id
int64
0
43.1k
text
stringlengths
98
149k
0
አየር መንገዱ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ጣሊያን በማምራት ላይ በነበረበት ጊዜ ረዳት አብራሪው የጉዞውን አቅጣጫ በመቀየር ጄኔቭ አውሮፓላን ማረፊያ በማሳረፍ እጁን ለፖሊስ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚኒኬሽን ባለስልጣን የሆኑት ሬድዋን ሁሴን አየር መንገዱ የተጠለፈው ሱዳን በቆመበት ጊዜ በተሳፈሩ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ነው በማለት መጀመሪያ ላይ ለረዩተርስ መግለጫ ቢሰጡም፣ የስዊዘርላንድ ፖሊስ ግን ፈጥኖ ጠላፊው የአየር መንገዱ ረዳት አብራሪ መሆኑንና የደህንነት ስጋት እንዳለበት በመግለጽ እጁን በሰላም መስጠቱን አስታውቀዋል። ማንነቱ ያልታወቀው ረዳት ፓይለት በ30 ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ ጄኔቭ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሰ በመስኮት በኩል በመውጣት እጁን በሰላም ለፖሊስ ሰጥቷል። ፖሊስ እንዳስታወቀውም ጠላፊው ምንም አይነት የጦር መሳሪያ አልያዘም። ጄኔቭ የሚገኘው የኢሳት ወኪል እንደዘገበው ምንም እንኳ ጄኔቫ አየር ማረፊያ ከሰአታት በሁዋላ ተራግገቶ ስራውን ለማከናወን የቻለ ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር እስከ ቀኑ 9 ሰአት ድረስ ተሳፋሪዎች ወደ ሮም አልተመለሱም፣ አውሮፕላኑም ባለበት ቆሞ ይታይ ነበር። ከቀኑ 9 ሰአት ከሰላሳ አካባቢ አውሮፕላኑ ለጥገና ወይም ተሰፋራዎችን ወደ ሮም ለመመለስ ሲንቀሳቀስ መታየቱን ወኪላችን ገልጾ፣ ጠላፊውን ለማግኘት የተደረገው ሙከራ በፖሊስ ጥብቅ ቁጥጥር የተነሳ ሊሳካ አልቻለም። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በተለያዩ ጊዜያት በአስተዳደሩ እንደሚማሩ ይታወቃል። አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በማንሳት ጠለፋውን ከፖለቲካ ጋር በማያያዝ ለማየት እየሞከሩ ነው። ረዳት ፓይለቱ አላማው ጥገኝነት መጠየቅ ቢሆን ኖሮ አውሮፕላኑን ሮም ላይ ካሳረፈ በሁዋላ ጄኔቭ ገብቶ በሰላም እጁን መስጠት ይችል እንደነበር ጁኔቭ የሚገኙ አንዳንድ አስተያየት ሰጪ ይናገራሉ። ረዳት ፓይለቱ ይህ እድል እያለው እና አውሮፕላን መጥለፍ ወንጀል መሆኑን እያወቀ እንዲህ አይነት እርምጃ ለመውሰድ የተነሳሳው አንድ ከባድ ምክንያት ቢኖረው ነው በማለት እኝሁ አስተያየት ሰጪ ገልጸዋል። ስቱዲዮ ከመግባታችን በፊት በአውሮፕላኑ ወስጥ ተሳፍራ የነበረች አንዲት ወጣት አግኝተናል። ወጣቱዋ እንደምትለው አውሮፐላኑ የተጠለፈው ከሮም ወደ ሚላን በሚመበርበት ጊዜ ነው። ሮም ማረፉንና መንገደኞችን ማሳፈሩን ወጣቷ ተናግራለች። አቶ ሬድዋን በበኩላቸው አውሮፐላኑ ሮም ሳያርፍ ወደ ጄኔቭ መሄዱን ተናግረዋል። ወጣቱዋ አብራሪው ረጅም ና ጠይም መሆኑንሮም ላይ ሻንጣውን ማውረዱንና ፊቱ ላይ አለመረጋጋት ይታይበት እንደነበር ገልጻለች። ‹‹ይህንን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መወያየት ክልክል ነው፡፡›› በማለት በተንጎላጀጀ ድምፅ ጠባቂው ተናገረ፡፡ ቀጠል አደረገናም ‹‹መነጋገር የምትችሉት ስለቤተሰብ ጉዳዮች ብቻ ነው›› በማለት ተናገረ፡፡ ይህን ከላይ ያለውን ሐሳብ የሚመለከት ማንኛውም አንባቢ፣ ጉዳይ የተፈፀመው እዚህችው እማማ ኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባሉ አጃኢበኛ እስር ቤቶች፣ ቤተሰብ መጠየቂያው እንደሆነ መጣራቱ አይቀርም፡፡ ይሁንና በመግቢያው ላይ ያለው ጽሑፍ ተቀንጭቦ የተወሰደ ‹እናት› ከተሰኘውና እ.ኤ.አ. በ1906 ከታተመው የስመ ጥሩው ሩስያዊ ደራሲ ማክሲም ጎርኪይ ታሪካዊ ልቦለድ ገፅ 102 ላይ ነው፡፡ የዛሬ 108 ዓመት አካባቢ ማለት ነው፡፡ አቤት ርቀቱ!… ይህ ርቀት ግን ለእኛ ምንም ማለት ያልሆነ ይመስላል፤ ለምን? ቢሉ ዛሬም ይህንንና ይህን የመሳሰለውን አስፍተን እየሠራን እንገኛለን፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ሁኔታዎች እየተጓዝን ያለነው የቁልቁለት ሩጫ በእጅጉ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል፡፡ ‹ጠበቅ ያለ እርምጃ፣ የማያዳግም እርምጃ፣ የማስወገድ እርምጃ፣…› ወዘተ የሞሉ ከሕግ መርሕዎች ሳይሆን ከጥላቻ ፖለቲካ የሚመነጩ ፀያፍ አነጋገሮችን በሕዝብ የመገናኛ ዘዴዎች ሲተላለፉ እየሰማን እየታዘብን ነው፡፡ ቃል በቃል ‹ቀይ ሽብር ይፋፋም› ብሎ ማወጅ የቀራቸው የሕግም የግብረገብም ሚዛን ያልወጣላቸው ቀረርቶች በተለይ በእስር ቤት የምንገኝ ኢትዮጵያውያንን እየሰበሰቡን ይገኛሉ፡፡ በኢ.ቴ.ቪ. የአብዮታዊ እርምጃ ፕሮግራሞች በቀረቡ ማግስት አሁን በዝርዝር ብለው የብዙ ቤተሰቦችን ስሜት ሊያሸማቅቁ የሚችሉ ሰቆቃና እንግልቶች በአስደማሚ ስልት ተቀናብረው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ እስኪ የተወሰኑትን እንይ፡፡ ማንኛውም ታሳሪ ቤተሰብ በቅርብ ሊጎበኘው በሚችለው እስር ቤት ይታሰር የሚለው ሕግ የተሻረው በእኛ ላይ ነው፡፡ ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት› ማለት ናት፡፡ ቤተሰብ ያን ያህል የበርሃ ጉዞ አቋርጦ የእኛዋ ሳይቤሪያ ሲደርስ በአድካሚና ግብረ-ገብ በጎደለው ፍተሻ መከራውን ማየቱ አንሶ ጆሮ ግንዱ ላይ በቆሙ የቤተሰብ አገናኞች ቤተሰባዊ ገመናውን አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሕፃናት ልጆች ወላጆቻቸው አንድ ላይ ሆነው ናፍቆታቸውን መወጣት አይችሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖሊሶቹ ሲዘናጉልን ልጆቻችንን አቅፈን እንስማለን፡፡ ይህ ከሆነ ቁጣና ዘለፋው ምንም አይደለም፡፡ ግን በሁኔታው ሕፃናቱ ክፉኛ ይበረግጋሉ፣ የእኛ ስጋት ይጋባባቸዋል፤ በዚህም መንፈሳቸው እርብሽብሽ ብሎ ወደቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ ሁኔታው በዚህ አያበቃም፡፡ ምንም እንኳን የመጠየቂያ ሰዓቱ በግልፅ የተቀመጠ ቢሆን ከቤተሰቦቻችን ጋር ገና መነጋገር ስንጀምር ‹‹በቃ… ቶሎ ጨርሱ›› የሚባልባቸው ጊዜዎች ብዙ ናቸው፡፡ ቀጥሎ የሚመጣው የእስር ቤት ማኅበራዊ ጉዳዮችን ማለትም ለሳሙና፣ ለምግብ ማጣፈጫ፣ ለሻይ ለቡና፣ ለውስጥ አልባሳት፣ ለውኃ ማከሚያ/ውኃ አጋር/ ወዘተ፤ ገንዘብ የሚያስፈልገን ቢሆንም እና እንደሚያስፈልጉ ቢታወቅም ጉዳዩ ለይቶለት የማሰቃየት፣ ማንገላታት፣ መበቀል ሆኗልና ለአንድ ወር ከአንድ መቶ ብር በላይ መጠቀም እንዳንችል የተከለከልን የመሆኑ አሳፋሪ ሐቅ ነው፡፡ ይህ እየተፈፀመ ያለው ደግሞ ዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ በዚህ የተነሳም ለመግለጽ በሚከብድ ሁኔታ ሰብኣዊ ክብራችንን የማዋረድ ሙከራዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡ በአገራችን ላይ እኔ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን የጨረስኩት ዝዋይ በመሆኑ ብዙ ወዳጅ ዘመዶቼ በእዚህ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ለአካባቢው ነዋሪዎች በሳምንት እንዲጠይቁን የተፈቀደላቸው አንድ ቀን /ረቡዕ/ ብቻ ሲሆን ‹‹የት ነው የምታውቁት? እንዴት አወቃችሁት? ምንድን ነው የሚያመላልሳችሁ?›› በሚሉትና በሌሎችም ጥያቄዎች ተደናግጠው መምጣቱን እርግፍ አድርገው ትተውታል፡፡ ሀገሩ ሞቃታማ ነውና በዚያ ላይ በእያንዳንዱ ቤት እስከ 150 ሰው ይታሰርበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ እስረኛው የቱንም ያህል ፅዳቱን ለመጠበቅ ቢሞክርም የተባዩ መርመስመስ የእነ ትኋን እንዲህ መራባት፤ ለማሰብ እንኳን ይዘገንናል፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ገላን ሲቆፍሩ ማደር ነው፡፡ ሊናገሩት ይከብዳል፣ አንባቢንም ቅር ያሰኛል፤ ግን ይህ የፊልም ትረካ ሳይሆን በእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ላይ ሆን ተብሎ እየተፈፀመ ያለ ደባ ነው፡፡ […] ግን የባሰ አታምጣ ማለት ነው! ግን የባሰ ነገር አለ፡፡ አፈር ቅጠል የማይል ምግብ ይቀርብናል፡፡ ‹በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ› ከፍተኛ የውኃ እጥረት /ዝዋይ ሀይቅ አናት ላይ ተቀምጠን/ አለ፡፡ የእስር እስር እንዲሉ ጄኔራል መኮንኖቹን ጨምሮ አብዛኛዎቹ አባሪዎቻቸውና ሌሎች ሌሎች የተወሰንን እስረኞች የምንገኘው በልዩ ቅጣት ጭለማ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ እንደምንም ለመቋቋም ጥረት ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ አዲሱ ስልት ግን መዘዙ በጣም አደገኛ በመሆኑ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ፣ እያንዳንዱ ሃይማኖት ያለው፣ ፈርሐ እግዚአብሔር ያለው፣ እያንዳንዱ የመሠረታዊ ሰብኣዊ መብቶችና ነጻነቶች መከበር የሚያሳስበው እያንዳንዱ ሰው የሆነ ሰው ሁሉ ሊያውቀው ይገባል ስንል ድምፃችንን እናሰማለን፤ በሕክምና ንፍገት ወደሞት እየተገፋን ነው፡፡ ከወር በፊት ገደማ ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ አባል ናትናኤል መኮንን ለሕክምና በሪፈር ወደ ቃሊቲ ተልኮ የነበረ ቢሆንም፣ የዛኑ ዕለት ሕክምናውን ተነፍጎ ከሌሊቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ እስካሁን በሕመሙ እየተሰቃየ ይገኛል፡፡ የኢብአፓ ሊቀመንበር የነበረው ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር እንደዚሁ ለተጨማሪ ሕክምና ሪፈር ተብሎ ሲጠባበቅ ከቆየ በኋላ ዘዴው ተፈፃሚ ሆነበት እጁን አጣጥፎ ተቀምጧል፡፡ ከሕመሙ ጋር በተያያዘ በአካሉ ላይ አሳሳቢ ሁኔታ እየታየበት ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ገልጬው የነበረው የእኔ የኩላሊት ሕመም አሁን ለመቀመጥም፣ ለመንቀሳቀስ እያወከኝ የሚገኝ ሲሆን፣ እኔን ከቃሊቲ ዝዋይ ለማምጣት የተደረገው የተቀናጀ መረብ ሩብ ያህሉን ለሰብኣዊነት አውለውት ቢሆን ኖሮ እኔም ፋታ፣ እነሱም እርካታ ባገኙ ነበር፡፡ ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ! የጄኔራል መኮንኖቹ አባሪዎች የነበሩት ኮረኔል ተስፋዬ ኃይሉ እና ኢንጂነር ክፍሌ ስንሻው፣ በዶክተር መረራ በሚመራው ኦሕኮ ፓርቲ አባል የነበሩት አሕመድ ነጃሺ፣ በጭለማ ቤት የከረመው ተስፋሀን ጨመዳ፣ የቤንሻንጉሉ አዛውንት ወዘተ ተገቢውን ሕክምና በማጣት ሕይወታቸውን ያጡ የእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ እንዴት ሕክምና ይከለከላል!? ግፍና ጭቆና ተቃውመው ደማቸውን ያፈሰሱና አጥንታቸውን የከሰከሱ ታጋዮችን በሥልጣን ማግስት ከፍርድ በመለስ በየእስር ቤቱ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻቸው በሕክምና እጦት ሲረግፉ በእርካታ ማርመምን ከየት ተማሩት!? የኢትዮጵያ ሕዝብስ ምን ይላል!? ሰው የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከቶ ምን ይላሉ!? “ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ ኢትዮጵያዊ ማንነት አለኝ” ብዬ ስል የራሴ (የግሌ) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የአከባቢ ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የክልል (የብሄር) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። ወይም እነዚህ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ማንነቶቼ መጥፋት አለባቸው ማለት አይደለም። እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ስል የራሴን ማንነት አልቀበልም ማለት አይደለም። የራሴ ማንነት ስላለኝ ነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ሊኖረኝ የቻለው። እኔ የግል ማንነት ባይኖረኝ ኑሮ ኢትዮጵያዊ አልሆንም ነበር። ምክንያቱም የግል ማንነት ከሌለኝ የሀገር ማንነት ሊኖረኝ አይችልም። እያንዳንዱ ሰው የግሉ የሆነ ማንነት አለው። የግሉ ማንነት ስላለው ነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ያለው። ኢትዮጵያዊ ማንነት ራሱ የቻለ የሁላችን የጋራ ማንነት ነው። የትግራይ ማንነት ካለን የኢትዮጵያ ማንነት ለምን አይኖረንም? “ትግራዮች አንድ ነን” ካልን “ኢትዮጵያውያን አንድ ነን” ብንል ችግሩ ምንድነው? ኢትዮጵያዊነትኮ ከብሄር (ከክልል) ሰፋ ያለ ሀገራዊ ማንነት ነው። ሀገራዊ ማንነታችንን ብንቀበል ችግሩ ምንድነው? ኢትዮጵያውያን አንድ አይደለንም አትበሉኝ። ምክንያቱም ኢትዮጵያውያን አንድ ካልሆንን ትግራዮችም አንድ አይደለንም፤ አማራዎችም አንድ አይደለንም፣ ኦሮሞዎችም አንድ አይደለንም። አንድ የሆነ አይኖርም። “ኢትዮጵያውያን አንድ አይደለንም ምክንያቱም የተለያየ ታሪክና ባህል አለን” አትበሉኝ። ምክንያቱም እያንዳንዱ ግለሰብ፣ አውራጃ፣ ክልል (ብሄር) ወዘተ…ም የተለያየ ታሪክና ባህል ሊኖረው ይችላል። ኢትዮጵያውያን የተለያየ ባህልና ታሪክ ስላለን አንድ አይደለንም ካላችሁኝ ኦሮሞዎችም አንድ አይደሉም እላቸዋለሁ፤ ምክንያቱም የወለጋ ኦሮሞዎች፣ የሸዋ ኦሮሞዎችና የአርሲ ኦሮሞዎች የተለያየ ታሪክና ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን የተለያየ ባህልና ታሪክ ስላለን አንድ አይደለንም ካላችሁኝ አማራዎችም አንድ አይደሉም እላቸዋለሁ፤ ምክንያቱም ወለየዎች፣ ጎጃሞችና ጎንደሬዎችም የተለያየ ታሪክና ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን የተለያየ ባህልና ታሪክ ስላለን አንድ አይደለንም ካላችሁኝ ትግራዮችም አንድ አይደሉም እላቸዋለሁኝ፤ ምክንያቱም ተምቤኖች፣ ዓድዋዎች፣ ዓጋሜዎች፣ ራያዎች፣ ወልቃይቶች የተለያየ ታሪክና ባህል አላቸው። “የተለያየነው በቋንቋ ነው” ካላችሁኝ። የተለያየ ቋንቋ የማንነት መለያ መስፈርት ከሆነና እኛ ኢትዮጵያውያን የተለያየ ቋንቋ ስለምንናገር የተለያየን ከሆንን ትግራዮችም አንድ አይደለንም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ አንድ ቋንቋ ብቻ የሚናገር ህዝብ አይደለም፤ አንድ ዓይነት ባህል ያለው ህዝብ አይደለም። ምሳሌ ኢሮብ (ቋንቋ ሳሆ) የራሳቸው ቋንቋና ማንነት አላቸው። ግን በትግራይ ክልል ዉስጥ ናቸው። በትግራይ ኩናማዎች አሉ (ወልቃይቶች ጨምሮ)። የራሳቸው ባህል አላቸው። ራያዎች የራሳቸው የሚኮሩበት ባህል አላቸው። ስለዚህ በትግራይ ክልል የተለያዩ ባህሎችና ቋንቋዎች አሉ። ግን ትግራዮች (ተጋሩ) አንድ ነን። ተጋሩ አንድ ነን ስንል አንድ ቋንቋ፣ አንድ ባህል ብቻ አለን ማለታችን አይደለም፤ ተጋሩ አንድ ነን ስልን ሌላ ቋንቋ፣ ማንነት፣ ባህል ወዘተ ያላቸው ህዝቦች እውቅና አንሰጥም ማለት አይደለም። ማንነታቸው እንዲቀይሩ እናስገድዳቸዋለን ማለትም አይደለም። ተጋሩ አንድ ነን ስንል የግላችን ማንነት ጠብቀን የጋራ በሆነ የትግራይ ማንነት በአንድነትና በእኩልነት እንኖራለን ማለት ብቻ ነው። ተጋሩ አንድ ነን። ኢትዮጵያውያንም አንድ ነን። የተለያየ ቋንቋ መናገራችን የተለያየን ስለመሆናችን ማረጋገጫ ሊሆን አይችልም። ስለ ኢትዮጵያዊ ማንነት ስናወራ ስለ ሌሎች ማንነቶች እውቅና እየሰጠን ነው። ምክንያቱም የያንዳንዳችን ማንነት ከሌለ የጋራ ማንነታችን አይኖርም። የያንዳንዱ ግለሰብ ማንነት ካከበርን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ማንነት እናከብራለን። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ ማንነት ማለትኮ የኛ ማንነት ማለት ነው። “እኛ” ማን ነን? እኛ ሁላችን ነን። ኢትዮጵያዊ ማንነትን ስናስቀድም ሁሉም ኢትዮጵያውያንን እናስቀድማለን። የዓድዋ ወይ የራያ ወይ የኢሮብ ማንነት ብናስቀድም እያስቀደምነው ያለነው ህዝብ የአንድ ወረዳ ወይ አከባቢ ብቻ ነው የሚሆነው። የትግራይ ማንነት ብናስቀድምም የምናስቀድመው የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው የሚሆነው። ትንሽ ጠበብ ያለ ነው። ሌሎችስ ለምን እንተዋቸዋለን? ሌሎች (አማራዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ሶማሌዎች፣ ደቡቦች፣ ዓፋሮች፣ ጋምቤላዎች፣ ቤኑሻንጉሎች፣ ጋምቤላዎች፣ ሃረሪዎች ወዘተ) ለምን በእኩል ዓይን አናስቀድማቸውም? የትግራይን ማንነት የሚያስቀድም ሁሉ የኢትዮጵያ ማንነትም ማስቀደም አለበት። ምክንያቱም የትግራይን ማንነት ስታስቀድም የሌሎች ወገኖች ማንነት ትተወዋለህ። የኢትዮጵያ ማንነት ስታስቀድም ግን የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች (የትግራይ ጨምሮ) ማንነት ነው የምታስቀድመው። በኢትዮጵያዊ ማንነት የማምነው ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ማስቀደምና ማክበር ስላለብኝ ነው። በኢትዮጵያ ዉስጥ እየኖረ የራሱን ብሄር የሚያስቀድም ሰው በሁሉም ብሄሮች (ኢትዮጵያውያን) እኩልነት አያምንም ማለት ነው። በብሄሮች እኩልነት የማያምን ደግሞ የኢትዮጵያን አንድነት ማስጠበቅ አይችልም። ምክንያቱም እኩልነት ከሌለ አንድነት የለም። አንድነት ከሌለ ሀገር የለም። ሀገር ከሌለ ሉአላዊነት የለም። ሉአላዊነት ከሌለ የህዝብ ደህንነት አይጠበቅም። ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነት የማያስቀድም ለህዝብ አይበጅም። የቡድን (የብሄር) መብትን የሚያስቀድመው የኢህአዴግ መንግስት የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች እኩልነት እንዳረጋገጠ ይተርክልናል። ግን በትክክል የኢህአዴግ መንግስት ሁሉንም ብሄሮች በእኩል ዓይን ያያል? ትንሽ እንውረድና …! በፓርላመንታዊ ስርዓት (ኢህአዴግ የሚከተለው ዓይነት) የሀገር ከፍተኛው የፖለቲካ ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስተርነት ነው። ሁሉም ብሄር፣ ብሄረሰቦች እኩል ናቸው ካልን ለዚህ ከፍተኛ የሀገር ፖለቲካዊ ስልጣን እኩል ዕድል አግኝተው መወዳድር አለባቸው። ታድያ በኢህአዴግ ዘመነ ስልጣን አንድ የዓፋር ወይ የሶማሌ ወይ የቤኑሻንጉል ጉሙዝ ወይ የሃረሪ ወዘተ ተወላጅ የጠቅላይ ሚኒስተርነቱን ስልጣን ለመያዝ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በእኩልነት የመወዳደር ዕድል አለው? በኢህአዴግ ዘመን ዓፋር ወይ ሶማል ወይ ጋምቤላ ጠቅላይ ሚኒስተር ሊኖረን ይችላል? አይችልም። ለምን? የሀገር ጠቅላይ ሚኒስተር ሁኖ መመረጥ የሚችለው የገዢው ፓርቲ አባል የሆነ ብቻ ነው። አባል መሆን ብቻ በቂ አይደለም። የፓርቲው ሊቀመንበር መሆን አለበት። የፓርቲ ሊቀመንበር የሚመረጠው ከፓርቲው አባል ፓርቲዎች ነው። የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች የደቡብ፣ ትግራይ፣ አማራና ኦሮምያ ብሄር ተወላጆች ብቻ ናቸው። ድርጅቶቹ ብሄር መሰረት ያደረጉ ናቸው። ስለዚህ በኢህአዴግኛ አሰራር አንድ የዓፋር ወይ የሶማል ወይ የቤኑሻንጉል ወይ የጋምቤላ ተወላጅ ጠቅላይ ሚኒስተር የመሆን ዕድል ወይ መብት የለውም። ይሄ ነው እኩልነት!? በግለሰባዊ ኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ግን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለማንኛውም ስልጣን ወይ ሐላፊነት እኩል የመወዳደር ዕድል ይኖረዋል። አንድ ኢትዮጵያዊ የሚመዘነው እንደ ሰው (እንደ ዜጋ) እንጂ በመጣበት ብሄር ወይ አከባቢ ወይ በሚናገረው ቋንቋ መሰረት አይደለም። ስልጣን ለመያዝ ወይ ስራ ለማግኘት ኢትዮጵያዊ ዜጋ መሆኑ ብቻ በቂ ነው። ከሌላው ጋር በትምህርት ደረጃው፣ በብቃቱ ወዘተ ይወዳደራል። ምክንያቱም ሁላችን እኩል ነን። ለሁሉም ነገር እኩል ዕድል ይኖረናል። የካቲት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከታህሳስ ወር 2006 ዓም ጀምሮ በመዲናዋ ሌሊት የሚጻፉ የተቃውሞ ጽሁፎችን ማየት የተለመደ እየሆነ መምጣቱን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ትናንት ሌሊት በአስኮ መስመር ጀኔራል ዊንጌት ከሚገኘው አደባባይ ጀምሮ አወሊያ፣ካኦጄጄ፣ አስኮ የሚወስደውን ዋና መንገዱን በመሃል በሚከፍለው እስከ 2.5 ሜትር ቁመት ባለው ግድግዳ ላይ የሙስሊሙን የመብት ጥያቄና የትግል ቀጣይነት የሚያንፀባርቁ ጽሁፎች በተለያዩ ቀለማት ተጽፈው ዛሬ ህዝብ ሲያነባቸው ታይቷል። በአዲስ አበባ ጦር ሀይሎች፣ ወይራ ሠፈር ፣ አዉጉሥታ፣ቤቴል እና ሌሎችም አከባቢዎች ተመሳሳይ መልእክቶችን ያዘሉ ጽሁፎች ተለጥፈው ማደራቸውን ለማወቅ ተችሎአል፡፡ የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፍተኛ የግብርና ምርት እንደተገኘ በመንግስት የመገናኛ ብዙሀን በሚገለጽበት በአሁኑ ወቅት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ካላገኙ ህይወታቸው አደጋ ላይ እንደሚወድቅ መረጃዎች አመልከተዋል። የዓለም ባንክ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በመግብ ለስራ የታቀፉ ዜጎችን ሳይጨምር ከ3 ሚሎዮን ያላነሱ ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። በምስራቅ አማራ፣ በደቡብ ምስራቅ ትግራይ፣ በአፋር እና ኦሮምያ የተከሰተውን ረሀብ ለማስታገስ ከ400 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ እርዳታ ያስፈልጋል። የአለማቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ አነስተኛ በሆነበት ሁኔታ በዚህ አመት ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ ጉዳት ሊደርስ እንደሚችል ነው ባለሙያዎች ያስጠነቀቁት። የኢትዮጵያ መንግስት ለፖለቲካ ፍጆታ በሚል በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተውን ረሀብ በመደበቅ ላይ ነው ያሉት ወገኖች፣ በረሀብ የተጎዱት ዜጎች ትክክለኛ አሀዝ ከተጠቀሰው ቁጥር በእጅጉ እንደሚልቅ እየተናገሩነው። ኤን ቢ ሲ በቅርቡ ባወጣው ዘገባ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያን የሞት ደመና እንዳንዣበበባቸው ገልጿል። ከ20 አመት በፊት አቶ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ህዝብ በቀን ሶስት ጊዜ ሲበላ ማየት እንደሚፈልጉ ፣ ከ3 አመት በፊት ደግሞ ኢትዮጵያን በአምስት አመታት ውስጥ በምግብ ራሱን ለማስቻል እቅድ መታቀዱ ተገልጾ ነበር። አሁን ያሉት መረጃዎች እንደሚያመለክትቱት ከ23 አመታት የውጭ እርዳታ በሁዋላ አገሪቱ ቀጣይ አመታትንም ከእርዳታ ስንዴ አትላቀቅም። ጥር ፳፮ (ሃያ ስድት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ለማዎቅ እንደተቻለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚታየውን የመኖሪያ ቤቶች ችግር በዘላቂነት ለማቃለል በሚል ከዚህ በፊት ከነበረው የ 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤት ልማት ፕሮግራም በተጨማሪ በአማራጭ የ 10/90 አነስተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እና ለመለስተኛና መካከለኛ ገቢ ላላቸው በ40/60 የቁጠባ ቤት ፕሮግራም መቅረጹን ተከትሎ እስከ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ተመዝግቦ ነበር። ይሁን እንጅ በአሁኑ ወቅት እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው የተለያዩ የቤት ልማት ፕሮግራም ተሳታፊ ዜጎች ከፕሮግራሙ እየወጡ መሆኑ ታውቋል። ይህን ዜና እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ከ30 ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ገንዘባቸውን ከባንክ አውጥተዋል። ባንክ ቤቶች ከዚህ በፊት ለምዝገባ ስራ ሲጨናነቁ ከነበረው ባልተናነሰ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ የስራ ጫና ውስጥ እንዳሉና ለዚህ አገልግሎት ብቻ አንድ መስኮት ለመልቀቅ እንደተገደዱ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የ20 /80፣ የ10/90 እና የ40/60 ቤቶችን ለመገንባት ከገንዘብ እጥረት በተጨማሪ የቦታ እጥረት ማጋጠሙን ኢሳት የውስጥ መረጃዎችን በማሰባሰብ መዘገቡ ይታወሳል። በተለይም የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ ከተሞችን በአዲስ አበባ ታላቁ ካርታ ውስጥ ለማስገባት ፈቃደኛ ሆኖ ባለመገኘቱ የፕሮጀክቱ ተፈጻሚነት አደጋ ውስጥ ወድቋል። መንግስት ወደ 10 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከባንክ በመበደር ቤቶችን ለመስራት ቢያስብም፣ ንግድ ባንክ በርካታ የብድር አገልግሎቶችን በመሰረዝ ለማግኘት የቻለው 6 ቢሊዮን ብር ነው። መንግስት በተለይ 40 በ60ን ተግባራዊ ለማድረግ ያወጣው እቅድ ቅጅው ለኢሳት ደርሶአል። በዚህ እስካሁን ይፋ ባልተደረገው እቅድ የቤቶች ዋጋ ቀድሞ ከተያዘለት በእጥፍ ጨምሮ በግል ከሚሰሩ ቤቶችም ጋር ሲነጻጸር እጅግ ውድ ሆኖ ተግኝቷል። ጥር ፳፮ (ሃያ ስድት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግጭቱ የተከሰተው ባለፈው ሳምንት ሲሆን፣ ለግጭቱ መነሻ የሆነውም ኮንሶዎች ባጋጠማቸው የመሬት እጥረት ሳቢያ ወደ ቦዲዮች አካባቢ ሄደው በመስፈራቸው መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ይገልጻሉ። ከዚህ በፊት ሁለቱ ብሄረሰቦች በተደጋጋሚ ሲጋጩ ቆይተዋል። ቀደም ሲል መንግስት የኮንሶ ሰፋሪዎችን ወደ ቦዴ አካባቢ በመውሰድ ማስፈሩ በአካባቢው ለሚታየው ችግር መንስኤ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ የፌደራል ፖሊስ ገብቶ አካባቢውን ተቆጣጥሮታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በጅንካ መብራት ለረጅም ጊዜ በመቋረጡ ህብረተሰቡ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጧል። የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት በአራት ቀናት አንድ ጊዜ የሚመጣው መብራት፣ ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር ዳርጓቸዋል። ይህ የያዝነው ወርሓ ለካቲት “የህወሓት ልደት የትግራይ ህዝብ ልደት ነው፣ ህወሓት ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ነው፣ የትግራይ ህዝብ ታሪክ ከደደቢት ይጀምራል፣ የህወሓት አላማና ፍላጎት የትግራይ ህዝብ አላማና ፍላጎት ነው፣ የትግራይ ህዝብ ከህወሓት ሌላ አማራጭ የለውም ዙሪያው ሁሉ ገደል ወይም ጠላት ነው፣ በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ህልውና ከህወሓት ህልውና ጋር የተቆራኘና ድርጅቱ ስልጣን ላይ ሲኖር ትግራይም የምትኖር ድርጅቱ ከጠፋ ወይም ስልጣን ላይ ከሌለ ደግሞ የትግራይ ህዝብም አብሮ የሚጠፋ ነው”……..እያሉ በመስበክ በሰማእታት መቃብር ላይ ቆሞው የውሸት ድራማ የሚሰሩበት፣ በትግራይ ህዝብ ደምና አንጡራ ሃብት ላይ የሚነግዱበት፣ በድምሩ “ጆሮውን ቆርጠው የሰጡት ውሻ ሥጋ የሰጡት ይመስለዋል” እንዲሉ የትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክብሩ፣ ዳር ድንበሩንና ብሄራዊ ጥቅሙን ለባዕድ ሽጠው ሲያበቁ ነፃ አውጥተናሃል!! ልማት አምጥተንልሃል!! እያሉ የሚዘምሩበትና የሚመፃደቁበት የካቲት 11 በዓል እየመጣ ነው። ይህ ዓይነቱ ጭፍን ፕሮፓጋንዳ መርዝ ደግሞ ዛሬ የመጣ ባህል አይደለም። ህወሓት ከተፈጠረበት ቀን አንስቶ እስካሁን ድረስ ለአርባ ዓመታት ያህል ለጀሮ እስከሚሰለች ድረስ በካድሬዎቹ አማካይነት ነጋ ጠባ በዚያች በተቀደሰች ምድር ትግራይ በአሁኑ በሃያ አንደኛ ክፍለ ዘመን የሚሰበክ የደደቢት የአደንቁረህ ግዛ ፍልስፍና መሆኑን ተራ የገጠር እረኛም ሳይቀር ያውቀዋል። ይሁን እንጂ ህወሓት ከድርጅትነት ወደ ቡድናዊ አምባ ገነንነት፣ በኋላም ከቡድናዊ አገዛዝ ወደ ፍፁም የቤተሰባዊ መዝርፊያና የማፈኛ የግል ኩባንያ ሆኖ ከተሸጋገረ ወዲህ እኖሆ ዓሰርቱ ዓመታት አስቆጥሯል። በመጨረሻም “ጊዜ ዳኛ ታሪክ ምስክሩ ነውና” ድርጅቱ ከባለቤቱ ከቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ጋር አብሮ ግብኣተ መሬት ገብቷል። ላይመለስ አብሮ ተቀብሯል። አሁን ያለው “በድርቆሽ የተሞላ ህይወት የሌለው የቆዳ ግሳንግስ ወደ(ዓርሲ)” ተለውጦ ባንድ በኩል በአቶ ስብሓት ነጋ የ80 ዓመት ጎበዝ አለቃ የሚመራ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኤርትራውያን የሚገፋ አሮጌ ጋሪና በወታደር የሚጠበቅ የደረቀ ሬሳ ሆኖ ቀርቷል” የሚሉ ብዙዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ናቸው። ይህ ምን ያህል እውነትነት አለው? አንድ የፓለቲካ ድርጅት ሞቷል ወይም ህይወት የለዉም ሲባልስ ምን ሲሆን ነው? ህወሓት ከበረሃ ጀግንነት ወደ ዱር አራዊትነት የተቀየረበት ጊዜስ መቼ ነው? እውነት የጥቂት ወሮ-በላና ከሃዲ መሪዎች በረሃ የገቡበትን ቀን የታላቁ የትግራይ ህዝብ ልደት ነውን? የትግራይ ህዝብ ከሌላው ሰማንያ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ህዝብ ምን የተለየ ጥቅም ስላገኘ ነው የአንድ መርሲነሪ የፓለቲካ ድርጅት ልደት የህዝቡን ብሄራዊ በዓል ተደርጎ የሚያከብረው? ለመሆኑ የትግላችን ውጤት ነው እየተባለ የሚነገርለት ሕገ መንግስት እውነት ለትግራይ ህዝብ ይመለከተዋልን? የሚሉና ሌሎች ተዛማጅ ጥያቄዎችን እንድንመልስ ግድ ይለናል። ወደ ዋናው የጥያቄው መልስና አርእስተ ጉዳይ ከመግባቴ በፊት ግን ለአንባቢዎቼና ለነፃ ሚዲያ ደንበኞቼ በአክብሮት የምጠይቀው በዚሁ ፅሑፍ ዙሪያ በመቃወምም ሆነ በመደገፍ ከቂም በቀል፣ ከስሜታዊ አስተሳሰብ፣ ከጭፍን ደጋፊነት፣ በአጠቃላይ የግለ ስብእና፣ የሃሳብ ነፃነትና ሰብኣዊ መብት በማይጋፋ መልኩ በዋናው ጉዳይ ላይ ያተኰረ ክርክር ወይም ሃሳብ ቢያቀርቡ ለመማማርና በቂ መልስ ለመስጠት ዝግጁ መሆኔን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለፅ እወዳለሁ። ፍርሃትን አስወግዶ የህሊና ባርነትን ሰብሮ በመውጣት የሀገርና የህዝብ ወገን ሆኖ መከራከር፣ ለሃቅ መመስከርና በፅናት መቆም ምንኛ ያኰራል!!! በዘመነ መሳፍንት አንዲት የጎጃም አልቃሽ ““ጎጃሜ ቡዳ ነው ቡዳ ነው ስትሉ ስትሉ አላየህም ወይ ትግሬ እርስ በርስ ሲባሉ” ብላ ተናግራለች” በማለት ከዛሬ አስራ አንድ ዓመት በፊት የህወሓት አመራር ለሁለት ተሰንጥቆ ሲፈረካከስ ያዩ አንድ አዛውንት ያለፉትን የትግራይ ባላባቶችና መሳፍንቶች ታሪክ ከህወሓት ታሪክ ጋር በማነፃፀር እንደዋዛ አጫውተውኝ እንደነበር አስታውሳለሁ። በሌላ መልኩ ደግሞ ስለ ህዝቡ ጀግንነት፣ ጨዋነት፣ ታጋሽነትና አትንኩኝ ባይነት እያስታወሱ የዛሬው ትውልድ ግን ሐሙት የፈሰሰ እንዲሁ ወኔው ተኰላሽቶ መቅረቱ በጣም ያሳዘናቸው መሆኑን በቁጭት ገልፀውልኛል። ነገር ግን በወቅቱ የነገሩኝን ሁሉ ብዙም ልብ አላልኩትም ነበር። በኋላ ግን ስለ ህወሓት የተፃፉ መፃሕፍቶች በተለይም የቀድሞ የህወሓት ታጋይና አታጋይ የነበሩት አቶ አስገደ ገብረ ስላሴ የፃፉትን ጋህዲ በሚል ሶስት ተከታታይ መፃሕፍቶችን ሳነብ “ማየት ማመን ነውና” የትግሉ ባለቤትና የድርጅቱን መስራች የነበሩት ሰዎች እንኳን ሳይቀር የመሰከሩለት ህወሓት ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ተግባሩ ሲመረመር ከላይ አዛውንቱ የነገሩኝ አባባል በትክክል የሚገልፅ መሆኑን ለመረዳት ችያለሁ። “የህወሓት ታሪክ የርስ በርስ መላላት፣ ህዝብ ለህዝብ የማናቆርና ሀገርን የማፍረስ ታሪክ ነው” ቢባል ከእውነት የራቀ አይደለም። ይህን በሚመለከት ዝርዝሩን ለታሪክ ፃፊዎች ትቼ አንድ ሁለት አብነቶችን ብቻ ልጥቀስ። ህወሓት ከትጥቁ ትግል ዘመን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለ40 ዓመታት ያህል የዘለቀው አንድ ገዢ መፈክር ነበረው። እሱም “ የቻለ ይሩጥ!! ያልቻለ ያዝግም!! ያበቃለት ይለይለት!!? በትግርኛ (ዝኻኣለ ይጉየ! ዘይካኣለ ይሳለ! ዘብቀዐ ይታኣለ) የሚል ነው። ከመፈክሩም ጎን ለጎን በድርጅቱ የኪነት ቡድን የተሰራ ከአቶ መለስ መልክ ጋር የሚመሳሰል ፊት ለፊቱ ደግሞ ጣቱን ወደ ሰዎች ቀስሮ የሚያስፈራራ ሥዕል በየስብሰባውና ታጋዮች ባሉበት ሁሉ የሚለጠፍ ነበር። ስዕሉ በጋሃድ በአደባባይ መውጣት የጀመረው ደግሞ ልክ እነ ዶ/ር አረጋዊ በርሄና አቶ ግደይ ዘርኣፅዮን ከድርጅቱ ተለይተው ከወጡ በኋላና “ማርክሰ ሌኒስት ሊግ ትግራይ (ማሌሊት)” ከተመሰረተ አንድ ዓመት ባልሞላ ውስጥ ነበር። ስዕሉ ያልተለመደ ነገር ስለነበረ ብዙ ታጋዮችን በተለይም ያልተማሩ የገበሬ ልጆች የሆኑትን ታጋዮች ግራ አጋብቷል። አንዳንድ ቦታም ሌሊት በሳንጃ እየቀደዱ ይጥሉት ነበር። ከጊዜ በኋላ ግን ስዕሉ ተለመደ። የሚገርመው ግን በወቅቱ የድርጅቱን የኪነ ጥበብ አባል ሆኖ ስዕሉን ያቀነባበረ ሳኣሊውንም ጭምር ከጥቂት ወራት በኋላ ድርጅቱን ለቆ በመውጣት ዛሬ በስደት ዓለም በህወይት ይገኛል። ስሙን ያልጠቀስኩበት ምክንያት ደግሞ የሱ ፍቃደኝነት መጠየቅ ስላለብኝ ነው። የመፈክሩ ዋና አላማና ስትራተጂም የሚከተሉትን ሶስት ዋና ዋና ነገሮችን ያቀፈ ነው፡- 1. አንደኛ የአቶ መለስ ዜናዊና የአቶ ስብሓት ነጋ ቡድን ተቀናቃኝ ወይሞ ሞጎደኛ ተብለው የሚጠረጠሩትን ያመራር አባላት፣ ምሁራንና የጦሩ አለቆችን (ይህችን ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም) በማለት ቀስ በቀስ የማፅዳት ስልትና ስትራተጂ ነው። ይህንንም ሰሞኑን በኢትዮ- ሚዲያ ድሕረ ገፅ የወጣውን የነ ሙሴ፣ ዶ/ር አታክልት፣ ገሰሰው አየለን ጨምሮ ተኩሉ ሃዋዝ፣ መለስ ካሕሳይ፣ ዶ/ር አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርኣፅዮንና ሌሎች በሽዎች የሚቆጠሩት የድርጅቱን ከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አባላትን ያካትታል። 2. ሁለተኛው የመፈክሩ አላማና ስትራተጂ የትግራይ ብሄረተኝነትንና ብሎም የኢትዮጵያዊነት ስሜትን ከትግራይ ምድርና ከህዝቡ አስተሳሰብ ከስረ መሰረቱ በመፋቅና በማጥፋት በምትኩ በትግራይ ብሎም በሀገራችን የኤርትራ ሻዕቢያዊ አመለካከት የበላይነት እንዲይዝ ማረጋገጥ ነው። በዚሁ ዙሪያ በቅድሚያ የተመቱት የድሮ አስተሳሰብ፣ ሀገራዊ ስሜትና እንዲሁም በኤርትራ ጉዳይና በአገር አንድነት ጉዳይ ላይ የከረረ አመለካከት አላቸው ተብለው የሚገመቱትን ባላባቶችንና የሀገር አዛውንቶችን ናቸው። ቀጥሎም የተመቱት የትግራይ መሁራኖች ናቸው። በኤርትራና በሀገር ጉዳይ ዙሪያ የሚከራከሩና ጥያቄ የሚያነሱ ምሁራን እንደ ኤለክትሪክ ይፈሩዋቸው ነበር። በዚህ መሰረት “ሽዋውያን ተጋሩ” የሚል የቅፅል ስም መለጥፍ ብቻ ሳይሆን በዘፈንም ሳይቀር ቅስማቸው እንዲሰበርና አንገታቸው እንዲደፉ ተደርጓል። በዚህ ምክንያት የቻሉትን ከድርጅቱ ሸሽተው እንዲያመልጡ ያልቻሉት ደግሞ ለእስርና ለግድያ ተዳርጓል። በዚህ ምክንያት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ የትግራይ ምሁራን ዛሬም ስለህዝባቸውና ሀገራቸው ጉዳይ ደፍረው ጥያቄ እንዳያነሱ ፍርሃት እንደ ወባ ዛሬ በአረና ትግራይ አባላትና ደጋፊዎቻቸው እየደረሰ ያለው ዱላም ከዚሁ የተለየ አይደለም። ለአንድ የአረና አባል ከአምስት በላይ ሰላዮች በመመደብ ኮቲያቸውን እየተከተሉ መውጫና መግቢያ ያሳጧቸዋል። ዛሬ ትግራይ ለነ ስብሓት ነጋና ሌሎች መሪዎች ታማኝ የሆኑትን የኤርትራ ተቃዋሚ ነን የሚሉ ድርጅቶች በነፃነትና በልበ ሙሉነት የሚንቀሳቀሱባት በአንፃሩ ከህዝቡ አብራክ የተፈጠሩ ለነ አረና ትግራይና ሌሎች ሀገር በቀል ድርጅቶች ግን በገዛ ሀገራቸው ተሸማቅቀውና በአደባባይ በዱላ እየተመቱ የሚኖሩባት ምድራዊ ሲኦል ሆና ትገኛለች። በመሆኑም ዛሬ ሰፊው የትግራይ ህዝብ ባንድ በኩል የትግራይ ሻዕቢያ በሌላ በኩል ደግሞ የኤርትራ ሻዕቢያ አጣብቅኝ ውስጥ ገብቶ በሁለት አለንጋ እየተገረፈ የሚገኝ ህዝብ ሆኗል። ታዲያ!! ለዘህ ሚስኪን ህዝብ አለሁልህ የሚል ወገን ማን ይሆን? 3. ሶስተኛው የመፈክሩ አላማና ስትራተጂ በህዝቡ የስነ ልቦናና የአካል ጥቃት በማድረስ በተለይም በትግራይ ምድር ፍርሃት፣ ሽብር፣ ጥርጣሬና ህወከት በማንገስና የህዝቡን ሁለንትናዊ አስተሳሰብ በመቆጣጠርና በማደንዘዝ ፀጥ ረጭ ብሎ እንዲገዛና ለጥቂት መሪዎች ዘላለማዊ ስልጣን አገልጋይ ሆኖ እንዲኖር ለማድረግ ነው። በሌላ አነጋገር ትግራይ ወፍ እንኳን ዞር የማይልባት፣ ሌላው ኢትዮጵያዊ በትግራይ ህዝብ ጉዳይ ላይ እንደማያገባው ተደርጎ መፈናፈኛ በማሳጣት በስመ ልማት እንደፈለጉ የሚግጥዋት የህወሓት የጓሮ አትክልት ሆና እንድትኖር ለማድረግ ነው። ልበ በሉ!! የትግራይ ህዝብ በጦርነት የደቀቀ ህዝብ ነው። ትግራይ ደርግ፣ ኢዲዩ፣ ጀብሃ፣ ሻዕቢያ፣ ኢሕአፓ፣ ህወሓትና ሌሎች ብረት ያነገቡ ሀይሎች የሚንቀሳቀሱባት ለአስራ ሰባት ዓመታት ያህል የጦርነት አውድማ ሆና ቆይታለች። ዛሬም ህዝቡ ከጥይት ጭኾት አልተላቀቀም። በኤርትራና በኢትዮጵያ በሁለቱም ሀገሮች ድንበር ከሩብ ሚሊዮን በላይ ሰራዊት በመሸገበትና በተፋጠጠበት የጦርነት ደመና ስር ሆኖ ዛሬ ነገ ውጊያ ይጀመራል እያለ በፍርሃት ተውጦ የሚገኝ ህዝብ ነው። በዚህም ላይ በየጊዜው ከያሉበት በታጣቂዎች እየታፈኑ ወደ ኤርትራ ተወስደው ደብዛቸው የማይታወቁ ንፁኃን ዜጎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። በዚሁ ፍርሃት ቀያቸውንና ቤታቸውን እየለቀቁ ወደ ዓረብ ዓለም የሚሻገሩና ወደ ማሀል ሀገር በመሸሽ የኢትዮጵያ ዋና ዋና ከተሞችን በልመና ያጥለቀለቁት የየተኛው አካባቢ እንደሆኑ ማንም ኢትዮጵያዊ ያውቃል። እነዚህ ግጭቶችም እንደ ፓለቲካ መሳሪያና ማስፈራሪያ እየተጠቀሙ “እኛ ከሌለን ያ ሁሉ ጠላት ይመለሳል፣ ሻዕቢያ ተመልሶ ይውጥሃል፣ ኦነግና ትምክሕተኞች ቂማቸው ይወጡቡሃል፣ የሽብርተኞች ዒላማ ትሆናለህ፣ በትግራይ የተተከሉ ፋብሪካዎች ተነቅለው ወደ ማሃል ሀገር ይወሰዳሉ፣ በትግልህ የቀበርካቸው ጠላቶች ከመቃብር ተነስተው ይመጣሉ፣ ወዘተ እያሉ ነጋ ጠባ ህዝቡን ማሸበርና ማደንቆር የተካኑበት ዋነኛ የአገዛዝ ጥበባቸው ሆኖ ይገኛል። ወንድሞቼ ሆይ!! ታዲያ እንዲህ ዓይነቱ የቆሸሸ ታሪክ ያለው ድርጅት ዛሬ በትግራይ ህዝብና በተለይም በአረና አባላትና ደጋፊዎቻቸው ላይ የአራዊት ስራ ቢሰራ የሚያስገርም አይደለም። ህዝብን ሁሉ ጊዜ ማታለል የማይቻል መሆኑን ያልገባቸውና ጊዜውም ጥሏቸው እየሄደ መሆኑንም የማይቀበሉ እንደ ሾላ ፍሬ ውስጣቸው የበሰበሱ መሪዎች እስከ ህልፈተ ቀናቸው ድረስ “የደንቆ ልቅሶ መልሶ መላልሶ” እንዲሉ ዛሬም የሚናገሩት ቋንቋና የሚሰሩት ስራ ያው በጫካ የለመዱት ዓይነት ነው። ከላይ የተጠቀሰው የመፈክራቸው አላማና ስትራተጂም በትክክል ሲተረጎም “እምቢ ያለ ሰው ጥይት አጉርሰው” ከሚለው የደርግ ስርዓት መፈክርና ተግባር ጋር አንድ ዓይነት መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ይስቷል ብዬ አልገምትም። የሚያሳዝነውና የሚያስገርመው ነገር ግን ትግራይን የጥፋትና የመከራ ሞዴል በማድረግ የሚፈፅሙትን ጉድ እንደ ኤይድስ ወረርሽኝ በሽታ ወደ ሌሎቹ ክፍላተ ሀገራትም እየተዛመተ መምጣቱ ነው። በዚሁ ነጥብ ዙሪያ በቀጣዩ ፅሑፌ ተመልሼ እመጣለሁ። ቸር ሰንብቱ። ሰሞኑን አገር ጥለው መኮብለላቸው የተደመጠው የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦሞት ኦባንግ በተለያዩ የዓለም ዓቀፍ ተቋማት ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆነ ታወቀ። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ፍትህ የተዛባባቸው ዜጎች ሁሉ መረጃ በማሰባሰብና ለድርጅታቸው በመላክ የዜግነት የቤት ስራቸውን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ኦሞትን ፍትህ ደጅ ለማቆም ከ19 ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በኅብረት እየሰሩ መሆናቸውም አመልክተዋል። በሌላም በኩል ኢህአዴግም “ነገር ሳይበላሽ” እያደናቸው እንደሆነ ተሰምቷል፡፡ በ2003 በጅምላ ለተጨፈጨፉና በሺህ ለሚቆጠሩ የአኙዋክ ተወላጆች መሰደድ ከመለስ ቀጥሎ ግንባር ቀደም ተጠያቂ የሚባሉት አቶ ኦሞት፤ ሳምንት በፈጀ ግምገማ ከክልሉ ሊቀመንበርነታቸው መነሳታቸውና የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዲኤታ ሆነው መመደባቸው ይታወሳል። “እውነተኛው ወያኔ” እየተባሉ የሚጠሩት አቶ ኦሞት ምንም እንኳ በሚኒስትርነት ደረጃ ቢመደቡም በሙስና ተወንጅለው እንደሚታሰሩ ጎልጉል ምንጮቹን ጠቅሶ መዘገቡ አይዘነጋም። በሰኔ 10፤2005 ዓም (june 17, 2013) የጎልጉል ዘገባ ላይ እንደተጠቀሰው ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውን፣ እንዲሁም በክልሉ የሚፈጸሙትን የተጭበረበሩ የበጀት አፈጻጸሞችንና ምዝበራዎችን የሚያጋልጡ ሰነዶችን በሚስጥር ተደራጅቶ ለኢህአዴግ የድርጅት ቢሮ ቀርቦ ነበር። የክልሉ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኢሬሳ ከፍተኛ ምስጢር ያላቸውን ሰነዶች በመያዝ ከመታሰራቸው በፊት መሰወራቸውን የጠቆመው ዘገባ “የቢሮ ሃላፊው ይዘው የተሰወሩት መረጃ አቶ ኦሞት የፈረሙባቸው ከፍተኛ የገንዘብ ሰነዶችና ሙስና የተከናወነባቸው የኮንስትራክሽንና የተለያዩ መረጃዎች ይፋ የሚያደርጉ ነበሩ። በወቅቱ “መረጃዎቹ አንድ ቀን ህዝብ ፍርዱን ይሰጥ ዘንድ ይፋ ይሆናሉ” ተብሎም ነበር። የመረጃ ምንጫቸውን ባይጠቅሱም አቶ ኦባንግ “ኦሞትን በተመለከተ ከበቂ በላይ መረጃ አለን፤ ህግ ፊት እናቀርበዋለን፤ በንጹን ደም ተጨማልቆና ህዝብ ላይ ግፍ ፈጽሞ መሰወር አይቻልም” በማለት በስልክ ለጎልጉል ተናግረዋል። አቶ ተስፋዬ ኢሬሳ በድንገት ምሳ እየተመገቡ ከመርዝ ጋር በተያያዘ ህይወታቸው በድንገት ማለፉ ይታወሳል። ከታህሳስ 23 ቀን 2004 ዓ ም ጀምሮ ሟቹ አቶ መለስ በላኳቸው አስገምጋሚዎች ለሳምንት በተካሄደ አውጫጪኝ አቶ ኦሞት “የአኙዋክ ተወላጆችን አስጨፍጭፈሃል” የሚል መነሻውና ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር። በወቅቱ ግምገማው ላይ የነበሩ እንዳሉት አቶ ኦሞት “እኔ በዚህ ጉዳይ ተጠያቂ ከሆንኩ መሳሪያና ወታደር የሰጠኝ መለስም ይታሰራል” በማለት መልስ ሰጥተው ነበር። በወቅቱ አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመሩት ድርጅት /አኢጋን/ አቶ መለስን በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ችሎት ተጠያቂ ለማድረግ ያቀረበው ማመልከቻ ተቀባይነት ያገኘበትና አቶ መለስ ላይ ክስ እንዲመሰረት ውሳኔ የተደረሰበት ዜና የተሰማበት ነበር። ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የጋምቤላ ምንጮች “አቶ መለስ አቶ ኦሞትን በጭፍጨፋው ተጠያቂ በማድረግና ርምጃ በመውሰድ ራሳቸውን ጲላጦስ ለማድረግ የወጠኑት አካሄድ እንደሆነ የፌዴራል ሰዎች ነግረውናል። ኦሞትም በሙስና በዘረጋው መዋቅር እስከላይ ድረስ ዘመድና ተቆርቋሪ ስላበጀ መረጃው ደርሶት ነበር” ብለዋል። /በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የተመሰረተው ክስ መለስ ቢሞቱም እስካሁን ክፍት ነው/ በሌላም በኩል ወቅቱ በክልሉ ኢህአዴግ ለልማት በሚሰጠው ርዳታ ዜጎችን ለማፈንና ረግጦ ለመግዛት የሚያስችለውን ሃይል ያደራጅበታል በሚል ተቆርቋሪዎች መረጃ አስደግፈው ባቀረቡት ክስ ዓለም ባንክ አጣሪ የላከበት ነበር። ከዚሁ ጋር ተያይዞ መሬታቸውን፣ የትውልድ ቀያቸውን በአንጋቾች የተነጠቁ ምስኪን ዜጎች ድምጽ ዓለም አቀፍ ትኩረት አግኝቶ ኢህአዴግን ክፉኛ የተፈታተነበት ነበር። ለዚህ ይመስላል ኢህአዴግ በግምገማ በርካታ የክልሉን ሃላፊዎች ወረዳ ድረስ በመዝለቅ በሙስና ሰበብ ሲያባርርና ሲያስር፣ አቶ ኦሞትን ወደ ፌዴራል በማዛወር በቅርብ ይከታተላቸው ነበር። አቶ ኦሞት ወደ ፌዴራል ሲዛወሩ “የቤንሻንጉል ጉምዝ ፕሬዚዳንት በነበሩት አቶ ያረጋል አይሸሹ ላይ የተደረገው ይፈጸምባቸዋል” ተብሎ አስቀድሞ ተተንብዮ ነበር። ለአብነት ከላይ በተዘረዘሩት መነሻዎችና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ሳቢያ የአቶ ኦሞትና የህወሃት ግንኙነት ማክተሙን የሚናገሩት ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ክፍሎች፣ “ቀደም ሲል ህወሃትን ሲያገለግሉ ኖረው መጨረሻቸው እስር እንደሆነው አራት የቀድሞ የክልሉ መሪዎች፣ ወይም እንደ አምስተኛው ፕሬዚዳንት አቶ ኦኬሎ አኳይ ስደት እጣ ፈንታቸው ይሆናል” የሚል ቅድመ ትንበያ ነበር። አቶ ኦኬሎ አኳይ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ የተፈጸመውን የጅምላ ጭፍጨፋ አስመልክቶ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ክልሉን ወክለው የተዛባ መረጃ እንዲሰጡ ታዘው ነበር። በአቶ አባይ ጸሃዬና ገብረአብ በርናባስ መመሪያ መሰረት ግጭቱ በጎሳ ላይ የተመረኮዘ የርስ በርስ እንደሆነ፣ በግጭቱ 59 ሰዎች ብቻ ሲሞቱ አንድ ቤት መቃጠሉን እንዲናገሩ የተሰጣቸውን መመሪያ ያልተቀበሉት አቶ ኦኬሎ ህይወታቸው አደጋ ላይ በመውደቁ አገር ጥለው መሰደዳቸው ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ በተደጋጋሚ ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ አቶ ኦኬሎ አኳይ በስደት ሆነው በይፋ በዚህ ጉዳይ መግለጫ ለመስጠት አለመድፈራቸው ብዙዎችን ግራ ያጋባ ጉዳይ ሆኗል። አቶ ኦሞት የክልሉ የደህንነት ሃላፊና ፖሊስ ኮሚሽነር ሆነው ባገለገሉበት ወቅት ፍጹም ታማኝ ስለነበሩ በ2005 የተሰጣቸው የክልል መሪነት ስልጣን ለህወሃት ለሰሩት ውለታ የተከፈለ ወሮታ እንደሆነ ተደርጎ ነው የሚወሰደው። በዚሁ መነሻ ይመስላል አብዛኛው የጋምቤላ ተወላጆች ለአቶ ኦሞት የከፋ ጥላቻ እንደነበራቸው የሚናገሩ ክልሉ ተወላጆች፣ ኦሞት ከአገር ኮበለሉ መባሉ አያስገርማቸውም። አሁን ጥያቄው ኦሞት ከኢህአዴግ አፍንጫ ስር እንዴት አመለጡ? አሁን የት ናቸው? መጪው እጣ ፈንታቸውስ? የሚለው ነው። አዲስ አድማስ ባለፈው ቅዳሜ እትሙ አቶ ኦሞትን የግምባር ዜና አድርጎ ሲያቀርብ አገር ጥለው መኮብለላቸውን የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ማረጋገጣቸውን አስነብቧል። አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል እንደገለጹት አቶ ኦሞት ከሁለት ወር በፊት ለስልጠና አውሮፓ ሲመጡ በነበራቸው ቪዛ ከሁለት ሳምንት በፊት ዓርብ ቀን አገር ጥለው እንደወጡ መረጃው አላቸው። ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ከ19 የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ እየሰሩ መሆናቸውን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ ሜቶ “ኦሞት መለስ በህይወት እያለ ቢኮበልል መልካም ነበር። አሁን ከኦሞት የምንፈልገው ችሎት ፊት በወገኖቹ ላይና በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ፣ ቶርቸር፣ እስር፣ ዝርፊያ፣ የመሬት ንጥቂያ፣ ወዘተ አስመልክቶ እንዲናዘዝ ነው” ብለዋል። ኮብላዩ አቶ ኦሞት የት እንደሚገኙ ተጠይቀው “አሁን እዚህ ነው የሚባልበት ደረጃ ላይ አይደለንም። ግን መሰወር የሚችል አይመስለኝም። በደም ተጨማልቆ በስደት ተበዳይ መስሎ መኖር አይቻልም። የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ከመለስ ጋር በተመሰረተው ክስ ላይ ኦሞት የተካተተ መሆኑ መዘንጋት የለበትም። እኛ እንኳ ዝም ብንል ፍትህ በርዋን አትዘጋም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ጎልጉል ባሰባሰበው መረጃ አቶ ኦሞት አገር ጥለው የወጡት ከሁለት ሳምንት በፊት ሲሆን አንድ ሳምንት ቢዘገዩ ኖሮ እስር ቤት ይገቡ ነበር። አስቀድሞ በደረሳቸው መረጃ መሰረት አቶ ኦሞትን እስር ቤት እንዲወረወሩ የሚያዘው የአስር ማዘዣ የሚቆረጥበት ግምገማ ተዘጋጅቶ ነበር። እሳቸው አስቀድመው አገር ጥለው በመውጣታቸው ግምገማው ተስተጓጉሏል። ግምገማው የዓለም ባንክ አጣሪ ቡድን በትላንትናው ዕለት ኢትዮጵያ ሲገባ በሙስናና በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ ኢህአዴግ ርምጃ በመውሰድ ዝግጅት አጠናቆ ለመጠበቅ የሚረዳው ነበር። ግን አልሆነም። በጋምቤላ በኢቨስትመንት ስም መሬት ወስደው ከሚሰሩት መካከል 70 ከመቶ የሚሆኑት የቀድሞ የህወሃት ታጋዮችና የትግራይ ተወላጆች መሆናቸው አቶ ኦሞት የሚደረግባቸውን ክትትል አልፈው አገር ሊወጡ እንደቻሉ ግምት አለ። አሁን “ባለሃብት” የሚባሉት እነዚህ ክፍሎች ባላቸው መዋቅር ሳቢያ አቶ ኦሞትን ሊታደጓቸው እንደሚችሉ ከግምት በላይ የሚናገሩ አሉ። አቶ ኦሞት ሆላንድ ገብተዋል የሚሉም አሉ። በሌላ በኩል ደግሞ አውሮፓ ሊገቡ አይችሉም በማለት ግምቱን የሚያጣጥሉ አሉ። እነዚህ ክፍሎች ወደ ማሌዢያ ሄደዋል የሚለውን ምንጭ ይደግፋሉ። በስፋት እንደሚነገረው ከሆነ አቶ ኦሞት ኤዢያ እንደሚሄዱ የሚያጠናክሩ ምልክቶች አሉ። አብዛኛው የኢህአዴግ ባለስልጣኖች በማሌዢያ ባንኮች ገንዘብ አላቸው። አቶ ኦሞትም በተመሳሳይ የማሌዢያ ባንክ ተጠቃሚ ናቸው ተብሎ እንደሚገመት የሚቀርቧቸው ይናገራሉ። በተመሳሳይ በኢንቨስትመንት ስም የተወዳጇቸው ባለሃብቶች በኤዢያ ከለላ ሊሆኗቸው ስለሚችሉ የመጀመሪያ ምርጫቸው ኤዢያ እንደሚሆን ይስማማሉ። ለጎልጉል ማንነታቸውን ሳይገልጹ መረጃ የሰጡ የኢህአዴግ ሰው እንዳሉት “ኦሞት ርቆ አልሄደም ይያዝል” በማለት ግምታቸውን ሰጥተዋል። ጉዳዩን በቅርብ እንደሚከታተሉ የገለጹት እኚህ ሰው “ኦሞት ብዙ ጉዳዮችን እንዳያበለሽ ጥንቃቄ ሲደረግ ነበር። እንዴት ለጊዜውም ቢሆን ተሰወረ?” የሚለው መነጋገሪያ መሆኑን ግን አልሸሸጉም። ኦሞት በወቅቱ የፈጸሙትን ከ400 በላይ የአኙዋኮችን ጭፍጨፋ፣ የተሳተፉበትን ሙስና፣ የመሬት ነጠቃ፣ ግድያ፣ ወዘተ የወንጀል ምስጢር በማውጣት ኢህአዴግን አሳጥተው ፍርድ እንዲቀልላቸው መደራደሪያ ከማድረጋቸው በፊት ኢህአዴግ የራሱ አደን አጠናክሮ እንደሚገኝ ተጨማሪ ዘገባዎች አሉ፡፡ አቶ ኦባንግ ሜቶ የኦሞት መሰወር አያስጨንቅም ባይ ናቸው። ኦሞትን ፍትህ አሳድዳ ትይዘዋለች የሚሉት አቶ ኦባንግ ትኩረታቸው ወንጀል የተፈጸመባቸው በሙሉ መረጃ በመሰብሰብና ወደ ጋራ ንቅናቄው በመላክ እንዲተባበሩ የመነሳሳታቸው ጉዳይ ላይ ነው። ህወሃቶች ወንጀል አሰርተው፣ መጨረሻ ላይ ፍትህ ወዳድ ለመምሰል በወንጀል ያጨማለቋቸውን ሰዎች ህግ ፊት አቅርበው እንደሚያስፈርዱባቸው ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ሌሎች ከዚህና ከቀድሞው ተሞክሮ ተማሩ። ኦሞትን ፍትህ አደባባይ ለማውጣት የሚሰራው ስራ ወንጀለኞችን ለመፋረድ የምናደርገውን ትግል አንድ ርምጃ ያሳድገዋል። እንደ ኦሞት ያሉት ወንጀለኞች ካሉበት ይለቀማሉ። ይህንን ማድረግ አቅም አለን። በደም ተጨማልቆ በስደት መኖር አይቻልም። ሌሎችም ካሁኑ ንስሃ ግቡ፤ ህብረተሰባችሁን አስቀድሙ” ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ህወሃትም ሆነ ኢህአዴግ በራቸውን መክፈታቸው ወይም ለውጥ እንዲመጣ እንዲፈቅዱ የሚገደዱበት ዘመን መቃረቡን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ነጻ ውጡና ህዝባችሁን ነጻ አውጡ፣ አዲሲቷ ኢትዮጵያ ለወንጀለኞች ቦታ የላትም፣ ትፋረዳቸዋለች” ሲሉ በድጋሚ ህዝብ በወንጀለኞች ላይ መረጃ በማሰባሰብ የቤት ስራውን በወጉ እንዲሰራ ጠይቀዋል።
1
ኢትዮጵያዊው ቱጃር ለለውጥ ብለው በኮንትራት ታክሲ በመሄድ ላይ ናቸው። እሳቸውን የጫነው ታክሲ መስቀል አደባባይ ላይ ሲደርስ በድንገት ቀጥ ብሎ ቆመ። ሾፌሩ ተደናጋጠ። መኪናውን እንደገና ለማስንሳት ብዙ ሞከረ። ከብዙ ሙከራ በኋላ ጥረቱ ስላልተሳካለት ቱጃሩን ለትብብር ጠየቃቸው። እንዲህ ሲል። “ወጣ ብለው ይግፉ።” ቱጃሩ በመገረም ሾፌሩን አዩት። ”ይግዙ” ማለትህ ነው ሲሉም መለሱለት። እኚህ ሰው መኪናውን ከመግፋት ይልቅ አዲስ መኪና መግዛት ይቀላቸዋል። የቤቶች ድራማ ላይ እከ ደከ አስር ጊዜ “እኔን ነው?” የሚለው ወዶ አይደለም። ማመን የሚቸግሩንን ነገሮች ማጣራት ስንፈልግ እንደጋግማለን። “ሃገር ቤት ገብተን በመታገል አዲስ ታሪክ እንሰራለን።” የሚል ነበር የዜና እወጃው ርዕስ። ይህን ርዕስ እንዳየሁ አይኔን በደንብ ጠረግ ጠረግ አደረግኩና እንደገና አነበብኩት። “ታሪክ እንሰራለን” የሚለው ሃረግ በስህተት የሰፈረ ነበር የመሰለኝ። ሌንጮ ለማለት የፈለጉት “ታሪክ እናነባለን” ይሆናል በሚል ጥርጣሬ ደጋግሜ ያየሁት። ያነበብኩት ነገር ትክክል ነው። ይህንኑ ቃል ከራሳቸው አንደበትም ሠማሁ። በስህተት የሰፈረ ዜና አልነበረም። ታሪክን ማንበቡም ሆነ መስራቱ ቀርቶ “ሃገር ቤት ገብተን አዲስ ታሪክ እንጽፋለን።” የሚል ቢሆን እንኳን ግርታውን ይቀንሰው ነበር። በፍትህ ሳይሆን ይልቁንም በአዋጅ በምትተዳደር ኢትዮጵያ፤ እጅና እግራቸውን ብቻ ይዘው በመግባት ታሪክ መስራት የሚችሉ ከሆነ በምትሃት አልያም በመለኮታዊ ሃይል ብቻ መሆን አለበት። ሌንጮ ሃገር ቤት ገብተው ሰላማዊ ትግል ለማድረግ መወሰናቸው ላይ ምንም ችግር የለብኝም። የዚህ ውሳኔ ትክክለኝነት የሚዳኘው አስቀድመው በሚተቹ እና በሚተነብዩ የፖለቲካ ነብያት አይደለም። ፍርድ የሚሰጠው ሂደቱ በተግባር ሲፈተን ብቻ ይሆናል። ይህን ለማየት ደግሞ ብዙም ሩቅ አይሆንም። በጎረበጠ የፖለቲካ መንገድ ላይ ጉዞ ለማድረግ ወደ ሃገር ቤት ለመግባት መወሰናቸው ግን አስመራ ላይ፤ በሻእቢያ ከታገቱት የኦነግ መሪዎች የተሻለ ውሳኔ ይመስላል። ታሪክ ለመስራት አስመራ የመሸጉት እነ ዳውድ ኢብሳ ታሪክ ሆነው ቀርተዋል። ችግሩ ያለው “ታሪክ እንሰራለን” ማለቱ ላይ ነው። እንደዚህ አይነት የፖለቲካ ትግል ውሳኔ ላይ መድረስ ቀላል ነገር አይደለም። ከመቅጽበት የመጣው ይህ ውሳኔ ልክ እንደ ኦሎምፒክ ውድድር ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ አትሌት ይመስላል። አትሌቲክስም ቢሆን የአካል ብቃትና በቂ ዝግጅትን ይጠይቃል። ፖለቲካ ደግሞ ዘው ብለው ገብተው ታሪክ የሚሰሩበት በኦሎምፒክ የውድድር መድረክ አይደለም። እነ ሌንጮ እየነገሩን ያሉት አዲስ አበባ ገብተው በባላገሩ አይደል ላይ ለመወዳደር አይደለም። በባላገሩ የጫወታ ደንብ ጥሩ ስራ የሰራም፤ አስቀያሚ ስራ የሰራም ይሸለማል። ሌንጮ ታሪክ እንሰራለን የሚሉት “ስልጣን ወይንም ሞት!” የሚል መፈክር አንግቦ እስካፍንጫው የታጠቀ ሃይልን በመጋፈጥ ነው። ታሪክን ለመስራት ብቃት ያላቸው ድርጅቶች በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ጠፍተው አያውቁም። ከኦሮሞ ድርጅቶችም ቢሆን እነ ኦቦ ቡልቻ ደመቅሳ እና ፕ/ር መረራ ጉዲና አሉ። የኦሮሞን ህዝብ አደራጅተው በምርጫም፣ በፓርላማም፣ በሰልፍም፣ በእርግማንም፣ በጸሎትና ምልጃም፣ በወረቀትም … ብዙ ተጉዘዋል። የእነዚህ ድርጅቶች አባላት እንደጥጃ እየተለቀሙ እስር ቤቱን ከማጨናነቃቸው በቀር ታሪክ ሲሰሩ አላየንም። አንድ እርምጃ ወደፊት፤ አስር እርምጃ ወደኋላ እየተጓዙ ሄደው…ሄደው በመጨረሻ ራሳቸውም ታሪክ ከመሆን አላለፉም። ይህ ለአቶ ሌንጮ ለታ እንግዳ ነገር አይደለም። አቶ ሌንጮ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ በከባድ ሚዛን ደረጃ የሚመደቡ ናቸው። በዛሬይቱ ኢትዮጵያ በፖለቲካ ታግሎ ታሪክ ከመስራት ይልቅ ነድጅ ቆፍሮ ታሪክ መስራት እንደሚቀል ለሌንጮም አዲስ ነገር አይደለም። እርግጥ ነው። የታሪክ ትርጉም አሰጣጣችን ላይ እንለያይ ይሆናል። የገዥው ፓርቲ የታሪክ ትርጉምም ከልማት ጋር ይያያዛል። በዘመናችን ብዙ ታሪኮችን እየሰማን ነው። ልማታዊ አስተሳሰብ ያለው ሰው ሁሉ ዛሬ ታሪክ ሰሪ ይባላል። ታሪክ ሰርተው የሚሸለሙ የልማት አርበኞችን በቴሌቭዥን እናያለን። በአነስተኛና ጥቃቅን እየተደራጁ የኮብል-ስቶን ድንጋይን እያናገሩ ያሉ ወጣት ምሁራንም በታሪክ መዝገብ ላይ እየሰፈሩ ይገኛል። ኦቦ ሌንጮ ታሪክ የሚሉን እንዲህ አይነቱን ድራማ እንደማይሆን እርግጠኞች አይደለንም። እኝህ የፖለቲካ መሪ ታሪክ መስራት ከነበረባቸው ግዜው አሁን አይደለም። በሽግግሩ ዘመን 20 ሺህ ጦር እና 20 መቀመጫ ይዘው በነበሩበት ጊዜ ለዚህ እድሉ ነበራቸው። ያንን እድል ይዘው ታሪክ ከመስራት ይልቅ ድርጅታቸው ጥቁር ነጥብ ጥሎ ነበር ያለፈው። አቶ ሌንጮ ታሪክ መስራት ከነበረባቸው በሽግግሩ መንግስት የኢትዮጵያ መሪ ሆነው በተመረጡ ግዜ ነበር። በወቅቱ ምን ነበር ያሉት? “በዚህ ላይ አልተዘጋጀሁበትም።” ሲሉ የእድሉን በር ራሳቸው ዘጉት። በርግጥ ያን ጊዜ ከኦሮሚያ የመገንጠል አዙሪት ውስጥ አልወጡም ነበር። ትልቅ ህዝብን ይዘናል እያሉ፤ የመገንጠል ጥያቄን ሲያነሱ በአለም ላይ የመጀመሪያዎቹ ብቻ አይደሉም። የኦሮሞን ህዝብ በፖለቲካ አናሳ ማድረጋቸው የታያቸውም ከ40 አመታት በኋላ መሆኑ ነው። በዚያን ወቅት ኢትዮጵያን መምራት እንችላለን ለማለት በራስ መተማመን አልነበራቸውም። አንድ ሰው አንድ ድምጽ በሚል መርህ ምርጫ አድርገው ከመጓዝ ይልቅ፤ እንደ አናሳ ጎሳ “መገንጠል አለብን” የሚል ያታሪክ ስህተት ውስጥ ነበሩ። ከኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር ወጥተው የኦሮሞ ዲሞክራቲክ ግንባርን መመስረታቸው ከታሪክ ተወቃጭሽነት ሊያድናቸው ይችላል ። ይህንን በማድረጋቸው የሰማይና የምድርን ያህል ርቆ የነበረውን የፖለቲካ መስመር ሊያጠበው እንደሚችል ግልጽ ነው። ዛሬ የመገንጠልን ጥያቄውን ውድቅ አድርገው ለዲሞክራሲና ለፍትህ መታገል መምረጣቸው ታሪክ ሰሪ ሊያደርጋቸው አይችልም። ይህ ሊሆን የሚችለው ለውጥ አምጥተው ፍትሃዊ ስርዓት ማስፈን ሲችሉ ብቻ ነው። ሌንጮ ለታ አዲስ አበባ በመግባት ታሪክ እሰራለሁ ሲሉ ይህ የመጀመርያቸውም አይደለም። እ.ኤ.አ. 1993 የስራ ባልደረባቸውን ከከርቸሌ ለማስፈታት አዲስ አበባ ዘው ብለው ገብተው ነበር። እኝህ ሰው ሲገቡ ቦሌ ላይ ልዩ አቀባበል ተደረገላቸው። በብረት ተጠፍረውም ከርችሌ ተወረወሩ። በወቅቱ አዲስ አበባ ላይ ተካሂዶ በነበረው የግዮኑ የሰላም እና እርቅ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ሲገቡ የታሰሩ ልኡካንን እዚያው ተቀላቀሉ። ሌንጮ በዚያ ሰዓት ታሪክ ይሰራሉ ብለን ጠብቀን ነበር። ግን ይቅርታ ጠይቀው ከእስር ለመውጣት አንድ ሳምንትም አልፈጀባቸውም። በወቅቱ ከአቶ ሌንጮ ለታ ጋር ረጅም ቃለ-መጠይቅ አድርጌ ይህንን ታሪክ በማሳትመው ጋዜጣ ላይ ለህዝብ ይፋ አድርጌዋለሁ። እርግጥ ነው። የሌንጮ ለታ ፖለቲካ እውቀት የሚደነቅ ነው። በፖለቲካ ብስለታቸውና ትንተናቸው ከማደንቃቸው የፖለቲካ ሰዎች አንዱ ናቸው። ፖለቲካ ማወቅ እና ህዝብን መምራት ግን በጣም የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ብዙውን ግዜ የሰዎችን የፖለቲካ ብቃት የምንለካው በንግግር ችሎታው ብቻ ነው። ጥሩ የፖለቲካ መሪ አስተዋይም መሆን አለበት። የመሪ አስተዋይ አለመሆን ደግሞ ችግር የመፍታት ብቃታ ማጣቱን ነው የሚያሳየን። ኦነግ ከ40 አመታት በላይ በትግል ላይ እንደሆነ ይነገረን እንጂ ድርጅቱ ድል አድርጎ አይተን አናውቅም። የሽግግሩን መንግስት ላይም ቢሆን የተገኘው በድል አድራጊነት ሳይሆን ከህወሃት እና ከሻእቢያ ጥሪ ተደርጎለት ነበር። በአሁኑ የአዲስ አበባ ጉዞ ሌንጮ እንደቀድሞው ልዩ አቀባበል ላይገጥማቸው ይችላል። በእርግጠኝነት ለመናገር ከጉዞው በፊት አንዳች ቅድመ ሁኔታዎች ወይንም ስምምነቶች ይኖራሉ። ይህ ካልሆነ ግን እኝህን ሰው በቀይ መስመር ላይ ማስቆም ወይንም ደግሞ ማኖ ማስነካቱ አይቀሬ ነው። እሳቸውን ቀይ መስመር ላይ ለማቆስም በጣም ቀላል ነው። የበደኖው፣ የዋተሩና የአርባጉጉ ፋይሎች እየተመዘዙ ማውጣት ብቻ ይበቃል። አልያም ቦሌ ላይ እነ ዋልታ ብቅ ብለው በካሜራ ይቀበሏቸዋል። ልማቱን እንዲያደንቁ ይጠየቃሉ። በእስር ያሉ ወገኖችና “ሽብርተኞች”ን ማውገዛቸውም የግድ ነው። በዚህ መስመር ላይ ከሄዱ ”አባ ጸበል ይርጩን” ብለው እንደገቡት እንደነ ስም አይጠሬ ተዋርደው ይመለሱና የፖለቲካ ሞትን ዳግም ይቀምሷታል። በጥንቱ ዘመን በኢትዮጵያ መቀመጫቸውን አክሱም ያደረጉት ነገሥታት ታሪካቸውን እና ጥበባቸውን በሳብኛና በግእዝ እያጻፉ አዘጋጀተዋል። በመቀጠልም መቀመጫቸውን ወደ ዛጔ፣ ላስታ ላሊበላ፣ ወሎ ሲተላለፍ በዚያ የነገሡ ነገሥታትም ታሪካቸውን እና ጥበባቸውን በግእዝና በአማርኛ እያዘጋጁ አልፈዋል። የነገሥታቱ መቀመጫ ከወሎ ወደ ሸዋ፤ ከዛም ወደ ጎንደር ሲሸጋገር፣ የነበረው ታሪክ፣ ጥበብና የነገሥታቱ ዝርዝር ሁኔታ ተዘጋጅተው ተመዝግበዋል። የታሪክ ሊቃውንት የነጋሥታቱን ብርቱና ደካማ ጎኖቻቸውን እና የሰሩትን ታሪክና ገድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ በማሳወቅ፣ ሕዝቡም በተራው ያለፉት ነገሥታት የጣሉበትን የጀግንነት አደራ እንዲጠብቅ አድርጎታል። የኢትዮጵያን ሉአላዊነት፣ ዝና እና ክብር እንዲሁም ታሪክና የታሪክ ቅርሶቿ በክብር እንዲንከባከባቸው በሰጡት አደራ መሰረት ኢትዮጵያ ለማንም ቅኝ ገዢ ሳትንበረከክ በዓለም ደረጃ ዝነኛ ሆና የወጣች ሃገር እንድትሆን አድርገዋታል። የታሪክ ሊቃውንት በ845 በኢትዮጵያ አክሱም ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ንጉሥ አንበሳ ውድም ልታወድም የተነሳችው ዮዲት ጉዲት ዙፋኑን ገልብጣ፣ አብያተ ክርስቲያናቱን በማቃጠል፣ ሃውልቶችን እያፈረሰች ታሪካዊ ቅርሶችን በማውደም፣ ክርስቲያኖችን በመጨፍጨፍ ብዙ ከባድ ግፎችን ፈጽማለች። ቀጥሎም በ1515 በአፄ ልብነ ድንግል ዘመን መንግሥት ግራኝ አህመድ የተባለ ጠላት ተነስቶ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን፣ ታሪካዊ ገዳማትን እና ታሪካዊ መዛግብትን ከማውደሙም በላይ፣ ክርስቲያኖችንም አንገታቸውን በሰይፍ እየቀላ ሕዝብ ጨርሷል። ታሪክ ጸሐፊዎችም በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አህመድ የተፈጸመውን ግፍ በጥቁር ታሪክነቱ ከትበው ለትውልደ ኢትዮጵያውያን አስተላልፈዋል። አሁን ባለንበት ዘመን ከሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ የመጣው ገዢ፣ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ከላይ ከተጠቀሱት የኢትዮጵያ ጠላቶች እጅግ በጣም ተወዳዳሪ የማይገኝለት፣ በክፉ መልኩ ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ያወደመ፣ የሃገር ሉአላዊነትን ያፈረሰ፣ ሃገር የሸጠ፣ ወጣት ሴቶችን እና ወንዶችን ለባርነትና ለስደት የዳረገ ነው። ከየት መጣ ሳይባል ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት በመቆጣጠር ሃገር በማፍረስ፣ ሕዝብን ከተወለደበት በማፈናቀል የሚፈጽመውን ፋሽስታዊ ተግባራቱን የታሪክ ጸሐፊዎችና የኢኮኖሚ ሊቃውንት ኢትዮጵያውያን እየጻፉት ነው። በህዳር 2006 መጨረሻ አስደንጋጭ ዜና በዓለም ሚዲያዎች ተነገረ። የደቡብ አፍሪካው የነፃነት አባት ኔልሰን ማንዴላ ከዚች ዓለም በሞት እንደተለየ ተገለጸ። የዓለም ሕዝብና መሪዎቹ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን በማስተላለፍ የኔልሰን ማንዴላን አንጸባራቂ ታሪክና ኤ.ኤን.ሲን በመምራት የከፈሉትን መስዋእትነት፣ በተካሄደው መራራ ትግል ደቡብ አፍሪካን ከአፓርታይድ ስርዓት አላቀው ሃገሪቷን እና ሕዝቧን ነፃ ምውጣታቸውን፣ እስከ ግባተ መሬታቸው ድረስ በትግል የፈጸሙትን አኩሪ ታሪካቸውን እና ገድላቸውን ካለምንም ማቋረጥ በዓለም ዙሪያ ነግሮላቸዋል፣ የሰላምና የእርቅ አባትም ተብለዋል። በቀብራቸው እለትም ከ100 በላይ የዓለም መሪዎች ደቡብ አፍሪካ ድረስ በመጓዝ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ያልታየ እጅግ የደመቀ የቀብር ስነስርዓት ተፈጽሞላቸዋል። የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ማንዴላ የፈጸሙት የትግል ድልና ታሪክ ነው። ስለሆነም ታሪክ ለባለ ታሪኩ እንደሆነና እንደሚገባ በኔልሰን ማንዴላ ታይቷል። ጥቁር ታሪክ የተሸከመው ወያኔ ህወሓት ደግሞ ከትወልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ፣ እየተረገመና እየተወገዘ ልክ እንደ ዮዲት ጉዲት በሳጥናኤል ምስል እየታወሰ ይኖራል። የኔልሰን ማንዴላን ህልፈት ተከትሎ የዓለም መሪዎች የተሰማቸውን ሃዘን ሲገልጹ፣ የዓለም ብዙሃን መገናኛዎችም ለሶስት ሳማንታት የቆየ ሰፊ ሽፋን ሰጥተውታል። በዚህም የተነሳ ለህወሓት አመራርና ካድሬዎቹ፣ እንዲሁም የፋሽስቱ ስርዓት መሳሪያ በመሆን የሚያገለግሉት ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደቡብ ህዝቦች ተብለው በሚታወቁት የገዢው አጎብዳጆች ላይ የራስ ምታት ለቆባቸው ሰንብቷል። ምክንያቱም የህወሓት መሪ ከዚህ ዓለም በሞት ሲቀጠፍ ማንም የዓለም መሪም ሆነ ሕዝብ ከግምት ውስጥ ስለአላስገባው። ሚዲያውን በተመለከተ አልጀዚራና ቢቢሲ ከ2 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያው አምባገነን መሪ ሞተ ብለው ከመናገር የዘለለ ምንም አልጨመሩም። - ጀግናው መለስ ዜናዊ ጦርነት ሳይንስ እንጂ በእድል የሚገኝ አይደለም ብሎ የተነተነ ምሁር ሲሆን፣ ፋሽስት በሆነው ደርግ ላይ ያረጋገጠ ጀግናና የብዙ ጀግኖች ፈጣሪ ነው ይላል፤ በመሰረቱ የዚህ ርእሰ አንቀጽ ጸሐፊ የመለስ ዜናዊን ማንነት የማያውቅ፣ ለጥቅሙ ብሎ በአየር ላይ የሚንሳፈፍ ፊኛ ፍጡር ነው። መለስ ዜናዊ ከተሓህት/ህወሓት ለትግል ከተደባለቀበት ጊዜ አንስቶ በጦርነት ተሳተፍ ተብሎ በግዴታ በተሰለፈባቸው ጦርነቶች ገና የመጀመሪያዋ ጥይት ስትተኮስ ፈርቶ የሸሸ ለመሆኑ በጊዜው የነበሩ የተሓህት ታጋዮች በሚገባ እናውቃለን። በተሓህት ህግና ስነሥርአት መሰረት ከጦርነት ያፈገፈገ ሞት ይፈረድበታል። መለስ ዜናዊ በአደዋ፣ ፈረሰማይ፣ አዲደእሮ፣ ማይቅንጣል፣ ሃገረሰላም፣ አዲ-ኮኸብ፣ ገለበዳ ወዘተ. በተደረጉት ጦርነቶች ፈርቶ የሸሸና ያፈገፈገ ግለሰብ ነው። ለምን እንደሌሎቹ አፈገፈጋችሁ ተብለው እንደተገደሉት መለስ ዜናዊ ስላልተገደለበት ምክንያት በቀዳሚነት የሚጠየቅበትና መልስ የሚሰጠው አረጋዊ በርሄ ነው። ጀግኖች የፈጠረ ማለት ቀልድና ቧልት ነው። ሌቦችን እና ዘራፊዎችን የፈጠረና ራሱም ቀንደኛ ዘራፊ የሆነ ሰው ጀግኖች ሊፈጥር አይችልም። መለስ ዜናዊ ምንም የጦርነት ሳይንስም ሆነ ወታደራዊ ጥበብ የለውም። - የባለ ራእይነትና አርባኝነት ትልቁ ዓላማው ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ከበለጽጉት ሃገሮች ጋር እንድትቀላቀል ማድረግ ነው። የትራንስፎርሜሽን እቅዱም የዚሁ ራእይ አካል ነው ይላል። ቀጠል በማድረግም፣ የታላቁ መሪ ራእይ ስኬታማ እየሆኑ መምጣታቸውን እየተመለከትን ነው። የኢትዮጵያን ሕዝብ ከጭቆና በማላቀቅ የኢኮኖሚ ባለቤትነቱን ያረጋገጠ ጀግና ነው ብሎም ያትታል። ባለርእሰ አንቀጹ ይህን ሲጽፍ ከጠባብ አስተሳሰብ በመነሳት ነው። ህወሓት ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ከተቆጣጠረበት ከግንቦት 1983 እስከ አሁን ድረስ በሃገሪቱና በሕዝቧ የወረደው ፋሽስታዊ አገዛዝ ረሃብ፣ በሽታ፣ እንክርት፣ መፈናቀል፣ እስራት፣ የሃገር መሬትና ድነበር ለባእዳን መሸጥ፣ ሰቆቃ፣ አፍኖ ማጥፋት ወዘተ. እየተፈጸሙ ያሉት የመለስ ዜናዊ ራእይና የህወሓት አመራሮች እቅድ መሆኑን ማወቅና መገንዘብ መቻል ያለበት ይመስለኛል። በመሰረቱ የርእሰ አንቀጹ ጸሐፊ ህወሓት ማነው? ሲፈጥርስ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ሆኖ የተፈጠረ ነው ወይ? የሕዝብ ፍቅርና ስሜት መስፈርቱ ነበር ወይ? በኢትዮጵያ ሉአላዊነት ያምን ነበር ወይ? የሚሉትን ጥያቄዎች ያላገናዘበ ከጠባብ ዘርኝነት ስሜት የመነጨ ነው። ውሸት በመደርደር መለስንም ሆነ የህወሓት አመራርን ለልማት የቆሙ አስመስሎ መጻፍ የጸሐፊው አባላት ሳይቀሩ ይታዘቡታል፣ ይንቁታል። ለምን ቢባል፣ ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ሃገር የሆነውን የህወሓትን ጥቁር ታሪክ በወርቃማ ቀለም መለወጥ አይቻልምና። ኢትዮጵያን ለማፍረስ ትልእኮው አድርጎ የተነሳ ድርጅት ነው። ከላይ የተጠቀሱትን ኢትዮጵያን ወሮ ከተቆጣጠረ ጀምሮ በተግባር ታይተዋል። ስለሆነም የመለስ ራእይ ለእድገትና ትራንስፎርሜሽን የሚበጅ ሊሆን አይችለም። የመለስና ግብረአበሮቹ ባህሪና የፖሊሲ አቋመቸው ጸረ-ዲሞክራሲ፣ ጸረ-ሃገርና ሕዝብ ነው። በቅጽበት ተለውጠው ለሕዝብና ለሃገር ተቆርቋሪ ሊሆኑ አይችሉም። ዲሞክራሲ ገና ከጅምሩ አንድ ድርጅት ሲፈጠር መሰረታዊ የዲሞክራሲ መሰሶዎች አበጅቶ የሚዳሰስ፣ የሚታይ ጠንካራ የህንጻ ብረት መሳሪያ መሰረቱን የጣለ ከሆነ ነው። ህወሓት ግን ከዚህ ያፈነገጠ ጠባብና ዘረኛ ፋሽስት ድርጅት የዲሞክራሲ መድረኩ አይፈቅድለትም። ስለዚህ፣ የኢኮኖሚ ባለቤትነትን ያረጋገጠ የመለስ ዜናዊ የጀግንነት መግለጫ ነው የሚለው አባባል ከእውነት የራቀ የጠባብ ዘረኝነት አስተሳሰብ ነው። ውሃ የማይቋጥር ቀዳዳ ጣሳ እንበለው። - መለስ ዜናዊ ከድህነት በላይ አዋራጅ ከድህነት በላይ ክፉ ጠላት የለም የሚለው ራእይ በወሰደው ቆራጥ አመራር የከተማና የገጠር ልማት ፖሊሲዎችና የአፈጻጸም ስልቶች የመለስን የልማት አርበኝነትና ጀግንነት በትክክል የሚያሳይና የሚያርጋግጡ ናቸው ይላል። የመለስ ዜናዊ የልማት፣ የእድገት አርበኝነት እያሉ በየቀኑ ሕዝብን የሚያደነቁሩ የህወሓት ካድሬዎች ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደቡብ ህዝቦች ናቸው። ህወሓት የፈጠራቸው ቅጥረኛ ድርጅቶች ሃገር እያፈረሱ፣ ሕዝብን እየጨፈጨፉ ሲሆን፣ መሪያቸው የህወሓት አመራር ድህነትን የተዋጋ፣ ሰፊ የልማት አውታር በመዘርጋት ኢትዮጵያን የለወጠ ብሎ መናገር ከሃዲነት ነው። ወያኔ ህወሓት በ1983 ሃገር ወሮ በቅኝ ግዘቱ ስር ባደረጋት ማግስት የኢትዮጵያ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ተለዋወጠ። ሕዝቡ በርካሽ እየገዛ የሚጠቀምባቸው የምግብ አይነቶች ጤፍ፣ ስንዴ፣ ቅቤ፣ ሥጋ ወዘተ. ዋጋ የሰማይ ጣራ ነካ። እስከ ደርግ ዘመን ፍጻሜ ድረስ ጤፍ በኩንታል ብር 45-60 ይሸጥ ነበር። ቅቤ፣ ዘይት፣ ስጋ ወዘተ. በተመጣጣኝ ዋጋ ይገበይ ነበር። በወያኔ ህወሓት አገዛዝ ቅቤ፣ ዘይት ወዘተ. ከገበያ ጠፍቷል። ጤፍ በኩንታል ብር 1500-1800 ደርሷል። ከአፄ ኃ/ሥላሴ እስከ ደርግ ዘመን ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በቀን ሶስት ጊዜ መብላት ይችል ነበር። በአሁኑ ስርዓት ግን በቀን አንድ ጊዜ ለመብላት የሚታገለው ሕዝብ ቁጥሩ በርካታ ሆኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪክ አይቶት ለማያውቀው ድህነት ከተዳረገ 23 ዓመት አስቆጥሯል። መራሹ ገዢ ህወሓት የኢትዮጵያን ሕዝብ ለከፋ ረሃብ፣ በሽታና ስደት ዳርጓል። “እንኳንስ ዘንቦብሽ ዱሮውንም ጤዛ ነሽ” እንደሚባለው፣ ከትግሉ መነሻ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ወያኔ ህወሓት ለኢትዮጵያና ህዝቧ ጠላት ሆኖ የተፈጠረ ድርጅት ነው። ከ1967 ጀምሮ ሕዝቧን በጎሳና በዘር ከፋፍዬ አጠፋታለሁ ብሎ የተነሳ ድርጅት ነው። ይህንን ከመጠን ያለፈ ጥላቻ ከትግሉ መነሻ ጀምሮ ሲያራምደው የመጣና ዛሬ በተግባር እያሳየው ነው። ምክንያቱ፣ ህወሓት ኢትዮጵያዊ አይደለምና። የህወሓት ካድሬዎችና ደጋፊዎች የምትናገሩትና የምትጽፉት ገደብ የለሽ ውሸት፣ በሙስና እና በዝርፊያ ባገኛችሁት ንብረት ከነቤተሰባችሁ እየተንደላቀቃችሁ ጠግባችሁ ብታድሩም፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የምትነግሩትና የምትጎስሙትን የውሸት ነጋሪት ውድቅ ካደረገው ዓመታት አልፈዋል። ህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደቡብ ህዝቦች በሕዝብ ፊት ቀርባችሁ ፍርዳችሁን የምታገኙበት ጊዜ ተቃርባለች። ህወሓት ኢትዮጵያን ሲቆጣጠር ተሸክሞት የመጣውን በቀል አማራው፣ ኦሮሞው፣ ጋምቤላው፣ አፋሩ፣ ኦጋዴኑ ወዘተ. ዘር የማጥፋት ተግባሩን ፈጽሞታል። አሁንም እያጠፋ፣ እየገደለ በየወህኒ ቤቶቹ እየማገደው ነው። ይዞት የመጣው ድህነትና በሽታን ብቻ ነው። ፖሊሲው የኢትዮጵያን ሕዝብ ከዓለም ሃገሮች በድህነት ከወለል በታች ያደረገ ስርዓት ነው። የኢትዮጵያ ገበሬ የመሬቱ ባለቤት በነበረበት ወቅት እራሱን እና ቤተሰቡን አብልቶ ቀሪውን ለገበያ በማቅረብ ሕዝቧ እንደአቅሙ በልቶና ጠጥቶ ያድር ነበር። የህወሓት አስተዳደር መሬት የመንግሥት ነው ብሎ በማወጁ የኢትዮጵያ ሕዝብ በገጠሩም በከተማም መሬት አልባ ሆኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በገዛ ሃገሩ ሁለተኛ ዜጋ ከመሆኑ የተነሳ ሲሞት እንኳን የሚቀበርበት ቦታ ያጣ ሕዝብ ሆኗል። የመለስ ራእይ እድገትና ልማት ነው ተብሎ የተጻፈው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በዚህ ሁኔታ ይቀጥላል የሚል አመለካከት ካለው ፈጽሞ ተሳስቷል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለገዢው ስርዓት መቃብር ቆፍሮ እየጠበቃቸው ነው። የሚተርፋቸው ጥቁር ታሪካቸው ከትውልድ ትውልድ መተለለፉ ብቻ ይሆናል። ለመለስ ዜናዊ ከድህነት በላይ ክፉ ጠላት የለውም ብሎ መጻፉ ትክክል ነው፣ እስማማበታለሁ። መለስ ዜናዊ የድሃ ቤተስብ ልጅ መሆኑ እንዳይታወቅበት ብዙ ጊዜ ሲከላከል እንደነበር የምናውቀ ሃቅ ነው። መለስ ዜናዊ የሹምባሽ አስረስ ተሰማ የልጅ ልጅ ነው። የሴት አያቱም ወ/ሮ ዘውዲቱ መንገሻ ይባላሉ። አድዋ አውራጃ የተወለደው አስረስ ተሰማ ደግሞ ኤርትራዊ ሲሆን፣ መለስ ዜናዊ በትግራይ ያለው ትውልድ በሴት አያቱ ብቻ ነው። ወራሪው ጣልያን ለሁለተኛ ጊዜ በአፄ ኃ/ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በተሸነፈበት ጊዜ የጣልያን ባንዳው ሹምባሽ አስረስ ተሰማ በግዞት አድዋ ውስጥ ነበር። በ6 ወራት ጣልያን ሙሉ በሙሉ ተሸንፎ ኢትዮጵያ ነጻነቷን ስትቀዳጅ አስራስ ተሰማ በደረሰበት ድንጋጤ ታሞ ሞተ። ዜናዊ አስረስም ከአድዋ ከተማ ወደ ኤርትራ አልተመለሰም። ቀደም ብሎ በጣሊያን ጊዜ ያገባቺው ሚስቱም አንዴ አድዋ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ አዲኳላ እየተመላለሱ ኖረዋል። ዜናዊ አስረስ ከወ/ሮ አለማሽ ወ/ልኡል መለስ ዜናዊን ጨምሮ 5 ልጆች ወልደዋል። ሌሎች ሁለት ኤርትራውያን ሴቶች ስለነበሩት በጠቅላላው 13 ልጆች አሉት። ዜናዊ አስረስ ጣልያንኛ በመጠኑ ይናገራል፣ ግን አይጽፍም። ዜናዊ አስረስ ሥራ ያልነበረው ድሃ ስለነበር ማመልከቻ ጸሐፊ በመሆን ኑሮውን ይገፋ ነበር። በኤርትራዊነቱ ስለሚታወቅ በአድዋ አውራጃ ውስጥ የእርሻ መሬት አልነበረውም። አባቱ ሹምባሽ አስረስ ተሰማ በሕዝብ ላይ ብዙ ግፍ የፈጸመና በጣሊያን ባንደነቱ የተነሳ አድዋ ውስጥ በጣም የተጠላና የተገለለ ነበር። ይህንን ሁሉም የአድዋ ሰው የሚያውቀው ሃቅ ነው። ድህነት የሚያሳፍርና የሚያሸማቅቅ አይደለም። የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ የድሃ ልጅ ነኝ፣ ስለሆነም አላፍርበትም። በድህነቴ እኮራለሁ እንጂ የሌለኝን አለኝ ብዬ አልመጻደቅም። መለስ ዜናዊ ግን ይህን አይቀበልም፣ ቤተሰቦቹም ይህን አይቀበሉም። ወንድሞቹ በክፉ ድህነት ያደጉ፣ እህቶቹ እነ ገርግስ ዜናዊ በአሁኑ ጊዜ ሚሊየነር ብትሆንም እንጀራ እየሸጠች ያደገች፣ ኒቆዲሞስ ዜናዊም እንቁላል እየቀቀለና እንጀራ በየጠላ ቤቱ ማታ ማታ እየሸጠ ያደገ ነው። ይህ ሁሉም ሥራ ነው፣ የሚያስከብር እንጂ የሚያሳፈር አይደለም። ዜናዊ አስረስ በአፄ ኃ/ሥላሴ ዘመን የአድዋ አውራጃ ገዢ ነበር ብሎ ዋሸ። የተናገረውን ሁሉ ረስቶ ለሞቱ በተቃረበ ጊዜ አፄ ኃ/ሥላሴ አዲስ አበባ ድረስ አስጠርተው የአባትህን ሥራ ልስጥህ፣ በአታሼ ድረጃ ሥራ ልመድብህ ሲሉኝ አልቀበልም አልኩ በማለት ተናግሯል። የወላጅ አባቴን ሃብትና ንብረት ጠብቄ ለልጆቼ አወርሳለሁ ብዬ ወደ አድዋ ተመልስኩ ብሎ የተናግረውን በድረ ገጾች አይቸዋልሁ። ይህ ሁሉ ደረቅ ውሸት ነው። የሚኖረው ተወልደን ባደግንበት አድዋ ከተማ ነው። እስከምናውቅ ድረስ ምንም አይነት ሃብት የሌለው፣ በማመልከቻ ጸሐፊነት የሚተዳደር ደሃ መሆኑን የወቅቱ የአድዋ ከተማ ሕዝብ ያውቀዋል። መለስም ሥልጣን እንደጨበጠ የደሃ ልጅ እንዳይባል በተክለ ሰውነቱ እንዳትጠጋው አደረጋት። ድህነት አያሳፍርም። በዚህ ዓለም አሳፋሪ ነገር ውሸት፣ ዝርፊያ፣ ሙስና፤ የንጹሃን ደም ማፈሰስ፣ ባጠቃላይ ወንጀል ናቸው። መለስ ዜናዊ የዚህ ሁሉ ቀንደኛ ተዋናይ ነው። አንድ እውነተኛ ታሪክ ላቅርብ። የታሪኩ ባለቤት የአድዋ ሰው ሲሆኑ አሁን ግን አልፈዋል። ታሪኩን በጊዜው የነበሩ የአድዋ ከተማ ኗሪ የሚያውቁት ትክክለኛ የታሪክ ሃቅ ነው። አባቶቻችን ለኛ ለልጆቻቸው ነግረውና አስተምረው አልፈዋል። አስረስ ተሰማ የታወቀ የጣሊያን ባንዳ ነበር። ጣሊያን ኢትዮጵያን እንደወረረ አስረስ ተሰማ የጣሊያኖች ታማኝ አሽከር ነበር። በጣሊያኖች የተሰጠው ማእረግ መጀመሪያ ኮማንዳቶሪ ሲሆን፣ ቀጥሎም ካባሌሪ ሆነ። ትንሽ እንደቆየም ሹምባሽ አስረስ ተብሎ ይጠራ ነበር። በአድዋ፣ አዲግራትና አክሱም በርካታ ግፎችን ፈጽሟል። ግለሰቦችን ሁለት እግራቸውን፤ እጆቻቸውን እና ጆሯቸውን በመቁረጥ እስከግድያ በሚደርስ ድርጊት አስቃይቷል። በገበያ ቀን ኢትዮጵያውያንን ሰላይ እያለ ሴት ከወንድ ሳይለይ ለገበያ በወጣው ሕዝብ ፊት አርባ አርባ ጅራፍ በመግረፍ ስፍር ቁጥር በሌለው ሕዝብ ላይ ስቃይ አድርሷል። በዚህ መጥፎ ተግባሩ የታወቀው ሹምባሽ አስረስ ተሰማ ለዓመታት በዚህ አይነት ሲቀጥል፣ የሕዝቡ አቤቱታ ለራስ ስዩም መንገሻ ይደርስ ነበር። ጣልያን ውድቀቱ በተቃረበበት ወቅት፣ ራስ ሥዩም ደጃዝማች ገ/ህይወት መሸሻን ይህንን ሰው እንደምንም ብለህ ይዘህ አምጣልኝ የሚል ትእዛዝ ሰጥተዋቸው ነበር። ደጃዝማቹ አካባቢውን ስለሚያውቁት በሶስት ሳምንት ክትትል አዲኳላ በምትገኘው ማይጫአት፣ ልዩ ስሟ አዲአዝማቲ ከምትባል ቦታ በሌሊት ተከታትለው ሹምባሽ አስረስ ተሰማን ከልጃቸው ዜናዊ አስረስ ጋር ማርከው ያዟቸው። በሌሊት ወደ አድዋ አሸጋግረው ለፊታውራሪ ገ/አምላክ ከነልጁ በግዞት እንዲቆይና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረጉ። ፊታውራሪ ገ/አምላክ ማለት የወያኔ ህወሓት መሪ የነበረው በ1993 ከነስየ አብርሃ ጋር የተባረረው የአለምሰገድ ገ/አምላክ ወላጅ አባት ናቸው። አስረስ ተሰማ ለጥቂት ወራት በግዞት ላይ እንዳለ ኢትዮጵያ ጣልያንን አሸንፋ ነጻነቷን ተቀዳጀች። አስረስ ተሳማና ዜናዊ አስረስን የራስ ሥዩም አሽከሮች ይኖሩበት ወደነበረው አድዋ እንዳሥላሴ አዘዋወሯቸው። የጣልያንን ሽንፈት በሰማ ጊዜ ታሞ ከትንሽ ጊዜ በኋላ ሞተ። ሹምባሽ አስረስ በሞተ ጊዜ የሚቀበርበት ቦታ ታጥቶለት ነበር። ጥቂት የሆኑት ቀባሪዎቹ እንዳሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በቦታው እንዲቀበር ቢማጸኑም፣ ንብሰ ገዳይና የጣልያን አሽከር በቤተ ክርስቲያናችን አናስቀብርም ብለው ከለከሉ። አስረስ ተሰማ ከቆየባት ቤቱ በግመት 300 ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው እንዳጽዮን ቤተ ክርስቲያን ሂደው ሲጠይቁ፣ ለምን እንዳሥላሴ አትቀብሩትም፣ የቤተ ክርስቲያኑ አለቃ አስረስ ተሰማ በዚች ቅድስት ማርያም ቦታ፣ ገዳይና ከሃዲ የጣልያን አሽከር አናስቀብርም የሚል መልስ ሰጥተው አሰናበቷቸው። በቀሪዎቹ ቤተ ክርስቲያናት እንደ እንዳ መድሃኔዓለም፣ እንዳ ገብርኤል፣ እንዳ ሚካኤል ፈጽሞ የማይታሰብ ሆነ። ያላቸው አማራጭ በረሃ ውስጥ ጉድጓድ ቆፍረው ምቅበር ብቻ ነበር። ማይ ምድማር ውሰዱ ተባሉ። ይህ ቦታ ደግሞ የወንድሞቻችን እስላሞች መካነ መቃብር ነው። በአጥር የተከለለ በጣም ሰፊ ሜዳ ነው። ቦታው በክብር የሚጠበቅ ስለሆነ ማንም ዝር አይልበትም። ስለሆነም እዛም አልተቻለም። እንደ አማራጭ ብለው ያሰቡት ማይ ምድማርን ተሻግሮ በሚገኝ ቦታ ላይ ሆነ። ማይ ምድማር ማለት፣ ከሰሜን በኩል ማይጓጓ ወንዝ፤ በፀሃይ መውጫ በኩል አሰብ ወንዝ የአድዋን ከተማ ለሁለት ሰንጥቆ የሚያልፍ ሲሆን፣ ሁለቱ የሚገናኙበት ቦታ ማይምድማር ተብሎ ይጠራል። አንዳንድ ጊዜም ጉራንጉር ተብሎ ይጠራል። ከማይምድማር ተሻግሮ የሚገኘው ቦታ ደግሞ የእንዳ ጊዮርጊስ መሬት ነው። ብዙ የመስኖ እርሻ ስላለበት ቀባሪዎቹ እዚያ ማድረግ እንደማይችሉ ስለተገነዘቡ፣ ሬሳውን ተሸክመው ወደ ተምቤን በሚያቀና መንገድ ተጉዘው አንድ በማይታወቅ ቦታ ቀበሩት። ከቀባሪዎቹ ከማስታውሳቸው መካከል አቶ ግብረቱ፣ አቶ ገብሩ፤ ልጃቸው ዜናዊ አስረስ ሲሆኑ ቀሪዎቹን ማስታውስ አልቻልኩም። የሹምባሽ አስረስ ተሰማ ሬሳ በረሃ እንደተጣለ አባቶቻን ነግረውናል። ይህንንም በወቅቱ የነበረው የአድዋ ሕዝብ በግልጽ የሚያውቀው ነው። ዜናዊ አስረስ ከሕዝብ የተገለለ፣ ልጆቹም ከሰው ተገልለው ማደጋቸው ሁሉም የሚያውቀው ሃቅ ነው። መለስ ዜናዊ በቤልጂየም ሆስፒታል መሞቱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያበሰረው ኢሳት ነበር። ሕይወቱ ያለፈችው ከብዙ ስቃይ ብኋላ ነው። ነብስ ይማር ያለው ኢትዮጵያዊ አልነበረም፣ እሰይ አምላክ ፍርድህን ሰጠህ ከማለት በስተቀር። ሬሳው ኢትዮጵያ ውስጥ ይቀበር አይቀበር አይታወቅም። የአያቱ ሹምባሽ አስረስ ተሰማ ሬሳ የገጠመው አይነት እድል እንደገጠመው እገምታለሁ። የማይቀረው ጊዜ ሲደርስ ስላሴ የተቀበረው ባዶ ሳጥን የአያቱን አይነት እድል እንዲሚያገኝ አልጠራጠርም። መለስ ዜናዊና ግብረ አበሮቹ ኢትዮጵያን ሲቆጣጠሩ በእናቱም በአባቱም የደጃዝማች ልጅ ነው ብለው በድረ ገጽ ተጽፎ አንብቤአለሁ። ከላይ እንደዘረዘርኩት ከእውነት የራቀ ነው። ባንዳዎቹ ኢትዮጵያ ወደ ነፃነቷ እያመራች በነበረችበት ጊዜ አስመራ ለነበረው ጄነራል ደቦኖ አቤቱታ አቅርበው ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት ለራሱ ሰዎች ራስ፣ ደጃዝማች፣ ፊታውራሪ ወዘተ. እያለ ማእረግ ሰጥቷቸዋል። እኛ የጣሊያን አሽከሮች ግን ምንም አይነት ማእረግ አልተሰጠንም። እኛም ልክ እንደ ኢትዮጵያውያኖቹ አይነት ማእረግ እንዲሰጠን እንፈልጋለን ብለው አቤት ብለው ነበር። አቤቱታቸውን ግራዚያኒ ወደ ሮም መንግሥት በማስተላለፍ ሹመቱን እንዲሰጥ ተፈቀደለት። በዚያም መሰረት የጣሊያኑ ባለሥልጣን ለባንዳዎቹ ደጃዝማች፣ ፊታውራሪ ወዘተ. እያለ አምበሸበሻቸው። ለአጭር ጊዜም ቢሆን፣ የዚህ ተጠቃሚ የሆኑት፣ የዜናዊ አስረስ ባለቤት የነበረች አለማሽ ገ/ልኡል፣ አባቷ ደጃዝማች ገ/ልኡል ሲሆኑ፣ ሹምባሽ አስረስም ደጃዝማችነት ተችሮት ነበር። ይሁንና ሳይጠራበት በኢትዮጵያ ጀግኖች ተይዞ ግዞት ገባ። ሌላው የዚህ ተጠቃሚ የነበሩት የስብሃት ነጋ አባት ፍታውራሪ ነጋ ነበሩ። ማእረጉን ባገኙ በጥቂት ወራት ጣልያን ተሸንፎ ሲወጣ፣ እስከ እለተ ሞታቸው ድረስ የአድዋ ሕዝብ በጣልያን የተሰጠውን ፊታውራሪነት አልተቀበለላቸውም። አብዛኛው ኗሪ አቶ ነጋ ሲላቸው፣ ጥቂት የቅርብ ጓደኞቻቸውና ዘመዶቻቸው በጣልያኑ ሹመት ፊታውራሪ ነጋ እያሉ ሲጠሯቸው አውቃለሁ። የደቡብ አፍሪካው መሪ ኔልሰን ማንዴላ በሞቱ ጊዜ የዓለም ሕዝብና መሪዎቻቸው መራራ ሃዘናቸውን ገልጸዋል። የዓለም ብዙሃን መገናኛዎችም ሶስት ሳምንታት ሙሉ የኔልሰን ማንዴላን አርበኝነት፣ የንፃነት መሪነታቸውን፣ የሰላምና የፍቅር አባትነታቸውን እና አንጸባራቂ ታሪካቸውን በስፋት ዘግበዋል። ይህ ነው እንግዲህ ታሪክ ለሰሪው፣ ታሪክ ለባለታሪኩ የሚባለው። መለስ በሞተበት ጊዜ ሕዝብ በቀበሌ ተገዶና ብር 100 የውሎ አበል እየተሰጠው ነው ለቀብር የወጣው። ከዓለም መሪዎች መካከል የተገኙትም ጥቂቶች ናቸው። አብዛኛዎቹም ከነአካቴው የሃዘን መግለጫ እንኳን አልላኩም። ሚዲያውም ቢሆን፣ በጣም ጥቂቶቹ፣ አምባገነኑ መሪ መለስ ዜናዊ ሞተ ብለው ከመዘብ ያለፈ አላደረጉም። የኢትዮጵያ ገዢው መደብ ግን በዚህ ተናዷል። በዚህ የተነሳ፣ “ማንዴላን በማሳበጥ የመለስ ራእይ አይሟሽሽም” ብለው ጽፈዋል። እናንተ በየጊዜው የነበራችሁ የህወሓት አመራር አብሎችና አባላት ሆይ፣ መሪዎቻችሁ የፈጸሙት ግፍና ግድያ ለናንተ ደስታ ይሰጣችኋል። በትግልና በአመራር ዘመናቸው ዘርፈዋል፣ በሙስና ተጨማልቀዋል፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለስደት፣ ለረሃብና ለሰቆቃ ዳርገዋል። እናንተም የዚህ ሁሉ ግፍ ተሳታፊዎች ናችሁ። ድርጊታችሁና ታሪካችሁ በደም የተጨማለቀ መሆኑን ዘንግታችሁ መለስ ዜናዊን ከኔልሰን ማንዴላ ጋር ማወዳደራችሁ በጣም አሳፋሪ ነው። በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት የሰማይና የምድርን ያክል ነው። ባለፉት ጽሑፎቼ እንደገለጽኩት፣ አጠር ባለ መልኩ፣ ሕወሓት ኢትዮጵያን ተቆጣጥሮ ያለ ድርጅት ነው። ስርዓቱም ፋሽስት፣ አምባገነን፣ ጠባብ ዘረኛ፣ ሽብርተኛ፣ ጸረ-ኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ጸረ-ኢትዮጵያ ሕዝብና የባእዳን ቅጥረኛ ነው። ከ1969 መጀመሪያ ጀምሮ በትግራይ ሰላማዊ ዜጋ ላይ ግድያውን አቀጣጠለው። ግድያው ሳያንሰው ሃብትና ንብረቱም ተወረሰ። ከደደቢት በረሃ የጀመረውን አማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው በማለት በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች አማራውን በመጨፍጨፍ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል። ለሴቶች በግዳጅ የማምከኛ መድሃኒት በመስጠት የአማራው ቁጥር እንዳይጨመር አድርገዋል። ከኖርበት ቀየውና መሬቱ በግዳጅ እንዲፈናቀል አድርገዋል። ህወሓት ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ ከ1985 መጀመሪያ ጀምሮ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ሰፊ የጥቃት ዘመቻ በመክፈት የግድያ፣ የቤት ማቃጠል፣ ንብረቱን መዝረፍና ከፍ ያለ ሰቆቃ አድርሶባቸዋል። እንደ አማራው ሁሉ ከመኖሪያ ቦታውና ከመሬቱ ላይ ተፈናቅሏል። የኦነግ አባል ናችሁ እየተባሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ያለምንም የፍርድ ውሳኔ ወደ ወህኒ ወርደዋል። በየቦታው በከፍተኛ ትምህርት ተቋሟት የሚማሩት የኦሮም ልጆች ከትምህርታቸው ተባረዋል። የተባረሩትም፣ መባረራቸው አልበቃ ብሎ ለእስር ተዳርገዋል። ደጉና ሩህሩሁ የኦሮሞ ሕዝብ ከእርሻው ተፈናቅሎ የረሃብና የበሽታ ሰለባ ሆኗል። ህወሃት በጋምቤላ አኝዋኮች ላይ በፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ተጠያቂ ነው። ሕዝቡ ከመሬቱ ተፈናቅሎ አብዛኛው በጎረቤት ሃገሮች ስደተኛ ሆነው በየሃገሩ እየተንከራተተ በችግር ላይ ነው። የኦጋዴን ሕዝብም የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሞበታል። ቤት ንብረቱ በህወሓት ወታደሮች ተቃጥሎበታል። ሴት ልጆቹና ሚስቶቹ ተደፍረውበታል። በተጨማሪም ከመሬቱ ላይ ተፈናቅሎ ለስደት ተዳርጓል። የአፋር ሕዝብም በሌሎቹ የኢትዮጵያ ጎሳዎች የደረሰው ደርሶበታል፣ እየደረሰበትም ነው። የኢትዮጵያን ሕዝብ ከማሰቃየት ባለፈ ደግሞ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለሱዳን መንግሥት ሸጠዋል። ሃገሪቱን ካለባህር በር አስቀርተዋል። የሃገር ሃብትና ታሪካዊ ቅርሶችን አውደመዋል፣ ሸጠዋል። ጊዜው ሲደርስ በኢትዮጵያ ሕዝብና በሃገሪቱ ላይ ለፈጸማችሁት ወንጀል ለፍርድ ያቀርባችኋል። ውድ የትግራይ ሕዝብ ሆይ!! ተሓህት ደደቢት በረሃ እንደወረደ በየሰበብ አስባቡ በየቤተ ክርስቲያናት እየመጡ፣ የትግራይ ሕዝብ በደመኛ ጠላትህ በአማራው የተጠቃህ ነህ። ነፃ የነበረችው ትግራይ ሃገርህ ወድቃልችና ተነስ። ከመሪ ድርጅተህ ተሓህት ጎን ተሰልፈህ አማራው ጠላትህን ደምስስ፣ ሲሉህ የሰጠኸው መልስ፣ አማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት አይደለም፣ ሆኖም አያውቅም፤ አብረን ተባብረን እና ጎን ለጎን ተሰልፈን፣ በአድዋና በማይጨው ጦርነት ጠላት የደመሰስን እና በደማችን አንድ የሆንን ኢትዮጵያውያን ነን። የአማራ ጠላት የሚባል አናውቅም። ትግራይ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያም ትግራይ ናት፣ የቅኝ ግዛት አይደለችም። ስለዚህ ኢትዮጵያዊነታችንን የሚነፍገን ምንም ሃይል አይኖርም። ድርጅታችሁ ትሓህት የምትሉትንም አናውቀውም፣ አንቀበለውም ብለህ መልሰሃል። ይህንን ዓላማቸውን ለማዛመት በየቦታው የተንቀሳቀሱት የተሓህት መሪዎች በሁሉም ቦታ ተመሳሳይ ተቃውሞ ገጠማቸው። ተቃውሞው በሁሉም ከተሞች ሲበዛባቸው በብስራት አማረ የሚመራው የፈዳያን ቡድን በጠራራ ፀሃይ ሕዝቡን ፈጀው። ከየከተማው ሰዎችን እያጋዙ በየእስር ቤቱ እያጎሩ ገደሉት። የገጠሩን ሕዝብ ደግሞ ‘ትግራዋይ ሸዋዊ’ (የትግራይ ሸዋ)፣ ፊውዳል፣ ጸረ-ትሓህት፣ ጸረ-ኤርትራ ትግል ወዘተ. በማለት በውሽት በመወንጀል በቀንና በሌሊት በአፋኝ ቡድን እየተያዘ፤ ሃብት ንብረቱ እየተወረሰ ሃለዋ 06 ተወረወረ። እዚያም ገብቶ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩት እንደተገደሉ አንተው እራስህ የምታውቀው ሃቅ ስለሆነ ምስክር አያስፈልግህም። ልጆችህ በተሓህት እየታፈኑ ወደ ሜዳ ወጥታችሁ ታገሉ እየተባሉ ብዙ ሺዎች ወንድና ሴት ልጆችህን ለሻእቢያ አሻግሮ ሸጠብህ። በቀይ ኮከብና በተለያዩ ዘመቻዎች ለሻእቢያ ተሰልፈው በማያውቁት የኤርትራ በረሃ ማለትም በሳህል፣ አቁርደት፣ ከርከበት፣ ናቅፋ፣ ሰሎሞና ወድቀው ቀሩብህ። በወቅቱ አንተው የትግራይ ሕዝብ ተሓህት/ህወሓትን በግለጽ የተቃወምከውና ያወገዝከው ስለነበረ መስካሪ አያሻህም። ኢትዮጵያዊነትህን እና ለሰንደቅዓላማዋ ያለህን ፍቅር አስመስክረሃል፣ ታሪክም ዘግቦታል። ውድ የትግራይ ሕዝብ ሆይ፤ የህወሓት አመራሮችን ማንነት ጠንቅቀህ ታውቃለህ። ዛሬ ኢትዮጵያ ሃገራችን በሰቆቃና በችግር ውቅያኖስ ውስጥ ሰምጣለች። ይህ የሆነበት ምክንያት የህወሓት መሪዎች ኤርትራውያን እና የትግራይ ባናዳዎች ተሰባስበው በህወሓት ስም ሃገር አውድመዋል። ባንተ ስም ብዙ ሸቅጠዋል። በስምህ የመጣውን ሰፊ እርዳታ የህወሓት መሪዎች ዘርፈው ሸጠዋል። ይህም ካንተ የተደበቀ አይደለም። ወያኔ በጠነሰሰው ተንኮል በጠራራ ፀሃይ ያለረህራሄ በቦምብ ተደብድበሃል፣ ይህ ነው የማይባል የሰውና የንብረት ውድመት ደርሶብሃል። ከኢትዮጵያውያን ወገኖችህ ጋር ቅራኔ ውስጥ ሊከቱህም ብዙ ጥረዋል። በቆራጥ ኢትዮጵያዊነትህ ቁጣህን በማሳየት የወያኔ መሪዎችን አሳፍረሃቸዋል፣ አሁንም በርታበት፣ ቀጥልበት። የህወሓት መሪዎች 40 ዓመት ሙሉ አሰቃይተውሃል፣ አሁን በቃኝ በል። ከኢትዮጵያዊ ወገነህ ጎን ተሰልፈህ ግንባር ቀደም በመሆን ይህንን የህወሓት ገዳይና ሽብርተኛ ቅጥረኛ ፋሽስት ስርዓት በተበባረው ሕዝባዊ አመጽ መቃብር አስገብተን የኢትዮጵያን ሉአላዊነት፣ አንድነታችንን እና ነፃነታችንን እንጎናጸፍ። የተከበርክ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ፤ ሰላማዊ ትግል እያልን ጊዜ አንስጠው። የተጀመረውን ሕዝባዊ ቁጣ በማቀጣጠል እጅ ለእጅ ተያይዘን በሕዝባዊ ማእበል ወያኔን ደምስሰን ሃገራችን ኢትዮጵያን ነፃ እናውጣት። የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ለመስዋእትነት ቁርጠኛ ሁናችሁ ውጡ፣ ሕዝቡን ምሩት። በውጭ ሃገር ያለህ ኢትዮጵያዊም የትግሉ የጀርባ አጥንት ስለሆንክ አስፈላጊውን ሁሉ ለማቅረብ ተዘጋጅ። በበረሃ ያላችሁ የትጥቅ ታጋዮችም ውጡ፣ የፋሽስቱን የወያኔ ሰራዊት በምታውቁት የውጊያ ስልት አጥቁት። የኢትዮጵያ ሕዝብ ያልተቆጠበ ድጋፉን ይሰጣችኋል። ጊዜው አሁን ነው፣ ሕዝቡም የናንተው ነው።
2
የወያኔ ዘረኛ፣ መድልኦዊ የአምባገነን አገዛዝ ኢትዮጵያ አገራችንን የባሕር በር አልባ ያደረገ፣ መሬታችንን ለሱዳን አሳልፎ የሰጣ፣ አንዲሁም የአገሪቱን ለም መሬቶች ለባዕዳን ፣ ለአራብ፣ለሕንድ፤ ለቱርክ፣ ለማሌዢያ፣ --- ወ.ዘ.ተ ለብዙ ዓመታት ከመቸብቸብ አልፎ ገንዘቡን የበላ፣ የአገሪቱ የስልጣኔ ምንጭና እድገት መሰረት የሆነውን ትምህርት ለመግዳል ባለው መሠሪ ዓላማ ትውልድ ገዳይ የትምህርት ፖሊሲ በባለሙያዎች ሳይሆን በካድሬዎቹ አማካይነት አንዲቀረጽ በማድረግ ትምህርት ላይ ትልቅ ወንጀል የፈጸመ፣ የአገሪቱን ታሪክ ለማጥፋት ባለው ቁርጠኛ አቋሙ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በኮሌጆች፣ በሀለተኛ ፣ በመለስተኛና በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የታሪክ ትምህርት እንዳይሰጥ ወይም የውሸት ታሪክ ትምህርት እንዲሰጥ ያደረገና በሕዝቡ ዘንድ ተወዳጅ ከሆኑት ከድርጅት መሪዎች እስክ ግለሰብ ድረስ የገደለና ያስገደለ የማፊያ ቡድን ነው። በነዚህ ታላላቅ አገራዊ ወንጀሎችና ክህደት ነው ወያኔ ጸረ-ኢትዮጵያ፣ ጸረ-ኢትዮጵያዊነትና ጸረ-ሕዝብ ነው የተባለው። ይህን የክህደት ተፈጥሮአዊ ተግባሩን ወያኔ ከስልጣን በሕዝብ ትግል እስከሚወገድ ድረስ ይቀጥላል እንጂ ይተዋል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው። ወያኔና ተባበሪ ተላጣፊ ድርጅቶች በስብሰናል የኢትዮጵያ ሕዝብን ይቅርታ እንጠይቃለን ያሉቡት ቃል ውሎ ሳያድር መሰሪው ወያኔ የአስቸኳይ ጊዚያዊ አዋጅ በማወጅ ቅዳሜ መጋቢት 1 ቀን 2010 ዓም በደቡቡ የአገራችን ክፍል በቦረና ዞን በሞያሌ ከተማ የወያኔ አጋአዚ ነፍሰ ገዳይ ጦር ቤት ለቤት በማሳስ፣ በመንገድ ላይ ሰላማዊ እንቅስቃሴ በሚያካሄዱ ዜጎቻችን፣ በቡና ቤት፣ በሻይ ቤቶች ፣ በገበያና በሱቅ ሆነው መደበኛ ስራቸውን ሲያከናውኑ በነበሩ የ7 እና የ10ዓመት ህፃነትን ጨምሮ ከ13 በላይ ዜጎችን አልሞ በመተኮስ በግፍ ሕይወታቸውን አጥፍቷል። በርካቶችንም አቁስሏል። በዚህ የግፍ ግድያ ወቅት የሙያ አጋራችን የሆነው በ2008 ዓም በኦሮሚያ ክልል በትምህርት ቤቱ ውስጥ ላበረከተው ትልቅ የትምህርት ስራና ላሳያው የሙያ ስነምግባር ሁለተኛ ደረጃ ተሸላሚ ፣ በአካባቢው ሕዝብ፣ በትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ተወዳጅ ፣ የአንድ ልጅ አባት ፣ የ34 ዓመት ጎልማሳ ርዕሳ መምህር የነበረው/የሆነው ታምሩ ነጌሶ በእረፍት ቀኑ ቅዳሜ መጋቢት 1 ቀን 2010 ዓም ጊዜውን ሰውቶ በመዶ ሚጎ ት/ቤት ውስጥ ከተወሰኑ መምህራን ነገር ያደርገው የነበረውን የትምህርት ስራ ጨርሶ ወደ ቤቱ ሲመለስ መንገድ በማቋረጥ እያለ የአግኣዚ ነፍሰ ገዳይ ጦር በሶስት ጥይት ደብድቦ ሕይወቱ እንዲጠፋ አድርጓል። ይህን የወያኔን የግፍ ግድያና የጅምላ ጭፍጨፋ በመሸሽ ከ60ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ጎረቤት አገር ኬኒያ ሊሰደዱ በቅተዋል።የወያኔን ዘረኛ ድርጊት የሞያሌ ከተማ ካንቲባ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት ሠራዊቱ የባእድ ጦር እንጂ የኢትዮጵያ አይመስልም ብለዋል። ታዲያ በዚህ ድርጊቱ ወያኔ ኢትዮጵያዊ ነው? ለኢትዮጵያ ሕዝብ የቆመ ነው? ቀደም ሲልም በተለያዩ ቦታዎች ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያዉያንን ከትውልድ ቄያቸው ክኖሩበት ስፍራ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን እንዲፈናቀሉ ያደረገ ፀረ-ሕዝብ ዘረኛ ቡድን ነው። ላለፉት 27 ዓመታት ወያኔ ኢትዮጵያዊ አይደለም የተባለው እነሆ ዛሬ ገሀድ ወጣ። ሰላማዊ ሕዝብ በወያኔ ሠራዊት በጠራራ ጸሐይ በጥይት እየተደበደበ ይገኛል። በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ ይህን የወያኔን በቦረና በሞያሌ ከተማ ህዝብ ላይ የፈጸመውን አራማኔያዊ ግድያ፣ በሕዝብ ላይ ያደረሰውን የአካል ማቁሰልና ጉዳት፣ ማፈናቀልን በጥብቅ ያወግዛል፤ ይኮንናል። እንዲሁም በሌሎች ቦታዎች በጎንዳር፣ በወልቂጤ፣ በነቀምት፣ በደምቢዶሎ ---ወ.ዘተ በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ግድያ፣ አስራት፣ የመሬት ቅሚያ፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት ብክነትን፣የተማሪዎችና የመምህራን እስርን፣ የአካዳሚክ ነፃነት መታጣትን በጥብቅ ይቃወማል። በአሁኑ ሰዓት የወያኔ አገዛዝ ከምንጊዜውም በላይ በፖለቲካ ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ቀውሶች ውስጥ ተዘፍቆ ይገኛል። የሕዝቡ በወያኔ አልገዛም፣ እምቢ አሻፈረኝ በማለት የጀመረውን ሕዝባዊ ሰላማዊ ትግል፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ፣ ከቀን ወደ ቀን እያደገ የመጣበት፣በወያኔና በኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል ያለው ቅራኔ ከመክረሩ የተነሳ ሊበጠስ የተቃረበበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። በሌላ በኩል ደግሞ የወያኔ አገዛዝ እንደቀድሞው ሊገዛ ያልቻለበት በሁሉም መስክ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተቀባይነትን ያጣበትና እየተዳከመ የመጣበት ሁኔታ ይስተዋላል። እኩል ባልሆኑ ኃይሎች መካከል የእኩልነት ሁኔታ የተፈጠረበት ክስተት ነው( equilibrium between unequal forces)። ለስርዓት ለውጥ ነባራዊ ሁኔታዎች የተሟሉበት ነገ ግን ይህን የሕዝቡን ትግል ከዳር ለማድረስ ህሊናዊ ሁኔታዎች ያልተሟሉበት በሂዳትም ክፍተቱን ለመሙላት ትግል እየተካሄደ ያለበት ሁኔታ ላይ ደርሰናል። የሕዝቡ ጥያቄ ከአካባቢ የውስጥ ጥያቄዎች በመዝለል አገራዊ ቅርዕ እየያዘ የመጣበት ሁኔታ ይታያል።ወያኔ በቃ፣( down down woyane) ወያኔ ይወደም ፣በወያኔ አንገዛም ፣ ሁሉንም ያካተተ የሽግግር መንግስት ይቋቋም ፣ የአዋጅ ጋጋተ የሕዝቡን ትግል አይገታም፣ ስር ነቀል ለውጥ ይደረግ ወያኔ ይወገድ የሚሉ ሕዝባዊ መፈክሮች በስፋት እየተስተጋቡ ይገኛሉ። የቀረው ይህን ወሳኝና ወቅታዊ መፈክሮችን በማንገብ በየአቅጣጫው በሁሉም ስፍራ እየተፋፋመ ያለውን የሕዝቡን እምቢተኝነት የአልገዛም ባይነት እርምጃዎችን ከግብ ለማድረስ ትግሉን ማስተባበርና ማስተሳሰር ነው። ለጋራ ጥያቄ የጋራ ትግል ያስፈልጋል። ስለዚህ በተለያዩ ቦታዎች በተለያዩ ስሞች በግንበር ቀደምተኝነት ትግሉን የሚካያሄዱ ወጣቶች በጋራ-በህብረት እንዲነሱ ማድረግና መርዳት የጊዜው ጥያቄ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ የሁላችንም ናት ከወጣቶቹ ጎን ሁላችንም መቆም አለብን። ለወጣቶቹ የቅርብ አጋዥ ኃይል መምህራን ናቸው። መምህራን በ1966ቱ አብዮት ወቅት ከወጣቶች ጎን በመቆም ለለውጡ መወለድ አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ሁሉ ዛሬም የትግል ልምዳቸውን በመጠቀም በሰሜን በደቡብ፣ በምስራቅ በምዕራብ እንዲሁም በመሐል አገር እየተቀጣጠለ በወጣቱ ግንባር ቀደምተኝነት የሚካሄደውን ትግል አገር አቀፍ ቅርዕ እንዲይዝ ማስተባበርና ማያያዝ ታሪካዊ ግዴታቸው ነው።መምህራን በሁሉም ቦታ የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ትግሉ ይበልጥ ጉልበት እንዲያገኝ የድርሻቸውን እንዲወጡ በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ በዚህ ወሳኝ የትግል ወቅት ጥሪውን ያቀርባል። እንናገራለን እንጂ አንማታም የ ገር ፍቅር ከሰዎች ፍቅርና ከሰው ሰውኛ ጉዳዮች ይነጥላል እንዴ?የህወሓት አካል የሆኑት የኦህዴድና የብአዴን ሞግዚቶች ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ስብከት የ መሩት ትንሽ ሰነባብቷል።ሰውየውከአነጋገሩ ክትነትና ከሚሰጠው ጣዕመ ምስጢር የተነሳ ሲሰሙትና ሲያዳምጡት ቢውሉ ቢያድሩ አይሰለችም ምክኒያቱም የኢትዮጵያ አንድነት ሲጠራ ደስ ይላል።ነገር ግን ኢትዮጵያን በመጥራት ብቻ ያለ ትግበራ ይሆናል እንዴ?እኔን ግራ የገባኝ ከ27 ዓመት በኃላ የኢትዮጵያ አንድነት የሚለው አባባል ያውም በባህር ዳር ስብሰባ ላይ ታሪክ ራሱን ይደግማል ተብሏል። ሲደግም ግን መቸም ቢሆን ያለፈው መቶ በመቶ ቅጂ እንደማይሆንም እንዲሁ ተነግሯል። የኅብረተሰብ ዕድገት ሕግ የሁኔታዎችን ለውጥ ግድ የሚል ነውና ታሪክ መመሳሰሉ አንድ ነው የሚያስብል አይደለም ።የአንድ ሀገር ሁኔታም ከሌላው ተወራራሽና ተመሳሳይ--ወይም አንድ ወጥ- ሊሆን እንደማይችልም የታወቀ ነው። የጅምላ ድምዳሜ ወደ ስህተት ሊያመራ የሚችል መሆኑን መገንዘብ የሚገባው ለዚህ ነው። ለዚህም ነው የየካቲትን አብዮት መደናቀፍ ካለፉ መፈንቅሎች ጋር ለማመሳሰል ሆነ በግፍና አምባገነንነት፤በአረመኔነትንና በፋሺስትነት ያላቸው መመሳሰል እንዳለ ሆኖ የወያኔን የስልጣን ንጥቂያ ከ 66ኡ የሻለቆች አብዮትን ማጅራት ምት ጋር አንድ ማድረጉ የማይቻለው። የየካቲት አብዮት ጽኑ መሠረትና ምክንያት ይዞ የፈነዳ ቢሆንም ግቡን ስላልመታ ከሚቀርቡት አሉታዊ ትችቶች አንዱ ጊዜው አልነበረም የሚል ነበር ። ዛሬም የወያኔ አገዛዝ በሞት አፋፉ ላይ ደርሶ ባለበት ሁኔታ ለመተካት የተዘጋጀ ኃይል የለምና ውድቀቱ ወቅታዊና ጠቃሚ አይሆንም የሚሉ ብቅ ብቅ እያሉ ነው ። በቅድሚያ ማጤን ያለብን አቢይ ጉዳይ አብዮት ወይም ስር ነቀል ለውጥ ወይም የሥዓአት ቅየራ የሚመጣው በማንም ውሳኔ ሳይሆን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት ሕዝብ በሚያደርገው ትግል ወይም አመጽ ነው። ትግል ወይም የአብዮት ፍንዳታ አልተዘጋጀንምና ቆይ ተብሎ ሊታገድ የሚችል አይደለም ። በውስጥ ውስጥም ሆነ በብቅ ጥልቅ ለዓመታት ሲግም ሲያስገመግም የቆየውን የአብዮት ፍንዳታ በሚያጎመራ ጊዜ ግብታዊ የሚል የተሳሳተ ቅጽል መስጠት የተለመደ ቢሆንም የአብዮት ፍንዳታ--የሕዝብ አመጽ ወቅቱን ጠብቆ የሚመጣ ነው ። ለምሳሌ በቦልሼቪክ ፓርቲ መሪነት የተካሄደው ታላቁ የሩስያ አብዮት ከመፈንዳቱ ስድስት ወር በፊት ሌኒን ራሱ ሁናቴዎች ገና ናቸውና ብዙ መስራት አለብን ያለው ሊጠቀስ የሚችል ሲሆን አብዮትን የሚጠብቁትም ቢሆን መቸ እንደሚፈነዳ አያውቁም የሚለውን አስተሳሰብ ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ ይሆናል። የየካቲት አብዮት ሲፈነዳ የህቡዕ እንቅስቃሴ በማድረግና ድርጅቱን በመገንባት ተግባር ተጠምዶ የነበረው ኢሕአፓ ገና ሁለት ዓመቱ ነበር ። በወቅቱ በተቻለው መጠን ትግሉን ሊያጠናክርና አቅጣጫ ሊያስይዝ ቢሞክርም የደርግን መፈንቅለ መንግሥት ሊያግድም ሆነ የድል ቅሚያውንም ሊያስቆምና ሊያከሽፍ አልቻለም ። ሆኖም የሕዝብ ጥያቄዎች መሠረታዊ ነበሩና፤ በወቅቱ ምላሽም ያገኙ አልነበሩምና ጸረ ደርጉን ትግል በስፋት በማካሄድና ትግሉን በመቀጠል ታሪካዊ ምዕራፎችን ጽፏል ። በቅድሚያ በመሠረቱ እስካዛሬም ምላሽ ያጣው የሕዝብ ጥያቄ ዴሞክራሲ ለሰፊው ሕዝብ አለገደብ የሚል ነበርና የደርግ ሕገ ወጥ ሥልጣን ይህንን መሠረታዊ ፍላጎት ተጻሮ የቆመ ሆነ ። ደርግ ዴሞክራሲን ማፈን ብቻ ሳይሆን ያሰበና ያሳሰበ ወንጀለኛ ነው ብሎ አፋኝ አዋጆችን አዥጎድጉዶ የግፍ አገዛዙን ጀመረ ። በዚህም የተባበሩት ሁሉ ወደዱም ጠሉም --ዛሬ ለወያኔ ተባባሪዎች እንድምንላቸው ሁሉ--የወንጀሉ ተባባሪ ሆነው አልፈዋል ። ቀጥሎ የተከሰተውን ሁሉም የሚያውቀው ነው። የየካቲት አብዮት ለምን ፈነዳ ? አብዮት በዘፈቀደና በአልባሌ ምክንያቶች የሚፈነዳ አይደለም ። ታምቆ ቢቆይም፤ ውስጥ ውስጡን እንደ እሳተ ገሞራ ቢያጉረመርም አብዮት የቆዩና መሠረታዊ የሕዝብ ቅራኔዎች ነጸብራቅና ፍንዳታ ነው። ፍናዳታው እውን ይሆን ዘንድ ሕዝብ አልገዛም በቃ ብሎ መነሳት አለበት። ገዢው መደብም እንደበፊቱ እንዳፈተተው ተንደላቆ የሚገዛበት ሁኔታ መዳከም ይገባዋል ። ሕዝብም በተወሰነ ደረጃ ለማመጽ ድፍረትን ኅብረትን ማግኘት ይኖርበታል ። እነዚህ ሁኔታዎች ሲሟሉና አብዩት ሲፈነዳ ለድል አስፈላጊ ሆኖ የሚገኘው የድርጅትና የኅብረቱ ጥያቄ ይሆናል። በየካቲት 66 ይህን ሁኔታ ከማሟላት አኳያ ግልጽ ድክመትና ጉድለት ነበርና ደርግ የተባለው የታጠቀ አድሃሪ ቡድን የሕዝብ ድል ሊቀማ ቻለ ። የቻይናም፤የሩስያም፤ የካቲትም ሁሉ አለጊዜያቸው የመጡ አብዮቶች ተብለዋል ። አብዮትን ማቆየትና ማስወገድም የሚቻለው በሥልጣን ያለው ሥርዓት መሠረታዊ ለውጥ ካደረገ ብቻ ነው ። አድሃሪ አገዛዞች ይህን ማድረግ ካልቻሉ አብዮት አየቀሬ ነው። አጼ ኃይለሥላሴ የለውጥን አስፈላጊነት ሊረዱ ባለመቻላቸው፤ መሠረታዊ ለውጥ ለማካሄድ ፈቃደኛ ሊሆኑ ባለመቻላቸው፤ ለመጣው አመጽ ማብረጃና ማስተንፈሻ የሚሆን ባለማቅረባቸው አብዮቱ ፈነዳባቸው ። መሬት ለአራሹ፤ ሕዝባዊ መንግስት፤ዴሞክራሲ አለገደብ ለጭቁኖች፤ ሉአላዊነት ለኢትዮጵያ፤ እኩልነት በሁሉም መስክና ፍትሐዊ አስተዳደር የሚሉትሕዝባዊ ጥያቄዎች--እንኳን ያኔም ዛሬም ቢሆን መፍትሔ ያገኙ አይደሉምና-- በዚህ የተነሳ አብዮት መፈንዳቱ ጊዜውና ወቅቱ ነበር ። ያን ትውልድ አብዮት አመጣብን ብለው የሚያወግዙትና የሚያላዝኑበት አንድም የወዳቂው ሥርዓት ተጠቃሚዎችና አዳናቂዎች ሲሆኑ በሌላም በኩል የለውጥ ተጻራሪዎች መሆናቸው ከወዲያው ታውቆ የተወገዙበት ነው ። ያን ሥርዓት እየጎዱትና ለውድቀት የዳረጉት ራሳቸው የሥርዓቱ ባለቤቶች ናቸው ። ወቅቱ የጠየቀውን ለውጥ ቢያደርጉ ኖሮ ሂደቱ ሌላ በሆነ ነበር ። የተቃዋሚዎቹ መፈክሮች ምላሽ አግኝተው አቀጣጣይነታቸውና አብዮት ቀስቃሽነታቸውም ባለተከሰተ ነበር ማለትም እንችላለን ።ለአንገብጋቢ የሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጠተው በነበር የየካቲት አብዮት ባልመጣባቸው ነበርም ማለት እንችላለን። የየካቲት አብዮት ሊከሰት የቻለባቸውና በኋላ የአብዮቱ መፈክሮቹ የሆኑት ዋና ዋና ጥያቄዎች ዛሬም ምላሽ ያላገኙ ጉዳዮች ናቸው ። አብዮቱን ካቀጣጠሉት ዋና ዋና ጥያቄዎች መከካል መሬት ለአራሹ፤ ዴምክራሲ ለጭቁኑ፤ ሉዓላዊነት ለኢትዮጵያ፤ ሕዝባዊ መንግስት ወዘት የሚሉት ይገኙባቸዋል። ምላሽ ባለማግኘታቸው ትግሉ ቀጠለ ። እስከዛሬ። እነዚህ መፈክሮችና ጥያቄዎች ደግሞ የሕዝብ ብሶት አንጽባራቂ ነበሩና፤ ችላ ተብለው ከርመው ቆይተዋልና በነበረው ተጨባጭ ሁኔ ታ ሕዝብ በቃኝ ብሎ ምላሽ ሊጠይቅ ሲነሳ--አብዮት ሲፈነዳ-- ገዢው ቡድን ወራጅ አለ ተብሎ ሊጨብጠው ሊይዘው ተስኖት ሲወጠር እውን የሆነው እውነታ ተጨባጩ ሁኔታ ያመጣው እንጂ የተወሰኑ ተራማጅ ወጣቶች ከብብታችው ስበው ያወጡት ክስተት አልነበረም ። ያ ትውልድ የተበላሹ ገዢዎችና ሥርዓቶች ያመጡትን ሀገራዊ ችግር ተጋፍጦ ለችግሮቹ መፍትሔ ለመሰጠት ጥረት አደረገ እንጂ ያልነበረን ችግር ፈጥሮ ሊያሰፍን አልተንቀሳቀሰም ። ለምንስ ማለቱ ቦታው ነው ። ምን ሊጠቀም? ምን ሊፈይድ ? ለተረከበው ችግር መፍትሔ ለማግኘት ሲነሳ ስህተት ፈጸመ በሚል ሊወቀስ ቢችልም የችግሩ ፈጣሪ ግን ከቶም የሚሆን አይደለም ። የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ በተመለከተ ምን መደረግ ነበረበት ለሚለው ወሳኝ ጥያቄ ምላሽ ሊሰጥ የጣረው ትውልድ ሊወቀስ ሳይሆን ሊመሰገን የሚገባው ሲሆን ለአቅዋሙ ደሙን ያፈሰሰ በመሆኑ ማንም--በተለይም ሀገርን ለመታደግ ትንሿን ጣቱንም ያላንቀሳቀሰው--ሊወቅሰው ሊያወግዘው የሚችልበት የሞራል የበላይነት የለውም ። ለማንኛውም ሀገር ገንቢ መንገድን የቀየሰው ትውልድ ዕድል ተነፍጎት፤ ታፍኖና ተጨፍጭፎ በመገኘቱ ለሀገራችን የነበረው ብሩህ ተስፋ ከስሞ ደርግ የተባለው መርገም በሀገራችን ላይ ሰፍኖ-- ከርሞብን፤ ለወያኔ ጨለማ አሳልፎም ሰጥቶናል፤ዳርጎናል ። በዚህ ረገድ ወያኔ የደርግ ውላጅ ነው ማለቱ አከራካሪም የሚሆን አይደለም። " የስድሳ ስድስቱ የኢትዮጵያዊ አብዮታዊ ትውልድ በብሔርም ሆነ በሃይማኖት ሳይከፋፈል ባንድ ላይ ተባብሮ የቆመው ለሀገሩና ለዜጎቿ መልካምን በማሰብ ነበር። ለዚህም አይከፍሉ መስዋዕትነት ከፍሏል ። ያ ሁሉ እንደ ቅጠል የረገፈው ምሁርና ወጣት ለሀገሩ የነበረው ራዕይ በብሩህ ተስፋ፤ በሀገር አንድነትና በሕዝብ እኩልነት ላይ የተመሠረተ ነበር ። ታዲያ ከደርግ ባለስልጣኖችና ጀሌዎች ይህንን ለኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ አንግቦ የቆመውን አዲስ ትውልድ እየጨፈጨፉ ኢትዮጵያን ለመከፋፈልና ለመቆራረስ ዓላማ አድርጎ የተነሳውን ጠባብ ብሔረተኛ ድርጅት ሰተት ብሎ አዲስ አበባ በመግባት ዓላማውን በተግባር እንዲተረጉም ዕድል ሰጡት ። ወደዱም ጠሉት በተጨባጭ ተባበሩት ። በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የመረጃ ሰነዶች እንደሚመሰክሩት ሕሊናቸውን በመሸጥ ከወያኔ ጋር ተባብረው የውስጥ መረጃ በማቀበል አሳፋሪ ድርጊት የፈጸሙት የደርግ ባለሥልጣናት ቁጥራቸው ጥቂት አይደለም። እነኚህ ደግሞ ለሀገር የቆመውን ኃይል በማጥፋት ብቻ ሳይወሰኑ ተተኪውን ትውልድም ጭምር እያወደሙ፤ኢትዮጵያን ለአውዳሚ ተምች አሳልፈው አስረክበዋል ። ይኽም ደግሞ ከጠፉም በኋላ የጥፋታቸው ጠንቅ እንዲቀጥል ሆኗል ። የኢትዮጵያን ጉዳይ የኋላ ልጅ ይጨነቅበት እንዳይሉ እንኳ የኋላ ልጅ እንዲተርፍ አላደረጉም ። መጪው ትውልድ በጠፋበት ኃላፊነት ይሰጠው ቢባል እንኳን የሚለጋለት ሀኬት ሊኖር አይችልም--አልቋልና ። ለአንድ ህገር ከሚወረሱት ውርሶች መካከል የኋላ ልጅ ይጨነቅበት የሚባለው ነገር፤ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል እንዳትችል የሚደረግ ጠላትነት ነው ። በግድ ኢትዮጵያ ሀገራችን የነገን ተረካቢ ትውልድ እንድትፈጥር ዕድል ሊሰጣት ይገባል"። ደርግ ተብዬው ይህን ዕድል አልሰጣትም--ወያኔ ለሚባል በሽታ ዳረጋት እንጂ ። በየካቲቱ ትውልድና በአብዮቱ ላይ ሊጨፍሩ የተነሱ የወያኔ አጋሮችና የደርግ የወንጀል ተካፋዮዎች አብዮቱ ያነሳው ጥያቄ ሁሉ ከመስመር ውጪ ነው ወይም በደፈናው የሆነ ርዕዮተ ዓለም ጭፍን ነጸብራቅ ነው ሊሉ እስካዛሬ አልተቻላቸውም ። ፊውዳሊዚም ይውደም፤ መሬትም ለአራሹ ይሁን መባሉ አግባብ አልነበረም ካላሉ በስተቀር ። የዘውድ አገዛዝ ተገርስሶ ሕዝብ የዴምክራሲ ባለቤት መሆኑ ሐጢያት ነው ለማለት ካልደፈሩ በቀር ። የእኩልነት ጥያቄ ሲነሳም በየዘርፉ ጭቆና መኖሩን በወቅቱ የነበረው ተጨባጭ ሁኔታ በሀቅ የሚመሰክር ሲሆን ይህንን መካድ የሕዝብን መብትና ፍላጎት መጻረር ካልሆነ በስተቀር ሌላ ትርጉም አልነበረውም ። የሀገራችንም ሉዓላዊነት ይከበር የሚለው ጥያቄ ያኔም ዛሬም እንደሌሎቹ ጥያቄዎች ሁሉ ምላሽ አጥቶ የሀገራችንን ችግሮች ገላጭ ሆኖ ይገኛል ። እናም የካቲት ጊዜውን የጠበቀ አብዮት ነበረ ። ያ ትውልድም ግዳጁን ተሸክሞ ከፍተኛ ዋጋን ከፍሎ ሀገሩን ሊታደግና አብዮቱንም ሊያስከብር መነሳቱና አልፎም የህይወት መስዋእትነት መክፈሉ የሚደነቅ እንጂ የያኔ ፈርጣጮችና የወንጀል ተባባሪዎች ዛሪ እንደሚጥሩት የሚወቀስ ከቶም አልነበረም፤አይደለምም ። የየካቲት አብዮት የሕዝብና የሀገርን አንድነት መሠረት አድርጎ የፈነዳና የተካሄደ ነው ። ቀን ሲደርስ አምባ ይፈርስ ነው ። በሁኔታው ሂደት የሕዝብ ኃይሎች ተጠናክረው አብዮቱን ሊጠብቁ ባልመቻላቸውና ድል በመቀመታቸው ዛሬም በተስፋ ቆራጭነት በመጠቃት ድል እንቀማለን ብሎ ሙሾ ከወዲሁ ከመደርደር ድላችንን የማንቀማበትን ቅድመ ሁኔታ ጸንቶ ማዘጋጀት እንዳለብን ታሪክም ያስተምረናል ። ለማንኛውም የታሪክ ግዳጁን ተቀብሎ ውድ ህይወቱን ለሀገሩ የሰጠውን ትውልድ እንደ አርአያ በመቀበል ፈንታ ወደ 40 ዓመት ታሪክ ተመልሶ --ያውም የተከለሰን ታሪክ በማቀንቀን- ያውም ያንን ትግል የሚያስንቅ ምንም ዓይነት ግብግብ ሳይታይ- - ወቀሳና ውግዘት መደርደር የሚያስገምት እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም ። ከዚህ ባሻገር ደግሞ ጊዜ የሰጠው ቅል በመሆን የኋላ መብራትን ቦግ አድርጎ እንዲህ ቢሆን ኖር ፤ ይህ ቢደረግ ኖሮ ዓይነት ግምገማ ጥሩና ትክክለኛ ግንዛቤን የሚሰጥ አይደለም ። መንግስቱም መለስም ጭራሽ ባይወለዱ ኖሮስ እንዳይከተል! በየካቲት 1966 የአብዮቱ ፍንዳታ ይጠብቁት የነበሩትን ሳይቀር ድንገተኛ ግብታዊ ስለሆነባቸው በዚያ ወቅት ኢሕአፓ በበቂ ተደራጅቶ፤ተመክሮ አካብቶ፤ ተዘጋጅቶ የተገኘ ባለመሆኑ አብዮቱን ማጅራት መትተው ጥቂት ምርጥ መኮንኖች-- ራሳቸውን ደርግ ብለው ሰይመው በኃይል የሕዝብን ድል ሊነጥቁና በሥልጣን ሊሰየሙ ችለዋል ። ኢሕአፓ አብዮቱ ሞግዚት አያሻውምና ሁሉን የሚያሳታፍ ጊዜያው ሕዝባዊ መንግሥት ይመሥረት በሚል ሕዝብን አደራጅቶ ታሪክ የመዘገበውን ትግል አካሂዷል ። ይህን የዴሞክራሲያዊ ሽግግር አማራጭ ደርግና የምሁር አጋሮቹ እምቢኝ ብለው ባይጥሉትና በድርጅቱም ላይ አፈና ለማካሄድ ባይወስኑ ኖሮ የታሪክ ሂደት ሌላ ሊሆን እንደሚችል ማንም ሊከራከር አይችልም ። ሁሉን አቀፍ መፍትሔ መመረጡ ሥልጣን በተወሰነ ቡድን እጅ ገብታ የጭቆና ሥርዓት በአዲስ መልክ እንዳይቀጥል እንደነበረም የተገለጸ ነበር ። ይህ አማራጭ በመጣሉ ደርግ ራሱን የአብዮቱ ጠባቂና ሞግዚት ብሎ ሰይሞ ሙሉ ሥልጣንንም በእጁ ለማስገባት ወደ ደም ማፍሰስ ተሸጋገረ ።ያስከተለውን አስከፊ ሁኔታ ታሪክ መዝግቦታል ። በሽግግሩ ዕቅድ ኢሕአፓ ያኔ ተሓህት ይባል የነበረውን ወያኔ፤ ኦነግን፤ልዩ ልዩ ቡድኖችና የሕዝብ ማኅበራትን፤ወታደሮችና መኮንኖችን፤ታዋቂ ግለሰቦችን ወዘተ ባካተተ መልኩ አማራጩን ማቅረቡም የሚታወስ ነው ። ዛሬም ወቅታዊ ሁኔታው ይህን አማራጭ ግድ የሚለው ወያኔና ሕዝብ ተፋጠው ባሉበት፤ወያኔ ዘረኝነትንና የርስ በርስ ግጭትን አስፋፍቶ ባለበት፤ አሁንም ወታደሩና የጸጥታው ክፍል በወያኔ ቁጥጥር ስር ባለበትና ጦሩ ወደ ሕዝብ ጎራ ባልገባበት ሁኔታ ተቃዋሚ ኃይሎች ተባብረው ከፍተኛ ብስለትና ጥበብን በማሳየት በወሳኝነት በሚካሄደው ግብግብ በአሸናፊነት መውጣት ይጠበቅባቸዋል ። ከ 15 ዓመት በፊት የነበረውን ሐቅ ስናቀርብ የጻፍነው ዛሬ ለዛሬም የሚሰራና መሠረት ያለው ሆኖ እናገኘዋለን ፤ "የተቃዋሚ ሃይሎች ኅብረት ቀዳማይ ተግባር ለሽግግር ወቅት የሚያስፈልጉትን ዝግጅቶች ማሟላትና ለአጭር፤ ለመካከለኛ ለሩቅ ጊዜ የሚሆኑ አጀንዳዎችን መንደፍ ይሆናል። ይህንንም ለማድረግ የኅሊናም ይሁን ነባራዊ ሁኔታዎች ዛሬ በሀገሪቷ ተሟልተው ይገኛሉ ማለት ይቻላል ። ዘረኛ የወያኔ ቡድን እየተፍረከረከ ይገኛል። " በሚል የሀገራችንን አስከፊ ሁኔታና የወያኔን ግፍ ከዘረዘረ በኋላ መሠረታዊ ና የሚያመረቃ ለውጥ ለማምጣትም ዋስትናው የሽግግር መንግሥት ነው ሲልም ደምድሞ ነበር ።ዛሬም የተለየ መፍትሔና አካሄድ ሊኖር አይገባንም ማለት ነው። ቀድሞ የነበሩትን ችግሮች ለመፍታት የታቀዱት ሁሉ በሥራ ባለመዋላቸው ጭቆናና ቀውስ፤ችግርና ግፍ ኑሮአችንን አጅበው ቆይተዋል ። የነበረውን የእኩልነት አለመኖር ችግር በፌዴራላዊ አወቃቀርና በዴሞክራሲና እኩልነት ለመፍታት የታለመውን እቅድ ወያኔ ወደ ጎን አድርጎት በትግሬ የበላይነት በተለጣፊ ቅፍቀፋ እና በአንቀጽ 39ኝ ግንጠላና ጠባብነት ተክቶ አበለሻሸው ። ለዚህም ነው በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ጽንፍ የያዙትን በዴሞክራሲና በኢትዮጵያ አንድነትን በማይንድ አወቃቀር ዙሪያ አብረን መሰለፍ እንችላለን የምንላችው ። መሬት ለአራሹ ዛሬም ምላሽን የሚጠብቅ ጉዳይ ሆኗል ። የሠርቶ አደሩ ሕዝብ መብት ተረግጧል፤ የሃይማኖት እኩልነትና የአማኞች መብትም ተደፍሯል፤የፖለቲካ እስረኞች ቁጥር ብዙ ብዙ ሺ ነው። ሕዝብ ተበዝብዞ ለረሃብና ለስቃይ ተዳርጓል... ወዘተ። ባጠቃላይም የየካቲት ጥያቄዎች እንኳን መፍትሔ ሊያገኙ ቀርቶ በየዘርፉ ተባብሰው፤ ሕዝባችንም አንዱ አምባገንን ሲሄድ የከፋውና የባሰው እየመጣበት ከዛሬውስ የትላንቱ ይሻላል ወደሚል አሳዛኝ ድምዳሜና ምጸት እየተዳረገ ይገኛል። በአንክሮና አንገብጋቢነት የሚቀርበው የኅብረት ጉዳይ ባሉት ውስብስብ ችግሮች የተነሳ አሁንም አስፈላጊና ወሳኝ ሆኖ የሚገኝ ነው ። በደርግ ውድቀት ዋዜማ የኅብረትን ችግር ምላሽ ለመስጠት በመካከላቸው ከፍተኛ የሆነ ጠብና ግጭት የነበራቸው ቡድኖችና ድርጅቶች ሳይቀሩ ሁሉም ኅብረት ሊመሰርቱ ሲዋደቁ ወያኔ፤ሻዕቢያና ለነሱ ያደሩ ምሁሮች እንቅፋት ሆነው የኅብረት ምስረታውን ለማደናቀፍ መጣራቸው ታሪክ የመዘገበው ነው ። ኢዴኅቅ ዘግይቶ ሲቋቋምም ከመቅጽበት ወያኔም አሜሪካም ሊያፈርሱት መነሳታቸው የሚታወቅ ሲሆን ከይሲው ወያኔ ለሥልጣን ሲበቃ በኅበረቱ ከተሰለፉት አባል ድርጅቶች ውስጥ የተወሰኑት ወደ ወያኔ ጉያ የገቡ መሆናቸውም ሐቅ ነው። የወያኔ የሥስልጣን ባለቤት እንዳይሆን ለማስቆምም ሆነ ለማገድ አልተቻለም ። ኢሠፓ ከላይ እስከታች ተፍረክርኮ፤ዋና መሪው በሚያሳፍር ሁኔታ የሀገር ሀብት ዘርፎ ፈርጥጦ፤ ጦሩ ፈርሶ ለወያኔ ሁሉ ነገር አመቻችቶ እንደሰጠ ደግሞ የምንረሳው አይደለም ። የኢሕአፓ ጦርም በወያኔ ፤ ሻዕቢያና ሱዳን ትብብርና በራሱም ድክመትም ሊመታ ቻለ ። ጸረ ወያኔውን የከተሞች ትግልም ምሁሮችና ጠባቦች ነጥለው በማዳከማቸው ሁኔታው ለወያኔ አመች ሆኖ ዘረኝነትን ተጠቅሞና አፈናን አጠናክሮ ሥልጣኑን ለማደላደል ችሏል። ይህን ወያኔን በሥልጣን በከፍተኛ ደረጃ ያገለገለውን የዘረኝነትና ሕዝብን የመከፋፈል ፖለቲካ በማጀብ በጸረ አማራነትና ኢትዮጵያዊነትን በመካድ የተሰማሩት ኃይሎች ሁሉ- ወደዱም ጠሉም- ለወያኔ የሥልጣን ዘመን መራዘም ከፍተኛ ጠቀሜታ አበርክተዋል። ወደ 1997 ዓ.ም. አካባቢ ብቅ ያሉት ኅብረትና ቅንጅት ሁለትነታቸው ራሱ የድክመታቸው ነጸብራቅ ሆኖ ፤አስፈላጊውን አንድነት አጥተው ግን በትግላቸው ወያኔን በምርጫ ቢያሸንፉም ድላቸውን ለማስከበር ዝግጅቱም ጽናትም እንዳልነበራቸው የተከተለው ሁኔታ ገሃድ አድርጎታል ። ካቸነፍን በኋላ ድላችንን ወያኔ ቢቀማስ ለሚለው ስጋት ይሰጥ የነበረው መልስ አሜሪካ አይፈቅድለትምና ብዙ የሚያሳስብ አይደለም የሚለው ከመሰረቱ የተሣተ ድምዳሜ ነበር ማለት ይቻላል። ልጁ ቀማኛ አባቱ ዳኛ ሆኖ ፍትህን መሻት ማለት ነው። ወይኔ ብዙ ሕዝብ ፈጅቶ እንደተፈራው ከሥልጣን አልወርድም ብሎ ሲደነፋ ይህን በመቃወም የሙት ከተማ አድማ ቢጠራ ይህን ያፈረሱት ራሳቸው የተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች መሆናቸውንም የምንረሳው አይደለም ። የወያኔ የክፍፍል ዓላማ በጎንደር ሕዝብ ታሪካዊ መፈክር ተሰርዞ፤ የሕዝብ ኅብረት በኢትዮጵዊነት ተጠናክሮ በመጣበት በአሁኑ ጊዜ የሥልጣን መሠረቱ እየተንገዳገደ ያለው ወያኔ ሕዝብን ለመከፋፈል አሁንም ከመወራጨቱ ባሻገር ኢትዮጵያን የእርስ በርስ ደም መፋሰስ አውድማ አድርጎ ካልሆነለትም ትግራይን ገንጥሎ ሊፈረጥጥ (የጎንደርማ የወሎን ለም መሬቶች ጠቅልሎ ከሱዳንም ተዋሳኝ ሆኖ የለ!) ተዘጋጅቷልና የተቃዋሚና ሀገር ወዳድ ኃይሎች ኅብረት ቀነ ቀጠሮ የማይሰጥ፤ለመጪው ትውልድ የማይለጋ ሐኬት ሆኖ ይገኛል። የተቃዋሚና የአገር ወዳድ ኃይሎች ኅበረት እየተንገዳገደ ያለውን የወያኔ ዘረኛና ከፋፋይ አገዛዝ ከሥሩ ለማስወገድም ሆነ ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚወስደውን የሽግግር ሂደት ሰላማዊ፤ የተረጋጋና ውጤታማ እንዲሆን ለማድረግ ቁልፍ ሚና ይኖረዋል። "በሽግግሩ ሂደት የፖለቲካ ድርጅቶች ብቻ ሳይሆኑ በእውቀታቸው፤በተመክሯቸው በሀገር ወዳድነታቸውና በዲሞክራሲ ዕምነታቸው እንከን ሊወጣባቸው የማይችሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች ሊሳተፉ የሚችሉበት መመዘኛ/መድረክ ቢኖር መሰረተ ሰፊ የሽግግር ወቅት ይሆናል እንላለን ። ይህም ማለት የመንግሥት፤ የኤኮኖሚውንና የሲቪል ኅብረተሰቡን ሚና በሚዛን አስተካክለው የሚያዩና የሚተረጉሙ ክፍሎች ከተሳተፉበት ለዴሞክራሲያዊው ሂደት አቅጣጫ ያረጋግጣል፤ይሰምራል ማለት ነው ።በዕርግጥም በአንድ ሀገር ውስጥ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት ካስፈለገ የመንግሥትና የሲቪል ኅብረተሰቡን ሚና በግልጽ ተለይቶ መደንገግ ይኖርበታል ። በሀገራችን የዴሞክራሲ ሂደትና ዕድገት በአመዛኙ ሊረጋገጥ የሚችለው የሲቪል ኅብረተሰቡ ሙሉ ተሳትፎ ሲረጋገጥ ነው። የዴሞክራሲንና የነጻነትን ዋስትናና ማረጋገጫ ለማስገኘት የሲቪል ኅብረተሰቡና በነጻ የሚንቀሳቀሱ ተሳታፊ ሕዝባዊ ተቋማት እንዲኖሩ የግድ ነው ። ሚዛኑ ያላጋደለ ቁጥጥር የመንግሥትን ኃይል ለመገደብ ዋስትና አለው ። በሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ላይ የተማከለ የማኅበራዊ ኑሮና የኤኮኖሚ ዕድገት ዕውን እንዲሆን ከተፈለገ ሁሉን ሊያሳትፉ የሚችሉ የኅብረተስብ ልዩ ልዩ ድርጅቶች በመላ ሀገሪቱ መስፋፋት አለባቸው ብለን እናምናለን ። ለዚህ ሁሉ ዘር መዘራት ያለበት በሽግግሩ ውቅት ቢሆን ተገቢ ይሆናል ።" ዴሞ ነሐሴ 1995 ስለ ሽግግሩ ከኅብረቱ በእኩል ማቅረባችን ጋሪውን ከፈረሱ ማስቀደማችን ሳይሆን ለሽግግሩ ወሳኝ የሆነውን ኅብረት ስናነሳ ሽግግሩንም በዕይታችን ማስገባቱ የግድ በመሆኑ ነው ። በተጨማሪም የሕዝብን ሚና--ወሳኝነትና የውሳኔ ባለቤትነት--ተገቢውን ቦታ ለመስጠት፤ በምርጦች ሕዝቡ ወደ ጥግ እንዳይደረግ ያለንን ጽኑ ፍላጎት ጫና ለመስጠትና የነገ ኢትዮጵያ ዕጣ አቅጣጫዋ የሕዝብ ውሳኔ ውጤት መሆን አለበት ለማለት ነው። ፈረሱማ ኅብረት ነው ። ተከታዩ የሽግግር መንግስት ነው ። ከዚህም አንጻርጥሪያችን ከዴሞክራሲናኢትዮጵያአንጻርበሁሉምጉዳይበጥሞናተወያይተንመፍትሔእንፈልግነው--ለጋራሀገራችን ። ያሉትን መለስተኛ ልዩነቶች ወደ ጎን በመተው ለሀገር ጠቃሚ የሆነ ኅብረት መመስረት ይገባል ብቻ ሳይሆን ይቻላልም ።ይህ ግን ግለኝነትን አቸንፎ ሀገርን ማፍቀርና ማስቀደምን ይጠይቃል ።ከሁሉም በላይ ኢትዮጵያ፤ ከሁሉም በፊት ሕዝባችን ካልን ሌሎች ጉዳዮች ፤ የሀሳብና የአቋም ልዩነቶች ክብደታቸው ይቀንሳል ። በሀገራችን ህልውና ላይ የተጋረጠውን አደጋ ከመጋተርና ከማስወገድ በፊት ሊቀድም የሚችል ምንም ግዳጅ የለም። አደጋውን ለማስወገድ መሳሪያ የሚሆነውን ኅብረት ከመመስረት የሚያግድ ምንም ጉዳይና ችግር ሊኖር አይችልም፤ አይገባም ማለት ነው ። ኅብረቱ እውን ከሆነ የሽግግሩ ሂደትም ቀና አቅጣጫን ይዞ መጓዙ የማያቀር ነው ። ተቃዋሚዎች ዓላማ የላቸውም፤ተከፋፍለዋል፤ወያኔ ከተወገደ ሕዝብ ያልቃል፤ለመሆኑ ማን ወያኔን ሊተካ ይችላል የሚሉት ተስፋ አስቆራጭ አነጋገሮች ሁሉ ያከትማሉ ማለት ነው ። ወያኔን አስወግዶ ሀገርን በፍትህና በዲሞክራሲ ለማስተዳደር--እንደ ወያኔ ለማጥፋት ለመበጥበጥ ሳይሆን--ችሎታውና ከዚያም በላይ ፍላጎቱ እንዳለን ሳናወላውል የተናገርነው ነው ። #ርዕሰ ዜና #ህፃናት ገዳዩ ወያኔ፣ የህፃናት ቀንን ማክበሩ አነጋጋሪ ነው ተባለ #የውጪ ምንዛሪ ኦና መሆን የወያኔን የደም ስሮች እየገደለ መሆኑ ተሰማ #የወያኔ ፓርላማ ወና እየሆነ መሄዱ ተጋለጠ #የኮካ ኮላ ኩባንያ ስኳር መዘረፉ ታወቀ #ከቻይና ውዳቂ የሆኑ የኤች. አይ.ቪ. መመርመሪያ ቁሶቁሶች ግዢ መፈጸሙ አነጋጋሪ ሆኗል #ወያኔ ከኳታር ጋር መፈጣጠሙ መዘዝ አለው እየተባለ ነው ##ዝርዝር ዜናዎች##  በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ህፃናት በርሀብ አለንጋ እየተገረፉ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሕፃናት በከተሞች በልመና፣ በጣም ዝቅተኛ በሆነ የጎዳ ላይ ንግድ እየተራወጡ ባሉበት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሕፃናት ትምህርት እንዳያገኙ በሆኑበት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሕጻናት በተለያዩ በሽታዎች እየማቀቁ ባለበት የዓለም የህፃናት ቀን በወያኔ አጋፋሪነት መከበሩ ገድሎ መቆንጠጥ ነው ተብሏል፡፡ ዛሬ ወያኔ በሚገዛት ኢትዮጵያ እድሜያቸው ከአንድ አመት በታች የሆኑ ህፃናት በመላው ኢትዮጵያ በወላጆቻቸው ድህነት ምክንያት ወይ ለልመና፣ ወይ ህፃናቱ በእራሳቸው እየተራወጡ የእለት ጉርሳቸውን ሲቃርሙ እንደሚውሉ የሚታወቅ በመሆኑ በርካታ የፖለቲካ አዋቂዎች ወያኔን በህፃናት ገዳይነት ይከሳሉ፡፡ ሕዝባዊ አመጾች በተካሄዱባቸው በርካታ አካባቢዎች የወያኔ የክብር ዘብ የሆነው አረመኔው አጋዚ ጦር በርካታ ወጣቶችን በአልሞ ተኳሾት በመግደሉ ወያኔን የህፃናት ገዳይ ያደርገዋል የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ ከዚህ በሻገርም ወያኔ በጉዲፈቻ ስም ህፃናትን እንደ ሸቀጥ እየቸበቸበ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በርካታ ሕህፃናት ለአደንዛዥ እጽ ሱሰኝነት ተጋልጠዋል፡፡ ወያኔ የእናቶችንና የህፃናትን ሞትን መቀነሱን ለፖለቲካ ተረፌታ ቢለፍፍም ሀቁ ተወልደው ሁለተኛ አመት ልደታው ሳይሞላ የሚቀጠፉ ህፃናት ቁጥርን ቤት ይቁጠረው የሚያሰኝ ነው የሚሉ ብዙዎች መሆናውን ተገንዝበናል፡፡ ባለፈው ሳምንት የተከበረው የዓለም ህፃናት ቀን በህፃናት ገዳዩ በወያኔ ሊከበር አይገባውም ነበር ተብሏል፡፡  በብሔራዊ ባንክ ለመጠባበቂያ ተይዞ የነበረው የውጪ ምንዛሪ በተለያዩ የወያኔ ቁንጮዎች ተሟጦ በመወሰዱ በአሁኑ ወቅት አንድም ዓይነት የውጪ ንግድ መፈጸም ፈጹም እማይቻልበት ደረጃ መድረሱ እየተነገረ ነው፡፡ በውጪ ምንዛሪ እጥረት የባህር ትራንስፖርት ድርጅት እንቅስቃሴ እየተሽመደመደ መሆኑ ተጋለጧል፡፡ ለህይወት እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መድሀኒቶች በውጪ ምንዛሪ እጥረት ሰበብ ወደ ሀገር ውስጥ መግባት ማቆማቸው በስፋት ይወራል፡፡  የወያኔ ፓርላማ ወንበሮች በየጊዜው በአብዛኛው ቦዶ ሆነው መታየታቸው የተለመደ ነው፡፡ በዚህ ባሳለፍነው ሳምንት የወያኔ ፓርላማ አባላት በዛት ከግማሽ በታች መውረዱ የወያኔ አባላት የእርስ በእርስ መናቆር ውጤት እንደሆነ ታጋለጠ፡፡ ከአምስት መቶ አራባ ሰባት አባላት ውስጥ ግማሹ እንኳ አለመገኘቱ የወያኔ መሰነጣጠቅ ምልክት መሆኑን የሚያስረዱ ብዙዎች ናቸው፡፡  የስኳር እጥረት በርካታ ቀውስ እያስከተለና ህብረተሰቡን ለግጭት እየዳረገ መሆኑ አሳሳቢ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ፡፡ የኮካ ኮላ ፋብሪካ ባህር ዳር ለሚገኘው ፋብሪካው በአራት ካሚዮን ሰባት መቶ ሃያ ኩንታል ስኳር ሰሜን ሸዋ፣ ጎሀ-ጽዮን፣ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ሰማንያ ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ የምትገኘው ወረ ጃርሶ ወረዳን አቋጠው እንዳያልፉ በአካባቢው የፖሊስ ኃይሎች መታገታቸውና ስኳሩም እንዲራገፍ መደረጉ ታውቋል፡፡ ይህ ሁኔታ ከደረሰው የስኳር እጥረት ጋር በተያዘ የተደረገ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን አነጋጋሪው ጉዳይ ግን የድርጊቱ ፈጻሚዎች የደምብ ልብስ የለበሱ የወያኔ የፀጥታ ኃይሎች መሆናቸው የወያኔ የእዝ ስንሰለት እየተልፈሰፈሰ መሆኑን የሚሳይ ነው ተብሏል፡፡  የኤች.ኤ.ቪ. ስርጭት እንደ ወረርሽኝ በአስደንጋጭ ሁኔታ እየተስፋፋ ባለበት ወያኔ ደረጃቸው ዝቅ ያሉ የበሽታው መመርመሪያ ማሳሪያዎች ከደረጃቸው ዝቅ ያሉ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን እጅግ በጣም ውዳቂ መሆናቸው ተጋለጠ፡፡ እነዚህ ቁሳቁሶች ያቀረበው ቤጅንግ ዋንቲ ባዮሎጂካል ኢንተርፕራዝ የተሰኘ ድርጅት ሲሆን የቀረቡት የኤች.ኤ.ቪ መመርመሪያ መሳሪዎች ደረጃቸው በእጅጉ ዝቅ ያሉ መሆናቸው ታውቋል፡፡ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት እንደዚህ የመሰሉ የቻይና የንግድ ድርጅቶች እንዲህ ያሉ ውዳቂ ሸቀጦችን ለማቅረብ የሚያደፋፍራቸው ምን ጊዜም ከጀርባቸው ያሉት የወያኔ ቁንጮዎች እንደሆኑ የሚታወቅ ነው ተብሏል፡፡  ወያኔ የሀገራችንን የትምህርት ጥራት እመቀ እመቃት በመክቱተቱ በሀገር አቀፍ ደረጃና በዓለም አቀፍ ደረጃ ውግዘት እየወረደበት መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በቅርቡ በትምህርት ቤቶች የትምህርት አሰጣጥን አስመልክቶ የተካሄደ ጥናት ይፋ እንዳደረገው ዘጠና አራት ከመቶው የሚሆኑት ትምህርት ቤቶች የትምህርት አሰጣጥ ደረጃቸው ከመደበኛው መስፈርት እጅግ በጣም የወረደ መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ የወያኔ ቁንጮዎች በገንዘብ የተገዙ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪዎች ባለቤት በሆኑባት ሀገር ወያኔ በስልጣን እስካለ ድረስ ትምህርት እየተልከሰከሰ እንጂ እየጠራ አይሄድም ተብሏል፡፡  ይህ የወያኔና የኳታር ጋብቻ የፖለቲካ እንደምታ እንዳለው በስፋት እየተነገረ ነው፡፡ በሳዑዲና በግብፅ የሚሽከረከሩት የባህረ-ሰላጤው ሀገራ ኳታርን ማግለላቸውና በአሸባሪው አይ ሲ ስ እረዳትነት መወንጀሏ የሚታወስ ሲሆን በዚህ ሳቢያ ኳታር አሰብ ወደብ ያሰፈረችውን ጦሯን ማስወጣቷ የሚታወቅ ነው፡፡ ወያኔ የውጪ ምንዛሪ እጥረቱን ለመቅረፍ በሚል ጭፍን አስተሳሰብና የግብፅን ተጽእኖ መቋቋም እንዲያስችል በሚል ከኳታ ጋር የጭፍን የተደረገው መፈራረም ሳይደርቅ ከሳዑዲና ከሸሪኮቿ ወያኔን ቀስፎ የሚይዝ ተጽእኖ እንደሚያደርሱ ይጠበቃል ተብሏል፡፡ ዘረኞቹ ህወሃት ወያኔዎች የምንወዳትን ኢትዮጵያ ገራችንን ደግመው ደጋግመው እንዳያደሙት የህዝባችን መከራና ስቃይ እንዲያቆም ገዳዮቻችንን አጥፊዎቻችንን ሊፋረዳቸው በህይወቱና በቤተሰቦቹ የጨከነ የስርዓቱን የውድቀት ምዕራፍ ወደፊት ያፋጠነ ወደፊት እንጂ ወደ ኃላ የምንመለስባት ሌላ ኢትዮጵያ እንደሌለን እውነታውን አስረግጦ ያስገነዘበን አንዳርጋቸው ፅጌ ዛሬ በወያኔ ህወሃት ውድቀት ዋዜማ ልናስታውሰው ይገባል። ዳኛውም ዝንጀሮ ፍርድ ቤቱም ገደል እምን ላይ ተሁኖ ይነገራል በደል እንዲሉ በሀገራችን ውስጥ ምንም ዓይነት ፍትህ እኩልነትና ዲሞክራሲ እንደሌለና ዜጎች በመናገራቸው የሚታሰሩበት የሚገደሉበት በዘራቸው ምክንያት እንደ ጠላት የሚፈረጁበት ከአንድ አካባቢ የመጡ ሰዎች ብቻ ገሪቱን ኢኮኖሚዋን ስልጣኑን ተቆጣጥረው ሌላውን ኢትዮጵያዊ የበይ ተመልካች አድርገው ወያኔዎች ሲጨርሱት ሲያስፈልጋቸው በጥይት ሲደፉት ይህንን እውነት ቀድሞ የተረዳው ያስቆጣው ያንገበገበው አንድአርጋቸው ፅጌ ፍትህ በዛች ገር ላይ እንዲሰፍን በማለት የኔ የሚለውን ነገ ሁሉ ላይ ጨክኖ ህወሀት (ወያኔን) ሊፋለም እስከ ህይወት መስዋአትነት ሊከፍል እርሱ ሞቶ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ነፃ ሊያወጣ ሁሉን ጥሎ ሜዳ ገብቶ አምባገኑን የወያኔ ስርዐትን ሊታገል የወሰነና የታገለ ሁሌም በኢትዮጵያዊያን ልብ እርሱ ነዶ ብርሀን ሆነ የድርሻውን ያለውን ሁሉ ለአንዲት ኢትዮጵያ ከፈለ። አምባገነኑ ስርዐት የአንዳርጋቸው ፅጌን አቅምና ችሎታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ እንቅልፍ ነስቶትና ስጋቱንም ከጫፍ አድርሶት እንደነበር ግልፅ ነው፡፡ ይህንን ታላቅ ታጋይ ወጥመድ ውስጥ ለማስገባት የህወሀት (ወያኔ) የስለላ ተቋም በሚልዮን የሚቆጠርን ዶላር ከማውጣት ምሮ ብዙ ድካምና ዋጋ እንዳሰከፈለው ግልፅ ነው ለዚህም ነው በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሀገራትን አቋርጦ በመሄድ ጠለፋን ያካሄደው የታጋይ አንድአርጋቸው ፅጌን ተፅእኖ ፈጣሪነትና ለሕወሀት ወያኔ ራስ ምታት እንደነበር የሚያሳይ ግልፅ ትእይንት ነው። አንድአርጋቸው ፅጌ ዛሬም ቢሆን በልባችን ውስጥ ያለ ግና ነው ባለው ፅኑ አቋምና ቆራጥነት አልበገሬነት የወያኔን አምባገነንና አፋኝ ስርዐትን እንቅልፍ የነሳ የቁርጥ ቀን ልጅ እንዲሁም የኢትዮጵያዊያን ባለውለታ ነው፡፡ ለሁሉም ነፃነት ናፋቂና ታጋይ ኢትዮጵያዊ ለትግል ጉዞ አርአያ በመሆን የቆራጥነትን ጥግ ያሳየ መሪ ነው፡፡ አቶ አንድአርጋቸው ፅጌ ከማንም በተሻለ ሁኔታ የወያኔ (ሕወ ት) መሰሪ አሰራርን ጠንቅቆ የሚያውቅ እና ኢትዮጵያ ገራችንን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየከተትዋት እንደሆነ የተረዳ ሰው ነው ዛሬ ላይም ለነፃነት፣ ለአንድነት ፣ ለዲሞክራሲ መከበር የምንታገል ኢትዮጵያዊያን ትግል ማለት ምን እንደሆነ በደንብ የተረዳነው ከአንድአርጋቸው ፅጌ የህይወት ቆራጥነት ነው ለነፃነት የሚከፍሉ መስዋዕትነት ግራ ቀኝን ማየት መመልከት አይጠይቅም፡፡ በጠቅላላ ትኩረት እና ሳብን ግብ ላይ ማድረግን ብቻ ነው የሚፈልገው። ይህ አጥፊ ስርዐት ላለፉት 26 አመታት ኢትዮጵያዊያን ላይ የቀበራቸው ፈንጂዎች ኢትዮጵያዊያን ላይ ሳይሆን ራሱ ላይ እያፈነዳ እየፈ ው ይገኛል። ግናው ታጋይ አንድአርጋቸው ፅጌን ቢያስሩም እርሱን የቆመለትን አላማ ማሰር አልቻሉም ለዚህም ነው ከሃገር ውስጥ ሆነ ከውጭ ገራት ወያኔን ገዝግዞ ሊጥለው የደረሰው አዲሱ ነፃነት ፈላጊው ትውልድ ያነገበው የፍትህ የዲሞክራሲ ጥያቄና ስርዐቱንም ከስልጣን የማስወገድ ትግል አቶ አንድአርገቸው ፅጌ ዋጋ የከፈለለትና ማየት የሚናፍቀው የነበር ነው ዛሬ ላይ ግን የእርሱ ህልም እውን ሊሆን የወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ዘመን ሊያበቃ ዘረኝነቱም ሊቋጭ ቀብሩ ሊፈፀም 11ኛ ሰዐት ላይ እንገኛለን፡፡ የነፃነት አባት የሆነውን አንድአርጋቸው ፅጌና ሌሎች ብዙ ዋጋ የከፈሉ ኢትዮጵያዊያንን የታሰሩ የተገደሉ አሁንም ድረስ በየ እስር ቤቱ የሚገኙትን ጨምሮ ሁሉንም ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ ሃገራችንን ኢትዮጵያን ሕወ ት ወያኔ አጥፍቶ ሳይጨርሳት ታጋይ አንድአርጋቸው ፅጌ እና ከፍተኛ የተቀዋሚ አመራሮችን ጨምሮ ህዝብን በማደራ ት እንዲሁም በማስተማርና ግንዛቤው እንዲጨምር በማድረግ የእያንዳንዳቸውን ድርሻ ቀድመው ተወተዋል ዛሬ የምናየው ህዝባዊ እንቢተኛነትና የነፃነት ትግል በእነ አቶ አንድአርጋቸው ፅጌ የመመካከርና የመተባበር አ ንዳ የመጣ ውጤት ነው፡፡ አሁን በምናየው የሃገራችን ሁኔታ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ እንዲያሸንፍ አንድነት ይል እንደሆነ ዘረኛውንና አሸባሪውን የወያኔ ስርዐት በዘረጋው የመከፋፈል እና የመበታተን ሃሳብ ውጤታማ እንዳይሆን ይህንን የሕወ ት (ወያኔ) ሴራ ቀድሞ በማጋለጥ አቶ አንድአርጋቸው ፅጌ ዋነኛና ቀዳሚ ነው፡፡ አንድአርጋቸው ፅጌ ለሃሩና ለወገኑ ቆመ እንጂ ወገኑንና ገሩን ለገንዘብና ለንዋይ አልሸጠም ለግል ክብሩ አልተጨነቀም የኢትዮጵያ ህዝብን እንደ መዥገር ከተጣበቀበት ስርዐት የወያኔ (ሕወሀት) ግፍና በደል የህዝባችን ዕሮሮ ማብቂያ ዋዜማ ላይ የደረስነው ቆራጥና ለአላማው ብርቱ የነበረው አንድአርጋቸው ፅጌ ያነገበውን አላማ ይዘን በፍጥነት ለመጓዝ ስለቻልን ነው ከዚህ በኋላ ያረጀው ስርዐት ምንም እድል ፋንታ የለውም በኢትዮጵያ ህዝብ እምቢተኛነት የተሸነፈ ነው፡፡አርቆ መቅበር ብቻ ነው የሚያስፈልገው። በሀገራችን ኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ ህወሃት ወያኔን እየናጠ የሚገኘው ተቃውሞ አምባ ገነኖቹ የህወሃት ወያኔ ባለስልጣናትን የስልጣን ዘመናቸው ማብቂያ ደውል መሆኑን አረጋግጦላቸዋል። በውድቀት አፋፍ ላይ የሚገኘው ህወሃት ወያኔ በሁሉም አቅጣጫ የኢትዮጵያ ክፍል ላይ የተነሳበትን ተቃውሞዎች መልካቸውን ቀይረው ወደ እርስ በርስ ግጭት እንዲያመራ ለማድረግ ሲሞክር በከፊልም ሲሳካለት እየተመለከትን ነው ህወሃት ወያኔ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል የሚለው አቋሙ በግልጽ ታይቷል። ለዚህም እንደማሳያ ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኦሮምያና ሶማሊያ ክልል በወያኔ ህወሃት መሪነት የተነሱት የእርስ በርስ ግጭቶች ማስታወስ ያስፈልጋል። ዜጎች ከገዛ ሀገራቸው ሲፈናቀሉ ከመቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ኦሮሞዎች ከሱማሊያ ክልል ሀብት ንብረታቸው ተዘርፈው ሲሰደዱ ሴቶቻቸው በሱማሊያ ሚሊሻ ሲደፈሩ ሲገደሉ አይተናል። ታዲያ ይህ ሁሉ አምባገነኑ ህወሃት ስልጣኑን ለማራዘም የሚጠቀምበት እንደሆነ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የተደበቀ አይደለም። ህወሃት ወያኔ ኢትዮጵያን ለማተራመስ ቀርፆ በሚጠቀመው ፖሊሲ መሠረት በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ላይ የዜጎችን ዘርን ተገን ያደረገ የእርስ በርስ ግጭት እያነሳሳ ይገኛል። ባሳለፍናቸው ሁለት ቀናቶች ውስጥ እንኳን በኢሊባቡር ከ 20 በላይ አማሮች በግማሽ ቀን ውስጥ ተጨፍጭፈዋል ተገለዋል በኢሊባቡር ወረዳዎች የአማራ ተወላጅ የሆነ ተለይተው እየተጠቁ እንደሆነ የተጎጂ ቤተሰቦች ሲናገሩ አድምጠናል። ስርዓቱን በመቃወም የተጀመረው የተቃውሞ ሰልፍ በህወሃት ወያኔዎች ሰርጎ ገብነት ሆን ተብሎ አላማውን እንዲስት ተደርጉዋል። በኢሊባቡር ደጋ የተፈናቀሉ አማራ ሴቶች በተሰደዱበት ጫካ ውስጥ እንዳሉ ሁለት ነፍሰጡሮች መውለዳቸው ተነግሯል። በጅማ ዞን ሊዪ ወረዳ የአማራ ተወላጆች ንብረት እየወደመ እንደሆነ አድምጠናል ብዙ ወራትን ያስቆጠረው የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ ጥቃትም የአማራ ልጆች ከትምህርት ገበታ ጭምር አስተጓጉሎ እንዲታገዱ አድርጉዋል። ሀላፊነቱን መውሰድ ያለባቸው የዚህ ሁሉ ሴራና ተንኮል አቀናባሪዎች የህወሃት ወያኔ ቱባ ባለስልጣናት ናቸው። ሴራቸውና ተንኮላቸው ተግባራዊ እንዲሆን ትዕዛዝ የሰጡት እነዚሁ ህወሃቶች የሚፈልጉት ደም መፋሰስና ግጭት ብቻ ነው። ስለዚህ አማራው ሆነ ሌላው ኢትዮጵያዊ በንፁሃን ወገኑ ላይ የደረሰውን ጅምላ ጭፍጨፋ አፀፋውን በመመለስ መቃወም ይገባዋል። ህወሃት ወያኔ ሲገድለን ሲያስገድለን 26 ዓመታት አስቆጥሯል ለገደለን ላስገደለን ጠላታችን ህወሃት ርህራሄ ፍፁም አያስፈልግም። በህወሃት ወያኔ ምክን ያት ከዚህ በኃላ ደሀው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ተቸግሮ ተሰቃይቶ መኖር ሊበቃው ይገባል። ወያኔ የውድቀት ጫፍ ላይ ያደረሰው የገዛ ማንነቱና ባህሪው ነው የአንድ ዘር የበላይነትን አንግሶ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ዜጋ እንደ መጤ ወይም እንደ ሁለተኛ ዜጋ በበታችነት ዐይን እያየ የአንድ አካባቢ ሰዎችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲስተም ዘርግቶ ሌላውን ያገለለችና ተጠቃሚ ያላደረገች ኢትዮጵያ ለመፍጠር ሲሞክር ከመላው ኢትዮጵያዊ የመረረ ተቃውሞዎች አንገዛም ህወሃት ወያኔ በቃን የሚል መልእክት እየተስተጋባ ነው ያለው። ብዙ ተምሮ ስራ ያጣ ወጣት ሀገሪቱን ሞልቷል የውትድርና ልምድ ባላቸው የወያኔ ባለስልጣናት የምትመራው ሀገር ኢትዮጵያ ዛሬም አድጋለች እያሉ ህዝቡን ሊያደነቁሩት ሲሞክሩ ታዝበናል። ውስን የወያኔ አገልጋዮችና ባለስልጣናት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ተቆጣጥረው ቀሪውን የሀገሪቱን ዜጋ በርሀብ ጠብሰውት የበይ ተመልካች ሆኖ ባለበት በዚህ ሰዓት ይህ የተራበ ሕዝብ መሪውን ሊበላ ደርሷል።አሁን በሀገራችን ያለው ነውጥ ወደ ለውጥ ለመቀየር ሁሉም ዜጋ በአንድነት ተነስቷል። ህወሃት ወያኔ ለመውደቅ መንገዳገድ ጀምሯል የተንገዳገደውን አምባ ገነኑን ስርዓት የመጣል ሀላፊነት የህዝቡ ነው የለውጡም ባለቤት የሚሆነው ህዝቡ ነው። የወያኔ ህወሃት ድርጅት አባላት በተናጠል ከወያኔ ጋር በማበር ህዝቡን የምታስጨፈጭፉት የኢትዮጵያ ህዝብ ሲደማ ምሽቱን ዳንኪራ የምትመቱ በገንዘብና በሌላም በሁሉ አቅጣጫ ከጎናቸው ያላችሁ ከአንድ አካባቢ የተሰበሰባችሁ እየሰራችሁ ያለው ታሪክ ተመዝግቦ የሚቀመጥ በደል ግፍ ትልቅ ዋጋ የሚያስከፍላችሁ መሆኑን እወቁት። አሁን የተጀመረው ህዝባዊ እንቅስቃሴ አድማሱን በማስፋፋት ትግሉን ወደ መጨረሻ ደረጃ ላይ መግፋቱ ልብ ልንል ይገባል የመጨረሻውን ውጤት ማሳመር እንዲቻል ትግሉን መደገፍ አለብን።
3
አዲስ አበባ ፡መስከረም 9/2011፡- ሁማኒቲፕላስ (h+) እና አይኮግ ላብ(icog lab) ባዘጋጁት የመጀመሪያው የሶልቭ ኢት የፈጠራ ውደድር በመሳተፍ ላይ ያሉ የፈጠራ ባለሙያዎች የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን(ኢመደኤ) ጎብንተዋል፡፡ በጉብኝታቸው ወቅት በኤጀንሲው ስለሚከናወነው የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ፣ የቴክኖሎጂ ልማት እና ምርምሮች እንዲሁም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ኦዲት ዙሪያ ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል፡፡
4
በትራንስፖርት ማኔጅመንት፣ በትራንስፖርት ኢኮኖሚክስ፣ በትራንስፖርት ፕላኒንግ፣ በስታትስቲክስ 5(7)፣ ኢኮኖሚክስ 5(7)፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ወይም በተዛማጅ የሙያ መስክ የምዝገባ ቦታና ሰዓት፤ ዮቴክ ኮንስትራክሽን 1ኛ ፎቅ የሰው ኃይል አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 106 በስራ ሰዓት ጠዋት 2፡30-6፡30 ከሰዓት 7፡30-11፡30 ድረስ፡፡ በምዝገባ ወቅት አመልካቾች ዋናውን የትምህትና የስራ ልምድ ማስረጃ ኦሪጅናልና ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም የግል ሁኔታ መግለጫ (c.v) ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5
የኦሮሚያ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ከዚህ በታች ባሉት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ በኮንትራትና በቋሚነት ሠራተኝነት መቅጠር ይፈልጋል፡፡
6
አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒውን በመያዝ የሰው ኃይል አስተዳደር ስራ ሂደት 3ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 311 በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ፡፡ ለሁሉም ክፍት የስራ መደቦች በስራ ላይ ላሉት ተመዝጋቢ ሰራተኞች ስለ ቅጥሩ አሳማኝ ምክንያቾች ካለና በቢሮ ሐላፊ ቅጥሩ ካልተፈቀደ በስተቀር በቻናል አንድ መመሪያ አንቀጽ 10.4 መሰረት ማንኛውም ቋሚ ሰራተኛ ስራ ከለቀቀ ከስድስት ወር ያላነሰ ጊዜ ያለው ካልሆነ በስተቀር ወደ ኮንትራት ተዛውሮ ሊቀጠር አይችልም ስለሚል ቋሚ የመ/ሰራተኛ ተመዝጋቢዎች በቅድሚያ ይህንኑ መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡
7
ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን ፋሽኑ ካለፈበትና ባለቀለም ቴሌቪዥን ከመጣ ከ50 አመታት በላይ ቢሆነውም፣ በእንግሊዝ ከ7 ሺህ በላይ ቤተሰቦች አሁንም ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን እንደሚያዩ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡በእንግሊዝ ባለቀለም ቴሌቪዥን ገበያ ላይ የዋለው እ.ኤ.አ በ1967 እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ በአገሪቱ 7 ሺህ 161 ያህል… በፈረንጆች አመት 2018 ያለፉት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ሜዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው ወደ አውሮፓ ለመግባት በጉዞ ላይ ሳሉ በባህር ውስጥ ሰጥመው የሞቱ የተለያዩ አገራት ስደተኞች ቁጥር፣ ከ2ሺህ በላይ መሆኑን ተመድ አስታውቋል፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ተቋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚለው፤ በሜዲትራኒያን ባህር በአስቸጋሪ… በህይወት ከሌሉ የአለማችን ዝነኞች ከፍተኛውን ገቢ በማግኘት ላለፉት አምስት አመታት በመሪነት የዘለቀው የፖፕ ሙዚቃ ንጉስ ማይክል ጃክሰን ዘንድሮም በ313 ሚሊዮን ፓውንድ አመታዊ ገቢ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጡ ተዘግቧል፡፡ማይክል ጃክሰን ከኤሚ ሚዩዚክ ፐብሊሺንግ በተባለው አሳታሚ ኩባንያ ውስጥ ካለው የአክስዮን ድርሻና በህይወት… 2.6 ቢሊዮን ወርሃዊ ተጠቃሚዎች፣ 33 ሺህ 606 ሰራተኞች አሉት ታዋቂው ማህበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ እስካለፈው መስከረም በነበሩት ያለፉት ሶስት ወራት ብቻ የ13.5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱንና በየዕለቱ የሚጠቀሙ ደንበኞቹ ቁጥርም 1.49 ቢሊዮን መድረሱን አስታውቋል፡፡የፌስቡክ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ማርክ ዙክበርግ ባለፈው… በአገሪቱ ከ88 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በከፋ ድህነት ውስጥ ይገኛሉ ባለፉት አራት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ናይጀሪያውያን ወደ ከፋ ድህነት መግባታቸውንና በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥር 88 ሚሊዮን መድረሱን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡ተቀማጭነቱን በቪየና ያደረገው ወርልድ ፖቨርቲ… እንዴት ሰነበታችሁሳ!እንደተመለደው አይደል የሚባለው…እንደተለመደው ምስኪን ሀበሻ ብሶቱን ይዞ አንድዬ ዘንድ ብቅ ብሏል፡፡ምስኪን ሀበሻ፡— አንድዬ፣ አኔ ምስኪኑ ፍጥረትህ ነኝ፡፡አንድዬ፡— (ይቆጣል) አሁን ደግሞ ምን ፈለግህ?ምስኪን ሀበሻ፡— ተቆጣኸኝ እኮ፣ ምን አጠፋሁ?አንድዬ፡— አሁን ሌላውን ነገር ተወውና፣ ምን ፈልገህ ነው አፍሪካ 1 ትሪሊዮን ዶላር ከሚደርሰው የአፍሪካ አመታዊ አለማቀፍ ንግድ ውስጥ የአህጉሪቱ አገራት ያላቸው ድርሻ 15 በመቶ ብቻ መሆኑን ኦልአፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡ የአፍሪካ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ ሰሞኑን ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው ሀገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቶች የታደለች ብትሆንም፣ በሰው ሰራሽ ችግሮች ስትጎዳ በመቆየቷ ልትበለጽግ አልቻለችም፡፡ የሰው ሰራሽ ችግሮቹ ዋነኛው ምክንያት የፖለቲካና የአስተዳደር መሪዎች መስራት የማይገባቸውን ስለሰሩና መስራት የሚገባቸውን ደግሞ ሳይሰሩ ስለቀሩ ነው ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ጡረታ የወጣች አህያና አንድ ከቤት የተባረረ ውሻ አገር ለቀን እንሂድ ተባብለው ሲጓዙ፤ አህያዋ፤ “የማንታወቅበት አገር ሄደን አዲስ ሥራ ብንጀምር ጥሩ ነው” አለች፡፡ ውሻው፤ “መልካም ሃሳብ dinnerware glasses & jugs serveware gas stoves cookers & steamers induction cookers electric kettle espresso coffee maker juicer mixer grinders
8
የገዢው ፓርቲ እና የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዴሞክራሲያዊ ህብረተሰብ በመገንባቱ ረገድ ድርሻቸውን ከፍ እንዲያደርጉ ተጠየቁ። ቪዥን ኢትዮፕያ ፎር ዴሞክራሲ የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነው ሀገር በቀል ድርጅት ባዘጋጀው የአንድ ቀን ዓውደ ጥናት ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቭል ማህበረሰብ ተወካዮች እና ጋዜጠኞች ተሳታፊዎች ነበሩ። ገዢው ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዓብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ ኢህአዴግ ግን በዓውደ ጥናቱ እንዲሳተፍ ግብዣ ቢቀርብለትም ሳይሳተፍ መቅረቱን የአዲስ አበባ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር በላከው ዘገባ አስታውቋል። ዶ/ር አብይ አህመድ የጠቅላይ ሚኒሥትርነቱን ሥልጣን ከያዙ ወዲህ በየአካባቢው የሚደረጉ በአብዛኛው ብሔርን ምክንያት ያደረጉ ግጭቶች እየተባባሱ መጥተዋል። ቀደም ሲል በተለያዩ ምክንያቶች ጎላ ብለው መታየት ያልቻሉ ጥያቄዎች በአሁኑ ወቅት የብዙዎችን ሕይወት የሚያጠፉ፣ በርካታ ሀብት እና ንብረት የሚያወድሙ ግጭቶችን እያስከተሉ ነው።
9
መእተዊ፣- ብዕምቆት ኣብቲ ክልስሓሳባዉን ግብራዊ ጋህድታት ካይኣተኩ ብቅርጡዉ ኣጋባብ ንምግላጹ፣ ኣብ መንጎ ክልተ ወይ ካብ ክልተ ንላዕሊ ሰባት ወይ ኣግእዞታት ዝካየድ ምትፍናንን ምጽራርን እዩ። ግርጭት ኣብ ሂወት ደቂሰባትን ነገራት ሞጎታዊ ህላዌ ዘራጋገጸ ባህርያዉን ማሕበራዊ ክዉንነት እዩ። ነዚ ክዉንነት’ዚ ብመገዲ ድቀተ-ሓሳብ፣ ተንካፊ ስምዒትን ተግባራዊ ባህርያት ደቂ-ሰባት ወይ ነገራት ይፍጠር ከምዞሎ ክንዕዞቦ ይክኣል። ዝኾነ ነገር ን ወዲሰብ ኣብ ገዛእ ርእሱን፣ ካብ ገዛእ-ርእሱ ወጻኢ ብክልተ ተጻረርቲ ዝጋራጨዉ ባህርያት ዝቆመ እዩ። ግርጭት ኣዉንታን ኣሉታን ገጽታታት (negative & positive aspects of conflict) ዘጣመረ እዩ። ምግርጫዋት ናይ ኣዉንታን ኣሉታ ገጽታ ግርጭታት ምዕባሊ ይፈጥር። እዚ ፈቲና ጸሊኢና ባህርያዊን ማሕበራዊ ሕጊ እዩ። ኩሎም ባህርያዊን ማሕበራዊ ሕጊታት ድማ ካብ ኣትሓሳስባን ምቁጽጻራትን ወዲ ሰብ ወጻኢ እዮም። ወዲ ሰብ ምስ ጥቕምታቱ ብምዝማድ ከማሓድሮም እንበር ካብ ቀጻሊ መስርሓቶም ደዉ ከብሎም እዉን ተኽእሎ የሎን። ኣብ መስርሕ ዉሽጣዊ ምፍሕፋሕን ምትፍናን ግርጭታት ኣዉንታ ባእታ ግርጭት ንኣሉታ ክዕብልሎ እንኮሎ፣ ኣዉንታ ዝዓብለሎ ዉጽኢት ምዕብልና ይህልዎ፣ ኣሉታ ባእታ ግርጭት ንኣዉንታ ባእታ ግርጭት ምስ ዝዕብልሎ ድማ ኣሉታ ዉጽኢት ይህልዎ። ክልቲኦም ኣሉታን ኣዉንታ ባእታታት ግርጭት ዝተወደነን ዝተማጣጠነን ሓይሊ ኣብቲ ዘካይድዎ ግጥም ምስ ዝህሉዎም መብዛሕትኡ ጊዝያት ኣዉንታዊ ምዕብልና ይህልዎ ስሕት ኢሉ ድማ ብኣሉታ ዉጽኢት ይዛዘም። ግርጭት ኣብ ዉሽጢ ገዛእርእስኻን ምስ ካልኦት ሓይልታት ካባኻ ወጻኢ ዝካየድ ካብኮነ፣ ንተርእዮታት ግርጭታት ብኸምዚ ዝስዕብ ክንገልጾም ይክኣል፣- ቀዳማይ ክፍታሕ ዘለዎ ግርጭት ሰብ ኣንጻር ባህሪ ዘካይዶ ቅልስ እዩ። ባህርያዊ ግርጭት ንጥሜት፣ ድርቀት፣ ሕማም፣ ሞት፣ ምዕልቅላቕ ዝናብ፣ ድኽነት፣ድንቁሩና…ወዘ.ተ ዘጣቃልል ኮይኑ፣ ንገሊኦም ብመሰረቱ ብጻዕርታት ወዲ ሰብ ክዉገዱ ዝኽእሉ እዮም፣ ገሊኦም ድማ ከም ባህርያዊ ዘይተርፍ ትዕድልቲ ተወሲዶም፣ ምስኦም ክትነብር ምርጫታት ዘይህቡኻ እዮም። ካልኣይ፣ ሰብ ኣንጻር ሰብ ግርጭት፣ ወዲ ሰብ ጥቅምታቱ ንምርግጋጽን ካብ ሽዉሃት ምግባትን ነቲ ካብ ኣታሓሳስብኡን ድሌቱን ወጻኢ ዝኾነ ነገራት ንሙቑጽጻር ተባሂሉ፣ ዘካይዶ ቅልስ ዝኹስኩሶ ግርጭት እዩ። ኪናት፣ ቅትለት፣ ምብካል ቀላያትን ባሕርታትን፣ ምቅያር ጠባያት ኣየር ህዋ፣ ምፍሕፋሕ ማሕበራዊ ቀጸላታት ሕብረተሰብ፣ ዉድድር-ብቕዓት (competence)ምዝራቕ ሓተላታት ኒክሌርን ሬድዮ ኣክቲቭ፣ ምጽናት እንስሳ ዘገዳም፣ ምጽናት ዓሌት ወዲሰብ…ወ.ዘ.ተ ሓፈሻዊ ከምዚ ኣብ ላዕሊ ዝጣሕመስክዎ ካብ ኮነ ግርጭታት፣ ንወዲ ሰብ ቀዳሞት ጸላእቱ እቶም ኣብ ቀዳማይ ዓይነት ግርጭታትሰብ ኣንጻር ባህሪ ተዘርዚሮም ዘለዉ ከንሶም፣ ወዲሰብ ነቶም መሰረታዉያን ባህርያዊ ጸገማት ንምፍታሕ ኣብ ዝቃለሰሉ እዋናት፣ ሰብ ኣንጻር ሰብ ግርጭታት ንህላዊኡ ስለዝፋታተንዎ፣ ነቲ ቀዳማይ ክፍታሕ ዘለዎ ጸገማት ንጊዚኡ ኣወንዚፉ ነቶም ንህላዊኡ ዝፋታተኑ ዘለዉ ሰብ ኣንጻር ሰብ ግርጭታት ክፈትሕ ይዉስን። እዚ ዳይነሚክ እዚ ዘገንዝበና ጉዳይ እንተሃልዩ፣ ወትሩ ግርጭታት ምስ ሂወትና መናብርትና ምኻኖምን፣ ከከም ኣድላይነቶም ድማ ብቅድመተከተል (sequence) ሰሪዕና ክምንፈትሖምን ከምንቃለስም እዩ። ብዘይካ እቶም ሰብ ኣንጻር ባህሪ ግርጭት፣ ሰብ ኣንጻር ሰብ ግርጭት ምስ ዝኸዉን፣ ብቀዳምነት መንዕብ-ስነኣእሙራዊ ቅኒት (psychodynamics) ሃንደስቲ እቲ ግርጭት፣ ነቲ ግርጭት ከላዕልዎ እንከለዉ፣ ኣፍሉጣዊ-ድርኺት (conscious motivation) ድዩ ዘለዎም ወይስ ኣፍልጦ-ኣልቦ ድሪኺት (unconscious motivation) ምኻኑ ብንጹር ምፍላጥን ምልላይን ከድሊ እዩ። ንቅሓት ድሪኺታቶም ብግቡእ እንተፈሊጥካ ነቲ ዝተጋህደ ግርጭት ብኣጋባብ ንምትሓዙን ንምፍትሑ ኣጸጋሚ ኣይከዉንን እዩ። ብመሰረቱ ግርጭታት ተጻረርትን ተማላላእት ስለዝኾኑ ድማ፣ ኣብ ኣጋባብ ኣታሓሕዝኦምን ኣፋታትሖም ከምዝፋላለ ክንግንዘብ ይግብኣና። 1. ከም ብዓልmao tsetung ናይ ቻይና መራሕቲ ዝነበሩ፣ ንቀዳማይ ግርጭት ብሓይሊ ብረት ከምዝፍታሕ እዮም ዝእምቱ። ኣብዚ ናይ ማዎ ፍልስፍና ምስ ማሕበራዊ ቀጸላታትን ናይ ግዳም ጸላትን ተኣሳሲሩ ብቅድመተከተል ዝትንተን ኣጋባብ ኣታሓሕዛን ኣፋታትሓ ግርጭት ንቀጻሊ ኣብ ጎነጻዊን ፖሎቲካዊን ቃልሲ ዝጸምደካ ይኸዉን። 3. ሓንፈጽ ኣፋታትሓን ኣታሓሕዛ ግርጭት (mixed handling of contradiction) እዚ ድማ ደቂ ሰባት ምስ ዝገጥሞም ብድሆታት ኣብ ግምት ብምእታዉ ኣብ ሓደ ጊዝየ ክልተ መልክዓት ቃልሲ የካይዱ፣ ንሱ ድማ ሰላማዊን ጎነጻዉን ቃልሲ እዩ። መብዛሕትኡ ጊዝየ እቲ ዝገጥሞም ዓይነት ግርጭት ኣዝዩ ቁጡዕን ኣድማይን ምስ ዝኸዉን ንነብሶም ክካላኸሉ ስለዝግደዱ ብረት የልዕሉ እሞ፣ እንተብፍላጥ ብዘይፍላጥ ኣብ ዲዕ ዝበለ ጎነጻዊ ቃልሲ ይኣትዉ እዮም። ሰለስቲኦም ኣጋባብ ኣታሓሕዛን ኣፋታትሓን ግርጭት ኣብ ዝተፈላለየ ሃገራት ብክልስሓሳብን ግብሪን ከምዝሰርሑ እዉን ተገንዚብና እኳ እንትኾና፣ ዉጽኢታቱ ግን፣ ከምዝፋላለ እዉን ተማሂርና። ወትሩ ብጉራዴ ዝነግስ ብጉራዴ ከም ዝእለን ብሰላም ዝነግስ ድማ ብሰላም ከምዝእለ ተማሂርና። ዋላእዉን ሉዕላዉነት ጥሒሱ ክልሕቀካ ዝደሊ ገዛኢ ብሰላማዊ ኣጋባብ ቃልሲ ተጠቂምካ ክትኣልዮ ከምትኽእል ካብ ኣህዛብን ሃገርን ህንዲ ተማሂርና። ስለዚ እቲ ሰላማዊ ኣጋባብ ቓልሲ ፈጺሙ ኣማራጺ ዘይብሉ፣ ንምግታእ ቀጻሊ ምድማይ፣ ሰብኣዊን ነገራዊን ዕንወት፣ ሕንፍሽፍሻት ዝጠቕምን ልዕሉ ኽሉ ድማ ብሰላማዊ መገዲ ናይ ምስግጋር ፖሎቲካዊ ስልጣን መስርሕ ዘካናወነ፣ ምምዕባል ሲቪላዊ ሕብረተሰብን ዘራጋግጽን ብሓባር ብሰላም ዘንብርን ማሕበራዊ ፍትሒ ዘራጋግጽ ምኻኑ ፈሊጥና ኣሎና። መንቀሊ ግርጭት ቡዙሓት ሰራዉር ዘለዎ እዩ። ኣብ ዉሽጢ ሕብረተሰብን ጎዶቦታቱን ዝላዓሉ ግርጭታት እቲ መሰረታዊ መንቀሊታት ካብ ሰብኣዊ-ባህርያዊ ንቅሓት (human instincts) ካብ ዉድድር፣ ካብ ምንዳይ ጸጋታትን ሓይሊን ስልጣንን ዝነቕል እዩ። ገሊኡ እዉን ንመንነቱ (identity-based needs) ንምንዳይ ዝነቕል ኣሎ። እቲ ኮይኑ እዚ ምንጪ ናይ ግርጭት (sources of conflict) ብግቡኡ እንተፈሊጥካ፣ ኣብ መርሓ-ገበይ ግርጭታት ብምስፋር ነቲ መስርሕ ክትቓጻጸሮን ክትፈትሖ ይክኣል እዩ። ስለዚ ኣብ ቀጻሊ መግለጺታተይ ንግርጭታት ብቅድመ ተከተል እኳ ክሰርዖም እንተኾንኩ፣ ቀዳማይ ብጎነጽ ክፍታሕ ኣለዎ፣ ካልኣይ ድማ ብሰላም ዝብል ክኸዉን ከምዘይኮነ ምግንዛብ ከድሊ እዩ። እንታይ ድኣ ቀዳምነት ናይ ቀዳምነታት ጥራይ ምስራዕ ምኻኑ ክፍለጥ ኣለዎ። 7. ኣብ መንጎ ስርዓት ኣስመራን ስርዓት ኣዲስ ኣበባን፣ ኣብ መንጎ ስርዓት ኣስመራን ስርዓት ጅቡቲን፣ ኣብ መንጎ ስርዓት ኣስመራን ማሕበረሰብ ዓለም ኣይኩናት ኣይሰላምን ዙሑል ዲፕሎማስያዊ ጂኦ-ፖሎቲካዊን ዓለምለኻዊን ግርጭታት ዝካየድ ዘሎ እዩ። 2. ንክስደድ ኣዝዮም ቡዙሓት ደፋኢን ጎታቲን ረቛሒታት እኳ እንተሃለዉዎ፣ ነቲ ቀንዲ ዝደፍኦ ዘሎ ርቛሒ በቲሪ ኣብ ኢዱ ተመን ኣብ እግሩ ከንሱ፣ ነዚ ራሕሪሑ ዘይተደነ ዓሰርተታት ኣሽሓትን ዶላራትን ኣዝዩ ከቢድን ሓደገኛ መሳናኽላትን ክሓልፍ እንተ ብምትላል፣ ብምርጭኡን ብምግዳድ ኣብ ትሕቲ ዘይሕጋዉያን ኣሳጋገርቲ ወዲ ሰብ (human trafficking) ወዲቁ ከምሳዕቤኑ፣- ምንጪ ምፍራይ ሙኡዙዛትን ዘይሙኡዙዛትን ጭዋዳታት(organ harvesting) ኣካላት ወዲሰብ፣ ምንጪ ፋይናንስ፣ ቀለብ ዓሳን ኣሞራን ጊልያ ናይ መርወይ ጾታዊ ስምዒት ወዲሰብ ንክኸዉን ርእሰ-ቅትለት ዝፍጽም ዘሎ ኣካል ህዝቢ ኤርትራ። ስለዚ ኣብ እዚ እዋን እዚ ስለስተ ዓበይቲ መሰረታዉያን ግርጭታት ይብድሁና ከምዘለዉን ዝጣራጥር ጉዳይ ኣይኮነን። ብዘለና ዓቕሚ፣ ኣታሃላልዋ፣ ዉዳቤን ፖሎቲካዊ ቦታ(position) ድማ፣ ንሰለስቲኡ ኣብ ሓደ ግዝየ ንምግጣሙ ተኽእሎ ከምዘየሎ ፍሉጥ እዩ። እቲ ቀዳማይን ናይ ቀረባ ጠንቂ፣ ግጉይ ኣዕናዊ ግደ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ እዩ። ንኤርትራን ህዝቢ ኤርትራን ገጢምዎ ዘሎ ብድሆታትን ግርጭታትን እኩብ ድሙር ናይ ዝተፈላለዩ ግዳማዊን ዉሽጣዊ ሮቓሒታት ኣኳ እንተኾነ፣ ነቲ ኣጋጢሙ ዘሎ ብድሆታትን ግርጭታትን እዉን ብሙሉኡ ምንጩ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ እዩ እኳ እንተዘይበልኩ፣ መብዛሕትኡ ንብድሆታትን ግርጭታት ንከይንፈትሕ ዕንቅፋት ኮይንና ዘሎ ብርግጽ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ እዩ። 1. ቀዳማይ ስለዚ ጽምዶ ቃልስናን መጀመርታ ክፍታሕ ዘለዎ ግርጭት ትኹላዊ (vertical) ኣብ መንጎ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ፣ ኩሉ መሰሉን መንነቱን ዝተመንዝዔ ህዝቢ ኤርትራ እዩ። ብባህርያቱ እቲ ግርጭት ድማ ናይ ማሕበራዊ ቀጸላታት ቃልሲ ስለዝኾነ፣ እቲ ዝካየድ ቅልስ ማሕበራዊ ሰዉራ ኮይኑ፣ ስለማዊ ኣጋባብ ቃልሲ ዝተኸተለ ክኸዉን ኣለዎ። ምኽንያቱ ንኹሉ ኤርትራዊ ዓቕምታት ኣብ ሓደ ጽምዶ ማኣዝን ኣትሒዝናን ኣዋህሊልና ነቲ ቀዳማይ ግርጭት ክንፈትሕ እንተወሲና፣ ኣብ ትሕቲ ዝኾነ ይኹን መስርሕን ታሪኽ ኩነታት ዓቕሚ ህዝቢ፣ ልዕሊ እቲ ኣብ ፖሎቲካዊ ስልጣን ዘሎ ፖሎቲካዊ ጉጂለ ስለዝኾነ ክዕወት እዩ። ኣብዚ ክፍለጥ ዘለዎ ሓቂ ግን፣ ህዝቢ ባዕሉ ካይተሳተፈን ካይተንቃሳቐሰ ሽግራቱ ብፖሎቲካዊ ዉድባት፣ ሰልፍታት፣ ግንባራትን ምንቅስቓሳትን ጥራይ ክፍታሕ ኣይክኣልን እዩ። ኣብ በኒን፣ ኣብ ዩጉዝላቪያ ነበር፣ ኣብ ደቡብ ኣፍሪቃ፣ ኣይቮሪኮስት፣ ላይቬርያ…ወ.ዘ.ተ ናይ ዝቀረበ ጽቡቕ ናይ ሕማቕ ኣብነት ክኸዉን ይኽእል እዩ። ዝተፈላለያ ዉድባት ነይረንኦም እቲ ጸገም ክፍታሕ ኣይተኻእለን፣ ህዝቢ ባዕሉ ምትእትታዉን ምንቅስቓስን ምስጀመረ ግን ፍታሓት ክጋሃድ ጀሚሩ። ብግብሪ እዉን ኣባና ክንዕዘቦ ይክኣል እዩ። ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ዝመርሓ ኤርትራ፣ ንተሳትፎ ህዝቢ ስለዘዋስንን ዝሕርም ዝያዳ ዉግእ፣ ስደት፣ ሓድሕዳዊ ጽልኢ፣ ድኽነትን ብትከት፣ ፋሕ-ጭንጋራሕ…ወ.ዘ.ተ ኮይኑ ኣሎ። ስለዚ ብዘይ ተሳትፎ ህዝቢ ዝፍታሕ ነገር ከምዘየሎ ብርግጽ ክንፈልጥ ኣሎና። 2. ካልኣይ ናይ ተቃዉሞ ኤርትራ ፖሎቲካዊያን ጨለታትን (elite) ፈሊጣን (scholars) ንዉልቃዊን ጉጂላዊ ረብሓታቶን ንምርግጋጽ፣ ዘናዓዕብዎን ዝኹስኹስዎ ኣዝዩ ጸቢብ ኣብ ትሕተ-ሃገርነትን ኣብ ሕሉፍ ተሞክሮ ዝተሰረተ ምትእስሳራት እዩ። እዚ ሓደገኛ ዘማዊ ሓይሊ እዚ ካብ ቅርሕንትን ሒነ ምፍዳይን ስለዝነቕል፣ ኩሉ ንቅሎታቱ ካብ ታሪኽ ጀብሃን ሻዕብያ ከም መወከሲ ብምጥቃም፣ ሒነ ክፈዲ ኣብ ዝተፋላለየ መድረኻት ሽሙን ፖሎቲካዊ መደብ ዕዩኡ ዝቕይር ብዉሽጡ ግን ሕልምታቱን ዕላማታቱን ፈጺሙ ዘይቅየር እዩ። እዚ ሓይሊ እዚ ካብ ገባቲ ስርዓት ዝፈልዮ ባህርያት የብሉን። ምስ ገባቲ ስርዓት ህግደፍ ባህሪ-ሓደ (homogeneous) ዘለዎም እዮም። ዝፈልዮም ዘይመሰረታዊ ነገር እንተሃልዩ እቲ ሓደ ፖሎቲካዊ ስልጣን ዓቲሩ ኣሎ፣ እቲ ሓደ ድማ ፖሎቲካዊ ስልጣን ዘይዓተረ ብሙኻኑ እዩ። እዚ ሓይሊ እዚ ልክዕ ከም ህ.ግ.ደ.ፍ ጸረ ሲቪክ ሃገራዉነት እዩ። ንሲቪክ ሃገራዉነት ኤርትራ ሃሪሙ ብሃይሞኖታዊ፣ ኤትኒካዊን ክሊ-ጂኦግራፊካዊ ሃገርነት ከራጋግጽ ዝጽዕት ወይ ድማ ንእኧርትራ ከምዚ ዓለባ ብመቀስ ቆራሪጹ ብምምቅቃል ቀጺሉ ክትክባ ዝህቕን እዩ። ልዕላዉነት ህዝቢን ሃገር ድማ ኣይንታዩን እዩ። ምስ ዝኾነ ናይ ግዳም ሓይሊ ተኣሳሲሩ ዕላሙኡ ክወቕዕ እዉን ፈጺሙ ዘእግሞ ኣይኮነን። እዚ ሓይሊ እዚ ዝጻዓረ እንተጽዓረ ኣብ ማሕበራዊ ስነኣእሙራዊ ኣቓዉማ ኤርትራ ቅቡል ስለዘይኮነ፣ መላእ ደገፍ ናይ ህዝቢ ስለዘይረክብ ዕርፍካ እንተኣጽኒዕካ ናብ ዘብሎ ስለዘይብሉ፣ ክናዓቕ ኣኳ እንተዘይተገብኤ ክጽይቕ ስለዝኽእል ብዉሕልነት ቀስ ብቀስ ካብ ህዝቢ ከምዝንጸልን፣ ጥራይ ዕርቓኑ ከምዝወጽእ ምግባር ኣኻሊ እዩ። እዚ ድማ ብሙዕብሉን ቬርገሳዊ ኣጋባብ ጽምዶን ሰላማዊ ኣጋባብ ቃልሲ ክትሓዝ ይክኣል እዩ። ንመረዳእታ፣- ካብ ሮራን ሰምሃርን ሳጊሞም ኣብ ዓላ-ባዚት ዝነብሩ ኣለዉ፣ ካብ ሓማሴን ሳጊሞም ኣብ ምዕራባዊ ቆላ ትግሬ ኮይኖም ዝነብሩ ኣለዉ፣ ገሊኦም ድማ ኣሰራቶም ኣብ ዓድታት ከበሳ ሓዲጎም ናይ መጨረስታ መዕሬፊኦም ኣብ ሰንሒት ሳሕል ባርካ ዝወድኡ ኣለዉ። ዓድ-ተማርያም፡ ቤት-ኣስገደ፡ ሓለንጋ ዝብሃሉ እንዳታት ካብ ህዝቢ ከበሳ ከም ዝመንጨው መዛግብ ታሪኽ ጥራይ ዘይኮነ ንሳቶም ባዕላቶም ዝኣምኑሉ ጉዳይ ኢዩ። ጽኑዕ መረዳእታ መታን ክከዉን እንዳ ሓለንገ መቦቖሎም ካብ ዓዲ ባሪ (ሕጂ ኣብ ሰራየ ዝርከብ ዓዲ እዩ፣ ቀደም ወራራት መሳፍንት ትግራይ ኣብ ዓዶም ዓዲ ባሪ መጽዮም ምስተዋግእዎም ሳጊሞም ንምዕራባዊ ቆላታት ወሪዶም ክሳብ መላእ ምብራቕ ሱዳን እዉን ተዘርጊሖም ኣለዉ። ካብ ዓዶም ዓዲ ባሪ ክድፍኡ እንኮሎዉ ቋንቕኦም ትግርኛ ሃይማኖቶም ክርስትና እዩ ዝነበረ። ኣብ ዝተሰድድሉ ቦታ ብካልእ ቋንቋ ብካልእ ሞሎኮታዊ እምነት ክርዕሙ ኪኢሎም ኣለዉ፣ ካብ ደማዊን ሞቦቆላዉነቶም ዝፈልዮም ጉዳይ ግን ኣይኮነን። 4. ራብዓይ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ምስ ጎራባብቲ ሃገራትን፣ ሃገራት ዓለምለኸ ዝፈጠሮ ናይ ኣይኩናትን ሰላምን ተታፋፋኒ ዲፕሎማስያዊ ግርጭታት እዩ። እዚ ግርጭት እዚ ምስ ጂኦ-ፖሎቲክስን ዓለምለኻዊ ፖሎቲካን ተኣሳሲሩ ስለዝግለጽ ኣዝዩ ሰፊሕ እዩ። መታን ኣብ ህዉተታ መታን ካየእትወና ብሕጽር ዝበለ ኣብቲ ቀንዲ ኣቶኪረ ክጥሕምሶ እየ። እቲ ቀንዲ ግርጭት ኣብ መንጎ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ሕሉፍ ሃገራዉነትን ፣ስርዓት ወያኔ ኤትኒክ ሃገራዉነት፣ ምንዳይ ኣፍደገ ባሕሪን፣ ሓበሻዊ ናይ ሩሑቕ ሃገርነት ጽንፋዉነት እዩ። ዓለምለኸ ምስ ኢትዮጵያ ምጽጋዕ ጥቕምታቱ ስለዘዉሕሰሉ ድማ ምስ ኢትዮጵያ ናይ ዲፕሎማስያዊ ቓል ኪዳን ብምምስራት ኣንጻር ኤርትራ ደዊ ኢሉ ኣሎ። ነዚ ዘይነጽፍ ምትሕግጋዝ ዓለምለኸ፣ ኢትዮጵያዉያን ብምጥቓም ድማ ነቲ ጉዳይ ካብግቡኡ ንላዕሊ ቀይሕ መስመር ብምጥሓስ፣ ንኤርትራዊ ሃገራዉነት ንምድኻምን ንምፍንጣሕን ሓንቲ ካልኢት ናይ ጊዝየ ብዘይሙቁራጽ ይሰርሑሉ ኣለዉ። 4. ኣብ ትሕቲ ሽፋን ምውዳቅ ስርዓት ኢሳያስ፡ ንኤርትራ ካብ ከባቢናን ዞናናን ዓለምን ንምንጻልን ንምድኻምን ዘይሕለል ዲፕሎማሲያዊ ቃልሲ የካይዱ፡፡ ናይ ባይቶ ጸጥታ ኣብ ልዕሊ ኤርትራ ዚተወስደ ናይ እገዳ ውሳኔ፡ ሓደ ካብቲ ዝገነየ ውጽኢት ናይ’ዚ ወፈራ’ዚ እዩ። 5. ኢትዮጵያውያን ህዝብና ብፍላይ ከኣ መንእሰያትና፡ ሃገሮም ገዲፎም ንኽስደዱ ዘተባብዕ ፖሊሲታት የዘውትሩ፡፡ መንእሰያትና ብብዝሒ ኣብ መደበራት ናይ ስደት ኢትዮጵያ እናኣከብካ ንምዕራብ ንምስፋሮም ዚካየድ ዘሎ መደባት ሓደገኛቱ ብሩህ’ዩ 7. ግሁድ፡ መንግስቲ ናይ “ምቅያር” ቀጥታዊ ኢድ ኣእታውነት ኣዋጃትን መደረታትን ብምስማዕ፡ ኣብ ኤርትራ፡ ናይ ሻቕሎትን ስግኣትን ቅልውላው ፈጢሮም፡፡ እቲ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ክህልው ዝነበሮ ዝምድና በዚ ኣብ ላዕሊ ዝተቕሰ ኢትዮጵያዊ ወስታታት ጥራሕ ኣይኮነን ንቡር መልክዑ ካብ ምሓዝ ዚበርዓነ፡፡ ካብ ተግባራት ኢትዮጲያ ብዘይንእስ፡ ህግደፋዊ ፖሊስን ተግባራትን እውን ዚዓበየ ተራ ኣለዎ፡፡ ካብዚ 7 መሰረታዉያን ነገራት ብምንቃል፣ ኣብ ቅድሚ’ዚ ኩነታት’ዚ፡ ሃገራውያን ሓይልታት ኤርትራ፡ ፍሉይ፡ ኩሉ ሸነኻዊ መጥቃዕትታት ኢትዮጲያ ብምምካት፡ ልዕላውነት ኤርትራ ዚዕቀበሉ፡ ሃገርናን ዞናናን ሰላምን ርግኣትን ዚረኽበሉ፡ ኩነታት ንምውሓስ ኣበርቲዖም ኪሰርሑ ከም ዘለዎም ንምርኣይ ኣሸጋሪ ኣይኮነን፡፡ እቲ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዘሎ ምውጣጥ ብቐንዱ ምናልባት፡ ኣብ ዞናና ናይ መን መርሔ፡ መን ዓብለለ፡ ኮይኑ፡ እንተወሓደ ናይ ባሕሪ ኣፍደገ ንምርካብ ንግዝኣታዊ ሓደነት ኤርትራ ዚፈታተን፡ እንተተኻኢሉውን ንኤርትራዊ ነጻነት ናይ ምቕልባሱ ኢትዮጵያዊ ሃንቀውታ ዚተሓዋወሶ ኣዩ፡፡ ክሳብ ህግድፍ ኣብ ኤርትራ፡ ህወሓት ኣብ ኢትዮጲያ ኣብ ስልጣን ዚህልዋ፡ ምናልባት’ውን ኣብ ክልቲኡ ሃገራት፡ ደሞክራሲያዊ መስርሕ ክሳብ ዚተኣታቶ፡ ዝምድና ኤርትራን ኢትዮጵያን ምሉእ ፍታሕ ክረክብ፡ ንቡር ናይ ክልተ ነጻ ሃገራት መልክዕ ክሕዝ ኣሸጋሪ ምዃኑ’ውን ተረዲና ኑጹር ስትራተጂን ስልቲን ክህልወና ይግባእ። ንዝኾነ እብ ልዕላዉነት ኤርትራ ዝስንዘር ወትሃደራዊ መጥቓዕቲ ክንኩኑኖን ስግሩ እዉን ምስ ህዝብና ደዉ ክንብል ከምዘሎና ንግምግም። ብዛዕባ ጅቡቲ እንተኾይኑ ለጠፍን ኣብ ምስሳይ ምጣኔ-ሃብታዊ ረብሓ ዝተሞርኮሰ ንቡር ንጥፈት እዩ። ጅቡቲ ነቲ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዘሎ ግርጭት መዝሚዛ፣ ወደባታ ኣፍደገ 85 ሚልዮን ህዝቢ ብሙኻን 1.4 ቢልዮን ዶላር ንዓመት ተእቱ ኣላ ። እዚ ድማ ኑቡር ሃገራት ዘካይድኦ ምጣኔሃብታዊ ስትራተጂን ስልቲን እዩ። ናይ ካልኦት ሃገራት ግርጭት መዝሚዝካ ረብሓታትካ ምርግጋጽ እንበር፣ ተጻራሪ ኣይኮነን። ከምኡእዉን ምስ ሱዳንን የመን ዘሎ። 6.ኣቀዲሙን ኣብ እዋን ሓርበኛዊ ቃልሲ ዝሰረጸ ኤርትራዊ ሲቪክ መንነት፣ ሲቪክ ሃገራዉነትን ሓድነት ህዝቢ ኤርትራ ዘዕቁብን ንምትራሩ ብግብሪ ዝሰርሕ ምስዝኸዉን። 8.ካብ መሳሪሒ ናይ ግዳም ሓይልታት ናጻ ምስ ዝኸዉንን ካብ ጸቢብን ትሕተ-ሃገራዊ ዝንባሌታት ዝተናገፈ፣ ኣብ ኤርትራ ብሰላም ብሓባር ንምንባርን ማሕበራዊ ፍትሒ ንምርግጋጽ ዝቃለስ ምስ ዝኸዉን። ኣብዘን መሰረታዉያን ጉዳያት ክንራዳዳእ እንተዘይተኻኢሉ፣ ብሓባር ኣብ ሓደ ዋላ ምስራሕ ኣጸጋሚ ክኸዉን እዩ። እቲ ዕላማ ዘተና ኣብ ኩሎም ወሰንቲ ሃገራዊ ሞቖምያታት ብምስምማዕ ናብ ሓደ ዘይምእኩል ናይ መሰረታት ምንቅስቓስ ብሓደ ዓቢ ቻርተር (grand charter) ዝምራሕ ናይ ጸቕጥን ለዉጢን ኡግሚ (potential) ንምፍጣር ስለዝኾነ እዩ። ኣብዚ ዋላ እዚ ንዝተፈላለየ መልክዕ ዉደባ ዘለወን ብሓባር ከስርሕ ዝኽእል እዩ። ንሱ ድማ ፖሎቲካዊ ዉድባትን ሰልፋዊ ቅርጻ፣ ሲቪል ምንቅስቓሳትን ሲቪክ ናይ መሰረታት ፖሎቲካዊ ምንቅስቓስ ክሳብ ንዉልቀ-ዜጋን እታ መሰረት ሓደ ሕብረተሰብ ዝኾነት ስድራቤት ኣብ ግምት ዘተወ እዩ። እዚ ዝተፈላለየ ቅርጻታት ንመትከላት ሲቪክ ሃገራዉነት ከዕዉት እንተተሳማሚዑ፣ ንካልኦት ኣብ ዚ ዋላ ዚ ዛጊት ዘይኣተዋ እዉን ከፋት ኣፍደገን ዘታባብዕን ኑጹርን ኣሳታፊን ቅርጻ ዘለዎ እዩ። 1.ነፍስወከፍ ምንቅስቃስ ብዲሞክራስያዊ ኣጋባብ ኣብ ዉሽጣ ዝተመርጸ፣ ብቀጥታ ኣባል ባይቶ ዋላ ዝኸዉን ሓደ ተወካሊ ኣባል ትሰድድ። እዚ ድማ ንሕቶ ተሳቶፍነትን ሕቶ ዉክልና ከራጋግጽ እዩ። 2.ምስ እዚ ኣቀዲምና ዝጣሕመስናዮ፣ ካልኦት ተወከልቲ ኣባላት ኣብቲ ዋዕላ ተሳቲፎም፣ ብኣባላት ዋዕላ ንኣባልት ባይቶ ብዉድድር ዝምረጹ ድማ ይስደዱ ማለት እዩ። እዚ ድማ ንሕቶ ተሳቶፍነት፣ ሕቶ ዉክልናን ሕቶ ብቕዓት ከራጋግጽ እዩ። ፈጻሚ ኣካል ክምረጽ እንኮሎ ቡቁዕ ሰብ ንዝበቕዖ ስራሓት(action oriented) መሰረት ብምግባር ይምረጽ። ዋዕላ ንኣባላት ባይቶ ዋላ ይመርጽ። ዝተመርጸ ባይቶ ኣቀዲሙ፣ ንዋና-ጽሓፊ-ልፍንቲ (ኣካያዲ ፈጻሚ አካል)፣ ኣካቢ-ባይቶን ጠቕላል ተቖጻጸርን ይመርጽ፣ ቀጺሉ ድማ ንፈጻሚ ኣካል ይመርጽ። ዋና-ጽሓፊ ልፍንቲ ንሓለፍቲ ክፍልታት ይሮቕሕ፣ ብቅዓቶም፣ ተወፋይነቶም፣ ድልዉነቶም…ወ.ዘ.ተ ብሓጋጊ ኣካል ልፍንቲ ተመዚኑ ይጸድቀሉ። ትሕቲ ምምቕራሕ ስራሕ ጽሓፍት ክፍሊታት ዘሎ ናይ ተሓጋገዝቲ-ጽሓፊቲ እዉን ብጽሓፍቲ ክፍሊታት ይሩቑሑ ንኣቦ ወንበር ይቀርበሉ፣ ኣቦ ወንበር ምስ ሓጋጊ ኣካል ብምርድዳእን ብምትዕግጋብን ይጽድቕ። 3.ምስ ካልኦት ኣዘመዉቲ ናይ ፖሎቲካ ሓይልታት፣ መሰረታዊ ናይ ስልትን ስትራተጂን ፍልልያት እኳ እንተሃለወና፣ ክሳብ ቀጥታዊ ጨቖንቲ ዘይኮኑ፣ እቲ ግርጭት ጋድማዊ እዩ። 4.ምስጎዶቦና ሃገራት ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ ጁቡቲ…ወ.ዘ.ተ ክሳብ ልዕላዉነት ሃገርን ህዝቢ ጥሒሰን ኣካላዊ ወራር ዘይፈጸማ እቲ ግርጭት ጋድማዊ ኮይኑ፣ ብፍላይ ምስ ኢትዮጵያ ኣብ ኣይኪናት ኣይ ሰላም ስለንርከብን፣ ኣብ ዉሽጢ ልዑላዉነት መሬት ኤርትራ ጎቢጦም ብምህላዎም ምስ ኣቀዲመ ኣብ ላዕሊ ዝጣሕመስክዎ ድንዕታታ ኢትዮጵያ ኣብ ልዕሊ ኤርትራ፣ እቲ ግርጭት ንሓንሳብ ትኹላዊ ንሓንሳብ ጋድማዊ ትሕዝቶ ዘለዎ እዩ። ከከም ኣማጻጽኡ ድማ መልክዕ እቲ ግርጭት ክሕዝ ይኽእል። ስለዚ ቀዳማይ ክፍታሕ ዘለዎ ግርጭት ኣብ መንጎ ህዝቢ ኤርትራን ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ዘሎ ግርጭት ከምዝኾነ ንመዝን። እዚ ግርጭት እዚ እንተድኣ ተፈቲሑን ቅዋማዊት ኤርትራ እንተተራጋጊጹ፣ ኩሉ ጋድማዊ ግርጭታት ብሙሉኡ እኳ እንተዘይኮነ መብዛሕትኡ ክፍታሕን ክማሓደርን ስለዘኽእል እዩ።
10
@dawit, i was the one among those who supported your decision of returning back to your home country hoping that you will continue reporting independently with full impartiality. but now, it seems that you are becoming loyal to the ruling party. ሬድዋን አንድ ስህተት ቢሰራ በድፍረት ለመተቸት የምትችልበት እድል ያለህ አይመስለኝም፡፡ እንደውም እሱን የሚተቹ ሰዎችን ስታብጠለጥል እያየን ነው (ቤን ላይ የጻፍከውን ማስታወስ በቂ ነው) አንተን የመሰለ የመርህ ሰው እንደማጣት ምን የሚያንገበግብ ነገር አለ፡፡ አንድ ቃል የተነፈሰን ሁሉ እንደ ጥጃ እያሰሩ ምዕራቡ አለም ከሚያደርገው የተለየ ምንም አላደረግንም ከሚሉት ጋር መድረክ ላይ ተቀምጠህ ልይህ…? ዳዊት ሆይ! ከሬድዋን ጎን ተቀምጠህ ጀርባችንን ታርዳለህ ብዬ አንድም ቀን ገምቼ አላውቅም ነበር፡፡ ነገ ጨለማው ሲገፈፍ መግቢያህ የት ይሆን… shame on you!
11
ለካ ሬድዋን አስሬ አሜሪካ የምትመላለሰው ይህንን ሊታጠና ነበር፡፡ እዚህ ዋሺንግተን ያለን አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ቪዲዮ ለስቴት ዲፓርትመንት ማቅረብ አለብን next time the us embassy in addis should stop issuing his entry visa to the us
12
"1/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት/ የመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ጽ/ቤት አስተዳዳራዊ እና መዋቅራዊ ችግሮች የዳሰሰ ምልከታ" ነጻ ፓትርያርክ ምርጫ ቢሆን ኖሮ ማንን ይመርጡ ነበር? እንበልና ሁሉም ነገር ሥርዓቱን ጠብቆ የተከናወነ የእጩዎች ምርጫ ቢሆን ኖሮ፣ አሁን የምናነሣቸው ጉድለቶች ባይኖሩ ኖሮ፣ 6ኛው ፓትርያርክ እንዲሆን የምትመርጡት ማንን ነበር? (ማሳሰቢያ፦ አሁን ያለው ክፍፍል እና የመንግሥት ተጽዕኖ ባይኖር ኖሮ ተብሎ የሚመለስ ጥያቄ ነው። የምን “ባይኖር ኖሮ ነው” የሚል አስተያየት ካለዎትም እናከብራለን።) ውድ ደጀ ሰላማውያን፤ የፌስቡክ “ጓደኞቻችን” ቁጥር 5 ሺህ በመሙላቱ አዲስ ሰዎችን መጨመር አንችልም። ስለዚህ አዳዲሶችም ሆናችሁ የቀድሞ የፌስቡክ ጓደኞቻችን ከዚህ በታች ያለውን እና "like" የሚለውን ቃል በመጫን በዚያ እንድትከታተሉን በትህትና እንጠይቃለን።
13
mxwtp, ቻይና ኤሌክትሮኒክ እና የኤሌክትሪክ መስክ ጫፍ 5 ላይ አንድ ባለሙያ በአንድ አቁም-ኤሌክትሮኒክ እና የኤሌክትሪክ ትሬዲንግ መድረክ, yueqing, ዠይጂያንግ, የቻይና ቻይና electron ከተማ ውስጥ ይገኛል. የአካባቢው እና በዙሪያው አካባቢዎች ውስጥ ሲጠናቀቅ የኢንዱስትሪ ሰንሰለቶች, የኢንዱስትሪ ጥቅሞች እና በርካታ ሀብቶች ላይ ተመርኩዘው, mxwtp ክወና ውስጥ ሽያጭ, የመጋዘን, ሎጂስቲክስ እና አገልግሎቶች ጋር በማዋቀር, 600 ሺህ ካሬ ሜትር መጋዘን ጋር አንድ ወጣት ኮከብ ድርጅት ውስጥ የዳበረ ነው. mxwtp በ 2016 ታላቅ ሽያጭ ጥራዞች ከ 100 ሚሊዮን rmb የተፈጠሩ ይህ ዓለም አቀፍ ደንበኞች ትብብር ለመወያየት የእኛ ኩባንያ መጥቶ ነው, እኛ ለማጫወት ያለንን በአካባቢው በጣም ታዋቂ እንደሚሯሯጥ huangtan ዋሻ ወሰዳቸው መስከረም 11, 2017 ላይ ሁለተኛው ሁሉ ጫፍ bbs "አካባቢ" የአገሪቱ ግዙፍ ዓ.ም አብረው ተነሳሽነት መለቀቅ "መንገዱን ሁሉ በመንገድ", ሆንግ ኮንግ የአውራጃ እና ኤግዚቢሽን ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ...
14
በቡድን ተደራጅተው የተለያዩ የወንጀል ተግባራትን ሲፈፅሙ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ በባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ - monday, 21 august 2017 09:11 በተለያዩ ቤተክርስቲያናት በመግባት ከሙዳየ ምፅዋት ውስጥ ገንዘብ ሲሰርቅ የነበረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ - wednesday, 01 november 2017 11:17 ዕውቅናና ማበረታቻ ተሰጠ!የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በስራ እንቅስቃሴዎቻቸው ጎልተው በመውጣት ከተጠርጣሪዎች የገንዘብ መደለያ አንቀበልም ሲሉ ለህግ በማቅረብ ለሰሩት አኩሪ ተግባር ለአመራርና ለአባላቱ የገንዘብ ሽልማት ሰጥቷል፡፡ መስከረም 12 እና መስከረም 22... *********************************መስከረም 01 ቀን 2011 ዓ/ም በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ሲሆን በቂርቆስ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው ቦልጋሪያ ( የድሮ በግ ተራ ) ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕድሜያቸው የ19 እና የ20 ዓመት የሆኑ እህትማማቾችን... የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን 1439ኛው የአረፋ በዓል በሰላም እንዲከበር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ ለመላው የእምነቱ ተከታዩች በዓሉ የሰላም የደስታ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን ገልፆል፡፡አዲስ አበባ የአረፋበዓል... የዓለም ባንክ በ175 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ 275 የሞተር ሳይክሎችን እና 32 ተሽከርካሪዎችን ግዢ በመፈፀም ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አበርክቷል፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ዶ/ር ኢ/ር ሠለሞን ኪዳኔ እና... የኢ/ፌ/ፖ/ኮ/ኮሚሽነር ጀኔራል ዘይኑ ጀማል እና ሌሎች የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የፖሊስ ኮሚሽነሮች እና አመራሮች በተገኙበት አዲስ አበባ ስብሰባቸውን አካሂደዋል፡፡የውይይቱ አጀዳዎች መካከል የፖሊስ ሪፎረም፤የሰራዊቱ ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም፤ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ የመሳሰሉት... የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የቦክስ ቡድን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌደሬሽን የሚያዘጋጀውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክልቦች ሻምፒዮና ውድድር ላይ ተካፋይ በመሆን አራት ዙር በሴት 6 የወርቅ፣ 3 የብር እና 6 ነሐስ በአጠቃላይ በ15... ሴት ሞተረኛ ትራፊክ …!የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ትራፊክ አደጋን በመከላከልና የትራፊክ ፍሰቱን ሊያሳልጡ የሚችሉ ለሦስት ወራት ያሰለጠናቸውን የሞተረኛ ትራፊክ አባላት አስመርቋል፤ በስልጠናው ላይ 173 አባላትን ያካተተ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ... የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦክስ ፌዴሬሽን ከጎጆ ክሬቲቭ ሚዲያ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የስፖንሰር የቦክስ ውድድር ላይ የተስተዋለው ስፖርታዊ ጨዋነት ለሌሎች አርአያ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ሪፖርተር፡- ኮን/ል አባበል ከበደ ጥቅምት 19 ቀን 2010... ለህክምና የመጣችውን የ3 ልጆች እናት አስገድዶ የደፈረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ፖሊስ ገለፀ፡፡ ሪፖርተር፡- ዋ/ሳጅን ከድር መሀመድ ነሀሴ 10 ቀን 2009 ዓ/ም ነው ወንጀሉ የተፈፀመው፡፡ ቦታው ደግሞ በልደታ ክ/ከተማ... ሪፖርተር፡- ዋና ሳጅን ከድር መሀመድ መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ/ም ነው ወንጀሉ የተፈጸመው ቦታው ደግሞ በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ማርያም ቤ/ክ ቅጥር ግቢ ነው ፡፡ ተከሳሽ ወደ... ‹‹ ራዕይ ሠንቀናል ለላቀ ድል ተነሳስተናል!! ››‹‹ ራዕይ ሠንቀናል ለላቀ ድል ተነሳስተናል!! ›› በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 10ኛዉ ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀንን ለማክበር የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከ3መቶ በላይ በየደረጃዉ... በአ/አበባ ከተማ በተለያዩ ክ/ከተሞች ጊዜ ተወስዶ በተደረገ ሰፊ ጥናት ፖሊስ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች በ88 የተለያዩ የወንጀል ፈፃሚዎች ቡድን የተደራጁ 216 ግለሰቦች መሆናቸውን የገለፁት በኮሚሽኑ የኢኮኖሚና የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዲቪዚዮን... በኦሮሚያ ክልል ሰበታ ሃዋስ ወረዳ ላይ በሚገኘው የደብል ተራራ ላይ የኮሚሸኑ አመራርና አባላት የችግኝ ተከላ ያካሄዱት ሐምሌ 23 ቀን 2009 ዓ.ም ነው፡፡ በዕለቱ ‹‹ ለአረንጓዴ ልማታችን ስኬታማነት ሁሌም በትጋት እንሰራለን... ሃይሉ ቡናሮ ወንጀሉን የፈፀመው ግንቦት 27 ቀን 2009 ዓ/ም በአራዳ ክ/ከተማ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የአ/አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት መነሻ ፌርማታ አካባቢ ነው፡፡ ተከሳሹ በተጠቀሰው ቀን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በመግባት ግምታቸው 6 ሺ... ወንጀሉ የተፈፀመው የካቲት 14 ቀን 2009 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ሲሆን በን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ልዩ ቦታው ላፍቶ ባንኮች ማህበር እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ ሟች አቶ ተወልደ ገ/አምላክ በመኖሪያ ቤታቸው...
15
(ደጀ ሰላም፤ ጃኑዋሪ 11/2011፤ ጥር 3/2003 ዓ.ም)፦ በዚህ ሰሞን አዳዲስ የጡመራ መድረኮች ወደ ንባብ ብቅ ብለዋል። አዲስ የጡመራ መድረክ (ብሎግ) በመክፈት አገልግሎት መስጠት የጀመሩት “አደባባይ” (የዲ/ን ኤፍሬም እሸቴ) እና “ግእዝ በመስመር ላይ፤ geezonline” ይሰኛሉ።
16
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ባለፉት 24 ዓመታት ፍፁም የበላይነት የያዘው ኢሕአዴግ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ወደ አመራር ከመጡ በኋላ ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች ቅድሚያ የያዘው መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚደ...
17
ፖሊስ መምህር ግርማ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት የሆነው ወንጀል የተፈፀመው መስከረም 2006 ዓ . ም ነው ብሏል። በየካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ወሰን ግሮሰሪ እየተባለ በሚጠራው ...
18
በቅርቡ ህይወቷን በመኪና አደጋ ያጣችው የተዋናይት ሰብለ ተፈራ ባለቤት አቶ ሞገስ ተስፋዬ የወንጀል ክስ ተመሰረተበት፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ በ 09/02/08 ፅፎ ያወጣበት የክስ ...
19
ኤጀንሲው ኣዲስ ለተሾሙ ባለስልጣኖች የሚሰጥ ቤት እንደሌለው ወይም ዕጥረት እንዳለበት በመደጋገም ይገልጻል :: ከ 30 በላይ የሚሆኑ የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ሠራተኞች በአፓርታማው ... ቁርጥራጭ ብረቶችን ወርቅ ነው ብሎ $ 95,553,413.89 ብር ከብሄራዊ ባንክ አጭበርብሮ ወስዷል ተብሎ የ 25 ዓመት ጽኑ እስራት እና 180 ሺ ብር የተፈረደበት ...
20
(ደጀ ሰላም፤ ጁላይ 15/2010)፦ የሚከተለው ሪፖርታዥ የተወሰደው ከማ/ቅዱሳን ድረ ገጽ ነው። በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው ታላቁ በዓታ ለማርያም ገዳም እንዴት ባለ አሳዛኝ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ያትታል። እንኳን ወደ ገጠር ሄደን እዚሁ ቤተ መንግሥቱ እና ቤተ ክህነቱ አጠገብ ያለው የአገር ቅርስ እንኳን እንዲህ ከጥቅም ውጪ እየሆነ ነው። በአንጻሩስ? ዞረን ዞረን ወደዚያው ሆነ እንጂ የሐውልቱ፣ የመኪናው እና የቅንጦቱ ነገር ውስጥ እንገባለን። ይህ ችግር እስካልተፈታ ድረስ እኛም መወትወታችን ይቀጥላል። መልካም ንባብ። (ማ/ቅዱሳን ድረ ገጽ)፦ በአዲስ አበባ የሚገኘው የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የመምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ ገዳም ከተመሠረተ ከ76 ዓመት በላይ ሆኖታል፡፡ በነዚህ የአገልግሎት ዘመናቱ ውስጥ በርካታ ታላላቅ ሊቃውንትን፣ መምህራንና ካህናትን አፍርቷል፡፡ ጥንታዊው የሀገራችን ቋንቋና ፊደል፣ ግእዝና ትምህርቱ ተጠብቆ እንዲቆይ፣ ለትውልድም እንዲተላለፍ በማድረግ በኩል ታላቅ ድርሻ አለው፡፡ ተቋሙን የሚያውቁት የቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምእመናን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያናችን አለኝታና ቅርስ መሆኑን በኩራት ይናገሩለታል፡፡ ይህ ታላቅ ገዳምና ትምህርት ማእከል በችግር ምክንያት እየፈራረሰ ነው። ተቋሙ በረዥም የአገልግሎት ዘመኑ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለአገር ከፍተኛ ጥቅም እንዳልሰጠ ሁሉ ዛሬ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል፡፡ ይህንን ችግር ምእመናን እንዲረዱትና ማሠልጠኛውን እንዲያውቁት ከገዳሙ አስተዳዳሪ ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ክርስቶስ ስብሐት እና ከትምህርት ቤቱ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀን እንግዳችን አድርገናል ተከታተሉን፡፡ ዐፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ከእንጦጦ የጥቂት ጊዜ ቆይታቸው በኋላ ፍልውኃ አካባቢ አሁን ታላቁ ቤተ መንግሥት የሚባለውን ለማሠራት ሲመርጡና አዲስ አበባ ከተማን ሲቆረቁሩ ለጠዋት ማታ ጸሎታቸው ማድረሻ አነስተኛ ሥዕል ቤት ከቤተ መንግሥታቸው አጠገብ አሠሩ፡፡ ሥዕል ቤቷን የቤተ መንግሥቱ ሰዎችና የአካባቢው ሕዝበ ክርስቲያን የኅብረት ጸሎት እያደረሱ ሲጠቀሙባት ቆዩ፡፡ ይህቺ ሥዕል ቤት ዛሬ በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ግቢ ውስጥ ስትገኝ፣ «ደብረ መንክራት ሥዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን» በመባል ትታወቃለች፡፡ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ባሳተመው «የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ» ቁጥር 1፤ ነሐሴ 1992 ዓ.ም መጽሔት ላይ የገዳሙን አመሠራረት በተመለከተ የታሪክ ድርሳናትን ጠቅሶ እንዳሰፈረው፤ ዐፄ ምኒልክ በሕይወተ ሥጋ ሳሉ ቅድስት ድንግል ማርያምን ዘወትር በጸሎት ይማጸኑዋት፣ ይማልዷትም ስለነበር ዕረፍታቸው ታኅሣሥ ሦስት በዕለተ ቀንዋ ሆነላቸው፡፡ ይህን ምስጢር የሚያውቁት ልጃቸው ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴና የሕዝብ እንደራሴዎች መክረውና አጥንተው የመልካም ሥራቸው መታሰቢያ የአፅማቸው ማረፊያ እንድትሆን የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያምን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በ1910 ዓ.ም መሠረቱን ጥለው በ1920 ዓ.ም ቤተ ክርስቲያኒቷን መፈጸሙን» መጽሔቱ በገጽ 271 ላይ ገልጿል፡፡ ሐመር መጽሔት በዘጠነኛ ዓመት በቁጥር ሦስት በሐምሌ /ነሐሴ 1993 ዓ.ም እትሙ ስለ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳምና የካህናት መምህራን ማሠልጠኛ ባወጣው ዘገባ ላይ በወቅቱ የነበሩትን የገዳሙ አስተዳዳሪ ጠቅሶ ስለገዳሙ አመሠራረት እንዲህ አስነብቦ ነበር፡፡ «ገዳሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ እምነት የተመሠረተ ባለ ታሪክ ገዳም ነው፡፡ የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል፣ የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እንዲሁም የሌሎችም ንጉሣውያን ቤተሰቦችና ጳጳሳት፣ አፅም ያረፈበት ጥንታውያን ንዋያተ ቅዱሳት፣ የብራና መጻሕፍት፣ ቅርሳ ቅርስ የሚገኙበት ታሪካዊ ገዳም ነው፡፡» በማለት የሚገልጸው መጽሔቱ፤ ቤተ ክርስቲያኑን በገዳምነት እንዲተዳደር ያደረጉት ነግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለመተዳደሪያ እጅግ በርካታ ገንዘብ ርስት፣ ሀብትና ንብረት ሰጥተው በ1925 ዓ.ም ገዳሙ እንዲመሠረት አደረጉ» ይላል፡፡ ገዳሙን የመሠረቱት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱና ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከማይንቀሳቀሰው ንብረት እና ርስት ሌላ ሦስት መቶ ሺሕ ማርያ ቴሬዛ ብር የገዳሙ መተዳደሪያ እንዲሆን ሰጥተዋል፡፡ ገዳሙ ተጨማሪ መተዳደሪያ በጀት የሚያስፈልገው መሆኑን በመረዳት ለዘለቄታው ራሱን ችሎ ሥራውን የሚያካሒድበት በርካታ የእርሻ መሬት ርስት ጉልት፤ የከተማ ቦታና ቤት፣ ጥሬ ገንዘብ የሰጡ እንደነ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ እና ሌሎችም በጎ አድራጊዎች ነበሩ፡፡ ጠቅላላ የገዳሙን ሥራ የሚያስተባብርና መንፈሳዊውን ሥራ የሚመራው በቤተ ክርስቲያኒቱ በቂ ዕውቀት እና የቁምስና መዓርግ ያለው «ሊቀ ሊቃውንት» ተብሎ የሚሾም አባት ነው፡፡ የገዳሙን ሀብትና ንብረት እየተቆጣጠረ ለሚያስፈልገው ተግባር መዋሉን የሚከታተል፡፡ የገዳሙን የገቢ ምንጭ ለማሳደግ የሚረዱ ሁኔታዎችን የሚፈጥር፣ የገዳሙን አስተዳደር፣ የትምህርቱን፣ የፋይናንሱን ወዘተ ሥራ የሚመራ በገዳሙ ሊቀ ሊቃውንት ሰብሳቢነት የሚመራ ባለ አደራ ቦርድ ገዳሙን በበላይነት እያስተዳደረ ሥራውን ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ባለ አደራ ቦርዱ ለገዳሙ ቋሚ የገቢ ምንጭ የሚያስገኙ በአዲስ አበባ ከተማ የሚከራዩ ሕንፃዎች በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን በገዳሙ ጽ/ቤት ግቢዎች ውስጥ ለተለያየ የገዳሙ አገልግሎቶች የሚውሉ ሕንፃዎች፣ የእህል ወፍጮና ዳቦ ማምረቻ ወዘተ አሠርቷል፡፡ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም በዚህ ሁኔታ በሚያገኘው ገቢ በሥሩ ያሉትን የመምህራንና ቀሳውስት ማሰልጠኛ ት/ቤት፣ ወላጅ የሌላቸውን ሕፃናት ማሳደጊያና የአረጋውያን መጦሪያ እያስተዳደረ እንዳለ በ1967 ዓ.ም በገጠር መሬት፣ በከተማ ቦታ ትርፍ ቤቶች አዋጅ የገዳሙ የእርሻ መሬቶች፣ የከተማ ቤቶችና ሕንፃዎች በሙሉ ተወረሱ፡፡ ደርግ የገዳሙን ሀብትና ንብረት ከወረሰ በኋላ፤ ለእጓለ ማውታው ማሳደጊያ፣ ለጡረታ ቤትና ለማሠልጠኛው መተዳደሪያና ለሠራተኞች ደመወዝ የተወሰነ በጀት መደበ፡፡ የባለ አደራ ቦርዱ በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ግንኙነት እያደረገ የተያዘለት በጀት በገንዘብ ሚኒስቴር እየተሰጠው ከበጎ አድራጊ ምእመናን በስጦታ ከሚያገኘው ገቢ ጋር እያቀናጀ በዚህ ዓይነት መተዳደሪያ ገዳሙ መንፈሳዊ አገልግሎቱን እያከናወነ እስከ መጋቢት 15 ቀን 1986 ዓ.ም ድረስ ቆየ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን የባለ አደራ ቦርዱ አስተዳደር እንዲፈርስ ተወስኖ የማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚሰጠው በጀት ቀርቷል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥር በቃለ ዓዋዲው መሠረት በሰበካ ጉባኤ እንዲተዳደር ተደርጓል፡፡ በዚህም መሠረት የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ከጠቅላይ ቤተ ክህነት በየዓመቱ ከሚሰጠው ድጎማ ጋር ከንዋዬ ቅድሳት መሸጫው፣ ከእህል ወፍጮና ዳቦ ማምረቻው እንዲሁም ከበጎ አድራጊ ምእመናን በስጦታ ከሚያገኘው ገቢ ጋር በማቀናጀት ጠቅላላ የገዳሙን መንፈሳዊ አገልግሎት የመምህራንና የቀሳውስት ትምህርት ቤቱን፣ እናት አባት የሌላቸውን ሕፃናት ማሳደጊያ እንዲሁም የአረጋውያን መጦሪያ በማስተዳደር ላይ ይገኛል፡፡ በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ሥር የሚተዳደረው የመምህራንና ካህናት ማሠልጠኛ የተቋቋመው፤ ከመላ ኢትዮጵያ የሚመጡትን ተማሪዎች በልዩ ልዩ የትምህርት ዓይነቶች በሊቃውንተ ቤተ ክርስተያን አስተምሮና አሠልጥኖ በየዘርፉ ብዙ ካህናትና መምህራንን በማፍራት ቤተ ክርስቲያንን እና ሀገሪቷን እንዲያገለግሉ ለማድረግ፤ የአገራችን ኢትዮጵያ ጥንታዊ ቋንቋ ፊደል በተለይ የግእዝ ትምህርት ተጠብቆ እንዲቆይ ለተተኪው ትውልድ እንዲተላለፍና ማኅበረሰቡ እንዲጠቀምበት ለማስቻል፤ ትምህርት ቤቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ለማስተማርና ለምርምር ተግባር ብቁ የሆኑ ጠበብትን ለማፍራት፤ በገዳሙ አካባቢ የሚኖሩትን ሕፃናት እየተቀበለ መሠረታዊ ትምህርት፣ ንባብና ጽሕፈት እንዲሁም አምስቱ አዕማደ ምሥጢርን በማስተማር በመልካም ሥነ ምግባር ተኮትኩተው እንዲያድጉ ለማድረግ ታስቦ በዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያነት በ1925 ዓ.ም ተመሠርተ፡፡ የተለያዩ የታሪክ መዛግብት እንደ ሚያስረዱት፤ ማሠልጠኛው ተቋቁሞ መምህራንና ካህናት እያሰለጠኑ ቢቆዩም ተማሪዎች ምግብና ልብስ እየተሟላላቸው በአዳሪነት እንዲማሩና ትምህርቱ በመደበኛ ሁኔታ በጥራትና በተጠናከረ መልኩ እንዲካሔድ የተደረገው ከ1950 ዓ.ም ጀምሮ ነው፡፡ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ በበዓታ ለማርያም ገዳም የቀሳውስትና የመምህራን ማሠልጠኛ የትምህርት ክፍል ሓላፊ /ርእሰ መምህር/ ናቸው፡፡ ስለማሰልጠኛው የትምህርት ሁኔታና የመግቢያ መሥፈርቶች የበፊቱን ከዛሬው ጋር እያነጻጸሩ ይናገራሉ፡፡ ቀደም ሲል ይሔ ቦታ ሁሉንም አስተባብሮ /አዋሕዶ/ ትምህርት ይሰጥ የነበረ ተቋም ነው፡፡ ሙዓለ ሕፃናት /መሠረተ ትምህርት/ ነበረው፡፡ እንደዚህ ዛሬ ሙዓለ ሕፃናት በየመንደሩ ሳይስፋፋ በነበረበት ሰዓት ለብቻው ቦታ አዘጋጅቶ ከሦስት መቶና ከአራት መቶ በላይ ሕፃናትን ሰብስቦ በክፍል ውስጥ መምህር ቀጥሮ ትምህርቱ ይሰጥ ነበረ፡፡ በዚህ የትምህርት ክፍል ውስጥ የንባብ መምህራን ሁለት ነበሩ፡፡ ፊደላቱን የሚያስቆጥርና በሳሎቹን ዳዊት የሚያስደግም፣ ንባብ የሚያስተምር ድርሳኑ፣ ስንክሳሩን የሚያስነብብ ወደ ፍጹምነት የንባብ ደረጀ ተማሪዎችን የሚያደርሱና የሚያስቀጽሉ መምህራን ነበሩ፡፡ አሁን ግን መምህሩ ሲሞቱ የሙዓለ ሕፃናቱ በጀት ታጠፈ ትምህርቱም ተቋረጠ /ሙዓለ ሕፃናቱም ቀረ፡፡/ በዚህ ላይ ብዙ ቅሬታ ተሰምቶ ነበር ብዙ ወላጆች ቢሮ ድረስ እየመጡ ልጆቻችንን የት እናስተምር እኛ ደሆች ነን ገዳሙ ደግሞ የድሆች መጠጊያ ነበር ለምን ትምህርቱን አስቀራችሁ ብን እያሉ ይጠይቁ ነበር መልስ ስላላገኙ ትምህርቱም በዚያው ቀረ፡፡ በማሠልጠኛው አሁን ትምህርት በመስጠት ላይ የሚገኘው ከንባብ የትምህርት ክፍል ጀምሮ ነው፡፡ ይኸውም የንባብ ትምህርት ቤቱ በመፍረሱ ትምህርቱ የሚሰጠው ሜዳ ላይ ነው፡፡ አሁን ተማሪዎቹ እየተማሩ ያሉት በዚህ ሁኔታ ነው የሚሉት ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን፤ በካህናትና መምህራን ማሠልጠኛው አሁን እየተሰጠ ያለውን የትምህርት ዓይነት በመዘርዘር የመግቢያ መሠፈርቱን ይገልጻሉ፡፡ እዚህ ቦታ ላይ ቀደም ሲል እንደነገርኩህ ከዘጠኝ በላይ ትምህርት ይሰጥ ነበር፡፡ ሙዓለ ሕፃናቱን ሳንቆጥር፤ ዘጠነኛ የነበረው ፍትሐ ነገሥት፣ አቡሻክር እና መጽሐፈ መነኮሳት በመምህር ንቡረእድ አብዬ ሆይ በሚባሉ አባት በጥምረት ይሰጥ ነበር፡፡ እሳቸው ሲያርፉ ጉዳዩን አስቦ ሌላ መምህር የሚተካ በመጥፋቱ በቸልተኝነት ጉባኤው ታጥፎ ይገኛል፡፡ ይላሉ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን፡፡ ለዜማ፡- ንባብን በሚገባ ማወቅ አለበት፡፡ ይህም ማለት አርባዕቱ ወንጌላትን፣ መልዕክተ ጳውሎስን፣ ራእይ ዮሐንስን፤ ከቻለ ደግሞ ስንክሳሩን፣ ድርሳናቱን ያነበበ በንባብ የበሰለ ያለ ከዚሁ ጋር ዳዊትን፣ ውዳሴ ማርያምን፣ መልክአ መልኩን በቃሉ ያጠና ወደ ዜማ ቤት ይገባል፡፡ ለአቋቋም ቤት፡- የአቋቋም መስፈርቱ ዜማ ያወቀ ነው፤ ይህም ማለት ውዳሴ ማርያም ዜማ የተማረ፣ የቃል ትምህርት መስተጋብእ፣ አርያም፣ ሠለስት የጾም ምዕራፍን ያወቀ፤ በተለይ ጾመድጓ የዘለቀ፣ ድጓ የተማረ ቢሆን ጥሩ ነው፡፡ መስፈርቱ እስከ ጾመ ድጓ ድረስ መማር ሲሆን ድጓውን ቢማር እጅግ ጥሩ ይሆናል፡፡ ለቅዳሴ፡- ውዳሴ ማርያምን በዜማ የዘለቀ፤ ዜማዊ የቃል ትምህርቶችን የተማረ ቢሆን ይመረጣል እነዚህን የተማረ ነው ወደዚህ የትምህርት ክፍል የሚገባው፡፡ ምክንያቱም የቅዳሴ ዜማ ረዘም ያለ ስለሆነ በውዳሴ ማርያምና በሌሎችም ዜማዎች መታሸት አለበት፡፡ ለትርጓሜዎች፡- ሐዲስ ኪዳንን መማር የሚፈልግ የግድ ቅኔ የተቀኘ መሆን አለበት፤ ቅኔ ከነአገባቡ በሚገባ የቀጸለ ቢሆን ይመረጣል፡፡ ምክንያቱም የትርጓሚያት ንባባቱ ከቅኔ ትምህርት ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ ሰዋስው አወቃቀሩ ይያያዛል፡፡ ለምሳሌ አንድ የሐዲስ ትርጓሜ ተማሪ ንባቡ ሲነበብለት ጥሬ ትርጉሙን ማወቅ አለበት፡፡ ቅኔ የማያውቅ በኛ ት/ቤት በሐዲስም ሆነ በብሉያት ውስጥ አይገባም፡፡ ስለዚህ ቅኔ በሚገባ ማወቅ ለትርጓሜያት ሁሉ ዋና መሥፈርት ነው፡፡ የበለጠ የተመረጠ የሚሆነው ግን ዜማን በተጨማሪነት ቢያውቅ ነው፡፡ ይህም የሚሆነው ሁለገብ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር ነው፡፡ ለቅኔ፡- ለቅኔ መሥፈርቱ ንባብን ማወቅ ነው፡፡ በአጠቃላይ ንባብ ነክ ትምህርቶችን ያወቀ ወደቅኔ ቤት ይገባል፡፡ ትምህርት ቤቱ /ገዳሙ/ መስፈርቱን ያዘጋጀው በሁለት መንገድ ነው፡፡ ለአዳሪ ተማሪ ለየአንዳንዱ ጉባኤ ተመድቦለታል በመደበኛነት ገብቼ መማር እፈልጋለሁ ላለ ገዳሙ ይሔን፣ ይሔን ማወቅ አለበት ብሎ አዘጋጅቷል፡፡ ስለዚህ አሁን የተጠቀሰው መስፈርት በአጠቃላይ ትምህርቱን ለመማር የወጣ መስፈርት ነው፡፡ ትምህርቱን ለመማር መመዘኛው አንድ ዓይነት ሲሆን ለአዳሪ ተማሪዎች ግን ተጨማሪ መመዘኛዎች አሉአቸው ማለት ነው፡፡ መታወቅ ያለበት ወደ ትምህርት ቤቱ ለመግባት በወጣው መሥፈርት ላይ እንደገና የመግቢያ ፈተና መኖሩን ነው፡፡ ጥንት ፈተናው በጣም ጠጣር ነበር፡፡ አሁን ግን የአብነቱ ትምህርት እየተዳከመ ስለሆነ ፈተናው ቢኖርም እንደጥንቱ በጣም ከባድ ፈተና አይደለም እየሰጠን ያለነው፡፡ የትምህርት ፍላጎቱ ካለውና መሥፈርቱን ካሟላ የመግቢያ ፈተናው ይሔን ያህል የከረረ አይደለም፡፡ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን በትምህርት ቤቱ ለሚሰጡት ትምህርቶች /ጉባኤያት/ የተመደበላቸው ጊዜ ላይ የትምህርት አስተዳደሩ ቆራጥ አቋም እንዳለው ይገልጻሉ፡፡ ለዚህም ጉባኤያቱ የሚፈጁት ጊዜ ተለክቶ ተቀምጧል፡፡ በተለይ ለአዳሪ ተማሪዎች እጅግ በጣም ጥብቅ ነው፡፡ በማለት ያስረዱት ሊቀ ጉባኤ፤ ምክንያቱንም እንደሚከተለው ይገልጻሉ፤ ትምህርቱን በጊዜ ገደብ መከፋፈሉ የትምህርት ጥራቱን ይጠብቃል፤ አንድ ተማሪ የተመደበለትን ጉባኤ በተመደበለት ጊዜ ካልጨረሰ ደጅ የሚጠኑ ተማሪዎችን ማለትም በአዳሪ ገብተው ለመማር ብዙ ጊዜ የሚጠብቁትን ተማሪዎች ያጉላላል፣ ስለዚህ አንድ ተማሪ በተመደበለት ጊዜ ካላጠናቀቀ በሱ ምትክ ሌላ ጎበዝ ተማሪ እንዲተካው ይደረጋል፡፡ የጉባኤው ዓመታት ውስንነት ጥብቅ የሆነው ከላይ በጠቀስኳቸው ምክንያቶች ነው፡፡ በሌሎቹ ጉባኤ ቤቶች ያየን ከሆነ ግን አንድ የአብነት ተማሪ በአንድ ጉባኤ ቤት ከ10 እስከ 15 ከዚያም በላይ በአንድ ጉባኤ ብቻ ይቆያል፤ በኛ ግን ይሔ አይታሰብም /የለም/፡፡ ከዚህ አንጻር በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የካህናትና መምህራን ማሠልጠኛ ት/ቤት ጉባኤያቱ እንደሚከተለው የጊዜ ገደብ ተመድቦላቸዋል፡፡ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም አስተዳዳሪ ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ክርስቶስ ስብሐት ስለ ማሠልጠኛውም ሆነ ስለመደበኛ ተማሪዎች አሁን ያለበትን ሁኔታ ከጥንቱ ጋር እያወዳደሩ ይገልጻሉ፡፡ ሊቀ ሊቃውንት «ለተማሪዎቹ የተመደበው በጀት ድሮ በነበረው ስሌት በመሆኑ አሁን ካለው ኑሮ ጋር የተመጣጠነ አይደለም፡፡ ተማሪዎቹ ቁርስ መብላት ካቆሙ ከሁለት ዓመት በላይ ሆኗቸዋል፡፡» ይላሉ፡፡ «ይህችኑ ለአንድ ተማሪ 150 ብር የሚመደበውን በጀት መሸፈን አቅቶን በትምህርት ቤቱ በአዳሪነት /በድርጎ/ መማር ከነበረባቸው 70 ተማሪዎች አሁን ተቀብለን ያለነው 60 ብቻ ነው፡፡ ለዚህም አቅማችን እየተዳከመ ነው» በማለት የተማሪዎቹ የአኗኗር ሁኔታ በችግርና በመከራ የተሞላ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን በበኩላቸው ተማሪዎቹ አሁን ያሉበትን ሁኔታ እንደ ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ክርስቶስ በማነጻጸር ጀምራሉ፤ ተማሪዎቹ በዓመት ዩኒፎርም፣ /የትምህርት ቤት ልብስ/ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የጤና መጠበቂያና ሽፋን ነበራቸው፤ ምግባቸ ውም በመጋቢው አማካኝነት ጾም ካልሆነ በቀር በሁሉም ሰዓት የተሟላና ጥሩ ነበረ፡፡ አሁን ግን ይሔ ከስምንት ሺህ በላይ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ያፈራ ከ38 በላይ ሊቃነ ጳጳሳትን ያወጣ፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ብዙ ለሀገርም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ምሁራንን ያስገኘው ተቋም ዛሬ ቤቱ ብቻ ሳይሆን እየፈረሰ ያለው የተማሪዎቹም ሕልውና ነው፡፡ ዛሬ የመምህራኑ ኑሮ ተጎሳቁሏል፡፡ በዚህም ምክንያት የመማር ማስተማሩ ሒደት ሕንፃው መፈራረስ ሌላ ችግር ነው፤ ዛሬ በማሠልጠኛችን የትምህርት አሰጣጥ ሥር ዓቱ እየተዳከመ ነው፡፡ መምህራን ሲያልፉ የሚተኳቸው መምህራን ማጣት በጣም አስቸጋሪ እየሆነብን ነው፡፡ ተማሪው በሦስት፣ በአስራ ስድስት እና የሰንበት ዕለታት በቤተ ክርስቲያን እንደንብ ተሰግስጎ ገብቶ እንዲያገለግል ይደረግ ነበር፤ ዛሬ ግን ከስብሐተ ነግህ በስተቀር ማኅሌቱንም ቅዳሴውንም እንደ ጥንቱ ተማሪው እንዲቆም ማድረግ አልቻልንም፡፡ ለምን ቢባል ተማሪው ሌሊት ሲያገለግል አድሮ ጠዋት የሚቀምሰው የሚልሰው ባለመኖሩ ይሔን ሳናሟላ ሐደህ አገልግል፤ ማኅሌቱንም ቁም ብሎ ለማስገደድ የሞራል ብቃቱ አንሶናል፡፡ ተማሪው ቁርስ የለውም፣ ምሳና እራቱም ቢሆን አጥጋቢ አይደለም፡፡ በዓመት የሚሰጠው ዩኒፎርም ቀርቷል፡፡ ብርድ ልብስም ሆነ ዩኒፎርሙ ከቆመ ሰባት ዓመታት አልፎታል፡፡ በቅርቡ ማኅበረ ቅዱሳን ከበጎ አድራጊዎች ጋር በመተባበር ለ70 ተማሪዎች ብርድ ልብስ፣ አንሶላና ጫማ ባይሰጥልን ኖሮ ተማሪው በሌሊት ልብስ ተራቁቶ ነበር፡፡ በአጠቃላይ የተማሪው የኑሮ ሁኔታ እጅግ አስቸጋሪ ደረጃ ላይ ደርሷል፤ የተማሪው መኝታው በላዩ ላይ እየፈራረሰ ነው፤ አልጋዎቹ ወላልቀው በጧፍና በገመድ ተጠፍረው ነው ያሉት፤ ከዚህ አንጻር የተማሪው መብት በመጓደሉ ግዴታውን እንዲወጣ ለማድረግ እያቃተን ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ማታ ሰርክ ጸሎት፣ መሐረነ አብ፣ እግዚኦታ ይደርሳል፣ ይሔ አገልግሎት ከዓመት ዓመት አይቋረጥም፡፡ ሌሊት ደግሞ ስብሐተ ነግሕ ሌሊቱን ሳይቆም በምንም ሁኔታ አይታደርም 365 ቀናት አይቋረጥም በዚህ ለየት ያለ ነው ትምህርት ቤታችን፡፡ ይህ ሁሉ ችግር እያለም ቢሆን ት/ቤቱ በአሁኑ ጊዜ ስምንቱን ጉባኤ የሚማሩ ከ60 በላይ የአዳሪና ከ240 በላይ ተመላላሽ ተማሪዎች አሉ፡፡ አኗኗራቸውም በመንፈሳዊ ትምህርት ቤት ሥርዓት መሠረት ነው፤ በየዓመቱም በአማካይ ከ30 በላይ እጩ መምህር እናወጣለን /እናስመርቃለን/ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም መምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ ቀንና ሌሊት /24 ሰዓት/ በጋና ክረምት ጉባኤው ሳይቋርጥ የሚካሔድበት ትምህርት ቤት ነው፡፡ ከተለያዩ አድባራት በሥራ ላይ ሆነው ሞያቸውን /ዕውቀታቸውን/ ለማሻሻል የሚመጡትን ሁሉ ያስተምራል፡፡ በመንግሥትና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ሥራ ላይ ያሉትንም የሥራ ሰዓታቸውን በማይነካ መልኩ ከመምህራቸው ጋር በመነጋገር አመቺ ሰዓት መርጠው በትርፍ ጊዜአቸው ይማራሉ፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችም /የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች/ በመምጣት እየተማሩ ነው፡፡ በደጅ ጥናት አዳሪ ትምህርት ቤት ለመግባት የሚጠባበቁትም ተመላላሽ ሆነው ሙሉ ቀን ይማራሉ፡፡ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን መደበኛ ከሆነው ትምህርት ውጪ ማሠልጠኛው ብዙዎችን ለማስተማር የሚረዱ ሥርዓተ ትምህርት ዘመኑን በዋጀ መልኩ በመቅረጽ በማስተማር ላይ እንደሚገኝ ይገልጻሉ፡፡ በቀጣይም ሥርዓተ ትምህርቱን ለሁሉም በሚመች መልኩ ለመቅረጽ የሰው ኃይል፣ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በማፈላለግ ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል፡፡ አሁንም ቢሆን ለመጀመር ብለን በቀረጽነው ሥርዓተ ትምህርት ብዙ የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች ተቀብለን እየስተማርን ነው፡፡ በዚህ ትምህርት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ግቢ ጉባኤ የሚማሩ ልጆችም ተካተው እየተማሩ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ የቤተ ክርስቲያኒቱን የአብነት ትምህርት ለመማር የሚፈልጉ ሁሉ ወደ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም የካህናትና መምህራን ማሠልጠኛ ገብቶ መማር እንደሚቻል ለመግለጽ እንወዳለን ይላሉ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ፡፡ ማሠልጠኛው ከሌሎች ተቋማት ጋር የመመረቂያ ልብስ ውሰት በቀር ይህ ነው የሚባል ድጋፍ እንደሌለው ሊቀ ጉባኤ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ከቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ የአብነቱን ትምህርት በአጭር ጊዜ ለመማር የሚፈልጉ ደቀ መዛሙርት ከኮሌጁ አጽፈው ሲመጡ ለሦስት ወርም ሆነ ባላቸው ትርፍ ጊዜ ሁሉ እናስተምራለን ይላሉ፡፡ በሌሎች የአብነት ትምህርት ቤቶች ጥቂት ካልሆኑ በቀር እንዲህ ተጠናክረው ጉባኤያቱን በአንድ ላይ የሚሰጡ ብዙ ጉባኤ ቤቶች የሉም፡፡ በዚህ ግን አንድ ተማሪ ሁሉንም ጉባኤ የመማር አቅምና ጊዜ አለኝ ካለ ስምንቱንም ጉባኤ መማር ይችላል፡፡ በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የካህናትና መምህራን ማሠልጠኛ ተማሪዎች፤ በትምህርት ቤቱ ካለባቸው ችግር በላይ የሚያሳስባቸው እና ሁልጊዜ በጭንቀት እንዲወጠሩ የሚያደርጋቸው ነገር አለ፡፡ ይኸውም በብዙ ድካምና ችግር ተምረው ካጠናቀቁ በኋላ ተመደበው ሥራ ያለማግኘታቸው ጉዳይ ነው፡፡ ከማሠልጠኛው ተምረው የሚወጡ ደቀ መዛሙርት እንደሌሎቹ ማለትም እንደቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ እንደ ሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ትምህርት ቤትና እንደሌሎችም መንፈሳዊ ኮሌጆች ተመራቂ ደቀመዛሙርት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ተመድበው ሥራ አይዙም፡፡ በዚህ ምክንያት ለቤተ ክርስቲያን እንደ መብራት ሆነው የሚያገለግሉ ሊቃውንት በየቀን ሥራው፣ በየሰው ቤት በዘበኝነት ተቀጥረው እያገለገሉ እንደሚገኙና አንዳንዶቹም፣ ዕድሉን አግኝተው ተቀጥረው ቤተ ክርስቲያንና ምእመናኑን እያገለገሉ እንደሚገኙ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ ይገልጻሉ፡፡ ሊቀ ጉባኤ እንደገለጹልን ችግሩን ለመቅረፍ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሣሙኤል ጊዜ ተማሪዎቹ ተመርቀው ሲወጡ በየደብሩ በየሙያቸው የመመደብ ሥራ ተጀምሮ እንደነበር ጠቅሰውልናል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት እየሰፋ ነው የሚሉት ሊቀ ጉባኤ፤ ይሔን እየሰፋ ያለውን አገልግሎት በትክክለኛው አገልጋይ እንዲሸፈን ለማድረግ በየጉባኤ ቤቱ እየሠለጠኑ የሚወጡ ደቀ መዛሙርትን በአገልግሎት ቦታ መመደብ ቤተ ክርስቲያን ጊዜ ልትሰጠው የማይገባ ጉዳይ ነው በማለት ማሠልጠኛው ያሳስባሉ፡፡ የገዳሙ አስተዳዳሪ ሊቀ ሊቃውንት ገብረ ክርስቶስ ትምህርት ቤቱ የሚገኝበትን የአሁኑን ሁኔታ የሚገልጹት ከዚህ በፊት ለቤተ ክርስቲያን ከሠራው ውለታና ካፈራቸው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብዛት አንጻር ነው፡፡ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የካህናትና መምህራን ማሠልጠኛ ከ38 በላይ ሊቃነ ጳጳሳትን፣ በርካታ ስለቤተ ክርስቲያን ሊጠየቁ የሚችሉ ሊቃውንትን፣ ለሀገርም በርካታ ውለታ የሠሩ ዶክተሮችንና ፕሮፌሰሮችን አፍርቷል ይላሉ፡፡ ሊቀ ሊቃውንት ገብረ ክርስቶስ፡፡ ዛሬ ግን ይሔ በርካታ ሊቃውንትን ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን ያበረከተው ማሠልጠኛ በመፈራረስ ዛሬና ነገ በላያችን ወደቀ እያልን በመሥጋት ላይ ነን፡፡ ግድግዳው የተመረገበት ጭቃ ረግፎ ማገሩ የተያያዘበት የሣር ገመድ በመበጣጠስ ላይ ይገኛል፡፡ የንባብና ሙዓለ ሕፃናት መማሪያ የነበሩት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ ፈርሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ሙዓለ ሕፃናት ክፍሉን የማስተማር ሥራውን ስንተወው የንባብ ትምህርቱን ግን መምህራኑ በሜዳ ላይ ፀሐይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው እያስተማሩ ይገኛሉ፡፡ ያልፈረሱት የመምህራኑና የተማሪዎቹ መማርያና መኖሪያ ክፍሎች ጣሪያዎችና ግድግዳው ክፍት በመሆኑ በፀሐይና በዝናብ እየተፈራረቀባቸው ይገኛል፡፡ መምህራኑም ሆኑ ተማሪዎቹ በችግር ላይ ናቸው፡፡ በክረምት ወቅት ቤቶቹ በማፍሰሳቸው ተማሪዎቹም ሆኑ መምህራኑ ክረምቱን የሚያሳልፉት በሠቀቀን ነው፡፡ በድርጎው በኩል ለተማሪዎቹ የምንደጉማት ገንዘብ አሁን ካለው የኑሮ ሁኔታ ጋር ባለመጣጣሟ ተማሪዎቹ ቁርስ እንዲያቆሙ ተደርጓል፡፡ በችግሩ ምክንያት የመቀበል አቅማችንን በአሥር ሰው ቀንሰናል፡፡ ጾም ሳይሆን የሚበሏት ምሣና አራትም ብትሆን ይሔን ያህል የምትበቃ አይደለችም፡፡ እንዲያው ለስም የሆነች ናት የሚሉት ሊቀ ሊቃውንት የማሠልጠኛው ችግር ከቃላት በላይ ነው ይላሉ፡፡ አስተዳዳሪው እንደሚሉት፤ የተማሪውን የድርጐ ሁኔታ ለማሻሻል የገዳሟ ገቢ አነሥተኛ በመሆኑ ለማስተካከል እየጨነቀን ቢሆንም፤ ትምህርት በቱን መልሶ ለመጠገን ግን ምእመናንን ተስፋ አድርገን ቆርጠን ተነሥተናል፡፡ ከዚህ በፊት ይሔን ትምህርት ቤት ለማደስ ያልተቋቋመ ኮሚቴ ያልተደረገ ጥረት እንዳልነበረ ሰምቼያለሁ፤ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት አልተሳካም፡፡ አሁነ ግን ቅዱስነታቸው በታኅሣሥ 3 ቀን 2002 ዓ.ም. የበዓታ ክብረ በዓል ላይ ለእድሳቱ ሃምሣ ሺሕ ብር ለመስጠት ቃል በመግባታቸውና ሥራው እንዲጀመር መመሪያ በመስጠታቸው የዲዛይን ኮሚቴ አቋቁመን እንቅስቃሴ ጀምረናል ይላሉ፡፡ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መፋጠን ደከመኝ ሰለቸኝ የማይለው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመን፣ መንፈሳዊ ማኅበራት፣ ለሀገር ታሪክ የሚቆረቆሩ የሀገር ወዳጆችና መንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለዚህ ታሪካዊ ትምህርት ቤት በጋራ በመቆም ድጋፍ እንዲያደርጉ ሊቀ ሊቃውንት ገብረ ክርስቶስና ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ ተማጽነዋል፡፡
21
የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት በሚል ራሳቸውን ያሰባሰቡት 16 የተቃዋሚ ድርጅቶች ሰሞኑን ባወጡት መግለጫ ግጭቶች ኢህአዲግ በጀመረው መንገድ ሊፈቱ እንደማይችሉ አሳስበዋል። ይህንኑ የ16ቱ ፓርቲዎች ጥምረት የሚያስተዳድሩት የኢትዮጵያዊያን የዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ኤዲፓ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ ሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች እንደሚቀላቀሏቸው ተስፋቸውን ገልጸዋል።
22
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መልዕክት “የእንግሊዝ ዜጋ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሰኔ 17 የመን ውስጥ መጥፋታቸው ሪፖርት ተደርጓል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የእንግሊዝ ባለሥልጣናት ለንደን የሚገኙትን የየመን አምባሣደርን ማነጋገርን ጨምሮ የየመን ባለሥልጣናት አቶ አንዳርጋቸው ያሉበትን ቦታ እንዲያገኙ ወይም እንዲገልፁልን ጫና ሲያሣድሩ ቆይተዋል፡፡ አሁን ግን የሚገኙት ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን የሚገልፁ ሪፖርቶች የደረሱን በመሆኑ የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት በአፋጣኝ እንዲያረጋግጡልን ሥጋታችንንም እየገለፅን እንጠይቃለን፡፡ ለቤተሰቦቻቸው የቆንስላ ድጋፍ መስጠታችንን እንቀጥላለን” ብሏል፡፡ የድርጅቱ የአፍሪካ ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮ በሰጡት መግለጫ “ኢትዮጵያ አቶ አንዳርጋቸውን ዓለምአቀፍ ግዴታዎቿን እንደምታከብር በሚያረጋግጥ ሁኔታ እንድትይዝ” ጠይቀዋል፡ የመን የሚገኙት የሂዩማን ራይትስ ዋች መርማሪ ቤልኪስ ቬለ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ አቶ አንዳርጋቸው የሚገኙት ኢትዮጵያ ለመሆኑ እርግጠኛ መሆናቸውንና የተላኩትም ሰንዓ አየር ጣቢያ ላይ በተያዙ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ መሆኑን ከታማኝ ምንጮች ማረጋገጣቸውን አስረድተዋል፡፡
23
የፓናማ ዶክሜንቶች (panama papers) በመባል የሚታወቀው፣ የበርካታ የዓለም መሪዎችና ባለጠጎች ምስጢር ያለበት ዶክሜንት የሕዝብን አመኔታ ያሳጣል፣ ዜጎችም ለአገራቸው ትምህርት ቤቶች፣ መንገዶችና ለሌሎች ተቋማት ግንባታ የሚያደርጉትን አስተዋፅዖም ይገድባል፣ ቀረጥ ከመክፈልም ይቆጠባሉ ሲሉ፣ የዓለም ባንክ ሁለተኛው ከፍተኛ ባለሥልጣን አስታወቁ።
24
ዋሽንግተን ዲሲ — ህዝባዊ ግንባር ለዲሞክራሲና ለፍትህ የተባለው የኤርትራ ገዢ ፓርቲ እንዲሁም መንግስታዊ ተቋማት ደረጃ በደረጃ ለውጥ የሚደረግባቸው ከወቅቱ ሁኔታ ጋር መራመድ ስላለባቸው ነው ሲሉ ፕረዚዳንት ኢሳያስ አፈውርቂ ተናግረዋል። ይህ ጉዳይ የሚኒስትሮች ሹም ሽርን ወይም የፖሊሲ ለውጥን የሚያመላክት ነው ወይስ ምንድነው? ለሚለው ጥያቄ አቶ አላዛር አብረህም የተባሉ ስለኤርትራ ጉዳይ የሚከታትሉ ሰው ሲመልሱ “ሀገሪቱ የምትገኝበትን አጠቃላይ ሁኔታ ስንመለከት የጠባብ መስናክሎችና ማነቆዎች ትግል የሚካሄድባት በመሆኑ ድርጅቱ እአአ በ 1994 አም ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ጉባኤው ቀደም ብሎ መካሄድ ነበረበት። በተለያዩ ማነቆዎችና ጠላታዊ ተግባሮች ምክንያት መሰንክል እየተከሰተ ከጊዚ ወደ ጊዜ ሲሸጋገር ቆይቷል" አቶ አሮን ብርሀነ በበኩላቸው“ ባለፉት አስር አመታት ውስጥ በነበረው አደረጃጀት ብዙ ወሳኝ የስልጣን ቦታዎች የነበርዋቸው ሰዎች አንድ በአንድ ትተውት ሲሄዱ ቆይተዋል። አንዳንዶቹ ስደት ላይ ነው ያሉት። እነዚህ ሰዎች የፈጠሩት የራሳቸው መረብ ሊኖር ይችላል። ስለሆነም በህዝቡ መካከል ሲጋጋም የቆየውን ተቃውሞና እንቅስቃሴ ለማዳከም የታቀደ ነው" ብለውታል።ዝርዝር ዘገባውን ያድምጡ።
25
አይ ወያኔ! ደሞ አዲስ ካድሬ አመጣችብን? ዘሪሁን ተሾመ አፈነገጠችባቸው መሰለኝ;የህዝቡን ልብ ለማራራት አዲስ (ገለልተኛ ለመምሰል የሚጥር) “ተንታኝ” እንድታስተዋውቅ ለዴቭ መመሪያ ተሰጥቷታል:: ዴቮ ተነቅቶብሻል:: ማንም ተንታኝ ይዘሽ ብትቀርቢ አንሰማሽም::
26
ዳዊት መቀሌ የሄደው ለከፍተኛ ፖለቲካዊ ስልጠና ነው፣ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ዶክመንተሪ ሽፋን ነው ብሎ አንዱ ጓደኛዬ ሲነግረኝ አላመንኩም ነበር:: ኧረ ዴቭ እውነትም ስልጠናው ውጤት ተኮር ነበር የምር እዚህ ላይ አወራርሽ ተለይቶብኛል:: እንዴ የዛሬን አያድርገውና ጋደኛሽ ነበርኩኮ
27
በህወሓት የበላይነት የሚመራው ኢህአዴግ ከአሁን በኋላ ፈርሷል፡፡ በምትኩ ሶስቱ ፓርቲወች ማለትም ኦህዴድ፣ ብአዴንና ደህዴን ሶስቱንም በእኩልነት ያቀፈ ኢህአዴግ በአዲስ መልክ ተመስርቷል፡፡ ይህንም ለማድረግ ያስገደደን በፍጥነትና ባልተጠበቀ መልክ በህዝብ ብሶት በገነፈለ ማዕበል መሰል ህዝባዊ አመፅ ሳቢያ በሀገር እየታየ ያለ ውስጣዊ ለውጥና የአለም አቀፍ ማህበረሰብም ስለጉዳዩ በአሳሳቢነቱ ትኩረት መስጠት ነው፡፡ የውጪ ሰው ስለኛ ሲያስብ እንዴት እኛ ስለራሳችን አናስብም በማለትም እኛነታችን በራሱ አሳስቦናል፡፡ እኛ የህዝብ ተመራጮችና ህዝብ አገልጋዮች እንጂ የህወሓት መጠቀሚያ አሽከሮችና ተላላኪዎች አይደለንምና ከአሁን በኋላ ከህዝባችን ጎን ሆነን ህዝባችንን ብቻ ነው በትክክል የምናገለግል፡፡ እኛ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወይም ስህተት የሆነ አቋም በመያዝ ለህወሓት አገልጋይ ሆነን ህዝባችንን ጎድተን ይሆናል፡፡ በዚህም ሳቢያ ህዝባችን ከመቀየምና ከመቆጣት አልፎ በኛ ላይ የጥላቻ ስሜት ያለበትና መበቀልን እንደ መፍትሄ የሚያስብ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁንና በአሁኑ ወቅት ግን ከዚህ የከፋና ሁላችንንም ለከባድ አደጋ ከሚጥል ደረጃ ላይ ስላለን በመካከላችን ያለን ማንኛውንም ጉዳይ ለጊዜው ወደጎን በማድረግ ለራሳችን ስንል ሁላችንም በጋራ ሀገራችንን ማዳን መቻል አለብን፡፡ የማያግባቡንና አንድ እንዳንሆን የማያደርጉን ምክንያቶች ግን በእውነት ተቀባይነት ያላቸው ሳይሆኑ እኛን እየለያየና እያጣለ ነገር ግን እሱ እንዳሻው ይሆን ዘንድ ህወሓት ሆን ብሎ በትልቅ ጥናት የሚፈጥራቸውና በጥረት በኛ ላይ የሚያስፈጽማቸው ተንኮሎች ናቸው፡፡ በመሆኑም በጠላት ወጥመድ በፈቃዳችን አየገባን እኛ እኛን በምንጎዳበት ጊዜ ለ25 አመታት እንደሚያደርገው ሁሉ እሱ እንደፈለገው እየሆነ እንዲጠቀም ማስቻል ሳይሆን አንድነት በመፍጠር በጋራ ሆነን የጋራ ጠላታችን የሆነን እሱን ማጥቃት ነው ብቸኛውና ትክክለኛው መፍትሄ፡፡ ህወሓት ከመምጣቱ በፊት እስኪ ማን ነው በብሄረሰብ፣ በሀይማኖት ወይም በሌላም ህወሓት ባመጣብን በሽታ ተለክፎ በዚህ ልዩነት የሚፈጥር፣ ጎራ የሚለይና የሚጣላስ የነበር፡፡ ይህን ከቫይረስና ከባክቴሪያ የከፋ የህወሓትን ህዝብ አጥፊና ሀገር አፍራሽ የነቀርሳ በሽታ መቀበላችንስ በእውነት እየጠቀመን ነውን ወይስ የበፊቱ ነፃነት ያለበት፣ ሰላም የሞላበትና አንድነት የጎለበተበት ሰውን በባህሪው ብቻ መረዳት መቻል? ከማንም በበለጠ እኛ የህዝብ ተወካዮች ከህወሓት ጋር ቅርበት ስላለን ስለሱ ብዙ እናውቃለን፡፡ ደካማ ወይም ጠንካራ ጎኖቹ ምን እንደሆኑ ላይተን የተረዳን ነን፡፡ ምን እንደሰራና እየሰራ እንደሆነም እሱ በምስጢር የያዘው የሚመስለውንም ጭምር እናውቃለን፡፡ በአጠቃላይ እሱን በተመለከተ ማንኛውንም ጉዳይ ከህዝብ በተሻለ የምናውቅ ስለሆን እሱን በተመለከተ ህዝብና እኛ በጋራ መስራት ጥቅሙ ትልቅ ነው፡፡ የኛ የአሁን አላማ ስልጣን ፍለጋ ወይም በሌላ ምክንያት ፈርተን ወይም ተገደን ሳይሆን አምነንበት ከሁኔታው መክበድ አኳያ የግድ ካለፈው ተቀይረን በሌላና በተሻለ መልክ ከህዝብ ጎን በመሆን የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅና የሀገርን ሰላም ለማስከበር ነው፡፡ የመጀመሪያውና ዋነኛው ስራችን መሆን ያለበት የሀገራችን ስላምና አንድነት እንዲሁም የህዝቦች ደህንነትና የቀን በቀን ስራቸውን መስራትና ኑሯቸውን ካለምንም መረበሽና ከእጅ ወደ አፍ የሚሉት ሳያጡ እንዲቀጥሉ ማስቻል ነው፡፡ ይህ ግን ሊሆን የሚችል የህወሓትን ሴራ፣ ተንኮልና ድርጊት እኛ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነውን ህዝብ የምንወክል የአዲሱ ኢሀአዴግ ፓርቲ አባላት ከሁሉም ህዝባችን ጋር በግልፅነት፣ ቅርበትና በጋራ ስንሰራ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም መላው ህዝባችን የኛን ሀሳብ በመረዳትና አላማ በመቀበል ከጎናችን ሆኖ ይህን በህወሓት አማካኝነት ከፊት ለፊታችን የተደቀነብንን ሀገር አጥፊና ህዝብ ጨራሽ ድርጊት በጋራ በመሆን ከየራሳችን ጀምሮ ከመላው ምድራችን ጠራርገን ልናጠፋውና የፊት ለፊታችንን ግልጽ፣ ንፁህ፣ ሰፊ፣ ምቹና መጨረሻው በማይታይ በረጅም ደምቆ የሚንጎገቦግ የተስፋ ብርሀን ልንተካው ይገባል፡፡ የአዲስ አበባ፣ ድሬ ዳዋ፣ ሶማሊ፣ አፋር፣ ሀረሬ፣ ጋምቤላና ቤሻነጉል መስተዳደሮችና ክልላዊ አስተዳደሮች ከነህዝባቸው የአዲሱ ኢህአዴግ አጋር ይሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን በደስታ እየገለፅን፤ ሁኔታውን ከግምት በማስገባት በጊዜ አወንታዊ ምላሽ እንደሚሰጡን ባለሙሉ ተስፋ ነን፡፡ የወቅቱም ሆነ ከዚህ በፊት ለሆነው የሀገራችን ችግሮችና የህዝቦች መሰቃየት ምንጩ ማንም ሳይሆን እኛ ነን፡፡ መፍትሄውም ማንም ሳይሆን እኛ ነን፡፡ የዘር ፖለቲካን ያህል መጥፎ የሆነ ህዝብ ከፋፋይና ሀገር አጥፊ በደል ያመጣብን ጠላት ቢሆንም የተቀበልነውና የተገበርነው ግን እኛ ነን፡፡ የመጨረሻ ውጤቱ ደግሞ ይኸው ከትልቅ ተራራ ጫፍ አፋፍ ላይ አድርሶ ሁላችሁንም ልጥላችሁ ነው እያለ እያስፈራን ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሌላ ሌላውን ወደ ጎን በመተው በአሳሳቢ ጉዳይ ላይ የምትገኝን የሁላችንም የጋራ ቤት የሆነች የሀገራችንን ጉዳይ የግድ መፈወስ መቻል አለብን፡፡ በዚህ አጋጣሚም የህዝብ ልጆች አካል የሆኑት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተርና የመከላከያ ሚኒስተር ለህወሓት ምን ያህል ወሳኝ እንደሆኑ የሚታወቅ ሲሆን አነሱን መጠቀሚያ በማደረግም ነው ወደፊት የከፋ በደል ሊያደርስብን የሚችልና ወደ እኛ ይመጡ ዘንድ ጥሪያችን አምላካዊ መልዕክት ያለውና ጩኸታችንም የቶሎ ድረሱልን ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህ ሁለት የህዝብ አካሎች ከህዝባቸው ጋር በመቀላቀል የህወሓትን በሀገር ላይ ሴራ፣ ተንኮልና አደጋ በጋራ ልናከሽፈው ይገባል እያልን መጠየቅ ብቻ ሳይሆን ለሀገርና ለህዝብ ስንል ዝቅ ብለንና ተንበርክከንም እየለመናቸው ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ህወሓትን ራሱንና በሀገር ላይ ስላለው ማንኛውን ጉዳይ በተመለከተ ወሳኝ ናቸውና ሳይዘገዩ ህሊና በመግዛት ህዝባቸውን ይመርጣሉና ሀገርም ከፊት ለፊት ከተደቀነባት ከባድ አደጋ ትድናለች የሚል በነሱ ትልቅ እምነት አለን፡፡ እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ከህወሓት ጋር ያላቸውን ግንኙነት ቢያቆሙ፣ ነገ የህወሀት ጥቃትና አደጋ ብቻ ሳይሆን ራሱ ህወሓት አይኖርም፡፡ ይህን በመረዳት ትልቅ ሀላፊነት ያለባቸው እንደሆኑ አምነው እነዚሀ ሁለት የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ከህዝባቸው ጋር በመቀላቀል ካለምንም ረብሻ ወይም የስራ መጓተት ሰላም የሞላበትና አንድነት ያለበት ለውጥ በጋራ እናመጣ ዘንድ ወሳኝ የሆነ ሚናቸውን መጫወት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሀላፊነት ብቻም ሳይሆን እንደ ዜጋ ለሀገራቸውና ህዝባቸው ለመሆን ግዴታም አለባቸውና ይህን ማድረግም ይኖርባቸዋል፡፡ አጥፍቶ አጥፍቶ ነገ ከሚጠፋ ዘረኛ ቡድን ጋር መቀጠል ግን ራስም ከቤተሰብ ጋር አብሮ መጥፋት ብቻ ነው ውጤቱ፡፡ ኢትዮጲያ ለዘላም ትኑር፡፡ ህዝብ የማያሸንፈው ምንም ነገር የለም፡፡ ይህ ግን መሆን የሚችል በጋራ ሲነሳና ካለምንም መፍራትና ማቅማማት ሀያልነቱን በተግባር ሲገልጽ ነው፡፡ ህገር የማንም ሳትሆን የህዝብ ነች፡፡ መንግስትም የማንም ሳይሆን የህዝብ ነው፡፡ ማገልገል ያለበትም ህዝብን እንጂ የራስን ቡድን እየመረጡ አይደለም፡፡
28
የሀገራችን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ አስመልክቶ ያደርጋችሁትን ውይይት ተከታትያለሁ። እንደተባለው መጀመርያ በኦሮምያ ቀጥሎም በአማራ ክልል የተካሄዱት ባለቤት አልባ ሰልፎች ከመካሄዳቸው በስተቀር የሚያመሳስላቸው ነገር የለም። ይዘዋቸው የወጡ መልክቶችና ባንዲራ ሳይቀር የተለያዩ ነበሩ። በማስተር ፕላን ሰበብ በኦሮምያ ሰልፍ ከተካሄደ በህዋላ ራሱን የዚህ ሰልፍ አደራጅና አክቲቪስት ነኝ የሚለው ጃዋር መሐመድ በተቃዋሚ ድያስፖራ ኢትዮጵያውያን ዘንድ በተበለጥንና ኦሮምያን እናጣለን ሥጋት ጃዋርን እስከመለማመጥና በህዋላም የጎንደሩን ሰልፍ አጋርነታቸው ለመግለፅ ተጠቅመውበታል። በሁለቱም ፅንፈኛ ቡድኖች መካከል የራስ ዳሸን ያክል ልዩነት ቢኖርም ዎያኔን ለመጣል በሚል ስልት ግን አብረው ይሰራሉ ። ሌላው በውይይቱ የተነሳው ነጥብና የብዙ ኢትዮጵያውያን ጥያቄም፣ በተለይም የጎንደሩ ሰልፍ ያነጣጠረው በህወሃትና በትግራይ ሕዝብ ላይ ነበረ፣ ቀጥሎም በተለያዩ ሚድያዎችና የቲቪ ጣብያዎች በተካሄዱት ውይይቶችና ክርክሮች ከአቶ ጌታቸው በስተቀር መልስ የሚሰጥ መጥፋቱ (ኢሕአዴግ አብሮት የዘለቀ ድክመት) ሌሎች ድርጅቶችና ባለስልጣኖችስ የት ሄዱ? ይህንን መንግሥት በማናቸውም ዘዴና ስልት ለመጣል የሚታገሉት ኃይሎች እንደሚሉት ‘ህወሃት ከተወገደ ሌላው ግድ የለም’ እውነት ነውንዴ ያስብላል።
29
የኢትዮጵያ የመንግስት መዋቅር ከ95 በመቶ በላይ የተያዘው በሕወሓት አመራሮች ነው፤ ቀሪው 5 በመቶ በሌሎች ቢሆንም ምክትላቸውና ደህንነቶች የራሳቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ለአብነት ብንመለከት የሕወሓት ህቡእ ቡድን አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው፡- ቁልፉ የመከላከያ ሚኒስተር በሕወሓት አመራሮች እጅ ነው፤ ከ95 በመቶ በላይ የወታደር አመራሮች በየቀጠናው የሕወሓት ሰዎች ናቸው፤ ውትድርና የተከበረ ሙያ ነው ለሌላው ግን ፈተና ነው፡፡ የመረጃና ደህንነት መረብ ኤጀንሲ ውስጥ ከባለሙያ ጀምሮ የሕወሓት ሰዎች ናቸው፡፡ ሳይንስና ቴክኖሎጅ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ፤ አራት ኪሎ ከወታደር ጀምሮ የአንድ ቋንቋ የበላይነት ይታይበታል፡፡ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ቁልፍ የመንግስት መዋቅሮች የተያዙት በሕወሓት ሰዎች ነው፤ ታጋይ ነኝ ያለ ሁሉ ባይማርም ዲግሪ ተሰጥቶት መሪ ይሆናል፤ አሁን ደግሞ ታጋይ ሲያልቅባቸው ለሰዎቻቸው ታጋይ የሚል ታፔላ እየተለጠፈ ወደ አዲስ አበባ እየተላኩ ነው፡፡ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ታላላቅ ሆቴሎች፤ታላላቅ ህንጻዎች፤ የንግድ ቦታዎች፤ አስመጭና ላኪዎች፤ ታላላቅ የግል ኮሌጆች፤ የግል ት/ቤቶች፤ ኢንቨስትመንቶች፤ የኮንስትራክሽን ተቋራጮች፤ ታላላቅ የቢዝነስ ቦታዎች ለሕወሓት ሰዎች ነው፡፡ ለኢንቨስትመንት ተብሎ የሚሰጠው ቦታ ለማንም የኢትዮጵያ ህዝብ አይሰጥም፤ ማንም ጠይቆ የኢንቨስትመንት ቦታ አያገኝም፤ መሰናክሎች ይበዙበታል፤ የትግራይ ተወላጅ ሆኖ በሕወሓት ዘሩ የተጠና ከሆን ጉዳይ ለማስፈጸም በሚሄድበት ቢሮ ሁሉ የይለፍ ደብዳቤ ተዘጋጅቶ ይጠብቀዋል፤ ይህ የኢሉሚንስቶች አሰራር በሕወሓት መንግስት ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ቆይቷል፤ አብዛኛው የሕወሓት ዘር ያለው ሰው በአዲስ አበባ ውስጥ በግልም በመንግስትም የተሰጠው ከበቂ በላይ መኖሪያ ቤት አለው፡፡ ከ100 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን አንኳን ቤት ሊኖረው ነገ ስለሚበላው ምግብ ሲጨነቅ ያድራል፡፡ ቢርበውም ጤና የሰጠኽኝ አምላኬ እያለ እያመሰገነ ይተኛል፡፡ አነጋጋሪው ጉዳይ ደግሞ ለሱዳን የተሸጠው መሬት አቀማመጥ ከትግራይ ተነስቶ ወደ ጎንደር 60 ኪሎ ሜትር ገባ ብሎ እስከ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ታላቁን የህዳሴ ግድብ ያለበት ስፍራ የሚነካ ቦታ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ በታላቅ ሞራልና ቁጭት የሚሰራው ግድብ ቢሆንም በአስደናቂ ሁኔታ የሕወሓት ህቡእ ቡድን እጁን ማስገባቱ ነው፡፡ የአሁኑ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን በወቅቱ የክልል ሶስት ምክትል ፕሬዝዳንት የነበረ ሲሆን የወቅቱ የክልል ሶስት ፕሬዝዳንት አቶ አያሌው ጎበዜ ከላይ የተጠቀሰው የመሬት ይዞታ ለሱዳን ይሸጥ የሚል ጥያቄ ሲቀርብላቸው አሻፈረኝ በማለታቸው በሌላ ምክንያት ወደ አሜሪካ እንዲሄዱ የሕወሓት ህቡእ ቡድን አዘዘ፡፡ ከዚያም ይህ የአሁኑ ምክትል ጠ/ሚንስተር ደመቀ መኮንን ቢሮ በመግባት የክልሉን መሬት የሽያጭ ውል እንዲፈርም ተደረገ፡፡ በጣም ለማመን የሚከብደው ግን ይህ የጎንደር ፤የቤንሻንጉል ጉሙዝ መሬት እስከ ግድቡ ድረስ ያለው በውሉ መሰረት ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ በኋላ ለሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ለትግራይ ክልል የሚመለስ እንደሆነ በተረዳ ጊዜ አቶ ደመቀ መኮንን ቅሬታ ቢያቀርብም በሳሞራ የኑስ ወታደሮች ታፍኖ የተለያዩ ማስፈራሪያዎች ሞትን ጨምሮ ተሰጠው፡፡ እሱ ግን በወቅቱ ከተሰጠው አማራጮች ለሱ የሚሻለውን አሁን ያለበትን ቦታ መረጠ፡፡ እነዚህ እኮ ናቸው አምርረው የሚጠሉትንና በተለያየ መንገድ ዘመቻ ከፍተው ለዘመናት በከባድ እየጎዱትና የዘር ማጥፋት ጦርነት ከፍተው የሚወጉትን አማራን ጭምር እናስተዳድራለን የሚሉን፡፡ “ታዲያ ጋላ ናቸሁ ማለት ነው? እኛ ከጋላ በታች ሰው ያለ አይመስለንም፡፡ አማራን የምንጠላና ጋላን ጨምሮ ሌላውን ከእግራችን ስር እንደሆነ እየተሰማን የምንንቅ ነን፡” ጊዜ ሲመጣና ቀን ሲወጣ መለስ ዜናዊን፣ ቲዎደሮስ አድሀኖምንና ሌሎችንም ትግሬዎችንና የነሱ ተባባሪ የሆኑትን የውጪ ሀይሎችና ድርጅቶች በዘር ማጥፋት የሚያስጠይቅ ወንጀል ከሆኑት ውስጥ አንዱን ይመልከቱ፡፡
30
በቅድሚያ አሁን በሀገሪቱ ያለው ምስቅልቅል “የመልካም አስተዳደር ፡ሙስና መር ኢኮኖሚ ” የሚሉ ቱማታዎች አደሉም።እነኝህ ኢህአዴግን ንቅዘት፡ የደጋፊና ተደጋፊ ፡አድናቂና ተደናናቂ ፡ጭብጫቦ ደንቁሮ ወደ ተራራ የተስፈነጠረበት ልዩ ምህታት ናቸው ። >>>> ተራራውን ያንቀጠቀጠ ጀግና ፡ልማታዊ ዴሞክራሲን የፈለሰፈው ፡ ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነትን የፈተለው ፡አውራው ፓርቲ ፡ገዢው ፓርቲ ፡የኢህአዴግ መንግሥት፡ መድብለ ፓርቲን በአጋር ፓርቲ የደቀለ የፓለቲካ ምሕዳርን አጥቦ ብዙ እስታዲየም በክልሎች ሲከፍት ብዙ የተፎካካሪ ፅሕፈት ቢሮ ይዘጋል እንግዲህ ትቢትና ንቀት የወለደው ብሶት የወለደውን ተራራውን ያንቀጠቀጠውን መሞገት ብቻ ሳይሆን የተራራውን ቁልቁለት ማመልከት ጀመረ ። >>>ምን አድርጌ ነው ? ለምን ህወሓትን ብቻ? አውርቶ በል፡አድር ባይ፡የአብዮቱ ተጠቃሚዎች የት ሄዱ?የኢኮኖሚው ዕድገት ተቋዳሾች ለምን አልተወገዙም ? በዚህ ቀውጢ ቀን ለምን አልጮሁም? (በአይጋ ፎረም የሚወጡ ፅሑፎች ከአውራ አምባ ታይምስ አስተያየት ጋር ይጣረሳሉ የህወሓትን የበላይነት፡ ጀግንነት፡ ሀብታምነት በሌላው በኩል እርስ በእርስ በሚያጫርስ ዘረኝነት መርዝ የተለከፉ ፡ ኦህዴድ፡ ደህዴን ፡ብአዴን፡ተራ በህውሓት ተጠፍጥፈው የተሠሩ በፈለገው ግዜ የሚሾምና የሚሽራቸው ከሥልጣን የሚያስወግዳቸው ፡በፈለገው ምክንያት ክልላቸውን በፌደራል ልዪ ኀይል ወሮ አስተዳደሩን እንደሚነጥቃቸው ሁሉ፡ይፃፋል ዕለት ከዕለት ሲተገበር ሕዝብ አረጋግጧል ።የሚከሰሱ ፡ከሥራ የሚባረሩ ፡የሚታሰሩ፡የሚፈናቀሉ ፡ሁሉ ቅድሚያ ታሪካቸው የሚብጠለጠለው በህወሃት ጉልበተኝነት እንጂ በገልተለኛ የፍትህ ሥርዓት እንዳልሆነ ተመጣጣኝ የሥልጣን መጋራትና መደላድል እንደሌለ አይጋ ይመሠክራል ። ***አሁን ተራው የሕዝቡ ነው ።መብረቅን በጃንጥላ ሆነ ውይይቱ ሁሉም የተነሱት ሐሳቦች ጥሩ ናቸው እናንተንም ቤት አሳታፊነት የለም ! አንድ ፖለቲከኛ ፡መምህር፡ የመንግስት ሠራተኛ ፡ተማሪ፡ወይም በብሔር ተዋጽኦ የሚደረገው ሌላውን ሕዝብ ማድመጥ ይቻላል ጉዳዩ የሀገር ሲሆን ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ለጭፈራ ብቻ ሳይሆን ሀዘናቸውም ይደመጥ ተቸጋሪም አስቸጋሪም ናቸውና ! *** አጋር ፓርቲ(ዲቃላ) ፻ ከመቶ ማሸነፍ (መሳቂያ መሳለቂያ )መድብለ ፓርቲ፡ (አሸባሪዎች ፡ የዕድገት እንቅፋቶች፡፡የድሮው ሥርዓት ናፋቂዎች ) ፓርላማው ፶፩ ለ፵፱ ቢሆን የህወሓት ኪሳራ ከአሁኑ ይበልጥ ነበር ? ለመሆኑ አሁን መብት ጠያቂው ትውልድ በህወሓት /ኢህአዴግ ‘ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት’ ናላው የዞረ የተከለለ እና የተከለከለ ፡የበይ ተመልካች ስለሆነ አደለም እንዴ? ዋሸሁ እንዴ?
31
ሰባት ጽቡቕ ስራሕ ይሰርሑሞ ፡ እቲ ዝሰርሑዎ ስራሕ ከኣ ካልእ ጽቡቕ ውጽኢት የመዝግብ። ኣብ ልዕሊ’ቲ ጽቡቕ ስራሕ ጽቡቕ ሓድሽ ፍረ ይድመሮ፡ ቡኡ መጠን ከኣ ጽቡቕ ኩነታት ይኽሰት፡ ነኒሕድሕዱ ዝደጋገፍ ዓወታትካ ዘቃላጥፍ ደያቢ ውጺኢታት ካኣ ተመዝግብ። እዚ ግን ነገራት ካብ ስበቶም ከይወጹ፡ መንገዶም ሓሊዮም እንተድአ ከይዶም ኢዩ። ይንዋሕ ይሕጸር፡ ኩነታት እናተመሓየሸ፡ ኣወንታዊ ተሞክሮን መሪሕነታው ጥበብን እናደለብካ ትኸይድ።
32
ወ/ሮ ነበቡ ደሳለኝ የሶስት ሴት ልጆች እናት ነች። ጥር 22/2009 ዓ.ም መንገድ ላይ ነበር ድንገት የደህንነት አባላት የያዟት። ሲይዟት ለጥያቄ ‘እንፈልግሻለን፣ ትመለሻለሽ’ ቢሏትም እሷ ግን አላመነቻቸውም። ስለዚህ መኪና ውስጥ ለመግባት ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። ይህ ግን የደህንነት አባላቱን አላስደሰተም። ስለዚህ መኪና ውስጥ አንስተው ወረወሯት። በዚህ ምክንያትም የመኪናው ወንበር ሆዷ ላይ መቷት ጉዳት እንደደረሰባት ትናገራለች፤ ጀርባዋንም ያማታል። ማዕከላዊ ከገባች በኋላ ሕክምና ለማግኘት የጠየቀች ቢሆንም ለሁለት ወር ያህል ተከልክላ እንደቆየች ለቢቢሲ ተናግራለች። መጀመሪያ የተወሰደችው ወደ ማዕከላዊ እንደነበር የምትናገረው ነበቡ ስልኳን ከተቀበሏት በኋላ ስልኳ ላይ የሰፈሩ ሰዎችን ማንነት እንድትናገር ምርመራው እንደጀመረ ታስታውሳለች። ቤተሰቦቿ መታሰሯን ያወቁት መርማሪዎች ቤቷን ለመበርበር በሄዱበት ወቅት እንደሆነ የምትናገረው ነበቡ “ቤተሰቦቼ ጠፍታለች በሚል ፍለጋ ላይ ተሰማርተው ነበር” ብላለች። በምርመራ ወቅት በተለያዩ ንግግሮች አእምሮዋን ለመጉዳት ደጋግመው እንደሞከሩ የምትናገረዋ ነበቡ “ሌባ፣ ቅጥረኛ፣ ሽብርተኛ የምታደራጂ” እያሉ ይሰድቧት ነበር ትናገራለች። ከዚህ የከፋው ደግሞ “ልጆችሽ በረንዳ ነው የሚወጡት፣ ለወደፊቱ ሴተኛ አዳሪዎች ነው የሚሆኑት፣ ልጆችሽን ቁጭ አድርገን ስለሰራሽው እንነግራቸዋለን፣ ስለዚህ አንቺ ደግሞ እዚሁ ነው የምትበሰብሽው” የሚሉና ሌሎች አፀያፊ ስድቦች ይሰነዘሩባት እንደነበር ታስታውሳለች። በማዕከላዊ የሥነ-ልቦና ቀውስ ደርሶብኛል የምትለው ነበቡ በምርመራ ወቅት ብቻ ሳይሆን በኑሮም ጉዳት ይደርሳል ትላለች። በእስር ቤት እሷን ለመጠየቅ የሚሄዱ ቤተሰቦቿ ሳይቀሩ ተንገላተው እንደሚገቡም ታስታውሳለች። “ሲፈልጉ ምግብ፣ ሲፈልጉ ቤተሰቤን የሚፈልጉትን ነገር ብለው ይመልሳሉ” ይህ ሁሉ ሥነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጉዳት አለው ትላለች ነበቡ። ኦዲዮውን እዚህ ላይ ያድምጡ ለሊሴ ባህሩ ክሳቸው ተቋርጡ በፌደራል መንግሥት ከተለቀቁ አምስት ሴት እስረኞች መካከል አንዷናት። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው ለሊሴ ሰኔ ስምንት 2008 ዓም ከምትኖርበት ሸጎሌ አካባቢ ሦስት ማንነታቸውን የማታውቃቸው ሰዎች በኃይል አስገድደው ወደ ማዕከላዊ በመኪና እንደተወሰደች ታስታውሳለች። ”አሞኝ ስለነበር ከሐኪም ቤት ወደቤት ተመልሼ ብዙም ሳይቆይ ቤቴ ተከበበ። ከዚህ በፊትም ይመጡ ስለነበር ልጆቼ ፊት እንዳይዙኝ በማለት ከቤት ወጣሁ፤ ከዛ በመኪና ተከተሉኝ። በኋላም በኃይል ወደ መኪና አስገቡኝ።” ብላ የተያዘችበትን ሁኔታ ታስታውሳለች። ለሊሴ በተያዘችበት ቀን አይኗን ታስራ ከተማ ውስጥ ሲያሽከረክሯት ከቆዩ በኋላ ማታ ላይ ወደ ማዕከላዊ እንደወሰዷትና ለሶስት ቀን ከቤተሰቦቿ ደብቀው እንዳቆይዋት ትናገራለች። ነበቡ ስለታሰረችበት ስፍራ ስትናገር “የሴቶች ክፍል ያለው ሁለት ነው። አራት በአራት ወይም ሶስት በሁለት ይሆናሉ ክፍሎቹ። 20 እና 30 እስረኛ ተፋፍገን ነው የምንኖረው” ብላለች። እስር ቤት ሳለች እፈታለሁ ብላ አስባ እንደማታውቅ የምትናገረው ነበቡ “እዚሁ በስብሰሽ ትቀሪያለሽ’ የሚለው ንግግር ስለነበር የሚመጣውን ነገር ሁሉ ለመቀበል ከመወሰን ውጭ ሌላ የማስበው ነገር አልነበረም” ትላለች። ነበቡ በደህንነቶች በቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ ለተከታታይ አምስት ወራት በየወሩ ፍርድ ቤት እየሄዱ የ28 ቀን ቀጠሮ ተቀብሎ ከመምጣት ውጪ ጉዳይዋ ታይቶ ፍትህ አገኛለሁ የሚል ተስፋ እንዳልነበራት ታስታውሳለች። “እኔ ንፁህ ነኝ ብልም በንፅህናዬ አላምንበትም ነበር” የምትለው ነበቡ ለዚህ ደግሞ ምክንያቷ ከሌሎች እህቶቼ እንዳየሁት እስከፈለጉት ድረስ በእስር ቤት ስለሚያቆዩ እኔም ለዚህ ራሴን አዘጋጅቼ ነበር ትላለች። ነበቡ እንደምትለው ለመፈታታቸው ምክንያት በሃገሪቱ የተለያዩ ስፍራዎች የተነሱት ተቃውሞዎች መንግሥት አካሄዱ ትክክል እንዳልሆነ እንዲረዳ ስላደረገው ነው ትላለች። በኋላም ከኦነግ ገንዘብ በእርሷ በኩል ይደርሰው እንደነበር ድሪብሳ በተባለ ግለሰብ ላይ መስክሪ ተብላ በተደጋጋሚ ተጠይቃ እንቢ በማለቷ ክፉኛ መደብደቧን ትናገራለች። ”ከግራና ከቀኝ በጥፊ ያጣድፉኝ ነበር። ጣቶቼ መካከል ማስመሪያ አስገብተው ይጨምቋቸዋል። በእስክርቢቶ አይኔን ለመውጋት በተደጋጋሚ ሞክረዋል” ትላለች። የማታውቀውን ነገር ወረቀት ላይ በመፃፍ ፈርሚ በማለት እንደተደበደበች እንዲሁ ትናገራለች። በማዕከላዊ መረገጥ፣ በጥፊ መመታት፣ አስተኝተው ጀርባ ላይ መሄድ፣ ስፖርት ማሰራት እና እርቃን በወንድ መርማሪዎች ፊት እንዲቆሙ በማድረግ የተለያዩ እንግልቶች ይደርስባቸው እንደነበር ታስታውሳለች። ከአራት ወር የማዕከላዊ ቆይታ በኋላ ወደ ቃሊቲ መዛወሯን የምትናገረው ለሊሴ፤ እዚያ ድብደባ ባይኖርም በፖለቲካ ምክንያት የታሰረ ሰው ከሌሎች እስረኞች እኩል መብት የላቸውም ትላለች። እርሷን ጨምሮ ሦስት ሰዎች የቀረበባቸው ምስክርም ሆነ የሰነድ ማስረጃ ስላልተገኘ፤ ስታወሩ የተቀዳ ነው ተብሎ ከቴሌ በመጣ የድምፅ ቅጂ በአሸባሪነት መከሰሷን ትናገራለች። የልጆች እናት የሆኑት ነበቡ ደሳለኝ እና ለሊሴ ባህሩ በማዕከላዊ የምርማራ ማዕከልና በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ ከቆዩ በኋላ መንግሥት በሰጠው ውሳኔ መሰረት ክሳቸው ተቋርጦ ከተለቀቁ እስረኞች መካከል በመሆን ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል። ወ/ሮ ነበቡ ደሳለኝ የሶስት ሴት ልጆች እናት ነች። ጥር 22/2009 ዓ.ም መንገድ ላይ ነበር ድንገት የደህንነት አባላት የያዟት። ሲይዟት ለጥያቄ ‘እንፈልግሻለን፣ ትመለሻለሽ’ ቢሏትም እሷ ግን አላመነቻቸውም።
33
ለክቡር ዶክተር አብይ አህመድ የአትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አዲስ አበባ ክቡር ሆይ ትላንት፣ ግንቦት 28 ቀን 2010 አም የኢህአዴግ ስራ ስፈጻሚ ኮሜቴ በቁልፍ የአኮኖሚ ተግባር የተሰማሩና እስካሁን በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ አገልግሎት ሰጪና አምራች ድርጅቶች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለግል ባለሀብቶች እንዲሸጡ መወሰኑን ተረድቻለሁ፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የባቡር አገልግሎት ለሽያጭ እንዲቀርቡ መወሰኑ ከፍተኛ ሀዘንና [...]
34
በትራንስፖርት ማኔጅመንት፣ በትራንስፖርት ኢኮኖሚክስ፣ በአርባን ማኔጅመንት 4(6)፣ በሲቪል ምህንድስና፣ በኢኮኖሚክስ 5(7)፣ በስታስቲክስ 5(7)፣ በትራፊክ ምህንድስና 0(0) ወይም በተዛማጅ የሙያ መስክ
35
1ኛ ከውልደቱ እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ ለኢትዮጵያ በጎ የማይመኘውና ከተቻለ ለማፈራረስ ሌት ተቀን የሚሰራው የሻአብያ መንግስት ብዙ ችግር በሀገራችን ላይ ሳያስከተል ማስወገድ እየተቻለ ራሱ በራሱ በስበሶ ይወድቃል፣ኢሳያስ አፈወርቂም ለመሞት የቀረው አንድ አርብ ነው ሲባል እነሆ መለስ ዜናዊ የሚያከል መሪ ቀብሮ፣ ኢትዮጵያ የማፈራረስ ሕልሙ እውን ለማድረግ ዛሬ ከማናቸውም ጊዜ በተሻለ ቁመና ላይ ይገኛል። አልፎ አልፎ በሀገራችን የሚከሰቱ ግጭቶች ሻዕብያን ተጠያቂ ማድረጉ የአሳያስን ምንነት ከማግዘፉ በስተቀር ለውጥ አላመጣም። አነስተኛ የሕዝብ ቁጥር፣ የደቀቀ እኮኖሚና በአንድ አምባገነን መንግስት የምትመራ ሀገር ይህነን ታደርጋለች ብሎ የምያምን ሰው አይኖርም። 2ኛ በዓላት ማክበርና መዘከር የነበረ፣ ያለና ወደፊትም የሚኖር ጉዳይ ቢሆንም እንደዚህ አመት የተንዛዛበትና ብዙ የሚነገሩ ጉዳዮች እያሉ ሰው ስልችት እስከሚለው ድረስ በሚድያ የተዘገበበት ወቅት የለም። የብአዴን ይህ ቀረሽ ክብረ በዓል ከወር በላይ ተነግሮ አበቃ ስንል የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሃምሳኛ አመት በማስመልከት ህዝቡ ከጫንቃው አውረዶ የጣላቸውን የቀድሞ ነገስታት እያነሱ በየቀኑ ማላዘኑ ማነን ይጠቅማል? 3ኛ ኢትዮጵያን ለአመታት በፈላጭ ቆራጭነት የመሩት፣ ብዙ ግፍና በደል የፈፀሙ ሰዎችና ልጆቻቸው ዛሬ ከተሰደዱበት አገር እኛ ያልገዛነው ሀገር እድገትና ልማት በአፍንጫችን ይውጣ ብለው በዘረኝነት ሀገሪቱን ለማፈራረስ ሁለመዳያዊ ትግል በሚያደርጉበት፣ ከውጭ ሀገር ሌት ተቀን የውሸት ፕሮፖጋንዳ ዘመቻ በከፈቱበት በአሁኑ ወቅት፣ አባሎቻቸው በቀድሞ የኢሕአፓ ሰንሰለት አይነት በየመንግስት ተቅዋሙና ህዝባዊ ድርጅቶች አሰርገው በማስገባት ህዝቡ እንድያማርርና ለሕዝባዊ አመፅ እንዲነሳ በሚያሴሩበት ወቅት፣ ጀሌዎቻቸውን መመንጠርና ማፅዳት ሲገባ እነሱ ባጠመዱት ወጥመድ ገብቶ ሆነ ተብሎ እየተፍፀመ ያለውን የመልካም አስተዳደርና ሌላም ሌላም ቸግሮች እያነሱ መለፈፉ ለእነዚህ ሰዎች አፍ መክፈቻ ከመሆን በስተቀር ሌላ ለውጥ አያመጣም፣ ሆን ተብሎ የሚሰራ ሻጥር ነውና ።ብርሃኑ ነጋ በቅርብ ጊዜ ዲስኩሩ; ” ከአሁን በህዋላ ሰሜን መሄድ አያስፍልግም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው የምንንቀሳቀሰው” ያለው ፈሪ ልቡን ቀይሮ ወይም ከአሜሪካ የሚወረወር ጦር አዘጋጀቶ ሳይሆን በየቦታው የተሰገስጉ ጀሌዎቹ ማለቱ ነው።
36
ኩንቲ ለቃሚና አምበጣ ቆርጣሚ ትግሬ በሙሉ አንድ በአንድ በወረንጦ ተለቅሞ ከመሃል ሀገር ወደ ድንጋያማዋ ትግራይ ይባረራል።ትግሬ ሌባና ለማኝ ነዉ ከጎንደርና ከወሎ የዘረፈዉን የወልቃይት ጠገዴንና የራያን መሬት በክብር ለአማራ ህዝብ ይመልሳል።ትግሬና ወያኔ አንድ ነዉ ወያኔ ለትግሬዎች ሃይማኖታቸዉ ነዉ።የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ደም ተቃብቷል፣ሆድና ጀርባ ሆኗል። ትግሬ እዩኝ እዩኝ እንዳላለ ደብቁኝ ደብቁኝ የሚልበት ቀን ይመጣል።ትግሬ ወደ መቀሌ፣ንብረት ወደ ቀበሌ፣ወያኔም ወደ ከርቸሌ የሚለዉ አዋጅ በቅርብ ቀን ይታወጃል። ድል ለሰፊዉ የኦሮሞ ህዝብ፣ድል ለሰፊዉ የአማራ ህዝብ፣ድል ለሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ሞት ለአናሳ ትግሬዎች!
37
የሩዋንዳውን -hate radio (rtlmc) የዘር ፍጭትን ያፋፋመውን ድርጊት ለመድገም ዳር ዳር ያልክ ይመስላል። በማንኛውም የተቃውሞ መፈክር tplf አና በዙሪያው ያሉ ተጠቃሚዎችን አንጂ የትግራይ ህዝብን በኣጠቃላይ ጠላት ነው ወይም ተጠቃሚ ነው ብሎ የተናገረ የለም። ቅሬታው በገዢው ፓርቲ ላይ አንጂ በህዝብ ላይ ኣይደለም ።
38
የድብቅ ቀረፃ የተደበቀንና ፊት ለፊት በግልፅ የማይወራንም ሆነ የማይደረግን ድርጊት አጋልጦ የሚያወጣ ነው፡፡ እዚህ ላይ ግን ምንም የሚታይም ሆነ የሚሰማ አዲስ ነገር የለም፡፡ እንዲያውም ይህ ሰው በግልፅና በፊት ለፊት ልከ እንደ መልአክ አይነት የሆነ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ እነ ህወሃትና ጪፍን ትገሬ ደጋፊወቻቸው በግልፅ፣ በፊት ለፊትና በተደጋጋሚ ለዘመናት ከሚያወሩትንና ከሚፈፅሙት ውስጥ በጣም ጥቂት የሆነውን ከዚሀ በታች በመመልከት በድብቅ ምን እንደሚያስቡ፣ አንደሚነጋገሩና እንደሚፈፅሙ በጣም ከባዱንና ጨካኝ አጥፈውን ስለመሆኑ ለመገመት አያዳግትም፡፡ ጊዜ ሲመጣና ቀን ሲወጣ መለስ ዜናዊን፣ ቲዎድሮስ አድሀኖምንና ሌሎችንም ትግሬዎችንና የነሱ ተባባሪ የሆኑትን የውጪ ሀይሎችና ድርጅቶች በዘር ማጥፋት የሚያስጠይቅ ወንጀል ከሆኑት ውስጥ ይመልከቱ፡፡
39
የማያዳግም ተቃውሞና የማይምር ሞት ለያንዳንዱ ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ የህወሃትና የትግሬ ተፅኖም ሆነ ጣልቃ ገብነትና የማያቋርጥ ዝርፊያና ብዝበዛ በአማራ ህዝብ ላይ፡፡ ብአዴንን በመግደል ህዝብን ለማትረፍ ይቻል ዘንድ በብአዴን ውስጥ የህወሃት ተላላኪና ቅጥረኛ የሆኑትን የአማራ ህዝብ ጠላቶች እንደ ገነት ዘውዴ፣ ታደሰ ካሳ፣ ካሳ ተክለ ብርሀን፣ በረከት ሰሞን፣ አለምነህና ሌሎችም እነዚህን የመሳሰሉትን ከላይ ከባህር ዳር ጀምሮ እስክ ታች ሰፈርና መንደር ድረስ ህወሃት አሰማርቶ በራሳቸው ህዝብ ላይ ጠላት እንዲሆኑ ያደረጋቸው ሁሉም መገርሰስ አለባቸው፡፡ ከላይ ጀምሮ እስከ ታች ቀበሌ፣ ሰፈርና መንደር ድረስ አንድም የህወሀት አገልጋይም ሆነ የትግሬ ተላላኪ ወይም ተባባሪ በአማራ ህዝብ ውስጥ እንዳይኖር ማድረግ ግድ የሚል ነው፡፡ የህወሀት ብአዴን ከአማራ ህዝብ ላይ ተወግዶ ሞቶ ተቀበረ ማለት ህወሀትም ከአማራ ህዝብ ላይ ሙሉ በሙሉ ተወገዶ ሞቶ ተቀበረ ማለት ነው፡፡ በመሆኑም የህወሃትም ሆነ የትግሬ ቅጥረኞች፣ አገልጋዮችም ሆኑ ስለነሱ ከጥላቻ በስተቀር ሌላ ስሜት ያላቸውን ከአማራ ህዝብ ላይ አየመነጠሩ ማውጣት ግድ የሚል ሲሆን ከዚህ የተለየ ሌላ ምክንያትም ሆነ ጊዜ የሚሰጠው አይደለም፡፡ አዲሱን ለህዝብ የሚሰራን ብአዴንን በራሱ ወይም በሌላ ስም ለመመስረት በጣም ቀላል የሆነና ጊዜ የማይሰጠው ሲሆን ይህም በህዝብ የሚወሰን ነው፡፡ ህዝብ ነው የራሱን መሪዎች መምረጥም ሆነ መሻር የሚችል እንጂ የአማራ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት ነኝ እያለ በአደባባይ የሚሰብክና ይህንኑ ድርጊት ለዘመናት የሚፈፅም ህወሃትና ትግሬ አይደለም፡፡ ደጉ አንዳርጋቸው ደግ ብቻ ሳይሆን የአማራንም ሆነ የኢትዮጲያን ህዝብ ማሰማማትና አንድ ማድረግ የሚችል ሰው ነው፡፡ በመሆኑም ታላቅና ጥንታዊ የሆነ የአማራ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር በመነሳት ለአቶ ደጉ አንዳርጋቸው የሀሳብ ድጋፍና የቁሳቁስ እርዳታ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ 30 ሚሊዮን የሆነ የአማራ ህዝብ በውስጡ በጎሳም ሆን በሀይማኖት መከፋፈል የሌለበት አንድ ህዝብ ነውና ከኢንቨስትመንትና የተለያዩ የኢኮኖሚና የእድገት እንቅስቃሴዎች በዚህ በተፈጥሮ በተመረጠና በተመረቀ ቦታ በነቂስ ወጥቶና ሆ ብሎ ተነስቶ በስፋት፣ ብዛትና ጥራት መሳተፍና መስራት አለበት፡፡ ግብርናውን ዘርፍ ማሳደግ ለሁሉም ዘርፍ እድገትና መሻሻል ቁልፍ የሆነ ነው፡፡ የትግራይ ዘራፊዎች እንደ ኢፎርት፣ መረት፣ ግለሰቦችና ሌሎችም ከአማራ ህዝብና መሬት ላይ ጨርሰው መወገዝና መወገድ አለባቸው፡፡ ራሱ ህዝቡና ሌላኛው የኢትዮጲያ ክፍል ህዝብ ከበቂ በላይ ነው፡፡ “አማራ ጠላታችን ነው፡፡ አማራን አከርካሪውን ስለሰበርነው ሽባ አድርገነዋል፡፡ አማራን ለራሱ እንዳይሆን አድርገነዋል፡፡ አማራን አዋርደንና አሳፍረን አግለነዋል፡ አማራን እንደ ሲጋራ አቃጥለን አመድ አድግረን ከቆሻሻ ጋር ጥለነዋለ፡፡ አማራን ሰባብረን፣ ረግጠንና ገድለን ጥርሰነዋል፡፡ አማራን አጥፍተነዋል፡፡ አማራን ቀብረነዋል፡፡ አማራን በሌላው ህዝብ ይናቅ፣ ይጠላ፣ ይዋከብ፣ ከቦታው ይፈናቀል፣ ንብረቱ ይዘረፍ፣ ይባረርና ይገደል ዘንድ አድርገነዋልና ሌላም ሌላም” እያሉ በአደባባይና ለረጅም ዘመን የሚሰብኩ ሀወሃትና ትግሬዎች እንዴት የአማራን ሀዝብ ለመዝረፍና በሱ ላይ ሸቀጥ ለማራገፍ ይቻላቸው፡፡ ከአሁን በኋላ አንድም የህወሃትም ሆነ የትገሬ ምርትና አውቶቡስንና የጭነት መኪናን ጨምሮ ግልጋሎት በከባድ ጎዱትና በሚጎዱት የአማራ ህዝብ ላይ መራገፍም ሆነ ለራሱ ስራ ፈጥሮ ጥቅም ማግኜት የለበትም፡፡ አንድም የአማራ ህዝብ ምርት ጤፍ፣ ስንዴን፣ ገብስንና ቦቀሎን ጨምሮ ወደ ትግራይ መሄድ የለበትም፡፡ ከመፍጨት ጀምሮ የምግብ ማቀነባበሪያ ፍብሪካዎችን በሚመረትበት አካባቢ በማቋቋም ከራስ የሚተርፍን ወደ አዲሰ እበባ በሸዋ በሉል፣ ወደ ምስራቁ ክፍል በወሎ በኩል፡ ወደ ምዕራቡና ደቡብ በወለጋና በሻንጉል በኩል መድረስ ይገባዋል፡፡ የህወሀት ብአዴን ተቀብሮ የህዝብ ብአዴን በዚህ መልክ ለህዝብ መስራት ሲጀምርና ኢፎርትን፣ መረትና ሌሎችንም የህወሃትና የትግሬ ዘራፊ ድርጅቶችን፣ ተቋማትንና ማንኛውንም የኢኮኖሚ ግንኙነት ማቋረጥ መቻል የህወሃትን በአማራ ህዝብ ላይ ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ጣልቃ ገብነት፣ ተፅኖ ወይም ዝርፊያ ሙሉ በሙሉ ማስቆም መቻል ብቻ ሳይሆን ህወሀትን ራሱን መግደልና ማጥፋት ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ህወሃትና ትግሬ በአማራ ህዝብ ላይ ያላቸውን ስር የሰደደና ዘመናት ያስቆጠረ በዘር ማጥፋት ላይ የተሰማራ ጥላቻና ወልቃይትን ጨምሮ ወደር የሌለው ጭፍጨፋና ማሰቃየት እንደሆነ ታውቆ ማንም አማራ ነኝ ባይ ከአሁ በኋላ ለህወሀትና ለትግሬ ሰራተኛ፣ ተባባሪና አገልጋይ መሆን ቀርቶ ሰላምም ሊላቸው አይገባም፡፡ ምን ያህል በደል እንዳደረሱ ከወልቃይና ከሁሉም የአማራ ቦታ ጀምሮ በመላው ኢትዮጲያ በአማራ ህዝብ ላይ የፈፀሙትና ያስፈፀሙትን ወንጀል ዞር ብለው ማጤን ይገባል፡፡ እነሱ በዝርፊያ ላይ ያሉ የአማራ ህዝብና ቦታ ቀንደኛ ጠላቶች ናችው፡፡ ራሳቸውም ይህን በአደባባይ የሚናገሩ ናቸው፡፡ ተመልከቱ ትግራይ ውስጥ ያለን የፋብሪካ አይነትና ብዛት እንዲሁም እድገትና እንስቃሴ ምንም እንኳ ቦታው በተፈጥሮ የተጎዳ ቢሆንም፡፡ ስሚንቶም ሆነ ሌላን ጥራት የሌለውን ምርት ከትግራይ ሳይሆን ከሌላው የኢትዮጲያ ክፍል መግዛት ግድ የሚል ሲሆን አማራ የራሱ የሆኑ ፋብሪካዎች ይኖሩት ዘንድ ግድ የሚል ነው፡፡ ይህም የህወሀት ብአዴን ሲሞትና አዲሱ በህዝብ የተመረጠ ለህዝብ የሚሰራ የደጉ አንዳርጋቸው ብአዴን ተመስርቶ ስራ ሲጀምር ይሳካል የሚል ትልቅ እምነት አለ፡፡ የአማራ ህዝብ ታላቅና ጥንታዊ የሆነ ብዙ ብቃቶች ያሉት ብቻ ሳይሆን የሚኖርበት ቦታ በውሃ ሀብት፣ ለም አፈር፣ መልካም አየርና ሰራተኛ ህዝብ ጭምሮ ታላቅ፣ ምቹና ተስማሚ ስለሆነ ቦታውን ለማልማት፣ ማሳደግና ህዝቡን ለመጥቀም ጥረት የሚጠይቅ እንጂ ከባድ የሆነ አይደለም፡፡ በህወሃት አማካኝነት ሰው ነበር የጠፋ፤ ከአሁ በ1ኋላ ግን ይህ ወሳኝ የሆነ ሰው ማጣት በደጉና ከሱ ጋር በሆኑ አማካኝነት ተፈውሷል፡፡ አማራ የሆነ ሁሉምና ኦሮሞን፣ ጉራጌን፣ ሲዳማውንና ሌሎችንም ጨምሮ ሁሉም ህዝቦች ከዚህ በህወሃትና ትግሬ አማካኝነት ሆን ተብሎ ሻጥር ሲሰራበትና ሰቆቃ ሲፈፀምበት በኖረ የኢትዮጲያ ጠቃሚ የአማራ ከፍተኛ ቦታ የእድገት እንቅስቃሴ መሳተፍ ይኖርባቸዋል፡፡ ክሀወሃት ውጪ የሆነች ኢትዮጲያ የሁላችንም የጋራ ሀብት ነች፡፡ ህወሃት ደግሞ የዘረፈውን ይዞ ለመሸሽ ሻንጣውን አያዘጋጀና መውጫውን እያመቻቸ ስለሆነ በቅርቡ ይወገዳለ የሚል እምነትና ተስፋም አለ፡፡ ይህም ሲሆን በሀገር ሰላም ሰፈነና አንደነት በህዝቦች መሀል ተመልሶ ጎለበት ማለት ነው፡፡ ቡትትህን ከቀየርህና ቅማልህን በኢትዮጲያ ህዝብ ላይ ካራገፍህ ጀምሮ መሳደብ ብቻ ሳይሆን እየገደልህ፣ ሀገርን አየከለልህና ህዝብን በብሄር ስም እየከፋፈለህ ትገኛለህ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አንተ አንበጣ ቆርጣሚ ኢትዮጲያ ሳትሆን አለምም የሁላችንም ነች ትለናለህ፡፡ ታዲያ ይህ ከሆነ ምነው ስልጣኑን፣ ሀብቱን፣ መብቱን፣ ሜዲያውን፣ ወታደሩን፣ ደህንነቱን፣ ፓሊስ ሀይሉንና ሁሉንም እናንተ ብቻ እየተቆጣጠራችሁት ትገኛላችሁ፡፡ ሁሉም ኢትዮጲያ የጋራ ከሆነ ታዲያ ለምን ተከዜን ተሻግራችሁ በመምጣት በምንም መንገድ ለናንተ ሆኖ የማያውቅንና ምን ጊዜም ሊሆን የማይችልን የጎንደርን ሰፊና ድንግል ለም መሬት በህገወጥ መንገድና በጉልበት የትግራይ አካል በማድረግ እንደ ጨካኝ ቅኝ ግዢዎች ልትሆኑ ቻላችሁ፡፡ ይህን በአፍህ የሚወጣ ግማታም ፈስህን ለዚያች እንደ አንተ አይነቱ ለወለደች፡፡፡፡፡ ንገራት፡፡ ወያኔ ግን ጠላት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ደጋፊዎቹም የሱ ዋነኛ አካሎች ናቸው፡፡ በመጨረሻ ላይ ውጤቱ ምን እንደሚሆን የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡ የሚታይ ነው፡፡
40
ለ 2000 አመታት ኢትዮጵያን አንዴ በሀይማኖት አንዴ በነገድ እየጠመደች ትኩረታችን እንዲበታተን ስታደርግ የዘለቀችው ግብፅ አሁን ጉዷ ፈላ ፡፡ ትኩረቱ የማይበተነዉ ትውልድ የአባይን ቧንባ እየገነባ ነው ፡፡ ክፍት ዝግት ነው ጭውቴው፡፡ ከጥቂት ማሞ ቂሎዎች በስተቀር ህዝቤ ገብቶታል፡፡ በለዉ፡ያዘው ፡አሳደው፡ስደበው ምናምን ሲሉ ጆሮውን በጥጥ ደፍኖ ግድቡን፡ባቡሩን፡መንገዱን፡ፋብሪካዎቹን፡ፓርኮቹን፡አየር ማረፊያውን፡ጤና ኬላውን፡አይቲ ፓርኩን አረ ምኑ ቅጡ….ቀን ከሌት ይገነባል፡፡ የስራ ማቆም አድማ ውጤታማ ሊሆን የሚችል ለህዝብ የቆመና ለሀገር የሚሰራ ሀላፊነት የሚሰማው መንግስት ሲኖር ብቻ ነው፡፡ በግድያና በዝርፊያ ተሰማርቶ በጪካኔ በማሸነፍ ስልጣን ላይ የወጣን ህወሀትን በስራ ማቆም አድማ እንደ መንግስት ይሰማውና የህዝብ ጥያቄን ይመልስ ዘንድ ለማድረግ መሞከር ግን ጉዳቱ በራስ ላይ ሲሆን በተለይም ከእጅ ወደ አፍ ህይዎት ላይ የቀን በቀን ስራ በተሰማራ የሀገራችን ህዝብ ላይ ጉዳት የሚያደርስ ነው፡፡ ወቅቱ የሀገሪቱ የአመት ቀለብና ለሌላም ወጪ የሚሆንን ሰብል ለማግኜት የሚታረስበት፣ የሚዘራበት፣ የሚታረምበት፣ የሚታጨድበትና የሚወቃበት ነውና እስከ ታህሳስ መጨረሻ ድረስ በህወሀት ላይ የሚደረግን የስራ ማቆም አድማ በሌላ ስራ በመተካት ከገበሬው ጋር በመቀላቀል የግብርናውን ስራ ማገዝ የሚቻልበት መንገድ መመቻቸት አለበት፡፡ ስራ ማቆም አድማ ህወሀትን ብቻ እየጎዳ ሌላውን የህዝብ ክፍል ግን በዚህም ሆነ በዚያ የሚጠቅም መሆን አለበት፡፡ በግብርና ስራ ላይ ዘመናዊ እውቀት ያላቸውም ሆኑ ሌሎች እገዛ የሚያደርጉ ሁሉ በተለይም በከፍተኛው የሀገሪት ክፍል የዝናብና የመኸር ወቅት አሁን ነውና ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ ከገበሬው ጋር በመቀላቀል መስራትና ማሰራት አለባቸው፡፡ ወጣቶችና የግብርና ባለሙያተኞች ከገበሬ ጋ በመሄድ በስራ ይቀላቀሉ ዘንድ ሀዝብ መገፋፋት ብቻ ሳይሆን ማስገደድ አለበት፡፡ ህወሃት ግን በስራ ማቆም አድማ የሀገሪት ስራ ሳይሰራ ቢቀርና ከምግብ እጥረት ጀምሮ ህዝብ ለተለያየ አደጋ ቢጋለጥ እሱ ስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ምንም ደንታ የለውም፡፡ ለ10 ሚሊዮን ህዝብ የምግብ እርዳታ እየለመኑ ነገር ግን የነሱ አኗኗር ካለፈው የተንደላቀቀና በዘረፋ ላይ ስር አየሰደደ እንደሆነ አየታየ ያለ ሌላው ወንጀላቸው ነው፡፡ በተለይም ጤፍ፣ ስንዴ፣ ግብስ፣ ሩዝ፣ ሰሊጥና የመሳሰሉት ዋነኛ የሀገር ምግቦች የሚመረቱበት ወቅት ላይ ስንሆን ይህም በጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋንና ወሎን ጨምሮ አንዳንድ የሀገሪት ክፍል በስፋት የሚካሄድበት ነው፡፡ በመሆኑም በስራ ማቆምም ሆነ በሌላ ምክንያት የገበሬው ስራ በፍፁም መስተጓጎል የለበትም፡፡ ዛሬ ካልተሰራና ነገ ካልተመረተ አመቱን ሙሉ የምንመገበው አናገኝምና አደራ ጥንቃቄ ይደረግበት፤ ትኩረትም ተሰጥቶት ከምን ጊዜም በበለጠ ገበሬው የበለጠ የሚያመርትበትን መንገድ ህዝብ ሊወያይና ስለተግባራዊነቱ ሊተባበር ይገባዋል፡፡ ከህወሃት ነፃ የሆነ የህዝብ አስተዳደር መኖር ግን አለበት፡፡ ይህም ለጊዜው በየአካባቢው ማድረግ የሚቻል ሲሆን በቅንጅት አሰራር ወረዳዊም ሆነ ቀጠናዊ ይዘት ይኖረው ዘንድ ማድረግ ይቻላል፡፡ ስራ ማቆም አድማ ህወሃትን እንጂ ህዝብን እንዳይጎዳ ከባድ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል፡፡ የኢፎርትን፣ መረትንና ማንኛውንም የህወሀትንና የትግሬን ዘራፊ ድርጅት፣ ንግድ ተቋምና የመዝረፊያ አውታር ሁሉ አየለዩ በማወቅና በማጋለጥ በዚህ ላይ አድማ ማደረግ ነው ህወሀትን በከባድ ሊጎዳው የሚችል እንጂ ለራስ ጥቅም የሚሆንን የቀን ከቀን ስራ ማቆም ግን ውጤቱ ራስን እየጎዳ ህወሀትን የሚጠቅም ነው፡፡
41
ወያኔ ሁኔታውን ለማርገብና ሰላማዊ ሂደት የያዘ ሀገራዊ ለውጥ ለጋራ ጥቅም ይመጣ ዘንድ ከፈለገ ከሁሉም በፊትና አሁኑ ባለትልቅና ሰፊ ሸለቆ ባለቤት የሆነ የተከዜ ወንዝ፡ በማንም ያልተጣሰና ምን ጊዜም ሊጣስ የማይችል በጎንደርና በትግራይ መካክል ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ድንበር መሆኑን መቀበልና ማክበር አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ግን እንኳን የአማራ ህዝብ በአንድነት ተነስቶ ቀርቶ የጎንደር ህዝብም ለብቻው ወያኔን፣ ትግሬንና የነሱ ተላላኪ የሆነን ሁሉ ትጥቅ የሚያስፈታና መብቱን በጉልበት የሚያስጠብቅ ታላቅ ብቃትና ችሎታ ያለው ታሪካዊና ጀግና ህዝብ ነው፡፡ ተከዜን ለመሻገር የማይችል ትግራይ በምንም መንገድ ከጎንደር የቦታ ባለመብትነት ሊያገኝ ቀርቶ ለመጠየቅም አይችልም፡፡ ይህን በተመለከተ የወያኔ ማንኛውም አይነት ዶሴ እንደ ቆሻሻና ብጥጣሽ ካርቶን እየታየ ሳይከፈት በአማራ ህዝብ ህይልና አንድነት ተቀዳዶ ተጥሏል፡፡ በተለይም ለትግሬ ህዝቦች በትግራይም ሆነ በያሉበት የሚኖሩ ሰላም ያገኙና እንደ ዜጋ ተከብረውና ተጠቅመው መኖር ይችሉ ዘንድ ለማድረግ አማራ እንኳ ሊጣላቸው ቢሞክር እነሱ ግን በምንም መንገድ ከአማራ ህዝብ ጋር መጣላት የለባቸውም፡፡ “በብዙ ጎናቸው አንድና ተመሳሳይ ስለሆኑ አማራ ይጠብቃቸዋል እያልን እንጂ የአማራ ጠላቶች መሆናቸውን ብናውቅ ኖሮማ ገና ድሮ ልካቸውን አሳይተናቸው አልነበር” ስለነሱ እያለ ስላለፈ ፀፀት አንዳንድ የህዝብ ክፍሎች ማሰማት መጀመር ይቅር ሊባል በማይችል ከአማራ ጋር ከተጣሉ ካለምንም ተከላካይና ተቆርቋሪ ወደፊት ትግራይም ውስጥ ጭምር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚጎዱ ነው የሚሆኑ፡፡ ወንጀለኛው ህወሃትና የሱ የወንጀል ተባባሪ የሆኑት የዘረፉትን ይዘው ሲጠፉ ነገር ግን እንደ ከብት እያዩት በሌላው ብሄረሰብ ላይ እንደ አውሬ ይሆን ዘንድ በጥላቻና በውሸት ሞልተው ያሰለጠኑት ህዝብ ነው በነሱ ሰበብ ለከባድ አደጋ የሚወድቅ፡፡ ህወሀትም ሆነ እነ አረጋዊ በርሄን ጨምሮ ሌችም ትግሬ ነን የሚሉ ሁሉ ማወቅ ያለባቸው ግን የተከዜን ወንዝ ተሻገረው በመምጣት ላለፉት 37 አመታት በጉልበት በመያዝ ኗሪዎችን አጥፍተው ሊጠቀሙበት ቢችሉም ነገር ግን ከአሁን በኋላ ከተከዜ ማዶ መጥተው ግን አንድም የጎንደር/አማራ ቦታ ባለቤትነት መብት የሚደግፍ ታሪካዊም ሆነ ህጋዊ ምክንያት እንደሌላቸው ነው፡፡ ስንጎዳዳ ኖሬን በመጨረሻ ላይ ግን በከባድ ተሸንፈው አንድም ከተከዜ ማዶ መሬት በግል ሀብትነት እንደማያገኙ ግን ከአሁኑ መረዳትና ይህን በማመን ለሁሉም ጥቅም ስለሚሆን መፍትሄ መሆን አለባቸው፡፡ ለመሆኑ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዴን ወደ ትግራይ ለመውሰድ መሞከራቸው ብቻ ሳይሆን ከጅምሩ ጀምሮ ማሰባቸው ከምን የመጣ ንቀት ነው ወይስ በእውነት ጭንቅላታቸው የዚህን ያህል የደነዘዘ ስለሆነ? ትግሬ በእውነት የዚህን ያህል ነው ያን በደንብ የሚያውቁትን ታላቅና ጥንታዊ የአማራ ህዝብ የሚመለከቱትና የሚንቁትስ? ለትግሬ ግን ጎንደሬ ለብቻው ከበቂ በላይ እንደሆነ ከድሮ ጀምሮ የሚያውቁት ሀቅ ነው፡፡ ዛሬ የወጣላቸው የሚመስል ቀን አጠቃቀሙን ባለማወቃቸው ነገ ድቅድቅ ባለ ጨለማ ይከታቸውና ይውጣቸው ዘንድ ፈልገው ከሳይጣን ጋር ተባብረው በርትተው የሚሰሩ ነው የሚመስሉ፡፡ ስለኮሎኔል ደመቀ የሚሆኑት ጉዳይ ራሳቸውን እያዋረደ ውስጣቸውን ገልቦ በእርቃን የሚያጋልጥና ከንቀትና ጨክኖ ማጥቃት ውጪ ሌላ የሚይገበቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሰውየው ጥፋት ካለበት ጥፋት ከሰራበት ቦታ መጠየቅ እንጂ በምን ምክንያት ነው ወደ ትግራይ የሚሄድ? ትግራይ ለኢትዮጲያ ማለት አሜሪካ ለአለም እንደማለት መስሏቸው ከሆነ ብዙ ጠላት ያለባት ደካማና በሽታ አስፋፊ ቆሻሻ ዝንብ እንደ ሰራተኛና ተናዳፊ ንብ ለመሆን ስትሞክር በበራሪ ወፍ፣ በጭራና በመሳሰለው ተመትታ ቦታዋ ከሆነ ከቆሻሻ የሚቀብራት መሆኑን ሊረዱ ይገባል፡፡ የነሱ ደግሞ በሀገርና በህዝብ በሽታ አስፋፈፊ የሆኑ ከዝንቦችም በጣም መጥፎና ቆሻሻ የሆኑ ናቸው፡፡ ከዛሬ 400 አመታት በፊት የነገስታትና የሊቃውንት ቦታ ከሆነ ታሪካዊና ጥንታዊ ጎንደር ላይ ሙሉ በሙሉ እጃችሁን ታነሱና ቆሻሻችሁን ጠራርጋችሁ ይዛችሁ ወደ ቦታችሁ ትሄዱ ዘንድ በከባድ ማስጠንቀቂያ እየተጠየቃችሁ ነውና ሁኔታው ሌላ አቅጣጫ ከመያዙ በፊት ልታስቡበት ይገባል፡፡ እንዲህ ዳምኖ ዳምኖ የዘነበ እንደሆን ጎርፍና ጭቃው በእናንተ ላይ እንደሚሆን እንዳትጠራጠሩ፡፡
42
ሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ በሚኖሩ ዜጎች ላይ የተፈጸመን የባሪያ ፍንገላን ዘመን የሚያስታውስ ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚያሳይ ፎቶ በማኅበራዊ ድረ-ገጽ ተሰራጭቶ አጀኢብ ጉድ ብለናል። ነገሩ ትናንትን እየረሳን ዛሬ ለሚያጋጥመን ነገር አዲስ እየሆንን ጉድ ጉድ ለምንለው ለእኛ ነው እንጂ አዲስነቱ ለወያኔ ከበረሃ ጀምሮ አብሮት የኖረ ተግባሩ ነው። አይደለም ሥልጣኑን ሊነጥቁት በተቃውሞ የተሰለፉ፣ እኩይ ድርጊቱን እያጋለጡ ማንነቱን ፀሐይ የሚያሞቁ፣ ሃሳብ ዕቅዱን እየተቃወሙ ጉዞውን የሚያደናቅፉ ቀርቶ፤ የህወሓት አባል ሆነው ስህተት የጠቆሙ፣ የዓላማቸውን መስመር መሳት የገለጹ፣ የመሪዎቹን እኩይ ተግባር የነቀፉ ወዘተ ምን እንደተፈጸመባቸው የዓይን ምስክር የሆኑ ሰዎች ሲናገሩ ሰምተናል፣ ጽፈው አንብበናል። ባዶ ምንትስ ይባሉ በነበሩት እስር ቤቶች በውልደታቸው ትግሬ፣ በድርጅታቸው ህወሓት የነበሩ ዜጎች ሳይቀሩ ምን አይነት ኢሰብዓዊ ድርጊት እንደተፈጸመባቸው እነ ገብረመድህን አርኣያ ደጋግመው የነገሩን ነው። ዛሬም በተለያየ የሥልጣን ስም ተቀምጠው አረመኔያዊውን ድርጊት የሚፈጽሙ፣ የሚያስፈጽሙት እነዛ የበረሀው ሲዖል እስር ቤቶች ኃላፊዎች የነበሩቱ ናቸው። ለሥልጣናቸው የሚያሰጋ፣ ያሰቡ ያቀዱትን ተፈጻሚ እንዳያደርጉ እንቅፋት የሚሆን፣ ማንም ሆነ ከየትም ከማጥፋት የማይመለሱት ወያኔዎች (በተለይም አቶ መለስ) ዘር ኃይማኖት ሳይለዩ አስሮ ማሰቃየቱን፣ አፍኖ መሰወሩን፣ ገድሎ መጣሉን ብሎም ርስ በርስ ማገዳደሉን አብይ ተግባራቸው አድርገው የኖሩ ለመሆናቸው ብዙ እጅግ ብዙ መረጃዎችን መዘርዘር ይቻላል። የህወሓት ቀኝ እጅ የነበረው የደህንነቱ ሹም ክንፈ፤ የአግልግሎት ግዜው ሲያበቃ እንዴት እንዳስገደሉትና የግድያ ትዕዛዙን በፈጸመው የዋህ ታዛዥ ላይ ያደረጉትን የምናውቅ፤ በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጽሙት አረመኔያዊ ተግባር ለምን አዲስ እንደሚሆንብንና እንደሚገርመን ራሱ የሚገርም ነው። ለህይወታቸው መድኅን፣ ለሥልጣናቸው ዘብ ሆነው የኖሩ ሰዎቻቸውን ለማጥፋት የማይመለሱ ሰዎች፤ አንገዛም ባሉ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጽሙት ኢሰብዓዊ ድርጊት ሁሌም አዲስ የሚሆንብን እኛ ትናንትን በመርሳት በሽታ በመለከፋችን፤ አለያም ሞኝ የሰማ/ያየ ዕለት እንደሚባለው እየሆነብን እንጂ፤ ድርጊቱ ለወያኔ አዲስ አይደለም። እንደውም ትናንትን የመርሳት ችግራችን ከእባብ እንቁላል ርግብ አይጠበቅም የሚለውን አባባል አስረስቶን፤ የተቃውሞአችን እንዴትነትና የጩኸታችን ምንነት ከወያኔ የባህሪው ያልሆነ ነገር የምንጠብቅ ያስመስለናል። መቅረጸ ድምጽም ሆነ ምስል ያልደረሰባቸው፣ የዓይን ምስክርም ተገኝቶ ይፋ ያላደረጋቸው ብዙ እጅግ ብዙ ዘግናኝ አረመኔያዊ ድርጊቶች በወያኔ ለመፈጸማቸው በመረጃ ከተረጋገጡት ድርጊቶቹ ተነስቶ መገመት ይቻላል። እነዚህ ሰዎች ለሥልጣን የበቁት የመረጃ ማስተላለፊያው ጥበብ እንዲህ ባለልተስፋፋበትና ባልተራቀቀበት ዘመን ቢሆን፤ ምን ያደርጉ ነበር ብላችሁ አስባችሁ ታውቃላችሁ። የሚሠሩት ብቻ ሳይሆን በር ዘግተው በምስጢር የሚነጋገሩት ድምጽ ከምስል እየሾለከ ለዓለም ህዝብ ዓይንና ጆሮ ሲበቃ የማያስደነግጣቸው፣ የማያሳፍራቸውና የማያስፈራቸው (ለነገሩ ማንን ሰው ብለው) ወያኔዎች በድብቅ የሚሠሩት ሁሉ ተደብቆ የሚቀር ቢሆን፤ የአረመኔነታቸው መጠን፣ የክፋታቸው ደረጃ፣ የአገዛዛቸው ግዞት እስከምን ይደርስ እንደነበር መገመት አይገድም። ጎምቱ ጋዜጠኞች ውሻ ሰው ነከሰ ዜና አይሆንም፤ ሰው ውሻ ቢነክስ ግን ትልቅ ዜና ነው ይላሉ። የአባባሉ ምንነት ግልጽ ነው። ውሻ ሰው መንከሱ የተፈጥሮው፣ የባህሪው፣ የሚጠበቅበት ተግባሩም ስለሆነ ነው ዜና የማይሆነው። ሰው ግን ውሻ ቢነክስ ያልተለመደ ብቻ ሳይሆን የማይጠበቅና የማይገመት አዲስ አስገራሚ ክስተት በመሆኑ ነው ትልቅ ዜና የሚሆነው። ወያኔም ማሰሩ፣ መግደሉ፣ ማሰቃየቱ፣ መዋሸቱ፣ ማታለሉ፣ ሰው በሀሰት መወንጀሉ ወዘተ ለሥልጣን የበቃበትና ሀያ አራት ዓመታትም ለመግዛት የቻለበት የተፈጥሮ ባህሪይው እና ተግባሩ በመሆኑ፤ በዚህ መልክ የሚፈጽማቸው ድርጊቶች ለጋዜጠኞች ዜና ሊሆኑ ቢችሉ እንኳን፤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን አዲስ ክስተት የሆኑ ያህል ሊያስገርሙን፣ ሊያስደንቁንም ሆነ ሊያስደነግጡን አይገባም ነበር። ምነው ቢሉ እየረሳናቸው ካልሆነ በቀር አብረውን ያሉ ናቸውና። ይልቁንስ ከወያኔ አንጻር ለመገናኝ ብዙኀን ትልቅ ዜና ሊሆን ከኢትዮጵያውያን አልፎ የኢትዮጵያን ጉዳይ (ለራሳቸውም ዓላማም ሆነ ለህዝቡ ጥቅም ሲሉ) በቅርብ ለሚከታተሉ ዓለም አቀፍ ግለሰቦች ቡድኖችና መንግሥትታ አስገራሚ ክስተት ሊሆን የሚችለው። • ሀያ አራት ዓመት የተጓዝንበት መንገድ ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ እየወሰደን እንዳልሆነ ስለተገነዘብን መሰረታዊ ለውጥ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል ቢባል፤ • ለዘመናት አብረውን የዘለቁ ሀገራዊ ችግሮችን እየቆፈሩ አዳዲስ ልዩነቶችን መፍጠር የዛሬ መንገዳችንንም ሆነ የነገ ግባችንን ከማሰናከሉም በላይ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ለማቆየት አስጋቸሪ የሚያደርጉ በመሆናቸው በእርቅ እልባት ሰጥቶ ሀገራዊ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበናል ቢባል፤ • የገደለ ያስገደለ፣ የሰረቀ የተባበረ፣ በህዝብ ሀብት የከበረ፣ ከሕግ በላይ ያደረ፣ ወዘተ ለፍትህ ቀርቦ የሕግ የበላይነትን በተግባር ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ርምጃዎች መታየት ቢጀመሩ፣ • የመገናኛ ብዙኀን ሠራተኞች አፋሽ አጎንባሽ መሆናቸው ቀርቶ እውነትን አነፍናፊ፣ የባለሥልጣናትን ፊት እያዩና ትንፋሽ እያዳመጡ የሚሠሩ ሳይሆን የሙያቸውን ነጻነት አክብረው ለህሊናቸው ታማኝ ሆነው መሥራት የሚችሉበትን አሠራር ተግባራዊ የማድረግ ጅምር ቢታይ፤ • ክልሎች በሕገመንግሥቱ የሰፈረው ሙሉ ነጻነታቸው ተጠብቆ ከህወሓት የሞግዚት አስተዳደር ተላቀው ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸውን በተግባር የሚያረጋግጥ ጅማሮ ቢታይ፤ • አባልም ሆነ አጋር የሚባሉት በህወሓት ተፈጥረው በህወሓት የሚዘወሩት ድርጅቶች የአገልጋይነት ዘመናቸውን ፈጽመዋል ተብሎ፤ በራሳቸው መቆም የሚያስችላቸው እንቅስቃሴ ቢጀመር። • በድርጅት ታጥሮ በታማኝነት ተወስኖ ሀገር መምራት እንደማይቻል የሀያ አራት ዓመት ልምዳችን አስተምሮናል፣ ስለሆነም ከዚህ በኋላ ሀገር መምራት በእውቀትና ሁሉን አሳታፊ በማድረግ መሆን እንዳለበት ተገንዝበናል ተብሎ፤ ይህንኑ ገቢራዊ ማድረግ የሚያስችል ተግባራዊ ርምጃ ቢታይ። ሌላም ሌላም ተመሳሳይ ነገር ከወያኔ ሰፈር ቢታይ ቢሰማ ትልቅ አስገራሚና ማራኪ ድንቅ ዜና ይሆናል። ከዚህ ውጪ መልካም አስተዳደር የፍትህ መጓደል እያሉ ማላዘንም ሆነ ይቅርታ እንጠይቃለን ማለት ሸብረክ ያሉ መስሎ ግዜ መግዣ የወያኔ የባህሪው ተግባር ነውና ሊደንቀን አይገባም። ነገር ግን ወያኔ ያልፈጠረበትን በምክርም በመከራም ሊቀበለው ያልቻለውን ይህን ቅዱስ ተግባር በምን ተዓምር ፈጽሞት ይህ እውነት ሆኖ ለመስማት እንበቃለን! አይታሰብም። ወያኔዎች ይህን ለማድረግ እንደገና መፈጠር ይኖርባቸዋል። እኛስ ትናንትን እየረሳን በየግዜው የሚገጥሙንን የወያኔን የባህርይ ድርጊቶች እንደ አዲስ ከማየት ለመላቀቅ እና ትግሉን በምሬትና በወኔ ለማጥበቅ እንደገና መፈጠር ይጠይቀን ይሆን? ትናትን እየረሱ የዕለት የዕለቱን አዲስ እያደረጉ መጮኹ፤ በትግሉ ላይ ትልቅ አሉታዊ ተጽዕኖ ያለው ለመሆኑ አጠያያቂ አይደለም። የበደል ሸክሙ የሚከብደን፣ የጥቃቱ ምሬት የሚመረን፣አንባገነናዊ አገዛዙ የሚያንገሸግሸን እስከ አሁን ያለውን ስናስታውስ ነው። የዛሬው ሲያስለቅሰን ሲያስቆጣን ብቻ ሳይሆን የትናንቱም ሲቆጠቁጠን ነው። የትናንቱን እየረሳን ለዛሬው አንድ ሣምንት እየጮኸን፤ ከዛም ሌላ አዲስ ነገር እስኪመጣ ይህን እየረሳን እኩል መብሰል ባለመቻላችን (ጥሬ ብስልና የአረረ) ነው ሀያ አራት ዓመት ሙሉ ትግል እንጂ ለውጥ ማስመዝገብ ቀርቶ አዳዲስ ጥቃቶችን ማስቀረት፤ ተጨማሪ ጥፋት እንዳይፈጸም ማስቆም ወያኔን ከደደቢት ህልሙ ስንዝር መግታት ያልቻልነው። እውቁ የጽሁፍ ሰው አቶ ከበደ ሚካኤል ልጆች ሆነን ባነበብነው አንድ ጽሁፋቸው፤
43
https://www.youtube.com/c/eastafricafilmproduction%20?sub_confirmation=1 "ወደማያውቁት" ሪያሊቲ ሾው የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያንን ማንነት በተጨባጭ የምናይበት በግርምት ተውጠን በውስጡ ለመኖር የምንገደድበት ከክንውኑ ጋር የምንፈተንበት ተሣታፊዎች ሲሳካላቸው የምንደሰትበት ሲያቅታቸው የምናዝንበት ከሠሜን እስከ ደቡብ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ የአገራችን ክፍሎች
44
https://www.youtube.com/c/eastafricafilmproduction%20?sub_confirmation=1  በኦዲዮ-ቪዥዋል የጥበብ ስራዎቹ የበርካታ ዓመታት ልምድ ያለው ድርጅታችን ኢስት አፍሪካ ፊልም ፕሮዳክሽን በዘርፉ ያለውን ልምድ ተጠቅሞ በአቀራረቡ ፣ በይዘቱና በዓይነቱ በአገራችን አዲስ የሆነውን እና በዓለም አቀፍ ተሞክሮ ላይ የተመሰረተውን ‹‹ወደማያውቁት›› የተሰኘ የሪያሊቲ ሾው በ
45
ውድ የዳና ድራማ ቤተሰቦች ዳና ድራማ ሲዝን 5 ክፍል 42ን በቴክኒን ችግር ምክንያት ማቅረብ ያልቻልን በመሆኑ ይቅርታ እየጠየቅን በሚቀትለው ሳምንት ክፍል 42ን የምናቀርብ መሆኑን በአክብሮች እናሳውቃለን ! መልካም እለተ ሰንበት ! dana drama season 5 episode 41 | ዳና ድራማ ሲዝን 5 ክፍል 41 https://www.youtube.com/c/eastafricafilmproduction%20?s
46
አርካንሳስ የግል ጄት የቻርተር የበረራ ዋጋ ጣይ ግሎባል ኤክስፕረስ xrs የቅንጦት ቻርተር አውሮፕላን በረራ ጣይ ግሎባል ኤክስፕረስ xrs አውሮፕላን ቻርተር ኪራይ አገልግሎት ቻርተር የግል ጄት ተክሰን ቻርተር የግል ጄት ዊስኮንሲን በመሸጥ የግል አውሮፕላን ዋዮሚንግ ቻርተር የግል አውሮፕላን ዊስኮንሲን የኮርፖሬት አውሮፕላን ሜምፊስ ቻርተር ውሻ ብቻ አየር መንገድ ፎርት ማየርስ የግል ጄት የቻርተር የበረራ ዋጋ gulfstream 5 አውሮፕላን የቻርተር gulfstream 5 የግል አውሮፕላን ቻርተር gulfstream 5 የግል አውሮፕላን የቻርተር gulfstream 5 የግል አውሮፕላን የቻርተር gulfstream g550 gulfstream g550 የቤት ውስጥ gulfstream v ባዶ እግራቸው ጀት ቻርተር የግል ጄት የቻርተር ተክሰን የቤት እንስሳት አውሮፕላኖች ወጪ የግል አውሮፕላኖች ላይ የቤት የግል አውሮፕላን ሜምፊስ ቻርተር የግል አውሮፕላን የቻርተር ተክሰን የግል አውሮፕላን ኪራይ ሜምፊስ የግል አውሮፕላን ኪራይ ተክሰን የግል ጄት የቻርተር አርካንሳስ የግል ጄት የቻርተር ኩባንያ ደላዌር የግል ጄት ቻርተር ኩባንያ ሳን ዲያጎ የግል ጄት የቻርተር ኩባንያ ዋዮሚንግ የግል ጄት የቻርተር በረራ ደላዌር የግል ጄት የቻርተር በረራ ሳን ዲያጎ የግል ጄት የቻርተር ፎርት ማየርስ የግል ጄት የቻርተር የቤት ተስማሚ ደላዌር አወጣጥ የግል ጄት ቻርተር የፍሎሪዳ አወጣጥ የግል ጄት ቻርተር የግል ጄት ቻርተር ዋጋ አሰጣጥን ሳን ዲያጎ ቴነሲ አወጣጥ የግል ጄት ቻርተር የግል ጄት የቻርተር ተመኖች ፍሎሪዳ የግል ጄት የቻርተር ተመኖች ቴነሲ የግል ጄት የቻርተር አገልግሎት ደላዌር የግል ጄት የቻርተር አገልግሎት ሳን ዲያጎ ኪራይ ዋዮሚንግ የግል አውሮፕላኖች የግል አውሮፕላን የቻርተር ዊስኮንሲን ኪራይ ሜምፊስ የግል አውሮፕላን የግል አውሮፕላን ዋዮሚንግ ይከራዩ ዊስኮንሲን የግል ጄት የቻርተር የበረራ ዋጋ የቅጂ መብት © 2018 https://www.wysluxury.com- በዚህ ድረ-ገጽ ላይ ያለው መረጃ አጠቃላይ መረጃ ዓላማ ብቻ ነው. ሁሉም አካባቢዎች በግል ይዞታ ሥር ሆነው የሚንቀሳቀሱ ናቸው. - አጠቃላይ ተጠያቂነት እና የሠራኞች ካሣ. በእርስዎ አካባቢ ውስጥ አካባቢያዊ ባለሙያ ውክልና አገልግሎት ጋር እንደተገናኙ ያግኙ! ****wysluxury.com ሳይሆን ቀጥተኛ ወይም ቀጥተኛ ያልሆነ ነው "አየር ሞደም" እና ባለቤት ወይም ማንኛውም አውሮፕላን ይሠራል ማለት አይደለም.
47
ከአዲስ አበባ አቅራቢያ የሚገኙ አርሶ አደሮችና ነዋሪዎች ተገቢ ካሳ ሳያገኙ ከይዞታቸው ሊፈናቀሉ ይችላሉ፤ በሚል ስጋት የተቃውሞ ሰልፍ እያካሄዱ ባሉበት የተማሪዎች ተቃውሞ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው፤” ሲል ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት (human rights watch) ዘገበ። በክልሉ የሚንቀሳቀሰው የተቃዋሚ ፖርቲ የኦሮሞ ፌድራላዊ ኮንግሬስ እና የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ስለ ተቃውሞዎቹ የገለጡ አንዳንድ የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች በተመሳሳይ “መንግስት ለውዝግቡ ከኃይል የጸዳ ሁነኛ እልባት ነው መሻት ያለበት፤” ይላሉ።
48
የኢህአዲግ 8ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ መስከረም 3 ቀን 2003 ዓ ም በናዝሬት ከተማ ተካሂዷል፡፡ በጉባኤው መክፈቻ ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ንግግር አሰምተዋል፡፡ የቻይና የህንድና የተለያዩ አገሮች ተወካዮችም እንግድነት ተገኝተዋል፡፡ አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ በቦታው በመገኘት፤ ለጊዜ ከፍተኛ ግምት ሊሰጥ እንደሚገባ አስታውሷል፡፡ ጉባኤውም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቀጥታ ተላልፏል፡፡ ዝርዝሩን በቦታው ተገኝቶ ካጠናከረው ዘገባ ያድምጡ፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ በመጠየቅ ያነጋገሩን የከተማዋ ነዋሪዎች በአምስቱ ዓመት መርሃ ግብር መሰረት ህዳር አንድ መጀመር የነበረበት የሞጣ-እስቴ መንገድ ግንባታ ተቀይሮ ከማህደረ ማሪያም እስከ ደብረ ታቦር እንዲሆን በመደረጉ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ እንደወጣ ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ገልጸዋል። ሆኖም የዞኑ ሃላፊ አቶ እዘዝ ዋሴ ጋዜጠኛ እናመጣለን በማለት ሲያታልሉን ቆይተው፣ ልዩ ሃይልና ፌደራል ፖሊስ በከተማዋ አሰማሩ ብለዋል። የህዝቡ ተቃዉሞ ሰላማዊና የልማት ጥያቄ ላይ ያተኮረ መሆኑን በተለይ የመጡት የልዩ ሃይል ተወካዮች የተገነዘቡ ቢሆንም ከወረዳው ባለስልጣናት የተነገራቸው ግን ሕዝቡ የመንግስት ተቋማትን እየደበደበ ነው የሚል ነው ብለዋል። ከአንድ ቀን ዉሎ በሁዋላ ግን ወጣት ልጆች ሳይቀሩ ወንድ የተባለ የከተማዋ ነዋሪ እየታፈሰ ወደ እስር ቤት መወሰዱን፣ ቃል የሰጡን ግለሰብም በሽሽት ጫካ ውስጥ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ዜናውን ያጠናቀረው አዲሱ አበበ ከመንግስት ባለስልጣናት ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ተለያዩ ቢሮዎች ስልክ ደውሎ ነበር። ስብሰባ ላይ እንዳሉ በመግለጽ እስካሁን መልስ አልሰጡም፣ እንደደረሰን እንዘግባለን።
49
የአፍሪካ ቀንድን በመታው ድርቅ ዙሪያ በተከታታይ በሚቀርቡት ዘገባዎች ከምንቃኛቸው አካባቢዎች ሪፖርተራችን ሄኖክ ሰማእግዜር ተዘዋውሮ የተመለከታቸው በደቡብ ኢትዮጵያ የቦረና ወረዳዎች ይገኙባቸዋል፡፡ ደቡብ ኢትዮጵያ ሁለት ዓይነት ገፅታዎች ያሏት መሆኑንና የክረምቱ ዝናብ በወቅቱ በጀመረባቸው ከአዋሣ ከተማ በፊትና አልፎም ስፋት ባላቸው አካባቢዎች አዝመራው ከወትሮው እንዳልቀነሰባቸው አርሶ አደሮቹ ገልፀዋል፡፡ ከብት አርቢዎችና ከፊል ከብት አርቢዎች ከሚኖሩባቸው ከአሥራ ሦስቱ የቦረና ቀበሌዎች በተለይ ዲሎ ድሬና ሞያሌ የሚባሉት አካባቢዎች የሚገኙባቸው አምስት ቀበሌዎች ከድርቁ የበረታ ችግር ግንባር ቀደም ተጎጂዎች ናቸው፡፡
50
አፍሪካ ኩዊን መኪና ክራይና ቱር በ2002 ዓም የመሰረተ የግል ካምፓኒ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በመኪና ክራይና በማስጎብኘ ስራ ላይ ተስማርቶ ይገኛል:: ካምፓኒያችን በዘርፉ የረጅም ጊዜ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚመራ ነው:: እርሶም ክእኛ ጋር አብረውን ለመስራት ፈቃደኛ ክሆኑ በደስታ የምንቀበልዎ መሆኑን እናሳውቃለን::
51
ያስተውሉ፡ ይህንን ዶኩመንት ለመተርጎም እርዳታ የሚፈልጉ ከሆነ፡ የጉዳዮን ሰራተኛ ይጠይቁ ወይም በሰልክ ቁጥር 1-844-217-3547 ይደውሉ። — amharic
52
matthew 13:15 በዓይናቸው እንዳያዩ፥ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል የሚል የኢሳይያስ ትንቢት በእነርሱ ይፈጸማል። amharic(i) 15 በዓይናቸው እንዳያዩ፥ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል የሚል የኢሳይያስ ትንቢት በእነርሱ ይፈጸማል።
53
ጉዳዩን በዋነኛነት የሚያንቀሳቅሱት ጀርመንና ፈረንሳይ ለችግሩ መከላከያ ይሆናሉ ያሏቸውን እቅዶች አዘጋጅተዋል ። በዚህ እቅድ ውስጥ በጀታቸውን መቆጣጠር የሚሳናቸው የዩሮ ተጠቃሚ አባል ሃገራት ወዲያውኑ ማዕቀብ እንዲጣልባቸው የሚጠይቀው ክፍል ይገኝበታል ። ይህ ተግባራዊ የሚሆነውም የእያንዳንዱ ሃገር የበጀት ጉድለት በህጉ ከተቀመጠው ከአጠቃላዩ የሃገር ውስጥ ምርት ከ 3 ከመቶ ሲበልጥ ነው ። ይህን ህግ የሚተላለፉ አባል ሃገራት ወደ አውሮፓ ህብረት ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ጀርመን አስቀድማ ያቀረበችውን ሃሳብ አንስታ በምትኩ ፍርድ ቤቱ አባል ሃገራት በብሔራዊ ህገ መንግስታቸው ውስጥ ማካተት የሚገባቸውን የተስተካከለ በጀት ደንቦች ከአዲሱ ወይም ከተሻሻለው የአውሮፓ ህብረት ውል ጋር የተጣጣመ መሆን አለመሆኑን የመፈተሽ ሥልጣን እንዲሰጠው ተደርጓል ።ለዩሮ የዕዳ ቀውስ በመፍትሄነት የቀረቡት እቅዶችና የአንዳንዶቹ ጥቅምና ጉዳት የዛሬው አውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅታችን ትኩረት ነው ። አፍሪቃዉያን ሴቶች በከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣን ላይ ተሳትፎአቸዉ ምን ይመስላል? በአህጉሪቱ ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ ሴቶች የከፍተኛ ስልጣናት መንበርን ሲረከቡ ይስተዋላል። በዓለማችን እጅግ ከፍተኛ ሐብት አላቸዉ ከሚባሉ ሰዎች መካከል አፍሪቃዉያን ሴቶች ይገኙበታል። የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ የአገርን ጥቅም እና ህልውና በሚጎዳ አደገኛ እና ሕገወጥ የባሕር ንግድ ላይ ተሰማርቶ እንደነበር አንድ የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማት ገለፁ። «ራይድ» የተባለዉ የታክሲ አገልግሎት ድርጅት የስም ማጥፋት ዘመቻ እና ጥቃት ደርሶብኛል በማለት ወቀሰ። የመለያ ቁጥር 3 ባለንብረቶች ህጋዊ ባልሆነ ደረሰኝ በትራፊክ ፖሊሶች እየተቀጣን ነው ሲሉም ተናገሩ።
54
እቶም ኣብ ነሓሰ 2013 ኣብ ኣዲስ ኣባባ ኣኼባ ዘካየዱ ፖለቲካዊ ሓይልታት ኤርትራ ካብ 31 ጥሪ ክሳብ 04 ለካቲት 2014 ኣብ ዘሎ ግዝያት እንደገና ካልኣይ ኣኼባ ኣካይዶም። እዞም ኩሎም ኣብዚ ኣኼባ’ዚ ዝተሳተፉ ውድባትን ሰልፍታትን ኣብ ቀዳማይ ኣኼባኦም ንህልዊ ኩነታት ሃገርናን ዞባናን ህዝቢ ኤርትራን ፖለቲካዊ ሓይልታቱን ኣብ ኤርትራ ሰላምን ደሞክራስን ንምስፋን ኣብ ዘካይድዎ ዘለው ቃልሲ ብሓፈሻ ብፍላይ ከኣ ሓያልን ድኹምን ጎኒ ደምበ ተቓውሞ ኤርትራ ንዝገምገሞም ብደረጃ ኣቦ መንበራት ቀጻልነት ረኺቡ ናብ ሓደ መዕለቢ ዝበጽሓሉ ካልኣይ መድረኽ ክእቶ ብዝተወሰነ መሰረት እዩ እዚ ኣኼባ’ዚ ዝተሰላሰለ። ካልኣይ ኣኼባ መድረኽ ምምኽኻር ፖለቲካዊ ሓይልታት ኤርትራ ነቶም ካብ ቀዳማይ ኣኼባ ብደረጃ ኣቦ መንበራት ወይ ተወከልቶም ቀጻልነት ረኺቦም ኣብ ሓደ መዕለቢ ካብ ዝበጽሑዎም ናይ ድኹማት ጎንታት መጽናዕታዊ ጽሑፋትን ናብ ሓደ ናይ ሓባር ጽላል ንምብጻሕ ክሕግዙ ዝኽእሉ ፍሉይ ትኹረት ዝተዋህቦም ነጥብታትን መፍትሕታትን ንምይይጣትን ኣብ ስምምዕ ንምብጻሕን ኣብ መደምደምታ ኸኣ እንታይ ክንገብር ከምዘሎና ንምርኣይን ነበረ። በዚ መስረት ኣኼባ ነዞም ዝስዕቡ ክልተ ኣጀንዳታት ማእከል ገይሩ ተመያይጠ፡- ኣኼባ ነቶም ዘቐረብዎ ሰነዳት በብሓደ ብምርኣይን ብምይያጥን ኣድላዪ ምምሕያሻት ብምግባርን ኣብ ክሊ ዝተሓተ መደብ ዕዮ ሓቢሮም ከቃልስዎን ከሳማምዕዎን ኣብ ሓደ ዝሰመረ ናይ ሓባር ናይ ፖለቲካዊ ሓይልታት ጽላል ከብጽሕዎን ጽገማቱ ኣብ ምፍታሕ ክሕግዝዎን ኣብ ምዕዋት ካልኣይ ሃገራዊ ጉባኤ ኤርትራዊ ሃገራዊ ባይቶ ንደሞክራስያዊ ለውጢ ናቱ ኣገዳሲ ተራ ክጻወት ከምዘኽእል እውን ኣረጋጊጹ። ካብዚ ሓቅታት’ዚ ብምብጋስን ህዝብን ሃገርን ኤርትራ ካብ ገባቲ /ዲክተታርያዊ ስርዓት ህግደፍ ዝገጥሞዎ ዘሎው ሓደጋታትን ህጹጽነት ናይዚ መድረኽ ዝጠልቦ ዘሎ ቃልሲን ሓድነትን ኣብ ጸብጻብ ብምእታው መድረኽ ምምኽኻር ፖለቲካዊ ሓይልታት ኤርትራ ኣብዞም ዝስዕቡ ስምምዓት /ምርድዳኣት/ በጺሑ። ኣብ መደምደምታ መድረኽ ምምኽኻር ፖለቲካዊ ሓይልታት ኤርትራ ህዝብን መንግስትን ኢትዮጵያ ካብመጀመርያ ኣትሒዞም ክሳብ ሕጂ ኣኼባ ብዓወት ክዛዘም ክገብሩልና ንዝጽንሑ ኩሉ ሽነኻዊ ምድግጋፍ ልዑል ምስጋናኡ ኣቕሪቡ።
55
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጊዶ ቬስተርቬለ ከብዙ ክርክር በኋላ የተዘጋጀውን ሰነድ ትናንት በይፋ አቅርበዋል። ብዙዎቹ የሀገሪቱ ሚንስቴሮች ጽንሰ-ሀሳቡ በተረቀቀበት ስራ ላይ ተሳታፊዎች ነበሩ። በአዲሱ የአፍሪቃ መርሀግብር ዝግጅት ላይ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ጠበብት ምክር በማካፈል የበኩላቸውን አስተዋጽዖ አበርክተዋል። በጥምሩ መንግስት ምስረታ ጊዜ እንደሚወጣ የተነገረለት አዲሱ የጀርመን የአፍሪቃ ጽንሰ-ሀሳብ ዝግጅት ከአንድ ዓመት በላይ የፈጀ ሲሆን፡ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ፡ የትምህርት እና የተፈጥሮ አካባቢ፡ እንዲሁም፡ የኤኮኖሚ ትብብር ሚንስቴሮች በጋራ ያረቀቁት ሰነድ ነው። በዚሁ ሀያ ስምንት ገጾች በያዘው እና የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጊዶ ቬስተርቬለ ትናንት በይፋ ባቀረቡበት ሰነድ ውስጥ አፍሪቃን በጠቅላላ የሚመለከት አዲስ የፖለቲካ መርሀግብር ተቀይሶዋል። « ከጎረቤታችን አህጉር ጋ ባለን ግንኙነት ላይ አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት እንፈልጋለን። እያደገ የመጣው የአፍሪቃ ትርጓሜ እና አፍሪቃም ለራስዋ ጉዳዮች በይበልጥ ኃላፊነቱን እየወሰደች የመጣችበት ሁኔታ ፍሬ እንዲያስገኝ እንፈልጋለን። » በሰሜን አፍሪቃ የተነቃቃው ዓብዮት ለመላው አህጉር ላይ ተጽዕኖ እንዳለው የገለጹት ቬስተርቬለ፡ በአፍሪቃ የሚኖረው ህዝብም ልክ በሌላው ዓለም እንደሚታየው ሁሉ ነጻነት፡ የህግ የበላይነት፡ ዴሞክራሲ እና የሰብዓዊ መብት ጥሙን ማርካት እንደሚፈልግ ማሳየቱን አረጋግጦዋል። በመሆኑም፡ ይላሉ ቬስተርቬለ፡ ጀርመን አፍሪቃውያን መንግስታት ሰላማዊ እና ነጻ የወደፊት ዕድል ለመፍጠር የጀመሩትን ጉዞ ለማበረታት ዝግጁ ናት። « አፍሪቃን ለወዳጅነት እንጋብዛለን፤ በእኩልነት ላይ ለተመሰረተ ወዳጅነት። ዘመን ካለፈበት የርዳታ ሰጪና ተቀባይነት ግንኙነት ባለፍ። የእኛ ዓላማ የአፍሪቃውያኑን ጥረት እና ኃላፊነትን ለመሸከም የሚወስዱትን ርምጃ ማበረታታት ነው። በእኩዮች መካከል የሚፈጠር በራስ መተማመን ላይ የተመሰረተ የእኩልነት እንዲኖር እንፈልጋለን። ዋናው መነሻችን፡ በእኩልነት ላይ ለተመሰረተ ወዳጅነት የተሰኘው ነው። ምክንያቱም የአህጉሮቻችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ከናንተ ጋ ባንድነት በእኩልነት ላይ በተመሰረት ወዳጅነት መገንባት እንፈልጋለንና። » ቻይና እና ህንድን የመሳሰሉ ሌሎች ሀገሮችም ከአፍሪቃ ጋ ግንኙነታቸውን አጠናክረው። ጀርመን በአፍሪቃ ጊዚያዊ ስኬቶችን የማስመዝገብ ዓላማ አላቸው በምትላቸው በነዚህ ሁለት ሀገሮች አንጻር ዘላቂነት የሚኖረው እና አፍሪቃውያንንም ጭምር ተጠቃሚ የሚያደርግ አጋርነትን መፍጠር ነው የምትፈልገው። እና የጀርመን ኤኮኖሚንም እና የአፍሪቃን ህዝብ የሚጠቅም አንድ የኃይል ምንጭ እና የጦሬ አላባ አጋርነትን ማቋቋም ፍላጎት እንዳላት የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ቬስተርቬለ አስረድተዋል። « ዓላማችን በመካከላችን ሊኖር የሚችለውን ትብብር በወዳጅነት ላይ በተመሰረተ ዘዴ እንድንጠቀምበት ነው። ይህ በአፍሪቃ ለሚኖረው ህዝብ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፡ መረሳት የሌለበትም ለራሳችንም ብልጽግና እና ጥቅምም የሚበጅ መሆኑ ነው። » በዚሁ ነጥብም ላይ ነው አሁን ጀርመናውያኑ የተቃውሞ ፓርቲዎች በአዲሱ የመንግስቱ የአፍሪቃ ጽንሰ-ሀሳብ ላይ ነቀፌታቸውን እየሰነዘሩ ያሉት። በፌዴራዊው ምክር ቤት፡ ቡንድስታግ የግራ ፓርቲ አንጃ እንደራሴ ኒየማ ሞፋሳት እንዳኣኣስረዱት፡ የጀርመን መንግስት የአፍሪቃን አህጉር እንደ ጥሬ አላባ መጋዘን በመመልከት፡ ለዘብተኛውን የገበያ መርህ ስር የተጀመረውን የልማት ትብብር የሚጎዳ ነው። የጀርመውያኑ የአፍሪቃ ጽንሰ-ሀሳብ በተለይ የወደፊቱን የጀርመንን ጥቅም ብቻ እንዲያስጠብቅ ሆኖ የተዘጋጀ በመሆኑ የአረንጓዴዎቹ ፓርቲ መሪ ክላውዲያ ሮትም ቅር እንደተሰኙ ገልጸዋል። አዲሱ የአፍሪቃ ጽንሰ-ሀሳብ በጋራለአፍሪቃ በሚል መጠሪያ ከሚታወቀው መንግስታዊ ካልሆነው ድርጅትም ሂስ ተሰንዝሮበታል።
56
” አልተነገረንም እንዳትሉ ነው” ሲሉ ነው ክፍተኛ የገንዘብና የውጭ ምንዛሬ ክምችት ያላቸውን ያሳሰቡትና የመከሩት። እጅግ ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ከፊት ለፊት መኖሩን በመጠቆም፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ምንዛሬ ወደ አገር እንደሚገባ በማመላከት በግል ዶላር ያከማቹ ወደ ባንኮች በመሄድ ራሳቸውን ከኪሳራ እንዲጠብቁ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ያስጠነቀቁት። የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ከሸኙ በሁዋላ በደቂቃዎች ልዩነት በቀጥታ ባስተላለፉት የምስጋና መልዕክት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለት ጉዳዮች ላይ አጠንክረው ተናገረዋል። በሶማሌ ክልልና በኦሮሚያ ክልል ድንበሮች ላይ በርካታ ዜጎች በተደጋጋሚ ህይወታቸው ማለፉን፣ በደቡብና ቦታውን በስም ሳይጠሩ ሰሜን ኢትዮጵያ ሲሉ በገለጹዋቸው አካባቢዎች የመከላከያ ሰራዊት ህገ መንግስታዊ አደራውን በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲወጣ አዘዋል። ሃዘን በተሞላበት ስሜት ትዕዛዝ ያስተላለፉት ዶክተር አብይ ከትዕዛዙ ጎን ለጎን ይህ በጥቂት ሰዎች ክብሪትና ቤንዚን አቀባይነት የሚከናወነው ደም አፋሳሽ ግጭት እንዲቆም ደም የጠማቸው አካላት መጠቀሚያ የሚሆኑ ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ መክረዋል። ዘክረዋል። ለምነዋል። ሁሌም እንደሚሉት ይህ አካሄድ ስለማይጠቅም የሚጠቅመንን የሰላምና የፍቅር መንገድ መከተል እንደሚያዋጣ ወትውተዋል። የከፍተኛ የዲፕሎማሲያዊ ድል ብስራት ለ”ሕዝባቸው” ካሰሙና “ሕዝባቸውን” በምስጋና ካከበሩ በሁዋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ከፋፍሎ ማጣላት የኖርንበት ነው። አልጠቀመንም” ሲሉ ይህ አብሮ ለዘመናት የኖረን ህዝብ እሳትና ቤንዚን እያቀበሉ የሚያጋድሉትን ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ ለምነዋል። ስለማይጠም ” ተውት” ሲሉም ተማጽነዋል። ” ለመግደል አንደመርም” ሲሉ በሜሊኒየም አዳራሽ የተናገሩት ዶክተር አብይ ይህ ክፉ አካሄድ እንዲቆም መማጸን የጀመሩት ወደ ሃላፊነት ከመጡ ማግስት ጀምሮ መሆኑ አይዘነጋም። ከዚህ ሁሉ ውትወታ በሁዋላ የመከላከያ ሰራዊት አገራዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ሲያዙ የተለመደው ፈገግታ አይታይባቸውም ነበር። ያም ሆኖ የመከላከያ ሰራዊት ንጹሃን ሳይሞቱና ሳይቆስሉ፣ እጅግ ሙያዊ ጥበብ በተሞላበት፣ በስልትና በማስተዋል የምረጋጋቱን ስራ እንዲሰራ አብዝተው አሳስበዋል። የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል በተደጋጋሚ እየወሰደ ያለው ጥቃት፣ በመተማ አቅጣጫ የሰሜን ሱዳን ወታደሮች የሚከፍቱት ግጭት፣ በጌዲዮ ህዝብ ላይ የደረሰው መፈናቀል፣ በሲዳማ የተከሰተው ከፍተኛ የርስ በርስ ግጭት ቀና አሳቢ ዜጎችን ያሳዘነ፣ ያስኮረፈና እልህ ውስጥ የከተተ ክስተት ሲሆን፣ አብዛኞች የህግ የበላይነት እንዲከበር ጥያቄ ያቀረቡበት ጉዳይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘው ያነሱት የውጭ ምንዛሬ ጉዳይን ነው። በከፍተኛ ደረጃ የውጭ ምንዛሬ ስለሚገባ በግል ቤታቸው የውጭ ምንዛሬ ያከማቹ በቀጥታ ወደ ባንኮች በመሄድ እንዲመነዝሩ መክረዋል። ” አልተነገረንም እንዳትሉ” ሲሉ እንዳስታወቁት አሁን ዋጋው እየረከሰ ያለው ዶላር ይበልጥ እንደሚረክስ በማሰብ ወደ ባንክ እንዲሄዱና እንዲመነዝሩ ዶላሩ ላላቸው ሲመክሩ አይይዘውም ከፍተኛ የገንዘብ ክምችት ያላቸውም በተመሳሳይ ብራቸውን ወደ ባንክ እንዲያዘዋውሩ መክረዋል። በቅርቡ ይህንን የገንዘብ ክምችት የሚያጠራ ኦፕሬሽን እንደሚካሄድ ያስታወቁት ጠቅላይ ሚስትር አብይ፣ ክፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ይዘው ወደ ባንክ የሚመጡ ክፍሎችን ባንኮች ያለምንም ማንገራገር እንዲያስተናግዷቸው አዘዋል። ይጀመራል ስላሉት ኦፕሬሽን ግን ዝርዝር ማብራሪያ አልሰጡም። ጠቅላይ ሚኒስሩ እግረ መንገዳቸውን መሐሙድ አህመድንና አሊ ቢራን ህመማቸውን ችለው ላበረከቱት ኢላማውን የመታ ድንቅ ስራ ስም ጠርተው ከልብ አመስግነዋል። አያይዘውም አርቲስቶች ሙያቸውንና ታዋቂነታቸውን ተጠቅመው ወደ ፍቅርና ሰላም የሚወስድ ተግባር ላይ እንዲያተኩሩ መክረዋል። በውቅቱ በቀጥታ ስርጭት እንደታየው አንዳንድ መዘላበድና ትርጉም የሌለው ከዝግጅቱ ጋር የማይሄዱ ሃሳቦች ከአንዳንድ አርቲስቶች መሰማቱ በርካቶችን ያበሳጨና ዓላማውን የሳተ መሆኑንን ለመገንዘብ ተችሏል። ኢትዮጵያና ኤርትራ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካው መስክ ከፍተኛ የተባለ ስምምነት ማድረጋቸውን ያስታወቁት ዶክተር አብይ፣ ሁለቱ አገራት በጸጥታ ጉዳይ አብረው ለመስራት መስማማታቸውን ይፋ አድርገዋል። ባልተለመደ ሁኔታ ደስታቸውን ሲገልጹ የታዩት ኢሳያስ በአማርኛ ቋንቋ ባደረጉት ንግግር አሁን የተጀመረውን ፍቅርና ሰላም ማንም አይቀለብሰውም ሲሉ መናገራቸው የተጀመረው የሰላም ንግግር ከድርድር አልፎ አንዱ ሌላውን የመጠበቅና የመንከባከብ ደረጃ የደረሰ መሆኑን አመላክች እንደሆነ ነው። በሃዋሳ ባደረጉት ንግግር ” አንተ ምራን፤ መሪያችን ነህ” እስከማለት የደረሱት ወዲ አፉወርቂ አድሮ ይፋ የሚሆን የሁለቱንም አገር ህዝብ የሚያስተሳስር ስምምነቶችን ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል። ይህ የዓለም ታላላቅ አገራትን አድናቆት የሳበና ያስደነቀ፣ ማንኛውም ዓይነት ድጋፍ የሚደረግለት ታሪካዊ የሰላም መንገድ የጎናጸፈርው የደስታ ስሜት የሚያንገበግባቸው ክፍሎች ይህን አንጸባራቂ ድል ለማንቋሸሽ ሲሞክሩ ይታያሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ክብሪትና ቤንዚን በማቅረብ አገሪቱ እንድትተራመስ እየሰሩ ነው። አቶ ለማ መገርሳ እንዳሉት ” በጀት የሚመድቡ ክፍሎች” ናቸው። በኢትዮጵያ ታሪክ በህዝብ ልብ ውስጥ የነገሱት፣ ምስላቸው በያንዳንዱ ቤት የተሰቀል፣ ህዝብ በልቡ ብቻ ሳይሆን በደረቱ ላይ ከፍ ያደረጋቸው፣ በቢሮውና በመኪኖቹ ውስጥ የማይለያቸው፣ ንግግሮቻቸውን ደጋግሞ እየሰማ ያከበራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህንን ህዝብ ” ሕዝቤ” ሲሉ ደጋግመው በመጥራት እምነታቸውን በየቀኑ እያጸኑ ነው። ለዚህም ይመስላል ከጀመሩት እንቅስቃሴ አንጻር፣ ከማይወዷቸው ክፍሎች ክፋት ብዛት ዜጎች የሚሰጉላቸው። የሚጸልዩላቸው። በህብረት ሆነው በጾም ጸሎት የሚያነቡላቸው። ይህንን የተረዱት ጠቅላይ ሚኒስትር በበኩላቸው ” አንድ አብይ ቢሞት መቶ ሚሊዮን አብዮች አሉ” ሲሉ ህዝባቸው እንዳይሰጋ ለማጽናናት የሞከሩት። ” የለውጥ አራማጅ ይሞታል እንጂ፣ ለውጥና የለውጥ ሃሳብ” አይሞትም ሲል የተሰሙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ደጋግመው እንዳሉት ህዝብ ከስሜት በመራቅ ከተራ ጥላቻና የጅምላ ፍረጃ ተላቆ ሁሌም የተጀመረዉ ለውጥ እንዳይጨናገፍ መትጋት ይገባዋል።
57
በአሁኑ ሰዓት የሕዝብ አልገዛም ባይነት አገሪችንን እያናወጣት ይገኛል። በየቀኑ ይህንን ያህል ቁጥር ሰዉ በዚህን አካባቢ በአጋዚ፣ በመከላከያ ሠራዊት ወይም በፌዴራል ፖሊስ ተገደለ የሚል ዜና መስማት እየተለመደ መጥቷል። የዜጎች ሕይወት እንዲሁ እንደዋዛ ሲቀጠፍ ከመስማት በላይ በእጅጉ የሚያሳዝን ነገር የለም። ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነዉ ደግሞ በዚህ ብቻ እንደሚቆም ዋስትና የሌለን መሆኑ ላይ ነዉ። ችግሩን መፍታት እንጂ ለምን ትከፋለህ፣ ለምንስ ብሶት አንገሸገሸህ፣ ለምንስ ምሬት ዉስጥ ትገባለህ … ወዘተ በሚል መግደልና ማንገላታት ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጣ ግን ሊረዱት ይገባል። በሕዝቡ ላይ የተጫነዉ ቀንበር ሊሸከመዉ ከሚችለዉ በላይ በመሆኑ ተቃዉሞዉን ለማሰማት በአደባባይ መዉጣት ከጀመረ ሁለት ዓመታት ሊቆጠሩ ነዉ። አልገዛም ባይነት እየጎለበተ ቢሄድም ለብሶት መነሻ የሆኑትን የአንድ ብሔር የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነት፣ ሥርዓቱ የተዘፈቀበት ሥር የሰደደ ሙስና፣ የሕግ የበላይነት አለመከበር … ወዘተ አስመልክቶ ከመንግሥት በኩል አንዳችም የማሻሻያ እርምጃ የመዉሰድ ተነሳሽነት አልታየም። እንደዉም ወያኔ ይህንኑ ሥርዓት በተሻለ ብቃት ያስፈጽማሉ ተብሎ የታመነባቸዉን ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልንና ወ/ሮ ፈትለወርቅን (ሞንጆሪኖ) የሕ.ወ.አ.ት. ዋናና ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ ሾሟቸዋል። ሾልከዉ ከሚወጡ መረጃዎችና ድርጅቱ ካወጣዉ መግለጫ መረዳት እንደሚቻለዉ በዚህ እንደማራቶን በተራዘመ ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ የተከሰተዉን ችግር ስለመፍታት የዉይይት አጀንዳ ሆኖ አለመቅረቡ በራሱ ሥርዓቱን የሚዘዉሩት ሰዎች ምን ያህል ከሕዝብ ጥቅም የራቁ መሆናቸዉን ያረጋግጣል። ከሁሉም በላይ ያስደነቀኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክቶ በትናንታዉ ዕለት (dec. 18, 2017) ለሕዝብ ያስተላለፉት መልእክት ነዉ። በመግለጫቸዉ ላይ ከመንግሥት ቁጥጥር በላይ የሆነ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑን አልካዱም። እንዲሁም “የጸጥታ አስከባሪ” ኃይሎች በሚወስዱት እርምጃ በርካታ ሰዎች መገደላቸዉንና መቁሰላቸዉን አምነዋል። ሆኖም ግን ከንግግራቸዉ ዉስጥ ሕዝቡና ተማሪዎች ስለሚያነሷቸዉ ጥያቄዎችና ስለመፍትሔዎቻቸዉ ያነሡት አንድም ነጥብ የለም። እንደዉም የአካባቢዉን ሰላም ለማስጠበቅ በሚል ሰበብ “የጸጥታ ኃይሎች” ተግባራቸዉን እንደሚቀጥሉ ነዉ ያሰመሩበት። በተጨማሪም “የሐሰትና የተጋነነ መረጃ” ያሰራጫሉ በሚሏቸዉ የሕዝብና የግል ሚዲያዎች ላይ መንግሥት እርምጃ እንደሚወሰድ ለማስፈራራት ሙከራ አድርገዋል። ለጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ መነሻ የሆነዉ በቅርቡ እንዳዲስ ያገረሸዉ በሱማሌና በኦሮምያ ክልል የተከሰተዉ ግጭት እንዲሁም በአማራ፣ በኦሮምያና ትግራይ ዉስጥ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች የተከሰቱት ብሔር ተኮር ግጭቶች እንደሆኑ መረዳት ይቻላል። በጨለንቆ ከ18 ሰዎች በላይ ለመገደልና ለበርካቶች መቁሰል ምክንያት የሆነዉ አንድ የኦሮሞ ተወላጅ በሶማሌ ልዩ ኃይል በመገደሉ ምክንያት ለተቃዉሞ በወጣዉ ሰላማዊ ሕዝብ ላይ እንደሆነ በተለያየ የዜና ማሰራጫዎች ተዘግቧል። በወቅቱ ሕዝቡ ተቃዉሞዉን በሰላማዊ መንገድ ከማሰማት ዉጭ የፈጸመዉ ሕገ ወጥ ተግባር ሳይኖር ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የጸጥታ ኃይላት” የሚሏቸዉ የመከላከያ ወይም የአጋዚ ሠራዊት በሕዝቡ ላይ ተኩስ መክፈታቸዉ ከፍተኛ ዉግዘት አስከትሏል። የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳም ድርጊቱን ከማዉገዝ ባሻገር የመከላከያ ሠራዊት አባላት በማን ትእዛዝ እንደገቡና ለምን ድርጊቱን እንደፈጸሙ አስቀድመዉ አለማወቃቸዉን በማዉሳት ይህንን ትእዛዝ የሰጡት አካላት በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል። የክልሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊም ይህንኑ አጠናክረዋል። በርግጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸዉ ላይ የጨለንቆን ጉዳይ ጨምሮ “የጸጥታ ኃይሎች” ተልእኮዋቸዉን በመፈጸም ላይ እንዳሉ ያጋጠሙ ክፍተቶች ካሉ መንግሥት አሠራሩን ተከትሎ እንደሚያጣራና ለሕዝብ እንደሚያሳዉቁ ገልጸዋል። ነጥቡ ያለዉ ግን ከሕገ መንግሥቱ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰነዘሩት አሳብ ምን ያህል ያስኬዳል የሚለዉ ላይ ነዉ። በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 52 (2) (ሰ) መሠረት የክልሉን ሰላምና ጸጥታ የማስጠበቅ ኃላፊነት የተጣለዉ በክልሉ ላይ ነዉ። ሆኖም ግን ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ የጸጥታ መደፍረስ በሚያጋጥምበት ጊዜ የክልሉ መሥተዳድር ጥያቄ በማቅረብ የፌዴራል መንግሥት የሀገሪቱን የመከላከያ ኃይል እንዲሰማራ ሊያደርግ እንደሚችል በአንቀጽ 51 ንዑስ ቁጥር 14 ላይ ተደንግጓል። እነዚህ ድንጋጌዎች በግልጽ እንደሚያስቀምጡት የክልል መሥተዳድሮች ጥያቄ ካላቀረቡ በስተቀር የመከላከያ ሠራዊት ክልል ዉስጥ በመግባት ማናቸዉንም የኃይል ተግባር የመፈጸም ሥልጣን አይኖረዉም ማለት ነዉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ የመከላከያ ሠራዊት ጨለንቆ ገብቶ የማረጋጋት ሥራ እንዲሠራ የኦሮምያ ክልል የፊዴራል መንግሥትን እንዳልጠየቁ ራሳቸዉ ፕሬዝዳንቱ ስለገለጹ የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌ በመተላለፍ መከላከያ ሠራዊቱን ወደጨለንቆ ያሰማራዉ ግለሰብ ወይም አካል ሕገ ወጥ ተግባር ስለመፈጸሙ የሚያጠራጥር አይደለም ማለት ነዉ። በዚህም መሠረት ትእዛዙን የሰጠዉ አካልና እንዳግባብነቱ እርምጃዉን የወሰዱት የሠራዊት አባላት ለደረሰዉ የሕይወት መጥፋትና የመቁሰል አደጋ ሙሉ ለሙሉ ተጠያቂ ከመሆን አይድኑም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን በመሸፋፈን “ … ተልኳቸዉን በመፈጸም ላይ እንዳሉ ያጋጠሙ ክፍተቶች ካሉ … ” በሚል ሠራዊቱ ወደ ክልሉ የመግባት ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት በማለፍ እንደተለመደዉ የተወሰደዉ የኃይል እርምጃ ተመጣጣኝ ነበር/አይደለም ወደሚል የማጣራት ሒደት እንደሚኬድ አመላክተዋል። ይህ አካኼድ በዋንኛነት መጠየቅ ያለበትን አካል/ግለሰብ በማዳን ወደሌሎች የማላከክና የተፈጸመዉን የጥፋት ደረጃ ዝቅ የሚያደረግ በመሆኑ በፍጹም ተቀባይነት የለዉም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕገ መንግሥት ተጥሶና የክልሉ መብት ተደፍሮ የዜጎች ሕይወት በመጥፋቱና ለብዙዎች መቁሰል በርግጥ የሚቆረቆሩ ከሆነ የማጣራት ሔደቱ መጀመር ያለበት ካለክልሉ ጥያቄ መከላከያ ሠራዊቱን ያሰማራዉ አካል ማነዉ ከሚል መሆን ይኖርበታል። ይህ አካኼድ ለዚህ ለተነሣዉ ጉዳይ ብቻ የሚያገለግል አይደለም። በተመሳሳይ ካለክልል ጥያቄና እዉቅና የመከላከያ ሠራዊት አባላት ወደክልሎች በመዝለቅ ሕዝቡንና ተማሪዎችን የመግደል፣ የማቁሰል፣ የመደብደብና የማንገላታት ተግባር እንዲፈጽሙ የሚያዙ አካላት/ግለሰቦች እንዲጠየቁ የማድረግ እርምጃ መወሰድ ይኖርበታል። ሆኖም ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደርዕሰ ብሔርነታቸዉና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛኝነታቸዉ ይህንን ኃላፊነት መወጣት ካልቻሉ በደፈናዉ “ለሞቱትና ጉዳት ለደረሰባቸዉ ዜጎቻችን አዝናለሁ” በሚል ብቻ ከንፈርን መምጠጥ ዋጋ የለዉም። ችግሩንም ከማባባስ ዉጭ የሚፈይደዉ ነገር አይኖርም።
58
ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር ተከታታይ የስራ ቀናት በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት የሰው ኃይል አስተዳደር ቢሮ መመዝገብ ይቻላል፡፡ አመልካቾች በምዝገባ ወቅት ከመቼ እስከ መቼ እንዳገለገሉ እና ደመወዝ የሚገልጽ አግባብ ያለው የስራ ልምድ ማስረጃ ኦርጅናልና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ አድራሻቸው ከአዲስ አበባ ከተማ ከመቶ ኪሎ ሜትር ርቀት በላይ የሆኑ አመልካቾች የተሟላ የስራ መጠይቅ ፎርም በመሙላት እና ማስረጃ በፋክስ.ቁ. 011 6 46 56 78 በመላክ መመዝገብ ይችላሉ፡፡ ፈተና የሚጥበት ጊዜ በውስጥ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡ ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ፡፡
59
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በዋናው ጊቢና በቡሬ ካምፖስ በተለያዩ ኮሌጆች ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የትምህርት መስኮች በከፍተኛ ትምህርት የመምህራን ደመወዝ ስሌክ መሰረት መምህራንን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት የመጀመሪያ ዲግሪ ተወዳዳሪዎች በመደበኛው (regular program) እንዲሁም በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ የሚወዳደሩ ተወዳዳሪዎች ደግሞ የመጨረሻው የትም/ፕሮግራም በመደበኛው ያጠናቀቁ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ የተወዳዳሪዎች ዕድሜ ለመጀመሪያ ዲግሪ ከ35 ዓመት እና የ2ኛ ዲግሪ ከ45 ዓመት ያልበለጠ የመመዝገቢያ ቦታ፡- ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ህንፃ ቁጥር 27 ቢሮ ቁጥር 206፣ ቡሬ ካምፖስ የሰው ሀብት አስተዳደር ቢሮ እና አዲስ አበባ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ጉዳይ ማስፈፀሚያ ቢሮ ቁጥር 07 ሲሆን በግንባር፣ በፖስታና በፋክስ በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
60
ምስኪን!! አይዞህ አንድ ቀን ሰው ስትሆን ቢሮህ መተው ኢንተርቪው ያረጉሀል :: የዛኔ ተሽከርካሪ ወንበርህ ላይ ሆነህ ትንቀባረርባቸዋለህ : ግን ግን እኔ የምመክርህ ፖለቲካው ቢበቃህና በግ መነገድ ብትጀምር ምን ይልሀል?? ከተባነነ እኮ ላሽ ማለት ነው : እሱ ወላዋይና ራስ ወዳድ ሰው ነው : ጽናት የለውም : በዚህ ሀገር ፖለቲካ የማይታረም ስህተት ፈጽሞል : ምረጡኝ ብሎ በተቃዋሚ ስም ቅስቀሳ ቢጀምር ይፈነክቱታል:
61
ውድ ዲነግዴ፤ ዲነግዴ በማለት ስም ለራስህ የሰጠህበት ምክንያት በውል ባይገባኝም ማወቅም ባልፈልግም አቶ ልደቱን ምስኪን በማለት መናገር ስትጀምር ለስልጣን ያለህን ክብር ነገር ግን ለሰው ልጅ ማየት ስችል አማርኛን ቋንቋ በኪቦርድ ተጠቅመህ መጻፍ የቻልክ ነገር ግን ችግር ያለብህ መሆንህ ምስኪንነትህ በግልጽ ያሳያል። ላንተ ሰው ማለት ስልጣን በሀይል ነጥቆ በተሽከርካሪ ወንበር ላይ አንዴ ቀና፣ አንዳንዴ ደግሞ ደፋ፣ ደግሞ ሌላ ጊዜ ጠረንጴዛ በቦክስ እየነረተ መግለጫ የሚሰጥ ነው፤ ቢሮ ያለው ነው። የአማርኛ ቋንቋ አጠቃቀምህ በራሱ ተስፋ ቆርጠው በሀሽሽ ቤቶችና በጫት ቤቶች ተሰባስበው የሚዘብቱ ጥቂት የምናምንቴ ሰዎች አይነት ነው። ሙድ የሚለው ቃል በራሱ ምን ማለት እንደሆነ በትክክል አታውቀውም። እንዳንተ አይነት መሆን የሚፈልጉትን የማያውቁ፣ ሌሎች የሚሆኑትን በግልጽ መረዳት የማይፈልጉ፣ የማይችሉ ሰዎች በመካከላችን በዝተው በመኖራቸው እንዲህ አይነቱን የፓለቲካ ትንታግ በመዝለፍና የተሳሳተ መረጃ በህብረተሰቡ ውስጥ በማናፈስ ልንደርስ የምንችልበትን የለውጥ ጊዜ አስመልጠውናል። በእንዳንተ አይነት ሰዎች ምክንያት እንዳንተ አይነቶች የራሳቸውን ቅዱስ የሌላውን ርኩስ የሚያድርጉ ወያኔዎች ከሀያ አመታት በላይ በህዝባችን ላይ እንዲዘፍኑበት መንገድ አንቦርቅቀን ከፍተንላቸዋል። የአንተ ንግግር አንዳንድ አንተን መሰል እብድ ሰዎች እንደሚሉት የአርድና ወይም የአራዶች ቀልድ አይደለም። የእብዶች ቀልድ ነው። አራዶች ስለሰው ልጅ ይገዳቸዋል። አራዶች ለሰዎች ሰብዓዊ መብቶች የሚታገሉ ናቸው። አራዶች በእንዳንተ አይነት ካለ አእምሮ በሚመነጭ ቃላት የታጨቁ አይደሉም። አራዶች ወደፊትን በተስፋ ይመለከታሉ። አንተ ምናልባት ጅል መስለህም የወያኔን መርዝ የምትተፋ ጠባብ ባለአእምሮ ከሆንክ ግን አልፈርድብህም። ለእርኩስ አላማህ የምትተጋና የምትፍገመገም እብድ ስለሆንክ። ለማንኛውም ኣንተንና አንተ እይነቶችን እግዚአብሄር እስኪፈውስልን ድረስ የሀገራችን የፖለቲካ ስራት አደጋ ላይ እንደወደቀ በርግጥ ግልጽ ነው። እግዚአብሄር ይፈውሰን። ራስህን ከጣልክበት ቆሻሻ ስፍራ ፈልገህ እንድታገኘው እመኝልሀለሁ። ምናልባት በአንድ የውጭ ሀገር ያለህ ከሆንክም ያለህበት ሀገር አምልኮ የተመቸህ በመሆኑ ከእንዲህ አይነቱ ማንነትህ ያላላቀቀህን አምላክ እያመለክህ በመሆኑ ሀዘኔ የከፋ ነው። ብዙ አሉ። የበግ ንግድ ሙያ መሆኑንም ማወቅ አለብህ። ለማንኛውም ጤናህ ተስተካክሎ ባይህ ደስ ይለኛል። ስለቁጣየ ወይም ስለድንፋታየ በጣም ይቀርታ። ከዚህ ዘመን በኋላ ከእኛ ከኢትዮጵያዊያን ይህን መሰል አስተያየት የሚጠበቅ እንደሆነ ስለማላምን ነው። ሰላም። አይ “ዲነግዴ”…የኦሮሞ ብሄር ተወላጅ እንደመሆኔ መጠን ገና ስምሽን ሳየዉ ነዉ “ዲነግዴን” የመረጥሽዉ “ቢነግዴ” ሲባል ሰምተሽ ኦሮሞ ለመምሰል እንደሆነ የነቃሁቢሽ…ይህ ለምን አስፈለገ? ልደቱን የምትቃወምበት የፖለቲካ አመለካከት ካለህ በቀጥታ ማለት ነዉ እንጂ, የመንደር ወሬ ለምን አስፈለገ..እኔ በበኩሌ ልደቱን የሚቃወም ወይ ጠባብ ዘረኛ, ወይ ጨቅዋኝ አድሃሪ ነዉ እንጂ, ሚዛን የጠበቀ ፖለቲካ ያለዉ ሰዉ አይቃወመዉም…ለደቱ ማለት, የአብዛኛዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ስሜት ማለት ነዉ.
62
ወይ ትደግፋለህ አልያም ትቃወማለህ ፣ there is nothing in between አንተ እኮ የምርጫ ካርድ ቢሰጡህ ለሁለት ሰንጥቀህ 50% ድምጼን ለወያኔ ሌላውን 50% ለልደቱ ብለህ ሚዛናዊ ምርጫ እንደምታረግ እጠብቃለሁ
63
ልደቱ የዘረዘራቸው ችግሮች ሁሉ ከቁጥር 3 ከተጠቀሰው በስተቀር በተመሳሳዩ በምእራባውያን ሀገሮችም አለ። ልዩነቱ ግን በነዚህ ሀገሮች ውስጥ ፣በመንግስት ለውጥ ላይ ፣ የገዢው ቡድን ሳይሆን፣ ወሳኝነት ያለው፣ ወሳኝነት ያለው የህግ የበላይነት ስለሆነ፣ እንደምክንያት የተጠቀሱት ሁሉ በህግ የበላይነት ዋጋ ያጣሉ። ልደቱ በዚህ ኢንተርቪው ላይ ከተሳሰሰተው አንዱ ነገር ቢኖር፣የቅንጅት መሪዎችን ስህተትን በአንደኛ ደረጃ መሆኑን መናገሩ ነው፣ ዋነኛውንና ወሳኙን ግን ፣ ማለት አሁን በስልጣን ላይ ያለውን ቡድን፣ ማለት ተቃዋሚዎችን እንዳይነሱ አድርጎ የማዳከም ስልት የሚጠቀመውን ቡድን፣ በሁለተኛ ደረጃ ልደቱ ማስቀመጡ ትልቅ ስህተት ነው። ከዛም ልደቱ እራሱን በራሱ ሲቃረን የታየው ነገር፣ “አኛ የሌሎችን የቅንጅት አባሎች መንገድ ብንከተል ኖሮ ሁለት አመት ታስረን ወይ ይቅርታ ጠይቀን እንወጣለን ወይ አንወጣም ነበር” ብሎ ሲናገር፣ ይህን የሚያስር የሚያፍን የገዢውን ቡድን ስልትን በማቃለል፣ የቅንጅት መሪዎችን ስህተት በማጋነን፣ በአሁኑ ሰአት የገዢውን ቡድን ጭልጥ ብሎ የመደገፍ ባህርይ ያሳየበት ኢንተርቪው ነው። ይህ ሁሉ ነገር ግን እንዳይሳካ ያደረገው፣የገዢው ቡድን ከምራጫው በፊትና በሁዋላም፣ በህገወጥ መንገድ ብዙ ነገሮች በመፈፀም ነው። የአውሮፓ ህብረት በወቅቱ የተሰሩትን፣ የገዢውን ቡድን ህገወጥ ስራዎች 25ቱን መዝግቦአል። ከዛ በሁዋላ ምእራባውያን ችላ ያሉትም፣ ይህ የፈረደበት anti terror alians ውስጥ በመኖሩ፣ ሌላው ነገር ጆሮ ዳባ ልበስ ተብሎ፣ ልደቱ የዘረዘራቸውን ምክንያቶች እንደ ዋና ምክንያት በማቅረብ፣ለገዢው ቡድን የዲፕሎማሲ ሽፋንና እርዳታ በመስጠት፣ሶማሊያ እንዲገባ በማደርግ ነው ነገሩ የተፈፀመው። እንጂ የታዛቢው ቡድን፣ ካርተር ሴንተር እንኩዋን ሳይቀር፣ ሲዘግብ ኢህአድግ አንድም ቦታ እንኩዋን በኢትዮጵያ ውስጥ አላሸነፈም ይላል። የሚጫወተው መንግስት ነው። እንጂ ሌላ አይደለም። ይህን የማያደርግ ከሆነ ደግሞ፣ እነደተለመደው ሌላው ተመሳሳይ ህገወጥ ቡድን መጥቶ መንግስትን ይቀይራል። የጊዜ ጉዳይ እንጂ፣መንግስት መቀየሩማ የማይቀር ነገር ነው።
64
እንግዲህ ኣቶ ልደቱ በጣም በስሏል ለዚህም በጣም ድንቅ የሆነ ቀለመጠይቅ ለመስማት በቅተናል።የቅንጅት መሪዎች እንደተለከፈ ውሻ እርስ በራሳቸው ሲናከሱ ኣንዲትም ቀን በጠረጴዛ ዙርያ መቀመጥ ኣቅቷቸው እዚህም እዛም ሲዘላብዱ ኣየናቸው እያየናቸውም ነው! ቅንጅቶች ያኔ ፓርላማ ቢገቡ ኖሮ ባገራችን ምን ያህል የፖለቲካ ለውጥ ይመጣ እንደነበረ ለመገመት ኣያቅትም፣ ግን ለስልጣን እንጂ በእውነት ህዝብን ሊያገለግሉ ኣልነበረም።እነዛ ቁጥራቸው ጥቂት የሆኑት የኢዴፓ መሪዎች እንኳ ፓርላማ በመግባታቸው የመጣው ለውጥ ለማየት ኣያዳግትም። በጋዜጠኞች ደረጃም ኣብዛኞቹ እንደ ጋዜጠኞች ሳይሆን እንደ ተቃዋሚ ኣክቲቪስት ነበረ የተንቀሳቀሱት ኣሁንም እየተንቀሳቀሱ ያሉት። በእስር ላይ ያሉትም ጋዜጠኞች ሳይሆኑ የተቃዋሚ ኣቀንቃኝ እንጂ ገለልተኛ ለህዝብ ኣሳቢ ኣይደሉም! እስኣሁን ኣቶ ልደቱ እንደገለጠው እድርጎ የተነተነ ጋዜጠኛ የለም! ባጠቃላይ ጋዜጠኞች ለገንዘብ ነው የሚሰሩት! በዚህ ዓለም የተፈጠሩት ጦርነቶችና እልቂቶች በሚያዳሉ ጋዜጠኞች በተረጨ መርዝ የተነሱ ናቸው! በሩዋን፣በዩጎዝላቭያ፣በጀርመን ወዘተ የፈጠሩ እልቂቶች ለማየት ይቻላል! ስለዚህ የሚያዳላ ጋዜጠኛ ምንያህ ኣደገኛ እንደሆነ መገመት እንችላለን! ቅንጅቶች ሃሳባቸው በእርግጥ በምርጫ ኣሸንፈው በትረስልጣን ለመጨበጥ ሳይሆን ምርጫ ከለላ በማድረግ በዘመኑ ፋሽን በቀለም ኣብዮት ተጠቅመው ከምእራቡ ምቹ ኑሮ ወደ ተመቻቸ ስልጣን ለመሸጋገር ነበረ! ፓለቲካ የፉል ታይም ስራ ሆኖ ላላማህ የሚከፈለውን ሁሉ ለመክፈል በመዘጀት በረጅም ጊዜ የሚሰራ ስራ እንጂ በስምንት ወር ከዋሽንግተንም ከሎንደንም በመሰባሰብ ባቋራጭ የሚሰራ ስራ ኣይደለም!
65
ሰው ተገኝቶ ሞቶ ነው ይሀን ወረበላ የ ቤቴክርስትያን እቃ ዘራፊ ሰው ብላቹ ስለ ፖለቲካ ምትጠይቁ? ሌባ ስልጣን ኖረውም ኣልኖረውም ከሌብነት ኣይወጣም እና ልደቱ ሌባ ነው ሌባ ሆኖም ይሞታል እሚገርመኝ እንዴት ይሀን ሰው ወደ ፖለቲካ እንደገባ ነው በጣም ያሳዝናል የልደቱ ወደ ፖለቲካ መግባት የኢትዮ ተቃዋሚዎች ምንግኛ ደካማ እና ከስልጣን ጉግት ውጭ ስለ ሃገር ማያስቡ መሆ ናቸውን ነው ምያሳየው ለዛም ነውየኢትዮጵያ ህዝብ ከ ኢሃዲግ ውጭ ኣማራጭ ያለ ያልመሰለው
66
በዚህ ቃለ ምልልስ ትልቁን ሞት እየሞተ ያለው ፣ ቀድሞውንም የፖለቲካ ስብዕናው የሞተው ልደቱ አያሌው ሳይሆን ፣ አንተ “ጋዜጠኛው” ነህ። ይህን የ97ቱን ጉዳይ አስመልክቶ ጋዜጠኛ ልትባል አትችልም። ምክንያቱም ፣ ከጋዜጠኝነት አልፎ ፣ ከህይወትህ ውስጥ ሁለት አመታትን በእስር የተነጠቅህ ስለሆንህ ፣ የዚህ ታሪክ ክፍል እንጅ ጋዜጠኛ አይደለህም። ይህንንም አለማገናዘብህ ይመስለኛል ፣ ልደቱ ቀልዶብህ እንዲሄድ የፈቀድህለት። በ97ቱ ምርጫ ዙሪያ ፣ ከኔ የበለጠ አንተ ታውቃለህ ብዬ ባምንም ፣ ልደቱን ያስተናገድኸው ግን ፍጹም አላዋቂ ሆነህ ነው። ለዚህም ምክንያትህ የሚመስለኝን በስተመጨረሻ እነግርሃለሁ። ወደ ነጥቡ ስመጣ ግን … 1) ውህደቱ እንዳይፈጸም ፣ ከፓርቲው ህልውና አንጻር የፈለገውን አቋም የመያዝ መብቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ፣ በወቅቱ ይሰጣቸው የነበሩት እጅግ መረን የለቀቁ ግለሰባዊ መግለጫዎቹን እውነት ዳዊት ረስተሃቸው ይሆን? 2) የፓርቲዎች አጠቃላይ ውህደት እስከ ቀበሌ ድረስ ተወርዶ ለማጠናቀቅ የሚፈልገው ጊዜ እና ምርጫ ቦርድ የቅንጅትን ህልውና ለማክተም ያደርግ የነበረውን ሩጫ አስመልክቶስ ፣ ልደቱ እንደፈለገ ሲቀባጥር ዝም ያልኸው ፣ “ጋዜጠኛ ዳዊት” የምታውቀው ነገር የለምን? … ብዙ ብዙ ማለት ይቻላል። … ዳዊት በጣም አዝኘብሃለሁ። እያወቅህ እንዳላዋቂ ሆነህ ይህንን ባዶ ሰውየ ያስተናገድህበት ምክንያትህንም ለመገመት ሞክሪያለሁ። በቆየህበት የዳያስፖራ ልምድህ ፣ የዳያስፖራው ፖለቲካ ምን ያህል የዘቀጠ እና የቆሸሸ መሆኑን ተረድተሃል። በዚህ በኩል ፣ እኔም እየኖርሁበት ያለሁት ስለሆነ እረዳሃለሁ። ያ ማለት ግን ፣ ገና ለገና የማትወዳቸው ሰዎች ስለተሰደቡልህ እና የምትነቅፈው አስተሳሰብ ስለበሻቀጠልህ ፣ የራስህ የሆነ የመንፈስ ልዕላህንም በዚህ መልኩ ማስደብደብ እለብህም። የፈለገ ተዓምር ቢፈጠር ፣ ከልደቱ የበለጠ አንተ የተሻለ ተሰሚነት ሊኖርህ እንደሚችል አትዘንጋ። ይህ ሰው በአንድ ወቅት እፍ እፍ ተብሎ እውቅና አግኝቶ ነበር ፣ ከታወቀበት እጥፍ ድርብ ግን ዛሬ በብዙሃኑ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ሞቷል። ስለዚህ ፣ የማይዋጥልህን ሁሉ ዝባዝንኬ ሲተፋ ዝም ማለትህ ፣ በታሪክ ተወቃሽ ያደርግሃልና ፣ እራስህን ከቂም እና ከበቀል አጽድተህ ለህሊናህ ታማኝ ጋዜጠኛ ሁን። ተከታታይ ጥይቄዎች (follow-up questions) ማቅረብ ይጠበቅብሃል። (በተለይ እንደዚህ አይነት ለስህይወትህ ቅርብ የሆነን ጉዳይ አስመልክቶ።) እንዲህ አይነት ቅጥፈት የተሞላበት መላሽ ሲመጣ አፋጥጦ መጠየቅ የሰውነት ግዴታህ ነው። እሱ ደፍሮ ፣ አንትና መሰል ጋዜጠኞች የከፈላችሁትን ችግር ክምንም ሳይቆጥር ፕረሶን እንደዚህ ሲሞልጭ ዝም ማለትህ ፣ በጓደኞችህና በታሪክ ምን አይነት ቦታ ይሆን የሚያሰጥህ?! በነገራችን ላይ ፣ በየትኛም አገር ያሉ ፕረሶች የፖለቲካ አቋም ይወስዳሉ። ሌላው ቀርቶ በአሜሪካ ውስጥ ያሉ እንደ “washington post, new york times” ያሉ ጋዜጦች የፈለጉት የፖለቲካ ተመራጭ ፣ በጽሁፍ ከማበረታታት ጀምሮ endorse እስከማድረግ ይሄዳሉ። እናም ፣ በ97ቱ ምርጫ አንተ እራስህ ዳዊትንም ጨምሮ ፣ ሌሎች ጋዜጠኞች በሃቅ ላይ የተመሰረተ ሃሳብ ብታትሙ ፣ ምንም አያስወቅስም። ትልቁ ሃላፊነታችሁ ፣ እናንተ ለምታስነብቡት ሃሳብ ተቃራኒውን ይዞ ለሚቀርብ ቦታ ካልሰጣችሁት ብቻ ነው። ስለዚህ ፣ ልደቱ የሚያወራው ፍጹም ውሃ የማይቋጥር እና ከፖለቲካ መቃብሩ ውስጥ ሆኖ የሚያስተጋባው ባዶ እስትንፋስ ነው።
67
ውድ ኣውራምባዎች በጣም ጥሩ እና በሳል የሆነ ቃለ መጠይቅ ነው፡፡ የሚጎለው ነገር ቢኖር ካሜራ ማን በጣም ደካማ ነው፡፡ ዓይን በሚረቢሽ መልኩ ፍሬም ሳይጠብቅ ሰማይ ሰማይ ስለቀረፀው ምስሉን ሳላይ እንደ ሬድዮ ድምፁን ብቻ እንዳዳምጥ አርጎኛልና፡፡ ምነው ከኣማተር ካሜራማን ይልቅ ቢያንስ ትንሽ እንኳን የካሜራ ሞያ ያለው ሰው ብታረጉ፡ ለናንተም ፕሮፈሽናል የሆነ ስራ ይሆንላችሁ ነበር ፡፡ በተረፈ ጥሩ ቃለመጠይቅ ነው ግፉበት፡፡
68
ጀግናችን ከምድራዊ ገሀነም የስቃይ ጀርባ ሆኖ በሞት ጥላስር ተከቦ እጅግ በጣም በሚገርም ሁኔታ አንዳችም ፍንጭ ላይሰጣቸዉ በጀግንነት ፈገግታ ሸኛቸዉ።እነ ሰወ በላም ጠብ የሚል መረጃ ሳያገኙ የተለመደዉን እጅእጅ የሚል ፕሮፐጋንዳ መሳይ ቢጤ ለመደስኮር ብለዉ ይበልጥ ዘቀጡ እስኪ እግዚያብሄር ያሳያች ሁ አሁን ከዚህ የማሰቃየት ምርመራ ምን ጠብ የሚል ነገር አገኙ ፧ እኔ እንደተረዳሁት ግን የነጻነት አርበኛው አንዳርጌ ትግሉን የሚያግዙ ብዙ የእምየ ኢትዮዽያ የቁርጥ ቀን አንዳርጌወች በምቾት በሚኖርበት አሜሪካና አዉሮፓ የሚኖሩ ሙህራን እንዳሉ እና ያስተላለፈላቸዉ መልክትም አብቅቶላችሗል የሚል ነዉ።የሙህራኑን ስም የተናገረውም ላፕቶፑ ላይ ዝርዝራቸዉ ስላለ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።በነገራችን ላይ የሙህራኑ የትግሉ አጋር መሆን ለኢትዮዽያ ህዝብ ይፋ መሆኑ ሁሉንም አካል ይበልጥ የሚያነሳሳ አርያነት ያለዉ አኩሪ ሀላፊንት በመሆኑ ልንኮራ ይገባል።ኢትቪ ዉለታ ዋለችልን አያስብልም ፧ወይ ፍንክች ያባ ቢላዋ ልጅ፦አይ የወያኔ ኪሳራ ይበልጥ ህዝቡን ለትግል አነሳሱት።ወገኖቼ የድል ቀን ተቃርቧል እግዚአብሄር ከኢትዮዽያ ጋር ነዉ ።እስኪ ፊልሙን ደግመዉ ይመልከቱ እስቲ በምን መስፈርት ነው፤ አንዳርጋቸውን የጀግንነት ሙገሳን ያከናነብከው። ይህ ወስላታ ባንዳ፣ የሚታወቀው በከሃዲነትና በፀረ ኢትዮጵያዊነት ነው። እሱን አጅበው የሚጃጃሉ ጥቂት ያንተ ቢጤ የሻቢያና የአረብ ሙፎ ተስፈኞች፤ ከሚፈጥሩት ጫጫታ በስተቀር፤ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዚህን የሥልጣን ጥመኛና ራስወዳድ ግለሰብ ምንነት ጠንቅቀው ያውቃሉ። ይህንን ቪዲዮ እንኳን አይተህ፤ ነገር የማይገባህ ከንቱ፤ በአደባባይ ስትንዘላዘል፤ ድንቁርና በሌጣው የሚጋልብህ አሳዛኝ ፍጡር መሆንክን ሳልገልፅ ባልፍ፤ የዕውነተኛ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችን ነፍስ ማሳዘንና ገድላቸውን ማኮስመን ይሆንብኛል።
69
>>ይህ ካለፈው የቀጠለ ድራማ መሆኑ ነው? እንዴት አንድ መንግስት ለዚያውም አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ታጋይ ልመታዊ መንግስት ይቺን በመሥራት ግዜውን ያባክናል?የአንድ የታላቅ ሀገር የቲቪ ጣቢያ ክሎቱንም ዚች ፉገራ ያስገመግማል? ካለፈው አኬልዳማ..የካድሬ ሃረካት ከሚሉ አጫጨር ግን አስቂኝ ክስተቶች አሁንም አልተማሩም? በጣም የወረደና የዘቀጠ ጭራሽ በጣም አስፎጋሪ የሀሳብ መቆራረጥ አንዱን ጅምሮ አንዱን ጥሎ ሌላውን የሚቀባዥር ቆርጦ ቀጥል ። ግን ግለሰቡ በአንድ ኢንተርቪ ሁለት ቱታ የለበሰው መንግስትን እንክብካቤ ለማሳየት ነው?የሰጠኃችሁ ላፕ ቶብ ምንም መረጃ የለውም..ፍላሹም ቢሆን ብዙ ነገር የለውም አዲስ ነው። አሁን ኢህአዴግ አንድ ሰው አይተርፈውም ገና ይችን ተጠቅሞ ከፍተኛ ፕወዛ ያደርጋል…ምርጫ አስኪያልፍ ትሩ ማደናገሪያ አገኘ መብራት አይጥፋ እንጂ በእየሳምንቱ የ፲ ደቂቃ አስገራሚ አስደናቂ ሰበር ዜና “ግንኦት፯ ለግንቦት ፳ ድራማ” እየቆራረጠ ያሰየናል…(ሰው ለሰው ድራማ አለቀ!?)ወይስ ቻይና ሊጨርሰው ተስማማ?
70
ዳዊት: እኔ: የወያኔ: ደጋፊ:እንኳ: ባልሆንም: የአላማህ: ብርቱ: ደጋፊ: ነኝ:: ከዘረኞች: በላይ: ዘረኛ: ከሆኑት: የውሸት: ኢትዮጵያዊነት: ካባን: በሚያሳስት: መልኩ: ከተከናነቡትና: ከሌሎች: ምሁራዊ: ገለጻና: ትንታኔ: ይልቅ: የነሱን: ባዶ: ተራ: ተረት: ከሚያስቀድሙ: ድኩማን: በተረት: ኖረው: በተረት: አድገው: በተረት: ለመሞት: ከሚያጣጥሩት: ዝባዝንኬዎች: ጎራ: እንኳን: በሰላም: ወጣህ:: ከሰሞኑ: እነኚህኑ: ጉዶች: የዳኛ: ማንትስ: የተባለ: ወልገድጋዳ: መጫጭር: ሲያዳንቁና: ሲያራግቡ: ሳይ: ወየው: ለነዶክተር: ብርሃኑ: ነጋ፣ ነጋሶ: ጊዳዳ፣ እና : እንዲሁም: ለአንዳንድ: በተራ: ተረታቸው: ለተወናበዱ: የዋሆች: ብያለሁ:: ሰዎቹ: በስም: እንጂ: በምግባር: ኢትዮጵያውያን: ሳይሆኑ: ልብ: ያለው: ልብ: ይበል: ከሞረሽም: እኛ: በግላችን: እንመርሽ: ወድያ: ወገኔዎች: ናቸው!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
71
ዳዊት ወደ ኢትዮጲያ ለሚገባው ጉዳይ ዲያስፖራ ተጠያቂ ሊሆን ነው እነዴ፣ በመጀመሪያ የትም ይሁን ተትም ጥሩ ሰው አለ እንዲሁም ክፉ ሰው አለ።ዲያስፓራ ወይም የሀገር ውስጥ እያሉ መከፋፈል የወያኔ ወይም የደርግ ፓለቲካ ነው፣ በተመሳሳዩ ሀገር ቤት ነፍጠኛ ጭቁን እያሉ ወይም የተማረ ነው ሀገር ያጠፋው እንደማሉት ማለት ነው።ይህን አይነት የመከፋፈል ስራ ኮሚኒስታዊ ባህሪ ባላቸው በአንዳንድ ተቃዋሚ ሀይሎች ይንፀባረቃል። ዲያስፖራ በእርግጥ ለወያኔ አያመችም። ወያኔም ቢሆን የሰረውን የዘረፈውን ይደግፈኝ ብሎ ማሰብ አይን አውጣነት ነው።ድጋፍ በለመደው የውሸት ፕሮፖጋንዳ ሊገኝ አይቻልም።ደግፉኝ ብሎ እነደ ኢትዮጵያ ማስገደድ አይችልም። ዳዊት ሀገር ቤት ገብቶ በፕሮፌሽኑ ቢሰራ እንደሀቅሙ ከብዛት አድማጭ ሊኖረው ይችላል። ኢትዮጵያ በተማረበት አሜሪካ እሰራበታለሁ ብሎ መጠበቅ የለበትም። አሜሪካ ለተማሩትም አሜሪካ ቀላል አይደለም። ዳዊት ወደ ሀገሩ ቢገባ የግል ስሜቱና ፍላጉቱ እንጂ ከሌላው ጋር ስላልተሰማማ መሆን የለበትም፣ >>አቶ ዳዊት ከበደ(ጋዜጠኛ)አምደኛ!ባለፈው ኢህአዴግ የሚያስረው መሰሎት የነበረው በሐሰተኛ ሰው ወሬ ተሰብኮ አሜሪካ መጣ አሁን አምባሳደር ተስፋዬ ብሩ ውሸት መሆኑን አረጋገጡለት።እንዲያውም ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ቃል ገቡለት እሱም ሃራይ አለ!ፅቡቅ ሆነ.. አስነካው በለው!እኔም ቀስ በቀስ ትግርኛ መዛረብ ተማርኩ ቆጥሎም የኤርትራው የቢሸፍቱ ሊቅ ንግግር ዛቻና ፉከራ…ተስፋ ነፋ “በውጭ ሀገር ሚሊዮን ጓደኞች አሉኝ በቅር ቀን እንደጎርፍ ሀገራችን እንገባለን ይህንን በእርግጠኝነት ነው የምነግራችሁ!” ተስፋዬ ገብረእባብ ከፎከረበት!ከሚሊየን አንድ አለ በለው!ግን አብረው ፓርቲ ሊመሠርቱ ነው? ወይንስ ሳይቀድመኝ ልቅደመው ብሎ ነው? ዘንድሮ አለ ነገር! *ተስፋዬ ገብረእባብና ጀዋር መሀመድ ፓርቲ ሊመሠርቱና መከላከያውንና ኢኮኖሚውን ሊረከቡ ነው።አምባሳደር ግርማ ብሩን የፓርቲ ፍቃድ እተማፀኑ ነው። አሁን ስንት ቱልቱላ ፖለቲከኛ መሳይ ይጋለጣል? ይቀለድባታል!እነ ሚሚ ይቀውጡታል!ሸገር ሥራ ተከፈተ አፍ ተከፈተ!ውጭማ ሰሞኑን ይነፋል! ይሰጣል! ይስጠጣል! ይንጣጣል!ተቃዋሚ መስለው ገንጣይ ተንታኝ መስለው በታኝ! ዘረኝነትን አማባገነንነትን በዘር መነገድን ሽብርን ብጠብጥን አመፅን የሚያራቡም አሁን ያላቸው ሚስጠር ይጋለጣል። *ዳዊት ከበደ “እየጠፋ ነው እየበራ ሲባል”ዳዊት እንደ ስሙ ይክበድ ከቀለለ ጉድ ነው ብዬ ነበር።አሁንም ከከበደ መልካሙን እመኝለታለሁ! …ይህንንም አስተያየቴን በራሱ ድረገጽ ስላስተናገደ ከሌሎች የተሻለ ነው አመስግኜዋለሁ። ምንም ቢሆን ሰው በሀገሩ፣ በወንዙ, በቋንቋው የተማሩት ጋዜጠኞች የት ደርሰዋል?ይሄው ከተስፋዬ ገብረአብና ጃዋር መሐመድ ጋር ያሽቃብጣሉ!እነሱን የነካ ሜንጫ ይላሉ ለአንገቱ ይላሉ! እስታር ባክስ ይውላሉ!ማታ ማታ ፖለቲካ ይቀውጣሉ!ቀን ቀን ህወአት ኤምባሲ ይቀላውጣሉ!እሁድ እሁድ በሃይማኖት ቦታዎች መፈክር ያሰማሉ!ይጮሃሉ!ይጨበጨብላቸዋል!ከሀገር ሀገር እየዞሩ ሽብር፣ እልቂት፣ ጦርነት፣ አፍረሰው! አቃጥለው!ብላው! በትነው! ይላሉ። በፓል ቶክ አባባ ይበተንላቸዋል ሁለት ወር አንድ ሆነው በሦስተኛው ይበታተናሉ! *በሬ ከአራጁ ይውላል…ውሻ ሲያባርሩ ጅብ እቤት ገብቶ ቁርበት ላይ ተኝቷል። አሪ በይ በከንቱ ፖለቲካ(ቡልጠቃ)?አሁን ዳዊት ይገለጣል! ይደገማል!አነድ ትግሬ ይቅርታ ብለህ ሁለት ሶስት ብሔር ብሔረሰብ ከእሥር መልቀቅ!!ለመሆኑ በስሕተት ፈራሁ ማለት አለ? እርግጠኛ: ነኝ: ይሄ: ሰው: ቀንደኛ: እብድ: ነው: ነፍጠኞች: አሁን: ደግሞ: ተገልብጠው: አብደው: አብደው: ነውጠኞች: ሆኑ: እንዴ? በቃ: እነበለው: ዳጨው: ምናምን: መቱን: ጠቅልለው: አበደው: አረፉት: እይደል:: እስቲ: የሚወራው: ስለ: ዳዊት: ወደ: ሀገር: ቤት: መመለስ: ሆኖ: እያለ: ጤነኛ: ሰው: ካላበደ: በቀር: ሳይትተኛ: በቀን: ስላለመው: ህልም: ማንም: ንገረኝ: ሳይለው: ይበጠረቃል:: አረ: እባካችሁ: በልክ: እበዱ: እነ: እንመርሽ: ወገኔዎች!!!!!!!!!!!!!!!! ወይ አቶ በለውkkkkk!!! አንተም ተቸግርክ የእናቴ ሀገር፣ የዱሮው አንድነት እያልክ ዕድሜህን ትጨርሳለ ፡፡ ካንተስ ዳዊት ይሻሻላል፡፡ የእምዬ ምንልክክን አንድነት ለማምጣት ሁሉን ነገር ከምትቦጭር የቀን ሥራሕን ብት ሠራ ውጤታማ ትሆናለ አለበለዚያ ከንቱ ልፋት ነው፡፡ የኔ አሳብ ካልሆነ ብሎ ድርቅ ከሚል ጋር አብሮ መሥራት ማለት በወቅጡት………. ሌባና ድሃ አንድንት ገጠሙና ገለታ ሲቆላ፣ ሄለን ስተፈጭ፣ ፈመ ሲቁላላ፣ ቶላ ሲበላ፣ ከቤ ሲምስ፣…ሥም ስትቀያይሩ በሃይማኖት ስትነግዱ ልብ ለወያኔ ቂጥ ስታፈነድዱ ዕድሜአችሁ ጨረሳችሁ! ልብ ካላችሁ ለምን የሰው ሀሳብ ታጠፋለችሁ? ላሳያችሁ ስንት የደንቆሮ ማኅበርተኞች በውሸት ሥም በመቀያር አንዳምታጭበረብሩ…ፋንዲያ ተማር አትፍራ!ዳዊት ኮንደምኒየም አያሰጥህም ብዙ ጭራህን አትቁላ ግለሰቡን “አልጠላሁትም ክበድ ማለት ነውር ሆኖ ቅልል ያላችሁት” እናንተ ናችሁ ።ሰው ሁኑ ህወአት የፈጠረህ ብሄር አትሁን በራስህ ተማመን “አድርባይ” አሉ ታጋይ አዜብ የሙስና ሻንጣ ተሸካሚ ሁሉ!!በለው!
72
ዳዊት በፖለቲካ ሰበብ መታሰሩ መካድ የለበትም። በጋዜጣውም ሰበብ የወያኔ ጥርስ ውስጥ መግባቱንም መካድ አይቻልም። በጥሩ የህዝብ ወገንተኝነቱም ተሸልሟል፤ ተወድሷል። ይሁን እንጂ የዳያስፖራው ገሚሱ ጭፍን ተቃዋሚ፤ ገሚሱ እበላ ባይ፤ ገሚሱ ደግሞ ጭፍን ደጋፊ በተለይም የሕወሀት አባላት ስደተኛው በሚያራግበው መልክና ቅርጽ የሌለው የፖሊቲካ ትኩሳት ተከትሎ ዳዊት አቋሙን አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ ሲል መቆየቱን የተመለከቱ ሰዎች በአንድ በኩል ስውር ወያኔ ሲሉት፤ ወያኔዎች ደግሞ ልጃችን ለማለት ጊዜ አልፈጀባቸውም። ዳዊትም በፓልቶክና በጽሁፉ ሳይቀር የብስጭት ድምጽና ጽሁፍ ሲያስተጋባ የነገሩ ምክንያታዊ ውል የጠፋ መሰለ። የዳዊት ድረ ገጽም መልኩን ለውጦና የቀድሞ ትኩሳቱን ረገብ አድርጎ ነጻ ነኝ ለማለት የሚፈልግ መሰለ። አይጋ ፎረምም ወዳጅነቱን አሳየ። ዳዊት አሳዶኛል ያለው ወያኔ አሁን ካለሁበት ይሻለኛል በማለት ለመስራት በመቁረጥ አዲስ አበባን ምርጫው አደረገ። በእርግጥ ወያኔ ከልማታዊ ጋዜጠኝነት ውጪ ነጻ ሚዲያ እንደማፈቅድ 1000% ቢረጋገጥም የዳዊት መመለስ የሚያመጣው ፋይዳ አይኖርም። ምናልባት ያለው ምርጫ ሁለት ነው። አውራምባ አዲሲቱ ሪፖርተር ሆና ትመጣለች፤ አለያም እውነትንና እውነትን ብቻ በመዘገብ ሰማዕት ሆና እንደሻማ ትቀልጣለች። የትኛውን ሆኖ ዳዊት እንደሚሰራ ለጊዜው ባናውቅም ዳዊት ተመልሶ ከገባ በኋላ የሚሰራውን ለማየት ትንሽ መጠበቅ ሳይሻል አይቀርም።
73
(reporter):- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛው ፓትርያርክ ሆነው ባለፈው ሐሙስ የተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በውጭ አገር ካሉት ጳጳሳት ጋራ እርቀ ሰላም ማድረጉ አሁንም ይቀጥላል አሉ፡፡ በጠቅላይ ቤት ክህነት አዳራሽ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. በተደረገው የስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫ ከፍተኛውን 500 ድምፅ በማግኘት የተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ከምርጫው ፍፃሜ በኋላ በተለይ ለሪፖርተር በሰጡት ቃለ ምልልስ አሜሪካ ከሚገኙትና ከአራተኛው ፓትርያርክ ጋር ሆነው ከተለዩት ጳጳሳት ጋር ንግግሩ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ‹‹ከአሁን ቀደም እርቁ ተሞክሯል፡፡ ውጭ አገር ካሉት ወንድሞቻችን ጋራ እርቀ ሰላም ለማድረግ በተደጋጋሚ ተሞክሯል፡፡ አሁንም ቢሆን ቅዱስ ሲኖዶስ በወሰነው መሠረት ይቀጥላል፤›› ብለዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ዓለም አቀፍ ግንኙነትም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በጀመሩት መንገድ እንደሚቀጥሉ እምነታቸውና ተስፋቸው መሆኑን የገለጹት አቡነ ማትያስ፣ ‹‹በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ይዞታ በሆነው ዴር ሡልጣን ገዳም ከግብፅ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውንና ከ1770 ዓ.ም. ጀምሮ ሥር የሰደደውን ችግር ለመፍታት፣ ከግብፅ ሲኖዶስ ጋር ተደርጎ የማያውቀውን ድርድር ከእነርሱ ጋር በመነጋገር መፍትሔ ለማምጣት እንጠይቃለን፤›› ብለዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ስድስተኛው ፓትርያርክ ሆነው መመረጣቸውን የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ካበሰሩ በኋላ ‹‹ሥራው ከባድ ቢሆንም ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከካህናትና ከምዕመናን ጋር አብረን ስለምንሠራ ሥራው የቀለለ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፤›› በማለት ንግግር ያደረጉት ተመራጩ ፓትርያርክ፣ በልዑል እግዚአብሔር ዕርዳታ የቤተ ክርስቲያኒቱን ምዕመናን ለማገልገል፣ ለማስተማርና ፍቅር አንድነትን ለመመሥረት ከምንጊዜው በበለጠ እንደሚተጉ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊ የኾኑትን ሁሉ መሥራት እንደሚቀጥሉ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ‹‹ለአፍሪካና ለኢትዮጵያ መልካም እረኛ እንዲሰጥ ለመፀለይና ለመምረጥ ነው የመጣነው፤›› ያሉትን የግብፅ አምስት ሊቃነ ጳጳሳት ጨምሮ ድምፅ ከሰጡት 806 መራጮች 500 ድምፅ በማግኘት ሲመረጡ፣ ሌሎቹ አራቱ ዕጩዎች አቡነ ዮሴፍ፣ አቡነ ማቴዎስ፣ አቡነ ሕዝቅኤልና አቡነ ኤልሳዕ በቅደም ተከተል 98፣ 98፣ 70 እና 39 ድምፅ ማግኘታቸውን፣ አንድ የድምፅ መስጫ ወረቀት ባዶ በመሆኑ መጣሉን የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢው ይፋ አድርገዋል፡፡ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ የኾኑት አቡነ ማትያስ ከ30 ዓመታት በላይ በውጭ አገር በመኖር ቤተ ክርስቲያኒቱን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ በ1934 ዓ.ም. በቀድሞው አጠራር በትግራይ ጠቅላይ ግዛት አጋሜ አውራጃ በስቡሕ ሳፅሲዕ ወረዳ ከአባታቸው አቶ ወልደ ጊዮርጊስ ከእናታቸው ከወይዘሮ ከለላ የተወለዱት አቡነ ማትያስ፣ የመጀመርያ መጠርያቸው አባ ተክለ ማርያም አሥራት ነበር፡፡ እንደ ወላጅ አባታቸው ሆነው የተጠሩባቸው ማዕርገ ምንኩስና የተቀበሉበት ጭኸ ገዳም አበምኔት መምህር አሥራተ ጽዮን ናቸው፡፡ ገጸ ታሪካቸው እንደሚያወሳው፣ በትግራይ ተምቤን አውራጃ በሚገኘው ጭክ ኪዳነ ምሕረት ገዳም፣ በአክሱም ቅዱስ ያሬድ መንፈሳዊ ትምህርት ቤትና የጎንደር ከፍተኛ የነገረ መለኮት ተቋም (የታላቁ ሊቅ አራት አይና ይባሉ ከነበሩትና የመጀመርያው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የዶክተርነት ማዕርግ የተሰጣቸው የአለቃ አየለ ጉባዔ ቤት) የነገረ መለኮት፣ የትርጓሜ መጻሕፍት፣ መዝገበ ቅዳሴና ቅኔ ባሕረ ሐሳብን አጠናቀው የተመረቁት አቡነ ማትያስ፣ በ1968 ዓ.ም. ሦስተኛው ፓትርያርክ ሆነው ለተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ቀሲስ (ልዩ ጸሐፊ) በመሆን ሠርተዋል፡፡ በ1971 ዓ.ም. የጵጵስና ማዕረግ ካገኙ በኋላ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ለሦስት ዓመት ካገለገሉ በኋላ ወደ አሜሪካ በመሻገር በሊቀ ጳጳስነት መንፈሳዊ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ በ1999 ዓ.ም. ዳግመኛ ወደ ኢየሩሳሌም በመመለስ ፓትርያርክ እስከሆኑበት ዕለት ድረስ አገልግለዋል፡፡ ከአማርኛና ከትግርኛ ቋንቋዎች በተጨማሪ እንግሊዝኛ፣ ዕብራይስጥ (ሂብሩ)፣ ግሪክና ዓረቢኛ ቋንቋዎች የሚያውቁት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በዓለ ሲመት እሑድ የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፡፡ በበዓለ ሲመቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ጳውሎስ ዳግማዊ የህንድ ፓትርያርክና የምሥራቅ አህጉር ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት፣ በብፁዕ አቡነ ጳኩሚስ መሪነት በምርጫው ላይ የተገኙትና ድምፅ የሰጡት የግብፅ ኦርቶዶክስ ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የእኅት አብያተ ክርስቲያናት ሊቃነ ጳጳሳት እንደሚገኙ ከመንበረ ፓትርያርክ የውጭ ግንኙነት መምርያ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ የእሑዱን በዓለ ሲመት የኮፕቲክ ቴሌቪዥን (ሲቲቪ) በቀጥታ ሥርጭት እንደሚያስተላልፈውም ታውቋል፡፡ የመጀመርያውን ፓትርያርኳን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስን በ1951 ዓ.ም. የመረጠችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን፣ ባለፉት 53 ዓመታት አምስት ፓትርያርኮች ብፁዓን ወቅዱሳን አቡናት ባስልዮስ፣ ቴዎፍሎስ፣ ተክለ ሃይማኖት፣ መርቆሬዎስ የመሯት ሲሆን፣ አምስተኛው ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (1928-2004) በመንበሩ ላይ 20 ዓመት (1984-2004) ከቆዩ በኋላ ያረፉት ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም. እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ጳጳሳት ጉባኤ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛ ፓትርያርክ ሆነው በመመረጣቸው የተሰማውን ደስታ ገልጿል፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር እንደከዚህ በፊቱ በመንፈሳዊና በልማት ሥራዎች በቅርበት በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን ገልጾ፣ ከዚህ በፊት የነበሩት ፓርትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመን በአገሪቱ በሃይማኖቶች መካከል የነበረውን መልካም ግንኙነትም በአዲሱ ፓትርያርክ ዘመን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሙሉ እምነቷ መሆኑን ብፁዕ አቡነ ብርሃነየሱስ ሊቀጳጳስ ዘካቶሊካውያን የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጳጳሳት ጉባዔ ፕሬዚዳንት በላኩት የደስታ መግለጫ ገልጸዋል፡፡
74
ቴዲ አፍሮ ከአሜሪካ ድምጹ አሉላ አበበ ጋር በvoa የዋሽንግተን ስቱዲዮ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አውግቷል፡፡‹‹ይቅርታ እጠይቃለሁ!›› ቴዲ አፍሮ በአሜሪካ ድምጽ ስቱዲዮteddy afro – voa amharic interview
75
ማመልከቻ ከማስገባት ጋር በተያያዘ የግልግል ስምምነት ህግ በድንጋጌው የቡድን ውክልና ስልጣን ለማረጋገጥ የሚመለከት ማስጠንቀቅያ ኦምሪ ናሆም ሲ.ዲ.ቢ.ኤስ የሳተላይት አገልግሎቶች (1998) ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት​​
76
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦክስ ፌዴሬሽን ከጎጆ ክሬቲቭ ሚዲያ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የስፖንሰር የቦክስ ውድድር ላይ የተስተዋለው ስፖርታዊ ጨዋነት ለሌሎች አርአያ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ጥቅምት 19 ቀን 2010 ዓ/ም አ/አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን ከጎጆ ክሬቲቪ ሚዲያ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ውድድር ላይ ከልዩ ልዩ የስፖርት ክለቦች የተወጣጡ የቦክስ ስፖርተኞች ተሳትፈውበታል፡፡ በዕለቱ ውድድሩን ለመከታተል በርካታ ቁጥር ያለው የስፖርት አፍቃሪ የታደመ ሲሆን ውድድሩ ስፖርታዊ ጨዋነት በተላበሰ መልኩ መጠናቀቁ የሌሎች ስፖርታዊ ውድድሮች ምሳሌ እንደሆነ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ም/ፕሬዝዳንት አቶ አብዱ ሰመር መሀመድ እና የአ/አ/ከተማ ቦክስ ፌዴሬሽን ም/ሃላፊ አቶ አሰፋ አብርሀ ገልፀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ስፖርት ማስተባበሪያ ሀላፊ ም/ኢ/ር ያረጋል ሙሉ በበኩላቸው ውድድሩ በጥሩ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የሚመለከታቸው አካላት ድርሻቸው እንደተወጡ ተናግረዋል፡፡ በተለይ ስፖርት አፍቃሪው ለስፖርቱ ማደግ እያደረገ ያለው ቀና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ በውድድሩ ላይ በ49 ኪ.ግ የአዲስ አበባ ፖሊሱ እንዳሻው አላዩ ከኢ/ያ ወጣቶች አካዳሚ ዳዊት ፍቃዱን፤ በ64 ኪ.ግ የአዲስ አበባ ፖሊሱ መስፍን ብሩ የማራቶን ክለቡን ተመስገን ምትኩን በማሸነፍ የወርቅ ሚዳሊያ ያጠለቁ ሲሆን በ75 ኪ.ግ ሁለቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ቦክሰኞች መክብብ ከማል እና ሰይፈ ከበደ የተገናኙ ሲሆን ሰይፈ ከበደ አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡
77
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል። ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
78
በአምቦ ዩኒቨርስቲ አዋሮ ግቢ ካለፈው አርብ ጀምሮ ውሃ መቋረጡን፣ መብራት ከዕረቡ ጀምሮ መጥፋቱን እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ መነሲቡ ወረዳ ከሠላሳ በላይ ሰዎች መታሠራቸው በዚህ ዘገባ ተካቷል። በዕረቡ ምሽት ዘገባችን ካለፈው አርብ ጀምሮ ውሃ በመቋረጡ ምክንያት ችግር ውስጥ መኾናቸውን የገለጹት አምቦ ዩኒቨርስቲ አዋሮ ግቢ ተማሪዎች በተጨማሪም መብራት እንደተቋረጠና ይህንንም ተከትሎ የግቢው ተማሪዎች በሙሉ ተቃውሞ ሲያቀርቡ አስለቃሽ ጭስ እንደተወረወረባቸውና እንደተደበደቡ አንዳንድ ተማሪዎች ገለጹ፡፡ በአምቦ ዩኒቨርስቲ አዋሮ ግቢ ካለፈው አርብ ጀምሮ ውሃ በመቋረጡ ተማሪዎች የሚጠጡትም ኾነ የሚታጠቡበት እንደሌላቸው፣ በመፀዳጃ ቤቶቹም ውሃ ስለሌ ከፍተኛ ችግር ውስጥ መኾናችውን ተማሪዎች ገለጹ፡፡ በምስራቅ ወለጋ መነሲቡ ወረዳ ውስጥ ሰኞ እና ማክሰኞ በተማሪዎችና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ግጭት መፈጠሩን ነዋሪዎች ገለጹ። ከግጭቱም በኋላ ከሰላሳ ሰው በላይ መታሰሩን ተናግረዋል። የከተማው ፖሊስ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም ይላል።
79
ጤና ይስጥልኝ በስራ ምክንያት ዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ለመቆየት በቅርቡ ከምኖርበት ሎስ አንጀለስ ከተማ እመጣለሁ። ለዚሁም ለተወሰነ ጊዜ ምቆይበት አንድ የተሟላ ክፍል እፈልጋለሁ። ክፍሉ ንጹህ ሆኖ […] ስፕሪንግፊልድ ቨርጂኒያ የሚከራይ ባለ 3 መኝታ ክፍል ታውንሃውስ:: ለትራንስፖርት በጣም ቅርብ የሆነ: በቅርብ የታደሰ ማብሰያ ቤት እና ጣውላ ወለል ያለው ሙሉ ቤት ይከራያል:: 3 bedrooms […]
80
መስቀል አደባባይ በተዘጋጀው የድጋፍ ሰልፍ ላይ የቦንብ ጥቃት ፈጽመዋል ተብለው ከተጠረጠሩት መካከል ደሳለኝ ተስፋዬ፣ አብዲሳ ቀነኒ፣ ህይወት ገዳ፣ ባህሩ ቶላ እና ጌቱ ግረማ ላይ ክስ ሊመሰረት ነው ተብሏል። ኢቢሲ የፖሊስ የምርመራ መዝገብን ጠቅሶ እንደዘገበው አንደኛ ተጠርጣሪ አብዲሳ ቀነኒ በዕለቱ በወንጀሉ ተጠርጥረው የህክምና ዕርዳታ እየተሰጣቸው የነበሩትን ሰዎች ለማስመለጥ ሙከራ አድርጓል ተብሎ ክስ ተመስርቶበታል። ሶስተኛው ተጠርጣሪ ጌቱ ግርማ ደግሞ የቦንብ ጥቃቱን በማስተባበር ወንጀል ነው የተጠረጠረው። አራተኛ ተጠርጣሪ የሆነችው ህይወት ገዳ በዕለቱ የአእምሮ ህመምተኛ በመምሰል በወንጀሉ ተሳትፋለች የተባለ ሲሆን አሁንም በአማኑኤል ሆስፒታል ህክምና እየተከታተለች መሆኑን የምርመራ ቡድኑ ገልጿል። አቃቢ ህግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ ለመመስረት 15 ቀን ይሰጠኝ ብሎ የጠየቀ ሲሆን ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው ለአቃቢ ህግ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው አይገባም፤ የዋስትና መብታችን ይጠበቅ፤ በማረፊያ ቤት የሚያጋጥመንም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይቁም ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። አቃቢ ህግ በበኩሉ ለተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት ሊፈቀድ አይገባም ሲል ተቃውሟል። ፖሊሲም ተጠርጣሪዎቹ ተፈጽሞብናል ያሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ትክክል አለመሆኑን ለዚህም የቪዲዮ ማስረጃ ማቅረብ እንደሚችል አሳውቋል። ፍርድ ቤቱ ሁለቱንም ወገን ካደመጠ በኋላ አቃቢ ህግ የጠየቀውን የክስ መመስረቻ የ15 ቀን ጊዜ ፈቅዷል። ከዚህ በተጨማሪም ተጠርጣሪዎችም በማረፊያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ አዟል። የስራ ክፍተት በመፍጠር የተጠረጠሩት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የነበሩት ግርማ ካሳን ጨምሮ ዘጠኝ የፌደራል ፖሊስ አባላትን በተመለከተ ለመጨረሻ ጊዜ የተሰጠው ቀጠሮ ዛሬ ከሰዓት በኋላ የሚታይ ይሆናል በማለት የዘገበው ደግሞ ፋና ነው።
81
እቲ ብጣዕሚ ዘህዝን ነገር፤ እቲ ተጋደልቲ ደሞም ዝዋህጅሉ ሕዝባዊ ስርዓት፤ ብኻልአይ ፋሽስታዊ ስርዓት ምትክኡን፤ ድኽሪ ፪፬ ዓመታት ናይ ወያኔ “ንግስና”፤ እቲ በሔራዊ ጭቆና ዝገደደ መዃኑ እዩ። ንፍትሕን ንናጽነት ዝፈሰሰ ደም መንእሰያት፤ ከንቱ ምዃኑ፤ እዩ ልብና ዝህመና።
82
ኤርሚያስ ለገሰ – ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት ህዉሃት በብሔር ብሔረሰቦች ዲሞክራሲያዊ መብቶች እየማለና እየተገዛተ ዝህቡን ለማታለል ብሎም ለመለያየት ቢሞክርም ያሰበውን አላማ ሊያሳካ አልቻለም። ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው በአገራችን የሰላም እጦት ከጫፍ እስከ ጫፍ እየታየ ነው። የስርአት ለውጥና የነፃነት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ የትግል ስልቶች ተቀርፀው ወደ ትግባር ተቀይረዋል። እየተደረጉ ያሉት ትግሎች አስተሳስረን ስንመረምር አሁን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ወደ መቃብር የወረደበት ሆኖ እናገኘዋለን። ከዚህ በኋላ ህዉሃት መንግስታዊ የበላይነትን ባገኘበት ሁኔታ የምርጫ ፖለቲካ አጀንዳው ተዘግቷል። የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እንዳሉት በምርጫ ፖለቲካ መቃብር ላይ ጥቁር አበባ ተቀምጦበታል። መቃብር ፈንቅሎ ትንሳኤ ይፈፀም ይሆን ለወደፊት የምናየው ይሆናል። ህዉሃት መራሹ ድርጅት በየጊዜው የሚሰጠው ድርጅታዊ መግለጫና እሱን ተከትሎ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተስፋ የሚያስቆርጠው የአገሬው ህዝብና የአለም መንግስታትን ብቻ አይደለም። የስርአቱ መስራችና ባለቤት የነበሩ እንዲሁም በተለያየ ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ ስልጣን ላይ የነበሩትን ጭምር ነው። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሚዲያዎችን ያጨናነቁት ጄኔራል አበበ እና ጄኔራል ፃድቃን በስርአቱ ምላሽ ላይ ምን ያህል ተስፋ እንደ ቆረጡ መገመት ይቻላል። “የስርአት ችግር ስላለ፣ ኢህአዴግ የተቀባይነት ችግር ስላጋጠመው የስርአት ለውጥ መምጣት አለብት!” ብሎ የተናገረው አንደበታቸውና የከተበው ብዕራቸው ዞር ብለው ሲመለከቱ ማፈራቸው የሚቀር አይደለም። እነ ፃድቃን “ሀገሪቷ የመበታተን አደጋ ሊያጋጥማት ይችላል” ቢሉም የቀድሞ የትግል ጓዶቻቸውና የስልጣኑ ባለቤቶች “ህገ-መንግስታዊና ዲሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርአት በጽኑ መሰረት ላይ ተገንብቷል” የሚል ዲስኩር ያሰማሉ። እነ ጆቤ “ህዝቡ በተስፋ እጦት ውስጥ ገብቷል” ብለው ሲፅፉ በተቃራኒው እነ አባይ ፀሀዬ “የአገራችን ህዝቦች በኢትዮጵያ የፈነጠቀውን የልማትና የዲሞክራሲ ጮራ ተማምነው በለመለመ ተስፋ ወደፊት ይመለከታሉ” የሚል ዘመን ተሻጋሪ ማብራሪያ ይሰጣሉ። እነ ፃድቃን በቀኝ ሆነው የመቶ ፐርሰንት ምርጫ በህዝብ ማላገጥ ነው” በማለት ብዕራቸውን ሲያነሱ በግራ የተሰለፉት እነ በረከት “ኢህአዴግ ስራ በምርጫ ካርድ የተሰጠውን ሃላፊነት አደራ ለመወጣት ቆርጦ ተነስቷል” ይሉናሉ። አራንባና ቆቦ!! እዚህ ላይ በሁለቱ የቀድሞ የጦር አዛዦችና የህዉሃት መራሹ መንግስት ሃይሎች መካከል በሁሉም ጉዳይ ተቃርኖ ውስጥ እንደገቡ የሚያስብ ካለ በደንብ ተሸውዷል። ሁለቱም ሃይሎች የህዉሃትን ብሎም የትግራይ ህዝብ ጥቅም ይነካል ብለው በገመቱት ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም አላቸው። ከዚህ አንፃር በቅድሚያ ሊነሳ የሚችለው በቀድሞ በትግራይ አስተዳደር ስር ያልነበሩና ዛሬ የተካለሉት ወልቃይትን የመሳሰሉ ቦታዎች ናቸው። የጦር አዛዦቹም ሆነ የህዉሃት ታጋይ ባለስልጣናት መጀመሪያ ሰሞን የወልቃይትና ተመሳሳይ ቦታዎች ፈጽሞ አንዳይነሱ፤ የሚዲያ ትኩረት እንዳያገኙ አድርገው ነበር። በጽሑፎቻቸውም ሆነ በመግለጫዎቻቸው በየትኛውም ቦታ ከመግለጥ ተቆጥበው ነበር። የቅማንትን ጉዳይ አጉልቶ የገለጠው “ጆቤ” ወልቃይት ላይ ሲደርስ የብዕሩ ቀለም በሚያስፎግር ሁኔታ አልቆበት ነበር። በኦሮሚያ ጥያቄዎች ላይ በምናቡ ከፈጠራቸው የኦሮሞ ልጆች ጋር ማውራቱን ሊነግረን የፈለገው ጄነራል አበበ ጠገዴና ጠለምት ፀለምት(ጨለማ) ሆነውበት ግድግዳ ተስታኮና ተንፏቆ ሲያልፋቸው ተመልክተናል። ሁኔታዎች እየገፋ ሲመጡና የትግሉ ማዕከሉ “ወልቃይት” መሆኑ ሲረጋገጥ እየተንፏቀቁም ቢሆን የወልቃይትን አጀንዳ ማንሳት ጀመሩ። ለምን ከዚህ በፊት ልታነሡት አልሞከራችሁም ሲባሉ “ይሔ ትልቅ ጉዳይ አይደለም:” የሚል ምላሽ ሰጡ። ቁምነገሩ እዚህ ጋር ነው። ለእነ ጄነራል ፃድቃን የቅማንት ጉዳይ ትልቅ እንደሆነ አድርገው ሊያገኑት ሲሞክሩ የማያቋርጥ የህዝብ ደም እየፈሰሰበት ያለውን ወልቃይት ንቀው እንደተውት ሊያሳዩ ሞከሩ። እነዚህ ሰዎች ይህን ምላሽ ሲሠጡ ወልቃይት “የትግል ማዕከል” እና “የኢፍትሃዊነት ማሳያ” መሆኑን ጠፍቷቸው አይደለም። ልክ አቶ መለስ በኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት ወቅት ካድሬዎች “ለምን ባድመን ለመሰለ ቁራሽ መሬት የ10ሺዎች ደም ይፈሳል?” ብለን ሥንጠይቀው እጁን እየጠበጠበ “ባድመ የትግላችን ማዕከል የሆነችው የኢፍትሐዊነት ማሳያ ስለሆነች ነው” በማለት የንዴት ምላሽ ሰጥቷል። በመሆኑም ባድመ የኤርትራ መንግስት በሃይል ስለወሰዳት መጀመሪያ ወደቀድሞው ቦታዋ ትመለስና ህጋዊ ውሳኔ ይሰጥባት እንደተባለ ሁሉ የወልቃይትም ተመሳሳይ ነው። ወልቃይት “ኢፍትሃዊነት ማሳያ” ስለሆነች መጀመሪያ ወደቀድሞው ታሪካዊ ባለቤቷ ትመለስና ሌሎች የህዝብ ጥያቄዎች ቂም በቀል በማይፈጥሩና የጋራ ድል (win_win) በሚያረጋግጡ መልኩ ይፈቱ ማለት የአባት ነው። ይገባልም። ይህ ካልሆነ ግን ምንአልባት ከባድመው ባልተናነሰ በ100ሺዎች የሚጠጋ ህይወት የሚወድቅበትና ደም መቃባቱ የሚያባራ ሊሆን ይችላል። በመቶ ሺዎች ሊገደሉ ይችላሉ የሚለውም ተራ ማስፈራራት አይደለም። ህዉሃት በተለይም የአማራ ተወላጆች ላይ የቋጠረው የቂም ቋጠሮ ከዚህ በላይ ሊገድል እንደሚችል ፍንጭ የሚሰጥ ነው። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር አሰፋ አቢዩ ከሳምንታት በፊት በሰጠው መግለጫ “99 ፐርሰንት ንፁህ ናቸው። እርምጃ የምንወስደው በተቀሩት ላይ ነው” በማለት ይፋ አድርጓል። አሁን ባለው የአማራ ክልል ንቅናቄ ከ5 ሚሊዮን የአማራ ተወላጆች በቀጥተኛ እየተሳተፉ እንደሆነ ዝቅተኛ ግምት ቢወሰድ እንኳን በኮሚሽነር አሰፋ ስሌት መሠረት ከ50 ሺህ በላይ ሠዎች እርምጃ ይወሰድባቸዋል። ህዝባዊ ማዕበሉ እየሰፋ ሲሄድ በአስቸኳይ የስርአት ለውጥ ካልመጣ እርምጃ የሚወሰድበት የአማራ ተወላጅ ሁለትና ሶስት እጥፍ ይሆናል። ለህዉሃት “የትግል ማዕከል” የሆኑትን ቦታዎች አሳልፎ መስጠት መቃብሩን በጥልቀት የመቆፈር ያህል ስለሚመለከተው በጅምላ ከመግደል የሚመለስ አይሆንም። በእኔ እምነት ኢትዮጵያ ውስጥ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ማዕበል ከህዉሃት ህልውና አንጻር በርካታ ዋልታዎች (multi- polar) ያሉት ቢሆንም፣ የዋልታዎቹ ምሰሶ ወልቃይት (wolqayit factor) ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የኦሮሚያ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ የተነሱት እምቢተኝነቶች ትላልቅ ዋልታዎች ቢሆኑም ህዉሃት ልቦና ገዝቶ በህይወት መቆየት ከፈለገ ወደ ምሶሶነት ሳያድጉ በተራዘመ ሂደት ሊያዳፍናቸው ይችላል። ለምሳሌ ህዉሃት ኤርትራ ላይ የሚያስበው (eritrian-factor፡ ኤርትራ በጦርነት ማሸነፍና አስመራ ላይ አሻንጉሊት መንግስት መመስረት) ከተሳካና ህዉሃት ኢትዮጵያን መምራት ከተነሳው የኦሮሚያን ጥያቄ እስከ ጫፍ ሊወስደው ይችላል። ይህም በኦሮሞ ጉዳይ የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና አክቲቪስቶችን የመከፋፈል እድሉ ሰፊ መሆኑ አይቀርም። ህዉሃት እስከ ጫፍ የሚወስደውን ፍላጎት ለመቀበል አዳዲስ ሃይሎች (emerging powers) የሚፈልቁበት ሁኔታ ይፈጠራል። በመሆኑም ህዉሃት በሚቀደው ሀገር የማፍረስ ቦይ የሚፈሱ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሰዎች ይኖራሉ። እንደ እውነቱ ከሆነ ሁለቱ የህዉሃት የቀድሞ ጦር አዛዦች በተለይም ሌ/ጄነራል ፃድቃን ወልቃይትና ሌሎች “የኢፍትሐዊነት ማሳያ” ቦታዎችና “የትግል ማዕከሎች” በተመለከተ ያስቀመጡት ምላሽ ህዝባዊ እምቢተኝነቱን የበለጠ ነዳጅ የሚጨምር ነው። ጄነራል ፃድቃን መጀመሪያ አካባቢ ባቀረባቸው ጽሁፎች በብልጣብልጥነት ሊያልፈው ቢፈልግም ቦታዎች ይበልጥ “የትግሉ ማዕከሎች” መሆናቸውን በህዝባዊ ማዕበሉ ሲመለከት ከድርቅና በተሻገረ አይን አውጣነት ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ እርስ በራስ የተምታታ ምላሽ ሰጠ። ይህ የጦር መኮንኑ ምላሽ የአማራ ህዝብ ትግልና መነቃቃት ከደረሰበት ደረጃ ጋር ፍፁም የማይመጥን ነው። የአሁኑ የአማራ ትግል የደረሰበት ደረጃ ፍልሚያው ተጧጡፎ አድማሱን በመስፋት ቅኝቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀይሯል። ከአስር አመት በፊት ሃሰን ዑመር አብደላ በመጣጥፋቸው እንደገለጡት ቅኝትና ምቱ ከተቀየረ እስክታውም መቀየር አለበት። በመሃመድ አህመድ የትዝታ ቅኝትና ምት ጥላሁን ገሠሠን “አንቺን ነው! ሰማሽ ወይ” የሚለው አይደነስም። በ “እምበር ተጋዳላይ” አጨፋፈር ስልት የይሁኔ “ሰከን በል” አይጨፈርም። እንደዚህ ከሆነ በአራዳ ቋንቋ ሽወዳ ይሆናል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ ደግሞ ውሽልሽል ምክንያት ሸውዶ ማለፍ የሚችልበት ወቅት ላይ አይደለንም። አለበለዚያም እውነት መድፈር ካልተቻለና የሚያስፈራ ከሆነ (ኮንስቲትወንሲያቸውን እንደሚያጡ ይገባኛል) ምላሽ አለመስጠት ይቻል ነበር። ፃድቃን ሊጠቀምበት የፈለገው “የሽወዳ ፖለቲካ” ህዝባዊ እምቢተኝነቱን አቀጣጥሎ መስዋዕትነቱን ከመጨመሩ ባሻገር በሌሎች ያቀረባቸው የመፍትሄ ሃሳቦችም ላይ በጥርጣሬ እንዲታይ ያደረገ ነው። ለማንኛውም ሌ/ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳይ “የትግሉ ማዕከል” በሆነው ወልቃይት ዙሪያ ለአዲስ አድማሱ ጋዜጣ የሰጠውን መግለጫ በመመልከት ፍርዱን እንስጥ። አዲስ አድማስ ጋዜጣ “በሰሜን ጎንደር አካባቢ ያለው ተቃውሞ በተለይ ከ “ወልቃይት አማራነት” ጋር የተያያዘ ነው። የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጉዳይ በምን አግባብ ነው መፈታት ያለበት?” ለሚለው ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቷል። “እኔ የወልቃይት ጉዳይ ለአንዳንድ ፖለቲካዊ አላማዎች ሽፋን ነው ብዬ ነው የማምነው። እንዴት ነው የሚፈታው ላልከው እኔ የሚታየኝ ህገ- መንግስቱን መሠረት አድርጎ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ ይሔ ትልቅ ጉዳይ መደረግ አልነበረበትም። ህዉሃትና ብአኤን ተመካክረው መፍታት የሚችሉበት ደረጃ ላይ መድረስ ነበረባቸው።…. በህጋዊ መንገድ ስንሄድም ህገ-መንግስቱን መሰረት አድርጎ መፍታት ያስፈልጋል ነገር ግን ክልሎች በሚወሰኑበት ወቅት ከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ ሰጪ አካል ውስጥ ነበርኩ። በወቅቱ ቋንቋና የህዝብ አሰፋፈርን መሰረት አድርገን እንወሰን በሚል ነው የወሰነው። በዚህ መሰረት ደግሞ የተወሰነው ተወስኗል።” አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቀጥሎ የጠየቀው “በወቅቱ ወልቃይት እንዴት ነው ወደ ትግራይ የተላከው?” በማለት ነበር። ሌ/ጄነራሉ እንዲህ በማለት አስገራሚ፣ አሳዛኝና እርስ በራሱ የሚደባደብ ምላሽ ሰጠ። “አሁን እየጠየከኝ ያለኸው መረጃ ነው። ይሄን መረጃ አሁን አላስታውሰውም። እንደዚህ ሆኖ ነበር ብዬ ለማለት አልችልም። የተጠቀምንበት አቅጣጫ ግን የፌደራሊዝሙን መነሻ ነው። የህዝቦች ቋንቋና ባህልን መነሻ አድርገን ነው የከለከልነው። እኔ እስከማውቀው ድረስ እዚያ አካባቢ ያለው አብዛኛው ህዝብ ትግርኛ ተናጋሪ ነው። ባህሉ የትግራይ ነው። በትግራይ ውስጥ ሊካተት የሚችል ህዝብ ነው። የሆነውም በዚህ አግባብ ነው።” በመሆኑም እነዚህ የህዉሃት ጦር ጄነራሎች “ህዉሃት አደጋ ላይ መውደቁን ሲያዩ ሊታደጉት መጡ” የሚለውን አባባል ለጊዜው እንተወውና የጎደላቸውን ነገር በጨዋ ቋንቋ እንንገራቸው። ከጄኔራል ፃድቃን አስተያየት ሳልወጣ አድናቆቴን መግለጽ የምፈልግበት አንድ አረፍተ ነገር አለ። ጄኔራሉ በሌሎች የህዉሃት ታጋዮች ባልተለመደ መልኩ አሁን ያለውን ሁኔታ ሲገመግሙ “የትግራይ ህዝብ በተለይም በከተሞች አካባቢ በሌሎች ማህበረሰቦች የመገለል ሁኔታ አጋጥሞታል። መተማመኛውንም የስልጣን የበላይነት አስጠብቆ ማቆየትና በመከላከያና ሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ተከልሎ መኖር” እንደሆነ ገልጧል። ይሄንን ግምገማ ሙሉ በሙሉ የምቀበለው ነው። ለረጅም ጊዜያቶች ይሄ ችግር እየመጣ እንደሆነ ደጋግመን ስንለፈልፍ በህዉሃት ጎራ ያሉ ሰዎች “ዘረኞች” የሚል ታፔላ ተለጥፎልን ነበር። ዛሬ የጦር መኮንኑ በግላጭ ሲያወጣው በህዉሃት መንደር የተፈጠረ ብዙም መንጫጫት አይታይም። ታዲያ! ጄኔራል ፃድቃን በዚህ ጉዳይ ላይ ይሄን ያህል ርቀት መጓዝ ከቻለ ከጥያቄው ጋር አብረው ለሚነሱት ሌሎች ጥያቄዎች ምላሽ ቢሰጥበት እኛንም ከስድብና ውርጅብኝ ያድነናል። ጥያቄው የትግራይ ህዝብ በተለይ በከተሞች ውስጥ በሌላው ማህበረሰብ እየተገለለ መሄዱ እውነት ሆኖ ሲያበቃ፤ የመገለሉ መንስ ኤና መሰረታዊ ምክንያት ምንድነው? መገለሉስ ከመቼ ጀምሮ የተፈጠረ ነው? ተጠያቂው ማነው?…. ወዘተ የሚሉ ናቸው። ይህንን ቁልፍ ጉዳይ መመለስ ከተቻለ ወደ ቁልፍ መፍትሄው የምንሄድበት መንገድ አልጋ በአልግስ ይሆናል። የትግራይ ኤሊቶች፣ የህዉሃት የቀድሞ የጦር ጄኔራሎችም ሆነ የቀድሞ ታጋይ ባላስልጣናት ከህዉሃት በፍጥነት ተፋተው ለአዲስ የስርአት ለውጥ ዝግጁ የማይሆኑባቸው ሌሎች ተጨማሪ መሰረታዊ ምክንያቶች አሏቸው። ከዚህ ውስጥ የቅድሚያ መስመር የምትይዘው ኤርትራ ናት (eriteria-factor)። ህዉሃት ከኢርትራ ጋር የገባበት ጦርነት ፍፃሜ የረጅም ጊዜ የመጠባበቂያ ህልሙን ያጨለመ ነው። ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው ከጦርነቱ በፊት ከኤርትራ መንግስት ጋር ለአመታት የተካሄደው ድርድርም ሆነ የጦርነት ውሳኔ የተወሰነው በህውሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ነው። ወደ ጦርነት ከተገባም በኋላ የመሪነቱን ሚና የጨበጡት ህዉሃቶች ናቸው። በጦርነቱ ምክንያት የአገሪቱ ካዝና በተራገፈና ሙጥጥ ባለ ሰዓት መንግስት ከሶስት ቢሊዮን ብር ያላነሰ የተበደረው ከህዉሃት የኢኮኖሚ ኢምፓወ ከሆነው ኤፈርት (ትእምት) ነበር። ለጦርነቱ የሚሆነውን የጦር መሳሪያ (ታንክ፣ ሮኬት፣ ሚሳየል፣ የውጊያ አውሮፕላኖች……) በየአህጉራቱ የተሽከረከሩ የሚገዙት የህዉሃት አመራሮችና የጦር አዛዦች ናቸው። (በነገራችን ላይ በአውሮፕላን ግዢ ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ከነበራቸው የጦር አዛዦች ግንባር ቀደሙን የሚይዘው የቀድሞ አየር ሃይል አዛዥ የነበረው ሜ/ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት ነው። አበበ የክፍፍሉ መጀመሪያ ወቅት እንቡር እንቡር ቢልም የአንጃዎቹ መጨረሻ ኩምሽሽ አድርጎታል። “አይተነው ጊዜ ወደሚያደላው” አይነት ባህሪ ያለው አበበ ገልብጦ የመለስን ቡድን ይቅርታ ቢጠይቅም የመለስን የቃሪያ ጥፊ ከማግኘት አልታቀበም። ከአዛዥነቱ በንፋስ ፍጥነት ተባረረ። ከዛ በኋላ ጆቦ በሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከኪሱ በማውጣት አሜሪካን ሀገር ተማረ። በትምህርቱም “የአሰብ ኢትዮጵያዊነት” ተገለጠለት። መገለጡ ቀልብ ይስባልና በኢትዮጵያ አየር ሃይል ላይ በተነው። ጆቤ! ዛሬ በወር 150ሺህ ብር የሚከራይ ቪላ አለው። ያውም በአዱገነት እምብርት! ለ100 አመት ይዞ ቢቆይና ከደሞዙ ሰባራ ሳንቲም ባያወጣ አሁን ያለውን ሀብት ሩብ አይኖረውም። እርግጥ ከርቀት እንደሰማነው ባለቤቱ ብቸኛዋ ሴት ጄኔራል ሆናለች።) እዚህ ላይ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ውጤት ለህዉሃት የበላይነት መምጣትና የትግራይ ተጠቃሚነት ዋስትና የፈጠረው አደጋ ለህዉሃት መሰንጠቅ መሰረታዊ ምክንያት ቢሆንም ሌሎች ተጨማሪ ምክንያቶች አሉት። እነዚህ አደጋዎች ከህዉሃት አፈጣጠር፣ የዘረጋው ስርአት ባህሪና ውስጠ- ድርጅት ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው። ህውሃት የበላይነቱን ያረጋገጠባት ኢትዮጵያ ካልቀጠለችና የአገር መበተን ካጋጠመ “የትግራይ ሪፐብሊክ” ነፃ ሀገር ፈጥሮ መኖር እንደ መጨረሻ ግብ ያስቀመጠ ቢሆንም ከኤርትራ ጋር የገባበት ቁርሾና ደም መፋሰስ ይህን ፍላጎቱን ከሞላ ጎደል ዝግ አድርጎታል። eriteria-factor የተባለው አንዱ ገፅታ ይሄ ነው። የጎንደር፣ አፋር፣ ወሎ ህዝብ ከታች ኤርትራ ከላይ ሆነው ትግራይን ሳንድዊች የሚያደርጉበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ከዚህ በኋላ “የትግራይ ሪፐብሊክ” ከህልም የዘለለ አይሆንም። ትግራይን ገንጥለን በሰላም እንኖራለን የሚባል ህልም ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣……ወዘተ ወደ ትግራይ የተከለሉ ሰአትና የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በተነሳ ሰአት ወደ መቃብር ወርዷል። የኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት አጨራረስ በአንድ በኩል ነፃ ሀገር ለመመስረት ህልም የነበረችውን የህዉሃት አመራሮች ወሽመጥ የቆረጠ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ኢትዮጵያዊነቱን አጥብቆ ለሚፈልገው የትግራይ ህዝብ ትልቅ ብስራት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው። በአጭሩ ኢትዮጵያን ወዳድ ለሆነው የትግራይ ህዝብ የጦርነቱ አጨራረስ በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ የሚፈጠር ጥሩ አጋጣሚ ነው። blessing in disguise!! የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አጨራረስ ህዉሃትን ለሁለት ሰንጥቋል የሚባልበት መሰረታዊ ምክንያት ይሄ ነው። የስዬ አብርሃ ቡድን የኢትዮጵያን ህዝብ ሀብትና ደም መከታ አድርጎ ኤርትራ በመደምሰስ አሻንጉሊት መንግስት ለመመስረት ሲያስብ ሌሎች አላማዎችን ለማሳካትም ጭምር ነበር። ህዳጣኑ ህዉሃት ከትግራይ ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ መግዛት ካቃተውና ህዝባዊ ማዕበሉ ካናወጠው ያለ ኤርትራ ስጋት “ነፃ የትግራይ ሪፐብሊክ” መመስረት ይችላል። የስዬ ቡድን ኤርትራ ላይ ለራሱ ተጠሪ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት መመስረት አለመቻሉ በክፉ ጊዜ መጠጊያ የምትሆነውን “ሪፐብሊክ ትግራይ” የመመስረት ራዕይ ተጨናገፈበት። በተለይ በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆቹን በመገብሩ ቁጭት ላይ የወደቀ መሆኑና ከዚህ በኋላ ጋሻነቱ ባከተመበት ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ጦርነት መግጠም ማለት የህዉሃት ፍፃሜ መሆኑ አይቀርም። በሌላ በኩል ጓድ መለስ በስልጣን ለመቆየት ካለው ጥማት በመነሳት ጦርነቱ ሊገፋበት አለመቻሉ እዛው ሳለ የትግራይን ነፃ መንግስት ህልም ባጭሩ የቀጨ ሆኗል። ይህ በመሆኑ ምክንያት በህዉሃት/ኤህአዴግ ህገ-መንግስት ውስጥ የሰፈረው አንቀጽ 39 ከህዉሃትና ትግራይ ህዝብ አኳያ ከወረቀት አንበሳነት የዘለለ አይሆንም። የህዉሃት አፈጣጠር መነሻ የሆነው “የትግራይ ነፃ ሪፐብሊክ” መመስረት እውን ሊሆን የሚችለው ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮች ሲሟሉ ብቻ ነው። አንደኛው ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት….. የመሳሰሉ መሬቶችን ለባለቤታቸው ሲመልሱ ይሆናል። ሁለተኛው ኤርትራ ላይ (eriteria-factor) ዳግም ጦርነት በመክፈትና ኤርትራን ወደ ዳግም ሱማሊያ መውሰድ፤ ከተቻለም ለህዉሃት ተጠሪ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት በመመስረት በተራዘመ ጊዜ በኮንፌደሬሽን መዋሃድ። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሌሎች ቀድሞ በትግራይ ክልል ያልነበሩ ቦታዎች ወደ ቀድሞ ቦታቸው ይመለሳል የሚለው ጥያቄ “በህዉሃት መቃብር” ላይ ብቻ የሚፈፀም ነው። ለዚህም ነው ከየትኛውም የኢትዮጵያ ቦታዎች በበለጠ ሁኔታ እነዚህ አካባቢዎች “የትግሉ ማዕከል” ናቸው የተባለበት ምክንያት። ኤርትራን በጦር ገጥሞ ለህዉሃት ተገዢ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት በአስመራ እናቋቁማለን የሚለውም ፍላጎት ያለቀና የደቀቀ ተደርጎ ባይወሰድም ወደ ዜሮ የቀረበ እድል (probability) ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው። እርግጥ ሌሎች ህዉሃትን ለሁለት የሰነጠቁ እንጭፍጫፊ ምክንያቶች እዚህ ላይ ሊጨመሩ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ እሙን ነው። የህዉሃት የፍጥረቱ የመጨረሻ ግብ ከመኮላሸቱ ጎ ለጎን የዘረጋው ስርአት ባህሪና የውስጠ- ድርጅቱ ሁኔታ ለመሰነጣጠቁ ምክንያት ነው። ህውሃት የዘረጋው ስርአት የፓርቲውን የበላይነትና የትግራይን የተለየ ተጠቃሚነት ዝርፊያ (ሙስና) አንዱ መለያ ባህሪው ነው። መንግስት እንደመሆኑ መጠን ወረራና ዝርፊያው “መንግስታዊ” መሆኑ አይቀርም። “መንግስታዊ ሌብነት”…. “መንግስታዊ ዝርፊያ”…. “መንግስታዊ ሙስና”…. “መንግስታዊ ውንብድና!”…. በመሆኑም የህዉሃት አንዱ መሰረታዊ መለያ ባህሪ በአዋጅ፣ በህግ፣ በመመሪያ የሚፈፅም የቡድን ዝርፊያ (“መንግስታዊ ሙስና”) ነው። ህዉሃት ገና ከጠዋቱ ቁልፍ ቁልፍ የሆኑ የመንግስትና ድርጅታዊ የስልጣን ቦታዎችን በቁጥጥር ስር ያዋለው በዚህ ምክንያት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ውጭ ጉዳይ፣ መከላከያ፣ ደህንነት፣ ፖሊስ፣ ሚዲያ፣ የድርጅት ቢሮ፣ የክልሎች ሞግዚት በመሆን አይናቸውን በጨው ያጠቡት ለዚህ ነው። ይህም ሆኖ የህዉሃት ስርአት በትግራይ ህዝብና ልሂቃን ዘንድ ያለው አረዳድ ከሌላው አካባቢ ጋር ተመሳሳይ አይደለም። አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ ከትግራይ ህዝብ የወጡት ህዉሓቶች በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ፈላጭ ቆራጭ በሆኑበት፤ ገዳዩ አሳሪው ገራፊውና መርማሪው እነሱ በሆኑበት፤ የመንግስት ስልጣንን በመጠቀም ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም በገነቡበት፤ በትግራይ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅና ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እልፍ አእላፍ ፋብሪካና የኢኮኖሚ አውታሮች በተገነቡበት፤ በጠብታ ኢኮኖሚ መልኩ በትግራይ ክልል የተገነቡት፤ መሰረተ ልማቶችና ማህበራዊ ፍትህ ማምጫ ተቋማት….. ወዘተ በፍጥነት ወደ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ሊቀላቀላቸው አይችልም። ራሳችንን ማምሸት ካልፈለግን በስተቀር የትግራይ ህዝብ በህዉሃት አገዛዝና አፈና ተማሮ ሊሆን ይችላል እንጂ “አዲስ ስርአት” ለመቀበል ዝግጁነቱ አይታይም። የህዉሃት አገዛዝ በፓርቲ መዋቅሩ አማካኝነት የሚፈጥረው ጭቆና፣ የዘመድ አዝማድ አድሎአዊ አሰራር፣ ኋላቀርነት፣ “አህያ ቢራገጥ” የሚመስል አይነት ቂም በቀል፣… አሰልቺ ስብሰባዎች እና መዋጮ….. ወዘተ የትግራይን ህዝብ ሊያስመረምረው ይዝል ይሆናል እንጂ ለስር-ነቀል ለውጥ የተዘጋጀ አይደለም። ግፋ ቢል ከአጭር ጊዜ አኳያ “ላም እሳት ወለደች” ከሚለው ብሂል የሚርቅ አይደለም። ይህ የብዙሃኑ የትግራይ ተወላጅ ፍላጎት አድርገን ልንወስደው የምንችል ነው። (ማስታወሻ – ይሄ መጣጥፍ የተዘጋጀው የዛሬ ሁለት አመት ጥቅምት 2016 ነበር። ያቀረብኩት ደግሞበሂውስተን ቴክሳስ ለህዝብ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው። ከአሁኑ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ይሄዳል ብዬ ስላሰብ
83
እቺ ልጅ ዜናውን ያገኘችበትን ምንጭም አብራ ጠቅሳለች፡፡ ከዜናው መረዳት እንደሚቻለው የዶናልድ ትራምፕ የውልደት ስሙ ዳውድ ኢብራሂም ካህን መሆኑን ነው፡፡ አበሻ ስለሆንኩ ጠርጥር እንዳትመነጠር በሚል መርህ አምናለሁ፡፡ ቅቅቅቅ፡፡
84
ይህ ሰው እነ ሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያምን ከሐረር ወደ አዲስ አበባ ያስመጣቸው፣ ደርግን የመሠረተውን የበታች መኮንኖች ጉባዔ በሊቀመንበርነት የመራ፣ የአፄው ሥርዓት ከናካቴው ለመገርሰስ ግንባር ቀደም ሚና የተጫወተ፣ በታጠቅ ጦር ሠፈር የሕዝባዊ ሚሊሺያ ማሠልጠኛ ዋና አዛዥ፣ እንዲሁም ኢትዮጵያን ቀደም ሲል በኤርትራ ጉዳይ ባነሱት ተቃውሞ በቤታቸው እንዳሉ በታንክ ተጨፍልቀው ከተገደሉት ከጄ/ል አማን ሚካኤል አንዶም ጋር፣ በመቀጠል ደግሞ በቤተመንግሥት ቢሮአቸው ባሉበት በመትረየስ ተኩስ እንዲገደሉ ከተደረጉት ከሊቀመንበሩ ከጄ/ል ተፈሪ ባንቲ ጋር ሀገሪቱን እንዲመሩ ከተመረጡ ሁለት የወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ምክትል ሊቃነመናብርት አንዱ በመሆን (ከሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያም ጋር) ሀገሪቱን በተከታታይ በምክትል ሊቀመንበርነት ያስተዳደረ በአንድ ወቅት ከፍተኛ የሀገር አደራን ተሸክሞ ያለፈ ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው ኢምፔሪያሊስት ተብለው ከተፈረጁት ሀገሮች ከአሜሪካ እና ከምዕራብ አውሮፓ ሃገራት ጋር በርዕዮተ-ዓለም የተመሠረተ ፀባችንን ትተን ለብሔራዊ ጥቅማችን ስንል የትብብር ወዳጅነት መፍጠር አለብን ብሎ ሽንጡን ገትሮ በደርግ ጉባዔ ላይ የተከራከረ፣ የኤርትራ ጉዳይ ከወታደራዊ አማራጭ ጎን ለጎን ሠላማዊ አማራጮች አብሮ ማፈላለጉ አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው በሚል አቋሙ የሚታወቅ፣ የሃገራችንን የኢኮኖሚ ፖሊሲ ልንነድፍ የሚገባን ‹‹የሦሻሊስት ኢኮኖሚ›› በሚል የርዕዮተ ዓለም ደጋፊነትና አቀንቃኝነት ሣይሆን… ሃገራችንና ሕዝባችን የሚገኙበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ያለፍንበትን ታሪካዊ እውነታ፣ እና ከዓለም ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አዋህደን መሆን ይገባዋል፣ በኢትዮጵያ ልናሰፍን የሚገባን የኢኮኖሚ ፖሊሲ.. አንዳንድ መሠረታዊ ነገሮችን መንግሥት የሚቆጣጠርበትና የሚመራበት.. ሌሎችን ደግሞ ለግለሰቦችና ለባለሃብቶች የሚለቅበት ቅይጥ የኢኮኖሚ ሥርዓት ነው በማለት በቃል ብቻ ሣይሆን ጥናቱንና አቋሙን በጽሑፍ በዝርዝር ገልጾ ለደርግ ጉባዔ ለክርክር ያቀረበ አስገራሚ ምሁራዊነትን የተላበሰ ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው ከኢህአፓ እና ከሌሎች ደርግን የሚቃወሙ የታጠቁም ሆነ ያልታጠቁ ኃይሎችና አብዮታዊ ፓርቲዎች ጋር.. እነሱም ሆኑ እኛ ሁላችንም የዚህች ሃገር ዜጎች እስከሆንን ድረስ.. ማናችንም በብቸኝነት ባለቤትነት የምንይዘውና የምናስፈጽመው የበላይና የበታች ሃሳብ ሊኖር አይገባውም… የሁላችንም ሃሳብ በነፃ ተንሸራሽሮ መታየት አለበት… እነ ኢህአፓም ሆኑ ሌሎች እናምንበታለን የሚሉትን አጀንዳና ሃሳብ ያምጡና.. በጋራ ተወያይተን.. በጋራ የሚያግባባንንና ለሃገራችን የሚበጃትን መንገድ ቀይሰን.. ልዩነቶቻችን ሳያጫርሱን በጋራ በሚያግባቡን ጉዳዮች… ደጋፊዎቻችንን አሠልፈን ለሃገር ዕድገት በጋራ ልንሠራ.. በጋራ ልንቆም ይገባናል እንጂ… እንደ ውጪ ጠላት ተያይተን… ልንዋጋቸው እና እርስ በእርስ ልንጨራረስ አይገባንም… ዞሮ ዞሮ የሚያልቀው የገበሬው የጭቁኑ ልጅ ነውና.. ብሎ… እጅግ በሚያስገርም ድፍረት… የደርግን የግራ አክራሪ ጉባዔተኞች… ሽንጡን ገትሮ የተከራከረ ልበ-ሙሉና ለወገን የሚያስብ ቅን አሳቢ አዕምሮ ከውስጡ ያልጠፋበት ገራም ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ይህ ሰው…. እና በተለይም በእነዚህ የመጨረሻዎቹ ሁለቱ አቋሞቹ የተነሣ… አብዮቱን የሚጻረሩና የሚሸረሽሩ በሚል በደርጉ ጉባዔ ፊት 12 ክሶች፣ እና ከአድኃሪያን ጎራ ጋር አጋርነትን በማሳየትና አብዮቱን ከሚጠሉ የውጪ ቅጥረኞች ጋር በመገናኘት በሚሉ 5 ክሶች… በአጠቃላይ 17 ክሶች ተነብበውበት (አብዮቱን ለባዕዳንና ለፀረ-ሕዝብ ድርጅቶች አሣልፎ የሰጠ፣ ወላዋይ አድኃሪ መስመርን የሚሰብክ፣ በጭቁኑ የኢትዮጵያ ሕዝብና ባቀጣጠለው አብዮት ላይ ዕምነት የሌለው፣ ለጭቁኑ ሕዝብና ለበታች መኮንኖች ትምክህትን የሚያሣይ፣ የደርግን ምስጢር ለሲ አይ ኤ አሣልፎ የሰጠ፣ አብዮቱን የሚቀለብስ የቅስቀሳ ንግግር በማድረግ፣ ወዘተ ወዘተ በሚል..) በቀድሞ ባልደረባውና ራሱ ወደ አዲስ አበባ ባስመጣው፣ አብረውም ንጉሡንና ባለሥልጣኖቻቸውን ከሥልጣን አውርደው ሲረሽኑ በነበሩት በገዛ ጓደኛው በሌ/ኮ/ል መንግሥቱ ኃይለማርያም ተላልፎ ተሰጥቶ… በደርጉ አባላት ክሱ ተዘጋጅቶ፣ በደርጉ ጉባዔ ፊት ክሱ ተሰምቶ፣ በራሱ በደርጉ ጉባዔ በክሶቹ ጥፋተኛ ነው ተብሎ በድምፅ ተወስኖበት፣ በውሳኔውም መሠረት በፈጸመው ‹‹አብዮቱንና ሀገሩን የመክዳት ወንጀል›› በሚል በራሱ በደርግ የሞት ፍርድ የተፈረደበት፣ በመጨረሻም በራሱ በደርጉ ትዕዛዝ በፍርዱ መሠረት የሚወዳቸውን እንኳ የመሠናበት ዕድል ሣያገኝ… ወዲያውኑ የሞት ቅጣት እንዲፈጸምበት የተደረገ… አብዮቱን አዋልዶ፣ ከአብዮቱ ተወልዶ፣ በመጨረሻም በአብዮት የተሰለቀጠ… አብዮት የገዛ ልጆቿን በላች እየተባለ ታሪኩ ሲነገርለት የሚኖር አሳዛኝ የጭቁን መለዮ ለባሾች አብዮተኛ ነው፡፡ ይህ ሰው… በሆለታ ገነት የወታደራዊ አካዳሚ ሠልጥኖ ከተመረቀባት ወቅት አንስቶ.. በምድር ጦር እና በአየር ኃይል.. ይህችን ሀገር እና ይለፍላቸው ያላላቸውን የዚህችን ሀገር ብቃዮች… በምድር በሠማይ ሲያገለግልና ሲከላከልላት.. ብሎም ለህዝብ የጠቀመ መስሎት (ወይም መሆኑን አምኖ) ‹‹ጠላቶቿ›› ካላቸው ጋር ሲዋደቅላት ኖሮ… በመጨረሻ ለሀገሩና ለወገኑ ለዋለው ውለታ… የህይወት ዘመን ብድራቱን… አሣዛኝ የሞት ዋጋ ተከፍሎት… በምድር የሚወዳትን የልጅነት ባለቤቱን ወይዘሮ አስናቀች ከበደን… ከነስድስት ልጆቹ ያለቤሳቤስቲን ትቶ ያለፈ አስገራሚ ትራጀዲያዊ ፍፃሜን ያደረገ ይህችን ሀገር በጭንቅ ቀኗ አለሁልሽ ብሎ በልበሙሉነት የቆመ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው፡፡ የኮ/ል አጥናፉ አባተ… ልጆች 1ኛ) ሳምሶን አጥናፉ፣ 2ኛ) ቴዎድሮስ አጥናፉ፣ 3ኛ) ሱራፌል አጥናፉ፣ 4ኛ) ጌታሁን አጥናፉ፣ 5ኛ) ሰለሞን አጥናፉና 6ኛ) መክብብ አጥናፉ… ናቸው፡፡ ይህ ሰው… ባልተረጋጋ ሀገርና አብዮት ውስጥ፣ ወገን እርስ በርሱ የሽብር ጎራ ለይቶ በሚፋጅበት የአብዮት ወላፈን ውስጥ… ትክክል ነው ብሎ ባመነበት ጎራ… እና በብዙ ትግልና ውጣ ውረድ ውስጥ አልፎ…. ከፋችም ለማችም… የታገለለትንና የቆመላትን.. እና ግን ትሩፋቷ እንደጉም የበነነበትን ይህችን ምስኪን ሀገሩን ከጭቁኑ ሕዝብ እና ርህራሄ ከሌለው የአብዮት ማዕበል ጋር ትቶ… ራሱ ‹‹ሀ›› ብሎ ባቋቋመው የደርግ ጉባዔ… የርሸና ትዕዛዝ መሠረት በገዛ የሥራ ባልደረቦቹና ጓዶቹ ተበልቶ… በህዳር 3 ቀን 1970 ዓ.ም. በተወለደ በ47 ዓመቱ… የኢትዮጵያን ምድር.. በማይመለስበት የሞት መንገድ.. እስከወዲያኛው የተሰናበተ… የ66ቱ አብዮት ዋና ጠንሣሽ፣ ዋና ተዋናይና ግንባር-ቀደም መሪ… እና አሣዛኝ የሞት ባለተራ…ይህ ሰው… ክቡር ኮሎኔል አጥናፉ አባተ.. ከነቤተሰቦቹ እንዲህ ማስታወሻውን ለታሪክ ጥሎልን አለፈ፡፡ ሞት ለማንም አይቀርም፡፡ ሁሉም ሰው ‹‹አለ›› ከመባል ወደ ‹‹ነበር›› መሸጋገሩ አይቀርም፡፡ ‹‹ሀ›› ብሎ ከበቀለባት ምድር… ‹‹ፐ›› ብሎ የመጨረሻ ትንፋሹን ጨርሶ መመለሱም አይቀርም፡፡ ህይወት ያለው ሁሉ ሞት አብሮት አለ፡፡ ሞት ለማንም አይቀርም፡፡ ነገር ግን እንዲህ እንደ ኮ/ል አጥናፉ አባተ.. ላመነበት ሀገራዊ አቋም… በሞት መንጋጋ ውስጥ እንኳ ቢሆን… ለህይወት መሥዋዕትነት ጭምር… ደረቱን በግላጭ ሰጥቶ በመቆም… ልጆቹ ቀና ብለው የሚራመዱበትን አኩሪ ታሪክ ትቶ ማለፍ ግን.. በህይወት ዘመን ከምንመላለሰው መሐከል… ለጥቂቶች ብቻ የተሰጠ… ልዩ ፀጋ ነው፡፡ በመሆኑም ነው.. ከሰው ሁሉ መሐል ነጥለን… በሞት ከእኛ በአካል ቢለዩም… ከታሪካችን የማትለይ ስማቸውን ግን… ስለሠሯት በጎ ነገር ስንል.. እንዲህ ደግመን የምናነሳቸው፣ የምናወሳቸው፡፡ አምላክ ለሀገራቸው ሲሉ… ለወገናቸው ሲሉ… በሞት ሸለቆ ውስጥ እንኳን ሆነው.. የታያቸውን የተስፋ ጭላንጭል ለሕዝባቸው አመላክተው… እነርሱ ግን አስከፊ ሞትን የሞቱትን ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ሁሉ… ለሥጋቸው ዕረፍትን፣ ለነፍሳቸው ሠላምን፣ ስለበጎ ነገራቸውም መወሳትን አይንፈጋቸው፡፡ አምላክ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ሁሉ አብዝቶ ይባርክ፡፡ እምዬ ኢትዮጵያ – በልጆቿ መተሳሰብ፣ በወገኖቿ መተዛዘን፣ በሕዝቦቿ መፋቀር፣ በትውልዶቿ ታላቅ ራዕይ – በጋራ በልጽጋ፣ አብባ፣ ደምቃ፣ ለምልማ… በደስታ፣ በሠላም፣ በትፍስህት – ለዘለዓለም ትኑር፡፡
85
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት “አዲስ ነገር ጋዜጣን” መክሰሱ ተሰማ። ከግንቦት 2001 ዓ.ም እስከ ሐምሌ አጋማሽ ድረስ በቅዱስ ፓትርያርኩና በቅ/ሲኖዶሱ መካከል የተፈጠረውን ውጥረትና አለመግባባት ስትዘግብ የነበረችው ሳምንታዊ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ታምራት ነገራ እና ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው ሪፖርተር አብርሃም በጊዜው በፖሊስ ተጠርተው የቀረቡት አዲስ አበባ ፖሊስ (አራዳ ክ/ከተማ) ሲሆን ቃላቸውን ሰጥተው በዋስ መለቀቃቸው ታውቋል። የቅዱስ ፓትርያርኩን ስምና ክብር በማጉደፍ፣ በሐሰት ስማቸውን በማጥፋት እንዲሁም ሐሰተኛ ዜና በማቅረብ የተከሰሱት ጋዘጤኞቹ የምርመራ መዝገባቸው ወደ አቃቤ ሕግ ከተላከ በሁዋላ የሚያስከስሳቸው ሆኖ ከተገኘ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል። ጋዜጠኛ አብርሃም ይህንኑ ዘግቦ ሲመለስ ባልታወቁ ሰዎች መደብደቡን መዘገባችን ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ “ደጀ ሰላም”፣ ቪኦኤና አንዳንድ የሀገር ውስጥ ጋዜጦች ከጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ጋር የሚቃረን ሥራ ሠርተዋል፣ የቤተ ክርስቲያንን ክብር አዋርደዋል ሲሉ አንድ የቤተ ክህነት ባለስልጣን ተናገሩ። ባለስልጣኑ መጋቤ ካህናት ኃ/ሥላሴ ዘማርያም “መሰናዘሪያ” ከተሰኘ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሚዲያዎቹን ከወቀሱ በሁዋላ በዚህ ጉዳይ አሉበት የተባሉትን ብፁዕ አቡነ ሳሙኤልን “ተሳስተዋል” ማለታቸው ታውቋል። መጋቤ ካህናት ኃ/ሥላሴ ወደ ካህናት አስተዳደር ከመምጣታቸው በፊት በድሬዳዋ ሀ/ስብከትና በቤቶች አስተዳደር የሰሩ ሲሆን በተለይም በቤቶች አስተዳደር ውስጥ በሚሰሩበት ወቅት የቤተ ክርስቲያኒቱን ቤቶች ቁልፍ በመሸጥ ሀብት ያካበቱ “የማፊያው ቡድን” አባልና “ሙሰኛ (ኮራፕት)” መሆናቸው ይነገራል። በዚህ ምግባራቸው ይታወቁ እንጂ ማንም ደፍሮ የማይናገራቸው በትግሉ ዘመን መሳሪያ አንስተው ከተዋጉትና ስልጣን በኢሕአዴግ እጅ ከገባ በሁዋላም ቀደም ብሎ በትግራይ የሰሩ ነባር ታጋይ በመሆናቸው ሳይሆን አይቀርም ተብሏል።
86
አዲስ አበባ, ህዳር 25 ቀን 2001 (አዲስ አበባ) - የሕዝብ ቆጠራ ኮሚሽን የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 73 ሚልዮን 918 ሺህ 505 መድረሱን ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት አስታወቀ፡፡ የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አዲሱ ለገሠ ለሕዝብ ተወካዮች ምከር ቤት ያቀረቡትን የሕዝብ ብዛት ሪፖርት ምክር ቤቱ በ278 ድጋፍ፣ በ61 ተቃውሞ እና በ16 ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ተቀብሎ አጽድቆታል፡፡ ግንቦት 20 ቀን 1999 እና ህዳር 20 ቀን 2000 ዓ. ም በተካሄዱ የሕዝብ ቆጠራዎች መሠረት ከአገሪቱ ሕዝብ 62 ሚልዮን የሚሆነው በገጠር የሚኖር ሲሆን ቀሪው 12 ሚልዮን የሚጠጋው ሕዝብ የከተማ ነዋሪ ነው፡፡ በሕዝብ ቆጠራው መረጃ መሰረት ከ33 ሚልዮን የሚበልጡት እድሜያቸው ከ14 አመት በታች፣ ከ37 ሚሊዮን በላይ የሆኑት ከ15 እስከ 59 አመት ቀሪዎቹ እድሜያቸው ከ60 አመት በላይ መሆኑን ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ አጠቃላይ የክርስትና እምነት ተከታዮች ቁጥር ከ46 ነጥብ 4 ሚልዮን የሚበልጥ ሲሆን የእስልምና ተከታዮች ቁጥር ከ25 ሚልዮን በላይ መሆኑንና ሌሎች ሃይማኖቶችና እምነቶችን የሚከተሉ ደግሞ ከ2 ነጥብ 4 ሚልዮን በላይ እንደሆኑ ተብራርቷል፡፡ የክልሎች የሕዝብ ብዛት ሲታይም የኦሮሚያ ሕዝብ ቁጥር ከ27 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ፣ የአማራ ከ17 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ከ15 ሚልዮን በላይ፣ የሶማሌ ከ4 ነጥብ 4 ሚልዮን በላይ፣ የትግራይ ከ4 ነጥብ 3 ሚልዮን በላይ፣ የአዲስ አበባ ከ2 ነጥብ 7 ሚልዮን በላይ፣ የአፋር ከ1 ነጥብ 4 ሚልዮን በላይ እንደሆነ ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሕዝብ ቁጥር 671 ሺህ እንደሚጠጋ፣ የድሬዳዋ 343 ሺህ እንደሚሆን፣ የጋምቤላ 307 ሺህ እንደሚጠጋና የሐረሪ ሕዝብ ቁጥር ከ183 ሺህ በላይ መድረሱን የቆጠራው ውጤት ጠቁሟል፡፡ ለተካሄደው የሕዝብ ቆጠራ ከ356 ነጥብ 3 ሚልዮን ብር በላይ ተመድቦ እንደነበርና ከዚህ ውስጥም በሶማሌና አፋር ክልል ለተካሄደው የሕዝብ ቆጠራ 78 ነጥብ 6 ሚልዮን ብር ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቅላይ ሚኒስትር አዲሱ ገልጸዋል፡፡ የቆጠራው ውጤት ከመውጣቱ በፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው መንገድ የመረጃው ትከክለኛነት መገምገሙንና የማይጣጣሙ መረጃዎች በተገኙ ጊዜ ሙያው በሚፈቅደው ደረጃና መመሪያ መሰረት አሰፈላጊው እርማት መከናወኑን አቶ አዲሱ ገልጸዋል፡፡ በዛሬው እለት ለምክር ቤቱ አባላት በቀረበው የሕዝብ ቆጠራ ሪፖርት ላይ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የኢህአዴግ አባላት እና ደጋፊዎች የተለያዩ ሃሳቦችን አቅርበው ውይይት አካሂደውበታል፡፡ ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶችም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አዲሱ ለገሠ እና የማእከላዊ እስታትስቲክስ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳሚያ ዘካሪያ ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ የአማራና የአዲስ አበባ ሕዝብ ብዛት ከተተነበየው በታች በከፍተኛ ልዩነት በመቀነሱ በኢሕአዴግ የፓርላማ አባላት ጭምር ጥያቄ አስነስቷል፡፡ የአማራ ክልልን ቆጠራ ዳግም የመፈተሽ ሥራ እንዲካሄድ ተወስኗል፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ቆጠራ ኮሚሽን የ1999/2000 የህዝብ ቆጠራ ሥራ አፈፃፀም እና የቆጠራውን የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት አስመልክቶ ሐሙስ እለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት በግንቦት 1999 የተገኘው የአማራ ህዝብ ብዛት ከትንበያው ጋር ሲወዳደር በአንፃራዊነት ዝቅተኛ ሆኖ መገኘቱን ይገልፃል፡፡ ተቃዋሚዎችና አንዳንድ የኢህአዴግ አባላት ግን የአማራ ክልል የህዝብ ዕድገት ምጣኔ ከሌሎች ክልሎችና ከአገር አቀፍ ማነሱ የኮሚሽኑን አሰራር እንዲጠይቁ ያደረጋቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በ1999 ከተከናወነው የህዝብ ቆጠራ በፊት የአገር አቀፍና ክልሎች የህዝብ ብዛት ትንበያ የተካሄደ መሆኑን በኮሚሽኑ ሪፖርት የተገለፀ ሲሆን፣ በቆጠራውና በትንበያው መካከል ከፍተኛ ልዩነት የታየው በአማራ ክልልና በአዲስ አበባ በቻ ነው፡፡ የአማራ ክልል ህዝብ ብዛት 19 ሚሊዮን 624 ሺ ይሆናል ተብሎ የተተነበየ ቢሆንም በቆጠራው የተገኘው ግን 17 ሚሊዮን 214 ሺ 56 ነው፡፡ በትንበያውና በቆጠራው መካከል ያለው ልዩነትም 2 ሚሊዮን 409 ሺ 944 ሆኗል፡፡ አዲስ አባ በበኩሏ የህዝብ ብዛቷ 2 ሚሊዮን 738 ሺ 248 ይደርሳል ተብሎ ቢተነበይም ከተተነበየው በ320ሺ 752 አንሶ በቆጠራ የተገኘው የህዝብ ብዛት 2 ሚሊዮን 112ሺ 737 ሆኗል፡፡ ግንቦት 20 ቀን 1999 ዓ.ም እና ኅዳር 20 ቀን 2000 ዓ.ም በተደረገው ቆጠራ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 73 ሚሊዮን 918 ሺ 505 መድረሱን የህዝብ ቆጠራ ኮሚሽን ሪፖርት ያመለክታል፡፡ በ1976 ዓ.ም በተካሄደው የህዝብ ቆጠራ 42 ሚሊዮን 616 ሺ 876 የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት በ1987 በተካሄደው ቆጠራ በ11 ሚሊዮን ጨምሮ 53 ሚሊዮን 477ሺ 265 ደርሶ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከ12 ዓመት በኋላ በተካሄደ ቆጠራ የህዝብ ብዛቱ በ20.4 ሚሊዮን ጨምሯል፡፡ በአሁኑ ቆጠራ የጾታ ስብጥር ሲታይ የሴትና የወንድ ቁጥር በጣም ተቀራራቢ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ የወንድ በዛት 37 ሚሊዮን 296 ሺ 657 (50.5 በመቶኛ) የሴት ደግሞ 36 ሚሊዮን 621ሺ 448 (49.5 በመቶኛ) መሆኑን የህዝብ ቆጠራ ውጤቱ አመልክቷል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ግን የሴቶች ቁጥር ከወንዶች ጋር ሲነፃፀር ከ2 በመቶ ያላነሰ ብልጫ አሳይቷል ተብሏል፡፡ ከአገሪቱ 73,918,505 ሕዝብ ውስጥ አጠቃላይ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች 46,421,740 (62.8 በመቶ) ሲሆን በተናጠል ኦርቶዶክስ 32,138,126 (43.5 በመቶ)፣ ፕሮቴስታንት 13,746,787 (18.6 በመቶ)፣ ካቶሊክ 536,827 (0.7 በመቶ) የእምነቱ ተከታይቶች እንዳላቸው ታውቋል፡፡ የእስልምና ተከታዮች ደግሞ 25,0455,50 (33.9 በመቶ) እንደሆነ የቆጠራው ውጤት ያመለክታል፡፡ ባህላዊና ሌሎች ሃይማኖቶችን የሚከተሉት በአንድ ላይ ሲጠቃለሉ 24,298,05 (3.3 በመቶ) መሆናቸውን የቆጠራው ውጤት አሳይቷል፡፡ የ1999 የቆጠራ ውጤት ከ1987 ጋር ሲወዳደር ደግሞ የአጠቃላይ የክርስትና ሃይማኖት ድርሻ በ1.2 በመቶ ሲጨምር የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ደግሞ 1.1 በመቶ መጨመሩን የቆጠራው ውጤት ጥንቅር ያመለክታል፡፡ ለአጠቃላይ የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ድርሻ መጨመር ከፍተኛውን አስተዋጽኦ ያደረገው ደግሞ የፕሮቴስታንት ሃይማኖት በ8.4 በመቶ መጨመር መሆኑን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ በሪፖርቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት ወ/ሮ ብርቱካን የተባሉ የኢህአዴግ አባል በአማራ ክልል ህዝብ ብዛት ላይ የተሰጠው ትንበያና በቆጠራው በተገኘው ውጤት መካከል ያለው ልዩነት 2.4 ሚሊዮን ሆኖ እያለ በ፣አንፃራዊነት፣ መባሉ ትክክል አለመሆኑን ገልፀዋል፡፡ በአማራ ክልል ያለ ዕድሜ ጋብቻ የሚታይበት መሆኑንና የክልሉ የገጠር አካባቢም ብዙ በመውለድ የሚታወቅ መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ ብርቱካን እርሳቸውን ወክሎ የላካቸው ህዝብ በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተቀይሮ የወሊድ መጠኑ ይቀንሳል የሚል እምነት እንደሌላቸው በመግለጽ የቆጠራውን ውጤት እንደሚጠራጠሩት ተናግረዋል፡፡ የድጋሜ ቆጠራ ሊካሄድ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡ የኢዴአፓ-መድህን ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው በበኩላቸው በአገር አቀፍ ደረጃ በቆጠራው የተገኘው ውጤት በ3 ሚሊዮን አንሶ መገኘቱ የኮሚሽኑን ሪፖርት ጥርጣሬ ውስጥ እንደሚከተው ገልፀው በተለይም አዲስ አበባ ላይ በ1976 ዓ.ም 3.0 የነበረው የልደት ምጣኔ በ1999 ዓ.ም 1.3 መሆኑ የማይታመን ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ “ስህተት ሆን ተብሎ ይሰራል ብለን አንገምትም” ያሉት አቶ ልደቱ በአማራ ክልል የታየው የ2.4 ሚሊዮን ልዩነት ከእውነታው የተራራቀ መሆኑን ጠቁመው የአንድ ክልል ህዝብ ቁጥሩ ከተቀነሰ በበጀት በውክልናና በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ተጽዕኖ የሚፈጥር በመሆኑ በአሰራር ላይ ስህተት ካለ በደንብ ተጣርቶ የሚቀርብበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠይቀዋል፡፡ አቶ መሀመድ አሊ በበኩላቸው የአንዳንድ ክልሎች የህዝብ ብዛት ዕድገት መጠን 4.1 ሆኖ እያለ የአማራ ክልል 1.7 ብቻ መሆኑ ሪፖርቱን ተቀባይነት እንደሚያሳጣው ገልፀዋል፡፡ አያይዘውም የክርስትና ሃይማኖት እድገት መጠን 1.2 ሆኖ የወሊድ ቁጥጥርን የማያበረታታውና አንድ ወንድ ከአንድ ሴት በላይ ማግባት የሚቻልበት የእስልምና ሃይማኖት ግን 1.1 ብቻ ማደጉ ከእውነታው ጋር የሚቃረን መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ አንድ ሌላ የአጋር ድርጅቶች የፓርላማ አባልም እንደዚሁ በእስልምና ሃይማኖት አንድ ወንድ ከአንድ ሴት በላይ ማግባት እንደሚቻልና እርሳቸውም አራት ሚስቶች እንዳሏቸው እንደምሳሌ በመጥቀስ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ከክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ማነስ እንዳልተዋጠላቸው ተናግረዋል፡፡ ከፖርላማ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሰ በአማራ ክልልና በአዲስ አበባ ከተማ የህዝብ ዕድገት አመታዊ ምጣኔ ከሌሎች ክልሎች አንሶ መገኘቱ ከታወቀ በኋላ እንደገና ፍተሻ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡ አቶ አዲሱ እንዳሉት ለትንበያው መነሻ የሆኑትን የልደት መጠን እና ዓመታዊ የህዝብ ዕድገት መጠን ዝርዝር እንደገና በማየትና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በናሙና በተመረጡ የቆጠራ ቦታዎች የድህረ ቆጠራ ሥራ በማከናወን የሽፋን ችግር አለመከሰቱ ተረጋግጧል፡፡ ቆጠራ በመስክ የተከናወነው በክልሎች በኩል በተመረጡ መምህራን መሆኑንና እያንዳንዱ ወረዳና ቀበሌ ሥራ በትክክል መከናወኑን የክልሉ ኮሚሽን ማረጋገጡን የገለፁት ም/ጠ/ሚኒስትሩ በቆጠራው ወቅት የሽፋን ክፍተት /ቤተሰቦችንና አባላትን የመዝለል ሁኔታ/ ተከስቶ እንደሆነ ለማጣራት በተደረገው የድህረ ቆጠራ በክልሉ ውጤቱን ሊያስቀይር የሚችል የሽፋን ክፍተት እንደሌለ መታወቁን አስረድተዋል፡፡ ካለፈው ቆጠራ ወዲህ የአማራ ክልል ህዝብ ወደ ተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በመፍለሱ ምክንያት በትንበያው ተጽዕኖ ይኖረው እንደሆነ በማለት የተደረገው ፍተሻም የተለየ ውጤት አለማስገኘቱን በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ በትንበያውና በቆጠራው መካከል ልዩነት የተከሰተበትን ምክንያት ለማወቅ ችግሩን ከስርመሰረቱ መፍታት እንደሚያስፈልግ የገለፁት አቶ አዲሱ እስካሁን ባለው ሂደት ግን በአማራ ህዝብ ብዛት ላይ ልዩነት እንዴት እንደተከሰተ ለማወቅ የተደረሰበት ውጤት የሚያረካ ሆኖ እንዳልተገኘ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባ ህዝብ ብዛት ሊቀንስ የቻለው ግን ቀን ቀን ከተማ የሚውለው ህዝብ ማታ ማታ ከአዲስ አበባ ወጥቶ የሚያድረው ህዝብ በመጨመሩ ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል፡፡ የአዲስ አበባ አጎራባች የሆነችው የቡራዩ ከተማ ህዝብ ብዛት ከ10ሺ ወደ 80ሺ መጨመሩም ለዚህ አይነተኛ ምሳሌ እንደሚሆን አቶ አዲሱ ገልፀዋል፡፡
87
(ደጀ ሰላም፤ ሰፕቴምበር 20/2010፤ መስከረም 10/2003 ዓ.ም):- ለካህናት እና ምእመናን ያላቸውን ንቀት እና አነስተኛ አባታዊ ክብር በተደጋጋሚ በማሳየት የሚታወቁት የሲዳማ፣ ጌዲኦ፣ አማሮ እና ቡርጂ ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፋኑኤል ሀገረ ስብከቱን ለመምራት ባለባቸው ከፍተኛ የብቃት ማነስ እና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገረ ስብከቱ እየተባባሱ ለመጡት ውዝግቦች መንሥኤ በመሆናቸው ከሐላፊነታቸው እንዲነሡ የሐዋሳ ከተማ ምእመናን ጠየቁ፡፡ ምእመናኑ ከሊቀ ጳጳሱ በተጨማሪ በእርሳቸው አቅራቢነት ከፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት በተጻፈ ደብዳቤ በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙት መልአከ ኀይል አባ ገብረ ጊዮርጊስ አብርሃም ከደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪነት ሐላፊነታቸው እንዲወገዱ ጠይቀዋል፤ ይህንኑ ጥያቄ ለሚመለከታቸው የመንግሥት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አካላት አቅርበው እና ተከታትለው የሚያስፈጽሙ የምእመናን ተወካዮችንም መርጠዋል፡፡ ምእመናኑ ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት በትናንትናው ዕለት እሑድ፣ መስከረም ዘጠኝ ቀን 2003 ዓ.ም ጠዋት የሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳምን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በቃለ ዓዋዲው ከተመለከተው ውጭ በአቡነ ፋኑኤል ቀጥተኛ ትእዛዝ በተጠቆሙ አስመራጭ ኮሚቴዎች እና በደንቡ ከተደነገገው የምርጫ ሥነ ሥርዐት በተፃራሪ ምርጫውን ለማስፈጸም የተደረገውን ሙከራ ባከሸፉበት ወቅት ነው፡፡ ቀደም ሲል ሊቀ ጳጳሱ በክልሉ የፍትሕ፣ ጸጥታ እና አስተዳደር ጉዳዮች ቢሮ ሐላፊዎች ፊት ተንበርክከው ይቅርታ በመጠየቅ የገዳሙን ሰበካ ጉባኤ ምርጫ የሰበካው መታወቂያ ያላቸው(የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ በተወጡ) የአጥቢያው ምእመናን ብቻ ተሳታፊ በሚሆኑበት መልኩ በአግባቡ በመፈጸም ዕርቅ እና ሰላም ለማውረድ ቃል ገብተው እንደ ነበር ተዘግቧል፡፡ የሰበካ ጉባኤው አባላት የሆኑ የፍትሕ እና ልማት ኮሚቴ ሽማግሌዎች ባለፈው ሳምንት ዓርብ አቡነ ፋኑኤል ይህን የዕርቀ ሰላም ስምምነታቸውን በማክበር የሰበካ ጉባኤ ግዴታቸውን ያልተወጡ የእርሳቸው ፈቃድ ፈጻሚዎች እና የማፊያ ቡድኑ አባላት የሆኑ ግለሰቦች በምርጫው ላይ እንዲሳተፉ ከማድረግ እንዲታቀቡ ተማፅነዋቸው ነበር፡፡ ይሁንና ከሀገረ አሜሪካ ኑሯቸው ጀምሮ አምና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን አስተዳደር ለማሻሻል እስከተደረገው የውስጥ ትግል ድረስ ባላቸው መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ግንኙነት(አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት አስመልክቶ በኦፌሴል ከተናገሩት ፖሊቲካዊ አቋም ፍጹም ተቃራኒ የሆነ እምነት በማራመድ ጭምር) በቃላቸው ባለማደር የሚታወቁት ሊቀ ጳጳሱ፣ ‹‹እናንተ የእነርሱ መሳተፍ ተገቢ አይደለም የምትሉትን ያህል ሌሎቹ ደግሞ ተገቢ ነው የሚሉበት ሁኔታ አለ፤ የምርጫውን ሂደት በተመለከተ ተቃውሟችሁን እዚያው ማሰማት ትችላላችሁ›› በማለት የዕርቀ ሰላም ስምምነቱን የሚሽር፣ አለመግባባቱን የጠብ መሣሪያ እና የወገናዊነት ማሳያ የሚያደርግ ምላሽ ሰጥተዋቸዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት ጠዋት ለ‹አስመራጮቹ› ምርጫው የሚካሄድበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ተቃውሟቸውን የሚገልጹ የምእመናን ተወካዮችን በእነ ያሬድ አደመ እና በጋሻው ደሳለኝ የተደራጁ የሊቀ ጳጳሱ ደጋፊዎች ለመደብደብ እና ሁከት ለመቀስቀስ ሲጋበዙ የነበረ ቢሆንም ቀደም ብሎ የሁኔታውን ውጥረት የተረዳው የከተማው አስተዳደር ያዘጋጃቸው የጸጥታ ኀይሎች ከምእመናኑ ጋራ በመተባበር ፍጥጫውን አረጋግተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ውይይቱ በመግባባት ቀጥሎ የምእመናን ተወካዮች የሆኑ የአገር ሽማግሌዎች ለተሰብሳቢው ተገቢውን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ማብራሪያውን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች የተሰጡ ቢሆንም አብዛኞቹ ሐሳቦች ያተኮሩት እና ጠንክረው የወጡት ግን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፋኑኤል እስከ አሁን በሀገረ ስብከቱ ለሚነሡት ውዝግቦች መንሥኤ እንደሆኑ እና በጊዜ ቆይታም ከአንድ ብፁዕ አባት በሚጠበቅ መልኩ ሀገረ ስብከቱን በመንፈሳዊ ልዕልና እና ሁሉንም በሚያስማማ ተጨባጭ አስተዳደራዊ ክሂል ለመምራት ያላቸው ችሎታ አጠያያቂ እንደ ሆነ መረጋገጡን የተመለከቱ ነበሩ፡፡ አቡነ ፋኑኤል በአዲስ አበባ ከአንድም ሁለት(አንዱ ቪላ ‹የሐዋሳ መንበረ ጵጵስና› እስከ መባል ደርሷል) ቪላዎችን ያሠሩ፣ አንዱን ቪላቸውን እስከ 25‚000 ብር ድረስ የሚያከራዩ፣ ይህም አልበቃ ብሏቸው በሀገረ ስብከታቸው ሥር በሚገኙ ወረዳዎች ከሥራ አስኪያጁ መልአከ ሕይወት ፀሐይ መልአኩ ጋራ ሲዘዋወሩ በስጦታ በሚቀርብላቸው ሳይሆን በቃላቸው ትእዛዝ ቅቤ እና ማር አዘውትረው የሚያስጭኑ፣ ለቤተ ክርስቲያን ቀናዒ ከሆኑ ካህናት፣ ሊቃውንት እና ወጣቶች ጋራ ከመሥራት ይልቅ ማንኛውንም ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም ፈቃደኛ የሆኑ ማፊያዎችን የመሰብሰብ እና ከእነርሱም ጋራ የመሥራት ልማድ ያላቸው እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፡፡ ከእርሳቸውም ጋራ በዐውደ ምሕረቱ እንዳይቆም የተከለከለውን እና አቡነ ፋኑኤልም ከክልሉ ባለሥልጣናት በተደረገ ውይይት የተስማሙበትን የያሬድ አደመን እግድ ማስፈጸም የተሳናቸው የገዳሙ አስተዳዳሪም መልአከ ኀይል አባ ጊዮርጊስ አብርሃም ለሁከቱ ምክንያት በመሆናቸው እሳቸውም ከሐላፊነታቸው እንዲነሡ ተጠይቋል፡፡ በመሆኑም ምእመናኑ ለሀገረ ስብከቱ መንፈሳዊ አገልግሎት ዕድገት እና ለልማቱ መጠናከር ሲባል የሊቀ ጳጳሱ እና እርሳቸው በሕገ ወጥ መንገድ እንዲሾሙ ያደረጓቸው የታላቁ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪ ከሐላፊነታቸው እንዲነሡ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ በመጨረሻም ይህንኑ ጥያቄዎቻቸውን ለሚመለከታቸው የመንግሥት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አካላት በማቅረብ የሚያስፈጽሙላቸውን ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ስብሰባውን አጠናቅቀዋል፡፡ ስለዚህም በአገልግሎት ላይ ያለውን የሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ደንብ(ቃለ ዓዋዲ) እና በገዳሙ የውስጥ አስተዳደር ከተደነገገው ውጭ ከሀገረ ስብከቱ በተላከ ግለሰብ በተጠቆሙ አስመራጮች ለማካሄድ ታቅዶ የነበረው ምርጫ በገዳሙ አጥቢያ ነዋሪ በሆኑ ምእመናን እና በምእመናኑ በተመረጡ የፍትሕ እና ልማት ኮሚቴ አባላት በገጠመው ጠንካራ ተቃውሞ ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በ1965 ዓ.ም በወጣ ዐዋጅ በካህናት እና ምእመናን ኅብረት በሰበካ ጉባኤ እንድትደራጅ የተደረገው በአስተዳደር፣ በፍትሕ መንፈሳዊ፣ በአገልግሎት እና በምጣኔ ሀብት በኩል በራሷ ሕግ እና ሥርዐት በመመራት እና በመደራጀት እንድትሠራ ለማድረግ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከአንድ ሳምንት በፊት በአቡነ ፋኑኤል በተሰጣቸው ትእዛዝ ከሀገረ ስብከቱ የተላኩት የሰበካ ጉባኤ መምሪያ ሐላፊ ቀሲስ አማረ በገዳሙ አስተዳደር የማይታወቅ የተድበሰበሰ ሪፖርት በሰበካ ጉባኤው ምክትል ሊቀ መንበር አማካይነት እንዲቀርብ ካስደረጉ በኋላ ራሳቸው በዐውደ ምሕረቱ ቆመው ከምእመኑ መካከል ቀድመው ያዘጋጇቸውን ሦስት ግለሰቦች በድርጅታዊ አሠራር እንዲጠቆሙ በማድረግ አስመራጭ ኮሚቴ ሠይመዋል፡፡ በቃለ ዓዋዲው አንቀጽ ስምንት ንኡስ አንቀጽ 1 - 5 እና አንቀጽ ዘጠኝ በተዘረዘረው መሠረት የሰበካውን የምርጫ ሥነ ሥርዐት የሚያስፈጽሙት ከሰበካው ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ቀበሌዎች የተውጣጡ ካህናት፣ ምእመናን እና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የሚገኙበት ከአምስት ያላነሱ ከዐሥራ አምስት ያልበለጡ ሆነው በካህናት፣ መነኮሳት እና ምእመናን ምልዓተ ጉባኤ በመሠየም ነው፡፡ እኒህ የምልዓተ ጉባኤው ሥዩማን የአስመራጭ ኮሚቴ አባላት በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታቸው የታወቁ፣ በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው ተመዝግበው የሚገባቸውን አስተዋፅኦ የተወጡ፣ በመንፈሳዊነታቸው፣ በግብረ ገብነታቸው እና በአስተዋይነታቸው የታወቁ እንዲሁም በሕገ ቤተ ክርስቲያን የጸኑ መሆን እንደሚኖርባቸው በዚሁ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ ሦስት እና አራት ላይ ተገልጧል፡፡ ይህን ለማስፈጸም ምርጫው ከመካሄዱ በፊት በሰበካው ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ወይም ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት አማካይነት ለአጥቢያው ካህናት እና ምእመናን ትምህርት እና ቅስቀሳ መደረግ እንደሚኖርበት፣ ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው በቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እንደሚመራ፣ ጉባኤውም ሕግንና ሥርዐትን ተከትሎ እርስ በርስ በመፈቃቀር፣ በስምምነት፣ በሰላም እና በጸጥታ መፈጸም እና ማስፈጸም እንደሚያስፈልገው፣ ድምፅ የሚሰጥባቸውን ጉዳዮችንም በድምፅ ብልጫ መወሰን እንደሚገባው በንኡስ አንቀጽ አንድ እና ሁለት ላይ ያዝዛል፡፡ ከዚህም ባሻገር በዚሁ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ አምስት እና አንቀጽ 11 ንኡስ አንቀጽ ሦስት መሠረት አዲስ የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ከመካሄዱ ከአንድ ወር በፊት በሥራ ላይ የነበረው የሰበካው አስተዳደር ጉባኤ በአገልግሎት ዘመኑ የፈጸማቸውን እና ያስፈጸማቸውን እንዲሁም በዕቅድ የያዛቸውን ተግባራት አጠቃላይ የሥራ እና የፋይናንስ ሪፖርት ለካህናት እና ምእመናን ምልዓተ ጉባኤ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ በቃለ ዓዋዲው አንቀጽ 11 ንኡስ አንቀጽ አንድ መሠረት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በአጥቢያው ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመውን ምርጫ የሚያጸደቀው፣ የሚያሻሽለው ወይም የሚሽረው በወረዳ ቤተ ክህነቱ አማካይነት ውጤቱ ከቀረበለት አልያም የምርጫው አፈጻጸም ትክክል ሆኖ ሳያገኘው ሲቀር ጉዳዩን በአስተዳደር ጉባኤ ከተመለከተው በኋላ ነው፡፡ ከአንድ ሳምንት በፊት በነበረው እሑድ በሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የሆነው እና የታየው ግን ከዚህ የቃለ ዓዋዲው ደንብ ቢያንስ ገሚሱን እንኳን ያሟላ አልነበረም፡፡ አቡነ ፋኑኤል ከእሑዱ የይስሙላ ትዕይንት በፊት የምርጫ አስፈጻሚዎችን በቀጥታ ልከው የነበረ ሲሆን በምእመኑ ከፍተኛ ተቃውሞ ሕገ ወጥ ተልእኴቸውን ሳያሳኩ መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ከዚህ ትምህርት ያልወሰዱት ሊቀ ጳጳሱ የገዳሙ አጥቢያ ካህናት እና ምእመናን ምልዓተ ጉባኤ ሳይደረግ፣ የምርጫው መካሄድ ታውቆ በቂ ቅስቅሳ እና ትምህርት ሳይሰጥ፣ በሥራ ላይ ያለው ሰበካ ጉባኤ በኀባር የመከረበት የክንውን እና ዕቅድ ሪፖርት ሳይቀርብ፣ በሕገ ወጥ መንገድ ከተሾሙት የገዳሙ አስተዳዳሪ እና ከሰንበት ት/ቤቱ አመራር ጋራ በተያያዘ የተፈጠሩት ችግሮች ተፈትተው የእርስ በርስ ስምምነት፣ ሰላም እና ጸጥታ መስፈኑ ሳይረጋገጥ የሀገረ ስብከቱን ሰበካ ጉባኤ መምሪያ ልኡክ በድንገት በመስደድ ቀድመው ለአስመራጭነት ልከዋቸው የነበሩትን ሦስት ግለሰቦች በቡድናዊ አሠራር እንዲጠቆሙ፣ የተጠቆሙት ግለሰቦች ከኦርቶዶክሳዊነታቸው፣ የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ ከመወጣታቸው፣ ከመንፈሳዊነታቸው፣ ግብረ ገባዊነታቸው እና ሞያዊ ብቃታቸው አኳያ የድጋፍ እና ተቃውሞ አስተያየት ሳይደመጥባቸው የቃለ ዓዋዲውን ቃል እና መንፈስ ፈጽሞ በተፃረረ አኳኋን የአስመራጭ ኮሚቴ ተብዬዎች ‹‹ምርጫ›› እንዲካሄድ አድርገዋል፡፡ ሁኔታውን የበለጠ አሳፋሪ የሚያደርገው ደግሞ በዚህ የአስመራጭ ኮሚቴ ተብዬዎች ‹‹ምርጫ›› የተጠቆሙት ሦስት ግለሰቦች ቀደም ሲል በሊቀ ጳጳሱ ተልከው ምእመኑ የተቃወማቸው መሆናቸው እንደ ሆነ የሰበካው ምእመናን ለደጀ ሰላም አስረድተዋል፡፡ በዕለቱ ለቅዳሴ በገዳሙ የተገኙት ምእመናን እና የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች የአስመራጭ ኮሚቴ ተብዬው ‹‹ምርጫ›› ሂደት ሕጋዊ አለመሆኑን ቢቃወሙም ሰሚ እንዳላገኙ በስፍራው የነበሩ ደጀ ሰላማውያን ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ይህ ውዝግብ በታላቁ የሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሲፈጠር በአዲስ አበባ የተቀመጡት አቡነ ፋኑኤል ከሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ጋራ ቀደም ሲል በሐዋሳ ከተማ ምእመናን ተወካዮች እንዲሁም በገዳሙ ሰበካ ጉባኤና ልማት ኮሚቴ አባላት የቀረበባቸውን የአስተዳደራዊ በደል እና ምዝበራ አቤቱታ እንዲያጣራ በመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የተሠየመውን አጣሪ ኮሚቴ ተግባር የሚያስናክሉበትን መንገድ በመፈለግ ላይ ነበሩ፡፡ ሊቀ ጳጳሱ የሐዋሳ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን አንዳንድ አስተዳዳሪዎች ወደ መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ድረስ እንዲመጡ በማዘዝ፣ ‹‹ዕርቅ ፈጥረናል፤ ተስማምተናል፤ አጣሪ ኮሚቴው ይቅር›› ለማሰኘት ሞክረዋል፡፡ ‹‹ዕርቅ ፈጥረናል›› የተባለው ሊቀ ጳጳሱ በክልሉ የአስተዳደር እና ጸጥታ ጉዳዮች ቢሮ ትእዛዝ በባለሥልጣናቱ ፊት ተንበርክከው የበደሏቸውን የምእመናን እና ካህናት ወገኖች ይቅርታ የጠየቁበትን አጋጣሚ ነው፡፡ ይሁንና ይህ ይቅርታ በአባት እና ልጅ መንፈሳዊ ዝምድና የተደረገ በመሆኑ ያለው ዋጋ እንደተጠበቀ ሆኖ በተጨባጭ የተፈጸመው አስተዳደራዊ በደል ደግሞ በአግባቡ ተጣርቶ ሊታወቅ እንደሚገባ አቋማቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ሊቀ ጳጳሱ በዘመን መለወጫ ማግሥት ቃሊቲ በሚገኘው ቪላቸው ፓትርያሪኩን ጨምሮ ለቋሚ ሲኖዶስ እና አንዳንድ የአጣሪ ኮሚቴውን አባላት ምሳ መጋበዛቸው ተሰምቷል፡፡ ይህ የአቡኑ ‹የማግባባት› እና ረብ የለሽ የሕዝብ ግንኙነት ምስነት የማጣራት ሂደቱን እንዳያስተጓጉለው የፍትሕ እና ልማት ኮሚቴው አባላት ያደረባቸውን ስጋት ተናግረዋል፡፡
88
አቶ ምትኩ በድርቅ በተመታች ሃገር ቅስፈታዊ የጎርፍ አደጋ የተከሰተበትን ምክንያት አብራርተዋል። ፖል ሃንድሊ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች የኦቻ ክፍል ሃላፊንም ለጎርፍ አደጋ አስቸኳይ ምላሽ የሚደረገውን ጥረት አብራርተውልናል። በምእራብ ወለጋ ጨሊያ ከተማ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ትላንት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና የአካባቢዉ ህዝብ ባደረጉት ሰልፍ ላይ አንድ ተማሪ መገደሉ ሌላ በጽኑ መቁሰሉና ታዉቋል። ትላንት በጨሊያ ከተማ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችና የአካባቢዉ ዜጎች የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ባካሄዱት ሰልፍ ላይ አንድ ተማሪ መገደሉና ሌላዉ በጽኑ መቁሰሉን ለደህነነቴ እስጋለሁ በማለት ስማቸዉ አንዳገለጥ የጠየቁ ነዋሪ በስልክ ለአፋን ኦሮሞ ባልደረባችን ናሞ ሳንዲ ገልጸዋል። የኦሮሚያ ፖሊሶችና አድማ በታኞች በጅምላ ህዝብ ላይ ከፍተዉ በርካታ ተማሪዎች ቆስለዋል ከፓሊሶቹ ሽሽት ጫካ የገቡም አሉ ብለዋል። የታሰሩ ተማሪዎችን ስም ዘርዝረዉ ቁጥራቸዉና ማንነታቸዉ ገና ያልተለዬ ሌሎችም መታሰራቸዉን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ፓሊስ ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ምክትል ኮሚሽነር እና የኮሚኒኬሽንስ ጉዳዮች ሃላፊ ሰለሞን ታደሰ በከተማዋ ሕዝባዊ ተቃዉሞ እንደነበርና ተኩስ ከያቅጣጫዉ ይሰማ እንደነበር ገልጸዉ፥ ተማሪዉ ከማን በተተኮሶ ጥይት እንደሞት እያጣራን ነዉ ብለዋል። በዛሬዉ እለት ሰላምና መረጋጋት በከተማዉ ስፍኗል ሲሉ ለአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ባልደረባችን ነሞ ዳንዲ ገልጸዋል። ትዝታ በላቸዉ በአማርኛ ያቀርበችዉን ዘገባ ፋይሉን በመጫን ያድምጡ።
89
ኣብ መብዛሕትኡ ኣብ ዲያስፖራ ዝነጥፍ ናይ ኤርትራ ተቃዉሞ፡ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዝጸንሔ ኩነተ-ኲናት፡ ብሰላማዊ ኣጋባብ ንክፍታሕ ምርጫ ዘይብሉ ከም ቀንዲ ፖሎቲካዊ መርገጺና ኮይኑ ጸኒሑ’ዩ። እዚ መርገጺ’ዚ ገሊኦም ንይምሰል፡ ገሊኦም ድማ ካብ ማሕበራዊ ስነ-ኣእሙራዊ እምነትናን መትከላትና ዝነቀለ ዝብልዎ ዝነበሩ ስለዝኾነ፡ ሕጂ ነቲ ግርጭት ኩነተ-ኲናት ብሰላማዊ ኣጋባብ ንምፍትሑ መስርሕ- ኣፈፌት ሰላም ኣብ ዝተኸፍተሉ፡ ብፍላይ እቶም ብመትከል ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዝጸንሔ ኩነተ-ኲናት፡ ብሰላማዊ ኣጋባብ ንክፍታሕ ዝኣሙኑ ዝነበሩ፡ ዝጸንሖም መትከላዊ እምነት ብዝተፈላለዩ ምኽንያታት ብምፍራኽ ዝቅይረሉ ወይ ዝፋኹሰሉ ምኽንያታት ክህሉ ዶ ምስተገብኤ? እቲ ጉዳይ ግን “ኣነ ዶ ካይሕዛ ነዊት፡ ንስኺ ዶ ካይትበልዒ ሸዊት፡ ሓቢርና መስከረም ንመዉት’ዩ” ዝመስል ዘሎ። “ዶብና ክሕንጸጽ ወይ ድማ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ን ዘለዎም ምስሕሓብ ክፍታሕ፡ ከም ቅድመ ኩነት፡ ብህዝቢ ዝተወከለ ዲሞክራስያዊ ስርዓት ክህሉ ኣለዎ ይብሃል ኣሎ”። ግርም! እዚ ኣባሃህላ’ዚ ንህልኽ ድዩ ወይስ ኣድማሳዊ ሓቕታት ዝሓዘለ’ዩ? ዶባት ኤርትራ ዶ፡ ንሕና ወይ ብኣና ዝተወከለ ስርዓት ዝተኸለለ ድዩ? ብገዛእቲ ኣብ መንጎ ጥልያን እንግሊዝ ፈረንሳን መነሊክን (ኢትዮጵያ) ብዝተበጽሔ ስምምዓት ዶ ኣይኮነን ተሓንጺጹ? እዞም ሓይልታት እዚኦም ንሕና ዝመረጽናዮም ድዮም ነይሮም? ብሓፈሻ ዶባት ሃገራት ዓለም ብፍላይ ድማ ዶባት ሃገራት ኣፍሪቃ በቲ ኣብ 1960 ብወሳኔ ቁጽሪ 1514 ዝልለ ናይ ሕቡራት ሃገራት ዓለም/ባይቶ ጸጥታ፡ ጉዙኣት ሃገራት ኣፍሪቃ ካብ ገዛእተን ናጻ ክወጻን መግዝእታዊ ዶባት ድማ ከምዝነበሮ ዶባት ሃገራት ንክኸዉን ወሰነ። ብኡ መሰረት ድማ መብዛሕትኣን ሃገራት ኣፍሪቃ ናጽነተንን ልዕላዉነተን (independence and sovereignty) ኣዋጃ። ቀጺሉ ዉድብ ኣፍሪቃዊ ሓድነት (oau) ድሕሪ ኣብ 25 ግንቦት 1963 ኣብ ኣዲስ ኣበባ ምምስራቱ፡ ኣብ ቀዳማይ ኣኼቡኡ ኣብ ካይሮ ብ 1964 ነቲ ዉሳኔ ባይቶ ጸጥታ ንዶባት ኣፍሪቃ ኣመልኪቱ ዝዎሰኖ ዉሳኔ ብምልኣት ኣጽዲቁዎ እዩ። እቲ መግዛእታዊ ዶባት ሃገራት፡ ብዘይ ዝኾነ ለዉጢ፡ ከምዝነበሮ ኣብ ትሕቲ መግዛእቲ እንከሎ፡ ክቕጽል ኣብ ዓለምለኻዊ መድረኽ ተኣዊጁ’ዩ። ቡኡ መሰረት ድማ ከም ናጻን ልዕላዉያን ሃገራት ተፈልጣ። እዚ ኣፍልጦ’ዚ ብዓለምለካዊ ሕጊ ኣዛራርባ፡ ኩለን ጉዙኣት ዝነበራ ሃገራት፡ ማዕረ እተን ገዛእተን ብታሪኽ ዝተፈጥራ ሃገራት ሉዑላዉያን ሙኻነን ስለዝተራጋገጸ፡ ምስሕሓብ ዶባት ክህሉ እንኮሎ በዚ መሰረት ጥራይ’ዩ ዝዳኔ። ሓቂ’ዩ ብህዝቢ ዝተወከለ ስርዓት ድሌታትን ረብሓታትን ህዝቢ ዘቀድምን ነባሪ ሰላም ከራጋግጽ ከምዝኽእል ዘሳሓሕብ ርእይቶ ኣይኮነን። የግዳስ ኤርትራዉያን ባዕልና ነቲ “ብህዝቢ ዘይተመርጸ” ስርዓት ንብሎ ክንቕይሮ ስለዘይክኣልና ግን ህዝቢ ኤርትራ ጅሆ ናይ ኣይሰላይ ኣይኪናት ክኸዉን ኣለዎ ማለት ድዩ? ብህዝቢ ዘይተመርጸ ስርዓት ንብሎ ሃገራዊን ህዝባዊን ረብሓታትና ንሓደጋ ክየሳጥሕ ምሕላዉን፡ ከምኡ ዓይነት ዝንባሌታት ከም ተርእዮ ኣብ ዝጋሃደሉ ብትሪ ምቕዋም ከዲሊ’ዩ። ኣድማሳዊ ፖሎቲካዊ ተቀባልነት ዘይብሉ ማሕበረሰብ ዓለም እዉን ንኽትግበር ዘፍቕድ ኣይመስለኒን እዩ። ስለዚ ኩቡራት ኤውርትራዉያን ኣሓተይን ኣሕዋተይን፡ እዚ ሕጂ ተጋሂዱ ዘሎ ተርእዮ ክመጽእ ሙኻኑ እኮ፡ ዘይግመት ጉዳይ ኣይነበረን። የግዳስ ቁምነገር ካይንገብር ስለዝሓንገድና ታሪኽ ይድገም ኣሎ። ሕጂ ኸ እንታይ ክንገብር ኢና? ካብዝሓለፈ ተሞክሮና ገምጊምና ንሕጽረታትናን ጉድለታትና ገምጊምና ንቃለስ ዶ ዋላ ንህልኽ ክንቃየቕ ጥራይ ክነብር ኢና? ዳግመ ግምገማ ከድልየና’ዩ። ስርዓተ ህ.ግ.ደ.ፍ ዝዘርኦ’ዩ ዝዓጽድ ዘሎ። ዘይዘራእካዮ ምህርቲ ኣይሕፈስን’ዩ። ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ብፍላይ ኣንጻር ወያኔ ብሓፈሻ ኣንጻር ኢህወደግ፡ ሓይልታት ምክልኻል ኤርትራ ዘይዓጠቕዎ ዕጥቂ ብምዕጣቕ። ዘይተመገብዎ መግቢን መስተን ብምቕራብን፡ ዘይለበስዎ ልብሲ ብምልባስ፡ ምስ ኩሎም ተቃወምቲ ኢትዮጵያዉያን ክሳብ ናጽነትን ልዕላዉነትን ኤርትራ ዘይኣሙኑ ሓይልታት እዉን እንተኾነ ምስኣቶም ብምሕባር ክቃለሶም ጸኒሑ’ዩ። ዓስቢ ኣሳላልፍኡን ኣበርክትኡን ድማ ሕጂ ምህርቱ ይሓፍስ ኣሎ። ኣብ ዉሽጢ እዚ ዝሓለፈ 20 ዓመታት ስርዓተ ህ.ግ.ደ.ፍ ብኩቱር ዓለምለኻዊ ተነጽሎ፡ ማዕቀብን ኣግእዞ-ሰብኣዊ መሰላት ጸምሉዩ ኣይንላዕሊ ኣይንታሕቲ ተሰሪሑሉ ዝነበረ ወቕቲ ንሕና ተቃዉሞ ኣብ ዲያስፖራ እንነጥፍ፡ ኣብ ከመይ ናይ ሓሸዉየ ጽምዶታት ከምዝነበርና ረሲዕኩሞ ዲኹም? ስለዚ ዓወታት ክንሓፍስ ይድለ እንተሃልዩ ተኮዲጭካ ብመልሓስካ ሃለዉሎው ክትብል ናይ ዝዉዓልካን ዝሓደርካን ስለዘይኮነ። ብዕትበት ኣብ ዑቱብ ጽምዶታት ክንቃለስ በዚ ኣጋጣሚ ይጽዉዕ ኣለኹ። ልዕሊ ኩሉ ብሓፈሻ ኣሜሪካ፡ ሱዑድ-ዓረብያን ኢማራት ኣልዓረብ ረብሓታቶም እዮም ዘቀድሙ፡ ከምኡ እዉን ብፍላይ ድማ ዶክተር ኣቢ ኣሕመድ ዓሊ መራሒ ናይ ሃገር ኢትዮጵያን ህዝቢ ኢትዮጵያን ኮይኑ፡ ረብሓታት ሃገር ኢትዮጵያን ንምርግጋጽ’ዩ ዝጥዓዓሞ ኣብ ኤርትራ እንተሃልዩ፡ ዋላ ምስ ሰይጣን ስምምዕ ክገብር ድሉዉ ክኸዉን ከምዝኽእል ዶ ኣይትግሙቱን ኢኹም? ስለምንታይን እንታይ ስለዘለኩም ንዓኹም ክሰምዓኩም ኣለዎ ኢልኩም ትግምቱ? ንኢልና በልና ላኪን ማኪን እንተኾይኑ ኣምላኽ ይሓግዝ! ኩላህና ክንግምቶ ከም እንኽእል፡ ኣብ ሕምርቲ ፖሎቲካዊ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ልዕለይን ልዕሊ ካልኦት ንሕና ኢና “ሃገራዉያን” ዝብሉ ሃገራዉያን ከምዘለዉ ዘካትዕ ኣይኮነን። ንዝሓለፈ 20 ዓመታት ሃገሮም ኣብ ሓደጋ ካይትወድቆም ካብ ዝብል ጉሩሁን ፍቅሪ-ሃገር ዝደረኾ ሓቦን ንሒን፡ ዉልቃዊ መሰላቶም፡ ሕቶ ጊዝኣተ ሕጊ፡ ሕቶ ዲሞክራሲ ….ወ.ዘ.ተ ካልኣዊ ብምስራዕ፡ ንዝዓበየ ዕላማ ንምዕዋት፡ ማለት “ናጽነትን ሉዑላዉነትን” ኤርትራ መታን ክዉሓስ ካብ ምባል ዝነቅል ድንግል-ሓልዮት፡ ብሓያል ትዕግስትን ምጽማም መዓንጥኦም ሸጥ ኣቢሎም ክምክቱ ጸኒሖም እዮም፡፡ ኩሉ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ካብኣቶም ዝጠልቦ ዝነበረ ፋይናንሳዊ ነገራዊን ካብ ኣፎሙን ኣፍ ደቆምን መንጢሎም እንዳመጠዉ ክሳልይዎን ብዘይ ቅድመ-ኩነታት ሞራላዊን ፖሎቲካዊን ደገፍ ክድግፍዎ ከምዝጸንሑ፡ ንሶም ይፈልጡ ንሕና እዉን ንፈልጦ ጉዳይ’ዩ። ን16 ዓመታት መመላእታ “ሰራዊት ኢትዮጵያ ካብ ሉዑላዊ መሬትና ካይወጸ ብፍጹም ኣብ ዘተ ኣይንኣቱን ኢና። ካብ መሬትና እንተወጽዩ ግን ንግሆ ዝወጸ፡ ድሕሪ ቀትሪ ንክንዛተ ድልዎት ኢና” ብምባል ይናጣጠፉ ከምዝነበረ ኩላህና ንፈልጦ ጉዳይ ኮይኑ፡ ካብዚ ዝነቐለ እዉን ስዓብቲ ህ.ግ.ደ.ፍ ቀጻሊ ይዳጋግምዎ ከምዝነበሩ ጥራይ ዘይኮነስ፡ ኣንካይ ዶ ንሶም ሓደ ሓደ ተቃወምቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ኣብ ደገ ዝነብሩ እዉን እንተኾኑ፡ነዚ ሓርግ እዚ ከም መጽረዪ ልሳኖም ኣግኣዚ-ኣቦጊዳ ብምዉሳድ ብቀጻልነት ይዳጋገም ከምዝነበረ ኩሉ ዝፍለልጦ’ዩ። ጥልመትን መራሕቲ ህ.ግ.ደ.ፍን ሰብን ጽላሎቱን ስለዝኾኑን፡ ከምቲ ወዲ ድሙ ነይሓድግ ግብረ እሙ ዝብሃል፡ ነቲ ን16 ዓመታት መመላእታ ዝዝረበሉ ዝነበረ ፖሊሲን መትከልን ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ራሕሪሑ ኣብ ዘተን ስምምዕን ክኣቱ ዝተዓዘቡ ኣባላቱ ደንጽዎም ኣፎም ከምዝዕበሱ ኮይኖም ኣለዉ። ክሳብ ሕጂ እዉን ብወግዒ ዝተዋህቦም መግለጺን ምምኽኻርን ኣብ ዉሽጢ ሃገር ይኹን ኣብ ደገ የሎን። ምዝንባዕን ምድንጋርን ከም ኣመል ስለዝተወስደ ናይ ኣጉል-ብድዔ ዘረባ “”ሕጂ ንሕና ኢና ንቀርኒ-ኣፍሪቃ ክንመርሓ ” ክብሉ ጀሚሮም ኣለዎ። ን3,200,000 ዝግምገም ብዝሒ ህዝቢ ኤርትራ ከማሕዱሩ ዘይክኣሉስ፡ ንቀርኒ-ኣፍሪቃ ክመርሑ? እዚ ሕልሚ እዚ ነቲ ቀንዲ ሕቶ ዶብን ሕቶ ሉዕላዉነት ካይልዓል ዝመጽእ ዘሎ መሀዉተቲ ዘረባ ስለዝኾነ፡ ኣቱም ኣብ ዉሽጢ ህ.ግ.ደ.ፍ ዘለኹም ሙዑታት ሃገራዉያንን ዲሞክራስያዉያን ባእታታ፡ ዝሓለፈ 20 ዓመታት ይኣክል! ይኣክል ይኣክል ማለት’ዩ ብምባል ክትብድህዎ ትጽቢት ይግበረልኩም ኣሎ። ካብ ዝሓለፈ ተሞክሮና ክንማሃር ኣሎና። ኣብ ንሃገራዊ ናጽነትን ሰብኣዊ ሓርነትን ንምርግጋጽ ዝሳላሰልናዮ 30 ዓመታት ዕጥቃዊ ሰላማዊን ፖሎቲካዊ ቃልሲ፡ ተጋዳላይ “ምእንቲ ሞጎጎ ትሕለፍ ኣንጭዋ” እንዳበለ፡ እቲ ዝዓበየ ዕላማ መታን ክዕወት እቲ መሳለጢ ንዋት ሰዉራና ኣብ ሓደጋ መታን ካይወድቕ ተባሂሉ፡ ነታ ኣንጭዋ ቀጠልያ ናይ ሕለፍ ፍቃድ ስለዝሃባ’ዩ ኣብ ዚ ኩሉ ዝሓለፍናዮን ዘሎናዮን መከራ ከምንሳጣሕ ኬና ዘሎና። ሕጂ ድማ ከም ቅድሚ ትማሊን ትማሊን ዝሓለፍናዮ ተሞክሮ ንደግም እንቴኼና ሃየንታ ክህሉዎ ሙኻኑ ዘጣራጥር ኣይኮነን። ደቂ-ኣንስትዮ ኤሪትራ ብዲሞግራፊያዊ ብዝሔን 57% ዝግምገማ፡ ብተሳትፍኦንን ዲሞግራፊያዊ ጸጋታተን ሙዑሩይን ዑዙዙን ግደ ክህልወን ኣንዳተገበኤ ከንሱ፡ ተራኣን ግን ባይታ ዝዘበጠ ጨፍሉቕ ኢዩ። ኣብ ልዕሊ’ቲ ከም ሰበን ዘጓንፈን ደርባዉን መግዛእታዊ ጭቆናን ሕሰምን፡ ኣባታዊ ሕብረተሰብኣዊን በጋሚዳዊ ባህርያት ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ኣብ ንዝኸፍኤ ሓደጋታት ኣቃሊዕወን ይርከብ ኣሎ። ዋላ እዉን ኣንጻር ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ዝተሰለፉ ሓይልታት እንተኾኑ’ዉን፡ ብተግባር ውሑዳት ሓዲካ መብዛሕትኦም፡ ካብቲ ኣባታዊ ኣታሓሳስባ ሓራ ዝወጹ ስለዘይኮኑ፡ ንደቂ-ኣንስትዮ ከምዚ ንዕዳጋ ዝተቀረባ ሃለኽቲ ነገራት ገይሮም ስለዝወስድወን፡ ከም መሳርሒ ንዋት ክጥቀሙለን ዘይፍሕርዎ ጉድጓድን ዘይፍትንዎ ነገራት የሎን። ኮይኑ ግን ናጻ ዝኾነ ናይ ገዛእ-ርእሳ ማሕበር፡ ከም ዋልታን ጭማራን ኮይኑ፡ ዉሑስነት ዝኾና፡ ቅድሚ ዝኾነ ይኹን ናይ ሓባር ስራሓት፡ ጓል-ኣንስተይቲ ነዚ ናይ ገዛእ-ርእሳ ናጻ ማሕበር ኣብ ምዱካን ክትጽመድ ኣለዋ። ከምኡ ስለዝኾነ ኢና ሲቪክ ዲሞክራስያዊ ምንቅስቓስ ኤሪትራ “ቀንዲ ሲቪክ መትከላትና ኣብ ፖሎቲካዊ ራእይና፣ ማሕበራዊ ፈልስታት ናይ ሲቪክ ሃገርን ሕብረተሰብን ኤርትራ ካብ ሕጂ ኣትሒዘን ክቦቕላን ክነጥፋን እዩ። እዘን ናጻ ደሞክራስያውያን ሃገራውያን ማሕበራት፣ ማሕበር ሰራሕተኛታት፣ ማሕበር መንእሰያት፣ ማሕበር ደቂ- ኣንስትዮ፣ ማሕበር ሓረስቶት፣ ማሕበር ስንኩላን፣ ማሕበር ሓርበኛታት … ወዘተ ይጠቓልል። ናጻ ሲቪላዊ ትካላትን ኣካላትን፣ ማሕበር ኩሉ ዓይነት ሞያ፣ ማሕበር ጋዜጠኛታት፣ ማሕበር ተጣበቕቲ ሰብኣዊ መሰላት፣ ማሕበር ሓካይም፣ ማሕበር ናይ ሕጊ ኪኢላታት/ ጠበቓታት/ ማሕበር መማህራን፣ ማሕበር ነጋዶ፣ ፣ ማሕበር ስነ-ጥበባውያን፣ ማሕበር ድሕነት/ኣንጻር/ ብከላን ልምዓትን፣ ማሕበር ተጣበቕቲ ህጻናት፣ ማሕበር ረድኤትን ምትሕግጋዝን….ወዘተ ናጻን ርእሰን ኪኢለን ክነጥፋን ክዕንብባን ካብቲ ቀንዲ ዕላማና እዩ። ናጽነተን ንምሕላዉ ድማ ኣብ ክንዲ ኣብ ትሕቲ ፖሎቲካዊ ምንቅስቃስ፣ ዉድብን ሰልፍን ተቆሪነን ዝሰርሓ ወይ መሳሪሒ ፖሎቲካዊ ምንቅስቃስ፣ ዉድብን ሰልፍን ዝኾና፣ ርእስን ኪኢለን ብነጻ ብዉሽጣዊ መደብ ዕዮን ሕግታተን መሪሒነታተን ክግዝኣ ስለዝግባእ ኣብ ክንዲ ቱኹላዊ ዝምድናታት ጋድማዊ ዝምድናታት ክህልወና ብመትከል ንኣምን”። እንብል። ኣብ ፖሎቲካዊ ባይታታት ኤርትራ፡ ቡዙሕ ጊዚየ ንሕና “ናጻ” ኢና ተባሂሉ ክዝረብን ክጽዓድን ይሰምዕ’የ፡ የግዳስ ከም ዑቱብ-ሓቂነት ዘለዎ ጽዕዶ ወሲደዮ ኣይፈልጥን። እቲ ምንታይስ “ናጻ” ካብ ምንታይ ሙኻኖም፡ ንጹር መግለጺ ስለዘይህቡሉን፡ ብተግባር እዉን “ናጻ” ሙኻኖም ብርግጽ ከእሙኑ ስለዘይኽእሉ ብሙኻኖም እዮ። “ናጻ” ኢና ክብሉ ይጸንሑ እሞ፡ ብድሕሪ መጋረጃ ድማ ኣእዳዉ ናይ ህቡኣን (ghost)፡ ብሩኡይ ኣጻብዕቶም ከንቃሳቑሱ ስለዝርኣዩን ሓሳባቶም ከንሂ ስለዝስሙዑን’ዩ። ካብዚ ቀጻሊ ዝዳጋገም ተርእዮታትን ዳይነሚክስን ብምንቃል፡ “ናጻ” የ ወይ “ናጽነት” ኣሎኒ ኢልካ ክትጽዕድ እንተኼንካ፡ ብቀዳምነት ምጣኔ-ሃብቲ ንፖሎቲካ ስለዝመርሕ፡ ንጹርን ጽኑዑን መትከላትን ፖሊሲታት ኣብ ምጣኔ-ሃብታዊ ኣካናዉናኻ ክህልወካ ኣለዎ። ብዝኾነ ኣምር ናጻ ን ናጽነት ኣብ ገብረ-ገብነት፡ ሰብኣዉነትን ጉቡኣት ዝቶሞርኮሰ ኮይኑ ፡ እንታይ ክገብር ኣለኒ? እንታይ’ዩ ኸ እቲ ቁኑዕ ክኸዉን ዝግብኦ? ንዝብል ሕቶታት ኣቀዲሙ ብምልኣት ብሓሳብን ተግባራትን ዝመለሰ ምስ ዝኸዉን’ዩ። ናጻን ናጽነት ካብ ጽቡቕ ድሌታትካን መርትዖ ዘለዎ ምኽንያት ነቂሉ፡ ብዘይ ግዳማዊ ጸቕጥታት፡ ጽልዋታት፡ ምወላታት፡ ሓሳባት …ወ.ዘ.ተ፡ ብናይ ገዛእ-ርእስኻ ሰናይ ድሌታትካን ዉሳኔታትካን ትሓስቦምን ተተግብሮሙን ነገራት ፡ በቶም ባዕልኻ ንነብስኻ ዝገበርካላ-መግቲኢታት ተቀይድካን ሓሲብካ ተትግብሮም ወይ ትብሎም (conscious free will )እዮም። ኣብ ፖሎቲካዊን ማሕበራዊን ንጥፈታት ሙሉእ ብሙሉኡ “ናጻን ናጽነትን” ዝብሃል ጉዳይ ብተግባር ኣሎ ድዩ (does free will exist) ዝብሉ ሕቶ ብገለ ግራቜናት፡ ዉልቃዊ ናጽነቶም ንካልኦት ዝመጠዉ: ነቲ ሓቂ ንምዝንባዕ ተባሂሉ ይልዓል’ዩ። እወ “ናጻን ናጽነትን” ካብ ገዛእ ርእስኻን ካብቲ ትነብረሉ ማሕበረ-ኮም ስለዝሙንጩ ህሉዉ’ዩ። ኣብ ዓለም ደቂ ሰባት ተሓጋጊዞም ስለዝነብሩ፡ ሓገዝ ምንዳይን ሓገዝ ምርካብን ነዉሪ ኣይኮነን። ከምኡ እዉን እቲ ዛዕባን ዕላማ ጽሑፈይን ኣይትታሓገዝ ወይ ኣይትሓግዝ ንምባል ኣይኮነን። እንታይድኣ መን ይሕግዘካ፡ ስለምንታይ ይሕግዘካ፡ ካብ መን ትቕበል፡ ንመን ሓገዝ ትሓትት…ወ.ዘ.ተ ብንጹር ዝፈለጥካን “ንናጻ”ን ናጽነትካን” ኣብ ዋጋ-ዕዳጋ ዘየሳጣሕካ ክትከዉን ኣሎካ፡ ናብ ዝብል ምኽሪ ዝዛዘወ እዩ። ፖሎቲካዊን ምጣኔ-ሃብታዊ ዕላማ ዘለዎም፡ ናይ ግዳም ይኹን ናይዉሽጢ መወልቲ ሓይልታት፡ ስለዝደለኻዮም፡ ስለዝዓደምካዮምን ስለዝለመንካዮም ኣይኮኑን ዝሙዉልኻ፡ እንታይ ድኣ፡ ነቲ ዝደልይዎ ፖሎቲካዊ ወይ ምጣኔ-ሃብታዊ ዕላማ ንምዕዋት ኣገዳሲ ንዋት ኴንካ ምስዝረኽቡኻ’ዩ። ኣገዳሲ ንዋት ክትከዉን ባዕሎም ይፈጥሩኻ ወይ ድማ ብግርህና ዝጀመርካዮ ምንቅስቓስ ኣብ ከርስኻ ናቶም ሰባት ይጸፍዩልካ። ብመንገዲ ዝተጸፍዮ ሰባቶሙን፡ በቲ ዝምዉልኻ ገንዘብን ገይሮም ድማ፡ ናብ ዝደለይዎ መዓላታት ወይ ማኣዝን ንምንቅስቓስካ ይመርሕኻ። እቲ ዘንቀልካሉ ድንግል ሓሳብን ዕላማን ድማ ብኸምዚ ብልሓት ተጨዉዩ፡ መኻዕበቲ ፋይናንሳዊ ትሕዝትኦሙን ፖሎቲካዊ ጡማሓቶሙን ኬንካ ትተርፍ። ብሕጋዊ ብልሓት ማሕበርካ ምስ ኣመዝገብካ፡ ከም መወከሲ (reference) ዝጥቀሙልካን ትጥቐመሎሙን ፍርዝን ዝበሉ ዓለምለኻዊ ዉድባት፡ ፖሎቲካዊን ማሕበራዊን ክብደታትን ተሳማዕነት ዘለዎም ዉልቀሰባትን ናይ ገበላ ምምኻር ጉጂለታት(lobby group) ክትረክብ ንዕብየትካን ምንቅስቓስካን ወሳኒ’ዩ። እዚ ክልተ ረቛሒታት ምሰተማልእ፡ ማሕበርካ ርዝነትን ተሰማዕነት (leverage) ይህልወካ እሞ፡ ድሕሪኡ ሻምቡቆ መስመር ገንዘብ ከም ዋሓዚ ማይ ቦሽቦሽ ይብልን ኣብ ሕጋዊ መጋባእያታት ናይ ዞናዊን ዓለምለኻዊ ዉድባት ድማ ቀጻሊተሳታፊ ትኸዉን። ኣብ ዶመኒካን ረፑብሊክ ሓደ ኤንሪኮ ሚራባል ፌርናንደዝ ዝብሃል ማእከላይ መነባብሮ ዝነበሮ ሰብ ምስ በዓልቲቤቱን ምስ ኣርባዕተ ኣዋልድ ደቁን ይነብር ነበረ። እታ በዅሪ ጓሉ ፓትሪያ ኣብ 1924 ክትውለድ ከላ፡ ካልአይቲ ኣዴላ፡ ሳልሰይቲ ሚኔርቫ እታ ሕሳስልደ ድማ ማርያ ተሬዛ ይብሃላ ነበራ። እዘን ኣርባዕተ ኣሕዋት ርኹባትን ፈቃራትን ስድራ ስለ ዝነበሩወን ኣብ ሓደ ጽቡቕ ናይ ካቶሊክ ቤትምህርቲ ክመሃራ ዕድል ረኺበን። ብትምህርተን ኣመና ንፉዓት መልክዐን’ውን ውቁባት ነይረን። ሽዑ አብ ዶመኒካን ረፑቡሊክ ራፋኤል ሌዮኒታስ ትሩሲሆ ኣብ 1930 ንክልተ እብረ ፕረሲደንት ኮይኑ ድሕሪ ምግልጋል፡ ኣብ 1952 ቅዋም ብምጥሓስ ንዕድመኡ ምሉእ ፕረሲደንት ከም ዝኾነ ኣወጀ። እዚ (ኤል ሴፈ) ወይ ድማ እቲ ሓለቓ ኢሉ ንርእሱ ዘጠመቐ ውልቀመላኺ እምብዛ ርጉም፡ ዓመጸኛን ህልኸኛን ኮይኑ ኣዝዩ ግፍዐኛ ሰብ’ዩ ነይሩ። ንህዝቢ ናይታ ሃገር ድማ በቲ ጨካን ምሕደራኡ ፈጥፈጥ ኣበሎ። ንተቓወምቱ ክኣስርን ክቐትልን ከሎ፡ ንዘስግኡዎ በብሓደ ኣብ ርእሲ ምሕቃቕ፡ ብኣባላት ጸጥታኡ ንምሉእ ህዝቢ አርዓዶ። ኣብ ግዜ ምሕደራ ኤል ሴፈ እተን ኣርባዕተ ደቂ ሚራቫል ንኣሽቱ እየን ነይረን። እታ ሳልሰይቲ ሚኔርቫ ጓል 15 ዓመት ምስ ኣኸለት ነቦአ ትምህርታ ክትቅጽል ለመነቶ። ኣብቲ እዋን’ቲ ደቂአንስትዮ ኣብ ትምህርቲ ልዑል ግስጋሰ ከርእያ ዘተባባዕ ሃዋህዉ’ኳ እንተ ዘይነበረ፡ ወላዲኣ ንሕቶኣ ብሕጕስ መንፈስ ተቐቢሉ ትምህርታ ክትቅጽል ኣፍቀደላ። ሚኔርቫ ትምህርታ ምስ ቀጸለት ብዛዕባ ኵነታት ሃገራ ከተስተውዕል ጀመረት። ፖለቲካ ናይ ሃገራ ክርድኣን ከተሓሳስባን ድማ ጀመረ። ብፍላይ እቲ ብማዕከናት ዜና ወጻኢ ብዛዕባ ኣብ ሃገራ ዘሎ ስርዓት ዝፍኖ ዝነበረ ዜና ይኹን መግለጺ ኣብ ኣእምሮኣ ብዙሕ ሕቶታት አበገሰ። እተን ሬድዮታት “ዲክታተር፡ ውልቀመላኺ፡ ሕጊ አልቦ . . .” ዝብል መግለጽታት’የን ዝህባ ነይረን። አብቲ ሃገር ሰፊኑ ዝነበረ ስርዓት ነቲ ሕብረተሰብ ብምሉኡ ስለ ዝተቘጻጸሮ፡ ናይ ምዝራብ፡ ምጽሓፍ፡ ምእካብ መሰላት ኣይነበረን። ብሓጺሩ እቲ ህዝቢ ተዓፊኑ እዩ ዝነብር ነይሩ። እዘን ናይ ወጻኢ ማዕከናት ዜና ዘቃልሖኦ ዝነበራ ፈነወ ንሚኔርቫን መማህርታን ብዛዕባ ኣብታ ሃገር ዘሎ ኵነታት ካብ ሕጊ ወጻኢ ምዃኑ ክበርሃለን ጀመረ። ሽዑ እያ ድማ ሚኔርቫ ሕጊ ክትመሃር ዝወሰነት። ልክዕ ኣብዚ እዋን’ዚ ምስ ሓደ ፔሪክሌስ ፍራንኮ ዝተባህለ ከምኣ ብዛዕባ ሃገሩ ዝግደስ፡ ኣብ ሳንቶ ዶሚንጎ ዘሎ ግፍዐኛ ስርዓት ክእለ ኣለዎ ዝብል፡ ተስፋ ዘሎዎ መንእሰይ ተላለየት። ካብዚ ዝተበገሰ ፍራንኮ ድሮ ብኣባላት ጸጥታ ኤል ሴፈ ክእሰርን ክፍታሕን ጀሚሩ’ሎ። እዚ ነገር’ዚ ንባዕሉ ንሚኔርቫ ናይ ቃልሲ መንፈሳ ከለዓዕሎ ጀሚሩ ጥራይ ዘይኮነ፡ ነሕዋታ’ውን ብፖለቲካ ሃገረን ከም ዝጽለዋ ገይሩወን። ንውልቀ መላኺ ኤል ሴፌ ድማ ከም ሓደ ደመኛ ጸላኢአን ቈጸሮኦ። ሓደ መዓልቲ፡ ካብ ኤል ሴፈ ነታ ስድራቤት ብምልእታ ናይ ዕድመ ደብዳቤ ተላእከላ። ሽዑ እተን ኣሕዋት መልኣከ ሞት ዝጽውዐን ዘሎ ኮይኑ ተሰምዐን። እቲ ዕድመ ኣብ አደራሽ ቤተመንግስቲ እዩ ነይሩ። እቶም ወለዲ አማራጺ ስለ ዘይነበሮም ነቲ ዕድመ ክቕበሉዎ ነይሩዎም። ዕላማ ናይ ኤል ሴፈ ንጎራዙ ናይቲ ሃገር ዓዲሙ ባህ ዝበለቶ ንምራጽ’ዩ ነይሩ። ኣብቲ ዕድመ ምስ ዝተረኽባ ቈናጁ ከዕልልን ቀመጽመጽ ክብልን ድማ ኣምሰየ። ሓንሳብ ምስ ሓንቲ ጸኒሑ ምስ ሓንቲ ካልእ ከዕልልን ክተናኸፍን ድሕሪ ምምሳይ ናይ መወዳእታ ምርጫኡ ሚኔርቫ ኮነት። ንሚኔርቫ ክምስጣ ስለ ዝደለየ፡ “ነፋሪተይ ከርእየኪ ትደልዪዶ?” ክብል ምስ ተወከሳ፡ “ደሓን የቐንየለይ፡” ክትብል መለሰትሉ። ቀዳመይቲ ናይ ዕድመ ምሸት ብሰላም ተዛዚማ እታ ስድራ ብሰላም ኣብ መንበሪ ገዛኣ በጽሐት። ናይ ካልአይ መዓልቲ ናብ ሚኔርቫ ጥራይ ዝተላእከ ደብዳቤ ግን ዕድመ ዘይኮነስ ትእዛዝ ነይሩ ክብሃል ይከኣል። ሚኔርቫ ናብ ቤተመንግስቲ ዘይኮነ ናብቲ ኣብ ገምገም ባሕሪ ዝርከብ ናይ ኤል ሴፈ ውልቃዊ መናፈሻ ክትመጽእ ዝጠልብ ነይሩ። ሚኔርቫ ብሕርቃን በግ ኢላ፡ “ኣይከይድን’የ” በለት። አቦአ ግን “እዛ ጓለይ፡ እዚ ርዅስ ሰብኣይ ነገር ከየምጽአልና እንተ ኸድኪ ይሓይሽ” በላ። ወላዲታ ድማ “በቃ ደሓን፡ አነን አቦኽን ምሳኺ ክንከይድ ኢና ኣጆኺ፡” ኢላ ምስ ኣተባብዓታ ግን ቃል ወለዳ ክተኽብር ከይፈተወት ሕራይ በለት። ተተሓሒዞም ድማ ናብቲ ዝተባህሉዎ ዕድመ ተበገሱ። ኤል ሴፈ ነቶም ኣጋይሽ “እንቋዕ ደሓን መጻእኩም” ድሕሪ ምባል ንሚኔርቫ ብኢዳ ሒዙ መሪሑዋ ንውሽጢ ቀጸለ። ሚኔርቫ ነቲ ኣብ መንደቕ ተሰቒሉ ዝነበረ፡ ኤል ሴፈ ዓቢ ጠበንጃ ሒዙ እናሃደነ ከሎ ዘርኢ ዓቢ ስእሊ ትርኢ ነበረት። ኤል ሴፈ ብድሕሪአ ጽግዕ ኢሉ፡ “ገዚፍ መሳርሒ ትፈትዊ ኢኺ” በላ። ሕርቃና ጥርዚ በጺሑ ኣዒንታ በርበረ መሰላ። ድምብርጽ ከይበላ፡ “ሰላም ዘይትህበና! ግደፈና’ስኪ! እንታይ ዝገበርና ሰባት ኢና?” ኸኣ በለቶ ብዓውታ። ነዚ ዝተዓዘቡ አቦን አደን ብራዕዲ ተዋሕጡ። ካልእ ዘረባ ከይወሰኸት ከላ ብኢዳ እናወጠጡ፡ “አኽቢርኩም ዝዓደምኩምና ነመስግን . . .፡” ኢሎም ዘረባኦም ምስ ጀመሩ፡ ሚኔርቫ፡ “ግደፋኒ፡ አይወዳእኩን ዘለኹ፡” ድሕሪ ምባል፡ “ተኣሲሩ ንዘሎ ኣፍቃሪየይ ፔሪክለስ ፍራንኮ ክትፈትሖ ኣለካ፡” በለቶ ብትብዓት። እቲ ዕድመ ብግቡእ ከይተዛዘመ ድማ ሚኔርቫ ምስ ወለዳ ብሰላም ገዛኦም በጽሑ። ኣሕዋታ ንኤል ሴፈ ዝበለቶ ምስ ሰምዓ ክድግፋኣ ከለዋ፡ ኤል ሴፈ ግን ኣይደቀሰላን። ድሕሪ ገለ መዓልታት ሕነኡ መታን ክፈዲ ነቦ ሚኔርቫ ኣሰሮ። እታ ስድራቤት ብምልእታ ሽዑ እያ ምሉእ ብምሉእ ኣንጻር ኤል ሴፈ ዝተስአት። ኩላተን ኣሕዋት ብመትከል ኣንጻር ኤል ሴፈ ደው በላ። ናይ ሚኔርቫ ድፍረትን ንዕቀትን ዝገረሞ ኤል ሴፈ፡ “ክርእያ እየ!” ኢሉ ብምፍካር አብ ብርቱዕ ህልኽ አተወ። ናይ አቦኣ ምእሳር ጥራይ ስለ ዘየዕገቦ ድማ ንሚኔርቫን ንመሓዙታን’ውን ኣብ ቀይዲ ኣእተወን። መርመርታ፡ “ምስ ማሕበርነታዊ ሰልፊ (ሶሳሊስት ሰልፊ) እንታይ ርክብ ኣሎኪ?” እናበሉ ብዛዕባ መስራቲ ሰልፊ ዝነበረ ኣፍቃሪኣ ፍራንኮ ብምሕታት ኢሰብኣዊ መርመራ ኣካየዱላ። “ንኤል ሴፈ ናይ ጣዕሳ ፎርም እንተ መሊእኪ ናጻ ክንሰደኪ ኢና፡” ብምባል’ውን ከታልሉዋ ፈቲኖም። ብፍላይ ብዛዕባ መስራቲ ማሕበርነታዊ ሰልፊ ዝነበረ ፍራንኮ ደጋጊሞም ሓቲቶማ። ንሳ ግን “እንታይ ገደሰኩም? ምስ ዝደለኹዎ ሰብ ክራኸብ ወይ ክመሓዞ መሰለይ እዩ፡” ኢላ ኣቕበጸቶም። ኣብ መወዳእታ ቀቢጾም ምስ ፈነዉዋ ዳግማይ ኣብ ትምህርታ ተመልሰት። ሽዑ እዋን እያ ድማ ማኖሎ ምስ ዝብሃል መንእሰይ ብምልላይ ብዙሕ ከይደንጐየት ዝተመርዓወቶ። ማኖሎ ካብኣ ብዘይፍለ ጸረ ምልካዊ ምሕደራ ኤል ሴፈ ኮነ። ማኖሎ ንሚኔርቫን ንቓልስን ብማዕረ ቃልኪዳን ኣትዩሎም። እተን ክልተ ኣሕዋት ሚኔርቫ ብወገነን ተቓወምቲ ምልካዊ ምሕደራ ስለ ዝነበራ እታ ስድራቤት ብምልእታ ናብ ደጀን ሰውራ ተቐየረት። ሚኔርቫ ናይ ትምህርታ መዛዘሚ ብዛዕባ መሰል ደቂ ሰባትን አድላይነት ለውጢ ኣብ ምሕደራ መንግስቲ (ለውጢ ናይ ዘሎ ስርዓት) ዝብል’ዩ ነይሩ። ኣብ 1957 ሚኔርቫ ኣብ ሃገራ፡ ናይ መጀመርያ ብሕጊ ናይ ዶክተርነት መዓርግ ዝረኸበት ጓልኣንስተይቲ ክትከውን በቕዐት። ኣብ ግዜ ምምራቓ ካብ ኢድ ኤል ሴፈ ምስክርነታ ክትቅበል ከላ፡ “እንቋዕ ሓጐሰኪ” ክብል ሓጪጩላ። አስዒቡ “ሓንቲ ነገር ክርደአኪ፡ አነ ብህይወተይ ክሳዕ ዘለኹ ፍቓድ ረኺበ ብሞያይ ክሰርሕ’የ ኢልኪ ከይትሓልሚ። ጕዳይኪ ባዕለይ ክከታተሎ ምዃነይ ፍለጢ” ዝብል ቃላት ኣስምዓ። አብቲ እዋን’ቲ አብ ላቲን አሜሪካ ብርክት ዝበሉ በዓል ባቲስታ ናይ ክዩባ ዝርከቡዎም ውልቀ መለኽቲ ካብ ስልጣን ክእለዩ ጀሚሮም ነይሮም። ስለዝኾነ፡ ህዝቢ ሳንቶ ዶሚንጎን ዓቢ ተስፋ ዘሕደሩሉ ወቕቲ’ዩ ነይሩ። በዓል ሚኔርቫን መቓልስታን ድማ ደገፍ ናይ ተቓለስቲ ክዩባ ክረኽቡ ሃንቀው በሉ። ንመንግስቲ ኤል ሴፈ ንምእላይ ብዕለት 14 ሰነ ምንቅስቓስ 14 ሰነ ዝብል ስም ዝሓዘ ሰልፊ ተመስሪሩ ለውጢ ከምጽእ ተበገሰ። ሚኔርቫ ምስ ብጾታ’ውን ተጸንበረቶ። ንሳን ክልተ ኣሕዋታን ድማ ጽምብላሊዕ ዝብል ምስጢራዊ መጸውዒ ተዋህበን። እቶም ኣባላት ምስጢራዊ ውድብ ናይቲ ሰልፊ ኵሉ ጊዜ’ዮም ዝእሰሩን ዝፍትሑን ነይሮም። ሚኔርቫን ኣሕዋታን ምስ ሰብኡተን ዝበዝሐ ግዜኦም አብ ኣብያተ ማእሰርቲ እየን ዝሕልፎኦ ነይረን።ሚኔርቫ ምስ ክልተ ኣሕዋታ አብ ካራንታ ዝብሃል ውሩይ፡ ዝኸፈአን ዝጸንዐን ቤትማእሰርቲ ብመግረፍቲ ተሳቕየን። ካብዚ ዝተበገሰ እዘን ሰለስተ ኣሕዋት ብህዝቢ ተፈላጥነት ክረኽባ ጀመራ። ብፍላይ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ዓገብ ክትብል ብምጅማር ደገፋ ለገሰትለን። ድሕር’ዚ ኣህጉራዊ አቓልቦ ክረኽባን ተፈላጥነተን ክዓዝዝን ምስ ጀመረ፡ ጸቕጢ ማሕበረ ሰብ ዓለም ዝበርትዖ ኤል ሴፈ ክሲ ክምስርተለን ተገደደ። ስለዚ፡ ንሃገራዊ ድሕነት ኣስጋእቲ እየን፡ ክድዓት ፈጺመን ብዝብል ክሲ ንሓሙሽተ ዓመታት ከም ዝፍረዳ ገበረ። ንሳተን ፍርደን ወዲኤን ከወጽኣ ከለዋ፡ ሰብኡተን ግን አብ ቤትማእሰርቲ ከም ዝጸንሑ ተገይሩ። ህዝቢ ሳንቶ ዶሚንጎ ነዘን ተቓለስቲ ኣሕዋት ከም ምልክት ተስፋ ናይ ናጽነት ክስእለንን ከለልየንን ጀመረ። እዚ ድማ ንኤል ሴፈ ብሓቂ ዝስግእ ጕዳይ ነይሩ። ሚኔርቫን ኣሕዋታን፡ ናይ ህዝቢ ደገፍ ምርካበን ንኤል ሴፈ ሻቕሎት ከም ዝፈጠረሉ ስለ ዝፈለጣ ብመጠኑ ስክፍታ ሓደረን። ኣብዚ ዝጥቀስ ዘሎ እዋን ንተቓወምቲ ብሓደጋ መኪና ዝተሃርሙ ኣምሲልካ ምቕንጻልን ምጭዋይን ገኒኑ ስለ ዝነበረ ክጥንቀቓ ግድነት ኮነን። ካብታ ዝፈረሖኦ አይወጽኣን ዕለት 25 ሕዳር 1960 ንሰብኡተን ክበጽሓ ናብ ቤት ማእሰርቲ ክኸዳ ከለዋ ተጸናጺኖም፡ አብ ጽምዋ መንገዲ ክጽበዩወን ድሕሪ ምጽናሕ ብሓንቲ መኪና ዓገቱወን። ንሰለስቲአን ብጎዘሞ ጨፍጪፎም ብምቕታል ድማ አብ መኪናአን ኣእትዮም ንገደል አጽዲፎም ቀተሉወን። ኤል ሴፈ ኣቐዲሙ ከም ዝተገልጸ፡ “ካብ ቤተመንግስቲ ብቃሬዛ’ምበር ህይወት ኣይወጽእን’የ፡ ካብ ስልጣነይ ዘውርደኒ የሎን፡” እናበለ ይፍክር ስለ ዝነበረ፡ መዓልቱ ይቃረብ ከም ዘሎ ዝፈለጠ ይመስል ነይሩ። ካብ ዝፈርሖ ኣይወጽአን ዕለት 30 ግንቦት 1961 ንኤል ሴፈ ሒዛ ዝነበረት መኪና ብዕጡቓት ምስ ተዓግተት ካብ ስሳ ጥይት ንላዕሊ ተተኵሱዋ መንፊት ኮነት። ኤል ሴፈ ድማ ብኡንብኡ ሞተ። ኤል ሴፈ ብድምር ኣብ ናይ ሰላሳን ሓደን ዓመት ናይ ስልጣን ዕድመኡ ልዕሊ ሓምሳ ሽሕ ንጹሃት ዜጋታት ቀንጺሉ። ድሕሪ ሞቱ ግን ህዝቢ ዶመኒካን ረፑብሊክ ካብ ናይ ሰላሳ ዓመታት ናይ ጸልማት ዘመን ተገላጊሉ። እቶም ነዚ መጥቃዕቲ ዝፈጸሙ ጀጋኑ ሓርበኛታት ተባህሉን ተሸለሙን። ኣብ ልዕሊ’ዘን ሰለስተ ተቓለስቲ ኣሕዋት ዝተፈጸመ ኣረሜናዊ ግፍዒ ንኸይርሳዕን ከይድገምን ተባሂሉ፡ 25 ሕዳር 1960 ኣብ ልዕሊ ደቂኣንስትዮ ንዝተፈጸመ ግፍዒ ብደረጃ ዓለም ዝዝክረላ መዓልቲ ኮይና ክትውዕል ብውድብ ሕቡራት ሃገራት ተወሲኑ። ኣብ ዶመኒካን ረፑብሊክ ድማ እዘን ሰለስተ ኣሕዋት ዝተወልዳላ ኣውራጃ፡ ብስመን ማለት ሄርማናስ ሚራባል ተባሂላ ትጽዋዕ ኣላ። ንክብሪ ናይዘን ሰለስተ ኣሕዋት ተባሂሉ፡ ዝፍለጣሉ ዝነበራ ምስጢራዊ መጸውዒ ሮዛ ጽምብላሊዕን ናይ ሰለስቲአን ስእልን አብ ናይቲ ሃገር ገንዘብ 200 ፔዞ ገንዘብ ከም ዝሕተም ተገይሩ። ኣቀዲመ ክገልጾ ዝደሊ ሓቂታት ኣሎ፡ ንሱ ድማ ካብ መርፍእ ክሳብ መድፍዕ: ኣቶ ኢሰያስ ኣፍወርቂ ዘይፈልጦ ንጥፈታት ኣብ ዉሽጥን ኣከባቢ ኤርትራን ኣይካየድን’ዩ። ኣንካይዶ ብሚልዮናት ዝግምገም ንግዳዊ ንጥፈታት’ሲ፡ ሓንቲ ደቓቕ ዑፍ ካብ ኤርትራ ዶብ ሱዳን ኤርትራ፡ ዶብ ኢትዮጵያ ኤርትራን ዶብ ጁቡቲን ኤርትራን ኣቓሪጻ እንተኣትያ’ዉን እንተኾነ፡ ብደቂቑ ከምዝፈልጥ ክትፈልጡ ኣለኩም። ኣቶ ኢሰያስ ኣፍወርቂ ካብ ታሕቲ ክሳብ ዝላዓለ ደረጃ እቲ ስርዓትን ህዝብን ብመገዲ ስለያዊ ትካላቱን ብዉልቑን ኣዝዩ ስጡም ጋድማዊን ትኹላዊን ሰንሰለታዊ ርኽክብ ዘለዎ መራሒ’ዩ። ኣንካይዶ ዝካየድ ዘይሕጋዊ ንግድታት፡ ኣብ መንጎ ሱዳንን ኤርትራን ዝካየድ፡ ኣብ ገዛኹም ኬንኩም ተዕልሉዎን ተሓምዩዎን ተራ ዕላል እዉን እንተኾነ ዝፈልጥ ሰብ’ዩ። ስለዚ እቲ “ኣቶ ኢሰያስ ኣፍወርቂ ዘይፈለጦ ኮይኑ ድዩ” ዝብል ኣዝራራርባ፡ ናይ ጉራሃት ዝመስል ተንኮለኛታት ንህዝቢ ንምድንጋር ዝዛረብዎ ዘረባ ሙኻኑ ብቀዳምነት ክግራሕ ዘለዎ ምህዞ-ምድንጋራት’ዩ። ባህሊን ልምድን ከተጥርዮ ኣዝዩ ቀሊል፡ ጨሪስካ ከተጥፍኦ ግን፡ ኣዝዩ ኣጸጋሚ ዝኾነ ነገር’ዩ። ኣብ ሃገራዊ ተጋድሎ ንናጽነት ኤርትራን ንሓርነት ዜጋታትን እንዳተቃለስና እንኮለና፡ ዉድብ ህ.ግ.ሓ.ኤ ምጣኔ-ሃብታዊ ትሕዝቶታቱ ንምኽዕባትን ነቲ ዝነበረ ሕጽረታት ጠለባትን ቀረባትን ህዝቢ ንምጽባብን ርእሰ-ምኽኣል ተባሂሉ ዳርጋ ድሕሪ ቀዳማይ ዉድባዊ ጉባኤና (1977) ኣብ ትሕቲ ክፍሊ ቁጠባ ዝማሓደር ሓደ ጨንፈር ንግድንሸቐጥን ዝብል ብምቛም፡ ኣብ ካብ መግዛእታዊ ሰራዊት ኢትዮጵያ ሓራ ዝወጸ ቦታታትን ንዝነብር ህዝቢ፡ ካብ ሱዳን ኣድለይትን ሃለኽትን ኣቑሑታት ብምቕራብ ይናጣጥጠፍ ከምዝነበረን፡ ስግሩ እዉን ኣብ ሱዳን ብሸሪከት ኣፍሮ ዝፍለጥ ናይ መጓዓዝያን ጽርበት ሓጺን ትካላት ኣገልግሎት ንሱዳናዉያን እንዳሃባ ርእሰማል ህ.ግ.ሓ.ኤ ንምዕባይን ርእስና እንኽእለሉ ህሞት ንምፍጣር ተባሂሉ ዝተጀመረ ሙኻኑ ኣዳዕዲዔ ይፈልጥ። ብልክዕ ኣብቲ እዋን’ቲ፡ ነቲ ንዘንቐሎ ዕላማን ስትራተጂን ከምዝወቕዔን፡ ጽቡቕ ዉጽኢት ከም ዘበርከተን ኣብ ተዘክሮታተይ ይጥሕምስ እየ። ካብ ዝተረኽበ ኣድማዒ ዉጽኢታቱ ብምንቃል ድማ፡ ብዉዱቡን ዝላዓለ መልክዓቱ ብ 09 ዝባሃል ኣሃዱ ንግድን ገለ ክፋል ሓይሊ ባሕሪ ነቲ ዘይሕጋዊ ስራሓት ንግዲ ስራሕና ኢሎም ስለዝተታሓዝዎ፡ ኣኻሊ ቀረባት ነቲ ኣብ ሓራ መሬት ዝነብር ዝነበረ ህዝቢ ካብ ምቕራብ ሓሊፎም፡ ን ኣብ ዉሽጢ ኣብ ትሕቲ መስመር ጸላኢ ዝነብር ዝነበረ ህዝቢ፡ ከም ቢራ ሄኒከን፡ ሽኮር፡ ሽጋራ…..ወ.ዘ.ተ ኣስሊኾም ብምእታዉ እዉን ይነግዱ ከምዝነበሩ ይዝክረኒ። ከምዚ ኢሉ እዩ እቲ ናይ ዘይሕጋዊ ንግዳዊ ንጥፈታት ኣብ ህ.ግ.ሓ.ኤ ተኣታትዩ። እዚ ባህሊ’ዚ ካብ 1977 ጀሚሩ ክሳብ እዛ ካልኢት፡ ደቂቕ፡ ስዓት ናይ ጊዚየ ዝጽሕፈላ ዘለኹ፡ ከም ባህሊን ልምድን ዉድብ ኮይኑ ይሰርሕ ከምዘሎ ይፈልጥ እየ። ሰባት ብመኽሰብን ክሳራን ክጥምትዎ ከምዝኽእሉ ዘጣራጥር ኣይኮነን፡ የግዳስ እቲ ቀደም ሕራይ ኣብ ቃልሲ ስለዝነበርና ብዘይሕጋዊ ብልሓታት ጸገማትና ክንፈትሕ ንህቕን ኔርና፡ ሕጂ ግን ልዑላዊ ሃገር፡ ህዝቢን መንግስትን እንተሃልዩ ሕጋዊን ትካላዊን ኣሳራርሓ ክስራሕ ግድነታዊ ጉዳይ’ዩ። የግዳስ ዘይሕጋዊ ባህሊን ልምድን፡ ንኣታሓሳስባ መራሕቲ እዚ ፖሎቲካዊ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ይገዝእዎን ይደግሶምን ስለዘሎ፡ ነዚ ኣብ 50 ዓመታት ዘጥረይዎ ባህሊን ልምድን’ዚ ራሕሪሖም፡ ናብ ሕጋዊ ስርሓት ክኣትዉ ባህልታቶሙን ልምድታቶሙን ኣየፍቕደሎሙን’ዩ። እቲምንታይስ ርስሓት ካምሻ ብሓንቲ ሕቃቅ ሳቡና ሓጺብካያ ክትጸሪ ትኽእል እያ፡ ብመንጹሩ! ወዲ ሰብ ኣብ ነዊሕ ሂወቱ ዝለመዶ ባህልታትን ልምድታትን ብቀሊሉ ክሓድጎን ከጽሩዮን ኣጸጋሚን ፈጺሙ ዘይክኣልን እዩ። ከምኡ ስለዝኾነ’ዩ ድማ ኣብ ባህላዊ ምስላና ”ኣመል ምስ መግነዝ” ተባሂሉ ዝምሰል እዩ። ስለዚ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ፡ ኤርትራ ናይ ባሕሪ ወደባት፡ ማርሳታት፡ ውሽመጣት….ወ.ዘ.ተ ያሃልዋ ኣይሃልዋ ብዘየገድስ፡ ኣብ ዘይሕጋዊ ንግዳዊ ንጥፈታት ክስህር ሙኻኑ ዘጣራጥር ኣይኮነን። ከምዚ ሓደ ብወልፊ ዕጸ-ፋርስ ዝተለኽፈ ሰብ ዕጸ-ፋርስ ካይወሰደ ዘይረግእ፡ መራሕቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ድማ ዘይሕጋዊ ስርሓት እንተዘይሰሪሖም ቀሲኖም ክድቑሱ ስለዘይክእሉ: ክቕጽልዎ ሙኻኖም ዘጣራጥር ኣይኮነን። ስለዚ እቲ ፍታሕ ብሱሩ ነዚ ብሕማቕ ባህልታትን ልምድታትን ዝመሽመሸ ስርዓት ካብ ሱሩ ቦርቒካ ምእላዩን ኣብ ዕኑኡ ሕጋዊ ፖሎቲካዊ ስርርዕን ጥዕና ዘለዎ ባህልታትን ልምድናታትን ሙኹስኻስ ጥራ’ዩ። ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ኣብ ባዕሉ ዝኣጎዶ መጋርያ ሓዊ ተሓቢኡ ዝስሕን ፖሎቲካዊ ስርርዕ’ዩ። ኩሉ ጉጉይ ሜላታቱ ኣብ ፖሎቲካዊ ምጣኔሃብታዊን ማሕበራዊን ሂወት ኤርትራን ህዝቢ ኤርትራን ዝፍጠር ጸገማት ድማ ባዕሉ ዘሳሰዮን ዘንበድበዶን ኮይኑ፡ ተገልቢጡ ነቲ ገባቲ ፖሎቲካዊ ስርርዕ ኣብ ሓደጋ ዘሳጥሕ’ዩ። ክሳብ ሕጂ ንስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ብተግባር ዝተንከፎ ተጻይ ሓይሊ የሎን። ባዕሉ እቲ ስርዓት ተጻይ ናይ ገዛእ ርእሱ፡ ሃገሩን ህዝቡን’ዩ፡ ኣብ ዝሓለፈ 21 ጥሪ 2013 ኣብ ከተማ ኣስመራ/ ፎርቶ ብናይ ምክልኻል ሓይልታት ኤርትራ ፈተነ ወትሃደራዊ ዕልዋ ምስተጋህደ፣ ኣብቲ እዋናት’ቲ ሰበ-ስልጣን ጃንዳ ህ.ግ.ደ.ፍ ሒቕታ ጎሲዖም እዮም። እቲ ጉሳዕ ድማ “እስላማዊ ምትእኽኻብን እስላማዊ ስጉምቲ ምኻኑ እዩ”። እዚ ሒቕታ እዚ ኣብ ዉሽጥ ኤርትራ ንኹሉ ዜጋ ንኣዝዩ ሓጺር ስዓታት ኣብ ደዉታ ምፍጣጥ ኣእትዩ ከምዝነበረን፣ ብቅጽበት ህዝቢ እዉን ከምዝነጸጎ ታሪኽ ዝራጋገጽ ሓቂ እዩ። ቀጺሉ ሕጂ ድማ ፡ ኣብ ዕለት 31 ጥቅምቲ 2017 ብተማሃሮን ስድራቤታት ቤት ትምህርቲ ኣልድያእ ኣል እስላምያ ኣኽርያ (ቀደም ብሓደ ካብቶም መስረቲ መምህር መሓመድ በሽር ኣሕመድ ኣብ 1969 (ብእንዳበሺር ቅጽል ስም ትፍለጥ’ያ) ኣብ ዝተጋህደ ሰላማዊ ሰልፊ 4 ሰባት ብጥይት ብኸቢድ ከምዝቖሰሉን 58 ድማ ከም ዝተኣስሩን ይግለጽ ኣሎ። ብኻልእ ሸነኽ ኣብ ዕለት 01 ሕዳር 2017 ኣብ ኣልጀዚራ ዝወጸ ሓበሬታ ክትኣምኖ ዘጸግም ድማ፡ 28 ሰባት ከምተቀትሉን ልዕሊ 100 ሙቕሳሎም ተሓቢሩ ኣሎ። ስርዓት ኣስመራ ብመንገዲ ትዊተር፡ ብሚኒስተር ሓበሬታን ፕሮፓጋንዳን ኤርትራ (ኣቶ የማነ ገብረመስቀል) ኣቢሉ ዝወጸ ሓበሬታ ግን፡ እቲ ወረ ሓሶት ምዃኑን፡ እቲ ዝተራእየ ናይ ሓንቲ ቤት ትምህርቲ ኣድማ ድማ ከም ፍሉይ ሓድሽ ዜና ተቖጺሩ ግምት ዝወሃቦ እውን ኣይኮነን ይብል። ቀጺሉ እቲ ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነት ብኣፈ-ሙዝን ምእሳርን ምስተደርቀሰ ንስርዓት ኣስመራ ኣዝዩ ቅርበት ዘለዎ ብቕጽል ስም hagerawi dihnet – ሃገራዊ ድሕነት፡- ኣብ ዕለት 7/11/2017 “ወከልቲ ወለድን መምሃራንን ሎሚ ኣኼባ ምስ ምምሕዳርን ወከልቲ ሚኒስትሪ ትምህርትን ከምዝካይዱ ከኣ ኣማሲኡ ብዝበጽሓና ሓበሬታ ተፈሊጡ ኣሎ፡ ወለዲ እቶም ቆልዑት ዝወሰድዎ ተግባራት ምስ ኤርትራዊ ባህልን ኣካይዳን ዘይከይድ ምዃኑ ብምግላጽ መንግስቲ ነቶም ነቲ ጉዳይ ናብ ጥቅሞም ቀይሮም ሕጻናት ቆልዑ ኣብዘፈልጥዎ ሓደገኛ ጉዳያት ከእትውን ደም ምፍሳስን ዝተጸበዩ ሰባት ግቡእ ስጉምቲ ብምውሳድ እቶም ወለሓንቲ ዘይፈልጡ ቆልዑትን መንእሰያትን ግና ክፈትሓሎም ብኣክብሮት ሓቲቶም፡ ፓሊስን ሰራዊትን ዋላ ነቶም ተጋግዮም እምኒ ዝደርበዩ ከይተረፈ ንላዕሊ መጠንቀቅታ ብምትካስ እምበር ንሂወት ሰብ ከየሕልፉ ዝገበርዎ ምጥንቃቅ ምስጋንኦም ብምግላጽ እቶም ነዚ ጉዳይንረብሖም ክጥቀምሉ ዝደለዩ ሰባት ኣብሞንገና ነቃዕ ክፍጠር ከምዘይኮነ ክፈልጡ ኣለዎም ኢሎም፡ መንግስቲ ከኣ ነቶም ትሕቲ ዕድመ ቆልዑት ብመጠንቀቅታን ብምግሳጽን ናብ ስድራቤቶም ከምዘረኮብምን እቶም ልዕሊ ዕድመ ከኣ ጉዳዮም እንዳተራእየ እቶም ኣሳወርቲ ብሕጊ ክሕተቱ ምዃኖም ተፈሊጡ ኣሎ፡ ካልእ ምዕባሌታት እንዳተኻታተልና ከነቅርበልኩም ኢና!” ክብል ኣብ ፌስቡክ ጽሑፉ ዘርጊሑ ኣሎ። ኣብ ኤርትራ፡ ኩሉ ተግባራትን ሓበሬታን፡ ብስቱር ስለዝተሓዝ፡ ናይቲ ኣብ ሰብ ዝወረደ ጉድኣት ብወግዓዊ ናጻ ብዝኾኑ ምንጪታት ብንጹር ንምርግጋጹ ኣዝዩ ኣጸጋሚ ኢዩ። ኣብ ዉሽጢ ኤርትራ ብቲሕምቲሒም ኣብ ማሕበራዊ መራኸቢታት ድያስፖራ ድማ ብጋህዲ ፡ ንፖሊሲታት ስርዓተ ትምህርቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ጥሒሱ ዝተወልዔ ናይ “እስላማዊ ፖሎቲካ” ብምባል የናዓዕብዎ ኣለዉ። ነዚ ኩነታትዚ ዝጋሃሀር ናይ ግዳም ሓደ ሓደ ሮቓሒታት ብ ዶር ዓብዱላሂ ዩሱፈን ኣብ ሱዳን ካልኦትን ናይ መራኸቢ-ቡዙሓን ማእከላት ኣለዉ። ንሳቶም ድማ ባዕሉኻትኩም ክትሰምዕዎን ክትመምይዎን ንኣኹም ይሓድጎ ኣለኹ። ወትሩ ዝኾነ ይኹን ኣብ ዉሽጢ ሃገር ዝካየድ ንጥፈታት መንግስቲ ብሚስጢር ስለዝሕዞን ንህዝቡ ጹጹይ ሓቤሬታ ስለዘይህብ፡ ሰባት ብቀሊሉ ንዕላማታቶም ንምዕዋት ንፕሮፖጋንዳ ስለዝጥቀሙሉ ህዝቢ ኣብ ነዉጺ ኣእሙሮ ይኣቶ። ኣይካብቲ ስርዓት ኣይ ካብቲ ተቃዉምኖ ዘራጋግኦ ዘይብሉ ህዝቢ ኣብ ጥራይ ጎልጎል ትጽቢታቱ ይዝርጋሕን ይጭበጥን እሞ ኣብ መጨረስትኡ ሞራሉ ኣዉዲቁ ንከይቃለስ ሮፈጥ ዘብል ክዉንነት’ዩ ዝጋሃድ ዘሎ። ዳይነሚክስ ናይ እቲ ናዕቢ እንታይ እዩ? ኣብ ክፍላ መስከረም 2017፡ ቤት ትምህርቲ ኣልድያእ ኣል እስላምያ፡ ገለ ሰባት ካብ ዉሽጢኡ ኤርትራ ኣፍልጦ ዘለዎም ከምዝብልዎ “ብመገዲ ሃይሞኖታዊ ጉዳያትን ሚኒስትርይ ትምህርትን ስርዓት ኣስመራ፡ ኩለን ኣብያተትምህርትታት ኣብ ትሕቲ ኣብያተክሪስትያናትን መሳጊድን ዝማሓደራ ዝነበራ፡ ኣብ ትሕቲ ሚኒስትሪ ትምህርቲ ክማሓደራ ዘነጽር ትእዛዝ ኣማሓላሊፉ ከምዝነበረን፡ ካብ 2016 ጀሚሩ ኣብ መንጎ ኩለን ኣብ ትሕቲ ቤተክርስትያንን መሳጊድን ዝማሓደራ ኣብያተትምህርት ምስሕሓብ እኳ እንተነበረ ኣብ መጨረስታ ኣብ ትሕቲ ሃይሞኖታዊ ትካላት ዝማሓደራ ኣብያተ ቤትምህርታት ንክፍሊ ትምህርቲ ክርከባ ዝእዝዝ ሓደ ዘዋሪ መልእኽቲ ከምዝሰደደን ፡ ብመሰረት ነቲ ዝተሰደ ዘዋሪ መልእኽቲ ብምቕዋም፡ ሓጅ ሙሳ መሓመድ ኑር ምስ ዛጊት ኣስማቶሙን ጽፍሒ ስልጣኖም ዘይተነግረሎም፡ ሰበስልጣን ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍ ኣካላዊ ርኽክባትን ዘተታት ከምዘካየዱን፡ ኣብቲ ዘካየድዎ ዘተታት ከምዘይተራዳዱኡን፡ ነቲ ዘካየድዎ ዘተ ድማ ናብ ስድራቤት ተማሃሮን ንኮሚተታት ወለዲ እታ ቤት ትምህርቲ ክቕርቡ ብሙኻኖም ኣፍሊጦም፡ ንኮሚተታት ወለዲ እታ ቤት ትምህርቲ ብምሕባር፡ ኮሚተታት ወለዲ እታ ቤት ትምህርቲ ኣቕሪቦም መልሶም ብጹሑፍ ክምልስሎም ሙኻኖም ከምተሳነበትዎም” ይገልጹ።ድሕሪኡ፡ ሓጅ ሙሳ መሓመድ ኑር ምስ ኮሚተታት ወለዲ እታ ቤት ትምህርቲ ተዛትዮም ፡ ንስድራቤት ተማሃሮ ኣኺባ ብምጽዋዕ ነቲ ኩነታት ክገልጽሎሙን ርእይቶታት ወለዲ ተማሃሮ ንክሰምዑ ብምባል ሰፊሕ ኣኼባ ብምጽዋዕ መግለጺ ን ንህዝቢ ነቲ ኩነታት ኣመልኪቶም ኣብ ዕለት 15/10/2017 ድሕሪ ምሃቦም ኣብ ወለዲ ተማሃሮ ቑጣዔ ከምተሰምዔ ነታ ቪድዮ ምርኣይን ምስማዕን ኣኻሊ እዩ። ከም መቀጸልታ’ዚ እኼባ’ዚ ኣብ 20 ጥቕምቲ 2017 ሓጂ ሙሳ መሓመድ ኑርን ካልኦት ዉሑዳት ሰባት ዝተወሰኽዎም ብጸጥታ እቲ ስርዓት ኣብ 5ይ መደበር ፖሊስ ከምትኣሱሩ ብንጹር ይገልጹ። ሳዕቤን እታ ኣኼባን ማእሰርቲ እዞም ውሩይን ቅቡልን ሓጂ ሙሳ መሓመድ ኑር፡ ናይዚ ኩሉ ኩነታት እኩብ ድሙር፡ ነቲ ኣብ 31/10/2017 ዝተኸስተ ናይ ቅሬታ ናዕቢ ሙኻኑ ክራጋገጽ ዝክኣል ሓቂ’ዩ። ዕልመናዊ ፖሎቲካዊ ስርርዕ (a secular state) ክሳብ ዝኾነ፡ መንግስቲ ኣብ ትካላት ሃይሞኖታት ኢዱ ከእቱ የብሉን! ሃይሞኖታዊ ትካላት እዉን ኣእዳወን ኣብ ፖሎቲካዊ ጉዳያት ከእትዋ ዘይብሎም ከንሶም፡ ስርዓተ ኣስመራ ብቀጻሊ ብክፍሊ ሃይሞኖታዊ ጉዳያት ኣቢሉ፡ ብእብረ ኣብ ሃይሞኖታዊ ትካላትን ጉዳያትን ክኣቱ ከምዝጸንሔ ኩሉ ዝፈልጦ ሓቂ እዩ። እዚ ጦብሎቕሎቃት ዝፈጠሮ ዕልቕልቕ ሙኻኑ ድማ ዘጣራጥር ጉዳይ ኣይኮነን። ኣብ ዉሽጢ ኤርትራ፡ ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነትን ምልዓላትን (civil disobedience) ሕጂ ሓድሽ ዝተራእያ ተርእዮ ኣይኮነን። ንትሕዞን ምሕደራ መሬትን ካልእ ሲቪክ መሰላት ኣልዒሎም ቅድሚ ሕጂ ዝተላዕሉን ብደረጃ ዓዲ ተንቀሳቂሶም ዓዲ ብሙሉኣ ዝተኣስሩ ከምዝነበሩ መላእ ህዝቢ ኤርትራ ዝፈልጦ ጉዳይ እዩ። የግዳስ ኩሉ ዝላዓል ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነት ኣብ ክንዲ ክሳብ እቲ ገባቲ ስርዓት ዝወድቕ ዝቕጽል፡ ዉልዕ ይብል እሞ ኣብ ዝሓጸረ ስዓታት ድማ ተደርቂሱ ይተርፍ። ስለምንታይ ይመስለኩም? ንኸምዚ ዓይነት ፍጻሜ ብኸመይ ብዉሑሉሉን ጥንቑቑን ብልሓት ንዓወት ትመርሖን ትኣልዮን እዩ። ኣብ ፖሎቲካዊ ባይታ ኤርትራ ዛጊት ክሳብ ሕጂ ንኸምዚ ሰላማዊ ኣጋባብ ብዉሑሉል ኣጋባብ ብዉጥን ፡ ዉጥን ሓደ ዉጡን ክልተ ዉጥን ሰለስተ ብምዉዳድ ብቕድመተከተል ክመርሕ ዝኽእል መሪሕ (vanguard-leadership) ዛጊት ኣይተፈጥረን ዘሎ። እቲ ምንታይስ እቲ ህዝቢ ካብቶም ኣብ ፖሎቲካ፡ ሰብኣዊ መሰላት፡ ኣብ ሲቪክ/ሲቪል ማሕበራትን ምንቅስቃስን ኣብ ናይተጻይ መራኸቢ ቡዙሓን ቁጽጽር ዝነጥፉ ዝነቕሔ ከንሱ ዛጊት ግን ናይ ገዛእ ርእሱ ሲቪክ/ሲቪል ፡ ማሕበረ ኮማዊን ሞያዊን ዉዳቤ ብዘይምህላዉን እዩ። ልዕሊ ኹሉ ከነስተብህላሉ ዝግባኣና መሰረታዊ ጉዳይ ኣሎ። ንሱ ድማ ኤርትራ ከምሓንቲ ናይ ፖሊስ-ሰራዊት ስርርዕ ዘለዋ ሃገር መጠን፡ ብሙሉኡ ኤርትራዊ ወትሃደራዊ ታዕሊም ዝወሰደን ኣጣቃቕማ ብረት ዝፈልጥ ስለዝኾነ፡ ዋላእዉን ብሰላማዊ ኣጋባብ ቃልሲ መሰሉ ንምርግጋጽ እንተነቀለ፡ ብቀሊሉ ንኣካላዊን ምርጻም ክቕየር ከምዝኽእል ዘማትእ ኣይኮነን። ነቲ ዉዱዕ ክዉንነት ኣብ ግምት ኣእትዩ ዝመርሕ ዝበቕዕ፡ ህዱኡ ዓቕሊ ናይ ሲቪል ሓንጎልን ባህረያትን ዝዉንን ናይ ዉሑዳን-ኣድማዕቲ ሰኪዔት መርበብን (effective minority networks) መሪሒነት ከድሊ’ዩ። እዚ ናይ ዉሑዳን-ኣድማዕቲ ሰኪዔት መርበብን ምስ ጹኑዕ ናይ ዜጋታት ህዝባዊ ዉደባታት ተዳማሚሩ፡ ኣብ ዉሽጥን ወጻኢን ከም መርፍእን ፈትልን ብምትእስሳር ንዘጋጥም ተረኽቦታትን ሲናርዮታትን ብዉጥንን ስሩዕ ስትራተጂን ስልቲን ክመርሕ ዝበቕዕ መሪሕነት ክፍጠር ኣለዎ። ከምዚ ዓይነት መሪሕነት እንተዘየሎ ኩሉ ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነት ከምዚ እንጣጢዕ ኣብ ዝረሰነ ሞቕሎ ክቕሎ እንኮሎ ጠራዕራዕ እንዳበለ ካብቲ ዝረሰነ ሞቕሎ ናብቲ መጋርያ ሓዊ ዝነጥብ! ልክዕ ከምኡ ክኸዉን’ዩ። ኩሎም ዝሓልፉ ህዝባዊ ምንዓዓባት እብ ኤርትራ ድማ ከምዚ ዝጣሕመስክዎ ዕድላት’ዩ ኣጋጢምዎም። ኣብ መዛዘሚ ዓንቀጸይ፡ ቡቁዕ ህዝባዊ መሪሕነት ዘይብሉ፡ ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነት ኣይዕወትን ስለዝኾነ፡ ንህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነት ዘታባብዑ ሮቓሒታት ክርኣዩ እንከለዉ ጥራይ ሰላማዊ ሰልፊ ምግባር ዘይኮነ ነዚ ዝመርሖ ጉሁዱን ስዉር ናይ ጽላሎት መሪሒነት ከነዋድድ ግቡእን መሰረታዊ ጉዳይ እዩ። ብዝኾነ ነቲ ኣብ ዕለት 31 ጥቅምቲ 2017 ብተማሃሮን ስድራቤታት ተምሃሮ ቤት ትምህርቲ ኣልድያ ኣል እስላምያን ደገፉቱን ተማጻደቑቱን ዝተኻየደ ቁጡዔ ኣብ ልዓቱ ዘሎን፡ ዝተራእየ ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነት እቲ ቀንዲ ኣጋባብ ቃልሲ መፍትሒ ናይቲ መንቀሊ ዝኾነ ጸገም ሙኻኑ፡ ይኣምንን ብኡ መስረት ድማ ደገፌታይን ምትብባዓተይ ይህቦ ኣለኹ። ኩሎም በዚ ጉዳይን ካልእ ፖሎቲካዊ ጉዳያት ተኣሲሮም ዘለዉ ዜጋታት፡ መንግስቲ ኤርትራ ብዘይ ዉዓል ሕደር ክፈትሖም ይምሕጸን ኣለኹ። ሕቶ ሰላምን ስምረትን ክልዓል እንከሎ ብሓፈሻ ህዝቢ ኤርትራን ህዝቢ ኢትዮጵያን፡ ብፍላይ ድማ ህዝቢ ኤርትራ ከቢድ ዋጋ ከፊሉ ክሳብ ሕጂ ዘይራጋገጾ ጉዳይ’ዩ። ኤርትራዉያን ንነዊሕ ዘመናት ብዝተፈላለዩ ባዕዳዉያን ወረርቲ ዝተቐጥቐጥናን ኣዝዩ መሪር ሰዉራ ብእስትንፍስ ዘይህብ ኪናት ዝተሰነየ ስለዝሓለፍና፡ ልዕሊና ንሰላም ዝደልያን ዝብህጋን ክህሉ ኣይክእልን እዩ እኳ እንተዘይተባህላ፡ ሰላም ከምእንደሊ ርጉጽ እዩ። ስለዚ ንሕና ጽሓፍቲ እዛ ዓንቐጽ እዉን’ዚ ሕቶ’ዚ ክልዓል እንከሎ ከም ሰብና ንብህጎን ኣንጻር ሰላምን ስምረትን ብፍላጥ ይኹን ብዘይፍላጥ ካይንጉስጉስ እንጥንቀቀሉ ጉዳይ እዩ። ኣብ ቶሞክሮናን ሂወትናን ዝቁሹሹ ሰባት: ፖሎቲካዊ ዉድባትን መንግስታትን ስለዝበዝሑና ግን ነዚ ተላዒሉ ዘሎ “መዝሙር ሰላም” ንሰላም ተባሂሉ ስለዝተዘመረ ከምዘለዎ ንቅቦሎን ንስዕቦን ዘይኮነ፡ ዉድዓዊን ባዕላዊ ኩዉንነቱ ዝበሰለን ብኸመይ ኣጋባብ…ወ.ዘ.ተ ዝብሉ ካብ ነቐፌታዊ-ኣታሓሳስባ ዘመንጨዉ ሕቶታት ብምልዓል ክንፍትሾ ወሲና ኣሎና። ብቀዳምነት ብንጹር ዝኾነ-ይኹን ሰብ ክፈልጦ ዝግብኣና ሓቕታት ኣሎ። ንሱ ድማ ፡ ዝምድና ኤርትራን ኢትዮጵያን ብቡዙሕ ምትሕልላኻት ዝሰገረ’ዩ። ዋላ እቶም መራሕቲ ኢትዮጵያ ክሳብ ሕጂ ዘይዓርፍሉ፡ ካብ ኣፍደገ-ባሕሪ ጀሚሩ ክሳብ ኤርትራን ኢትዮጵያን ኣብ ሓደ ሃገር ናይ ምጥርናፈን ከይተረፈ፡ ቅድም ብመልክዕ ወራራት ራእሲ-ኣሉላ፡ ቀጺሉ ብፈደረሸን፡ ቀጺሉ ኤርትራ ከም ሓንቲ ክፍሊ-ግዝኣታት ኢትዮጵያ ብምጽንባር ንነዊሕ ወሎዶታት ተፈቲኑ ኣበርዒኑ ዝተረፈ’ዩ። እኩብ ድምር ናይ’ዚ ናይ ዓመጽን ምግባትን ተሞክሮ’ዚ ውጽኢት ናይ’ዚ፡ ኢትዮጵያውያ ንኤርትራ ኣብ ምስሳይን ምምራሕ፡ ኣብ ጊዜ እምባሮጣርያዊ ሃይለ ስላሴ፡ ቀጺሉ’ውን ስርዓት ደርጊ፡ ሕጂ እዉን ኣብ ጊዚያት ወያኔ ከምዘይተዓወተ ንመላእ ዓለም ዘጣራጥር ታሪኽ ኣይኮነን። ድሕሪ ኣዝዩ መሪርን ሰፍ-ዘይብል ዋጋ ዝተኸፍሎ ናይ 30 ዓመታት ሓንፈጽ ጎነጻዉን ፖሎቲካዊን ተጋድሎ፡ ዝተራጋገጸ ናይ ኤርትራ ልዑላዉነትን መሬታዊ ነጻነት እዩ። ህዝቢ ኤርትራ ነዚ ካብ ኢትዮጵያ ብቀጻሊ ዝዉርወር ጡሙሓት ከም መቀጸልታ ወትሃደራዊ ፖሎቲካዊን ዓወቱ፡ ብሕጋዊ ሪፈረንደም ሓንሳብ ንሓዋሩ መደምደምታ ክገብረሉ ፈቲኒ የግዳስ እቲ ዝጸንሔ ዕድላትን ጥሙሓትን ብኡ ክዉዳእ ከምዘይክኣለ ኣጸቢቕና ተረዲናዮ ኣሎና፡፡ ኤርትራ ይኹን ኢትዮጵያ ዋላ እንተደለያ ንዝምድና ናይ ክልቲኡ ሃገራት፡ ከም ድላያን፡ ክዉልዕዖን ክጥፍኦኦን ኣይክእላን እየን። እቲምንታይስ ኤርትራ ምስ ኢትዮጵያ ብኣንጻሩ ኢትዮጵያ ምስ ኤርትራ፡ ዘሎና ዝምድና፡ ከም ተራ ናይ ካልኦት ሃገራት ጎሮባብቲ፡ ከም ናይ ጂቡትን ኢትዮጵያን፡ ሶማልን ኢትዮጵያን፡ ሱዳንን ኢትዮጵያን ጥራሕ ኣይኮነን፡፡ ካብ’ዚ ብዕሙቐት ዚፈልዮ፡ ናይ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዝምድና፡ ብስልጣኔዊ፡ መግዛእታዊ፡ ደማዊ ቅድመሱሩት ዝምድናታት፡ ታሪኻዊ፡ ባህላዊ፡ ኤትኒካውን …ወ.ዘ.ተ ገጽታታት ስለዘለዎ፡ እቶም ናይ ፖሎቲካ ጨለታት ካብ ክልቲኡ ኣህዛብ ዝፈርዩ፡ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዘሎ ፍልልይ ምስ ተንካፊ ስነኣእሙራዊን ስምዒታዊን ብምትእስሳር ንምንጻሩ ስለዘሸግሮም ነቲ ህዝቢ እዉን ኣብ ሽግር የእትዉዎ። እቲ ምንታይስ ኤርትራዊ መቦቆል ዘለዎ ንኢትዮጳዊ መንነት ዝተቀበለን፡ ኢትዮጵያዊ መቦቆል ዘለዎ ንኤርትራዊ መንነት ዝተቀበሉ ቀንዲ መንቀሊታቱ እዚ ኣቀዲምና ዝገለጽናዮ ምትሕዉዋስ’ዩ። ከምኡ ስለዝኾነ ሓደ መራሒ ናይ ኤርትራ፡ ኢትዮጵያ እዉን ናቱ ትመስሎ፡ እቲ ኣብ ኢትዮጵያ ዝመርሕ ዘሎ ድማ ንኢትዮጵያ እንዳመርሔ ከንሱ ኤርትራ ናቱ ትመስሎ። ካብዚ ዝነቐለ እዩ ድማ እቲ ናይ ኤርትራን ኢትዮጵያን ጉዳይ ዝተሓላለኽን ሰላምን ቅሳነትን ተሳኢኑ ዘሎ። ኣብዚ ቅንያት’ዚ ኣብ ዉሽጢ ኢትዮጵያ ናይ “መዝሙር ሰላም” ንህዝቢ ኢትዮጵያን ኤርትራን ዝብል ጭርሖ ብምልዓል ኣብ መንጎ ዜጋታት ኤርትራን ኢትዮጵያን ናይ ሰላም ዘተ-ጽምዶ ክካየድ ሙኻኑ ብጹዑቕ ይጉስጎስን ብመንጽሩ ተቃዉሞታት የንሂ ኣሎ። ነዚ ህቦቡላ መንቀሊኡን መዕለቢኡን ዘይተፈለጡ፡ ብሃዉሪ ዝድግፍን ዝነጽግን ጽሑፋት ኣብ መራኸቢ-ቡዙሓን ሽታሕታሕ ክብሉ ይርኣዩ ኣለዉ። ዘደንጹ ነገር እንተሃልዩ ድማ ብቀጻሊን ብዘይስክፍታን ምስትዉዓልን፡ ህቦቡላ ምስተላዕለ፡ ብቅጽበት ዝላዓሉ ብብዝሒ ሰባት ምህላዉም’ዩ። ነቲ ተላዒሉ ዘሎ ህቦቡላ ካይፈለጥዎ፡ ካይመርመርዎን ካይተረድእዎ ድማ፡ ብጹሑፋቶም ገሊኦም ክጻረፉ፡ ክንእዱ፡ ክርዕሙ ወይ ክነጽጉ ይርኣዩ ኣለዉ። እዚ ጻዉዒትን ተበግሶን’ዚ ኣብ ኢትዮ-ኤርትራ ግርጭት ሓድሽ ነገር ኣይኮነን። ቅድሚሕጂ እዉን ገለ ኤርትራዉያን ዝወደብዎ ኣብ ንሓንቲ ለይቲ ንሓደ ሰብ $300.00 ዶላር ዝኽፈሎ ሆቴል ብምክራይ፡ ኣብ ሕቡራት ሃገራት ኣሜሪካ (usa) ኣብ 2011 ንሰላም ቀርኒ-ኣፍሪቓ ናይ ዘተ-ጽምዶ ኣልዒሉ ዝዘተየ ዋዕላ ተኻይዱ ነይሩ’ዩ። ከሙ እዉን ኣብ ትግራይ ነዚ ኣብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዘሎ ፖሊሲ ኣይሰላም ኣይኩናት፡ ብሓፈሻ ነቲ ኣብ ዶባት ክልቲኡ ሃገራት ዝነብር ህዝቢ፡ ብፍላይ ድማ ንህዝቢ ትግራይ ይሃስዮ ስለዘሎ፡ እቲ ኣይሰላም ኣይኩናት ፖሊሲ ክቕየር ከምዘለዎ ዝጠልብ ተበግሶታት ብዉልቀሰባት ተጋሩ ተላዒሉ ከምዝነበረ እዉን ዝዝከር እዩ። እዚ ሕጂ መዝሙር ሰላም ቢሉ ተላዒሉ ዘሎ እዉን ብትሕዝትኡን ኣቃዉሙኡ ካብቶም ኣቐዲሞም ዝተኻየዱ ዝፍለ እኳ እንተዘይኮነ፡ ኣብ ስርዓት ኣዲስ-ኣበባ ብዉሽጡን ብደገን ኣብ ወጥሪ ኣብ ዝኣተወሉ ጊዚያት ብሙኻኑ፡ ምናልባሽ ከም ትኪ ካብ ተዓብዒቡሉ ዘሎ ወጮ ሽግራት መዉጽኢ ዶ ክጥቀሙሉ ይደልዩ ኣለዉ ዝብል ሓሳብ ቅጅል ይብለካ’ዩ። ኣብ ዝሓለፈ ጊዚያት ገለ ካብ ላዕለዎት ክዋድራትን ናይ ፖሎቲካ ጨሌታት (elites) ተጋሩ፡ ከም ብዓል ኣቶ ገብሩ ኣስራት፡ ኣቶ ስብሓት ነጋን ፈሊጣናቶም ኣብ መራኸቢ ቡዙሓን ክጎስዕዎ ዝጽንሑ ዘረባታት ኣሎ። ንሱ ድማ “ ኣቀዲምና ኣብ ናይ ኤርትራ ኩነታት ዝነበረና ኣራዳድኣን ፖሎቲካዊ መርገጺታት ዳግም ግምታት ክግበሮ ኣለዎ” ብምባል ፡ ኣንጻር እቲ ኣቀዲሙ ዝነበሮም መርገጺታቶም ኣብ ልዕሊ ኤርትራ ንክቕየር ኣብ ዝተፈላለዩ ኣጋጣሚታት ከጽዕዱ ከምዝጸንሑ” ኩሉሰብ ዘዳመጾን ዝተረድኦን ጉዳይ’ዩ። ኣቀዲሙ ዝነበሮም መርገጺ ኤርትራ ናጻ ክትወጽእ፡ ህዝቢ ኤርትራ ልዕላዊን ሓራ ህዝቢ ክኸዉን እዩ ዝነበረ። ሕጂ ድኣ እንታይ ዘጣዕስ ጉዳይ ስለዝተረኽበ’ዩ ነዚ ሰፍ ዘይብል መርገጺኦም ከም ሰተታ ብቀሊሉ ክግልብጥዎ ዝዋናወኑ ዘለዉ? ይክኣል ዶ ይኸዉን? ነዚ ብዉሽጦም ዝሓስብዎ ዘለዉ መተግበሪ ዕድሜ፡ ናይ ወጻኢ ሃገራት ፖሎቲካዊ ደገፍን ንዋትን ክረኽብሉ ዝኽእሉ፡ ኣዝዩ ጸቢብ ዕድላት እኳ እንተኾነ፡ ባህግታቶም ከምቲ ጀነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ፡ ሓለቓ ስታፍ-ነበር ሰራዊት ኢትዮጵያ፡ ኣብቲ ምስ ኣዲስ ዘመን ዚበሃል መንግስታዊ ጋዜጣ ዚገበሮ፡ ኣብ 12 ሰነ 2017 ተሓቲሙ ዚተዘርግሐ፡ ነዊሕ ቃለ-መጠይቕ፤ ብሓጺሩ፡ ኢትዮጵያ ዓባይ ናይ ቀይሕ ባሕሪ ሃገር ምዃና፣ ዳግም ናይ ቀይሕ ባሕሪ ሃገር ኪትከውን ከም ዘለዋ፣ ቀይሕ ባሕሪ ንምቍጽጻር፡ ብወተሃደራዊ ሓይሊ ይዅን ብዚዀነ መንገዲ፡ ዕድመ ሻዕብያ ምሕጻር፡ ንኢሳያስ ምልጋስ ከም ዘድሊ፣ ብምግላጽ የራጋግጾ’ዩ። እቶም ዓበይቲ ናይ ፖሎቲካ ጨሌታት ከምዚ እንዳበሉ፡ እቶም ንሳቶም ዝመልመልዎምን ዝልእኹዎሙን ክዋድራት ከመይ ቢሎም ኣንጻር እዚ ክሓስቡን ከተግቡሩን ይኽእሉ ኣብ እእሙሮና ምምላስ ከድሊ’ዩ። ኪናትን ሰላምን ናይ ገዛእ ሩሱን ዓለምለኻዊ ሕጊታት ኣለዎ። ስለዚ ሃገራትን ኣህዛብን ብዓለምለኻዊ ሕግታት ተቀይዶም ክናበዩ ስለዘለዎም ። ንኪናትን ሰላምን ኣመልኪቱ ኣብ 24 ጥቅምቲ 1945 ኣብ ተግባር ዝዉዓለ ናይ ሕቡራት ሃገራት ቻርተር ከምዚ ዝስዕብ ብምባል ኣስፊርዎ ኣሎ፡- 2.ዓንቀጽ 2 (4) ኣባላት ሕቡራት ሃገራት ኣብ ዓለምለኻዊ ዝምድናታተን፡ ንናይ ካልኦት ሃገራት መሬታዊ ልዑላዉነትን ፖሎቲካዊ ናጽነተን ብዝጻባእ ዓይነት ሓይሊ ካብ ምጥቃም ወይ ክኣ ሓይሊ ክንጥቀም ብምባል ካየፈራርሓ ክቁጠባ ከምዘለወን የነጽር። 3.ዓንቀጽ 51 ሓንቲ ሃገር ንኻልእ ሃገር ብኣጽዋር-ኪናት ምስተጥቕዓ፡ ተጠቓዒት ሃገር ብዉልቃ ወይ ድማ ምስ ማሓዙታን ካልኦት ጉዱሳትን ብምትሕብባር ንርእሳ-ክትኻላኸል ሓይሊ ክጥቐም ከምትኽእል የነጽር። ከምዚ ዓይነት ሕጊታት ምህላዉ እንዳፈለጡ ‘ዮም ብዓል ጀነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ፡ ኣብ መራኸቢ ቡዙሓን ኪናት ዝእዉጁ ዘለዉ። ስለዚ በቲ ሓደ ወገን መዝሙር ሰላም ብኻልእ ወገን ወረ ኪናት ከመይ ከምዝጥዓዓም ንምርድኡ ኣጸጋሚ እዩ። ብዝኾነ እቲ ኣብ መንጎ ኢትዮጵያን ኤርትራ ዘሎ ጸገማት፡ ኣብ ላዕሊ ብሕጽር ዝበለ ኣሚትና እኳ እንተሃለና፡ ናብዚ ድሒሩ ኣብ 1998 ብዶብ ተሳቢቡ ዝተፈጥረ ግርጭት ገጽና ከነስተብህል መታን፡ ኢትዮጵያ ነቲ ኣቀዲማ ዝተቀበለቶ ዉሳኔ ዶብ ኮሙሽን ኣብ 13 ሚያዝያ 2002 ዝተኣወጀ ብምቅዋም፡ ከም መተካእታ ናይቲ ዓለምለኻዊ ዉሳኔ ዳንነት፡ “ብመትከል ነቲ ዉሳኔ ተቀቢልናዮ ኣለና፡ የግዳስ ንኣታጋብርኡን ካልኦት ጉዳያትን ብዝምልከት ንምዝታይ ከም ቅድመኩነት ኣብ ዘተ ክንኣቱ ኣሎና ብምባል”፡ ነቲ ክካየድ ዝደልይዎ ዘተ “ሰላም” ዝገርሑ ብዓል 5 ነጥብታት እማሜ ኣብ 2004 ነዲፉ ከምዝኣወጀ ኩሉ ዓለም ዝፈልጦ ጉዳይ’ዩ። ኣየናይ ስርዓት እዩ ጸግዒ ናይ ዓለምለኻዊ ዳንነትን ሕጊን ከምዘለዎ እዉን ሙሉ ጊንዛቤታት ከምዞሎና ክርሳዕ የብሉን። ቅድሚኡ ካብ ግንቦት 1998 ጀሚሩ ክሳብ እዛ ዕለት እዚኣ፡ ኢትዮጵያ ኣብ ልዕሊ ኤርትራ ዝተኸተልዎ ፖሊሲታት ናይ ኩሉእንትናዊ ዓቕምታት ናይ ምሽምራርን ወትሃደራዊ መናወራ ፖሊሲ (policies of containment and deterrence) ን ቀጺሉ ምስ ምእዋጅ 5 ነጥብታት ሰላም ፡ ፖሊሲ ኣይሰላም ኣይኩናትን (no peace, no war) ብምድራብን ካልኦት ዝተፈላለዩ ዓለምለኻዊ ዲፕሎማስያዊ ሽርሕታት ብምጥቃም ንኤርትራ ኣብ ትሕቲ ማዕቐብን ዓለምለኻዊ ዲፕሎማስያዊ ተነጽሎ ከምትድቕደቕ ገይሮም እዮም። እዚ ንኤርትራን ፖሎቲካዊ ስርዓታን ብደም-ዋሕዲ ዝተጠቕዔት ሃገር (anaemic state) ኮይና ንናይ መልኣከ-ሞት ሃገር (phantom state) ከትቅየር ንምግባራ ዝተዋደደ ፖሊሲ’ዩ ነይሩ። እዚ ፖሊሲ’ዚ ብሃበስ-ቀደስ ዘይተገብረ፡ ከም ሳዕቤኑ ምዉዳቕ ስርዓት ኣስመራን ምብትታን ህዝቢ ኤርትራ ክጽበዩ ጸኒሖም እዮም። ስለዚ ከምተጸበይዎ ሙሉእ-ብሙሉእ ስለዘይሰርሓሎም ብመንጸሩ ንዖኦም እዉን ስለዝሃሰዮምን፡ እቲ ኣብ ማእከላይ ምብራቕ ዝተፈጥረ ኩነታትን ጂኦ-ፖሎቲካዊ ኩነታት ቀርኒ-ኣፍሪቃ ስለዝተቃያየረ ስርዓተ ኣስመራ ማይ-ሓይሊ ረኺቡ ብመንጸር ስርዓት ኣዲስ ኣበባ ሂወት ዘሪኡ ብምቅጻሉን ኣብ ዉሽጢ ኢትዮጵያ ቀጻሊ ህዝባዊ ዘይሙኡዙዙነትን ናዕብን ብእብረ ይቕጽል ብምህላዉን እቲ ናይ ምዕራብ ሃገራት ምድግጋፍ እንዳስሓወ ምኻዱ(እዚ ሕጂ “መዝሙር ሰላም” ዝብሃል ዘሎ “ሓድሽ ኣጋባብ” ተጠቂሞም ንህዝቢ ኤርትራ ነቲ ቀጺሎም ክወስድዎ ዝደልዩ ስጉምትታት ከዳልዉዎን ከላሙድዎን ዝደልዩ ዘለዉ ይመስሉ። ኣብዚ እዋን’ዚ ኤርትራ ብደም-ዋሕዲ ዝተጠቕዔት ሃገርን ናይ መልኣከ-ሞት ሃገርን መንእሰያታ ኣብ መላእ ዓለም ፋሕ ዝበለ ሃገር ኮይና፡ ኤርትራዊ ሃገራዉነትን ሓርበኛነትን ድማ ብሓያል ናዕታ ብዉሽጥን ደገን ተሃሪሙ ክሳብ “ሰዉራ ኤርትራ ክካየድ ኣይነበሮን” ኣብ ምባል ኣብተበጽሓሉ እዉን’ዩ “መዝሙር ሰላም” ዝብሃል ዘሎ። እዚ ዘይተወደነ ኩዉንነት ዝፈጥሮ ነባሪ ሰላም ከ ክመጽእ ይኽእል ዶ? 3.ደፋእትን ቀለስቲ ሰላም መን እዮም? ቀንዲ መላዕሊኦም (motive) እንታይ እዩ? ሕቶ ሰላም ድዩ ወይስ ሙቀት ህዝቢ ኤርትራን ኢትዮጵያን ንምዕቃኑን ኣጋዉል ኩነታቱ ኣዛሪብካ ንምፍላጡ እዩ። 7.ሕቶ ምምልካት ዶብ፡ ሕቶ ሉዕላዉነት፡ ሕቶ ኣይሰላም ኣይኩናት…ወ.ዘ.ተ ክሳብ እቲ ናይሰላም ዘተ ዝዕወት ከምዘለዎ ክቕጽል ድዩ?……..ወ.ዘ.ተ ኣእላፍ ሕቶታት ክምለሱ ዘለዎም ኣለዉ። እዞም ሕቶታት እዚኣቶም ብርግጽ መልስታቶም ምስተፈልጠ ጥራይ እዩ ዘተ ሰላም ክካየድ ዝግባእ ኮይኑ ይስማዓና ኣሎ። ስለዚ መን እዮም ነዚ ንድፊ ሰላም ሓንጺጾም ንምትግባሩ ተዳልዮም ዘለዉ? ሰለብሪቲ-ኢቨንትስ ዝብሃል ትካል ድዩ? ከመይሉ ሓደ ትካል ህዝቢ ወይ ህዝባዊ ትካል ዝኸዉን? እቲ ምንታይስ ህዝቢ ኤርትራን ኢትዮጵያን ሰላም ዝደሊ ኣህዛብ ይኹን እንበር፡ ክሳብ ሕጂ ስርዓት ኣስመራ ይኹን ስርዓት ኣዲስ ኣበባ፡ ህዝቢ ናይ ልቡን ድሌቱን ክገብር ዕድል ኣይሃቡዎን ዘለዉ። መን እዮም ከ ኣብዚ ዘተ ክሳተፉ ዝድለዩ ዘለዉ? ኣብ ኢትዮጵያን ኤርትራን ዘለዉ ፖሎቲካዊ ስርርዓት እንታይ ሙኻኖምን ብኸመይ ይሰርሑ ኣጸቢቕና ንፈልጥ ኢና። ካብ ኣፍሉጦና ዝነቀለ ድማ ክልቲኡ ስርዓታት ንቀርኒ-ኣፍሪቃ ሓደጋ ሙኻኖሙን ክእለዩ ከምዘለዎም ንመዝን። ምእላይ ናይዞም ስርዓታት ጥራይ ዘይኮነ መተካእትኦም’ዉን ብናይ ዘመናዊ ናይ ዜጋታት ሃገርን ፖሎቲካዊ ስርርዓት ኽኾኑ ንቃለስ። ናይ ኢትዮጵያ ጉዳይ ኢትዮጳዉያን ኣለዉዎ ፡ ናይ ኤርትራ ጉዳይ ድማ ኤርትራዉያን ኣለናዮ። ብዝኾነ ነቲ ኣይሰላም ኣይኩናት ኩነታት ብተክኒካዊ ኣዛራርባ እዘን ሃገራት ኣብ ኪናት ከምዘለዋ ስለዝምዘን፡ እቲ ኩነታት ንምፍትሑ ክልተ መገድታት ጥራይ እዩ ዘሎ። ሳልሳይ ወይ ራብዓይ መገዲ ወይ ሓሙኽሽታይ ሕብሪ ዝባሃል ነገር የሎን። ቀዳማይ መገዲ ፍታሕ፡- እቲ ኣይሰላም ኣይ ኪናት ፖሊሲ ብስርዓት ኣዲስ ኣበባ ዝተገብረ ስለዝኾነ፡ ነዚ ፖሊሲ ከልዕልዎ ኣዝዩ ቀሊል እዩ። እዚ ፖሊሲ’ዚ እንተተላዒሉ፡ ብቀጥታ ናብቲ ዉሳኔ ናይ ዶብ ኮምሽን ኢትዮ-ኤርትራ ክመርሕ ስለዝኾነ፡ ነቲ ኣብ ካርታ ብስእሊ ሰፊሩ ዘሎ ዶብ (boundary delimitation) ኣካላዊ ምምልካት ምግባር’ዩ። ስለዚ እዚ ስጉምትታት’ዚ ነቲ ናይ ሰላም መገዲ ሓደ ክልተ እንዳበለ ብቅድመተከተል ክመርሖ ሙኻኑ ዘጣራጥር ኣይኮነን። ንምንጻሩ ዝኣክል፡ እቲ ኣብ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዝነበረን ዘሎ ግርጭታት ኣብ መንጎ ክልቲኡ ኣህዛብ ዘይኮነ፡ ኣብ ናይ ክልቲኡ ኣህዛብ ዝፈርዩ ዝገቡቱን ዝመርሑን ፖሎቲካዊ ስርዓታትን ፖሎቲካዊ ዉድባትን ዝነበረን ዘሎን’ዩ። እቶም ስርዓታት’ዮም ድማ ነዚ ክልተ ኣህዛብ ነንሕድሕዱ ዘፋልስዎ ዝነበሩን ዘለዉን እንበር፡ ኣብ መንጎ ህዝቢ ኤርትራን ህዝቢ ኢትዮጵያን መረስረታዊ ግርጭት የሎን። ነንሕድሕዱ ዝተቓራረበ ኣህዛብ ስለዝኾነ ብዘይ ገለ ጸገም ብሰላም ክነብር ዝኽእል’ዩ። ስለዚ ህዝቢ ኣኪብካ ንፖሎቲካዊ ስርዓታት ምዕራቕ ዶ ይቀልል ወይስ እቶም ፖሎቲካዊ ስርዓታት ብሕጊን ፍትሒን ተቀይዶም ኣብ ማዕርነትን ምክብባርን ዝተመስረተ ናይ ሰናይ ጉርቡትና ፖሊሲ ከምዝኽተሉ ምግባር? እንተሓንጊዶም ድማ ምእላዮም ጥራይ’ዩ ዘዋጽእ። ስለዚ ናይ ብሓቂ ሰላም ዝድለ እንተሃልዩ ብዓለምለኻዊ ሕጊ ተቀይድካ ናይ ማዕርነትን ምክብባርን ንናይ ሓባር ረብሓ ንምርግጋጽ ክሕሰብ ኣለዎ እምበር፡ ኣብ መጋራጃ “መዝሙር ሰላም” ተሓቢካ ንእኪት ምሕሳብ ናይ ኮንቱ ኮንቱነት እዩ። ዘተ ሰላም ኢትዮ-ኤርትራ ክዕወት መጀመርታ እቶም ገዘፍቲ መሳናኽል ዝኾኑ፡ ገባቲ ስርዓት ህ.ግ.ደ.ፍን ሓዉሲ-ምልካዊ ስርዓትወያኔ ክእለዩ ኣለዎም። ድሕሪኡ ብዉሱናት ሰባት ወይ ብዝተሓርዩ ሰባት ጥራይ ዘይኮነ፡ በብጽፍሑ ህዝቢ ብቀጥታ ብተወከልቱን መራሕቱን ዝሳተፈሉ ክዉንነት ክፍጠር ኣለዎ። ሳሕቲ ነገራት ይርኣዩኻ እሞ ብዛዕብኡ ክትጽሕፍን ክትዛረብን ኣይትደሊን፡ እቲ ምንታይስ ምናልባሽ ንህዝቢ ኣብ ምጥርጣራት ኣእትዩ፡ ካብ ቃልሲ ከየርሕቖም ስለዘስግእ እዩ። ብመንጽር’ዚ ርእይቶ’ዚ ሕቡር ህዝቢ፡ ሓያልን ንቁሑን ቃልሲ ስለዘካይድ ድማ ዝርኣየካ ነገራት ክትቃደሶ የታባብዓካ’ዩ። ብዝኾነ ኣብዚ ዓለምና ንእስትራተጂኡ ዘይተገርሔ ኣንፌት ብሕነት ኣብ ትዉርወረሉ ዘላ ክዉንነት፡ ኣንፈቶም ዘይፈልጡ ኣህዛብ፡ ሃገራት፡ መንግስታትትን ተቃዉሞታቶም ምስዝህልዉ፡ ቀዳሞት ግዳይ ናይ ዓለምና ክኸኑ እዮም። ኣንፈትና ስለዝሳሓትና ታሪኽ ብሓሶት፡ ብዋጭዋጭታን ብባጫን ዝቕየር ስለዝመስለና ልዕሊ ደረት ኣእምራዊ ብቕዓትና፡ ልዕሊ ማሕበራዊን ፖሎቲካዊን ክብደትና፡ ልዕሊ ኣኳዳምያዊ ብቕዓትና፡ ተሞክሮናን መሰልናን ከነንሂ ስለንዉዕልን ንሓድርን ኣንፈት ጽምዶታት ቃልስና ስሒትና ኣብ መስርሕ ኪደት ርእሰ ቅትለት ንርከብ ኣለና። ንታሪኽ ዝቕይር ህሞት እቲ ንርእዮ ኣንፈቱን ደረቱን ዝሳሓተ ርኡይ ተንቃሳቓሲ ኣግዕዞ ዘይኮነስ፡ እቲ ብቀሊሉ ክትርእዮን ክትድህስሶን ዘይትኽእል (ሙስጡር) ኣግዕዞ ጥራይ እዩ ዝቕይር። ከምኡ ስለዝኾነ ድማ መላእ ህዝቢ ኤርትራ ዝተቓለሰሉ ሰዉራ (ካብ1961-1991) ብዉሑዳን ኣብ ዉሽጠና ማዓንጡና ብመልክዕ ሰልፊ (e.p.r.p)ተወዲቦም ዝዓዩ ዝነበሩ፡ ንጉዑዞ ታሪኽን ትሕዝትኡን ከምዝቕየር ገይሮም እዮም። ሕጂ እዉን ብተመሳሳሊ እዮም ዝሰርሑ ዘለዉ። ነዚ ክዉንነት ፈሊጥና ፡ ህዝቢ ብጥበብ-ምድንጋራቶም ካይ ምእዘን፡ ካይታፋነን፡ ኣብ ዕንክሊሊን ኮንቱ ኮንቱነት ሃዋህዉ …. ወ.ዘ.ተ ከይኣቱ፡ ኣብ ዉዲታቶም ክይንሳፈፍ፡ ሰላል ካይብልን ካይሳራሰርን ናይ ምርድኡ ዓቕምታቱ ዝዓቤሉ ባይታ ክንፈጥር ክንቃለስ ኣሎና። ህዝቢ ብቁኑዕ-ሓቤሬታን ብቁኑዕ ዉደባን እንተተኣሳሲሩ፡ ልክዕ ከምቲ እቲ ብርሃን ንጸልማት ትስዕራ፡ ህዝቢ ነዞም መዳናገርቲ ክስዕሮም’ዩ። ካብቲ ስርዓት ንኤርትራ ተቃጻጺሩ ዝመርሓ ዘሎ ጀመሪ፡ ክሳብ እቶም ኣንጻሩ ደዉ ኢሎም ዘለዉ ንነብሶም “ደምበ-ፍትሒ” ኢሎም ዝሰምዩን ዝጽዕዱን ዝተፈላለዩ ሓይልታት ኣብ ዉሽጥን ዲያስፖራ፡ ኣብዚ ክልተ ፖሎቲካዊ መስመራት ዝጣቀለሉ (ዝምደቡ) እዮም። ካብዚ ክልተ መስመራት ወጻኢ ሳልሳይ መስመር ዝብሃል ብጭራስ የሎን። ዓንቀጸይ ንምዝዛሙ ንዝኣክል ሕጂ እዉን ከም ኣመሎም ብፍላይ ነቲ “ህ.ግ.ደ.ፍ ሰፊሕ ሃገራዊ ግንባር” ዝመርሕ ሕቡእ ሰልፊ ፡ ብሓፈሻ ድማ ብደረጃ ኤርትራን ኢትዮጵያን ንሚሲጢራዊ ሰልፍታት ማለሊት(mllt) 1983-1991 ን ህ.ሰ.ሰ.ኤ (eprp) 1972-1992 ዝተክኤ ናይ ዉሑዳት ሰብ ረብሓ ሚስጢራዊ ሰልፊ ዘሎ ይመስእል! እቲ ምንታይስ ስርዓት ኣዲስ ኣበባን ስርዓት ኣስመራን ፖሊሲታቶም ነንሕድሕዱ ዝተሓጋገዝን ዝባራረን ልዕሊ ህዝቢ ኢትዮጵያን ኤርትራን ብሙኻኒ’ዩ። ኣብ ከምዚ ፖሎቲካዊ ድሕሪ-ባይታታት፡ ቅድመ-ደማዊ ምትእስሳራትን ምቅሉፍላፋትን እቲ እንኮ መፍትሒ ካብ ዝንኣሰት ቦታን ካብ ሓደ ዉልቀ ዜጋ ጀሚሩ ንመላእ ዓለም ዝዝርጋሕ ህዝባዊ ሰኪዔትን፡ ኣብ ካብ ታሕቲ ንላዕሊ ዝዝርጋሕ ዳይነሚክ ህዝባዊ ዉደባን ምስ ህዝባዊን ሰብኣዊን ኑጹር ዕታር-መትከላት ምስ ዝላፈን ጥራይ እዩ። ኣቃልቦና ዘድልዮ ድቐተ-ሓሳብ፡ ማካቬሊ ከምዚ በለ፡- ኣብ ሓደ እዋን ክትፍራሕን ክትፍቐርን እንተዘይተኻኢሉ፡ ኣብ ክንዲ ብተናጸል ክትፍቐርን ፡ ክትፍራሕ ይምረጽ ይብል “better to be feared than loved, if you cannot be both.”። ንኣባሃህልኡ ቁቡል ዝገብሮ ምኽንያታት የቕርበሉ እኳ እንተኾነ፡ ፍቕሪ ዶ ፍርሒ ይብርትዕ ንዝብል ሕቶ ገሊኦም ፍቕሪ ይብሉ፡ ገሊኦም ፍርሒ ይብሉ: ኣነ እዉን ምስቶም ፍርሒ ይብርትዕ ዝቡሉ ሰባት እየ። ፍርሒ ብግዳማዊ ሓይሊ ዝፍጠር ቀታሊ ሰብኣዊ መንፈስ ኒሕን ሕልናንን ስለዝኾነ፡ ብቀሊሉ ካብ ዉሽጣዊ መንፈስካን ህዋሳዊ ስምዒታትካን ከተወግዶ ዘይትኽእል ብስግኣታት ዝተመልኤ ተንካፊን ሓላኺ ተርእዮ’ዩ። እቲ ምንታይስ ነቲ ፍርሒ ኣብ ዉሽጢ ስነኣእሙራዊ ቅኒትካን ህዋሳትካን ዝፈጠረ ሓይሊ፡ እንተዘይፈሪሕካዮ(እንተዘይተማእዚዝካዮን ዘይተመለኽካሉን) ከም ሳዕቤኑ ሓያል ቃንዛን ዕንወትን ዘለዎ ስጉምትታት ኣብ ልዕሌኻን ስድራቤትካን ብምዉሳድ ዳርካ ስለዘርእየካ እዩ። ከም ሉሉያት ግዳያት ናይዚ ክዉንነት፡ ገለ ሙሱልያትን ነቲ ኩዉንነት ብግቡእ ክርድእዎ ዘይክእሉ፡ ‘’ፍርሕና ቅንጢጥና ወይ ድማ ካብ ፍርሒ ናጻ ወጺና” ቢሎም ብምጽዓድ ፡ ፍርሒ ከምዘይብሎም መሲሎም ክርኣዩ ተባሂሉ፡ ሰብ ኣንጻር መላእ ሕብረተሰብ ክናጣጠፉን ክዛረቡን ይርኣዩን ይስሙዑን እዮም። እቲ ዝወረዶም ቛንዛ፡ ገበን፡ ብትከት፡ ዓቕሊ-ጽበት፡ ጥፍሽና …ወ.ዘ.ተ ኣብ ልዕሊኦም ስነኣኣሙራዊ፡ ኣካላዊን መንፈሳዊን ኩነት ኩነታቶም ናይ ኣእሙሮን ማሕበራዊ ምዝንባላት ስለዝፈጥረሎም ድማ ኣንጻር እቲ ግዳይ ዝገበሮም ፖሎቲካዊ ስርርዕ ጥራይ ዘይኮነ ኣንጻር መላእ ሕብረተሰብ ይልዓሉ። ናብ ሓዉሲ ጽላሌ፡ ብትከትን ተነጽሎታትን ስለዝዓዝሮም፡ ካብዚ ንምዉጻእን ኣቃልቦ-ሰብ ንምርካብን ዉሕስነቶም ንምርግጋጽ ተባሂሉ ናብታ ቅድመ-ስሩት ዝምድናታት ማለት ዓሌት፡ ሃይማኖት፡ ኣዉራጃ …ወ.ዘ.ተ ስግሩ እዉን ሃገርን ህዝቢን ኣብ ሓደ ጊዚየ ከፍሩሱን ክሸጡን ክልዉጡን ናይ ምድላይ ድንዕታቶም ካብ ዓዉ ኢሎም ምዝራብ ኣይቁጠቡን። ስለዚ ናይ ከምዚኦም ዓይነት ጽላሌን ዝሓዞም ዜጋታትን ናይቲ ቀንዲ ፍርሒ ዝፈጠረ ፖሎቲካዊ ሓይሊ ተዳማሚሩ ነቲ ሕብረተሰብ ናብ ዓሚቕ-ፍርሕ ይድቕድቆ። ጠመቱኡን ጽምዶታቱን ኣብ ክንዲ ናብቲ ቀንዲ ፍርሒ ዝፈጠረ ሓይሊ ዝኸዉን፡ ናብቶም ቡቱኻት ይኸዉን እሞ ምርጫታቱ ጌጋ ይኸዉን። ሓደ ሕብረተሰብ ምስ 5 ህዋሳቱ እንከሎ ፡ እንዳሰምዔ ዝጸመመ እንዳርኣየ ዝዓወረ ንኽከዉን ዘገድዶ ድንቁርና ዘይኮነ፡ ኣብ ኣዝዩ ዓሚቕ ፍርሒ ምስ ዝሽመም ጥራይ’ዩ። ንብፍርሒ ዝተዓዝረን ዝተማረኸን ሕብረተሰብ ኣብ ሕማቕ ኩነታት ከምዝርከብ ንከተረድኦን ከተእሙኖን እዉን ኣዝዩ ኣጻጋሚ’ዩ። ምኽንያቱ እቲ ኣብ ልዕሊኡ ዝወርድን ዝፍጸምን ቃንዛን ገበንን ብሓደ ዘይኮነ ብእብረ ዝካየድ ሰለዝኾነ፡ እቲ ቃንዛ ብሓደን ኣብ ሓደ ጊዚየን ስለዘይስምዖ፡ ንምርድኡን ምምሕዳሩን የጸግም እሞ ጉጉይ ምርጫታት ይወሲድ። እዚ ጸገም’ዚ ድማ ብሓደ ንከይርዳእ፡ ንከይስምዖን ብሓደ ንከይልዓልን ይገብሮ። እቲ ኩቱር ፍርሒ እንዳሰምዔ ዝጸመመ እንዳርኣየ ዝዓወረ ንኽከዉንን ገለ ሰብኣዊ ህዋሳቱ ንከጥፍእ የገድዶ እዩ። ንመረዳእታ ሓደ 2 ህዋሳቱ ማለት ናይ ምስማዕን ምርኣይን ህዋሳት ዘጥፍኤ ሰብ፡ ሓጋዚ ቴክነሎጂካዊ ንዋት ወይ ድማ ናይ ዓይነ ስዉራን ፌደላት ንምንባብን ምጽሓፍን ዘይተማህረ (braille) ምስ ዝኸዉን ኣቡኡ ወይ ኣዲኡ ከምዝሞቶ ከመይ ጌርካ ከተርድኦ ትኽእል? ካብተን 5 ህዋሳቱ ዝዉንነን ዝተረፍኦ ናይምድህሳስ፡ ናይ ምስትምቛርን ናይ ምሽታትን ጥራይ እየን በዚኤን 3 ህዋሳት ከመይ ጌርካ ከተርድኦ ትኽእል? ፈጺምካ ስለዘይክኣል ፍታሕ ከተናዲ ኣሎካ። እቲ እንኮ ፍታሕ ድማ እቲ ዝሞተ ኣቡኡ እንተኾይኑ፡ ነዲኡ ከተምጻ ኣለካ ዳህሲሱ ኣዲኡ ከምዘላ መታን ክፈልጥ። ድሕሪኡ ኣቐንዛዊ ተረኽቦ ከምዘጋጠመ ንከተረድኦ ከተቀንዝዎ ስለዘሎካ፡ ብሓዊ ክትክሶ ኣለካ ማለት’ዩ። ብሓዊ ምስተኮስካዮ ገለ ቃንዛ ዝፈጥር ጉዳይ ኣጋጢሙ ከምዘሎን ኣቡኡ ምስ ኣዲኡ ካብዘይመጸ፡ ኣቡኡ ገለ ኮይኑ ከምዘሎ ግንዛቤታት ከሕድር’ዩ። ብኸምዚ ክዉንነት ዝሓለፈ ሕብረተሰብ ብቀጥታን ሃንደበትን ናብ ንቡር ቦቱኡን ዲሞክራሲ ከተሳጋግሮ እዉን ኣዝዩ ኣጸጋሚ ዝኾነሉ ህሞት ዘሎን ዘጋጥምን እዩ። ከመይ ገይሩ ዝብል ሕቶ ክልዓል ይኽእል ስለዝኾነ፡ ንመረዳእታ ዓሚትካዮ ዝጸናሕካ ዓይንኻ፡ ቓሕ ምስ ተብሎ፡ ጻዕቂ ጭራ ብርሃን ንዓይንና ስለዝደግሖ ሕዉዝዉዝ ከምዝብል ይገብሮ እሞ ናይ ምርኣይ ተኽእሎታትና ኣብ ጽልግልግ ይኣቱ እዩ። ብተወሳኺ ከም ልክዕ ብልጓም ተቀይዱ ዝኸይድ ፈረስ፡ ሉጓሙ ፈኒኻ ምስ ሓደካዮ ፈረስ ናብ ገደሉ ወይ ድማ ናብ ዘይትሓስበ መኣዝን ዝጋልብ፡ ሕብረተሰብ እዉን ከምኡ ንክኸዉን ዝተዋደደ እኩብ ሰብን እኩብ ድሪኺትን ዝዉንን ስለዝኾነ በቡቁሩብ ናብ ንቡር መኣዝኑ ከተማእዝኖ ከምዘለካ ዝግመት ጉዳይ እዩ። ከምኡ ስለዝኾነ፡ ነዚ ክዉንነት እዚ ብግቡእ ዝርዳእ ሓያልን እሙን መራሒ ከድሊ እዩ።
90
ቦ ጊዜ ለኩሉ እንደሚባለው ሁሉ ለሁሉም ሁለት ፊት ገጽታ አለ ሊባል ይቻላል። ወያኔ በአራቱም አቅጣጫ ቢታይ አስቀያሚ መሆኑ አይቀሬ ቢሆንም የክልል አንድ ልጆች ቆንጆ ነው ማለታቸው መጠበቅ ያለበት ነው። የአድዋ ልጆች የዓይን ችግር አለባቸው ለማለት ሳይሆን በጥቅም ታውረዋል ለማለት ነው። ሰይጣኑ መለስ ሲሞት ጮቤ የረገጠው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊው ሲሆን ዕንባ ያነባው ደግሞ ወያኔና ሆዳሙ ብቻ ነው። ጅላ ጅሎችም--ሁሉም ሀገር ዘለዓለማዊ ሞኞችን ይይዛል። ሁለት ገጽታ ለሁሉም። ይህ መንደርደሪያ የመጣው ወደ ኦባማና ኢትዮጵያን ለመጎብኘት መነሳቱን በተመለከተ የተነሳውን ውዝግብና ተቃውሞ የሰይጣን ጠበቃ ሆኜ ለመከራከር በመፈለጌ ነው። የዛሬ ስንት ዓመት ባራክ ኦባማ አሜሪካዊ ሳይሆን ኬንያዊ፤ አፍሪካዊ፤ ጥቁርም የመሰላቸው ጥቂቶች አልነበሩም። ግለሰቡ አሜሪካዊና ለሀገሩ ጥቅም ብቻ የሚቆም መሆኑንም በተመለከተ ብዥታ ሰፍኖ ነበር ማለት ይቻላል። ሀገራቸውን የረሱ እንበልና ስንት ኢትዮጵያውያን የነበሩ ሁሉ ለኦባማ ገንዘብ ሰበሰቡ፤ ሲመረጥም ፈነደቁ፤ አንዳንዶቹማ ኦባማ ስለዴሞክራሲ የለፈፈውን አምነው፤ ፖለቲከኛ መሆኑን ረስተው፤ ለአሜሪካ ጥቅም የቆመ መሆኑ ዘንግተው ወያኔ አለቀላት ሲሉም ተደምጠዋል። ማለቅ የጀመረው የራሳቸው የተሳሳተ ድምዳሜ ሆኖ ሳለ። የአሜሪካ ብሔራዊ ጥቅም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጋር ተጻሮና ተፋጦ ከቆየ ዘመን ያለፈ ቢሆንም ታሪክን ማወቅና መረዳት ያቃታቸው ክፍሎች ይህን ሀገር የኢትዮጵያ ወዳጅ አድርገው ለመፈረጅ ሁሌም ደፋ ቀና ሲሉ ማየት ምጸታችን ከሆነም እንዲሁ ዘመን አልፏል። ኦባማ የኢትዮጵያ ወዳጅ ሳይሆን ባለው ሀላፊነት የአሜሪካ ቡችላና መጋዣ ለሆነ ወያኔ ጥብቅና የሚቆም መሆኑን መገመት ባላዳገተ ነበር። ለወያኔ ስልጣን መያዝና ለተከተለው የኤርትራ መገንጠል ዋናው ደጀን/ረዳት አሜሪካ ካልነበረ ማን ሌላ ሊወቀስ ነው! አሜሪካንን በሚገባው ቋንቋ ማነጋጋር ሲገባ (ይህን ትምህርት ደግሞ ሞቃዲሾም ቤይሩትም ብሎ መማር ይቻል ነበር) አትርሱን፤ እዘኑልን፤ ፕሊስ ፕሊስ ማለቱና መለመኑ ስለበዛ መናቅ መከተሉ የሚጠበቅ ነበር:: አሜሪካም ወያኔን ስትደግፍ ህዝብን ግን ንቃለች፤ አሁንም የተለወጠ የለም። ኦባማ ደግሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት እንደመሆኑ የአሜሪካን ጥቅም ማስቀደሙ የሚጠብቅ ነውና 90 ሚሊዮን ድሀ ደንታ ሊኖረው አይችልም። የለውምም። ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት መሄዱ ለምን ብዙዎችን እንዳስቆጣ በበኩሌ ግራ አጋብቶኛል። ተቃውማችሁ አትሰለፉ ለማለት ሳይሆን እንዲያው ለነገሩ እንዲሉ ምን አለበት ለማለት ነው። አንድ ባሕታዊ “ምን አለበት?” ሲባል “በእበትማ ትል አለበት” ሲሉ አስታውሳለሁ፣ ግን በዚህ ጽሁፍ ልረሳው ወስኛለሁ። ኦባማ ኢትዮጵያ ቢሄድ ምን አጠፋ ለማለት የተነሳሁት ክሱ አባት ልጁን፤ የውሾ ባለቤት ቡችላውን አይይ አይጠይቅ ዓይነት ስለመሰለኝ ነው። የኦባማና አሜሪካ ወዳጅ ወያኔ እንጂ የኢትዮጵያ ሕዝብ አይደለም። ለአሜሪካ የቆመ ወያኔ እንጂ የሀሬን ሉአላዊነት ላስጠብቅ ባዩ ሕዝብ አይደለም። ለአሜሪካ ጦር ሰፈር የሰጠው (በጋሞ ጎፋ ወዘተ ) ወያኔ እንጂ ህዝብ አይደለም። ወያኔ በስልጣን መቀጠሉን አሜሪካ ትፈልገዋለች። ለዚህም ነው ኦባማ ህግን ጥሶ ለአራተኛ ጊዜ ሊመረጥ የሚንገዳገደውን የጅቡቲውን ኦማር ገሌ የምትደግፈው፡፡ ለዚህም ነው ትዕዛዟን ተቀብሎ ወደ ሶማሊያ ጦር የላከው የቡሩንዲውን ጨቋኝና በሕዝብ የተጠላ መሪ መሪ ወዳጅ የምትለው። አንዳንድ ዜጎች አሜሪካ በኢራንና አፍጋኒስታን ለዴሞክራሲና ለሕዝቦች ጥቅም ስትል ውጊያ የገባች ይመስላቸዋል። ጋዳፊ የተገደለው ለሊቢያ ህብ ደግ ታስቦም የሚምስላቸው የዋሆች አሁንም አሉ። መደናገራቸውን ግን በኦባማ ላይ ማሳበብ አይችሉም። ፖለቲከኛ ወንዝ በሌለበት ድልድይ ሊሰራና ድልድይ በማያስፈልግበት ወንዝ ሊያስገባ ቃል ሊገባ መነሳቱ መጠበቅ ያለበት ሆኖ ሳለ በግልቡና በሌጣው ወይም እንደወረደ የሚለፈፈውን የሚያምኑ (ብጿአን ማለቱ ይከብዳል) ሞልተዋል። ኦባማ በሙስና ያልተጨማለቁ መሪዎችን እንፈልጋለን ሲል ከልቡ ይመስላቸዋል። ዴሞክራሲን ካላከበራችሁ አንረዳችሁም ሲልም አምነውት እስየው ጉድ ፈላ ይላሉ። አረቦች ካለም ፋዲ--የማይረባ ንግግር--የሚሉት መሆኑን አይገነዘቡም። አሜሪካም ሆነ ምዕራቡ በዝባዥ ዓለም ሀገር ወዳድ መሪን አይፈልጉም:: ሉአላዊነትን ሲያስከብር ዝርፊያችውን ያስቆማቸዋልና። የሕዝብ መንግስትንም ይጠላሉ በዚሁ የተነሳ። ንክሩማህ፤ ሉሙምባ፤ ሞሳዴግህ ከኢራን፤ ሳንካራ ፤ መንግስቱና ገርማሜ ንዋይ፤ ዳጃዝማች ታከለ ወልድ ሀዋርያት፤ ኢሕአፓ ወዘተ ተፈላጊ ያልሆኑት፤ የተጠቁት፤የተገለበጡትና አሁንም የሚጠቁት በዚሁ የተነሳ ነው። ይህን በግንዛቤ ከያዝንና ስለ አሜሪካና ኦባማ የተዛባ ግምትን ካስወገድን እንዳውም ኦባማ እስካሁን እንዴት ወያኔን ከወረረው መዲና ድረስ ሄዶ እንዳላመሰገነውና እንዳላሞገሰው አነጋጋሪ ይሆናል። ወያኔ ለጌታው በፍጹም ታማነትና ተገዥነት ያደረ ውሾ ሆኖ እንጂ ቅሬታውን እስካሁን ባሰማ ነበርም ማለት ይቻላል። ማንም በስልጣን ያለ የአሜሪካን ፕሬዚዳንት ወያኔን የጎበኘው ባይሆንም ኦባማ በብዙ መስክ የመጀመሪያው መሆንን ይመርጣልና ብቅ ማለቱ ወያኔን የሚያስፎክር ባይሆንም ማስደሰቱ አያስገርምም። ኦባማ በአሜሪካ ታሪክ የመጀመሪያ ግማሽ ጥቁር (ግማሽ ነጭነቱም ሳይረሳ) ፕሬዚዳንት መሆኑ በታሪክ ያለው የሆነ እንዴ አንደምታ እንዳለ ሆኖ (የአሜሪካውን ለሚያውቁት ስንተው) ለአፍሪቃ ግን ቡሽ ሶስተኛው እንጂ የተለየ ፍጡር አልሆነም፡፡ ባይብስ እንዳውም የሚሉ ብዙ ናቸው! የኦባማ የአፍሪቃ ወዳጆች አምባገነኖች ናቸው። የፈረደበትን ሙጋቤንና የጎረቤቱን አል በሺር ዓይናችሁን ላፈር ሲል የአዲስ አበባዎቹን፤ የካምፓላን፤ የጅቡቲን፤ የቻድና ኤክዋቶሪያል ጊኒና ሌሎችንም አምባገነኖች ግን ወዳጅ ብሎ አቅፏል፤ አሞግሷል፤ ደግፏል። ወደ ዋሺንግተን ድረስ ጋብዞም አጆሃ፤ ካሪ ኦን ሲላቸው ቆይቷል። እኛ እንደ ህዝብ ማየት ያቃተንን የወያኔና የአረመኔውን መለስ ዴሞክራሲያዊነት አይቶ ተገለጸልኝ ተዓምር ሲልም ተደምጧል። አዲስ አበባ ሲሄድ የሚለው የተለይ ነገር አይኖርም። ኤኮኖሚው ማደጉን፤ የድህነት ብዛቱ መቀነሱን፤ ወያኔ የአሜሪካ ወዳጅ መሆኑን፤ ወዘተ ልብ ወለዶች አንስቶ ይሞጋገሳል። ዋሾነት የወያኔ የብቻ ንብረት አይደለምና የአሜሪካ ባልስልጣኖች ከወያኔ ባልተናነሰ ስለ ወያኔ ሲዋሹ ብዙ ዓመታት ተቆጥረዋል። የማይነሱ ነገሮችም ምስጢር አይደሉም። ወያኔ ከ፵/40 ሺ ያላነሰ የፖለቲካ እስረኞⶭ ማገቱና በስየል መጥበሱ አይነሳም። ወያኔ ዓይን አውጣ የመርጫ ማጭበርበርን አካሂዶ መቶ በመቶ ምርጫ አሸነፍኩ ማለቱ በዝምታ ይታለፋል። ሚሊዮኖች በረሃብ መጠቃታቸው፤ መቶ ሺዎች መጠለያ ማጣታቸው፤ ወያኔ በሙስና መጨማለቁ፤ የሀገሪቷ ለም መሬት ለባዕዳን ተሸጦ ብዙ መቶ ሺዎች መፈናቀላቸው፤ ተቃዋሚዎች መታገታቸውና መገደላቸው፤ የጋዜጠኞች ሰቆቃ ወዘተ የሚነሱ ጉዳዮች አይደሉም። የአሜሪካ ባለስልጣኖች ከአምባገነኖች ጋር መተቃቀፋቸውን ለመደበቅ ወይም ውግዘትን ለማለዘብ በይፋ ሳይሆን በር ዘግተን ሁሉም ችግር እናነሳለን የሚሉት የሞኝ የተበላ፤ ማንም የማይቀበለው አሳዛኝ ማደናገሪያ ብጤ አላቸው። በኦባማ ጉብኝት ጊዜ ይህ መባሉ መጠበቅ ያለበት ነው። ኦባማ እስቲ ቃሊትንና ሊሎችን እስር በኢቶች ልጎብኝ እንዲል ባይጠበቅም ጉዞው ለሙገሳ እንጂ ለወቀሳ አለመሆኑን የሚስት ሊኖር አይችልም፤ ሊኖርም አይገባም። መለስ ሞተ ብለው ያላቀሱ ደግሞ በየመንገዱ ተኮልኩለው ኦባማዬ ብለው ቢጮሁ የሚያስገርም ሊሆን አይገባም። ከዚህ ባሻገር ኦባማ ከወያኔ በቀጥታ ሊቀስማቸው የሚችላቸው ትምህርቶች አሉ። ይሉኝታንና ማፈርን መቼና እንዴት እንደገደሉት ማወቅ መፈለጉ አይቀርም። የውሸት ችሎታቸውንም ከቅርብ ሆኖ ቢረዳ የሚጠላም አይሆንም። ድርቅናቸውን ወይም እስራኤሎች ቹትዝፓህ የሚሉትን እንዴት እንደተራቀቁበት ሊያስረዱትም ይችላሉ። ምርጫ ሰርቀው ዴሞክራሲያው ምርጫ ተካሄደ፤ ተቃዋሚ ገድለው ከጥይት ፊት ድርቅ ብሎ ቆሞ ራሱን ገደለ፤ የሶማሊያን ድንበር ተሻገርን እንጂ ወረራ አላካሄድንም፤ ወዘተ ብለው በድፍረት ለዓለም የሚለፍፉትን በተመለከተ ድፍረታቸውን ቢጋራም ደስታውን የሚችለው አይሆንም። ኦባማ ስልጣን ከያዘ ወዲህ መገርጣቱና መጎሳቀሉ ሲታይ የአዲስ አበባዎቹና የአፍሪካ አምባገነኖች ግን ለምንና እንዴት እንደሚወፍሩ እንደሚደልቡ መወያየት ማወቅም ይፈልጋል ተብሏል። ኦባማ ኦባማ ነውና ለዚህ ሁሉ ለወያኔ የማጭበርበር ዘመቻ ተጠያቂ እኔና አሜሪካንም ነን ሊል መቸም የሚጠበቅ አይሆንም። ማን ኦሳማ ቢን ላደንንና አክራሪ ሰው አራጆችን ረዳ! ማን ሳውዲና ሌሎችንም አቅፎ ደግፎ ባጀ! ምላሽ የሚጠበቅ አይሆንም። ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ መጓዙ ስለ ዴሞክራሲ የሚለፍፈውና ከአምባገነኖች ጋር አንተቃቀፍም የሚለውን ሁሉ ከንቱነት የሚያጋልጥ በመሆኑ ቢቻልማ ኖሮ ወጪውን በኢትዮጵያ ላይ ብለን በጋበዝነው ነበር። “አሜሪካ እናቴ/ኦባማ አባቴ/ እኔ ምን ሊገደኝ ቢቆረስ መሬቴ/ ቢደፈርም መብቴ/ቢዋረድ ታሪኬ” ለሚሉት ሁሉ ምናልባትም የንቁ ደወል ይሆንላቸው ይሆናል። ተስፋ አይከለከልም አይደል! ወያኔ በኦባማ መጎብኘቱ የሚያስደስተው የቆሸሸና የከረፋ ስሙንና መልኩን ስለሚያድስለት ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የኦባማን ትልቂቷን ልጅ የኬንያ ሀብታም በላምና በሬ ገዝሚ ሳይወስዳት የገዢዎቹ ልጆች ሊያጯት ይችሉ እንደሆነም ለማየት ነው የሚልም ጥርጣሬ አለ። ለዚህም ነው ኦባማ ቤተሰቡን ይዞ መሄድ ያለበት። ሂላሪ ክሊንተን ከተጠላው ሰምብል እስር ቤት አጠገብ ከነሴት ልጇ ከኢሳያስና የያኔ ሚስቱ ጋር ደርብ ብላ እንደጨፈረችው ሁሉ የኦባማ ሚስትም ከአዜብ ወይም ከሌሎቹ የወያኔ ሚስቶች ጋር አስረሽ ምቺው ብላ እንደ ባሏ በኢትዮጵያ ቁስል ላይ ጨው ስትነስነስ ማየትም እንችል ይሆናል። ይህን ከማየት እምቢ የሚል ይኖራል ብሎ መገመት ሊከብድ ይችላል። አሚሪካ ለስንቱ ቪዛ እየሰጠች ኢትዮጵያ እንዴትስ ኦባማን ባለህበት ቆይ፤ አትምጣብን ልትለው ትችላለች የሚሉም አሉ። ጨዋ ሕዝብ አይደለንም እንዴ! የስልጡንና ተንበርክኮ ትግል አማኝ መሆናችን ቀረ! አሜሪካንን ተቃውመን ስንሰለፍ እንኳን ባንዲራቸውን ልናቃጥል ሳይሆን በክብር እያውለበለብን መሆኑን ማንስ ዘንግቶ ነው ጠበቅ ያለ ተቃዋሞ የሚታሰበው ማለትም የግድ ሊሆን ይችላል። ሉዓላዊነታችንን ለባዕዳን ካስረከብን ውሎ አድሯልና ኦባማ ኑ ዋሺንግተን ስገዱን ትቶ ወደ ኬንያና ኢትዮጵያ ብቅ ለማለት መወሰኑ ነገሮች ሁሌም ሁለት ገጽታ አላቸው ብለው ዶክተሮቻችን እንደሚገስጹን ጠቀሜታም ሊኖረው ይችላል። ውርደትን ክብር ማለት የወያኔ ብቻ ጉድ አይደለምና እንኳን ደህና መጣህ ብለው እንደ ጆሴፍ ቲቶ ቢቀበሉት መገረም የለብንም። አትሂድ የሚሉትም ይበሉት--ለታሪክ ተቃውሞን ለማስመዝገብ። በበኩሌ ግን ኦባማ በግላጭ ያውም አዲስ አበባ ድረስ ሄዶ ወያኔን ማቀፉ የተበላሸና ሕዝብና ሀገርን የሚጎዳውን የአሜሪካ ፖሊሲ፤ አቅዋምና ፖለቲካ ያጋልጣልና አደራህን ብቻህንም ቢሆን መጓዙን እንዳትተው ብዬ ባያዳምጥም እነሆ መክሪያለሁ።
91
የዘጠና ሶስት ዓመቱ የቀድሞው ዝምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ በመጨረሻው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ። በሃያ ዓመታት የሚያንሷቸውና በንጽጽርም ወጣት ተደርገው የተወሰዱት የሰባ አምስት ዓመቱ የቀድሞ ምክትላቸው ኢመርሰን ምናንጋግዋ የፊታችን አርብ ቃለ መሃላ ፈጽመው የሥልጣን መንበሩን ይረከባሉ። በአፍላ ወጣትነታቸው እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1970ዎቹ በቻይና የሰለጠኑት፥ የዚያን ዘመኑ ሽምቅ ተዋጊ፥ ደም ባፋሰሰውና ለነጻነት በተደረገው ትግል ከሞጋቤ ጋር በመሆን ከተዋጉት ውስጥ አንዱ ናቸው። ላለፉት ሰላሳ ሰባት ዓመታት ያችን አገር በጠንካራ መዳፍ ተጭነው የመሯት የፕሬዝዳንት ሮበርት ገብርኤል ሙጋቤ የቀኝ እጅና ብርቱ ተካከላካያቸው ነበሩ። አወዛጋቢው ሁኔታዎች መታየት እስከ ጀመሩበት ቅርብ ጊዜ ድረስ። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከምክትል ፕሬዝዳንትነት ሥልጣናቸው በሙጋቤ የተነሱትና ባለፈው ሳምንት ጦር ሠራዊቱ ሙጋቤን በቁም እሥር አውሎ ወደ ሥልጣናቸው እንዲመለሱ ያደረጋቸው ምናንጋግዋ፤ ዛሬ ደግሞ የቀድሞ አለቃቸውን (በፈቃዳቸው ከማለት .. በተደረገባቸው ከፍ ያለ ግፊት ተገደው ማለት ይሻላል) ሥልጣን መልቀቅ ተከተሎ የነገዪቱን ዝምባብዌ ሊመሩ ከሽግግሩ ደጃፍ ቆመዋል። በያዝነው ወር መጀመሪያ ግድም ሙጋቤ በእርሳቸው ላይ “የነበረኝን እምነት አጥቻለሁ” በሚል ከሥልጣን ሲያስወግዷቸው፤ እርምጃው ሙጋቤ እምብዛም ተቀባይነት የሌላቸውን ባለቤታቸውን የሃምሳ ሁለት ዓመቷን ግሬስ ሙጋቤን ወደ ሥልጣን መንበር ለማምጣት አመቺ አጋጣሚ ለመፍጠር ተብሎ የተደረገ ሆኖ ነው፤ የታየው። ምናንጋግዋ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ1980ዓም አንስቶ የብሔራዊ የደህንነት ኃላፊነት ጨምሮ በተለያዩ የካቢኔ የሥልጣን ኃላፊነቶች ተሰይመው ከመሥራታቸው በላይ፤ እንደ አውሮፓውያኑ በ2014ዓም ሙጋቤ የቀድሞ ምክትላቸውን ጆይስ ሙጂሩ’ን (የዛሬ ዋና ተቺያቸውን) ከሥልጣን ማንሳታቸውን ተከትሎ ለምክትል ፕሬዝዳንትነት በቁ። የምናንጋግዋ ለከፍተኛው የሥልጣን እርከን መብቃት ታዲያ በፓርቲው ውስጥ በሁለት ትውልዶች መካከል ለሚታየው ብርቱ የሥልጣን ሽኩቻ ማብቂያ የሚያበጅ ተደርጎም ተወስዷል። እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1965ዓም “አዞው” የሚለው ቅጽል ሥም በተሰጣቸው በማናንጋግዋ የሚመራው የቀድሞ የነጻነት ዘመን ተዋጊዎች፤ የዛሬዎቹ የፖለቲካ መሪዎች በአንድ ወገን በዚያ ዘመን የተወለዱትና የባለቤታቸውን ሁነኛ የፖለቲካ እንደ ልብ ድጋፍ ያገኙ በነበሩት ግሬስ ሙጋቤ ይመራ የነበረው ደግሞ በሌላው ናቸው። የኢመርሰን ምናንጋግዋ የአመራር ዘመን ገና ድሮ የጀመረ ይመስላል። የአረጀው የሙጋቤ አመራር መሰናበት የፈጠረው ትኩስ ስሜት ከበረደ በባላ በእርግጥ ለዚያች አገር ሕዝብ አንዳች ዘላቂ ለውጥ ያመጣ ይሆን?
92
የዶላር ምንዛሪ 14.60 ብር እንደሆነ ተሰራጭቶ የነበረው ዜና በጉግል ሰረች ላይ በተከሰተ ስህተት እንደሆነ ተገለፀ፡፡ በዛሬው ዕለት ያለው ትክክለኛው የምንዛሪ መጠን ለማወቅ ከታች ያለውን አድራሻ በመጫን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክን መረጃ ይመልከቱ፡፡
93
ከዚህ በታች በተመለከተው የሥራ መደብ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ስለሚፈልግ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃዎቻችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ እየቀረባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡ በደረጃ 12 እና 14 (ከተ.ቁ 1-9) አመልካቾች በኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ለገሀር ዋናው መ/ቤት የሰው ሀብት አስተዳደር ዋና ክፍል 4ኛ ፎቅ ከደረጃ 2 እስከ ደረጃ 9 (ከተ.ቁ 10-94) አመልካቾች በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ቃሊቲ ቅርንጫፍ የሰው ሀብት አስተዳደር ዋና ክፍል ቢሮ ቁጥር 104 መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ሁለተኛ/የመጀመሪያ ዲግሪ በቢዝነስ ማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግ፣ በትራንስፖርት ማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ በማርኬቲንግ፣ በትራንስፖርት ኢኮኖሚክስ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ሁለተኛ /የመጀመሪያ ዲግሪ በትራንስፖርት ማኔጅመንት በኢኮኖሚክስ/በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንተ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ሁለተኛ/የመጀመሪያ ዲግሪ በሜታል ቴክኖሎጂ በሜካኒካል ምኅንድስና/በጠቅላላ ሜካኒክስ/በሜታለርጂ የሠለጠነ/ችና የአውቶካድ ወይም ዲዛይን ዴቨሎፕመንት ኦፕሬሽን ስልጠና የተከታተለ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክ፣ በሎጀስቲክስ ማኔጅመንት /በትራንስፖርት ማኔጅመንት/ በማርኬቲንግ/ በትራንስፖርት ኢኮኖሚክስ ወይም አግባብነት ባለው የትምህርት መስክ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ ኢንቫይሮሜንታል ሳይንስ፣ በሙያ ደህንነትና ጤንነት/occupational health & safety/፣ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ ኢንቫይሮሜንታል ሳይንስ፣ በሙያ ደህንነትና ጤንነት /occupational health & safety/ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የደረጃ iv በዲፕሎማ /10+3/ በአውቶ መካኒክስ/ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል፡፡ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ በአካውንቲንግ፣ በማርኬቲንግ፣ በሎጀስቲክስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ በአካውንቲንግ፣ በማርኬቲንግ፣ በሎጀስቲክስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒዩተር ሳይንስ፣ በኤም አይ ሴስ፣ ቢአይ ኤስ፣ በኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒዩተር ሳይንስ፣ በኤም አይ ሴስ፣ ቢ አይ ኤስ፣ በኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ በትራንስፖርት ማኔጅመንት/ በማርኬቲንግ፣ በትራንስፖርት ኢኮኖሚክስ ወይም አግባብነት ባለው የትምህርት መስክ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ መጀመሪያ ዲግሪ በትራንስፖርት በማኔጅመንት/ በማርኬቲንግ/ በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/በትራንስፖርት ኦፕሬሽን/ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ /ኮሌጅ በትራስፖርት በማኔጅመንት/ በማርኬቲንግ/ በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/ በትራንስፖርት ኦፕሬሽን/ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በትራንስፖርት በማኔጅመንት/በማርኬቲንግ/በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/ በትራንስፖርት ኦፕሬሽን/ ሆኖ /ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል፡፡ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በትራንስፖርት በማኔጅመንት/ በማርኬቲንግ/ በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/ በትራንስፖርት ኦፕሬሽን ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በኢኮኖሚክስ፣/ በማርኬቲንግ በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/በትራንስፖርት ማኔጅመንት ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በመጀመሪያ ዲግሪ በሜካኒካል ምህንድስና/ኤሌክትሪካል ምህንድስና/ አውቶሞቲቭ ምህንድስና/ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ ወይም በተመሳሳይ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በመጀመሪያ ዲግሪ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ/በሜካኒካል ምህንድስና/ በአውቶሞቲቭ ምህንድስና/ በሜታል ቴክኖሎጂ/ ወይም በተመሳሳይ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በመጀመሪያ ዲግሪ በአውቶሞቲቭ ቴክግሎጂ/በሜታል ቴክኖሎጂ/ በሜካኒካል ምህንድስና/ በማኑፋክቸሪንግ ምህንድስና ወይም በተመሳሳይ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በዲፕሎማ ከተቋም በአውቶ ሜካኒክስ/ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ /10+3/ ወይም ደረጃ iv ወይም በተመሳሳይ የሠለጠነ/ች የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በዲፕሎማ በአውቶ ሜካኒክስ /10+3/ ወይም ደረጃ iv ወይም በአውቶ ሜካኒክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬት የሰለጠነ/ች ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በጠቅላላ መካኒክስ /10+3/ ወይም ደረጃ iv የሰለጠነ/ች ወይም በጠቅላላ መካኒክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬትና ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በዲፕሎማ /ደረጃ iv ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ ኤሌክትሪሲቲ በኤሌክትሮኒክስ የሰለጠነ/ች ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በመጀመሪያ ዲግሪ/ዲፕሎማ በማኔጅመንት/በማቴሪያልስ ማኔጅመንት/ በሰፕላይስ ማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት/ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ዲፕሎማ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካኒክ /10+3/ ወይም ደረጃ iv ወይም ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካኒክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬት የሰለጠነ/ች ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል፡፡ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ዲፕሎማ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካኒክ /10+3/ ወይም ደረጃ iv የሰለጠነ/ች ወይም በሰርተፊኬት ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካኒክ /10+2/ ወይም ደረጃ iii የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በጠቅላላ መካኒክ /10+3/ ወይም ደረጃ iv መካኒክስ ወይም ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በጠቅላላ መካኒክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬትና ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በጠቅላላ መካኒክ /10+3/ ወይም ደረጃ iv ደረጃ ወይም ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በጠቅላላ መካኒክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬት ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካኒክስ /10+3/ ወይም ደረጃ iv በዲፕሎማ የሰለጠነ/ች እና የ5 ደረጃ መንጃ ፈቃድ ያለው ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የሙያ ደረጃ iv ዲፕሎማ /10+3/ በአውቶ መካኒክስ ወይም /10+2/ ወይም ደረጃ iii በሰርተፊኬት የሰለጠነ/ች ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በሜታል ቴክኖሎጂ/በመካኒካል ምህንድስና/በጠቅላላ መካኒክስ/በሜታለርጂ የሰለጠነ/ችና የአውቶካድ ወይም ዲዛይን ዴቨሎፕመንት ኦፕሬሽን ስልጠና የተከታተለ ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በጠቅላላ መካኒክስ በማሽን ቴክኖሎጂ/በጠቅላላ ብረታ ብረት ቴክኖጂ 10+3 ወይም ደረጃ iv የሰለጠነ/ች ወይም በጠቅላላ መካኒክስ (10+2) ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬትና ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በጠቅላላ መካኒክስ /10+3/ ወይም ደረጃ iv የሙያ ደረጃ የሠለጠነ/ች ወይም በጠቅላላ መካኒክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii በሰርተፊኬት የሰለጠነ/ች ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም የኮሌጅ ዲፕሎማ ደረጃ iv በነርሲንግ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ በላብራቶሪ ቴክኒሽያንነት የመጀመሪያ በዲግሪ የሰለጠነ/ች ወይም በላብራቶሪ ቴክኒሽያንነት /10+3/ ወይም ደረጃ iv በዲፕሎማ የሰለጠነ/ች የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የሞያ ደረጃ iv /የኮሌጅ ዲፕሎማ በሴክሬተሪያል ሳይንስ ወይም ኦፊስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል፡፡ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የሙያ ደረጃ iv ኮሌጅ ዲፕሎማ በማኔጅመንት እና 3ኛ ደረጃ መንጃ ፈቃድ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ና የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ/የሞያ ደረጃ iv/ የኮሌጅ ዲፕሎማ በሴክሬተሪያል ሳይንስ ወይም ኦፊስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል፡፡ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በአውቶሞቲቭ/ በቀለም ቅብ ቴክኖሎጂ /በአውቶ መካኒክ ሙያ /10+2 ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬት ወይም በአውቶሞቲቭ/ በቀለም ቅብ ቴክኖሎጂ/በአውቶ መካኒክስ ሙያ /10+1/ ወይም ደረጃ ii ሰርተፊኬት ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶመካኒክስ /10+3/ ወይም ደረጃ iv በዲፕሎማ የሰለጠነ/ች እና የ5 ደረጃ መንጃ ፈቃድ ያለው ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ/የሙያ ደረጃ iv ኮሌጅ ዲፕሎማ፣ በማኔጅመንት አድሚኒስትሬቲቭ ሰርቪስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ በማኔጅመንት በማቴሪያልስ ማኔጅመንት/በሰፕላይስ ማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲንግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የሙያ ደረጃ iv ኮሌጅ ዲፕሎማ በአካውንቲንግ ወይም በተመሳሳይ ሙያ ወይም ደረጃ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ና የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በፕሮኪውርመንትና ሰፕላይስ ማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ በማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት በማቴሪያልስ ማኔጅመንት / በሰፕላይስ ማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲንግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የሙያ ደረጃ iv ኮሌጅ ዲፕሎማ ሰፕላይስ ማኔጅመንት በማቴሪያልስ ማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግ ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ና የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት/በማቴሪያልስ ማኔጅመንት/ በሰፕላይ ማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲንግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት/በማቴሪያልስ ማኔጅመንት/ በሰፕላይ ማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲንግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሰለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት/በማቴሪያልስ ማኔጅመንት/ በሰፕላይ ማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲንግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ ሰለጠነ/ች የሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ በማኔጅመንት/ በአካውንቲንግ/ በፋይናንስና አካውንቲንግ/ በቢዝነስ ማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ ሙያ የሠለጠነ/ች ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በአውቶሞቲቭ/ በቀለም ቅብ ቴክኖሎጂ /በአውቶ ሜካኒክ ሙያ/ 10+2 ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬት ወይም በአውቶሞቲቭ /በቀለም ቅብ ቴክኖሎጂ/ በአውቶ መካኒክስ ሙያ /10+1/ ወይም ደረጃ ii ሰርተፊኬት ሲኦሲ የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ በዲፕሎማ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ/ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካኒክስ /10+3/ ወይም ደረጃ iv ወይም ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በአውቶ መካነክስ /10+2/ ወይም ደረጃ iii ሰርተፊኬት የሰለጠነ/ች ሆኖ/ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ደረጃ iv/በዲፕሎማ/ በአውቶ መካኒክስ /10+3/ የሰለጠነ/ች ወይም አውቶ መካኒክስ /10+2/ ደረጃ iii በሰርተፍኬት የሰለጠነ/ች ሆኖ/ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ የሙያ ደረጃ iv በዲፕሎማ /10+3/ በጠቅላላ መካኒክስ ወይም /10+2/ ወይም ደረጃ iii በሰርተፍኬት ወይም በተመሳሳይ የሰለጠነ/ች ሆኖ/ሆና የcoc የምዘና ውጤት ማቅረብ ይጠበቃል
94
በትላንትናው ዕለት በአስመራ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ትላንት ማምሻውን በአስመራ ቤተ መንግሥት የእራት ግብዣ ተደርጎለታል፡፡በአስመራ የተደረገውን ሞቅ ያለ አቀባበል አስመልክተው በጃፓን የኤርትራ አምባሳደር እስጢፋኖስ አፈወርቂ፣ በኤርትራ ይህን መሰል አቀባበል የተደረለት የሌላ ሐገር መሪ የለም ብለዋል፡፡ ጉብኝቱን ተከትሎ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ለዓመታት ተቋርጦ የነበረው የስልክ ግንኙነት ተጀምሯል፡፡ከዚህም በተጨማሪ ወደብ በጋራ ለመጠቀም፣ የሁለቱ ሐገራት አየር መንገዶች ወደ ሁለቱ ሐገራት በረራ እንዲጀምሩ፣ የሁለቱም ሐገራት ዜጎች እንደልባቸው በሁለቱ ሐገራት ተዘዋውረው መስራት እንዲችሉ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
95
ከአርብ እስከ ሐሙስ በነበረው የአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ሦስት ትልልቅ በዓላት ነበሩ፡፡ … ታላቁ የዐድዋ ድል መታሰቢያ፣ የኦስካር ሽልማት ስነ - ስርዓት የተከናወነበትና የሴቶች ቀን የተከበረበት … ማርች 8!! ሶስቱም ውስጥ ታላላቅ ሴቶች አሉ፣ ሶስቱም ውስጥ አሸናፊነት አለ፡፡ … የዐድዋ ድል የተገኘው በዋናነት በሴቶች ብርታት ነው፡፡ ጣይቱ ብጡል ዋናዋ ተዋናይ ብትሆንም በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ውሃ በመቅዳት፣ ምግብ በማብሰል፣ ጠጅ በመጣል፣ ቁስለኛን በማከምና በመንከባከብ፣ በዘፈንና በሽለላ ዘማቹን በማበረታታት ለድል አብቅተውናል። ሁለተኛው ደግሞ እሁድ ምሽት በተካሄደው የኦስካር ሽልማት ስነ - ስርዓት ስቲፈኒ ሃዱሽ አሸንፋ በቀዩ ምንጣፍ ላይ በሃበሻ ልብስ ሽር ብትን ማለቷ ነው፡፡ ሶስተኛው ደግሞ ማርች 8፣ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ የአስራ ሰባት ዓመቷ አሜሪካዊ ተማሪ ኤማ ጎንዳሌዝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተመረጡ አንድ መቶ ሃያ ተፅዕኖ ፈጣሪ የዘመኑ ሴቶች ውስጥ በቁጥር አንድ ደረጃ ተመርጣለች፡፡ ወዳጄ፡- ሴቶች ሁሌና የትም አሉ፡፡ … ይኖራሉም፡፡ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሴቶች የማይሳተፉበት፣ ድጋፋቸውን የማይሰጡበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አይሳካም፡፡ ስልጣኔያችንን ወደፊት በሚያራምዱ የሳይንስ የጥበብና ፍልስፍና፣ የአዳዲስ ቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ግኝቶች፣ ለሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሚደረጉ ትግሎች … የሴቶች ሚና ከፍተኛ ቢሆንም ገና ብዙ መንገድ መጓዝ እንደሚቀር አያጠራጥርም፡፡ በህብረተሰብ ዕድገት መንገድ ላይ ወይም በመጣንባቸው የታሪክ ጉዞ ውስጥ ሴቶች የወንዶችን ፍላጎት ለመፈፀም፣ ወንዶችን ለማገልገል የተፈጠሩ፣ እንደ ግል ንብረት ይቆጠሩ የነበሩት፣ በአጉል ልማድና ወግ የተተበተቡ፣ ጎታችና ኋላ ቀር ማህበረሰቦች ውስጥ በሴቶች ላይ የነበረው ፆታዊና መደባዊ ጭቆና የከፋ ነበር፡፡ የተጫነባቸው ቤተሰብአዊ ኃላፊነትና የስራ ድርሻ ሊሸከሙት ከሚችሉት በእጅጉ የከበደ ነበር፡፡ አሁን፣ አሁን ግን እነዚህ ሁኔታዎች ከዕውቀት መስፋፋትና ከስልጣኔ ዕድገት ጋር እየተሻሻሉ ፆታዊ ጭቆና እየደበዘዘ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጭቆና እየጎላ፣ ትግሉም አቅጣጫውን እየቀየረ የመምጣት አዝማሚያ እያሳየ ነው፡፡ አንዳንድ የመብት ተሟጋቾች የወንድ የበላይነትና የሴቶች የበታችነት የሚባለውን ጉዳይ … ወንድና ሴት ሆኖ ከመፈጠር ጋር የተገናኘ የልዩነት ሚዛን ሳይሆን፣ በተሳሳተ ግንዛቤ ላይ የዳበረና የደረጀ አጉል ባህል የፈጠረው አስተሳሰብ ነው ይላሉ፡፡ ይህንንም አስተሳሰብ በሰለጠነና ሁሉን አቀፍ በሆነ አዲስ ቅኝት በመለወጥ ጭቆናን ከፆታ ጋር የሚያዛምደውን እምነት መቀየር ይቻላል፣ ዕኩልነትን በመተሳሰብ መሰረት ላይ ማቆም አያስቸግርም፣ ፆታ ተፈጥሯዊ ፀጋ እንጂ አንዱን አስልጦ ሌላውን የሚያሳንስ ምክንያት ሊሆን አይገባም፤ ሲሉ ይሞግታሉ፡፡ … የግድ እንደ ምክንያት ቢቆጠር እንኳ ሴቶች ባላቸው ስራና ማህበራዊ ኃላፊነት ላይ ልጆች የመውለድ፣ የማጥባትና የመንከባከብ ፀጋቸው ከተፈጥሮ ጋር ስለሚያቀራርባቸው የበላይነቱ የነሱ መሆን አለበት በማለትም ይከራከራሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሴቶች እንደ ማናቸውም ፍጡር፤ ተፈጥሮ በራሷ ህግ ምክንያት የሰውነት አካላቸውም ሆነ ስነ ልቦናቸው ለሚሰማሩበት የስራ ድርሻ እንዲመጥኑ አድርጋ በልክ ያነፀቻቸው በመሆኑ ወንዶች የሚሰሩትን ሁሉ መስራት አይጠበቅባቸውም፡፡ ሁሉን መስራት እየቻሉ ባላቸው ጭቆና ምክንያት እንዳይሰሩ ተደርገዋል ማለቱ አያስኬድም፣. ተፈጥሮ ለሁሉም ዕኩል ዓይን አላት፣ ወንድነት የራሱ ምክንያት፣ ሴትነት የራሱ ምክንያት አላቸው፤ “ዓይብና ቅልጥምም ወዴት ግጥምጥም” በማለት ይሟገታሉ፡፡ ከነዚህ አስተሳሰቦች ጋር በአንዳንድ ጎን የሚስማሙ፣ በሌላው ደግሞ የሚቃረኑ፣ የራሳቸው ፍልስፍናና ምክንያታዊነት ያላቸው እሳቤዎችም ጥቂት አይደሉም፡፡ ሶቅራጥስ (ፕሌቶ)፣ ካንትና ፍራንሲስ ቤከንን የመሳሰሉት ቀደምት ፈላስፋዎችና እንደ ሲግመንድ ፍሮይድ አይነቶቹ የዘመናዊ ሳይኮሎጂ ሊቃውንትም በዚህ ጉዳይ ላይ ያላቸውን እሳቤዎች በመጽሃፎቻቸው አስፍረዋል፡፡ የጉዳዩ ባለቤቶች ነን ከሚሉት ውስጥ ደግሞ ፈላስፋዋ ሼሪ አርትነርን ጨምሮ ሱዛን ቦርዶ፣ ስምኦን ዶቩዋ፣ ኬት ሚሌት፣ ካሮል ጁሊያን፣ ኤቨሊን ኬለንና የመሳሰሉት የሴቶችን ጭቆናና የመፍትሄውን አቅጣጫ በየፅሁፎቻቸው በዝርዝር አብራርተዋል፡፡ ከሴቶች ጉዳይ ባለፈ አለማችን ለሰው ልጆች የተሻለ የመኖሪያ ቦታ እንድትሆን የታገሉ በእግረ መንገድም የሴቶች ችግር ከሌሎች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ጋር ያለውን ጥብቅ ተያያዥነት በድርሰቶቻቸው የገለፁ ሴት ልብ ወለድ ፀሐፍት ብዙ ናቸው፡፡ ከነዚህም ውስጥ አየን ራንድ፣ ማርጋሬት ሚቸል፣ ቮርጂኒያ ዎልፍ፣ በርታ ክሌይ፣ ዳኒኤላ ስቲልና ሌሎች ይገኙበታል፡፡ ማርጋሬት ሚቸል በአስራ ስምንት መቶ አጋማሽ አካባቢ በነበረው የአሜሪካ እርስ በርስ ጦርነት ምክንያት የተፈጠረውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ የገለፀችበት gone with the wind (“ነገም ሌላ ቀን ነው” በሚል ርዕስ ነቢይ መኮንን ወደ አማርኛ መልሶታል) መጽሃፍዋ ውስጥ የታሪኩ ማጠንጠኛ የሆነችው በቀውሱ ምክንያት ሊፈርስ የነበረ ትልቅ ቤተሰብ የማስተዳደር ኃላፊነት የወደቀባት፣ የወደደችውን ማግባት ያልቻለች፣ ያገባችው በሳምንት ውስጥ የሞተባትን ገፀ ባህርይ ምሳሌ በማድረግ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶች በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ በተለይ በሴቶች ላይ የሚያሳድሩትን እንግልት በገፀ ባህሪዋ አስታክካ እንዲህ በማለት ገልፃለች፡-
96
ወደኛ ሀገር ስንመለስ፤ ሴቶች የወንድ አገልጋይና ልጅ አሳዳጊ ብቻ ሆነው እንዳይቀሩ፣ ከማጀት ወደ አደባባይ እንዲወጡ፣ ወንዶቻቸው ከትምክህት ተላቀው አጋሮቻቸው እንዲሆኑ፣ የሚደርስባቸውን ፆታዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጫናዎች ተቋቁመው በአገር ልማት ተግባራት ተሳትፎ እንዲያደርጉና ትምህርት እንዲማሩ በማሳመን ጥርጊያ ያሰናዱ፣ የብርሃን ጮራ የፈነጠቁ፣ የስልጣኔ ብርሃን እንዲገባ መስኮት የከፈቱ፣ ፆዊ በደል ለደረሰባቸው ጥብቅና የቆሙ፣ ሃኪም ቤት አቋቁመው ቁስላቸውን ያጠገጉ፣ የውርደት እንባቸውን ያበሱ፣ ሲርባቸው አጉርሰው፣ ሲታረዙ አልብሰው፣ መጠለያና መጠጊያ የሆኑ፣ በሙዚቃ፣ በቴአትር፣ በሲኒማ፣ በስነ ፅሑፍና በግጥም ብሶታቸውን የከወኑ፣ በሬዲዮናቸው የአየር ሰዓት መድበው፣ ፕሮግራም አዘጋጅተው ያስተማሩ ትልልቅ ሴቶች ነበሩ፡፡ … አሁንም አሉ!! በፋሽስት ወረራ ወቅት በዱር በገደል በመንከራተት፣ ከአርበኛው ጎን የተዋደቁ፣ የሚስጢር መልዕክት በማቀበል የነፃነት ትግሉን ያፋፋሙ ጀግና ሴቶች ብዙ ናቸው፡፡ በነፃነት ማግስት አንዳንዶቹ “አቶ” ተብለው ሲጠሩ እንደነበር ሰምቻለሁ፡፡ ወዳጄ፡- የአገራችን ሴቶች በማናቸውን ጉዳይ ብቁ ሆነው ራሳቸውን እንዲችሉ በግልም ሆነ በማህበሮቻቸው በኩል ድጋፍ በማድረግ ላይ የሚገኙ እንደ ኢትዮጵያ ሴቶች የህግ ባለሙያዎች ማህበር፣ የኢትዮጵያ ሴቶች ደራስያን ማህበር፣ ሴቶች ይችላሉ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበር፣ የሴታዊነት ንቅናቄና የመሳሰሉት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላችንን ማዋጣት ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ማርች, ኤይትን ስናስታውስ ለነሱ እያጨበጨብን ነው!! ወዳጄ፡- የዛሬው የሃሳብ መንገድ ርዕሳችን “እማማ ሻማውን አብሪ…” የሚል ነው፡፡ ይህን ያለው በሰሞኑ የኦስካር ሽልማት ስነ - ስርዓት ላይ በምርጥ አክተርነት አሸናፊ የሆነው ጌሪ ጎልድማን ነበር፡፡ ጌሪ የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ዕድሜ ባለፀጋ ለሆኑት እናቱ “mama light the candle, am bringing oscar” ብሎ ነበር፡፡ … አቤት ግጥምጥሞሽ!!
97
ባለፈው ያቀረብኩት ክፍል 1 ጽሑፌ “ተሓህት/ወያነ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭና ጥቅም አስከባሪ ነውን? የትግራይ ሕዝብ ከመሰረቱ ጀምሮ የተሓህት/ወያነን ዓላማ ደግፎና በእርሱ ተመርቶ ተንቀሳቅሷልን?” የሚሉትን ጥያቄዎች ነበር የተመለከተው:: የተጠቀሱትን ጥያቄዎች ስንወያይ ያቀረብኳቸው ታሪካዊ ማሳያዎች የሚያደርሱን ሀቅም የትግራይ ሕዝብ ተሓህት/ወያነን ይቃወምና ይፋለመውም እንደነበር፣ አሁንም እግር ከወርች ታፍኖ እንዳለ በመሆኑ “እንዴት ሆኖ ታዲያ ተሓህት/ወያነ አሸነፈ?” በማለት አንባቢያንን መሰናበቴ ይታወሳል:: ከዚያው ልቀጥል:: የትግራይ ሕዝብ ተሓህት/ወያነን ይቃወም ነበር እንጂ አልደገፈም ሲባል ይህንን በተመለከተ ተዘውትረው የሚደመጡና የሚነሱ ጥያቄዎች አሉ። ሕዝቡ ተሓህትን የሚቃወም ከነበረ እንዴት ሆኖ ታዲያ ተሓህት/ወያነ አሸነፈ? ለምንስ አይቃወመውም ወይም ሲቃወመው አይታይም? በማንስ ተደግፎ ነው አገሪቱን አምቆ እየገዛ ያለው? የሚሉትና የመሳሰሉት:: አንዳንድ ወገኖች የፋሺስቱ መንደርተኛ ድርጅት የተሓህት/ወያነንና የትግራይ ሕዝብን አንድነት ለማስረገጥ እንደ መከራከሪያ የሚያቀርቡት ነጥብ ታዲያ ለምን አይታገላቸውም የሚል ነው። ግራ የሚያጋባው ግን ለምን ይህ ጥያቄ ሌላውን የአገራችንን ሕዝብንም አስመልክቶ እንደማይቀርብ ነው። እንኳንስ በልጅ ፣ በቤተ-ሰብ፣ በሥራ ቦታ፣ በአካባቢ ሚሊሻ፣ በካድሬ፣ በ”ሕዝባዊ” ማኅበራት፣ … የስለላ ድር ተጠፍንጐና በግል ንብረትነት ደረጃ ታግቶ ያለው የትግራይ ሕዝብ ቀርቶ በንጽጽር ሲታይ፤ በፈራ ተባም ቢሆን፤ ድምጹ የሚያሰማለት ወገን ያለው የሌሎች ክፍለ-ሀገራት ሕዝብም ቢሆን በእመቃው ብዛት ምክንያት ሆኖ መገኘት የሚገባውን ሆኖ ሲገኝ አይታይም። ያም ተባለ ይህ የትግራይ ሕዝብ በርግጥ ተሓህት/ወያነን ይቃወም ነበር፤ ተዋግቶታልም። ይህ ማለት ግን ድርጅቱ አመጹን ሲጀምርም ሆነ በቀጠሉት ዓመታት በትግራይ ውስጥ ወይም የትግራይ ተወላጅ የሆነ ምንም ደጋፊ አልነበረውም ወይም የለውም ማለት አይደለም። ነበረው። ለምሳሌ፥ ከጅምሩ ጀምሮ ጥላው ባጠላበት አካባቢ ነዋሪ በነበረውና በተለያየ ምክንያት ከትግራይ ውጭ ይኖር በነበረው የክፍለ ሀገሩ ተወላጅ ውስጥ በጭፍን የትግራዋይነት ስሜት የተመሠረተ ውሱን ድጋፍ ነበረው። ጠባብ አመለካከት ያጠቃቸው፣ በአማራው ጐሳ ጥላቻ የሰከሩ (የመጀመሪያው “ውፈር ተበገስ ተጋዳልይ ትግራይ፣ ሲሕብካ በሎ ነዙ ዓሻ አምሓራይ”፤ ዘፈናቸውን ልብ ይለዋል። ትርጉሙ “ዝመት ተነስ የትግራይ ታጋይ፣ ሳብ አርገህ ግጨው ያንን ጅል አማራ” ማለት ነው)፣ በትግራይ ኪሳራ ኤርትራን የማስገንጠል አጀንዳ ያነገቡ፣ የፊውዳላዊው ሥርዓት ተንኮታኩቶ የአባቶቻቸው መሬት በመወረሱ ያኰረፉ ቀለም ቀመሶችና ጭፍን ተከታዮቻቸው፣ ወዘተ … የዚሁ ድርጅት የድጋፍ እምብርት ነበሩ። በዚህ ጽሑፍ ለማመልከት የተፈለገው አብዛኛው የትግራይ ሕዝብ፤ በተለይ ደግሞ ከምዕራብ እና ከፊል መሃል ትግራይ ውጭ የነበረው የክፍለ-ሀገሩ ሕዝብ ተሓህት/ወያነን የማይደግፍ እንደነበረ ነው። ያም ሆነ ይህ ግን የትግራይ ሕዝብ ፀረ-ተሓህት/ወያነ አቋም በረጅም ሂደት ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች እየተዳከመ መጥቷል። ከምክንያቶቹ ጥቂቱን መጥቀስ አስፈላጊ ነው። ለ14 ዓመታት ያህል ተሓህት ወያነ ትግራይን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ሳይችል ቆይቷል። በተለይ እስከ 1976/77 ድረስ እንደሽምቅ ተዋጊነቱ ድንገተኛ አደጋ እየጣለ በአንዳንድ ከተሞች በነበሩ ወታደራዊ ሠፈሮችና በመጓጓዣ አጀባ ወቅት ጉዳት እያደረሰ ሲያፈገፍግ የነበረ ቢሆንም አብዛኛው እንቅስቃሴው በከፊል መሃልና በምዕራባዊው ክፍል ተገድቦ ቆይቷል። በሰሜን፣ ምስራቅ፣ ደቡብና ከፊል መሃል ትግራይ የነበረው ተቀባይነትም የጐላ ሳይሆን ቆይቷል፤ በፋሺስታዊ ተግባሩ ከመፈራቱ በቀር። ከ1976/77 ዓ.ም. ጀምሮ ግን የአገርና የሕዝብ ደኅንነት መ/ቤት በፈጸመው አሳዝኝ በክህደትም ይሁን የሙያ ብቃቱን ደካማነት ባጋለጠ ስህተት ወይም፤ በሌላ የተሻለ አገላለጽ፤ በአገር አንድነትና ደኅንነት ላይ የፈጸመው ወንጀል ምክንያት ሁኔታው በፍጥነት መቀየር ጀመረ። እጅግ በርካታ የክፍለ-ሀገሩ ተወላጆች ባልዋሉበትና ባልሆኑት የተገንጣይ ቡድኖች አባላት ሆነው ተገኙ በማለት ለእስራት፣ ለግርፋት፣ ለአካል መጉደልና ለሞት ዳረጋቸው። የእነዚህ የአንድነት ኃይሉ ግምባር ቀደም ተዋናዮች ቤተሰብ ፈረሰ፤ ልጆቻቸውና የሚጦሩት ሁሉ ለችጋር ተዳርገ፤ ለመሳቀቅና አንገት ለመድፋት ተገደደ። እነዚህ ሰዎች በትግራይ ውስጥ ከክፍለ-ሀገር እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ በመንግሥትና በማኅበራት መዋቅር ውስጥ ተመድበውና ተመርጠው ሲሰሩ የነበሩ ጉልህና ጽኑ ፀረ-ተሓህት አቋም የነበራቸው ሰዎች ናቸው። በትጥቅ ትግሉም ጭምር ተሓህት/ወያነን እያሳደዱ ሲቀጡና መግቢያ መውጫ ሲያሳጡ የነበሩ ጽኑ ኢትዮጵያዊ አቋም የነበራቸው ሰዎች ናቸው። እነዚህ ሰዎች ናቸው እንግዲህ በተሓህት/ወያነ ሥውር ደባና በዋናነት ግን በአገርና የሕዝብ ደኅንነት ጥበቃ መሥርያ-ቤቱ የሀገር ክህደትም ይሁን ንዝህላልነትና ብቃት ማነስ ”የወያነ አባለት” ተሰኝተው ከውጭ አገር ሳይቀር በወረንጦ ተለቅመው ለተባለው እስርና መከራ የተዳረጉት። ይህንን ጉዳይ አቶ ገብሩ አሥራትም በመጽሓፋቸው ጠቅሰዉታል (ገብሩ፣ 2006፣ ገፅ 159-161)። ከነዚህ ሰዎች መካከል ጥቂቱ በተለያየ ምክንያት ሕይወታቸውን በእስር-ቤት አጥተዋል። ገሚሱ በጀ/ል ታሪኩ ላይኔ የትግራይ ጦር አዛዥነት ወቅት ተሓህት/ወያነ የመቀሌ ወኅኒ-ቤትን በወረረበት ጊዜ አስፈትቶ ወስዷቸው ከፊሉ ድርጅቱን ሲቀላቀሉ ከፊሉ ደግሞ በሱዳን በኩል ወደ ምዕራብ አገራትና ጥቂቱ ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። አብዛኛዎቹ ደግሞ ከ1976 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ቆይተው ወያነ የተረከባቸው ሲሆን ከፊሉን ፈቶ ከፊሉን ደግሞ አባሎቹ ናችሁ በተባሉለት በወያነ ዘመንም እስራታቸው ቀጥሎ እስካሁንም ድረስ ያልተፈቱ አሉ፤ ጥቂቱ ደግሞ በግርግሩ አምልጠው በስደት ይኖራሉ። ይህ መከራ ከደረሰባቸው ሰዎች ውስጥ የተወሰኑት በተሓህት/ወያነ ውስጥ ታቅፈው ለበርካታ ዓመታት የሠሩና እየሠሩ ያሉ ሲሆን፤ ጥቂቶቹ በደረሰባቸው የኅሊና ቁስል በበቀል ስሜት ተነሳስተው ከልብና በፈቃደኝነት ያገለገሉትን የደርግን ሥርዓት “ትግራዮችን ለማጥፋት የተነሳ” ብለው እስከ መክሰስ ድረስ ሄደዋል። በኰ/ል ተስፋዬ ወልደ-ሥላሴ የአገርና የሕዝብ ደኅንነት ሠራዊት በተሓህት/ወያነ አባልነት ተወንጅለው በአፈሳ ለእስር፣ ለስየልና ለሞት ከተዳረጉት የትግራይ ተወላጆች መካከል፣ የራሳቸው ድርጅት ተንኰል ጠልፎ የጣላቸው በጣት የሚቆጠሩ የወያነ አባላት የነበሩ ቢሆንም አብላጫዎቹ ግን ለወያነ ህልውና አደጋ የጋረጡ ፀረ-ወያነ ታጋዮች ነበሩ። በጣም የሚገርመው በአገር ጉዳይ ቀርቶ በራሳቸው ህይወትም የረባ ዓላማ ያልነበራቸውም አብረው መታፈሳቸው ነው። ከእነዚህ በወቅቱ ወያነ ተብለው በኰ/ል ተስፋዬ የጅብ ሠራዊት የታፈሱ ዜጎች መካከል አብዛኛዎቹ በወያነ ዘመንም በፀረ-ትግራዋይነት ለበርካታ ዓመታት ታስረው የተፈቱና በእስር በመማቀቅ ላይ ያሉም ይገኙባቸውል። ዕድሉ የገጠማቸው ደግሞ ለማምለጥ በቅተው ኑሮኣቸውን በስደት ዓለም እየገፉ ናቸው። የተሓት/ወያነን ፀረ ኢትዮጵያ አቋም አንደግፍም ያሉና ምንም ፖለቲካዊ ተሳትፎ የሌላቸው፣ የሌሎች ኀብረብሄር እና አፍቃሪ የኢትዮጵያ አንድነት የፖለቲካ ድርጅቶች አባላት የሆኑ የትግራይ ተወላጆች አይደሉም፣ በኢሠፓ መንግሥትም ውስጥ ፖለቲካዊ ተሳትፎ የነበራቸው እንኳ ተገድለዋል፣ ተሠቃይተዋል፣ ከትግል ታግተዋል:: በወያነ ተከል የመንግሥት አካላት:: ባለኝ ትንሽ ቆየት ያለ መረጃ መሠረት ከነዚህ በሺዎች ከሚቆጠሩት ግፉአን መካከል ለምሳሌ ያህል የሚከተሉትን ማየት ይቻላል። አቶ በላይ በርሄ (በቅደም ተከተል፥ የተምቤን አውራጃ የሕዝብ ድርጅት ኃላፊ፣ የትግራይ ክፍለ-ሀገር የሕዝብ ድርጅት ኃላፊ፣ ሲታሰር የጎንደር ክፍለ-ሀገር የኢሠፓአኰ ሥራ-አስፈጻሚ ኰሚቴ አባልና የኅብረት ሥራ ማህበራት ጉዳይ ኃላፊ፤ ታስሮ ደብዛው የጠፋ)፣ አቶ ኃይለ-ኪሮስ አሰግድ (የግምባር ገድሊ ሓርነት ትግራይ አመራር አባል፣ የራያና አዘቦና የእንደርታ አውራጃዎች አስተዳዳሪ እና የዘንዶ ሠራዊት መስራችና አዛዥ የነበረ፤ በኢሠፓአኰ/ኢሠፓ ዘመን ለስድስት ዓመታት ያህል ታስሮ የቆየና ተሓህት/ወያነም እስራቱን ቀጥሎበት እስከ ቅርብ ጊዜ በእስር የማቀቀ።)፣ መምህር ታደሰ ገብረ እግዚአብሔር (መጀመሪያ የየካቲት 66 ፖለቲካ ትምህርት-ቤት አስተዳዳሪ፤ ሲታሰር የኢሠፓኰ ማዕከላዊ ኰሚቴ አባልና የሸዋ ክፍለ-ሀገር/የአዲስ አበባ የርዕዮተ-ዓለም ጉዳይ ኃላፊ፤ ታስሮ ደብዛው የጠፋ)፣ አቶ ኅሩይ አስገዶም (በቅደም ተከተል የትግራይ ክፍለ-ሀገር ትምህርት ቤቶች ጽህፈት ቤት ምክትል ሥራ-አስኪያጅ፣ የዓጋመ አውራጃ አስተዳዳሪ፣ የትግራይ ክፍለ-ሀገር ተቀዳሚ ምክትል አስተዳዳሪ፤ በቁጥጥር የማዋል ሙከራ ወቅት እጄን አልሰጥም ብሎ ተታኩሶ የሞተ)፣ አቶ አብራሃ በላቸው (የሽሬ አስተዳዳሪ የነበረ፤ የተሓህት/ወያነ የሌሊት ቅዠት፣ እያሳደደ ይቀጣቸው የነበረ እና በጣም ይፈሩት የነበረ፤ በኢሠፓአኰ/ኢሠፓ ዘመን ለስድስት ዓመታት ያህል ታስሮ የቆየና ተሓህት/ወያነም እስራቱን ቀጥሎበት በእስር እየማቀቀ ያለ። የቅርብ ጊዜ መረጃ የለኝም።)፣ አቶ ተስፋሁን አወቀ (የዓድዋ አውራጃ የሕዝብ ድርጅት ኃላፊ፤ በኢሠፓአኰ/ኢሠፓ ዘመን ለስድስት ዓመታት ያህል ታስሮ የቆየና ተሓህት/ወያነም እስራቱን ቀጥሎበት በእስር እየማቀቀ ያለ። የቅርብ ጊዜ መረጃ የለኝም።)፣ አቶ አብረሃ ውበት (የገርዓልታ እና የሳምሬ ወረዳ አስተዳዳሪ፤ በታሰረበት ወቅት አሁን የተረሳኝ የአንድ የትግራይ አውራጃ የኢሠፓአኰ ቁጥጥር ኰሚሽን ሰብሳቢ የነበረ፤ በኢሠፓአኰ/ኢሠፓ ዘመን ለስድስት ዓመታት ያህል ታስሮ የቆየና ተሓህት/ወያነም እስራቱን ቀጥሎበት በእስር እየማቀቀ ያለ። የቅርብ ጊዜ መረጃ የለኝም።) መምህር ብርሃኑ ማሞ (በደርግ ዘመን የመቀሌ ከተማ የመጀመሪያ ከንቲባ፤ በኢሠፓአኰ/ኢሠፓ ዘመን ለስድስት ዓመታት ያህል ታስሮ የቆየና ተሓህት/ወያነም እስራቱን ቀጥሎበት እስከ ቅርብ ጊዜ በእስር የማቀቀ። በዚህ ወቅት የደርጉ ቀዳሚ ዘመቻ መምሪያ መቀሌ ሰፍሮ ነበር)፣ መምህር አሰፋ እሸቱ (በደርግ ዘመን የመቀሌ ከተማ የመጀመሪያ ምክትል ከንቲባ፤ በኢሠፓአኰ/ኢሠፓ ዘመን ለስድስት ዓመታት ያህል ታስሮ የቆየና ተሓህት/ወያነም እስራቱን ቀጥሎበት እስከ ቅርብ ጊዜ በእስር የማቀቀ።)፣ እነዚህ በመቶዎች ከሚቆጠሩት ተሓህት/ወያነን ቀጥ አድርገው ከመከቱትና ድርጅቱ ይፈጥረው የነበረውን ችግርንም ለዘለቄታው ለመፍታት ጥረት ካደረጉት የክፍለ-ሀገሩ ግንባር ቀደም ፀረ-ተሓህት/ወያነ ሰዎች ውስጥ ተቆንጥረው ለአብነት የተገለጹ ናቸው። ይህን ከፍ ብሎ የተገለፀው በኢሠፓ ሥርዓት ውስጥ ሲያገለግሉ የነበሩትንና የተሓህት/ወያነ ዓላማን ሳይቀበሉ ከፖለቲካው ዓለም ውጭ ሆነው በመንግሥትም ይሁን በግል የሥራ ዓለም ተሰማርተው ይገኙ የነበሩትን ለኢሠፓ መንግሥት የደኅንነት ቢሮ የጥቃት ኢላማ እንዲሆኑ ያበቃ ሴራ ተሓህት/ወያነ የሰራው ሴራ ነው። ድርጅቱ እነዚህ ሰዎች አባሎቹ እንደነበሩ የሚያስመስል መረጃ የኢሠፓ መንግሥት የደኅንነት ቢሮ ጆሮ ዘንድ እንዲደርስ በማድረጉ ነው የጅምላ እስሩ የተፈፀመው። ይህ ዕውነታ ከያኔ ጀምሮ ሲነገር የኖረና በስተመጨረሻም ኢሠፓ ራሱም ነቅቶበት ያቆመው አሳዛኝ ተግባር ሲሆን አሁን አቶ ገብሩ በጽሑፋቸው አረጋግጠዉታል። ይህ ተግባር ለተሓህት/ወያነ የመንግሥት ሥልጣን መቆጣጠርና ኤርትራን የማስገንጠል ድርጊት በር የከፈተ አስዛኝ ስህተት/ወንጀል ሲፈፀም ክፍለ-ሀገሩ በነሻለቃ ሙሉጌታ ሓጐስ (የኢሠፓኣኰ/ኢሠፓ 1ኛ ፀሓፊ)፣ ጀነራል ከፈለኝ ይብዛ (የክፍለ-ሀገሩና የጦሩ የበላይ አስተዳዳሪ)፣ ኰ/ል ፈቃደ ዋኬኒ (የክፍለ-ሀገሩ ዋና አስተዳዳሪ)፣ ጀነራል ታሪኩ ላይኔ (የትግራይ ዕዝ አዛዥ)፣ ሻለቃ ደስታ መሸሻ (የክፍለ-ሀገሩ ምክትል አስተዳዳሪ)፣ አቶ አምባቸው ደምሴ (የክፍለ-ሀገሩ የኢሠፓኣኰ/ኢሠፓ የሥራ-አስፈጻሚ ኰሚቴ አባልና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ)፣ አቶ ሳሙኤል ሃብቴ (አቶ አምባቸው ደምሴን ተክቶ የኢሠፓኣኰ/ኢሠፓ የሥራ-አስፈጻሚ ኰሚቴ አባልና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ)፣ አቶ አፈ-ወርቅ (የክፍለ-ሀገሩ የኢሠፓኣኰ/ኢሠፓ የሥራ-አስፈጻሚ ኰሚቴ አባልና የርዕዮተ-ዓለም ኃላፊ)፣ ሻለቃ ሰሙ-ንጉስ (የክፍለ-ሀገሩ የኢሠፓኣኰ/ኢሠፓ የሥራ-አስፈጻሚ ኰሚቴ አባልና የቁጥጥር ኰሚቴ ሰብሳቢ)፣ ኰ/ል ገብረመድህን (የክፍለ-ሀገሩ ፖሊስ አዛዥ፣ በኋላ በጀነራል ማዕርግ የኤርትራ ፖሊስ አዛዥ [?])፣ አቶ ውብሸት (የክፍለ-ሀገሩ የሕዝብ ደህንነት መ/ቤት ኃላፊ) ወዘተ… ይተዳደር ነበር። እነዚህ ባለሥልጣኖች ተሓህት/ወያነ በትግራይ ውስጥ የበላይነት ለማግኘት ስለቻለበት ሁኔታ ተጠያቂነት ያላቸው ሰዎች ናቸው። ዋነኛ ተጠያቂዎቹ ግን ሻለቃ ሙሉጌታ ሓጐስ፣ ሜ/ጀነራል (?) ከፈለኝ ይብዛ፣ ጀነራል ታሪኩ ላይኔ፣ አቶ ውብሸት (?) እና ማዕርጋቸውና ሥማቸው የተዘነጋኝ የትግራይ ወታደራዊ ዕዝ የፖለቲካና የወታደራዊ ደኅንነት ኃላፊዎች ናቸው። በዋናነት የእነዚህ ሰዎች አደራን ያለመወጣት ተግባር ነው ኢትዮጵያ አሁን ለደረሰችበት መታመስ በር የከፈተው። በተለይ ሻለቃ ሙሉጌታ ሓጐስ፣ ሜ/ጀነራል (?) ከፈለኝ ይብዛ፣ አቶ ሳሙኤል ሀብቴ፣ ብ/ጀነራል ታሪኩ ላይኔ፣ አቶ ውብሸት የትግራይ ሕዝብን የትግል ስሜት ያላሸቁ፤ የአንድነት ታጋዮችን ያዳከሙና አብዛኛው ክፍለ-ሀገሩ በሙስና ተግባር እንዲዘፈቅ ምክንያት የሆኑ አደራ-በሎች ናቸው። የእነዚህ ሰዎችና መሰሎቻቸው በሥልጣን መማገጥና በግል ጥቅም ማሳደድ ላይ አትኩረው መደበኛ ዕለታዊ የስምንት ሰዓት የሥራ ኃላፊነታቸውን ያለመወጣት ተግባር ነው ኢትዮጵያ አሁን ለደረሰችበት መታመስ በር የከፈተው። የእነዚህ ሰዎች አደራ-በይነትና የፈጠሩት ሁለንተናዊ ንቅዘት ለተሓህት/ወያነ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ መድረስ በር የከፈተ ግዙፍ የአገር ክዳት ስለሆነ በሚገባ ሊገለጽ የሚገባው የአገሪቱ የፈተና ወቅቶች ታሪክ አካል ነው። ወደፊት ተነጥሎ ሰፋ ባለ መልኩ ይታያል። ሌላኛው እስካሁን ድረስ ምስጢሩ በቅጡ ያልተገለጠው ሕዝቡን ያስቆጣ ተግባር በሓውዜን ላይ የተደረገው የአየር ድብደባ ነው። በዚህ ድብደባ እጅግ በርካታ የከተማውና የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ሰላማዊ ወገኖቻችን በአሰቃቂና አሳዛኝ ሁኔታ ሕይወታቸውን አጥተዋል። ድብደባው የተካሄደው በብርጌዶች የሚቆጠር የተሓህት/ወያነ ጦር በከተማው ሰፍሮ መቀሌን ለማጥቃት ዝግጅት እያደረገ ነው የሚል መርጃ በክቶ ለነበረው የኢሠፓ መንግሥት የደህንነት መሥሪያ-ቤት በመድረሱ ነው። ይህንን አቶ ገብሩና ሌሎቹም የወያነ መሪዎች አሌ ያሉት ቢሆንም የዓጋመና የኽልተ-አውላዕሎ ሕዝብ ቁጣ ለመቀስቀስ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ሴራ ነው። ይህ ተግባር እንደ ብዙ ሌሎች ነገሮች የስብሓት/መለስ ቡድን ከሌሎቹ የድርጅቱ የአመራር አባላት ጀርባ የፈፀመው ሊሆን ቢችልም ዕውነቱ ግን ይኸው ነው። ልቦናቸውን ጨፍነው አገዛዙን የሚደግፉ ደካሞችና ጠባብ ጐሰኞች ይህንን ተሓህት/ወያነ የፈጸመውን በርካታ የክፍለ-ሀገሩ ልጆችን ለእስራት፣ ለአስቃቂ ግርፋት፣ ለአካል መጉደልና ለሞት የዳረገበትን አረመኔያዊ ደባም ሆነ ሌላው ሁሉ የሕዝብንና የአገርን ደኅንነትና ጥቅምን የጐዳ ተግባር መፈጸሙ “ለትግሉ መጐልበት ጠቃሚ ስለነበረ ተግቢ ነው” የሚል ነፈዝ መከላከያ ያቀርቡለታል። ለነዚህ ነፈዞች ተሓህት/ወያነ ሙሉእ በኵሌሁ የሆነ ምንም ዓይነት ጥፋት የማይፈፅም ድርጅት ነው። በእነዚህ አዕምሮ-ስውራን እይታ ኤርትራን መገንጠሉና (ኤርትራን የገነጠለው እሱ ነውና) አገሪቱን የባሕር በር አልባ ማድረጉ፣ የአገሪቱ ታሪካዊና መተክላዊ ጠላቶች በሆኑት በግብጽና በሱዳን እና በሶማሊ እየተረዳና ከርነሱ ጋር አብሮ የአገር አንድነትን አደጋ ላይ መጣሉ፣ መሬት እየቆረሰ ለሱዳን መስጠቱ፣ የድርጅቱ አቋም የተፃረሩትንና በድርጅቱም ውስጥ ሆነው ከአመራሩ ጋር ልዩነት ያሳዩትን ማስገደሉና መግደሉ፣ ወዘተ … ሁሉ ተገቢም አስፈላጊም ልክም ነበር፤ ነውም። ሌላው ወገን የሕዝብና የአገር ሉዓላዊነትን ለድርድር ሳያቀርብ ተሓህት/ወያነን ከማይወዱ ኃይሎች ድጋፍና ትብብር ሲጠየቅ ግን አገራዊ ክህደት፣ ፀረ-ሉዓላዊነት፣ አሸባሪነት፣ ወዘተ ወዘተ ነው። ደርግ ወይም ሻዕቢያ የትግራይ ተወላጆችን ያሰረ፣ የገደለ እንደሆነ ዘር ማጥፋት ነው፤ ተሓህት ወያነ ከዚያ በበለጠ ይህንን ያደረገ እንደሆነ ግን ለትግሉ መስመር አስፈላጊ ነው። ወይም ተራ ስህተት ነው። ደርግ እንደ መንግሥት፤ በዋናነት ደግሞ የሕዝብ ደኅንነት መሥሪያ ቤትና በክፍለ-ሀገሩ የነበሩ የሲቭልና ወታደራዊ ባለሥልጣኖች ተጠያቂ ለመሆናቸው አጠያያቂ ባይሆንም ይህንን ሴራ በመዶለቱ ተሓህት/ወያነም ቢያንስ እኩል ተጠያቂ መሆኑን ግን ዘንግተዋል። ሌላው የተሓህት/ወያነ ደጋፊ ኃይል ደግሞ በጠባብ የጐሳ/መንደር ስሜት የሰከረው ጨለምተኛ ክፍል ነው። መለስ ጠቅላይ ሚኒስቴር፣ በርካታ የዓድዋ ልጆች ”ጄነራል”፣ ሚኒስቴር፣ ቱጃር (ዋልጌውን ሼክ ልብ ይለዋል)፣ ወዘተ … ስለሆኑ ዓድዋ በመላ፤ እንዲያም ሲል ትግራይ በመላ የሆነ የሚመስላቸው በህልም ዓለም የሚዋዥቁ የዋኅን እና መንፈሰ-ደካሞች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ሌላው እዚህ ውስጥ የሚመደበው ቡድን ደግሞ ከኤርትራ ተባርረው የመጡ እዚያው ተወልደው ያደጉና ትግራይ ተወልደው ኤርትራ ያደጉ ያቀፈው ነው። ለነዚህ ሰዎች የኢትዮጵያ ታሪክ ከግንቦት 20፣ 1983 ዓ.ም. ነው የሚጀምረው። ስለ ትግራይ የገዘፈ የኢትዮጵያ ታሪክ ባለድርሻነት፣ ከዚያ በፊት የትግራይ ሕዝብ ለኢትዮጵያ አገሩ አንድነትና ህልውና እውን መሆንና መከበር የከፈለው መስዋዕትነትና ያደረገው ገድል ያላቸው እውቀት መሬት የወረደ ነው። እዚያው ተወልደው ያደጉ በመሆናቸው አርቲፊሻል ትግራዋይነት የሚሰማቸውና ትግራይም ሆነች ኢትዮጵያ የስደት መጠጊያ ከመሆን ያለፈ ብዙ ትርጉም የሚሰጣቸው አይደለም። በርካታ ኤርትራ ውስጥ ሰርተው ሃብት አፍርተውና ከብረው የኖሩ በሻዕቢያ ተዋርደውና ንብረታቸው ተዘርፈው የተባረሩትም የተሓህት/ወያነ ስሜታዊ ደጋፊዎች ናቸው። እነዚህ ወገኖች ጫጉላው አልቆ ተሓህት/ወያነና ሻዕቢያ/ህግደፍ ሲራገጡ ተሓህት/ወያነ በደላቸውን የተበቀለላቸው መስሏቸው በስሜታዊነት ሰክረው አድረዉለታል። የተሓህት/ወያነና ሻዕቢያ መራገጥ የሌላ ጐሳ ተወላጆችም ተሓህት/ወያነ ኢትዮጵያዊ የሆነ መስሏቸው እንዲደናበሩ ያደረጋቸው ሲሆን፤ ራስ አሞኝ ”ብልጣ-ብልጦቹ” ደግሞ ሰበብዋን ተጠቅመው ወደ አገዛዙ ጠጋ እንዲሉ ሰበብ ፈጥሮላቸው ግብር ለመስፈር ሲጣደፉ ተስተውለዋል። በአጠቃላይ ከዚህ በላይ እንደተጠቀሰው የደርግ መንግሥት የፀጥታው ቢሮ ባሳየው የዘቀጠ የሙያ ድክመትና በፈጸመው በጣም አሳዛኝ ክህደት በክፍለ-ሀገሩ ቁልፍ ቦታዎችና በግምባርም ጭምር የነበሩ ፀረ-ተሓህት/ወያነና ሻዕቢያ ባለሥልጣናትና ታጋዮች አፍሶ ዘብጥያ አውርዶ ክፍተት በመፍጠሩ ፀረ-አንድነት አማጽያኑ የፖለቲካና ወታደራዊ ምህዳሩ ያለ ከልካይ እንዳሻቸው እንዲፈነጩበት ዕድል አገኙ። ሕዝቡም ተስፋ መቁረጥ ዳምኖበት ደርግን ያመነና ውኃ የዘገነ ብሎ አረፈው። ከዚህ ውጭ ግን የትግራይ ሕዝብ በመላ ወይም አብላጫው ክፍል የተሓህት/ወያነ ደጋፊና ተከታይ ሆኖ የታየበት ጊዜ አልነበረም። ድርጅቱም ደግሞ የሕዝቡ ጋሻና መከታ አልነበረም። አሁንም፤ እላይ ለማብራራት እንደተሞከረው፤ የሕዝቡን ስትራቴጂያዊ ጥቅሞች እየጐዳ የትግራይ ሕዝብ ጥቅም አስከባሪ ሊሆን አይችልም። የትግራይ ሕዝብ በነፃነት የኖረና ነፃም ሕዝብ ስለሆነ ነፃ አውጭ አልሻውም፣ አያሻውምም። መብቱና ክብሩ ተጠብቆና በልፅጐ ለመገኘት እንዲችል ግን እንደ 1930ዎቹ አሁንም ለፍትሃዊ ሥርዓት መስፈን ይታገላል። ይህ ግን የብተና ፊተውራሪና የባዕዳን ተልዕኰ ፈጻሚ በሆኑት በተሓህት/ወያነ እና በሻቢያ መሪነት እውን ሊሆን አይችለም። ይህ እውን ሊሆን የሚችለው እነሱን በማስወገድ ወይም እነዚህ ቡድኖች በሆነ ተአምር የያዙት አጥፊ ፀረ-ሕዝብና ፀረ-አገር ዓላማ ሲተዉ ብቻ ነው። የትግራይ ሕዝብ ኢትዮጵያዊነትና የአገር ፍቅር ማንኛውም እዚያ ክፍለ-ሀገር የኖረና ተዘዋውሮ ያየ ሰው ሊመሰክረው የሚችል ግልጽ ጉዳይ ነው። ይህንን እንደነ አቶ ተክሌ የሻው የመሳሰሉ በክፍለ-ሀገሩ ቁልፍ ቦታ ላይ ተመድበው የሠሩ ሰዎችም ያዩት ኃቅ በመሆኑ ሊመሰክሩለት ይገባ ዘንድ ኢትዮጵያዊ አደራና ሰብኣዊ ግብረ-ገብነት ግድ ይላቸዋል። ዛሬ ሌላ ጊዜ ላይ ነው ያለነው። በዛሬው ወቅት የትግራይ ሁኔታ በአያሌ ውስብስብ ምክንያቶች ሳቢያ ሌላ መልክ ይዟል። ቢሆንም ግን ስለ ትግራይም ሆነ ስለ ሌላው አካባቢ አስተያየት ሲሰጥ የትላንቱን በትላንት የዛሬውን በዛሬ እየተለካና እየተቀመጠ ነው መሆን ያለበት። የትግራይ ሕዝብ ዛሬ ያለ ጠበቃና እውነተኛ ወኪል ቀርቶ፣ የተሓህት/ወያነ የግል ንብረት እስኪመስል ድረስ በጠባብ መንደርተኛ ነፍጠኞች፣ ባዕድ ነን ባይ ከሃዲዎችና የባንዳ ተተኪዎች ታግቶ መጫወቻ ሆኖ ያለ ሕዝብ ነው። ሌሎች ስለ አካባቢው ምንም ዕውቀት የሌላቸው፤ ወይም በጣም የደከመ የአሉ ተባለ መረጃ ያላቸው፤ ወይም በአገዛዙ ፕሮፓጋንዳ ግዳይ የተጣሉ፤ አለያም ለሆነ ጠባብ ዓላማ ሲሉ እውነታውን መካድ የመረጡ ሕዝቡን ከአገዛዙ ጋር አዳብለው ስለሚመለከቱት አለኝታ አልባነት እየተሰማው የሚኖር ሕዝብ ሆኗል። ከዚህ በላይ ደግሞ አንዳንድ ያልተገሩ ደካማና ለአገዛዙ ያደሩ ፍርፋሪ ለቃሚዎች እምር እያሉ በሚያሰሙት ቀረርቶ ቀረሽ ዛቻ (ሌላ ቃል የተሻለ አይገልጸውም) የበለጠ ጥርጣሬ እንዲያድርበትና ’እኛ ከሌለን አለቀልህ’ የሚለውን የፋሺስቱ መንደርተኛ ቡድን አርቲ ቡርቲ ሰበካ ለመቀበል እንዲያቅማማ እየተገደደ ያለ ሕዝብ ነው። እውነቱ ይነገር ከተባለ ይህ መንደርተኛ ፋሺስታዊ ድርጅት በሥሙ ይነግዳል እንጂ ወኪሉም፣ ነፃ-አውጪውም አይደለም፤ ያደረገለትም ነገር የለም። በርግጥ አገዛዙም ሆነ ደጋፊዎቻቸው ፋብሪካ ተሰራ፣ ቤት ተሰራ፣ ቪላ በቪላ ሆነ፤ በየወረዳው ትምህርት-ቤትና የጤና ተቋምት ፈሉ፣ ወረዳዎቹ በመንገድ ተገናኙ፣ ወዘተ … ይሉናል። አዎ፤ ግን ማን የሠራው ፋብሪካ፣ ባለቤትነቱ ማን የሆነ? የነማን ቤትና ቪላ? የዘመነኛ ነፍጠኞች፣ የአገዛዙ ሹሞችና የአገዛዙ አጨብጫቢ አረመኔ ከበርቴዎችና የአየር ባየር ሞጭላፎች ቪላና ህንፃ ለሕዝቡ ምኑ ነው? ለነገሩማ መንግሥት የሚባል ነገር’ኰ እንዲህ ዓይነት ተግባራት ሊያከናውን እንጅማ የማን ጐፈሬ ሊያበጥር ነው ሕዝቡ የሚቀጥረው?! የተሓህት/ወያነዎች ይህን ቢያደርጉ ኖሮስ ነን ብለው ከሚቦተሉክት አንፃር ደጋፊዎቻቸው ለምን ይደነቃሉ?! ለመሆኑ ይህ ሁሉ በዚያ ኋላ በቀረ የኢኰኖሚ አቅምም ሳይገደቡ ልዑል ራስ መንገሻ ሥዩምም ሕዝቡን እያስተባበሩ የፈጸሙት ተግባር እንደሆነ የተሓህት/ወያነ ጀሌዎች ያውቃሉ? በርግጥ ልዑሉ በዘመናቸው ያሠሩት ሁሉ ጠላት እንዳይጠቀምበት በሚል ፈሊጥ ተሓህት አፍርሶና ነቃቅሎ አጥፍቶታል፣ በፈንጅ ደረማምሶታል። ዛሬ ይህ መንደርተኛ ፋሺስት ቡድን ይህንን ትላንት ያወደመውን ቢተካ ምን ይገርማል? እላይ ቆንጠር ተደርጐ ለመግለጽ እንደተሞከረው የአብላጫው የትግራይ ሕዝብ ዓላማና የፋሺስቱ መንደርተኛ ቡድን ተሓህት/ወያነ ዓላማ ፈጽሞ ተቃራኒ ነው። ለማብራራት እንደተሞከረው የዚህ ፋሺስታዊ ቡድን ዋነኛው የተፅእኖ አካባቢ ምዕራባዊው እና ከፊል መሃል የትግራይ ክፍል ሲሆን በሌላው ክፍል እኩል የሆነ ተቀባይነትና ድጋፍ ለማግኘት ሳይችል እስከ የኢሠፓ ሥርዓት መፈረካከስ ዋዜማ ድረስ ለመቆየት ተገድዷል። በተጨማሪም እላይ ጠቆም እንደተደረገው የድርጅቱ አመራር በአብላጫው በአሽዓ (አክሱም፣ ሽሬ፣ ዓድዋ) ተወላጆችና በኤርትራዊያን የተሞላ ነበር፣ ነውም። ከእነዚህም አብዛኛዎቹ አፍቃሪዬ-ኤርትራ የሆኑ ለኢትዮጵያ አንድነት በጐ አመለካከት ያልነበራቸው (አሁንም የሌላቸው) ስለነበሩ ይህንን ዓላማ ይፃረሩ የነበሩትን እጅግ አብላጫው ከሌሎቹ የትግራይ ክፍሎች የሆኑትን አባሎቻቸውን ገና ከማለዳው በግልጽም በሥውርም አጥፍተዋቸዋል። ይህ ደግሞ በአብዛኛዎቹ የደቡብ፣ ምሥራቅ፣ ሰሜንና ከፊል መሃል ትግራይ ተወላጆች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሮ የኖረ በመሆኑ ድርጅቱ በአካባቢው ሚዛን የሚደፋ ተቀባይነት እንዳይኖረው ጋሬጣ ሆኖበት ዘልቋል፤ ምንም እንኳን በተለያዩ ምክንያቶች በተነጻጻሪ አነስተኛ የሆኑት የአካባቢው ተወላጆች ድርጅቱን የተቀላቀሉ ቢሆንም። ምክንያቶቹ በዋናነት የኢኰኖሚ ችግር፣ እላይ እንደተጠቀሰው ዓይነት የደህንነቱ መሥሪያ-ቤት የሠራው ዓይነት ጥፋት፣ በጦርነቱ መራዘም ምክንያት የወደፊት ሕይወት አስመልክቶ ተስፋ መቁረጥ፣ ዛሬም እንደሚታየው የምዕራቡ ዓለም የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ወደ ስደት ሲያመሩ ድርጅቱ በሚቆጣጠረው ክልል ሲያልፉ ለጠባብ ብሄረኛ ፕሮፓጋንዳ ተጋልጠው ግዳይ በመሆን፣ ወዘተ … ናቸው። የእነዚህ አካባቢዎች ሕዝብ እንደ ምዕራቡ እና ከፊል መሃሉ ድርጅቱን ሙሉ በሙሉ ባለመደገፉ በድርጅቱ ግምባር ቀደም መሪዎች ዘንድ ጥርስ ተንክሶበት ኖሮዋል። የድርጅቱ አመራር በአብዛኛው የምዕራብ ልጆች በመሆናቸው የበለጠ መደጋገፍና ግልጽ አድልዎም ይፈፅሙ ነበር። ለዚህም እንደ የጐላ ምሳሌ መለስ ዜናዊ ከግዳጅ ሲፈረጥጥ የተሰጠው ድርጅቱ በወቅቱ ይከተለው ከነበረው ደንብ ጋር የማይመጣጠን ቅጣት መጥቀስ ይቻላል። እንዲህ ዓይነቱ ተግባር የድርጅቱ አባሎች በሆኑት የሌሎች አካባቢዎች ተወላጆች ዘንድ የፈጠረው ቅሬታ በድርጅቱ ዘንድ ህንፍሽፍሽ በመባል ለሚታወቀው የውስጥ መታመስና ለገሚሶቹም ድርጁትን ጥለው ለመኮብለል ምክንያት እስከ መሆን በቅቷል። ዛሬም ቢሆን ይህ ሁኔታ ቀጥሎ ያለ ሲሆን ይህንን ለመረዳት የድርጅቱ ወታደራዊና የሲቭል መሪዎች የትውልድ አካባቢ መፈተሽ ይበቃል። ድርጅቱ በውስጠ-ድርጅት ሕይወቱ ብቻ ሳይሆን በአደባባይም በግልጽ የሚታይ አድልዎ እየፈፀመ ይገኛል። አድልዎው ጊዜያዊ ሳይሆን ከምዕራቡ ክፍል ውጭ ያለውን ሕዝብ ማንነት መለያ የሆኑ ጉዳዮችንም እስከነአካቴው ለመቀየር ያለመ ነው። ሌላኛው እንደ ምሳሌ መመልከት የሚቻለው በቋንቋ ረገድ እየተደረገ ያለው ዘመቻ ነው። በትግራይ ውስጥ የተለያዩ የትግርኛ ዘዬዎች (dialects) አሉ። ዓድዋ፣ አክሱምና ሽሬ አካባቢ የሚነገረው ትግርኛ አንድ ዓይነት ወይም በጣም ተቀራራቢ ሲሆን፤ የኽልተ-ኣውላዕሎና የዓጋመ አውራጃዎች ደግሞ አንድ ዓይነት ወይም በጣም ተቀራራቢ ነው። የእንደርታና የተምቤን ትግርኛ የተለየ ሲሆን ትንሽ ተቀራራቢነት አለው። የራያ ትግርኛ ደግሞ ራሱን የቻለ ነው። በእርግጥ በኩታ ገጠም አውራጃዎች ወይም አካባቢዎች የሚነገረው ትግርኛ ተቀራራቢነት ሊኖረው ይችላል። የሆነ ሆኖ ዓድዋ፣ አክሱምና ሽሬ አካባቢ የሚነገረው ትግርኛ ራያና እንደርታ ከሚነገረው ትግርኛ ይልቅ አንድ ዓይነት ነው ለማለት በሚያስደፍር ደርጃ ኤርትራ ውስጥ ከሚነገረው ትግርኛ ጋር ይመሳሰላል። እላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ዛሬም አብላጫው የመንደርተኛው ፋሺስታዊ ቡድን ተሓህት/ወያነ መሪዎች የምዕራቡ ክፍል ተወላጆች፣ የኤርትራ ተወላጆች እና የትውልድ ሃረጋቸው ከዚያው የሚመዘዙ ናቸው፤ እንደነ ዶ/ር አዲስ-ዓለም ባሌማ፣ ወ/ሮ ሮማን ገብረ-ሥላሴ (አቶ መለስ ደንቆሮ ብለው የሰየሙዋቸው መንፈሰ-ስንኩል)፣ … የመሳሰሉ እፍኝ የማይሞሉ ማፈሪያዎች ቢያስኰለኩሉም። ዛሬ የድርጅቱ መሪዎች ባላቸው የሌሎቹን አካባቢዎች ማንነት የመጥላት፣ የመናቅ፣ የማኰሰስና የማጥፋት ዓላማ መሠረት የሁሉም አካባቢ ልጆች በአስገዳጅ ከኤርትራ ጋር የሚመሳሰለውን የዓድዋ፣ አክሱምና ሽሬ ትግርኛ ዘዬ እንዲማሩ እያደረጉ ነው። ይህንን ደፍረው የሚቃወሙ የእነዚህ አካባቢ ተወላጆች በርክተውና ጐልተው አለመታየታቸው ደግሞ የበለጠ አስዛኝና አሳሳቢ ነው። ነገረ ግርምቢጥ ሆኖ አንዳንድ አወቅን መጠቅን የሚሉ የእነዚህ አካባቢ ተወላጆች ግለሰቦችም በነሱ ብሶ ይህንን ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ ነው የሚታየው። እሩቅ ሳንሄድ የአቶ አበበ ተክለ-ኃይማኖትን (ጆቤ) የአቶ ገብሩ አሥራትን መጽሓፍ የተቹበት ጽሑፍ ላይ የተጠቀሙት የትግርኛ ዓይነት መጥቀስ ይቻላል። አቶ አበበ ተክለ-ኃይማኖት ከርዕሱ አንስቶ የተጠቀሙበት ቋንቋ እራሳቸው የተወለዱበት አካባቢና የአፍመፍቻቸው የሆነውን፤ ያደጉበትን ዓይነት ትግርኛ ሳይሆን የአማቾቻቸው አካባቢ ዘዬን ነው (የአቶ አበበ ተክለ-ኃይማኖት ሚስት ወ/ሮ አስካለ የዓድዋ ተወላጅ መሆናቸው ልብ ይለዋል)። የተሓህት/ወያነ አፈቀላጤዎች ይህንን ማለት መከፋፈልና ዘር-ቆጠራ ነው ብለው ሊመፃደቁ የችላሉ። መልሱ አጭር ነው። እንዲህ ማለት በናንተ ቋንቋ ለመናገር ያህል ሳይሆን ዕውነቱን ለመግለጥ ነው። ሁሉም ባህሉና ቋንቋው ይከበርለት ከተባለ ኽልተ-ኣውላዕሎም፣ ራያና አዘቦም፣ እንደርታም፣ ተምቤንም፣ … የራሱ ቋንቋ ዘዬ፣ ልምድና ወግ፣ ወዘተ… ስላለው አክብሩለት ለማለት ነው። አንዳንድ የዞረባቸውና ማንነታቸው የሚያሳፍራቸው፣ የእነዚህ ማንነታቸው እንዲከስም እየተደረጉ ያሉት አካባቢዎች ተወላጆችና የትውልድ ሃረጋቸው እንደምንም ከኤርትራ ጋር ለማቆራኘት ፍዳቸውን የሚቆጥሩ እንጭጮች ይህንን ተሓህት/ወያነ የሌሎቹን እየተጫነ እያስፋፋው ያለውን የኤርትራ መሰል የምዕራብ ትግራይ ልሳን የውድብ ቋንቋ በማለት ሊያድበሰብሱትና ሊኳኩሉት ሲዳዳቸው ይታያል። የውድብ (የድርጅት) የሚባል ቋንቋ የለም። እንዲያሸንፍና ሌላውን እንዲያጠፋ እየተደገፈ ያለው ቋንቋ የኤርትራ-መሰሉ የምዕራብ ትግራይ ትግርኛ ነው። የነ አቶ መለስ፣ አቶ ስብሓት ነጋ፣ የአቶ ብርሃኔ ገብረ-ክርስቶስ፣ የአቶ በረከት ስምዖን፣ የአቶ ሳሞራ የኑስ፣ የአቶ ቴድሮስ ሓጐስ፣ ወዘተ ወላጆች ወይም ከወላጆቻቸው የአንዱ አገር ልሳን ነው። ኃቁ ይህ ነው። የኤርትራው ትግርኛ የበላይነት የማቀዳጀቱ ዘመቻ ተሓህት/ወያነ ብቻ ሳይሆን የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮም ሥራ ሆኖ ነው የሚገኘው። ሌላኛው የተሓህት/ወያነ መንደርተኝነት፣ ለምዕራቡ የትግራይ ክፍልና ለኤርትራ የሚያደላና የበለጠ የሚቆረቆር መሆን፣ መላው ትግራይን በዕኩል ዓይን እንደማይመለከት አስረጅ የሆነ አብይ ጉዳይ ሥልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ እንዴት የክፍለ-ሀገሩን ካርታ (map) እንደለዋወጠው ነው። ይህ ጉዳይ ከተሓህት/ወያነ የትግራይ ነፃ አውጭ ነኝ ባይነት ጋር ተያይዞ የሚነሳ ጉዳይ በመሆኑ፤ አንዳንድ ወገኖችም ከተሳሳተ መነሻ በመንደርደር ድርጅቱ መላ ትግራይን ዕኩል የሚያፈቅርና ታላቅ ትግራይን የመመስረት አጀንዳ ያለው አድርገው ስለሚቆጥሩ በሚገባ ሊብራራ የሚገባ ታላቅ ጥያቄ ነው። እላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው የትግራይ ሕዝብና የተሓህት/ወያነ ዓላማዎች ለየቅል ናቸው። ድርጅቱም የትግራይን ሕዝብ በመላ በእኩልነት ዓይን እንደማይመለከት እላይ ለመግለጽ ተሞክሯል። ተሓህት/ወያነ ለምዕራባዊው ክፍል የሚያደላ፣ ለሚወደው ለሚሳሳለት አካባቢ ጨምሮለትና (ይህ ራያን አይመለከትም፤ የተወሰደበት መሬት ከተጨመረለት ያነሰ ነው።) የሚጠላውንና ቂም የቋጠረበትን ግን ጐምዶ ጐማምዶ ያስቀረውን ትግራይን የመገንጠል አጀንዳው (ከኢትዮጵያ ገንጥሎ ከኤርትራ ጋር ለማዋሃድ) ያልቀየረ፣ የትግራይ ሕዝብ ስትራቴጂያዊ ጥቅሙ የሚያስከብርለትንና በዘመናት መስዋዕትነት የገነባውን ኢትዮጵያዊነቱን የሚገድል ድርጅት እንጂ ለትግራይ ጥቅምና ታላቅነት የሚጥር ድርጅት አይደለም። የተሓህት/ወያነ የትግራይ መውደድና ተቆርቋሪነት የሚገለጸውና እውን የሚሆነው በነባራዊው ዓለም ሳይሆን እውነቱን ማየት በተሳናቸው ተቃዋሚዎችና በያዘው ልቀቀው ዘፈንና በወርቅ ዘር አፍዝዝዝ አደንዝዝ ፕሮፓጋንዳ በታወሩ የዋኅን የክፍለ-ሀገሩ ተወላጆች ምናብ ውስጥ ነው። በነባራዊው ዓለም የምናየው እውነታ ግን የዚህ ተቃራኒ ነው። በመሠረቱ የተሓህት/ወያነ አመራር የትግራይን ሁሉንም አካባቢዎች እኩል ወይም በተመዛዛኝ ሁኔታ ያልወከለ፣ የክፍለ-ሀገሩን ሕዝብን በእኩል ዓይን የማያይ፣ ከብቅለቱም ጀምሮ በምዕራብ ትግራይ ተወላጆች የተሞላና ለዚያ የሚያደላ ሆኖ የተፈጠረ ስለሆነ ታላቅ ትግራይን የመፍጠር ዓላማ አልነበረውም፤ የለውምም። በርግጥ ግምባር ገድሊ ሓርነት ትግራይ (ግ.ገ.ሓ.ት. = tlf) የተባለው ተሓህት/ወያነ ያጠፋው ድርጅት እንዲህ ዓይነቱን ዓላማ ይዞ ተንቀሳቅሶ የነበረ በመሆኑ የተጫረውን ስሜት ለመሳብ አልሞ ሊሆን በሚችል ምክንያት ተሓህት/ወያነም እንዲያ የመሰለ ግን ጠበብ ያለ ካርታ ይዞ የተወሰነ መንገድ ተጉዟል። እውነተኛው አጀንዳውና ዓላማው ግን ሥልጣን በጨበጠ ጊዜ አሳይቷል። በእርግጥ ተሓህት/ወያነ ገና የቀረው ያልቋጨው ቁልፍ አጀንዳ አለ። ይህም ቢቻል እሱ የፈጠራትን የአሁንዋን ትግራይ በመላ ካልሆነ ደግሞ ምዕራባዊና ሰሜናዊ ክፍሏን ገንጥሎ ከኤርትራ ጋር የማጠቃለል አጀንዳ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እነ አቶ ስብሓት ነጋ ትግራይና የቀሩት የክፍለ-ሀገሩ ክፍሎች ታሪክና ግንኙነት አስመልክቶና ኤርትራን አስመልክቶ ፍንትው እያደረጉልን ያሉት አመለካከት ልብ ላለው ሰው ይህንን ጠቋሚ ነው። ’’የራስዋ እያረረባት የሰው ታማስላለች’’ አንዲሉ ለዜጐችዋ በቂ የትምህርት ተቋማትና ጥራት ያለው ትምህርት ማቅረብ ያልቻለችው ኢትዮጵያ ጠላታችን ነሽ ብለው ጡቷን ለነከስዋትና መገንጠልን መርጠው ለጠነጠንዋት የኤርትራው ክፍል ተወላጆች ሲሆን ጊዜ በርዋን በርግዳ ማምበሽበሽዋ አቶ መለስ የደሰኮሩልንም ሌላ ነገር አይደለም የሚያሳየን። አቶ መለስ ይህንን ሲነግሩን በብሽቅ ቀመር እርር-ድብን በሉ ለማለት ፈልገው ይሁን ወይም እንደ ድል ቆጥረዉት፤ ወይም ለእናታቸው የትውልድ አካባቢ ሰዎች ያላቸው የተለየ ፍቅር ሊያሳዩን ፈልገው ይሁን እምብዛም ሳይገደን ዓላማው ግን በኢትዮጵያዊያን ሃብት ኤርትራን በተማረ የሰው ኃይል (human capital) ለማጠናከር መሆኑን ማወቅ ይገባል። ከፍ ሲል ደግሞ ለመጪው የትግራይ-ትግርኚ ምሥረታ ቅድመ ዝግጅት ሊሆን እንደሚችል አለመጠርጠር የአእምሮ ስንኩልነት ነው። በአጭሩ ተሓህት/ወያነ ታላቅ ትግራይ የመመስረት ዓላማ የለውም። ተሓህት/ወያነ ለኤርትራ ካለው ፍቅር በቀር ይዞት የዘለቀ መሠረታዊ አስተሳሰብ የሌለው፣ ከግራ ጫፍ ወደ ቀኝ ጫፍ የሚንከላወስ፣ በየወንዙ ዳር አቋሙን የሚለዋውጥ የአየር-ባየር ፖለቲካ አራማጅ ስለሆነ እንዲህ ወይም እንዲያ አያደርግም ወይም ያደርጋል ማለት ቀላል ባይሆነም ቢያንስ እስካሁን እንዲህ ዓይነት ዓላማ የለውም። ተሓህት/ወያነ ታላቅ ትግራይን የመመሥረት ዓላማ ቢኖረው ኖሮ ሂሳብ ሳያወራርድ ተሯሩጦ ኤርትራን ባላስገነጠለ፣ በረጅም ዕቅዱና ህልሙ መሠረት ወደፊት ኢትዮጵያ ብትንትኗ ወጥቶ በትናንሽ መንግሥታት ስትተካ ትግራይ ወደ ባሕር ቅርበት እንዳይኖራት በማቀድና (ባሕሩ ያለው በምሥራቅ በኩል ስለሆነ!) በትግርኛ ተናጋሪው ሕዝብና በአፋር ሕዝብ መካከል የግጭት ጥንስስ እንዲሆን በማሰብ የቀድሞዋ ትግራይ ግማሽ ያህል የሆነውን የክፍለ-ሀገሩን ምሥራቃዊ፣ ሰሜናዊ-ምስራቅና ደቡባዊ-ምሥራቅ ክፍልን ቆርጦ ወደ አፋር ክልል ባላካተተ ነበር (ካርታ ቁ. 4, 5 እና 6 ይመልከቱ)። የተሓህት/ወያነ መሪዎች በምሥራቃዊ ትግራይ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጥላቻ፣ ፍርሃትና ንቀት የተደበላለቀበት ስሜትና አጀንዳ ይዘው ነው የሚጓዙት። የአቶ ስብሓት “እንደርታዎች ትልቅ ዳቦ እንጂ ትልቅ ሰው የላቸውም፣ እንደርታዎች ሙያተኛ ለማኞች ናቸው፣” ዓይነት ብልግና የተመላበት አነጋገር፤ የምዕራቡ ክፍል ተወላጅ የሆኑና የነሱ አሽከሮች እንደሚያላዝኑት እንደርታዎች፣ ዓጋመዎች፣ ራያዎች ምንም አልተዋጉምና የጠላት መሣሪያ ነበሩ፤ “ትግርኛ ዓድዋ ተወለደች፣ አክሱምና ሽሬ አደገች፣ ዓጋመና ተምቤን ታመመች፣ መቐለ ሞታ ራያ ተቀበረች፤” ወዘተ … የመሳሰሉ ብልግና የተመላባቸው የንቀት አነጋገሮች የተራው ዜጋ መረን የለቀቁ የመሸታ ቤት ቀልዶች ወይም መዘራጠጦች አይደሉም፤ የቱባ ቱባ የድርጅቱ መሪዎች እምነቶችና አመለካከቶች ናቸው። ድርጅቱ ደግሞ የሚመራው እንዲህ ዓይነት የዘቀጠ አሳፋሪና ኋላ ቀር አመለካከት የሚያመነጭ አእምሮ በተሸከሙና እንዲህ ዓይነት አቋም በሚያራምዱ ፋሺስቶች ነው። የተሓህት/ወያነ መሪዎች እንዲህ ዓይነት አመለካከት አንግበው ደግሞ እንዲህ ከሚንቁትና ከሚጠሉት ሕዝብ ጋር የሚያቆራኛቸውን ታላቅ ትግራይ ለመመስረት የሚነሱበት አሳማኝ ምክንያት የለም፤ እስስትን የሚያስንቀው ተለዋዋጭ ባህሪያቸው እንዳለ ሆኖ። ካርታ ቁጥር 4 ተሓህት/ወያነ ሥልጣን ከመቆጣጠሩ በፊት የነበረው የትግራይ እና ተጐራባች ክፍለ-ሀገሮች ክልል የሚያመለክት ሲሆን ከዚህ በታች የሚታየው ካርታ ቁጥር 5 ደግሞ ድርጅቱ የመንግሥትን ሥልጣን ወሮ ከያዘ በኋላ ያወጣው ነው። ካርታ ቁጥር 5 ድርጅቱ መጀመሪያ ቀርፆዓቸው ከነበሩት ሁለት ካርታዎች ፈጽሞ የተለየ ነው (በክፍል 1 ውስጥ እና ወረድ ብሎም በአባሪነት ከቀረቡት ካርታ ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 ጋር ያነጻጽሩ)። እንዲህ ዓይነቱ መገለባበጥ አንድም የድርጅቱን የመነሻና የመድረሻ አቋምና አምክንዮ አልባነት፣ አለያም ወንዝ በተሻገረ ቁጥር የሚጠቀምበት ተራ የማጭበርበር ዘዴ ከመሆን አልፎ ሌላ ምንም ነገር ሊሆን አይችልም። ተሓህት/ወያነ ሲመሠረት ፀረ-አማራ ጠባብ ብሄርተኛ ድርጅት፣ ሰንበት ብሎ ደግሞ የብሄር-ብሄረሰቦች መብት የተከበረባት ኢትዮጵያ እውን ለማድርግ የሚታገል አገራዊ ኃይል፤ አንዴ በማርክሳዊ-ሌኒናው ርዕዮተ-ዓለም የሚመራና ዓለም-አቀፋዊ ራዕይ ያለው (እሱ ነኝ እንደሚለው የትግራይ ብሄረተኘቱን ሳይለቅ) የዓለም የላብ አደሮች ትግል አካል፣ ከረምረም ብሎ ደግሞ የካፒታሊስት ሥርዓት አራማጅና የሥርዓቱ አፍሪካዊ ደቀ-መዝሙር፣ ሌላም ሌላም መሆኑን ላስተዋለ ይህ ድርጅት ከአየር ባየር ተራ የፖለቲካ አጭበርባሪነትና አቋም የለሽነት በቀር ሌላ ባህርይ ሊያይበት አይችልም። ተወደደም ተጠላም ተሓህት/ወያነ ከውልደቱ ጀምሮ ያልቀየረው አላማ ቢኖር ኤርትራ የተባለችን አገር መፍጠርና ጥቅሟን ማስጠበቅ ብቻ ነው። ተሓህት/ወያነ አገሪቱን ከመቆጣጠሩ በፊትና ከተቆጣጠረ በኋላ ያሉት ካርታዎች (ካርታ ቁጥር 4 እና 5) አንድ ላይ ተጣምረው ሲነጻጸሩ ተሓህት/ወያነ ምንን ከማንና ከየት ወስዶ ለማንና በየት በኩልስ እንደጨመረ በግልጽ ለመረዳት ይቻላል። ድርጅቱ በከበሮ አሳጅቦ የሚለፍፈውን ሳይሆን የሚያደርገውን ለማየትና ለማወቅ ለሚፍልጉ ይህ ተግባሩ ቢያንስ ቢያንስ የድርጅቱ አድላዊነት ለማን እንደሆነ ለመገንዘብና ዓላማውን ለማወቅ የሚያስችል መነጸር ነው (ካርታ ቁጥር 6 ይመልከቱ)። ከዚህ በታች በካርታ ቁጥር 6 ለማመልከት እንደተሞከረው በቁጥርና ፊደል ከተመለከቱት የትግራይ አውራጃዎች ቆርጦ ወደ አፋር ክልል ያካተተው በካርታው ላይ የተመለከቱት አውራጃዎች የቆዳ ስፋት አሁን ቀርቶ ካለው በእጅጉ የበለጠ ነው፤ ከዓጋም አውራጃ በቀር። ትክክለኛ ግምቱን ለካርታ ባለሞያዎች ትቶ የዓይን ግምት ቢሰጥ ከድሮዋ ትግራይ ግማሽ (50 %) ያህሉን ነው ተሓህት/ወያነ ወደ አፋር ክልል የሰደደው። ይህ የተደረገው ደግሞ ከዓድዋ፣ አክሱምና ሽሬ ሳይሆን ከዓጋመ፣ ከኽልተ-ኣውላዕሎ፣ ከእንደርታና ከራያና አዘቦ ነው። ከፊል ተምቤንን ጨምር እነዚህ አውራጃዎች ደግሞ ድርጅቱ በኢድኅ፣ በኢሕኣፓና በደርግ ደጋፊነት፤ ለትግሉ ምንም ወይም የረባ አስተዋፅዖ ባለማድረግ፣ በፀረ-ኤርትራነትና በመሳሰሉት ሌሎች የተለያዩ ምክንያቶች ቂም ቋጥሮባቸው የኖሩ አካባቢዎች ናቸው። እላይ ለማመልከት እንደተሞከረው የትሓህት/ወያነና የትግራይ ሕዝብ ዓላማ ሆድና ጀርባ ነው። የትግራይ ሕዝብ በአሁኑ ወቅት ጐልቶ በሚታይ ደርጃ ይህንን ፋሺስታዊ መንደርተኛ ቡድንን ሲቃወም አለመታየቱ በገሃድ የሚታይ ነገር ነው። ይህ ግን የትግራይን ሕዝብ ብቻ የሚመለከት ጉዳይ አይደለም። አፋሩን፣ ጉራጌውን፣ ኦሮሞውን፣ ሶማሌውን፣ አማራውን፣ ቤንሻንጉሉን፣ … በአጠቃላይ መላውን የአገሪቱን ሕዝብ የሚመለክት ነው። ከዚህ በላይ ደግሞ ይህ ጐሳ-በቀል ፋሺስታዊ አገዛዝ (ethno-fascist regime) ትግራይን ነጥሎና ከርችሞ ዘግቶ ከሌሎች ክፍሎች በተለያ ሁኔታ የሚገዛበት ሥርዓት ፈጥሯል። የትግራይ ሕዝብ በተሓህት/ወያነ፣ በሕዝብ ደኅንነት፣ በገበሬዎች ማኅበር፣ በወጣቶች ማኅበር፣ በሴቶች ማኅበር፣ በአካባቢ ህዝባዊ ሠራዊቶች፣ ከድርጅቱ ጦር በተቀነሱ ታጋይ-ነበሮችና በሌሎች መሰል መዋቅሮች እጅ-ተወርች ተቀፍድዶ ያለ ሕዝብ ነው። አገዛዙ ኢትዮጵያን በእስካሁን ታሪክዋ ዓይታው በማታውቅ የደኅንነት መዋቅርና (አንድ ለአምስትን አደረጃጀትን ልብ ይሉዋል) የመረጃ ሠራዊት ተብትቦ በመንፈሳዊ ሽብር አሸማቅቆ እየገዛ ያለ ለመሆኑ እሙን ቢሆንም የትግራይ ሁኔታ ግን ከዚህ እጅግ በጣም የከፋና የጠጠረ ነው። እንኳንስ በአገር ውስጥ በውጭ አገርም በተለያዩ ስብስቦች ለመተብተብ ድርጅቱ የሚሠራው ሥራና የዘረጋው መዋቅር ቀላል አይደለም። የትግራይ ተወላጆች እንደሌላው በንግድ ፈቃድ፣ በቤት ምሪትና በኮንደምንየም ዕደላ እየተሸነገሉ ሳይሆን አንድም ከሀዲ ትግሬ ተሰኝቶ ላለመነጠል ብለው ነው በድርጅቱ ዙርያ የተኰለኰሉት። ከዚያ ካለፈ ደግሞ እኛ ከሌለንና ከእኛ ጋር ካልወገንክ አማሮችና ነፍጠኞች ያጠፉሃል በሚል መንፈሳዊ ሽብር ተቀፍድደው ነው ከድርጅቱ ጐን የሚኰለኰሉት። ከዚህ በላይ ደግሞ የድርጅቱ የግል ንብረት ተደርጐ ስለ ተሸነሸነ ማንም የክልሉ ተወላጅ ተሓህት/ወያነ እንዲያስብ ከሚፈልገው ውጭ እንዲያስብ እንኳን አይፈቀድለትም። ትግራይ ውስጥ የክፍለ-ሀገሩ ተወላጅም ቢሆን ከድርጅቱ ሌላ ዝር እንዳይል ተደርጐ የተሸነሸነ በመሆኑ ትላንት አብርዋቸው በቆሰሉና በደሙ የትላንት ጓዶቻቸው የተለየ አመለካከት ስለያዙ ብቻ የሚፈጽሙባቸው አረመኔያዊ ተግባር መመልከቱ ይበቃል። ይህ ማመን የሚከብዳቸው ካሉ የችግሩን ሀሁ መገንዘብ እንዳልቻሉ መረዳት ይገባቸዋል። ምንም እንኳን አብላጫው የየትኛውም የትግራይ ክፍል ሕዝብ የተሓህት/ወያነን ዓላማ የማይደግፍ ቢሆንም አገዛዙ በሚያካሂድበት የስነ-ልቦና ዘመቻ ወዳጁንና ጠላቱን በመለየት ረገድ ብዥታ የለበትም ማለት ግን አይደለም። አገዛዙ ጐሳን ማእከል ባደረገ የግዛት ክፍፍልና ከፋፍለህ ግዛ ዘዴ በመጠቀም በሕዝቡ መካካል የመፈራራትን ንቃቃት ለመፍጠር ያደረገው ጥረት ቀላል አይደለም። እኛ ከሌለን አማሮች፣ ነፍጠኞች፣ የድሮው ሥርዓት ናፋቂዎች፣ የደርግ ርዝራዦች፣ ሻዕቢያ፣ ኦነግ፣ ወዘተ … ያጠፉሃል የሚለው ፕሮፓጋንዳ ዝም ብሎ አሸዋ ላይ እየፈሰሰ ነው ብሎ ማሰብ አስፈሪ ድንቁርና ነው። ይህ ጥረት ደግሞ የፈጠረው አደጋ የለም ማለት አይቻለም። በዝቅተኛ ደረጃም ቢሆን ጐሳዊ አመለካከት እንዲነሳሳና አጥንትና ሥጋ እንዲለብስ እየበቃ ነው። በተቃዋሚው ጐራ ውስጥ የተሰገሰጉ አንዳንድ ዋልጌዎችና የአገዛዙ ስውር መለእክተኞች የሚያሰሙት በትግራይ ሕዝብ ላይ ያነጣጠረ ዛቻና ማቅራራትም በአገዛዙ አፈቀላጤዎችና በየአዋቂ አጥፊ ድርጐኞቻቸው እየተጋነነ ለዚህ ማረጋጋጫና አቀጣጣይ ነዳጅ ሆኖ እያገለገለ ነው። የተቃዋሚው ጐራ ከእንደዚህ ዓይነት መተክላዊና ስልታዊ (strategic and tactical) ስህተት የጸዳ መሆን ይገባዋል። እላይ ለማብራራት እንደተሞከረው የትግራይ ሕዝብ ወዲህ፤ ተሓህት/ወያነና ሻዕቢያ ከነግሳንግስ ኹርኹሮቻቸው ደግሞ ወዲያ መሆናቸው ተገቢው ግንዛቤ አግኝቶ ሕዝቡን በዕኩልነት የተመለከተና በሙሉ ቅንነትና ኢትዮጵያዊ ፍቅር የሚያይ፣ ታጋሽነት የተመላበት አቋምና የትግል ስልት መከተል የዴሞክራሲያዊ ኃይሉ ይዋል ይደር የማይባል ሥራ ነው። ይህ ደግሞ የዴሞክራሲያዊ ትግሉ ዓቢይ ጥያቄ እንጂ የትግራይንም ሆነ የሌላውን የአገራችን ሕዝብ በተናጠል የሚመለከት ጉዳይ አይደለም። ስለዚህም ነው ዴሞክራሲያዊ የተቃዋሚ ኃይሉ ቆምና ሰከን ብሎ ወዳጅና ጠላትን በቅጡ መለዬት ዋነኛውና ቀዳሚው ግዴታው የሚሆነው። መላውን የአገሪቱ ሕዝብም ይህንን ጉዳይ በሚገባ ማየት እንዲችል ለማብቃት በብቃት መሥራት ያለበት። የሚሰምር ትግል ለማካሄድ ከማን ጋር ተጎዳኝቶ ማንን መታገል እንደሚገባ፤ ማን ጊዜያዊ ወዳጅ፣ ማንስ የዘለቄታ አጋር እንደሆነ መለየት የትግሉ ሀሁ ነው። ወዳጅንና ጠላትን አብጠርጥሮ ማወቅ ለትግሉ ስኬት ወሳኝ አስተዋጾ አለው። እነ ክህደቱን የመሳሰሉ ለወያነ ያደሩ ወይም፤ ቢያንስ ቢያንስ የማይጎረብጡት መጫኛዎች፤ መገለል ያለባቸው መዥገሮች ናቸው ሲባሉ አልሰማ ያሉት የከፈሉት ዋጋና በትግሉ ያደረሱት ጉዳት ለአፍታም ቢሆን ሊዘነጋ አይገባም። ከዚህ እሳቤ በመነሳት የሚከተሉትን ጥቂት ጥያቄዎች አንስቶ ተገቢ መልስ መስጠት ያስፈልጋል ብዬ አምናለሁ። የትግሉ ዓላማ ምንድነው? ጠላት ማን ነው፣ ለምንስ በጠላትነት ተፈረጀ? በትግሉ ውስጥ ተሳታፊ ነን የሚሉት ወገኖች እነማን ናቸው? ታጋይ ነን ከሚሉቱ ውስጥ ከጠላት ዓላማ ጋር የሚቃረን ግልጽ ዓላማ ያላቸው እነማን ናቸው? የፖለቲካ ሥራ-አጦችና ቀላዋጮች፣ የግል ዝና አስዳጆች? ጠጠር ያለ ነገር ሲያጋጥም ሸብረክ የሚሉ ልፍስፍሶች የሆኑትስ እነማን ናቸው? የሕዝቡ ዝግጁነትስ ምን ያህል ነው? ለምንስ ነው ሕዝቡ ታጋይ ነኝ ላለ ሁሉ ልቡን የሚሰጠው? እንደነዚህ የመሳሰሉ መሠረታዊ ጥያቄዎች ተገቢው መልስ ባላገኙበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ወደፊት ለመጓዝ መጣር አውድማ ማስኬድ ነው። የአውድማ በሬ መንዳት ነው። ከትግል ስልትና ወዳጅና ጠላት ከመለየቱ ሥራ ጋር ተዛምዶ ሊነሳ የሚችል ሌላ አንድ በጣም ወቅታዊ የሆነ ጥያቄ አለ፤ ለምንድን ነው የሆነ የፖለቲካ አጀንዳ ይዞ የሚታገል ድርጅት እያለ የተቀዳ እስኪመስል ድረስ ተመሳሳይ የሆነ መርሃ-ግብር ነድፎ ብቅ የሚል አዲስ ድርጅት የሚያስፈልገው? ከመብት ጥያቄ አኳያ ይህንን ማድረግ በመሠረቱ ስህተት ባይሆንም አገራችን በምትገኝበት የክፍፍል አደጋ ውስጥ ተሆኖ ግን ቅንጦት ብቻ ሳይሆን በእሳት መጫወት ነው። እየዬ ሲደላ ነውና ቢቆየንስ?!
98
ethiopia zare (ዓርብ ጥቅምት 28 ቀን 2001 ዓ.ም. november 7, 2008)፦ ሦስት ረዳት ኢንስፔክተሮችና ሁለት ኮንስታብሎችን ጨምሮ፣ አድራሻቸው እንደሚገልፀው 147 የቤንሻጉል ክልል ነዋሪዎች፤ በብሔረሰብ አንድ የኾነን ህዝብ በሞላ ወይም በከፊል ለማጥፋት በማሰብ የኦሮሞ ብሔረሰብ ተወላጅ በሆኑ አርሶ አደሮች ላይ ጉዳት በማድረስ የ98 ሰዎችን ህይወት አጥፍተዋል፣ የአካል ጉዳት አድርሰዋል፣ አንዲት ሴት ለ16 በመኾን አስገድደው ደፍረዋል፣ 300 የሚኾኑ ቤቶች አቃጥለዋል፣ በርካታ የቀንድና፣ የጋማ ከብቶችን፣ አልባሳትና እህል ዘርፈል ባላቸው ተከሳሾች ላይ የፌደራል ዓቃቤ ሕግ ክስ መሠረተ። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ተከፍቶ፣ በዳኛ አደም ኢብራሂም፣ በዳኛ አሰፋ አብርሃና በዳኛ ዘሪሁን ቦዳ እየታየ በሚገኘው የዓቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ፤ እንደሚያስረዳው በ147 ተከሳሾች ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ክሱም በአራት የተከፈለ ነው። በተከሳሾቹ ላይ የቀረበው አንደኛው ክስ እንደሚያስረዳው፤ ከ1ኛ እስከ 66ኛ ተራ ቁጥር የተዘረዘሩ 66 ተከሳሾች፤ ከ67ኛ እስከ 82ኛ፣ ከ97ኛ እስከ 147ኛ የተዘረዘሩ 67 ተከሳሾች፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ ተወላጅ በሆኑት አርሶ አደሮች ላይ አመፅ እንዲያነሳሱ በመቀስቀስ፣ በማደራጀትና በርካታ የጦር መሣሪያ በማከማቸትና በማስታጠቅ ከግንቦት 8 ቀን እስከ 23 ቀን 2000 ዓ.ም፣ በኦሮሚያና በቤንሻጉል ክልሎች አዋሳኝ በሆኑት ቦታዎች በአንገር ሸንኮራ፣ እንገዎች አንገር ሚጤ፣ ሳይዶልቻ፣ ሰኞ፣ ዲዲጋ ሆሮዎታ፣ ዶም ጠና አይዳ ቀበሌዎች ውስጥ፣ ሁሉም የጦር መሣሪያ ይዘው በመግባት፣ 105 የሚሆኑት ተከሳሾች የኦሮሞ ብሔረሰብ ተወላጅ በሆኑት አርሶ አደሮች ላይ አመፅ በማነሳሳት፣ ቁጥራቸው 98 በሆኑ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ ጎልማሶችና አረጋውያን ላይ የጦር መሣሪያ በመተኮስና በጦር በመውጋት፣ ሕይወታቸው እንዲያልፍ በማድረግና የአካል ጉዳት አድርሰዋል ሲል ዓቃቤ ሕግ የተከሳሾቹን ማንነት በዝርዝር ጠቅሶ ክስ አቅርቧል። በአንደኛው ክስ የተከሰሱትን ጨምሮ 36 ተከሳሾች፣ በሁለተኛ ክስ የተከሰሱ ሲሆን ግድያው በተፈፀመበት ዕለት ብዛታቸው 300 በሆኑ የሳር ክዳን ቤቶች ላይ እሳት በማቀጣጠል በውስጣቸው ካሉት በርካታ የቤት ቁሳቁሶች አልባሳት፣ ምግብና እህል ጋር በእሳት እንዲጋዩ በማድረጋቸው፣ … ክስ ማቅረቡን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ላይ አሥፍሯል። በሦስተኛው ክስ ከ110ኛ እስከ 125ኛ ያሉ ተከሳሾች ክስ የቀረበባቸው ሲሆን፣ በምሥራቅ ወለጋ ዞን በለሙ ወረዳ፣ ሳሲጋ ቀበሌ ውስጥ፣ ተከሳሾቹ፣ በአንደኛና በሁለተኛ ክስ የተጠቀሰባቸውን ሰው ገለውና ቤት አቃጥለው ሲያበቁ አንዲትን ሴት ወጣት በያዙት መሣሪያ በማስፈራራት እንዳትከላከል ካደረጓት በኋላ በመፈራረቅ ለ16 ግብረ ሥጋ ግንኙነት ፈጽመውባት ጤናዋ እንዲታወክ በማድረጋቸው፣ በግብረ አበርነት በፈፀሙት አስገድዶ መድፈር ወንጀል መከሰሳቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ላይ አሥፍሯል። በአራተኛው የዓቃቤ ሕግ ክስ ከ97ኛ እስከ 109ኛ እና ከ126 እስከ 147ኛ ያሉ 35 ተከሳሾች የጦር መሣሪያ ይዘው በመደራጀት፣ የህዝብን ፀጥታ አደጋ ላይ በሚጥል ጭካኔ የተሞላበት ኃይል ተጠቅመው የሠላማዊ አርሶ አደሮች ንብረት የሆኑ በርካታ የቀንድና የጋማ ከብቶችን፣ ቁሳቁሶችን፣ አልባሳትና እህል በመዝረፋቸው በአጠቃላይ በግብረ አበርነት በፈፀሙት ወንጀል ዓቃቤ ሕግ ክስ መሥርቶባቸዋል። ተከሳሾቹ በእስር ከሚገኙበት ዴዴሳ ማሠልጠኛ፣ ቃሊቲ በሚገኘው አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዛወሩ የተደረገ ሲሆን፣ ሰኞ ጥቅምት 24 ቀን 2001 ዓ.ም. በነበረው ቀጠሮ ከ147 እስረኞች 123ቱ ሲቀርቡ 23 እስረኞች ባለመቅረባቸው፣ ፖሊስ ተከታትሎ ይዞ እንዲያቀርብ ታዟል። ተከሳሾቹ መንግሥት ጠበቃ እንዲያቆምላቸው በመጠየቃቸው፤ የተከላካይ ጠበቆች ጽ/ቤት ለተከሳሾች ጠበቃ እንዲያቆም ታዞ፣ ለኅዳር 8 ቀን 2001 ዓ.ም. ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
99
ኽቡራት ኣሓትን ኣሕዋትን ብቀዳምነት ቅንያት ናጽነት ስለ ዝኾነ ንመላእ ህዝብና ዮሃና ንብል። ምስኡ ለጊቡ ድማ ሰማእታትና ዝዝከሩሉ ግዜ ስለ ዝኾነ፡ ንስድራ ሱዉኣት ሓዘና እናገለጽና ሱዉኣትና ዝሓደጉልና ሕድሪ ክሳብ ሎሚ ስለ ዘይተተግበረ መንፈስ ቓልሲ ኣሓዲስና ምስ ህዝብና ኮና ብፍትሒ ዲሞክራሲ ክነተግብሮ ቅሩብነትና ንገልጽ። ዲሞክራስያዊ ውድብ ብሄረ ብሌን ኤርትራ/ሆደ፡ ኣብ’ዚ ዝሓለፈ ግዜ ቀዳማይ ሚኒስተርን ፈጻሚት ስራሕ ናይ መንግስቲ ኢትዮጵያን (ኢሃወደግ) ንሃገሮም ብዙሕ ተስፋ ዝሃበ ዉሳኔታት ከሕልፉን ገለ ከኣ ብግብሪ ክሰርሑሉን ሪኢና። እዚ ዓይነት ተባዕ ፖሎቲካዊ ውሳኔታት ንሰላምን ዲሞክራስን ምዕባሌን ኣብ ዞባና ዳርጋ ኣብ ቀድማይ ቦታ ዝስራዕ ታሪኽ’ዩ። ንኹሉ ኣፍሪቓን ዓለማዊ ሰላም ዘርብሕ ስለ ዝኾነ ከኣ ንምጉሶም። ምስኡ ተአሳሲሩ ድማ ሰሉስ 5 ሰነ 2018 እቲ አብ መንጎ ኤርትራን ኢትዮጵያን ንዘሎ ናይ ዶብ ጎንጾ፡ብመሰረት ናይ አህጉራዊ ቤት-ፍርዲ ውሳኔ ብዘይ ቅድመ ኩነት ተቀቢልናዮ አብ ምትግባሩ ድማ ድልዋት ኢና ምባሎም ነቲ ዳርጋ 20 ዓመት ዝጸንሔ ናይ ጥፈኣት ደመና ዝቅንጥጥ አዋጅ ንሓድሽ ምዕባሌ ርሒብ አፍደገ ዝኸፍት መግለጺ ኢሂወደግ በአውንታ ተቀቢልናዮ አለና። መንግስቲኤርትራነዚ ብመንግስቲ ኢትዮጵያ ተውሲዱ ዘሎአውንታዊ ምዕብልና ተጠቒሙ፣ እቲ ንነውሕ ግዜ አብ ደውታ ዝጸንሔ ጉዳይዶብዘላቒሰላምንኽርክብ፡ አብ ዞባና ንዘሎ ተአፋፊ ኩነታት አብ ምህዳእ ብግዲኡ አውንታዊ መልሲ ክህብን ንህዝቢ ዘማእከለ ሰላም ክእምምን ንጹዉዕ። ኣብ መደምደምታ ድማ፡ ኩሎም ኤርትራዊ ፖለቲካዊውያንሓይልታትንበርጌሳውያንማሕበራትንከምኡ’ውንሰፊሕሓፋሽህዝብና ነዚ ንህዝብን ሃገርን ጅሆ ሕዙ ዘሎ አይ ሰላም አይ ኩናት ፖሊሲ መሊኡ ክስዓር ጸቅጢ አብ ልዕሊ ስርዓት ህግደፍ ሓቢሮም ከካይዱ ንላቦ። ምኽንያቱ ካብዚ ዘሎ አይ ሰላም አይ ኩናት ተጎዳአይ ቀንዲ ህዝቢ ኤርትራ ነሱ ባዕሉ ሰለዝኾነ፡ ነዚ ሰናይ አጋጣሚ`ዚ እዚ ተጠቂምና አብ ኤርትራ ሃገርና ምሉእ ሰላምን ደሞክራስን ክህሉ ሓቢርና ክንሰርሕ፡ዲሞክራስያዊ ውድብ ብሄረ ብሌን ኤርትራ/ሆደ፡ጻዊዒቱ የቅርብ።