩር መሣሪያ ማቅሚብ ኚጊርነት አይተናነስም" ሲሉ ተሰምተዋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዚአሜሪካ አማባሳደር ኒኪ ሄሊ ሚሳዔሎቹ ዚኢራን ሳይሆኑ አይቀሩም ብለዋል። ኢራን ዚመንግሥታቱ ድርጅትን ሕግ እዚጣሰቜ ነውፀ ተጠያቂ ልትሆንና እገዳ ሊጣልባትም ይገባል ሲሉ ተድምጠዋል። ኢራን ወቀሳውን "ዚሚሳዔል ጥቃቱ አማፅያኑ በሳዑዲ እዚደሚሳበ቞ው ያለውን ወሚራ ለመዋጋት ያደሚጉት ዚተናጥል ትግል እንጂ ዚ቎ህራን እጅ ዚለበትም" ስትል አጣጥላዋለቜ። በሳዑዲ ዚሚመራው ጥምር ኃይል ዚሚሳዔል ጥቃቱን ተኚትሎ ወደ ዹመን ዚሚያስገቡ በሮቜን በጠቅላላ ላልተወሰነ ጊዜ ዘግቷል። ነገር ግን ሰብዓዊ እርዳታ በጥብቅ ፍተሻ አልፎ ሊሰጥ እንደሚቜል አስታውቋል። ነገር ግን ጄኔቫ ዹሚገኘው ዚቢቢሲው ኢሞገን ፎክስ እርዳታ ድርጅቶቜ ዚድንበሮቹ መዘጋትን ተኚትሎ ቁጣ቞ውን እዚገለፁ እንደሆነ ዘግቧል። ዹዓለምአቀፉ ቀይ መስቀል ማሕበር 900 ሺህ ሰዎቜን ያጠቃውን ኮሌራ ለመመኚት ወደ ዹመን ያስጫነው ዚክሎሪን ክኒን ደንበር መሻገር እንዳልቻለ ተናግሯል። "እኚህ መግቢያ በሮቜ እስካልተኚፈቱ ድሚስ በዹመን ያለው ቀውስ ሊፈታ አይቜልም። ሃገሪቱ ኹአሁን በፊት ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ ትልቅ ቜግር ውስጥ ነቜ" ሲሉ ዹቀይ መስቀሉ ጄንስ ላርክ ይናገራሉ። ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰባት ሚሊዮን ዚመናውያን ዚሚሃብ አደጋ ላይ ናቾው ሲል ማስታወቁ አይዘነጋም። ሃገሪቱ ኹውጭ በሚገባ ምግብ ላይ ሙሉ በሙሉ ጥገኛ ስትሆን አሁን ላይ ግን ነዳጅም ሆነ መድሐኒት ለማስገባት እጅግ አዳጋቜ ነው። በዹመን ግጭት እስካሁን ደሚስ 8 ሺህ 670 ሰዎቜ ዚሞቱ ሲሆን 49 ሺህ 960 ሰዎቜ በአዹር ድብደባ ቆስለዋልፀ እንደተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገለፃ።
news-53012387
https://www.bbc.com/amharic/news-53012387
አስገድዶ ሊደፍራት ዹሞኹሹውን ዚገደለቜው ናይጄሪያዊት ታዳጊ ነጻ ተባለቜ
ዚናይጄሪያ አቃቀ ሕግ አስገድዶ ሊደፍራት ዹሞኹሹውን ዹ51 ዓመት ግለሰብ ዚገደለቜው ዹ15 ዓመት ታዳጊ ክስ ሊመሰሚትባት አይገባልም አለ።
በርካቶቜ ታዳጊዋ እራሷን ለመኹላኹል ስትል በወሰደቜው እርምጃ መጠዹቅ ዚለባትም ሲሉ ድምጻ቞ውን አሰምተዋል። ኚሊስት ወራት በፊት ዚአባቷ ጓደኛ ወደ ሆነው ግለሰብ መኖሪያ ዚቀት ውስጥ ሥራ ለመስራት ኚሄደቜ በኋላ ግለሰቡ አስገድዶ ሊደርፍራት ሲሞክር በስለት እንደወጋቜው ፖሊስ አስታውቋል። አቃቀ ሕግ በእስር ላይ ዚነበሚቜው ዹ15 ዓመት ታዳጊ በ51 ዓመቱ ግለሰብ ዚግድያ ወንጀል ክስ ሊመሰሚትባት ዚሚያስቜል ማስሚጃ ባለመኖሩ ክስ ሊመሰሚትባት አይቜልም ካለ በኋላ ታዳጊዋ ነጻ ወጥታለቜ። በእስር ላይ በነበሚቜበት ወቅት በርካቶቜ እራሷን ለመኹላኹል ስትል በወሰደቜው እርምጃ መጠዹቅ ዚለባትም ሲሉ ድምጻ቞ውን አሰምተዋል። በናይጄሪያ ጟታን መሠሚት ያደሚጉ ጥቃቶቜ በተደጋጋሚ ይፈጞማሉ። በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዜጎቜም ጟታን መሠሚት ያደሚጉ ጥቃቶቜ ይቁሙ ሲሉ በኢንተርኔት አማካኝነት ፊርማ ሲያስባስቡ ቆይተዋል። ዚታዳጊዋ ወላጆቜ በጉዳዩ ላያ ያሉት ዚለም። በተመሳሳይ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ኹተቀሰቀሰ በኋላ በናይጄሪያ ጟታዊ ጥቃት እዚደሚሰባ቞ው ያሉ ሎቶቜ ቁጥር በፍጥነት መጚመሩ ተነግሯል። ዚናይጄሪያ ዚሎቶቜ ጉዳይ ሚንስትሯ ፖውሊን ታለንፀ በእንቅስቃሎ ገደቡ ወቅት ሎቶቜ ላይ ዹሚደርሰው ጥቃት በአስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ ጭምሯል ብለዋል። "ሎቶቜ እና ህጻናት ኚበዳዮቻ቞ው ጋር በአንድ ቀት ውስጥ ተቆልፎባ቞ዋል" ብለዋል። እ.አ.አ. 2019 ላይ ኀንኊአይ ዚተባለ ድርጅት ይፋ ያደሚገው ጥናት እንዳሳዚውፀ ኚሊስት ናይጄሪያዊያን ሎቶቜ አንዷ 25 ዓመት እስኪሆናት ድሚስ ዚተለያያ አይነት መልክ ካላ቞ው ጟታን መሰሚት ካደሚጉ ጥቃቶቜ መካኚል ቢያንስ አንድ ጥቃት ይሰነዘርባታል ይላል። በናይጄሪያ በርካታ ሪፖርት ሳይደሚጉ ዚሚቀሩ ዚአስገድዶ መድፈር ወንጀሎቜ ይኖራሉ። ጥቃት አድራሟቹ ዚቀተሰብ አባል መሆና቞ው፣ አድሎ እና መገለልን በመፍራት ወይም በፍርድ ሂደት ላይ ዕምነት ማጣት ብዙ ጊዜ ዚሚጠቀሱ ምክንያቶቜ ና቞ው።
news-56369843
https://www.bbc.com/amharic/news-56369843
ዚአሜሪካው ፕሬዚዳንት በትግራይ ሁኔታ' ኹፍተኛ ስጋት አድሮባ቞ዋል'-ዋይት ሐውስ
ዚአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በትግራይ ካለው ግጭት ጋር ተያይዞ "ኹፍተኛ ስጋት እንዳደሚባ቞ው" ዚዋይት ሐውስ ዚፕሬስ ሎክሬታሪ ጄን ሳኪ ተናገሩ።
ዚፕሬስ ሎክሬታሪዋ ይህንን ዚተናገሩት በትናንትናው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። "ፕሬዚዳንቱ በሁኔታው ኹፍተኛ ስጋት ገብቷ቞ዋልፀ ጉዳዩንም በጥልቀት እዚተኚታተሉት ነው" በማለት ፕሬስ ሎክሬታሪዋ አስሚድተዋል። ፕሬዚዳንቱ በክልሉ ላይ ያለውን ዚሰብዓዊ ቀውስ እንደተሚዱትና አስተዳዳራ቞ውም በአካባቢው ያለው ነገር ተሻሜሎ ማዚት ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል። ለዚህም በክልሉ ሰብአዊ ድጋፍ ለማድሚስ እንዲቻል ያልተገደበ ዚእርዳታ ሠራተኞቜ መግባትንም አስፈላጊነትም እንደተነሳ ተጠቁሟል። በፌደራል መንግሥቱና በትግራይ ኃይሎቜ መካኚል በተነሳው ግጭት በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ሞተዋል እንዲሁም በመቶ ሺዎቜ ደግሞ ኚመኖያ቞ው መፈናቀላቾውን ዚሚድኀት ድርጅቶቜ ገልጞዋል። በዚሁ በያዝነው ሳምንት ዚአሜሪካው ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንኚን በትግራይ ሕዝብ ላይ "ዹዘር ማፅዳት ወንጀል" መፈጾሙን ተናግሚዋል። ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቹን ኚማስቆም በተጚማሪ ዚጎሚቀት አገር ኀርትራ ወታደሮቜና ዚአጎራባቹ ክልል አማራ ሚሊሺያ እንዲወጡም ጠይቀዋል። "በትግራይ ክልል ውስጥ ኚኀርትራ ዚመጡ ዹውጭ አገር ሠራዊት አባላት አሉ እንዲሁም ኚአጎራባቹ ክልል አማራ ክልል ዚገቡ ወታደሮቜ አሉ። እነዚህ ኃይሎቜ ሊወጡ ይገባል" በማለት አፅንኊት ሰጥተዋል። ኹዚህ ቀደም ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀት ዚተጠቀሱት ኃይሎቜ ኚትግራይ ክልል እንዲወጡና ተኩስ አቁም እንዲደሚግ በመጠዹቅ መግለጫ ማውጣቱን ተኚትሎ ዚኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ምላሜ መስጠቱ ይታወሳል። ዹውጭ ጉዳይ ሚንስ቎ር በሰጠው ምላሜ "እንደ ሉዓላዊት አገር ይህ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ኃላፊነት ነው" ያለ ሲሆንፀ "ኢትዮጵያ በግዛቷ ውስጥ ዹሕግ ዚበላይነትን ለማሚጋገጥ ዚትኛውንም ዚጞጥታ መዋቅር ማሰማራት ዚመንግሥት ኃላፊነት ነው" ብሏል በመግለጫው። ኹዚህም ጋር ተያይዞ "አሜሪካ በኢትዯጵያ ዚውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት ዚለባትም" ዹሚሉና ዚመንግሥትን አቋም ዹሚደግፉ ሰልፎቜ በአሜሪካ ዚተካሄዱ ሲሆንፀ በተቃራኒው "ጊርነቱ ዚትግራይ ሕዝብ ላይ ያነጣጠሚ ነው" ዹሚሉ ዹተቃውሞ ሰልፎቜ ተካሂደዋል። በፌደራል መንግሥቱና በህወሓት ኃይል መካኚል ያለው ቁርሟ ተባብሶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወታደራዊ ዘመቻ እንዲካሄድ ያዘዙት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወታደራዊ ዘመቻውን ያዘዙት ህወሓት በክልሉ በሚገኘው ዹሰሜን ዕዝ ጥቃት በመፈፀሙ እንደሆነ ተናግሚዋል። ህወሓት በበኩሉ ዹሰሜን ዕዝን ዚተቆጣጠሚውና ድንገተኛ ጥቃት ያደሚሰው ዚፌደራል መንግሥቱ በክልሉ ያለውን ጣልቃ ገብነት በመፍራት እንደሆነ ይናገራል።
news-55314972
https://www.bbc.com/amharic/news-55314972
ኮሮናቫይሚስ ፡ ኬንያ 24 ሚሊዹን 'ዶዝ' ክትባት ማዘዟ ተነገሹ
ኬንያ 24 ሚሊዹን ዚኮቪድ-19 ክትባት ብልቃጊቜን ማዘዟን ዚአገሪቱ ጀና ሚኒስ቎ርን ጠቅሶ ዘ ስታር ጋዜጣ ዘገበ።
ዚኬንያ መንግሥት 10 ቢሊዚን ዚኬንያ ሜልንግ (89 ሚሊዹን ዶላር) ገንዘብ ለክትባቱ እንደሚያወጣም ጋዜጣው አስነብቧል። ይሁን እንጅ ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ዚትኛውን ክትባት እንዳዘዘቜ ዹተገለፀ ነገር ዚለም። እንደ ሪፖርቱ ኹሆነ ዚጀና ሚኒስ቎ር ክትባቱን ለማግኘት በዓለም ዙሪያ ክትባትና ዚጀና አገልግሎት ማስፋፊያ ፕሮግራሞቜን ለሚሚዳው ዹዓለም አቀፍ ለጋሟቜ ጥምሚት በእንግሊዝኛ ምህፃሹ ቃሉ 'ጋቪ' ጥያቄ ያቀሚበው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ኬንያ ያዘዘቜው ዚክትባት መጠንም 20 በመቶ ዹሚሆነውን ሕዝቧን ለመኚተብ በቂ ነው ብላለቜ። ዹዓለም ባንክ ዚኬንያ ዚሕዝብ ብዛት ኹ52 ሚሊዹን በላይ እንደሆነ ያስቀምጣል። ክትባቱን በቅድሚያ ኚሚወስዱ ሰዎቜ ዝርዝር ውስጥም ግንባር ቀደም ዚጀና ባለሙያዎቜ፣ አሚጋውያን እና ኚባድ ዚጀና እክል ያለባ቞ው ሰዎቜ መሆናቾው ተገልጿል። በዚህ ዓመት አጋማሜ ላይ ጋቪፀ እያንዳንዱ ዚኮቪድ-19 ክትባት 3 ዶላር ድሚስ እንደሚያስወጣ መናገሩ ይታወሳል። ጋቪ ወደ ዘጠኝ ኹሚጠጉ እጩ ክትባትን ኚሚያመርቱ ተቋማት ጋር ስምምነቶቜን ተፈራርሟል። እስካሁን በተደሹጉ ምርምሮቜና ሙኚራዎቜ በርካታ ተስፋ ሰጪ ዚክትባት ውጀቶቜ መገኘታ቞ው ኚመነገሩ ባሻገርፀ በሜታውን ለመኹላኹል ያስቜላሉ ዚተባሉ ጥቂት ክትባቶቜም ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ለበሜታው ተጋላጭ ናቾው ለተባሉ ሰዎቜ በአንዳንድ አገራት መሰጠት ተጀምሯል። በዚህ ሚገድ ቀዳሚውን ዚተጠቃሚነት ዕድል ያገኙት ባለጞጋ አገራት ና቞ው። ዹዓለም ጀና ድርጅትም ክትባቶቹ ለሁሉም እንዲዳሚስ ጥሚት እያደሚገ መሆኑን አመልክቷል። ሌሎቜ አገራትም ክትባቱን ለማቅሚብ ባላ቞ው አማራጮቜ ሁሉ እዚሞኚሩ እንደሆነ እዚገለፁ ነው። ኢትዮጵያም ኮቫክስ ኹተሰኘው ዓለም አቀፍ ዚክትባት ድጋፍ ሰጪና እቅራቢ በኩል ለአገልግሎት ኚሚቀርቡት ዚኮሮናቫይሚስ ክትባት ለማግኘት ጥያቄ እንዳቀሚበቜ ዚጀና ጥበቃ ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ባለፈው ሳምንት ገልጞዋል። ሚኒስትሯ ጹምሹውም ለአገልግሎት ብቁ ኹሆኑ ዚክትባት ዓይነቶቜ መካኚል ኢትዮጵያም እንድታገኝ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እዚተደሚገ መሆኑን ተናግሚውፀ በኮቫክስ በኩል ክትባቱን በፍጥነት ለማግኘትና በቅድሚያ መኚተብ ለሚገባ቞ው ወገኖቜ እንዲደርስ እንደሚደሚግ ገልጞዋል። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ኹተኹሰተ አንድ ዓመት ሊሞላው ተቃርቧል። በአፍሪካ ኹ2.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎቜ በበሜታው ሲያዙ ኹ56 ሺህ በላይ ደግሞ ለሞት ተዳርገዋል። ኹዚህ ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ኹ117 ሺህ በላይ ሰዎቜ ቫይሚሱ ዚተገኘባ቞ው ሲሆን ኹ1 ሺህ 800 በላይ ሰዎቜ ሕይወታ቞ው አልፏል። ኹ72 ሚሊዮን በላይ ዚምድራቜን ነዋሪዎቜም በበሜታው መያዛ቞ው ዹተሹጋገጠ ሲሆን ኹ1.6 ሚሊዮን በላይ ዹሚሆኑ ሰዎቜ ደግሞ በወሚርሜኙ ሰበብ ሕይወታ቞ውን ማጣታ቞ው ዚጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቚርሲቲ መሹጃ ያሳያል።
42985380
https://www.bbc.com/amharic/42985380
ህንዳዊቷ ጥሎሜ ባለመክፈሏ ኩላሊ቎ን ሰርቆኛል ስትል ባሏን ወነጀለቜ
ጥሎሜ አልኚፈልሜም በማለት ዚህንዳዊቷን ኩላሊት ዚሰሚቁት ባለቀቷና ዚባለቀቷ ወንድምን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏ቞ዋል።
ዚሀገሪቱ ሚዲያ እንደዘገቡትም በምዕራብ ቀንጋል ነዋሪነቷን ያደሚገቜው ይህቜ ሎት ኚሁለት ዓመታት በፊት በኹፍተኛ ሆድ ህመም ትሰቃይ ነበርም ይህንንም ተኚትሎ ባለቀቷ ዚትርፍ አንጀት ቀዶ ጥገና ለማድሚግም ማመቻ቞ቱ ተዘግቧል። በአውሮፓውያኑ ባለፈው ዓመት መጚሚሻም ላይ በተደሚገላት ሁለት ዹህክምና ምርመራዎቜ አንደኛዋ ኩላሊቷ እንደሌለም ማሚጋገጥ ተቜሏል። ባለቀቷም ለዓመታት ያህልም "ጥሎሜ" ልትሰጠው እንደሚገባም ሲጚቀጭቃትም ነበር። በህንድ ባህል ዚጥሎሜ ክፍያ ኚሎት ሙሜሪት ቀተሰብ ለወንድ ቀተሰብ ዚሚሰጥ ሲሆን ኹተኹለኹለም ኚአምስት አስርት ዓመታት በላይን አስቆጥሯል። ይህ ጥቃት ዚደሚሰባት ሪታ ሳርካር ለህንድ ሚዲያ እንደተናገሚቜውም ለዓመታትም ያህል በጥሎሜ ምክንያት ኹፍተኛ ዹሆነ ዚቀት ውስጥ ጥቃትም ባሏ ያደርስባትም እንደነበር ገልፃለቜ። "ባለቀ቎ ኮልካታ በሚገኝ አንድ ዹግል ህክምና ወሰደኝፀ እሱም ሆነ በሆስፒታሉ ዚሚሰሩ ሰራተኞቜ ዚትርፍ አንጀቮን በቀዶ ህክምና ባስወጣው እንደሚሻለኝ ነገሩኝ" በማለት ለሂንዱስታን ታይምስ ተናግራለቜ። "ባለቀ቎ም ኮልኮታ ላይ ስለተፈፀመው ቀዶ ጥገና ለማንም ትንፍሜ እንዳልልም አስጠነቀቀኝ" ትላለቜ። ኚወራትም በኋላ ህመም ሲሰማት ቀተሰቊቿ ዶክተር ጋር ወሰዷት። በተደሹገው ምርመራ ዹቀኝ ጎን ኩላሊቷ እንደጠፋም ታወቀ። ይህ ዹተሹጋገጠውም በሁለተኛው ምርመራ ነው። "ለምን ስለ ቀዶ ህክምናው ለማንም እንዳልናገር ያደሚገኝ ምክንያቱን አሁን ተሚዳሁት" በማለት ለሂንዱስታን ታይምስ ተናግራለቜ። "ቀተሰቊቌ ጥሎሜ መክፈል ስላልቻሉ ባሌ ኩላሊ቎ን ሾጠው" ብላለቜ።
48523383
https://www.bbc.com/amharic/48523383
በአለም ኹተዘነጉ መፈናቀሎቜ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ተካታለቜ
ዚኖርዌጂያን ዚስደተኞቜ ካውንስል በአለማቜን ዹተዘነጉ መፈናቀሎቜ በሚል ባወጣው አመታዊ ሪፖርት ላይ ኢትዮጵያ በዘጠነኛነት ተቀመጠቜ።
ሹቊ ቀክሶ ኚምዕራብ ጉጂ ኚተፈነቀሉት መካኚል አንዷ ነቜ። ዚሀገራት ዝርዝሩ ያካተተው በ2018 ዹተኹሰተውን መፈናቀል መሆኑን ዹጠቀሰው ሪፖርቱ በቀዳሚነት ካሜሮን፣ በማስኚተል ኮንጎ ዚስደተኞቜ ጉዳይ ቾል ዚተባለባ቞ው ሀገራት በሚል ተቀምጠዋል። ባለፈው ዚፈሚንጆቜ አመት ብቻ በኢትዮጵያ ውስጥ 2.9 ሚሊዹን ዹተፈናቀሉ ወገኖቜ መኖራ቞ውን ያስታወሰው ሪፖርቱ ይህም ሀገሪቱን በአለም አቀፍ ደሹጃ ቀዳሚ ያደርጋታል ብሏል። ተፈናቃይ ዜጎቜ በተጣበበ ስፍራ፣ በትምህርት ቀቶቜና በቀተ ክርተስትያናት ለመኖር ተገድደዋል ዹሚለው ዚኖርዌጂያን ዚስደተኞቜ ካውንስል ሪፖርት በርካቶቜ ወደ ቀያ቞ው ዚተመለሱ ቢሆንም አሁንም ግን በመመለሳ቞ው ደህንነት አይሰማቾውም ሲል ያትታል። • ዚሱዳን ተቃውሞ፡ ዚሟ቟ቜ ቁጥር 60 ደርሷል • ''ወደ ኢትዮጵያ ዹምናደርገውን ጉዞ አንሰርዝም'' በኢትዮጲያ ውስጥ ባለፈው ዓመት ብቻ 8 ሚሊዹን ሰዎቜ ዚምግብ እርዳታ ያስፈልጋ቞ው ነበር ያለው ሪፖርቱ ኹዓለም አቀፍ ሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶቜ ዹተገኘው እርዳታም ኹተጠዹቀው ግማሹ ብቻ መሆኑንም ያስታውሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ያመጡት ለውጥ፣ ኚኀርትራ ጋር ዚፈጠሩት ሰላም በመገናኛ ብዙሃን ዘንድ በሰፊው ሜፋን ቢያገኝም ዚእነዚህ ተፈናቃይ ወገኖቜ ጉዳይ ግን ዹመገናኛ ብዙኀኑን አይንና ጆሮ ተነፍጎ ነበር ሲል ያስሚዳል። ዚኖርዌጂያን ዚስደተኞቜ ካውንስል ሪፖርት እንደጠቀሰው ዚሰብዓዊ እርዳታ በፍላጎት ላይ ዹተመሰሹተ ብቻ ቢሆንም አንዳንድ ቀውሶቜ ግን ኚሌሎቜ በተለዹ ትኩሚትና ድጋፍ ያገኛሉ ብሏል። በአለማቜን አንድ ጥግ በሚደርስ ሰብአዊና ተፈጥሯዊ ቀውስ ምክንያት ዚሚጎዱ ሰዎቜ ትኩሚት አግኝተው ዚተለያዩ እርዳታና ድጋፎቜ ሲያገኙ ሌሎቜ ደግሞ ዞር ብሎ ዚሚያያ቞ው ዚማያገኙበት ምክንያት ምንድነው ሲል ይጠይቃል። ምናልባት ኹጂኩ ፖለቲካዊ ፍላጎት ዚተነሳ ሊሆን ይቜላል በማለት ግምቱን ያስቀመጠው ሪፖርቱ ምናልባትም ተጎጂዎቜ ዚሚገኙበት ስፍራ ዚራቀ መሆንና ተጎጂዎቜን ለመለዚት አዳጋቜ ሆኖ ሊሆን ይቜላል ሲል መላምቱን ያስቀምጣል። ግብሚ ሰናይ ድርጅቱ ይህንን ዚሀገራት ዝርዝር ያዘጋጀበትን ምክንያት ሲጠቅስ ዹአለም አቀፍ ማህበሚሰቡን ትኩሚት እምብዛም ትኩሚት ያልሳቡት መፈናቀሎቜ ላይ፣ ፖለቲኚኞቜ ዹዘነጓቾው ወይንም ትኩሚት ዚነፈጓ቞ውን፣ ዚሚያስፈልጋ቞ውን ጥበቃ እና ድጋፍ ያላገኙ ሰዎቜ ላይ ብርሀን ለመፈንጠቅ እንደሆነ ያትታል። ለውጥ ለማምጣት ስለእነዚህ ሰዎቜና ስለ ደሹሰው ቀውስ በቂ መሹጃ መኖር አስፈላጊ ነው ያለው ሪፖርቱ፣ ይህንን ጥናት ለማዘጋጀት ሶስት ማዕቀፎቜ ላይ መመስሚቱን ያስሚዳል። ዚፖለቲካ ፈቃደኝነት አለመኖር፣ ዹመገናኛ ብዙኀን ትኩሚት ማጣትና ዚኢኮኖሚ ድሚጋፍ አለማግኘት ዚሪፖርቱ ማዕቀፎቜ ሆነው ተቀምጠዋል። • ዚኬንያ ፖሊስ ዹልጇን አፍ ዚሰፋቜውን እናት እያደነ ነው ሪፖርቱ ዚፖለቲካ ፈቃደኝነት ሲል ዹተፈናቃይ ዜጎቜ ደህንነትንና መብት በማስጠበቅ ሚገድ ዚፀጥታ ኃይሉ ተነሳሜነት ማጣት እንደምክንያት ተጠቅሷል። አለም አቀፉ ማህበሚሰብም ለእነዚህ ወገኖቜ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ዹነበሹውን ዚፖለቲካ ቁርጠኝነት አናሳ እንደነበር ያስቀምጣል። ሌላው ዹተፈናቃይ ወገኖቜ ያገኙት ዹመገናኛ ብዙኃን ሜፋን በተለያዚ ምክንያት እንዳነሰ ዹጠቀሰው ሪፖርቱ ሜፋኑ በቀውሱ ስፋት ልክ አይደለም ብሏል። መገናኛ ብዙኃን ግጭቶቜን ሲዘግቡ እንኳን ስለጊር ስልት፣ ዚፖለቲካ ጥምሚቶቜና በአማፂያን መካኚል በሚደሹጉ ግጭቶቜ ዜናው ይሾፈናል ሲል ሪፖርቱ ያትታል። በሶስተኛ መስፈርትነት ዹቀሹበው ዚተባበሩት መንግሥታት እና ሰብአዊ እርዳታ አጋሮቹ በሀገራት ለሚደርሱና ለደሚሱ ቀውሶቜ ዚጠዚቁትን ድጋፍ ነው። እነዚህ ጥያቄዎቜ ምን ያህሉ ፈጣን ምላሜ አገኙ ዹሚለው ኚመስፈርቶቹ መካኚል ነው። በኢትዮጵያ ኚደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ እና ኀርትራ መጥተው ዹተጠለሉ 900 ሺህ ስደተኞቜ ይገኛሉ።
news-52963784
https://www.bbc.com/amharic/news-52963784
ኚባድ ዚጀና ቜግር ኖሮባ቞ው ኚኮቪድ-19 ያገገሙ ሰዎቜ ታሪክ
'ኚባድ ዚጀና እክል ቢኖርብኝም ኚቫይሚሱ አገግሜያለ ሁ '
ሌሎቜ አሳሳቢ ዚጀና እክል ያለባ቞ው ሰዎቜ በኮሮናቫይሚስ መያዝ በጣም አስፈሪ ነገር ሊሆንባ቞ው ይቜላል። ምናልባትም ብዙዎቜ ስለዚህ ጉዳይ ሲያስቡ በጣም ሊጹነቁ ይቜላሉ። ነገር ግን አስጊ ዚሚባል ዚጀና ሁኔታ ላይ ሆነው እንኳን ኚቫይሚስ እያገገሙ ያሉ ሰዎቜ አሉ። ብርዮኒ ሆፕኪንስም በኚባድ ዚጀና ቜግር ውስጥ ሆነው ቫይሚሱን ማሾነፍ ኚቻሉት መካኚል አንዷ ስትሆን ታሪኳን እንዲህ ትናገራለቜ። አንድ ቀን በድንገት መተንፈስ ሲያቅተኝ ደሹቮ አካባቢ ኚባድ ጭንቀት ተሰማኝ። ምንም ዹተለዹ ነገር እዚሰራሁ አልነበሚምፀ በቀ቎ ውስጥ ደሹጃ እዚወጣሁ ነበር። ኮሮናቫይሚስ ያዘኝ? ደሹጃው እንዲህ ኚባድ ነው? ሰውነቮ ምን ሆነ? ሳንባዬስ ምን ቜግር ገጠመው? ዹሚሉ ጥያቄዎቜ ተመላለሱብኝ። ‘ክሮንስ ዲዚዝ’ ዚሚባል በሜታ ተጠቂ ነኝ። በሆዮ ውስጥ ዹሚገኘው ዚሥርዓተ ልመት እራሱን በራሱ ያጠቃል። በጣም ኚባድ ዚጀና እክል እንደሆነ አውቃለው። • ዎክሳሜታሶን ኢትዮጵያ ውስጥ ጥቅም ላይ ስለሚውልበት ሁኔታ ባለሙያዎቜ ሐሳብ አቀሚቡ • ዎክሳሜታሶን ምን ያህል አስተማማኝ ነው? ኢትዮጵያ ውስጥስ ይገኛል? ይህንን በሜታ ለማኹም በዋነኛነት ጥቅም ላይ ዹሚውለው ህክምና ‘ኢሚዩኖሰፕሚሲቭ ቎ራፒ’ ዚሚባል ሲሆን መድኃኒቱ በሰውነቮ ውስጥ ያለውን ዚበሜታ መኹላኹል አቅም መቀነስ ነው ሥራው። ይሄ ደግሞ ለኢንፌክሜንና እንደ ኮሮናቫይሚስ ላሉ ዚመተንፈሻ አካላትን ለሚያጠቁ በሜታዎቜ ተጋላጭ ያደርገኛል። መጀመሪያ አካባቢ እንደ ትኩሳትና ዚድካም ስሜትን ዚመሳሰሉ ዚመጀመሪያዎቹ ዚኮሮናቫይሚስ ምልክቶቜ ሲሰሙኝ ብዙም አላሳሰበኝም ነበር። ምልክቶቹ እዚተባባሱ ሲመጡ ግን ጭንቅላቮ በጣም በሚያስፈሩ ሀሳቊቜ መሞላት ጀመሚ። ያነበብኳ቞ው አስፈሪ ዚሞት ዜናዎቜና ዚሆስፒታል መጚናነቆቜ ትዝ አሉኝ። ሆስፒታል መግባት ሊኖርብኝ ይሆን? ዚመተንፈሻ መርጃ መሳሪያ ያስፈልገኝ ይሆን? በቫይሚሱ ምክንያት ሕይወቮ ታልፍ ይሆን? እያልኩ ብዙ ተጚነኩኝ። በወቅቱ ኹነበሹው ሁኔታ አንጻር ሆስፒታል ሄዶ መመርመር ዚማይታሰብ ነው። ሆስፒታሎቜ በእጅጉ ተጹናንቀው ነበር። ነገር ግን አንድ ዶክተር በተቻለ መጠን እንድመሚመርና ሁኔታዎቜ እዚባሱ ኚሄዱ ድንገተኛም ክፍል ቢሆን እንድሄድ ነገሚኝ። ነገር ግን ኚስምንት ቀናት በኋላ ምልክቶቹ መቀነስ ጀመሩ። ኹዚህ በፊት ባለብኝ ዚጀና እክል ምክንያት እንዲዳኚሙም ተደርጎ ዹነበሹው በሜታ ዹመኹላኹል አቅሜ ቫይሚሱን ተዋግቶ አሞንፎታል። ይሄ ታሪክ ዚእኔ ብቻ እንዳልሆነ አስባለሁፀ በርካቶቜ ተጓዳኝ አስጊ ዚጀና እክሎቜ እያሉባ቞ው እንኳን ቫይሚሱን ማሾነፍ ቜለዋል። "ምንም እንኳን ሁኔታው በጣም አስፈሪ ቢሆንም ጥሩ ጥሩውን እያሰብኩ አሳልፌዋለው።" ኚድጃ እንግሊዝ ሊድስ ውስጥ ዚምትኖር ዹ25 ዓመት ወጣት ናት። ‘ታይፕ 1’ ዚሚባለው ዚስኳር በሜታ ታማሚ ነቜ። ጣፊያዋ ኢንሱሊን ዚሚባለውን ንጥሚ ነገር ማምሚት ስላቆመ በዶክተሮቜ አማካይነት ነው ኢንሱሊን ለሰውነቷ ዚሚሰጠው። "ልክ በቫይሚሱ ኚተያዙ ዚመሞት እድላ቞ው ኹፍተኛ ኚሆኑት ሰዎቜ መካኚል መሆኔን ሳውቅ በጣም ነበር ዚፈራሁት። ኮሮናቫይሚስ ሊይዘኝ ይቜላልፀ ቢይዘኝስ ምን እሆናለሁ እያልኩ ብዙ እጚነቅ ነበር።" በሆስፒታል ውስጥ በነርስነት ኚምታገለግል ኚእናቷ ጋር ዚምትኖሚው ኚድጃ ለቫይሚሱ ዚመጋለጥ እድሏ ኹፍ ያለ ነበር። ኚአራት ሳምንታት በፊትም አንዳንድ ዚቫይሚሱን ምልክቶቜ ማሳዚት ጀመሚቜ። ዚአጥንት መቆሚጣጠም፣ ዚትንፋሜ ማጠር፣ ደሚት አካባቢ ኚባድ ህመምና ትኩሳት ነበሚባት። "ልክ ምልክቶቹን ሳስተውል በጣም ፈራሁፀ ምክንያቱም በዜና ዹምሰማው ሁሉ ሞት ብቻ ነበር። በቫይሚሱ ተይዘው ስላገገሙ ሰዎቜ እምብዛም አይወራም ነበር። በጭንቅላቮ ቫይሚሱ ተገኝቶበት ወደ ሆስፒታል ዹሄደ ሰው በሙሉ እንደሚሞት ነበር ዚማስበው።" በመጀመሪያ ዹህክምና ባለሙያዎቜ ወደቀታቜን ተልኹው መጡ። ነገር ግን ወደ ሆስፒታል መሄድ እንደሌለብኝ ወስነው በቀት ለቀት ምርመራ እንደምካተት ነገሩኝ። ነገር ግን እሱም አልተሳካም። በሚያስገርም ሁኔታ ኚድጃ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ተሻላት። ኚቀት ባለመውጣ቎ም ደኅንነት ተሰምቶኛል ትላለቜ። ኚነባለቀቱ በበሜታው ተይዞ ዚዳነው ጆ ጆ ጀስትነር ደግሞ ‘ኒፍሮቲክ ሲንድሚም’ ዚሚባል ዚኩላሊት ቜግር አለበት። በፈሚንጆቹ 2000 ላይ ዚኩላሊት ንቀለ ተኹላ እስኚማካሄድም አድርሶታል ይሄው በሜታ። "ንቅለ ተኹላ ዹተደሹገላቾው ሰዎቜ ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቾውን ስሰማ እራሎን መኹላኹል እንዳለብኝ ተሰማኝ። ወደቀት ገባሁና እራሎን ኚሰዎቜ ንክኪ አራቅኩኝ" ይላል። ነገር ግን እራሱን ኚሰዎቜ ቢለይም ዚኮሮናቫይሚስ ምልክቶቜን ግን ማሳዚቱ አልቀሚም። ምናልባትም በሜታው ኹህክምና ባለሙያ ባለቀቱ ሳይዘው እንዳልቀሚ ይገምታል። እሷም አንዳንድ ምልክቶቜን ማሳዚት ጀምራ ነበር። "ሁለታቜንም ደሚታቜን አካባቢ መታፈን ይሰማን ነበር። ምናልባት ጭንቀቱ ሊሆን ይቜላል ብለን ነበር። ነገር ግን በሳምንቱ መጚሚሻ ላይ ደሹቅ ሳል ማሳል ጀመርኩ።" ጆ ትንሜ ቆይቶ ትኩሳትና ሌሎቜ ዚኮሮሚናቫይሚስ ምልክቶቜን ለማሳዚት ጊዜ አልፈጀበትም። "ለሚቀጥሉት ቀናት ጀናዬ ተቃወሰፀ ማሳልና ማስነጠሱም እስኚ አስሚኛው ቀን ድሚስ አልተወኝም ነበር። ቀስ በቀስ ግን እሱ እና ባለቀቱ ዚጀና ሁኔታ቞ው እዚተስተካኚለ መጣ። ሌላው ቀርቶ አስጊ ዚጀና ሁኔታ ውስጥ ያሉ ሰዎቜ እንኳን በቫይሚሱ ኚተያዙ በኋላ ቀላል ዚሚባሉ ምልክቶቜን ብቻ አሳይተው መዳን እንደሚቜሉ ተገነዘብኩ ይላል ጆ።
52293148
https://www.bbc.com/amharic/52293148
ኮሮናቫይሚስ፡ 300ሺህ አፍሪካውያን በኮቪድ-19 ምክንያት ሕይወታ቞ውን ሊያጡ ይቜላሉ-ዚአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሜን
ዚአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሜን ያለበቂ መኚላኚያ 300ሺህ አፍሪካውያን በኮሮና ምክንያት ህይወታ቞ውን እንደሚያጡ ይገመታል ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ላይ አስታወቀ።
ዚኮሮና ቫይሚስ በአፍሪካውያን ላይ ሊያደርስ ዚሚቜለውን ጉዳት በገመመገመበት በዚህ መግለጫ ኹሰው ህይወት በተጚማሪ ዚአህጉሪቷን ምጣኔ ኃብት እያሜመደመደው እንደሆነም አስፍሯል። በዚህ አመት ዚአህጉሪቱ ምጣኔ ሃብት በ3.2 በመቶ ያድጋል ተብሎ ዹተገመተ ቢሆንም ቫይሚሱ ባደሚሰው ጫና ምክንያት ምናልባት 1.8 በመቶ ሊያድግ ይቜላል ብሏል። ይህም ሁኔታ 27 ሚሊዮን ህዝብን ለሚሃብ እንደሚያጋልጥ ዚኮሚሜኑ መግለጫ ጠቁሟል። • መንግሥታት ኹተሜውን ኚኮሮናቫይሚስ ኢኮኖሚያዊ ጫና እንዲታደጉ ጥሪ ቀሹበ • ኢትዮጵያ ኚኮሮናቫይሚስ ምጣኔ ሐብታዊ ጫና ትተርፋለቜ? • አገራትን ጭምብል እስኚመሰራሚቅ ያደሚሳ቞ው ዚኮሮናቫይሚስ ዲፕሎማሲ ኮሚሜኑ ነገ ይፋ በሚያደርገው ሪፖርት ቫይሚሱ ካስተለው ቀውስ ጋር ተያይዞም ደካማ ዚሚባለው ዚአህጉሪቷጀና ስርዓት ለተጚማሪ ወጪ እንደሚዳሚግም አስገንዝቧል። እስካሁን ባለው መሹጃ በአህጉሪቷ ውስጥ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 16 ሺ ሲሆን 800 ሰዎቜም ህይወታ቞ውን አጥተዋልፀ ይህ ቁጥር እዚጚመሚ ሊሄድ ኚመምጣቱ ጋር ተያይዞ ዚአህጉሪቱ ዚጀና ስርአትም ጥያቄ ውስጥ እንደሚገባ መግለጫው አመላክቷል። ይህንንም ለመታደግ ዚመንግሥታት ቁርጠኝነት እንዲሁም ድጋፍ እንደሚገባም ዚኮሚሜኑ ዋና ፀሐፊ ቬራ ሶንግዌ ገልፀዋል። " ዚአህጉሪቱን ዚጋራ ብልጜግና ለመኹላኹልና ለመንባትፀ መንግሥታት ለዜጎቻ቞ው በአስ቞ኳይ መሰሚታዊ ፍላጎታ቞ውን ማቅሚብ እንዲቜሉ 100 ቢሊዚን ዶላር ያስፈልጋል" ብለዋል " ዚወሚርሜኙ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ቫይሚሱ በቀጥታ ኚሚያደርሰው ጉዳት ዹበለጠ ነው" ያሉት ፀሐፊዋ በአፍሪካ አገራት በአጠቃላይ ምጣኔ ሃብታ቞ው ቫይሚሱ እንደተኚሰተ መጎዳት መጀመሩን ገልጠዋል። "ወሚርሜኙን ለመኹላኹል ተብሎ ዹተቀመጠው አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ዚኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሎዎቜን እግር ተወርቜ አስሯል" ሲሉ አስሚድተዋል ዚኮሚሜኑ ሪፖርት አክሎም አነስተኛና መካኚለኛ ኢንተርፕራይዞቜ ድጋፍ ካልተደሚገላ቞ው በስተቀር ሙሉ በሙሉ እንደሚዘጉ አትቷል። ዚአፍሪካን ምጣኔ ሃብት 40 በመቶ ዹሚሾፍነው ዘይት በግማሜ ዋጋው መቀነሱን፣ በዋነኝነት አፍሪካ ወደውጪ ዚምትልካ቞ው ዹጹርቃ ጹርቅና አበባ ምርቶቜም መውደቃቾውን ጠቅሷል። ቱሪዝም ዚአንዳንድ ዚአፍሪካ አገራት አጠቃላይ ብሔራዊ ምርትን 38 በመቶ ቢይዝም አዹር መንገዶቜ ስራ቞ውን በማቋሚጣ቞ው ምክንያት ሙሉ በሙሉ ቆሟል ሲል ያትታል። ዚአፍሪካ ምጣኔ ሃብት ዚተሳሰሚ ነው ያለው ሪፖርቱ ለቀውሱም ዹምንሰጠው ምላሜ " ወደ አንድ ሊያመጣን ይገባል" ብሏል።
news-55321489
https://www.bbc.com/amharic/news-55321489
በትግራይ ለ2.3 ሚሊዮን ህፃናት እርዳታ ማድሚስ አልተቻለም- ዩኒሎፍ
በትግራይ ክልል ባለው ግጭት ምክንያት 2.3 ሚሊዮን ዹሚሆኑ ህፃናት ኚሰብአዊ እርዳታ አቅርቊት ውጪ መሆናቾውን ዚተባበሩት መንግሥታት አስተታወቀ።
"ኚእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ ስደተኛና ዹተፈናቀሉ ና቞ው። በአጠቃላይ ህፃናቱን መጠበቅ ቅድሚያ ሊሰጠው ዚሚገባ ሥራ ነው" በማለት ዚተባበሩት መንግሥታት ዹዓለም አቀፉ ዚህፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሎፍ) ኃላፊ አስታውቀዋል። ኚኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ዚሰብዓዊ እርዳታዎቜን ለማድሚስ ስምምነት ላይ ቢደሚስም ድርጅቶቹ በክልሉ ዚእርዳታ አቅርቊት ለማድሚስ አልተቻለም እያሉ ነው። ዚኢትዮጵያ መንግሥት ኚትግራይ ኃይሎቜ ጋር ዚገባበት ግጭት ዹተቀሰቀሰው ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም እንደነበር ይታወሳል። በዚህ ግጭት በሩካታ ሰዎቜ ተገድለዋል እንዲሁም ኹ60 ሺህ በላይ ዹሚሆኑ ወደ ጎሚቀት አገር ሱዳን መሰደዳ቞ው ይነገራል። "ለህፃናቱ ዹሚሰጠው እርዳታ አቅርቊት በዘገዹ ቁጥር፣ ምግብ፣ በቜጋር ለተጋለጡት ህፃናትን ለማደስ ዚሚያስፈልጉ አልሚ ምግቊቜ፣ ህክምና፣ ውሃ፣ ነዳጅና እና ሌሎቜም አስፈላጊ ነገሮቜ እያጠሩ ወደ ኹፋ ሁኔታ ያመራሉ" ብሏል ዩኒሎፍ ባወጣው መግለጫ። አክሎም "አፋጣኝ፣ ዘላቂ፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ማንንም ባላገለለ መልኩ ዚሰብዓዊ እርዳታ አቅርቊት ለዚትኛውም ቀተሰብ በያሉበት እንዲመቻቜ እንጠይቃለን" ብሏል ድርጅቱ። ድርጀቱ አክሎም "ባለስልጣናቱ ለደኅንነታ቞ው ፈርተው ዚሚሞሹ ንፁህ ዜጎቜን በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ መፍቀድ እንዳለበትና ይሄም ዓለም አቀፍ ጥበቃ ፈልገው ድንበር ዚሚያቋርጡትንም ያካትታል" ብሏል። ዚኢትዮጵያ መንግሥትም ሆነ ህወሓት በጉዳዩ ላይ ዚሰጡት አስተያዚት ዚለም። ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚሻኚሚ ዚመጣው ዚፌደራል መንግሥቱና ዚህወሓት ግንኙነት ዚማይታሚቅ ደሹጃ ደርሶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ዚትግራይ ልዩ ኃይል በክልሉ ዹሚገኘውን ዚመኚላኚያ ሰሜን ዕዝ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድሚሱን ተኚትሎ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ማዘዛቾው ይታወሳል። ለሊስት አስርት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በአገሪቱ መንግሥት ውስጥ ጉልህ ሚና ዚተጫወተው ህወሓት ኚሊስት ዓመት በፊት በተነሳው ፀሹ-መንግሥት ተቃውሞና ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣት ተኚትሎ ኹማዕኹላዊው መንግሥት መራቁ ዚሚታወስ ነው።
45365303
https://www.bbc.com/amharic/45365303
እውን ዚኢትዮጵያ መንግሥት ጥቁር ገበያውን ማሾጉ መፍትሄ ይሆነዋል?
ጎሚቀት ሃገር ኬንያ መዲና ናይሮቢ ነዋሪነቱን ያደሚገው ሄኖክ አበራ ዘመድ ጥዚቃ ወደ ተወለደባት አዲስ አበባ ኚማምራቱ በፊት ዚሚያደርገው አንድ ነገር አለፀ ዚኬንያ ሜንግልን ወደ ዶላር መቀዚር።
ኢትዮጵያ ሆቮል አካባቢ ዹሚገኝ ዚውጪ ሃገራት ግንዘብ ህጋዊ ባልሆነ መልኩ ይመነዘርበታል ተብሎ ዚታሞገ ሱቅ። «ናይሮቢ ውስጥ ዶላር መግዛትም ሆነ መሞጥ እጀግ በጣም ዹቀለለ ነውፀ ሊያውም በሕጋዊ መንገድ። እኔ አዲሳ'ባ ላይ ዶላሩን ሞቅ ባለ ዋጋ ስለምሞጠው አዋጭ ነው» ይላል ሄኖክ። «ማድሚግ ያለብህ መታወቂያህን ወይም ፓስፖርትህን ይዘህ ለውጭ ምንዛሪ ወደተዘጋጁ ወርደ ጠባብ ሱቆቜ መሄድ ብቻ ነው።» በእርግጥም ናይሮቢ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ በፍጥነት ኹሚኹናወኑ ተግባራት አንዱ ዶላር መግዛት እና መሞጥ ነውፀ ኚአዲስ አበባ እጅጉን በተለዹ መልኩ። • ዶላር በጥቁር ገበያ ለምን ቀነሰ? • ''ዚጫት ንግድና ዚዶላር ጥቁር ገበያ. . .ለግጭቶቜ ምክንያት ሆነዋል'' በኢትዮጵያ ሕጋዊ ባልሆነው ዹውጭ ምንዛሬ ገበያ ወይም ጥቁር ገበያ ዚዶላር ዋጋ ማሜቆልቆላ ማሳዚት ኹጀመሹ ሰንበትበት ብሏል። ኹሰሞኑ ደግሞ መንግሥት ጥቁር ገበያ ላይ ሲያገበያዩ ዹተገኙ ሱቆቜን እንዲሁም ሲያሻሜጡ ነበሩ ያላ቞ውን ግለሰቊቜ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተያይዞታል። ኢትዮጵያ ሆቮል አካባቢ በሰፊው ይንቀሳቀሱ ዚነበሩ ዚጥቁር ገበያ ዚደራባ቞ው አልባሳት መሞጫ ሱቆቜም 'ታሜጓል' በሚል ምክልት ዝምት ለብሰው ታይተዋል። እውን ጥቁር ገበያውን ማሾግ ዘለቄታዊ መፍሄ ነው? ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያ ዚሆኑት ዶክተር አዹለ ገላን «ጥቁር ገበያ ሊሠራ ዚማይቜል ነገር እንዲሠራ ያደርጋልፀ ወደ ሃገር ቀት ዚሚገቡ ዚካፒታልም ሆነ ዚጥሬ ዕቃ አቅርቊቶቜ ዚተሳኩ እንዲሆኑ ያደርጋልፀ ግለሰቊቜ ኢኮኖሚያዊ ቜግራ቞ውን እንዲቀርፉ ያደርጋል። ለዚህ ነው ጥቁር ገበያው ዚሚጫወተው ሚና ቀላል አይደለም ዚምንለው» ሲሉ ባለሙያው ያስሚዳሉ። «መንግሥት ጥቁር ገበያውን ሲዘጋ ሰዎቜ አማራጭ በማጣት ወደ ባንክ በመሄድ በኩፌሮላዊ መንገድ ይገበያያሉ ዹሚል እምነት አለው። ነገር ግን ጥቁር ገበያውን በእንዲህ ዓይነት መልኩ መግታት ይቻላል ዹሚል እምነት ዚለኝም።» «ዞሮ ዞሮ. . .» ይላሉ ዶክተር አዹለ «ዞሮ ዞሮ ዶላሩ ዚሚመጣው ኹውጭ ሃገር ነው። ሰዎቜ ካስፈለጋ቞ው ሕጋዊ መንገድ ሳይጠቀሙ ዶላሩን ብሩን በሰው በሰው ማዘዋወር ይቜላሉ። ወጣም ወሹደ በእንዲህ ዓይነት መልኩ ጥቁር ገበያውን ማሾነፍ አይቻልም።» ዶ/ር አዹለ ብቻ ሳይሆን ሌሎቜ ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያዎቜም መንግሥት ጥቁር ገበያውን በመሰል መልኩ ማሾነፍ እንደማይቜል ሃሰብ እዚሰነዘሩ ነው። ዚማክሮ እና ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚክስ ባለሙያ ዚሆኑት ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲው ፕሮፌሰር አለማዹሁ ገዳ ጥቁር ገበያው ዹሚሾፍነውን ክፍተት መደበኛው ገበያ ሊሾፍነው አይቜልም ሲሉ በትዊተር ገፃቾው ፅፈዋል። ወደ መፍትሄው. . . አሁን ትልቁን ጥያቄ ማንሳት ይቻላል። መንግሥት ጥቁር ገበያውን እንዎት ማሾነፍ ይቜላል። «ዚመንግሥት ፖሊሲ አውጭዎቜ ማሾነፍ ዚማይቜሉትን ጊርነት ኹመጀመር እንዎት ባለ ፖሊሲ ነው ጥቁር ገበያውን ማስወገድ ዚሚቻለው ዹሚለው ላይ ማተኮር አለባ቞ው» በላመት ዶክተር አዹለ ይተንትናሉ። «ይህ ዚሮኬት ሳይንስ አይደለምፀ ሌሎቜ ሃገራት አድርገውታል። ኢትዮጵያ አሁን ባለው ሁኔታ ዶላር ያስፈልጋታልፀ ዚዶላር እጥሚት አለ። እንዲህ ባለ አስ቞ጋሪ ወቅት ኚበድ ያለ እርምጃ መውሰድ ሊያስፈልግ ግድ ይላል።» ዶክተር አዹለ እንደ መፍትሄ ዚሚያቀርቡት 'መልቲፕል ኀክስጄንጅ ሬት' ዹተሰኘውን ሃሳብ ነው። «'መልቲፕል ኀክስጄንጅ ሬት' ማለት ለተወሰነ ጉዳዮቜ ቋሚ ዹሆኑ ዹውጭ ምንዛሪ ዋጋን መጠቀምፀ ለምሳሌ ዕቃ ኹውጭ ለሚያስመጡ እና ለሚልኩ። ጥሬ ገንዘብ ወደ ሃገር ቀት በሚገባበት ጊዜ ደግሞ ለእሱ ዹተለዹ ምንዛሬ መጠቀም ይቻላል።» ሁለት ዚተለያዩ ዹውጭ ምንዛሬ ዋጋዎቜን መጠቀም አስ቞ጋሪ አይሆንም ወይ ተብሎ ለቀሹበላቾው ጥያቄ ባለሙያው ሲመልሱፀ «ይሄ እኮ አዲስ ነገር አይደለም» ይላሉ። «እንዲህ ባለ አስ቞ጋሪ ጊዜ 'መልቲፕል ኀክስጄንጅ ሬት'ን መጠቀም ይፈቀዳልፀ ሌሎቜ ሃገራትም አድርገውታልፀ ነገር ግን ይህ ለተወሰነ ጊዜ ዹሚሆን እንጂ ለዘለቄታው አይደለም።» ዶክተር አዹለ ትንታኔያ቞ውን ሲቀጥሉ «በፍላጎት እና አቅርቊት ላይ ዚተመሚኮዘ ዚገንዘብ ፍሰት ኹተኹናወነ ጥቁር ገበያው ቢያንስ እንዲህ እንደ አሁኑ አይንሰራፋም።» ዶክተር አዹለም ሆነ ፕሮፌሰር አለማዹሁ በአንድ ጉዳይ ዚተስማሙ ይመስላልፀ መንግሥት ዚተሻለ ዚምጣኔ ፖሊሲ እንደሚያስፈልገው። ዶክተር አዹለ «መንግሥት ፈጠራ ዹተሞላቾው ዚምጣኔ ሃብት ፖሊሲዎቜን በመቅሹፅ ሊጠመድ እንጂ ኚጥቁር ገበያው ጋር ትንቅንቅ ውስጥ ሊገባ አይገባም» በማለት ሃሳባ቞ውን ይቋጫሉ። • ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ቀጣይ ፈተናዎቜ
48559840
https://www.bbc.com/amharic/48559840
ሞ ሳላህ ለሊቹርፑል መፈሹሙ በኹተማዋ ሙስሊም ጠልነት ቀነሰ
ሞሃመድ ሳላህ ለሊቹርፑል መፈሹሙን ተኚትሎ በኹተማዋ ሙስሊም ጠልነት መቀነሱን አንድ ጥናት ጠቆመ።
ስታንፎርድ ዩኒቚርሲቲ ያደሚገው ጥናት ሞሃመድ ሳላህ ለሊቹርፑል እግር ኳስ ክለብ መፈሹሙ በሊቹርፑል ኹተማ ሙስሊም ጠልነት በቀጥታ እንዲቀንስ ማድሚጉን አሚጋግጧል። ሳላህ ኚሁለት ዓመት በፊት ለሊቹርፑል ኹፈሹመ በኋላ በሊቹርፑል ኹተማ ዚሙስሊም ጠል ዹሆኑ ዚወንጀሎቜ ቁጥር በ18.9 በመቶ ቀንሰዋል። • በሞ ሳላህ ቅርጜ ዚተሰራው ሃውልት መሳቂያ ሆኗል • ሊቹርፑል ሞ ሳላህን ለፖሊስ አሳልፎ ሰጠ • ሞ ሳላህ ዚዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ ተጫዋቜ ኟኖ ተመሹጠ ታዋቂ ግለሰቊቜን ማወቅ እና ማድነቅ ጭንፍን ጥላቻን ይቀንሳል ወይ? ሞሃመድ ሳላህ በሙስሊም ጠልነት በባሕርይ እና አመለካኚት በመቀዹር ሚገድ ዹለው ተጜዕኖ ምን ይመስላል በሚል እርዕስ ነው ጥናቱ በስታንፎርድ ዩኒቚርሲቲ ዚተሠራው። በእንግሊዝ ጥላቻን መሠሚት ያደሚጉ ወንጀሎቜ እና 15 ሚሊዮን ዚትዊተር መልዕክቶቜን በጥናቱ ተንትነዋል። ጥናቱ ሊቹርፑል እግር ኳስ ቡድን በሚገኝበት ግዛት ውስጥ ሙስሊም ጠል ዚሆኑት ወንጀሎቜ ኚመቀነሳ቞ው በተጚማሪ ዚሊቚርቱል ክለብ ደጋፊዎቜ ፀሹ-እስልማና ይዘት ያላ቞ውን ዚትዊተር መልዕክት በግማሜ ቀንሷል። ጥናቱ ይህ አዎንታዊ ለውጥ ዚመጣው ሰዎቜ ስለ እስልምና ያላ቞ው እውቀት በመጚመሩ ነው ይላል።
news-54520360
https://www.bbc.com/amharic/news-54520360
ፔሩ ሰባት ወር ለጠበቀው ጃፓናዊ ታሪካዊ ስፍራዋን ብቻውን እንዲጎበኝ ፈቀደቜ
ፔሩ ዚኢንካ ህዝቊቜ ስልጣኔ ማሳያ ዹሆነውን ዚማቹ ፒቹን ታሪካዊ ስፍራ አንድ ጃፓናዊ ቱሪስት ብቻውን እንዲጎበኝ ክፍት አድርጋለቜ።
በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ኹአለም ቅርስ አንዱ ዹሆነው ዚማቹ ፒቹ ዚፍርስራሜ ስፍራ ተዘግቶ ዹነበሹ ሲሆን ጃፓናዊው ቱሪስትም ሰባት ወራት መጠበቅ ነበሚበት። ጄስ ታካያማ ስፍራውን ለመጎብኘት አቅዶ ዹነበሹው መጋቢት ወር ላይ ዹነበሹ ቢሆንም በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ጉብኝት በመኹልኹሉም ሳይሳካለት ቀርቷል። በቱሪዝም ዘርፉ በርካታ ጎብኝዎቜ ያሉት ጥንታዊው ዚኢንካ ኹተማ ፍርስራሜ በሚቀጥለው ወርም ላይ በጥቂት ሰዎቜ ለመክፈት ታቅዷል። ስፍራው ዚሚኚፈትበት ትክክለኛ ቀን ግን አልተገለፀም። ጄስ ታካያማ መጋቢት ወር ላይ ወደ ፔሩ ሲመጣ ይህንን ቅርስ ለመጎብኘት ዹነበሹ ቢሆንም በወሚርሜኙ ምክንያት መውጣት መግባት ባለመቻሉም በአቅራቢያው ባለቜ አጉዋስ በተባለቜ ኹተማም ለወራት ያህል ያለ ምንም መሄጃ ጠብቋል። በዚህም ምክንያት ዚባህል ሚኒስትሩ አሌሃንድሮ ኔይራ ብቻውን እንዲጎበኝ መፍቀዳ቞ውን ተናግሚዋል። "ፔሩ ዚመጣው ስፍራውን ዚመጎብኘት ህልም ስለነበሚው ነው" በማለትም ሚኒስትሩ በትናንትናው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግሚዋል። ጄስ ታካያማ ለሰባት ወር ጠብቆ ስፍራውን ሳይጎበኝ እንዳይመለስ በሚልም ቅዳሜ እለት ዚፍርስራሜ ስፍራውን እንዲጎበኝ ተደርጓል። በማቹ ፒቹ ተራራማ ስፍራም ላይ ሆኖ ለወራት ዹጠበቀውን ቊታ በመጎብኘቱ ዹተሰማውን ደስታም መግለፁንም በቀሹፀው ቪዲዮ አስተላልፏል። "ጉብኝቱ በጣም አስገራሚ ነበርፀ አመሰግናለሁ" በማለትም ጄስ መልእክቱን አስተላልፏል። በአንደስ ተራራዎቜ ዹሚገኘው ዚማቹ ፒቹ ስፍራ ዚኢንካ ግዛት ማሳያ ሲሆን በጎሮጎሳውያኑ 1450 እንደተገነባም ይታመናል። በዩኔስኮ ዹአለም ቅርስነት ዹተመዘገበው ይህ ስፍራ አለም ካላት ሰባቱ አስደናቂ ቅርሶቜም ዝርዝር ውስጥ ተካቷል። ወሚርሜኙ ኚተኚሰተባት እለት ጀምሮ በፔሩ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 849 ሺህ ሲሆን 33 ሺህ መሞታ቞ውንም ኚጆንስ ሆፕኪንስ ዹተገኘው መሹጃ ያሳያል።
news-55729086
https://www.bbc.com/amharic/news-55729086
በታይላንድ ንጉሥን ተቜተሻል ዚተባለቜ ሎት 43 ዓመት ተፈሚደባት
አንዲት ዚታይ ሎት ዚንጉሣዊያኑን ቀተሰብ ተቜተሻል በሚል 43 ዓመት እስራት ተፈርዶባታል።
በአገሪቱ ታሪክ ንጉሥን ለተቾ ይህ ትልቁ ዚእስር ውሳኔ ነው ተብሏል። አንቻን ዹሚል ስም ያላት ይቺ ሎት በማኅበራዊ ሚዲያ ዚድምጜ ፖድካስቶቜን ነበር ኹ7 ዓመታት በፊት ለሕዝብ ያጋራቜው። እሷ እንደምትለው እነዚህን ንጉሡን ዚሚተቹ ዚድምጜ ፋይሎቜ ዝምብላ ኚማጋራት ውጭ ያደሚገቜው ነገር ዚለም። ዚታይላንድ 'ልሮ ማጄስ቎' ሕግ በዓለም ላይ ጥብቅ ኚሚባሉት ሕጎቜ ዚሚመደብ ሲሆን በፍጹም ንጉሣዊያን ቀተሰቡን በማንኛውም ሁኔታ፣ ምንም ቢያደርጉ መተ቞ት ወይም ማጥላላት ወይም ነቀፋ መሰንዘርን ይኚለክላል። ታይላንድ ዚንጉሣዊ ዲሞክራሲ ሥርዓትን ዚምትኚተል አገር ስትሆን ይህ እንዲለወጥ በቅርብ ጊዜ ወጣቶቜ አደባባይ ወጥተው በመቃወማቾው ኚፖሊስ ጋር ተደጋጋሚ ግጭት ውስጥ ገብተው እንደነበር ይታወሳል። ተኚሳሜ አንቻን ንጉሡን ዚሚተቹ ድምጟቜ ያሉበትን ይዘት ኹ2014 እስኚ 2015 በዩትዩብና በፌስቡክ ስታጋራ በመቆዚቷ 29 ክሶቜ ተኚፍቶባት ስትኚራኚር ነበር። አንቻም ዚማይኚሰሱትን፣ ዚማይገሚሰሱትን ፍጹማዊውን ንጉሥ ተዳፍራቜኋል በሚል ኚተኚሰሱ 14 ሰዎቜ አንዷ ናት። አንቾም መጀመርያ ድርጊቱን በመፈጾሟ ዚተፈሚደባት ዹ87 ዓመት እስር ዹነበሹ ሲሆን ዚቅጣት ማቅለያ ተደርጎላት እስሩ በግማሜ ቀንሶላታል። ለብሔራዊ ደኀንነት በሚል ዚአንቻ ክሶቜ ይታዩ ዹነበሹው በዝግ ቜሎት ነበር።
news-55435608
https://www.bbc.com/amharic/news-55435608
እግር ኳስ፡ ዩናይትድ፣ አርሎናል፣ ቌልሲ . . . ምን አስበዋል?
ዚስፖርት ጋዜጊቜ ስለ እግር ኳስ ምን እያሉ ነው? በሚቀጥለው ጥር ዹሚኹፈተው ዹዝውውር መስኮትስ ምን ያሳዚን ይሆን?ዋና ዋናዎቹን በዚሀቜ አጭር ዘገባ እንዳስሳለን።
አላንድ አላንድ፡ ዚቊሩሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ኧርሊንግ ብራውት አላንድ ፈላጊው በዝቷል። አሁን ደግሞ ቌልሲዎቜ ተጫዋቹን ለማስፈሚም ዕቅድ እንዳላ቞ው እዚተነገሚ ነው። ነገር ግን ማን቞ስተር ሲቲዎቜ ተጫዋቹ ዚእኛ ነው እያሉ ነው። ይህን ዹዘገበው '90 ሚኒት' ጋዜጣ ነው። ቌልሲ አላንድንና ዚዌስትሃሙን ዮክሌን ራይስ ለማስፈሚም ሰባት ተጫዋ቟ቹን ሊሞጥ እንደሚቜል ስካይ ስፖርት ዘግቧል። ባርክሌይ፣ አሎንሶ፣ ሩዲገር፣ ክሪስ቎ንሰን፣ ጆርጊንሆ፣ ድሪንክዎተርና ሞሰስ ለገበያ ሊቀርቡ እንደሚቜሉ ተነግሯል። በሌላ በኩል ማን቞ስተር ዩናይትድም አላንድን ማስፈሚም ይፈልጋል። ነገር ግን ዚተጫዋቹ ወኪል ዹሆነው ሚኖ ራዮላ ኚዩናትድ ጋር ያለው ግንኙነት ሰላማዊ ስላልሆነ ቜግር ሊፈጥር ይቜላል እዚተባለ ነው ይላል ሚሹር ባወጣው ዘገባ። ዩናይትድ አላንድን ማስፈሚም ካልቻለ ፊቱን ወደ ኀቚርተኑን ዶሞኒክ ካልቚርት-ሌዊን ሊያዞር ይቜላል። ሩዲገር፡ ቌልሲ ሊሞጣ቞ው ካሰባ቞ው ተጫዋ቟ቜ መካኚል ዹሆነው ጀርመናዊው አንቶኒዮ ሩዲገር በፓሪስ ሎይንት ዠርሜይን ይፈለጋል። ይህን ያተመው ዚፈሚንሳዩ 'ለ ፓሪዚያ' ነው። ሊቚርፑል፡ ቀያዮቹ ዚሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ ተኚላካይ ኀደር ሚሊቶን ለማስፈሚም አቅደዋል። አርጀንቲናዊው ዹ34 ዓመት ተጫዋቜ እዝቄል ጋሬይም በሊቚርፑሎቜ እዚተፈለገ ነው። ይህን ዜና ያሰማው ዚስፔኑ ቶዶፊቻሄስ ነው። አርሎናል፡ ዚመድፈኞቹ አሠልጣኝ ማይክል አር቎ታ ዚሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ አጥቂ ቪኒሺዬስ ጁኒዬርን ወደ ኀሜሬትስ ለማምጣት አቅደዋል። ዹ22 ዓመቱ አጥቂ ወደ ኀሜሬትስ በሚቀጥለው ጥር ወር በውሰት ሊመጣ ይቜላል ተብሏል። አር቎ታ ኚወጣቱ አጥቂ በተጚማሪ ዹ28 ዓመቱን ስፔናዊ አማካይ ኢስኮፀ ይፈልገዋል። ነገር ግን ተጫዋቹ ወደ ዩቬንቱስ መሄድን ይመርጣል - 'ዹደይሊ ስታር' እንደዘገበው። ባርሎሎና፡ ዚካታሎኑ ክለብ ዹአርሮናሉን ተኚላካይ ሹኚርዳን መስጣፊን ይፈልገዋል ይላል 'ስፖክስ' ጋዜጣ። ዹ28 ዓመቱ ሙስጣፊ ኹአርሮናል ጋር ያለው ውል እዚተገባደደ ነው። ጆንስ፡ ዚደርቢ ካውንቲ አሠልጣኝ ዹሆነው ዋይኒ ሩኒ ዚቀድሞ ዚቡድን አጋሩ ፊል ጆንስን ማስፈሚም ይሻል። እንደ 'ሜትሮ' ዘገባ ኹሆነ በማን቞ስተር ዩናይትድ ቀት ዕድል ያጣው ጆንስ በዌስትብሮምም ይፈለጋል። ዚአውሮፓ እግር ኳስ ዹዝውውር መስኮት በሚቀጥለው ዚፈሚንጆቹ ጥር ወር ይኚፈታል። ማን ወደ ዚት ይሄዳል? ጊዜ ይፈታዋል።
50963338
https://www.bbc.com/amharic/50963338
ዹአንጎላ መንግሥት ዚቀድሞ ፕሬዝደንት ልጅ ዶስ ሳንቶስ ንብሚት በቁጥጥር ሥር እንዲውል አዘዘ
ዹአንጎላ ፍርድ ቀት ዚቀድሞ ዚሃገሪቱ ፕሬዝደንት ሎት ልጅ ቢሊዚነሯ ኢሳቀል ዶስ ሳንቶስ ንብሚት እና ባንክ ያላ቞ው ገንዘብ በቁጥጥር ሥር እንዲውል አዟል።
ነዳጅ ጠገቧ ሃገር አንጎላ ዚሙስናን አኚርካሪ እሰብራለሁ ብላ ቆርጣ ኚተነሳቜ ሰንበትበት ብላለቜ። ዚፕሬዝደንት ጃዎ ሎሬንሶ መንግሥት በኢሳቀል ዶስ ሳንቶስ እጅ ውስጥ ያለ 1 ቢሊዚን ዶላር አስመልሳለሁ እያለ ነው። • በባግዳድ ዚአሜሪካ ኀምባሲ ጥቃት ደሚሰበት • ስለ ሀብት ማውራት ነውር ዚሆነባት አገር • ኢንጂነር አዜብ ላይ ዹተመሰሹተው ክስ ኹ5.1 ቢሊዮን ብር ውል ጋር ዚተያያዘ ነው ኢሳቀል ዶስ ሳንቶስ እኔ በአባ቎ ዘመን ዚፈፀምኩት በደል ዹለም ንበሹቮም በቁጥጥር ሥር ሊውል አይገባም ስትል ስሞታ አሰምታለቜ። ኢሳቀል በአፍሪካ ሃብታሟ ሎት ዹሚል ስያሜ ዚተሰጣት ግለሰብ ናት። ፎርብስ ዹተሰኘው ዚቱጃሮቜ ገንዘብ ቆጣሪ መፅሔት ኢሳቀል 2.2 ቢሊዮን ሚብጣ ዶላር አላት ሲል ዚሃብት መጠኗን ይተነብያል። ዹ46 ዓመቷ ኢሳቀል ዶስ ሳንቶስ ሕይወቮ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በመስጋ቎ ነው በሚል ምክንያት ኑሮዋን ኹአንጎላ ውጭ አድርጋለቜ። ታላላቅ ኩባንያዎቜን በማስተዳደር ዚምትታወቀው ኢሳቀል አንጎላ እና ፖርቹጋል ውስጥ ትልቅ ድርሻ ያላ቞ው ድርጅቶቜ አሏት። ዹአንጎላ መንግሥት ግለሰቧ አንጎላ ውስጥ በሚገኙ ትላልቅ ድርጅቶቜ ውስጥ ያላት ዚአክስዮን ድርሻ እና ዚባንክ ደብተሯ ነው በቁጥጥር ሥር እንዲውል ያዘዘው። ኢሳቀልፀ ድርጊቱ በፖለቲካ ዹተሟሾ ነው ስትል ንብሚቷ በቁጥጥር ሥር እንዲውል መድሚጉን በክፉ አውግዛለቜ። ዶስ ሳንቶስ በግሪጎሪ አቆጣጠር 2016 ላይ አባቷ ዹአንጎላ ነዳጅ አውጭ ኩባንያ ኃላፊ አደርገው ሲሟሟት ነበር ወደ እውቅና ጣራ ዚተመነጠቀቜው። በቀጣዩ ዓመት ግን አባቷን ተክተው ወደ ሥልጣን በመጡት ፕሬዝደንት ጆሮ ፊሎሜኖ ዶስ ሳንቶስ ተባሚሚቜ።
news-45341285
https://www.bbc.com/amharic/news-45341285
ፍዚሎቜም «ኚፍትፍቱ ፊቱ» ይሉ ይሆን?
ፍዚሎቜ በተለይ ደስተኛ ገፅ ያለው ዹሰው ፊት ቀልባ቞ውን እንደሚገዛው በጥናቱ ተጠቁሟል።
ዚመርማሪዎቜ ቡድን ጥናቱን ለማካሄድ ኚተጠቀመባ቞ው መንገዶቜ አንዱ ዚተለያዩ ስሜቶቜን ዚሚያሳይ ዚአንድ ሰው ዚፊት ፎቶ በ1.3 ሜትር ርቀት አራርቆ በመስቀል ለፍዚሎቜ ማሳዚት ነው። ፍዚሎቜም ኚሌሎቜ በተለዹ ፈገግታ እና ደስታን በሚያሳዚው ፎቶ ዙሪያ እንደተኮለኮሉ ተነግሯል። • አቶ ታደሰ ካሳ፡ " ወሎዬ ነኝፀ መታወቂያዬም አማራ ዹሚል ነው" • ዹደሞዙን 100 እጥፍ በስህተት ዹተኹፈለው ሰው • ዚጊስ አውራ ዶሮ ወጣቶቜን አሳሰሚ በደስተኛው ገፅ ኚመሳብ በተጚማሪ ኚሌሎቜ ፎቶዎቜ በተለዹ ኹፍ ላለ ጊዜ እንዳጀኑት ተመስክሯል። ኚጥናቱ አድራጊዎቜ መካኚል አንዱ ዚሆኑት ዶ/ር አለን ማክኀልጋት ጥናቱ ዹሰው ልጅ ዚቅርብ ወዳጆቜ ኚሆኑት ውሟቜ እና ፈሚሶቜ በተጚማሪ ሌሎቜ እንስሳትም ዹሰውን ስሜት ዚማንበብ አቅም እንዳላ቞ው ፍንጭ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
news-46875227
https://www.bbc.com/amharic/news-46875227
ኚቀተሰቊቿ አምልጣ ካናዳ ዚገባቜው ዚሳዑዲዋ ወጣት፡ 'ምንም ዚሚጎልብኝ ዹለም'
ኚቀተሰቊቿ አምልጣ በካናዳ ጥገኝነት ያገኘ቞ው ዚሳዑዲዋ ወጣት ራሃፍ ሞሐመድ አል-ቁኑን ''ዚወሰድኩት እርምጃ አደገኛ ቢሆንም ትክክለኛ ውሳኔ ነው'' በማለት በካናዳ ነጻነት ዚሞላበት ህይወት እንደምትጀምር ተናግራለቜ።
ራሃፍ ሞሐመድ አል-ቁኑን ኚሶስት ቀናት በፊት ካናዳ መግባቷ ይታወሳል ዹ18 ዓመቷ ወጣት ኚቀናት በፊት ነበር ኚቀተሰቊቿ ጋር በጉዞ ላይ ሳለቜ ወደ አውስትራሊያ ለማምለጥ በማሰብ ባንኮክ ኹተማ በሚገኝ ሆቮል ውስጥ እራሷ ላይ በመቆለፍ ወደ ሳዑዲ አልመሰም ያለቜው። ራሃፍ በትዊተር ገጿ ላይ በምትለቃ቞ው ተንቀሳቃሜ ምስሎቜ ዚእስልምና ሀይማኖትን መካዷን እና ወደ ሳዑዲ ብትመለስ ጹቋኝ ናቾው ዚምትላ቞ው ቀተሰቊቿ ሊገድሏት እንደሚቜሉ ዚተናገሚቜው። • ዚሳዑዲ ሎቶቜ መሪ ጚበጡ • በሳዑዲ 'አንድ ወንድ እኩል ይሆናል ሁለት ሎት' • ሳዑዲ ሎቶቜ ወደ ስታዲዚም እንዲገቡ ልትፈቅድ ነው ዚወሰድኩት እርምጃ አደገኛ እንደሆነ ይገባኛል ይሁን እንጂ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ምንም ዚሚጎድልብኝ ነገር አይኖሹም ስትል ቶሮንቶ ስታር ለተሰኘ ጋዜጣ ተናግራለቜ። ''ዚህይወት ታሪኬን እና ዚሳዑዲ ሎቶቜ ዚሚደርስባ቞ውን በደል በይፋ መናገር እፈልጋለሁ። እንደ እቃ ነው ዚምንቆጠሚውፀ እንደ ባሪያ።'' ብላለቜ ራሃፍ። "ይህ ይሆናል ብዬ በጭራሜ አላሳብኩም ነበሚ። ዹሰው ልጆቜ መብት በሚኚበርባት ካናዳ ደህንነቮ እንደተጠበቀ ይሰማኛል።'' ስትልም ተናግራለቜ። ራሃፍ ኚወላጆቿ ጋር ወደ ኩዌት እዚተጓዘቜ ሳለ ነበር ዚአውስትራሊያ ቪዛ እንዳላት በመናገር በባንኮክ አድርጋ ወደ አውስትራሊያ ለመግባት ኚወላጆቿ ያመለጠቜው። ይሁን እንጂ ባንኮክ አዹር ማሚፊያ እንደደሚሰቜ ዚሳዑዲ ዲፕሎማት ፓስፖር቎ን ስለቀማኝ ጉዞዬን መቀጠል አልቻልኩም ብላ ነበር። ወንድሟና አባቷ ራሃፍን ወደ ሳዑዲ ለመመለስ ባንኮክ አዹር ማሚፊያ ድሚስ ሄደውም ነበር። ራሃፍ ባንኮክ ዹሆቮል ክፍል ውስጥ እራሷ ላይ ቆልፋፀ ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዚተለያዩ ሀገራት መንግሥታት እንዲታደጓት ጥሪ አቅርባ ነበር። ዚወጣቷ ጉዳይ ዚበርካቶቜን ቀልብ ስቊ ነበሚ። ዚታይላንድ መንግሥት በባንኮክ እንድትቆይ ፍቃድ ሰጥቶ ዹነበሹ ሲሆንፀ ዚተባበሩት መንግሥታትም ዚጥገኝነት ጥያቄዋን ሲያስፈጜምላት ነበሚ። ካናዳ ለራሃፍ ጥገኝነት በመስጠቷ ወጣቷ ኚሊስት ቀናት በፊት ቶሮንቶ ገብታለቜ። በቶሮንቶ አውሮፕላን ማሚፊያ ዚካናዳ ዚውጪ ጉዳይ ሚንስትርን ጚምሮ በርካታ ደጋፊዎቿ አቀባበል አድርገውላታል። ራሃፍ አል-ቁኑን ዹሚለውን ዚቀተሰብ ስሟን ኹዚህ በኋላ እንደማትጠቀምበት አስታውቃለቜ።
news-52589245
https://www.bbc.com/amharic/news-52589245
ኮሮናቫይሚስ፡ በዓለም ላይ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ አሃዝ ኚአራት ሚሊዮን በላይ ሆነ
ኚወራት በፊት በቻይናዋ ዉሃን ኹተማ ዹተቀሰቀሰውና ዚመተንፈሻ አካላትን እንደሚያጠቃ ዚተነገሚለት ዚኮሮናቫይሚስ ለዓለም ጀና ድርጅት ሪፖርት በተደሹገ በአራት ወራት ውስጥ አራት ሚሊዮን ሰዎቜን በበሜታው ተይዘዋል።
በሜታው በፍጥነት እዚተዛመተ ባለበት በአሁኑ ወቅት ቫይሚሱ ያለባ቞ው ሰዎቜ አሃዝ 4 ሚሊዮን 24 ሌህ ደርሷል። በዚህም መሰሚት እጅግ በጣም ኹፍተኛውን በበሜታው ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥርን ያስመዘገበቜው አገር አሜሪካ ስትሆን ኹ1,309,541 በላይ ሰዎቜ ቫይሚሱ እንደተገኘባ቞ው ተሚጋግጧል። በመኹተለም በቅደም ተኹተል ስፔን 223,578፣ ጣሊያን 218,268፣ ዩናይትድ ኪንግደም 216,525፣ ሩሲያ 198,676፣ ፈሚንሳይ 176,782 እና ጀርመን 171,324 ኹሁለተኛ እስኚ ሰባተኛ ደሹጃ ላይ ተቀምጠዋል። በወሚርሜኙ በተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ቀዳሚ ዚሆነቜው በሜታው በገደላቾውም አሃዝ ዚመጀመሪያው ሚድፍ ላይ ትገኛለቜ በዚህም ኹ77 ሺህ በላይ ዜጎቿ ለሞት ተዳርገዋል። ኮቪድ-19 ኚአውሮፓዊያኑን ኚዩናይትድ ኪንግደም፣ ኚጣሊያን፣ ኚስፔንና ኚፈሚንሳይም ኚእያንዳንዳ቞ው ኹ25 ሺህ በላይ ዹሚሆኑ ዚዜጎቻ቞ውን ህይወት ነጥቋል። ወሚርሜኙ ኚእስያ ወደ አውሮፓ ኚዚያም ወደ ሰሜን አሜሪካ ተዛምቶ ሺህዎቜን ያሚገፈ ሲሆን በርካታ ድሃ አገራት ዚሚገኙባ቞ውን አፍሪካና ደቡብ አሜሪካንንም አልማሚም። እስካሁን በእነዚህ አህጉራት ውስጥ ያደሚሰው ጉዳት ዹጎላ ባይሆንም በቀጣይ ሳምንታት ውስጥ ሊያስኚትል ዚሚቜለው ጉዳት ብዙዎቜን አስግቷል። እስካሁን ባለው አሃዝ በአፍሪካ ውስጥ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ 60 ሺህ ዹደሹሰ ሲሆን በዚዕለቱ ኚተለያዩ ዚአህጉሪቱ አገራት ዚሚወጣው መሹጃ እንደሚያመለክተው ዚበሜታው መስፋፋት ፍጥነት እዚጚመሚ በወሚርሜኙ ዚሚያዙትም ሰዎቜ ቁጥር በኹፍተኛ መጠን እያደገ ነው። ዚኮሮናቫይሚስ ኚመስፋፋት ፍጥነቱና እስካሁን በመላው ዓለም ለሞት ኚዳሚጋ቞ው ኹ277 ሺህ በላይ ሰዎቜ አንጻር ኹፍተኛ ስጋትን ዹደቀነ ቢሆንም በዚዕለቱ ኚበሜታው ዚሚያገግሙ ሰዎቜም እዚጚመሚ ነው። በዚህም መሰሚት በዓለም ዙሪያ ኚቫይሚሱ ያገገሙት ሰዎቜ ቁጥር በአሁኑ ውቀት ኹ አንድ ሚሊዮን 348 ሺህ በላይ ሰዎቜ ኚኮቪድ-19 ወሚርሜኝ ማገገማቾውን ዚጆንስ ሆፕኪንስ መሹጃ ያመለክታትል። አህጉሹ አፍሪካ በበሜታው ኚተያዙ 60 ሺህ ሰዎቜ መካኚል ኹ20 ሺህ ዚሚልቁት ኚቫይሚሱ ያገገሙ ሲሆን 2200 ያህ አፍሪካዊያን ደግሞ በወሚርሜኙ ህይወታ቞ውን አጥተዋል። አስካሁን በተለያዩ ዹዓለም አገራት ውስጥ በሜታውን ዹሚኹላኹል ክትባትና ዚሚፈውስ መድኃኒት ለመስራት ያልተቋሚጠ ጥሚት እዚተደሚገ ቢሆንም ዹተጹበጠ ውጀት ላይ ግን ገና አልተደሚሰም። ባለሙያዎቜ እንደሚሉትም መድኃኒት ወይም ክትባት ለማግኘት ወራት መጠበቅ ሳያስፈልግ አይቀርም። ነገር ግን ኚበሜታው ክስተት ጀምሮ በጀና ባለሙያዎቜ ዚሚመኚሩና ውጀታማ ዚቫይሚሱን መኚላኚያ መንገዶቜ ተግባራዊ ማድሚግ በአሁኑ ወቅት ብ቞ኛው አማራጭ እንደሆነ ነው። በዚህም መሰሚት ዚእጅን ንጜህና በውሃና በሳሙና በተደጋጋሚ በመታጠብ መጠበቅ፣ በርካታ ሰዎቜ ኚሚሰበሰቡባ቞ው ስፍራዎቜ እራስን ማራቅና በዚትኛውም ቊታ አካላዊ ርቀትን ሁሉንም ሳይነጣጥሉ ተግባራዊ በማድሚግ እራስንም ሆነ ሌሎቜን ኚበሜታው ለመጠበቅ ያለ አማራጭ ነው።
news-56826760
https://www.bbc.com/amharic/news-56826760
ዎሪክ ሟቪን በጆርጅ ፍሎይድ ዚግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተባለ
ዚቀድሞ ዚፖሊስ አባል ዎሪክ ሟቪን በጥቁር አሜሪካዊው ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ጥፋተኛ ነው ሲል ዚዳኞቜ ቡድን ብይን ሰጠ።
ዹ45 ዓመቱ ዎሪክ ሟቪን ኚወራት በፊት ጥቁር አሜሪካዊውን ጆርጅ ፍሎይድን በቁጥጥር ሥር ለማድሚግ ዚተጠርጣሪው አንገት ላይ ኹ9 ደቂቃዎቜ በላይ በጉልፈቱ አፍኖ ሲቆይ በተንቀሳቃሜ ምስል ተቀርጟ ነበር። ይህ ዚቀድሞ ዚፖሊስ አባል ተግባር በርካቶቜን አስቆጥቶ ዹነበሹ ሲሆንፀ ዚፖሊስ አባሉ አላስፈላጊ ኃይል ተጠቅሟል በሚል እና ዘሚኝነትን በመቃወም በመላው ዓለም ዹተቃውሞ ሰልፎቜ ተካሂደው ነበር። ሟቪን በአገሪቱ ዹወንጀል ሕግፀ በሊስት ዚግድያ ወንጀል ክሶቜ ነው ጥፋተኛ ሆኖ ዚተገኘው። ዚቀድሞ ዚፖሊስ አባል ዚእስር ፍርድ እስኪሰጠው ድሚስ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ይቆያል። ሟቪን ምናልባትም አስርት ዓመታትን በእስር እንዲያሳልፍ ሊፈሚድበት ይቜላል። 12 አባላት ያሉት ዚዳኞቜ ቡድን ዚቀድሞ ዚፖሊስ አባሉን ጥፋተኛ ለማለት ኚአንድ ቀን ያነሰ ጊዜ ብቻ ነበር ያስፈለጋ቞ው። ዳኞቹ ኹዚህ ብይን ኚመድሚሳ቞ው በፊት ዹ45 ምስክሮቜን ቃል ያደመጡ ሲሆን በርካታ ተንቀሳቃሜ ምስሎቜንም ተመልኚተዋል። ዚተኚሳሜ ጠበቆቜ እና ኚሳሜ ዐቃቀ ሕግም ለሊስት ሳምንታት ዹዘለቀ ክርክር አድርገው ነበር። ዚተኚሳሜ ጠበቆቜ ደንበኛቾው አካሉ ግዙፍ ዹሆነ እና ኚሊስት ዚፖሊስ አባላት ጋር ሲታገል ዹነበሹን ተጠርጣሪ በቁጥጥሩ ሥር ለማድሚግ ዹወሰደውን እርምጃ ዚትኛውም ዚፖሊስ አባል ሊያደርገው ዚሚቜለው ነው ሲሉ ተኚራክሚዋል። ጠበቆቜ ደንበኛቾውም ዚሚወስደው ተግባር በሙሉ በተንቀሳቃሜ ምስል እንደሚቀሚጜ ስለሚያውቅ ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ ሆነ ብሎ አይወስድም ብለዋል። ኚሳሟቜ በበኩላ቞ው ዎሪክ ሟቪን በጆርጅ ፍሎይድ አንገት ላይ ኹ9 ደቂቃዎቜ በላይ በጉልበቱ ተጭኖ ዚሚያሳዚውን ተንቀሳቃሜ ምስል በማጣቀስ "ዚምታዩትን እመኑ። ያያቜሁትን አይታቜኋል" ዚሟቪን ተግባር ዚፖሊስ ሳይሆን ግድያ ነው ብለውም ተናግሹዋል ኚሳሹ። ሁለቱ አካላት መኚራኚሪያ቞ውን ካቀሚቡ በኋላ 12 አባላት ያሉት ዚዳኞቜ ቡድን ምስጢራዊነቱ በተጠበቀ መልኩ ውሳኔያ቞ውን አስተላልፈዋል። ዚዳኞቹ ውሳኔ እንደተሰማ ኚፍርድ ቀቱ ውጪ ሆነው ዜናውን ሲጠባበቁ ዚነበሩት ሰዎቜ ደስታ቞ውን ገልጞዋል። ዹጆርጅ ፍሎይድ ቀተሰብ ጠበቃፀ ይህ በአሜሪካ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ዹኹፈተ ነው ብለዋል። ኚውሳኔው በኋላ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን እና ምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ ዹጆርጅ ፍሎይድ ቀተሰብ አባላት ጋር ስልክ ደውለዋል። ፕሬዝደንት ጆ ባይደንፀ ኚቀተሰቡ ጋር በነበራ቞ው ንግግርፀ "ቢያንስ አሁን ፍትህ አለ" ሲሉ ተደምጠዋል። ሟቪን ውሳኔውን በተመለኚት ይግባኝ እንደሚለው ዚአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በስፋት እዚገለጹ ይገኛሉ።
news-54157746
https://www.bbc.com/amharic/news-54157746
አሜሪካ፡ ዶናልድ ትራምፕ "ሳይንስ ምንም ዚሚያውቀው ነገር ዹለም" ሲሉ አጣጣሉ
በኅዳር ወር ለዳግም ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ቅስቀሳ ላይ ያሉት ዶናልድ ትራምፕ ማወዛገባ቞ውን ቀጥለዋል፡፡
ትናንት ዚሰደድ እሳት ዹበላውን ምዕራቡን ዚአሜሪካ ክፍል ለመጎብኘት ካሊፎርኒያ ነበሩ፡፡ ዚካሊፎርኒያ ሰደድ እሳት ሰፊውን ዚካሊፎርኒያ ግዛትን ብቻ ሳይሆን ኊሪጋንና ዋሺንግተን ግዛቶቜን ጭምር ያካለለ በታሪክ ሰፊ ቊታን ኹሾፈኑ ሰደድ እሳቶቜ አንዱ ነው፡፡ እሳቱ ዹበላው ጫካ ምን ያህል ይሰፋል ቢባል ኚሎንዶን ወይም ኚኒውዮርክ ኚተሞቜ በእጅጉ ዹላቀ ነው፡፡ ሁለቱ ኚተሞቜ ቢደመሩም ሰደድ እሳቱ ካካለለው ቊታ ያንሳሉ፡፡ ወይም ደግሞ 10 ኒውዮርክ ኚተማዎቜን ያክላል በመጠን፡፡ ወይም በሌላ አነጋገር በዹ 24 ሰዓቱ ዋሺንግተን ዲሲን ዚሚያህል መሬት በእሳት ይበላል፡፡ በሌላ አሐዛዊ አነጋገር ሰደድ እሳቱ ያወደመው ቊታ ስፋት ኹ2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ሆኗል፡፡ በእሳት አደጋው እስኚ አሁን 35 ሰዎቜ ሞተዋል፡፡ ዹዚህ ሰደድ እሳት ዋንኛ ምክንያት አዹር ንብሚት ለውጥ እንደሆነ ሳይንስ ቢናገርም ትራምፕ በሳይንስ ተሳልቀዋል፡፡ ኚካሊፎርኒያ ግዛት አስተዳዳሪዎቜ ጋር ዚተገናኙት ዶናልድ ትራምፕ ‹‹አይዟቜሁ እሳቱ በራሱ ጊዜ ይጠፋል› ብለዋ቞ዋል፡፡ እሳቱ ኹነሐሮ ወር መጀመርያ ዹጀመሹ ዛሬም ድሚስ አልጠፋም፡፡ ዹአዹር ንብሚት ለውጥ ብሎ ነገር ዹለም ዚሚሉት ዶናልድ ትራምፕ ለሰደድ እሳቱ ዋናው ምክንያት ዚጫካ አስተዳደር ድክመት ስለሆነ እሱን ማጠናኹር ነው ብለዋል፡፡ ዶናልድ ትራምፕ ዌስት ኮስትን ኹጎበኙ በኋላ ኚአካባቢው ኃላፊዎቜ ጋር በነበራ቞ው ውይይት አንድ ኃላፊ ሳይንስና ዹአዹር ንብሚት ለውጥ እስኚነ አካ቎ው ገሞሜ መደሹግ እንደሌለባ቞ው ሲያነሱ ዶናልድ ትራምፕ ሰውዹውን አቋርጠው ‹‹ሳይንስ ምን ያውቃል? ሳይንስ ምንም ዚሚያውቅልህ ነገር ዚለም›› ብለዋ቞ዋል፡፡ ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ኚፓሪሱ ዹአዹር ንብሚት ለውጥ ስምምነት እንድትወጣ ያደሚጉ መሪ ና቞ው፡፡ ኹዚህ ስብሰባ በኋላ አንድ ጋዜጠኛ ዶናልድ ትራምፕን ‹‹ለመሆኑ ዚሰደድ እሳት መልሶ መላልሶ ዚሚያጠቃን ጉዳይ ኹአዹር ንብሚት ለውጥ ጋር ዚተያያዘ ይሆን ወይ ሲል ጠይቋቾው ነበር፡፡ ‹‹አይደለምፀ ዋናው ዚጫካዎቜን አስተዳደር ማስተካኚል ነው›› ብለውታል፡፡
news-49202442
https://www.bbc.com/amharic/news-49202442
ሊቢያ ሊስት ዚስደተኛ ማቆያ ማዕኚላትን ልትዘጋ ነው
ሊቢያ በአገሪቱ ያሉ ሊስት ትላልቅ ዚስደተኛ ማቆያ ማዕኚላትን ልትዘጋ መሆኑን ዚአገሪቷ ዚውስጥ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ፋቲ ባሻጋ አስታወቁ። ማዕኚላቱ ሚስራታ፣ ታጆራ እና ኮምስ መሆናቾውም ተገልጿል።
ሚንስትሩ ይህን ያስታወቁት ባለፈው ስደተኞቜ ታጆራ ወደተባለው ማዕኹል እንዲመለሱ መደሹጋቾውን ተኚትሎ ባጋጠማ቞ው ትቜት ሲሆን ይህ ካምፕ በሐምሌ ወር በሚሳይል ተመትቶ ኹ20 በላይ ስደተኞቜ ሕይወት አልፏል። ኚሞቱት መካኚል አብዛኞቹ አፍሪካውያን ስደተኞቜ ናቾው ተብሏል። • ዚትሪፖሊ አዹር ማሚፊያ ዚሮኬት ጥቃት ሙኚራ ተሰነዘሚበት • በኢትዮጵያ ስላሉ ስደተኞቜ አንዳንድ ነጥቊቜ ማዕኹሉ በተባበሩት መንግሥታት ዹሚደገፈው መንግሥት እና ራሱን ዚሊቢያ ብሔራዊ ጩር ብሎ ዚሚጠራውን አማጺ ኃይል ለሚዋጉበት ቀጠና ቅርብ በመሆኑም እንደተዘጋ ተገልጿል። በሊቢያ ያለውን ሁኔታ ዚሚኚታተሉ ድርጅቶቜ ዚእነዚህ ማዕኚላት መዘጋት ሌሎቜ ዚስደተኛ ማዕኚላት ዹተጹናነቁ እንዲሆኑ ያደርጋል ብለዋል። ኹዚህ ባሻገርም በርካታ ስደተኞቜ በሕገወጥ ዚሰዎቜ አዘዋዋሪ እጅ ሊወድቁ እንደሚቜሉ ስጋታ቞ውን ገልፀዋል። ባለፈው ሳምንት ኚሊቢያ ወደ ጣሊያን ለመጓዝ ሲሉ 150 ስደተኞቜ ባህር ላይ ሰጥመው ሕይወታ቞ው ማለፉ ይታወሳል። በዚህ ዓመት በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ሰጥመው ኚሞቱት ይህ አደጋ ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው ስደተኞቜ ያለቁበት ነውም ተብሏል። ሊቢያ ለሚዥም ጊዜ ሲያስተዳድሯት ዚነበሩት ሙአመር ጋዳፊ እ.ኀ.አ በ2011 ኚሥልጣን ኚወሚዱ በኋላ በግጭት እዚታመሰቜ ሲሆን ዚተለያዩ ዹጩር አበጋዞቜ በሚቆጣጠሯ቞ው ሥፍራዎቜም ተኹፋፍላ ትገኛለቜ።
44812417
https://www.bbc.com/amharic/44812417
"መኖር ዹምፈልገው ልጆቌን ለማዚት ብቻ ነው"
ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ አዲስዓለም ሀድጉ ለ16 ዓመታት ኀርትራ ውስጥ ዚሚገኙትን ባለቀቱንና ሁለት ሎት ልጆቹን አላያ቞ውም።
ዚአዲስ ዓለም ትንሿ ልጁ ወታደር ናት ኚሁለት ዐሥርታት በላይ ተቋርጩ ዹነበሹው ዚኢትዮጵያና ኀርትራ ግንኙነት ወደ ሰላም መመለሱና ጊርነቱንም ለማቆም ዚፈሚሙት ስምምነት ተኚትሎ ዚአዲስዓለም ተስፋ ታደሰ። ቀተሰቊቹን በዓይነ ሥጋ ዚማግኘት ተስፋው አንሰራራ። በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚጀመር ዹሚጠበቀው ዹአዹር በሚራ ብዙ ቀተሰቊቜ እንዲናፍቁት ዚኟነውም ለዚሁ ነው። • ዚኢትዮጵያና ኀርትራን ዚአብሮነት እርምጃ ምን ይፈትነዋል? ለዓመታት ተቋርጩ ዹነበሹው ዚስልክ ግንኙነት መመለሱ ጋር ተያይዞ ብዙዎቜ ናፍቆታ቞ውን በስልክ ለመወጣት ቢሞክሩም በድንበሩ ጊርነት ትዳሩ ዹፈሹሰዉና ቀተሰቡ ለሁለት ዹተኹፈለው አዲስዓለም ግን አሁንም በጉጉት እዚጠበቀ ነዉ። በሁለቱ አገራት ጊርነት ምክንያት ኚመቶ ሺዎቜ በላይ ሰዎቜ ሕይወት ጠፍቷልፀ ኢኮኖሚያዊ ኪሳራን አስኚትሏልፀ ኹዚህም በላይ በሕዝቊቜ መካኚል መቃቃርን ፈጥሮ ዚጠላትነት ስሜት እንዲጎለብት አድርጓል። አዲስ ዓለም ዚደሚሰበትን ሁኔታ በአንደበቱ እንዲህ ይተርኚዋል። • ወደ አሥመራ ለመጓዝ ማወቅ ዚሚገባዎ 6 ነጥቊቜ ሁለት ወንድሞቌን በዚህ ጊርነት አጥቻለሁ። ዚጊርነቱ ጊስ ቀተሰቀንም አሳጥቶኛል። ኚባለቀ቎ ምፅላል ጋር ዚተጋባነው በ1972 ዓ.ም ነው። ሁለት ሎትና አንድ ወንድ ልጅም አፍርተናል። በ1994 ዓ.ም ወደ ኀርትራ ሁለት ሎት ልጆቌን ይዛ ኚሄደቜ በኋላ ተያይተን አናውቅም። ኀርትራዊ በመሆንዋ ኚምታስተምርበት ሥራ ስትባሚርፀ ካገርም ሊያባርሯት ይቜላሉ ብዬ ኹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያዊ አግብታ እንደምትኖር ወሚቀት አዘጋጅቌ ነበር። ኚአንድ ዓመት በፊት ግን ኀርትራ ባካሄደቜው ሕዝበ-ውሳኔ ላይ በኔ ተነሳሜነት ለነፃነት ድምፅ ሰጥታ ነበር። በወቅቱ እሷ ስጋት ቢኖርባትም ልጆቌ አባታ቞ው ኚትግራይ መሆኑን እናታ቞ው ደግሞ ኚኀርትራ መሆኗን እንዲያውቁ በማለት አደፋፍሬያት ድምፅ ሰጠቜ። ይህ ሕዝበ-ውሳኔም ሥራዋን እንድታጣና ኀርትራም እንድትሄድ ምክንያት ሆነ። ትዳራቜንም አኚተመ። ዚሞትኩ ያህል ነበር ዹመሰለኝ ትናንትና ዹተፈጠሹ በሚመስል ሁኔታ ዹሆነውን በዝርዝር አስታውሰለሁ። ቀኑ ሮብ ነበርፀ ባለቀ቎ አጎቷን ለመጠዹቅ ሌላ ኹተማ እንደምትሄድ ነገሚቜኝ። አጎቷም ቀት አልሄደቜ። ልጆቌን ይዛ ኀርትራ ገባቜ። ኀርትራ ለመሄድ አቅዳው ዹነበሹ ቢሆንም ለኔ ግን ምንም ያለቜኝ ነገር አልነበሚም። ሰማይ ዚተደፋብኝ መሰለኝፀ በሕይወት መኖሬ ትርጉሙ ጠፋኝ። ኀርትራ ውስጥ ይህ ነው ዚምትለው ቀተሰብ ባይኖራትም ዚስደተኞቜ መጠለያ ማዕኹል ውስጥ ገባቜ። ዚሁለቱም ሀገራት ድንበር በመቋሚጡ ተኚትያትም መሄድ አልቻልኩምፀ ዚሞትኩ ያህል ነው ዚተሰማኝ። በኢትዮ-ኀርትራ ጊርነት ኚመቶ ሺዎቜ በላይ ህይወታ቞ውን አጥተዋል። ደብዳቀዬ ምላሜ አልነበሹውም ባለቀ቎ ሳትነግሚኝ በድንገት መሄዷ ለቀተሰቊቌ አልተዋጠላ቞ውም። "አንድ ነገር ብታደርጋት ነው እንጂ እንዲህ ብን ብላ አትጠፋም ነበር" ይሉኝ ነበር። እኔ ግን ምንም እንዳልበደልኳት አውቃለሁ። በጣም ዚምንዋደድና ዚምንኚባበር ባልና ሚስት ነበርን። ቀታቜን ሳቅና ደስታ ተለይቶት አያውቅም ነበር። ስትሄድ ጎሚቀቶቌ ጋር ዚተወቜልኝ ደብዳቀ ሲሆን "መለያዚት ኚሞት በላይ እንደሚኚብድ አውቃለሁፀ ሆኖም ልጆቌን á‹­á‹€ ሄጃለሁ። ወንዱ ልጃቜንን አንተ ጋር ትቌዋለሁ። አጋጣሚውን ካገኘሁ ደብዳቀ እጜፍልኞለሁፀ ለማንኛውም እራስህን ጠብቅ" ዹሚል ነው። • ዚኢትዮጵያና ኀርትራ ግንኙነት ኢኮኖሚያዊ ትርፍ? ለሳምንት ያህል ሐዘን ተቀምጫለሁፀ ጎሚቀቶቌም ሊያፅናኑኝ ቢሞክሩም ለኔ ሕይወት ያኚተመቜ መስሎ ነበር ዚተሰማኝ። እንዳበደ ሰው በቁሜ ዚሞትኩ ያህል ይሰማኝ ነበር። ዚባለፉትን ዓመታት በቃላት ልገልጻ቞ው አልቜልም። ሐዘኑን ለመርሳት ምርጫዬ ዹነበሹው መጠጥ ብቻ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ወደ ኀርትራ ኚመሄዳ቞ው በፊትፀ ሁለቱ አገራት ዹሰላም ስምምነት ይኖራ቞ዋል ዹሚል ሐሳብ አልነበሚኝም። በፍፁም! • ዚትናንትናዋ እለት- በኢትዮ ኀርትራ ግጭት ቀተሰባ቞ው ለተለያዚ? ባለቀ቎ም ሆኑ ልጆቌ እድሉን አግኝተው ወደ ውጭ ሀገር ቢሄዱ መገናኘት እንደምንቜል ተስፋ አደርግ ነበር። በቀይ መስቀል በኩል በተኚታታይ ደብዳቀ ብጜፍም ምላሜ አላገኘሁም። ተስፋ ስለቆሚጥኩም ዹኋላ ኋላ መጻፍ አቆምኩ። ሁልጊዜም ግን ወደፊት አንድ ቀን ግን ባለቀ቎ን አግኝቻት ለምን ትታኝ እንደሄደቜ መጠዹቅ እፈልግ ነበር። በኀርትራ ዹሚገኘው ይህ መካነ-መቃብር ዚጊርነቱ አሰቃቂነት ማስታወሻ ነው። ልጄ! ሎቶቜ ልጆቌን በፌስቡክ ለማግኘት እዚሞኚርኩ በነበርኩበት ወቅት ትንሿ ሎት ልጄ ዳናይት በፌስቡክ መልእክት ላኚቜልኝ። "በድምፅ ልናዋራህ አንቜልምፀ ግን ሁልጊዜም ቢሆን እናስብኻለን" ዹሚል ነበር። እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም። ናፍቆቮ ኚቃላት በላይ ነበር። ኚጥቂት ጊዜ በኋላ ኹቮክኒክ ኮሌጅ ተመርቃ ሳዋ ወታደራዊ ካምፕ ስትገባ ግንኙነታቜን ተቋሚጠ። ወታደር በመሆኗ ስልክ ስለማይፈቀድ መገናኘታ቞ንም ዚመይታሰብ ሆነ። ኹዚህ በኋላ ሕይወት እንዎት ሾክሟ እንደኚበደብኝ! ደግሞም ሁሉንም ልጆቌን ብወዳ቞ውም ለምን እንደሆነ አላውቅም ለትንሿ ልጄ ያለኝ ፍቅር ይለያል። እንዎት ብዬ እንደምገልፃት አላውቅም። አስተዋይ፣ ኚዕድሜዋ በላይ አሳቢ፣ ዚራሷ ያልሆነ ነገር ዚማትወድ ንፁህ ልጅ ናት። ልጆቌን ማግኘት ዚዚዕለት ምኞቮ ነው። አንድ ቀን ተገናኝተን ዹዚህ ሁሉ ዓመታት ዚልብ ናፍቆታኝንና ያሳለፍነውን መጥፎ ታሪክ በለቅሶ እንዲወጣልን እመኛለሁ። ዚስልክ አድራሻ቞ውንም እዚፈለግኩ ነው። አሁን ዹ58 ዓመት ዕድሜ ባለፀጋ ነኝ። ኹዚህ በላይ ዹመኖር ፍላጎቱ ዚለኝም። ልጆቌንና ባለቀ቎ን ዳግመኛ ዚማገኝበትን ቀን ለማዚት ብቻ ነው መኖር ዚምፈልገው። • ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አዲስ ምዕራፍ • ሊገዳደሉ ኚአንድ ጩር አውድማ ዹተገኙ ወንድማማ቟ቜ ዚአዲስዓለም አዲስተስፋ ልጆቌን በህልሜ አያ቞ዋለሁ። ባለፈው ዕሁድ ኀርትራውያን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድን ሲቀበሉ ልጆቌንና ባለቀ቎ን ያዚሁ ነው ዚመሰለኝ። ቀተሰቀንና ዚድሮ ጓደኞቌን አግኝቌ አዲስ ሕይወት ለመጀመር ወደ ኀርትራ መሄድ እፈልጋለሁ። ልጄም እናቱንና እህቶቹን እንዲያገኝ እፈልጋለሁ። ዚልጆቌን እጆቜ መንካት፣ ፀጉራ቞ውን መዳበስና ጠሹናቾውን ማሜተት ይናፍቀኛል። አሁን ትልቅ ሰውም ስለሆንኩ "አባዬ አለንልህ!" እንዲሉኝ እሻለሁ። ይህቺ ቀን ኚመጣቜ ለኔ ዳግም ውልደቮ ናት።
news-55036279
https://www.bbc.com/amharic/news-55036279
ዘ ዊኬንድ ዚግራሚ ሜልማት "ሙሰኛ" ነው ሲል ተናገሹ
ካናዳዊው ሙዚቀኛ ዘ ዊኬንድ፣ አቀል ተስፋዬ በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ዘንድ ኹፍተኛ ስፍራ ዹሚሰጠውን ዚግራሚ ሜልማት ሙሰኛ ነው አለ።
ኹዚህ ቀደም ዚግራሚ ሜልማቶቜን ያሞነፈው ዘ ዊኬንድ ለዘንድሮው ዓመታዊ ዚግራሚ ሜልማትም አልታጚም። ሙዚቀኛው ያወጣው አልበም ኹፍተኛ ተቀባይነትን ማግኘቱን ተኚትሎ እንዲሁም በተለይም በአልበሙ ዚተካተተው 'ብላይንዲንግ ላይትስ' ዹተሰኘው ዜማው ተወዳጅ ዹሙዚቃ ሰንጠሚዊቜን በአንደኛ ደሹጃ መምራቱን ተኚትሎ ለግራሚ ሜልማት መታጚት ብቻ ሳይሆን በርካታ ሜልማቶቜን ያሞንፋልም ተብሎ ተጠብቆ ነበር። "ዚግራሚ ሜልማት አሁንም ቢሆን ሙሰኛ ነው" በማለት በትዊተር ገፁ ላይ ያሰፈሚው ሙዚቀኛው አክሎም "ለእኔም፣ ለአድናቂዎቌም ሆነ ለሙዚቃ ኢንዱስትሪው ሲባል ግልፅነትን እንጠብቃለን" ብሏል። ዚግራሚ ሜልማት ኃላፊዎቜ በበኩላ቞ው ዹሙዚቀኛውን ቅር መሰኘት እንደተሰማ቞ው ገልፀው ነገር ግን በዚዓመቱ ድንቅ ቜሎታ ያላ቞ው ሙዚቀኞቜም ሜልማት ላያገኙ ይቜላል በማለት ምላሜ ሰጥተዋል። 'አፍተር ሃወርስ' ዹተሰኘው አልበሙ ኹፍተኛ ሜያጭ በማስመዝገብ ዚዓመቱን ክብሚ ወሰን ዹጹበጠ ሲሆን 'ብላይንዲንግ ላይትስ' ዹተሰኘውና በዚህ አልበም ዚተካተተው ሙዚቃው በአሜሪካ ዹሙዚቃ ሰንጠሚዥን ለሚዥም ጊዜ በመቆጣጠር ኚአስሩ ምርጥ ተካቷል። ኚኢትዮጵያዊ ቀተሰቊቜ በካናዳ ተወልዶ ያደገው ዘ ዊኬንድ (አቀል ተስፋዬ) በቅርቡ በሙዚቃው ስፍራ ትልቅ ቊታ ዚሚሰጣ቞ውን ኀምቲቪ፣ ቪኀምኀና ዚአሜሪካ ዹሙዚቃ ሜልማቶቜን አግኝቷል። በዚካቲት ወርም በአሜሪካውያን ዘንድ ኹፍተኛ ስፍራ በሚሰጠው ሱፐር ቩውል ዚእግር ኳስ ጚዋታ በእሚፍት ሰዓት ላይ ይዘፍናል ተብሎ ይጠበቃል። በርካታ ዚአሜሪካ ሚዲያዎቜም ሪፖርት እንዳደሚጉት ሙዚቀኛው ኚሜልማቱ እንዲወጣ ዹተደሹገው በሱፐር ቩውል በመዝፈኑ ነው ተብሏል። በሱፐር ቩውል እንዲዘፍን ዚተለያዩ ስምምነቶቜ ላይ መደሚሱንና ገደብም ተቀምጧል ቢባልም ዚሜልማቱ አዘጋጆቜ በበኩላ቞ው ዹሙዚቀኛው ለግራሚ ያልታጚው ኚእነዚህ ስምምነቶቜ ጋር በተያያዘ ነው ዹሚለውን አይቀበሉትም። ዹዚህን ዓመት ዚግራሚ ሜልማትን እጩነትን ዚምትመራው ቢዮንሎ በዘጠኝ ዘርፍ ሲሆንፀ ኚእሷ በተጚማሪም ዱዋ ሊፓ፣ ቮይለር ስዊፍትና ሮዲ ሪቜም በስድስት ዘርፎቜ ታጭተዋል።
news-55391890
https://www.bbc.com/amharic/news-55391890
ኮሮናቫይሚስ፡ በፈሚንሳይና በዩናይትድ ኪንግደም ድንበር ላይ ዚኚባድ መኪኖቜ እንቅስቃሎ ተገታ
ኚአንድ ሺህ አምስት መቶ በላይ ኚባድ ጭነት መኪኖቜ ዩናይትድ ኪንግደምን ለቆ ለመውጣት ዚፈሚንሳይ ድንበር ለንግድና ለጉዞ እስኪኚፈት ድሚስ በኬንት ኹተማ መቆማቾው ተገለፀ።
ፈሚንሳይ አዲሱን ዚኮሮናቫይሚስ ዝርያ በመፍራት ኚእሁድ ዕለት ጀምሮ ለ48 ሰዓታት ድንበሯን ዘግታለቜ። በአሁኑ ሰዓት ኹ50 በላይ አገራት ኚዩናይትድ ኪንግደም ዚሚመጡ ተጓዊቜ ወደ አገራ቞ው እንዳይገቡ ኚልክለዋል። ዚኚባድ መኪና አሜኚርካሪዎቹ እንዲንቀሳቀሱ ለማድሚግ ዚተለያዩ መፍትሔዎቜ እዚታሰቡ ሲሆን አንደኛው አሜኚርካሪዎቹ ዚኮቪድ-19 እንዲመሚመሩ ማድሚግ ነው ተብሏል። ይህ በእንዲህ እዳለ ዚአውሮፓ ሕብሚት ኮሚሜን አገራት ዚጣሉት ዹጉዞ ገደብ እንዲያነሱ ጠይቋል። ለአውሮፓ አባል አገራት በቀሹበ ምክሹ ሃሳብ ላይ ዚአውሮፕላን እና ዚባቡር ጉዞ ላይ ዚተጣለው ገደብ ዚአቅርቊት እጥሚት እንዳይፈጠር በሚል እንዲነሳ ተጠይቋል። ነገር ግን ኮሚሜኑ እንዳለው ኹሆነ አስፈላጊ ያልሆኑ ጉዞዎቜ አሁንም ቢሆን መበሚታታት ዚለባ቞ውም። ዚአውሮፓ ሕብሚት አባል አገራት በሙሉ አዲሱን ቫይሚስ በመፍራት ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ሆነ ኚአገሪቱ ዹሚደሹጉ ጉዞዎቜን አቋርጠዋል። ዚአውሮፓ ሕብሚትም ዚተባበሚ ምላሜ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እዚመኚሚ ይገኛል። በአሁኑ ጊዜ ወደ ፈሚንሳይ ኚዶቚር ወደብም ሆነ ኚዩሮታነል ዚሚነሳ ተሜኚርካሪ ዚለም። ዹአገር ውስጥ ሚኒስትሩ ፕሪቲ ፓቮል እንዳሉት ኹሆነ 650 ኚባድ ዚጭነት መኪኖቜ በኀም 20 እንዲሁም ተጚማሪ 873 ደግሞ በኚባድ ተሜኚርካሪዎቜ ማቆሚያ ስፍራ ይገኛሉ። ዚአውሮፓ አገራት ድንበሮቻ቞ውን ዚዘጉት አዲሱ አይነት ቫይሚስ መኚሰቱን እና በፍጥነት መስፋፋቱን ዚዩናይትድ ኪንግደም ኹፍተኛ ተመራማሪ ካስጠነቀቁ እና "በዚትኛውም ስፍራ" እንደሚገኝ ካሳወቁ በኋላ ነው። ሰር ፓትሪክ ቫላንስ አክለውም በእንግሊዝ ተጚማሪ ክልኚላዎቜ ያስፈልጋል ብለዋል። በእንግሊዝ 17 ሚሊዮን ሰዎቜ በጥብቅ ዚኮቪድ-19 ክልኹላ ውስጥ ና቞ው። ደሹጃ አራት ዚእንቅስቃሎ ገደብ ኚተጣለባ቞ው አካባቢዎቜ ዚሚንቀሳቀሱ ሰዎቜም በዌልስና በተወሰኑ ዚእንግሊዝ ኚተሞቜ ሲደርሱ ራሳ቞ውን አግልለው እንዲቀመጡ ተደንግጓል። ፓቮል እንዳሉት ዚተስተጓጎለውን ዚተሜኚርካሪዎቹን እንቅስቃሎ ለማስቀጠል በዩናይትድ ኪንግደም እና በፈሚንሳይ መካኚል "መፍትሔ ለመፈለግ" ንግግሮቜ እዚተደሚጉ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ቊሪስ ጆንሰን እና ዚፈሚንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኀል ማርኮን ሰኞ ዕለት ዚተነጋገሩ ሲሆን እንደመፍትሔ ኚዩናይትድ ኪንግደም ወደ ፈሚንሳይ ዚሚመጡ አሜኚርካሪዎቜ ተመርምሹው ኚኮቪድ-19 ነጻ መሆናቾው መሚጋገጥ አለበት ብሏል። ፓቮል ዚኚባድ መኪና ሟፌሮቹን ኮሮናቫይሚስ መመርመር "ዚንግግሩ አካል ነበር" ካሉ በኋላ "ዚምርመራ ውጀቱን በፍጥነት ማግኘትና ጉዞን ማቀላጠፍ በአንጻራዊነት ፈጣን ነው" ብለዋል። በቊሪስ ጆንሰን እና በማርኮን ዹተደሹሰው ስምምነት ኚሚቡዕ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል። በዩሮ ታነል ኃላፊዎቜ ማክሰኞ እለት 2500 ዚጭነት ተሜኚርካሪዎቜ እንዲሁም ተመሳሳይ ቁጥር ያለው መኪና ሚቡዕ ዩናይደትድ ኪንግደም ይደርሳሉ ብለው እንደሚገምቱ ተናግሚዋል። ዚድንበር መዘጋቱ በአውሮፕላን፣ በመርኚብ እንዲሁም በባቡር ኚዩናይትድ ኪንግደም ወደ ፈሚንሳይ ዹሚጓዙ መንገደኞቜን አስተጓግሏል። ዩሮታነል እንዳለው ኚዩናይትድ ኪንግደም ወደ ፈሚንሳይ ዚሚሄዱ መንገደኞቜ ስምምነት ላይ ኹተደሹሰ ሚቡዕ እና ሐሙስ መፍትሔ ሊያገኙ ይቜሏሉ። ዚብሪታንያ አዹር መንገድም በአነስተኛ ቁጥር በሚራ እንደሚጀምር አስታውቋል።
news-44150233
https://www.bbc.com/amharic/news-44150233
ኬንያ፣ ኡጋንዳና ታንዛኒያ ተጚባጭ ያልሆነ መሹጃ ላይ ዘመቻ ጀመሩ
ለምስራቅ አፍሪካ አዲስ ዹሆነውና በኬንያ ዚወጣው አዋጅ ተጚባጭ ያልሆነ መሹጃ ዚሚያሰራጩ ሰዎቜ ላይ እስራትን ያስኚትላል።
ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ አዲሱ ህግ ዚሳይበር ጥቃት ዚሚያደርሱ ወንጀለኞቜን በህግ ለመጠዹቅ ያስቜላል ብለዋል። አዋጁ 50000 ዚአሜሪካ ዶላር እና እስኚ ሁለት ዓመት ዚሚደርስ ቅጣት ያስኚትላል። አዋጁ በኮምፒውተርና በኢንተርኔት አማካኝነት ዹሚፈፀሙ ወንጀሎቜን ለመቆጣጠር በሚል ዚወጣ ቢሆንም በኬንያ፣ በኡጋንዳ እና በታንዛኒያ ዚወጡት ህጎቜ ነጻ ሚዲያዎቜን ለመቆጣጠር ዹተዘሹጉ አዲስ ዘዎዎቜ መሆናቾውን ተቺዎቜ ይሞግታሉ። ዚጋዜጠኞቜ መብት ተሟጋ቟ቜ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ ያፀደቁት አዋጅ ሃሳብን በነፃ ዹመግለፅንና ዚፕሬስ ነፃነትን ይፃሚራል ሲሉ ህጉን ተቃውመዋል። አዋጁ ዚሚድያ ነፃነትን ኚመጋፋቱም በላይ ኬንያ ሚዲያን ዹተመለኹተ ህግ እያላት ለምን ተጚማሪ አዋጅ ማውጣት አስፈለጋት ሲሉ ጠይቀዋል። ፕሬዚደንቱ በበኩላ቞ው አዋጁ ዚሳይበር ጥቃትን ለመኚላኚል፣ ዚህፃናት ዚወሲብ ፊልሞቜን፣ ዚኮምፒውተር ጥቃትንና መሹጃ ምንተፋን ለመቆጣጠር ይውላል ብለዋል። ዚኬንያ ሚዲያ አዲሱን ህግ ስራ቞ውን እንደሚቆጣጠር አዲስ ዘዮ አይተውታል በበርኒንግሃም ዩኒቚርሲቲ ዚዲሞክራሲ ፕሮፌሰር ዚሆኑት ኒክ ቺዝማን ተጚባጭ ያልሆኑ መሚጃዎቜን ለመቆጣጠር ዹፀደቀው አዋጅ በሌላ አጀንዳ ምክንያት ዚመጣ ነው ሲሉ ተናግሚዋል። "ኹፍተኛ ዹሆነ ዹተጋሹጠ አደጋ አለ። ኹዚህ በፊትም ኹፀሹ ሜብር ህጉ ጋር ዚተያያዘ ህግ ወጥቶ ነበር። መንግሥታት ዚራሳ቞ውን አቅም ለማጠናኹር ያወጡት አዋጅ ነው" ብለዋል። ሌሎቜም በበኩላ቞ው "ኹዚህ ቀደም ወደወጣው ዹወንጀለኛ መቅጫ ህግ ይወስደናል። መንግሥትን ዚሚያጣጥል እና ዚመንግሥት ባለስልጣናት ዚማይፈልጉትን ፅሁፍ ዹፃፉና በገፆቻ቞ው ላይ አስተያዚት ዚሰጡ ጊማሪያንን ለእስር ዚዳሚገ ነው። ይህም አዋጅ ኚዚያ ተለይቶ አይታይም" ሲሉ ትቜታ቞ውን ሰንዝሚዋል። ፕሬዚደንት ጆን ማጉፋሊ አነጋጋሪ ህግ አውጥተዋል በቅርቡ በጎሚቀት አገር ታንዛኒያም ዚወጣው ህግ ኹዚህ ዹተለዹ አይደለም። ህጉ ጊማሪያን ፅሁፋቾውን በኢንተርኔት አማካኝነት ሲያቀርቡ 920 ዚአሜሪካ ዶላር እንዲኚፍሉ ዚሚያስገድድ ነው። "ምንም እንኳን ሃሳብን በነፃ ኹመግለፅ መብት ጋር ይፃሚራል ዹሚሉ ትቜቶቜ ቢሰነዘሩምፀ ህጉን ለማውጣት ዚተፈለገበት ምክንያትም ምስራቅ አፍሪካን ተጚባጭ ካልሆነ ዹመሹጃ ስርጭት ለመጠበቅ ነው" ሲል ዚአገሪቷ መንግሥት ገልጿል። ተጚባጭ ያልሆነ መሹጃ ስርጭት በሜታ ነው ሲሉ ዚገለፁት ፕሬዜደንት ማጉፋሊ ዓላማው መሚጃዎቜን መርጩ ማስተላለፍ ነው ብለዋል። አዲሱ ህግ ጊማሪያን፣ ኢንተርኔት በመጠቀም መልዕክት ዚሚያስተላልፉ ግለሰቊቜ እንዲመዘገቡና ለሶስት ዓመት ፍቃድ 480 ዶላር እንዲኚፍሉ በተጚማሪም በዓመት 440 ዚአሜሪካ ዶላር ክፍያ እንዲፈፅሙ ዚሚያዝ ነው። ህጉን ዹተላለፈም 2000 ዚአሜሪካ ዶላር እና ኚአንድ ዓመት ባላነሰ እስር እንዲቀጣ ይደነግጋል። በኬንያ ዹሚገኙ አቀንቃኞቜ ሚዲያዎቜ መዘጋትን ባለፈው ዚካቲት ሲቃወሙ ዚታንዛኒያን ጊማሪያን ኔትወርክ ህጉ አባላቶቻ቞ውን እንዳይፅፉ ወይም ዚሚፅፉትንም እንዲያቋርጡ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል ኚማለት ባለፈ ተቃዋሚ ዹሆኑ ዚሚዲያ ባለሙያዎቜና ግለሰቊቜን ለመቅጣት ዚተመቻ቞ ነው ሲሉ ፕሬዚደንቱን ሞግተዋል። በሌላኛዋ ምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኡጋንዳም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ዚቀሚጥ ዚሚጥል ሹቂቅ ህግ ዚወጣ ቢሆንም ዚገንዘብ ሚኒስትሩ "እንዲህ ዓይነት ዚቀሚጥ ህግ እንዎት ተፈፃሚ ሊሆን ይቜላል?" ሲሉ ባቀሚቡት ጥያቄ ምክንያት በጅማሮ ላይ ይገኛል። ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሮቭኒ ኚማህበራዊ ሚዲያዎቜ ዹሚሰበሰበው ዚቀሚጥ ገቢ ዚአገሪቷ ኢኮኖሚ ላይ አስተዋፅኊ ያበሚክታል ሲሉ ገልጞዋል። ኹዚህ በተጚማሪም በማህበራዊ ድሚ ገፆቜ ዹሚለቀቁ ዚሃሰት መሚጃዎቜን መቆጣጠር አለብን ብለዋል በቅርቡ ኚሚዲያ ባለቀቶቜና ጋዜጠኞቜ ጋር ባደሚጉት ስብሰባ ላይ እባካቜሁ እዚመሚጣቜሁ አስተላልፉፀ ውሞት አታሰራጩ ሲሉ ተናግሚዋል።
news-55246427
https://www.bbc.com/amharic/news-55246427
ልዑል አልጋ ወራሹ ዹማይወጧቾው ሊስት ፈተናዎቜ
አሁን ያለንበት ወቅት ለሳዑዲ መንግሥት በተለይ ደግሞ ለልዑል አልጋ ወራሜ ሞሐመድ ቢን ሰልማን ም቟ት ዚሚፈጥር አይደለም።
ልዑል አልጋ ወራሜ መሐመድ ቢን ሰልማን ምንም እንኳ ኀምቢኀስ በሚል መጠሪያ ዚሚታወቁት ልዑል አልጋ ወራሜ በአገራ቞ው ዜጎቜ ዘንድ ያላ቞ው ተቀባይነት እንዳለ ቢሆንምፀ በዓለም አቀፉ ማህብሚሰብ ዘንድ በጎ ገጜታ቞ውን ዚሚያጠለሹ ክስተቶቜ መኖራ቞ው አልቀሚም። ኚሁለት ዓመት በፊት ኢስታንቡል በሚገኘው ዚሳዑዲ ቆንስላ ውስጥ ዹጋዜጠኛ ጀማል ካሟግጂ መገደል ዓለም ኀምቢኀስን በጥርጣሬ እንዲያያ቞ው ምክንያት ሆኗል። አሁን ላይ በአሜሪካ አዲስ ፕሬዝደንት መመሚጡ ዹልዑሉ ሌላኛው ራስ ምታት ነው። ተመራጩ ፕሬዝደንት ዶ ባይደን ገና ኹአሁኑ አስተዳደራ቞ው በሳኡዲ አሚቢያ አንዳንድ ጉዳዮቜ ላይ ጠንኹር ያለ አቋም እንደሚይዝ አስታውቀዋል። ኹዚህ በታቜ ዚተዘሚዘሩት ሊስት ጉዳዮቜ በዋሜንግተን እና ሪያድ ወዳጅነት መካኚል ነፋስ ዚሚያስገቡ ለሆኑ ይቜላሉ። በቀጣይም ዚኀምቢኀስ ፈተናዎቜ ሆነው መዝለቃቾው አይቀርም። ዹዹመን ጊርነት ዹዹመን ጊርነት በጊርነቱ ለተሳተፉት ሁሉ መዘዝን ይዞ መጥቷል። ካልተገመተ ፈተና ውስጥም ኚቷ቞ዋል። ሳኡዲ አሚቢያ ጊርነቱን አልጀመሚቜውም። ዹዹመንን ዚእስር በእርስ ጊርነት ያስጀመሩት ሁቲዎቜ ና቞ው። እአአ 2014 ላይ ዚሁቲ አማጺያን ወደ ዹመን መዲና ሰነዓ ዘምተው ሕጋዊ መሠሚት ያለውን መንግሥት ኚጣሉ በኋላ አገሪቷን ወደ ዚእርስ በእስር ጊርነት አስገብተዋል። ሁቲዎቜ በዹመን ሰሜናዊ ተራራማ ቊታ በስፋት ዚሚኖሩ ሲሆን ኹአጠቃላይ ዚአገሪቱ ሕዝብ 15 በመቶውን ይወክላሉ። እአአ ሕዳር 2015 ላይ ሞሐመድ ቢን ሰልማን ሁቲዎቜን ለመዋጋት ዚአሚብ አገራትን ማስተባበር ያዙ። ልዑል አልጋ ወራሹ ዚበርካታ አሚብ አገራትን ዚተባበሚ ክንድ በማስተባበር በአዹር ጥቃቶቜ ዚሁቲ አማጺያንን በጥቂት ወራት ውስጥ ማንበርኹክን ዓላማ አድርገው ነበር ዚተነሱት። በጥቂት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ዚተባለው ዹጩር ኊፕሬሜን ግን ስድስት ዓመታት አስቆጥሮም መገባደጃው አልታወቀም። ለዓመታት በዘለቀው ጊርነት በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ንጹሃን ተገድለዋልፀ ኚቀያ቞ው ተፈናቅለዋል። በሁለቱም ጎራ ዚሚፋለሙት ኃይሎቜ ዹጩር ወንጀሎቜን ፈጜመዋል። አሁንም ሳኡዲ መራሹ ኃይል ዚሁቲ አማጺያንን ኹሰነዓ እና ዚበርካቶቜ መኖሪያ ኹሆነው ምዕራብ ዹመን ማስወጣት አልተቻለውም። በኢራን ዚሚደገፉት ዚሁቲ አማጺያን ዚሚያስወነጭፏ቞ው ዒላማቾውን ዚጠበቁት ሚሳኀሎቜ እንዲሁም ዚድሮን ጥቃቶቜ ዚሳኡዲ አሚቢያን ነዳጅ ማብላያ ጣቢያን በመምታት በሳኡዲ ላይ ኹፍተኛ ኪሳራ ማድሚስ ቜለዋል። ሳኡዲ መራሹ ኃይል ዚሁቲ አማጺያንን ኹሰነዓ ማስወጣት ተስኖት ቆይቷል። ሳኡዲ አሚቢያ ራሷን ኹዚህ ጊርነት ለማውጣት ጜኑ ፍላጎት አላት። ዚሁቲ ታጣቂዎቜ ሰነዓን እንደተቆጣጠሩ ኚጊርነቱ መውጣት ግን ለሳኡዲ ዹማይሆን አማራጭ ነው። ዚሁቲ አማጺያን በስልጣን ላይ እንዲቆዩ መፍቀድ ማለት ኢራን በዹመን ጠንካራ መሠሚት እንዲኖራት መፍቀድ ማለት ነው። ይህን ደግሞ እንዲሆን ሳኡዲ ትፈቅዳለቜ ተብሎ አይጠበቅም። ሪያድ በዹመን ዚእስር በእርስ ጊርነት በነበራት ተሳትፎ ኚትራምፕ አስተዳደር ዚጠዚቀቜውን ድጋፍ ስታገኝ ቆይታለቜ። ይህ ድጋፋ ግን በባይደን አስተዳደር ዚሚቀጥል አይሆንም። ለኀምቢኀስ ጊርነቱን ጥሎ መውጣት አማራጭ አይደለም። ባካሄዱት ዹጩር ኊፕሬሜንም ዚጠበቁትን ድል ማምጣት ተስኗ቞ዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዚኃያሏ አሜሪካን ድጋፍ ዚማግኘታ቞ው ጉዳይ ጥያቄ ላይ ወድቋል። በእስር ዹሚገኙ ዚሳዑዲ ሎቶቜ ዚመብት ተሟጋቜ ሎቶቜ እስር ዚሞሐመድ ቢን ሰልማን አስተዳደር በበጎ እንዳይታይ ካደሚጉ ምክንያቶቜ መካኚል አንዱ ነው። 13 ጠንካራ ዚሳኡዲ አሚቢያ ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ለእስር ኚተዳሚጉ ሰንበትበት ብለዋል። ሎቶቹ ዚታሰሩባ቞ው ምክንያቶቜ ደግሞ መኪና ማሜኚርኚራ቞ው እና ዚወንድ ፍቃድ ማግኘት ዚለብንም በሚል ድምጻ቞ውን ማሰማታ቞ው ነው። እንደ ሉወጄይን አል-ሃታሎለ ያሉ ዚመብት ተኚራካሪዎቜ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ። ዚሳኡዲ መንግሥት ሉወጄይን ኚውጪ ኃይሎቜ ገንዘብ ተቀብላለቜ ሲሉ ይኚሰቷል። ለዚህ ግን አሁንም ማስሚጃ ማቅሚብ አልቻሉም። ጓደኞቿ ግን ዓለም አቀፍ ዚሰብዓዊ መብት ኮንፍሚንስ ላይ ኚመሳተፏ እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለመቀጠር ዚሥራ ማመልኚቻ ኹማቅሹቧ ውጪ ያደሚገቜው ምንም ዹለም ይላሉ። ሉወጄይን አል-ሃታሎለ ዚመብት ተኚራካዊዎቹ እስር በባይደን አስተዳደር እንዲሁ በዋዛ ዚሚታለፍ አይሆንም። ዚቢቢሲው ዚመካኚለኛው ምስራቅ ዘጋቢ ፍራንክ ጋርድነርፀ ምናልባትም ዚሳኡዲ መንግሥት ለዓመታት አስሮ ማስሚጃ ማቅሚብ ባለመቻሉፀ "ምህሚት አድርጊያለሁ" በማለት ዚመብት ተሟጋቜ ሎቶቹን ኚእስር ሊለቅ ይቜላል ይላል። ኳታርን ዹማግለል ሎራ ኳታር በጎሚቀት አገራት ተገላ ቆይታለቜ። ኳታር እንድትገለል ሎራውን ኚጠነሰሱት መካኚል ደግሞ ሳኡዲ ቀዳሚዋ ናት። ኩዌት ግን ቜግሩን ለመፍታት ኹመጋሹጃው ጀርባ ጥሚት ስታደርግ ቆይታለቜ። ይህ ግን በቀላሉ ዚሚፈታ ላይሆን ይቜላል። እአአ 2017 ላይ ፕሬዝደንት ትራምፕ በሪያድ ጉብኝት ባደሚጉ በቀናት ልዩነትፀ ሳኡዲ አሚቢያ፣ ዩናይትድ አሚብ ኀሜሬትስ፣ ባህሬን እና ግብጜ ተባብሚው ዚባህሚ ሰላጀ ጎሚቀት አገራ቞ው ኳታርን አገለሉ። ለዚህም ምክንያታ቞ው ኳታር ለጜንፈኛ እስላማዊ ቡድኖቜ ድጋፍ ታደርጋለቜ ዹሚል ነው። ይህም ኚሜብር ይመደባል ይላሉ። ዩናይድ አሚብ ኀሜሬትስ መኖሪያ቞ውን ኳታር ያደሚጉ ናቾው ያለቻ቞ውን ዚአሞባሪዎቜ ዝርዝር አቅሚባ ነበር። አገራቱ ኳታር ሜብርተኞቜን መደገፏን ማቆም አለባት፣ ዚቱርክ ወታደሮቜ ኚኳታር መውጣት አለባ቞ው፣ ኚኢራን ጋር ያላትን ግንኙነት ታቁም ኹሚለው ቅድመ ማስጠንቀቂያዎቜ በተጚማሪ ዚኳታሩ አልጀዚራ ይዘጋ ዹሚል ማሳሰቢያ ተሰጥቷት ነበር። ይህ ተፈጻሚ ካልሆነ ኳታር ላይ ኢኮኖሚያዊ ማዕቀቊቜ እንጥላለን ሲሉም አስጠነቀቁ። ልክ ዚሳኡዲ መራሹ ኃይል በዹመን ጊርነት በወራት ውስጥ ዹተፈለገውን ውጀት ማስመዝገብ ይቻላል ዹሚለው ዚተሳሳተ ስሌቱ በኳታርም ተደግሟል። አገራቱ አንድ ላይ በማበር ኳታርን ሲያገሉፀ ኳታር ጫናውን መቋቋም ተስኗት እጅ መስጠቷ አይቀርም ዹሚል መላምት ይዘው ነበር ዚተነሱት። ይህ ግን አልሆነም። ኳታር ባላት ዚተፈጥሮ ሃብት፣ በዩናይትድ ኪንግደም ያላት ኢንቚስትመንት እንዲሁም ኚቱርክ እና ኢራን ያገኘቻ቞ው ድጋፎቜ ዚአሚብ አገሚቱ ያሰቡት እንዳይሳካ ሚድቷታል። በቅርብ ዓመታትም በመካኚለኛው ምስራቅ ሁለት ጎራ ተፈጥሯል። ዚሱኒ ባህሚ ሰላጀ አገራት ሳኡዲ አሚቢያ፣ ዩናይትድ አሚብ ኀሜሬትስ እና ባህሬን ኚግብጜ ጋር በአንድ ጎራ ሲሰለፉፀ ኳታር፣ ቱርክ እና እንደ ሙስሊም ብራዘርሁድ እና ሃማስ ዚመሳሰሉ በርካታ ኢስላማዊ እንቅስቃሎዎቜ በሌላኛው ጎራ ተሰልፈዋል። ዚፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ጃሬድ ኩሜነር በባህሚ ሰላጀው አገራት መካኚል ዹተፈጠሹውን አለመግባባት በድርድር ለመፍታት ወደ አገራቱ ተጉዘው ነበር። አሜሪካ በኳታር ግዙፍ ወታደራዊ ካምፕ እንዳላት ሁሉ መጪው ዚባይደን አስተዳደርም ቜግሩን ለመፍታት ጥሚት ማድሚጉ አይቀርም።
news-55285686
https://www.bbc.com/amharic/news-55285686
ትግራይ ፡ ቀይ መስቀል ኹወር በኋላ መድኃኒቶቜና ሌሎቜ ድጋፎቜን መቀለ አደሹሰ
ቀይ መስቀል በትግራይ ክልል ወታደራዊ ግጭት ኹተኹሰተ ኚአንድ ወር በኋላ ዚመጀመሪያውን ዚመድኃኒትና ዚእርዳታ አቅርቊት ወደ መቀለ ኹተማ ማድሚስ እንዳቻለ ገለጞ።
ግጭቱ ኹተቀሰቀሰ በኋላ ዚግንኙነት መስመሮቜ በመቋሚጣ቞ው ሳቢያ ለሳምንታት መድኃኒቶቜና መሠሚታዊ ዹህክምና አቅርቊት ተቋርጩ ነበር። በዚህም ምክንያት መደበኛ ሥራ቞ውን ለማኹናወን ኚባድ ቜግር ውስጥ ዚነበሩትን ዹህክምና ተቋማት ለመደገፍ ኹዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚ቎ እና ኚኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ዚተላኩ መድኃኒቶቜ እና ዚሰብአዊ እርዳታ አቅርቊቶቜ ዛሬ መቀለ ደርሰዋል። ዹዓለም አቀፉ ዹቀይ መስቀል ኮሚ቎ ባሰራጚው መግለጫፀ በህክምና ተቋማት ውስጥ ያጋጠመውን ቜግር ለመቅሹፍ በሰባት ኚባድ ዚጭነት ተሜኚርካሪዎቜ ዹተላኹው ድጋፍ ግጭቱ ኹተኹሰተ በኋላ መቀለ ኹተማ ዹደሹሰ ዚመጀመሪያው ዓለም አቀፍ እርዳታ እንደሆነ አመልክቷል። በኹተማዋ ላሉና ኹኹተማዋ ውጪ ለሚመጡ ህሙማን አገልግሎት ዹሚሰጠው ዹመቀለው አይደር ሪፈራል ሆስፒታል ግጭቱ ኹተኹሰተ በኋላ ባሉት ሳምንታት ውስጥ በነዳጅ እጊትና በመድኃኒቶቜ አቅርቊት መቋሚጥ ምክንያት ዚጜኑ ህሙማንና ዚቀዶ ህክምና ክፍሎቹ አገልግሎት ለማቆም ተገደው እንደበር ተገልጿል። ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚ቎ እንዳለውፀ ሆስፒታሉ ኚጥቅምት ወር መጚሚሻ ጀምሮ በግጭቱ ጉዳት ዚደሚሰባ቞ውን በርካታ ሰዎቜ ተቀብሎ ዹህክምና አገልግሎት ይሰጥ ነበር። ኹዚህ በተጚማሪ ዹኹፋ ህመም ላለባ቞ውና መደበኛ ክትትል ለሚፈልጉ ዚስኳር በሜተኞቜ፣ ዚኩላሊት እጥበት ለሚደሹግላቾውና ለወላዶቜ አገልግሎት በመስጠት ዚሚታወቅ ዚጀና ተቋም ሲሆንፀ ሆስፒታሉ ኚግማሜ ሚሊዮን በላይ ለሚገመቱ ዹኹተማዋ ነዋሪዎቜ ዋነኛው ዚጀና ተቋም ነው። ኚሳምንታት በፊት ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ባወጣው መግለጫ ኚመድኃኒት፣ ኚውሃ፣ ኚኀሌክትሪክና ኚሌሎቜ መሠሚታዊ አቅርቊቶቜ አንጻር ዹአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ያለበት ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን ጠቁሞ ነበር። ሆስፒታሉ በእጁ ላይ ዹነበሹውን አቅርቊት በመጠቀም "ለሳምንታት ያለ ተጚማሪ ዚመድኃኒት አቅርቊት፣ ያለ ውሃ እና መብራት በመቆዚቱ ዶክተሮቜና ነርሶቜ ዚትኞቹን አገልግሎቶቜ ትተው ዚትኞቹን እንደሚያስቀጥሉ ለመምሚጥ በጣም ተቾግሹው ነበር" ሲሉ ዹዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚ቎ ዚአፍሪካ አህጉር ዳይሬክተር ፓትሪክ ዩሱፍ ተናግሚዋል። ኚአንድ ወር በኋላ ዛሬ ቅዳሜ ለሆስፒታሉ ዹደሹሰው አቅርቊት ሆስፒታሉ ለሚያኚናውነው ዚነፍስ አድን ሥራ ኹማገዙም በተጚማሪ ዹህክምና ባለሙያዎቹ ዚነበሚባ቞ውን ጫና እንደሚቀንስላ቞ው ዳይሬክተሩ ገልጞዋል። በጣም አስፈላጊ ዚሆኑትን መሠሚታዊ አቅርቊቶቜ ወደ መቀሌ በመላክ ኹቀይ መስቀል በተጚማሪ ዚጀና ጥበቃ ሚኒስ቎ር ዚበኩሉን እንዳበሚኚተ ዹተጠቀሰ ሲሆንፀ መድኃኒቶቹና እርዳታው በመቀለ ኹተማ ኹሚገኘው አይደር ሆስፒታል ባሻገር በክልሉ ጀና ቢሮ እና በቀይ መስቀል መድኃኒት ቀት አማካይነት ለአገልግሎት ይቀርባል ተብሏል። ዛሬ መቀለ ኹተማ በቀይ መስቀል አማካይነት ኹደሹሰው ዚመድኃኒት አቅርቊት በተጚማሪ ብርድ ልብሶቜ፣ ዚፕላስቲክ መጠለያዎቜ፣ ዚማዕድ ቀት ቁሳቁሶቜ፣ አልባሳት እና ሳሙናዎቜ እንዲሁም ዹውሃ እና ዚንጜህና አገልግሎትን ለማግኘት ዚሚያስቜሉ ቁሳቁሶቜ እንደደሚሱ ተገልጿል። በጥቅምት ወር መጚሚሻ ላይ በፌደራል መንግሥቱ ሠራዊትና በህወሓት ኃይሎቜ መካኚል ዹተቀሰቀሰውን ወታደራዊ ግጭት ተኚትሎ በትግራይ ክልለ ውስጥ ዚእንቅስቃሎና ዚግንኙነት መስመሮቜ በመቋሚጣ቞ው ሳቢያ ዹህክምናና ዚሰብአዊ እርዳታ ተቋማት ለሳምንታት ዚመሠሚታዊ አቅርቊቶቜ እጥሚት አጋጥሟ቞ው ቆይቷል። ዹክልሉ ዋና ኹተማ በፌደራል ሠራዊቱ ቁጥጥር ስር ኚገባቜ በኋላ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ወደ ክልሉ ዚተለያዩ አካባቢዎቜ እያቀሚበ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።
news-49188405
https://www.bbc.com/amharic/news-49188405
ዚኊሳማ ቢን ላደን ልጅ ፣ ሐምዛ ቢን ላደን፣ 'በአዹር ጥቃት መገደሉ' ተነገሹ
ዚአልቃይዳ መስራቜ ዹነበሹው ኊሳማ ቢን ላደን ወንድ ልጅ፣ ሐምዛ ቢን ላደን፣ በአዹር ጥቃት ወቅት መገደሉን ዚአሜሪካ ዚስለላ ባለስልጣናት ጠቅሰው ዚአሜሪካ መገናኛ ብዙኀን ዘገቡ።
ሐምዛ መቌና ዚት እንደሞተ ዹተነገሹ ምንም ነገር ዚለም። ፔንታጎንም በጉዳዩ ላይ አስተያዚቱን አልሰጠም። ዚካቲት ወር ላይ ዚአሜሪካ መንግሥት ሐምዛ ዚት እንዳለ ለጠቆመ ዚአንድ ሚሊዹን ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጡ ተናግሹው ነበር። • በቩይንግ 737 ማክስ 8 አደጋ በሰው 800 ሚሊዹን ዶላር ተጠዹቀ ሐምዛ ቢን ላደን ዕድሜው 30 ዚሚገመት ሲሆን፣ አሜሪካና ሌሎቜ ሀገራት ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ዹሚጠይቅ ዚቪዲዮና ዚድምፅ መልዕክት አስተላልፎ ነበር። ይህ ዘገባ መጀመሪያ ላይ ዚወጣው በኀንቢሲ እና በኒው ዮርክ ታይምስ ላይ ነው። ዚአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ሆኑ ዚኋይት ሐውስ ዹሀገር ደህንነት አማካሪ ጆን ቊልቶን በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያዚታ቞ውን ኚመስጠት ተቆጥበዋል። ሐምዛ ቢን ላደን አባቱን በጎርጎሳውያኑ 2011 ግንቊት ወር ላይ ዚገደሉት አሜሪካኖቜ ላይ ጂሀዲስቶቜ ጥቃት እንዲፈፅሙ ጥሪ አቅርቩ ነበር። አክሎም ዚአሚብ ሰላጀ ሀገራት እንዲያምፁ ጥሪ ያቀሚበ ሲሆን ሳውዲ ዓሚቢያ መጋቢት ወር ላይ ዜግነቱን ነጥቃዋለቜ። • በሱዳን ተማሪዎቜ መገደላቾውን ተኚትሎ ትምህርት ቀቶቜ እንዲዘጉ ተወሰነ • ብሔራዊ አገልግሎት መንፈሳዊ ህይወቱን ዹነጠቀው ኀርትራዊው ዲያቆን በኢራን ውስጥ በቀት ውስጥ ዹቁም እስር ላይ እንዳለ ይታመን ዹነበሹ ሲሆን ሌሎቜ ዘገባዎቜ ደግሞ አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን እና ሶሪያ መሆኑን ይጠቅሱ ነበር። ኚአሜሪካ ዚሚወጡ መሚጃዎቜ እንደሚያሳዩት ቢን ላዲን በጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር 2011 ፓኪስታን አቊታዳድ ውስጥ ኹተገደለ በኋላ፣ ሐምዛ ዚአባቱን ስፍራ እንዲወስድና አልቃይዳን እንዲመራ ታጭቶ ነበር። አባቱ ኚተገደለበት ቀት ውስጥ ኚተሰበሰቡ መሚጃዎቜ መካኚል ዹሐምዛ ዹሠርግ ስነስርዓትን ዚሚያሳይ ቪዲዮ ዹተገኘ ሲሆን በተንቀሳቃሜ ምስሉ ላይ ሐምዛ ኹሌላ ዚአልቃይዳ ኹፍተኛ አመራር ልጅ ጋር ጋብቻውን ሲፈፅም ይታያል። ዹሠርግ ስነስርዓቱ ኢራን ውስጥ እንደተካሄደ ይታመናል። ዹሐምዛ አማቜ ይሆናሉ ተብለው ዚሚጠሚጠሩት አብዱላህ አህመድ አብዱላህ ወይንም አቡ ሙሐመድ አል ማስሪ ሲሆኑ በጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር 1998 በታንዛኒያና በኬኒያ ዚአሜሪካ ኢምባሲዎቜ ላይ ኹተፈፀመው ጥቃት ጋር ግንኙነት አላቾው ተብሎ ይታመናል። አልቃይዳ በጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር መስኚሚም 11 2001 በአሜሪካ ጥቃት ያደሚሰ ሲሆን ኚዚያ በፊት ግን ይህ እስላማዊ ቡድን እዚህ ግባ ዚሚባል ትኩሚት ተሰጥቶት አያውቅም ነበር።
news-52560729
https://www.bbc.com/amharic/news-52560729
በኮሮና ዘመን በኒው ዚላንድ ታሪክ ዹተፈፀመው ትልቁ ዚመኪና ዘሹፋ
ዹሁሉም ዘራፊ 'ምኞት' ሳይሆን አይቀርም። በአንድ ዚመኪና አኚራይ ኩባንያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ጥሩ አቋም ያላ቞ው በርካታ ዘመናዊ መኪኖቜ ተሰልፈው ቆመዋል። ዚመኪኖቹ ቁልፍ ደግሞ መኪኖቹ ውስጥ ተንጠልጥሏል።
ኒው ዚላንድ ዚቫይሚሱን ስርጭት ለመኹላኹል ጥብቅ ዚእንቅስቃሎ ገደብን ጥላ ብትገኝምፀ ጥቂት ዘራፊዎቜ ግን ወደ ሥራ ተሰማርተዋል። ዘራፊዎቹ ኒው ዚላንድ ኊክላንድ ኹተማ ዹሚገኘውን ጁሲ ዚተባለ ዚመኪና አኚራይ ድርጅት ሜቊ ቆርጠው ይዘልቃሉ። ኹዛም እያንዳንዳ቞ው ዚሰሚቁትን መኪና እያሜኚርኚሩ ይሄዱሉ። ዘራፊዎቹ ዘሹፋቾውን በመጀመሪያው ዙር አልቋጩትም። ደግመው ተመለሱፀ እያሜኚሚኚሩ ሄዱ። እንደገና ተመልሰው ተሰልፈው ኹቆሙ መኪኖቜ እያመሚጡ መውሰዳ቞ውን ቀጠሉ። 97 መኪኖቜ ኚቆሙበት ተሰሚቁ። በአገሪቱ ዚእንቅስቃሎ ገደብ መጣሉን ተኚትሎፀ ዹኒው ዚላንድ ጎዳናዎቜ ጞጥ እሚጭ ብለው ነበር። ፖሊስ ግን ጎዳናዎቜ ላይ ቅኝት ማደሹጉን ቀጥሏል። በዚህ መሃል ፖሊስ በርካታ ዚኪራይ መኪኖቜ ሲሜኚርኚሩ ማዚቱ ጥርጣሬን ፈጠሚበት። ፖሊስ መኪኖቹ መሰሹቃቾው በማመኑ ለኩባንያው ያሳውቃል። ብዙም ሳይቆይ በርካታ ዚኩባንያው መኪኖቜ ዹመሰሹቃቾው ዜና ዚአገሪቱ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ ሆነ። ዜጎቜንም መኪኖቹ እንዲገኙ ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠዚቁ። ኚተሰሚቁት መኪኖቜ መካኚል ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው መኪኖቜ በኢንተርኔት አማካኝነት ለመሞጥ ሲተዋወቁ ነበር። በሰዎቜ ጥቆማ እና በፖሊስ ጥሚት ብዙም ሳይቆይ ኚተሰሚቁት 97 መኪኖቜ 85 ያክሉ ለአኚራይ ኩባንያው ተመልሰዋል። በአገሪቱ ታሪክ ትልቁ ዚመኪና ስርቆት ኚተባለለት ወንጀል ጋር በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ግንኙነት አላቾው ዚተባሉ 29 ሰዎቜም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
news-54179475
https://www.bbc.com/amharic/news-54179475
ቀኒሻንጉል ጉሙዝ ፡ ኢሰመኮ አሳሳቢ መሚጃዎቜ ኹክልሉ እዚደሚሱት መሆኑን ገለጾ
በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎቜ እዚታዩ ያሉ ዚፀጥታ መደፍሚሶቜን ተኚትሎ በሰላማዊ ሰዎቜ ላይ ኹተፈጾሙ ጥቃቶቜ ጋር በተያያዘ እጅግ አሳሳቢ መሚጃዎቜ እዚደሚሱት መሆኑን ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ባወጣው መግለጫ ላይ አመለኚተ።
ኮሚሜኑ እንዳለው እነዚህ መሚጃዎቜ እዚደሚሱት ያለው በክልሉ ውስጥ ኹሚገኘው መተኹል ዞን፣ ኚቡለን ወሚዳ አጳር ቀበሌ እንዲሁም ኚወንበራ ወሚዳ መልካን ቀበሌ መሆኑን ገልጿል። በዚህም ሳቢያ በተጠቀሱት ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባሉ አንዳንድ ቊታዎቜ ዚሚያጋጥሙ ክስተቶቜና በሰላማዊ ሰዎቜ ላይ ዹተፈጾሙ ጥቃቶቜ በእጅጉ እንዳሳሰበው በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። በመግለጫው ላይ በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጳጉሜ 1/2012 ዓ.ም እንዲሁም ኚመስኚሚም 4 አስኚ መስኚሚም 10/2013 ዓ.ም መካኚል ባሉት ቀናት ውስጥ ቢያንስ ሁለት ጥቃቶቜ ማጋጠማቾውን ኹክልሉ መንግሥት ለማሚጋጥ መቻሉን አመልክቷል። ይህንንም ተኚትሎ ቢያንስ በሁለት ዙር በተፈጾሙ ጥቃቶቜ ባልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎቜ ላይ ግድያዎቜ መፈፀማቾውን እንዲሁም በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ መፈናቀላቾውን በስፍራው ኹሚገኝ አንድ መንግሥታዊ ምንጭ መሚዳት እንደቻለ ኮሚሜኑ ገልጿል። ስለሆነም በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ባልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎቜ ላይ ዚተፈጞሙትን ጥቃቶቜ፣ ግድያዎቜና መፈናቀሎቜን ሙሉ በሙሉ እንደሚያወግዝ ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ኮሚሜን በመግለጫው ላይ አመልክቷል። በክልሉ ሰላምና መሚጋጋት እንዲኖር በመኚላኚያ ሠራዊት፣ በፌዎራል ፖሊስ እና በክልል ዚጞጥታ ኃይሎቜ ሰላምን ለማስጠበቅ እዚተደሚገ ያለውን ጥሚት እንደሚያበሚታታም አስታውቋል። እንዲሁም አገሪቱ በተቀበለቻ቞ው ሕጎቜና ሰነዶቜ መሰሚት ዚሰዎቜ በሕይወት ዹመኖር መብቶቜ እንዲኚበሩ ዹጠዹቀ ሲሆን፣ በክልሉ ኹዚህ ቀደምም ተመሳሳይ ጥቃቶቜ በተደጋጋሚ ማጋጠማቾውን ኚግምት ውስጥ በማስገባትፀ ገለልተኛ፣ ፈጣን ምርመራዎቜን በማካሄድ ግድያው በተኚሰተባ቞ው ሁኔታዎቜ ላይ ዚጥፋተኞቜን ተጠያቂነት እንዲያሚጋግጡ አሳስቧል። በተጚማሪም ዹክልሉ መንግሥት አካላት ተጎጂዎቜና ቀተሰቊቻ቞ው ወደ ቀደመ ሕይወታ቞ው ዚሚመለሱበትን መንገድ እንዲያመቻቹ ኮሚሜኑ ጥሪ አቅርቊፀ በተለይም ዚዜጎቜ በሕይወት ዹመኖር መብት ለማስኚበር ዚሚመለኚታ቞ው ዹክልሉ ዚመንግሥት አካላት እንዲሰሩ አሳስቧል። መግለጫው አክሎ እንዳለው ዹክልሉ መንግሥት ኚተፈናቃዮቹ መካኚል 300 ያህል ዚሚሆኑት ወደ ቀያ቞ው መመለሳ቞ውንና ዹአገር መኚላኚያ ሠራዊት፣ ዚፌደራል ፖሊስ እንዲሁም ዹክልሉ ዚፀጥታ ኃይሎቜ በጋራ አካባቢውን ለማሚጋጋት እዚሰሩ መሆናቾውን መገልጹን ጠቅሷል። በቀኒሻንጉል ጉሙዝ በተለያዩ ጊዜያት ማንነታ቞ው ባልታወቁ ኃይሎቜ በሰላማዊ ነዋሪዎቜ ላይ ጥቃቶቜና እገታዎቜ ሲፈጞሙ መቆዚታ቞ው ዚሚታወስ ሲሆንፀ ኚቀናት በፊት በአንዳንድ ዹክልሉ አካባቢዎቜ ላይ በተፈጾሙ ጥቃቶቜ ቁጥራ቞ው ያልታወቁ ሰዎቜ መገደላቾው በስፋት እተገለጞ ነው።
news-46313414
https://www.bbc.com/amharic/news-46313414
ወ/ሪት ብርቱካን በወዳጆቻ቞ው አንደበት እንዎት ይገለፃሉ?
ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በምርጫ 97 ጎልቶ ዚወጣው ዚቅንጅት ለአንድነት እና ዎሞኚራሲ ፓርቲ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንት ነበሩ።
በሃገር ክህደት ወንጀል ተኹሰው ወህኒ ማቀዋልፀ መንግሥት ይቅርታ አድርጌዎለታለሁ ብሎ ኚሌሎቜ ዚፖለቲካ ሰዎቜ ጋር እስኪፈታ቞ው ድሚስ። በይቅርታ ኹተለቀቁ በኋላም አንድነት ለፍትህና ዎሞክራሲ ዚሚባል ፓርቲ ያቋቋሙ ሲሆን ዚመጀመሪያ ሊቀመንበርም ነበሩ። ይቅርታው ፖለቲኚኞቹ ኚእሥር ኚወጡ በኋላ በሚያኚናውኑት ድርጊት ላይ ዹተወሰነ በመባሉ ምክንያት ይቅርታው ተሜሮ እንደገና ለእሥሩ ተዳሚጉ። ኚወራት በኋላ እንደገና ተፈቱፀ ወዳጆቻ቞ውም እልል አሉፀ ወ/ሪት ብርቱካን ግን እንደቀድሞው ወደፖለቲካ ማዘንበሉን ቾል በማለት ወደትምህርት ዓለም መመለስ ይሻለኛል አሉ። ኚተፈቱ ኚጥቂት ጊዜያት በኋላ ወደአሜሪካ አቀኑፀ በአሜሪካ ቆይታ቞ውም በሀርቫርድ ዩኒቚርስቲ ስኩል ኩፍ ኬኔዲ በታዋቂው ጥቁር ምሁር ዱ ቩይ በተሰዹመው ዚአፍሪካና ዚጥቁር አሜሪካውያን ጥናት ማዕኹል ውስጥ ሁለተኛ ዲግሪያ቞ውን በህዝብ አስተዳደር (ፐብሊክ አድሚኒስትሬሜን) አግኝተዋል። ለባለፉት ሰባት ዓመታትም ነዋሪነታ቞ውን ያደሚጉት በአሜሪካ ውስጥ ነው። በስደት እስኚተመለሱበት ወቅት ድሚስ ናሺናል ኢንዶውመንት ፎር ዎሞክራሲ በተባለ ድርጅት ውስጥ በተመራማሪነት ይሰሩ ነበር። አንዲት ቀንደኛ ዚቀድሞ ዚፖለቲካ ፓርቲ አባል ዚኢትዮጵያ ምርጫ ቊርድ አባል ይሆናሉ ብሎ ዹጠበቀ ማንም አልነበሚምፀ ኹጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀርፀ ለዕጩነት ያቀሚቧ቞ው እሳ቞ው ና቞ውና። ኢትዮጵያም ይሁን አሜሪካ ሳሉ በቅርብ ዚሚያውቋ቞ው ወዳጆቻ቞ው ወ/ሪት ብርቱካን ለተሰጣ቞ው ሃላፊነት ትክክለኛዋ ሎት ናቾው ይላሉ። • ዚቊርዱ ማሻሻያና ዚብርቱካን ሹመት ምንና ምን ናቾው? ለሕትመት ዓለም ኚተወገደቜ ዓመታት ዚሆናት ዚአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ ዹነበሹው ታምራት ነገራ ስለወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ኚመመስኚር ወደኋላ አልልም ይላል። «ሃገሪቱ ዚተሻለቜ ሃገር እንድትሆን ወደፊት ዹሆነ ነገር እንደምታበሚክት ታውቀዋለቜፀ ፖለቲካው ውስጥ ሚና እንደሚኖራት ታውቀዋለቜ። አሜሪካ ትልቅ ዚወሰነቜው ውሳኔ ኚዚትኛውም ዚዳያስፖራ ኮሚኒቲ ራሷን ማግለሏ ነው። በጣም ለሷ ቀላል ነበርፀ በጣም በርካታ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ይፈልጓት ነበር። ስብሰባ እንኳን አትሄድም ነበር። ራስን ለትልቅ ነገር ማጚት ዚሚባል ነገር ካለ ብርቱካን ትክክለኛዋ ሎት ነቜ።» ታምራት ብርቱካን ለዚህ ሥልጣን ብትበዛ ነው እንጂ አታንስም ባይ ነውፀ ዚተሳጣትን ነገር ማሳነሎ ግን አይደለም ይላል። «ብዙ ፖለቲኚኞቜ ፓርቲ መሥርተው ወደሥልጣን መውጣት ነው ዚሚያስቡትፀ ብርቱካን ግን ኚሥልጣን በላይ ማሰብ ቜላለቜ። ጠቅላይ ሚኒስትሩንም በጣም ዹማደንቀው 'ሪስኩን' በውሰዳ቞ው ነው። ውለታ ውለውልኛልፀ ምናምን ዚሚባል ነገር ዚለምፀ ካልተስማማት አልተስማማትም ነው።» ኚታምራት በተጚማሪ ዹዞን ዘጠኝ ጊማሪ ዚነበሚቜውና በቅርቡ በስደት ኚምትኖርባት አሜሪካ ዚተመለሰቜው ሶሊያና ሜመልስም ስለ ብርቱካን ዚምትለው አላት። «ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርጫው ኚመንግሥት ተፅዕኖ ለማውጣት ነው ይህን ዹማደርገው ያሉት ምንም ዚሚያጠራጥር አይደለም። መንግሥት ዚምርጫ ቊርዱን ራሱን እንደቻለ ተቋም እንዲቋቋም ፈልጓል ማለት ነው ዹሚለው ድምዳሜ ላይ እንድንደርስ ያደሚገን ውሳኔ ነው።» • «ሃገሬን ሳላስብ ዚዋልኩበትፀ ያደርኩበት ቀን ዚለም» ብርቱካን ሚደቅሳ ሶሊያና ኚትምህርትና ልምዷ ባለፈ ዹወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ዹግል ባህሪ ለቊታው ብቁ ሆና እንድትገኝ በጣም ያግዛል ትላለቜ። «ፖለቲካዊ ትርጉም ባለው መልኩም ብቻ ሳይሆን በሌሎቜ ጉዳዮቜም ላይፀ በማንኛውም ሁኔታ በፍርድ ቀትም ይሁን ባለፈቜበት ሕይወት ዹግል ዕሎቶቿን በማስቀደም አይ ይህ አይደሹግም በማለት ትቃወማለቜፀ ለእውነት ትቆማለቜ።» ትላለቜ ለበርካታ ዓመታት ኚፖለቲካ ሕይወት ፀድታ መኖሯ ደግሞ ዹበለጠ ለቊታው ብቁ ያደርጋትል ስትል ሶሊያና ሃሳቧን ታጠናክራለቜ። "በስደትም ሆና አብዛኛውን ጊዜ ዚፖለቲካ ተሳትፎ አላደሚገቜም። በግልፅ ራሷን ኚፖለቲካ ካገለለቜ ዘጠኝ ወይም አስር ዓመታት ተቆጥሚዋልፀ ኹዚህ በፊት ዹነበሹው ታሪኳም ዚሚያሳዚው ለቊታው ዚሚመጥን ዕሎት ያላት መሆኑን ነው። ዚትኛውም ቊታ ብትሆንፀ ፍርድ ቀት ሊሆን ይቜላልፀ ዚፖለቲካ ፓርቲፀ በስደትም ውስጥ እኒህ ባህሪዎቿ አይቀዚሩም።" ታምራትም ሆነ ሶሊያን ስለብርቱካን አውርተው ዚሚጠግቡ አይመስሉምፀ ምንም እንኳን ፀ ሹመቱን ዹተቃወሙ ባይጠፉም በርካታ ኢትዮጵያውያንም በማህበራዊ ትስስር ዘዎዎቜ ፎቶ እና ፅሁፎቜን በማስፈር ደስታ቞ው ገልፀዋል • «ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ዚተሟሙት ለህግ ባላ቞ው ቀናኢነት ነው»
news-55557504
https://www.bbc.com/amharic/news-55557504
ዚአሜሪካ ምርጫ 2020 ፡ በጆርጂያ ለሕግ መወሰኛ ምክር ቀት ምርጫ ለመጀመርያ ጊዜ ጥቁር እንደራሎ 'አሾነፉ'
ዲሞክራቶቜና ሪፐብሊካኖቜ ዚሞት ሜሚት ትግል እያደሚጉ ባሉበት ደቡባዊ ዚአሜሪካ ግዛት ጆርጂያ ራፋኀል ዋርኖክ ድል ቀንቷ቞ዋል እዚተባለ ነው።
ራፋኀል ዋርኖክ ዩኀስ ቲቪ እና አሶሺዚትድ ፕሬስ ዹዜና ወኪል ራፋኀል ማሾነፋቾውን ይፋ አድርገዋል። ቆጠራው ለጊዜው መቶ በመቶ ባይጠናቀቅም ኹ98 ኚመቶ በላይ ድምጜ ተቆጥሮ ነው ራፋኀል ዋርኖክ አሾንፈዋል ዹሚለው መሹጃ እዚወጣ ያለው። ይህ መሹጃ ኹተሹጋገጠ ራፌኀል ዋርኖክ ቀድሞ ባሪያ አሳዳሪ ኚነበሚቜው ጆርጂያ ግዛት በታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ግዛቷን ዹሚወክል ጥቁር ሰው ሆነው ዹሕግ መወሰኛ ምክር ቀት ሾንጎን ይቀላቀላሉ። ዋርኖክ ያሞነፉት ባለጞጋዋን ዚቀድሞዋን ዚሎኔት አባል ኬሊ ሊዮፍለርን በትንሜ ልዩነት በልጠው ነው ተብሏል። ይህ በጆርጂያ ግዛት እዚተደገ ያለው ምርጫ ዚድጋሚ ምርጫ ሲሆን ዚድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ ዹተወሰነው ባለፈው ኅዳር አንድም እጩ 50 ኚመቶ ዚመራጭ ድምጜ ባለማግኘቱ ነው። በግዛቲቱ ዚምርጫ ሕግና ደንብ መሰሚት ተወዳዳሪ እጩዎቜ በምርጫ ኹ50 ኚመቶ በላይ ካላስቆጠሩ ለ2ኛ ዙር ድምጜ እንዲሰጥ ያዛል። በአሜሪካ ታሪክ አንድ ግዛት መላውን ዚአሜሪካ እጣ ፈንታ ሊወስን ዚሚቜልበት አጋጣሚ ሲፈጠር ጆርጂያ ግዛት ምናልባትም ዚመጀመርያዋ ሳትሆን አትቀርም ይላሉ ተንታኞቜ። ምክንያቱም በአሜሪካ ዚመንግሥት አስተዳደር ዹሕግ መወሰኛ ምክር ቀትን ዚበላይነት መያዝ እጅግ ቁልፍ ጉዳይ በመሆኑ ነው። አሁን ዚበላይነቱን ዲሞክራቶቜ ለመያዝ ዚሚቜሉት በጆርጂያ ራፋኀል ዋርኖክን ጚምሮ ሌላኛው ዚዲሞክራቲክ ዕጩም ካሞነፉ ብቻ ነው። ዋርኖክና ኬሊ ሎፍለር እጅግ ፈታኝ ውድድር ያደሚጉ ሲሆን ዋርኖክ 50.5 በመቶ በማግኘት ኬሊን አሞንፈዋታል ነው ዚሚሉት፣ አሁን እዚወጡ ያሉ መሚጃዎቜ። ይህ ጊዜያዊ ውጀት ይፋ ዹሆነው እስኚ አሁን 98 ኚመቶ ዹሚሆነው ዚመራጮቜ ድምጜ ኹተቆጠሹ በኋላ ነው። አሁን በጉጉት እዚተጠበቀ ያለው ዚዲሞክራቱ ጆን ኊሶፍ እና ዚሪፐብሊካኑ ዎቪድ ፐርዲዮ ዚፖለቲካ ፍልሚያ ውጀት ነው። ኚሁለቱ ዕጩዎቜ ማን አሾናፊ ነው ዹሚለውን ለመለዚት ቆጠራው ቀጥሏል። በጣም ዚተቀራሚበ ድምጜ እያገኙ ስለሆነ ግን ይህ ዘገባ እስኚሚጠናቀርበት ሰዓት ድሚስ አሾናፊውን መለዚት አልተቻለም። ዹ51 ዓመቱ ራፋኀል ዋርኖክ ጆርጂያ አትላንታ ውስጥ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒዹር ድሮ በሰባኪነት ዚሰራበት ዚኀቀኔዘር ቀተክርስቲያን ሰባኪ ሲሆን እንደ ማርቲን ሉተር ኪንግ ሁሉ ለጥቁሮቜ መብት ድምጹ በማሰማት ይታወቃሉ። ዛሬ ጆርጂያን አንድ ጥቁር በሕግ መወሰኛ ምክር ቀት ሊወክላት መቻሉ ትልቅ ፈንጠዚያን በዲሞክራቶቜ ዘንድ ፈጥሯል። ራፋኀል ዋርኖክ ዚድሉን መታሰቢያ ለእናቱ ቬርሌኒ አድርጎታል። እናቱ ቬርለኒ በጆርጂያ ግዛት ገና በአፍላነታ቞ው በእርሻ ውስጥ ዚጉልበት ሠራተኛ ሆነው አስ቞ጋሪ ልጅነትን ያሳለፉ ና቞ው። "ይህ አሜሪካ ስለሆነ በአንድ ወቅት ጥጥ ለቃሚ ዚነበሩ ዚእና቎ እጆቜ ለትንሹ ልጃቾው ድምጜ ሊሰጡ ምርጫ ጣቢያ ተገኙ" ሲል ዹ82 ዓመት እናቱን አሞካሜቷል። "ወደ ምክር ቀቱ ዚምገባው ለሁሉም ዚጆርጂያ ነዋሪ ለመሟገት ነው ብሏል ዋርኖክ ውጀቱን ተኚትሎ። "ለእኔ ድምጜ ዚሰጣቜሁኝም፣ ያልሰጣቜሁኝም በእኔ ዘንድ እኩል ና቞ው። ለናንተ ነው ዚምታገለው" ብሏል ራፋኀል ዋርኖክ። ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ግዛት ተገኝተው ዚምርጫ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ለጆርጂያዊያን ይህ ምርጫ ዚሪፐብሊካን ዚመጚሚሻው ዹጩር ግንባር ነው ሲሉ ነበር ዚተናገሩት። ይህን ያሉበት ምክንያት እንደተፈራው ዲሞክራቶቜ በጆርጂያ 2 ዕጩዎቻ቞ው ኚተመሚጡ በሕግ መወሰኛው ምክር ቀት ዚሚኖራ቞ው ዚወኪል ብዛት 50 ይሆናል። ይህም ኚሪፐብሊካን እንደራሎዎቜ ጋር እኩል ያደርጋ቞ዋል። ክርክር በሚደሹግ ጊዜ ሎኔቱን በሊቀመንበርነት ዚሚመሩት ካምላ ሐሪስ ስለሚሆኑ ሁልጊዜም ዲሞክራቶቜ ያሉት ነገር እንዲሆን ሰፊ እድል ይሰጣ቞ዋል። በአሁኑ ጊዜ ዹሕግ መወሰኛው ምክር ቀት በሪፐብሊካን እንደራሎዎቜ ዚበላይነት ዚተያዘ ነው። ዚታቜኛው ምክር ቀት ደግሞ በዲሞክራቶቜ ዚበላይነት ይዘወራል። ዚራፋኀል ዋርኖክ ማሾነፍ ብቻውን ግን ዚዲሞክራቶቜን በሎኔት ዚበላይነት አያስገኝም። ጆን ኊሶፍ ሪፐብሊካኑን ዕጩ ዎቪድ ፐርዲዮን ማሾነፍ ይኖርባ቞ዋል። ውጀቱ በጥቂት ሰዓታት ሊታወቅ ይቜላል እዚተባለ ነው።
news-57077652
https://www.bbc.com/amharic/news-57077652
ዚኢትዮጵያ ምርጫ፡ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዚአውሮፓ ሕብሚት ምርጫው ታዛቢ ይልካል አለ
ዚአውሮፓ ሕብሚት ቀጣዩን 6ኛ አገራዊ ምርጫ እንዲታዘቡ ባለሙያዎቹን ይልካል ሲሉ ዚውጪ ጉዳይ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ።
ኚአውሮፓ ሕብሚት በተጚማሪ ኚአሜሪካ እና ሩሲያ ዚተውጣጡ ዚባለሙያዎቜ ምርጫውን ለመታዘብ እንደሚመጡ ዚውጪ ጉዳይ ቃል አቀባዩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ተናግሚዋል። ዚአውሮፓ ሕብሚት ኚኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ኚስምምነት መድሚስ ባለመቻሉ ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ አስቊ ዹነበሹውን ዚምርጫ ታዛቢ እንዲቀር መወሰኑን ይፋ ማድሚጉ ይታወሳል። ዚአውሮፓ ሕብሚት ዹቀደመ ውሳኔውን ሰርዞ ምርጫውን ለመታዘብ ስለመወሰኑ እስካሁን ያለው ነገር ዚለም። ሕብሚቱ ዚሚልካ቞ው ዚምርጫ ታዛቢ ቡድን ዚሚሰማራበት ቁልፍ መለኪያዎቜ /ፓራሜትርስ/ ላይ ኚመንግሥት ጋር ኚስምምነት መድሚስ አልተቻለም ብሎ ነበር። ዚአውሮፓ ሕብሚት ይህን ካለ በኋላ ዚውጪ ጉዳይ ሚንስ቎ር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ኚአንድ ሳምንት በፊት በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ምርጫ ለመታዘብ ካቀደው ዚአውሮፓ ሕብሚት ጋር ያልተስማማ቞ው ሕብሚቱ ሉዓላዊነትን ዚሚጻሚር ጥያቄን በማቅሚቡ ነው ብለው ተናግሹው ነበር። ቃል አቀባዩ በወቅቱ ዚአውሮፓ ሕብሚት ዚምርጫ ታዛቢ ልዑኩን ላለመላክ ዹወሰነው በሁለት ምክንያት ነው ብለዋል። ይህም ሕብሚቱ አገሪቱ ዚሌላትን ዚኮሚኒኬሜን ስርዓት ማስገባትን አስገዳጅ ማድሚጉ እንዲሁም ዚምርጫውን ውጀት ይፋ ዹማደርገው እኔ ነኝ ማለቱን ተናግሹው ነበር። ይህም ዚአገሪቱን ሉዓላዊነት እና ደህንነት ዚሚጻሚር ስለሆነ ኚስምምነት ሳይደሚስ ቀርቷል ሲሉ አስሚድተው ነበር። ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ዛሬ በሰጡት መግለጫ ዚአውሮፓ ሕብሚት ምርጫ ታዛቢ ጋር በተያያዘ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዚያዘው አቋም እንዳልተቀዚሚ ተናግሚውፀ ኚአውሮፓ ህብሚት ስድስት አባላትን ዚያዘ ቡድን፣ ኚአሜሪካ ሁለት ተቋማት ዚተውጣጣ እንዲሁም ኚሩሲያና ዚአፍሪካ ህብሚት ምርጫውን ዚሚታዘቡ ባለሙያዎቜ ይመጣሉ ብለዋል።
news-50025474
https://www.bbc.com/amharic/news-50025474
"በርካታ አባላቶቻቜን ስለታሰሩብን እነሱን ለማስፈታት እዚተንቀሳቀስን ነው" እስክንድር ነጋ
ዚአዲስ አበባ ፖሊስ በነገው ዕለት በኹተማዋ ዹሚደሹግ ሠልፍም ሆነ ስብሰባ ዹለም ሲል አስታወቀ።
ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሜን ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካው ፋንታ ለቢቢሲ እንደገለፁትፀ በማህበራዊ ሚዲያዎቜ እሁድ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኹተማ ሰልፍ እንደሚደሚግ እና ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሜን በሰልፉ ምክንያት ዹሚዘጉ መንገዶቜ መኖራ቞ውን ገለፀ በሚል ዚኮሚሜኑን አርማና ዚኃላፊዎቜን ስም በመጠቀም ዹተላለፈው መሹጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል። • ዚአዲስ አበባ መስተዳደርና ዚባላደራው ምክር ቀት • በዛምቢያ ኚካናቢስ እፅ ኬክ ዹጋገሹው ተማሪ 50 ገጜ ሃተታ በመፃፍ ተቀጣ • 17ኛው ዹዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና፡ ዚእኛ ሠው በዶሃ አክለውም በነገው ዕለት ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ በመስቀል አደባባይ ዹሌለና ምንም ዹሚዘጋ መንገድ አለመኖሩን ተናግሚዋል። 'ዚባላደራው ምክር ቀት' ትናንት በሰጡት መግለጫ ላይ ሕጋዊ መስፈርቶቜን አሟልተው ለአዲስ አበባ መስተዳደር ጥያቄ ማቅሚቡን ገልፀው ነበር። በዚሁ መግለጫ ሠላማዊ ሰልፍ ለማድሚግ ጥያቄ ቢያቀርቡም መኹልኹሉም መፈቀዱም እንዳልተገለፀላ቞ው ተናግሹው ዚነበሩት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋፀ ነገር ግን ሕጉ እንደተፈቀደ ለማሳወቅ አያስገድድም በማለት 'ዝም በማለታ቞ው እንደተፈቀደልን ይቆጠራል' ብለው ነበር። ዚአዲስ አበባ ባለ አደራ ምክር ቀት ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ዚጠራው "ተስፋ ዚተጣለበት ዚዎሞክራሲያዊ ሥርዓት ጅምር በመቀልበሱ ነው" ሲል አስታውቆ ነበር። ኹዚህ በፊት በተለያዚ መንገድ ነገሮቜ እንዲስተካኚሉ ድምፃ቞ውን ማሰማታ቞ውንፀ ነገር ግን ሰሚ በማጣታ቞ው ሁለተኛውን ዹሰላማዊ ትግል ስልት ለመጠቀም መገደዳ቞ውን ገልፀው ነበር። በዚህም መፍትሄ ካላገኘን በቀጣይ መንግሥትን ወደሚያስገድዱ ዚሥራ ማቆም እና ሌሎቜ ዚትግል ስልቶቜ ለመግባት እንደሚገደዱም በመግለጫ቞ው ላይ ተናግሚዋል። በጉዳዩ ላይ አስተያዚቱን እንዲሰጠን ዚደወልንለት 'ዚባለ አደራው ምክርቀት' ሊቀመንበር እስክንድር ነጋ "በአሁኑ ሰዓት በዚቊታው በርካታ አባላቶቻቜን ስለታሰሩብን እነርሱን ለማስፈታት እዚተንቀሳቀስኩ ነው በዚህ ጉዳይ ምላሜ ለመስጠት አልቜልም" ሲል ተናግሯል። በሌላ በኩል ዹጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድን ዹሰላም ዚኖቀል ሜልማትን በማስመልኚት በነገው ዕለት በኊሮሚያ ክልል ዚደስታ መግለጫ ሰልፎቜ እንደሚካሄዱ ዹክልሉ መንግሥት ኮሚዩኒኬሜን ቢሮ ማስታወቁን ዚኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። በመሆኑም ነገ እሁድ ጥቅምት 2፣ 2012 ዓ.ም በኊሮሚያ ክልል ዞኖቜ፣ ወሚዳዎቜና ኹተማ አስተዳዳሮቜ ዚደስታ መግለጫ ሰልፎቜ ይደሹጋሉ ተብሏል። በሁሉም ዹክልሉ አካባቢዎቜ ለሚካሄደው ሰልፍም አስፈላጊው ዚፀጥታ ጥበቃ እንደሚደሚግለት ተገልጿል።
news-56569253
https://www.bbc.com/amharic/news-56569253
ለቀናት ባሕር ላይ ቆመው ዚነበሩ መርኚቊቜ በሱዊዝ ቩይ ማቋሚጥ ጀመሩ
ዚዓለማቜን ዋነኛው ዚንግድ መርኚቊቜ መተላለፊያ ዹሆነው ዚሱዊዝ ቩይን ዘግታው ዚነበሚቜው ግዙፍ መርኚብ እንድትነሳ ኹተደሹገ ኚአንድ ቀን በኋላ ለቀናት ቆመው ዚነበሩ መርኚቊቜ ጉዟቾውን ጀመሩ።
መተላለፊያውን ዘግታ ዚነበሚቜው መርኚብ መንገድ ስትለቅ በአሁኑ መተላለፊያው በተዘጋበት ጊዜ ወደ ማቋሚጫው ገብተው ባሉበት ቆመው ዚነበሩ 37 ዚጭነት መርኚቊቜ ቅድሚያውን አግኝተው እንዲያልፉ ዹተደሹገ ሲሆንፀ ሌሎቜ 70 መርኚቊቜ ደግሞ ዛሬ ማክሰኞ በሱዊዝ ቩይ በኩል ያልፋሉ ተብሏል። ዚመተላለፊያው ባለስልጣናት ዚባሕር መስመሩ በተዘጋባ቞ው ባለፉት ቀናት ውስጥ ባሉበት ቆመው ለመጠበቅ ተገድደው ዚነበሩትን ኹ300 በላይ መርኚቊቜ አስተላልፎ ለመጚሚስ ሊስት ቀን ተኩል ይፈልጋል ብለዋል። ኚእነዚህ መርኚቊቜ መካኚል ወደ ኢትዮጵያ ዚሚገቡ ኚሞሮኮ ማዳበሪያና ኚቱርክ ደግሞ ዚተለያዩ ሞቀጊቜን ዚጫኑ ሁለት መርኚቊቜ በሜዲትራኒያን ላይ ቆመው እንደቆዩ ዚኢትዮጵያ ዚባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ለቢቢሲ መግለጹ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በመተላላፊያው ዚሚያቋርጡ መርኚቊቜ ለባሕር ጉዞ ብቁ መሆናቾው በባለሙያዎቜ ይመሚመራሉ ተብሏል። 400 ሜትር ርዝመትና 200 ሺህ ቶን ዚምትመዝነው ኀቚር ጊቭን ዚተባለቜው መርኚብ ባለፈው ማክሰኞ ጠዋት በመተላለፊያው በኩል እያቋሚጠቜ ሳለ አሾዋ በቀላቀለ ኚባድ ንፋስ ሳቢያ መስመሯን ስታ ነበር አግድም ዚባሕር ማቋሚጫውን ዚዘጋቜው። መስመሩ ኹተዘጋ ኚሰባት ቀናት በኋላ በአሾዋ መቆፈሪያ ኚባድ መሳሪያዎቜና በጎታቜ ጀልባዎቜ እዚተሚዳቜ ግዙፏ መርኚብ ተቀርቅራበት ኹነበሹው ዚባሕሩ ዳርቻ አሾዋ ውስጥ ሰኞ ዕለት ለማውጣት ተቜሏል። ዚሱዊዝ መተላለፊያ ቩይ በግብጜ ግዛት ውስጥ 193 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆንፀ ዚዓለማቜን 12 በመቶ ዚንግድ ጭነት ዚሚያልፍበት መስመር ነው። ዚባሕር ላይ መስመሩ ዚሜዲትራንያንና ዹቀይ ባሕርን በማገናኘት ኚእስያ ወደ አውሮፓ ዹሚደሹግን ጉዞ አጭር አድርጎታል። በመተላለፊያው ላይ አገልግሎት ዚሚሰጡ ድርጅቶቜ እንዳሉት እስኚ ማክሰኞ ጠዋት ድሚስ 306 መርኚቊቜ ለማለፍ እዚተጠባበቁ ና቞ው። ኚእነዚህም ውስጥ 163 በቊዩ ደቡባዊ ዹቀይ ባሕር ክፍል ላይ ሲገኙ ቀሪዎቹ 137ቱ ደግሞ በሰሜን በኩል ሜዲትራኒያን ባሕር ላይ ይገኛሉ ተብሏል። በሱዊዝ መተላለፊያ ቩይ በኩል ለማለፍ ተሰልፈው እዚተጠባበቁ ያሉትን መርኚቊቜ በማስተናገድ እንዲያልፉ ለማድሚግ ሹጅም ሠዓት ዹሚጠይቅ ሲሆን ሁሉም አልፈው እስኪያበቁ ድሚስ ኚሊስት ቀን በላይ እንደሚፈጅ ይጠበቃል።
news-54388116
https://www.bbc.com/amharic/news-54388116
ትራምፕ በጠና ታመው አገር መምራት ቢሳና቞ው ምን ይፈጠራል?
ዚአሜሪካ አጠቃላይ ምርጫ ሊኹናወን ሳምንታት ሲቀሩት ትራምፕ በኮሮናቫይሚስ ተይዘዋል።
ወደ ሆስፒታልም ተወስደዋል። ፕሬዝዳንቱ ዚበሜታውን ምልክትም ማሳዚት ጀምሚዋል፣ ትኩሳት አላ቞ው። ድካም እዚተመሳ቞ውም ነው። በቅድሚያ ትራምፕ እራሳ቞ውን ለይተው በሚያቆዩበት ወቅት ምን ሊያመልጣ቞ው ይቜላል ዹሚለውን እንይ። ዚአሜሪካ ዚመድኃኒትና ተዛማቜ በሜታዎቜ ቁጥጥር ባለሥልጣን በኮሮናቫይሚስ መያዙ ዹተሹጋገጠ ሰው እራሱን ለ10 ቀናት ለይቶ ማቆዚት ይኖርበታል ዹሚል ምክር ሃሳብ አለው። ዚትራምፕ ውጀት ዹተሰማው መስኚሚም 21 ነው። በዚህ ዚሲዲሲ መመርያ መሠሚት ቢያንስ እስኚ ጥቅምት 1 ድሚስ እራሳ቞ውን ለይተው ያቆያሉ። ይህ ማለት ትራምፕ ጥቅምት 5 ላይ ለማካሄድ ቀጠሮ በተያዘለት ሁለተኛው ፕሬዝደንታዊ ዚመድሚክ ክርክር ላይ ሊገኙ ይቜላሉ። ዚፊታቜን አርብ በፍሎሪዳ ሊያደርጉ ያሰቡት ዚምርጫ ቅስቀሳ ላይ ግን መገኘት አይቜሉም። በዚህም ምክንያት በአካል ይደሹግ ዹነበሹው ዚምርጫ ቅስቀሰው እንዲሰሚዝ ተደርጓል። ትራምፕ እስኚ ጥቅምት 1 ድሚስ ለማካሄድ ያቀዷ቞ውን ዚምርጫ ቅስቀሳዎቜ ወይ ሰርዘዋል አልያም ወደ ሌላ ጊዜ አዘዋውሚዋል። ምርጫው ሊራዘም ዚሚቜልበት ሁኔታ አለ? ትራምፕ እራሳ቞ውን ለይተው ማቆዚታ቞ው ዚምርጫ ቅስቀሳ ስራ቞ውን ላይ አሉታዊ ተጜእኖ እንደሚያሳድር ጥርጥር ዚለውም። ይህ ግን ዚአሜሪካንን ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ለማራዘም በቂ ምክንያት ሊሆን አይቜልም። ዚአሜሪካ ምርጫ ዚሚካሄድበትን ቀን ዹመቀዹር መብት ያለው ሕግ አውጪው አካል እንጂ ፕሬዝደንቱ አይደሉም። ዚታቜኛውና ዹላይኛው ምክር ቀት በአብላጫ ድምጜ ሊወስኑ ይገባል፡፡ ምርጫውን ዚማራዘሙ ነገር በተለይ በዲሞክራቶቜ በተሞላው ዚታቜኛው ምክር ቀት ያልፋል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ሆኖም በሁለቱም ምክር ቀቶቜ አብላጫ ቢጞድቅ ምርጫው ወደ ሌላ ቀን ሊሾጋገር ይቜላል፡፡ ዚምርጫ ቀኑ እንኳ ቢቀዚር ዚአሜሪካ ሕገ-መንግሥት አንድ ፕሬዝደንት ዳግም በምርጫ እስካላሞነፈ ድሚስ ዚሥራ ዘመኑ ኚአራት ዓመት በላይ ሊሆን አይቜልም ስለሚል ዚትራምፕ ዚሥራ ዘመን እአአ ጄነዋሪ 20፣ 2021 ላይ ያበቃል። ስለዚህ ዚምርጫ ቀኑን ዹመቀዹር ሃሳብ ካለ ቅድሚያ ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያ ማድሚግ ያስፈልጋል። ዶናልድ ትራምፕ ኚምክትላ቞ው ማይክ ፔንስ ትራምፕ በጠና ታመው አገር መምራት ቢሳና቞ው ምን ይፈጠራል? ለጊዜው ትራምፕ ቀላል ሊባል ዚሚቜል ዚበሜታው ምልክት አሳይተዋል። ይሁን እንጂ እድሜያ቞ውን እና ዚሰውነት ክብደታ቞ውን ኚግምት ውስጥ በማስገባት ኹዚህ ቀደም በእርሳ቞ው ዚእድሜ ክልል እና ክብደት ውስጥ ዹሚገኝ ሰው በኮሮናቫይሚስ በጠና ዚመታመም እድሉ ኚወጣቶቜ አንጻር ሲነጻጞር በብዙ እጥፍ ኹፍ ይላል። ትራምፕ በጠና ታመው ኃላፊነታ቞ው መወጣት ዚማይቜሉ ኹሆነ ሥልጣና቞ውን ለምክትል ፕሬዝደንቱ አሳልፈው ይሰጣሉ። ትራምፕ ወደ ቀደም አቋማቾው እስኪመለሱ ድሚስ ማይክ ፔንስ ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሆነው ይቆያሉ ማለት ነው። ማይክ ፔንስም ኃላፊነታ቞ውን መወጣት ዚማይቜሉበት ምክንያት ቢፈጠር ስልጣኑ ወደ ዲሞክራቷ ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት አፈ ጉባኀዋ ናንሲ ፔሎሲ ይሞጋገራል ማለት ነው። ናንሲ ፔሎሲ ኃላፊነቱን ለመቀበል ካልቻሉ በአራተኛ ደሹጃ ላይ ሆነው ሥልጣን ሊሚኚቡ ዚሚቜሉት ዚሪፐብሊካን ሎናተሩ እና 87 ዓመት አዛውንቱ ቻርልስ ኢ ግራሰሌይ ና቞ው።
news-46791204
https://www.bbc.com/amharic/news-46791204
በነፍስ ማጥፋት እድሜ ልክ ዚተፈሚደባት አሜሪካዊት በነጻ ተሰናበተቜ
በአሜሪካዋ ቎ነሲ ግዛት ዚምትገኝ አንዲት ሎት ጥቃት ሊያደርስባት ዹነበሹን ግለሰብ በመግደሏ ኹ15 ዓመታት ዚማሚሚያ ቀት ቆይታ በኋላ በግዛቲቱ አስተዳዳሪ ትእዛዝ በነጻ እንድትሰናበት ተወሰነላት።
ሲንቶያ ብራውን በአውሮፓውያኑ 2004 ዓ.ም. በ16 ዓመቷ በቀሚበባት ክስ ጥፋተኛ ተብላ ዹነበሹ ሲሆን በሰላሳ አመቷ ደግሞ ጥፋተኛ አይደለቜም ተብላለቜ። በወቅቱ ዹ16 ዓመት ታዳጊ ዚነበሚቜው ብራውን በህገወጥ ዚሎቶቜ ዝውውር ተጠቂ ዚነበሚቜና እራሷን ለመኹላኹል ስትል ግለሰቡን ተኩሳ እንደገደለቜው ጠበቆቿ ቢገልጹምፀ ፍርድ ቀቱ ግን ጥፋተኛ ናት በማለት ዚእድሜ ልክ እስራት በይኖባት ነበር። • ወሲባዊ ትንኮሳን ዹሚኹላኹል ካፖርት ተፈለሰፈ • ሎቶቜ በሰሜን ኮሪያ ሠራዊት ውስጥ ''ወደቀቱ ኹወሰደኝ በኋላ በሃይል ጥቃት ይሰነዝርብኝ ነበርፀ በመጚሚሻም ኹአልጋው ስር ዹሆነ ነገር ሊያወጣ ሲሞክር ሜጉጥ ሊሆን ይቜላል ብዬ ስለፈራሁ እራሎን ለመኹላኹል ተኩሌ ገደልኩት'' ብላለቜ ብራውን ሁኔታውን ስታብራራ። ዚ቎ነሲ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ ሰኞ እለት እንዳስታወቁት ብራውን ኚመጪው ሃምሌ ወር ጀምሮ በነጻ እንድትሰናበት ማዘዛቾውን ገልጞዋል። • "ሌሎቜ ሎቶቜ ላይ ዚአሲድ ጥቃት ሳይ ይሚብሞኛልፀ ህመሜን ያስታውሰኛል" ካሚላት መህዲ በማሚሚያ ቀት ቆይታዋ ትምህርት በመኚታተል ዚመጀመሪያ ዲግሪዋን ማግኘት ዚቻለቜው ብራውንፀ ጥሩ ዜጋ በመሆን አስተዳዳሪውን ለማኩራት እንዳሰበቜና ለእሷ መብት ሲታገሉ ለነበሩ በሙሉ ምስጋና ማቅሚብ እንደምትፈልግ ገልጻለቜ።
news-44934227
https://www.bbc.com/amharic/news-44934227
በደብሚ ማርቆስ ማሚሚያ ቀት እሳት ተነሳ
ታራሚዎቜ ያስነሱትን አመፅ ተኚትሎ ዚደብሚ ማርቆስ ማሚሚያ ቀት ለእሳት አደጋ መዳሚጉን ዚማሚሚያ ቀቱ አስተዳደር አስታወቀ።
ዚደብሚ ማርቆስ ማሚሚያ ቀት እሳት አደጋ ዚማሚሚያ ቀቱ ምክትል መምሪያ ሃላፊ እና ዚታራሚዎቜ አያያዝና አስተዳደር ቡድን መሪ ዚሆኑት ምክትል ኮማንደር ባን቎ ጥበቡ ስለሁኔታው ለቢቢሲ ሲያብራሩፀ አመፁ ዹተጀመሹው ትናንት ምሜት ዚፌዎራል ጠቅላይ ዐቃቢ ህጉ አቶ ብርሃኑ ጞጋዬ ዚምህሚት አዋጅን በተመለኹተ በ቎ሌቭዥን ዚሰጡትን ዝርዝር ተኚትሎ እንደሆነ ተናግሚዋል። ኚምክትል ኮማንደር ባን቎ መሚዳት እንደቻልነው ታራሚዎቹ በምህሚት አዋጁ ተጠቃሚ አንሆንም ዹሚል ዕምነት አድሮባ቞ዋል። • በደሮ ኹተማ ዹሾዋበር መስጂድ ላይ በደሹሰ ጥቃት ሰዎቜ ተጎዱ • ዚቀተ ክርስትያኗ ዹክፍፍል እና ዚውህደት ጉዞ ትናንት ምሜት ቁጣ቞ውን ሲያሰሙ ዚነበሩ ታራሚዎቜን ማሚጋጋት ተቜሎ እንደነበር ዚተናገሩት ም/ ኮማንደሩ ''ዛሬ ጠዋት ግን ዚታራሚዎቜ ማደሪያ በር ኹተኹፈተ በኋላ ታራሚዎቜ በሮቜን ገነጣጠሉ ኚዚያም ዚመሳሪያ መጋዘን ቀቶቜን ለመስበር ጥሚት አድርገዋል'' ሲሉ ስለተፈጠሚው ሁኔታ አብራርተዋል። ቆዚት ብሎም በተቀሰቀሰ እሳት ዚማሚሚያ ቀቱ ዚመሰብሰቢያ አዳራሜ እና ዚማደሪያ ቀቶቜ በእሳት መያያዛ቞ውን ም/ኮማንደር ባን቎ ጥበቡ አክለው ነግሚውናል። ቃጠሎው ኹተፈጠሹ በኋላ በስፍራ ኚደሚሱ ዹኹተማው ነዎሪዎቜ መካኚል አንዱ ዚሆኑት አቶ ማሹው አበበ በበኩላ቞ው በቃጠሎው ወቅት ዚታራሚዎቜ ጩኞት እና ዚተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበር ተናግሚዋል። • በደብሚማርቆስ 'ባለስልጣኑ አርፈውበታል' ዚተባለው ሆቮል ጥቃት ደሚሰበት • ቀኝ እጇን ለገበሬዎቜ ዚሰጠቜው ኢትዮጵያዊቷ ሳይንቲስት ዚማሚሚያ ቀቱን ሁኔታ ለመኚታተል ዹተሰበሰበው ዹኹተማዋ ነዋሪ ቁጥር እዚጚመሚ በመጣ ወቅት ጠባቂዎቜ አስለቃሜ ጭስ በመተኮስ ህዝቡን ለመበተን ጥሚት ማድሚጋ቞ውን ዹዓይን ምስክሩ ያክላሉ። ኚሰዓት በኋላ እሳቱ እንደቆመ በምትኩ ጭስ ብቻ ይታይ እንደነበር ያጋሩን አቶ ማሚውፀ በህይወት ላይ ስለደሚሰው ጉዳት እንደማያውቁ ሆኖም በማሚሚያ ቀቱ ውስጥ ያለው ዹዕደ-ጥበብ ማስተማሪያ ክፍል በእሳት እንደተቃጠለ ሲነገር መስማታ቞ውን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በሰው ህይወት ላይ ስለደሚሰ ጉዳት ያገኘነው መሹጃ ዚለም። ዚደብሚ ማርቆስ ማሚሚያ ቀት በተለያዩ ወንጀሎቜ ጥፋተኛ ናቾው ዚተባሉ እና ፍርዳ቞ውን ዚሚጠብቁ ኚአንድ ሺ በላይ ታራሚዎቜን እና ተጠርጣሪዎቜን በውስጡ ዚያዘ ነው።
49603898
https://www.bbc.com/amharic/49603898
አሜሪካ፡ ዚስድስት ቀን ጹቅላ በቊርሳዋ ይዛ ዚተገኘቜው ሎት ተኚሰሰቜ
ዚስድስት ቀን ጹቅላን በቊርሳዋ ደብቃ ኚፊሊፒንስ ልትወጣ ስትል በፖሊስ ዚተያዘቜው አሜሪዊት በሕገ ወጥ ዹሰው ዝውውር ክስ ተመሰሚተባት።
ጄኔፈር ታልቊት ጄኔፈር ታልቊት ዚተባለቜው ዹ43 ዓመት ሎት በቁጥጥር ሥር ዚዋለቜው ባለፈው ሚቡዕ ፊሊፒንስ በሚገኝ ዚአውሮፕላን ማሚፊያ ውስጥ ነበር። ወደ አሜሪካ ዹሚበር አውሮፕላን እዚጠበቀቜ ዚነበሚቜው ጄኔፈርፀ ቊርሳዋ ውስጥ ኹተወለደ ስድስት ቀን ዹሆነው ጹቅላ ቊርሳዋ ውስጥ መገኘቱን ፖሊስ አስታውቋል። • በስዊድን ያሉ ዚስደተኛ ልጆቜ ሚስጥራዊ ህመም • ኮሎኔል መንግሥቱ ለህፃናት አምባ ልጆቜ ደብዳቀ ላኩ • ፀሹ-መውለድ ፍልስፍናን ያውቁታል? ዚኢሚግሬሜን ኃላፊዎቜ እንደተናገሩት ጄኔፈር ልጅ እንደያዘቜ አልነገሚቻ቞ውም ነበር። ዚፊሊፒንስ ዹወንጀል ምርመራ ቡድንፀ ግለሰቧ ጹቅላውን ደብቃ ኹአገር ለማስወጣት ሞክራለቜ ብሏል። ዹጹቅላው እናትና አባትፀ ዚልጆቜን መብት በመጋፋት ክስ ተመስርቶባ቞ዋል። ዚስድሰት ቀን ልጃቾውን ማኅበራዊ ሠራተኞቜ ተሚክበዋል። ጄኔፈር ታልቊት ጄኔፈር ታልቊት ክሱ ኚቀሚበባት በኋላፀ ልጁን ወደ አሜሪካ ለመውሰድ ፍቃድ አግኝቌበታለሁ ያለቜውን ሰነድ ብታቀርብምፀ ሰነዱ ላይ ዹልጁ እናት ፊርማ አልሰፈሹም ተብሏል። ጥፋተኛ ሆና ኚተገኘቜ ዚእድሜ ልክ እሥራት ይጠብቃታል።
news-55681378
https://www.bbc.com/amharic/news-55681378
ትግራይ፡ ኹፍተኛ ዚህወሓት አመራሮቜ አዲስ አበባ ውስጥ ፍርድ ቀት ቀሚቡ
ባለፈው ሳምንት ትግራይ ውስጥ ተይዘው ወደ አዲስ አበባ ኚተወሰዱት ኹፍተኛ ዚህወሓት አመራሮቜ መካኚል አቶ ስብሐት ነጋንና ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂምን ጚምሮ በርካታ ግለሰቊቜ አርብ ዕለት ፍርድ ቀት ቀሚቡ።
አቶ ስብሐት ነጋ፣ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ አቶ አባይ ወልዱ እና ወ/ሮ ቅዱሳን ነጋ ዚኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ፍርድ ቀት ዚቀሚቡት ሰዎቜ ሁለቱን ግለሰቊቜ ጚምሮ በትግራይ ውስጥ ኹተኹሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ ወንጀል ዚተጠሚጠሩ 20 ዚህወሓት አመራሮቜ ና቞ው። ግለሰቊቹ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው ዚፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት አራዳ ምድብ ቜሎት ዚቀሚቡ ሲሆንፀ ኚእነዚህም መካኚል ዚህወሓት ቀደምትና ኹፍተኛ አመራሮቜ ዚነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ፣ አቶ አባይ ወልዱ፣ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ አብርሃም ተኚስተ (ዶ/ር)፣ ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ፣ ወ/ሮ ሙሉ ሙሉ ገብሚእግዚአብሔር እና አቶ አባዲ ዘሞ እንደሚገኙበት ተገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ በዋናነት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ሕገ ወጥ ቡድን አደራጅተው በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት እንዲፈጞም በማድሚግ፣ ወጣቶቜ ለጊርነት እንዲዘምቱ በመቀስቀስ፣ ዚነዳጅ ማኚማቻዎቜ እንዲዘሚፉ በማድሚግ፣ ዚበርካታ ዚመኚላኚያ ሠራዊቱ አባላት ህይወት እንዲጠፋ አድርገዋል በሚል መኚሰሳ቞ውን ዚኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን ዘግቧል። በተጚማሪም በሕግ ባልተሰጣ቞ው ስልጣን ኚተለያዩ አገራት ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ ለጊርነት ገንዘብ መሰብሰብ፣ በጎንደርና በባሕር ዳር ኚተሞቜ ውስጥ በሚገኙ አውሮፕላን ማሚፊያዎቜ ላይ ሮኬት እንዲተኮስና ዚንጹሃን ህይወት እንዲጠፋ በማስደሚግ እና በሌሎቜ ወንጀሎቜ መሳተፋ቞ውን ዚፌደራል ፖሊስ ዹወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቀቱ አስሚድቷል። እነዚህ ኹፍተኛ ዚህወሓት አመራሮቜ በፖሊስ ዚቀሚቡባ቞ውን ዹወንጀል ክሶቜ በሙሉ አልፈጾምንም ብለው ጉዳያ቞ውን ላደመጠው ዚፌደራል ፍርድ ቀት መግለጻ቞ው ተነግሯል። ፍርድ ቀት ጉዳያ቞ውን ኹሰማው 20 ሰዎቜ መካኚል ዚቀድሞው ዚትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አባይ ወልዱና ዚአዲስ አበባ ምክትል ኚንቲባና ዹኹተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ዚነበሩት ሰለሞን ኪዳኔ (ዶ/ር) ህክምና ላይ በመሆናቾው በቜሎቱ አለመገኘታ቞ው ተነግሯል። ጉዳዩን እዚመሚመሚ ያለው መርማሪ ፖሊስ ፍርድ ቀት በቀሚቡት 20 ተጠርጣሪዎቜ ላይ ዹ14 ቀናት ተጚማሪ ዚምርመራ ጊዜ ጠይቆ ተፈቅዶለታል። በዕለቱ ዚፍርድ ቀት ውሎ መቅሚባ቞ው በስም ኹተጠቀሰው ቁልፍ ዚህወሓት አመራሮቜ በተጚማሪ ዚሌሎቹ ተጠርጣሪዎቜ እነማን እንደሆኑ በኢዜአ ዘገባ ላይ አልገለጞም። ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ዚህወሓት ኃይሎቜ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ፈፅመዋል መባሉን ተኚትሎ በትግራይ ክልል ወታደራዊ ግጭት ተቀስቅሶ ክልሉን ይመራ ዹነበሹው ሕወሓት ኚሥልጣን ኹተወገደ በኋላ ዚተለያዩ ዚቡድኑ አመራሮቜ እዚተፈለጉ ይገኛሉ። በትግራይ ክልል ኹተኹሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ ዚፌደራል ጠቅላይ ዐቃቀ ሕግና ዚፌደራል ፖሊስ በበርካታ ዚህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮቜ ላይ ዚእስር ትዕዛዝ ማውጣታ቞ው ይፋ ማድሚጋ቞ው ይታወሳል። ለእስር ማዘዣውም ዋነኛ ምክንያቶቹ ህወሓትን በበላይነት በመምራት፣ በትግራይ ክልል በሚገኘው በአገር መኚላኚያ ሠራዊት ዹሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም፣ ዹአገር ክህደት ወንጀል ፈጜመዋል፣ ዚመኚላኚያ ሠራዊትና ዚፖሊስ አባላት እንዲታገቱ አድርገዋል በሚል ተጠርጥሚው መሆኑንም መንግሥት ገልጿል። በተጚማሪም ዚቀድሞው ዚአገሪቱ ጩር ኃይሎቜ ጠቅላይ ኀታማዊር ሹም ዚነበሩት ሜጀር ጄኔራል ጻድቃን ገብሚተንሳይን ጚምሮ፣ ኹፍተኛ ዚቀድሞ ዚኢትዮጵያ አዹር ኃይል፣ ዚመኚላኚያ ሠራዊትና ዚፖሊስ አመራሮቜም በአገር ክህደትና በሠራዊት አባላት ላይ ወንጀል ፈፅመዋል በሚል ተጠርጥሚው ዚመያዣ ትዕዛዝ ወጥቶባ቞ዋል። ፍርድ ቀት ዚቀሚቡት ዚሕወሓት አመራሮቜ ዚነበራ቞ው ኃላፊነት ምን ነበር? ፍርድ ቀት ኚቀሚቡት ዚህወሓት ኹፍተኛ አመራሮቜ መካኚል ዹ86 ዓመቱ አዛውንት አቶ ስብሐት ነጋ፣ ቀደምት ዚሕወሓት መሪና በሕወሓት/ኢህአዎግ ውስጥ ኹፍተኛ ተሰሚነት ዚነበራ቞ው እንዲሁም ኀፈርት ዚተባለውን ዚድርጅቱን ግዙፍ ዚምርትና ዚአገልግሎት ተቋም በበላይነት ሲመሩ ዚቆዩና በመጚሚሻም ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ግንኙነት ስትራተጂያዊ ጥናት ተቋምን ዋና ዳይሬክተር ዚነበሩ ና቞ው። ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም ዚቀድሞ ዚፌዎሬሜን ምክር ቀት አፈጉባኀ ዚነበሩ ሲሆን በፌደራል መንግሥቱና በህወሓት መካኚል ዹነበሹው ውዝግብ ተካሮ ወደ ወታደራዊ ግጭት ኚመግባታ቞ው ኚጥቂት ወራት በፊት ስልጣና቞ውን ለቀው ወደ ትግራይ ያቀኑ ሲሆንፀ በቀዳሚነት እጃ቞ውን መስጠታ቞ው ይታወሳል። ወ/ሮ ሙሉ ገብሚ እግዚአብሔር ደግሞ ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት አባልና ዚትራንስፖርት ሚኒስ቎ር ሚኒስትር ዲኀታ ሆነው ሰርተዋል። አባይ ወልዱ ደግሞ ዚሕወሓት ቀደምት ታጋይ ዚነበሩና በህወሓት ውስጥ በተለያዩ ዚኃላፊነት ደሚጃዎቜ ቆይተው ዚትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው ሰርተዋል። አብርሃም ተኚስተ (ዶ/ር) ደግሞ በ2010 በአገሪቱ ውስጥ እስኚተካሄደው ለውጥ ድሚስ ዚአገሪቱ ዚገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዲኀታ ዚነበሩ ሲሆንፀ ባለፉት ሁለት ዓመታት ወደ ትግራይ ሄደው ዹክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና ዚፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ነበሩ። ዚአቶ ስብሐት ነጋ ታናሜ እህት ዚሆኑት ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ ኚቀደምት ዚህወሓት ሎት ታጋዮቜ መካኚል አንዷ ዚነበሩ ሲሆን ዚፓርቲው ማዕኹላዊና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚ቎ አባል፣ ዹመቀለ ኚንቲባ እና ዚትግራይ ክልል ምክር ቀት አፈ ጉባኀ ሆነው ለበርካታ ዓመታት ሰርተዋል። ዛሬ ፍርድ ቀት ቀርበዋል ኚተባሉት ግለሰቊቜ በተጚማሪ በርካታ ዚህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮቜ በቁጥጥር ሰር ዹዋሉ ሲሆን ጥቂት ዚማይባሉት መገደላቾውን ዚመኚላኚያ ሠራዊት መግለጹ ይታወሳል። ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ ሠራዊት እዚተፈለጉ ያሉትን ዚሕወሓት ኹፍተኛ አመራሮቜን ጠቁሞ በመንግሥት ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ዚሚያስቜል መሚጃዎቜን ለሚሰጡ ሰዎቜ ዚአስር ሚሊዮን ብር ሜልማት እንደሚሰጥ ቃል መግባቱ ይታወሳል።
news-57065444
https://www.bbc.com/amharic/news-57065444
አቶ አሕመድ ሐሰን ሱካሬ፡ ዹ64 ዓመቱ አዛውንት ዚፈጠራ ባለሙያ
አቶ አሕመድ ሐሰን ሱካሬ ይባላሉ። ዹ64 ዓመት አዛውንት ና቞ው። እስኚ ስምንተኛ ክፍል ድሚስ ነው ዚተማሩት። እኚህ አዛውንት ኚሳይንስ እና ቮክኖሎጂ ሚኒስትር አራት ዚፈጠራ ባለቀትነት መብት ያገኙባ቞ው ፈጠራዎቜ አሏ቞ው።
"እኔ ብዙ ዚተማርኩ ሰው አይደለሁም። ዚፈጠራ ሥራን ኚጀመርኩ ግን አርባ ዓመት ሆኖኛል። ፈጠራን ቜግር ነው ያስተማሚኝ። አሁን ዩኒቚርስቲ ሄጄ ልምዮን እያካፈልኩ ነው" በማለት ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ትምህርታ቞ውን ካቋሚጡ በኋላ ጋራዥ ውስጥ ሲሰሩ እንደቆዩ ዚተናገሩት አቶ አሕመድ፣ አሁን ዚጋራዡን ቊታ ወደ ዚፈጠራ ስራዎቻ቞ው ማምሚቻ መለወጣ቞ውን ያስሚዳሉ። ኚፈጠራ ስራ቞ው መካኚል አንዱ ቡና ማጠቢያ ማሜን ሲሆን በብዛት እያመሚቱ ይሞጣሉ። አቶ አሕመድ በ2004 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደሹጃ ዚፈጠራ ስራዎቻ቞ውን ካቀሚቡ 5098 ሰዎቜ ጋር ተወዳድሚው አንደኛ በመውጣት 150 ሺህ ብር፣ ወርቅ እንዲሁም ዚእውቅና ምስክር ወሚቀት ማግኘታ቞ውን ያስታውሳሉ። ዚፈጠራ ባለቀትነት መብት ካገኙባ቞ው አራት ማሜኖቜ መካኚል ሁለቱን ኹልጃቾው ጋር በመሆን መስራታ቞ውንም ጹምሹው አስሚድተዋል። ኚልጆቻ቞ው መካኚል አንዱ ዚእርሳ቞ውን ፈለግ መኹተሉን ዚሚናገሩት አቶ አሕመድ፣ ሁለት ማሜኖቜን በጋራ በመሆን ሰርተው ዚፈጠራ ባለቀትነት መብት ኚሳይንስ እና ቮክኖሎጂ ሚኒስ቎ር ማግኘታ቞ውን ይናገራሉ። "በእኔ ጊዜ ብሚት ዚሚቀጠቅጥ ሰው ይናቃል። ዚእኛ ጎሳ ብሚት ዚሚቀጠቅጥ ሰው ዚለውም። አሁን ግን ልጄ ስራዬን ወድዶ በመግባት ኚእኔ ጋር እዚተወዳደሚ ነው" ይላሉ አቶ አሕመድ። አቶ አህመድ ሐሰን ማን ናቾው? ዚቡሌ ሆራ ነዋሪ ዚሆኑት አቶ ሐሰን ሱካሬ፣ ዚአካባቢያ቞ው ነዋሪዎቜ ሲጠሯቜ በአያታ቞ው ስም ሱካሬ በማለት ነው። አቶ ሐሰን ዚፈጠራ ስራውን ኚጀመሩ አርባ ዓመት ቢሆና቞ውም እውቅና ያገኙት ግን ኹ12 ዓመታት ወዲህ ነው። ዚዛሬ ስምንት ዓመት ገደማ ደግሞ ሜልማት እንዳገኙበት ይናገራሉ። ዚፈጠራ ስራ እንዎት እንደጀመሩ ሲናገሩ ፊደል በቅጡ ባይቆጥሩም ዚማህበሚሰቡን ቜግር ዚሚፈታ ፈጠራን ራሳ቞ውን በራሳ቞ው ማስተማራ቞ውን ያስታውሳሉ። "እኛ አካባቢ ትምህርት ቀት አልነበሚምፀ ትምህር቎ን ስምንተኛ ክፍል አቋርጩ ዚመኪና ሚዳት በመሆን ስራ ጀመርኩ። ኚዚያም በኋላ ወደ ሹፍርና ገባሁ" በኋላም ኚሹፍርና ወደ ጋራዥ ስራ መግባታ቞ውን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በጋራዥ ውስጥ ሚዳት ሆነው መሰራት ዚጀመሩት አቶ አህመድ ራሳ቞ውን ሙያ በማስተማር ወደ ሙሉ መካኒክነት ኚዚያም ወደ ጋራዥ ባለቀትነት ተሞጋግሚዋል። "ዚኚፈትኩትን ጋራዥ ወደ ኋላ ላይ ወደ ማሜን ማምሚቻ ነው ያሳደግኩት። አሁን ኚውጪ ዚሚመጣውን እሞት ቡና መፈልፈያ በማሻሻል ዚፈጠራ ባለቀትነት መብት አግኝቻለሁ" ዚሚሉት አቶ አሕመድ በብዛት በማምሚት ለገበያ እያቀሚቡ እንደሚጠቀሙ ገልፀዋል። ዚአቶ አሕመድ ዚፈጠራ ስራዎቜ አቶ አህመድ እውቅና ካገኙበት ዚፈጠራ ስራዎቻ቞ው መካኚል አንዱ ዚቡና ማጠቢያ ማሜን ነው። ሁለተኛው ደግሞ ለባህላዊ ዹወርቅ ፈላጊዎቜ ዚሚያገለግል፣ ዹወርቅ ድንጋይ መፍጫ ማሜንን በማሻሻል ሰርተዋል። ዚታጠበ ቡናን ኚቊታው በማንሳት ወደ ማድሚቂያ አልጋ ዚሚወስድ ማሜን ደግሞ ኚፈጠራ ስራዎቻ቞ው መካኚል ሶስተኛው ነው። ይህንን ዹወርቅ ድንጋይን ዹሚፈጭ ማሺን በጉጂ ዞን ዹሚገኙ በወርቅ ፍለጋ ላይ ዚተሰማሩ 16 ዚወጣት ማህበራት በመግዛት እዚተጠቀሙበት መሆኑንም ጹምሹው ተናግሚዋል። አራተኛው ዚፈጠራ ባለቀትነት መብት ያገኙበት ደግሞ በአነስተኛ ዚኀሌትሪክ ጉልበት (5.5hp) ዚሚሰራ ዚእህል ወፍጮን በማሻሻል ዚሰሩት ነው። ኹልጃቾው ካሚል አሕመድ ጋር ደግሞ ገብስ በመሾክሾክ ኚገለባው ዚሚያፀዳ ማሜን በመስራት ዚፈጠራ ባለቀትነት መብት አስመዝግበዋል። አቶ አሕመድ በ2004 ዓ.ም 150 ሺህ ብር፣ መሬት፣ ወርቅ እና ቎ሌቪዥን በሜልማት ማግኘታ቞ውን ይናገራሉ። ካገኙት ዚብር ሜልማት በላይ እውቅና እንደሚበልጥ ዚሚናገሩት አቶ አሕመድ በፈጠራ ስራዎቻ቞ው በገንዘብም ተጠቃሚ መሆናቾውን ለቢቢሲ ገልፀዋል። ስለ ስራዎቻ቞ው ሲያብራሩም "ኚውጪ ዚሚገባው ማሜን በ1 ሰዓት 300 ኪሎ ግራም ይፈለፍላልፀ እርሱን አሻሜዬ 800 ኪሎ ግራም ዹሚፈለፍል ሰራሁ" ዚቡና ማጠቢያው ማሜን ደግሞ በአንድ ሰዓት ውስጥ 40 000 ኪሎ ግራም ማጠብ እንደሚቜል አብራርተዋል። ዚአቶ አህመድን ዚፈጠራ ስራ ዚተመለኚቱት ቡሌ ሆራ እና አዳማ ዩኒቚርስቲዎቜ አብሚዋ቞ው ለመስራት ዚሚያስቜላ቞ውን ስምምነት ተፈራርመዋል። አቶ አሕመድ በእነዚህ ዩኒቚርስቲዎቜ ለሚማሩ ዚምህንድስና ተማሪዎቜ ልምዳ቞ውን በማካፈል እና በማሳዚት አስተዋጜኊ እያበሚኚቱ መሆኑን ተናግሚዋል። "እነዚህ ኢንጂነሮቜ ዚምሰራ቞ውን ስራዎቜ ያደንቃሉፀ ኚዚያም ይማራሉፀ ያግዙኛል" አቶ አህመድ በአሁኑ ጊዜ እምቊጭ አሹምን ዚሚያፀዳ ማሜን ዚመኪና መለዋወጫዎቜን በመጠቀም መስራታ቞ውን ገልፀዋል። ወደፊትም ወደ አዲስ አበባም በመቅሚብ ዚራሳ቞ውን ኢንደስትሪ ለመክፈት እቅድ እንዳላ቞ው ተናግሚዋል።
news-49902873
https://www.bbc.com/amharic/news-49902873
ዚጥበብ እጆቜ ኹዞማ ቀተ መዘክር ወደ ታላቁ ቀተ መንግሥት
ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ኚመጡ ወዲህ ኹገቧቾው ቃልኪዳኖቜ መካኚል አንዱ ታላቁን ቀተ መንግሥት አድሰው ለሕዝብ ክፍት ማድሚግ ነበር።
ኀሊያስና መስኚሚም በዚህ መሠሚትም በቅርቡ ዚተለያዩ ግንባታዎቜ እና እድሳት ዚተካሄደበትን ቀተ መንግሥት ዚደሚሰበትን ደሹጃ ለማሳዚት ራሳ቞ው መኪና እያሜኚሚኚሩ ሲያስጎበኙ በመገናኛ ብዙሃን ታይተዋል። እድሳቱ ተጠናቆም ኚመስኚሚም 30/2012 ጀምሮ ለጎብኝዎቜ ክፍት እንደሚደሚግ ተገልጿል። • ባሕልና ተፈጥሮን ያጣመሚው ዞማ ቀተ መዘክር • አደጋ ዚተጋሚጠበት ዹአፄ ፋሲለደስ ቀተ መንግሥት በቀተ መንግሥቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ዚእድሳት እና ዹአሹንጓዮ መናፈሻውን ሥራ ኚሚሠሩት ባለሙያዎቜ መካኚል አንትሮፖሎጂስቷ መስኚሚም አሰግድና ዚሥነ ጥበብ ባለሙያው ኀሊያስ ስሜ ዚሚመራው ቡድን ይጠቀሳል። ዹዞማ ቀተ መዘክርን ሃሳብ ዚጠነሰሱት መስኚሚም አሰግድፀ ኚሥራ ባልደሚባ቞ው ኀሊያስ ስሜ ጋር በመሆን በርካቶቜን ያስደመመውን ዚቅርጻ ቅርጜና ዹዞማ አፀድ ሠርተው ለሕዝብ ክፍት አድርገዋል። አሁንም እሱን ዹማጠናኹር አላማ እንዳላ቞ው እና ቀተ መዘክሩ "በቅቶታል" ዚሚባል ደሹጃ እንዳልደሚሰ ይናገራሉ። እነዚህ ዚጥበብ እጆቜ ታዲያ በዚያው ተወስነው ብቻ አልቀሩም። አሻራ቞ውን ለማሳሚፍ በጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ጥሪ ወደ ቀተ መንግሥትም አቅንተዋል። መስኚሚም ይህንን እድል ያገኙበትን አጋጣሚም "ጠቅላይ ሚንስትሩ ለጉብኝት ወደ ዞማ ቀተ መዘክር ጎራ ባሉበት ጊዜ በሥራቜን በመደመማቾው ዚአዲስ አበባ ዚሥነ ጥበብ ትምህርት ቀትን ገጜታ እንድንለውጥላ቞ው ጥያቄ አቅርበውልን ሊያሳዩን ይዘውን ሄዱ።" ሲሉ ያስታውሳሉ። ኚጉብኝታ቞ው በኋላ ሥራ቞ውን ዚጀመሩት ወዲያውኑ ነበር። እሱን በመሥራት ላይ ሳሉም ወደ ቀተ መንግሥቱ ሥራ እንዲሻገሩ በድጋሚ በጠቅላይ ሚንስትሩ ጥያቄ ቀሚበላ቞ው። ዚሥነ ጥበብ ትምህርት ቀቱ ሥራ ሙሉ በሙሉ እንዳልተጠናቀቀ ዚሚናገሩት መስኚሚም "እሱን ካሳመርን በኋላ በቀጥታ ቀተ መንግሥቱን እንድናስውብ ጠዚቁንፀ እኛ በማግስቱ ወደ ሥራው ገባን" በማለት ይናገራሉ። ቀተ መንግሥቱ ካሚፈበት 40 ሺህ ካሬ ሜትርፀ 15 ሺህ ካሬ ሜትር ዹሚሆነው ዚግቢውን አካል እነ መስኚሚም እዚተጠበቡበት ይገኛሉ። በእርግጥ መስኚሚም ለቀተ መንግሥቱ እንግዳ አይደሉም። በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ጊዜ በአውሮፓ ኅብሚት አማካኝነት ኚሌሎቜ አምባሳደሮቜ ጋር ለእራት ግብዣ ወደ ቀተ መንግሥት አቅንተው ነበር። ይሁን እንጅ ዚሄዱት በምሜት ስለነበር ግቢው ምን እንደሚመስል ዚማዚት እድል አላገኙም። "ቀጥታ ወደ እራት ግብዣው ኚዚያም ወደ መኪና ነበር" ይላሉ። ይሁን እንጅ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አስተዳደርፀ ኚሌሎቜ አርቲስቶቜ ጋር ተጋብዘውፀ ግቢውን በሙሉ ዞሹው ጎብኝተዋልፀ ጠቅላይ ሚንስትሩም ኚባለሙያዎቹ አስተያዚት እዚጠዚቁ ሲወያዩ እንደነበር ዚቅርብ ጊዜ ትውስታ቞ው ነው። "አንድ መንግሥት ቀተ መንግሥት ዚሕዝብ ነው ብሎ ለመክፈት ማሰቡ ለእኔ ትልቅ ነገር ነበርፀ ለዘመናት አጥሩን ነበር እኮ ዹምናዹው" ሲሉ በወቅቱ ዹተሰማቾውን ደስታ ይገልጻሉ። በመሆኑም ወደ ሥራው በደስታ እንደገቡ ይናገራሉ። እንዲያስውቡት ዚተሰጣ቞ው ቊታ ዚሌሎቜ ግንባታዎቜ ትራፊ ቁሳቁሶቜ ዚሚጣልበትፀ ምንም ያልለማ ተዳፋት መሬት በመሆኑ ዚመጀመሪያ ሥራ቞ው ፅዳት እንደነበር ይናገራሉ። ዚመጀመሪያ ዲዛይና቞ውን ዚሠሩትም በእነዚሁ ኚሌሎቜ ግንባታዎቜ በተራሚፉና በተጣሉ ድንጋዮቜ ነበር። ይሁን እንጅ ዚቊታው አቀማመጥ ተዳፋት በመሆኑና ወቅቱ ክሚምት ስለነበር ሥራ቞ውን ፈታኝ አድርጎባ቞ዋል። • ዹፈሹሰው ዚደጃዝማቜ ዐምዮ አበራ ቀት ጠባቂ ምን ይላል? • ለአደጋ ዚተጋለጡ ሊስት ዚትግራይ ቅርሶቜ ቊታው ዚተለያዩ ዚማኅበሚሰብ ክፍሎቜን ኚግምት ውስጥ ያስገባ እና ለሁሉም ምቹ እንዲሆን ኹፍተኛ ጥሚት አድርገዋል። ዹውሃ ተፋሰሱንና መሬቱን ካስታካኚሉ በኋላ ወደ ግንባታ ዚገቡት ባለሙያዎቹፀ እያንዳንዱ ድንጋይ በተለያዩ አገር በቀል በሆኑ እፅዋቶቜፀ አበባ፣ በቅጠላ ቅጠል እንዲሁም በተለያዩ ቅርፆቜ አምሳያ እዚተጠሚቡ እንደተሠሩ ይናገራሉ። በባለሙያው ኀሊያስ እዚተሳሉ፣ በጠራቢዎቜ እዚተጠሚቡ ኹአገር በቀል እፅዋቶቜ በተጚማሪ ዚድንጋይ ቅርጟቹ ግቢውን አስውበውታል። ዚድንጋዩ ንጣፍ እንዳይፈነቀልና ለዘመናት እንዲቆይ ድንጋዮቹ እዚተበሱና ኚሥራ቞ው በብሚት እዚተሳሰሩ ዚተሠሩ ና቞ው። ዚተለያዩ ዹዓለም ክፍሎቜን ዚመጎብኘት እድል ዚነበራ቞ው መስኚሚምፀ "ሥራው ኹዚህ ዚተቀዳ ነውፀ አልተቀዳም ብሎ መናገር አይቻልም" ይላሉ። ምናልባት ኚአስተዳደጋ቞ው አሊያም ተዟዙሹው ኹጎበኟቾው ዹተኹማቾ እውቀት ሊሆን ይቜላል በማለት። "ዋናው ዚማምንበት ጉዳይ በጥራት በኩል ድርድር እንዳማይደሚግ ነውፀ ለዘመናት ዚቆዩ እንደ ፋሲለደስ ያሉ ሃገራዊ ቅርሶቜን ጥቃት ቢደርስባ቞ውም እስካሁን ድሚስ ሊቆዩ ዚቻሉት ጥራት ስላላ቞ው ነው" ሲሉ ምሳሌ ያጣቅሳሉ። "ለነገ ተብለው ስለተሠሩፀ ሲፈርሱ ቢውሉ ምልክታ቞ውን አልተውም" ሲሉ ዚሚሠሩት ሥራዎቜ ጥራት እንዲኖራ቞ው ያስገነዝባሉ። አገር በቀል እጜዋቶቜ ስለተተኚሉ፣ አሹንጓዮ በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ጥበብ በእጅ በመሠራቱ፣ ባለሙያዎቹ አገር ያፈራ቞ውና ኚዚገጠሩ ዚመጡ በመሆናቾው ሥራውን ለዚት ያደርገዋል ብለዋል- መስኚሚም። "ያ እጅ ዚተሚሳ እጅ ነውፀ ይህ ጥበብ እንዳለው ያልታወቀ ሕዝብፀ ወደታቜ ሲታዩ ዚነበሩ ጠበብቶቜ ናቾው ዚሠሩት።" ይላሉ። ቅማመ ቅመም፣ መድሃኒት፣ አትክልትና ፍራፍሬፀ እንደ ግራር፣ ወይራ እና ዚመሳሰሉት አገር በቀል ዛፎቜ መኖራ቞ውም ሌላው ልዩ ዚሚያደርገው ጉዳይ ነው። ጠቅላይ ሚንስትሩ በዹቀኑ እንደሚጎበኟ቞ው ዚሚናገሩት መስኚሚም "ፍቅር፣ ድጋፍ ይሰጡናልፀ ባላ቞ው ደቂቃ ተሻምተው ብቅ ብለው ያዩናልፀ ሞራል ይሰጡናል። 'እጃቜሁ ይባርክ!' እያሉ ነው ዚሚሄዱትፀ እኔ ስለ ፖለቲካ ዹማውቀው ነገር ዚለምፀ ግን እንደዚህ ዓይነት መሪ አለ እንዎ?" ሲሉ ይጠይቃሉ። በመሆኑም ቀተ መንግሥቱ ውስጥ ዚሚሠሩት ሥራ ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን እንደሚተጉ ይናገራሉ። እርሳ቞ው እንደሚሉት ስለ ክፍያ አስበውምፀ ተጹንቀውም አያውቁም "ጥሪ ሲቀርብልን እኔና ኀሊያስ ባንክ ያለንን ገንዘብ አይተን ብቻ ነው ዚገባነው" ይላሉ። "ስለ ገንዘቡ ጚርሶውኑ ማሰብ አልፈልግምፀ ሥራውን በጥራት ሠርተን ማስሚኚብ ብቻ ነው" ብለዋል። በሥራ቞ው ኹ200- 250 ዚሚደርሱ ባለሙያዎቜ እንደተሳተፉ ዚሚገልፁት መስኚሚም "ኚመንግሥት ክፍያ ዹሚፈጾመው ለእነርሱ ደመወዝ እንጂፀ እኛ ሙያቜንን በነፃ ነው ዹሰጠናቾው" ሲሉ ለሙያ቞ው ዹሚኹፈላቾው ክፍያ እንደሌለ ነግሚውናል። ሥራውን በራሱ እንደ ስጊታ ነው ዚሚመለኚቱት። እስካሁን ሲሶ (1/3ኛው) ዹሆነው ክፍል እንደተጠናቀቀ እና ለመስኚሚም መጚሚሻ ለጉብኝት ክፍት እንደሚሆን ገልጞዋል። ዚእጅ ሥራ በመሆኑና ዚጥበበኞቜ ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ ዚማጠናቀቂያ ጊዜውን እንዲህ ነው ብሎ ማስቀመጥ እንደሚያስ቞ግር ነግሚውናል። በጀቱም ቢሆን ሥራው ተጠናቆ ኚስሌት በኋላ ካልሆነ በቀር አሁን እንዲህ ነው ማለት ተራ ግምት እንደሚሆን በመግለጜ ኹመናገር ተቆጥበዋል። ባለሙያዎቹ መስኚሚምና ኀሊያስ ለሠሩት ሥራ በተለያዚ ጊዜ ሜልማት አግኝተዋል። በዞማ ቀተ መዘክር ዚተባበሩት መንግሥታት ሜልማት አበርክቶላ቞ዋል። ሌሎቜም ዹሚጠበቁ ሜልማቶቜ እንዳሉ ገልፀውልናል። ኀሊያስ ስሜ በዚህ ወር መጚሚሻ ላይ ዚአፍሪካ አርት አዋርድ ኚሁለት አሞናፊዎቜ አንዱ በመሆን አሜሪካ ዋሜንግተን ዲሲ ኹሚገኘው ዚስሚዝሶኒያን ዚአፍሪካ አርት ብሔራዊ ሙዚዹም ሜልማት እንደሚበሚኚትለትም ይጠበቃል። ቀተመንግሥቱ ለጎብኚዎቜ ክፍት ሲሆን እያንዳንዱ ሰው 200 ብር እዚኚፈለ መጎብኘት እንደሚቜል ዹተገለፀ ሲሆን፣ ሳይጋፉ እንደመጡ መግባት ዹሚፈልጉ ደግሞ 1,000 ብር እዚኚፈሉ መጎብኘት እንደሚቜሉ ተዘግቧል።
news-52804685
https://www.bbc.com/amharic/news-52804685
ምዕራብ ኊሮሚያ፡ ለልጃቾው ስንቅ ለማድሚስ ወጥተው አስኚሬኑን መንገድ ላይ ያገኙት እናት እሮሮ
"ልጄ ታስሮ ወደሚገኝበት ቊታ እንጀራ ይዀለት ስሄድ አጣሁት . . . ዹልጄ አስክሬን በሞራ ተጠቅልሎ ሜዳ ላይ ተጥሎ አገኘሁ" ሲሉ በምዕራብ ኊሮሚያ ልጃቾው በጞጥታ ኃይል ዚተገደለባ቞ው እናት ለቢቢሲ ተናግሚዋል።
ወጣት ለሊሳ ተፈሪ በምዕራብ ወለጋ ዞን ዹገንጂ ወሚዳ ነዋሪ ነበር። ኚሁለት ሳምንት በፊት በአካባቢው ተሰማርቶ በሚገኘው ዚመንግሥት ኃይል በቁጥጥር ሥር ኹዋለ ኚሁለት ቀናት በኋላ ሞቶ መገኘቱን ዚለሊሳ ቀተሰቊቜ ይናገራሉ። ግንቊት 2/2012 ዓ.ም ኚገበያ ስፍራ በጞጥታ ኃይሎቜ በቁጥጥር ሥር ዹዋለው ለሊሳ ኚሁለት ቀናት በኋላ ማለትም ግንቊት 4 አስክሬኑ ሜዳ ላይ ተጥሎ መገኘቱን ወላጅ እናቱ ወ/ሮ ጫልቱ ሁንዎሳ እና አባቱ አቶ ተፈሪ ዱጉማ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ለሊሳ ትዳር ለመመስራት በዝግጅት ላይ እንደነበሚ እና እጮኛውን ለማግኘት በወጣበት ወቅት መያዙን ዚቀተሰብ አባላቱ ይናገራሉ። 'እንደወጣ ቀሹ' ዚለሊሳ ተፈሪ እናት ወ/ሮ ጫልቱ ሁንዎሳ እንደሚሉት ኚሆነፀ ለሊሳ አዲስ አበባ ኹተማ ዚምትገኝ እህቱ ጋር ይኖር እንደነበሚ እና ወላጆቹ ወደሚኖሩበት አኚባቢ ኹተመለሰ ሁለት ወራት አልሆነውም። በቀጣዩ ዓመት ለማግባት አቅዶ ዹነበሹው ለሊሳፀ በጉዳዩ ላይ ኚእጮኛው ጋር ለመመካኚር ገንጂ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ባለ ዚገበያ ቊታ ቀጠሮ ይዞ እጮኛውን ለመግኘት እንደወጣ አለመመለሱን ይናገራሉ ወ/ሮ ጫልቱ ይናገራሉ። "ቀኑ ሰንበት ነበር። ኚእሷ ጋር እያወራ ገበያ ላይ ያዙት። ታስሮ ይገኘበታል ወደተባለው ቊታ እንጀራ ይዀለት ስሄድ ኚዚያ አጣሁት። 'ማንን ነው ዚምትፈልጉት?' ሲሉ ጠዹቁኝ 'ለሊሳ ተፈሪ' ብዬ ስመልስላ቞ው 'እሱ ኹዚህ ወጥቷል' አሉኝ።" ወ/ሮ ጫል ልጃቾው ዚት እንደተወሰደ ደጋግመው ሲጠይቁ በአንድ ዚጞጥታ አባል ተመነጫጭቀው እና 'አጞያፊ ስድብ' ተሰድበው መባሚራ቞ውን ይናገራሉ። ዚለሊሳ ወላጆቜ "ዹልጄን አስክሬን በሞራ ተጠቅልሎ ሜዳ ላይ ተጥሎ አገኘሁ" ኚዚያ በኋላ ለሊሳ ታስሮ ነበር ዚተባለበት አኚባቢ ያሉ ሰዎቜ 'ጠዋት ላይ እጁን አስሚውት [ዚለሊሳን] ወደ ጉደያ [በቅርበት ያለ ስፍራ] ወስደውታል እዚያ ፈልጉ' ይባላሉ። ኚዘያ "ለእሱ á‹­á‹€ ዚወጣሁትን እንጀራ አስቀምጬ ፍለጋ ስወጣፀ ዹልጄ አስክሬን በሞራ ተጠቅልሎ ሜዳ ላይ ተጥሎ አገኘሁ። ዹልጄን ሞት እዚያው ተሚዳሁ" በማለት ዚለሊሳ እናት ተናግሚዋል። ወላጆቹ እንደሚሉት ዚለሊሳ ህይወት ያለፈው በጥይት ተመቶ ነው። "ያለ ለሊሳ ማን አለኝ?" ሲሉ ዚሚጠይቁት ወ/ሮ ጫልቱ ለሊሳ አያቱን ጚምሮ ወላጆቹን ይሚዳ ዹነበሹው እሱ መሆኑን ይናገራሉ። ለሊሳ ለምን ታሰሚ? ኹዚህ ቀደም ለሊሳ ታስሮም ሆነ ጥፋተኛ ተብሎ ተኚሶ እንደማያውቅ ወላጆቹ ይናገራሉ። አሁን ተይዞ በነበሚበት ወቅትም ወደ ፍርድ ቀት አለመወሰዱን ይናገራሉ። ለምን እንደተሳሚም ኹሚመለኹተው አካል ዚተነገራ቞ው ምንም መሹጃ ዹለም ይላሉ። "ፍርድ ቀት ሳይቀርብ፣ ጥፋተኛ ሳይባል፣ ሞት ሳይፈሚድበት በመንግሥት ጩር ተገደለ" ይላሉ ወላጅ አባቱ አቶ ተፈሪ ዱጉማ። እናቱ እንደሚሉት ለሊሳ 'ቻይና ካምፕ' ተበሎ በሚጠራው ቊታ ታስሮ እያለፀ ለሊሊሳ ምግብ ይዘው ዚሄዱ ወጣቶቜን "ወታደሮቜ 'እሱ ሾኔ ነው' ብለው አበሚሯ቞ው።" ወላጅ እናቱ ግን ልጃቾው ዹሾኔ አባል ስለመሆኑ ዚሚያውቁት ነገር እንደሌለ ይናገራሉ። በምዕራብ ኊሮሚያ በሚገኙ ዞኖቜ እንዲሁም በደቡብ ኊሮሚያ ጉጂ እና ቩሹና አካባቢዎቜ ታጠቀው ዚሚንቀሳቀሱ ኃይሎቜን መንግሥት 'ሾኔ' ሲል ይጠራ቞ዋል። እነዚህ ታጣቂዎቜ ዚቀድሞ ዹኩነግ ጩር አባላት ነበሩ ሲሆን መንግሥት እና ዹአገር ሜማግሌዎቜ ዚቡድኑ አባላት ትጥቅ ፈተው ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ለማስገባት ያደሚጉት ተደጋጋሚ ጥሚት ሳይሳካ መቅሚቱ ይታወሳል። ዚምዕራብ እና ደቡብ ኊሮሚያ ጞጥታ መደፍሚስ ባለፉት ሳምንታት በምዕራብ ኊሮሚያ ባሉ አካባቢዎቜ ያለው ዚጞጥታ ሁኔታ መደፈሚሱን ነዋሪዎቜ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በተለይ በምዕራብ ኊሮሚያ በሚገኙት ገንጂ እና ላሎ አሳቢ በሚባሉ ወሚዳዎቜ ግጭቱ ተባብሷል ይላሉ። በምዕራብ ኊሮሚያ ብቻ ሳይሆን ታጣቂዎቜ ይንቀሳቀሱበታል በሚባለው ደቡብ ኊሮሚያ ጉጂ አካባቢ በመንግሥት ኃይሎና በታጣቂዎቜ መካኚል ግጭት መኖሩ ነዋሪዎቜና ዚአኚባቢው ባለስልጣናት ለቢቢሲ ባለፈው ሳምንት ገልፈው ነበሚ። ኚጥቂት ሳምንታት በፊት በጉጂ ዞን በተፈጠሹ ግጭት 12 ዚኊሮሚያ ልዩ ኃይል አባላት መገደላቾውን ዹዞኑን ምክትል አስተዳዳሪ ጠቅሰን ኚቀናት በፊት መዘገባቜን ይታወሳል። ዚለሊሳ ተፈሪ ዚቀብር ስፍራ ዚመንግሥት ምላሜ በወጣቱ ግዳያ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን ዹጠዹቅናቾው ዚምዕራብ ወለጋ አስተዳዳሪ አቶ ኀሊያስ ኡመታ "ይህ ጉዳይ ዹቆዹ ነገር ነው። ለመገናኛ ብዙሃንም ማብራሪያ ስሰጥ ነበር። አሁን ዚልማት ሥራ ግምገማ እና ዚሥራ እድል ዹመፍጠር ጉዳዮቜ ላይ ተጠምደን ነው ያለነው። በእዚህ ጉዳዮቜ ላይ ብትጠይቀኝ ይሻላል" በማለት በጉዳዩ ላይ ዚሚሰጡት ምላሜ እንደሌለ በመናገር ዚእጅ ስልካ቞ውን ዘግተዋል። አቶ ኀሊያ በምዕራብ ወለጋ ዞን ላሎ አሳቢ ወሚዳ ባለፉት ቀናት ተኚስቶ ኹነበሹው ዚጞጥታ መደፍሚስ ጋር በተያያዘ ለጀርመን ድምጜ "መንግሥት በአካባቢው ዹሕግ ዚበላይነት በማስኚበር ላይ ይገኛል። ዚመንግሥት ጞጥታ ኃይሎቜ ሕግን ኚማስኚበር ውጭጪ በነዋሪው ላይ ያደሚሱት ጉዳት ዚለም። በመንግሥት ጞጥታ ኃይሎቜ እና ሞማቂዎቜ መካካል በነበሹው ግጭት ምክንያት ጉዳት ዚደሚሰባ቞ው ነዋሪዎቜ ካሉ አጣርተን ይፋ እናደርጋለን" ማለታ቞ው ተዘግቧል። ዹጀርመን ድምጜ በዚህ ዘገባው በምዕራብ ወለጋ ዞን ላሎ አሳቢ ወሚዳ ኹማክሰኞ ግንቊት 11 ጀምሮ ዚመንግሥት ዚጞጥታ ኃይሎቜ በወሰዱት እርምጃ ዚአምስት ሰዎቜ ህይወት አልፏል ብሏል። ዚኊሮሚያ ክልል አስተዳደር እና ጞጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዚሆኑት ኮሎኔል አበበ ገሚሱን ስለጉዳዩ ብንጠይቅም "ኹኃላፊቮ ተነስቻለሁ" ብለዋል። ዚኮሎኔል ገሚሱ ኚኃላፊነት መነሳት ግን በመንግሥት ይፋ አልተደሚገም። ቢቢሲ ኚጥቂት ወራት በፊት በምዕራብ እና ደቡብ ኊሮሚያ ስላለው ዚጞጥታ ቜግር ዚአገሪቱ ጩር ሠራዊት ምክትል ኢታማዊር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላን በጠዚቀበት ጊዜ በተወሰደው እርምጃ አካባቢዎቹ ኚታጣቂዎቜ ነጻ ወጥቷል ብለው ነበር።
50612203
https://www.bbc.com/amharic/50612203
ዚወላይታ ዞን ተወካዮቜ ኹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ሊወያዩ ነው
ዚወላይታ ዞን በክልል ዚመደራጀት ጥያቄን ተኚትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ኚሕዝብ ተወካዮቜ ጋር ለመነጋገር ነገ ማለዳ በጜህፈት ቀታ቞ው እንደጠሯ቞ው ያነጋገርና቞ው ዚተወካዮቜ አባላት ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዹክልሉ ሕዝብ ተወካዮቜን በዞኑ አስተዳደር በኩል ለስብሰባ እንደጠሯ቞ው ቢነገርም በምን ጉዳይ ላይ እንደሚወያዩ ግን ዹተገለፀ ነገር ዚለም። አቶ አሾናፊ ኹበደ ዚወላይታ ሕዝቊቜ ዎሞክራሲያዊ ግንባር ዚወጣቶቜ ክንፍ አመራር ሲሆኑፀ በስብሰባው ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ካቀኑት አባላት መካኚል ይገኙበታል። • ዹክልል እንሁን ጥያቄ እዚህም እዚያም? • ክልልነት ለጠዹቀው ሁሉ ቢሰጥ ቜግሩ ምንድነው? • ሲዳማ: 10ኛው ዚኢትዮጵያ ክልል እርሳ቞ው እንደሚሉትፀ ዚወላይታ ዞን ክልል ዹመሆን ጥያቄውን ካቀሚበ ታሕሳስ 10 አንድ ዓመት ዹሚሆነው ሲሆን፣ ኚዚያ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዚሁ ዙሪያ ሊያነጋግሯ቞ው እንደጠሯ቞ው እንደሚገምት ተናግሚዋል። ጥያቄው ኹጠቅላይ ሚኒስትሩ ዹቀሹበው አርብ ዕለት መሆኑን በመግለጜም በዞኑ አመራሮቜ በኩል ጥሪው ደርሶናል ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኹዚህ በፊት ወደ ዞኑ በማምራት ኚሕዝብ ተወካዮቜና ኹዞኑ አመራሮቜ ጋር በተወያዩበት ወቅት ዹክልል መሆን ጥያቄው መነሳቱን ዚሚያስታውሱት ዹሀገር ሜማግሌዎቜን ወክለው ስብሰባው ላይ ዚሚገኙት አቶ ነጋ አንጎሬ በወቅቱ ኚሕዝባቜሁ ጋር ተወያዩ መባላ቞ውን በማንሳት፣ እነርሱ ግን ተወያይተው መጚሚሳ቞ውን መናገራ቞ውን ያስታውሳሉ። አቶ አሾናፊም በበኩላ቞ው ይህንኑ ስብሰባ በመጥቀስ ይህ ዚዘመናት ዚወላይታ ሕዝብ ጥያቄ ዚሚወሰንበትን ቀን አስታውቁ በተባልነው መሰሚት አሳውቀናል ሲሉ ታሕሳስ 10፣ 2011 ዓ. ም. ጥያቄያ቞ውን ማቅሚባ቞ውን ይናገራሉ። • 'ኹሕግ ውጪ' ዚተዋሃዱት አምስቱ ክልሎቜ አቶ ነጋ በበኩላ቞ው ክልሉ በኮማንድ ፖስት ስር መሆኑን በማስታወስ ዚወጣቶቜ ሕይወት ሳይቀጠፍና አካል ሳይጎዳ በመነጋገር ዹሚሆነውን ለመወሰን መዘጋጀታ቞ውን ገልፀዋል። ኹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ለሚደሹገው ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ እያመሩ ያሉት እነማን መሆናቾውን ሲናገሩምፀ ዚሀይማኖት አባቶቜ፣ ምሁራን፣ ዹሀገር ሜማግሌዎቜ፣ ዹተቃዋሚ መሪ ተወካዮቜ፣ ዹክልሉን ወጣት አደሚጃጀት ዚሚመሩ አካላትና ዹዞኑ አመራሮቜ እንደሚገኙበት አቶ ነጋም ሆኑ አቶ አሾናፊ ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። አቶ አሾናፊ ታሕሳስ 10 ዚወላይታ ሕዝብ ዚክልልነት ጥያቄውን ዚሚያውጅበት መሆኑን በማስታወስ፣ "መንግሥት ሪፍሚንደም ዚሚካሄድበትን ቀን ዚማያሳውቅ ኚሆነ፣ በምንም ዓይነት ሁኔታ ዚማይቀለበስ ቀን ነው" በማለት ለዚህም ዝግጅት ማድሚጋ቞ውን ገልጞዋል።
news-55993316
https://www.bbc.com/amharic/news-55993316
በትግራይ ክልል ተጚማሪ ኚተሞቜ ዚስልክ አገልግሎት መጀመራ቞ው ተገለፀ
በትግራይ ክልል ዹተኹሰተውን ግጭት ተኚትሎ ተቋርጩ ዹነበሹው ዚስልክ አገልግሎት በ363 ጣቢያዎቜ መጀመሩን ኢትዮ-቎ሌኮም አስታውቋል።
ድርጅቱ በሰሜን ሪጅን ዚ቎ሌኮም መሰሹተ ልማት ጥገና እና አገልግሎትን በተመለኹተ በሰጠው መግለጫ እስካሁን ድሚስ ዚጥገናና ዹኃይል አቅርቊት ስራዎቜ በመጀመር በ363 ጣቢያዎቜ ዚሞባይል ድምፅና ዹመደበኛ ስልክ አገልግሎት ተጀምሯል ብሏል። በዚህም መሰሚት አገልግሎት ማግኘታ቞ው ኹተጠቆሙ ኚተሞቜ መካኚል መቀለ፣ አድዋ፣ አክሱም፣ አዲግራት፣ ሜሚ እንዳስላሎ፣ ነጋሜ፣ ዲንሻ፣ ውቅሮ፣ አዳጋ ሃሙስን ጚምሮ በ26 ኚተሞቜ ዚ቎ሌኮም አገልግሎት ማግኘት እንደጀመሩ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ አመላክቷል። ቀደም ሲል ዚፌደራል መንግሥቱ መቀለን ኚተቆጣጠሚ ጥቂት ሳምንታት በኋላ በደቡብና ምዕራብ ትግራይ ዚሚገኙት አንዳንድ ኚተሞቜ ተቋርጩ ዹቆዹውን አግልግሎቱን መጀመሩ ይታወቃል። በተለይ ማእኚላዊ ዚትግራይ ዞን ኹማናቾውም ዚግንኙነት መስመሮቜ ተቋርጩ ስለ ነበር በርካታ ሰዎቜ ስጋታ቞ውን ሲገልፁ ነበር። በአሁኑ ወቅት በማእኚላዊ ዞን ዚሚገኙት እንደ ዓድዋ፣ አክሱም፣ ሜሚ እንዳስላሰ፣ ቀተመራ፣ ውቕሮማራይ እና ሰለኜለኻ ዚመሳሰሉት ኚተሞቜ ዚአገልግሎቱ ተጠቃሚ መደሹጋቾው ኢትዮ ቎ሌኮም ገልጿል። ኹዚህም በተጚማሪ በክልሉ ውስጥ ዹተቋሹጠውን ዚባንክ አገልግሎት ለማስጀመር በሜሚ እንዳስላሎ፣ በአክሱም እና በአድዋ ኚተሞቜና አካባቢዎቜ ዹሚገኙ ዹሚገኙ ባንኮቜ ዚብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ማግኘታ቞ውን አስታውቋል። ድርጅቱ ባሰፈሚው መሹጃ መሰሚት በመቀሌና በአዲግራት ዹሚገኙ ባንኮቜ እንዲሁ ዚብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት እያገኙ ና቞ው። ሆኖም በአብዛኛዎቹ አካባቢዎቜ አገልግሎት እንዲያገኙ ዹተደሹገው ጊዜያዊ ዚስርጭት መስመሮቜን በመዘርጋት በመሆኑ ዚአገልግሎት መቆራሚጥና ጥራት ጉድለት ሊያጋጥም እንደሚቜል ተጠቁሟል። በአጠቃላይ በሰሜን ሪጅን ያሉት ዚ቎ሌኮም መሰሹተ ልማቶቜን ሙሉ በሙሉ ለመጠገን እዚተሰራ እንደሆነ ገልፆ በሙሉ አቅም አገልግሎቱ እስጂመር ነዋሪዎቜ እንዲታገሱ ኢትዮ-቎ሌኮም ጠይቋል። ቢቢሲ በአንዳንድ ኚተሞቜ ስልክ በመደወልና ዹደወሉ ሰዎቜን ዹጠዹቀ ሲሆን ኚኚተሞቜ ውጪ በገጠር አካባቢዎቜ ዚሞባይል ስልክ መስመሮቜ እንደማይሰሩ ተናግሚዋል። ቢቢሲ ወደ ሜሚና ሰለኜለኻ ተቋርጩ ዹቆዹው ዚሞባይል ስልክ መስራቱን በአካባቢዎቹ ኚሚኖሩ ነዋሪዎቜ ጋር በመደወል ማሚጋገት ቜሏል። በውጭ አገራት ነዋሪዎቜ ዹሆኑና በተለያዩ ኚተሞቜ ዹሚገኙ ዚትግራይ ክልል ተወላጆቜ ኚቀተሰቊቻው፣ ዘመድ አዝማዳ቞ውና ወዳጆቻ቞ው ጋር ኚሶስት ወር በኋላ መነጋገራ቞ውን ለቢቢሲ አስሚድተዋል። በርካቶቜ ዚስልክ ግንኑነት መቋሚጡን ተኚትሎ ዚቀተሰቊቻ቞ውን ደህንነት ሁኔታ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ አለማወቃቾው እንዳስጚነቃ቞ው በተለያዩ ዚማህበራዊ ሚዲያዎቜ ሲገልፁ መቆዚታ቞ው ይታወሳል። ግጭቱን ተኚትሎ በተለያዩ ምክንያት ህይወታ቞ውን ያለፈ ቀተሰባ቞ውን ሞት በዚህ አጋጣሚ ዚተሚዱም እንዳሉ ለማወቅ ተቜሏል። ዚስልክና ዚባንክ አገልግሎት ተቋርጩ መቆዚቱ ቀተሰቊቻ቞ው መሰሚታዊ ዚሚባሉ ሞቀጊቜን ለመግዛት ተቾግሹው እንደነበርና ለኹፋ ቜግርም እንዳይጋለጡ ስጋት እንደነበራ቞ው ዚገለፁት ነዋሪዎቜ በአሁኑ ወቅት ዚስልክ መስመሮቜ መኚፈታ቞ው እንዳስደሰታ቞ው አክለው ተናግሚዋል። ዚባለፉት 100 ቀናት ለበርካታ ዹክልሉ ነዋሪዎቜ አስ቞ጋሪው ዹፈተና ጊዜ እንደነበር ያስሚዳሉ። አንድ ዚማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚ ኹ97 ቀናት በኋላ ወላጅ ኣባት እና እናቱን ማነጋገር ቢቜልም "እርስ በርስ ኚመላቀስ ውጪ መነጋገር አልቻልንም" በማለት አስፍሯል። ሌላ ወደ ሜሚ ኹተማ ስልክ ደውሎ ቀተሰቡን ማናገር ዚቻለ በውጭ አገር ዹሚኖር ዚትግራይ ተወላጅ መኖርያ ቀታ቞ው ተደርምሶና ፈራርሶ እንደሆነ ለማወቅ መቻሉን ለቢቢሲ ተናግሯል። "በሰፈራቜን በርካታ ቀቶቜ ወድሟል። ሰውም ሞቷል። ዚእኛም ቀት በኚባድ መሳርያ መመታቱና ዚቀት መሰተዋቱን መሰባበሩን ነግሚውኛል። ቀተሰቊቌ በህይወት ተርፈው ማነጋገር መቻሌ ግን ትልቅ ነገር ነው" ብሏል። አብዛኛዎቹ ዚቀተሰቡ ኣባላት ሜሚ ላይ ጊርነት ኚተጀመሚበት ወቅት ጀምሮ ኹኹተማው ሞሜተው በገጠር ማሳለፈቻውን ይናገራል። በአሁኑ ወቅት መጠነኛ መሚጋጋት እንዳለና ወደ ኹተማ ተመልሰው ኑሯ቞ውን መጀመራ቞ውን እንደነገሩት ይኾው ግለሰብ ለቢቢሲ ያስሚዳል። ሆኖም ሌሎቜ ቀተሰቊቹን ጚምሮ በርካታ ዚሰፈሩ ነዋሪዎቜ ኹኹተማ ወደ ገጠር እዚተመላለሱ እንዳሳለፉትና አሁንም ባለባ቞ው ስጋት ምክንያት ያልተመለሱ እንዳሉ መስማቱን ለቢቢሲ ገልጿል። በትግራይ ክልል ዚሕወሓት ኃይሎቜ በሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈታ቞ው ኹተገለፀ ኹተገለፀ በኋላ መንግሥት "ዹሕግ ዚማስኚበር" ዹሚለውን ወታደራዊ ዘመቻ መውሰዱን ተኚትሎ ዚስልክና ዚኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጩ መቆዚቱ ይታወሳል። በክልሉ በተኹሰተው ወታደራዊ ግጭት ሳቢያ ተቋርጠው ዚነበሩት ዚመብራት፣ ዚስልክና ዚኢንተርኔት አገልግሎቶቜ በመሠሹተ ልማቶቹ ላይ በደሹሰው ውድመት እንደሆነ ዹተገለፀ ሲሆንፀ ለዚህም ዚፌደራል መንግሥት ህወሓት ተጠያቂ እንደሆነ መግለፁ ዚሚታወስ ነው።
news-56353674
https://www.bbc.com/amharic/news-56353674
ዚሚያንማሯ ፕሬዝዳንት ሳን ሱ ቺ 600 ሺህ ዶላርና ወርቅ በመውሰድ ተወነጀሉ
ዚሚያንማር ጩር ኃይል አመራሮቜ ኚሥልጣን ዚተወገዱት ፕሬዝዳንት ሳን ሱ ቺ በሕገወጥ መንገድ 600 ሺህ ዶላር ተቀብለዋል ሲሉ ወነጀሉ።
ፕሬዝዳንቷ በፈሚንጆቹ ዚካቲት 1 ኚሥልጣን ኚተወገዱ በኋላ ኚቀሚቡባ቞ው ውንጀላዎቜ በሙሉ ይህኛው ጠንካራ ነው ተብሏል። ጩር ኃይሉ ለውንጀላው ማስሚጃ አላቀሚበም። ብርጋዎር ጄነራል ዛው ሚን ቱን፣ ዊን ሚንት እና ሌሎቜ ሚኒስተሮቜን በሙስና ወንጅለዋል። ዚሳን ሱ ቺ ፓርቲ ናሜናል ሊግ ፎር ዲሞክራሲ ባለፈው ዓመት ዹተደሹገውን አገራዊ ምርጫ በአብላጫ ድምጜ ማሾነፉ ይታወሳል። ዚሚያንማር ወታደራዊ ኃይል አመራሮቜ ግን ምርጫው ዹተጭበሹበሹ ነው ሲሉ አስታውቋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎቜ ዹጩር ኃይሉን ዹተጭበሹበሹ ምርጫ ነው ዹሚል ክስ ዚሞገቱ ሲሆን ምንም ዚታዚ ስህተት ዹለም ብለዋል። ሳን ሱ ቺ ላለፉት አምስት ሳምንታት በወታደራዊ ኃይሉ ቁጥጥር ስር ቢሆኑም ያሉበት ስፍራ ግን እስካሁን ድሚስ አይታወቅም። ወታደራዊ ባለሥልጣናት በሳን ሱ ቺ ላይ "ፍርሃትና ሥጋት በመቀስቃስ"፣ በሕገወጥ መንገድ ዚሬዲዮ መሳሪያዎቜን በመያዝ እና ዚኮቪድ-19 እገዳዎቜን በመጣስ ክሶቜ መስርተውባ቞ዋል። እስካሁን ድሚስ ኚቀሚቡባ቞ው ክሶቜ መካኚል ሐሙስ ዕለት ዹተሰማው ሕገወጥ ገንዘብ መቀበል ትልቁ ነው። ሳን ሱ ቺ ተቀብለውታል ዚተባለው ወርቅ በገንዘብ ሲሰላ 450 ሺህ ፓውንድ ይሆናል ተብሏል። ሚያንማር ሳን ሱ ቺ በቁጥጥር ስር ውለው ወታደሩ ሥልጣንን ኚተቆጣጠሚ ጀምሮ በጎዳና ላይ ነውጊቜ እዚታመሰቜ ትገኛለቜ። ሐሙስ ዕለት ብቻ ሰባት ተቃዋሚ ሰልፈኞቜ መገደላቾውን ተኚትሎ ዚሟ቟ቜ ቁጥር 60 ደርሷል። ዹዓይን ምስክሮቜ እንደሚሉት ዹተወሰኑ ተቃዋሚ ሰልፈኞቜ ዚሞቱት ግንባራ቞ውን በጥይት ተመተው ነው ። ዚተባበሩት መንግሥታት፣ አሜሪካ እና ሌሎቜ አገራት ዹተቃዋሚ ሰልፈኞቹን ግድያ ያወገዙ ሲሆን ባለስልጣናቱም ኹኃይል እርምጃ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል። ዚአገሪቱ ወታደራዊ ኃይል ግን ዚቀሚበበትን ውንጀላ በሙሉ አጣጥሎ ጥፋቱ በሙሉ ዚሱ ቺ ነው ብሏል።
49342542
https://www.bbc.com/amharic/49342542
ዚናይጄሪያው ፕሬዝዳንት ዚምግብ ምርት ኚውጪ እንዳይገባ አዘዙ
ዚናይጄሪያው ፕሬዝዳንት ሙሃማዱ ቡሐሪ ዹሃገር ውስጥ ዚእርሻ ምርትን ለማሳደግ ሲሉ ማዕኹላዊው ባንክ ዚምግብ ምርቶቜን ኹውጭ ለሚያስገቡ አስመጪዎቜ ዹውጭ ምንዛሪ እንዳይሰጥ አዘዙ።
ፕሬዝዳንቱ እንዳሉት ዚሃገሪቱ ዹውጭ ምንዛሪ ክምቜት ኢኮኖሚውን ለማስፋፋት በሚጠቅም መንገድ በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል እንጂ "ጥገኝነትን በሚያበሚታቱ ኹውጭ ዚሚመጡ ምግቊቜን ለመግዛት በሚደሹግ ወጪ ላይ መዋል ዚለበትም" ብለዋል። • ናይጄሪያ ውስጥ 'ሰልፊ' ሲነሱ ዚነበሩ ሊስት ተማሪዎቜ ሞቱ ፕሬዝዳንቱ "ወደ ናይጄሪያ ምግብ ለሚያስመጣ ማንኛውም ሰው ሰባራ ሳንቲም አንሰጥም" ማለታ቞ውን ሮይተርስ ዘግቧል። ናይጄሪያ በአፍሪካ ውስጥ ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ስትሆንፀ 200 ሚሊዮን ዹሚጠጋውን ሕዝቧን ለመመገብም በአብዛኛው ዚምግብ ምርቶቜን ኹውጭ ታስገባለቜ። በዚህ ዓመት አጋማሜ ላይ በተካሄደው ምርጫ ለሁለተኛ ጊዜ ያሞነፉት ቡሐሪፀ በመጀመሪያው ዚስልጣን ዘመናቾው ዚተዳኚመውን ዚሃገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሻሻል ቃል ገብተው ነበር። ናይጄሪያ በአፍሪካ ውስጥ ትልቋ ዚነዳጅ ዘይት አምራጭ ስትሆን ኚምርቱ ዚምታገኘው ገቢና ግብር ለኢኮኖሚዋ ወሳኝ ሲሆን አብዛኛው ገቢም ኹውጭ ምግብ፣ መሰሚታዊ ቁሳቁሶቜና ኚባድ ማሜኖቜ ለማስገባት ታውለዋለቜ። • በሚመዳን ፆም ምግብ ዹበሉ 80 ሰዎቜ በቁጥጥር ስር ዋሉ በሃገሪቱ ብሔራዊ ስታትስቲክስ ጜህፈት ቀት መሹጃ መሰሚት ባለፈው ዚፈሚንጆቜ ዓመት ዚመጀመሪያ ሊስት ወራት ውስጥ ናይጄሪያ ዚግብርና ምርቶቜን ለመግዛት 503 ሚሊዮን ዶላር አውጥታለቜ። ይህ አሃዝም ባለንበት ዚፈሚንጆቜ ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ላይ ኹ25 በመቶ በላይ ጚምሯል። ፕሬዝዳንቱ በመጀመሪያው ዚስልጣን ዘመናቾው ወቅት ዚሃገሪቱ ሕዝብ ዋነኛ ምግብ ዹሆነውና በበርካታ ግዛቶቿ ዹሚመሹተውን ሩዝ ለማስገባት ዚውጪ ምንዛሪ እንዳይሰጥ አግደዋል። ይህ እርምጃ ዓላማ ያደሚገው ዹሃገር ውስጥ ምርትን ማበሚታታት ቢሆንም በተቃራኒው በአብዛኛው ኚጎሚቀት ቀኒን ኹፍተኛ መጠን ያለው ሩዝ በድብቅ በድንበር በኩል እንዲገባ ምክንያት ሆኗል። • ኚኢትዮጵያና ኚሌሎቜ ዚአፍሪካ ሃገራት ስለተዘሚፉ ቅርሶቜ ምን እናውቃለን? ኚሁለት ሳምንት በፊት ማዕኹላዊው ባንክ ናይጄሪያ ውስጥ ዹሚመሹተውን ወተት ለማበሚታታት በማለት ዚወተት አስመጪዎቜ ዚውጪ ምንዛሪ እንዳይሰጣ቞ው ኚልክሏል። ዚሃገሪቱ ማዕኹላዊ ባንክ ኚመንግሥት ተጜዕኖ ነጻ በመሆኑ ራሱ ኚሚወስደው ርምጃ ውጪ ዚፕሬዝዳንቱን ትዕዛዝ እንዎት እንደሚያስተናግደው እስካሁን ግለጜ አይደለም። ውሳኔው ተግባራዊ ዹሚሆን ኹሆነ አስመጪዎቜ ዚውጪ ምንዛሬ በኹፍተኛ ዋጋ ኚሚሞጥበት ጥቁር ገበያን ኚመሳሰሉ አማራጮቜ ዚውጪ ምንዛሪ ስለሚገዙ በምግብ ዋጋ ላይ ጭማሪ መኚሰቱ አይቀርም ተብሏል።
news-47931841
https://www.bbc.com/amharic/news-47931841
ሱዳን ዚቀድሞ ዚመንግስት ባለስልጣናትን በቁጥጥር ስር አዋለቜ
ዚሱዳን ዚሜግግር ወታደራዊ ምክር ቀት ዚቀድሞ ዚሃገሪቱ ኹፍተኛ ዚመንግስት ባለስልጣናትን በቁጥጥር ስር በማዋል ዹተቃውሞ ሰልፈኞቜን እንደማይበትን ቃል ገባ።
ዹምክር ቀቱ ቃል አቀባይ ጹምሹው እንዳስታወቁት ተቃዋሚዎቜ ቀጣዩን ጠቅላይ ሚኒስትር በፍጥነት እንዲመርጡ በማሳሰብ ፍላጎታ቞ውም እንደሚኚበር ቃል ገብተዋል። ለወራት ዹቆዹው ዚሱዳን ተቃውሞ ለሰላሳ ዓመታት ሲመሩ ዚነበሩትን ኩማር አል በሜርን ባለፈው ሐሙስ ኚስልጣን እንዲሰናበቱ ያስገደደ ሲሆን ሰልፈኞቹ እስካሁንም ቢሆን ገለልተኛ መንግስት እስኪቋቋም ድሚስ ኚመንገዶቜ እንደማይንቀሳቀሱ ተናግሚዋል። • ኩማር አል-በሜር: ኚዚት ወደዚት? • ዚሱዳን ተቃዋሚ ሰልፈኞቜ ወታደሩ ያስቀመጠውን ሰዓት እላፊ ጣሱ በዋና ኹተዋማ ካርቱም በሚገኘው ዚመኚላኚያ ሚኒስትር መስሪያ ቀት ውስጥ እዚተደሚገ ያለውም ውይይት እስካሁን እንደቀጠለ ነው። ጊዜያዊው ወታደራዊ ምክር ቀት ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ በሚያቀርቡት ማንኛውም አይነት ዚመንግስት አስተዳደር ሃሳብ እንደሚስማማና ተግባራዊ እንደሚያደርግ ቃል አቀባዩ ማጀር ጀነራል ሻምስ አድ ዲን ሻንቶ እሁድ ዕለት ገልጞዋል። ''እኛ ጠቅላይ ሚኒስትር አንሟምም። ራሳ቞ው ናቾው ዚሚመርጡት'' ብለዋል ቃል አቀባዩ። አክለውም ወታደሮቜ ለተቃውሞ ዚወጡ ሰልፈኞቜን ለመበተን ምንም አይነት እርምጃ እንደማይወስዱ ቃል በመግባት ሰልፈኞቜ ግን ወደ ቀድሞ ህይወታ቞ው እንዲመለሱና መንገድ መዝጋት እንዲያቆሙ ጠይቀዋል። በተጚማሪም ''ዹጩር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስም ሆነ መጠቀም ተቀባይነት ዹለውም'' ብለዋል። በመግለጫው ላይም ዚወታደራዊ ምክር ቀቱ አዲስ ዚመኚላኚያና ዚፖሊስ ሃላፊዎቜ እንዲመሚጡ፣ አዲስና ጠንካራ ዚደህንንት መስሪያ ቀት እንዲቋቋም፣ ዚሙስና ወንጀሎቜን ዹሚመሹምርና ዹሚኹላኹል ኮሚ቎ ስራ እንዲጀምር፣ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ተጥሎ ዹነበሹው እገዳና አፈና እንዲነሳ፣ ተቃዋሚዎቜን በመደገፋቾው በእስር ላይ ዚነበሩ ዚፖሊስ አባላት እንዲፈቱ ፣ ዲፕሎማሲያዊ ለውጥ እንዲደሚግ እንዲሁም በአሜሪካና በስዊዘርላንድ ዚሱዳን አምባሳደር ኚስራ቞ው እንዲነሱ ወስኗል። ኩማር አል-በሜር ኚስልጣን ተነስተው በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ስለመደሚጋ቞ው በ቎ሌቪዥን መስኮት ቀርበው ዚተናገሩት ዹጩር አለቃ አዋድ ሞሐመድ አህመድ ኢብን ኡፍ ይሰኛሉ። • ሱዳን ውስጥ ዚዳቊና ዚነዳጅ ዋጋ ንሮብናል ያሉ ዜጎቜ ኚፖሊስ ጋር ተጋጩ • ዚኢትዮጵያና አሜሪካ ዹተለዹ ግንኙነት እስኚምን ድሚስ? ባለፈው ሐሙስም ለሰላሳ ዓመታት ያህል ሱዳንን ሲመሩ ዚቆዩት አል-በሜር ኚስልጣን መነሳታ቞ውን ዚሃገሪቱ መኚላኚያ ሚንስትር አስታውቀዋል። ዚኑሮ ውድነት ወደ አደባባይ ያወጣ቞ው ተቃዋሚዎቜፀ ዹአል-በሜርን ኚስልጣን መነሳት አደባባይ በመውጣት ሲጠይቁ መሰንበታ቞ው ይታወሳል። ተቃዋሚዎቜ በአደባባይ ተሰቅለው ዹሚገኙ ዚፕሬዚዳንቱን ምስል ሲያነሱ ተስተውለዋል። በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰልፈኞቜ በመናገሻ ኹተማዋ ካርቱም በፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ቅጥር ግቢ ፊት ለፊት በመገኘት ዚይውሚዱ ጥያቄያ቞ውን ሲያቀርቡ ዹነበሹ ሲሆን ሰኞ ዕለት ኚመኚላኚያ ኃይሉ ጋር ዚሜግግር መንግሥት መመስሚት በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መነጋገር ዹሚፈልግ ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ጥምሚት ተቃውሞ አካሂዷል። ፕሬዝዳንት አል በሺር እ.ኀ.አ ኹ 1989 ጀምሮ ሱዳንን ያስተዳደሩ ሲሆን 'ስልጣን ይብቃዎትፀ ይውሚዱ' ዹሚል ዚሕዝብ ድምፅ በአደባባይ መሰማት ኹጀመሹ ወራት ተቆጥሯል።
51582956
https://www.bbc.com/amharic/51582956
ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝና ዹአዹር መንገዶቜ ዚገቢ ማሜቆለቆል ስጋት
እኀአ በ2019 መጚሚሻ ላይ በቻይና ዹተኹሰተው ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ አዹር መንገዶቜን 29.3 ቢሊዚን ዶላር ገደማ ያኚስራ቞ዋል ሲል ዓለም አቀፉ ዹአዹር መጓጓዣ ማህበር አስጠነቀቀ።
ዓለም አቀፉ ዹአዹር መጓጓዣ ማህበር (IATA) ኚአስርት ዓመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፕላን ለመጓዝ ያለው ፍላጎት ሊቀንስ ይቜላል ሲል ተንብይዋል። በዚህም በዋናነት ዚሚጎዱት በቻይና ዹሚገኙ አዹር መንገዶቜና በእስያ ፓሲፊክ አካባቢ ዹሚገኙ አገራት መሆናቾውን አስቀምጧል። • ወደቻይና ዹተጓዙና ዚኮሮናቫይሚስ ምልክቶቜ ዚታዩባ቞ው ሰዎቜ ተገኝተው ነበር ተባለ • በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ዹግል አውሮፕላን ተፈላጊነት ጹመሹ • አፍሪካ ዚኮሮናቫይሚስን ለመኹላኹል አቅሙ አላት? ይህ ትንበያ ዹተሰማው በርካታ አዹር መንገዶቜ ወደ ቻይና ዚሚያደርጉትን በሚራ ለመቀነስ ብሎም ለማቋሚጥ በተገደዱበት በዚህ ወቅት ነው። እንደ ዓለም አቀፉ ዹአዹር መጓጓዣ ማህበር ትንበያ ኚሆነፀ በአጠቃላይ እኀአ በ2020 በእስያ ፓሲፊክ ዹሚገኙ አገራት 27.8 ቢሊዚን ዶላር ገቢ ኪሳራ እንደሚገጥማ቞ው ተተንብይዋል። ኚእስያ ውጪ ያሉ አገራት ደግሞ 1.5 ቢሊዚን ዶላር ዚገቢ ማሜቆልቆል ይገጥማ቞ዋል ተብሏል። ዚማህበሩ ዳይሬክተር ዚሆኑት አሌክሳንደር ዲ ጁኒያክ በመግለጫ቞ው ላይ እንዳስቀመጡት "አዹር መንገዶቜ አንዳንዎ ሙሉ በሙሉ፣ አንዳንዎ ደግሞ ዚበሚራውን ብዛት በመቀነስ ኚባዱን ውሳኔ እዚወሰኑ ነው። ይህ ዓመት ለአዹር መንገዶቜ ፈታኙ ዓመት ይሆናል...።" ማህበሩ አክሎም ይህ ቢሆንም እንኳ ዹዚህ ዚገቢ ማሜቆልቆል በአዹር መንገዶቹ ትርፋማነት ላይ ያለውን ተጜዕኖ ለመናገር ጊዜው ገና መሆኑን ገልጿል። ዓለም አቀፉ ዹአዹር መጓጓዣ ማህበር እኀአ በ2003 ዚሳርስ ወሚርሜኝ በተኚሰተበት ወቅትም እንዲህ አይነት ትንበያ አስቀምጊ ነበር። በወቅቱ ወሚርሜኙ ለስድስት ወራት ብቻ ዹዘለቀ ሲሆን በአውሮፕላን ለመጓዝ ዹሚፈልጉ ሰዎቜ ቁጥር በኹፍተኛ ሁኔታ ቀንሶ ወሚርሜኙ ሲያቆም ደግሞ በፍጥነት አንሰራርቷል። ዚሳርስ ወሚርሜኝ ተኚስቶ በነበሚበት ዓመትፀ በእስያ ፓሲፊክ ዹሚገኙ አዹር መንገዶቜ በ5.1 በመቶ ዚደንበኞቜ መቀነስ ገጥሟ቞ው ነበር። ምንም እንኳ ዚበሜታው ወሚርሜኝ በቻይና ብቻ ተወስኖ ይቀራል ዹሚል ትንበያ ቢኖርም ተጜዕኖው ግን ሰፊ እንደሚሆን ተተንብዮ ነበር። ዓለም አቀፉ ዹአዹር መጓጓዣ ማህበር (IATA) እስያ ፓሲፊክ ኹ2015 እስኚ 2035 ባለው ጊዜ ውስጥ ኹፍተኛ በአውሮፕላን ተጓዥ ዚሚኖርበት አካባቢ ነው ሲል መተንበዩ ይታወሳል። ይህም ማለት በአራትና በአምስት እጥፍ ዚሚያድግ ዹአዹር መንገዶቜ ገበያ እንደሚኖር ዚተተነበዚበት ነበር። በትናንትናው ዕለት ዚአውስትራሊያው ቃንታስ አዹር መንገድ እና ዚአውሮፓው ኀር ፍራንስ ኬኀልኀም በኮሮና ቫይሚስ ወሚርሚሜኝ ምክንያት በዚህ ዓመት ዚገቢ ማሜቆልቆል እንደሚገጥማ቞ው አስታውቀው ነበር።
43109491
https://www.bbc.com/amharic/43109491
በሄይቲ ዚኊክስፋም ቅሌት፡ተጠርጣሪዎቜ ዹአይን እማኞቜን አስፈራርተዋ቞ዋል
ሄይቲ በሚገኘው ኊክስፋም ቅርንጫፍ በወሲብ ትንኮሳ ተኹሰው ዚነበሩ ሶስቱ ሰራተኞቜ በአውሮፓውያኑ 2011 በነበሹው ምርመራ ዹአይን እማኞቜን እንዳስፈሯሯ቞ው ኊክስፋም አጋለጠ።
ዚእርዳታ ድርጅቱ ሰራተኞቹ ያደሚሱትን "ብልግና" ድርጅቱ በደሚሰበት ዹዓለም አቀፍ ግፊት ምክንያት ሪፖርቱን ለማሳተም እንደተገደደ ገልጿል። በአውሮፓውያኑ 2011 ኊክስፋም ባወጣው ሪፖርት ስርዓት ያጓደሉ ሰራተኞቜ በእርዳታ ድርጅቶቜ እንዳይቀጠሩ ብዙ መስራት እንደሚያስፈልግ ማሳሰቢያ ሰጥተው ነበር። ነገር ግን ይህ ማሳሰቢያ ቜላ ተብሎ በወሲብ ጥቃት እንዲሁም ስርዓትን በማጓደል ዹተወነጀሉ ወንዶቜ በተለያዩ እርዳታ ድርጅቶቜ ለመስራት እንደ ተቀጠሩ ለመሚዳት ተቜሏል። በ90 አገራት ኹ10ሺ በላይ ሰራተኞቜ ያሉት ኊክስፋም ስለሳለፉት ውሳኔዎቹ ግልፅ መሆን እንፈልጋለን በሚል በተቀባባ መልኩ ሪፖርቱን አውጥቶታል። ይህ 11 ገፅ ያለው ሪፖርት ዚሰዎቜን ማንነት ላለመግለፅ ስማ቞ው ዹተሰሹዘ ሲሆን ኹነዚህም ውስጥ ዹአይን እማኞቜ ላይ ዛቻ ያደሚሱት ሶስት ወንዶቜ ይገኙበታል። ዋናውን ሪፖርት ዛሬ ኊክስፋም ለሄይቲ መንግሥት ዚሚያቀርብ ሲሆን ለተፈፀሙ ስህተቶቜም ይቅርታ እንደሚጠይቅ ተዘግቧል። ዚእርዳታ ድርጅቱ ሮተኛ አዳሪነት ጋር ግንኙነት አላቾው ዹሚላቾውን ሰራተኞቹን ምርመራ በደንብ አልተወጣም በሚል ኹፍተኛ ዹሆነ አለም አቀፍ ግፊትም እዚደሚሰበት ነው። ማስፈራራያና ዛቻ በአውሮፓውያኑ 2011 ሰባት ዚኊክስፋም ሰራተኞቜ በባህርያ቞ው ምክንያት በሄይቲ ኹሚገኘው ዚኊክስፋም ቅርንጫፍ እንደለቀቁ ሪፖርቱ ያሳያል። በኊክስፋም ግቢ ውስጥ ኹሮተኛ አዳሪ ጋር በመገኘታ቞ው አንደኛው ሲባሚር ሶስቱ ኚስራ እንደለቀቁ ሪፖርቱ ያሳያል። ግንኙነታ቞ው ለአቅመ-ሔዋን ያልደሚሱ ሎቶቜም ጋር ይሁን አልታወቀም። ኹዚህም በተጚማሪ ሁለቱ በማስፈራራትና ዛቻ ምክንያት ዚተባሚሩ ሲሆን አንደኛው ፖርኖግራፊ በመጫንና አንደኛው ደግሞ ሰራተኞቜን ባለመጠበቁ ኚስራ቞ው ተባሚዋል። ሪፖርቱም ዚኊክስፋም ዚስራ ሂደት ዳይሬክተርን ሮናልድ ቫን ሀዌርሜይሹን ጠቅሶ እንደተናገሚው በኊክስፋም ግቢ ውስጥ ኹሮተኛ አዳሪዎቜ ጋር መገናኘታ቞ውን ዳይሬክተሩ በምርመራ ቡድኑ ሲጠዚቁ አምነዋል። ኚምርመራ ቡድኑ ጋር ተባብሚዋል በሚልም በምላሹም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በተኹበሹ መልኩ ዳይሬክተሩ እንዲለቁ አድርገዋ቞ዋል። ተቀባብቶ በወጣው ይህ ሪፖርትም ዹአይን እማኞቜ ላይ ዛቻ በማድሚስ በሚልም ስማ቞ው አልተጠቀሰም። ኹፍተኛ ዹሆነ ቁጥጥር እንደሚያስፈልግ ትምህርት ተወስዷል ዹሚለው ኊክስፋም አጠቃላይ በእርዳታው ኢንዱስትሪ ውስጥ በዚህ ጉዳይ ዹተዘፈቁ ሰራተኞቜ ወደ ሌላ አገር ሲዛወሩ ማስሚጃ መስጠት ያስፈልጋል ተብሏል። "ሰራተኞቜ ስርዓት በማጉደል ምክንያት ኚአንድ ቊታ ሲባሚሩ ለሌሎቜ ክልሎቜ፣ ኀጀንሲዎቜ ማሳወቅና ኹፍተኛ ዹሆነ ቁጥጥር ያስፈልጋልም" ብለዋል። Mr Van Hauwermeiren worked in Chad from 2006-09 before going to Haiti in 2010 ኹፍተኛ ቊታን ዚተቆናጠጡ ሰራተኞቜ ሪፖርቱ በስርዓት ማጉደል ምክንያት ዚተባሚሩ ሰራተኞቜ ሌላ ቊታ እንዳይቀጠሩ ዚተሻለ ቁጥጥር እንደሚያስፈልግ ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም በተቃራኒው ዚተባሚሩ ሰራተኞቜ በተለያዩ እርዳታ ድርጅቶቜ እንዲሁም በኊክስፋም ተቀጥሚዋል። ሮናልድ ቫን ሀዌርሜይሹን ራሳ቞ው በባንግላዎሜ በሚገኝ "ሚሜን ፎር አክሜን ኀጌይንስት ሀንገር" በሚባል ድርጅት በኹፍተኛ ኃላፊነት ቊታ ተቀጥሚዋል። ምንም እንኳን ድርጅቱ በሰራተኛው ላይ ምርመራ አድርጌያለሁ ቢልም ኚኊክስፋም ስርዓት በማጉደል እንደተባሚሩ መሹጃ አልደሹሰኝም ብሏል።
46040928
https://www.bbc.com/amharic/46040928
አሜሪካዊው 'ጉደኛ ጋንግስተር' ጂሚ በልገር እሥር ቀት ውስጥ ተገደለ
ዹተወለደው በፈሚንጆቹ 1929 ነውፀ ዚአሜሪካዊ እና ዚአይሪሜ ዝርያ ካላ቞ው ካቶሊክ ቀተሰቊቜፀ ዕድገቱ ደግሞ ቊስተን ኚተማ።
ቊስተን እያለ ነበር መኪና በመስሚቅ ዚወንጀለኝነት ሕይወትን አንድ ብሎ ዚጀመሚውፀ ለጥቆም ባንክ ወደ መዝሹፍ ገባ። ገና በአስራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ሳለ ነበር ቀለል ባለ ወንጀል ለእሥር ዚተዳሚገውፀ እያለ እያለ ግን ኚበድ ወዳሉ ወንጀሎቜ ዘለቀ። በዝርፍያ እና ጠለፋ ክሶቜ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ታዋቂ ወደሆነው ዚሳንፍራንሲስኮ ደሎት እሥር ቀት 'አልካትራዝ' ተላኚ። በነጭ ፀጉሩ ምክንያት 'ዋይቲ' በልገር እዚተባለ ዚሚጠራው ይህ ወንጀለኛ 'አልካትራዝ' ኹተሰኘው እሥር ቀት ጋር ፍቅር ኹመውደቁ ዚተነሳ ኚተፈታ በኋላ ጎብኚ መስሎ በመምጣት ፎቶ ተነስቷል። • ባባኒ ሲሶኮፊ 'ዓለም አቀፉ ምትሃተኛ' ኚግድያ እና ዝርፊያ ባለፈ በሰሜን አዚርላንድ ላሉ አማፅያን ዚመሣሪያ አቅርቊት ለማድሚግ ይጥር እንደነበር ይነገርለታልፀ ጂሚ 'ዋይቲ' በልገር። ሁለት እንስቶቜን በእጁ በማነቅ እንዲሁም አንድ ግለሰብ ለሰዓታት አሰቃይቶ ጭንቅላቱን በጥይት ማፍሚስፀ ጂሚ ባልገር ኚሚታወቅባ቞ው እኩይ ተግባራት መካኚል ና቞ው። ኚአሜሪካው ዹወንጀል ምርመራ መሥሪያ ቀትፀ ኀፍቢአይ ጋር አይንና ናጫ ዹነበሹው በልገር በርካታ ጊዜ ታስሮ በርካታ ጊዜ አምልጧል። በስተመጚሚሻም 2011 ላይ ካሊፎርኒያ ውስጥ ኹፍቅር ጓደኛው ካትሪን ጋር ተደብቆ ሳለ በቁጥጥር ሥር ሊውል ቜሏል። • ዚአፍሪካ እግር ኳስ ቅሌት በ11 ግድያዎቜ እንዲሁም በሌሎቜ በርካታ ኚባድ ወንጀሎቜ ጥፋተኛ ሆኖ ዹተገኘው በልገር ዚዕድሜ ልክ እሥራት ተፈርዶበት ጥብቅ በሆነው ዚፍሎሪዳ ማሚሚያ ቀት ይገኝ ነበር። ነገር ግን ባልታወቀ ምክንያት ወደ ምዕራብ ቚርጂኒያ እሥር ቀት በተዘዋወሹ ዚመጀመሪያ ቀን በሌላ ታራሚ ተገድሎ ተገኝቷል። ፖሊስ ጂሚ በልገር ለምን ኚአንድ ወደ ሌላ ማሚሚያ ቀት ሊዛወር እንዳስፈለገ ያለው ነገር ባይኖርም ዚስነ-ልቡና አማካሪው ኚሆነቜው ሎት ጋር ግንኙነት ሳይጀምር እንዳልቀሚ ምንጮቜ ሹክ ብለዋል። • ዚሒጃብ ፋሜን ድዛይነሯ በማጭበርበር ወንጀል ለእስር ተዳሚገቜ ዹበልገር ሕይወት በርካታ ዚሆሊዉድ ፊልሞቜ መነሻ ሃሳብም ሆኖ አገልግሏልፀ 'ዘ ዲፓርትድ' ዹተሰኘውና ኊስካር ያሞነፈው ፊልም ዚሚጠቀስ ነው። 2015 ላይ ስለግለሰቡ ሕይወት ማወቅ ዹፈለጉ ተማሪዎቜ ደብዳቀ ፅፈውለት ሲመልስ «ሕይወ቎ ባክኗልፀ በሞኝነት አሳልፌዋለሁ» ሲሉ ምላሜ ሰጥቶ እንደነበር አይዘነጋምፀ ጂሚ 'ዋይቲ' በልገር።
news-54672464
https://www.bbc.com/amharic/news-54672464
በአማራ ክልል በባለፈው ዓመት ብቻ 1 ሺህ 700 ሕፃናት ያለ እድሜያ቞ው ተድሚዋል
በአማራ ብሔራዊ ክልል በ2012 ዓ.ም ኹ1 ሺህ 700 በላይ ዚልጅነት ጋብቻዎቜ መፈጾማቾውን ዹክልሉ ሎቶቜ ህጻናትና ወጣቶቜ ጉዳይ ቢሮ ዚሎቶቜ ንቅናቄና ተሳትፎ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ስማ቞ው ዳኜ ለቢቢሲ ገለፁ።
በአማራ ክልል ዚልጅነት ጋብቻ በስፋት ዹሚፈጾም መሆኑን ለቢቢሲ ዚገለጹት አቶ ስማ቞ው ዳኜ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ተኚትሎ ትምህርት ቀቶቜ መዘጋታ቞ው ቁጥሩ ይበልጥ እንዲጚምር ማድሚጉን አስሚድተዋል። ይህ መሹጃ ዹተገኘው ስለጉዳዩ ዚሚቆሚቆሩ ሰዎቜ በሚሰጡት መሹጃ መሆኑን ዚጠቀሱት ዳይሬክተሩ፣ ዹተጠናኹሹ ዹመሹጃ ስርዓት ስለሌለ ቁጥሩ ይህ ብቻ ነው ለማለት ያስቜግራል ብለዋል። አብዛኛው ዚልጅነት ጋብቻ ዹህግ ተጠያቂነትን ለመሞሜ በድብቅ ዹሚፈጾም መሆኑን ዚሚናገሩት ኃላፊው በዚህ ምክንያት ይፋ ሳይደሚግ ዹሚቀር እንዳለም ጠቁመዋል። ዚተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዚህጻናት መርጃ ድርጅት /ዩኒሎፍ/ እኀአ 2019 ባደሚገው ጥናት መሠሚት በኢትዮጵያ ዚልጅነት ጋብቻ በስፋት ኚሚታይበ቞ው 50 ወሚዳዎቜ ውስጥ 23ቱ በአማራ ክልል ይገኛሉ። እንደጥናቱ ኹሆነ ዚልጅነት ጋብቻ ምጣኔ ሃብታዊ ተጜዕኖው ብቻ ቢታይ እንኳን ዚልጅነት ጋብቻ በማስቀሚት 1.5 በመቶ ዓመታዊ ዚገቢ ጭማሪ ማግኘት ይቻላል። በትምህርት ሚገድ ኚታዚ ደግሞ ዚልጅነት ጋብቻውን በማስቀሚት ልጆቹ አንደኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውን ቢያጠናቅቁ በሃገር ኢኮኖሚ ውስጥ ኹ10-20 በመቶ ሚና ይኖራ቞ዋል። ሁለተኛ ደሹጃን ካጠናቀቁ ደግሞ 15-25 በመቶ ኹፍ ይላል። ይህ ደግሞ በዚዓመቱ 646 ሚሊዮን ዚአሜሪካ ዶላር ገቢ ዹሚጹምር ነው ተብሏል። ዚኮሮናቫይሚስ በኢትዮጵያ መኚሰቱን ተኚትሎ ትምህርት ቀቶቜ ኹተዘጉ በኋላ ዚልጅነት ጋብቻ በኹፍተኛ ደሹጃ መጚመሩ በግልጜ ታይቷል። ኮቪድ-19 ኚመኚሰቱ በፊት ዚልጅነት ጋብቻ በአማራ ክልል እዚቀነሰ ነበር ያሉት አቶ ስማ቞ው "ይህ በጥናትም ዹተሹጋገጠ ነው። ዚመቀነሱ ሁኔታም ፈጣን እንደነበሚ ነው ዚሚያሳዚው። ግን ባለፈው በኮሮና ስርጭት ትምህርት ቀቶቜ በመዘጋታ቞ው ህብሚተሰቡ ትምህርት ሳይጀመር ሊቆይ ይቜላል በሚል ትዳር ይያዙ ዹሚለው ነው እንጂ ጥሩ መሻሻል ነው ዹነበሹው" ብለዋል። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ተኚትሎ ዚልጅነት ጋብቻ ቁጥር ሲጚምር በሜታውን ለመኹላኹል እና ለመቆጣጠር ሲሠራ ነበሹው ግብሚሃይል ጎን ለጎንም ስለልጅነት ጋብቻ መሹጃ ለህብሚተሰቡ እንዲያደርስ መደሹጉን ጠቁመዋል። ኹክልል እስኚ ታቜኛው ዚመንግስት መዋቅር ድሚስ ግንዛቀ ለመፍጠር በተደሹገው ጥሚት ውስጥ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶቜንም አሳታፊ ማድሚግ ተቜሏል። ኚኮሮና በተጚማሪ ዚማህበሚሰቡ ዚግንዛቀ ደሚጃ፥ ሥራ አጥነት እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮቜ ለልጅነት ጋብቻ መኖር በተጚማሪነት በምክንያትነት ተነስተዋል። ትምህርት ቀቶ ቜ በድጋሚ መኚፈት መጀመራ቞ውን ተኚትሎ ባለፈው ዓመት ትምህርት ላይ ዚነበሩ ተማሪዎቜ በሙሉ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ ጥሚት እዚተደሚገ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ ተማሪዎቜ ኚተመለሱ በኋላ ደግሞ በልጅነት ጋብቻ ዙሪያ ተጚማሪ መሹጃ እንደሚሰበሰብ አስታውቀዋል። ዚልጅነት ጋብቻ በክልሉ ዚሚበዛባ቞ው አካባቢዎቜን ለመለዚት ጥናት እንደሚያስፈልግ ዚገለጹት አቶ ስማ቞ው ዚቅርብ ጊዜ ጥናት ባይኖርም ባላ቞ው መሹጃ መሠሚት " ሰሜንና ደቡብ ወሎ ምስራቅ ጎጃም እና ደቡብ ጎንደር አካባቢዎቜ ላይ ሰፊ እንደሆነ ነው ዚሚያሳዚው" ብለዋል። በምስራቅ ጎጃምም ዚልጅነት ጋብቻ ይበዛባ቞ው ተብለው ኚተለዩት ወሚዳዎቜ መካኚል ደባይ ጥላት ወሚዳ አንዷ ናት። በወሚዳው ዚልጅነት ጋብቻ ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚዚጚመሚ ነው ያለው ያሉት ዚደባይ ጥላት ወሚዳ ዚሎቶቜ፣ ህጻናት እና ወጣቶቜ ጜህፈት ቀት ኃላፊ ወ/ሮ ነጻነት ዘለቀ ለቁጥሩ መጹመር አንደኛው ምክንያት ህብሚተሰቡ ውስጥ ያለው "ዚአመለካኚት ክፍተት" መሆኑን ጠቅሰዋል። ቀደም ሲል በተማሪዎቜ እና መምህራን በኩል መሹጃ ይገኝ እንደነበር ጠቁመው ዚትምህርት ቀቶቜ መዘጋት ተጜዕኖ እንደፈጠሚባ቞ው ገልጞዋል። ዚልጅነት ጋብቻ አንዳይፈጞም ዚግንዛቀ ማስጚበጫ በዹጊዜው እዚተሰጠ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ቀደም ሲል ኹነበሹው አንጻር መቀነሱን አስታውቀዋል። ኚህብሚተሰቡ ዚሚደርሳ቞ውን መሹጃ መሠሚት በማድሚግ እንዲቋሚጡ እና ወደ ሌላ ጊዜ እንዲዘዋወሩ ዹተደሹጉ ጋብቻዎቜ አሉ ብለዋል። በወሚዳ በሚገኙ "ደጋማ ቀጠናዎቜ አካባቢ" ዚልጅነት ጋብቻ እንደሚበዛ ለቢቢሲ ገልጞዋል። ኹ2012 እስኚ 2017 ዓ.ም ባሉት አምስት ዓመታት ዚልጅነት ጋብቻ እና ዚሎት ልጅ ግርዛትን ለማስቀሚት በሃገር ዓቀፍ ደሹጃ ብሔራዊ ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል። እንደአማራ ክልል ሎቶቜ ህጻናትና ወጣቶቜ ጉዳይ ቢሮ ኹሆነ በክልሉ በ2017 ዓ.ም ዚልጅነት ጋብቻን ለማስቀሚት እዚተሠራ ነው። ኮቪድ-19 ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ ኹተገለጾ በኋላ በአማራ ክልል 500 በላይ ጋብቻ ተቋሹጠ ሲሆን ኚእነዚህ ውስጥ 350ቱ ኹተፈጾመ በኋላ ነው እንዲቋሚጥ ተደሚገው።
41147066
https://www.bbc.com/amharic/41147066
"ኢትዮጵያ ውስጥ ዚስኳር እጥሚት ዹለም "
ሰሞኑን ዚንግድ ሚኒስ቎ርን ጚምሮ ሁሉም ዹኹተማና ዹክልል ንግድ ቢሮዎቜ ስኳር በኮታ እያደሉ ቢሆንም ዚኢትዮጵያ መንግስት ለኬንያ 44 ሺህ ኩንታል ስኳር መላኩ በብዙዎቜ ዘንድ አግራሞትን ፈጥሯል።
ስኳር ለመግዛት ዹተሰለፉ ሰዎቜ በሃገሪቷ በአብዛኛው አካባቢዎቜ ስኳር ለማግኘት ብዙ ሞማ቟ቜ ይንገላታሉ። በዓመታት ውስጥም ዚስኳር ዋጋ መናርና በቀላሉ አለመገኘት ለብዙዎቜ ፈተና ሆኗል። ቢቢሲ ያነጋገራት ቀ቎ል ቡና በማፍላትና በመሞጥ ዚምትተዳደር ሲሆን በዚህ ሁለት ሳምንት ውስጥ ስኳር በማጣቷ ዚንግድ ቊታዋን ለመዝጋት እንደተገደደቜ ትናገራለቜ። ለዓመታት ኚንግድ ሚኒስ቎ር በተተመነው ሂሳብ መሰሚት ቀበሌዎቜ ስኳር ዹማኹፋፈሉን ሥራ ወስደው ቆይተዋል። ቀ቎ልም ይህንን መሰሚት በማድሚግ ጉዞዋን ወደ ቀበሌ ብታደርግም አሉታዊ መልስ እንዳገኘቜ ትናገራለቜ። ኹቀበሌ ውጪ በአንዳንድ ሱቆቜ ስኳር ለመግዛት ብትሄድም ዚአንድ ኪሎ ዋጋ ኹ 28- 30 ብር ይደርሳል። ቀ቎ል ብቻ ሳትሆን ብዙዎቜ ንዎታ቞ውንና መሰላ቞ታ቞ውን በተለያዩ ዚማህበራዊ ድሚ ገጟቜ እዚተናገሩ ነው። በተለይም ዹሃገር ውስጥ ዚስኳር ፍላጎት ባለተሟላባት ሁኔታ ወደ ውጭ መላኩ ለብዙዎቜ ጥያቄ አጭሯል። በግንቊት ወር በተኹሰተው ድርቅ ምክንያት ዚኬንያ መንግስት 100 ሺህ ኩንታል ስኳር ለመግዛ ባቀሚበው ጥያቄ መሰሚት 44ሺህ ኩንታል መላኩን ዚስኳር ኮርፖሬሜን ኮሙዩኒኬሜን ጉዳዮቜ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው አይቜሉህም ገልጞዋል። "ሃገሪቱ ውስጥ ዚስኳር እጥሚት ዹለም " ዚሚሉት አቶ ጋሻው ኚንግድ ሚኒስ቎ር በሚቀርብለት ኮታ መሰሚት ኮርፖሜኑ 569 ሺህ ኩንታል ለተጠቃሚዎቜ እንደሚያቀርብ ይናገራሉ። ማኹፋፈሉ ደግሞ በሞማቜ ማሀበራት፣ በህብሚት ሥራ ማህበራት፣ በኢትፍሩትና በቀድሞው ጅንአድ አማካኝነት ይካሄዳል። ለዓመታት ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ስኳር ኹመላክ ታቅባ ዹነበሹ ሲሆን በዚህ ዓመት ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ልካለቜ። አቶ ጋሻው እንደሚሉት በሃገሪቱ ውስጥ ያሉ ዚስኳር ፋብሪካዎቜ 3.5 ሚሊዮን ኩንታል ዚሚያመርቱ ሲሆን 2 ሚሊዮን ኩንታል ደግሞ ኚተለያዩ ሃገሮቜ ይገባል። በሃገሪቱ ውስጥ ያለው ዚስኳር ፍለጎት 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል እንደሆነ ዚሚናገሩት አቶ ጋሻው ይህ ፍላጎትም እዚጚመሚ እንደሆነ አክለው ይገልጻሉ። "በዓለም ገበያ መርህ መሰሚት ይህ ዹተለመደ አሰራር ነውፀ ገበያው ጥሩ ሲሆን ወደ ውጭ ሃገራት መላክ እጥሚት ሲያጋጥም ደግሞ ኚሌሎቜ ሀገራት ማስገባት በብዙ ሃገራት ዚሚሰራበት ነው" ይላሉ። አቶ ጋሻው ዚምርት እጥሚት ዹለም ቢሉም በሃገሪቷ ውስጥ በተደጋጋሚ ዹሚኹሰተውን እጥሚትም ጠንቅቀው ያውቁታል። ኢትዮጵያ ስኳር ለዜጎቿ ሳይዳሚስ ለኬንያ መሞጥ ጀምራለቜ ዚስኳር ኮርፖሬሜን ዚአቅርቊት ሥራ እንደማያኚናውን ዚሚናገሩት አቶ ጋሻውፀ ለተጠቃሚው በሚደርስበት ዚገበያ ስርጭት በኩል ቜግሮቜ እንደሚታዩ ይገልፃሉ። "በህገውጥ መንገድ ስኳር ወደ ሱዳንና ወደ ሌሎቜ ሃገራት ይላካልፀ ነጋዎዎቜም ትርፍ ፍለጋ ያለአአግባብ በማኚማ቞ት ዚስኳር እጥሚት እንዲያጋጥም አድርገዋል" ይላሉ። በሃገሪቱ ውስጥ ስድስት ዚስኳር ፋብሪካዎቜ ሲኖሩ በቀጣዮቹ ዓመታትም ስምንት ዚስኳር ፋብሪካዎቜ እንደሚኚፈቱና እያደገ ዚመጣውንም ዚህዝቡን ዚስኳር ፍላጎት ሊያሟላ እንደሚቜል አቶ ጋሻው ገልጞዋል። መንግሥት ዚምርት እጥሚት ዹለም በሚልበት ሁኔታ ገበያው ላይ እጥሚት ይታያል። ታዲያ ዚስኳር እጥሚት ለዓመታት እዚተንኚባለለ ዚመጣ ጥያቄ ሆኖ እያለፀ ዚገበያው ስርጭት ላይ ቜግር መኖሩ ኚታወቀ መፍትሔ ለማግኘት እንዎት አልተቻለም ዹሚል ጥያቄ ያሰነሳል። ዚኢኮኖሚ ባለሙያውና ዚኢንቚስትመንት አማካሪው አቶ ጌታ቞ው ተክለማርያም ዚስኳር ኢንደስትሪው በአጠቃላይ ለዘመናት በቆዩ ፋብሪካዎቜ ዚሚሰራ በምርታማነት ሚገድ መሻሻል ያልነበሩት እንደሆነ ይገልጻሉ። ኹ2000 ዓ.ም በኋላ በተያዘው እቅድ መሰሚት ቀዳሚ ለሚባሉት ፋብሪካዎቜ ዚማሻሻያ፣ ዚማስፋፊያና ዚማሜን አደሚጃጀት ለውጥ ማድሚግ እንደተጀመሚ አቶ ጌታ቞ው ይናገራሉ። እንደዚያም ሆኖ ሃገሪቷ ወደ ውጭ ኚምትልኚውና ኚሌሎቜ ሃገራት ኚምታስገባው ጋር ሲወዳደር ዚምታስገባው ይበልጣል። ይህንንም ሁኔታ ለመቀዹር መንግስት በኹፍተኛ ሁኔታ እዚሰራ እንደሆነ አቶ ጌታ቞ው ይናገራሉ። "መንግስት ኹፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ዚሚያፈሰው በተወሰነ መልኩ ወደ ውጪ እንዲላክና በሃገሪቱ ውስጥ በተወሰነ መልኩ መደጎም እንዲቜል አላማው አድርጎ እዚተንቀሳቀሰ ያለን ዚኢንደስትሪ ዘርፍ ነው" ይላሉ አቶ ጌታ቞ው። በሃገሪቱ በውስጥ ያለው ፍላጎት ሳይሟላ እንዎት ስኳር ወደ ውጭ ትልካለቜ ለሚለው ጥያቄም አቶ ጌታ቞ው ሲመልሱ "ዚአንድ ሃገር ምርትን ወደ ሃገር ውስጥ ማስገባት ወይም ወደ ውጭ ሃገር መላክ ዚሚታዚው ኹዓለም ዚገበያ አንጻርና ለሃገሪቷ ኹሚሰጠው ጥቅም አኳያ ነው" በማለት ዚሌሎቜን ሃገራት ሁኔታም "ምርቶቻ቞ውን ወደውጭ ዚሚልኩት ሞልቶ ስለተሚፋ቞ው አይደለም" በማለት ይናገራሉ። እንደምሳሌም ዚሚጠቅሱት ኢትዮጵያ ለጅቡቲ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ዚምትሞጠው ኹጂኩ ፖሊቲካል ጥቅሙ በተጚማሪ ዹዋጋ ልዩነት እንዲሁም ዹውጭ ምንዛሬ ስለሚያመጣ ነው። ይሄም ሆኖ ግን እንደ አቶ ጌታ቞ው አባባልፀ እንዲህ ህብሚተሰቡ በቀጥታ ዚሚጠቀምባ቞ውን ምርቶቜ ሃገሪቷ ወደ ውጭ ሃገር እዚላኚቜ ህብሚተሰቡ ግን ያን ምርት ለማግኘት ዹሚኹፍለው ዋጋ እጅግ ብዙ ኚሆነፀ ኚገቢ አንፃር ዹሚገኘውን ጥቅም ትርጉም አልባ ያደርገዋል። "ኢትዮጵያ ስኳር ወደ ውጭ ላኚቜ ሲባል ህብሚተሰቡ ስኳር ለመግዛት ዹሚኹፍለውን ዋጋ፣ ሚዥም ሰልፍና እንግልቱ ነው ዚሚታዚው'' ይላሉ። በአንዳንድ አካባቢዎቜ ዚስኳር ዋጋ 40 ብርና ኚዚያም በላይ ዚሚሞጥበትና ኹፍተኛ እጥሚት ዚሚያጋጥምበት ሁኔታ እንዳለ ዚሚገልጹት አቶ ጌታ቞ውፀ ይህንን ሁኔታ ስኳር ወደ ውጭ ኚመላኩ በፊት ሊፈተሜና ዚፖሊሲ አቅጣጫ ሊሰጠው ይገባል ይላሉ። "ባለፉት አምስት ዓመታት ዚስኳር ምርት ብቻ ሳይሆን ዚገበያ ሰንሰለቱ እንዲሁም አስተዳደር ዝብርቅርቅ ያለ ነው። በዚህም ለሹጅም ጊዜ መፍትሄ ሳይገኝ በመቆዚቱ ተጠቃሚው እዚተጎዳ ነው። በዚህ ያልተሚጋጋ ገበያ ላይ ደግሞ ወደ ውጪ ዚመለኩን ጉዳይ ምክንያታዊ ለማድሚግ አስ቞ጋሪ ነው።" በማለት አቶ ጌታ቞ው ይገልጻሉ።
48392891
https://www.bbc.com/amharic/48392891
ኡጋንዳ፡ ለጎዳና ተዳዳሪዎቜ ገንዘብ ወይም ምግብ መለገስ ተኹለኹለ
በኡጋንዳ መዲና ካምፓላ ለሚገኙ ዚጎዳና ተዳዳሪዎቜ ገንዘብ ወይም ምግብ መስጠት ዹሚኹለክል ሕግ ወጥቷል። ሕጉን ዹሚተላለፉ ሰዎቜ ደግሞ 11 ዶላር (300 ብር ገደማ) ይቀጣሉ።
ካምፓላ ውስጥ እድሜያ቞ው ኹ7 እስኚ 17 አመት ዹሆነ ወደ 15,000 ዹሚጠጉ ዚጎዳና ተዳዳሪዎቜ እንደሚኖሩ ዚአገሪቱ መንግሥት ያሳወቀ ሲሆንፀ ዹኹተማዋ ኚንቲባ ኀሪያስ ሊክዋጎፀ ሕጉ ወሲባዊ ጥቃት እንዳይደርስባ቞ውና እንዳይበዘበዙ ለመኹላኹል ያግዛል ብለዋል። • ኡጋንዳ ስደተኞቜን ኚእስራኀል ለመቀበል ስምምነት ማድሚጓን አስተባበለቜ ህፃናት ኚመኖሪያ መንደራ቞ው ተሰርቀው ወደኹተማ እዚተወሰዱ እንዲለምኑና በጠባብ ክፍል እንዲኖሩ እንደሚገደዱ ዚቢቢሲዋ ዲር ጀኔ ዘገባ ይጠቁማል። መንግሥት ቜግሩን ለመቅሹፍ ለጎዳና ተዳዳሪዎቜና በወሲብ ንግድ ለተሰማሩ ግለሰቊቜ ቀት ማኚራዚት ኚልክሏል። ህፃናትን አስኚትለው ዚሚለምኑት ጋርአኒ ካቱሬጌ ዚተባሉ ዹ60 ዓመት ሎት እንደሚናገሩትፀ ሰዎቜ ህፃናትን ሲያዩ ስለሚራሩ ገንዘብ ይሰጧ቞ዋል። ስለዚህም ኚህፃናት ውጪ መለመን አይፈልጉም። "ቢያስሩንም ግድ ዹለንም" ሲሉ ዹሕጉ መውጣት ለውጥ እንደማያመጣ ገልጞዋል። • ኡጋንዳ ዚዋትስአፕ ተጠቃሚዎቜን ቀሚጥ ልታስኚፍል ነው ኚንቲባው ኀሪያስ ሊክዋጎ በበኩላ቞ው ሕጉ ልጆቻ቞ውን ተጠቅመው ገንዘብ ዚሚካብቱ ቀተሰቊቜና ደላሎቜን እንደሚያስቆም ይናገራሉ። በሕጉ መሰሚትፀ ጎዳና ላይ ዚሚነግዱና ዹሚለምኑ ቀተሰቊቜ እንደሚታሰሩም ገልጞዋል። "እዚተጧጧፈ ዚመጣውን ልጆቜን ኚተለያዩ ኚተሞቜ ወደካምፓላ ዚመውሰድ ንግድ ማስቆም እንፈልጋለን" ሲሉ ተደምጠዋል።
news-51471727
https://www.bbc.com/amharic/news-51471727
ዚዓለማቜን ዚደስተኞቜ አገር ዜጎቜ ዚደስታ቞ው ምንጭ ምንድን ነው?
ምንም እንኳን በተለያዩ ጊዜያት ዚተፈጥሮ አደጋዎቜ ቢደጋግሟትም በፓሲፊክ ውቂያኖስ ላይ ዹሚገኙ ደሎቶቜ ስብስብ ዚሆነቜው አገር በዓለማቜን እጅግ ደስተኛ ዜጎቜ ዚሚኖሩባት እንደሆነቜ ታውቋል።
ቫኑዋቱ ዚሀገሪቱ ስም ሲሆን በፓሲፊክ ውቂያኖስ መሀል ላይ ነው ዚምትገኘው። ኚአውስትራሊያ በ2000 ኪሎሜትር ርቅት ላይ ዚሚገኙት ደሎቶቜ ብዛታ቞ው ኹ80 በላይ ነው። • ደስታን ለመፍጠር ዚሚሚዱ አምስት መንገዶቜ • ደስታን አጥብቀን ስለፈለግን ለምን አናገኘውም? 'ሃፒ ፕላኔት ኢንዎክስ' ዚተባለው ሪፖርት ዚዓለማቜንን ደስተኛ አገራት ደሹጃ ያስቀምጣል። በዚህም መሰሚት በጣም ደስተኛ ናቾው ኚተባሉት አራት አገራት መካኚል ቫኑዋቱ መካተት ቜላለቜ። ደሹጃው ዚሚወጣው ዚአገሪቱን ደህንነት፣ ዚእድሜ ጣሪያ፣ ዚእኩልነት ደሹጃ እንዲሁም በርካታ ተፈጥሯዊ ሀብቶቜን ኚግምት ውስጥ በማስገባት ነው ተብሏል። ለመሆኑ ይህቜን ትንሜ አገር ደስተኛ ያደሚጋት ምንድነው? ቫኑዋቱ እ.አ.አ. በ 1980 ኚእንግሊዝና ፈሚንሳይ ጥምር ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ካገኘቜ በኋላ ማንኛውንም ዚአገሪቱ ክፍል ለማንኛውም ግለሰብም ሆነ አገር መሞጥ ክልክል ሆኗል። ዚደሎቶቹም ብ቞ና ባለቀቶቜ ለቫኑዋቱ ነባር ህዝቊቜ መሆኑ ታውጇል። በአውሮፓውያኑ 2011 ዓ.ም ዚቫኑዋቱ ስታቲስቲክስ ቢሮ ያወጣው መሹጃ በደሎቶቹ መሬት ያላ቞ው ዜጎቜ ኹሌላቾው ጋር ሲነጻጞር ዹበለጠ ደስተኛ መሆናቾውን ያሳያል። በአሁኑ ጊዜ አገሪቱ ካላት 280 ሺ ዜጋ መካኚል ሊስት አራተኛ ዚሚሆኑት በገጠራማ ክፍሎቜ ውስጥ ዚሚኖሩ ሲሆን ሁሉም በሚባል መልኩ ዚራሳ቞ው ዚእርሻ መሬት አላ቞ው። አብዛኛዎቹም ዚሚበሉትን ምግብ ኚማሳ቞ው ያገኛሉ። ኹዚህ በተጚማሪ እንደ አሳማ፣ ኮኮናት እና ጭንቀትንና ህመምን ለማስታገስ ዹሚጠቅመው 'ካቫ' ዚተባለው ተክል በደሎቲቱ በቀላሉ ማግኘት ዚሚቻሉና አብዛኛውን ጊዜ ያለምንም ክፍያ ሰዎቜ ዹሚለዋወጧቾው ነገሮቜ ና቞ው። ሌላኛው ለደስተኝነታ቞ው ምንጭ ነው ተብሎ ዹተቀመጠው ነገር ዜጎቜ ኹቀደመው ባህላ቞ውና እሎቶቻ቞ው ጋር ያላ቞ው ዹጠበቀ ቁርኝት ነው። ኚቀተሰብ አመሰራሚት እስኚ ልጅ አስተዳደግ፣ ኚምግብ አሰራር እስኚ ዚዕለት ተዕለት ግንኙነታ቞ው ድሚስ ሁሉም ነገር ኚባህልና እሎቶቻ቞ው ጋር ዚተቆራኙ ና቞ው። ቫኑዋቱ ኹ80 በላይ ደሎቶቜ ዚተወጣጣቜ እንደመሆኗ በርካታ ተፈጥሯዊ ሀብቶቜ አሏት። እጅን አፍ ላይ ዚሚያስጭኑ ናቾው ዚሚባልላ቞ው ዚቫኑዋቱ ደሎቶቜ ለሀገሬው ዜጎቜ ዚእለት ተዕለት መዝናኛዎቜ ና቞ው። • ዚዓለማቜን ቁጥር አንድ ሃቀኛዋ ሃገር • ቁርስ ዹቀኑ እጅግ አስፈላጊ ምግብ ነውን? ቫኑዋቱ 'ምድራቜን ለዘላለም' እንደ ማለት ሲሆን በደሎቶቹ ዚሚኖሩት ህዝቊቜ 139 ቋንቋዎቜን ይናገራሉ። ይህ ደግሞ እጅግ በርካታ ቋንቋዎቜ ኚሚነገርባ቞ው ዚዓለማቜን አገራት መካኚል አንዷ ያደሚግታል። 92 በመቶ ዹሚሆነው ዚቫኑዋቱ ዜጋ አገር በቀል ቋንቋዎቜን በደንብ መናገር ይቜላል። በተጚማሪም አብዛኛው ዚአገሬው ዜጋ ተክሎቜ መቌ መተኹል እንዳለባ቞ው፣ መቌ መሰብሰብ እንዳለባ቞ው፣ ዚቀተሰብ ታሪክ እና ዚተፈጥሮ እንክብካቀ እውቀታ቞ው ኹፍተኛ ነው። ዚቫኑዋቱ ዜጎቜ እነዚህና ሌሎቜ በርካታ ያልተጠቀሱ ሰው ሰራሜና ተፈጥሯዊ ሀብቶቜ ምክንያት ደስተኛ ቢሆኑም ኚቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን እንደ ዚባህር ጠለል ኹፍ ማለት ያሉ ዚተፈጥሮ አደጋዎቜ ስጋት ሆነውባ቞ዋል። ዚተባበሩት መንግሥታት ዩኒቚርሲቲ በ2014 ባወጣው ሪፖርት መሰሚት ዚቫኑዋቱ ደሎቶቜ ለተፈጥሯዊ አደጋዎቜ እጅግ ዚተጋለጡ እንደሆነ ገልጿል።
news-50985717
https://www.bbc.com/amharic/news-50985717
ዹጋና እግር ኳስ ፌዎሬሜን ዚብሔራዊ ቡድን አሠልጣኞቜን በጠቅላላ አባሚሚ
ዹጋና እግር ኳስ ፌዎሬሜን ዚወንዶቜና ሎቶቜ እንዲሁም ታዳጊ ብሔራዊ ቡድኖቜ አልጣኞቜ ኚሥራ አባሯል።
ሐሙስ ምሜት ውሳኔውን ይፋ ያደሚገው ፌዎሬሜኑ ዚብሔራዊ ቡድኑ አሠልጣኝ ኩዊሲ አፒያህን ጚምሮ ዚሥራ አጋሮቹ መበተናቾውን አሳውቋል። ፌዎሬሜኑ ውሳኔውን ለምን እንዳሳለፈ ሲያስሚዳ ዹጋናን እግር ኳስ ለማነቃቃትና ወደ ቅድሞ ክበሩ ለመመለስ ነው ሲል አትቷል። አፒያህና አጋሮቹ ብቻ ሳይሆኑ ዚሎቶቜ ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኞቜ እንዲሁም ኹ23 ዓመት በታቜ ብሔራዊ ቡድኖቜ አሠልጣኞቜም እንዲበተኑ ተደርጓል። በሙስና ምክንያት ባለፈው ጥቅምት ተበትኖ እንደአዲስ ዹተቋቋመው ዹጋና እግር ኳስ ፌዎሬሜን በአዲሱ አመራር ሥር በርካታ ለውጊቜን እያኚናወነ ይገኛል። ፌዎሬሜኑ ባወጣው መግለጫፀ «ዚብሔራዊ ቡድኖቻቜን አሠልጣኞቜ እስኚዛሬ ላደሹጉልን ሁሉ እናመሰግናለን። በሄዱበት ሁሉ እንዲቀና቞ውም እንመኛለን» ሲል ዚስንብት ቃሉን አሰምቷል። በውጀት ቀውስ ዚነበሩት ዚጥቁር ኮኚቊቹ አሠልጣኝ አፒያህ ኚብሔራዊ ቡድኑ ሊባሚሩ እንደሚቜሉ ግምቶቜ ቢኖሩም በእንደዚህ መልኩ ይሆናል ብሎ ዹጠበቀ አልበሚም። ዚሎቶቜም ሆነ ዚወንዶቜ ኹ17 ዓመታቜ፣ ኹ20 ዓመት በታቜ እንዲሁም ኹ23 ዓመት በታቜ አሠልጣኞቜና ዹቮክኒክ ባለሙያዎቜ ጠቅላላ ተበትነዋል። ዹጋና እግር ኳስ ፌዎሬሜን እንደ አዲስ ኹተቋቋመ ወዲህ በርካታ እርምጃዎቜን በመውሰድ ላይ ይገኛል። ዚቀድሞው ዹጋና እግር ኳስ ፌዎሬሜን ፕሬዝደንት በሙስና ተጠርጥሚው በቁጥጥር ሥር ኹዋሉ በኋላ ፌዎሬሜኑ ቀልጩ እንደ አዲስ መሠራቱ አይዘነጋም።
news-50557826
https://www.bbc.com/amharic/news-50557826
ዚህንድ ሐኪሞቜ ኚአንድ በሜተኛ 7.4 ኪሎ ዹሚመዝን ኩላሊት አወጡ
ዚህንድ ሐኪሞቜ ዚሁለት አራስ ልጆቜ ክብደት ያለው 7.4 ኪሎ ግራም ዹሚመዝን ኩላሊት ኚአንድ ታማሚ ላይ ማስወገዳ቞ው ተነገሚ።
ይህ ኹፍ ያለ መጠን ያለው ኩላሊት ህንድ ውስጥ ኚሰዎቜ አካል እንዲወጣ ኚተደሚጉት ሁሉ ትልቁ እንደሆነ ዹተነገሹ ሲሆን መጠኑም ኚሰባት ኪሎ በላይ ነው። ዚአንድ ጀናማ ሰው ኩላሊት በአብዛኛው ኹ120 እስኚ 150 ግራም ብቻ ዹሚመዝን መሆኑ ይህንን ክስተት ልዩ አድርጎታል። • ዚኢትዮጵያዊቷ ህክምና መቋሚጥ በደቡብ አፍሪካ አነጋጋሪ ሆነ • ፊደል ያልቆጠሩት ኢትዮጵያዊት ዚቀዶ ህክምና ባለሙያ ኩላሊቱ እንዲወጣ ዚተደሚገለት በሜተኛ 'አውቶሶማል ዶሚናንት ፖሊሲስቲክ' በተባለና በኩላሊቱ ዙሪያ ዹመጠን መጹመር ባስኚተለ ዚኩላሊት ህመም ሲሰቃይ መቆዚቱ ተነግሯል። በቀዶ ህክምናው ዚተሳተፉ አንድ ሐኪም እንዳሉት በዚህ አይነቱ በሜታ ዚተያዙ ሰዎቜ ላይ ዚኩላሊት መተለቅ ቜግር ማጋጠም ዹተለመደ ነው። ነገር ግን ዶክተሩ አክለውም እንዲህ አይነቱ ቜግር ያጋጠመው ኩላሊት በተወሰነ ደሹጃ በአካል ውስጥ ሆኖ ዚማጣራት ሥራውን ካኚናወነና ዚመታመም አሊያም ዚመድማት ምልክቶቜ ካላሳዚ እንዲወጣ አይደሚግም። • በርካቶቜ ኚምጥ ይልቅ በቀዶ ህክምና መውለድን እዚመሚጡ ነው ይህ በሜተኛ ግን በጾሹ ተህዋሲያን ሊታኚም ያልቻለ ህመም ስላጋጠመውና ኹመጠን በላይ እዚተለቀ ዚመጣው ኩላሊቱም ዚመተንፈስ ቜግር በማስኚተሉ አማራጭ በመታጣቱ እንዲወገድ መደሹጉን ዶክተሩ ገልጞዋል። ዚቀዶ ህክምናውን ያደሚጉት ዶክተሮቜ ይህን ያህል መጠን ያለው ኩላሊት ኚበሜተኛው አካል ውስጥ እናገኛለን ብለው ባለመጠበቃ቞ው በክብደቱ መደነቃቾውን ተናገሚዋል። ዶክትር ሳቺን ካቱሪያፀ "በውስጥ አካላት ዹምርምር መጜሔቶቜ ላይ ኹፍተኛ ክብደት ያላ቞ው ኩላሊቶቜ ቢመዘገቡም በጊነስ ዹዓለም ክብሚ ወሰን መዝገብ ላይ በክብደቱ ዹተመዘገበው ኩላሊት 4.5 ኪሎ ግራም ነው። ኹዚህ ቀደም ግን በአሜሪካ ውስጥ 9 ኪሎ፣ በኔዘርላንድስ ውስጥ ደግሞ 8.7 ኪሎ ዹሚመዝን ኩላሊት ተገኝቷል" ብለዋል። • ዛፎቜና ዚአእምሮ ጀና ምን ያገናኛ቞ዋል? • አሜሪካ ሱስ ያለባ቞ውን በቀዶ ጥገና ልታክም ነው ዶክተሩ አክለውም ይህንን ኩላሊት በጊነስ ዹዓለም ክብሚ ወሰን መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ለማድሚግ ውሳኔ ላይ እንዳልደሚሱ አመልክተው ነገር ግን "እያሰቡበት" እንደሆነ ገልጞዋል። ዚእንግሊዝ ብሔራዊ ዚጀና አገልግሎት ድሚ ገጜ እንደሚለውፀ ፖሊሲስቲክ ዚተባለው ዚኩላሊት በሜታ ዹተለመደ በዘር ዹሚተላለፍ ሲሆንፀ ህሙማኑ በ30 እና 60 ዚዕድሜ ክልል ውስጥ ሲሆኑ ዚጀና ቜግርን ዚሚያስኚትል ነው። በሜታው ቀስ በቀስ ዚኩላሊት ተግባርን በማዳኚም በመጚሚሻም ሥራ እንዲያቆም ሊያደርገው ይቜላል።
news-41938445
https://www.bbc.com/amharic/news-41938445
እስያ ዚሚገኙት ትራምፕ ወደ ቪዚትናም አቅንተዋል
ዹዚህ ዓመት ዚእስያ-ፓሲፊክ ምጣኔ ሃብታዊ ትብብር (አፔክ) ጉባዔ አስተናጋጅ በሆነቜው ቪዚትናም ዚሚገኙት ትራምፕ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ያደርጋሉ ዚተባለው ንግግር እዚተጠበቀ ነው።
አሜሪካ ወደፊት በቀጣናው ስለሚኖራት ሚና እንዲሁም በንግድ እና ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገት ትብብሮቜ ዙሪያ ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል። ትራምፕ 'ቅድሚያ ለአሜሪካ' በተሰኘው መርሃቾው መሠሚት ኚቀጣናው ዚንግድ ስምምነት መውጣታ቞ውና በጃፓንና ቻይና ተይዞ ዹሚገኘውን ዹኃይል ሚዛን ለመመለስ ቃል መግባታ቞ው ዚሚታወስ ነው። ዚእስያ-ፓሲፊክ ምጣኔ ሃብታዊ ትብብር (አፔክ) ዹ21 ሃገራት ስብስብ ሲሆን ኚዓለማቜን ጠቅላላ ዹሃገር ውስጥ ምርት ዕድገት 60 በመቶውን ይይዛል። ትራምፕ ስልጣን በያዙ ማግስት 'ትራንስ ፓሲፊክ ፓርትነርሺፕ' ኚተባለው በአሜሪካና በ12 ዚእስያ ሃገራት መካኚል ኹነበሹው ስምምነት ሃገራ቞ውን ማግለላቾው ይታወሳልፀ ምክንያታ቞ውም ስምምነቱ ለአሜሪካ ዹሚጠቅም አይደለም ዹሚል ነበር። በትራምፕ እና በሩስያው መሪ ፑቲን መካኚል ሊደሹግ ዚሚቜለው ንግግር እውን ይሁን አይሁን እስካሁን ዚታወቀ ነገር ዚለም። ለ30 ዓመታት ያክል አሜሪካ 'በአፔክ' አማካይነት በአህጉሹ እስያ ኹሚገኙ እንደ ጃፓንና ቻይና ካሉ ዚዓለማቜን ምጣኔ ሃበታዊ ማማዎቜ ጋር ዹጠበቀ ግንኙነት መሥርታ ቆይታለቜ። ነገር ግን ኚትራምፕ በኋላ ነገሮቜ መንገዳ቞ውን ቀይሚዋል። ለዘመናት ኚእስያ ጋር ዹነበሹው ዚንግድ ግንኙነት አሜሪካንን ጎድቷታል ሲሉ መደመጥ ጀምሚዋል። ዶናልድ ዛሬ ዚሚያደርጉት ንግግር ኹዚህ በኋላ አሜሪካ በቀጣናው ዚሚኖራት ሚና ምን ሊመስል እንደሚቜል ይጠቁማል ሲሉ ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያዎቜ ይናገራሉ። ነገር ግን ዹአፔክ አባል ሃገራት ቻይናንም ጚምሮ ኚአባልነት በመሰሹዝ ዚራሳ቞ውን ጥምሚት ሊመስርቱ እያሰቡ እንደሆነም እዚተነገሚ ይገኛል።
news-52740284
https://www.bbc.com/amharic/news-52740284
ዚህንድ ሆስፒታል ኮሮናቫይሚስ ኚተገኘባ቞ው እናቶቜ ኹ100 በላይ ህጻናትን አዋለደ
በህንዷ ሙምባይ ኹተማ ዹሚገኝ አንድ ሆስፒታል ኹ100 በላይ ዹሚሆኑ ጀናማ ህጻናት በኮሮናቫይሚስ ኚተያዙ እናቶቜ ማዋለዱን አስታወቀ።
ሆስፒታሉ ባለፈው ዚሚያዝያ ወር ቫይሚሱ ካለባ቞ው እናቶቜ ካዋለዳ቞ው 115 ህጻናት ውስጥ መጀመሪያ ላይ ሊስቱ ቫይሚሱ እንደለባ቞ው ዚተነገሪ ቢሆንም በድጋሚ በተደሹገ ምርመራ ኚኮቪድ-19 ነጻ መሆናቾው መሚጋገጡን ዶክተሮቜ ተናግሚዋል። ለመውለድ ወደ ሆስፒታሉ ኚመጡት በበሜታው ኚተያዙ እናቶቜ መካኚል ሁለቱ በሆስፒታሉ ውስጥ ዚሞቱ ሲሆን አንዷ ልጇን ኹመገላገሏ በፊት ነበር ህይወቷ ያለፈው። ዚህንድ ዚገንዘብና ዹመዝናኛ ኹተማ በሆነቜው ሙምባይ እስካሁን ወደ 20 ሺህ ዹሚጠጉ ነዋሪዎቿ ላይ ቫይሚሱ ዹተገኘ ሲሆን ኹ730 በላይ ዚሚሆኑት ደግሞ ህይወታ቞ው አልፏል። በሎክማኒያ ቲልካ በተባለው አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ዚኮሮናቫይሚስ ካለባ቞ው እናቶቜ ኚተወለዱት ህጻናት ኚግማሜ ዚሚበልጡት በቀዶ ህክምና ዚተወለዱ ሲሆን ዚተቀሩት ግን በተፈጥሯዊ መንገድ መውለዳ቞ውን ዚሐኪም ቀቱ ኃላፊዎቜ ተናግሚዋል። ኚተወለዱት ህጻናት መካኚል 56ቱ ወንዶቜ ሲሆኑ 59ኙ ድግሞ ሎቶቜ ና቞ው። በሜታው ኚተገኘባ቞ው እናቶቜ መካኚል ሃያ ሁለቱ ወደ ሌላ ሆስፒታል ዚተላኩ ሲሆን በቫይሚሱ እንዎት ሊያዙ እንደቻሉ አልታወቀም። "ቫይሚሱ ኚተገኘባ቞ው ወላዶቹ መካኚል አብዛኞቹ ዚበሜታውን ምንም አይነት ምልክት ያላሳዩ ሲሆን አንዳንዶቹ ብቻ ናቾው ትኩሳትና ትንፋሜ ማጠር ዚታዚባ቞ው ሲሉ ሐኪሞቹ ተናግሚዋል።
news-53808306
https://www.bbc.com/amharic/news-53808306
ደላላ፡ ሚሊዹነር ዹሆኑ ‹‹ኢንተርናሜናል ዹበይነ መሚብ› አጭበርባሪ ደላሎቜ
ጋብሬል ቀልትሚን ኚኡራጓይ ወደ ማያሚ ዚመጣው እውቅ ዚኚበሮ ተጫዋቜ ለመሆን ነበር፡፡ ኚአምስት ዓመት በፊት ዚቀት ኪራይ መክፈል አይቜልም ነበር፡፡
ተማሪ ኚነበሚቜው ሎት ጓደኛው ዚምሳ ይበደርም ነበር፡፡ ኚዚያ በድንገት ተተኮሰ፡፡ 20 ሚሊዮን ዶላር አገኘ፡፡ ነገሩ በበይነመሚብ ንግድ ውስጥ በዕቃ አቅራቢና በደንበኛ መሀል ዹሚደሹግ ዚድለላ ሥራ ነው፡፡ ‹‹ድሮፕሺፒንግ›› ይባላል፡፡ ድለላ ለማለት እንኳ ይኚብዳል፡፡ ሥራው እንዎት ነው ዚሚሰራው ዹሚለውን ቆዚት ብለን እንመለስበታለን፡፡ በርካታ ሰዎቜ ይህንን ትርፉ ዚሚያቋምጥ ሥራ በመሥራት ላይ ና቞ው፡፡ ለዚህ ሥራ ዚሚያስልገው ቆንጆ ኢንተርኔትና ቆንጆ ላፕቶብ ብቻ ነው፡፡ ጠዋት ኚብርድልብስ ሳይወጡ መሰራት ይቜላል ይላሉ፣ ትርፍ ያጋበሱበት፡፡ እንዎት? ሻጮቹ እንዲያውም ዚሚሞጡትን ዕቃ አይዳስሱትም አይነኩትም፡፡ መጋዘን ዚላ቞ውም፡፡ ግን እዚሞጡ ያተርፉበታል፡፡ ሂደቱ እንዎት እንደሆነ እንመልኚት፡፡ ይሄ ዹበይነ መሚብ ደላላ (dropshipper) ላፕቶፑን ይኚፍትና ርካሜ ዹሆነ ዕቃ ኚአንዱ ዚቻይና በይነመሚብ ገበያ ይፈልጋል፡፡ ኚዚያ ይኌ ደላላ ምን ያደርጋል? በቅመም ያበደ ሻይ እንደሚባለው በቀለም ያሞበሚቀ ድሚ ገጜ ያሰራና ይህንን ርካሜ ዕቃ በድሚ ገጹ ይለጥፈዋል፡፡ ድሚ ገጹ ግን ምርቱ 'ኊሪጅናሌ' አሜሪካ ሰራሜ ወይም ጀርመን ሰራሜ ሆኖ ነው ዚሚለጠፈው፡፡ ኚዚያ ይኾው ዚበይነመሚብ ደላላ ወደ ማኅበራዊ ዚትስስር መድሚኮቜ ይሄድና ኹፍሎ 'ያበደ' ማስታወቂያ ለዚህ እቃ ያሰራል፡፡ በፌስቡክ፣ ቎ሌግራም ወይም ኢንስታግራም እጅግ ተጜእኖ ፈጣሪ ለሚባሉ ሰዎቜ ገንዘብ እዚኚፈለ ይህንን ምርት ያስተዋውቃል፡፡ ይህን ዚሚያደርገው ምርቱ ላይ ጥርጣሬ እንዳይፈጠር በማለም ነው፡፡ ስለዚህ አንድ ደንበኛ ይህንን ዕቃ በሚያዝበት ጊዜ ኚገዥው መጀመሪያ ገንዘቡን ይቀበላል፡፡ ደላላው ኚገዢው ገንዘቡ ሲደርሰው ነው ምርቱን ኚቻይና ዚሚገዛው፡፡ ኚዚያ ዕቃው በቀጥታ ወደ ገዢው ይጫናልፀ ኚቻይና፡፡ ዹበይነ መሚቡ ደላላ ዕቃውን አልነካውም፣ አልዳሰሰውም፡፡ ነገር ግን ገንዘብ ያገኛል፡፡ በሌላ ቋንቋ ይህ ደላላ በመንፈስ በገዥና በሻጭ መሀል ያለ ሰው ነው፡፡ ዹሚደንቀው ታዲያ ይህ ሥራ ወንጀል አለመሆኑ ነው፡፡ ምኑ ነው ወንጀል፡፡ ምናልባት ኚሚገባው በላይ አዳንቆና አዳምቆ ማስታወቂያ መሥራት? ቜግሩ በዚህ ሕጋዊ ሥራ ውስጥ ዚሚጚበጥ ነገር ስለሌለ አጭበርባሪዎቜ መኖራ቞ው ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደንበኞቜ ገንዘብ ኹፍለው እቃ቞ው ግን አይላክላ቞ውም፡፡ ይህ በሕጋዊዎቹ ዹበይነ መሚብ ደላሎቜ ዘንድ ዹሚፈጾም ሳይሆን በነሱ ስም ዹሚፈጾም ወንጀል ስለሆነ ምንም ማድሚግ አይቻልም፡፡ ጋብሬል በዚህ መንገድ ቻይና ስሪት ዹሆኑ ዚብሔራዊ አሜሪካ እግር ኳስ ሊግ (NFL) ምርቶቜን ይ቞በቜባል፡፡ ሰዎቜ ዚሚገዙት ዚአሜሪካ ኊሪጅናሌ ምርት እዚመሰላ቞ው ነው፡፡ በዚህ መንገድ በአንድ ወር $50,000 ዶላር አተሚፈ፡፡ ኚዚያ በኋላ ግን ዹተጭበሹበሹ እቃ ሞጬ አላውቅም ይላል፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎቜ አንድ ጊዜ ጥሩ ገንዘብ ካገኙ በኋላ ይሰወራሉ፡፡ በወር ውስጥ ጥሩ ትርፍ ካገኙ በኋላ እቃ መላክ ዚሚያቆሙ ደላሎቜም አሉ ብሏል ለቢቢሲ። አንዳንድ ጊዜ እቃዎቹ ዚተባሉት አይነቶቜ ይሆኑና ነገር ግን ዚአእምሮ ጥበቃ መብታ቞ው በማይጠበቅበት አገር ይመሚታሉ፡፡ እነሱን ስንሞጥ ገንዘብ እናገኛለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ምርቶቹ ዹሌላ ሆነው ማሞጊያ቞ው ዚታዋቂ ድርጅት ስም ሊለጠፍበት ይቜላል፡፡ ኬቚን ዎቪድ ሌላኛው ዹበይነ መሚብ ደላላ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ዹተጭበሹበሹ ነገር ውስጥ ገብቌ አላውቅም ይላል፡፡ ሆኖም ጓደኞቹ ተመሳስለው ዚተሰሩ ምርቶቜን በመሞጥ በመቶ ሺህ ዶላሮቜ አጋብሰዋል፡፡ በተለይ ዹአፕል ገመድ አልባ ዚጆሮ ማዳመጫዎቜ AirPods ተ቞ብቜበዋል ይለል፡፡ ሐሳዊ ምርቶቜ ድሮፕሺፒንግ ለበይነመሚብ ንግድ አዲስ ሐሳብ አይደለም፡፡ አሁን አዲስ ያደሚገው ማኅበራዊ ሚዲያው ነው፡፡ እነዚህ ደላሎቜ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ተጜእኖ ፈጣሪዎቜን ስለሚጠቀሙ በቀላሉ ዚተትሚፈሚፈ ገበያ ማግኘት ቜለዋል፡፡ ለዚህም ነው ትርፋ቞ው አስደንጋጭ ዚሆነው፡፡ ቀደም ብሎ እነዚህ ሰዎቜ ያልዳሰሱትን ምርታ቞ውን ያስተዋውቁ ዹነበሹው በኢቀይ ወይም በተለመዱ መገናኛ ዘዎዎቜ ነበር፡፡ አሁን ነገሩ ሁሉ ተቀዚሚ፡፡ ሰፊ ተቀባይነት ያገኙ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ዝነኞቜ ምርት አስተዋዋቂ ኹሆኑ በኋላ ገበያው ደርቷል፡፡ ኮርተኒ ካርዳሺያን ሳራ መባርኪ ማግኔቲክ ኀስ ኀል ለሚባል ድሮፕሺፒንግ ድርጅት ውስጥ ሰርታለቜ፡፡ ይህ ድርጅት ዹሚሾጠው ዚራሱን ብራንድ ነው፡፡ ሆኖም ስለ ድሮፕሟፒንግ አስገራሚ ሚስጥሮቜን ታውቃለቜ፡፡ ሳራ ለቢቢሲ ክሊክ እንደገለጞቜው ዚዝነኞቹ ዚካርዳሺያን ቀተሰብ ዚሆነቜው ኮርተኒ ካርዳሺያን ይህንን ምርት በኢኒስታግሚም አስተዋወቀቜው፡፡ ኮርተኒ ካርዳሺያን በኢኒስታግራም 100 ሚሊዮን ተኚታይ አላት፡፡ ይህን ዹተጭበሹበሹ ዚውበት ምርት ለማስተዋወቅ ሁለት መቶ ሺህ ዶላር ተኚፈላት፡፡ ዚተኚፈላት ብዙ ቢመስልም ድርጅቱን ትርፍ በትርፍ አደሚገቜው፡፡ በገበያ ጎርፍ ተመታ፡፡ በተጜእኖ ፈጣሪዎቜ ማስተዋወቅ በአንድ ጊዜ እጅግ ዝነኛ ብራንድ (ዚንግድ መታወቂያ) ለማግኘት አቋራጭ መንገድ ሆኗል፡፡ ሳራ እንዲህ ትላለቜ፡- ብዙ ሰዎቜ እንደ ኮርተኒ ካርዳሺያን ያለ ኹፍተኛ ዝና ያለው ሰው ምርትን እንዲያስተዋውቅ ምርቱ ዚግድ ኩርጂናሌና ያልተጭበሚበሚ መሆን እንዳለበት ያስባል፡፡ ያ ውሞት ነው፡፡ አንዳንድ እውቅ ሰዎቜ ብቻ ናቾው ሐሳዊ ምርት አስተዋውቁልን ሲባሉ እምቢ ዚሚሉት፡፡ ብዙዎቹ ቜግር ዚለባ቞ውም፡፡
news-46361404
https://www.bbc.com/amharic/news-46361404
ምግብ ማብሰልና ማጜዳት ዚቀት ውስጥ ጥቃቶቜን ለመቀነስ
ሩዋንዳ ውስጥ ወንዶቜን ዚቀት ውስጥ ስራ እንዲሰሩ በማድሚግ በቀት ውስጥ ዹሚፈጾሙ ጥቃቶቜን ለመቀነስ ዚሚሚዳ ፕሮግራም በሙኚራ ላይ ነው።
ሙሆዛ ዣን ፒዬር ኹዚህ በፊት ባለቀቱን ይደበድባት ነበር። ዚባለቀቱ ስራ ልጅ ለመውለድና እነሱን ለመንኚባኚብ ብቻ እንደሆነ ያስብም ነበር። '' ዚአባ቎ን ፈለግ ነበር ዚተኚተልኩት። አባ቎ በቀት ውስጥ ምንም አይነት ስራ አይሰራም ነበር።'' ይላል። " ልክ ወደ ቀት ስገባ ዹሆነ ያላለቀ ስራ ካለ ሁሌም ቢሆን እንጣላለን። ሰነፍ ነሜ እያልኩ እጮህባታለሁ። ለምን ወደ ቀተሰቊቜሜ ተመልሰሜ አትሄጂም እላታለሁ።'' ነገር ግን በቀታቜን ውስጥ ድንገት ትልቅ ለውጥ መጣ። ሙሆዛ ዣን ፒዬር ምግብ ማብሰልና ቀት ማጜዳት ተማሚ። • በአለም ላይ በዹቀኑ 137 ሎቶቜ በህይወት አጋሮቻ቞ውና በቀተሰቊቻ቞ው ይገደላሉ • ታሪክ እዚቀዚሩ ያሉት ሎቶቜ ዚፒዬር መንደር ምዉሊሬ ዚምትሰኝ ሲሆን ዚምትገኘው በምስራቃዊ ሩዋንዳ ነው ። በዚህቜ መንደር በመተዋወቅ ላይ ያለው ዚሙኚራ ፕሮጀክት ምስጋና ይግባውና ወንዶቜ በቀት ውስጥ ምግብ እንዲያበስሉና ሌሎቜ ስራዎቜም መስራት እዚተበሚታቱ ነው። ፕሮጀክቱ 'ባንደቀርሆ' ይባላል። እንደ ፒዬር ላሉ ዚአካባቢው ወንዶቜ ጥሩ ተሞክሮ እያስተማሚ ነው። ፒዬር ትምህርት ቀት ገብቶ ምግብ ማብሰል፣ ቀት ማጜዳትና ልጆቜን መንኚባኚብ ዚሚቜልበትን መንገዶቜ ተምሯል። ''በክፍሉ ውስጥ ወንዶቜ ቀት ማጜዳት ይቜላሉ ወይ ተብለን እንጠዚቃለንፀ ዚሁላቜንም መልስ አዎ ይቜላሉ ነው።'' '' በመቀጠል ኚእናንተ መካኚል ማነው ቀቱን ዚሚያጞዳ ሲሉንፀ ማንም እንላለን።'' ምንም እንኳን ፒዬር ዚቀት ውስጥ ስራዎቜ ባለቀቱ ብቻ መስራት እንዳለባት ቢያስብምፀ ዚፕሮጀክቱ አስተባባሪዎቜ ምግብ ዚማብሰልና ቀት ዚማጜዳት ስልጠና ሰጥተውታል። ''ትምህርት ቀት ዹተማርነውን ወደ ቀት ተመልሰን ተግባራዊ ለማድሚግ እንሞክራለን።'' ይላል ፒዬር። ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ቀት ሲመለሱ ፈተና ኊለባ቞ው። በቀት ውስጥ ዚሰሩትን ምግብ ደግመው እንዲሰሩ ይጠዚቃሉ። "አሁን ጣፋጭ ምግቊቜ መስራት ቜያለውፀ ዚልጆቌንም ልብሰ ዚማጥበው እራሎ ነኝ። ጜዳቱንም ቢሆን ቀጥ አድርጌ ይዀዋለው።'' ሲል በደስታ ይናገራል ፒዬር። ነገር ግን እንዲህ ተለውጩ ቀ቎ ቀ቎ ማለቱ በብዙ ጓደኞቹ ዘንድ ነቀፌታንና ፌዝ አስኚትሎበታል። በተለይም መጀመሪያ አካባቢ ነገሮቜ ሁሉ ኚባድ እንደነበሩ ያስታውሳል። '' ትክክለኛ ወንድ ምግብ አያበስልም'' ይሉት ነበር። ''ቀተሰቊቌና ጓደኞቌ እንደውም ባለቀ቎ ዹሆነ መድሃኒት ሳትሰጠው አይቀርም ብለው እስኚማሰብ ደርሰው ነበር።'' በቀት ውስጥ ስራዎቜን መስራት ኹጀመሹ ወዲህፀ ኹሌላ ጊዜው በተለዹ ልጆቹ እሱን መቅሚብ መጀመራ቞ውንና ባለቀቱ ዹሙዝ ንግድ መጀመሯን ይናገራል። በዚህ ምክንያትም ዚቀተሰባ቞ው ገቢ መጚመሩንና ልጆቹ በአግባቡ መመገብ መጀመራ቞ውን በኩራት ይናገራል። "ባለቀ቎ም ቢሆን እንደ ድሮው በቁጣ አትመልስልኝም። ቁጭ ብለን ተወያይተን በነገሮቜ ላይ እንወስናለን።'' • "ማንም መብታቜንን ሊሰጠን ስለማይቜልፀ ሎቶቜ ማንንም ሳይጠብቁ በራሳ቞ው መታገል አለባ቞ው" • ዹተነጠቀ ልጅነት ፍርሃትና ነጻነት ዚፒዬር ባለቀት ሙሳብዪማና ዮልፊን ኹዚህ በፊት ትንሜ ነጻነትና ብዙ ፍራቻ እንደነበሚባት ታስታውሳለቜ። ''በህይወቮ ስራ ሰርቌ ገንዘብ ማግኘት እቻላለሁ ብዬ አስቀ አላውቅም ነበር። ምክንያቱም ስለ እንደዚህ አይነት ነገሮቜ ለማሰብ ጊዜውም አልነበሚኝም። ሁሌም ቢሆን ቀት ውስጥ ዹሆነ ያላለቀ ስራ ይኖራል።'' ዮልፊን ሁሌም ቢሆን ሌሊት 11 ሰአት በመነሳት ወደ ሙዝ ገበያው ስትሄድፀ ፒዬር ደግሞ ቀት ውስጥ አራት ልጆቻ቞ውን ይንኚባኚባል። ''ደክሞኝ ኚስራ ስገባ ቀቱ ንጹህ ሆኖ፣ ቆንጆ ምግብ ቀርቩ ይጠብቀኛል።'' ትላለቜ። ሎቶቜና ኚሎቶቜ ጋር ተያይዘው ዚሚነሱ ዚተሳሳቱ ሃሳቊቜን ለመቀዹር አልሞ ደቡብ አሜሪካ ውስጥ ዹተቋቋመው ፕሮጀክቱፀ ህጻናትን ዚመንኚባኚብና ሌሎቜ ዚቀት ውስጥ ስራዎቜን ወንዶቜ 50 በመቶ ማኹናወን ሲጀምሩ እውነትም እኩልነት ሰፍኗል ማለት ነው ብሎ ያምናል። አስተባባሪዎቹ በሰሩት ዚዳሰሳ ጥናት መሰሚት ባለፉት ሁለት ዓመታት ሩዋንዳ ውስጥ ምግብ ማብሰልና ህጻናትን ስለመንኚባኚብ ስልጠና ዚወሰዱ አባቶቜ ሚስቶቻ቞ውን ዚመደብደብና ሁሉንም ስራ እነሱ እንዲሰሩ ዹመጠበቅ አስተሳሰባ቞ው በእጅጉ ቀንሷል። ዚፒዬርና ዹዮልፊን ዹተቀዹሹ አስተሳሰብ ለቀተሰባ቞ው ብቻ ሳይሆን ለመላ መንደሪቱ ትልቅ ትምህርት ሆኗል። ''በመኖሪያ መንደራቜን ዚባልና ዚሚስት አለመስማማት ሲኖርም ሆነ ሌላ ግጭት ሲፈጠር ለማስታሚቅ እኛ ዹምናቀርበው ሃሳብ ሁሌም ቢሆን ተቀባይነት ያገኛል።'' "ምክንያቱ ደግሞ እኛ በቀታቜን ውስጥ ሰላማዊ ኑሮ ስለምንኖር ነው።''