Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet Duplicate
instruction
stringclasses
4 values
extractive_text
stringclasses
5 values
summary
stringclasses
5 values
Write a brief headline summarizing the article below.
ዚወባ በሜታን እ ኀ አ በሁለት ሜህ ስላሳ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ብሄራዊ ወባን ዚማጥፋት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ እንቅስቀሎ እዚተደሚገ መሆኑን ተገለጞ። ሚኒስትር ደኀታው ዶክተር ደሹጀ ዱጉማ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደሹጃ በሜታውን ለማጥፋት ዹሚደሹገው እንቅስቃሎ አካል በመሆኗ ዚወባ በሜታን እ ኀ አ በሁለት ሜህ ስላሳ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ብሄራዊ ወባን ዚማጥፋት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ በስድስት ክልሎቜ፣ ዞኖቜና ሁለት መቶ ስላሳ ዘጠኝ ወሚዳወቜ ወደ ስራ መግባትቱን ገልጞዋል። ባህር ዳር፡ ታሃሳስ ሃያ ሰባት ሁለት ሜህ አመተ ምህሚት አብመድ በኢትዮጵያ ባለፉት አመታት ዚወባ በሜታን በመኹላኹልና በመቆጣጠር ዙሪያ በተኹናወነው ተግባር ውጀቶቜ መመዝገባ቞ውን ዚጀና ሚኒስ቎ር አስታውቋል። ይሁን እንጅ በተለይ ኚኮሚናቫይሚስ ወሚርሜኝ መኚሰት ጋር ተያይዞ በተፈጠሩና በሌሎቜም አንዳንድ ቜግሮቜ ምክንያት ዚወባ ማጥፋት መለኪያወቜ አፈፃጾም ውጀት በሚጠበቀው ደሹጃ እዚተተገበሚ አለመሆኑን ጠቁመዋል። ኚወባ ማስወገድ ጋር በተያያዘ ዚሚታዩ ጠንካራ ጎኖቜ እንድሁም ቜግሮቜ ላይ በመመስሚት በቀጣይ ስድስት ወራት ትኩሚት ተሰጥተው መኹናወን ባለባ቞ው ተግባራት ላይ ዚስራ መመሪያ ተሰጥቷል ብለዋል።
ዚወባ በሜታን እ ኀ አ በሁለት ሜህ ስላሳ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ብሄራዊ ወባን ዚማጥፋት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ እንቅስቀሎ እዚተደሚገ መሆኑን ተገለጞ።
Create a short title for the given news content.
ጠቅላይ ሚንስር አብይ አህመድ ኹ አመት በፊት ዚኊሮሞ ነፃነት ግንባር ኩነግ ዚምእራብ እዝ መሪ በነበሹው ለገሰ ወጊ ላይ መንግስት ሊፈጜም አቅዶት ዹነበሹውን ጥቃት በተመለኹተ ለግንባሩ አመራር መሹጃ አቀብለው እንደነበሚ ግንባሩ ገለጞ። ዹኩነግ ጩር መሪ በትግላቜን እንቀጥላለን አለ ኩነግ በመግለጫው ህዝቡ አሁን ያለውን መንግስት ለኊሮሞ ፖለቲካ አድስ ነው በሚል ዚሚያቀርበውን ትቜት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀደም ሲል ለኩነግ ዚሰጡትን መሹጃ ለዚህ እንደምላሜ እዚተጠቀሙበት ሊሆን ይቜላል ብሎ እንደሚያምን ጠቅሷል። ኩነግ አሁን ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዚሆኑት አብይ አህመድ በወቅቱ ዚመንግስት ዚጞጥታ ሃይሎቜ ለገሰ ወጊ ዚተባለውን ዚግንባሩ ጩር መሪን ለመግደል ክትትል እዚተደሚገ መሆኑን መሹጃ እንደሰጡት አምኖፀ ነገር ግን በወቅቱ በመሹጃው መሰሚት ለገሰ ወጊ ኚጥቃቱ እራሱን እንድያድን በአመራሩ ቢነገሚውም እሱ ግን ዚእራሱን ውሳኔ መውሰዱን መግለጫው ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በተደጋጋሚ ዹለገሰን ግድያና ኹኩነግ ጋር ዚነበራ቞ውን ግንኙነት ማንሳታ቞ው ለትግሉ አስተዋጜኊ እንደነበራ቞ው ዚሚያሳይ ቢሆንም ሌላ ዚሚያመለክተው ነገር አለ ብለው አቶ ሚካኀል ያምናሉ ለለገሰ መገደል በእኛ በኩል ጉድለት እንዳለ ለማስመሰልና አላስፈላጊ ጥርጣሬ ህብሚተሰቡ ውስጥ ሊፈጥር ይቜላል ይላሉ። በደኖ ዚሚባል ቊታን ሹግጹው አላውቅም አቶ ሌንጮ ለታ አቶ ሚካኀል አክለውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምን ስለለገሰ ብቻ ያነሳሉ በማለት ጠይቀው አገር ዚሚያስተዳድር መንግስት ለሹጅም አመታት በግንባሩ አባላት ላይ ጥቃት ሲያካሂድ እንደቆዚና አሁንም በዚህ ወቅት ጥቃቱ እንዳልቆመ ይናገራሉ። ለገሰ ወጊ ኩነግ አርብ ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳመለኚተው ዹአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስት ኚጥቃቱ ቀደም ብለው በግንባሩ ዹጩር መሪ ላይ ሊፈጾም ስለታቀደው ጥቃት መሹጃ በውጭ ለሚገኙት አመራሮቜ መስጠታ቞ውን አሚጋግጧል። ኊሮሞ እና አማራን ዚሚነጣጥሉ አይሳካላ቞ውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰሞኑን ኹኹፍተኛ አመራሮቜ ጋር በመሆን በተለያዩ ዚአገሪቱ አካባቢወቜ ተኚስቶ ዚሰባ ስምንት ሰወቜን ህይወት ዹቀጠፈውን ጥቃትና ግጭት ለማሚጋጋት ኚህዝብ ጋር ውይይት ባካሄዱበት ወቅት መቀመጫውን ኀርትራ አድርጎ ኹነበሹው ኩነግ ጋር ስለነበራ቞ው ግንኙነት ጠቅሰው እንደነበር ተሳታፊወቜ ተናግሚዋል። ዚግንባሩ መግለጫ ኹዚህ በተጚማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚኢንፎርሜሜን መሚብ ደህንነት ኀጀንሲ ውስጥ ሲሰሩ በነበሩበት ወቅት መንግስት በምእራብ ዚአገሪቱ ክፍል ሲንቀሳቀስ በነበሹው ዹኩነግ ቡድን ላይ ዘመቻ ሊያካሂድ እንደነበሚ መናገራ቞ውን ይገልፃል። ሲያጠቃልሉም ኹዚህ በፊት ለገሰን በተመለኹተ ስላደሚጉት ነገር ኚሚናገሩ ይልቅ ዛሬ ስልጣን በእጃ቞ው እያለና ዹኩነግ አመራር አድስ አበባ ውስጥ ባለበት ጊዜፀ ዛሬ ኚዚያ ዹበለጠ መስራት ይቻላል ብለዋል። ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ ጜህፈት ቀት በኊሮሞ ነፃነት ግንባር መግለጫ ላይ ስለተጠቀሰው ጉዳይ እስካሁን ያለው ነገር ዚለም።
ኚአስር አመት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ መሹጃ አቀብለውት እንደነበር ኩነግ ገለጾ
Provide a news headline based on the following text.
ዚኮሮና ወሚርሜኝ ለሙስና ወንጀል ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ተነገሚመንግስት በተለያዩ ሁኔታወቜ በሙስና ወንጀል ዚተመዘበሩ ሃብቶቜን ለማስመለስ ጥሚት እያደሚገ ቢሆንም፣ እስካሁን በተደሹገ ጥናት በአገር ውስጥና በውጭ አገሮቜ ተደብቆ ዹሚገኝ ኚአንድ መቶ ስላሳ ቢሊዮን ብር በላይ ሃብት እንዳለ ተጠቆመ። ምክትል ዳይሬክተሩ ስለቀጣይ አስር አመታት እቅድ አፈፃጾምና በሁለት ሜህ በጀት አመት ዚስራ እቅድ እንዳብራሩት፣ በማስሚጃ አለመሟላት ምክንያት በርካታ ዹተኹማቾ መዛግብት ላይ ማስሚጃወቜን በማሟላት ውሳኔ እንደሚያሰጡ፣ ለምርመራ በሚል ተመላሜ ዹተደሹጉ መዛግብትን ኚመኚታተል ባለፈ፣ በኚባድና ውስብስብ ወንጀሎቜ ምርመራ ላይ በቀጥታ እንደሚሳተፉ ማቀዳ቞ውን አስሚድተዋል። ዚኊድት ስራ ዚሚሰሩ አካላት በመደበኛነት ኚሚሰሩ ኊድት ውጭ ኹወንጀል ምርመራ ጋር ዚተያያዙ ኊድቶቜን በአፋጣኝ ሰርቶ ለመላክ ውስንነት እንዳለባ቞ው ጠቁመው፣ ጥፋተኛውን በግልጜ ኚማሳዚት አንፃር ጉድለት እንደሚታይባ቞ውና በሰሩት ኊድት ላይ ምስክርነት ሲጠዚቁ ፈቃደኛ ለመሆን ተግዳሮቶቜ እዚገጠማ቞ው መሆኑንም አስሚድተዋል። በሁለት ሜህ በጀት አመት ዚስራ አፈፃጾም ኚሰባት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ዹተመዘበሹ ሃብት ማስመለስ መቻሉን፣ በተለያዩ ወንጀሎቜ ዚተመዘበሩ ሃብቶቜን ዚሚያስመልስ ዳይሬክቶሬት በማቋቋም፣ በአገር ውስጥ ዹተደበቁና ወደ ውጭ አገሮቜ ዚሞሹ ሃብቶቜን በተመለኹተ ዚማጥናት እና አገሪቱን ዚመለዚት ስራ እዚተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። ዳይሬክቶሬቱ ዚተለያዩ ተግዳሮቶቜ እንደገጠሙት ዹጠቆሙ ምክትል ዳይሬክተሩ፣ ማስሚጃወቜን ኚሚመለኚታ቞ው አካላት በተገቢው ፍጥነት ለማግኘት አለመቻሉ፣ በማስሚጃወቜ ላይ ተጚማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣ አግባብነት ዹሌላቾው ማስሚጃወቜን መስጠት፣ ሙስና ዚሚፈጞምባ቞ው ተቋማት ቢኖሩም ዚሚመለኚታ቞ው አካላት ሪፖርት አለማድሚጋ቞ውን ጠቁመዋል። ኹፍተኛ ዚህዝብና ዚመንግስት ጥቅም ያላ቞ው ትልልቅ ዚሙስና ወንጀል ጉዳዮቜን ኚምርመራ ጀምሮ ቅድሚያና ልዩ ትኩሚት ሰጥተው እንደሚሰሩ፣ በዋና ኊድተር ዚኊድት ስራ ዚተሰራባ቞ው ዚመንግስት መስሪያ ቀቶቜና ዩኒቚርሲቲወቜ ጋር በተያያዘ ያልተወራሚደ ሂሳብ እንድወራሚድና በህግ ዹመጠቀም ተግባር በስፋት እንደሚኚናወን መታቀዱን ምክትል ዳይሬክተሩ ገልጞዋል። ምንም እንኳን እንድህ አይነት ተግባራት ያሉ ቢሆንም፣ በሌላ በኩል ደግሞ ባለፉት ሁለት አመታት በአገሪቱ ያለውን አለመሚጋጋት በመጠቀም ዚሙስና ሁኔታ በተደራጀ መልኩ እዚተፈጞመ መሆኑን ጠቁመዋል። በሙስና ወንጀል ዹተመዘበሹ ሃብትን ኚማስመለስ አንፃር ጥሚቶቜ እዚተደሚጉ ቢሆንም፣ በወንጀሉ ዹተገኘውን በአገር ውስጥና በውጭ አገሮቜ ተደብቆ ዹሚገኝን ኚአንድ መቶ ስላሳ ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ማስመለስ አለመቻሉንም ጠቁመዋል። ኚመሬት ወሚራ፣ ኚባንክ ገንዘብ ማጭበርበር፣ ሃሰተኛ ሰነዶቜን ኹመጠቀምና ህገወጥ ገንዘብን ህጋዊ አስመስሎ ኚማቅሚብ ጋር በተያያዘ፣ ዚሙስና ወንጀሎቜ በስፋት እዚጚመሩ መምጣታ቞ውን ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። ዚኊድት ተቋማት ዚተሚጋገጡ ጥፋቶቜን ለሚመለኹተው አካል ማሳወቅ፣ ዚህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ተጠያቂነትን ኚማሚጋገጥ አንፃር አስፈፃሚ ተቋማት ላይ ተጜእኖ መፍጠር፣ እንባ ጠባቂ ተቋም ደግሞ ኹበደል ጋር በተያያዘ በትብብር መስራት፣ ጾሹ ሙስና ኮሚሜን ዚስነ ምግባር ትምህርቶቜን አጠናቅሮ በመስጠትና ሚድወቜም ዚምርመራ ጋዜጠኝነት ስራ በማናወን ሙስናን እንድያጋልጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ አንድ መቶ ስላሳ ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ
Generate a news headline for the following article.
አድስ አበባ ፣ መስኚሚም ፣ ሁለት ሜህ ኀፍ ቢ ሲ ዚሃሚሪ ክልላዊ መንግስት ለመላው ዚክርስትና እምነት ተኚታዮቜ እንኳን ለደመራና ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደሚሳቜሁ እያለ ዚመልካም ምኞት መልእክት አስተላለፈ። ህዝበ ክርስትያኑ ዚደመራ በአል አኚባበር እሎቱን ጠብቆ እንድኚበር በማድሚግ ዚተ቞ገሩ ወገኖቜን በማብላትና ዚተጠሙትን በማጠጣት እንድሁም ዹተለመደ ዹመተዛዘንና ዚመሚዳዳት ባህሉን በመተግበር በአሉን እንድያኚብር ጥሪውን አቅርቧል። በተያያዘም ህዝበ ክርስትያኑን ጚምሮ መላው ዹክልሉ ነዋሪ ሰላምን፣ አብሮነትን፣ መተባበርንና ወንድማማቜነት በማጎልበት እንድሁም በክልሉ ዚተጀመሩ ሁሉን አቀፍ ዚልማት ተግባራት እንድጠናኚሩ ድጋፋን እንድያጠናክርም መልእክት አስተላልፏል። ዚመስቀል በአል ለሹጅም ጊዜ ዚተራራቁ ዚቀተሰብ አባላት እና ወዳጅ ዘመዳሞቜ ዚሚገናኙበት፣ ዚተጣሉ ዚሚታሚቁበት፣ ዚተ቞ገሩ ወገኖቜ ዚሚደገፉበት፣ አድስ ጎጆ ዚሚመሰሚትበት እና ሌሎቜ ማህበራዊ ኩነቶቜ ዚሚኚወኑበት ታላቅ በአልም ነው ብሏል በመልእክቱ። በርካታ ህዝብ በታደመበት ዹሚኹበሹው ዚደመራ በአል አኚባበር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዚትምህርትና ዚባህል ተቋም ዩኔስኮ መመዝገቡን አስታውሷል። በአሉም ዚሰላም፣ ዚአንድነት፣ ዚመተሳሰብ፣ ዚደስታና ዹፍቅር እንድሆን ኚልብ ይመኛል።
ዚሃሚሪ ክልል ህዝበ ክርስቲያኑ ዹመተዛዘንና ዚመሚዳዳት ባህሉን በመተግበር በአሉን እንድያኚብር ጥሪ አቀሹበ
Create a short title for the given news content.
ኢትዮጵያ በቀይ ባህርና በህንድ ውቅያኖስ መካኚል ዚባህር ሃይል ጩር ሰፈር ልትገነባ መሆኑን ዚመኚላኚያ ምክትል ጠቅላይ ኢታማዊር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ። ኢትዮጵያ እስካሁን ዹቀይ ባህርን ለሞቀጥ ማጓጓዣ ብቻ ስትጠቀምበት ነው ዚኖሚቜው ያሉት ጀነራሉፀ ይህ ሁኔታ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ይቀዚራልፀ በቀይ ባህር ላይ ዚራሷ ዚባህር ሃይል ይኖራታል ብለዋል። ሶማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ፑንትላንድና ኀርትራን ጚምሮ በርካታ አገሮቜ ዚባህር ሃይል ጩር ሰፈር ለመገንባት መዘጋጀታ቞ውን ዚጠቆሙት ጀነራሉፀ ኢትዮጵያ ዚባህር በር ባይኖራትም ዚግደታ ዚባህር ሃይል ጩር ያስፈልጋታልፀ ይህን እውን ለማድሚግም እዚተንቀሳቀስን ነው ብለዋል። በቀይ ባህር ላይ ዚባህር ሃይል መገንባቱ ሃገሪቱ በአካባቢው ላይ ያላትን ስትራ቎ጅካዊ ጥቅሞቜ ለማስጠበቅና ራሷን ኚሚቃጡባት ዹውጭ ጥቃቶቜ ለመኹላኹል በእጅጉ አጋዥ መሆኑንም ጀነራሉ ገልጞዋል። አሁን ዚሚገነባው ዚባህር ሃይል አለም ዚደሚሰበትን ዘመናዊ ቮክኖሎጅ ሙሉ ለሙሉ ያሟላ፣ በእጅጉ ዹዘመነና ዚአንድ መቶ ሚሊዮን ህዝብ ሃያል ሃገር መሆኗን ዚሚያሳይ ይሆናል ተብሏል። ዚባህር ሃይል ጩር ሰፈሩ ዚሚገነባው ኹቀይ ባህር ዳርቻ ወደ ውስጥ ስልሳ ኪ ሜትር ገብቶ በውሃው አካል ላይ ይሆናል ተብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ኹዚህ ቀደም ዚኢትዮጵያን ዚባህር ሃይል እንደገና ዹማቋቋም ውጥን እንዳላ቞ው መግለፃቾው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ዳርቻ ዚባህር ሃይሏን ልታቋቁም ነው ለማስጠበቅና ራሷን
README.md exists but content is empty.
Downloads last month
5