id
stringlengths 4
5
| url
stringlengths 31
537
| title
stringlengths 1
65
| text
stringlengths 183
241k
|
|---|---|---|---|
22874
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8E%E1%88%BD
|
ጎሽ
|
ጎሽ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ አጥቢ እንስሳ ነው።
የእንስሳው ሳይንሳዊ ጸባይ
«ጎሽ» የተባለው በደንብ የአፍሪካ እንስሳ () ሲሆን፣ የሚከተሉት ኗሪ ዝርያዎች ደግሞ «ጎሽ» ይባላሉ፦
የእስያ ጎሽ ወገን (
የእስያ ጎሽ - ሕንድና ደቡብ-ምሥራቅ እስያ
የውሃ ጎሽ - የእስያ ጎሽ ለማዳ
የሚንዶሮ ድንክ ጎሽ - በአንድ የፊልፒንስ ደሴት
የደጋ አኖዋ እና የቆላ አኖዋ (ወይም የሱላዌሲ ድንክ ጎሽ) - በአንድ የኢንዶኔሲያ ደሴት ብቻ
የስሜን አሜሪካ ጎሽ ወገን (
የስሜን አሜሪካ ጎሽ
የአውሮፓ ጎሽ
የአፍሪካ ጎሽ ወይም ዝም ብሎ ጎሽ ወገን አንዱ ዝርያ ብቻ ሲሆን () የተለያዩ ንዑስ-ዝርዮች አሉ፦
ደቡባዊ ሳርማ ጎሽ
የደን ጎሽ
ሱዳናዊ ጎሽ
የአባይ ጎሽ
የተራራ ጎሽ
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር እና ብዛቱ
የእንስሳው ጥቅም
የኢትዮጵያ አጥቢ እንስሳት
የቶራ አስተኔ
|
32446
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%BD%E1%88%9B%E1%8C%8D%E1%88%8C%E1%8B%8E%E1%89%BD%20%E1%8C%A8%E1%8B%8B%E1%89%B3
|
የሽማግሌዎች ጨዋታ
|
የሽማግሌዎች ጨዋታ
ሁለት የተወሰነ የእድሜ ልዩነት ያላቸው ሽማግሌዎች ስላሳለፉት የቀደሞ ህይዎታቸው እየተጫወቱ ሳለ በእድሜ አነስ የሚለው ሽማግሌ ጥቂት ለሚበልጠው ሽማግሌ በህይወት ዘመንህ ተመኝተህው የተሳካልህ ነገር አለ? ብሎ ይጠይቀዋል በእድሜ ከፍ ያለው ሽማግሌም ሲመልስ አዎ አለ በልጂነቴ ጥፋት አጥፍቸ እናቴ ጸጉሬን ስትይዘኝ በጣም ስለሚያመኝ ምነው መላጣ በሆንኩ እል ነበር ይሄው አሁን ተሳክቶልኛል አለ ይባላል።
|
18645
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%88%AB%E1%8B%B5%E1%8D%8E%E1%88%AD%E1%8B%B5
|
ብራድፎርድ
|
ብራድፎርድ (እንግሊዝኛ: ) በሰሜን እንግሊዝ፣ ብራድፎርድ ከተማ እምብርት ላይ ትገኛለች። ህዝብ በብዛት ከሚኖርባቸው የእንግሊዝ ከተሞች አንዱ ነው። ይህ ከተማ በእ.አ.አ. 1847 በመዋቅር ተይዞ ከ27 ዓመት በኋላ በ1874 የከተማነትን ማዕረግ አግኝቷል።
ጥበብ እና ዲዛይን
ሙዚየም እና ስብስቦች
ስነ ህንፃ
ምግብ እና መጠጥ
ሳይንስ እና ግኝቶች
እህት ከተሞች
የውጭ ማያያዣ
የእንግሊዝ ከተሞች
|
49448
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B6%E1%88%AA%E1%8A%96%20%E1%8D%88%E1%88%AD%E1%8B%96%E1%8A%96%E1%89%BD%20%E1%8B%9D%E1%88%AD%E1%8B%9D%E1%88%AD
|
የቶሪኖ ፈርዖኖች ዝርዝር
|
የቶሪኖ ፈርዖኖች ዝርዝር ወይም በተለመደ የቶሪኖ ቀኖና ምናልባት 1250 ዓክልበ. ያሕል የተቀነባበረ የጥንታዊ ግብጽ ፈርዖኖች ዝርዝር ፓፒሩስ ነው። አሁን በቶሪኖ፣ ጣልያን ሙዚየም ይቆያል።
ፓፒሩሱ በግብጽኛ በሂየራቲክ (የተያያዘ ግብጽ ሃይሮግሊፍ ጽሕፈት) በሌላ ሰነድ ጀርባ ላይ ተጽፈው ነበር። በ1812 ዓም ጣልያናዊ ተጓዥ ቤርናዲኖ ድሮቨቲ ፓፒሩሱን በሉክሶር ጤቤስ አገኘው። ፓፒሩሱ ግን በ1816 ዓም በቶሪኖ ሙዚየም በደረሰበት ጊዜ፣ ተሰባብሮ ብዙ ትንንሽ ቁራጮችና ክፍሎች ሆኖ ነበር። ቁራጮችና ክፍሎች በትክክል ለመሰብሰብ ከባድ እንቆቅልሽ ሆነ፣ ስለ መረጃው አይነተኛነት ግን ብዙ መምህሮች ጣሩበት። ከተዘረዘሩት ስሞች ከግማሽ በላይ በፍርስራሽ ጠፍተዋል፤ የቀረው መረጃ ግን ለግብጽ ታሪክ ቀድም-ተከትል ትልቅ ሚና አጫወተ።
ከዚህ በታች ዘመናዊ ምሁራን እንደሚያስቡት እስከሚቻል ድረስ የዝርዝሩን ይዞታ ያሳያል። ሌሎችም መፍትሄዎች ሊገኙ ይቻላል። መጀመርያ 2.5 ዓምዶች የአፈታሪካዊ ወይም ቅድመ-ታሪካዊ አለቆች እንደ ዘረዘሩ ይታስባል። አሁን የጠፋ መጨረሻ 12ኛ ዓምድ እስከ 1250 ዓክልበ. ድረስ እንደ ቀጠለ ይታስባል።
የሊቃውንት አዲስ ትርጉም
ጥንታዊ ግብፅ
የነገሥታት ዝርዝሮች
|
8361
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B1%20%E1%88%88%E1%88%9B
|
መንግስቱ ለማ
|
መንግሥቱ ለማ በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም።
መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል።
መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ"ን ደርሷል:: ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል።
መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል።
መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው።
የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
|
2772
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9E%E1%8A%95%E1%8C%8E%E1%88%8D%E1%8A%9B
|
ሞንጎልኛ
|
ሞንጎልኛ ከሞንጎሊክ ቋንቋ ቤተሠብ ሁሉ የታወቀውና ለአብዛኛው የሞንጎልያ ኗሪዎች ዋና ቋንቋ እንዲሁም የሞንጎልያ መደበኛ ቋንቋ ነው። ደግሞ በአካባቢው ባሉት የሩሲያና የቻይና አውራጃዎች ውስጥ ሲናገር የሩሲያ ክፍላገር ቡርያትያ እና የቻይና ክፍላገር ውስጣዊ ሞንጎልያ መደበኛ ቋንቋ እሱ ነው። በሞንጎልያ ውስጥ ካሉት ተናጋሪዎች ብዙኃን የሓልሓ ቀበሌኛ ይናገራሉ። በቻይናም ዋናው ቀበሌኛ ቻሃር ይባላል።
አንዳንድ ሊቃውንት ሞንጎልኛን ለቱርክ ምናልባትም ለጃፓንኛ ለኮሪይኛም ዝምድና እንዳለው ይቆጠሩታል። እርግጥ የተዛመደ ቋንቋ በሩሲያ የተገኘው ካልሙክኛ ነው። በሞንጎልያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ተናጋሪዎች ሲኖሩ በአገሮቹ ሁሉ በጠቅላላ 5.7 ሚልዮን ያሕል ይችሉታል።
ባሕላዊ የሆነው የሞንጎል ፊደል በ12ኛ ምዕተ አመት ከሶግዲያን ፊደል በኡይጉር ሕዝብ አማካይነት ወጣ። እስከ ዛሬ ድረስ በቻይና ውስጥ ሞንጎልኛ ለመጻፍ የሚጠቀመው ጽሕፈት እሱ ነው። በሞንጎልያ ግን በ1935 ዓ.ም. ይህ ባሕላዊ ጽሕፈት በቂርሎስ አልፋቤት ተተካ። ከዚህ በላይ በቻይና በኦይራት ሕዝብ ዘንድ ቶዶ ጽሕፈት በተሰየመ በሌላ አይነት ባሕላዊ ፊደል ነው ቋንቋቸው የሚጻፈው።
|
22880
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%88%8D%E1%8D%88%E1%88%8D
|
ፍልፈል
|
ፈልፈል ምድር ውስጥ የሚቆፈር አጥቢ እንስሳ ነው።
የእንስሳው ሳይንሳዊ ጸባይ
ፍልፈል መሰል በምድር ውስጥ የሚቆፈር አጥቢ እንስሳ ከአንድ ጊዜ በላይ ተፈጠረ። እነዚህ «እውነተኛ ፍልፈሎች» የተባሉት በስሜን አሜሪካ፣ እስያና አውሮፓ ይገኛሉ፤ በትድግ ክፍለመደብ ውስጥ መሆናቸውም ታውቋል።
በተጨማሪ እነዚህ ሌሎች ፍጡሮች ወደ ምድር ውስጥ ቆፍረው በመኖራቸው ሰውነታቸው ልክ እንደ ዕውነተኛው ፍልፈል መስሏል፦
ወርቃማ ፍልፈል - በደቡባዊ አፍሪካ የሚገን፤ የርሱ የወርቃማ ፍልፍል ክፍለመደብ ከአሽኮኮ፣ አዋልደጌሳና ዝሆን ጋር አንድላይ በአንድ ላእለ-ክፍለመደብ ውስጥ ናቸው።
ኪሴ ፍልፈል - በአውስትራልያ የሚገኝ፤ የርሱ የኪሴ ፍልፈል ክፍለመደብ ከሌሎች ኪሴ እንስሳት እንደ ካንጋሮ ጋር ይመደባሉ።
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር እና ብዛቱ
የእንስሳው ጥቅም
አጥቢ እንስሳት
የዱር አራዊት
|
53925
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9A%E1%8A%95%E1%8C%8A
|
ሚንጊ
|
ሚንጊ ማለት በደቡባዊው የኢትዮጲያ ክፍል በተለይም በኦሞ ወንዝ አካባቢ ኑሯቸውን ባደረጉ የኦሞ እና የሀመር ህዝቦች የሚዘወተር ባህላዊ ልማድ ነው። በባህሉ መሰረት ሚንጊ ናቸው ተብለው የተፈረጁ ልጆች ንጹህ እንዳይደሉ እና በማህበረሰቡም ላይም እርግማን ያመጣሉ ተብሎ ይታሰባል። ከዚህም የተነሳ የተለያዩ እርምጃዎች ህጻናቱ ላይ ይደርስባቸዋል። አንድ ህጻን ሚንጊ ነው የሚባለው ከታችኛው ጥርሱ ቀድሞ የላይኛው ጥርሱ ከበቀለ፣ ልጆቹ መንታ ሆነው ከተወለዱ እንዲሁም ከጋብቻ ውጪ የተወለዱ ልጆች ሲሆኑ ነው። ሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምሮች እንደሚያሳዩት የህጻን ልጆች ጥርስ የአንዳንዱ የላይኛው ቀድሞ ሲበቅል የአንዳንዱ ደግሞ ታችኛው ቀድሞ ይበቅላል። ይህም በልጆቹ ጤንነት ላይ የሚያሳድረው ምንም አይነት አሉታዊ ተጽዕኖ የለም። መንታ ልጅ መውለድም ቢሆን እርግማን አይደለም።
የጎሳ መሪ የሆኑ ሰዎች በአካባቢያቸው ሚንጊ የሆነው ልጅ እንዳለ ካወቁ ቶሎ ብለው መጥተው ልጁን ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ወይም ወንዝ በመወርወር ፣ አፉ ውስጥ ብዙ አፈር በመጨመር እንዲሁም ህጻኑን ጫካ ውስጥ በመጣል ህይወቱ እንዲያልፍ ያደርጋሉ። በዚህ ባህል እጅግ በጣም ለዉጥር የሚታክቱ ብዙ ህጻናት ተሰውተዋል። ሚንጊ ናቸው ተብለው ከሚፈረጁት ህጻናት ባለፈ የአካል ጉዳተኛ ሆነው የሚወለዱ ወይም ከተወለዱ በኋላ በለጋ እድሜያቸው የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ህጻናትም ይሄው እጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ የሚሞቱ ህጻናት ስርዓቱን የጠበቀ የቀብር ስነ ስርዓት እንኳን አይደረግላቸውም። ሚንጊ እንደሆኑ እንደታወቀ የጎሳው መሪ አካላት ወደ ቤታቸው በመሄድ ህጻናቱን ከእናታቸው እጅ ነጥቀው በመውሰድ ህይወታቸው እንዲያልፍ ያደርጋሉ።
መቼ እና እንዴት ተጀመረ?
ይሄ ባህል መቼ እና እንዴት እንደተጀመረ በውል የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ነገር ግን በተለያየ ምክኒያት ለአካባቢው ማህበረሰብ ጥንክሮ በመስራት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ ማይችሉትን ለመቀነስ ታስቦ የተጀመረ ባህል እንደሆነ አንዳንዶች መላ ምታቸውን ያስቀምጣሉ። ከዚህ መላ ምት ያለፈ የተጻፈ እና የተሰነደ ስለ ባህሉ ታሪካዊ አመጣጥ የሚገልጽ የታሪክ መዝገብ የለም።
ሆኖም ግን ለረዥም ጊዜያት ሲተገበር እንደኖረ ግልጽ ነው። በዚህ ባህል ምንም የማያውቁ ህጻናት ገና ምንም ሳያውቁ እርግማን ታመጣላችሁ በሚል ሰበብ ህይወታቸው እንዲያልፍ ይደረጋል። እናቶችም ለዘጠኝ ወራት በሆዳቸው ተሸክመው፣ በብዙ ስቃይ አምጠው ወልደው፣ አጥብተው ያሳደጉትን ልጅ የጎሳቸው መሪዎች በጉልበት ነጥቀው ወስደው አይናቸው እያየ በሚዘገንን ሁኔታ ጭካኔ በተሞላው መንገድ ሲሞቱ ማየት ቀላል ነገር ሊሆንላቸው አይችልም። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ከፍተኛ የሆነ የሞራል ጉዳት እና ስብራት ይደርስባቸዋል። ሆኖም ባህሉ እጅግ ስር የሰደደ እና በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ ስለሆነ ልጃቸውን በእምባ ከመሸኘት በስተቀር አማራጭ የላቸውም።
እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ቀመር ከ1936 - 1947 ዓ.ም ባለው ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጲያ የኔ ግዛት ናት ባለችበት ወቅት በምስራቅ አፍሪካ የኢጣሊያ ግዛት ናቸው በተባሉ ቦታዎች ሁሉ ላይ መሰል ድርጊቶች እንዳይደረጉ አግዳ ነበር። በዚህ መቀትም ሚንጊ ናቸው ብሎ ልጆችን መፈረጅ እና ህይወታቸው እንዲያልፍ ማድረግ እንደ ትልቅ ወንጀል ይቆጠር እና ያስቀጣ ነበር። ከብዙ አመታት በኋላም በ2012 ዓ.ም የካሮ ህዝቦች ሚንጊ የሚለው ባህል መቀረት እንዳለበት ስምምነት አድርገው ነበር። ሆኖም ይሄው ስምምነት በተፈለገው ደረጃ መሬት ላይ ሊወርድ አልቻለም ነበር። አሁን ድረስም ከ680,000 ያላነሱ የማህበረሰቡ አካላት ይህንኑ ጎጂ የሆነ ባህል እንደሚተግብሩት ይታወቃል።
የማስቆም ሂደት
ላሌ ላቡኮ የተባለ የካሮ ጎሳ ተወላጅ ገና የአስራ አምስት አመት ልጅ እያለ ሚንጊ ነው ተብሎ በማህበረሰቡ የተወገዘ ህጻን ልጅ ሲገደል በማየቱ እጅግ በጣም አዝኖ ነበር። ላሌ ከዚህ ፣አህበርሰብ ከተገኙ ሰዎች መካከል በሚሽነሪ ትምህርት ቤቶች የመማር እድል ያገኘ ልጅ ነበር። ካደገ በኋላም እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም አንዲት ህጻን ወላጆቿ በትዳር ሳይጣመሩ የወለዷት በመሆኗ ብቻ ልትገደ እያለ የሚችለውን ሁሉ በማድረግ ህይወቷን ያተረፋል። ከዚህም በኋላ ቀስ በቀስ እንደዚህ ሚንጊ የተባሉ ልጆችን ከሞት በማትረፍ እና ወደ ከተማ በመወሰድ ለህጻንቱ የሚሆን መጠለያ ስፍራ በማዘጋጀት ያሳድጋቸው ጀመር። ይሄ በጎ ስራውም ቀስ በቀስ እየተሰማ ሄዶ የዚህን ህዝብ ታሪክ እና የእርሱን መልካም ስራ የሚዘክሩ ሁለት ዶክመንታሪዎች ተሰርተዋል። የመጀመሪያው የሚል እና በ2012 የተሰራ ሲሆን ከዚህ በመቀጠልም በ2015 ዓ.ም ጆን ሮው () በሚባል እውቅ ፊልም ፕሮዲዩሰር አማካኝነት የሚል ዶክመንታሪ ተሰርቶ ለእይታ በቅቷል። ዶክመንታሪዎቹም ሽልማትን አግኝተው ነበር። ከጊዜያት በኋላም ላሌ ከፕሮዲዩሰሩ ጋር በመሆን የኦሞ ልጆች ድርጅትን ከፍተው ህጻናትን ከሞት ለማትረፍ እየሰሩ ይገኛሉ። በ ር አጋዥነት ለዚሁ አላማ በተሰራ መጠለያ ቤት ውስጥም ወደ 50 የሚደርሱ እድሜያቸው ከ 1 እስከ 11 የሆነ የእድሜ ክልልየሚገኙ ህጻናት ከሚንጊ ሞት ተርፈው ይኖራሉ።
|
17754
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%8B%B5%E1%8B%8B%20%E1%8C%A6%E1%88%AD%E1%8A%90%E1%89%B5
|
የአድዋ ጦርነት
|
የአድዋ ጦርነት በየካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ.ም. በኢትዮጵያና ኢጣሊያ መካከል የተካሄደ ውጊያ ሲሆን የአንደኛው የኢትዮጵያና ጣሊያን ጦርነት ክፍል ነው። በ ኢትዮጵያ አሸናፊነት የጣልያን የቀኝ ግዛት ማስፋፋት ተኮላሸ።
ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ጊዜ አበሻ፤
ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ
መድፍ አገላባጭ ብቻለብቻ፤
የአድዋ ሥላሴን ጠላት አረከሰው
ገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሰው፤
የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብር ማኅተም፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል ነው፡፡ የመላው ዓለም ተፈጥሮአዊ ግብር እና ሰብአዊ ክብር የታደሠው፤ በእውነትና በፍትህ ህልውናና ምልዓት ላይ የተሰካ ትልቅ ጥርስ የተነቀለው … በአድዋ የታላቅ ህዝቦች ታላቅ ድል ነው፡፡
ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ስንሄድ 1066 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታላቁ ጦርነት የተደረገበትና ታላቁ ድል የተገኘበት ሥፍራ አድዋ ከተማና የከተማው ግድም ገመገሞች ይገኛሉ፡፡ በኢትዮጵያውያን አቡሻኽር () የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም፤ ወይም በአውሮጳውያን የዘመን አቆጣጠር ( (የካቲት) መጨረሻ እና (መጋቢት) መጀመሪያ ላይ 1896. ለጦርነቱ መነሻ የሆነው ውል የተፈፀመው በዚሁ ዘመን ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 468 ኪሎ ሜትር ርቀት ግድም ከውጫሌ ከተማ ግርጌ ከአምባሰል ተራራ ሥር ወሎ ውስጥ ንጉሥ ይስማ እየተባለ በሚጠራ ሥፍራ ነው፡፡
ሸልዶ ተራራ ወይም (ሶሎዳ ተራራ)፤ ማርያም ሸዊቶ፤ አዲ ተቡን፤ ረቢ አርእየኒ (እግዚሃር አሳየኝ)… በመሠኘት የሚታወቁት እነዚህ ገመገሞችና ተራራማ ሥፍራዎች ዋነኞቹ የጦር ግንባሮች ናቸው፡፡ በመቶ ሺህ የሚሠላ የኢትዮጵያ ገበሬ ሠራዊት ከአንድ ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የአውሮጳ ቅኝ ገዢ ወራሪዎችን ድባቅ ከመታና ረግጦ ካስወጣ በኋላ ከምሽቱ አራት ሰዓት ግድም (የካቲት 23 ቀን) እንዳማርያም ላይ ተሰባስቦ በአንድ እግሩ ቆሞ ቀኙን (ድሉን) ለሰጠው አምላክ ምሥጋና አቅርቧል፡፡ አባት ሆይ፤ ንቀውን የመጡ የአገራችንን ድንበርና ልዕልና የደፈሩ የአውሮጳ ኮሎኒያሊስት ወራሪዎችን እንድናሸንፍ (ድል እንድናደርግ) ስለረዳኸን እናመሰግንሃለን ...
ሃያ ዘጠኝ ሺህ ፈረሰኞችን ጨምሮ ከመቶ ሺህ እስከ መቶ ሃያ ሺህ የሚገመት አንድ ሺህ ኪሎ ሜትር በባዶ እግሩ የተጓዘ የኢትዮጵያ የገበሬ ሠራዊት በወታደራዊ አካዳሚ የሠለጠነውን የአውሮጳ ወራሪ ጦር የካቲት 23 ማለዳ አሥራ አንድ ሰዓት ግድም ገጥሞ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ማሸነፉን አረጋግጧል ይለናል የታሪክ ተመራማሪው ጆርጅ በርክሌይ የአድዋ ጦርነትና ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ በተሰኘና ዳኘው ኃይለሥላሴ ወደ አማርኛ በተረጐሙት መጽሐፉ ላይ፡፡ የኢትዮጵያ ገበሬ ሠራዊት ፈረሱ ላይ ሆኖ የጋሻውን እምብርት መሬት ላይ እያጠቀሰ ጐራዴውን አየር ውስጥ እየቀዘፈ ባበደ መንፈስ (በተቆጣና በቆረጠ መንፈሥ) በጀግንነት ተዋግቷል፡፡
ጦርነቱ በተጀመረ ከአምስት ሰዓት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ሃምሣ ስድስቱም የኢጣሊያ መድፎች ሙሉ ለሙሉ ተማርከዋል፤ የቅኝ ገዢውን ወራሪ ሠራዊት ከመሩት ጀኔራሎች ጄኔራል አልቤርቶኒ ሲማረክ የሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጄኔራል ባራቴሪ ከጥቂት አጃቢዎቹና በሽንፈት ከተበታተኑ የኢጣሊያ ወታደሮች ጋር ሸሽቷል፡፡
በዚህ ድብልቅልቅ ያለ ውጊያ ከሃምሣ ስድስቱ የኢጣሊያ መድፎች በተጨማሪ ብዙ ሺህ ቀላልና ከባድ መትረየሶች እንዲሁም የነፍስ ወከፍ ጠመንጃዎች በአሥር ሺሆችና በመቶ ሺዎች ከሚቆጠሩ መሰል ጥይቶቻቸው ጋር ተማርከዋል፡፡ በአጠቃላይ ምርኮው ወደ አዲስ አበባ የተጓጓዘው በአምስት መቶ አጋሰሶች ተጭኖ ነው፡፡
በማግስቱ የካቲት 24 ቀን 1888 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ የኢጣሊያ ምርኮኞች በምኒሊክ ድንኳን ፊት ሲያልፉ የኢትዮጵያ ጀግና የገበሬ ሠራዊት እየፎከረ እየሸለለ አሳልፉዋቸዋል፡፡ ጄኔራል አልቤርቶኒ በምርኮኛነት ኢትዮጵያ ውስጥ ቆይቶ አገሩ ከተመለሰ በኋላ በፃፈው መጽሐፍ ላይ ከሚፎክሩት ጥቁር የነፃነት ተዋጊዎች መሃከል አንዱ እንደ እኛው ነጭ አውሮጳዊ ነው ብሎአል፡፡ ይህ ሰው ከፈረንሣይ አገር ወደ ኢትዮጵያ ለጦር መሣሪያ ጥገና የመጣ ካፒቴን ኦርዲናንስ ሲሆን፤ አሁን ጊዜው የጦርነት ስለሆነ ወደ አገርህ ተመለስ ቢባል ቢሠራ አሻፈረኝ ብሎ ከእኛ ጋር አድዋ ድረስ የዘመተ ነው፡፡
ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት ላይ ከተዋጋችባቸው የጦር መሣሪያዎች ሠማንያ ሺህ የሚሆኑት አሮጌ ጠመንጃዎች የተገዙት ከፈረንሳይ አገር በምሥጢር ነው፡፡ ጠመንጃዎቹን ገዝተው ወደ ኢትዮጵያ ያስገቡት ለመጀመሪያ ጊዜ መኪና ወደ ኢትዮጵያ ያስገቡት በሥጋ በደምና በትውልድ አርመናዊ በነፍስና በመንፈስ በዜግነትና በልብ ፍቅር ኢትዮጵያዊ የሆኑት የኢትዮጵያ የልብ ወዳጅ ሰርኪስ ቴሪዝያን ናቸው፡፡
አሁን በመዲናችን የሚገኘው የአርሾ ላቦራቶሪ ባለቤትና በዓለም ላይ ኢትዮጵያን የመሰለ ውብ አገር የለም ያሉኝ ዶክተር አርሻቪር ቴሪዝያን ኢትዮጵያ ውስጥ አርመናዊ ትውልድ ኖሮት ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌለው (ኢትዮጵያዊ ያልሆነ) አርመን ያለመኖሩን ያጫወቱኝ ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት ነው፡፡ የሠማንያ ሺህ ጠመንጃዎቹን አገዛዝ ሁናቴ የሚያውቁት ደግሞ ከአርሾ ቀደም የሚሉትና ከአሥራ ስድስት ዓመታት በፊት ለሪፖርተር ጋዜጣ ይሄንኑ በአንደበታቸው የገለፁት አቬዲስ ቴሪዝያን ናቸው፡፡ ሠርኪስ ቴሪዝያን ጠመንጃዎቹን ከገዙ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ያስገቡት በጅቡቲ በኩል ነፋስ ባህሩን ሲያነሳና እንደ ግድግዳ ሲያቆም በዚያ ተፈጥሮአዊ ክንውን በመጠቀም ደብቀውና ሸሽገው ነው፡፡
የአድዋ ድል ለመጀመሪያ ጊዜ የተከበረው በሠባተኛ ዓመቱ በ1895 ዓ.ም (እ.ኤ.አ በ1903) ከአንድ መቶ ዘጠኝ ዓመታት በፊት አሁን ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ያለበት ሥፍራ ምኒሊክ አደባባይ ነው፡፡ በክብረ በዓሉ (በድል በዓሉ) ላይ ዲፕሎማቶችና የውጪ አገር መንግሥታት ተወካዮች አርበኞች የመንግስት ባለሥልጣኖች ብዙ ሺህ ፈረሰኞችና ሥፍር ቁጥር (ወፈ ሠማይ የሆኑ) ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ መገኘታቸውን፤ ከፈረሰኞቹ ብዛት የተነሳ ፀሐይ በአቧራ እስከመጋረድ መድረሷን ጳውሎስ ኞኞ የኢጣሊያና የኢትዮጵያ ጦርነት በተሰኘ መጽሐፉ ላይ ጽፎአል፡፡ እንዲሁም ተክለፃዲቅ መኩሪያን የመሳሰሉ ኢትዮጵያውያን የታሪክ ተመራማሪዎችና የውጪ አገር ዜግነት ያላቸው ፀሐፍትና ተመራማሪዎች በተለያዩ መፃሕፍቶቻቸው ይሄንን አሣምረው ጽፈውታል፡፡
ታላቁ የጥቁር ህዝቦች ድል (የአድዋ ድል) በመላው ዓለም ፖለቲካ ላይ ከፍተኛና ዋነኛ ለውጦች አምጥቶአል፡፡ የእንግሊዝ ጋዜጦች በአድዋ ድል ማግስት የዓለም ታሪክ ተገለበጠ ታላቅ የትውልድ ኃይል በአፍሪቃ ተቀሰቀሰ … ብለው ፃፉ፡፡ በኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ፡- ዘመናዊት ኢትዮጵያን የፈጠረ የተባሉት ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክ በሌሉበት (እርሳቸው በአካል ባልተገኙበት የነፃነት ተጋድሎ መሪዎች ጉባኤ) የአፍሪቃና የመላው ዓለም ጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ መሪ ተደርገው ተመረጡ፡፡
ጦርነቱ ከመደረጉ በፊት እ.ኤ.አ በ1880ዎቹ መጀመሪያ ጀርመን አገር በርሊን ከተማ ላይ በተደረገው የአውሮጳ ቅኝ ገዢ (ኮሎኒያሊስት) መንግስታት ሥልጣናትና ልሂቃን የጦር ጄኔራሎችና ሊቃውንት ስብሰባ ላይ ጥቁር ትልቅ ትል ነው ቅንቡርስ ነው እንጂ ነፍስ ያለው ሰው አይደለም ብለው የነበሩ አፈሩ፤ እውነትና ፍትህ ኢትዮጵያና አፍሪቃ ከበሩ፡፡ ከሲግመንድ ፍሮይድ የሳይኮ አናላይሲስ ጥናትና ምርምር በፊት፡- ጥቁር ህዝብ ትልቅ ትል ላይሆን ነፍስ ያለው ሰው ከሰውም ሰው ጀግና መሆኑን በተጨባጭ ያስመሰከረ የኢትዮጵያ ገበሬ ሠራዊት ነው፡፡
ከፈረንጅ የአውሮጳ መንግሥታት ሩሲያና ፈረንሳይ የአድዋን ድል ከልብ ደገፉ፡፡ ጀኔራል ባራቴሪ በአገሩ በኢጣሊያ ጦር ፍርድ ቤት ቀርቦ ማዕረጉ ተገፈፈ፡፡ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲኞር ክሪስፒ በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ፡፡
የኢጣሊያዊው ንጉሥ አማኑኤል ኡምቤርቶ የልደት ቀን የሀዘን ቀን እንዲሆን ተወሰነ፡፡ ሮማ (ሮም)ን ፍሎሬንስን ሚላኖ (ሚላን)ን ቬነስን…የመሳሰሉ የኢጣሊያ ከተሞች ምኒሊክ ለዘላለም ይኑር በሚሉ የተቆጡ አውሮጳውያን ትዕይንተ ህዝብ አድራጊዎች ተጥለቀለቁ፡፡ ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት ወቅት በዋናው የጦር ግንባር ገጥማ በፍልሚያ ድል ማድረግ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በአራት መስክ ሠለጠነች በምትባለው አውሮጳዊት አገር ኢጣሊያ ላይ ድል ተቀዳጅታለች፡፡ ይኸውም፡- በጦርነት እና በወታደራዊ መረጃ ()፤ በዲፕሎማሲና በፖለቲካ ጥበብ ነው፡፡
በፖለቲካ ጥበብ በኢጣሊያ ቅኝ ገዢ ብልጣብልጥ የመንግሥት ሥልጣን ላይ ድል የተቀዳጀችው ገና ጦርነቱ ሳይጀመር ለጦርነቱ መጀመር መነሻ የሆነው የውጫሌ ውል በተደረገበት ሥፍራ ነው፡፡
የውጫሌ ውል አንቀጽ አሥራ ሰባት የጣሊያንኛው፡- ኢትዮጵያ ከአውሮጳ መንግሥታት ጋር ማድረግ የምትፈልገውን ግንኙነት በኢጣሊያ መንግስት በኩል ማድረግ አለባት ሲል፤ አማርኛው ደግሞ ኢትዮጵያ ከአውሮጳ መንግሥታት ጋር ማድረግ የምትፈልገውን ግንኙነት በኢጣሊያ መንግሥት በኩል ማድረግ ትችላለች ይላል፡፡
የአማርኛው የኢትዮጵያን ሉአላዊነትና ልዕልና ያከብራል፤ የጣሊያንኛው የኢትዮጵያን ሉአላዊነትና ልዕልና መድፈር ብቻ ሳይሆን ብሔራዊ ክብሯንና ጥቅሟን ይነካል፡፡ ይሄን የተገነዘቡት የኢትዮጵያ መሪዎች የውሉ አንቀጽ አሥራ ሰባት የጣሊያንኛ ትርጓሜ የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም በማይነካና ሉአላዊነቷን በሚያከብር መልኩ እንዲስተካከል በተደጋጋሚ ወተወቱ፡፡ መወትወቱ ውጤት ሳያመጣ ቢቀር፤ ምኒሊክ፡- መዘግየት አደገኛ ነው ጣይቱ አሉ፤ ስለዚህ ጉዞ ወደ ወሳኙ ጦርነት (ማድረግ) የግድ ነበር፡፡
የኢትዮጵያን አገራዊ ክብርና ጥቅም ህልውናና ልዕልና ሲሆን ሲሆን በውድ ካልሆነ ደግሞ ሳይወድ በግድ ማስከበርና ማስጠበቅ የአንድ አገር መንግሥት ዋነኛ ግዴታና ኃላፊነት ነው፡፡
ስለዚህ አባቶቻችን (የጥንት ወላጆቻችን) ውትወታቸው አልሰማ ቢል ጦር እንግጠም አሉ፡፡
ይሄ የፖለቲካ ጥበብ ብልጫ ወይም ድል ነው፡፡
በወታደራዊ መረጃ () ብልጫ የኢንቲጮ ተወላጅ በሆኑት ባሻዬ አውአሎም ሀረጐት አማካይነት ኢትዮጵያ ሠለጠነ የተባለውን የአውሮጳ ኃይል አሸንፋ ጣሊያኖች ባልፈለጉት ቦታና ባልመረጡት ጊዜ ወደ ጦርነት እንዲገቡ አድርጋለች፡፡
በወታደራዊ ሣይንስ () አገባብ ለጦርነት የተንቀሳቀሰ አንድ ሠራዊት ወዲያውኑ ወደ ጦር ግንባር መግባት አለበት፡- ይሄ አንድ ነጥብ ነው፡፡ ሌላው ነጥብ አንድ ለግዳጅ የተንቀሣቀሠ ሠራዊት ለመሰናዶም ሆነ ለመከላከል ውጊያ በአንድ የመከላከያ ወረዳ ከሠፈረ በዚያ መከላከያ ወረዳ ከስድስት ወራት በላይ መቆየት የለበትም፡፡ በአንድ ቦታ ላይ ከስድስት ወራት በላይ ከቆየ ሊደርስ የሚችል የወታደራዊ ሥነልቦና () ጉዳት አለ፡፡ የመሸገበትን የመከላከያ ወረዳ እየተለመማመደ ሲሄድ ስለሚዘናጋና የውጊያ ስሜቱ እየቀነሰ (እየቀዘቀዘ) ስለሚመጣ ጉዳት አለው፡፡ ከሎጂስቲክ አኳያ የውጊያ ዝግጁነቱም አደጋ ላይ ስለሚወድቅ (በሌላ አነጋገር ስንቅ እየጨረሰ ስለሚሄድ) በነዚህ ምክንያቶች በአፋጣኝ ወደ ጦርነት መግባት ለሠራዊቱ ድል አድራጊነት ትልቅ ጥቅም አለው፡፡
የኢትዮጵያ በሠላም ጊዜ ገበሬ በጦርነት ጊዜ ጀግና ተዋጊ እንጂ ዘመናዊ ወታደራዊ መሠረት ያለው ባልነበራት በዚያ ዘመን ለአንድ መቶ ሃያ ሺህ ሠራዊት የሎጂስቲክ አገልግሎት እየሰጡ ለረጅም ጊዜ መቆየት አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ የጀግንነት ግለት ሳይበርድ የሎጂስቲክ (ስንቅ ትጥቅ መድሃኒት) አቅም ሳይዳከም በፍጥነት ጦር መግጠም እጅግ አስፈላጊ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ሠራዊት ጦርነቱን ፈጥኖ ለመግጠም ጣሊያኖች ወደ አድዋ መምጣት አለባቸው፤ ወይም ደግሞ የእኛ ሠራዊት ጣሊያኖች ወደመሸጉበት የኤርትራ ከፍተኛ ቦታዎች መሄድ አለበት፡፡ ከነዚህ ሁለት ሁኔታዎች የአንደኛው መሆን የግድ ነበር፡፡ ወደ ጣሊያኖች መሄድ ከፖለቲካ ሁኔታዎች ባሻገር ከወታደራዊ ሳይንስ አንፃር የሚመረጥ አይደለም፡፡ በምሽግ ውስጥ ሆኖ የሚከላከል ሠራዊትና ከምሽግ ወጥቶ የሚያጠቃ ሠራዊት መስዋዕትነት የመክፈል ዕድሉ እኩል አይደለም፤ ለሚከላከል አንድ ወታደር ሶስት የሚያጠቃ ወታደር ነው የሚያስፈልገው፡፡
ስለዚህ ጣሊያኖች ወደ አድዋ እንዲመጡ ማድረግ የግድ ሆነና የአድዋ ድል ቁልፍ የምላቸው የአርባ ዓመቱ ጐልማሣ ባሻዬ አውአሎም ሀረጐት ተጠሩና ለአንድ ታላቅ አገራዊ ኃላፊነት እንዲሠናዱ ተደረገ፡፡ ይሄ ሁሉ በምሥጢር ነው የተከወነው፡፡ በሚቀጥሉት ቀናት አውአሎም ለኢጣሊያ ኮሎኒያሊስት ወራሪዎች ከሚሠልሉ የአገር ተወላጆች (ፌርማቶሪዎች) ጋር ወደ ባራቴሪ ተላኩ፡፡ ከመሄዳቸው በፊት ስንቅ ማለቁና ተስቦ በሽታ በሠራዊቱ ውስጥ መግባቱ ፌርማቶሪዎች ባሉበት ተለፈፈ፡፡ አውአሎምና ፌርማቶሪዎቹ ወደ ኤርትራ ዘልቀው ለጄነራል ባራቴሪ ይሄንኑ ነገሩት፡፡
ባራቴሪ ጊዜው አሁን ነው አለና የካቲት 22 አመሻሽ ላይ በአውአሎም መሪነት ሠራዊቱን ይዞ ወደ አድዋ ተመመ፡፡ የካቲት 21 እንዳይነሣ ዝናብ ስለያዘው እንጂ ታላቁ ጦርነት የካቲት 22 ሊደረግ ይችል ነበር፡፡ ስለዚህ ጄነራል ባራቴሪ በዝናብ በመያዙ ምክንያት ዘመቻውን በማግሥቱ አደረገና የካቲት 22 ቀን 1888 ዓ.ም ሌሊቱን ሙሉ ሲጓዝ አድሮ ሊነጋ ሲል የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም አድዋ ጦር ግንባር ደረሠ፡፡ አውአሎም ከፊት ለፊታቸው የጀግናው የቱርክ ፓሻ የአፍሪቃ ጀኔራል አሉላ አባነጋ የገበሬ ሠራዊት ምሽግ እንደታያቸው መሮጥ ጀመሩ፡፡ ባራቴሪ፡- አውአሎም አውአሎም ብሎ ተጣራ፡፡ እስሀ ዝዋአልካዮ አያውለና ብለውት ዘለው አሉላ ምሽግ ውስጥ ገቡ፡፡ ዛሬ አንተን አያድርገኝ ማለታቸው ነው በአማርኛ፡- እስሀ ዝዋአልካዮ አያውለና፡፡
ከጥቂት ደቂቆች በኋላ ምድር ቁና የሆነችበት ድብልቅልቅ ያለው ጦርነት ተጀመረ፡፡ የኢትዮጵያ ጀግና የገበሬ ሠራዊት ከጠዋቱ አራት ሠዓት ግድም ታላቁን የአድዋ ድል መቀዳጀቱን አረጋገጠ ፡፡ ብዙ ሺህ የኢጣሊያ ወታደሮች በጦር ሜዳ ተገደሉ፡፡ ብዙ ሺዎች ደግሞ ቁስለኛና ምርኮ ሆኑ፡፡ የተቀረውንና ድል ተመትቶ የተበታተነውን የኢጣሊያ ወታደር እያሣደደና እያባረረ አፍሪቃዊው ኃይል ፈጀው ብሎ ፅፎአል ጆርጅ በርክሌይ፡፡ ከሚሸሹት መሃከል አንዱ የአውሮጳዊው ወራሪ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጄኔራል ባራቴሪ ነው፡፡
ይሄ (በአውአሎም ብስለትና ሥልጡንነት መስዋዕትነትና ኢትዮጵያዊ ፍቅር የተገኘው) ሰለጠነ በሚባለው የአውሮጳ ኃይል ላይ አልሰለጠነም በሚባለው አፍሪቃዊ ኃይል የተጨበጠ ትልቅ የወታደራዊ መረጃ () ብልጫ ወይም ድል ነው፡፡
በወታደራዊ ሣይንስ ደግሞ ወታደራዊ መረጃ ለወታደራዊ ግጃጅ አፈፃፀም ዋነኛና ወሣኝ ጠቀሜታ አለው፡፡ በዚህች ዓለም ላይ ከተደረጉ አብዛኞቹ ጦርነቶች ድል ያደረጉት የወታደራዊ መረጃ ብልጫ የነበራቸውና ፍትህና እውነትን ፖለቲካዊ መሠረት ያደረጉት ናቸው፡፡ እኛ ሁለቱንም ነበረን፤ ዓላማችን የአገራችንን ጥቅምና ክብር ህልውናና ልዕልና ማስከበር ነፃነታችንን ማስጠበቅ ሲሆን፡- ይህም የፍትህና የእውነት ነፍሥ ነው፡፡ በአገር ወዳዱ ባሻዬ አውአሎም ሀረጐት አማካይነት ደግሞ በአውሮጳ ላይ የወታደራዊ መረጃ ብልጫን ተቀዳጀን፡፡ ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን ታሪኳ ከውጪ ወራሪዎች ጋር ባደረገቻቸው ጦርነቶች ሁሉ፡- እውነትና ፍትህን መሠረት አድርጋለች፡፡
የዲፕሎማሲያዊ ድሉን የተቀዳጀችው ኢትዮጵያ፡- አውሮጳ ውስጥ ባስቀመጠቻቸው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወላጅ አባት ራስ መኮንንና ግራዝማች ዮሴፍ በተሰኙ ዲፕሎማቶቿ አማካይነት ነው፡፡ ጣሊያኖች ኢትዮጵያውያን ያልሰለጠኑ በመሆናቸው በምርኮኞች ላይ ሠብአዊነት የጐደለው ድርጊት ይፈፅማሉ ብለው ያስወራሉ፡፡ ግራዝማች ዮሴፍ በተለያዩ ቋንቋዎች እየፃፈ ለአውሮጳ ጋዜጦች ይሄን ያስተባብላሉ፡፡ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ደግሞ ኢትዮጵያ ልክ ዲፕሎማቶቿ እንዳሉት ምርኮኞችን ግብር አብልታ አካላቸዉም ምቾታቸውም ሳይጓደል ወደ አገራቸው ሰደደች፡፡
በዚህም ዲፕሎማሲያዊ ሥልጣኔዋን ለመላው አውሮጳ እና ለመላው ዓለም በተጨባጭ አሳየች፡፡ ከመቶ ዓመታት በላይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላት ብቸኛ አፍሪቃዊት አገር፡- ኢትዮጵያ ነች፡፡ የአብዛኞቹ የአፍሪቃ አገሮች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ረጅም ዕድሜ ከስድሣ ዓመት አይዘልም፡፡ ኢትዮጵያ፡- ከኢጣሊያና ከፈረንሣይ ከአሜሪካ () እና ከእንግሊዝ ከሩሢያና ከጀርመን (ከስድስት አገራት) ጋር ከመቶ ዓመታት ለሚበልጥ ጊዜ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን አዳብራ እና አፅንታ ቆይታለች፡፡
በአድዋ ድል፡-
ዋነኛው ድል በጦር ግንባር ፍልሚያ የተገኘው ድል ነው፤ ታላቁ የአድዋ ድል፡፡
የአድዋ ጦርነት(የጥቁሮች የነፃነት ተምሳሌት) የተደረገው በሁዳዴ ፆም ውስጥ ነው፡፡ ከዚያ በፊት በአፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት የተደረገው የመቅደላ ጦርነትም በሁዳዴ ፆም ውስጥ ነው የተካሄደው፡፡ በአድዋ ጦርነት ፆምና ውጊያ አብሮ ስለማይሄድ ግብፃዊውን ጳጳስ ሠራዊቱን ይፍቱትና እንደ ልቡ ይዋጋ ቢባሉም ባለመፍታታቸው ከኢትዮጵያ የገበሬ ሠራዊት ጿሚ የሆነው እየፆመ ለመዋጋት ተገዶአል፡፡ በመቅደላ ውጊያ ዓፄ ቴዎድሮስ [ካሣ ኃይሉ ወልደጊዮርጊስ (አባ ታጠቅ ካሣ) (መዩሣው ካሣ) (ወሬሣው ካሣ)] ሊወጋቸው ለመጣው እንግሊዛዊው ጄኔራል ናፒዬርና ሠራዊቱ ፆምህን ፈትተህ ከእኔ ጋር ውጊያ ግጠም ብለው አንድ ሺህ በጐች ልከውለታል፡፡
ከአድዋ ጦርነት በፊት ባሉት ጥቂት ወራትና ሣምንታት መቀሌና አምባላጌ ላይ የተደረጉ ጦርነቶች አሉ፡፡ የመቀሌን ከተማ በኢጣሊያዊው ኮሎኔል ጋሊያኖ ከሚመራው አውሮጳዊ ሠራዊት ለማስለቀቅ መስዋዕትነቱ የበዛ በመሆኑ፡- መቀሌ የተለቀቀችው በፈረንጆች ሚሊኒየም ) የሚሊኒየሙ ምርጥ ሠብዕና ብሎ ከአህጉር አፍሪቃ ባጫቸው ከጐንደር ቤተሠብ በሚወለዱት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ሥልጡን ወታደራዊ መላ ነው፡፡
ዝርዝሩን እዚህ አላወሣውም እንጂ መቀሌ በጣይቱ ልዩ ወታደራዊ ብቃት መያዝዋን መግለፅ ይጠቅማል፡፡ በኋላ ላይ ኮሎኔል ጋሊያኖ በአድዋ ጦርነት ተማርኮ፡- የምንሊክን ፊት ከማይ ግደሉኝ ብሎአል፡፡ በአምባላጌው ጦርነት ሊቀ መኳስ አባተ መድፍ ተኩሠው በጣሊያን መድፍ አፍ ውስጥ እስከ መክተት የዘለቀ አነጣጣሪነታቸውን አሣይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ሥልጣናት፡- ማዕከል ወሎ ውጫሌ በነበረበት ሁናቴ፤ ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክ (አባ ዳኘው) ለህዝባቸው የክተት ጥሪ ካደረጉ በኋላ ከዳር እስከ ዳር የተንቀሣቀሠው የተቆጣ ኢትዮጵያዊ ሠራዊት ሢተም፤ ሲገባኝ ከሠሜን ኢትዮጵያ ከጐንደር ከጐጃም ከወሎና ከትግራይ … የተንቀሳቀሰው አትንኩኝ ያለ ኢትዮጵያዊ ጀግና ከሚተምመው ሠራዊት የተገናኘው በትውልድ አቅራቢያው ሆኖ ነው፡፡
መጓጓዣ በሌለበት ዘመን የሠሜኑን የኢትዮጵያ ጀግና የገበሬ ሠራዊት ወደ ሰሜን ለማዝመት ሲባል በመሀል አገር ማሰባሰብ የሚያስፈልግበት ሁኔታ አልነበረም፡፡
ታላቅ ድል።
|
35137
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%AD%20%E1%8A%A4%E1%8A%95%20%E1%8A%A4
|
አር ኤን ኤ
|
አር ኤን ኤ እንደ ዲ ኤን ኤ ከኒክሉኢክ አሲድ የተሠራ ነው። እንደ ዲ ኤን ኤ አራት ቤዝ () አለው። እነሱም አዴናዪን ፤ ዩራሲል ( ዲ ኤን ኤ ግን በዩራሲል ፋንታ ታያሚን ነው ያለው) ጓኒን እና ሳይቶሲን ። ኑክሌይክ አሲዶች ደግሞ ሶስት መሰረታዊ አካላቶች አላቸው። ቤዝ፡ ሱካሩ እና ፎስፌት ግሩፑ ናቸው። አር ኤን ኤን ከዲ ኤን ኤ የሚለየዉ ሌላው ነገር የአር ኤን ኤ ስኳር ሁለተኛ ካርቦን ሀይድሮክሲል ሲኖረው ዲ ኤን ኤ ግን ያለው ኤች ብቻ ነው። ይህም አር ኤን ኤን በጣም ተለካካፊ አድርጎታል።
|
38093
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%80%E1%8B%B0%E1%88%9D%E1%89%B5%20%E1%88%B3%E1%8B%AD%E1%8A%95%E1%88%B3%E1%8B%8A%20%E1%8D%8D%E1%88%8D%E1%88%B5%E1%8D%8D%E1%8A%93%E1%8B%8E%E1%89%BD
|
ቀደምት ሳይንሳዊ ፍልስፍናዎች
|
ቀደምት ሳይንሳዊ ፍልስፍናዎች፤ በቀድሞው ወቅት ሳይንስ ሳይራቀቅ ቴክኖሎጂም ዓለምን በፍጥነት ከመቀየሩ በፊት የነበሩት የጥንት ፈላስፎች ለአሁኑ ዘመን የሳይንስ እድገት የራሳቸውን አሻር አሳርፈዋል። ታዲያ የጥንት ፈላስፎች ሲነሱ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱት የግሪክ ፈላስፎች ሆነው ይገኛሉ። ሪናን የተባው ፀኃፊ እንዳለው፣ «ሶቅራጥስ ለሰው ልጅ ፍልስፍናን አበረከተ። አሪስቶትል ደግሞ ሳይንስ አበረከተ» ከሶቅራጠስ በፊትም ቢሆን ፍልስፍና ነበሩ። ከአሪስቶትልም በፊት ቢሆን ሳይንስ ነበር። ነገር ግን ከሶቅራጠስና ከአሪስቶትል በኋላ ፍልስፍናም ሆነ ሳይንስ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል። ከነሱ በኋላ የተሰራው ሁሉ እነሱ በጣሉት መሠረት ላይ የተገነባው ነው” ሲል የቀደሙትን ፈላስፎች ሚና ያረጋግጣል።
ለመጀመሪያ ጊዜ በግልፅ ለማይታወቁት ክስተቶችና ድርጊቶ ተፈጥሯዊ ማስረጃዎችን ማቅረብ የጀመሩት ኢዮኒያዊን ግሪኮች እንደነበሩ ታሪክ ይናገራል።
የተለዩ ገጠመኞችን ምክንያቶች ወይም መነሻዎች በፊዚክስ አማካኝነት ለማግኘት ሞክረው ነበር እንዲሁም በፍልስፍና አማካኝነት ለማድረግ የሞከሩት ደግሞ ለአጠቃላይ (ክስተቶች) ተፈጥሯዊ ንድፈ ሃሳብ በማግኘት ነበር።
ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ640 እስከ 550 እንደኖረ የሚነገርለት እና “የፍልስፍና አባት” ተብሎ የሚታወቀው ታለስ የመጀመሪያ የከዋክብት ሳይንስ ተመራማሪን ሳይንሳዊ ፍልስፍና እናያለን።
እሱም አንድ ወቅት ሚልተስ በተባለ ስፍራ የሚኖሩ ተወላጆችን ያስደነቀው ፀሃይና ከዋክብት ከእሳት የተሰሩ ኳሶች ናቸው በማለት ነበር። ሰዎቹ ግን ፀሃይንና ከዋክበትን አምላኮች ናቸው ብለው ያምኑ ነበር። ከክርስቶስ ልደት በፊት 610-540 መካከል ይኖር የነበረው የዚህ ፈላስፋ ተማሪ የነበረው አናክሊማንደር ለመጀመሪያ ጊዜ ከዋክብትንና መልክዓ ምድርን የተመለከተ ቻርቶች ወይም ስዕች የሰራ ሰው ነው። በእሱ እምነት ዓም የተጀመረው እንደ አንድ ወጥ ክምችት ሆኖ ነው። ሁሉም ነገር ከዚህ የተገኘው የተቃራኒዎች መለያየት በሚለው ሂደት ነው። የከዋክብት ታሪክ እራሱን የሚደጋግምና ቁጥር ስፍር የሌላቸው አለማት እንደሚፈጠሩና ተመልሰውም እንዲጠፉ አስተምሮ ነበር። እንደሱ አባባል መሬት በራሷ ውስጣዊ ግፊት ሚዛኗን ጠብቃ የቆመችና የማትንቀሳቀስ አካል ናት። ፕላኔቶች በሙሉ በአንድ ወቅት ከፈሳሽ አካል የተሰሩ ነበሩ፤ ህይወት ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው ከባህር ሲሆን ወደ ደረቅ መሬት የመጣውም የባህር ውሃ ሲቀንስ ነው። በዚህ ሁኔታ ደረቅ መሬት ላይ የቀሩት እንስሳት ቀስ በቀስ አየር የመተንፈስ ችሎታን በማዳበር ከዚህ በኋላ በምድር ላይ ለተፈጠሩት ህይወቶች መነሻ ሆነዋል የሰው ልጅም ከመጀመሪያ ጀምሮ አሁን የሆነውን ዓይነት ፍጡር የማያውቅ ከነበረና ከማደግ ይን ያህል ጊዜ የሚፈጅበት ከሆነ እስካሁን በህይወት መቆየት አይችልም ነበር ኪልም አትቷል።
ከክርስቶስ ልደት በፊት በ450 ይኖር የነበረው አናክሊሜኔስ የተባለው ሌላው ተመራማሪ ደግሞ የነገሮችን የጥንት ሁኔታ ሊገለፅ አንድ ወጥ ጋዝ እንደነበረና ቀስ በቀስም ወደ ነፋስ፣ ጉም፣ ውሃ፣ መሬትና ድንጋይና እንደ ተለወጠ ይናገራል። እንደሱ አባባል የቁሳቁስ ሦስቱ ቅርፆች ማለትም ጋዝ፣ ፈሳሽና ጠጣርነት፣ የመቀዝቀዝ የተለያዩ ደረጃዎች ናቸው።
የመሬት መንቀጥቀጥ የሚከሰተው ደግሞ ፈሳሽ የነበረው የመሬት አካል በሚጠጥርበት ወቅት ነው። ህይወትና ነፍስ አንድ ናቸው። ከማንኛውም ቦታና በማንኛውም ነገር ውስጥ እንቅስቃሴ ኃይል ይገኛል ብሏል።
ሌላው እና አስገረሚው ግሪካዊ ፈላስፋና ከ500-428 ይኖር የነበረው አናግዛጎራስ የሰውን ልጅ የማሰብ ችሎታ በተመለከተ የፊት እግሮችና እጆች መንቀሳቀቀስ በሚያቆምበት ጊዜ በሚፈጥር የኃይል ሂደት የተገኘ ነው ሲል አስተምሮ ነበር።
በመጨረሻ አንድ ኤምፔኮክሌስ የተባውና ከክርስቶስ ልደት በፊት በ445 ሲሲሊ በምትባል ደሴት ይኖር የነበረ ሌላ ተመራማሪ ደግሞ የአዝጋሚ ለውጥን ፅንሰ ሃሳብ አንድ እርምጃ አስኪዶት ነበር። እሱ እንዳለው አካላት የሚፈጥሩት አስቀድሞ በነበረ መመሪያ ሳይሆን በምርጫ ነው። ተፈጥሮ በተለያዩ ህይወት ያላቸው አካላት ላይ ብዙ ሙከራዎችን ታደርጋለች። የተለያዩ አካላትን በተለያዩ መልኮች ታዋህዳለች። ውህደቱ የአካባቢውን ፍላጎት የሚያሟላ ከሆነ አካሉ በህይወት መኖሩን ዘሩን ማራባት ይችላል። ውህደቱ ካልሰመረ ደግሞ አካሉ ታርሞ ይጣላል። ጊዜ እያለፈ በሄደ ቁጥር የተለያዩ ህይወት ያላቸው አካላት አካባቢዎችን እየተለማመዱበት ይካሄዳሉ ሲል ሳይንሳዊ ፍልስፍናውን በየጊዜ ተናግሮ ነበር።
እንግዲህ እነዚህ ጥንታዊ ፈላስፎች የሳይንስ ብልጭታ ባልነበረበት ወቅት ፍልስፍናዊ ትንታኔዎችን በማዳበር ለሳይንሳዊ ንድፈ ሃሳቦችን ማደግ የማይናቅ ጥንታዊ ድርሻቸውን በአግባቡ ተወጥተው አልፈዋል።
|
9605
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%8C%A8
|
ተረት ጨ
|
ጨረቃ ሲጠፋ ኮከብ አባወራ ይሆናል
ጨዋነሽ ቢሏት ሳቁ ገደላት
ጨው ለራስህ ብለህ ጣፍጥ አለበለዚያ ድንጋይ ነው ብለው ይወረውሩሀል
ጨጓራ ለመፍጨት አንጀት ለመጎተት በለው ዋተት ዋተት
ጫማ የለኝም ብለህ አትዘን ካልሲ የሌለው አለና
ጫማ የለኝም ብለህ አትዘን እግር የሌለው አለና
ጭድ ይዞ እሳት ሳል ይዞ ስርቆት
ጭድ ይዞ ወዘት ሳል ይዞ ስርቆት
ጭለማ ቢመጣ አትፍራ ይነጋልና
|
32684
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B4%E1%89%A2%E1%89%B5%20%E1%8A%AB%E1%88%AD%E1%8B%B5
|
ዴቢት ካርድ
|
ዴቢት ካርድ ደምበኞች የባንክ አካውንታቸን ሂሳብ ቀጥታ እንዲያገኙ የሚረዳ የፕላስቲክ ካርድ ነው። በዚህ ካርድ ከኤቲኤም ገንዘብ ማውጣት ሲቻል፣ እቃዎችንም በቀጥታ ለመግዛት ይረዳል። ሆኖም በዴቢት ካርድ እና በተመሳሳዩ የክሬዲት ካርድ መካከል ብዙ ልዩነት አለ።
ዴቢት ካርድን ደንበኞች ሲጠቀሙ፣ በ አካውንት ቁጥራቸው ውስጥ ካለው ገንዘብ በላይ እንዳይጠቀሙ ጥንቃቄ ማድርገ ያሻል። አለበለዚያ ደንበኞች ካላቸው ገንዘብ በላይ በዴቢት ካርዳቸው ሲከፍሉ፣ ባንኩ በጣም ከፍተኛ ቅጣት ሊቀጣቸው ይችላል። ብዙ ሱቆች ደንበኞቻቸው ዴቢት ካርድ ሲጠቀሙ፣ ተጨማሪ ክፍያ ያስከፍላሉ። ይህን ሲያደርጉ፣ በስውር እንጂ በግልጽ ላይሆን ይችላል።
ቼኪንግ አካውንት
|
16257
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%89%BA
|
ስላንቺ
|
ስላንቺ የኢትዮጵያ አስቂኝ የፍቅር ፊልም ነው። ፊልሙ በኢትዮጵያ ሲኒማ ቤቶች ረዥም ጊዜ የቆየ ሲሆን በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቷል። በ4ኛው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል 3 ሽልማቶችን ያገኘ ሲሆን በኒው ዮርክ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ላይም በተመሳሳይ ምርጥ ዓለም አቀፍ አስቂኝ የፍቅር ፊልም ተብሎ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያ ፊልሞች
|
48863
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A6%E1%88%8E%E1%88%9D%E1%8D%92%E1%8A%AD%20%E1%8C%A8%E1%8B%8B%E1%89%B3%E1%8B%8E%E1%89%BD
|
የኦሎምፒክ ጨዋታዎች
|
የኦሎምፒክ ጨዋታዎች (ወይም ኦሊምፒክስ) በየአራቱ ዓመታት የሚከሠት ትልቅ ዓለም አቀፍ እስፖርት ውድድር ድርጊት ነው። የሞቄ ወቅት ኦሎምፒክ ጨዋታዎች በኢትዮጵያ ክረምት ወቅት በሞቀ ቦታ ይደረጋል፤ የበረድ ወቅት ኦሎምፒክ ጨዋታዎች ደግሞ በኢትዮጵያ በጋ በስሜኑ ክፍለ-አለም ይደረጋሉ።
በጥንት መጀመርያ ኦሎምፒክ ጨዋታዎች ከ784 ዓክልበ. ጀምሮ እስከ 385 ዓም ድረስ በየአራቱ አመታት በግሪክ አገር ተቀጠሉ። ዘመናዊ ጨዋታዎች በ1888 ዓም ተጀመ.
|
12321
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8E%E1%88%8D%E1%8D%8D
|
ጎልፍ
|
ጎልፍ በስሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓና በህንድ ባሉ ሃገራት ተወዳጅ የሆነ ስፖርት ነው። ስለ አጀማመሩ ትክክለኛ መረጃ ባይኖርም በቀደምት ሮማውያን እንደሆነ ይነገራል። ጎልፍ በአገራችን ገና ከምንለው አጨዋወት ጋር የሚያመሳሰለው በበትር ኳሷን መቀወሩ ሲሆን ጎልፍ ግን በአሬንጓዴያማ ሣር ሜዳ ሆን ተብሎ በተዘጋጀውና በውድ ዋጋ በሚገዛ የመግቢያ ቲኬት በሚገባ ተመልካች የሚታጀብ ጨዋታ ነው።
|
1542
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%80%E1%88%90%E1%8B%AD
|
ፀሐይ
|
ፀሓይ (ምልክት፦) በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ።
ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው።
ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና።
ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ።
የፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና።
ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም።
የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው።
ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። (በጣም ጐልተው ከሚታዩ ሜጋሊቶች ውስጥ ጥቂቱ በ ናባታ ፕላያ፣ ግብጽ፣ እና በ ስቶንሄንጅ፣ እንግሊዝ፣ ውስጥ ይገኛሉ።)
ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ።
በምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ።
የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ።
ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች።
በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል።
|
52191
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%90%E1%89%A5%E1%8B%B1%E1%88%8D%E1%8C%80%E1%88%8A%E1%88%8D%20%E1%88%B8%E1%8A%BD%20%E1%8B%90%E1%88%8A%20%E1%8A%AB%E1%88%A3
|
ዐብዱልጀሊል ሸኽ ዐሊ ካሣ
|
ዐብዱልጀሊል ዐሊ ካሣ (ዐብዱልጀሊል ሸኽ ዐሊ ካሣ)
በደቡብ ወሎ ቦረና ወረዳ መካነ-ሠላም ከተማ በህዳር 18/1977 ዓ.ም ከአባቱ ከሸኽ ዐሊ ካሣና ከእናቱ ከወይዘሮ አመተልመሊክ ዑምር ሙሐመድ ተወለደ።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በቦረና 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። ከ9-10ኛ ክፍል በቦረና ከፍተኛ ትምህርት ቤት፣ ፕሪፓራቶሪ ትምህርቱንም እዛው ቦረና ፕሪፓራቶሪ ትምህርት ቤት ተከታትሎ በ1998 ዓ.ል ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ በ2000 ዓ.ል በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ድግሪውን በማዕረግ ተመርቋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ተከታትሏል፣ ከዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ በደቨሎፕመንት ኢኮኖሚክስ ሁለተኛ ድግሪውን (ኤም ኤ ድግሪ) ሲይዝ በ2009 ዓ.ል ጣልያን አገር ሄዶ ሎምባርዲያ ሪጅን ከሚገኘው ብሬሽያ ዩኒቨርስቲ በኢንተርናሽናል ቢዝነስ ሌላ ተጨማሪ ማስተርስ ድግሪ ተመርቋል።በክንፈ የደህንነት ማሰልጠኛ ተቋም ከሰለጠነ በኋላ በቀድሞው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በኢኮኖሚ ደህንነት ክፍል፣ በታክስ ኢንቨስትጌሽን ክፍል ለስምንት አመታት ሰርቷል።
ኪነት ያገነነው አጼ የሚለውና በ2010 ዓ.ል የታተመው መጽሐፉ በአገሪቱ በብዙው የተወራለትና መነጋገሪያ ሆኖ የዘለቀ ሲሆን ተምኔታዊት ደሴት የሚለው ጥነታዊ መጽሐፉ ደግሞ ሁለተኛው መጽሐፉ ነው።
|
15791
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%88%8B
|
ባላ
|
ይህ መጣጥፍ ስለ ሥነ ሂሳባዊው መስመር ነው። ለሰዶም ንጉሥ፣ ባላ (የሰዶም ንጉሥ) ይዩ።
ባላ (ፓራቦላ) በሂሳብ ጥናት ውስጥ የተስተካከለ የባላ ቅርጽ ያለው የሂሳብ መስመር ነው ቃል ነው። ባላ በሂሳብ እንዲህ ሲደረግ የፈጠራል፡ ባንድ ጠፍጣፋ ሜዳ ላይ አንድ ነጥብና አንድ መስመር እንውሰደ። ለዚህ ነጥብ እና ለመስመሩ እኩል ርቀት ላይ የሆኑ ነጥቦቹን በሜዳው ላይ ብንደረድር የምናገኘው ስዕል ባላ/ፓራቦላ ይሆናል ማለት ነው። ነጥቡ ፎከስ ሲባል፣ መስመሩ ዳይሬክትሪክስ ይባላል።
የባላ ቀመር በደካርት ሰንጠረዥ
ለተጨማሪ ማብራሪያ ኳድራቲክ እኩልዮሽን ይመልከቱ
ዳይሬክትሪክስ መስመር ቢኖን እና ፎከሱ ቢሆን () ደግሞ የባላው ነጥቦች ቢሆኑ፣ ከነጥቡና ከመስመሩ ያሉትን እኩል ርቀቶች ግምት ውስጥ በማስገባት ይህን እናገኛለን
ሁለቱንም ጎኖች በየራሳቸው ስናበዛና ስናስተካክል ይህን እናገኛለን
ይህን ባላ በሜዳው ሁሉ ስናዘዋውረው ይህን መልክ ይይዛል
እንግዲህ ይህ ሲስተካከል
የሰጣል። በሂሳብ ጥናአት የባላ አጠቃላይ ቀመር ተብሎ የሚታወቀው ነው
ባላ በተፈጥሮ
የተተኮሰ ጥይት፣ የተወረወረ ድንጋይ፣ ሮኬቶች፣ ወዘተ.... በምድር ግስበት ምክንያት እንዲሁ የባላ ቅርጽ ይዘው ለመጓዝ ይገደዳሉ።
|
17785
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%89%E1%89%A5%E1%8C%A0%E1%89%B5
|
ጉብጠት
|
ጉብጠት አንድ መስመር ወይም ገጽታ ከቀጥተኛ መስመር ወይም ከጠፍጣፋ ጠለል የሚለይበትን መጠን የምንለካበት የሂሳብ ጽንሰ ሃሳብ ነው። ከዚህ አንጻር ጉብጠት ማለት በአንድ መስመር ላይ የሚያጋጥመን የአቅጣጫ ለውጥ በእያንዳንዷ የርዝመት መስፈርት ሲካፈል ማለት ነው። ቀስ ብሎ አቅጣጫው ከቀየረ፣ አንስተኛ ጉብጠት አለው እንላለን። አቅጣጫው በፍጥነት ከቀየረ ከፍተኛ ጉብጠት አለው እንላለን
የጉብጠት ጽንሰ ሃሳብ መነሻ ክብ ነው። ሁለት ክቦችን የሚለያያቸው የሬዲየሳቸው መጠን ነው። ከፍተኛ ራዲየስ ወይም ሰፊ ክቦች በቀስታ የሚጎብጡ ስሆኑ ዝቅተኛ ራዲየስ ያላቸው ደግሞ በቶሎ ይጎብጣሉ። ስለዚህ የአንድ ክብ ራዲየስና ጉብጠቱ የተገላቢጦሽ ግንኙነት አላቸው። ስለሆነም የአንድ ክብ ሬዲየስ ቢሆን ጉብጠቱ 1/ ይሆናል ማለት ነው።
እንግዲህ ከዚህ ተነስተን የማናቸውንም መስመሮች ጉብጠት ለመለካት እንሞክራለን።
አንድ ጎባጣ መስመር ቢሰጠንና ነጥብ እላዩ ላይ ቢሆን, አንድ የተለየ ክብ ያንን ጎባጣ መስመር በዚያ ነጥብ ላይ ከሁሉ በላይ ይቀርበዋል። ይህ ክብ ኦሱሌቲንግ ክብ የሚባለው ነው። ስለሆነም በዚህ ነጥብ ላይ የሚገኘው ኦሱሌቲን ክብ ሬዲየስ ግልባጭ የዚያ መስመር ጉብጠት ይባላል።
በማዕዘን (አቅጣጫ መለኪያ) የአንድን መስመር ጉብጠት እንዲህ እንለካለን፣ -- እዚህ ላይ ኢምንት ርዝመት ሲሆን፣ የግሪኩ ፋይ ደግሞ ማዕዘን መለኪያ ነው
የነጥቡን አቀመማመጥ በቬክተር በዚህ መልኩ ብንጽፍ ፣ እዚያ ነጥብ ያለውን ጉብጠት በቬክተር ስሌት እንዲህ እንጽፋለን፦
ይህ ዋናው ቀመር ቢሆንም ለተጨባጭ ስራ ስለማያመች፣ ግልጽ የሆኑ ቀመሮቹን እንዲህ እናሰላለን፡
ቀመር 1 ፡
ቀመር 2 ፡
ቀመር3 ፡
መስመሩ በፖላር ኮርዲኔት ከተወከለ፣ ጉብጠቱ እንዲህ ይሰላል
ሥነ ጉብጠት
|
49964
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A5%E1%8A%90%20%E1%8D%88%E1%88%B3%E1%88%BD
|
ሥነ ፈሳሽ
|
ሥነ ፈሳሽ የተፈጥሮ ኅግጋት (ፊሲክስ) ጥናት ክፍል ሲሆን ትኩረት ሰጥቶ የሚመራመረው ስለ ፈሳሽ፣ አየር እና ፕላዝማ ቁስ አካላት ሥነ እንቅስቃሴ ነው። የዚህ ዕውቀት መስራች ተብሎ የሚታዎቀው የጥንቱ ግሪክ አርኪሜድስ ነው። አርኪሜድስ «ጠጣር ነገሮች በፈሳሽ ነገር ውስጥ ለመንሳፈፍ ምን ምክንያት አላቸው?» የሚለውን ጥያቄ ለመፍታት ሞክሮ፣ በኋላም ስለዚህ ጉዳይ መሪ ሃሳብ ሲያገኝ፣ ዩሬካ እያለ በደስታ በግሪክ አገር መንገዶች እራቁቱን እንደሮጠ ትርክት አለ።
|
19762
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%81%E1%88%98%E1%89%B5%20%E1%88%98%E1%8A%A8%E1%88%AD%E1%8A%A8%E1%88%9D
|
ቁመት መከርከም
|
ቁመት መከርከም, ወይም በ ምህጻረ ቃል መልዕክትን በራዲዮ ሞገድ ለመላክ የሚያገለግል በጣም ቀላሉ ዘዴ ነው። ይህ መልዕክትን የመላኪያ መንገድ ለረጀም ርቀት ግንኙነት ጠቃሚ ነው ምክንያቱም ከመሬት ከባቢ አየር ላይ በመንጠር ለብዙ ርቀት መጓዝ ይችላልና።
ቁመት እዚህ ላይ የአንድን ሞገድ ቁመት ይወክላል። ተሸካሚው ሞገድ (ራዲዮ ሞገድ) ላይ የድምፅ ሞገድ በመጫን የተሸካሚው ሞገድ ቁመት ይከረከማል። በዚህ መንገድ የተዋሃደው ሞገድ እንደማንኛውም የኤሌክትሮመግነጢስ ጨረራ በኅዋ ውስጥ ይጓዛል። በዚህ መንገድ ይተበጀው የራዲዮ መልዕክት ኤ.ኤም ራዲዮ ይሰኛል፣ የሚሰራጨውም ዝግጅት፣ በክሪስታል ራዲዮ ለመቀበል ይቻላል።
ኤ.ኤም (ቁመተ ክርክም) መልዕክቶች ብዙ ጊዜ የሚላኩት በመካከለኛና በአጭር ሞገዶች ነው። በዚህ መንገድ የተላኩት ድምጾች ሊሰሙ ቢችሉም ጥራት ግን ይጎላቸዋል። ቁመተ ክርክም (ኤ.ኤም) ራዲዮ ስርጭት በኤሌክትሪክ መስመሮች እና በፀሐይ ጨረራ ሊጠለፍ ይችላል፣ አልፎ አልፎም ደመቅ-ቀዝቀዝ የማለት ባህርይ ሊያሳይ ይችላል።
በድሮ ጊዜ ቁመት ክርክም ራዲዮ የሚሰራጨው በመካከለኛ ሞገድ (ከ 540 እስክ 1600 ድግግም በሰከንድ) ነበር። አጭር ሞገድ (ከ 3000 እስክ 30,000 ኪሎ ሳይክል) ምድርን መዞር ስለሚችል፣ አንድ አንድ አገሮች የራዲዮ ዝግጅታቸውን በዚህ መስመር ሲልኩ ይታያሉ። ኤፍ.ኤም ራዲዮ ጥራቱ ከቁመተ ክርክም ራዲዮ ይሻል እንጂ፣ ብዙ ርቀት መጓዝ አይችልም።
መደብ :ራዲዮን
|
34076
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%9E%E1%8B%9D%20%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%89%A3%20%E1%8C%8A%E1%8B%AE%E1%88%AD%E1%8C%8A%E1%88%B5
|
ዞዝ አምባ ጊዮርጊስ
|
ዞዝ አምባ ጊዮርጊስ አሰራሩ ቤተ አባ ሊባኖስን የሚያስታውስ በበለሳ ወረዳ ፣ ሰሜን ጎንደር የሚገኝ አለት ፍልፍል ቤተክርስቲያን ነው። እንደ ታሪክ አጥኝው ክላውድ ለ ፔጅ አንድ አንዱ የዚህ ቤተክርስቲያን አቅድ ከላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት በፊት ይሰራበት የነበር ዓይነት ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ ከላሊበላ በኋላ በተሰሩ አብያተ ክርስቲያናት ያሉ አይነቶች ናቸው። ስለሆነም ቤተክርስቲያኑ ከላሊበላ አብያተክርስቲያነት በፊት ወይንም በኋላ እንደተሰራ ለማዎቅ እንዳልቻለ ያትታል።
የውጭ ማያያዣ
የአካባቢው ካርታ]
ፓኖራማ ፎቶ]
አለት ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት
|
12577
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%81%E1%88%8A%E1%8B%AB%20%E1%88%AE%E1%89%A0%E1%88%AD%E1%89%B5%E1%88%B5
|
ጁሊያ ሮበርትስ
|
ጁሊያ ሮበርትስ ወይም ጁሊያ ፊዮና ሮበርትስ ጥቅምት 27 1967 እ.ኤ.አ. አሜሪካ ውስጥ የተወለደች ተዋናይት ነች። ጁሊያ ፕሪቲ ዉመን በተሰኘው ፊልም ከሪቻርድ ጊር ጋር በመተወን ገና ለመውጣት ችላለች። ስቲል ማግኖሊያስ የተሰኘውና በ1990 እ.ኤ.አ. የመጀመሪያዋን አካዳሚ አዋርድ ያገኘችበትን ጨምሮ በ1991 ፕሪቲ ዉመን እና በ2001 ኤሪን ብሮኮቪች በተስኙት ፊልሞቿ ልትሸለም በቅታለች።
የአሜሪካ የፊልም ተዋናዮች
|
15845
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%BE%E1%8C%A3%E1%8C%A3%20%E1%8A%AD%E1%8D%8D%E1%88%8E%E1%89%BD
|
የሾጣጣ ክፍሎች
|
በሂሳብ ትምህርት የሾጣጣ ክፍሎች የምንላቸው መስመሮች ቀጥተኛ ክብ ሾጣጣን በጠፍጣፋ ስንከትፍ የምናገኛቸውን ቅርጾች ነው። እኒህ መስመሮች በሌላም መንገድ ሲተረጎሙ የሾጣጣ ክፍሎች ማለት ከአንድ ነጥብ (ፎከስና ከአንድ መስመር (ዳይሬክትሪክስ) ያላቸው ርቀት በቋሚ ውድር ላይ የተመሰረቱ ማናቸውንም መስመሮች ያጠቃልላል።
በነገራችን ላይ የሾጣጣ ክፍሎች ከዛሬ 2200 አመታት በፊት በግሪካዊው አፖሎኒየስ ዘፐርጋ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተጠንተዋል።
|
11351
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%88%AB%E1%8A%93%20%E1%88%98%E1%89%85%E1%8B%B0%E1%88%B5
|
ብራና መቅደስ
|
ብራና መቅደስ በሙት ባሕር ብራናዎች መኃል አንድ ነው። ይህ ብራና ጥቅል በ1948 ዓ.ም. በዋሻ ቢገኝም እስከ 1959 ዓ.ም. ድረስ በሊቃውንት አልተተረጎመም ነበር። የተጻፈው በዕብራይስጥ ሲሆን ስለቤተ መቅደስ የሚነኩ የእግዚአብሔር ትዕዛዛት ለሙሴ ይከትታል።
በነዚህ ትእዛዛት የዘላለማዊ ቤተ መቅደስ ዝርዝሮች፣ ሥርዓቶችና ደንቦች ለሙሴ ይገለጻሉ። ሆኖም በታሪክ የእስራኤል ንጉስ ሰሎሞን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም በሠሩ ጊዜ፣ አሠራሩ በዚህ አይነት እቅድ አልነበረም። በዚህ ብራና የተገለጸው ቤተ መቅደስ ገና መቸም አልተሠራም። ቤተ መቅደሱ በዚህ የተሰጠው መጠን በነቢዩ ሕዝቅኤል ራዕይ ከታየው ቤተ መቅደስ መጠን ይልቅ ይበልጣል (ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕ. 40-47)። በምዕራብ ሊቃውንት አስተያየት ዘንድ፣ ያልታወቀ ደራሲ፦ «የኢየሩሳሌም መቅደስ እንደ ሰሎሞን መቅደስ ሳይሆን እንዲህ መሆን ነበረበት» የሚል ሀሣብ ለማቅረብ ፈልጎ ነበር።
ብራናው በየዓመቱ ስለሚከበሩ በዓላት ስርዓቶች ይዘረዝራሉ።
የቂጣ በዓልና ነዶውን መወዘወዙ
የሰንበታትና የበኲር መከር በዓላት
የወይን በዓል
የዘይት በዓል
የእንጨት በዓል
መሠረቱ ቅዱስ ስለሚሆን፣ ፈሻሽ ነገር ያለበት ሰው ወደ መቅደሱ ግቢ ሳይገባ ለ7 ቀን በርኩስና መቆየት አለበት። እንዲሁም መቅደሱ ያለበት ከተማ (ዘላለማዊው ኢየሩሳሌም) በሙሉ ቅዱስ ስለሆነ ግብረ ስጋ ግንኙነት በከተማው ውስጥ ይከለክላል። ማንም ባለትዳር ወደ ከተማው ሳይገባ ከሩካቤ ሁሉ 3 ቀን መቆየት አለበት። ነገር ግን በዚህ ብራና የተጻፉት እነዚህና ብዙ ሌሎች ደንቦች በታሪክ ውስጥ መቸም በተግባር አልታወቁም ነበር።
የውጭ መያያዣ
አንድ የእንግሊዝኛ ትርጉም
ኦሪጂናል ቅጂ (ዕብራይስጥ)
ሥነ ጽሁፍ
ሥነ ቅርስ
|
20058
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%81%E1%88%B5%E1%89%8B%E1%88%9D%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D
|
ቁስቋም ማርያም
|
ደብረ ፀሐይ ቍስቋም ማርያም ከጎንደር ከተማ በስተ ስሜን ምዕራብ ወጣ ብሎ በሚገኘው በደብረ ፀሐይ ቁስቋም የተሰራ ቤተክርስቲያን ነው። ደብረ ፀሓይ ቁስቋም በእቴጌ ምንትዋብ፣ ከ1725 ዓ.ም. እስከ በ1738ዓ.ም. ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሲሆን በጊዜው 360 መስታዎቶች የነበሩት፣ በቀይና ሰማያዊ ሃር አልባሳት ያሸበረቀ፣ እንደ ደብረ ብርሃን ስላሴ በጥሩ ኪነት የተዘጋጀ፣ ከወርቅና ከብር የተሰሩ የቤተ ክርስቲያን ማገልገያወች የነበሩት፣ በጊዜው የተደነቀ ቤተ ክርስቲያን ነበር። ደብረ ፀሐይ በተመሰረተበት ዘመን የራሱ ጉልት የነበረው ሲሆን ይኼውም በእብናት፣ በለሳ እና አርማጭሆ ተሰባጥሮ ይገኝ ነበር፤ ስለሆነም 260 ቀሳውስትን በስሩ ያስተዳድር ነበር፡፡ ከህንጻ ይዘቱ አንጻር በዚሁ ዘመን በምንትዋብ ከተገነባው ናርጋ ስላሴ ጋር ይመሳስል እንደንበር ግንዛቤ አለ።
የቁስቋም ግቢ ሦስት ጊዜ ጉዳት ደርሶበታል። በመጀመሪያ በ1858፣ ዓፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ሊያሰሩት ላሰቡት ቤተ ክርስቲያን ከቤተክርስቲያኑ የተለያዩ ንዋያትን መውሰዳቸው ነበር። ሁለተኛው ጉዳት የደረሰው በ1870ወች፣ ደርቡሾች ግቢውን በእሳት በማጋየት ያደረሱት ዋናው ጉዳት ነበር። በዚህ ቃጠሎ ቁስቋም ማርያም ሊፈርስ ችሏል። ቤተክርስቲያኑ አሁን የያዘውን ቅርጽ ያገኘው በጣሊያኖች ጊዜ ሲሆን ያሁኑ መልኩ ከድሮው እጅግ ይለያል። የእቴጌ ምንትዋብ፣ የልጇ ዳግማዊ እያሱ እና ልጅ ልጇ እዮዋስ አጥንቶች በመስታዎት ሳጥን ሆነው በዚህ ቤተክርስቲያን ይገኛሉ። ከእሳት የተረፉ የእቴጌ ምንትዋብ መገልገያዎች አሁን ድረስ በቤተክርስቲያኑ ይገኛሉ።
|
52411
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%88%8D%E1%8B%9B%E1%89%A4%E1%89%B5%20I
|
ኤልዛቤት I
|
ኤልዛቤት (ሴፕቴምበር 7 1533 - መጋቢት 24 ቀን 1603) [ሀ] የእንግሊዝ እና የአየርላንድ ንግስት ከህዳር 17 ቀን 1558 በ1603 እስከሞተችበት ጊዜ ድረስ የእንግሊዝ እና የአየርላንድ ንግስት ነበረች። አንዳንድ ጊዜ ድንግል ንግሥት እየተባለች የምትጠራው ኤልዛቤት ከአምስቱ የንጉሠ ነገሥታት ቤት የመጨረሻዋ ነበረች። ቱዶር.
ኤልዛቤት የ21⁄2 አመት ልጅ እያለች የተገደለችው የሄንሪ ስምንተኛ እና ሁለተኛ ሚስቱ አን ቦሊን ልጅ ነበረች። የአን ከሄንሪ ጋር የነበራት ጋብቻ ፈርሷል፣ እና ኤልዛቤት ህጋዊ እንዳልሆነ ተነገረች። ግማሽ ወንድሟ ኤድዋርድ ስድስተኛ እ.ኤ.አ. በ 1553 እስኪሞት ድረስ ገዝቷል ፣ ዘውዱን ለሴት ጄን ግሬይ ውርስ በመስጠት እና የሁለቱን ግማሽ እህቶቹ የሮማ ካቶሊክ ማርያም እና የታናሽቷ ኤልዛቤትን የይገባኛል ጥያቄ ችላ በማለት ፣ ምንም እንኳን በተቃራኒው የሕግ ሕግ ቢኖርም ። የኤድዋርድ ኑዛዜ ወደ ጎን ቀረበ እና ማርያም ንግሥት ሆና ሌዲ ጄን ግሬይን ከስልጣን አወረደች። በማርያም የግዛት ዘመን ኤልዛቤት የፕሮቴስታንት አማፂያንን ትረዳለች ተብላ ተጠርጥራ ለአንድ ዓመት ያህል ታስራለች።
እ.ኤ.አ. ንግሥት ሆና ካደረገችው የመጀመሪያ ተግባሯ አንዱ የእንግሊዝ የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን መመስረት ሲሆን ለዚህም ዋና አስተዳዳሪ ሆነች። ይህ የኤልዛቤት ሃይማኖታዊ ሰፈራ ወደ እንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን መቀየር ነበረበት። ኤልዛቤት አግብታ ወራሽ ታፈራለች ተብሎ ይጠበቅ ነበር; ይሁን እንጂ ብዙ መጠናናት ቢያደርግም እሷ ግን ፈጽሞ አላደረገችም። እሷ በመጨረሻ የመጀመሪያ የአጎቷ ልጅ ሁለት ጊዜ ተወግዷል, ጄምስ ስድስተኛ የስኮትላንድ; ይህም የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት መሠረት ጥሏል። እሷ ቀደም ሲል የጄምስ እናት ማርያም፣ የስኮትላንድ ንግሥት ለእስር እና ግድያ ተጠያቂ ሆና ነበር።
በመንግስት ውስጥ ኤልዛቤት ከአባቷ እና ከፊል ወንድሞቿ እና እህቶቿ የበለጠ ልከኛ ነበረች። አንዱ መፈክሯ "ቪዲዮ እና ታይኦ" ("አየሁ እና ዝም አልኩ") ነበር። በሃይማኖት በአንጻራዊ ሁኔታ ታጋሽ ነበረች እና ስልታዊ ስደትን አስወግዳለች። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በ1570 ዓ.ም ሕገ-ወጥ መሆኗን ካወጁ በኋላ ተገዢዎቿን ከመታዘዝ ከለቀቀች በኋላ፣ በርካታ ሴራዎች ሕይወቷን አደጋ ላይ ጥለውታል፣ ይህ ሁሉ በፍራንሲስ ዋልሲንግሃም በሚመራው የአገልጋዮቿ ሚስጥራዊ አገልግሎት ተሸነፈ። ኤልዛቤት በፈረንሳይ እና በስፔን ዋና ዋና ኃያላን መንግስታት መካከል በመቀያየር በውጭ ጉዳይ ላይ ጠንቃቃ ነበረች። በኔዘርላንድ፣ ፈረንሣይ እና አየርላንድ ውስጥ በርካታ ውጤታማ ያልሆኑ፣ በቂ ሀብት የሌላቸውን ወታደራዊ ዘመቻዎችን በግማሽ ልብ ብቻ ደግፋለች። በ1580ዎቹ አጋማሽ እንግሊዝ ከስፔን ጋር ጦርነትን ማስወገድ አልቻለችም።
እያደገች ስትሄድ ኤልዛቤት በድንግልናዋ ተከበረች። በጊዜው በስዕሎች፣በገጸ-ባህሪያት እና በስነ-ጽሁፍ ይከበር የነበረው የስብዕና አምልኮ በዙሪያዋ ወጣ። የኤልዛቤት ንግስና የኤልዛቤት ዘመን በመባል ይታወቃል። ወቅቱ እንደ ዊልያም ሼክስፒር እና ክሪስቶፈር ማርሎው ባሉ ፀሀፊ ፀሃፊዎች የሚመራ የእንግሊዝ ድራማ በማበብ እና እንደ ፍራንሲስ ድሬክ እና ዋልተር ራሌይ ባሉ የእንግሊዝ የባህር ላይ ጀብደኞች ብቃቶች ታዋቂ ነው። አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች ኤልዛቤትን እንደ አጭር ግልፍተኛ፣ አንዳንዴም ቆራጥ የሆነች ገዥ አድርገው ይገልጻሉ፣ ከእርስዋ ትክክለኛ የዕድል ድርሻ በላይ የምትደሰት። በንግሥናዋ መገባደጃ አካባቢ፣ ተከታታይ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ችግሮች ተወዳጅነቷን አዳከሙ። ነገር ግን፣ ኤልዛቤት እንደ ገሪዝማቲክ ተዋናይ እና ውሾች በህይወት የተረፈች በነበረበት ዘመን መንግስት በተጨናነቀ እና ውስን በሆነበት እና በአጎራባች ሀገራት ያሉ ነገስታት ዙፋኖቻቸውን አደጋ ላይ የሚጥሉ የውስጥ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ነው። ከግማሽ ወንድሞቿ እና እህቶቿ አጭር የግዛት ዘመን በኋላ፣ በዙፋኑ ላይ ያሳለፉት 44 ዓመታት ለመንግሥቱ መረጋጋትን አስገኝተው ብሔራዊ ማንነት እንዲገነዘቡ ረድተዋል።
የመጀመሪያ ህይወት
ኤልዛቤት በሴፕቴምበር 7 1533 በግሪንዊች ቤተመንግስት የተወለደች ሲሆን በአያቶቿ በዮርክ ኤልዛቤት እና በሌዲ ኤልዛቤት ሃዋርድ ስም ተሰየመች። እሷ ከልጅነቷ ለመዳን በጋብቻ የተወለደችው የእንግሊዙ ሄንሪ ስምንተኛ ሁለተኛ ልጅ ነበረች። እናቷ የሄንሪ ሁለተኛ ሚስት አን ቦሊን ነበረች። ስትወለድ ኤልዛቤት የእንግሊዝ ዙፋን ወራሽ ነበረች። ሄንሪ ወንድ ወራሽ ለመምሰል እና የቱዶርን ተተኪነት ለማረጋገጥ በማሰብ ከማርያም እናት ካትሪን ከአራጎን ጋር ትዳሩን ሲያፈርስ ታላቅ እህቷ ማርያም የሕጋዊ ወራሽነት ቦታ አጥታ ነበር። ሴፕቴምበር 1533 እና የእርሷ አምላክ ወላጆች የካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ቶማስ ክራንመር ነበሩ; ሄንሪ ኮርቴናይ, 1 ኛ ማርከስ ኦቭ ኤክሰተር; ኤልዛቤት ስታፎርድ, የኖርፎልክ ዱቼዝ; እና ማርጋሬት ዎቶን፣ ዶዋገር ማርሽዮነስ ኦፍ ዶርሴት። በአጎቷ ጆርጅ ቦሊን ፣ ቪስካውንት ሮችፎርድ በሕፃኑ ላይ በተከበረው ሥነ ሥርዓት ላይ አንድ ሽፋን ተደረገ ። ጆን , የስሌፎርድ 1 ኛ ባሮን ሁሴ; ጌታ ቶማስ ሃዋርድ; እና ዊልያም ሃዋርድ፣ 1ኛ ባሮን ሃዋርድ የኤፊንጋም።
የአራጎን ካትሪን በተፈጥሮ ምክንያት ከሞተች ከአራት ወራት በኋላ እናቷ በግንቦት 19 ቀን 1536 አንገቷ ተቆርጦ ኤልዛቤት የሁለት አመት ከስምንት ወር ልጅ ነበረች። ኤልዛቤት ህጋዊ እንዳልሆነ ተፈርጆ ነበር እና በንጉሣዊው ተተኪነት ቦታዋን ተነፍጓል። ንግሥት ጄን የዙፋኑ አልጋ ወራሽ የሆነው ልጃቸው ኤድዋርድ በተወለደ ብዙም ሳይቆይ በሚቀጥለው ዓመት ሞተች። ኤልሳቤጥ በጥምቀት በዓል ወቅት ክርስቶስን ወይም የጥምቀትን ጨርቅ ይዛ በወንድሟ ቤተሰብ ውስጥ ትቀመጥ ነበር።የኤልዛቤት የመጀመሪያዋ አስተዳዳሪ ማርጋሬት ብራያን “በህይወቴ ውስጥ የማውቀውን ያህል ለሕፃን እና ለሁኔታዎች ጨዋ ነች” በማለት ጽፋለች። ካትሪን ቻምፐርኖውኔ ፣ በኋላ በእሷ የምትታወቅ ፣ ካትሪን “ካት” አሽሊ ያገባች ፣ በ 1537 የኤልዛቤት አስተዳዳሪ ሆና ተሾመች እና በ 1565 እስክትሞት ድረስ የኤልዛቤት ጓደኛ ሆና ቆይታለች። . በ1544 ዊልያም ግሪንዳል ሞግዚቷ በሆነበት ጊዜ ኤልዛቤት እንግሊዘኛ፣ ላቲን እና ጣሊያንኛ መጻፍ ችላለች። ጎበዝ እና ጎበዝ ሞግዚት በሆነችው ስር እሷም በፈረንሳይኛ እና በግሪክኛ እድገት አሳይታለች። በ12 ዓመቷ የእንጀራ እናቷን ካትሪን ፓረርን የሃይማኖት ሥራ ጸሎቶችን ወይም ሜዲቴሽን ከእንግሊዝኛ ወደ ጣሊያንኛ፣ ላቲን እና ፈረንሳይኛ መተርጎም ችላለች፣ ይህም ለአባቷ እንደ አዲስ ዓመት ስጦታ ያቀረበችለትን ነው። በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ከነበረችበት ጊዜ ጀምሮ እና በህይወቷ ሙሉ በላቲን እና በግሪክ የበርካታ ክላሲካል ደራሲያን ስራዎችን ተርጉማለች፣የሲሴሮ ፕሮ ማርሴሎ፣ የቦይቲየስ ደ መጽናኛ ፍልስፍና፣ የፕሉታርክ ድርሰት እና የታሲተስ አናልስን ጨምሮ። በዘመናዊው ዘመን ከነበሩት አራት የእንግሊዝኛ ትርጉሞች መካከል አንዱ የሆነው ከላምቢት ቤተ መንግሥት ቤተ መፃህፍት የታሲተስ ትርጉም በ2019 የኤልዛቤት የራሷ እንደሆነ ተረጋግጧል፣ የእጅ ጽሁፍ እና ወረቀት ላይ ዝርዝር ትንታኔ ከተሰጠ በኋላ።
በ1548 ግሪንዳል ከሞተች በኋላ፣ ኤልዛቤት ትምህርቷን በወንድሟ ኤድዋርድ አስተማሪ ሮጀር አስቻም ፣ መማር መሳተፊያ መሆን እንዳለበት በማመን አዛኝ አስተማሪ ተቀበለች። አሁን ያለው የኤልዛቤት ትምህርት እና ቅድመ-ትምህርት እውቀት በአብዛኛው የመጣው ከአስቻም ትውስታዎች ነው። በ1550 መደበኛ ትምህርቷ ሲያልቅ፣ ኤልዛቤት በትውልዷ ውስጥ ካሉት ምርጥ የተማሩ ሴቶች አንዷ ነበረች። በህይወቷ መጨረሻ ላይ ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ የዌልስ፣ ኮርኒሽ፣ ስኮትላንዳዊ እና አይሪሽ ቋንቋዎችን እንደምትናገር ታምኖ ነበር። የቬኒስ አምባሳደር በ1603 “[እነዚህን] ቋንቋዎች በሚገባ ስለያዘች እያንዳንዳቸው የአፍ መፍቻ ቋንቋዋ እስኪመስሉ ድረስ” ተናግራለች። የታሪክ ምሁሩ ማርክ ስቶይል ምናልባት ኮርኒሽኛን በዊልያም ኪሊግሬው፣ የፕራይቪ ቻምበር ሙሽራ እና በኋላም ቻምበርሊን ኦቭ ዘ ኤክስቼከር እንዳስተማራት ጠቁመዋል።የኤልዛቤት የመጀመሪያዋ አስተዳዳሪ ማርጋሬት ብራያን “በህይወቴ ውስጥ የማውቀውን ያህል ለሕፃን እና ለሁኔታዎች ጨዋ ነች” በማለት ጽፋለች። ካትሪን ቻምፐርኖውኔ ፣ በኋላ በእሷ የምትታወቅ ፣ ካትሪን “ካት” አሽሊ ያገባች ፣ በ 1537 የኤልዛቤት አስተዳዳሪ ሆና ተሾመች እና በ 1565 እስክትሞት ድረስ የኤልዛቤት ጓደኛ ሆና ቆይታለች። . በ1544 ዊልያም ግሪንዳል ሞግዚቷ በሆነበት ጊዜ ኤልዛቤት እንግሊዘኛ፣ ላቲን እና ጣሊያንኛ መጻፍ ችላለች። ጎበዝ እና ጎበዝ ሞግዚት በሆነችው ስር እሷም በፈረንሳይኛ እና በግሪክኛ እድገት አሳይታለች። በ12 ዓመቷ የእንጀራ እናቷን ካትሪን ፓረርን የሃይማኖት ሥራ ጸሎቶችን ወይም ሜዲቴሽን ከእንግሊዝኛ ወደ ጣሊያንኛ፣ ላቲን እና ፈረንሳይኛ መተርጎም ችላለች፣ ይህም ለአባቷ እንደ አዲስ ዓመት ስጦታ ያቀረበችለትን ነው። በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ከነበረችበት ጊዜ ጀምሮ እና በህይወቷ ሙሉ በላቲን እና በግሪክ የበርካታ ክላሲካል ደራሲያን ስራዎችን ተርጉማለች፣የሲሴሮ ፕሮ ማርሴሎ፣ የቦይቲየስ ደ መጽናኛ ፍልስፍና፣ የፕሉታርክ ድርሰት እና የታሲተስ አናልስን ጨምሮ። በዘመናዊው ዘመን ከነበሩት አራት የእንግሊዝኛ ትርጉሞች መካከል አንዱ የሆነው ከላምቢት ቤተ መንግሥት ቤተ መፃህፍት የታሲተስ ትርጉም በ2019 የኤልዛቤት የራሷ እንደሆነ ተረጋግጧል፣ የእጅ ጽሁፍ እና ወረቀት ላይ ዝርዝር ትንታኔ ከተሰጠ በኋላ።
በ1548 ግሪንዳል ከሞተች በኋላ፣ ኤልዛቤት ትምህርቷን በወንድሟ ኤድዋርድ አስተማሪ ሮጀር አስቻም ፣ መማር መሳተፊያ መሆን እንዳለበት በማመን አዛኝ አስተማሪ ተቀበለች። አሁን ያለው የኤልዛቤት ትምህርት እና ቅድመ-ትምህርት እውቀት በአብዛኛው የመጣው ከአስቻም ትውስታዎች ነው። በ1550 መደበኛ ትምህርቷ ሲያልቅ፣ ኤልዛቤት በትውልዷ ውስጥ ካሉት ምርጥ የተማሩ ሴቶች አንዷ ነበረች። በህይወቷ መጨረሻ ላይ ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ የዌልስ፣ ኮርኒሽ፣ ስኮትላንዳዊ እና አይሪሽ ቋንቋዎችን እንደምትናገር ታምኖ ነበር። የቬኒስ አምባሳደር በ1603 “[እነዚህን] ቋንቋዎች በሚገባ ስለያዘች እያንዳንዳቸው የአፍ መፍቻ ቋንቋዋ እስኪመስሉ ድረስ” ተናግራለች። የታሪክ ምሁሩ ማርክ ስቶይል ምናልባት ኮርኒሽኛን በዊልያም ኪሊግሬው፣ የፕራይቪ ቻምበር ሙሽራ እና በኋላም ቻምበርሊን ኦቭ ዘ ኤክስቼከር እንዳስተማራት ጠቁመዋል።
ቶማስ ሲይሞር
ሄንሪ ስምንተኛ በ1547 ሞተ እና የኤልዛቤት ግማሽ ወንድም ኤድዋርድ ስድስተኛ በ9 ዓመቱ ንጉስ ሆነ። የሄንሪ መበለት ካትሪን ፓር ብዙም ሳይቆይ ቶማስ ሲይሞርን፣ የሱዴሊ 1ኛ ባሮን ሲይሞርን፣ የኤድዋርድ ስድስተኛ አጎት እና የሎርድ ጠበቃ ኤድዋርድ ሲይሞርን ወንድም፣ የሱመርሴት 1 መስፍንን አገባች። ጥንዶቹ ኤልዛቤትን ወደ ቼልሲ ቤታቸው ወሰዱ። እዚያም ኤልዛቤት አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች በቀሪው ሕይወቷ እንደነካት የሚያምኑትን የስሜት ቀውስ አጋጥሟታል። ቶማስ ሲሞር ከ14 ዓመቷ ኤልዛቤት ጋር በፈረስ ግልቢያ እና የሌሊት ልብሱን ለብሳ ወደ መኝታ ቤቷ መግባቱን፣ መኳኳትን እና ቂጥ ላይ በጥፊ መምታት ጨምሮ ነበር። ኤልዛቤት በማለዳ ተነሳች እና ያልተፈለገ የጠዋት ጉብኝቶችን ለማስቀረት እራሷን በገረዶች ከበበች። ፓር ባሏን ተገቢ ባልሆነ እንቅስቃሴው ከመጋፈጥ ይልቅ ተቀላቀለች። ሁለት ጊዜ ኤልዛቤትን ስትመታ አብራው ነበር፣ እና አንድ ጊዜ ጥቁር ጋዋንዋን "በሺህ ቁርጥራጮች" ቆርጦ ያዘቻት። ሆኖም፣ ፓር ጥንዶቹን በእቅፍ ካገኛት በኋላ፣ ይህንን ሁኔታ ጨርሳለች። በግንቦት 1548 ኤልዛቤት ተባረረች።
ቶማስ ሲይሞር ግን የንጉሣዊ ቤተሰብን ለመቆጣጠር ማሴሩን ቀጠለ እና የንጉሱን ሰው ገዥ ለመሾም ሞከረ። ፓር በሴፕቴምበር 5 1548 ከወሊድ በኋላ ሲሞት፣ እሷን ለማግባት በማሰብ ትኩረቱን ወደ ኤልዛቤት አድሷል። ሴይሞርን የምትወደው አስተዳዳሪዋ ካት አሽሊ ኤልዛቤት እሱን እንደ ባሏ እንድትወስድ ለማሳመን ፈለገች። እሷም ኤልዛቤትን ለሴይሞር እንድትጽፍ እና “በሀዘኑም እንድታጽናናው” ለማሳመን ሞክራለች፣ ነገር ግን ኤልዛቤት ቶማስ በእንጀራ እናቷ ሞት እንዳሳዘነች ተናግራ መጽናኛ እንደፈለገች ተናግራለች።
በጥር 1549 ሲይሞር ወንድሙን ሱመርሴትን ከተከላካይነት ለማውረድ፣ ሌዲ ጄን ግሬይን ለንጉስ ኤድዋርድ 6ኛ ለማግባት እና ኤልዛቤትን እንደ ራሷ ሚስት ለማድረግ በማሴር ተጠርጥሮ ተይዞ በግንቡ ውስጥ ታስሯል። በ ሃትፊልድ ሃውስ የምትኖረው ኤልዛቤት ምንም አትቀበልም። ግትርነቷ ጠያቂዋን ሰር ሮበርት ቲርዊትን “ጥፋተኛ መሆኗን በፊቷ አይቻለሁ” ሲሉ ዘግበውታል። ሲይሞር መጋቢት 20 ቀን 1549 አንገቱ ተቆረጠ
ንግስና ማርያም
ኤድዋርድ ስድስተኛ በጁላይ 6 1553 በ15 ዓመቱ አረፈ። ኑዛዜው የ1543 የዘውድ ሥልጣንን ቸል በማለት ማርያምን እና ኤልዛቤትን ተተኪነት አገለለ እና በምትኩ የሄንሪ ስምንተኛ ታናሽ እህት የማርያም የልጅ ልጅ የሆነችውን ሌዲ ጄን ግሬይ ወራሽ አድርጎ ገልጿል። ጄን በፕራይቪ ካውንስል ንግሥት ተባለች፣ ነገር ግን ድጋፏ በፍጥነት ፈራረሰ፣ እና ከዘጠኝ ቀናት በኋላ ከስልጣን ተባረረች። እ.ኤ.አ. ኦገስት 3 1553 ማርያም በድል አድራጊነት ወደ ለንደን ገባች፣ ኤልዛቤትም ከጎኗ ነበር።በእህቶች መካከል ያለው የአብሮነት ትርኢት ብዙም አልዘለቀም። አጥባቂ ካቶሊክ የነበረችው ሜሪ ኤልዛቤት የተማረችበትን የፕሮቴስታንት እምነት ለማጥፋት ቆርጣ ተነስታ ሁሉም ሰው በካቶሊክ ቅዳሴ ላይ እንዲገኝ አዘዘች። ኤልዛቤት በውጫዊ ሁኔታ መስማማት ነበረባት። የማርያም የመጀመሪያ ተወዳጅነት በ 1554 የቅዱስ ሮማዊው ንጉሠ ነገሥት ቻርልስ አምስተኛ ልጅ እና ንቁ የካቶሊክ እምነት ተከታይ የሆነውን ስፔናዊውን ፊሊፕ ለማግባት ማቀዷን ስታስታውቅ ነበር። ብስጭት በአገሪቱ በፍጥነት ተሰራጭቷል፣ እና ብዙዎች የማርያምን ሃይማኖታዊ ፖሊሲዎች በመቃወም ኤልዛቤትን እንደ ትኩረት አድርገው ይመለከቱ ነበር።
በጥር እና በፌብሩዋሪ 1554 የዋይት አመጽ ተነሳ; ብዙም ሳይቆይ ታፍኗል። ኤልዛቤት ፍርድ ቤት ቀርቦ ስለእሷ ሚና ተጠይቃለች፣ እና በመጋቢት 18፣ በለንደን ግንብ ውስጥ ታስራለች። ኤልዛቤት ንፁህነቷን አጥብቃ ተቃወመች። ምንም እንኳን ከዓመፀኞቹ ጋር ማሴር ባትችልም አንዳንዶቹ ወደ እርሷ እንደቀረቡ ይታወቃል። የማርያም የቅርብ ታማኝ፣ የቻርልስ አምስተኛ አምባሳደር ሲሞን ሬናርድ፣ ኤልዛቤት በምትኖርበት ጊዜ ዙፋኗ መቼም ቢሆን ደህና አይሆንም ሲል ተከራከረ። እና ሎርድ ቻንስለር እስጢፋኖስ ጋርዲነር፣ ኤልዛቤት ለፍርድ እንድትቀርብ ሠርተዋል። በመንግስት ውስጥ ያሉ የኤልዛቤት ደጋፊዎች፣ ዊልያም ፔጅን፣ 1ኛ ባሮን ፔጅትን ጨምሮ፣ በእሷ ላይ ጠንካራ ማስረጃ በሌለበት ማርያም እህቷን እንድትታደግ አሳመኗት። በምትኩ፣ በግንቦት 22፣ ኤልዛቤት ከግንቡ ወደ ዉድስቶክ ተዛወረች፣ እዚያም በሰር ሄንሪ ቤዲንግፌልድ ክስ ውስጥ ለአንድ አመት ያህል በቤት እስራት ልታሳልፍ ነበር። ህዝቡ በመንገዱ ሁሉ ደስ አሰኝቷታል።እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 17 ቀን 1555 ኤልዛቤት የማርያምን ግልፅ እርግዝና የመጨረሻ ደረጃ ላይ ለመገኘት ወደ ፍርድ ቤት ተጠራች። ማርያምና ልጇ ቢሞቱ ኤልሳቤጥ ንግሥት ትሆናለች፣ነገር ግን ማርያም ጤናማ ልጅ ከወለደች፣ የኤልሳቤጥ ንግሥት የመሆን እድሏ በጣም እያሽቆለቆለ ይሄዳል። ማርያም እንዳልፀነሰች ሲታወቅ ልጅ መውለድ እንደምትችል ማንም አላመነም። የኤልዛቤት ተተኪነት የተረጋገጠ ይመስላል።
በ1556 የስፔን ዙፋን ላይ የወጣው ንጉስ ፊሊፕ አዲሱን የፖለቲካ እውነታ አምኖ አማቱን አሳደገ። በፈረንሳይ ያደገችው እና ከፈረንሳይ ዳፊን ጋር ከታጨችው ከዋነኛው አማራጭ ሜሪ፣ የስኮትላንዳዊቷ ንግሥት የተሻለ አጋር ነበረች። በ1558 ሚስቱ ስትታመም ንጉስ ፊልጶስ ከኤልሳቤጥ ጋር ለመመካከር የፌሪያን ግዛት ላከ። ይህ ቃለ ምልልስ የተካሄደው በጥቅምት 1555 ለመኖር በተመለሰችው ሃትፊልድ ሃውስ ነው። በጥቅምት 1558 ኤልዛቤት ለመንግሥቷ እቅድ አውጥታ ነበር። ማርያም ህዳር 6 ቀን 1558 ኤልዛቤትን እንደ ወራሽ አወቀች፣ እና ኤልሳቤጥ ንግሥት ሆና በኖቬምበር 17 ማርያም ስትሞት
ኤልሳቤጥ በ25 ዓመቷ ንግሥት ሆነች፣ እና ፍላጎቷን ለምክር ቤትዋ እና ሌሎች ጓደኞቿን ታማኝ ለመሆን ወደ ሃትፊልድ ለመጡት ተናገረች። ንግግሩ የሉዓላዊውን "ሁለት አካላት" የመካከለኛው ዘመን የፖለቲካ ሥነ-መለኮትን የተቀበለችበትን የመጀመሪያ ዘገባ ይዟል፡ አካል ተፈጥሯዊ እና ፖለቲካዊ፡
ጌቶቼ፣ የተፈጥሮ ህግ ለእህቴ እንዳዝን ያነሳሳኛል; በእኔ ላይ የወረደው ሸክም አስገረመኝ፣ ነገር ግን እኔ የእግዚአብሔር ፍጡር እንደ ሆንኩ በመቁጠር፣ ሹመቱን እንድፈጽም የተሾምኩ፣ ለዚያም እሺ እሆናለሁ፣ አገልጋይ ለመሆን የጸጋውን እርዳታ ለማግኘት ከልቤ እመኛለሁ። በዚህ ቢሮ ውስጥ ስላለው ሰማያዊ ፈቃዱ አሁን ለእኔ የተሰጠኝ። እኔ በተፈጥሮ አንድ አካል እንደ ሆንሁ፥ ምንም እንኳን በእርሱ ፈቃድ አንድ የፖለቲካ አካል ለመምራት፥ ሁላችሁንም ... በእኔ ፍርድ እናንተም ከእናንተ አገልግሎት ጋር በመልካም ሒሳብ እንድትሰጡኝ ረዳቱ ትሆኑ ዘንድ እፈቅዳለሁ። ለልዑል እግዚአብሔር እና በምድር ላይ ላሉ ዘመዶቻችን አንዳንድ መጽናናትን ይተውልን። ሁሉንም ድርጊቶቼን በጥሩ ምክር እና ምክር መምራት ማለቴ ነው።
በዘውድ ሥርዓቱ ዋዜማ የድል ግስጋሴዋ በከተማዋ ሲታመስ፣ በዜጎች በሙሉ ልቧ የተቀበሏት እና በንግግሮች እና ትርኢቶች የተቀበሏት እጅግ በጣም ጠንካራ የፕሮቴስታንት ጣእም ያለው ነው። የኤልዛቤት ግልጽ እና የጸጋ ምላሽ ሰጪዎች “በድንቅ የተደፈሩ” ተመልካቾችን እንድትወድ አድርጓታል። በማግስቱ፣ ጥር 15 ቀን 1559፣ በኮከብ ቆጣሪዋ ጆን ዲ፣ ኤልዛቤት የተመረጠችበት ቀን በዌስትሚኒስተር አቢ በካርሊል የካቶሊክ ጳጳስ ኦወን ኦግሌቶርፕ ዘውድ ተቀዳጀች። ከዚያም ሰዎቹ እንዲቀበሏት ቀረበች፣ በሚሰሙት የአካል ክፍሎች፣ ፊፋ፣ ጥሩምባ፣ ከበሮ እና ደወሎች መካከል። ምንም እንኳን ኤልዛቤት በእንግሊዝ ንግሥት ሆና እንኳን ደህና መጣችሁ ብትልም፣ ሀገሪቱ አሁንም በሃገር ውስጥ እና በባህር ማዶ የሚደርሰው የካቶሊክ ስጋት፣ እንዲሁም ማንን እንደምታገባ በመምረጡ ስጋት ላይ ነች።
የቤተክርስቲያን ሰፈር
የኤልዛቤት የግል ሃይማኖታዊ እምነቶች በሊቃውንት ብዙ ክርክር ተደርጎባቸዋል። እሷ ፕሮቴስታንት ነበረች፣ ነገር ግን የካቶሊክ ምልክቶችን (እንደ ስቅለት ያሉ) ትይዛለች፣ እና የፕሮቴስታንት ቁልፍ የሆነውን እምነት በመቃወም የስብከትን ሚና አሳንሳለች። ኤልዛቤት እና አማካሪዎቿ በመናፍቃን እንግሊዝ ላይ የካቶሊክ የመስቀል ጦርነት እንደሚያስፈራራ ተገነዘቡ። ስለዚህ ንግስቲቱ የእንግሊዝ ፕሮቴስታንቶችን ፍላጎት እየተናገረች ካቶሊኮችን በእጅጉ የማያስከፋ ፕሮቴስታንት መፍትሄ ፈለገች፣ነገር ግን ሰፊ ተሃድሶ እንዲደረግ የሚገፋፉትን ፒዩሪታኖችን አትታገስም። በዚህ ምክንያት የ1559 ፓርላማ በኤድዋርድ ስድስተኛ ፕሮቴስታንት ሰፈር ላይ የተመሰረተ ቤተክርስትያን ንጉሱ ራስ ሆኖ ነገር ግን እንደ አልባሳት ያሉ ብዙ የካቶሊክ አካላት ላሉት ቤተክርስቲያን ህግ ማውጣት ጀመረ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀሳቦቹን አጥብቆ ደግፏል፣ ነገር ግን የላዕላይነት ረቂቅ ህግ በጌቶች ምክር ቤት በተለይም ከጳጳሳት ተቃውሞ ገጠመው። የካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ጨምሮ ብዙ ጳጳሳት በወቅቱ ክፍት በመሆናቸው ኤልዛቤት እድለኛ ነበረች። ቢሆንም፣ ብዙዎች አንዲት ሴት ለመሸከም ተቀባይነት እንደሌለው በማሰብ ኤልዛቤት ይበልጥ አከራካሪ ከሆነው የበላይ አለቃ ይልቅ የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ገዥ የሚለውን ማዕረግ ለመቀበል ተገድዳለች። በግንቦት 8 ቀን 1559 አዲሱ የበላይነት ህግ ህግ ሆነ። ሁሉም የመንግስት ባለስልጣናት ለንጉሱ የበላይ ገዥ በመሆን ታማኝነታቸውን መማል ወይም ከስልጣን መባረር አለባቸው። በማርያም ይፈጸም የነበረው ተቃዋሚዎች ስደት እንዳይደገም የኑፋቄ ሕጎቹ ተሽረዋል። በተመሳሳይ ጊዜ፣ ቤተ ክርስቲያን መገኘትን እና የ1552 የጋራ ጸሎት መጽሐፍን በተሻሻለው እትም መጠቀምን የሚያስገድድ አዲስ የወጥነት ሕግ ወጣ፣ ምንም እንኳን በዳግም መቀበል ወይም አለመገኘት እና አለመከተል ቅጣቶች ጽንፍ ባይሆኑም .
የጋብቻ ጥያቄ
ከኤሊዛቤት ንግሥና መጀመሪያ ጀምሮ ታገባለች ተብሎ ይጠበቅ ነበር, እና ጥያቄው ለማን ተነሳ. ብዙ ቅናሾችን ብታገኝም አላገባችም እና ልጅ አልባ ሆና ቀረች; ለዚህ ምክንያቱ ግልጽ አይደለም. የታሪክ ተመራማሪዎች ቶማስ ሲሞር ከፆታዊ ግንኙነት እንዳቋረጠ ይገምታሉ። ሃምሳ እስክትሆን ድረስ ብዙ ፈላጊዎችን አስባለች። የመጨረሻ የፍቅር ጓደኝነት የ22 ዓመቷ የአንጁው መስፍን ፍራንሲስ ጋር ነበር። በስፔናዊው ንጉስ ፊሊፕ 2ኛ እጅ እንደተጫወተችው እህቷ ስልጣኗን ሊያጣ እንደሚችል ስጋት ውስጥ ገብታለች፣ ትዳር ወራሽ የመሆን እድል ፈጠረላት። ሆኖም የባል ምርጫ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት አልፎ ተርፎም ዓመፅ ያስነሳል።
ሮበርት ዱድሊ
በ1559 የጸደይ ወራት፣ ኤልዛቤት ከልጅነት ጓደኛዋ ከሮበርት ዱድሊ ጋር ፍቅር እንደነበራት ግልጽ ሆነ። ሚስቱ ኤሚ ሮብሳርት "በአንደኛው ጡቷ ላይ በሚታመም በሽታ" እየተሰቃየች እንደነበረ እና ንግስቲቱ ሚስቱ ብትሞት ዱድሊን ማግባት እንደምትፈልግ ተነግሯል። እጅ; ትዕግሥት የለሽ መልእክቶቻቸው ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ አሳፋሪ ንግግር ውስጥ ተሰማርተው እና ከምትወደው ጋር ጋብቻ በእንግሊዝ ውስጥ ተቀባይነት እንደሌለው ዘግበዋል: - “በእሱ እና በእሷ ላይ በቁጣ የማይጮህ ሰው የለም… እሷ ከተወደዱ በስተቀር ማንንም አታገባም ። ሮበርት." ኤሚ ዱድሊ በሴፕቴምበር 1560 ከደረጃ በረራ ላይ በመውደቁ ሞተች እና ምንም እንኳን የምርመራ ተቆጣጣሪው የአደጋ ምርመራ ቢያገኝም ፣ ብዙ ሰዎች ባሏ ንግሥቲቱን እንዲያገባ ሲል ሞቷን አመቻችቷል ብለው ጠረጠሩት። ኤልዛቤት ዱድሊንን ለተወሰነ ጊዜ ለማግባት አስባ ነበር። ሆኖም ዊልያም ሴሲል፣ ኒኮላስ ትሮክሞርተን እና አንዳንድ ወግ አጥባቂ እኩዮቻቸው አለመስማማታቸውን በማያሻማ መልኩ ግልጽ አድርገዋል። ጋብቻው ከተፈጸመ ባላባቶች እንደሚነሱ የሚነገር ወሬም ነበር።
ሮበርት ዱድሊ ለንግስት ተብለው ከሚታሰቡ ሌሎች የጋብቻ እጩዎች መካከል፣ ለሌላ አስርት ዓመታት ያህል እንደ እጩ መቆጠር ቀጠለ። ኤልዛቤት በፍቅሩ በጣም ትቀና ነበር፣ ምንም እንኳን እሷ ራሷ ልታገባው ባትፈልግም ነበር። እ.ኤ.አ. በ1564 ዱድሊንን እንደ የሌስተር አርል አሳደገችው። በመጨረሻም በ 1578 እንደገና አገባ, ንግሥቲቱ ለባለቤቱ ሌቲስ ኖሊስ ተደጋጋሚ ብስጭት እና የዕድሜ ልክ ጥላቻ ምላሽ ሰጥታለች. አሁንም፣ ዱድሊ የታሪክ ምሁር የሆኑት ሱዛን ዶራን ሁኔታውን እንደገለፁት ሁል ጊዜ “[የኤልዛቤት] ስሜታዊ ሕይወት መሃል ላይ ይቆዩ ነበር። እ.ኤ.አ. በ1588 የስፔን ጦር ከተሸነፈ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ሞተ። ኤልዛቤት ከሞተች በኋላ፣ በጣም ከግል ንብረቶቿ መካከል ከእርሱ የተላከ ማስታወሻ ተገኘች፤ በእጇ በጻፈችው ጽሑፍ ላይ “የመጨረሻው ደብዳቤ”
የውጭ አገር እጩዎች
የጋብቻ ድርድር በኤልዛቤት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ውስጥ ቁልፍ አካል ነበር። በ1559 መጀመሪያ ላይ የግማሽ እህቷ ሚስት የነበረችውን የፊሊፕን እጅ አልተቀበለችም ፣ ግን ለብዙ ዓመታት የስዊድን ንጉስ ኤሪክ አሥራ አራተኛውን ሀሳብ አቀረበች። ቀደም ሲል በኤልዛቤት ሕይወት ውስጥ ለእሷ የዴንማርክ ግጥሚያ ውይይት ተደርጎበታል ። ሄንሪ ስምንተኛ በ1545 ከዴንማርክ ልዑል አዶልፍ ፣የሆልስታይን-ጎቶርፕ መስፍን ጋር እና ኤድዋርድ ሲይሞር ፣የሱመርሴት መስፍን ከፕሪንስ ፍሬድሪክ (በኋላ ፍሬደሪክ 2) ከበርካታ አመታት በኋላ እንዲጋቡ ሀሳብ አቅርበው ነበር ፣ነገር ግን ድርድሩ በ1551 ቀነሰ እ.ኤ.አ. በ1559 አካባቢ የዳኖ-እንግሊዘኛ ፕሮቴስታንት ህብረት ታሳቢ ተደርጎ ነበር፣ እና የስዊድንን ሃሳብ ለመቃወም ንጉስ ፍሬድሪክ በ1559 መጨረሻ ላይ ለኤልዛቤት ጥያቄ አቀረበ።ለብዙ አመታት እሷም የፊሊፕን የአጎት ልጅ ቻርልስ ፣ የኦስትሪያውን አርክዱክን ለማግባት በቁም ነገር ተደራድራለች። እ.ኤ.አ. በ 1569 ከሀብስበርግ ጋር ያለው ግንኙነት ተበላሽቷል ። ኤልዛቤት በተራው ከሁለት የፈረንሣይ ቫሎይስ መኳንንት ጋር ጋብቻን አስባ ነበር ፣ በመጀመሪያ ሄንሪ ፣ የአንጁዱ መስፍን ፣ እና ከ 1572 እስከ 1581 ወንድሙ ፍራንሲስ ፣ የአንጁው መስፍን ፣ የቀድሞ የአሌንኮን መስፍን። ይህ የመጨረሻው ሀሳብ በደቡባዊ ኔዘርላንድ የስፔን ቁጥጥር ላይ ከታቀደው ጥምረት ጋር የተያያዘ ነው። ኤልዛቤት የፍቅር ጓደኝነትን ለተወሰነ ጊዜ በቁም ነገር የወሰደችው እና ፍራንሲስ የላከላትን የእንቁራሪት ቅርጽ ያለው የጆሮ ጌጥ ለብሳለች።
እ.ኤ.አ. በ 1563 ኤልዛቤት የንጉሠ ነገሥቱን ልዑክ “የተፈጥሮዬን ዝንባሌ ከተከተልኩ ይህ ነው-ለማኝ ሴት እና ነጠላ ፣ ከንግሥት እና ከጋብቻ ይልቅ። በዓመቱ በኋላ፣ ኤልዛቤት በፈንጣጣ መታመሟን ተከትሎ፣ የመተካካት ጥያቄ በፓርላማ ውስጥ የጦፈ ጉዳይ ሆነ። አባላት ንግስቲቱ እንድትጋባ ወይም ወራሽ እንድትሰይም አሳስቧታል፣ ስትሞት የእርስ በርስ ጦርነትን ለመከላከል። እሷም ለማድረግ ፈቃደኛ አልሆነችም። በ 1566 ታክስ ለመጨመር ድጋፉን እስክትፈልግ ድረስ እንደገና ያልተሰበሰበውን ፓርላማ በኤፕሪል አነሳች ።
ከዚህ ቀደም ለማግባት ቃል ገብታ፣ ሥርዓት ለሌለው ቤት እንዲህ አለች፡-ለክብር ስል በአደባባይ የተነገረውን የልዑል ቃል በፍጹም አላፈርስም። ስለዚህም ደግሜ እላለሁ፣ በተመቸኝ መጠን አገባለሁ፣ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ላገባው የምፈልገውን ወይም ራሴን ካልወሰደው፣ ወይም ሌላ ታላቅ ነገር ቢፈጠር።
እ.ኤ.አ. በ 1570 በመንግስት ውስጥ ያሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኤልዛቤት በጭራሽ አታገባም ወይም ተተኪ አትሰይም ብለው በግል ተቀበሉ። ዊልያም ሴሲል ቀድሞውንም ለተከታታይ ችግር መፍትሄዎችን እየፈለገ ነበር። ኤልዛቤት ባለማግባቷ ብዙ ጊዜ በኃላፊነት የጎደለው ድርጊት ትከሰሳለች። ዝምታዋ ግን የራሷን የፖለቲካ ደህንነት አጠንክሯል፡ ወራሽ ብትሰይም ዙፋንዋ ለየግል ግልበጣ እንደሚጋለጥ ታውቃለች። "እንደ እኔ ሁለተኛ ሰው" በቀድሞዋ ላይ የሴራዎች ትኩረት የተደረገበትን መንገድ አስታውሳለች.
የኤልዛቤት ያላገባች ሁኔታ ከድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ የድንግልና አምልኮን አነሳሳ። በግጥም እና በቁም ሥዕላዊ መግለጫ፣ እርሷ በድንግልና፣ አምላክ ወይም ሁለቱም ተመስላለች እንጂ እንደ መደበኛ ሴት አይታይም። መጀመሪያ ላይ ኤልሳቤጥ ብቻ የድንግልናዋን መልካም ነገር አደረገች፡ በ1559 ለጋራ ማህበረሰብ እንዲህ አለች፡- “እናም፣ በመጨረሻ፣ ይህ ይበቃኛል፣ የእብነበረድ ድንጋይ ንግሥት እንዲህ ያለ ጊዜ እንደነገሠች ያስታውቃል። በድንግልና ኖረች ሞተችም። በኋላ፣ ገጣሚዎች እና ጸሃፊዎች ጭብጡን አነሱ እና ኤልዛቤትን ከፍ ያደረገችውን ምስል አዘጋጁ። እ.ኤ.አ. በ 1578 ለድንግል የተሰጡ የህዝብ ውለታዎች ንግሥቲቱ ከአሌንኮን መስፍን ጋር ባደረገችው የጋብቻ ድርድር ላይ የተቃውሞ ኮድ ማረጋገጫ ሆኖ አገልግሏል። በመጨረሻ፣ ኤልዛቤት በመለኮታዊ ጥበቃ ስር ከግዛቷ እና ከተገዥዎቿ ጋር እንዳገባች አጥብቃ ትጠይቃለች። በ 1599 ስለ "ባሎቼ ሁሉ, የእኔ ጥሩ ሰዎች" ተናገረች.ይህ የድንግልና ይገባኛል ጥያቄ በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት አላገኘም። ካቶሊኮች ኤልዛቤትን ከሰውነቷ ጋር በምሳሌያዊ ሁኔታ የሚያረክሰውን “ርኩስ ፍትወት” ውስጥ ገብታለች ሲሉ ከሰሷት። ፈረንሳዊው ሄንሪ አራተኛ የአውሮፓ ታላላቅ ጥያቄዎች አንዱ "ንግሥት ኤልሳቤጥ ገረድ ነበረች ወይስ አይደለም" የሚለው ነው።
የኤልዛቤት ድንግልና ጥያቄን በተመለከተ ዋናው ጉዳይ ንግስቲቱ ከሮበርት ዱድሊ ጋር የነበራትን የፍቅር ግንኙነት ፈጽማለች ወይ የሚለው ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1559 የዱድሊ መኝታ ቤቶች ከራሷ አፓርታማዎች አጠገብ እንዲዛወሩ አደረገች። እ.ኤ.አ. በ1561 ሰውነቷ እንዲያብጥ ባደረገው ህመም ሚስጥራዊ በሆነ መልኩ የአልጋ ቁራኛ ሆናለች።
በ1587 ራሱን አርተር ዱድሌይ ብሎ የሚጠራ ወጣት በስፔን የባህር ዳርቻ በሰላዩ ተጠርጥሮ ተይዟል። ሰውዬው የኤልዛቤት እና የሮበርት ዱድሌይ ህገወጥ ልጅ ነኝ ሲል በ1561 በህመም ወቅት ከልደቱ ጋር የሚስማማ እድሜው ነበር። ለምርመራ ወደ ማድሪድ ተወሰደ፣ እዚያም ወደ ስፔን በግዞት በተወሰደው የካቶሊክ መኳንንት እና የንጉስ ፊሊፕ 2ኛ ፀሃፊ በሆነው ፍራንሲስ ኢንግልፊልድ ተመርምሯል። አርተር በንጉሣዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ ከተወለደበት ጊዜ አንስቶ ወደ ስፔን እስከሚደርስበት ጊዜ ድረስ የሕይወቱ ታሪክ መሆኑን የሚገልጹ ሦስት ደብዳቤዎች ቃለ-መጠይቁን የሚገልጹ ሦስት ደብዳቤዎች ዛሬ አሉ። ሆኖም ይህ ስፔናዊውን ማሳመን አልቻለም፡ ኢንግፊልድ የአርተር “አሁን ያለው የይገባኛል ጥያቄ ምንም አይደለም” ሲል ለንጉስ ፊሊፕ አምኗል፣ ነገር ግን “እንዲሸሽ መፍቀድ የለበትም፣ ነገር ግን በጣም ደህንነቱ የተጠበቀ ነው” ሲል ጠቁሟል። ንጉሱ ተስማምተው ነበር፣ እና አርተር ከአሁን በኋላ አልተሰማም። የዘመናችን ስኮላርሺፕ የታሪኩን መሰረታዊ መነሻ “የማይቻል” በማለት ውድቅ አድርጎታል እና የኤልዛቤት ህይወት በዘመኗ በነበሩ ሰዎች በጣም በቅርብ ይታይ ስለነበር እርግዝናን መደበቅ አልቻለችም ሲል ተናግሯል።
የስኮትስ ንግሥት ማርያም
በስኮትላንድ ላይ የኤሊዛቤት የመጀመሪያ ፖሊሲ የፈረንሳይን መኖር መቃወም ነበር። ፈረንሳዮች እንግሊዝን ለመውረር እንዳቀዱ እና የካቶሊክ ዘመድ የሆነችውን የስኮትላንድ ንግሥት ማርያምን በዙፋኑ ላይ እንዳስቀምጧት ፈራች። ሜሪ የሄንሪ ስምንተኛ ታላቅ እህት ማርጋሬት የልጅ ልጅ በመሆኗ የእንግሊዝ ዘውድ ወራሽ እንደሆነች ብዙዎች ይቆጠሩ ነበር። ማርያም “የቅርብ ዘመድ ያላት ሴት” በመሆኗ በኩራት ተናግራለች። ኤልዛቤት የፕሮቴስታንት አማፂያንን ለመርዳት ወደ ስኮትላንድ ጦር እንድትልክ ተገፋፍታ ነበር፣ እና ዘመቻው የተሳሳተ ቢሆንም፣ በጁላይ 1560 የወጣው የኤድንበርግ ስምምነት የፈረንሳይን ስጋት በሰሜን በኩል አስወገደ።[] ሜሪ በ1561 ወደ ስኮትላንድ ስትመለስ በስልጣን ላይ ሀገሪቱ የተመሰረተች የፕሮቴስታንት ቤተክርስትያን ነበራት እና የምትመራው በኤሊዛቤት ድጋፍ በፕሮቴስታንት መኳንንት ምክር ቤት ነበር። ማርያም ስምምነቱን ለማጽደቅ ፈቃደኛ አልሆነችም።
እ.ኤ.አ. በ 1563 ኤልዛቤት የራሷን ፈላጊ ሮበርት ዱድሊን ለማርያም ባል እንድትሆን አቀረበች ፣ የሚመለከታቸውን ሁለት ሰዎች ሳትጠይቅ ። ሁለቱም ደስተኞች አልነበሩም እና በ 1565 ሜሪ ሄንሪ ስቱዋርትን ጌታ ዳርንሌይን አገባች, እሱም የራሱን የእንግሊዝ ዙፋን ይዞ ነበር. ጋብቻው ድሉን ለስኮትላንድ ፕሮቴስታንቶች እና ለኤልዛቤት ካስረከበው በማርያም ከተከሰቱት ተከታታይ የፍርድ ስህተቶች የመጀመሪያው ነው። ዳርንሌይ በፍጥነት ተወዳጅነት አጥቷል እና በየካቲት 1567 በሴረኞች ተገደለ፣ በእርግጠኝነት በጄምስ ሄፕበርን ፣ 4ኛ አርል የ ። ብዙም ሳይቆይ፣ በሜይ 15፣ 1567፣ ሜሪ ቦዝዌልን አገባች፣ ይህም ባሏን በመግደል ላይ ተካፋይ እንደነበረች ጥርጣሬን አስነስቷል። ኤልሳቤጥ ማርያምን ስለ ጋብቻ ነገረቻት፣ እንዲህ በማለት ጻፈቻት።
እንደዚህ አይነት ጉዳይ ለማግባት ከመቸኮል ይልቅ ለክብርሽ ከዚህ የከፋ ምርጫ እንዴት ሊደረግ ቻለ። እኛ በውሸት እናምናለን።
እነዚህ ክስተቶች በሎክ ሌቨን ካስት ለማርያም ሽንፈት እና እስራት በፍጥነት አመሩ። የስኮትላንድ ጌቶች በሰኔ 1566 የተወለደውን ልጇን ጄምስ ስድስተኛን እንድትገልፅ አስገደዷት። ጄምስ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ሆኖ እንዲያድግ ወደ ስተርሊንግ ካስል ተወሰደ። ሜሪ በ1568 ከሎክ ሌቨን አመለጠች ነገርግን ሌላ ሽንፈት ካደረገች በኋላ ድንበሩን አቋርጣ ወደ እንግሊዝ ሸሸች። የኤልዛቤት የመጀመሪያዋ ደመ ነፍስ አብረዋት የነበሩትን ንጉሣዊቷን መመለስ ነበር; ግን እሷ እና ምክር ቤቷ በምትኩ በደህና መጫወትን መረጡ። ማርያምን ከእንግሊዝ ጦር ጋር ወደ ስኮትላንድ ከመመለስ ወይም ወደ ፈረንሣይና የእንግሊዝ ካቶሊካዊ ጠላቶች ከመላክ ይልቅ እንግሊዝ ውስጥ አስሯት ለቀጣዮቹ አሥራ ዘጠኝ ዓመታት ታስራለች።
የካቶሊክ ምክንያት
ማርያም ብዙም ሳይቆይ የአመፅ ትኩረት ሆነች። በ 1569 በሰሜን ውስጥ ትልቅ የካቶሊክ እምነት ተከታይ ነበር; ግቡ ማርያምን ነፃ ማውጣት፣ የኖርፎልክ 4ኛ መስፍን ከቶማስ ሃዋርድ ጋር ማግባት እና በእንግሊዝ ዙፋን ላይ ማስቀመጥ ነበር። አማፂዎቹ ከተሸነፉ በኋላ ከ750 በላይ የሚሆኑት በኤልዛቤት ትእዛዝ ተገድለዋል። ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ አምስተኛ በ1570 ዓ.ም ረጅናንስ በኤክሴልሲስ የተሰኘ በሬ አወጡ፣ እሱም “ኤልዛቤት፣ የመሰለችው የእንግሊዝ ንግሥት እና የወንጀል አገልጋይ” እንድትገለል እና መናፍቅ እንደሆነች በማወጅ ሁሉንም ፈታለች። ለእሷ ከማንኛውም ታማኝነት ተገዢዎች ። ትእዛዞቿን የሚታዘዙ ካቶሊኮች የመገለል ዛቻ ደርሶባቸዋል። የጳጳሱ በሬ በፓርላማ በካቶሊኮች ላይ የሕግ አውጭ እርምጃዎችን ቀስቅሷል፣ ሆኖም ግን በኤልዛቤት ጣልቃ ገብነት የተቀነሰው። እ.ኤ.አ. በ 1581 የእንግሊዘኛ ትምህርቶችን ወደ ኤልዛቤት ያላቸውን ታማኝነት ለማንሳት "ዓላማ" ወደ ካቶሊካዊነት መለወጥ የሞት ቅጣትን የሚያስከትል ክህደት ፈፅሞ ነበር. ከ 1570 ዎቹ ጀምሮ ከአህጉራዊ ሴሚናሮች የተውጣጡ ሚስዮናውያን ካህናት በድብቅ ወደ እንግሊዝ ሄዱ "የእንግሊዝ ዳግመኛ መመለሻ" ምክንያት. ብዙዎች ተገድለዋል፣ የሰማዕትነት አምልኮን በመፍጠር።
በኤክሴልሲስ የሚገኘው ሬጋንስ እንግሊዛዊ ካቶሊኮች ማርያምን እንደ ህጋዊ የእንግሊዝ ሉዓላዊ ገዢ እንድትመለከቱ ጠንካራ ማበረታቻ ሰጥቷቸዋል። ማርያም እሷን በእንግሊዝ ዙፋን ላይ ለማስቀመጥ ስለ እያንዳንዱ የካቶሊክ ሴራ አልተነገራቸውም ፣ ግን በ 1571 ከሪዶልፊ ሴራ (የማርያም ፈላጊ ፣ የኖርፎልክ መስፍን ፣ ጭንቅላቱን እንዲያጣ ያደረገው) በ 1586 ወደ ባቢንግተን ሴራ ፣ የኤልዛቤት የስለላ አስተዳዳሪ ሰር ፍራንሲስ ዋልሲንግሃም እና የንጉሣዊው ምክር ቤት በእሷ ላይ ክስ አሰባሰቡ። በመጀመሪያ ኤልሳቤጥ የማርያምን ሞት ጥሪ ተቃወመች። እ.ኤ.አ. በ 1586 መገባደጃ ላይ በባቢንግተን ሴራ ወቅት በተፃፉ ደብዳቤዎች ማስረጃ ላይ የማርያምን ችሎት እና ግድያ እንድትቀበል ተገፋፍታለች። የኤልዛቤት የቅጣት አዋጅ ማወጁ “የተነገረላት ማርያም፣ የአንድ ዘውድ ባለቤት መስሎ፣ በዛው ግዛት ውስጥ የተለያዩ ነገሮችን ዞራ በንጉሣዊው ሰውነታችን ላይ የሚደርሰውን ጉዳት፣ ሞት እና ጥፋት አስባ ነበር። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. ግድያው ከተፈጸመ በኋላ ኤልዛቤት የተፈረመውን የግድያ ማዘዣ እንዲላክ አላሰበችም ስትል ፀሐፊዋን ዊልያም ዴቪሰንን ሳታውቅ ተግባራዊ አድርጋለች በማለት ወቅሳለች። የኤልዛቤት ፀፀት ቅንነት እና የፍርድ ቤት ማዘዣውን ለማዘግየት ፈለገች ወይስ አልፈለገችም በዘመኗም ሆነ በኋላ የታሪክ ፀሃፊዎች ጥያቄ ውስጥ ገብተዋል።
ጦርነቶች እና የባህር ማዶ ንግድ
የኤልዛቤት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በአብዛኛው መከላከያ ነበር። ለየት ያለ ሁኔታ ከጥቅምት 1562 እስከ ሰኔ 1563 ድረስ የእንግሊዝ የሌሃቭር ይዞታ ነበር፣ ይህ የሆነው የኤልዛቤት ሁጉኖት አጋሮች ከካቶሊኮች ጋር በመተባበር ወደቡን መልሶ ለመያዝ ባደረገ ጊዜ ሳይሳካ ቀርቷል። የኤልዛቤት አላማ በጥር 1558 በፈረንሣይ የተሸነፈችውን ሌሃቭርን ወደ ካሌ መቀየር ነበር። ይህ ከስፔን ጋር በተደረገው ጦርነት ፍሬያማ የሆነ ሲሆን 80 በመቶው የተካሄደው በባህር ላይ ነው። እ.ኤ.አ. ከ1577 እስከ 1580 ድረስ ፍራንሲስ ድሬክን ከዞረ በኋላ ፈረሰች እና በስፔን ወደቦች እና መርከቦች ላይ ባደረገው ወረራ ታዋቂነትን አገኘ። የባህር ላይ ዝርፊያ እና ራስን ማበልጸግ ንግሥቲቱ ብዙም ቁጥጥር ያልነበራቸው የኤሊዛቤት የባህር ተጓዦችን አባረራቸው።
በ1562-1563 ሌሃቭር ከተያዘች እና ከጠፋች በኋላ ኤልዛቤት እስከ 1585 ድረስ የእንግሊዝ ጦር በላከችበት ወቅት በአህጉሪቱ ወታደራዊ ጉዞዎችን ከማድረግ ተቆጥባ የፕሮቴስታንት ደች ሆላንድን በፊሊፕ ላይ ያመፀው ።ይህም በ 1584 የንግስቲቱ አጋሮች ዊልያም ሞትን ተከትሎ ነበር ። ዝምተኛው፣ የብርቱካን ልዑል፣ እና የአንጁው መስፍን፣ እና ተከታታይ የደች ከተማዎች ለስፔን ኔዘርላንድስ የፊልጶስ ገዥ የፓርማ መስፍን አሌክሳንደር ፋርኔስ መሰጠታቸው። በታህሳስ 1584 በፊሊፕ እና በፈረንሣይ ካቶሊካዊ ሊግ በጆይንቪል መካከል የተደረገ ጥምረት የአንጁ ወንድም ፈረንሣዊው ሄንሪ ሳልሳዊ የስፔን የኔዘርላንድን የበላይነት ለመቃወም ያለውን አቅም አሳጣው። በተጨማሪም የካቶሊክ ሊግ ጠንካራ በሆነበት በፈረንሳይ የባህር ዳርቻ ላይ የስፓኒሽ ተጽእኖን አስፋፍቷል እና እንግሊዝን ለወረራ አጋልጧል። እ.ኤ.አ. በ1585 የበጋው ወቅት አንትወርፕ የፓርማ መስፍን ከበባ በእንግሊዘኛ እና በ ደች. ውጤቱም ኤልዛቤት ለደች ወታደራዊ ድጋፍ ለመስጠት ቃል የገባችበት የነሀሴ 1585 የኖንሱች ስምምነት ነበር። ስምምነቱ እ.ኤ.አ. በ 1604 እስከ ለንደን ስምምነት ድረስ የዘለቀውን የአንግሎ-ስፓኒሽ ጦርነት መጀመሪያ ያመላክታል ።
ጉዞውን የተመራው በኤልዛቤት የቀድሞ ፈላጊ፣ የሌስተር አርል ነው። ኤልዛቤት ከጅምሩ ይህን ተግባር አልደገፈችም። ሌስተር ሆላንድ በገባ በቀናት ውስጥ ከስፔን ጋር ሚስጥራዊ የሰላም ድርድር ስትጀምር ላዩን ላይ ያሉትን ደች በእንግሊዝ ጦር ለመደገፍ የነበራት ስልቷ ከሌስተር ጋር ግጭት ውስጥ መግባት ነበረበት። ንቁ ዘመቻ. ኤልዛቤት በበኩሏ "ከጠላት ጋር ምንም አይነት ወሳኝ እርምጃ እንዳይወስድ" ትፈልጋለች። ከኔዘርላንድስ ጄኔራል የጠቅላይ ገዥነት ቦታ በመቀበል ኤልዛቤትን አስቆጣች። ኤልዛቤት ይህንን የኔዘርላንድስ ሉዓላዊነት እንድትቀበል ለማስገደድ የተደረገ የደች ተንኮል አድርጋ ተመለከተች፣ይህም እስካሁን ድረስ ሁሌም ውድቅ አድርጋ ነበር። ለሌስተር ጻፈች፡-
ከዚች ምድር ርዕሰ ጉዳይ በላይ የሆነ ሰው በራሳችን ተነሥቶ በእኛ እጅግ የተወደደ፣ በንቀት ምክንያት ትእዛዛችንን ይጥሳል ብለን ልንገምት አንችልም ነበር (በልምምድ ሲወድቅ ባናውቅ ኖሮ)። በአክብሮት እጅግ በጣም የሚነካን ... እና ስለዚህ የእኛ ግልጽ ደስታ እና ትዕዛዛት ፣ ሁሉም መዘግየቶች እና ማመካኛዎች ተለያይተው ፣ በታማኝነትዎ ግዴታ ላይ ወዲያውኑ ታዘዙ እና የዚህ ተሸካሚው በእኛ ውስጥ እንዲያደርጉ የሚዘዙትን ሁሉ እንዲፈጽሙ ነው። ስም ስለዚህም አትሳቱ፣ በተቻለ መጠን ተቃራኒውን መልስ እንደምትሰጥ።
የኤልዛቤት “ትዕዛዝ” መልእክተኛዋ የተቃውሞ ደብዳቤዋን በሆላንድ ምክር ቤት ፊት በይፋ በማንበብ ሌስተር በአቅራቢያው መቆም ነበረባት። ይህ የ"ሌተናል ጄኔራል" ህዝባዊ ውርደት ከስፔን ጋር የተለየ ሰላም ለመፍጠር ከቀጠለችበት ንግግር ጋር ተዳምሮ ሌስተር በኔዘርላንድስ መካከል ያለውን አቋም በማያዳግም ሁኔታ አሳፈረ። ኤልዛቤት በረሃብ ለተቸገሩ ወታደሮቿ ቃል የተገባለትን ገንዘብ ለመላክ ደጋግማ በመቅረቷ ወታደራዊ ዘመቻው ክፉኛ ተስተጓጎለ። ለጉዳዩ እራሷን ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆኗ፣ እንደ ፖለቲካ እና ወታደራዊ መሪ የሌስተር ድክመቷ፣ እና በቡድን የተሞላው እና የተመሰቃቀለው የኔዘርላንድ ፖለቲካ ሁኔታ የዘመቻውን ውድቀት አስከትሏል። በመጨረሻም ሌስተር ትእዛዙን በታህሳስ 1587 ለቀቀ።
የስፔን አርማዳ
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ሰር ፍራንሲስ ድሬክ በ1585 እና በ1586 በካሪቢያን ባህር በሚገኙ የስፔን ወደቦች እና መርከቦች ላይ ትልቅ ጉዞ አድርጓል። ጦርነቱን ወደ እንግሊዝ ለመውሰድ ወስኗል ። እ.ኤ.አ. ሐምሌ 12 ቀን 1588 የስፔን አርማዳ ፣ ታላቅ የመርከብ መርከቦች ፣ የስፔን ወረራ ኃይልን በፓርማ መስፍን ስር ከኔዘርላንድ ወደ ደቡብ ምስራቅ እንግሊዝ የባህር ዳርቻ ለማጓጓዝ በማቀድ ወደ ጣቢያው ተጓዙ ። የስፔን መርከቦችን ወደ ሰሜናዊ ምስራቅ የበተነው የተሳሳተ ስሌት፣ መጥፎ ዕድል እና የእንግሊዝ የእሳት አደጋ መርከቦች በጁላይ 29 ከግሬቪላይን ላይ የተደረገ ጥቃት፣ አርማዳውን አሸንፏል። የአየርላንድ የባህር ዳርቻ (አንዳንድ መርከቦች በሰሜን ባህር በኩል ወደ ስፔን ለመመለስ ከሞከሩ በኋላ እና በአየርላንድ ምዕራባዊ የባህር ጠረፍ በኩል ወደ ደቡብ ይመለሱ)። የአርማዳውን እጣ ፈንታ ሳያውቁ የእንግሊዝ ሚሊሻዎች በሌስተር ኦፍ ሌስተር ትእዛዝ ሀገሪቱን ለመከላከል ተሰበሰቡ። ሌስተር ኤልዛቤት ወታደሮቿን በኤሴክስ በቲልበሪ እንድትመረምር ነሐሴ 8 ጋብዟታል። በነጭ ቬልቬት ቀሚስ ላይ የብር ጡት ለብሳ በጣም ዝነኛ በሆነው ንግግሯ ላይ እንዲህ ብላ ተናግራቸዋለች። አፍቃሪ ወገኖቼ፣ ለደህንነታችን በሚጠነቀቁ አንዳንድ ሰዎች አሳምነናል፣ ክህደትን በመፍራት ራሳችንን ለታጠቁ ሰዎች እንዴት እንደምንሰጥ እንጠንቀቅ። ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፥ ታማኝና አፍቃሪ ሕዝቤን ሳልታመን ልኖር አልወድም... ደካማና ደካማ ሴት አካል እንዳለኝ አውቃለሁ፥ ነገር ግን የንጉሥና የንጉሥ ልብና ሆድ አለኝ። የእንግሊዝ አገር፣ እና ፓርማ ወይም ስፔን፣ ወይም ማንኛውም የአውሮፓ ልዑል የግዛቴን ድንበሮች ሊደፍሩ ይገባል ብለው መጥፎ ንቀት ያስቡ።ወረራ ሳይመጣ ህዝቡ ተደሰተ። በቅዱስ ጳውሎስ ካቴድራል ለምስጋና አገልግሎት የኤልሳቤጥ ሰልፍ የዘውድ ንግዷን እንደ ትርኢት ተቀናቃኙ። የአርማዳ ሽንፈት ለኤልዛቤትም ሆነ ለፕሮቴስታንት እንግሊዝ ጠንካራ የፕሮፓጋንዳ ድል ነበር። እንግሊዛውያን በድንግል ንግሥት ሥር የእግዚአብሔርን ሞገስ እና ሀገሪቱን የማይደፈርስ ምልክት አድርገው ይወስዱታል። ይሁን እንጂ ድሉ በጦርነቱ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት አልቻለም, ይህም ቀጥሏል እና ብዙ ጊዜ ለስፔን ይጠቅማል. ስፔናውያን የኔዘርላንድን ደቡባዊ ግዛቶች አሁንም ይቆጣጠሩ ነበር, እናም የወረራ ስጋት አሁንም አለ. ሰር ዋልተር ራሌይ ከሞተች በኋላ የኤልዛቤት ማስጠንቀቂያ ከስፔን ጋር የሚደረገውን ጦርነት እንዳደናቀፈ ተናግሯል፡-
ሟች ንግሥት እንደ ጸሐፍዎቿ ሁሉ ተዋጊዎቿን ብታምን ኖሮ፣ እኛ በሷ ጊዜ ያን ታላቅ ግዛት ጨፍጭፈን ንጉሣቸውን በሾላና በብርቱካን አደረግን እንደ ቀድሞው ዘመን። ነገር ግን ግርማዊነቷ ሁሉንም ነገር በግማሽ ያደረጉ ሲሆን በጥቃቅን ወረራዎች ስፔናዊውን እራሱን እንዴት መከላከል እንዳለበት እና የራሱን ድክመት እንዲያይ አስተምሮታል።
ምንም እንኳን አንዳንድ የታሪክ ምሁራን ኤልዛቤትን በተመሳሳይ ምክንያቶች ቢተቹም፣ የራሌይ ብይን ብዙ ጊዜ ኢ-ፍትሃዊ ነው ተብሏል። ኤልዛቤት እራሷ እንዳስቀመጠችው በአንድ ወቅት በተግባር ባሳዩት አዛዦቿ ላይ ብዙ እምነት እንዳትጥል በቂ ምክንያት ነበራት።
እ.ኤ.አ. በ1589፣ ከስፔን አርማዳ በኋላ፣ ኤልዛቤት የእንግሊዙን አርማዳ ወይም ከ23,375 ሰዎች እና 150 መርከቦች ጋር፣ በሰር ፍራንሲስ ድራክ እንደ አድሚራል እና ሰር ጆን ኖሬይስ በጄኔራልነት ወደ ስፔን ላከች። የእንግሊዝ መርከቦች ከ11,000–15,000 ሰዎች ተገድለዋል፣ ቆስለዋል ወይም በበሽታ ሞቱ እና 40 መርከቦች በመስጠም ወይም በመማረክ አስከፊ ሽንፈት ደርሶባቸዋል። እንግሊዝ በስፔን አርማዳ ላይ ያሸነፈችው ጥቅም ጠፋ፣ እና የስፔን ድል በሚቀጥሉት አስርት አመታት ውስጥ የፊሊፕ 2ኛ የባህር ሃይል መነቃቃትን አሳይቷል።
በ 1589 የፕሮቴስታንት ሄንሪ አራተኛ የፈረንሳይን ዙፋን ሲወርስ, ኤልዛቤት ወታደራዊ ድጋፍ ላከችው. በ1563 ከሌ ሃቭር ካፈገፈገች በኋላ ወደ ፈረንሳይ የመግባት የመጀመሪያዋ የመጀመሪያዋ ነበር።የሄንሪ ርስት በካቶሊክ ሊግ እና በፊሊፕ 2ኛ ከፍተኛ ክርክር ነበረበት።እና ኤልዛቤት የስፔን የቻናል ወደቦችን እንዳይቆጣጠር ፈራች። በፈረንሳይ ተከታዩ የእንግሊዝኛ ዘመቻዎች ግን ያልተደራጁ እና ውጤታማ አልነበሩም። ፔሬግሪን በርቲ፣ 13ኛ ባሮን ዊሎቢ ደ ኤሬስቢ፣ በአብዛኛው የኤልዛቤትን ትእዛዝ ችላ በማለት፣ በሰሜን ፈረንሳይ ብዙም ሳይቆይ 4,000 ሰራዊት ይዞ ዞረ። በታህሳስ 1589 ግማሹን ወታደሮቹን በማጣቱ በችግር ውስጥ ወድቋል። በ1591፣ 3,000 ሰዎችን ወደ ብሪታኒ የመራው የጆን ኖሬይስ ዘመቻ የበለጠ ጥፋት ነበር። እንደነዚህ ያሉትን ጉዞዎች በተመለከተ፣ ኤልዛቤት አዛዦቹ በጠየቁት አቅርቦቶች እና ማጠናከሪያዎች ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ፈቃደኛ አልነበራትም። ኖርሬስ ለበለጠ ድጋፍ በአካል ለመማፀን ወደ ለንደን ሄደ። እሱ በሌለበት ጊዜ፣ አንድ የካቶሊክ ሊግ ጦር በግንቦት 1591 በሰሜን ምዕራብ ፈረንሳይ ክራኦን የሠራዊቱን አጽም ለማጥፋት ተቃርቧል። በሐምሌ ወር ኤልዛቤት ሄንሪ አራተኛን እንዲከበብ ለመርዳት በሮበርት ዴቬሬክስ፣ የኤሴክስ 2ኛ አርል የሚመራ ሌላ ጦር ላከች። ሩዋን ውጤቱም እንዲሁ አስከፊ ነበር። ኤሴክስ ምንም ነገር አላደረገም እና በጥር 1592 ወደ ቤት ተመለሰ። ሄንሪ በሚያዝያ ወር ከበባውን ተወ። እንደተለመደው ኤልዛቤት ከአዛዦቿ ውጭ አገር ከነበሩ በኋላ መቆጣጠር አልቻለችም። ስለ ኤሴክስ “እሱ ባለበት፣ ወይም የሚያደርገው፣ ወይም ምን ማድረግ እንዳለበት፣ እኛ አላዋቂዎች ነን” ስትል ጽፋለች።
አየርላንድ ከሁለቱ መንግሥቶቿ አንዷ ብትሆንም፣ ኤልዛቤት በጠላትነት ፈርጆ ነበር፣ እና በራስ ገዝ በምትሆን ቦታ፣ የአየርላንድ ሕዝብ የካቶሊክ እምነት ተከታይ የሆነች እና ሥልጣኗን ለመቃወም እና ከጠላቶቿ ጋር ለማሴር ፈቃደኛ ነበረች። በዚያ የነበራት ፖሊሲ ለአሽከሮችዎቿን መሬት መስጠት እና አማፂያኑ ስፔንን እንግሊዝን የምታጠቁበት መሰረት እንዳይሰጡ ማድረግ ነበር። በተከታታይ ህዝባዊ አመጽ የዘውዱ ሃይሎች መሬቱን በማቃጠል ወንድ፣ ሴትና ህጻን ጨፍጭፈዋል። እ.ኤ.አ. ገጣሚው እና ቅኝ ገጣሚው ኤድመንድ ስፔንሰር ተጎጂዎቹ "ማንኛውም የድንጋይ ልብ እንዲሁ ያበላሸው ነበር" ሲል ጽፏል። ኤልዛቤት አዛዦቿን አይሪሽ፣ “ያ ጨዋና አረመኔያዊ ሕዝብ” በደንብ እንዲያዙ መከረቻቸው። ነገር ግን እሷ ወይም አዛዦቿ ኃይል እና ደም መፋሰስ ፈላጭ ቆራጭ አላማቸውን ሲፈጽሙ ምንም አይነት ጸጸት አላሳዩም።
እ.ኤ.አ. በ 1594 እና 1603 መካከል ፣ ኤልዛቤት በአየርላንድ በዘጠኝ ዓመታት ጦርነት ወቅት እጅግ በጣም ከባድ ፈተና ገጠማት ፣ ከስፔን ጋር በተደረገው ከፍተኛ ጦርነት ፣ የአመፅ መሪውን ሂዩ ኦኔል ፣ የታይሮናዊውን አርል ደግፋለች። በ 1599 ጸደይ, ኤልዛቤት አመፁን ለማጥፋት ሮበርት ዴቬሬክስ, 2 ኛ አርል ኦቭ ኤሴክስ ላከ. ለብስጭቷ፣ ትንሽ እድገት አላደረገም እና ትእዛዟን በመጣስ ወደ እንግሊዝ ተመለሰ። እሱ በቻርልስ ብሎንት ተተካ፣ ሎርድ ሞንጆይ፣ አመጸኞቹን ለማሸነፍ ሦስት ዓመታት ፈጅቷል። ኦኔል በመጨረሻ ኤልዛቤት ከሞተች ከጥቂት ቀናት በኋላ በ1603 እጁን ሰጠ። ብዙም ሳይቆይ በእንግሊዝ እና በስፔን መካከል የሰላም ስምምነት ተፈረመ።
ኤልዛቤት በመጀመሪያ በግማሽ ወንድሟ በኤድዋርድ ስድስተኛ የተቋቋመውን ከሩሲያው ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጠለች ። ብዙ ጊዜ ለኢቫን ዘሪብል በትህትና ትጽፍ ነበር፣ ምንም እንኳን ዛር ብዙ ጊዜ በወታደራዊ ህብረት ላይ ከማተኮር ይልቅ በንግድ ላይ ባላት ትኩረት ተበሳጭታ ነበር። ዛር እንኳን አንድ ጊዜ ሀሳብ አቀረበላት እና በኋለኛው የግዛት ዘመን ግዛቱ አደጋ ላይ ከወደቀ በእንግሊዝ ጥገኝነት እንዲሰጥ ዋስትና ጠየቀ።የሙስኮቪ ኩባንያ ተወካይ ሆኖ ስራውን የጀመረው እንግሊዛዊው ነጋዴ እና አሳሽ አንቶኒ ጄንኪንሰን ሆነ። በኢቫን ዘሪብል ፍርድ ቤት የንግሥቲቱ ልዩ አምባሳደር በ1584 ኢቫን ሲሞት፣ ብዙም ፍላጎት የሌለው ልጁ ፌዮዶር ተተካ። እንደ አባቱ ሳይሆን ፌዮዶር ከእንግሊዝ ጋር ልዩ የንግድ መብቶችን ለማስጠበቅ ምንም ቅንዓት አልነበረውም። ፌዮዶር መንግስቱን ለሁሉም የውጭ ዜጎች ክፍት መሆኑን አውጇል እና ኢቫን በቸልታ የታገሉትን የእንግሊዝ አምባሳደር ሰር ጀሮም ቦውስን አሰናበተ። ኤልዛቤት አዲስ አምባሳደርን ዶክተር ጊልስ ፍሌቸርን ላከች ከገዢው ቦሪስ ጎዱኖቭ ዛርን እንደገና እንዲያጤነው እንዲያሳምንለት ለመጠየቅ። ድርድሩ ከሽፏል፣ ፍሌቸር ፌዮዶርን ከበርካታ ርዕሶች ሁለቱን በማውጣቱ ምክንያት። ኤልዛቤት በግማሽ ማራኪ፣ ግማሽ የሚያንቋሽሽ ደብዳቤዎች ለፌዮዶር ይግባኝ ማለቷን ቀጠለች። ኅብረት እንዲመሠርት ሐሳብ አቀረበች፣ ከፌዮዶር አባት ሲቀርብላት ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆነችውን ነገር ግን ውድቅ ተደረገች።
የሙስሊም ግዛቶች
በኤልዛቤት የግዛት ዘመን በእንግሊዝ እና በባርበሪ ግዛቶች መካከል የንግድ እና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተፈጠረ። እንግሊዝ ከስፔን ጋር በመቃወም ከሞሮኮ ጋር የንግድ ግንኙነት መስርታ የጦር ትጥቅ፣ ጥይቶች፣ እንጨትና ብረት በመሸጥ የሞሮኮ ስኳር በመሸጥ ላይ ነበር፣ ምንም እንኳን የፓፓል እገዳ ቢኖርበትም። በ1600 የሞሮኮ ገዥ ሙላይ አህመድ አል ማንሱር ዋና ፀሀፊ አብዱል ኦዋህድ ቤን መስኡድ በንግሥት ኤልሳቤጥ ቀዳማዊ ፍርድ ቤት አምባሳደር በመሆን እንግሊዝን ጎበኘ፣ የአንግሎ-ሞሮኮ ኅብረትን በስፔን ላይ ለመደራደር። ኤልዛቤት “ተስማማች። የጦር መሳሪያ ቁሳቁሶችን ለሞሮኮ ለመሸጥ እና እሷ እና ሙላይ አህመድ አል-ማንሱር በስፔን ላይ የጋራ ዘመቻ ስለመጀመር ተነጋገሩ። ይሁን እንጂ ውይይቶቹ ያልተቋረጡ ሲሆን ሁለቱም ገዥዎች ከኤምባሲው በሁለት ዓመታት ውስጥ ሞተዋል.
ከኦቶማን ኢምፓየር ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትም በሌቫንት ካምፓኒ ቻርተር እና የመጀመሪያውን የእንግሊዝ አምባሳደር ወደ ፖርቴ በመላክ በ1578 ዓ.ም. በሁለቱም አቅጣጫዎች ተልከዋል እና በኤሊዛቤት እና በሱልጣን ሙራድ መካከል የኤፒስቶላር ልውውጥ ተደረገ። በአንድ የደብዳቤ ልውውጡ ላይ፣ ሙራድ እስልምና እና ፕሮቴስታንት “ከሮማ ካቶሊክ ጋር ካደረጉት የበለጠ የሚያመሳስላቸው ነገር አለ፣ ሁለቱም የጣዖት አምልኮን አይቀበሉም” የሚለውን አስተሳሰብ አስተናግዶ በእንግሊዝ እና በኦቶማን ኢምፓየር መካከል ህብረት ለመፍጠር ተከራክሯል። ካቶሊካዊ አውሮፓ፣ እንግሊዝ ቆርቆሮ እና እርሳስ (ለመድፍ ለመወርወር) እና ጥይቶችን ወደ ኦቶማን ኢምፓየር ላከች እና ኤልዛቤት በ1585 ከስፔን ጋር ጦርነት በተቀሰቀሰበት ወቅት ፍራንሲስ ዋልሲንግሃም በቀጥታ ኦቶማን እንዲመራ ሲጠይቅ ከሙራድ ጋር በጋራ ወታደራዊ ዘመቻ ላይ በቁም ነገር ተወያይታለች። የጋራ የስፔን ጠላት ላይ ወታደራዊ ተሳትፎ
በ1583፣ ሰር ሃምፍሬይ ጊልበርት በኒውፋውንድላንድ ላይ ቅኝ ግዛት ለመመስረት ወደ ምዕራብ ተጓዙ። ወደ እንግሊዝ አልተመለሰም። የጊልበርት ዘመድ ሰር ዋልተር ራሌይ የአትላንቲክ ውቅያኖስን ቃኝተው የቨርጂኒያ ግዛት ይገባኛል፣ ምናልባት ለኤልዛቤት፣ “ድንግል ንግሥት” ክብር የተሰየመ ሊሆን ይችላል። ይህ ግዛት ከኒው ኢንግላንድ እስከ ካሮላይና ድረስ ካለው ከአሁኑ የቨርጂኒያ ግዛት በጣም ትልቅ ነበር። በ1585 ራሌይ ከጥቂት ሰዎች ጋር ወደ ቨርጂኒያ ተመለሰ። ከአሁኑ ሰሜን ካሮላይና ወጣ ብላ በምትገኘው በሮአኖክ ደሴት አረፉ። ከመጀመሪያው ቅኝ ግዛት ውድቀት በኋላ ራሌይ ሌላ ቡድን መለመለ እና ጆን ዋይትን አዛዥ አደረገው። ራሌይ በ1590 ሲመለስ የተወው የሮአኖክ ቅኝ ግዛት ምንም ዱካ አልተገኘም ነገር ግን በሰሜን አሜሪካ የመጀመሪያው የእንግሊዝ ሰፈራ ነበር።
የምስራቅ ህንድ ኩባንያ
የምስራቅ ህንድ ኩባንያ በህንድ ውቅያኖስ ክልል እና በቻይና ለመገበያየት የተቋቋመ ሲሆን በታህሳስ 31 ቀን 1600 ቻርተሩን ከንግሥት ኤልዛቤት ተቀበለ ። ለ 15 ዓመታት ኩባንያው በምስራቅ ምስራቅ ካሉ አገሮች ጋር በእንግሊዝ ንግድ ላይ በሞኖፖል ተሸልሟል ። የጥሩ ተስፋ ኬፕ እና የማጅላን የባህር ዳርቻዎች ምዕራብ። ሰር ጀምስ ላንካስተር በ1601 የመጀመሪያውን ጉዞ አዘዙ። ኩባንያው በ18ኛው እና በ19ኛው ክፍለ ዘመን በህንድ ውስጥ ግማሹን የአለም ንግድ እና ጠቃሚ ግዛት ተቆጣጠረ።
የግርማዊቷ ንግስና መጨረሻ መምጣት
እ.ኤ.አ. በ 1588 የስፔን አርማዳ ከተሸነፈ በኋላ ያለው ጊዜ ለኤልዛቤት እስከ ንግሥናዋ መጨረሻ ድረስ አዲስ ችግሮች አምጥቷል ። ከስፔን እና አየርላንድ ጋር የነበረው ግጭት እየገፋ ሲሄድ የግብር ሸክሙ እየከበደ ሄዶ ኢኮኖሚው ደካማ በሆነ ምርት ተመታ። የጦርነት ዋጋ. ዋጋ ጨምሯል እና የኑሮ ደረጃው ቀንሷል። በዚህ ጊዜ የካቶሊኮች ጭቆና ተባብሷል እና ኤልዛቤት በ1591 የካቶሊክን ሰዎች እንዲጠይቁ እና እንዲከታተሉ ኮሚሽኖችን ሰጠች። የሰላም እና የብልጽግናን ቅዠት ለማስቀጠል በውስጣዊ ሰላዮች እና ፕሮፓጋንዳ ላይ ትተማመናለች። በመጨረሻዎቹ ዓመታት ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ ትችት ህዝቡ ለእሷ ያለው ፍቅር ማሽቆልቆሉን ያሳያል።ለዚህ “ሁለተኛው የግዛት ዘመን” የኤልዛቤት አንዱ መንስኤ፣ አንዳንድ ጊዜ ተብሎ እንደሚጠራው፣ በ1590ዎቹ ውስጥ የነበረው የግላዊነት ምክር ቤት የኤልዛቤት አስተዳደር አካል የተለወጠ ባህሪ ነው። አዲስ ትውልድ በስልጣን ላይ ነበር። ከሎርድ በርግሌይ በስተቀር፣ በ1590 አካባቢ በጣም አስፈላጊዎቹ ፖለቲከኞች ሞተዋል፡ የሌስተር አርል በ1588 ዓ.ም. ሰር ፍራንሲስ ዋልሲንግሃም በ1590 ዓ.ም. እና ሰር ክሪስቶፈር ሃቶን በ1591። ከ1590ዎቹ በፊት በመንግስት ውስጥ ከፋፋይ ግጭትና ግጭት አሁን መለያው ሆነ በሎርድ በርግሌይ ልጅ በሮበርት ሴሲል እና በሎርድ ቡርግሌይ ልጅ መካከል መራራ ፉክክር ተፈጠረ። እና በግዛቱ ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን ለመያዝ የተደረገው ትግል ፖለቲካውን አበላሽቷል። በ1594 ታማኝ በሆነው ዶክተር ሎፔዝ ጉዳይ ላይ እንደሚታየው የንግሥቲቱ የግል ሥልጣን እየቀነሰ ነበር። በኤርል ኦፍ ኤሴክስ በአገር ክህደት በስህተት በተከሰሰበት ወቅት፣ በመታሰሩ የተናደደች እና ጥፋቱን ያላመነች ቢመስልም ከመገደሉ ማስቀረት አልቻለችም።
በመጨረሻዎቹ የንግሥና ዓመታት ኤልዛቤት በጦርነት ጊዜ ተጨማሪ ድጎማዎችን ለፓርላማ ከመጠየቅ ይልቅ ሞኖፖሊዎችን ከዋጋ ነፃ የሆነ የደጋፊነት ስርዓት በመስጠቱ ላይ ትተማመን ነበር። በሕዝብ ወጪ የቤተ መንግሥት አባላትን ማበልጸግ እና ቂም መብዛት። ይህ በ 1601 ፓርላማ ውስጥ በኮመንስ ሃውስ ውስጥ ቅስቀሳ አብቅቷል ። እ.ኤ.አ. ህዳር 30 ቀን 1601 በታዋቂው “ወርቃማው ንግግር” በኋይትሆል ቤተመንግስት 140 አባላትን ለተወካዩት ኤልዛቤት በደሉን እንደማታውቅ ተናግራ አባላቱን በተስፋ ቃል አሸንፋለች። እና ለስሜቶች የተለመደው ይግባኝሉዓላዊነታቸውን ከስህተቱ ሂደት የሚጠብቃቸው፣ በድንቁርና ሳይሆን በዐላማ ወድቀው ሊሆን ይችላል፣ ምን ምስጋና ይገባቸዋል፣ ቢገምቱትም እናውቃለን። እናም የዜጎቻችንን ልብ በፍቅር ከመጠበቅ የበለጠ ውድ ነገር ስላልሆነ፣ የነጻነታችንን ተሳዳቢዎች፣ የህዝባችን አራማጆች፣ የድሆች ጠላፊዎች ባይነገሩን ኖሮ ምንኛ ያልተገባ ጥርጣሬ ፈጠርን ነበር። !በኢኮኖሚና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት የታየበት ተመሳሳይ ወቅት ግን በእንግሊዝ ታይቶ የማይታወቅ የስነ-ጽሁፍ አበባ አፍርቷል። በ1578 ከጆን ሊሊ ኢፉዌስ እና ከኤድመንድ ስፔንሰር ዘ ሼፐርድስ ካላንደር ጋር በ1578 ዓ.ም. በ1590ዎቹ የእንግሊዝ ሥነ-ጽሑፍ ታዋቂ የሆኑ አንዳንድ ታዋቂዎች በኤልዛቤት የግዛት ዘመን በሁለተኛው አስርት ዓመታት መጨረሻ ላይ የአዲሱ ሥነ-ጽሑፍ እንቅስቃሴ የመጀመሪያ ምልክቶች ታይተዋል። ዊልያም ሼክስፒር እና ክሪስቶፈር ማርሎዌን ጨምሮ። በያቆብ ዘመን በመቀጠል፣ የእንግሊዝ ቲያትር ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይደርሳል።የታላቅ የኤልዛቤት ዘመን አስተሳሰብ በአብዛኛው የተመካው በኤልሳቤጥ የግዛት ዘመን ንቁ ተሳትፎ በነበሩት ግንበኞች፣ ድራማ ባለሙያዎች፣ ገጣሚዎች እና ሙዚቀኞች ላይ ነው። የኪነ ጥበብ ዋና ደጋፊ ላልሆነችው ንግሥቲቱ በቀጥታ የተበደሩት ትንሽ ነው።
ኤልዛቤት ሲያረጅ ምስሏ ቀስ በቀስ ተለወጠ። እሷ እንደ ቤልፎቤ ወይም አስትሪያ፣ እና ከአርማዳ በኋላ፣ እንደ ግሎሪያና፣ የኤድመንድ ስፔንሰር ግጥም ዘላለማዊ ወጣት ፌሪ ኩዊን ተመሰለች። ኤልዛቤት ለኤድመንድ ስፔንሰር የጡረታ አበል ሰጠች; ይህ ለእሷ ያልተለመደ ስለነበር ሥራውን እንደወደደች ያሳያል። የተሳሉት የቁም ሥዕሎቿ ከእውነታው የራቁ ሆኑ እና ከእርሷ በጣም እንድታንስ ያደረጓት የእንቆቅልሽ አዶዎች ስብስብ ሆኑ። እንዲያውም ቆዳዋ በ1562 በፈንጣጣ ተጎድቶ ነበር፣ ግማሹ ራሰ በራዋን ትቶ በዊግ እና በመዋቢያዎች ላይ ጥገኛ ነች። ጣፋጮች መውደዷ እና የጥርስ ሀኪሞችን መፍራት ለከባድ የጥርስ መበስበስ እና ኪሳራ አስተዋጽኦ አድርጓል በዚህም መጠን የውጪ ሀገራት አምባሳደሮች ንግግሯን ለመረዳት እስኪቸገሩ ድረስ የፈረንሳዩ ሄንሪ አራተኛ ልዩ አምባሳደር አንድሬ ሁራልት ደ ማይሴ ከንግስቲቱ ጋር ተገኝተው ነበር ። በዚህ ጊዜ "ጥርሶቿ በጣም ቢጫ እና እኩል አይደሉም ... በግራ በኩል ደግሞ ከቀኝ ያነሱ ናቸው. ብዙዎቹ ጠፍተዋል, ስለዚህም በፍጥነት ስትናገር ሰው በቀላሉ ሊረዳት አይችልም." እሱ ግን አክሎም፣ “መልክዋ ፍትሃዊ እና ረጅም እና በምታደርገው ነገር ሁሉ የተዋበች ናት፤ እስከሆነ ድረስ ክብሯን ትጠብቃለች፣ ነገር ግን በትህትና እና በጸጋ። ሰር ዋልተር ራሌይ "ጊዜ ያስገረማት ሴት" ብሏታል።የኤልዛቤት ውበቷ እየደበዘዘ በሄደ ቁጥር አሽከሮችዎቿ ያወድሱታል። ኤልዛቤት ይህን ሚና በመጫወት ደስተኛ ነበረች፣ነገር ግን በህይወቷ የመጨረሻ አስር አመታት ውስጥ የራሷን አፈጻጸም ማመን ጀምራለች። የሌስተር የእንጀራ ልጅ የሆነችውን እና እሷን ይቅር ያለችለትን የማራኪውን ወጣት ሮበርት ዴቬሬክስን፣ አርል ኦቭ ኤሴክስን ትወዳለች እና ትወደዋለች። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚሄደው ኃላፊነት የጎደለው ድርጊት ቢሆንም፣ እሷም ለወታደርነት ሾመችው። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በየካቲት 1601 ጆርጅ በለንደን አመጽ ለማነሳሳት ሞከረ። ንግሥቲቱን ሊይዝ አስቦ ነበር ነገር ግን ጥቂቶች ለድጋፉ ተሰበሰቡ እና በየካቲት 25 አንገቱ ተቆርጧል። ኤልዛቤት ለዚህ ክስተት በከፊል ተጠያቂው የራሷ የተሳሳተ ፍርድ እንደሆነ ታውቃለች። አንድ ታዛቢ በ1602 እንዲህ ሲል ጽፏል:- “ደስታዋ በጨለማ ውስጥ መቀመጥ እና አንዳንድ ጊዜ እንባ በማፍሰስ ኤሴክስን ለማልቀስ ነው።
የኤልዛቤት ከፍተኛ አማካሪ ዊልያም ሴሲል 1ኛ ባሮን በርግሌይ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 4 ቀን 1598 ሞተ። የፖለቲካ ካባው ለልጁ ሮበርት ሴሲል ተላለፈ፣ እሱም ብዙም ሳይቆይ የመንግስት መሪ ሆነ። ለስላሳ ቅደም ተከተል. ኤልዛቤት ተተኪዋን በፍፁም ስለማትጠራት፣ ሲሲል በድብቅ የመቀጠል ግዴታ ነበረባት።[]ስለዚህ ከስኮትላንዳዊው ጄምስ ስድስተኛ ጋር በኮድ ድርድር ውስጥ ገባ፣ እሱም ጠንካራ ነገር ግን እውቅና የሌለው የይገባኛል ጥያቄ ነበረው። ኤልዛቤት እና "የከፍተኛውን ሰው ልብ ጠብቅ፣ ወሲብ እና ጥራት ምንም ነገር ትክክል ያልሆነው እንደ አላስፈላጊ ማብራሪያዎች ወይም በራሷ ድርጊት ብዙ ጉጉ" ነው። ምክሩ ሰራ። የጄምስ ቃና ኤልዛቤትን አስደስቷታል፣ እሷም ምላሽ ሰጥታለች፡- “እንግዲህ እንደማትጠራጠር አምናለሁ፣ ነገር ግን የመጨረሻ ደብዳቤዎችሽ ተቀባይነት ባለው መልኩ ተወስደዋል ምክንያቱም የእኔ ምስጋና የሚጎድላቸው ስላልሆኑ፣ ነገር ግን በአመስጋኝነት መንፈስ አቅርቡልኝ። በታሪክ ምሁር ጄ.ኢ.ኔል እይታ ኤልዛቤት ምኞቷን ለያዕቆብ በግልፅ ተናግራ ላትሆን ትችላለች፣ነገር ግን “የተሸፈኑ ሐረጎች ከሆነ የማይታለሉ” በማለት አሳውቃቸዋለች።በጓደኞቿ መካከል ተከታታይ ሞት እስከ 1602 መኸር ድረስ የንግስት ጤንነት ጤናማ ነበር ። እ.ኤ.አ. በመጋቢት ወር ኤልዛቤት ታመመች እና "በተቀመጠ እና ሊወገድ በማይችል የጭንቀት ስሜት" ውስጥ ቆየች እና ለሰዓታት መጨረሻ ላይ ትራስ ላይ ሳትነቃነቅ ተቀመጠች። ሮበርት ሴሲል መተኛት እንዳለባት ሲነግራት፣ “ትንሽ ሰው ለመኳንንት የምትጠቀምበት ቃል መሆን የለበትም” ብላ ተናገረች። ማርች 24 ቀን 1603 በሪችመንድ ቤተመንግስት ከጠዋቱ ሁለት እና ሶስት መካከል ሞተች። ከጥቂት ሰአታት በኋላ ሴሲል እና ምክር ቤቱ እቅዳቸውን አውጥተው የእንግሊዝ ንጉስ ጀምስ አወጁ።
እ.ኤ.አ. በ1750ዎቹ የእንግሊዝ ካላንደር ማሻሻያ ተከትሎ የንግሥቲቱን ሞት በ1603 መመዝገብ የተለመደ ቢሆንም፣ እንግሊዝ መጋቢት 25 ቀን አዲስ ዓመትን ታከብራለች፣ በተለምዶ ሌዲ ቀን በመባል ይታወቃል። ስለዚህም ኤልዛቤት በአሮጌው አቆጣጠር በ1602 የመጨረሻ ቀን ሞተች። ዘመናዊው ኮንቬንሽን አዲሱን ለዓመት ሲጠቀሙ አሮጌውን የቀን መቁጠሪያ ለቀን እና ለወሩ መጠቀም ነው.የኤልዛቤት የሬሳ ሣጥን በምሽት ከወንዙ ወርዶ ወደ ኋይትሃል፣ ችቦ በበራ ጀልባ ላይ ተወሰደ። በኤፕሪል 28 የቀብር ሥነ-ሥርዓቷ ላይ የሬሳ ሳጥኑ በጥቁር ቬልቬት በተሰቀለ በአራት ፈረሶች በተሳለ መኪና ላይ ወደ ዌስትሚኒስተር አቢ ተወሰደ። ታሪክ ጸሐፊው ዮሐንስ ስቶው እንዳሉት፡-
ዌስትሚኒስተር በጎዳናዎቻቸው፣በቤታቸው፣በመስኮቶቻቸው፣በመሪዎቻቸው እና በገንዳዎቻቸው ላይ ብዙ አይነት ሰዎች ተጭነው ነበር፣ይህን ለማየት በወጡት፣እናም የእርሷን ምስል በሬሳ ሣጥን ላይ ተዘርግቶ ሲያዩ፣እንዲህ አይነት አጠቃላይ ማልቀስ፣ማቃሰት እና በሰው ትዝታ ውስጥ እንዳልታየ ወይም እንዳልታወቀ ማልቀስ።
ኤልሳቤጥ በዌስትሚኒስተር አቢ ውስጥ ታስራለች፣ ከግማሽ እህቷ ሜሪ 1 ጋር በተጋራው መቃብር ውስጥ። በመቃብራቸው ላይ የላቲን ፅሁፍ " ተባባሪዎች & " ወደ "" ተተርጉሟል። መንግሥትና መቃብር፣ እንተኛለን፣ ኤልሳቤጥ እና ማርያም፣ እህቶች፣ በትንሣኤ ተስፋ።
ኤልዛቤት በብዙ ተገዢዎቿ አዘነች፣ ሌሎች በመሞቷ ግን እፎይታ አግኝተዋል። የንጉሥ ጄምስ የሚጠበቀው ነገር በጣም ተጀመረ ነገር ግን ውድቅ አደረገ። በ1620ዎቹ የኤልዛቤት አምልኮ ናፍቆት መነቃቃት ነበር። ኤልሳቤጥ የፕሮቴስታንቶች ጀግንነት እና የወርቅ ዘመን ገዥ ተብላ ተወድሳለች። ጄምስ የተበላሸ ፍርድ ቤትን ሲመራ የካቶሊክ ደጋፊ ሆኖ ተሣልፏል። ኤልዛቤት በንግሥና ዘመኗ መጨረሻ ላይ ያዳበረችው የድል አድራጊ ምስል፣ ከቡድንተኝነት እና ከወታደራዊ እና ከኢኮኖሚያዊ ችግሮች ዳራ አንፃር፣ ከጥቅም ውጪ የሆነች እና ስሟ ከፍ ከፍ አለ። የጎልፍሬይ ጉድማን የግሎስተር ኤጲስ ቆጶስ፣ “የስኮትላንድ መንግሥት ልምድ ባገኘን ጊዜ ንግሥቲቱ ሕያው የሆነች ትመስላለች። ከዚያ በኋላ የማስታወስ ችሎታዋ በጣም ከፍ ያለ ነበር።” የኤልዛቤት መንግሥት ዘውድ፣ ቤተ ክርስቲያን እና ፓርላማ በሠሩበት ጊዜ ተስማሚ ሆነ። ሕገ መንግሥታዊ ሚዛን.
በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በፕሮቴስታንት አድናቂዎቿ የተሳለችው የኤልዛቤት ምስል ዘላቂ እና ተደማጭነት ነበረው። የማስታወስ ችሎታዋም በናፖሊዮን ጦርነት ወቅት እንደገና ታደሰ፣ ሀገሪቱ እንደገና በወረራ አፋፍ ላይ ስትገኝ። በቪክቶሪያ ዘመን የኤልዛቤት አፈ ታሪክ በጊዜው ከነበረው የንጉሠ ነገሥታዊ ርዕዮተ ዓለም ጋር ተስተካክሎ ነበር, እና በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ኤልዛቤት ለውጭ ስጋቶች ብሔራዊ ተቃውሞ የፍቅር ምልክት ነበረች. የዚያን ጊዜ ታሪክ ጸሐፊዎች እንደ ጄ.ኢ.ኔል እና ኤ.ኤል. እና ደግሞ በግል ንግሥቲቱን ሃሳባዊ: እሷ ሁልጊዜ ትክክል ሁሉንም ነገር አደረገ; የእሷ ይበልጥ ደስ የማይሉ ባህሪያት ችላ ተብለዋል ወይም እንደ ጭንቀት ምልክቶች ተብራርተዋል.
ይሁን እንጂ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ጸሐፊዎች ስለ ኤልዛቤት የበለጠ የተወሳሰበ አመለካከት ወስደዋል. የግዛት ዘመኗ በ1587 እና 1596 በካዲዝ ላይ በተካሄደው ጦርነት በስፓኒሽ ላይ በተሳካ ሁኔታ ወረራ በመፈጸሙ ታዋቂ ነው፣ ነገር ግን አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች በየብስ እና በባህር ላይ ወታደራዊ ውድቀቶችን ያመለክታሉ። በአየርላንድ የኤልዛቤት ጦር በመጨረሻ አሸንፏል። ነገር ግን ስልታቸው መዝገብዋን ያበላሻል። የፕሮቴስታንት ብሔራትን በስፔንና በሐብስበርግ ላይ ደፋር ተሟጋች ከመሆን ይልቅ በውጭ ፖሊሲዎቿ ውስጥ ጠንቃቃ ትሆናለች። ለውጭ ፕሮቴስታንቶች በጣም የተገደበ እርዳታ ሰጥታለች እና አዛዦቿ በውጭ ሀገር ለውጥ ለማምጣት ገንዘብ ሳትሰጥ ቀርታለች።
ኤልዛቤት ብሄራዊ ማንነትን ለመቅረፅ የሚረዳ የእንግሊዝ ቤተክርስትያን መስርታ ዛሬም በቦታው ይገኛል። በኋላ የፕሮቴስታንት ጀግና ብለው ያመሰገኗት ሰዎች ሁሉንም የካቶሊክ እምነት ልማዶች ከእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ለማቋረጥ ፈቃደኛ አለመሆኖን ችላ ብለውታል። በእሷ ዘመን ጥብቅ ፕሮቴስታንቶች በ1559 የተካሄደውን የሰፈራ እና የአንድነት ድርጊት እንደ ስምምነት አድርገው ይመለከቱት እንደነበር የታሪክ ተመራማሪዎች አስታውሰዋል። እንዲያውም ኤልዛቤት እምነት የግል እንደሆነ ታምናለች እና ፍራንሲስ ቤከን እንዳሉት “በሰዎች ልብ ውስጥ መስኮቶችን እና ምስጢራዊ ሀሳቦችን መሥራት” አልፈለገችም።
ኤልዛቤት በአብዛኛው የመከላከያ የውጭ ፖሊሲን ብትከተልም, የግዛቷ ዘመን የእንግሊዝን የውጭ አገር ደረጃ ከፍ አድርጎታል. ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሲክስተስ አምስተኛ “ሴት ብቻ ነች፣ የግማሽ ደሴት እመቤት ብቻ ነች፣ ሆኖም ግን እራሷን በስፔን፣ በፈረንሳይ፣ በግዛቱ፣ በሁሉም እንድትፈራ ታደርጋለች። በኤልዛቤት ዘመን፣ ሕዝበ ክርስትና እንደተበታተነች ብሔሩ አዲስ በራስ የመተማመን እና የሉዓላዊነት ስሜት አገኘ። ኤልዛቤት አንድ ንጉስ በሕዝብ ፈቃድ እንደሚገዛ የተገነዘበች የመጀመሪያዋ ቱዶር ነበረች። ስለዚህ ሁል ጊዜ ከፓርላማ እና ከአማካሪዎቿ ጋር ትሰራለች እውነቱን ይነግሯታል—የእሷ ስቱዋርት ተተኪዎቿ ሊከተሉት ያልቻሉትን የመንግስት ዘይቤ። አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች እድለኛ ብለው ይጠሩታል; አምላክ እንደሚጠብቃት አምናለች። ኤልዛቤት "ብቻ እንግሊዘኛ" በመሆኗ እራሷን በመታበይ በእግዚአብሔር ታምናለች፣ እውነተኛ ምክር እና የተገዥዎቿ ፍቅር ለአገዛዟ ስኬት። በጸሎቷ እግዚአብሔርን አመሰገነች፡-
ጦርነቶች እና ብጥብጦች በአስከፊ ስደት በዙሪያዬ ያሉትን ሁሉንም ነገስታት እና ሀገራት ባናደዱበት ጊዜ፣ የእኔ ንግሥና ሰላማዊ ነበር፣ እና የእኔ ግዛት ለተሰቃየች ቤተክርስቲያንሽ መቀበያ ነው። የሕዝቤ ፍቅር ጸንቶ ታየ የጠላቶቼም አሳብ ከሸፈ።
|
23202
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A4%E1%89%B0%20%E1%88%98%E1%88%AD%E1%89%86%E1%88%AC%E1%8B%8E%E1%88%B5
|
ቤተ መርቆሬዎስ
|
ቅዱስ ላሊበላ ካሳነጻቸው አስራ አንዱ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ነው። ቤት ከርስቲያኑ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ከመሰየሙ በፊት የፍትህ አግልግሎት ይሰጥበት እንደንበር አሁን የተገኙ መረጃወች ይጠቁማሉ። ከነዚህ መረጃወች መካከል የእግር ብረቶች ቋሚ ምስክር ናቸው። ህንጻው ልበዙ ጊዜ ፈርሶ የነበር ሲሆን የአካባቢው ህዝብ በ1982 በአደረገው የገንዘብ ማሰባበሰብና መልሶ መገንባት ስራ፣ ታቦቱ እንደገና ወጥቶ ከነበረበት ቤተ አማኑኤል እንደገና ሊገባ ችሏል።
አለት ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት
|
18379
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%B0%E1%88%9A%E1%8A%AD%20%E1%88%B0%E1%8B%93%E1%89%B5
|
አተሚክ ሰዓት
|
አተሚክ ስዓት በጣም ትክክለኛ የሆነ ሰዓት ቆጣሪ ሲሆን ጊዜ የሚቆጥረው በተንቀሳቃሽ ግዙፍ ቁሶች ሳይሆን በአቶሞች ነው። የሰዓቱ ድግግሞሽ የሚመነጨው ከኤሌክትሮኖች ጨረር መቋረጥ ነው። በአለንበት ዘመን አተሚክ ሰዓቶች ከማንኛውም የሰአት ቆጣሪዎች በበለጠ ትክክል ነው።
በአለም ላይ 260 የአተሚክ ሰዓቶች 60 ቦታወች ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ የሚመነጩ መረጃዎች ፓሪስ፣ ፈረንሳይ ተጠራቅመው ይቀመራሉ። አለም አቀፉ የአተሚክ ሰዓት በዚያው በፓሪስ ይሰላል።
የአተሚክ ሰዓት ትልም የተደራጀው በኢሳዶር ራቢ ነው።
መደብ :ማሽን
መደብ :ጊዜ
መደብ :ሰዓት
|
44658
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%96%E1%88%AA%E1%8A%A9%E1%88%9D
|
ኖሪኩም
|
ኖሪኩም በዛሬው ኦስትሪያና ስሎቬኒያ የነበረ ጥንታዊ አገርና በኋላ የሮሜ መንግሥት ክፍላገር ነው።
የኖሪኩም ብሔር ምናልባት ከ400 ዓክልበ. አካባቢ ጀምሮ ሲጠቀሱ የከልቲክ ቋንቋዎች ቤትሠብ ተናጋሪዎች መሆናቸው ይመስላል። በ56 ዓክልበ. የዩሊዩስ ቄሳር ጓደኞች ቢሆኑም በ24 ዓክልበ. ከፓኖኒያ ሰዎች ጋር እስትሪያን ወርረው የሮሜ አገረ ገዥ በኢሉዋርያ፣ ፑብሊዩስ ሲሊዩስ፣ አሸነፋቸውና ለሮሜ ተገዥ አደረጋቸው። በሮሜ ቄሣር ክላውዴዎስ ዘመን (33-46 ዓም) ኖሪኩም በይፋ የሮሜ መንግሥት ክፍላገር ሆነ።
የሮሜ መንግሥት
የአውሮፓ ታሪካዊ አገሮች
|
22644
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%88%9D%E1%89%A6
|
ቅምቦ
|
ቅምቦ ወይም ጦቢያ () ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ
ቊጥቋጦ ወይም አነስተኛ ዛፍ፣ ወፍራም ልጥ፣ ታላቅ ቅጠል አለው።
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር
በቆላ ከ1500 በታች ተራ ነው። በዚህም ውስጥ ደረቅ፣ አሸዋማ ፈሳሽ መውረጃ ይመርጣል።
የተክሉ ጥቅም
ላስቲኩ ባጠቃላይ ለሰውም ሆነ ለከብት እንደ መርዝ ይቆጠራል። እንስሶች አይበሉትም። ሆኖም፣ ቅጠሉና ቅርንጫፎቹ በመሬት ላይ ለአንድ ሌሊት ቢደረቁ፣ ለከብት መኖ ጸጥ ይላል።
ላስቲኩ የልብ ሽባነት ያደርጋል። እንድ መድሃኒት ለቁምጥና ተጠቅሟል።
አረንጓዴ ቅጠሉ በአፍአዊ አምቅ ማበጥን ለመቀነስ ተጠቅሟል። ሥሩም እንደ ቶኒክ፣ ለአባላዘር በሽቶች ወይም ለእባብ ነከስ እንደሚረዳ ተብሏል።
የኢትዮጵያ እጽዋት
|
50920
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%80%E1%8B%AD%E1%88%89%20%E1%8B%88%E1%88%AD%E1%89%81
|
ሀይሉ ወርቁ
|
ሀይሉ ወርቁ በኢትዮጵያ ስነፅሑፍ ራሱን በራሱ ስነፅሑፍን በማስተማር ከአስር በላይ መፅሐፍትን የፃፈ ደራሲ ነው። በሦስት ቋንቋም ይፅፋል።
ደራሲው ሐይሉ ወርቁ የአስራ አንድ መጽሐፍት ደራሲ፥
ላለፉት አስር ዓመታት በበርካታ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥናት አድርጎ ከአስር ባላይ መፅሐፍትን የፃፈ፣
በበርካታ አገራዊ ጥናቶች ላይ የተሳተፈ፣
የመጀመሪያው የአማርኛ ቃላት መሰብሰብ ፕሮጅክት የመራ እና እየሰራ ያለ፣
የውጪ ሐይሎች በኢትዮጵያ የሚሰሩትን የዳርስቶጵያ ፕሮጀክትን በጥናት በተደገፈ ሰነድ ያዘጋጀ እና በዚሁ ጥናት ላይ ተመስርቶም የፓቶጵያ ፍቅር የተሰኘ መፅሐፍ የፃፈ፣
የፒ.ኤች.ዲ ትምህርቱን እየተማረ ያለ ለአገር እና ለወገን ተቆርቋሪ፣ በሥራው ታታሪ ሰው ነው።
ሞት በውክልና
የመፅሐፊ አጠቃላይ ሁኔታ
ሞት በውክልናመፅሐፍ ታሪክ ግጥም የተገጥመለት፣ ዘፈን የተዘፈነለት ድንቅ ታሪክ ነው። ሞት በውክልና በፍቅር ዘውግ የተፃፈ መፅሐፍ ሲሆን ፥ ልብን ትርክክ አድርጎ፣ አኧምሮን በማመራመር ፤ አንጀት የሚያላውስ ድንቅ የፍቅር ታሪክ ላይ የተፃፈ ነው ታሪካዊ መፅሐፍ ነው።
ይህ ታሪክ በታገል ሰይፉ ተፅፎ፣ በሀይለየሱስ ግርማ ዜማ ስላዜመለት ሰው ታሪክ ብቻ አይደለም። ያ ሚስኪን ሰው ስላፈቀራት እና በስተመጨረሻ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ፤ ለሦስተኛ ጊዜ ሞተች ተብሎ ዕድርተኛው ቀብሩን ሊቀብር፣ በእአባቷ ግቢ ቢሰበሰብም፤ እሷ ግን ዛሬም እንደ ባለፈው መሞት አቅቷት ክፉኛ ተሰቃይታ፤ ቤተሰቡን እያሰቃየች ስለነበረች እና መሞት አቅቷት በጣዕረ ሞት ከተያዘች እነሆ ዛሬ ዘጠና አራተኛ ስላስቆጠረች ልዩ ሴት ነው።
ይህን ባለ 256 ገፅ የሆነው መፅሐፍ፥ የአርታኦት ሥራው የሰራው ታዋቂው አርታኢ እና የፊልም ተዋናይ፣ የአማርኛ ቋንቋና ሥነጽሑፍ ምሩቅ ዳዊት (ዴቮ) ነው።
አንድ ሰው ነበረ፤ የተለየ ልብ ያለው። አኧምሮውን ማዘዝ እና ማስቆም የሚችል ልብ። አኧምሮው ሲያስቆመው አካሉም እዛው ተገተረ። ያለ ተስፋ፣ ያለረዳት፣ እዛው እንድቆመ ፤ ለምን እንደሆነ ባላወቀው ምክንያት፣ ሁሉም ነገር በዙሪያው በፍጥነት ይለዋወጥ ነበር። ለተመለከተው ፊቱ ይናገራል፣ እሱ ለውጡ አልገባውም። እዛው በመንገዱ ዳር እንደቆመ መልኩ ጠፉ፣ ውበቱ ረገፈ። ዓመታት አለፉ።
መንገደኛው ሁሉ ይህ ሰው ብቸኛ ነው ብሎ ያዝናል። እሱ ግን ለምን እንደታዘነለት፣ ነገሮችም ሁሉ እየተለወጡ መሆናቸውን አያውቅም። በዚያች ቦታ ለዓመታት ከመቆሙ የተንሳ፣ እርሱ የቦታው ምልክት ሆኗል። ሰው ሁሉ ቦታውን ለመለየት የተለየ ሥዕሎች እና ማስታወቂያ አላስፈልገውም።
ሰዎች እሱን እዚያ ቦታ ላይ ለሲሶ ምዕተ ዓመት ያህል ዘመን የገተረው ጉዳይ ምን እንደሆነ አያውቁትም፣ ቢያውቁትም አይገባቸውም። ምክንያቱም ሰዎች ሁሉ እሱ ያለው ዓይነት ልብ የላቸውም ! ይህ መፅሐፍ ግን ስለእርሱ ሳይሆን፤ እርሱ ስለሚያውቃት፣ እና መኖርም መሞትም አቅቷት ስለምትሰቃይ ቤተልሔም ስለተባለች ሴት እንጂ።
ሁሉም ገፀባህሪያት የየራሳቸው ቀለም አላቸው። ሞትን ለዘጠና አራት ቀናት የተዋጉትን ቀስ አገኘውን፣ ሰላቢዋ ፅጌ፣ ቀላብላባዋ ወ/ሮ ማንጠግቦሽ፣ የሰውን ሚስት ይዞ አሜሪካ በመግባት፣ ሰውን 32 ዓመታት መንገድ ላይ የገተረውን ይሀይስን …. ብቻ ሁሉንም ማንም መርሳት አይችል።
አፃፃፉ ዘይቤ
በልማዱ የልብ ወለድ ድርሰት ደራሲዎች ከፍ ወይም ዝቅ ብለው የሚገመቱት ለድርሰታቸው የሚፈጥሩት ታሪክ፣ ላንባቢዎች በሚሰጠው ትምህርት እና ታሪኩን በጥሩ አጻጻፍ አስጊጦ ለማቅረብ ባላቸው ችሎታ ነው። ላንባቢዎች አኧምሮ ትምርትን፣ ለልባቸው ደስታን የሚሰጥ ልብ ወለድ ድርሰት ጥሩ ድርሰት ይባላል። እንዲህ ላሉ ድርሰቶች ደራሲዎችም ትልቅ ደራሲዎች ይባላሉ።
እኔ ይህች “ሞት በውክልና” ብዬ ሰይሜ ላንባቢዎች የማበረክታት ልብ ወለድ ድርሰት በታሪክዋም ሆነ ባጻጻፍዋ ጥሩ ድርሰቶች የሚባሉት በያዙት ደረጃ እንኩዋንስ ልትደርስ እንደማትቀርብ አውቃለሁ። ነገር ግን ብዙ ጥሩ ድርሰቶች ያልያዙት መልክት ላንባቢዎች ለማድረስ የተሰናዳች ስለሆነችና በተለይ የኢትዮጵያን አንባቢዎች ለሚያሳስቡ እስከ ዛሬ ድረስ መልስ ላላገኙ አንዳንድ ጥያቄዎች መልስ ሊሆኑ የሚችሉ አሳቦች ይዛ ስለምትቀርብ አንባቢዎች ሳይሰለቹ በማስተዋል እንዲመለከቱልኝ ተስፋ አደርጋለሁ።
ሌሎች የደራሲው ሥራዎች
በማስተዋል ወደ ባለጠኘት ማደግ
የፓቶጵያ ፍቅር
ምናሴ መናጢው እና የኢትዮጵያ መምህራን
ዕብዱ አጥናፉ ወርቁ
ዕጸ ሐበቅ እና ጭራ አልባዎቹ
የነፍስ እናት እና ልጇ
የዴልታው ጌታ
የሁፐስ ፍቅር
የጠፏ የአዲስ አበባ ሴቶች
ዲ ሳንግዌ
የመጨረሻው ወታደር ልጅ እና ሌሎች
የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
|
11564
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%8B%E1%8B%AD%20%E1%8A%A0%E1%8D%88%E1%88%AD
|
ላይ አፈር
|
ላይ አፈር (ላያፈር፣ ላይኛ አፈር፣ ላይኛፈር) ከምድሩ አፈር ላዕላይ ንብብር ሲሆን ጥልቀቱ ከ5 እስከ 20 ሴንቲሜትር ድረስ ሊሆን ይችላል። ካርቦናዊ ቁስ አካልና ደቂቅ ዘአካል (ጥቅን ሕዋስ) በላይ-አፈሩ ውስጥ በመብዛቱ፣ ስሙ ደግሞ «ሕያው አፈር» ሊባል ይችላል። የምድር ሥነ-ሕይወታዊ ተግባር በብዛት የሚፈጸምበት በዚህ አፈር ንብብር ነው። አትክልት በተለይ ሥሮቻቸውን በእርሱ ሰድደው ንጥረ ምግቦችን ከእርሱ ሊቀበሉ ይችላሉ። ላይ አፈር ከንፋስ ወይም ከጎርፍ የተነሣ ቢጠፋ ኖሮ ብዙ አትክልት በዚያ ለማብቀል አይቻልም።
ላያፈር አለም ዙሪያ በአጸድም ሆነ በእርሻ በሰፊ ይጠቀማል። ልዩ ልዩ አይነቶችም በሱቅ እየተሸቀጡ ነው።
ሥነ ሕይወት
የመሬት ጥናት
|
11457
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%B5
|
ገብስ
|
ገብስ (ሮማይስጥ፦ ) የእህል አይነት ነው። እንዲሁም እህሉ ከዘሮቹ የመጣው የሣር ተክል አይነት ነው። ከጥንት ጀምሮ ለሰዎች ምግብና ለእንስሶች መኖ ይጠቅማል፤ ከዚህም በላይ ብቅል በማድረግ ቢራና ሌላ መጠጥ ለመሥራት ይጠቀማል። ከእህሉም የወጣው ዱቄት እንደ ዳቦ ሊሠራ ይችላል። ይህ እህል ለዕድሜ እጅግ ጤነኛ ምግብ መሆኑ ይታወቃል።
የገብስ ዱቄት በውሃ ለሆድ ቁስል (አልሰር) ይበላል።
|
13247
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8D%E1%8B%B5%E1%88%AD
|
ውድር
|
ውድር () የሁለት መጠኖችን አንጻራዊ ልዩነት የምንለካበት መንገድ ነው። በበለጠ ለማስረዳት ውድር ማለት አንዱ መጠን በሌላው መጠን ስንት ጊዜ ይገኛል ብለን ለምንጠይቀው ጥያቄ የምናገኘው መልስ ነው። ለምሳሌ 3 ሜትር እንጨት በ9 ሜትር እንጨት 3 ጊዜ ይገኛል፣ ስለዚህ የትልቁ ለትንሹ ውድር 3 ነው ማለት ነው።
ሥነ ቁጥር
|
50989
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%93.%E1%88%9D.
|
ዓ.ም.
|
ዓመተ ምሕረት ከኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ አለም መምጣት ጋር ተያይዞ በአብዘኛው ክርስቲያናዊ ማሕበረሰብ ዘንድ ለዘመን መግለጫነት ወይም መጠሪያነት የሚሰጥ ስያሜ ነው።
በመካከለኛው ዘመን ላቲንኛ ዐኖ ዶምኒ () ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ትርጓሜው ዘመነ ጌታ ወይም የጌታችን ዘመን የሚል ነው፤ ይህም የተወሰደው "ዐኒ ዶምኒ ኖስትሪ ጄሱ ክርስቲ" (በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ዘመን) ከተሰኘ ላቲን ኃይለ ቃል ነው። በኢትዮጵያም ለዚሁ በቀረበ መልኩ ዓመተ ምሕረት በመባል ተተርጉሟል። አንዳንድ ጊዜ ሰኩለር ለማድረግ ስፈልጉ የተለያዩ ፀሐፍት ከ፲፯ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ጀምሮ የጋራ ዘመን ወይም ኮሜን ኢራ(ሲ.ኢ) በማለት የመጻፍ የጀመሩ ቢሆንም እንደምክንያትነት የሚወሰደው ነገር የኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር መምጣት እንድሆነ ይታምናል።
|
32592
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%AC%E1%8A%94%E1%8B%9D%E1%8B%8C%E1%88%8B
|
ቬኔዝዌላ
|
ቬኔዝዌላ (እስፓንኛ፦ ) የደቡብ አሜሪካ አገር ነው። ዋና ከተማው ካራካስ ነው።
2011 ዓም የመሪነት ቀውስ
በ2011 ዓም በቬኔዝዌላ የመሪነት ክርክር አለ። ባለፈው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አቶ ኒኮላስ ማዱሮ አሸነፈ። የተቀራኒው አቶ ዋን ጓይዶ ወገን ግን በምርጫ ስላልተሳተፈ እሱ አልተመረጠም። ዳሩ ግን አቶ ጓይዶ በዋሺንግተን ዲሲ ድጋፍ አሁን በራሱ አዋጅ ራሱን ለፕሬዚዳንትነቱ ሾመ።
የዋሺንግተን ቅርብ ጭፍሮ አገራት ሁሉ የአቶ ጓይዶን ፕሬዚዳንትነት ጸድቀው፤ በ«ዲሞክራሲ» ዘመናዊ ትርጉም ዘንድ የአገሩ ሕዝብ ድምጽ ከዋሺንግተን ዲሲ ፈቃድ አይበልጥም ማለታቸው ነው። በተጨማሪ ዋሺንግተን ለዓለም አገራት ሁሉ «ወገናችሁን ምረጡ» ብሎ ያስገድዳል።
|
18663
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B2%E1%8D%8A%E1%8A%93%E1%89%85
|
ቲፊናቅ
|
ቲፊናቅ (ቲፊናቕ) በስሜን አፍሪቃ የሚገኙት የበርበር (ኢማዚቐን) ብሔሮች የሚጠቅሙት አጻጻፍ ነው። ያለ አናባቢዎች የሆነ ቲፊናቕ በተለይ በማሊና በኒጄር የሚኖሩት ቷሬግ ሕዝብ ቋንቋቸውን ለመጻፍ ይጠቀማል። ከዚህ በላይ ባለፈው ቅርብ አመታት አናባቢዎች ጨምረው በሞሮኮ አዲስ ቲፊናቅ መደበኛ ሁኔታ አገኝቷል።
የ«ቲፊናቅ» ትርጉም «የፊንቄ ጽሕፈት» እንደ ሆነ ይታመናል። በጥንት በስሜን አፍሪቃ ከሠፈሩት ዘሮች መካከል የፊንቄ ወይም ከነዓን ሰዎች በተለይ በቀርታግና ዙሪያ እንደ ነበሩ ታውቋል። ፊንቄያውያንም የአልፋቤት አባቶች በመሆናቸው የስሜን አፍሪቃ ኗሪዎች ከነርሱ የተማሩበት ወቅት ግን አይታወቅም። የአሁን ሊቃውንት ከ500 ዓክልበ አስቀድሞ አይሆንም ሲሉ ለዚህ መልስ ማስረጃ የለም። የቲፊናቅ ጽሕፈት ከጥንታዊ የሊብያ በርበሮች ጽሕፈት ጋር ተመሳሳይነት ስላለው አደረጃጀቱ በዚህ ሊታይ ይችላል።
የውጭ መያያዣ
ቲፊናቅ በኦምኒግሎት]
|
43765
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%89%E1%8A%A9%E1%88%B5
|
ሉኩስ
|
ሉኩስ በ1490 ዓ.ም. አኒዩስ ዴ ቪቴርቦ የተባለው ጣልያናዊ መነኮሴ ባሳተመው ዜና ማዋዕል ዘንድ፣ የኬልቶች (በጋሊያ፣ አሁንም ፈረንሳይ አገር) ስምንተኛ ንጉሥ ነበረ። የ2 ባርዱስ ተከታይ ሲሆን ለ30 ዓመት (ምናልባት 2016-1986 ዓክልበ. ግድም) እንደ ነገሠ በሌላ አፈታሪካዊ ምንጭ ተብሏል።
ሉኩስ ፓሪስ የተባለውን ከተማ እንደ መሠረተ በአንዳንድ ደራሲ ይታስባል። ይህ ከተማ ከሮሜ መንግሥት ዘመን አስቀድሞ ፓሪሲ የተባለው የኬልቶች ጎሣ ዋና ከተማቸው ሉኮቶኪያ ሆኖ ነበር። እንዲሁም ሌውኪ (ወይም «ሉከንሴስ») የተባለው የኬልቶች ጎሣ እን ዋና ከተማቸው ቱል ከሉኩስ ጋራ ግንኙነት እንዳላቸው በአንዳንድ ጸሐፊ ዘንድ ይታመናል።
በሌላ መጽሐፍ በኩል ሉኩስ አዳኝ ሲሆን በማደን እያለ ቤቱን በሴን ወንዝ ደሴት (የአሁን ፓሪስ ሥፍራ) ላይ ሠርቶ ነበር። ከዚያም በላይ ለዝ-አን-ኤኖ የሚባለውን ቦታ በአሁኑ ቤልጅግ እንደ መሠረተ ይላል።
በብዙ ምንጮች ዘንድ ሉኩስ የ፪ ባርዱስ ልጅ ነበረ፤ የሉኩስም ልጅና ተከታይ ኬልቴስ ሆነ። አንዳንድ መጽሐፍ ግን ኬልቴስ የባርዱስ አንድያ ሕጻን ልጅ ስለ ሆነ አካለ መጠን እስከሆነበት ወቅት ድረስ ሉኩስ በእንደራሴነት ገዛ ይለናል።
የፈረንሣይ አፈታሪካዊ ነገሥታት
|
53964
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%88%8D%E1%8C%A9%E1%89%B5%20%E1%8B%8B%E1%89%85%E1%88%8B%E1%88%9A%E1%8B%8E%E1%89%BD
|
ባልጩት ዋቅላሚዎች
|
ባልጩት ዋቅላሚዎች “” ባሲላሮፋይታዎች የሚባሉት ናቸው፡፡ በአስደናቂ ሁኔታ ውብ የሆነ የሲሊካ ቅርፊት ወይም ፍሩስቱል “” ያላቸው ሲሆን ባልጩት ዋቅላሚዎች በጣም ከሚወደዱ ደቂቅ ቅሪተዓካላት ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ደግሞም እጅግ በጣም አስፈላጊ የሚባሉ የውሃ ውስጥ ደቂቅ አካላት ናቸው፡፡ ጨዋማ በሆኑ እና ባልሆኑ የውሃ ስርዓተ ምህዳሮች ውስጥ በመንሳፈፍ እንዲሁም በደለል ውስጥ እጅግ በስፋት ይገኛሉ፡፡ በብርሃን አስተፃምሮ ምግብ ማምረት የሚችሉ በመሆናቸው ለውሃ ውስጥ ፍጥረታት እንደ ምግብነት ያገለግላሉ፡፡ እንደውም አንዳንዶቹ በአፈር ውስጥና እርጥበታማ በሆኑ ሳረንስቶች ላይ ይገኛሉ፡፡
|
13722
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%B8%E1%8A%90%E1%8D%88%E1%89%BB%E1%89%B8%E1%8B%8D
|
አሸነፈቻቸው
|
እሩቅ አገር ላልህሄደው መሽቶባቸው ከሚያውቋቸው ቤተሰብ ቤት ደርሰው አርፈዋል። ቤተሰቡም ካስተናገዳቸው በኋላ በይ መደቡ ላይ አንጥፊላቸው ብለው እናቱዋ ለልጂቱ ይነግሩዋታል። ልጅቷም የአንድ ትንሽ ፍየል አጎዛ ወስዳ ታነጥፍና ትመጣለች። አለቃ አንጥፌልዎታለሁና ሄደው ሊተኙ ይችላሉ ትላቸዋለች። ሄደው ሲመለከቱ አጎዛዋ እጅግ ትንሽ ከመሆኗ የተነሳ መደቡ መሐል ሆና አንሳ ትታያቸዋለች። ይሄኔ ይህች ድብዳብ እንድተኛባት መቼ ትበቃኛለች ይሏታል። ልጅቱም ስትመልስላቸው እሱን ከጨረሱ በኋላ እጨምርልዎታለሁ አለቻቸው ይባላል።
መደብ : የኢትዮጵያ ቀልዶች
|
18648
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%96%E1%89%B2%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%83%E1%88%9D
|
ኖቲንግሃም
|
ኖቲንግሀም (እንግሊዝኛ: ) በምስራቅ መካከለኛው [እንግሊዝ]] ከሚገኙ ከተሞች አንዱ ነው። ይህ ከተማ በራስ ገዝ አስተዳደርነት የሚመራ ሲሆን ስምንት አባላት ካሉት የከተማ አጋርነት አንዱ ነው።።
ጥበብ እና ዲዛይን
ሙዚየም እና ስብስቦች
ስነ ህንፃ
ምግብ እና መጠጥ
ሳይንስ እና ግኝቶች
እህት ከተሞች
የውጭ ማያያዣ
የእንግሊዝ ከተሞች
|
14317
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%81%E1%88%88%E1%89%B5%20%E1%8C%8A%E1%8B%9C%20%E1%8A%90%E1%8B%8D%20%E1%8B%A8%E1%8B%B6%E1%88%AE%20%E1%88%8D%E1%8B%B0%E1%89%B5%20%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B1%20%E1%89%A0%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%89%81%E1%88%8B%E1%88%8D%20%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B1%20%E1%89%A0%E1%8C%AB%E1%8C%A9%E1%89%B5
|
ሁለት ጊዜ ነው የዶሮ ልደት አንዱ በእንቁላል አንዱ በጫጩት
|
ሁለት ጊዜ ነው የዶሮ ልደት አንዱ በእንቁላል አንዱ በጫጩት የአማርኛ ምሳሌ ነው።
ሁለት ጊዜ ነው የዶሮ ልደት አንዱ በእንቁላል አንዱ በጫጩት የአማርኛ ምሳሌ ነው።
ዶሮ እንቁላሉን ስትጥል እና እንቁላሉ ሲፈለፈል ሁለት ጊዜ ትወለዳለች። ይህ ተረትና ምሳሌ ምናልባትም ከቤ/ክርስቲያን ውይይት የመነጨ ሳይሆን አይቀርም።
መደብ : ተረትና ምሳሌ
|
49116
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8B%AB%E1%88%AC%E1%8B%B5
|
ቅዱስ ያሬድ
|
አባታችን ቅዱስ ያሬድ ሚያዝያ ፭ ቀን በ፭፻፭ ዓ.ም በአክሱም ከተማ ተወለደ፡፡ አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ ይባላል እናቱ ክሪስቲና ወይም ታውክልያ ትባላለች።
ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በ7 ዓመቱ አባቱ ስለሞተ እናቱ የአክሱም ገበዝ ለነበረው ለአጎቱ ለጌዴዎን እንዲያሳድገውና እንዲያስተምረው አደራ ሰጠችው፡፡
ያሬድ ከአጎቱ ዘንድ መዝሙረ ዳዊት በሚማርበት ጊዜ ስለሚቆጣውና ስለሚገርፈው መታገስ ተስኖት ማይኪራህ ወደምትባል ቦታ ሄዶ ተደበቀ ያም ቦታ የቀዳማዊ ምኒልክ መቃብር ቦታ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድም ወደ አንዲት ዛፍ ስር ተጠግቶ አርፎ እያለ አንዲት ትል የዛፍ ፍሬ ለመብላት ዛፉ ላይ ለመውጣት ስድስት ጊዜ ሲወጣና ሲወርድ ከቆያ በኃላ በሰባተኛው ከዛፉ ላይ ወጥቶ የዛፉን ፍሬ ሲበላ ተመለከተ፡፡ ቅዱስ ያሬድ የትሉን ተስፋ አለመቁረጥ ከፍተኛ የሆነ ትጋቱን እንዲሁም ወደላይ ለመውጣት ብዙ ጊዜ እየሞከረ ቢወድቅም ከዓላማው ሳይናወጥ ከብዙ ድካምና ጥረት በኃላ ያሰበው እንደተፈጸመለት ተመልክቶ “ሰውነቴ ሆይ ግርፋትን ለምን አትታገሽም፤ መከራንስ ለምን አትቀበይም” ብሎ ሰውነቱን ከገሰጸ በኃላ ወደ መምህሩ ተመልሶ “አባቴ ሆይ ይቅርታ አድርግልኝ እንደቀድሞ አስተምረኝ” አለው፡፡ መምህሩ ጌዴዋንም ተቀብሎ ያስተምረው ጀመር፡፡
ጥበብና ቅዱስ ያሬድ
ወደ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን አዘውትሮ እየሄደ ጥበብና እውቀትን የሚገልጽ የጌታዬ እናቱ እመቤቴ ሆይ አይነ ልቦናዬን ያበራልኝ ዘንድ ለምኝልኝ እያለ ይለምን ነበር፡፡ ከዚያም በአንድ ቀን 150 መዝሙረ ዳዊት፣ መኃልየ ነቢያት፣ መኃልየ ሰሎሞን ሌሎችን እና ትርጓሜ መጻሕፍት ብሉያትና ሐዲሳትን አወቀ፡፡ በዚያ ዘመን ድምጽን ከፍ አድርጎ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ዜማ አልነበረም ቀስ ብሎ እንደ ውርድ ንባብ እያዜሙ ያመሰግኑ ነበር እንጂ፡፡ እግዚአብሔርም በያሬድ ቃልና ከፍ ባለ ዜማ መመስገን በወደደ ጊዜ ኅዳር 5 ቀን 527ዓ.ም በኤዶም ገነት በሥላሴ አምሳል ሦስት አእዋፍን ወደ እርሱ ላከ እነሱም በግዕዝ፣ ዕዝል እናበአራራይ ዜማ እንደዚሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ፡፡ ሦስቱ አእዋፍ ቅዱስ ያሬድ በቆመበት ቦታ ፊት ለፊት በአየርላይ ቆመው “ብፁዕ ያሬድ ብፅዕት ከርሥ እንተ ጾረተከ ወብፁዕት አጥባት እለ ሐፀናከ፤ የተመሰገንክና የተከበርክ ያሬድ ሆይ አንተን የተሸከመች ማህጸን የተመሰገነች ናት አንተን ያሳደጉ ጡቶችም የተመሰገኑ ናቸው” አለችው ቅዱስ ያሬድም ይህንን ቃል በሰማ ጊዜ ወደ ሰማይ ተመልክቶ እናንተ በሰው አንደበት የምትናገሩ ወፎች ከወዴት መጣችሁ አላቸው ከሦስቱ አንዲቱ እንዲህ ስትል ተናገረችው ከኤዶም ገነት ወደ አንተ ተልከን ሲሆን ይኸውም ከሃያ አራቱ ካህነት ሰማይ ማኅሌትን ትማር ዘንድ ልንነግርህ መጣን አሉት፡፡ ከዚያም ቅዱሳን መላእክት በዜማ ወደ ሚያመሰግኑባት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም በአካል ተነጠቀ፡፡ በዚያም መላእክት ሰማያውያንና ምድራውያን ደቂቀ አዳምን የፈጠረ እግዚአብሔርን በመኅሌት በቅኔ በከፍተኛ ድምጽ ያለማቋረጥ በመንበሩ ዙሪያ ሆነው ሲያመሰግኑት በሰማ ጊዜ ካለበት ስፍራ ተነስቶ እነሱ ወዳ አሉበት ቦታ ሊገባ ወደደ ነገር ግን አልተቻለውም፡፡ ከዚያም በኃላ እነዛ አእዋፎቹ ወደ እርሱ ተመልሰው መጥተው ያሬድ ሆይ “የሰማኸውን አስተውለኸዋል” ብለው ጠየቁት “አላስተዋልሁም” ብሎ መለሰላቸ እንግዲያውስ አዲሱን የእግዚአብሔርን ምስጋና ጥራ እርሱም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው አለችው ቅዱስ ያሬድም “ማኅሌትን በዓይነቱ ልቤ መልካምን ነገር አውጥቶ ተናገረ” እያለ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ተማረ፡፡ ቅዱስ ያሬድም የመላእክት ሥርዐታቸውን ዐይቶ፣ ማሕሌታቸውን አጥንቶ ኅዳር 6 ቀን 527 ዓ.ም በጠዋት ሦስት ሰዓት ወደ ቀድሞ ቦታው ተመልሷል፡፡
ቅዱስ ያሬድና ቤተክርስቲያን
ከዚያም አክሱም ከተማ ወደምትገኝው ወደ ጽዮን ቤተክርስቲያን ገብቶ በዓውደ ምህረቱ ቆሞ ድምጹን ከፍ አድርጎ “ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ ብሎ በልሳነ ግዕዝ አዜመ፡፡ ይህም ማለት ዓለም ሳይፈጠር ለነበረና ዓለምን አሳልፎ ለዘለዓለም ለሚኖር ለአብ ምስጋና ይገባል፤ ለወልድም ምስጋና ይገባል፤ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፤ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ፤ ዳግመኛም ደብተራ ኦሪትን እንዴት አድርጎ መሥራት እንዳለበት ለሙሴ አሳየው ማለት ነው፡፡” ከሰማይ እንደተመለሰ ለመጀመሪያ ጊዜ ጣዕመ ዜማውን ያሰማበት ቦታ “ሙራደ ቃል” (የቃል መውረጃ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ይኸውም ዜማው ከሰማይ የወረደ ለመሆኑ እውነተኛ ማስረጃ ነው፡፡ ይህችንም ዜማ “አርያም” አላት፡፡ ይህም ማለት ከመላእክት ወይም ከሰማይ የተገኘች ማለት ነው፡፡ ይህንንም ዜማ ከፍ አድርጎ በሚያሰማ/ በሚያዜም/ ጊዜ ሰው፣እንስሳና አዕዋፍ ሁሉ እርሱ ወዳለበት ቦታ ተሰብስበው ከጣዕሙ የተነሣ መንፈስን የሚያድሰውን ልቡናን የሚያስደስተውንና አጥንትን የሚያለመልመውን ሰማያዊን ዜማ ይሰማሉ፡፡ ቅዱስ ያሬድ በግእዝ፣ በዕዝልና በዓራራይ ዜማውን እያስማማ እግዚአብሔርን ማመስገኑን ቀጠለ፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል የዜማውን ጣዕም ከሰሙና ከተረዱ በኋላ እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን መገልገያና ለሕዝቡ መባረኪያ የሰጣቸው መሆኑን በመገንዘብ ሊቃውንቱንና ካህናቱን “ተቀበሉትና ለቤተ ክርስቲያን መገልገያ ይኹን” ብለው አዘዟቸው። ነገር ግን ካህናቱና ሊቃውንቱ ምን ምልክት ዐይተን እንቀበለው ብለው መለሱላቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ንጉሡ እርሱ አምላካችን እግዚአብሔር ይግለጽልን ብለው ከታኅሣሥ አንድ ቀን ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ ሰባት ቀን ሱባዔ እንዲያዝ አወጁ፡፡ ታኅሣሥ አንድ ቀን ሰኞ ዕለት ውሎ ነበርና ከሰኞ እሰከ እሑድ አንድ ሱባዔ ይዘው በየቀኑ የአክሱም ጽዮን ማርያምን ቤተ ክርስቲያን እየዞሩ አራት መቶ እግዚኦታና አርባ አንድ በእንተ ማርያም እያደረሱ ምሕላውን አካሔዱ፡፡ በሰባተኛው ቀን እሑድ ዕለተ ምሕላውን ጨርሰው ሲያሳርጉ ጌታ በዕለተ ዐርብ እንደተሰቀለ ሆኖ በአክሱም ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ተገለጸ፡፡ ከዚህም አያይዞ ቅዱስ ያሬድ “ዘበመስቀሉ ተቀነወ ወበነቢያት ተሰብከ መላእክት ወሊቃነ መላእክት ሰብሕዎ ኪያሁ ንሰብክ መድኅነ” ብሎ ነገረ መስቀሉን በማውሳት የወልድ ምሳሌ በሆነው በዕዝል ዜማ ዘመረ፡፡ ትርጓሜውም “በነቢያት ትንቢት የተነገረለትና በመስቀሉ ላይ የተቸነከረው ጌታ መላእክትና የመላእክት አለቆች አመሰገኑት፤ እኛም እርሱ መድኃኒት እንደሆነ እንናገራለን” ማለት ነው፡፡ በዚህ በተገለጸው ምስክርነት መሠረት ዜማው ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ መሆኑ ታምኖ ከዚያን ዕለት ጀምሮ የቅዱስ ያሬድ ዜማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መደበኛ መገልገያ ሆነ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ይህ ቀን ስብከት ተብሎ ተሰይሟል፡፡ ስብከት መባሉም ቅዱስ ያሬድ ዜማ ማስተማር የጀመረበት ነቢያት ይወርዳል፣ ይወለዳል ብለው የተናገሩት ትንቢት ለመፈጸሙ መታሰቢያ ስለሆነ ነው ይህም ቀን አስከ ታኅሣሥ 13 ታስቦ ይውላል፡፡
የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች
ቅዱስ ያሬድን ብቸኛ የግእዝ ሥነ ጽሑፍ መስራች አድርጎ ለማየት በቂ ምክንያት አለን ፡፡ እንዲያዉም የግእዝ ስነ ጽሑፍ
መስራች ከማለት ይልቅ የኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ መሥራች ልንለዉ ይገባል ፡፡
"ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ኃይሌ የቅዱስ ያሬድ ታሪክና የግእዝ ስነ ጽሑፍ ፤ 1999 ፤ ገጽ 3" በዚሁ ጥናታቸዉ እንዳብራሩት የግእዝ ስነ ጽሑፍን ለሁለት ልንከፍለዉ እንችላለን
ይላሉ ፡፡ ምክንያቱን ሲያስረዱ ፦ አንዱ ክፍል ከባህር ማዶ ተጽፈዉ ወደ ግእዝ የተተረጎሙትን መጻሕፍት ይይዛል ፡፡
ሁለተኛዉ ክፍል በቀጥታ በግእዝ የተደረሱትን ድርሰቶች ያጠቃልላል ፡፡
እነዚህም ፡-የቅዱስ ያሬድ፣
የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ ፣ የርቱዐ ሃይማኖት ፣ የአፄ ዘረአ ያዕቆብ ፣ የዐርከ ሥሉስ ፣ የአባ ባሕርይ ድርሰቶች የሚቀድም በግእዝ ቋንቋ የተደረሰ ድርሰት እስከ አሁን አለመገኝቱን ጥናቱ ያሳያል ፡፡
ቅዱስ ያሬድ ድርሰቶችን ሲያዘጋጅ ከቅዱሳን መጻሕፍት የወሰዳቸዉን ርእሰ ጉዳዮች በፈርጅ በፈርጁ እየለየ በድርሰት
ሥራዎቹ እንደ ፈርጥ ተጠቅሞባቸዋል ፡፡
ብሉያትን ከሐዲሳት፣ከሊቃዉንት እያጣቀሰ ያለምንም ችግር የድርሰት ሥራዉን ሊያከናዉን ችሏል ፡፡
የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች መንፈሳዊ ይዘት ያላቸዉ ናቸዉ ፡፡
በድርሰቶቹ የሚታዩት የቃላት አመራረጥ ፣
የዐረፍተ ነገር አወቃቀር ፣ የሚስጥር ፣
የዘይቤ አገላለጥ ቅዱስ ያሬድ ከፍተኛ የስነ-ጽሑፍ ተሰጥኦ እንደነበረዉ ለመረዳት ይቻላል፡፡
በቅዱስ ያሬድ የተደረሱት የዜማ መጻሕፍት አምስት ናቸዉ እነርሱም :
የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች
|
11440
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B4%E1%88%AB
|
ዴራ
|
ዴራ አርሲ ክፍለ ሃገር በዶዶታ ስሬ ወረዳ ከናዝሬት 25 ኪ.ሜ. ደቡብ የምትገኝ ከተማ ናት። በአብዛኛው ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላት ሲሆን በአንድ ከፍተኛ እና በሁለት ቀበሌዎች የተከፋፈለች ከተማ ናት።
የኢትዮጵያ ከተሞችስሬ ከናዝሬት 40 ኪሎሜትር በደቡብ ምስራቅ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የተለያዩ እምነቶች አማርኛና አፋን ኦሮሞ የሚነገርባት አየር ንብረቷም ወይን አደጋ በስንዴ ምርት ስትታወቅ ሌሎች አዝዕርትም የሚመረትባት ድንቅ አካባቢ ናት
|
12952
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%93%E1%8B%AD
|
ፓይ
|
ፓይ ወይም በተለምዶ አጻጻፉ የሚታወቀው ቁጥር የማንኛውም ክብ መጠነ ዙሪያ ለወገብ ርዝመት (ዲያሜትሩ) ሲካፈል የሚገኘው ምንጊዜም የማይቀየረው ቋሚ ቁጥር ነው።
የፓይን እርግጠኛ ዋጋ ማወቅ ባይቻለም ከ 3.141593 እንደሚጠጋ ግን በሂሳብ ስሌት የተደረሰበት ጉዳይ ነው። የፈለግነውን ሁለት ሙሉ ቁጥሮች አካፍለን ፓይን ማግኘት ስለማንችል ኢራሽናል ቁጥር ነው ማለት ነው። በዚህ ምክንያት ፓይ በነጥብ ስርዓት () ሲጻፍ አሃዞቹ ወይም አያበቁም ወይም ደግሞ እራሳቸውን አይደግሙም ፣ ይልቁኑ በማያባራ ዘፈቀደ ሁኔታ ይነጉዳሉ። ይህን ጉዳይ እታች በበለጠ እናየዋለን።
መሰረታዊ ሃቆች
የፓይ ፊደል
በሌላ በኩል ደግሞ ሙሉ ቁጥሮችን በተወሰኑ የመደመረ መቀነስ ማካፈል ማባዛት ክፍ ማድርገና ስኩዌር እና ኩቢክ ሩት በመውስድ ፓይን ማግኘግ ስለማንችል ታራንስዴንታል ቁጥር ተብላላለች። ይህን ሁኔታ ያረጋገጡት በ19ኛው ክፍለ ዘመን የነበር የጀርመን ሂሳብ ተማሪወች ሲሆኑ ጥናቱ እንደ ትልቅ ድል እስካሁን ሲወሳ ይኖርል። በነገራችን ላይ ፓይ () የሚለውን ፊደል ለ ዚህ ቁጥር ያዋለው የኤንግሊዙ ተማሪ
ዊልያም ጆንዝ በ1707 ነበር የወሰደውም ከግሪኩ ቃል "" (የክብ መጠነ ዙሪያ ማለት ነው)" ።
የጆሜትሪ ትርጉሙ
እንግዲህ የክብ መጠነ ዙሪያ ለ ወገብ ርዝመት ስናካፍል የምናገኘው ቋሚ ቁጥር ነው። ክቡ ይነስም ይብዛ ይህ ቁጥርም ምንጊዜም አንድ ነው።:
በሌላ አንጻር ፓይ የክቡ መጠነ ስፋት ለአቋራጭ መስመሩ ግማሽ () ስኴር ሲካፈል የምንገኘው ቋሚ ቁጥርን ነው። አሁንም የክቡ ትልቅነት ወይም ትንሽነት ለዚህ ውድር() ምንም ለውጥ አያመጣም።
በነጥብ ሲጻፍ
የመጀመሪያወቹ የ ፓይ ሓምሳ ቁጥሮች ሲዘረዘሩ ይህን ይመስላሉ...
እርግጥ ነው ከዚ በላይ ሰወች የፓይን የአሃዝ ዝርዝር አስልተዋል አንዳንዶች እስከ መቶ ሌሎች እስክ ሚሊየን እና ቢሊየን በኮምፒውተር ትግዘው ለማስላት ችለውል። በአሁኑ ስዓት ከሁሉ በላይ በማስላት ማእርጉን የያዘው የፓይን አሃዞች ከትሪሊየን በላይ ቁጥሮች, በማግኘት ነው። ይሁንና ማንኛውንም መሬት ያለን ክብ መጠነ ዙርያ ለማግኘት ከ11 አሃዞች በላይ አያስፈልገንም። በአይን የሚተያውን ህዋ በሙሉ የሚያዳርስ ክብንም ለመለካት ከ39 በላይ የፓይ አሃዞች አያስፈልጉንም
የ ዋጋ ሲገመት
የጥንቶቹ ግምት ግን 3 ነበር ። በመስጽሃፍ ቅዱስም ይህ ሲሰራበት ይታያል። ነገር ግን ትክክለኛው ዋጋ ከ3 ይበላጣል።
ሥነ ቁጥር
|
45541
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%89%85%E1%8B%B0%E1%88%9A
|
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ቅደሚ
|
"ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ቅደሚ" በደርግ ዘመነ መንግሥት የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር ነበር።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ቅደሚ
በኅብረተሰባዊነት አብቢ ለምልሚ!
ቃል ኪዳን ገብተዋል ጀግኖች ልጆችሽ
ወንዞች ተራሮችሽ ድንግል መሬትሽ
ለኢትዮጵያ አንድነት ለነፃነትሽ
መስዋዕት ሲሆኑ ለክብር ለዝናሽ!
ተራመጂ ወደፊት በጥበብ ጎዳና
ታጠቂ ለሥራ ላገር ብልጽግና!
የጀግኖች እናት ነሽ በልጆችሽ ኩሪ
ጠላቶችሽ ይጥፉ ለዘላለም ኑሪ!
ግጥም: አሰፋ ገብረማርያም
ዜማ: ዳንኤል ዮሐንስ
ብሄራዊ መዝሙር
የኢትዮጵያ ዘፈኖች
|
12392
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%8B%93%E1%88%8A
|
ሰዓሊ
|
ሥዕል የተለያዩ ቀለሞችን በመጠቀም ሀሳባዊ እና እውነታዊ ምስሎችን በመደብ ላይ የማስቀመጥ ጥበብ ነው። ሥነ-ጥበብ ድርጊት እና ውጤትን የያዘ ጥበብ ሲል ይገልፀዋል፤ ሥዕልን። በሰዓሊነት ሙያ ውስጥ ሸራ፣ ብሩሽ፣ ወረቀት እና ሌሎች መሳሪያዎች ሊያስፈልጉ ይችላሉ። ነገር ግን በዘመናዊ የሥዕል ጥበብ ውስጥ በአሸዋ፣ የሸክላ አፈር እና ሌሎች ነገሮችን መጠቀም ተችሏል። ሥዕል ውድ በሆኑ ነገሮች (ለምሳሌ ወርቅ) ሊዋብ ይችላል።
|
37518
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%8A%B3%E1%8B%B6%E1%88%AD
|
ኤኳዶር
|
ኤኳዶር () በደቡብ አሜሪካ የሚገኝ አገር ሲሆን ዋና ከተማው ኪቶ ነው። በጐረቤቶቹ ኮሎምቢያ፣ ፔሩ፣ እና በፓሲፊክ ውቅያኖስ ይዋሰናል። ይፋዊው ቋንቋ እስፓንኛ ነው። ኤኳዶር በእስፓንና «የምድር ወገብ» ማለት ሲሆን ስሙን ያገኘው በዚያው ኬክሮስ ላይ በመቀመጡ ነው።
የኤኳዶር ሪፐብሊክ ዴሞክራስያዊ ሀገር ሲሆን በፕሬዚደንት ይመራል። ከደቡብ አሜሪካ 1000 ኪ/ሜ. ወደ ምዕራብ በፓሲፊክ የሚገኙት ጋላፓጎስ ደሴቶች የኤኳዶር ናቸው። በተጨማሪ ኤኳዶር በተለያዩ ተፈጥሮአዊ መናኸሪያዎች በጣም ብዙ ልዩ ልዩ የዱር አራዊትና አትክልት አሉበት፤ ለምሳሌ የጋላፓጎስ ታላላቅ ባሕር ኤሊ። እነዚህ ኤሊዎች ከአንድ መቶ ዓመት በላይ በሕይወት ሊኖሩ ይችላሉ፣ አንዱ ኤሊ እንኳን የ170 ዓመታት ዕድሜ ነበረው። የተፈጥሮአዊ መናኸሪያ መብቶች በኤኳዶር 2000 ዓ.ም. ሕገ መንግሥት ተረጋግጠዋል።
ኤኳዶር ነፃነቱን በ1822 ዓ.ም. አገኘ። ከዚያ በፊት በስፓኒሽ መንግሥት ቅኝ ግዛት ለረጅም ጊዜ ስትሆን ለአጭር ጊዜ ደግሞ በግራን ኮሎምቢያ ሪፐብሊክ ውስጥ ተጨመረ። የነፃነቱ ትግል ለረጅም ዘመን ቆይቶ ብዙ የሰው ልጅ ሕይወት ፈጅቶ ነበር። ከዚያ ጀምሮ አገሩ ወይም ሲቪል ወይም ወታደራዊ መንግሥታት በመፈራረቅ ኖሮዋል። ምጣኔ ሀብቱ የተለማ ነው። የኗሪ ብሔሮችና አፍሪካዊ-ኤኳዶራውያን ሕዝብ ሁለቱም በኤኳዶር ባሕል ላይ ተጽእኖ በመሆናቸው የአስተዋጽኦ ሚና አጫውተዋል።
|
32546
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%83%E1%89%A2%E1%8A%90%E1%89%B5
|
አቃቢነት
|
አቃቢነት ወይንም ካፓሲታንስ የሚለካው የአንድ ቁስን የኤሌክትሪክ ሙላት (ቻርጅን) የማጠራቀም ችሎታ ነው። የበለጠ ትክክል ለመናገር አንድ ቁስ ላይ በሚያርፍ የቮልቴጅ ጫና ምክንያት ያ ዕቃ ሊያጠራቅመው የሚችለው የኤሌክትሪክ ሙላት መጠን የዚያ ቁስ አቃቢነት ይባላል። ስለሆነም አቃቢነት በአንድ ቁስ ውስጥ የሚገኝ የኤሌክትሪክ ሙላት እዚያ ዕቃ ላይ በተጫን ቮልቴጅ ሲካፈል ይገኛል፡፡ በሒሳብ ቋንቋ፦
መለኪያውም ፋራድ ሲሰኝ 1 ፋራድ 1 ኩሎምብ ሙላት በ1 ቮልት ማለት ነው።
አቃቢነት በኤሌክትሪክ ዑደት ስራ ላይ ተፈላጊ እንዲሁ ያልተፈለገ ባህሪ ሊሆን ይችላል፡፡ ተፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እራሳቸውን ይቻሉ አቃቢዎች በተፈለገው መጠን ዑደቱ ውስጥ ይገባሉ።
አንድ አቃቢ ለመስራት የሚያገለግሉ ኤሌክትሪክ አስተላላፊዎች፣ ጂዎሜትሪያቸው ከታወቀና በነዚህ አስተላላፊዎች መካከል ያሉ ኤሌክትሪክ አጋጅዎች የ ዳይኤሌክትሪክ ጸባይ ቁጥር ከታወቀ የአቃቢው ዋጋ ምን ሊሆን እንዲችል መተንበይ ይቻላል። ለምሳሌ የ"ትይይዩ ሳህን" አቃቢን ብንወስድ፣ ሳህኖቹ ስፋታቸው ቢሆን፣ በመካከላቸው ያለው ክፍተት ርዝመት ቢሆን፣ ከኒህ ሳህኖች የተሰራ አቃቢ ዋጋው እንዲህ ይሰላል
እዚህ ላይ
አቃቢነት ሲሆን
የሁለቱ ሳህኖች ንብብር ስፋት
በሁለቱ ሳህኖች መካከል ያለው ቁስ አንጻራዊ ቋሚ አስተላላቲፍነት ( ወይንም ዳይኤሌክትሪክ ቁጥር) ነው። ( ይህ ቁጥር ለኦና = 1 ዋጋ አለው)
0 የ ኤሌክትሪክ ቋሚ ቁጥር ሲሆን
ደግሞ በሁለቱ ሳህኖች መካከል ያለ ክፍተት ነው።
አቃቢነት እንግዲህ ከሳህኖቹ ተነባባሪ ስፋት ጋር እኩል ሲያድግ፣ በሳህኖቹ መካከል ከሚፈጠረው ክፍተት ርዝመት አንጻር የተገላቢጦች ያድጋል ማለት ነው።
በአቃቢ ውስጥ ሙላት ሲጠራቀም፣ አቅም ም ይጠራቀማል። የዚህ የተጠራቀመ አቅም መጠን እንዲህ ይሰላል፦
የተጠራቀመው አቅም ሲሆን ; አቃቢነት; እና ቮልቴጅ ናቸው።
የተለያዩ የአስተላላፊ ቅርጾች የተለያዩ አቃቢነት እንዳላቸው
ተጨማሪ ንባብ
ኤሌክትሪክ ዑደት
|
51202
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%B4%E1%8A%95%E1%8C%A4
|
ጴንጤ
|
(ከ በግዕዝ : ጴንጤ) አንድ መጀመሪያ ነው - ትግርኛ ለ ቋንቋ ቃል የጴንጤቆስጤ እና ሌሎች የምስራቅ-ተኮር የፕሮቴስታንት ክርስቲያኖች ውስጥ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ , እና የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የዲያስፖራ. ዛሬ ቃሉ የሚያመለክተው በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ማኅበረሰቦች ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም የወንጌላውያን ክርስቲያን ቤተ እምነቶች እና ድርጅቶች የኢትዮጵያ-ኤርትራዊ ወንጌላዊነት ወይም የኢትዮጵያ-ኤርትራዊ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያንን ነው ፡ አንዳንድ ጊዜ ቤተ እምነቶች እና ድርጅቶች ወኒግላው (ከ ግእዝ -በልዩላዊ) በመባል ይታወቃሉ ፡
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ወንጌላውያን ክርስቲያኖች በአሜሪካ እና በአውሮፓውያን የፕሮቴስታንት የወንጌል ተልእኮ ምክንያት ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት በተውጣጡ ሥነ-መለኮታዊ ልዩነቶች ምክንያት በወጡ ወጣቶች ላይ እና በኋላም በእነሱ ላይ ስደት በተስፋፋባቸው ወጣቶች መካከል ነው ፡ ክርስቲያኖች የ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናት, ሌላ ቅርንጫፎች ክርስትና, ወይም ወደ የፕሮቴስታንት ሚስዮናውያን እርዳታ ጋር ሌሎች ሃይማኖቶች የተቀየሩ ንስሐ የኢትዮጵያ ክርስትና መሠረተ-መለኮታዊ ማሳለፊያዎች አስተዋሉ ነገር. የፔንታይ አብያተ ክርስቲያናት እና ድርጅቶች ከተፈጠሩበት ጊዜ አንስቶ በመካከላቸው የታወቁ እንቅስቃሴዎች ጴንጤቆስጤዝም ፣ የባፕቲስት ባህል ፣ሉተራናዊነት ፣ ሜቶዲዝም ፣ ፕሬስቢቴሪያኒዝም እና ሜኖናውያን ፡
ሥር-ነክ ጥናት
ይህ ቃል እ.ኤ.አ. በ 1960 ዎቹ መጨረሻ የተፈጠረ ሲሆን በጴንጤቆስጤ ተሞክሮ እና በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ለሚያምኑ አብያተ ክርስቲያናት ደስታን የሚያገለግል ነበር ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ኤርትራዊያን ያልሆኑ የአከባቢ ፕሮቴስታንት ክርስቲያኖችን ለመግለፅ ይጠቀም ነበር ፡ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ (በአጠቃላይ በመባል ይታወቃል ክርስቲያናት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ). የሚለው ቃል ቃል "የጴንጤቆስጤ" አንድ በማሳጠር ነው; ሆኖም እሱ ሁሉንም ፕሮቴስታንት ክርስቲያኖችን በተለይም ደግሞ የወንጌላውያን ፕሮቴስታንት ክርስቲያኖችን በእውነቱ በቤተ-እምነት ተከታይም ይሁን አልሆነም ፡ አንዳንድ የምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ እንዲሁ ቃሉን ለትንሽ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የካቶሊክ ሕዝቦች ይተገብራሉ (ግን ይህ ያልተለመደ ነው) ፡ በብዙ ሌሎች ቋንቋዎች ያለው አተረጓጎም “ወንጌላዊ” ነው ፡፡ የሚለው "ወንጌላዊት" ማለት ሲሆን ጎን ለጎን ጥቅም ላይ ውሏል . ከእነዚህ ቡድኖች ውስጥ ብዙዎቹ ሃይማኖታዊ አሠራሮቻቸውን በባህላዊ ምስራቅ ክርስቲያን ፣ ግን ፕሮቴስታንታዊ ወንጌላዊ እንደ ዶክትሪን ይገልጻሉ ፡
ቤተ እምነቶች
ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ዋና ዋና የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች ተወላጅ ምክንያት, በቅርበት የተገናኘ አንድ ቡድን ናቸው (ወደ ክፍል የአማርኛ : አብያተ ክርስቲያናት , [ የጥቅስ አስፈላጊ ] ወይም የማህበረሰብ አብያተ ክርስቲያናት) ባፕቲስት , የሉተራን , የጴንጤቆስጤ እና የመኖናውያን ቤተ እምነቶች።
የመጀመሪያ ደረጃ ቤተ እምነቶች
የ የኢትዮጵያ መካነየሱስን (የሕይወት ቃል) ቤተ ክርስቲያን , አንድ ተዓምራዊ ጋር ወንጌላዊት የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት የጴንጤቆስጤ እና ወቅዱስ መጥምቁ ( ባፕቲስት ) ስሮች. እሱ ከሱዳን የውስጥ ተልዕኮ ጋር የተገናኘ እና እርስ በእርስ የተደራጀ ድርጅት ሲሆን የኤርትራ ቅርንጫፍ አለው ፡
የ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ (የኢየሱስ ቦታ) , አንድ የሉተራን አንድ የሚያካትተው ቤተ እምነት የፕረስቢተሪያን - ሲኖዶስ. የኤርትራ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዚህ የወንጌላውያን ፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን ኤርትራዊ የሉተራን ቅርንጫፍ ነው ፡፡ የኢትዮጵያ የሉተራን ቤተ እምነት ትልቁ የሉተራን ክርስቲያናዊ ቤተ እምነቶች ትልቁ ነው (የክርስቲያን ቤተ እምነቶች ዝርዝርን በአባላት ብዛት ይመልከቱ ) ፡
በ የኤርትራ ወንጌላዊት ሉተራን ቤተ ክርስቲያን , አንድ የሉተራን ወደ ተቀላቅለዋል የትኛው ቤተ እምነት የሉተራን ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽን በ 1963.
የ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች 'ቤተ ክርስቲያን , አንድ የጴንጤቆስጤ ቤተ ጋር ቤተ እምነት የሜኖናውያን ተጽዕኖ.
የ (ክርስቶስ ፋውንዴሽን) ቤተ ክርስቲያን , አንድ የሜኖናውያን ጋር ቤተ እምነት የጴንጤቆስጤ ተጽዕኖ.
ክርስቲያን ወንድሞች
አንዳንድ የፔንታይ ማህበረሰቦች በተለይም የመካነ ኢየሱስ ሉተራን ቤተክርስትያን - ዋናውን ባህላዊ የኢትዮጵያ እና የኤርትራን የክርስቲያን ስነ ህዝብ በሚወክሉ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ-ክርስትያናት ተጽዕኖ ተደርገዋል ፣ ግን በአብዛኛው በአምልኮአቸው እና በስነ-መለኮታቸው በጣም ጴንጤ ናቸው ፡፡ .
ሌሎች ቤተ እምነቶች
አማኑኤል ባፕቲስት ቤተክርስቲያን
ምስጋና ቤተክርስትያን ኢትዮጵያ
የእግዚአብሔር ጉባኤዎች - ጴንጤቆስጤ
ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን (የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን)
እምነት ክርስቶስ
ብርሃነ ወንጌል - የወንጌል ብርሃን
የኢትዮጵያ አዲስ ኪዳን ባፕቲስት ቤተክርስቲያን
ወንጌላዊት ቤተክርስትያን ኤርትራ
የሉተራን ቤተክርስቲያን ኤርትራ
የመካከለኛው ምስራቅ አጠቃላይ ተልዕኮ
የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን
ወደ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ውስጥ ይወከላል በኢየሩሳሌም ኤፒስኮፓል ቤተ ክርስቲያን እና በመካከለኛው ምስራቅ እና የእስክንድርያው ኤፒስኮፓል የአንግሊካን ጠቅላይ ግዛት : ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሁለቱም የአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም የሰሜን አፍሪካ ቀጠናን ያካተተ የግብፅ ሀገረ ስብከት አካል ናቸው ፡ በኢትዮጵያ ሁለት የኤስ ቆስ አብያተ ክርስቲያናት አሉ ፣ አንደኛው አዲስ አበባ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በጋምቤላ ሲሆን በኤርትራ ውስጥ በአሁኑ ወቅት በግልፅ የሚሰሩ ምዕመናን የሉም ፡
አንድነት እና ኢ.ሲ.ኤፍ.
የ , ወይም የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ህብረት, አንድ በጊዜያዊ ነው የተወለደው-እንደገና , ሥላሴን ክርስቲያኖች. 22 አባላት ያሉት አብያተ ክርስቲያናት ያሉት ሲሆን እ.ኤ.አ. በ 2004 ስታቲስቲክስን መሠረት በማድረግ 11.5 ሚሊዮን አባላት በየአመቱ 4 ሚሊዮን ያድጋሉ ፡ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት, በየትኛውም ቤተ እምነት የተነሳ, በአገር የታወቁ ናቸው እንደ አብያተ ክርስቲያናት ( ' ወይም ') [ የጥቅስ ያስፈልጋል ] በአማርኛ አንድ 'ክርስቲያኖች መካከል ማህበረሰብ' ያለውን የስሜት ሕዋሳት ውስጥ 'አብያተ ክርስቲያናት' ትርጉም ፣ የኢትዮጵያ ኦፊሴላዊ የሥራ ፌዴራላዊ ቋንቋ ፡፡ ከእነዚህ አብያተ ክርስቲያናት መካከል አብዛኞቹ እንደ የኢትዮጵያ ምረቃ ሥነ መለኮት ትምህርት ቤት ፣ የወርቅ ዘይት ሚኒስትሮች ፣ የወንጌላዊያን መንፈሳዊ ኮሌጅ ፣ የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር እና መሰረተ ክርስቶስ ኮሌጅ ያሉ ሚኒስትሮችን ፣ ኮሌጆችን እና የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበራትንም ያገለግላሉ ፡፡ እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ብዙውን ጊዜ ሰባኪዎችን በመለዋወጥ እና የቤተክርስቲያን ጉባኤዎችን በማዘጋጀት አብረው ይሰራሉ ፡
እ.ኤ.አ. በ 2005 ከአለም የክርስቲያን ዳታቤዝ ባወጣው አኃዛዊ መረጃ መሰረት የኢትዮጵያውያን የበዓለ አምሣ / የካሪዝማቲክ አባላት ከ 16 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሀገሪቱን የኢትዮጵያ ፔንታይስ አድርገው ይሸፍናሉ ፡ ግለሰባዊ ቡድኖቹ የቃል ሕይወት ቤተክርስቲያን (ቃሌ ሄወት) ቤተክርስቲያን ፣ መካነ ኢየሱስ ፣ የክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት ፣ የምስጋና ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ፣ የእግዚአብሔር ጉባኤ ፣ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ፣ እምነቶች ክርስቶስ ፣ መሰረት ክርስቶስ ፣ የብርሃን ሕይወት ቤተክርስቲያን ፣ ሙሉ ወንጌል (ሙሉ የወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን) እና በኢትዮጵያ ውስጥ በትንሹ ከ 12 ሚሊዮን በላይ ፔንታይስ የተገነቡ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ፡፡ ሆኖም እንደ ወርልድ ክርስትያን ኢንሳይክሎፔድያ የወንጌላውያን ማህበረሰብ ከ 13.6% ብቻ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው ፡ በ 1994 ቱ የመንግስት ቆጠራ መሠረት ፕሮቴስታንት ክርስቲያኖች 10% የሚሆነውን ህዝብ ይይዛሉ (ዛሬ ከ7-8 ሚሊዮን ያህል ነው) ፡፡ በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት እና ቤተ እምነቶች በተሰጡ የአባልነት እና ተጣማሪ መረጃዎች መሠረት የኢትዮጵያ ፕሮቴስታንቶች ከ 18.59% የሚሆነውን የአገሪቱን ህዝብ ቁጥር እንደሚይዙ ይናገራል ይህም ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በቅርቡ የተገኘው መረጃ ነው ፡
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ያሉ የወንጌላውያን ሰዎች አንድ ሰው የሚድነው ኢየሱስን ለኃጢአት ይቅርታ ጌታ እና አዳኝ አድርጎ በማመን ነው ፡ የሥላሴ አንድ አካል በሆነው በአብ ፣ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ያምናሉ ፡ ቀኖናዊ ወንጌሎችን እንደሚቀበሉ ሌሎች የክርስቲያን ቡድኖች ሁሉ ፔንታይስ በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ብዙ ጊዜ እንደተጻፈ እና አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ በተጠመቀ እንደሚያሳየው ‹ ዳግም መወለድ › ያምናሉ ፡ እንዲሁም የውሃ ጥምቀት. በልሳን መናገር እንደ አንድ ምልክት ተደርጎ ይታያል ፣ ግን “ክርስቶስን መቀበል” ብቸኛው ምልክት አይደለም ፣ ይህም አዲስ የአኗኗር ዘይቤ እና ማህበራዊ ባህሪን ማካተት አለበት ፡
ምንም እንኳን በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ያሉ ሁሉም የወንጌላውያን ፕሮቴስታንት ቅርንጫፎች በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ አንድ ወይም ሁለት ሥነ-መለኮታዊ ልዩነቶች ወይም የተለያዩ አቀራረቦች ቢኖራቸውም ፣ አራቱም ዋና ዋና ቅርንጫፎች በሙሉ ለተወለዱ ክርስቲያኖች የተለመዱትን እምነቶች ይከተላሉ ፡፡ አራት ዋና ዋና እምነቶች ደግሞ ፓስተሮች (ለመለዋወጥ ) እና (ተጋብዘዋል ጊዜ ሰባኪዎች በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ለማገልገል መፍቀድ ሙሉ የኅብረት ). ሁሉም አራቱ ዋና ዋና አብያተ ክርስቲያናት እና ሌሎችም እንዲሁ የተለያዩ የወንጌል ዘፋኞችን ፣ መዝሙሩን (የወንጌል ሙዚቃን ወይም የመዝሙር ) አዘጋጆችንና የመዘምራን ቡድኖችን ያካፍላሉ እንዲሁም ያዳምጣሉ ፡
ለአብዛኛው ክፍል የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ፕሮቴስታንቶች እንደሚናገሩት የክርስትና ቅርፃቸው የአሁኑ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ-ክርስቲያናት ማሻሻያ እና ወደ ቀደመው የኢትዮጵያ ክርስትና መመለስም ነው ፡፡ የኢትዮ ያ ኦርቶዶክስ ክርስትና ከ 960 ዎቹ በኋላ በንግስት ጉዲት ዘመነ መንግስት አብዛኛው የቤተክርስቲያኗን ንብረት እና የቅዱሳት መጻሕፍትን በማጥፋትና በማቃጠሏ አረማዊነት ያምናሉ ፡ እነዚህ ክስተቶች የምስራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ-ክርስቲያናት ቀስ በቀስ ወደ አረማዊነት እንዲመሩ እንዳደረጋቸው ይናገራሉ ፣ ይህም አሁን በአምልኮ ሥርዓቶች ፣ በጆሮ መስማት እና በተረት ብቻ ተቆጥሯል ይላሉ ፡ የፔንታይ ክርስትያኖች የአሁኑን የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናትን “ሴኩላሪዝድ አስተምህሮ” የተባሉትን ፣ አብዛኛዎቹ የኦርቶዶክስ ተከታዮች በመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያ እና በገጠር ካህናት በሚጠቀሙት ዲቶሮካኖኒካል መጻሕፍት መሠረት ለመኖር አለመቻላቸውን ተጠቅሰዋል ፡ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትምህርት ላይ ላላቸው እምነትም እንዲሁ በዋናነት ይመሳሰላል ፡፡ የፔንታይ ክርስቲያኖች ከ 1960 ዎቹ በፊት የነበረውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና ታሪክ ምንም እንኳን የታሪክ ቀጣይነት ባይኖራቸውም እንደራሳቸው ታሪክ ይጠቀማሉ ፡፡
የአሜሪካ እና የአውሮፓውያን ሚስዮናውያን በሱዳን የውስጥ ተልዕኮ (ሲም) አማካኝነት ከመናውያን እና ከጴንጤቆስጤ አብያተ ክርስቲያናት ጋር ፕሮቴስታንትን ያሰራጩት በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነበር ፡ ሲም ኢትዮጵያ ከጣሊያን ጋር በገባችበት ጦርነት ከአጭር ጊዜ እገዳ በኋላ እንቅስቃሴውን በቀጠለበት ጊዜ ሚስዮናውያኑ በመጀመርያ ተልእኳቸው ፍሬ እንደተደነቁ ተጽ ል ፡ ሲም በኢትዮጵያ ላይ ትልቅ ተፅእኖ ነበረው ፡ ጴጥሮስ ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያው የፕሮቴስታንት ሚስዮናዊ ነበር እና የ ላይ ከፍተኛ ተደማጭነት ተጽዕኖ ነበረው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ , አንድ የሉተራን ቤተ እምነት (አንዳንዶች [ ማን? ] እንደ ፔንታይ ወይም የዌኒግላው እንቅስቃሴ እንቅስቃሴ መሥራች አድርገው ይመለከቱታል [ ጥቅስ ያስፈልጋል ] ) ፡ ፕሮቴስታንት ክርስትያኖች አሁንም በገጠር ክልሎች ስደት እያጋጠማቸው የሰማዕታት ድምፅ ይረዷቸዋል ፡ ሆኖም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ፣ ሙስሊሞች እና በሀገሪቱ ከተሞች ውስጥ እየጨመረ በሚሄደው የፔይንታይ ክርስቲያኖች መካከል መቻቻል እየጨመረ መጥቷል ፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የበላይነት እና እየጨመረ በሄደው የሙስሊም ህዝብ ብዛት የፔይንታይ ክርስቲያኖች ብዛት ወደ 16.15 ሚሊዮን (ከጠቅላላው ህዝብ 19 በመቶ) እንደሚገመት መረጃው ይፋ አድርጓል ፡፡የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፡
ሙዚቃ ፣ የበለጠ በቴክኒካዊ ደረጃ የሚናገሩ “መዝሙሮች” ወይም “መዝሙሮች” ( መዝሙር - መዝሙር - በአማርኛ ፣ [ የጥቅስ አስፈላጊነት ] የኢትዮጵያ ኦፊሴላዊ ቋንቋ እና እንዲሁም በሌሎች የኢትዮጵያ-ኤርትራዊ ቋንቋዎች) በስብከት እና በየቀኑ የፔንታይ / የወንጌላውያን ክርስቲያኖች ሕይወት። ሙዚቃ ለእግዚአብሄር ፣ እና ለእርሱ ብቻ መሆን አለበት በሚል እምነት ፣ መዝሙሩ የዘር ወይም የባህል ወሰን የለውም ፣ እንዲሁም በምን ዓይነት ዘይቤ ወይም መሳሪያ ላይ እንደሚጠቀም ገደብ የለውም ፡ ሆኖም ፣ ወደ አሜሪካዊው የወንጌል ሰባኪዎች ወደ ንግድ ሥራ እና ወደ ማቋረጥ እንዲመሩ ያደረጓቸው ግልጽ ተጽዕኖዎች አሉ ፡፡ ሲዲ ፣ ካሴት እና ዲቪዲ ሽያጮች አሁን እየጨመረ ከሚገኙት ብርቅዬ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ አንዱ ናቸው ፡፡
የፔንታይ ሙዚቃ ታሪክ
ምንም እንኳን ከቀድሞ ትውልድ ዘፋኞች መካከል ካሴት ለመስራት የሚያስችላቸው የገንዘብ አቅም ባይኖራቸውም በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በሚዘምሩበት ጊዜ በተለያዩ መንገዶች በኢትዮጵያ ሙዚቃ ላይ ተጽዕኖ አሳድረዋል ፡፡ ከቀደምት ዘማሪዎች መካከል አዲሱ ወርቁ ፣ ለገሰ ዋትሮ ፣ በምስራች ድምፀት ራዲዮ ይዘምሩ የነበሩት አርአያ ቤተሰቦች ይገኙበታል ፡፡
የመካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ከስዊድን የመጡ መዝሙሮችን በመተርጎም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በመላመድ ቀዳሚ ሆነች ፡፡ በ 1970 ዎቹ መጀመሪያ ላይ መሰረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መዘምራን ተቋቋሙ ፡፡ ከሙሉ ወንግል ከጽዮን መዘምራን የተወሰኑት አዲስ ከተቋቋመው የመዘምራን ቡድን ጋር በመቀላቀል መሰረተ ክርስቶስ በኢትዮጵያ ቋንቋዎች መዝሙሮችን ማዘጋጀት ቀጠለ ፡፡ በእነዚህ የመጀመሪያ ዓመታት ፣ እንደ ቤቴል ዘማሪዎች ያሉ ሌሎች ቡድኖችም እንዲሁ የኢትዮጵያን የወንጌል መዝሙሮችን ያዘጋጁ ነበር ፡፡
ቀደምት መጡ
ከቀደምት መጪዎቹ መካከል ሙሉ ወንግል እና መሰረቴ ክርስቶስ የመዘምራን ቡድን የነበሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት እስከ ቾር ኢ እና ኤፍ ያሉ ሲሆን እያንዳንዳቸው 8,9 አልበሞች አሏቸው በሌሎች ቅርንጫፍ ከተሞች ውስጥ ከሚገኙት ከእነዚህ አብያተ ክርስቲያናት መካከል የተወሰኑት ለዝማሬ ስሞች ነጠላ ፊደላትን መጠቀማቸውን አቁመው በምትኩ ስሞችን ይተገብራሉ ፡፡ ሌሎች ቀደምት መጤዎች መካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን መዘምራን ፣ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን መዘምራን ፣ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን () የመዘምራን ቡድን በ 1970 ዎቹ አካባቢ ደርሷል ፡፡ በእነዚህ እና በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሶሎ ድምፃውያን በፍጥነት ፈጠሩ ፡፡ አዲሱ ወርቁ ፣ ደረጀ ከበደ ፣ ታምራት ዋልባ ፣ ተስፋዬ ጋቢሶ ፣ እየሩሳሌም ተሾመ ፣ ታምሬት ኃይሌ ፣ ታደሰ እሸቴ ፣ ግዛቸው ወርቁ ፣ አታላይ ዓለም እና ሸዋዬ ዳምጤ ቀደም ብሎ የተጀመረውን ይህንን ዝርዝር ይሞላሉ ፡፡
ከ 20 ኛው ክፍለዘመን መጨረሻ ዘፋኞች መካከል ቃሌ ህይወት ቤተክርስቲያን ካልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) ፣ አሃህህ የወንጌል መዘምራን ፣ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ዳግማዊ ጥላሁን (ዳጊ) እና የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ኤልያስ አበበ ይገኙበታል ፡፡ ሌሎች አውታር ከበደ ፣ ሶፊያ ሽባባው ፣ መስፍን ጉቱ ፣ ምህረት ኢተፋ ፣ አቶዓለም ጥላሁን (ላሊ) ፣ ገዛኸኝ ሙሴ ፣ አዜብ ኃይሉ እና ሌሎችም ይገኙበታል ፡፡ መጋቢዎች የሆኑ ዘፋኞችም አሉ ፣ ከእነዚህም መካከል ዳዊት ሞላልኝ ፣ ካሳሁን ለማ እና ዮሐንስ ግርማ ናቸው ፡ የኦሮሚኛ ቋንቋእንደ ካባ ፊዶ ፣ አባባ ታምስገን ፣ ኢዮብ ያዳታ ፣ ባአካ ባይያና ፣ መጋርሳ ባቅቃላ ፣ ዳስጣ ኢንሳርሙሙ ፣ ቢሊሴ ካርሳአ እና ሌሎችም ያሉ ዘፋኞች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትን አገልግለዋል ፡፡ በትግርኛ ቋንቋ እንደ ዮናስ ኃይሌ ፣ ምህረት ገብረታቲዮስ ፣ ሰላም ሀጎስ ፣ ሩት መኩሪያ ፣ የማነ ሀብቴ ፣ አድሃኖም ተክለማሪያም እና ዮናታን እና ሶሱናን የመሰሉ ዘፋኞች አሉ ፡፡ አዳዲስ ዘይቤዎችን በማስተዋወቅ በበርክሌይ የሙዚቃ ኮሌጅ የተማሩ እንደ ዳዊት "ዳኒ" ወልዴ ያሉ ወጣት ተዋንያን ናቸው ፡
ክላሲካል እና መሳሪያዊ የወንጌል ዘፈኖችም ከፍቅሩ አሊጋዝ እና ከቤቴል ሙዚቃ አገልግሎት ጋር አብረው አድገዋል ፡፡ እንዲሁም ፍቅሩ አሊጋዝ እ.ኤ.አ. ከ 1998 አንስቶ በዓመት ሁለት ጊዜ ለአከባቢው ክርስቲያን እና ክርስቲያን ያልሆኑ የማህበረሰቡ አባላት ለመድረስ ከቤቴል የውዳሴ እና አምልኮ መዘምራን ጋር ለሦስት ቀናት የውዳሴና የአምልኮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ፡፡ የበለጠ ልዩነትን አምጣ ፡፡ እንዲሁም እንደ ሂሩት በቀለ ፣ ሰለሞን ዲሳ እና ሙሉቀን ያሉ ቀደምት ዓለማዊ ዘፋኞች ከተለወጡ እና እንደገና ከተወለዱ በኋላ የወንጌል ዘፈኖችን አፍርተዋል ፡፡ በክርስቲያን ግርማ (በአሁኑ ጊዜ በዴንቨር ፣ በኮሎራዶ) ፣ እንደ አቤኔዘር ግርማ ፣ እነኩ ግርማ ፣ ናትናኤል በፍቃዱ ፣ ብሩክ በድሩ ፣ ዳንኤል በእውነቱ ፣ በረከት ተስፋዬ ፣ ሳምሶን ታምራት ፣ ያቤትስሰማ ፣ አሜሃ መኮንን ያሉ በርካታ የሙዚቃ አቀናባሪዎች አሉ ፡፡ , እንዳልካቸው ሃዋዝ ፣ እስጢፋኖስ መንግስቱ ፣እና ስፍር ቁጥር የሌላቸው የቤተክርስቲያን የሙዚቃ አጫዋቾች አሉ ፡፡ ዲጂታዊ የሙዚቃ ቅንብር ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ሲኤምኤምኤ ፣ ቲ.ኤስ.ዲ.ኤስ. ፣ ፣ ሳሚ ፣ ናቲ ፣ ላንጋኖ ፣ ቤጌና ፣ ኪኔይ ፣ አልባስተር ፣ ሻሎም ፣ ዘፀአት እና ቤተልሔምን ጨምሮ ከሃያ በላይ ክርስቲያን የሙዚቃ ስቱዲዮዎች አሉ ፡፡
በወላይታ ፣ በሀዲያ ካምባታ ፣ በሲዳማ እና በሌሎችም የደቡብ አካባቢዎች የሚዘፍኑ የወንጌል ዘማሪዎችም አሉ ፡፡
በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘመናዊ የሙዚቃ ውዝግብ
በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የተጫወቱት እንደ ኤልያስ መልካ ያሉ በኢትዮጵያ ውስጥ በጣም ዝነኛ የሙዚቃ አጫዋቾች ከዚያ በኋላ ወደ ዓለማዊ ሙዚቃ ተለውጠዋል ፡፡ አንዳንድ ዘመናዊ ዘፋኞች ብዙውን ጊዜ የአሜሪካን ወንጌላዊያን አርቲስቶችን ያስመስላሉ ፣ የባህላዊው የኢትዮጵያ ወንጌላዊነት እውነተኛ ሥዕል ያልሆኑ ሌሎች የአኗኗር ዘይቤዎችን አካተዋል ፡፡ የአጥቢያ ቤተክርስቲያኖች የቡድን መዘምራን ባህል በተወሰነ ደረጃ ተተኪ ተተኪ ሆኗል ነጠላ ዜማዎች በአኗኗራቸው በአወዛጋቢነት ታዋቂነትን ያተረፉ በግለሰባዊ ነጠላ ዘፋኞች ብዙውን ጊዜ ዓለማዊ ዝነኞችን ከሚመስሉ ፡፡
: ጴንጤ) : ወንጌላዊ).
(ጴንጤ) / (ወንጌላዊ)
አብያተ ክርስቲያናት (
— መዝሙር –
|
45283
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%88%E1%8A%AB%E1%8B%89
|
ለካዉ
|
ግእዝ ቋንቋ እንማር፦
ሰላም ለኩልክሙ = ሰላም ለእናንተ ይሁን
እፎ ሀለውክሙ = እንዴት አላችሁ
ለእመ ንትመሀር ልሳነ ግእዝ = ግእዝ ቋንቋ ብንማር
ምንት ይመስለክምሙ? = ምን ይመስላችኋል
የግእዝ ቋንቋ አስፈላጊነት እና አሁን ያለበት ሁኔታ፦
ግእዝ ቋንቋ በኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ እስከ አጼ ይኩኖ አምላክ ዘመነ-መንግሥት ድረስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ ነበር።
በግእዝ ቋንቋ የኢትዮጵያ ታሪክ፥ የቤተክርስቲያን መጻሕፍት ከግሪክ፥ ከዕብራይስጥ፥ ከአረብኛ፥ ከሱርስት ቋንቋዎች የተተረጎሙብት ጥንታዊ ቋንቋ ነው። ላቲን የምዕራባውያን ቋንቋ እና ታሪክ መሠረት እንደሆነ ግእዝም የኢትዮጵያውያን ቋንቋ፥ ታሪክ፥ ወግ፥ ልማድ፥ ሃይማኖት፥ ጥበብ፥ ፍልስፍና መሠረት ነው።
ኢትዮጵያን ለማጥናንት፥ የአባቶችን ጥበብ ወደ ልጆች ለማስተላለፍ ግእዝ እጅግ አስፈላጊ ነው፣ ግእዝ አሁን በኢትዮጵያ በመጠኑም ቢሆን በአሁኑ ሰዐት አገልግሎት የሚሰጠው በኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው።
በአሁኑ ሰዓት የግዝ መጻሕፍት ሁሉ ወደ አማርኛ በመተርጎም ላይ በመሆናቸው፣ የቤተክርስቲያኒቱ አገልግሎትም ሕዝቡ ወደሚጠቀምበት ቋንቋ ወደ አማርኛ እያደላ ይገኛል።
አግልግሎቱ በማኅሌትና፥ ከዜማ ጋር በተያያዙ አገልግሎቶች እየተወሰነ ነው።
በሀገር ደረጃም፥ እንኳን ኢትዮጵያውያንን መላውን አፍሪካ የሚያኮራው ብቸኛው የአፍሪካውያን የግእዝ ፊደል እና የግእዝ ቋንቋ በወቅቱ ባለው አገርና ታሪክን የሚገድል የክፍፍክ ፖለቲካ ሂደት ምክንያት ተገቢው ትኩረት ተነፍጎታል፤ አንዲያውም የነጻነት ቤቱን፥ ተወልዶ ያደገበት ሀገሩን ኢትዮጵያንም እንዲለቅ የላቲኖች ፊደል ቅኝ ግዦቹ ሆነው ገብተው በገዛ-ምድሩ ላይ ነጻነቱን፥ ታላቅንቱን፣ መብቱን ገፈውት ይገኛል።
በግዝ ፊደል በኢትዮጵያ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች ቋንቋዎችን ሁሉ መጻፍ እንደሚቻል፣ ከዚያም አልፎ ለእናቱ ፍሪካም «አንድ ለናቱ» እንደ ሆነ ይታወቃል።
እንኳ ኢትዮጵያውያን የላቲንን ፊደል እደ ጣሊያን ወታደር መርዝ አስታጥቀው ወደ ኢትዮጵያ የላኩት ምዕራባውያንም አሳምረው ያው ቃሉ።
ግእዝና የግእዝንም ፊደል እናስታምምህአለን ብለው በቤታቸው (በአውሮጳ) እስተኝተው ሞቱንም ሽረቱንም እየተከታተሉት ነው።
ይህም ማለት በጉለበት እየቀሙ የወሰዱአቸው ግእዝ መጻሕፍት በብዛት በእጃቸው ይገኛሉ፣ በልዩ ልዩ ትምህርት ቤቶችም ግእዝ ቋንቋን ያስተምራሉ። ይህም የግእዝን ማንነት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያውያንን ክብርና ጥበብ እንዲረዱ ማገዙ የታወቀ ነው።
ታዲያ ያን እያወቁ ለምን በኦሮምያ ክልል የግእዝ መልክ እንዲጠፋ ወሰኑበት?
የሚሳዝኑት የፍሪካን ማንነት መገለጫ የሁኑትን ታሪኮች፥ ቋንቋዎች፥ ፊደሎች ሁሉ እንዳጠፉ በታሪክ የሚታዎቁትና የላቲንን ፊደልን በግእዝ ፊደል ለመተካት የወሰኑት ምዕራባውያን አይደሉም፣ የሚያስገርሙት በቀደመው የባርንት ዘመን አፍሪካውያን የገዛ ወንድሞቻቸውንና እህቶቻቸውን ከባርያ ፈንጋዮች ተዋግተው በማትረፍ ፈንታ ተባባሪወች በመሆናቸው፥ በታሪክም፦ በትውልድም ላይ የፊት ሀፍረት የሆነ በደል ሰርተው እንዳለፉ ሰዎች፥ አሁንም በሀገራችንም የግእዝን ፊደል፥ በላቲን ተክተው፥ ለመጠቀም የተስማሙ ኢትዮጵያውያን ናቸው።
የአፍሪካውያን ሁሉ የነጻነትን እና ማንነት ምልክት የሆነውን፣ ልጆቻቸው የኛ የሚሉትን እና መለያ ምልክታቸው የሆነውን የግዝ ፊደል ቦታ፥ ለላቲን ፊደል በመስጠታቸው አሰነዋሪ ታሪክ የሆንባቸዋል፤ አሁን ቀኝ ገዞች በተወገዱበት፣ የባሪያ አሳዳሪው ስርአትም በተንኮታኮተበት ዘመን፣ አፍሪቃዊው ግእዝ በላቲን ፊደል ሀገሩን ለምን ይቀማል?
ለምንስ ሌሎች ነጻነቱን በሀገሩ ላይ ገፈውና ማርከው፥ በላዩ ላይ ሌላ የላቲን ፊደል ሹመው፥ ወደ አሮፓ ወሰዱት?
የኢትዮጵያውያንን የክብር ፊደል፥ የፍሪካን ምልክት ማነው በሀገሩ ላይ በላቲን ሰንሰለት እጅ እግሩን ያሰረው?
ተፈቶ በነጻነት ሊሄድ ይገባዋል፤ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የራሳችውን ፊደል ሊጠቀሙ እንጂ፥ «የሰው ወርቅ አያደምቅ» እንዲሉ የሚታወቁት በጥንታዊ ግእዝ ፊደላችው እና ቋንቋቸው ስለሆነ የግእዝን ቋንቋ ማወቅና ማሳወቅ፥ ወደ ትውልድም ማስተላለፍ፥ የሁሉም ኢትጵያውያን ኃላፊነት ነው።
የግእዝን ቋንቋ ወደ ትውልድ ማስተላለፍ ማለት ታሪክን፣ ክብርን፣ ማንነትን፣ ሃይማኖትን፣ ጥበብን፣ አብነትን ለትውልድ ማቆየትና ራስንም ማወቅ ነው።
ግእዝ እንማር
ግእዝ ቋንቋ በቀለሉ ሊጠና የሚችል፥ የተስተከከለ የቋንቋ ህግ ያለው፥ ጥንታዊ ቋንቋ ነዉ፤ ስለዚህ ይህን ጥንታዊ ቋንቋ መማውርና የኢትዮጵያን ጥንታውያን መጻሕፍት መመርመር ለምትፈልጉ ሁሉ የቋንቋውን በር የሚከፍት ትምህርት ለመስጠት ዝግጁ አስተማሮች አይነተኛ ናቸው።
|
45625
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%B3%E1%8B%AD%E1%8A%95%E1%88%B5%E1%8A%93%20%E1%89%B4%E1%8A%AD%E1%8A%96%E1%88%8E%E1%8C%82%20%E1%88%98%E1%88%A8%E1%8C%83%20%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%8A%A8%E1%88%8D%20%28%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%29
|
የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ኢትዮጵያ)
|
የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ሳ.ቴ.መ.ማ.)፣ ኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን የመሰብሰብ፣ የመምረጥ፣ የመተንተንና እሴት አክሎ የማሰራጨት ኃላፊነት የተጣለበት የመንግስት ድርጅት ነው።
የአመሰራረት ታሪክ
በኢትዮጵያ ውስጥ ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎች ስብስብ ማዕከልን ለማቋቋም የመጀመሪያውን ሀሳብ የወጠነው በ1977 እ.ኤ.አ. የኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን (ኢ.ሳ.ቴ.ኮ) ነበር። ኢኒስቲቲዩቱ የተመሰረተበት ዋነኛ ዓላማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን ለመሰብሰብ፣ ለማደራጀት እና ለማሰራጨት የሚያስፈልጉ የተለያዩ አገልግሎቶችንና መገልገያ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ነው።
ዋና መቀመጫውን አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ልዩ ስሙ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ያደረገው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ሳ.ቴ.መ.ማ) በማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር 257/2004 የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን በማፈላለግ፣ በመሰብሰብ፣ በመመምረጥ፣ በማደራጀት፣ በመተንተን እና በጥናትና ምርምር እሴት ጨምሮ በማሰራጨት የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ሽግግር ሂደት የማፋጠን ተልዕኮን በመያዝ የተመሰረተ ነው።
የማዕከሉ ስትራቴጂክ መሰረቶች
የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ በመንግስትና በሕዝብ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለማሳካት የተልዕኮ አፈፃፀም አቅጣጫ ጠቃሚ ኮምፓሶች የሆኑት ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶችና ተቋማዊ ፍልስፍናዎች (ስትራቴጂክ መሰረቶች) ያስፈልጉታል። በመሆኑም የማዕከሉ ስትራቴጂክ መሰረቶች እንደሚከተለው ቀርቧል።
• በ2015 ዓ.ም የኢንፎርሜሽን ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚያስችል የሳይንስና ቴክኖሎጂ ልዕቀት ማዕከል ተገንብቶ ማየት፤
• ቴክኖሎጂን ለልማት ለመጠቀም በሚደረግ ጥረት ዘላቂ የኢንፎርሜሽን ምንጭ መሆን፤
• የባለቤትነት ስሜት
• መደመር
• ተማሪነት
ተቋማዊ ፍልስፍና
• መረጃችን ለሀገራዊ ቴክኖሎጂ ምጥቀት፤
• ተቋማዊ ልዕቀታችን በሰው ኃይላችን፤
• እሴት በማከል እንተማለን፤
ተቋማዊ አወቃቀር ዳይሬክቶሬት
• የምርምርና ትንተና ዳይሬክቶሬት
• የእውቀት አስተዳደርና ስርጭት ዳይሬክቶሬት
• የኢንፎርሜሽን መሰረተ ልማት ዳይሬክቶሬት
የኢትዮጵያ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ
የኢትዮጵያ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ በ2004 ዓ.ም የፀደቀ ሲሆን ሀገሪቷ ውጤታማ የሆኑ የውጭ ቴክኖሎጂዎችን ለማፈላለግ፣ ለመምረጥ፣ ለማስገባት እንዲሁም ለመጠቀም የሚያስችላትን ሀገራዊ የኢኖቬሽን ስርዓት ለመፍጠርም ያለመ ነው።
የፖሊሲው ዓላማ ውጤታማ የሆኑ የውጭ ቴክኖሎጂዎችን በማፈላለግ፣ በመምረጥ እና በማስገባት በማምረቻና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥ የመማር፣ የማላመድ እና የመጠቀም ሀገራዊ አቅም ለመገንባት የሚያስችል የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕቀፍ መፍጠር ነው።
የሀገሪቷን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ችግሮች ጥናትና ምርጥ ተሞክሮ ያላቸው የሌሎች ሀገራት ሁኔታ ላይ የዳሰሳ ጥናት የተካሄደ ሲሆን በዚህም መሰረት አስራ አንድ ወሳኝ የፖሊሲ ጉዳዮች ተለይተዋል። እነዚህም፡- የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የማምረቻና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ ምርምር፣ የፋይናንስ ሥርዓትና ማበረታቻ ሥርዓት፣ ብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት፣ የዩኒቪርሲቲዎች፣ የምርምር ተቋማት፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማትና የኢንዱስትሪ ትስስር፣ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ፣ የአካባቢ ልማትና ጥበቃ እንዲሁም ዓቀም አቀፍ ትብብር ናቸው።
ሀገራዊው የኢኖቬሽን ሥርዓት አስተዳደር መዋቅር የፖሊሲውን አፈፃፀም ለመምራት፣ ለመደገፍ እና ለመከታተል እንዲያስችል ተዘርግቷል። የኢኖቬሽን ሥርዓቱ ዋና ዋና ተዋናዮችም፡- ሀገራዊው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምክር ቤት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ሌሎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዲሁም የኢኖቬሽን ድጋፍና የምርምር ሥርዓት ናቸው።
የኢንፎርሜሽን ስርጭት
የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል አንዱ ቁልፍ ተግባር እሴት የታከለባቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን ማሰራጨት ሲሆን እነዚህን መረጃዎች ለማሰራጨት ማዕከሉ የተለያዩ የማሰራጫ ስልቶችን ይጠቀማል። ከስልቶቹ መካከል የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ድረ-ገፅ ወይም የሳይበር እና የህትመት ሚዲያን ይጠቀማል።
ማዕከሉ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ቴክ-ሳይንስ የተሰኘ መጽሐፍን በሶስት ወር አንድ ጊዜ የሚያሳትም ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ በሳምንት አንድ ቀን ለ30 ደቂቃ ቆይታ የሚያደርግ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አለው። ይህ የቴሌቪዥን ፕሮግራም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢ.ቢ.ሲ) የቴሌቪዥን ጣቢያ የሚሰራጭ ነው።
ሌላው መረጃ የማሰራጫ ስልት የሳይበር ሚዲያ ሲሆን ማዕከሉ የራሱ የሆነ ድረ-ገፅን (/ ወይም ) ይጠቀማል። ይህ ድረ-ገፅ በየቀኑ ከዓለማችን የተሰበሰቡና እሴት የታከለባቸው የተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዜናዎችን የያዘ ሲሆን በተጨማሪም የተለያዩ የምርምር ጥናቶችንና ህትመቶችን የያዘ ነው።
የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካቾች
የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካቾች ስለ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስርዓት፣ ዉስጣዊ መዋቅር፣ ከኢኮኖሚና ከማኅበረሰብ ጋር ስላለው ትስስር እንዲሁም ስርዓቱን የሚያስተዳድሩ አካላት፣ በውስጡ እንቅስቃሴ ለሚያደርጉ እና ስርዓቱ ተፅዕኖ ለሚያደርስባቸው አካላት ጥያቄዎችን የሚመልሱ ተያያዥነት ያላቸው መረጃዎች ናቸው። ይህ የሚያመላክተው በብሔራዊ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስርዓት ላይ የሚመጣ ለውጥ በአምራችና አገልግሎት ሰጪ (የንግድ ተቋማት)፣ ተመራማሪዎች፣ የመንግስት ኤጀንሲዎች፣ በዘርፉ የሚሳተፉ ባለድርሻ አካላት መካከል ያለ ትስስርና ግንዛቤ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንደሚያመጣ ነው።
የምርምርና ስርፀት ሰርቬይ
ምርምርና ስርፀት አንዱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ነው። ይህ አመላካች አዲስ ግኝቶችን ለመፍጠር የሚያስችሉ የዕውቀት ክምችትን እድገት፣ ከግለሰቦች የሚገኝን፣ ከባህልና ከማኅበረሰብ የሚገኝን እውቀት የሚያካትት እንዲሁም የዕውቀት ክምችትን መጠቀምን የሚያጠቃልል ነው። የመጀመሪያው ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ዳሰሳ ጥናት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በ2010 እ.ኤ.አ. የተካሄደ ሲሆን በ2013 እ.ኤ.አ. ሳ.ቴ.መ.ማ ኃላፊነቱን ወስዶ ሁለተኛውን ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ዳሰሳ ጥናት በማከናወን የጥናቱን ውጤት በ2014 እ.ኤ.አ. አውጥቷል።
ዳሳሳ ጥናቱ ሀገሪቱ በምርምርና ስርፀት ላይ ያላትን ኢንቨስትመንትና የሰው ኃይል አግባብ በአራት ዘርፎች ከፋፍሎ የሚያሳይ ጥናት ነው። የመንግስት ተቋማት፣ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ የቢዝነስ ተቋማት እና የግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጥናቱ የዳሰሳቸው ዘርፎች ናቸው። በ2014 እ.ኤ.አ. የታተመው ጥናት በዋነኛነት ሀገሪቱ ለምርምርና ስርፀት የምታወጣው ወጪ ከሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ምን ያህል እንደሆነ ለመጠቆም ነው። ከጥናቱም የተገኘው ውጤት እንደሚያመለክትው የምርመርና ስርፀት ወጪ የሀገሪቱን አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 0.6 በመቶ ነው። ይህም በአፍሪካ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 1 በመቶ የሚሆነውን ወጪ ለምርምርና ስርፀት ማዋል ተብሎ የተቀመጠውን አቅጣጫ የሳተ ውጤት እንዳልሆነ ለመገንዘብ ተችሏል። በተጨማሪም በ2010 እ.ኤ.አ. ከተከናወነው ጥናት ውጤት ጋር ሲነፃፀር አመላካቹ (0.24 በመቶ) በ3 እጥፍ እድገት አሳይቷል።
የኢኖቬሽን ሰርቬይ
ኢትዮጵያ ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገርና የተጀመረውን የልማት ጎዳና ቀጣይነት ባለዉ መልኩ ለማስኬድ እውቀት መር ኢኮኖሚ ልትከተል ይገባል። በእውቀት መር ኢኮኖሚ ኢኖቬሽን ቁልፍ ሚና ይጫወታል። ይህንንም በመገንዘብ በሀገሪቱ ውስጥ ያለዉን የኢኖቬሽን ደረጃ ለመገንዘብና ተቋማት ለኢኖቬሽን እንቅስቃሴዎች የሚያወጡትን ወጪና ከተለያዩ ተቋማት ጋር እውቀትንና ክፍሎትን ለማዳበር የሚያደርጉትን ግንኙነቶች ለመረዳት እንዲሁም ዘርፉን ለማስተዳደር የሚችል ፖሊሲ ለመቅረፅ በ2007 የመጀመሪያውን የኢኖቬሽን ሰርቬይ ለማካሄድ ታቅዷል። ይህንንም እንዲያከናውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል ሙሉ ሀላፊነት ተጥሎበታል። ማዕከሉ የንግድ ተቋማትን እንደዋነኛ የጥናት ክፍል በመውሰድ በአራት ዘርፎች ላይ፣ ከዘጠኙ ክልሎችና በሁለቱ የፌደራል ከተማ መስተዳድሮች ውስጥ በናሙና የተመረጡ ተቋማት በሚያመርቷቸው ምርቶች ላይ፣ ከአመራረት ሂደት አንፃር፣ ከተቋም አስተዳደር እና ከግብይት ስርዓት አንፃር የሚያከናውኗቸው ኢኖቬሽኖች ላይ ጥናት ሊያከናውን አቅዷል። ተቋሙ ጥናቱን በሀምሌ 2006 ጀምሮ በሰኔ 2007 ዓም የሚያጠናቅቅ ሲሆን አሁን ማለትም በሚያዚያ ወር ላይ የጥናቱ 90 በመቶ ተገባዷል።
የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ተብለው ከሚጠቀሱት ውስጥ ሌላው ቢብሎሜትሪክስ ነው። ቢብሎሜትሪክስ የጥናታዊ ፅሁፍ ህትመቶችንና ማጣቀሻዎቻቸውን አህዛዊ ትንተናና ስታስቲክስን በመጠቀም የሚለካ ነው። ቢብሎሜትሪክስ ስታትስቲካዊ ትንተና በመጠቀም የማጣቀሻና የቃላት ድግግሞሽ ትንተና በማከናወን መረጃዎች አቅጣጫ ማግኘት ነው። የህትመቶችንና የማጣቀሻዎቻቸውን አህዛዊ ልኬትን በመጠቀም መለካት በመላው ዓለም ጥቅም ላይ እየዋለ ያለ አካሄድ ነው።
ቢብሎሜትሪክስ የጥናቶችን አቅም ለመለካት ጥቅም ላይ ይውላል። ቢብሎሜትሪክስን የጥናቶችን አቅም ለመለካት ከሚጠቀሙ መካከል ዩኒቨርሲቲዎችና የመንግስት ላቦራቶሪዎች፣ ፖሊሲ የሚቀርፁ አካላት፣ የምርምር ዳይሬክተሮችና አስተዳደሮች፣ የመረጃ ልዩ ሙያተኞች እና ላይብረሪያኖች እንዲሁም የምርምር ባለሙያዎች ዋነኞቹ ናቸው። እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ የቢብሎሜትሪክስ ትንተና በሀገሪቱ የጥናት ባለሙያዎች አልተከናወነም። የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል በ2014 እ.ኤ.አ. የቢብሎሜትሪክስ ትነተና ለማከናወን ዕቅድ ይዟል።
የአይ.ሲ.ቲ ሲስተሞች
• ዌብ መሰረት ያደረገ የሰው ኃይል አውቶሜሽን ሲስተም
በማዕከሉ ውስጥ የሚኖረው የሰው ኃይል አስተዳደር ስራ የተማከለና በአንድ መስኮት የሚከናወን ለማድረግ ምቹ የሆነ፣ የሰራተኞችን ማህደር በመያዝ ሰራተኞች የግል መረጃዎቻቸውን ማየትና ማስተካከል እንዲችሉ የሚረዳ ሲስተም ነው።
• ዌብ መሰረት ያደረገ የእውቀት አስተዳደርና ኢለርኒንግ ሲስተም
በማዕከሉ በሚገኙት ሰራተኞች ዉስጥ የሚኖርን እውቀት ተደብቆ እንዳይቀር እርስ በእርስ የመማሪያና የእውቀት መገበያያ መድረክ በመሆን የሚያገለግል ሲስተም ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ መንገዶች የተሰበሰቡ እውቀቶችን ከማዕከሉ ዉጪ ለሚገኙ ተጠቃሚዎች ለማጋራት አመቺ ስፍራ የሚፈጥር ሲስተም ነው።
• የመረጃ ማነፍነፊያ ሲስተም
ይህ ጎልጉል የተሰኘው የመረጃ ማነፍነፊያ () ሲሆን መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች መረጃዎችን ኢንዴክስ በማድረግ የተጠቃሚዎችን የመረጃ ጥማት ለማርካት የተበለፀገ ሲስተም ነው።
• የብሔራዊ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዲጂታል ላይብረሪ ሲስተም
መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መስኮች ዙሪያ የሚገኙ መጽሐፍትን ተጠቃሚዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በኢንተርኔት እንዲያገኙ የሚያስችል ሀገራዊ ይዘት የተላበሰ ሲስተም ነው።
• ዌብ መሰረት ያደረገ የአዕምሯዊ ንብረት ሲስተም
በቴክኖሎጂ ሽግግሩ መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የትኩረት መስኮች የተሰበሰቡ የፓተንት መረጃዎች ለስራ ፈጣሪዎችና ተመራማሪዎች በሚያመችና ቀላል በሆነ ሀገራዊ ይዘትን በተላበስ መንገድ ማግኘት እንዲቻል የተበለፀገ ሲስተም ነው።
• የ (ኦፕቲካል ካራክተር ሪኮግኒሽን) ሲስተም
በህትመት መልክ የሚገኙ አማርኛን ጨምሮ በሌሎች ቋንቋዎች ያሉ ማንኛውም አይነት መረጃዎች ስካን ከተደረጉ በኋላ በቀላሉ በኮምፒውተር አማካኝነት መረዳትና መነበብ እንዲሁም ኤዲት መደረግ እንዲችሉ የሚያግዝ ሲስተም ነው።
• የማዕከሉ ድረ-ገፅ
በማዕከሉ የሚገኙትን ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ እውቀቶችና ትኩስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዜናዎችን ተደራሽ ለማድረግ ማራኪ ገፅታን ተላብሶና የተጠቃሚዎችን ፍላጎት መሰረት አድርጎ በአማርኛና እንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ድረ ገፅ ነው።
• የማዕከሉ የውስጥ መገናኛ ኢንተርናል ፖርታል
ይህ የዉስጥ ለዉስጥ መገናኛ በማዕከሉ ዉስጥ የሚገኙ ሰራተኞች የማዕከሉን መተዳደሪያ ሕግና ደንብ፣ ፖሊሲና መመሪያዎች እንዲሁም ማስታወቂያዎች በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል፣ የማዕከሉን ወቅታዊ የስራ ሂደትና የሰራተኞች የአፈፃፀም ደረጃ የሚያሳይ ሲሆን በተጨማሪም ሰራተኞች እርስ በእርስ የሚኖራቸውን የስራ ግንኙነት በይበልጥ ለማጠናከር የሚያግዝ ሲስተም ነው።
• ዌብ መሰረት ያደረገ ሲስተም
ይህ አውቶሜትድ የውጤት ተኮር ምዘና ሲስተም የማዕከሉን፣ በማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ የስራ ሂደቶችን፣ የቡድን መሪዎችና ግለሰቦች ስራዎቻቸውን የሚያቅዱበት፣ አፈፃፀማቸውን የሚመዘግቡበትና የአፈፃፀም ምዘና ሪፖርት ማግኘት የሚችሉበት ያለምንም ሰው ጣልቃ ገብነት በኮምፒውተር አማካኝነት የሚከወን የተማከለ ሲስተም ነው።
ቴክኖሎጂ ትንተናና ትንበያ
በሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል ስር ከሚገኙት ዋና ዋና የስራ ሂደቶች ዉስጥ አንዱ ሲሆን በዋነኝነት ቴክኖሎጂዎችን ከማህበረ-ኢኮኖሚያዊ፣ ከባህል፣ ከዝግጁነት፣ ከአካባቢ፣ ከስጋት፣ ወደፊት ከሚያስከትሉት ተፅዕኖ እና ከሌሎች ዕይታዎች አንፃር በማየት ላይ ትኩረት ያደርጋል። የቴክኖሎጂ ትንተናና ትንበያ ስራን ለማከናወን የተለያዩ ደረጃዎች የሚታለፉ ሲሆን መረጃ ማሰባሰብ፣ መለየት፣ የቴክኖሎጂዎችን ቅድመ ትንተናና ትንበያ መረዳት እና የማጠቃለያ ሃሳብ ማስቀመጥ ከደረጃዎቹ መሀከል የሚገኙ ናቸው። ከትንተናና ትንበያ የሚገኘው መረጃ ለፖሊሲ አርቃቂዎች፣ ተመራማሪዎች፣ የፈጠራ ባለሙያዎችና ልዩ በሆኑ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመረጃ ምንጭነት ያገለግላል።
ኢሳይንስ በእያንዳንዱ የሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ገፅታ ላይ ትልቅ ሚና የሚጫወት መስክ ነው። ለማንኛውም አይነት ፈር ቀዳጅ ለሆኑ ሳይንሳዊ ጥናቶችና ግኝቶች ከመጀመሪያ ፅንሰ ሃሳብ ጀምሮ የተለያዩ በስርዓት የተቀረፁ ሙከራዎችን ለማካሄድ፣ መረጃዎችን በስርዓት ለመሰብሰብ እንዲሁም ተጓዳኝ የሆኑ መረጃዎችን ለመተንተን የሚያገለግል አስቻይ መሳሪያ ነው። ማንኛውም አይነት የሳይንሳዊ ፅንሰ ሃሳብም ሆነ መላምት ፍላጎት መጠነ ሰፊ የሆነ መረጃ መሰብሰብ መቻል አለበት። ይህንንም ለማጎልበትና ለማሳካት የሚያግዙ ሲስተሞችን ባደጉ የኮምፒውቲንግ ስርዓቶች ለመደገፍ ኢሳይንስ ትልቅ አስተዋፅዖ ይኖረዋል። ኢሳይንስ ሳይንቲስቶች የስራቸውን ውጤት ለማከማቸት፣ ለማብራራት፣ ለመተንተን፣ የግንኙነት አውታራቸውን ለመዘርጋት እንዲሁም የራሳቸውን መረጃ ለሌላ ተመሳሳይ ቡድን ለማካፈል የሚያስችል አሰራርና ሂደትን በውስጡ ያዘለ ነው። የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል የመረጃ ማዕከል እንደ መሆኑ ኢሳይንስን ተግባራዊ ማድረጉ የመረጃ የመሰብሰብና ማሰራጨት ስራዎች በዋናነት ለማቀላጠፍ ያስችላል። እንዲሁም የመረጃ ማዕከሉ በውስጡ የምርምር ስራዎችን የሚሰራ ስለሆነ የምርምር ስራዎችን በተሻለ ጥራትና አቅም እንዲሰሩ ኢሳይንስ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው።
ከሳ.ቴ.መ.ማ. ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት
• የኮሪያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ተቋም
• የቻይና ሳይንሳዊና ቴክኒካል ኢንፎርሜሽን ተቋም
• የማሌዢያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ተቋም
• የፊሊፒንስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ተቋም
የኢትዮጵያ ድርጅቶች
የኢትዮጵያ መንግሥት
የመረጃና የመገናኛ ቴክኖዎሎጂ
|
22318
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%88%8D%E1%8C%A4
|
ስልጤ
|
ስልጤ የኢትዮጵያ ብሔር ነው።የስልጤ ብሔረሰብ በሀገራችን ከሚገኙ በርካታ ብሔሮች: ብሔረሰቦችና ህዝቦች
አንዱ ነው: ብሔረሰቡ በአዲስ አበባ-ሆሳዕና መንገድ በ172 ኪ.ሜ ርቀት
ከመንገዱ ግራና ቀኝ 60 ኪ.ሜ ያህል ገባ ብሎ በሚገኘው በደቡብ ክልል
ስልጤ ዞን በስፋት ይኖራል የዞኑ ጠቅላላ ስፋት 3ሺ² ነው:: እኤአ 2004
በተደረገ ቆጠራ በዞኑ የሚኖረው 850ሺ በዞኑ መስደደር ቢቻ የነበረ ሲሆን የዞኑ
ተወላጆች ያዞኑ ህዝብ በሁኑ ሰዓት ከ900ሺ በለይ ይሆናል ተቢሎ ይታሰበል
።ከዞኑ በተጨማሪ ከ1 ምሊዬን በለይ ከዞኑ ጎራቤት ካጉራጌ፣ካሀድያ ፣ካኣለበ ና
ካኦሮሞ ቤሔራሰቦች ታቀለቅሎ ሳፍሮወል እነም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና
የውጪ ሀገራትም በስፋት ተሰራጭተው ይኖራሉ:: ከብሔረሰቡ 100% የሚሆነው
የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው::0.9 % የኣመራና የሌላ ብሔርሰብ ኦርቶዶክስ
ክርታን ይኖርበታል ።ከዞኑ ውጭ የሉ ስልጤዎች 100% የስልምና ተካታይ ሲሆኑ
በታጫር ከ99 % በለይ በከፍል ስልጤ ሙስልሞች ነቸው። መለትም በኣበት
ዎይም በእነት የስልጤ ዝርየነት የለቸው ነቸው።ግብርና ዋነኛ የኢኮኖሚ
መሠረት ሲሆን ከብት አርባታና ንግድም እንዲሁ የብሔረሰቡ የሀብት ምንጭ
.. ዞኑ አሁን በስምንት ማለትም:- ምዕራብ አዘርነት:ምስራቅ
አዘርነት:አልቾውሪሮ:ዳሎቻ:ላንፎሮ:ሳንኩራ :ሁልባረግና ስልጢ ወረዳዎች
የተዋቀረ ነው::የብሔረሰቡ ቋንቋ ስልጢኛ ሲሆን ከሴማዊያን ቤተሰቦች
ይመደባል .. የቋንቋው ስፋት ከሀረሪኛና የዛይ ቋንቋ ጋር በጣም ሲመሳሰል
በበርካታ የቃላት ትርጉዋሜ ደረጃ ከአረብኛ: አማርኛ ትግርኛ አርጎቢኛና ኦሮምኛ
ጋርም ይገናኛል::
"ስልጤ" የሚለው ስም በዞኑ በሚገኙ በዋነኛነት አምስት ማኅበረሰቦች ማለትም
ስልጢ:መልጋ:ሁልባረግ:አዘርነት በርበሬና አልቾውሪሮ የጋራ መጠሪያ ሲሆን
ማኅበረሰቦቹ በታሪክ: በማኅበራዊ ኑሮ :በባህል: በቋንቋና በሀይማኖት እንዲሁ
ተመሳሳይ ናቸው የስያሜውን መነሻ በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎች ያሉ ሲሆን
ስያሜውን ያገኘው ከሀጂ አሊዬ 5ተኛ ልጅ ከሆኑት ገን-ስልጤ አልያም
ሱልጣኔት ከሚለው አረብ ኢስላማዊ መንግስት ጥንታዊነት እንዲሁም ነባር
ኢስላማዊ መንግስታትና ማኅበረሰቦች የታሪክ ወራሽነትን በማሰብ ነው የሚለው
በስፋት ይገለፃል::
ስልጤ የምጣረበቸው ታጨመር ስሞች `` እስላም``ታብሎ ስጣራ ፡ ቋንቋቸው`
እስለምኛ `በመበል በደቡብ ክፍል እስከ ዘሬ ይታዎቀል .ክሰሜን' ጉራጌ` ታብሎ
የምታዎቅ ብሆንም ስልጤ የረሱን ዞን ከመሰራተ ጀምሮ ስሙ ለይመለስ
የስልጤ ብሔረሰብ
ብሔረሰቡ በዋናነት በክልሉ በስልጤ ዞን ውስጥ በሚገኙ ስምንት ወረዳዎች
በሀገር ውስጥ ፣ በዎላይታ፣ በሲዳማ እና ጌዲኦ ዞኖች፣ በሀዋሣ ከተማ እና
በሀላባ ልዩ ወረዳ እንዲሁም ከክልሉ ውጪ በጂማ፣ በወለጋ፣ በናዝሬት /አዳማ/
፣ በሐረር፣ በድሬዳዋ፣ በአደስ አበባ ከተሞች ከሌሎች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች
ጋር በስብጥር ይኖራሉ፡፡
ብሔረሰቡ በዋናነት የሚኖርበት ሥፍራ በሰሜን እና በሰሜን ምዕራብ የጉራጌ
ዞን፣ በደቡብ የሀዲያ ዞን እና የሀላባ ልዩ ወረዳ፣ በምዕራብ የሀዲያ ዞን ፣
በምስራቅ የኦሮሚያ ክልል ያዋሰኑታ፡፡
የብሔረሰቡ ዋነኛ መገኛ ሥፍራ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ በአብዛኛው
ሜዳማ ሲሆን የተወሰነው በተለይም ምዕራባዊው ክፍል ተራራማነት ያለው ነው፡፡
የአየር ንብረቱ በተለያዩ ደረጃ ደጋማ፣ ወይናደጋማ እና ቆላማ ሲሆን አብዛኛው
ክፍል ወይናደጋማ ነው፡፡ የሕዝቡ ኢኮኖሚ የተመሰረተው በዋናነት በእርሻ ሲሆን
ከዚሁ ጐን ለጐን የተወሰነው ክፍል የከብት እርባታን፣ ንግድን፣ እና አንዳንድ የእደ
ጥበብ ውጤታችን በማምረት ኑሮአቸውን ይመራሉ፡፡ በዋናነት ከሚመረቱ የእርሻ
ምርቶች መካከል በርበሬ ፣እንሰት፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ ፣ ገብስ፣ አተር፣ ባቄላ፣
ቦሎቄ፣ አደንጓሬ፣ ቡና፣ ጫት፣ ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
የስልጤ ብሔረሰብ አፍ መፍቻ ቋንቋ ስልጢኛ ሲሆን ከሴማዊ የቋንቋ ቤተሰብ
ይመደባል፡፡ ቋንቋው ከአረብኛ፣ ከጉራጊኛ ፣ ከሐረሪ፣ ቋንቋዎች ጋር ይመሳሰላል፡፡
የብሔረሰቡ አባላት ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ በከተሞች አካባቢ ያሉ
አማርኛን እንዲሁም እንደ አጐራባችነታቸውና ቅርበታቸው የሀድይኛ፣ የማረቆኛ፣
የጉራግኛ፣ የኦሮምኛ እና የሀላብኛን ቋንቋዎች በሁለተኛ ደረጃ ይናገራሉ፡፡
ሌሎችም አጐራባች ብሔረሰቦች እንዲሁ የስልጢኛን ቋንቋ እንደየቅርበታቸው
ለመግባቢያነት ይጠቀማሉ፡፡
ስልጢኛ ከ6ዐ ዓመት በፊት የአረብኛ ፊደልን በመጠቀም ለጽሑፍ የዋለ ቋንቋ
ቢሆንም ከ1967 ዓ/ም ጀምሮ ልዩ ልዩ አዋጆች እና የመሰረተ ትምህርት
ማስተማሪያ መጽሐፍት የሳባ ፊደልን በመጠቀም በቋንቋው ተተርጉመዋል፡፡
ከ1987 ዓ/ም ጀምሮ የ1ኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሣይክል የመማሪያ መጽሐፍት
በቋንቋው ተዘጋጅተዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የትምህርት ቋንቋ ሆኖ በማገልገል ላይ
ይገኛል፡፡ እንደዚሁም የሣባ ፊደልን በመጠቀም የመማሪያ መጽሐፍት፣ የስልጢኛ
መዝገበ ቃላት፣ የስልጤ ሕዝብ ታሪክ እና ሌሎች መጽሀፍቶች በቋንቋው
ተጽፈው አገልግሎት እየሠጡ መሆናቸው ቋንቋው በማደግ ላይ ያለ ስለሚሆኑ
የሚገልፁ እውነታዎች ናቸው፡፡
ታሪካዊ አመጣጥ
የስልጤን ብሔረሰብ ታሪካዊ አመጣጥ በተመለከተ በብሔረሰቡ የዕድሜ
ባለፀጋዎች የሚነገሩ የትውፊት እና አንዳንድ የተገኙ የጽሑፍ መረጃዎችን
በሁለት መልኩ ከፍለን እንመለከታለን፡፡ የመጀመሪያው የትውፊት መረጃ
እንደሚያመለክተው በጥንት ጊዜ ዛሬ የብሔረሰቡ አባላት በሚኖሩበት ሥፍራ
"ዡራ" ወይንም "ሀርላ" በመባል የሚታወቁ ሕዝቦች ይኖሩ እንደነበር ይገልፃል፡፡
ሌላው መረጃ ደግሞ በ8ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ የተወሰኑ ቀደምት
የብሔረሰቡ አባላት ከምድረ ሣውዲ አረቢያ ተነስተው የኤደን ባህረ ሰላጤን
አቋርጠው በስተምስራቅ አቅጣጫ በዘይላ ደሴት በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ
ያመለክታል፡፡ እነዚህ ሕዝቦች በፀሐይ መውጫ አቅጣጫ ወደ አገሪቱ ክፍል
ከገቡ በኋላ በሐረር ጀበርቲ ዛሬ “አደሬ” ወይንም "ሐረሪ" በሚባለው አካባቢ
ቆይታ አድርገው ወደ ዛሬው መገኛ ሥፍራ በመምጣት ከነባሩ ሕዝብ ጋር
ተቀላቅለው መኖር እንደጀመሩ ይነገራል፡፡
የነዚህ ክፍሎች አመጣጥ በአብዛኛው እስልምናን ከማስተማር ጋር የተያያዘ
እንደነበር የተገኙ የትውፊት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የተወሰኑ የብሔረሰቡ
አባላት ደግሞ የግራኝ መሀመድ ወረራ ካበቃ በ1ዐኛው ዓመት ገደማ
ከ1553/63 በሀጂ አልዬ መሪነት የተለያዩ ቦታ እየሠፈሩ አሁን በዋናነት ወደ
ሚኖሩበት አካባቢ እንደደረሱ ይነገራል፡፡ ሀጂ አልዬ በአባታቸው ኢትዮጵያዊ
በእናታቸው የአረብ ዝርያ እንዳላቸው የሚነገር ሲሆን በስፍራው ሲደርሱ
በመጀመሪያ መቀመጫቸውን ያደረጉት አልቾ ወሬሮ ላይ እንደነበር በታሪክ
ይነገራል፡፡ በዚያን ወቅት የነበረው የስልጤ ሕዝብ ወደአሁኑ ስፍራ ከመድረሱ
በፊት ገደብ ዝዋይ / ላቂ ደንበል/፣ ሲዳማ፣ አሊቶ ዳገት /ቡልቡላ አጠገብ/
በሚባሉ አካባቢዎች ቆይታ እንዳደረገ የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በወቅቱ
ለሕዝቡ እንቅስቃሴ እንደምክንያት የሚገለፀው በግራኝ መሀመድ የተነሣ ጥሩ
የመኖሪያ አካባቢ ለመፈለግ እንደሆነ ይነገራል፡፡
በታሪክ አጥኚዎች ደሞ እንደሚነገረው ስልጤ ጙራጌ እና ሌሎች በአካባቢው የሚገኙ ብሄረሰቦች፥ በቋንቋቸው፡ በደማቸው ጥናት (ጀነቲክስ)፡ በስነ ልቦናቸው፥ በባህላቸው ወዘተ፥ ከሰሜን ኢትዮጵያ በተለይ ከዐማራ ብሄር በ8ኛው-10ኛው ክፍለ ዘመን ፈልሰው በአካባቢው የሰፈሩ ሰፋሪዎች እንደሆኑ ያመላክታል። ይህም ጊዜ ከኦሮሞ ፍልሰት 5መቶ-7መቶ አመታት በፊት ነው።
የኢትዮጵያ ብሔሮች
|
37267
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9D%E1%88%B5%E1%88%B5%E1%88%8D
|
ምስስል
|
ምስስል በየሳይንስ ፍልስፍና ውስጥ የአንድ አመክንዮአዊ ዓረፍተ ነገርን እውነትነት እና ውሸትነት መካከል ያለውን ልዩነት መለያ ዘዴ ነው። መነሻው ሃሳብም ማናቸው የሳይንስ ኅልዮቶች በአጠቃላይ መልኩ ውሸት ቢሆኑም ፣ ዳሩ ግን አንዳቸው ከሌላው በተሻለ መልኩ ወደ እውነቱ ይቀርባሉ። ስለዚህ ምስስል አንድ የሳይንስ ኅልዮት ለእውነቱ ወይንም ለሃቅ ከሌሎች ኅልዮቶች በተሻለ ቀርቦ እንደሚገኝ የሚታዎቅበት ዘዴ ነው።
እንደ ፈላስፋው ካርል ፓፐር፣ አንድ ኅልዮት ከሌላው ኅልዮት ወደ እውነቱ የበለጠ የቀረበ እንደሆነ እሚወስነው ነገር ያ ኅልዮት ያለው እውነት እና በውስጡ ያዘለው የእውነት መጠን ናቸው። አንድ ኅልዮት ከሌሎች ኅልዮቶች ጋር ሲዎዳደር የበዛ እውነታ በውስጡ ካዘለ፣ ወደ እውነቱ ይቃረባል፣ ሃቅን ይመሳሰላል እንላለን።
የኢሳቅ ኒውተን የእንቅስቃሴ ህግጋት ከፈላስፋው አሪስጣጣሊስ ይበለጠ እውነቶችን ያዘለ ነበር። ሆኖም የሁለቱም ኅልዮቶች በውስጣቸው ውሸት እንዳለባቸው የታዎቀ ነው። ይሁን እንጂ የኒውተን ኅግጋት ለእውነቱ የበለጠ ይቀረበ ነበር። በሌላ ጎን ሁለት ኅልዮቶች ወይንም አረፍተ ነገሮች እኩል እውነት ቢሆኑም ቅሉ በውስጣቸው ያዘሉት የእውነት መጠን አንዱን ከሌላው ይበለጠ ምስስል እንዲኖረው ያደርጋል። ለምሳሌ "በሚቀጥለው ሳምንት ሐሙስ ዕለት ዝናብ ይዘንባል" የሚለው አባባል እውነት ቢሆንና ሌላ ዓረፍተ ነገር «በሚቀጥለው ሳምንት ሊዘንብ ወይንም ጸሐይ ሊዎጣ ይችላል» ቢል፣ ምንም እንኳ ሁለቱም ዓረፍተ ነገሮች እውነት ቢሆኑም የመጀመሪያው ዓረፍተ ነገር ከሁለተኛው አረፍተ ነገር በበለጠ ለእውነቱ ይጠጋል፣ ስለሆነም የበለጠ ምስስል አለው እንላለን።
የሳይንስ ፍልስፍና
|
13457
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B3%E1%8B%AD%E1%8A%95%E1%88%B3%E1%8B%8A%20%E1%8B%98%E1%8B%B4
|
ሳይንሳዊ ዘዴ
|
ሳይንስ ከሌሎች የዕውቀት ዘርፎች (ለምሳሌ ፍልስፍና ወይም ሂሳብ ወይም ስነ ሃይማኖት) የሚለይበት ዋናው ቁም ነገር የሳይንስ ዘዴን በመጠቀሙ ነው። እርግጥ ነው ። ሳይንሳዊ ዘዴ ተብሎ የሚታወቀው ስርዓት ብዙ ጊዜ በዝርዝር ድረጃ በድረጃ በሚከተለው መልኩ ሲቀርብ እናያለን፦
ስለሚታየው አለም "ጥያቄ" አንሳ። ሁሉም የሳይንስ ስራ የሚጀምረው ጥያቄ በማቅረብ ነው። ትክክለኛና በ"ተመክሮ" ሊመለስ የሚችል ጥያቄ የማቅረብ ችሎታ እንደ ትልቅ የሳይንስ ጥበብ ይቆጠራል።
ለጥያቄህ መልስ ሊሆን የሚችል "መላ ምት" ፍጠር። "መላ ምት" ማለት የግምት አይነት ሲሆን እንዲሁ በዘፌቀደ የሚደረግ ግምት ሳይሆን ያለፈን ተመክሮ እና ትምህርትን ያገናዘበ ነው። በተረፈ ይህ መላ ምት እውነት ወይም ውሽት መሆኑ ሊረጋገጥ የሚችል መሆን አለበት። ለምሳሌ "ሰማያዊ ቀለም ከቀይ ቀለም የተሻለ ነው" የሚል አስተሳሰብ "ሳይንሳቂ መላ ምት" ሊሆን አይችልም ምክንያቱም እውነት ይሁን ውሽት ማረጋገጥ ስለማይቻል። ነገር ግን ለምሳሌ "ሰማያዊ ቀለምን የሚወድ የሰው ብዛት ቀይ ቀለምን ከሚወደው ይበዛል።" ይህ "ሳይንሳዊ መላምት ሊሆን ይችላል ምክንያቱም እውነት ይሁን ውሸት ሰወችን በመሰብሰብ እና በመጠየቅ በተሞክሮ ማረጋገጥ ይቻላልና።
መላ ምትህን ሊፈትን የሚችል ሙከራ ዘይድ። እውነተኛ ሳይንሳዊ መላምት በሙከራ ሊፈተን የሚችል ነው። በሙከራ ሊፈተን ካልቻለ በርግጥም ሳይንሳዊ አይደለም። ከዚህ በተረፈ፣ ሙከራው የመላምቱን ውሸትነት ሊያረጋግጥ ይችላል፣ እውነቱነቱን ግን ሊናገርም ላይናገርም ይችላል። ለምሳሌ አንድ መኪና አልነሳ ቢል፣ በሳይንሳዊ መንገድ ጥያቄ መጀመሪያ እናቀርባለን "ለምንድን ነው ያልተነሳው?" መላ ምታችን "ባትሪው ስላለቀ ነው" ይሆናል። ይህን መላምት ለመፈተን የባትሪውን አቅም በቮልት ሜተር እንድንለካ የሙከራ አቅድ እናወጣለን። ባትሪውን ስንለካ ሃይሉ ሳይሟጠጥ ካገኘነው በርግጥም መላምታችን ስህተት መሆኑን በሙከራ አረጋገጥን ማለት ነው። ባትሪው ሃይሉ ተሟጦ ካገኘነው ግን መላምታችን ትክክል መሆኑን አያሳይም ምክንያቱም መኪናው ሌላም ችግር ሊኖርበት ይችላልና። ለምሳሌ "ስታርተሩ" ላይሰራ ይችላል። ስለዚህ ሙከራ አንድን የሳይንስ መላምት ውሽትነት ማረጋገጥ ቢችልም እውነትነቱን ግን አያረጋግጥም።
ሙከራህን አካሂድ በዚያውም መረጃ ሰብስብ።
ከሙከራህ ተነስተህ ድምዳሜ ላይ ድረስ። በርግጥ ያቀረብከው መላምት ውሽት መሆኑን ሙከራህ ያሳያል? ካላሳየ መላምትህ ለጊዜው (በሌላ ሙከራ እስካልተስባበለ ድረስ) ልክ ነው ማለት ነው። ውሽት መሆንኑን ካረጋገጥክ ከጀረጃ 2 ጀምረህ እንደገና ሞክር።
ድምዳሜህንና መላምትህን ለሌሎች አስታውቅ። ይህ ደረጃ ሳይንቲስቶች የጋን መብራት እንዳይሆኑ ከማገዱም በላይ ያንድን ሰው መላምቶችና ተመክሮወች በሌሎች ሳይንቲስቶች እንዲመዘን እና እንዲረጋገጥ መንገድ ይከፍታል።
እነዚህ እርከኖች በርግጥ ሁልጊዜ በሁሉ ሳይንቲስት የሚደረጉ ባይሆን፣ ነገር ግን ባጠቃላይ መልኩ ስለዓለማችን አስተማማኝ ሃቆችን ለማግኘት የሚረዱ መሆናቸው ይታመንባቸዋል።
እምነትና ተጨባጭ ሃቅ
ሰዎች በአንድ ነገር ላይ ያላቸው እምነት የሚያዩትን ነገር ሁሉ አንሻፈው እንዲገነዘቡ ሊያስገድዳቸው ይችላል። ስር የሰደደ ግን ተጨባጭነት የሌለው እምንተ፣ በሌሎች ተቃውሞ ቢደርስበት እንኳ ባለቤቱ እስከመጨረሻው ሙጥኝ ሊለው ይችላል።
ተማሪዎች በምርምር እንደደረሱበት፣ ብዙ ሰዎች በነገሮች ላይ ያላቸው የመጀመሪያ እይታ ትክክለኛነት ይጎድለዋል። ሁለተኛና ሶስተኛ ጊዜ የተደገመ የተሞክሮ እይታ፣ ለሃቅ ቀርብ ይላል። ከአንድ ተመክሮ ላይ እውነተኛው ሃቅ የመውጣቱ ወይም እስከመጨረሻው የመደበቁ ምስጢር ተመክሮውን በሚያደርገው ሰው የአእምሮ ክፍትነት፤ ልምድ፣ በራስ መተማመን፣ ጊዜ፣ እና ምቾት ላይ ይመሰረታል
በድሮ ቻይናዎች እና አውሮጳ ሰዓሊዎች ዘንድ፣ የሚጋልቡ ፈረሶች እግሮቻቸው ተበልቅጠው ይታያሉ። ይሄ እንግዲህ ሰዓሊዎቹ ስለ ፈረሶች ኮቴ ከነበራቸው እምነት የመጣ እንጂ በርግጥም በተፈጥሮ የሚገኝ ጉዳይ/ሃቅ አልነበረም። ኤድዋርድ ሞይብሪጅ የሚጋለብን ፈረስ ተንቀሳቃሽ ስዕል በመቅረጽ እና ቅጽበት በቅጽበት በመመርመር ከላይ የተጠቀሰው እምነት ውሸት እንደሆነ አሳየ። በዚህ ምርምር መሰረት፣ ሁሉም የፈረስ ሸኮናዎች መሬትን ሲለቁ፣ ከመበልቀጥ ይልቅ ፣ አንድ ላይ የመሰብሰብን ሁኔታ እንደሚያሳዩ ታወቀ።
ስለሆነም በሳይንሳዊ ዘዴ አካሄድ፣ መላምቶች ምንጊዜም እንዲፈተኑ ስለሚያጠይቅ፣ የተንሻፈፉ እምነቶች (ለምሳሌ የሚንሳፈፍ ግልቢያ) ከአንድ ግለሰብም ሆነ ህብረተሰብ አዕምሮ ውስጥ ተነቅለው እንዲዎጡ ይረዳል።
የሳይንሳዊ ዘዴ ምሳሌ: ስኳር ውሃ ውስጥ ሲሟሟ
ስኳር ውሃ ውስጥ የሚያደርገውን የሟሟት ሂደት አንድ አንድ ነገሮች እንዴት ተጽኖ እንደሚያረጉበት በሙከራ ለማወቅ እንፈልግ እንበል። ከዚህ ቀጥሎ በሳይንሳዊ ዘዴ የሄን እንዴት እንደምናከናውን እንመልከት፡-
አላማ /ጥያቄ
ስኳር በቀዝቃዛ ውሃ ውስጥ ነው ወይንስ በሞቀ ውሃ ቶሎ የሚሟሟው? የሚለውን ጥያቄ አነሳን እንበል።
መላምት መፍጠር
ከጥያቄ በኋላ መላምት መፍጠር ስላለብን አንደኛው መላምታችን እንዲህ ይነበባል "ስኳር ከቀዝቃዛ ውሃ ይልቅ በሞቀ ውሃ በቶሎ ይሟሟል።" (መላምታችን የዚህ ተቃራኒ ሊሆን ይችላል፣ ይፈቀዳል)። ይህ እንግዲህ በሙከራ ሊፈተን የሚችል መላ ምት ነው። ሙከራውን በምናካሂድበት ጊዜ ስኳር ከሞቀ ውሃ ይልቅ በቀዝቃዛ ውሃ በቶሎ ወይም ደግሞ እኩል ከሟሟ መላምታችን ስህተት መሆኑን ማረጋገጥ እንችላለን ማለት ነው።
ለሙከራው እቅድ ማውጣት
አንዱ ቀላሉ ዘዴ እንግዲህ የተለያየ ሙቀት ያለው ውሃ በተለያዩ ብርጭቆወች በማስቀመጥ በያንዳንዱ ብርጭቆ ውስጥ እኩል ስኳር በማድረግ ለመሟት የሚፈጀውን ጊዜ መመዝገብ ነው።
በሙከራው ጊዜ እኩል ስኳር እና እኩል ውሃ መጠቀም ይኖርብናል አለበለዚያ የስኳሩ የመሟሟት ፍጥነት በውሃው የሙቀት መጠን ብቻ ይሁን በውሃው ብዛት ወይም ስኳር ብዛት ማወቅ አንችልም። ስለዚህም ሙከራችንን በጥንቃቄ ማቀድ የሳንሳዊ ዘዴ አንዱ ወሰኝ እርከን ነው። በሙከራችንም ጊዜ የውሃው ሙቀት እንዳይለወጥ ጥንቃቄ ማድረግ እጅግ አስፈላጊ ነው።
ይህ እንግዲህ "አንዱን ተለዋዋጭ መለየት" ይባላል - አንድ ነገር ብቻ በአንድ ጊዜ እንዲለወጥ ስናደርግ የዚያን ነገር ተጽዕኖ ማረጋገጥ እንችላለን ማለት ነው።
ሙከራውን ማካሄድ
ሙከራውን በሶስት ደረጃ እናካሂዳለን። ሦስቱም ሙከራወች ከውሃው ሙቀት ውጭ አንድ አይነት ናቸው።
አንድ ሊትር ቀዝቃዛ ውሃ ውስጥ 25 ግራም ስኳር እንጨምራለን። ሳናማስል እንጠብቃለን። አጠቃላይ ስኳሩ ለመሟት 30 ደቂቃ እንደወሰደ እናስተውላለን።
አንድ ሊትር ለብ ያለ ውሃ ውስጥ 25 ግራም ስኳር እንጨምራለን። ሳናማስል እንጠብቃለን። አጠቃላይ ስኳሩ ለመሟት 15 ደቂቃ እንደወሰደ እናስተውላለን።
አንድ ሊትር የሞቀ ውሃ ውስጥ 25 ግራም ስኳር እንጨምራለን። ሳናማስል እንጠብቃለን። አጠቃላይ ስኳሩ ለመሟት 4 ደቂቃ እንደወሰደ እናስተውላለን።
ድምዳሜ ላይ መድረስ
ድምዳሜ ላይ ለመድረስ አንዱና ቀላሉ መንገድ ያገኘነውን መረጃ በሰንጠረዥ ማስቀመት ነው። (ለዚህ ስራ እንዲቀለን፣ የተቀየሩትን ነገሮች ብቻ መዘርዘሩ ጥሩ ነው) ለምስሌ፦
ሌሎቹ የሙከራወቹ አካሎች አንድ አይነት ከሆኑ (ለምሳሌ የተለያየ የስኳር መጠን ካልተጠቀምን፣ ሁልጊዜ ካላማሰልን ወዘተ..)፣ እንግዲህ ሙከራችን ለመላምታችን ጥሩ ደጋፊ መረጃ ነው፡ ማለት የውሃ ሙቀት መጨመረ በስኳርን መሟት ላይ ትፅኖ እንደሚያደርግ።
ይሄ በራሱ ግን የስኳሩን የመሟት ፍጥነት ሌላ የተደበቀ ነገር ትጽኖ እንደማያረግብት አይነግረንም። እነዚህ የተደበቁ ነገሮች በታወቁ ቁጥር እነሱን የሚለይ ሙከራ በማቀድ ይፈተናሉ ማለት ነው። በሂደት እውነቱ እየጠራ ይሄዳል።
ውጤትን ስለመመዝገብና ስለማስተዋወቅ
ውጤት ሲመዘገብ በሙከራችን ላይ የታዩትን ያለምንም መቀየር መሆን አለበት። ይህ ምዝገባ ከመጀመሪያው የሳይንሳዊ ዘዴ (ለምን ጥያቄ አቀረብን?) ጀምሮ እስከመጨረሻው መሆን አለበት። መላ ምታችንን፣ ምንን ግምት ውስጥ እንዳስገባን ወዘተ በዝርዝር ማሰመጥ ይኖርብናል። እያንዳንዱ ሙከራ እና ከሙከራው የተገኘው መርጃ ያለምንም መቀየር መቀመጥ ይኖርበታል። የደረስንበትም ድምዳሜ እንዲሁ መስፈር አለበት። ይህ ጽህፈት እንግዲህ ሌሎች ሳይንቲስቶች በመላክ በሌሎች መፈተሽ ይገባዋል። በሳይንሳዊ ሂደት ውስጥ ድምዳሜያችን በሌሎች ሳይንቲስቶች ስህተት ሆኖ ቢገኝ ምንም አይደለም ምክንያቱም ሳይንስ እያደገ የሚሄደው በማያቋርጥ መተራረም እንጂ በቋሚነት በጸና እውነት አይደለም።
የሳይንስ ፍልስፍና
|
52436
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%89%A8%E1%8A%95%20%E1%88%83%E1%8B%8D%E1%8A%AA%E1%8A%95%E1%8C%8D
|
ስቲቨን ሃውኪንግ
|
እስጢፋኖስ ዊሊያም ሃውኪንግ (እ.ኤ.አ. ጥር 8 ቀን 1942 - መጋቢት 14 ቀን 2018) እንግሊዛዊ የቲዎሬቲካል የፊዚክስ ሊቅ ፣ የኮስሞሎጂ ባለሙያ እና ደራሲ ሲሆን በሞቱ ጊዜ በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የቲዎሬቲካል ኮስሞሎጂ ማእከል የምርምር ዳይሬክተር ነበሩ ። . በ 1979 እና 2009 መካከል በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሉሲያን የሂሳብ ፕሮፌሰር ነበሩ።
ሃውኪንግ በኦክስፎርድ ውስጥ ከዶክተሮች ቤተሰብ ተወለደ። በጥቅምት 1959 በ 17 አመቱ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ጀመረ እና በፊዚክስ የመጀመሪያ ክፍል ዲግሪ አግኝቷል። በጥቅምት 1962 የድህረ ምረቃ ስራውን በካምብሪጅ ትሪኒቲ አዳራሽ የጀመረ ሲሆን እ.ኤ.አ. መጋቢት 1966 የፒኤችዲ ዲግሪያቸውን በተግባራዊ ሂሳብ እና በቲዎሬቲካል ፊዚክስ በአጠቃላይ አንፃራዊነት እና ኮስሞሎጂ ስፔሻላይዝድ አግኝተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1963 ሃውኪንግ ቀደም ብሎ የጀመረው ቀስ በቀስ እየተሻሻለ የመጣው የሞተር ነርቭ በሽታ (አሚዮትሮፊክ ላተራል ስክለሮሲስ - ኤ ኤል ኤስ ፣ ለአጭር ጊዜ) ቀስ በቀስ በአስርተ ዓመታት ውስጥ ሽባ እንዳደረገው ታወቀ። ንግግሩን ካጣ በኋላ በመጀመሪያ የእጅ ማብሪያ / ማጥፊያን በመጠቀም እና በመጨረሻም አንድ ነጠላ የጉንጭ ጡንቻን በመጠቀም ንግግርን በሚፈጥር መሳሪያ በኩል ተናገረ።
የሃውኪንግ ሳይንሳዊ ስራዎች ከሮጀር ፔንሮዝ ጋር በጠቅላላ አንፃራዊነት ማዕቀፍ ውስጥ በስበት ነጠላ ንድፈ ሀሳቦች ላይ ትብብርን እና ጥቁር ቀዳዳዎች ጨረሮችን እንደሚያመነጩ የንድፈ ሃሳባዊ ትንበያ፣ ብዙ ጊዜ ሃውኪንግ ጨረር ይባላል። መጀመሪያ ላይ የሃውኪንግ ጨረር አወዛጋቢ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1970 ዎቹ መገባደጃ ላይ እና ተጨማሪ ምርምር ከታተመ በኋላ ፣ ግኝቱ በቲዎሬቲካል ፊዚክስ ውስጥ እንደ ትልቅ ግኝት በሰፊው ተቀባይነት አግኝቷል። ሃውኪንግ የአጠቃላይ አንፃራዊነት እና የኳንተም ሜካኒክስ ፅንሰ-ሀሳብ በህብረት የተብራራ የኮስሞሎጂ ፅንሰ-ሀሳብን ለማዘጋጀት የመጀመሪያው ነው። እሱ የኳንተም ሜካኒክስ የብዙ-ዓለማት ትርጓሜ ጠንካራ ደጋፊ ነበር።
ሃውኪንግ በብዙ የታወቁ የሳይንስ ስራዎች የንግድ ስኬትን አስመዝግቧል በዚህም ፅንሰ-ሀሳቦቹን እና ኮስሞሎጂን በአጠቃላይ ተወያይቷል። “” የተሰኘው መጽሃፉ በእሁድ ታይምስ የባለሞያዎች ዝርዝር ላይ ለ237 ሳምንታት ሪከርድ ሰበረ። ሃውኪንግ የሮያል ሶሳይቲ ባልደረባ፣ የህይወት ዘመን የጳጳሳዊ ሳይንስ አካዳሚ አባል እና የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛው የሲቪል ሽልማት የፕሬዝዳንት የነፃነት ሜዳሊያ ተሸላሚ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 2002 ሃውኪንግ በቢቢሲ የ100 ታላቋ ብሪታንያ ህዝብ ምርጫ 25 ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ከ 50 ዓመታት በላይ በሞተር ነርቭ በሽታ ከኖረ በኋላ በ 76 ዓመቱ በ 14 2018 ሞተ.
የመጀመሪያ ህይወት
ሃውኪንግ የተወለደው እ.ኤ.አ. ጥር 8 ቀን 1942 በኦክስፎርድ ከአባታቸው ፍራንክ እና ኢሶቤል ኢሊን ሃውኪንግ (ከተወለደው ዎከር) ነው። የሃውኪንግ እናት በግላስጎው ፣ ስኮትላንድ ውስጥ ከዶክተሮች ቤተሰብ ተወለደች። ከዮርክሻየር የመጣው ባለጸጋ አባቱ ቅድመ አያቱ የእርሻ መሬት በመግዛት እራሱን ከመጠን በላይ ማራዘሙ እና ከዚያም በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በታላቅ የግብርና ጭንቀት ውስጥ ወድቋል። የአባታቸው ቅድመ አያት በቤታቸው ትምህርት ቤት በመክፈት ቤተሰቡን ከገንዘብ ውድመት ታደጉት። የቤተሰቦቻቸው የገንዘብ ችግር ቢኖርባቸውም፣ ሁለቱም ወላጆች በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ነበር፣ ፍራንክ ህክምናን ሲያነብ ኢሶቤል ደግሞ ፍልስፍናን፣ ፖለቲካን እና ኢኮኖሚክስን አንብቧል። ኢሶቤል ለህክምና ምርምር ተቋም ፀሃፊ ሆኖ ሰርቷል፣ ፍራንክ ደግሞ የህክምና ተመራማሪ ነበር። ሃውኪንግ ፊሊፕ እና ሜሪ የተባሉ ሁለት ታናናሽ እህቶች ነበሩት እና የማደጎ ወንድም ኤድዋርድ ፍራንክ ዴቪድ ።
እ.ኤ.አ. በ 1950 ፣ የሃውኪንግ አባት በብሔራዊ የህክምና ምርምር ተቋም የፓራሲቶሎጂ ክፍል ኃላፊ በሆነ ጊዜ ፣ ቤተሰቡ ወደ ሴንት አልባንስ ፣ ሄርትፎርድሻየር ተዛወረ። በሴንት አልባንስ፣ ቤተሰቡ በጣም አስተዋይ እና በተወሰነ መልኩ ወጣ ገባ ተደርጎ ይወሰድ ነበር፣ ምግቦች ብዙ ጊዜ ከእያንዳንዱ ሰው ጋር መጽሃፍ በማንበብ ያሳልፋሉ። በትልቅ፣ በተዝረከረከ እና በደንብ ባልተጠበቀ ቤት ውስጥ ቆጣቢ ኑሮ ኖረዋል እና በለንደን ታክሲ ውስጥ ተጓዙ። የሃውኪንግ አባት በአፍሪካ ውስጥ ብዙ ጊዜ በማይሠራበት ወቅት፣ የተቀረው ቤተሰብ በማሎርካ አራት ወራትን ያሳለፈው የእናቱን ጓደኛ በርልን እና ባለቤቷን ገጣሚውን ሮበርት ግሬቭስን ለመጠየቅ ነው።
የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ዓመታት
ሴንት አልባንስ ለሴቶች ልጆች ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለጥቂት ወራት ተምሯል። በዚያን ጊዜ ትናንሽ ወንዶች ልጆች በአንዱ ቤት መገኘት ይችላሉ.
ሃውኪንግ በአንድ አመት መጀመሪያ ላይ አስራ አንድ -ፕላስ ካለፈ በኋላ በመጀመሪያ የራድልት ትምህርት ቤት እና ከሴፕቴምበር 1952 ጀምሮ በሴንት አልባንስ ትምህርት ቤት በሁለት ገለልተኛ (ማለትም ክፍያ የሚከፈል) ትምህርት ቤቶችን ተምሯል። ቤተሰቡ ለትምህርት ከፍተኛ ዋጋ ሰጥቷል. የሃውኪንግ አባት ልጁ በደንብ በሚታወቀው የዌስትሚኒስተር ትምህርት ቤት እንዲማር ፈልጎ ነበር ነገርግን የ13 አመቱ ሃውኪንግ የስኮላርሺፕ ፈተና በወጣበት ቀን ታሞ ነበር። ቤተሰቦቹ ያለ ስኮላርሺፕ የገንዘብ ድጋፍ የትምህርት ቤቱን ክፍያ መግዛት አልቻሉም፣ ስለዚህ ሃውኪንግ በሴንት አልባንስ ቀረ። አወንታዊ ውጤቱ ሃውኪንግ በቦርድ ጨዋታዎች፣ ርችቶች ማምረት፣ ሞዴል አውሮፕላኖች እና ጀልባዎች፣ እና ስለ ክርስትና እና ስለ ክርስትና ረጅም ውይይቶች ከሚወዳቸው የጓደኞቹ ቡድን ጋር መቀራረቡ ነበር። ከ1958 ዓ.ም ጀምሮ በሂሳብ መምህር ዲክራን ታህታ አማካኝነት ኮምፒውተር ከሰአት ክፍሎች፣ አሮጌ የስልክ መቀየሪያ ሰሌዳ እና ሌሎች እንደገና ጥቅም ላይ የዋሉ አካላት ገነቡ።
ምንም እንኳን በትምህርት ቤት "አንስታይን" ተብሎ ቢታወቅም, ሃውኪንግ በመጀመሪያ በአካዳሚክ ስኬታማ አልነበረም. ከጊዜ በኋላ ለሳይንሳዊ ትምህርቶች ከፍተኛ ችሎታ ማሳየት ጀመረ እና በታህታ ተመስጦ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሂሳብ ለማንበብ ወሰነ። የሃውኪንግ አባት ለሂሳብ ተመራቂዎች ጥቂት ስራዎች ስለሌለባቸው ህክምና እንዲያጠና መከረው። ልጁም የራሱን አልማ ተማሪ በሆነው በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ እንዲማር ፈለገ። በዚያን ጊዜ ሂሳብ ማንበብ ስለማይቻል ሃውኪንግ ፊዚክስ እና ኬሚስትሪ ለማጥናት ወሰነ። ርእሰ መምህሩ እስከሚቀጥለው አመት እንዲቆይ ቢመክሩም ሃውኪንግ በመጋቢት 1959 ፈተናውን ከወሰደ በኋላ የነፃ ትምህርት ዕድል አግኝቷል።
የመጀመሪያ ዲግሪ ዓመታት
ሃውኪንግ በጥቅምት 1959 በ17 ዓመቱ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ኦክስፎርድ ጀመረ። በመጀመሪያዎቹ አስራ ስምንት ወራት ውስጥ አሰልቺ እና ብቸኛ ነበር - የአካዳሚክ ስራውን "በሚያስቅ ቀላል" አገኘው። የፊዚክስ አስተማሪው ሮበርት በርማን በኋላ ላይ "አንድ ነገር ማድረግ እንደሚቻል ማወቅ ለእሱ ብቻ አስፈላጊ ነበር, እና ሌሎች ሰዎች እንዴት እንዳደረጉት ሳያይ ማድረግ ይችላል." እንደ በርማን አባባል ሃውኪንግ "ከልጆች አንዱ ለመሆን" የበለጠ ጥረት ባደረገበት በሁለተኛውና በሦስተኛው አመቱ ለውጥ ተፈጠረ። ወደ ታዋቂ፣ ሕያው እና ብልህ የኮሌጅ አባል፣ ወደ ክላሲካል ሙዚቃ እና ሳይንሳዊ ልብ ወለድ አደገ። የለውጡ ከፊሉ የኮሌጁ ጀልባ ክለብ የሆነውን የዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ጀልባ ክለብን ለመቀላቀል ባደረገው ውሳኔ የቀዘፋ ቡድን አባላትን ደግፏል። በወቅቱ የቀዘፋው አሰልጣኝ ሃውኪንግ ደፋር ምስል በማዳበር መርከበኞቹን ወደ ተበላሹ ጀልባዎች የሚያደርሱ ኮርሶችን በመምራት 1,000 ሰዓታት ያህል እንዳጠና ገልጿል። እነዚህ የማያስደስት የጥናት ልማዶች የመጨረሻ ውድድሩን መቀመጥ ፈታኝ አድርገውታል፣ እና እውነተኛ እውቀት ከሚጠይቁት ይልቅ የቲዎሬቲካል ፊዚክስ ጥያቄዎችን ብቻ ለመመለስ ወሰነ። የአንደኛ ደረጃ ዲግሪ በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ በኮስሞሎጂ ላቀደው የድህረ ምረቃ ጥናት የመቀበል ቅድመ ሁኔታ ነበር። ተጨንቆ፣ ከፈተናው በፊት በነበረው ምሽት ጥሩ እንቅልፍ ተኝቷል፣ እና የመጨረሻው ውጤት በአንደኛ እና በሁለተኛ ደረጃ በክብር መካከል ባለው ድንበር ላይ ነበር ፣ ይህም ከኦክስፎርድ ፈታኞች ጋር ቪቫ (የአፍ ምርመራ) አደረገ።
ሃውኪንግ እንደ ሰነፍ እና አስቸጋሪ ተማሪ መቆጠሩ አሳስቦት ነበር። ስለዚህ እቅዱን እንዲገልጽ በቪቫ ሲጠየቅ፣ “አንደኛ ከሸልሙኝ፣ ወደ ካምብሪጅ እሄዳለሁ፣ ሁለተኛ ከተቀበልኩ በኦክስፎርድ እቆያለሁ፣ ስለዚህ መጀመሪያ እንደምትሰጡኝ እጠብቃለሁ። ." እሱ ከሚያምነው በላይ ከፍ ያለ ግምት ተይዞ ነበር; በርማን እንደተናገረው፣ ፈታሾቹ “ከራሳቸው በጣም ብልህ ከሆነ ሰው ጋር እንደሚነጋገሩ ለመገንዘብ በቂ አስተዋዮች ነበሩ”። በፊዚክስ የመጀመሪያ ክፍል ቢኤ ዲግሪ ተቀብሎ ከጓደኛው ጋር ወደ ኢራን ያደረጉትን ጉዞ ካጠናቀቀ በኋላ በጥቅምት 1962 በካምብሪጅ ትሪኒቲ አዳራሽ የድህረ ምረቃ ስራውን ጀመረ።
የድህረ ምረቃ ዓመታት
የሃውኪንግ የዶክትሬት ተማሪ ሆኖ የመጀመሪያ አመት አስቸጋሪ ነበር። ከታዋቂው የስነ ፈለክ ተመራማሪ ፍሬድ ሆዬል ይልቅ የዘመናዊ ኮስሞሎጂ መስራቾች አንዱ የሆነውን ዴኒስ ዊልያም ን እንደ ተቆጣጣሪ መመደቡ መጀመሪያ ላይ ቅር ብሎት ነበር፣ እና የሒሳብ ትምህርት በአጠቃላይ አንፃራዊነት እና ኮስሞሎጂ ውስጥ ለስራ በቂ እንዳልሆነ ተገንዝቦ ነበር። የሞተር ነርቭ በሽታ እንዳለበት ከታወቀ በኋላ, ሃውኪንግ በመንፈስ ጭንቀት ውስጥ ወደቀ - ምንም እንኳን ዶክተሮቹ ትምህርቱን እንዲቀጥል ቢመከሩም, ምንም እንኳን ትንሽ ጥቅም እንደሌለው ተሰማው. ዶክተሮቹ ከተነበዩት በላይ በሽታው በዝግታ እያደገ ሄዷል። ምንም እንኳን ሃውኪንግ ሳይደገፍ መራመድ ቢከብደውም፣ ንግግሩም ሊታወቅ የማይችል ቢሆንም፣ ሁለት ዓመት ብቻ እንደቀረው በመጀመርያ ምርመራው መሠረተ ቢስ ሆኖ ተገኝቷል። በ ማበረታቻ ወደ ስራው ተመለሰ። ሃውኪንግ በጁን 1964 በነበረው ንግግር የፍሬድ ሆይል እና የተማሪውን ጃያንት ናርሊካርን ስራ በይፋ ሲቃወም የብሩህነት እና የድፍረት ስም ማዳበር ጀመረ።
ሃውኪንግ የዶክትሬት ትምህርቱን ሲጀምር በፊዚክስ ማህበረሰብ ውስጥ ስለ አጽናፈ ሰማይ አፈጣጠር ወቅታዊ ጽንሰ-ሀሳቦች- ላይ ብዙ ክርክር ነበር። በጥቁር ጉድጓዶች መሃል ላይ ያለው የጠፈር ጊዜ ነጠላነት በሮጀር ፔንሮዝ ቲዎሪ በመነሳሳት ሃውኪንግ ተመሳሳይ አስተሳሰብን ለጽንፈ ዓለሙ ሁሉ ተግባራዊ አደረገ። እና በ 1965 ውስጥ, በዚህ ርዕስ ላይ የመመረቂያ ጽሁፎችን ጻፈ. የሃውኪንግ ተሲስ በ 1966 ጸድቋል. ሌሎች አዎንታዊ እድገቶች ነበሩ: ሃውኪንግ በካምብሪጅ ውስጥ በጎንቪል እና በካዩስ ኮሌጅ የምርምር ህብረት አግኝቷል. የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በተግባራዊ ሂሳብ እና በቲዎሬቲካል ፊዚክስ፣ በጠቅላላ አንፃራዊነት እና ኮስሞሎጂ ስፔሻላይዝድ በመጋቢት 1966 ዓ.ም. እና “” ድርሰቱ ከፔንሮዝ ጋር የዚያን አመት የተከበረውን የአዳም ሽልማትን በማሸነፍ ከፍተኛ ሽልማቶችን አጋርቷል።
ከ1966-1975 ዓ.ም
በስራው እና ከፔንሮዝ ጋር በመተባበር ሃውኪንግ በዶክትሬት ዲግሪው ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የዳሰሰውን ነጠላ ንድፈ ሃሳቦችን አራዘመ። ይህ የነጠላ አካላት መኖርን ብቻ ሳይሆን አጽናፈ ሰማይ እንደ ነጠላነት ሊጀምር ይችላል የሚለውን ንድፈ ሃሳብም ይጨምራል። የጋራ ድርሰታቸው በ1968ቱ የስበት ምርምር ፋውንዴሽን ውድድር አንደኛ ሆኖ የወጣው። እ.ኤ.አ. በ1970 አጽናፈ ዓለማት ለአጠቃላይ የአንፃራዊነት ፅንሰ-ሀሳብ የሚታዘዝ ከሆነ እና በአሌክሳንደር ፍሪድማን ከተዘጋጁት የፊዚካል ኮስሞሎጂ ሞዴሎች ጋር የሚስማማ ከሆነ፣ እንደ ነጠላነት መጀመሩን የሚያሳይ ማረጋገጫ አሳትመዋል። እ.ኤ.አ. በ1969 ሃውኪንግ በካይየስ ለመቆየት በልዩ ሁኔታ የተፈጠረውን የሳይንስ ልዩነት ህብረት ተቀበለ።
እ.ኤ.አ. በ 1970 ሃውኪንግ የጥቁር ጉድጓድ ተለዋዋጭነት ሁለተኛ ህግ ተብሎ የሚታወቀውን ፣ የጥቁር ጉድጓድ ክስተት አድማስ በጭራሽ ሊቀንስ እንደማይችል አውጥቷል። ከጄምስ ኤም ባርዲን እና ብራንደን ካርተር ጋር፣ ከቴርሞዳይናሚክስ ጋር ተመሳሳይነት በመሳል አራቱን የብላክ ሆል ሜካኒኮች ህግጋትን አቅርቧል።ለሃውኪንግ ብስጭት፣የጆን ዊለር ተመራቂ ተማሪ የሆነው ጃኮብ ቤከንስታይን በመቀጠል ቴርሞዳይናሚክ ፅንሰ ሀሳቦችን ተግባራዊ ለማድረግ እና በመጨረሻም በትክክል ሄደ። በጥሬው.
እ.ኤ.አ. በ 1970 ዎቹ መጀመሪያ ላይ የሃውኪንግ ሥራ ከካርተር ፣ ቨርነር እስራኤል እና ዴቪድ ሲ ሮቢንሰን ጋር የዊለርን ያለፀጉር ንድፈ ሃሳብ አጥብቆ ደግፎ ነበር ፣ ይህም አንድ ጥቁር ቀዳዳ ከየትኛውም የመጀመሪያው ቁሳቁስ ቢፈጠር ሙሉ በሙሉ ሊገለጽ እንደሚችል ይናገራል ። የጅምላ, የኤሌክትሪክ ክፍያ እና የማሽከርከር ባህሪያት. “ጥቁር ሆልስ” በሚል ርዕስ የጻፈው ድርሰቱ በጥር 1971 የስበት ምርምር ፋውንዴሽን ሽልማት አሸንፏል።የሃውኪንግ የመጀመሪያ መጽሃፍ፣ ፣ ከጆርጅ ኤሊስ ጋር የተጻፈው በ1973 ታትሟል።
ከ 1973 ጀምሮ ሃውኪንግ ወደ ኳንተም ስበት እና የኳንተም መካኒኮች ጥናት ገባ። በዚህ አካባቢ ያከናወነው ሥራ ወደ ሞስኮ በመጎብኘት እና ከያኮቭ ቦሪሶቪች ዜልዶቪች እና አሌክሲ ስታሮቢንስኪ ጋር ባደረጉት ውይይት ተነሳስተው ሥራው በእርግጠኝነት ባልታወቀ መርህ መሠረት የሚሽከረከሩ ጥቁር ቀዳዳዎች ቅንጣቶችን እንደሚለቁ አሳይቷል ። ለሃውኪንግ ብስጭት ፣ ብዙ የተፈተሸ ስሌት ፣ ጥቁር ጉድጓዶች በጭራሽ ሊቀንሱ አይችሉም ከሚለው ሁለተኛው ህግ ጋር የሚቃረኑ ግኝቶችን አቅርቧል ፣ እና የቤከንስታይን ስለ ኢንትሮፒያቸው ያለውን ምክንያት ይደግፋል።
ሃውኪንግ እ.ኤ.አ. ከ1974 ጀምሮ ያቀረበው ውጤቶቹ እንደሚያሳየው ዛሬ ሃውኪንግ ጨረር በመባል የሚታወቀው ጥቁር ቀዳዳዎች ጨረሮችን እንደሚያመነጩ እና ጉልበታቸውን እስኪጨርሱ እና እስኪተን ድረስ ሊቀጥል ይችላል. መጀመሪያ ላይ የሃውኪንግ ጨረር አወዛጋቢ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1970 ዎቹ መገባደጃ ላይ እና ተጨማሪ ምርምር ከታተመ በኋላ ፣ ግኝቱ በቲዎሬቲካል ፊዚክስ ውስጥ ትልቅ ግኝት ሆኖ በሰፊው ተቀባይነት አግኝቷል ። ሃውኪንግ የሃውኪንግ ጨረር ከታወጀ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ በ 1974 የሮያል ሶሳይቲ () ባልደረባ ተመረጠ ። በዛን ጊዜ እሱ ከታናሽ የሳይንስ ሊቃውንት አንዱ ነበር.
ሃውኪንግ እ.ኤ.አ. - 1 ጥቁር ጉድጓድ ነበር. ውርዱ ጥቁር ቀዳዳዎች የሉም የሚለውን ሃሳብ በመቃወም "የኢንሹራንስ ፖሊሲ" ነበር. ሃውኪንግ በ1990 ውድድሩን እንዳጣ አምኗል።ይህ ውርርድ ከብዙዎቹ መካከል የመጀመሪያው የሆነው ከቶርን እና ከሌሎች ጋር ነው።ሃውኪንግ ከካልቴክ ጋር ያለውን ግንኙነት ጠብቆ ነበር፣ከዚህ የመጀመሪያ ጉብኝት ጀምሮ በየአመቱ ማለት ይቻላል አንድ ወር አሳልፏል።
1975-1990 (አውሮፓ)
ሃውኪንግ በ1975 ወደ ካምብሪጅ ተመለሰ በስበት ፊዚክስ አንባቢ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ደረጃ። እ.ኤ.አ. በ 1970 ዎቹ አጋማሽ እና መገባደጃ ላይ ህዝባዊ ፍላጎት በጥቁር ጉድጓዶች እና እነሱን በማጥናት ላይ የነበሩት የፊዚክስ ሊቃውንት እያደገ የመጣበት ወቅት ነበር። ሃውኪንግ ለህትመት እና ለቴሌቭዥን በመደበኛነት ቃለ መጠይቅ ይደረግለት ነበር።በተጨማሪም ለስራው ከፍተኛ የአካዳሚክ እውቅና አግኝቷል። እ.ኤ.አ. በ 1975 ሁለቱም የኤዲንግተን ሜዳሊያ እና ፒየስ የወርቅ ሜዳሊያ ፣ እና በ 1976 የዳኒ ሄኔማን ሽልማት ፣ የማክስዌል ሜዳሊያ እና ሽልማት እና የሂዩዝ ሜዳሊያ ተሸልመዋል ። እ.ኤ.አ. በ1977 በስበት ፊዚክስ ወንበር ፕሮፌሰር ሆነው ተሾሙ። በሚቀጥለው ዓመት የአልበርት አንስታይን ሜዳሊያ እና የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት አግኝተዋል።
እ.ኤ.አ. በ 1979 ሃውኪንግ በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሉሲያን የሂሳብ ፕሮፌሰር ተመረጠ። በዚህ ሚና የመክፈቻ ንግግራቸው፡ “መጨረሻው በቲዎሬቲካል ፊዚክስ እይታ ላይ ነውን?” የሚል ርዕስ ነበረው። እና የፊዚክስ ሊቃውንት እያጠኗቸው ያሉትን በርካታ አስደናቂ ችግሮችን ለመፍታት ን እንደ መሪ ሃሳብ አቅርቧል። የእሱ ማስተዋወቅ ከጤና-ቀውስ ጋር የተገጣጠመ ሲሆን ይህም ምንም እንኳን ሳይወድ በቤት ውስጥ አንዳንድ የነርሲንግ አገልግሎቶችን እንዲቀበል አድርጓል። ከዚሁ ጋር በሒሳብ ማስረጃዎች ላይ አጥብቆ ከመናገር ይልቅ በፊዚክስ አካሄዱ ላይ ሽግግር እያደረገ ነበር። ለኪፕ ቶርን "ከጠንካራነት ትክክል መሆንን እመርጣለሁ" ሲል ተናግሯል። እ.ኤ.አ. በ 1981 በጥቁር ጉድጓድ ውስጥ ያለው መረጃ ጥቁር ጉድጓድ በሚተንበት ጊዜ ሊጠፋ በማይችል ሁኔታ ይጠፋል የሚል ሀሳብ አቀረበ ። ይህ የመረጃ አያዎ (ፓራዶክስ) የኳንተም ሜካኒክስ መሰረታዊ መርሆችን ይጥሳል፣ እና "የጥቁር ሆል ጦርነት" ከሊዮናርድ ሱስኪንድ እና ከጄራርድ 'ት ሁፍት ጋር ጨምሮ ለዓመታት ክርክር መርቷል።የኮስሞሎጂካል የዋጋ ግሽበት - ከቢግ ባንግ በኋላ አጽናፈ ዓለሙ መጀመሪያ ላይ በሚያስደንቅ ፍጥነት መስፋፋቱን የሚጠቁም ፅንሰ-ሀሳብ ወደ ቀርፋፋ መስፋፋት ከመምጣቱ በፊት - በአላን ጉት ሀሳብ የቀረበ እና እንዲሁም በአንድሬ ሊንዴ የተሰራ ነው። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 1981 በሞስኮ ከተካሄደው ኮንፈረንስ በኋላ ሃውኪንግ እና ጋሪ ጊቦንስ በ1982 የበጋ ወቅት የኑፍፊልድ አውደ ጥናት በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ በዋናነት ያተኮረው አውደ ጥናት በኑፍፊልድ ወርክሾፕ አዘጋጁ። ወደ አጽናፈ ሰማይ አመጣጥ የኳንተም-ቲዎሪ ምርምር መስመር። እ.ኤ.አ. በ 1981 በቫቲካን ኮንፈረንስ ፣ ወደ አጽናፈ ሰማይ - ወይም መጀመሪያ ወይም መጨረሻ - ድንበር ላይኖር እንደሚችል የሚጠቁሙ ስራዎችን አቅርበዋል ።
በመቀጠል ሃውኪንግ ከጂም ሃርትል ጋር በመተባበር ጥናቱን ያዳበረ ሲሆን በ1983 ደግሞ ሃርትል-ሃውኪንግ ግዛት በመባል የሚታወቅ ሞዴል አሳትመዋል። ከፕላንክ ዘመን በፊት አጽናፈ ሰማይ በቦታ-ጊዜ ውስጥ ምንም ወሰን እንደሌለው ሀሳብ አቀረበ። ከቢግ ባንግ በፊት ጊዜ አልነበረውም እና የአጽናፈ ሰማይ መጀመሪያ ጽንሰ-ሀሳብ ትርጉም የለሽ ነው ። የጥንታዊው ቢግ ባንግ ሞዴሎች የመጀመሪያ ነጠላነት ከሰሜን ዋልታ ጋር በሚመሳሰል ክልል ተተካ። አንድ ሰው ከሰሜን ዋልታ ወደ ሰሜን መሄድ አይችልም, ነገር ግን ምንም ወሰን የለም - በቀላሉ ሁሉም የሰሜን መስመሮች የሚገናኙበት እና የሚያልቁበት ነጥብ ነው. መጀመሪያ ላይ፣ ድንበር የለሽ ፕሮፖዛል የተዘጋውን አጽናፈ ሰማይ ይተነብያል፣ እሱም በእግዚአብሔር መኖር ላይ አንድምታ ነበረው። ሃውኪንግ እንዳብራራው፣ "ዩኒቨርስ ድንበሮች ባይኖሩት ግን ራሱን የቻለ ከሆነ...እግዚአብሔር አጽናፈ ሰማይ እንዴት እንደጀመረ የመምረጥ ነፃነት አይኖረውም ነበር።"
ሃውኪንግ የፈጣሪን መኖር አልከለከለም ፣በጊዜ አጭር ታሪክ ውስጥ “የተዋሃደ ንድፈ ሃሳብ የራሱን ህልውና የሚያመጣ ነውን?” ሲል ጠይቋል ፣እንዲሁም “ሙሉ ንድፈ-ሀሳብ ካገኘን የመጨረሻው ይሆናል” ብሏል። የሰውን ምክንያት ማሸነፍ - ለዚያ የእግዚአብሔርን ሀሳብ ማወቅ አለብን"; በመጀመሪያ ሥራው፣ ሃውኪንግ ስለ እግዚአብሔር በምሳሌያዊ አነጋገር ተናግሯል። በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ የአጽናፈ ሰማይን አመጣጥ ለማብራራት የእግዚአብሔር መኖር አስፈላጊ እንዳልሆነ ጠቁሟል. ከጊዜ በኋላ ከኒይል ቱሮክ ጋር የተደረገው ውይይት የእግዚአብሔር ሕልውና ክፍት ከሆነው አጽናፈ ዓለም ጋር የሚስማማ መሆኑን እንዲገነዘቡ አድርጓል።
በጊዜ ቀስቶች አካባቢ በሃውኪንግ የተደረገ ተጨማሪ ስራ እ.ኤ.አ. በ 1985 የወረቀት ንድፈ ሀሳብ ታትሟል ፣ ድንበር የለሽ ሀሳብ ትክክል ከሆነ ፣ ያኔ አጽናፈ ሰማይ መስፋፋቱን ሲያቆም እና በመጨረሻ ሲወድቅ ፣ ጊዜው ወደ ኋላ ይመለሳል ። በዶን ፔጅ የተፃፈው ወረቀት እና በሬይመንድ ላፍላሜ የተፃፈው ገለልተኛ ስሌቶች ሃውኪንግ ይህንን ፅንሰ-ሀሳብ እንዲያነሳ አድርጓቸዋል። ክብር መሰጠቱን ቀጥሏል፡ እ.ኤ.አ. በ1981 የአሜሪካ ፍራንክሊን ሜዳሊያ ተሸልሟል እና በ1982 አዲስ አመት ክብር የብሪቲሽ ኢምፓየር ትዕዛዝ () አዛዥ ሾመ። እነዚህ ሽልማቶች የሃውኪንግን የፋይናንሺያል ሁኔታ ጉልህ ለውጥ አላደረጉም እና የልጆቹን ትምህርት እና የቤት ወጪዎችን ፋይናንስ ለማድረግ በማነሳሳት በ 1982 ስለ አጽናፈ ሰማይ ለሰፊው ህዝብ ተደራሽ የሆነ ታዋቂ መጽሐፍ ለመጻፍ ወሰነ ። በአካዳሚክ ፕሬስ ከማተም ይልቅ የጅምላ ገበያ አሳታሚ ከሆነው ባንተም ቡክስ ጋር ውል ተፈራረመ እና ለመጽሃፉ ትልቅ እድገት አግኝቷል። የጊዜ አጭር ታሪክ ተብሎ የሚጠራው የመጽሐፉ የመጀመሪያ ረቂቅ በ1984 ተጠናቀቀ።ሃውኪንግ በንግግር መፍጠሪያ መሳሪያው ካሰራቸው የመጀመሪያ መልእክቶች አንዱ ረዳቱ የታይም አጭር ታሪክ ፅፎ እንዲጨርስ ያቀረበው ጥያቄ ነው። በባንታም የሚገኘው የሱ አርታኢ ፒተር ጉዛርዲ ሃሳቦቹን በግልፅ ቴክኒካል ባልሆነ ቋንቋ እንዲያብራራ ገፋፍቶታል ይህ ሂደት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ከሚሄደው ተናዳፊ ሃውኪንግ ብዙ ክለሳዎችን የሚያስፈልገው። መጽሐፉ በኤፕሪል 1988 በዩኤስ እና በሰኔ ወር በእንግሊዝ ታትሟል እና ያልተለመደ ስኬት ሆኖ ተገኝቷል ፣ በፍጥነት በሁለቱም ሀገራት ከፍተኛ የተሸጠው ዝርዝር ውስጥ በመውጣት እና እዚያ ለወራት ቆየ። መጽሐፉ ወደ ብዙ ቋንቋዎች ተተርጉሟል, እና በመጨረሻም ወደ 9 ሚሊዮን የሚገመቱ ቅጂዎች ተሽጧል.
የሚዲያ ትኩረት ከፍተኛ ነበር፣ እና ኒውስዊክ መጽሔት ሽፋን እና የቴሌቭዥን ልዩ ሁለቱም “የዩኒቨርስ ጌታ” ሲሉ ገልፀውታል። ስኬት ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማቶችን አስገኝቷል፣ ነገር ግን የታዋቂነት ሁኔታ ተግዳሮቶችም ጭምር። ሃውኪንግ ስራውን ለማስተዋወቅ ብዙ ተጉዟል፣ እና በትናንሽ ሰአታት ድግስ እና መደነስ ይወድ ነበር። ግብዣውን እና ጎብኝዎችን አለመቀበል መቸገሩ ለስራ እና ለተማሪዎቹ የተወሰነ ጊዜ እንዲቆይ አድርጎታል። አንዳንድ ባልደረቦች ሃውኪንግ በአካለ ጎደሎነቱ ምክንያት ስለተሰማው ትኩረት ተቆጥተው ነበር።
አምስት ተጨማሪ የክብር ዲግሪዎችን፣ የሮያል አስትሮኖሚካል ሶሳይቲ የወርቅ ሜዳሊያ ፣ የፖል ዲራክ ሜዳሊያ እና፣ ከፔንሮዝ፣ ከታዋቂው ጋር በጋራ ጨምሮ ተጨማሪ የትምህርት እውቅና አግኝቷል። እ.ኤ.አ. በ 1989 የልደት ክብር ፣ የክብር ጓደኛ () ተሾመ ። በ 1990 ዎቹ መገባደጃ ላይ የእንግሊዝ የሳይንስ የገንዘብ ድጋፍ ፖሊሲን በመቃወም የ ውድቅ እንዳደረገ ተዘግቧል ።
1990-2000 (አውሮፓዊ)
ሃውኪንግ በፊዚክስ ውስጥ ስራውን ቀጠለ፡ እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በ1994 በካምብሪጅ ኒውተን ኢንስቲትዩት ሃውኪንግ እና ፔንሮዝ በ1996 "የህዋ እና የጊዜ ተፈጥሮ" በሚል የታተሙ ተከታታይ ስድስት ትምህርቶችን ሰጥተዋል። እ.ኤ.አ. በ1997 ከኪፕ ቶርን እና ከካልቴክ ባልደረባ ጆን ፕሬስኪል ጋር የተደረገውን የ1991 የህዝብ ሳይንሳዊ ውርርድ አምኗል። ሃውኪንግ የፔንሮዝ የ"ኮስሚክ ሳንሱር ግምት" ሀሳብ - በአድማስ ውስጥ ያልታሸጉ "ራቁት ነጠላ ነገሮች" ሊኖሩ እንደማይችሉ - ትክክል መሆኑን ተወራርዶ ነበር።
የእሱ ስምምነት ያለጊዜው ሊሆን እንደሚችል ካወቀ በኋላ፣ አዲስ እና የበለጠ የተጣራ ውርርድ ተደረገ። ይህ እንደዚህ ያሉ ነጠላ ነገሮች ያለ ተጨማሪ ሁኔታዎች እንደሚከሰቱ ገልጿል። በዚያው ዓመት፣ ቶርን፣ ሃውኪንግ እና ፕረስኪል ሌላ ውርርድ አደረጉ፣ በዚህ ጊዜ ስለ ጥቁር ጉድጓድ መረጃ አያዎ (ፓራዶክስ)። ቶርን እና ሃውኪንግ አጠቃላይ አንፃራዊነት ለጥቁር ጉድጓዶች መፈልፈያ እና መረጃ ማጣት የማይቻል ስላደረገው በሃውኪንግ ጨረር የተሸከመው የጅምላ ሃይል እና መረጃ “አዲስ” መሆን አለበት እንጂ ከጥቁር ቀዳዳ ክስተት አድማስ መሆን የለበትም ሲሉ ተከራክረዋል። ይህ የጥቃቅን ምክንያት የኳንተም መካኒኮችን ስለሚቃረን፣ የኳንተም ሜካኒክስ ንድፈ ሐሳብ እንደገና መፃፍ ይኖርበታል። ፕሬስኪል በተቃራኒው ተከራክሯል፣ ኳንተም ሜካኒክስ በጥቁር ጉድጓድ የሚለቀቀው መረጃ ቀደም ሲል ከወደቀው መረጃ ጋር ስለሚገናኝ በአጠቃላይ አንፃራዊነት የተሰጠው የጥቁር ጉድጓዶች ጽንሰ-ሀሳብ በተወሰነ መንገድ መሻሻል አለበት ብሏል።
ሳይንስን ለብዙ ተመልካቾች ማምጣትን ጨምሮ ሃውኪንግ ይፋዊ መገለጫውን ጠብቋል። በኤሮል ሞሪስ ዳይሬክት የተደረገ እና በስቲቨን ስፒልበርግ ፕሮዲዩስ የሆነ የፊልም እትም በ1992 ታየ። ሃውኪንግ ፊልሙ ባዮግራፊያዊ ሳይሆን ሳይንሳዊ እንዲሆን ፈልጎ ነበር፣ ነገር ግን እሱ በሌላ መልኩ አሳምኖታል። ፊልሙ, ወሳኝ ስኬት ቢሆንም, በሰፊው አልተለቀቀም. በ1993 ብላክ ሆልስ እና ቤቢ ዩኒቨርስ እና ሌሎች ድርሰቶች በሚል ርዕስ የታዋቂ-ደረጃ ድርሰቶች፣ ቃለመጠይቆች እና ንግግሮች ታትመዋል እና ስድስት ክፍሎች ያሉት ተከታታይ የቴሌቭዥን ስቴፈን ሃውኪንግ ዩኒቨርስ እና ተጓዳኝ መጽሃፍ በ1997 ታየ። ሃውኪንግ እንደጸና በዚህ ጊዜ ትኩረቱ ሙሉ በሙሉ በሳይንስ ላይ ነበር
2000–2018 (አውሮፓዊ)
ሃውኪንግ ለታዋቂ ተመልካቾች ጽሑፎቹን በመቀጠል በ2001 ዘ ዩኒቨርስ በአጭሩ አሳተመ እና በ2005 ከሊዮናርድ ሎዲኖው ጋር የፃፉትን የቀድሞ ስራዎቹን ለብዙ ተመልካቾች ተደራሽ ለማድረግ በማለም የፃፉትን ። እና አምላክ ኢንቲጀርን ፈጠረ፣ በ 2006 ታየ። ከቶማስ ሄርቶግ በ እና ጂም ሃርትል ከ2006 ጀምሮ ሃውኪንግ የኮስሞሎጂን ከላይ ወደ ታች ያዘጋጀው ፅንሰ-ሀሳብ ፈጠረ። ስለዚህም የአጽናፈ ዓለሙን ውቅር የሚተነብይ ንድፈ ሐሳብ ከአንድ የተለየ የመነሻ ሁኔታ መቅረጽ ተገቢ አይደለም ይላል። ይህን ሲያደርጉ፣ ንድፈ ሃሳቡ ጥሩ የማስተካከል ጥያቄን ሊፈታ የሚችልበትን ሁኔታ ይጠቁማል።
ሃውኪንግ ወደ ቺሊ፣ ኢስተር ደሴት፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ስፔን (የፎንሴካ ሽልማትን በ2008 ለመቀበል)፣ ካናዳ እና በርካታ ወደ አሜሪካ የተደረጉ ጉዞዎችን ጨምሮ በሰፊው መጓዙን ቀጠለ። ከአካል ጉዳቱ ጋር በተያያዙ ተጨባጭ ምክንያቶች፣ ሃውኪንግ ከጊዜ ወደ ጊዜ በግል ጄት ይጓዛል፣ እና እ.ኤ.አ. በ2011 የአለምአቀፍ ጉዞ ብቸኛው መንገድ ሆነ።
|
47276
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AB%E1%8B%9B%E1%8A%AD%E1%8A%9B
|
ካዛክኛ
|
ካዛክኛ ( /ቃዛቅሻ/) በካዛክስታንና በጎረቤት አገሮች በተለይም በቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክና በሞንጎሊያ በ15 ሚሊዮን ያሕል ተናጋሪዎች የሚነገር የቱርኪክ ቋንቋዎች ቤተሠብ አባል ነው። በካዛክስታን ከ1932 ዓም እስካሁን የሚጻፈው በቂርሎስ ጽሕፈት ሲሆን በቅርቡ ወደ ላቲን ጽሕፈት ለመመለስ የሚል እቅድ አለ። በቻይና ከ1956 እስከ 1976 ዓም ድረስ በላቲን ጽሕፈት ተጽፎ ከ1976 ዓም ወዲህ በአረብኛ ጽሕፈት ተጽፏል። ይህም አረብኛ ጽሕፈት ደግሞ በቀድሞው ሶቭየት ኅብረት ከ1919 ዓም አስቀድሞ ለካዛክኛ ይጠቀም ነበር።
ቱርኪክ ቋንቋዎች
|
17567
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%A3%E1%8A%95%E1%89%B1%20%E1%8D%8D%E1%88%8D%E1%88%B0%E1%89%B5
|
የባንቱ ፍልሰት
|
የባንቱ ፍልሰት የመጀመሪያውን የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሕዝቦች ከዛሬዎቹ ካሜሩን እና ናይጄሪያ በአንድ ሺህ ዓመታት ጊዜ ውስጥ ያደረጉት ፍልሰት ነበር። በአቅራቢያቸው ከሚገኙት ሕዝቦች ጋር ቋንቋና ዕውቀት በመለዋወጥ አዳዲስ ኅብረተሰቦችን ፈጥረዋል። ፍልሰቱ የተጀመረው ግብርና ከተጀመረ በኋላ እንደሆነ የሚታመን ሲሆን በመጀመሪያ ወደ ምሥራቅ ከዚያም ወደ ደቡብ አቅጣጫ አምርቷል።
የአፍሪካ ታሪክ
|
49737
|
https://am.wikipedia.org/wiki/1%20%E1%8A%A0%E1%88%95%E1%88%9E%E1%88%B5
|
1 አሕሞስ
|
አሕሞስ (ግብጽኛ፦ /ያሕመስ/) በጥንታዊ ግብጽ የግብጽ አዲስ መንግሥትና የ18ኛው ሥርወ መንግሥት መሥራች ሲሆን ምናልባት 1558-1534 ዓክልበ. አካባቢ የገዛ ፈርዖን ነበረ። በዘመኑ ሂክሶስን ከግብጽ አባረራቸው።
የአሕሞስ ወንድም ካሞስ ካረፈ በኋላ አሕሞስ የደቡብ ግብጽ ብቸኛ ፈርዖን ሆነ። የዙፋን ስሙ ነብፐሕቲሬ ሆነ። በ1548 ዓክልበ. ገደማ በመጨረሻ አቫሪስን ከሂክሶስ ንጉሥ ኻሙዲ ያዘ። ሂክሶስ ከግብጽ ሸሽተው የዕብራውያን ነገደ ስምዖን ርስት የሆነውን ሻሩሄንን ያዙ። አሕሞስም በሻሩሄን ለ6 አመት ከብቦአቸው በ1542 ዓክልበ. ሻሩሄንን ያዘባቸው። ሻሩሄንን ከያዘ በኋላ ወደ ደቡብ ተመልሶ ቡሄንን በኖቢያ ከኩሽ መንግሥት ያዘ። የጦር አለቃው የአሕሞስ ወልደ አባና ጽሑፍ እነዚህን ዘመቻዎች ይዘርዝራል።
ሌላ አለቃው አሕሞስ ፐን-ነኽበት በጽሑፉ ውስጥ ንጉሥ አሕሞስ በጃሂ (ፊንቄ) እንደ ዘመተ ይላል። በንጉሡ አሕሞስ 22ኛው አመት የተቀረጸ ጽሑፍ እንደሚል ከፊንቄ የተማረኩት በሬዎች የግንባታ ድንጋይ ለመሸከም ይጠቅሙ ነበር፤ ስለዚህ በፊንቄ የዘመተ ከ1536 ዓክልበ. ትንሽ በፊት እንደ ሆነ ይመስላል። ከፊንቄ የብርጭቆ ኢንዱስትሪ በግብጽ የተመሠረተው በዚህ ወቅት ያህል እንደ ሆነ ይታስባል።
አሕሞስ እንደ አባቱ በመምሰል ሦስቱን እኅቶቹን አገባቸው። መቃብሮቻቸውና የአሕሞስ ፒራሚድ ሁሉ ለሥነ ቅርስ ታውቀዋል። ልጁም 1 አመንሆተፕ በፈርዖንነት ተከተለው።
የአዲስ መንግሥት ፈርዖኖች
|
22809
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%A5%E1%89%81%E1%88%AD%20%E1%8A%A3%E1%8B%9D%E1%88%99%E1%8B%B5
|
ጥቁር ኣዝሙድ
|
ጥቁር ኣዝሙድ () ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር
የተክሉ ጥቅም
ጥቁር አዝሙድ ቅመሙ ለአያሌ ምክንያት ይጠቀማል፣ ከነዚህም አንዱ የማጣፈጫው ጸባይ ነው። በጥንት ዳቦዎችን ለማጣፈት ብዙ ይጠቀም ነበር። አሁን ግን በተለይ በመጠጥ፣ ከቁንዶ በርበሬ፣ ኮረሪማና ዝንጅብል ጋራ ተቀላቅሎ ይጠቀማል። ብርቱ መጠጦች እንደ አረቄ ወይም ካቲካላ ይህን ጨምረዋል።
ለጥቁር አዝሙድ ጥቅም የተደረጀው ምክንያት የራስ ምታት እና የተለያዩ በሽቶችን ለማባረር ችሎታው እንዳለው በአፍ ይነገራል። ራስ ምታቱን ለማባረር፣ ዘሮቹ፣ ከተቀለጠ ቅቤ ጋር ተቅላቅለው፣ በንጹሕ ጨርቅ ተጠቅልለው፣ ባፍንጫው ይሸተታሉ።
የኢትዮጵያ እጽዋት
|
13440
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A5%E1%88%AB
|
ሥራ
|
ሥራ ፣ በተፈጥሮ ህግጋት ጥናት መሰረት፣ በጉልበት የሚተላለፍ አቅም መጠን ማለት ነው። የሥራ መለኪያ መስፈርቱ ጁል () ይባላል።
የሥራን ጽንሰ ሃሳብ ያገኘው ፈረንሳዊው ሂሳብ ተመራማሪ ጋስፓርድ ጉስታቭ ሲሆን በሱ ትርጓሜ ሥራ ማለት ጉልበት ሲባዛ በርቀት ነበር።
ሥራ = ጉልበት ርቀት ... ግን ጉልበቱ በርቀቱ አቅጣጫ መሆን አለበት።
ከላይ የጻፍነውን አባባል በቀላሉ በሂሳብ ቋንቋ ማስቀመጥ ይቻላል። ለዚህ ተግባር የዶት ብዜትን መጠቀም ግድ ይላል።
ሌሎች ድሮች
|
3279
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%8A%9E
|
ሰኞ
|
ሰኞ በእሑድ እና በማክሰኞ መሀከል የሚገኝ በብዙ አገሮች የሳምንቱ ሁለተኛ ቀን፣ በሌሎች ብዙዎች ዘንድ (ለምሣሌ፦ የአውሮፓ አገሮች) ደግሞ የመጀመሪያ ቀን ነው።
ሰኞ በአሁኑ ጊዜ
የሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን እሑድ በሆነባቸው አገሮችም ጭምር ብዙዎች ሰኞን የመጀመሪያ አድርገው ይወስዱታል። ይህም በአብዛኛው ለብዙ ሰራተኞችና ተማሪዎች ከቅዳሜ እና እሑድ እረፍት በኋላ የመጀመሪያው የሥራ ወይም የትምህርት ቀን በመሆኑ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ይህ እውነታ ሰኞን በአንዳንዶች ዘንድ እንደ መጥፎ ቀን እንዲቆጠር አድርጎታል።
ሰኔና ሰኞ
በኢትዮጵያ ውስጥ በአንዳንዶች ዘንድ ሰኔ አንድ ሰኞ ቀን ከዋለ መጥፎ ነው የሚል ምንም ሳይንሳዊም ሆነ ኃይማኖታዊ መሠረት የሌለው አጉል እምነት አለ። "ሰኔና ሰኞ" መነሻው አንድ ሰኞ ቀን በዋለ ሰኔ አንድ ተግባር ላይ በዋለ አዋጅ ሳይሆን እንደማይቀር ይገመታል። አዋጁ በኢትዮጵያ ውስጥ መኪና የሚነዳበትን የመንገዱን ክፍል የቀየረ ነበር፤ በመንገዱ በግራ ክፍል መነዳቱ ቀርቶ በቀኝ ክፍል እንዲነዳ የሚያዝ አዋጅ ነበረ። በተፈጠረው ለውጥ ብዙ አደጋ በመድረሱ፡ ከዚያ ጀምሮ ሰኔና ሰኞ ሲገጣጠሙ እንደመጥፎ እድል ይታያል።
|
35785
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%89%80%E1%88%8C%20%E1%8A%A0%E1%88%89%E1%88%8B%20%E1%8A%A0%E1%89%A3%20%E1%8A%90%E1%8C%8B%20%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%20%E1%8A%A0%E1%89%80%E1%8D%8D%20%E1%8A%A0%E1%8B%A8%E1%88%AD%20%E1%88%9B%E1%88%A8%E1%8D%8A%E1%8B%AB
|
መቀሌ አሉላ አባ ነጋ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ
|
መቀሌ አሉላ አባ ነጋ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ ከመቀሌ በአሥር ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ዘመናዊ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ነው።
አየር ማረፊያው በዘመናዊ መልክ የተገነባ እና የተደራጀ ሲሆን ከባሕር ወለል በ ፪ሺ ፪መቶ ፶፯ ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል። ባሁኑ ጊዜ አየር ማረፊያው አንድ ባለ ፫ሺ ፮፻ ሜትር ርዝመት በ፵፫ ሜትር ስፋት ያለው አስፋልት የለበሰ ማኮብኮቢያ ያለው ሲሆን እንደ ቦይንግ ፯መቶ ፶፯ አይነት አየር ዠበቦችን ማስተናገድ ይችላል። ዓለም አቀፍ በረራዎችን ለማከናወን የሚያስችሉት እንደ ጉምሩክ፣ ኢሚግሬሽን፣ የደህንነት ተቋማትና ኳራንቲን የመሳሰሉ መሰረተ ልማቶችን ያሟላ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባሕር-ዳርን እና መቀሌን ከካርቱም ጋር በማገናኘት ጥቅምት ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ዓለም አቀፍ በረራ የጀመረ ሲሆን፣ የሁለቱን አገራት የንግድ፤ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ምዕራፍ ለማሸጋገር የላቀ ሚና እንደሚኖረው ይገመታል። የበረራ መስመሩ በሳምንት ለአራት ቀናት የሚከናወን ሲሆን፣ ሰሜን ሱዳንን ከሰሜን የአገራችን ክፍል በቀጥታ የሚያገናኝ ነው። አየር መንገዱ ከሱዳን ለሚመጡ ጎብኝዎች የአባይ ወንዝን ምንጭ፤ የጢስ እሳት ፏፏቴን፤ በ፯ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተገነባውን እና በአፍሪቃ የመጀመሪያው መስጊድ እንደሆነ የሚነገርለትን አል ነጃሺ መስጊድ እና ሌሎችንም የሰሜን ኢትዮጵያ መስህቦዎችን ለመጎብኘት እንደሚያመቻች ይታመናል።
ከዚህ በተጨማሪም መቀሌ አሉላ አባ ነጋ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በቅርቡ ያስገባውን፣ ፻፶ ቶን ማስተናገድ የሚችል ቀዝቃዛ መጋዘን በመጠቀም የአበባ፤ ፍራፍሬና አታክልት፤ ዓሣ እና የሥጋ ምርቶችን በቀጥታ ወደዓለም ገበያዎች ማጓጓዝ በቅርቡ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ አየር ማረፊያዎች
|
52645
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%8C%E1%8A%AD%E1%88%B3%E1%8A%95%E1%8B%B0%E1%88%AD%20%E1%89%AE%E1%8A%95%20%E1%88%83%E1%88%9D%E1%89%A6%E1%88%8D%E1%89%B5
|
አሌክሳንደር ቮን ሃምቦልት
|
ፍሬድሪክ ዊልሄልም ሃይንሪች አሌክሳንደር ቮን ሁምቦልት (ጀርመንኛ: ; ሴፕቴምበር 14፣ 1769 - ግንቦት 6፣ 1859) እንዲሁም ታዋቂው አሌክሳንደር ቮን ሃምቦልት (), የጀርመን ፖሊማት ፣ ጂኦግራፈር፣ የተፈጥሮ ተመራማሪ ፣ አሳሽ እና ደጋፊ ሮማንቲክ እና ሳይንስ ነበር ፣ እሱ እንደ የፕሩሲያ ጠቅላይ ሚኒስትር ታናሽ ወንድም ቪልሄልም ፎን ሀምቦልት.
ከ1799 እስከ 1804 ባለው ጊዜ ውስጥ ሃምቦልት በዘመናዊው የምዕራቡ ዓለም ሳይንሳዊ እይታ ለመጀመሪያ ጊዜ በማሰስ እና በማብራራት ወደ አሜሪካ በስፋት ተጉዟል። የጉዞው መግለጫ ከ21 ዓመታት በላይ ተጽፎ በብዙ ጥራዞች ታትሟል። ሃምቦልት ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር የሚዋሰኑት መሬቶች አንድ ጊዜ ተቀላቅለዋል (በተለይ ደቡብ አሜሪካ እና አፍሪካ) የሚል ሀሳብ ካቀረቡ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች አንዱ ነበር።
ሁምቦልት ኮስሞስ የሚለውን ቃል ከጥንታዊው ግሪክ ከሞት አስነስቶ ኮስሞስ ለተባለው ባለ ብዙ ጥራዝ ድርሰቱ መድቦ የተለያዩ የሳይንስ እውቀትና የባህል ቅርንጫፎችን አንድ ለማድረግ ፈለገ።
ይህ ጠቃሚ ስራ ስለ አጽናፈ ሰማይ እንደ አንድ መስተጋብር አካል ያለውን አጠቃላይ ግንዛቤ አነሳስቷል፣ እሱም የስነ-ምህዳር ፅንሰ-ሀሳቦችን ወደ የአካባቢ ጥበቃ ሀሳቦችን አስተዋወቀ። እ.ኤ.አ. በ1800 እና በ1831 ዓ.ም በሳይንስ በጉዞው ወቅት በተፈጠሩት ምልከታዎች ፣በአካባቢው የሚከሰቱ የልማት ተፅእኖዎች በሰው ልጅ የአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ገለፁ።
የጀርመን ታሪክ
የጀርመን ሰዎች
|
31394
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%BB%E1%8B%8D%E1%8A%AB%E1%8A%95%E1%8C%8D
|
ሻውካንግ
|
ሻውካንግ (ቻይንኛ፦ ) በጥንታዊ ቻይና የሥያ ሥርወ መንግሥት ዘመን ንጉሥ ነበር።
በ1946 ዓክልበ. ግድም አባቱ ሥያንግ በአመጸኞቹ ሃን ዥዎና ልጁ ጅያው ተገደለ፤ ንግሥቷ ሚን እርጉዝ ሆና አመለጠችና በሚከተለው ዓመት በስደት ሻውካንግን ወለደች።
እርሱ አድጎ ሻውካንግና ቢትዎደዱ ሜ ከ1926 እስከ 1906 ዓክልበ. ድረስ አመጸኖቹን ተዋጉ። በመጨረሻ በ1906 ዓክልበ. በአንዪ በሆነ ውግያ ሃን ዥዎና ልጁ ጅያው ተገደሉ፣ ሻውካንግም ንጉሥ ሆኖ የቻይና መንግሥት ያንጊዜ አልጠፋም።
የቀርከሃ ዜና መዋዕል በተባለው ጽሑፍ ዘንድ፣ በመጀመርያው ዓመት መሳፍንቱ ወደ ግቢው መጥተው ተገዙለት፤ በሚከተለውም ዓመት የፋንግ አሕዛብ መጥተው ተገዙለት። በ፫ኛው ዓመት የእርሻ ሚኒስትር ወደ ሹመቱ መለሰው። በ፲፩ኛው ዓመት ሚኒስትሩን የሻንግ መስፍን ሚንግ ቢጫ ወንዝን እንዲያስቆጣጠር አዘዘው። በ፲፰ኛው ዓመት ጊቢውን ወደ ይወን አዛወረው። በ፳፩ኛው ዓመት፣ ዓረፈና ልጁ ዡ ተከተለው።
የሥያ ሥርወ መንግሥት
|
17657
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%8B%B2%E1%88%B5%20%E1%8A%A0%E1%89%A0%E1%89%A3%20%E1%8A%A8%E1%89%B0%E1%88%9B%20%E1%88%9B%E1%8B%98%E1%8C%8B%E1%8C%83%20%E1%89%A4%E1%89%B5
|
የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት
|
የአዲስ አበባ ከተማ የሕዝብ እድገት፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና የከተማዋ የቆዳ ስፋት እየጨመረ በመምጣቱ፣ ለንጉሱ ግብር ለማስገባት ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ የክልል አስተዳዳሪዎችም በመብዛታቸው እነዚህን እንቅስቃሴዎች በአግባቡ ለማስተናገድ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር መመስረት ያስፈልጋል ተብሎ የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት በ1909 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ተመሰረተ፡፡ የማዘጋጃ ቤት አስተዳደር ከተመሠረተ በኋላ ሊዮ ሸፍኑ በተባለ አንድ ፈረንሳዊ እና እድሊቢ በተባለ ሶሪያዊ ግፊት ማዘጋጃ ቤቱ አድዋ ሲኒማ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እንዲመሠረት ተደረገ፡፡ ማዘጋጃ ቤቱም የከተማው ማሕበር ቤት ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ ይህ ሥያሜ የተሰጠውም ማዘጋጃ ቤቱ እንዲመሰረት ግፊት ሲያደርጉ በነበሩት በሶሪያዊው እድሊቢ ነው፡፡ ተቋሙ የከተማ ማሕበር ቤት ተብሎ ቢሰየምም አንድም የከተማዋ ነዋሪ በአባልነት አለመመዝገቡ፣ ይልቁንም የማዘጋጃ ቤቱን ሥራ የሚያከናውኑት የመንግሥት ተቀጣሪዎችና የተለያዩ የውጭ አማካሪዎች በመሆናቸው፣ ለተቋሙ የተሰጠው የከተማው ማሕበር ቤት የሚለው ስያሜም “” የሚለውን የእንግሊዝኛ አቻ ቃል አይወክልም በሚል በወቅቱ ከንቲባ የነበሩት ኅሩይ ወልደሥላሴ (ብላቴን ጌታ) በ1920 ዓ.ም ማዘጋጃ ቤት የሚል ስያሜ እንደተሰጠው በታሪክ ሰፍሯል፡፡
ማዘጋጃ ቤቱ በወቅቱ ማዘጋጃ ቤታዊ የታክስ ምንጮችን መመስረትና ታክስ መሰብሰብ፣ ለውጭ ሰዎችና በንጉሱ እውቅና ለተሰጣቸው ባለሥልጣናት መሬት ማደል፣ የንግድ ፈቃድ መስጠት፣ ማዘጋጃ ቤታዊ የሆነ የፍትህ አገልግሎት ማዳረስ የመሳሰሉትን ተግባራት ያከናውን ነበር፡፡
ይህ ለአዲስ አበባ ከተማ እድገትና ለከተማዋ ህዝብ ደህንነት የተቋቋመው ማዘጋጃ ቤት በ1926 ዓ.ም የሚያከናውናቸውን ተግባራት በ16 ዋና ዋና የሥራ ክፍሎች በመከፋፈል ከ250 ባልበለጡ ሠራተኞች ሥራውን ያከናውን ነበር፡፡ እነርሱም የከንቲባ ጽ/ቤት፣ የርስት ክፍል፣ የካርታ ማንሳትና የግምት ክፍል፣ የመንገድ ክፍል፣ የሂሳብ ክፍል፣ የግምጃ ቤት፣ የዳኝነት ክፍል፣ የአራዳ ዘበኛ፣ የተሽከርካሪና የመንጃ ፈቃድ/የቁማር ጨዋታ ቁጥጥርን ጨምሮ/ክፍል፣ የጽዳት ክፍል፣ የህክምና ክፍል፣ የገንዘብና የሥራ መቆጣጠሪያ ክፍል፣ የምሥጢር ክፍል /ልዩ ጓዳ/፣ የውል ክፍል፣ የእሳትና አደጋ መከላከያ ክፍልና የጋራዥ ክፍል የተባሉት ነበሩ፡፡ እነዚህ የሥራ ክፍሎች ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ እያንዳንዱ ክፍል ንዑስ ቅርንጫፎች ነበሩት፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ ከላይ የተዘረዘሩት ዋና ዋና ክፍሎች ይኑሩት እንጂ ለከተማዋ እድገት ሲያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ አመርቂ እንዳልነበረ የተለያዩ ጽሁፎች ያስረዳሉ፡፡
ለዚህም ምክንያቱ ማዘጋጃ ቤቱ በራሱ ከሚያገኘው ገቢ ውጪ በመንግሥት የሚመደብለት የመተዳደሪያ በጀት ስላልነበረው ነው፡፡ በዘመኑ ያገኝ የነበረው የአገልግሎት ዋጋ ወይም ግብር የሚሰበሰበው ከተወሰኑ ድርጅቶች ብቻ ሲሆን የሚያስከፍለው ግብር ደግሞ በጣም አነስተኛ ነበር፡፡ በዘመኑ ገቢ የሚገኘው ማዘጋጃ ቤቱ ከሚያከራያቸው ከራሱ ቤቶች፣ ከንግድ ፈቃድ፣ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ካላቸው ቦታዎችና ከውጭ አገር ዜጐች ጋር ተቀጥረው ከሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ብቻ ነበር፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ የቦታ ካርታ መሰጠት የተጀመረው በ1903 ዓ.ም ሱሆን፣ በ1920ዎቹ በዚህ ዙሪያ በርከት ያለ ገቢ አይሰበሰብም ነበር፡፡ በዚህ ሂደት አገልግሎቱን ሲሰጥ የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ከከተማዋ እድገት ጋር ተያይዞ የመጣውን የህዝቡን የከተማ ኑሮ ለማሻሻልና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል አደረጃጀትና ሕንጻ ያስፈልገዋል ተብሎ ዛሬ በማገልገል ላይ የሚገኘው የማዘጋጃ ቤት ሕንፃ እንዲገነባ ጥቅምት 23 ቀን 1942 ዓ.ም በዓፄ ኃይለ ሥላሴ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ፡፡ በዚህ ጊዜ የማዘጋጃ ቤት አማካሪዎች የሚባል ምክር ቤት የነበረ ሲሆን የም/ቤቱ ምርጫም በየዓመቱ የሚካሄድ ነበር፡፡ በወቅቱ ማዘጋጃ ቤቱ ለህዝቡ የሚሰጠውን አገልግሎት እያሰፋ የሄደ ሲሆን ለአብነት ያህልም ለማዘጋጃ ቤት ጥያቄ በማቅረብ በግለሰብ ደረጃ በየቤቱ የውሃ ቧንቧ ካስገባው የከተማዋ ነዋሪ በተጨማሪ ህዝቡ በነፃ በየሰፈሩ ውሃ የሚቀዳባቸው 58 የውሃ ማደያዎች /ቦኖ/ ነበሩ፡፡
እንዲሁም የኤሌከትሪክ ብርሃንን በተመለከተ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለከተማው መንገዶች ለሚሰጠው የመብራት አገልግሎት ማዘጋጃ ቤቱ ዋጋ ይከፍል ነበር፡፡ በወቅቱ አዲስ አበባ ውስጥ የነበረው የመብራት ኃይል 45,000 ቮልት ነበር፡፡
በዚያን ጊዜ ማዘጋጃ ቤት ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች አንዱ ድሆችን መጦር ሲሆን፣ የድሆች ጡረታ ቤት የሚባል የሥራ ዘርፍ በማቋቋም በከተማዋ ውስጥ ጠዋሪ የሌላቸውን ደካሞች ይረዳ ነበር፡፡ ለዚህም አገልግሎት በጊዜው 15693.00 ብር ያወጣ ነበር፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት በዚህ ሂደት የአገልግሎት አድማሱን እያሰፋና በጀቱንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ በመምጣት በአሁኑ ወቅት ለከተማዋ ነዋሪ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን በስፋት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
ዋቢ ምንጭ
አ.አ. ሚሌኒየም ጽ/ቤት አዲስ አበባ ባለፈውና በአዲሱ ሚሌኒየም ገጽ 10-12
አዲስ አበባ
|
30921
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%84%E1%88%AD%E1%8A%A9%E1%88%8C%E1%88%B5%20%E1%88%8A%E1%89%A2%E1%8A%A9%E1%88%B5
|
ሄርኩሌስ ሊቢኩስ
|
ሄርኩሌስ ሊቢኩስ ወይም ሊብዩስ ጣልያናዊው መኖኩሴ አኒዩስ ዴ ቪቴርቦ በ1490 ዓ.ም. ባሳተመው ዜና መዋዕል ዘንድ፣ በጣልያን ሀገር የነገሠ ንጉሥ ነበር። በሮሜ አፈ ታሪክ ደግሞ የሄራክሌስ ስም «ሄርኩሌስ» ነበረ።
በአኒዩስ ጽሑፍ መሠረት፣ ሄርኩሌስ የኦሲሪስ አፒስ ልጅ ነበር። አባቱ ኦሲሪስ የግብጽ ፈርዖን ሲሆን በ2003 ዓክልበ. ግድም በቲፎን ተገደለ። ልጁ ሄርኩሌስ ግን የአባቱን ቂም በቅሎ ቲፎንን ገደለውና ለአጭር ጊዜ ፈርዖን ሆነ። ቶሎ ግን ለግብጽ ተገዥ ወደ ሆኑት አገራት ሄዶ አመጸኛ አገረ ገዦቹን አስወጣቸው። ቡሲሪስን ከፊንቄ (ከነዓን)፣ ሌላውን ቲፎን ከፍርግያ (ማዮንያ)፣ ሚሊኑስን ከቀርጤስ፣ አንታዮስን ከሊብያ አስወጣቸው። ከዚያ ፫ቱን ሎምኒኒዎች ከእስፓንያ አስወጥቶ በፈንታቸው ሂስፓሉስን ንጉሥ ሆኖ ሾመው። ከዚያ በኬልቲካ (ፈረንሳይ) አለፈና የንጉሣቸውን ኬልቴስን ልጅ ጋላጠያን አግብቶ ጋላጤስን ወለደችለት። ከዚያ ሄርኩሌስ ለ፲ ዓመት ያህል በጣልያን ንጉሥ ሌስትሪጎን ላይ ጦርነት አድርጎ አሸነፈውና በ1992 ዓክልበ. ግድም ዘውዱን ተከተለው።
ለ፳ ዓመታት ጣልያንን በሰላም ገዝቶ ብዙ መንደሮች ሠራ። በ1973 ዓክልበ. ግድም ግን የጊጋንቴስ ወገን እንደገና ጦርነት ጀመሩ። በ1968 ዓክልበ. ግድም አጠፋቸውና እንደገና ሌላ 30 አመታት ገዛ። በ1938 ዓክልበ. ግድም ልጁን ቱስኩስ ከዶን ወንዝ ጠርቶ የጣልያን ንጉሥ አድርጎ ወደ እስፓንያ ተመለሰና የልጁን ልጅ ሂስፓኑስን በዙፋን ተከተለው። በዚህ ወቅት ከሠሩት ከተሞች ባርሴሎና በሄርኩሌስ እንደ ተሠራ የሚል ልማድ አለ። በ1929 ዓክልበ. ግድም ሄርኩሌስ ዓረፈና በጋዲር እንደ ተቀበረ አኒዩስ ይለናል።
ዮሐንስ አቬንቲኑስ ባሳተማቸው መዝገቦች ውስጥ ስለ ሄርኩሌስ ሊቢኩስ ትንሽ ዝርዝሮች ይጨመራሉ። በፍርግያ በሌላው ቲፎን ፋንታ ኦምፋሌን አሾመ። ሄርኩሌስ ደግሞ በጀርመን ሲቆይ የጋምብሪቪዩስ ሴት ልጅ አራክሳን አግብቶ አራት አለቆች ወለደችለት፦ ቱስኩስ፣ ትንሹ ስኩቴስ፣ አጋጡርሲስ፣ ፔውኪንገር፣ ጉጦ ናቸው ይጽፋል።
በ1842 ዓ.ም. አንድ መቃብር ቦታ በታራጎና እስፓንያ ተገኝቶ የሄርኩሌስ መቃብር እንደ ነበር የሚል ማስታወቂያ ታተመ። በዚሁ መቃብር ያለው ጽሑፍ በግብጽኛ እና በኢቤርኛ ሲሆን ሄርኩሌስና ወገኑ ከግብጽ ወደ እስፓንያ ስለ መድረሳቸው እንደ ነበር ተባለ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ውስጥ የአውሮፓ ሊቃውንት ይህ ሃሣዊ ሥነ ቅርስ እንደ መሰላቸው አሳወቁ።
የእስፓንያ አፈታሪካዊ ነገሥታት
የጣልያን አፈታሪካዊ ነገሥታት
|
15944
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%85%E1%88%8D%E1%8B%8D%E1%8A%93%20%E1%89%80%E1%8B%8D%E1%88%B5
|
የኅልውና ቀውስ
|
የኅልውና ቀውስ የምንለው አንድ ግለሰብ በህይወት ጎዳናው ላይ በድንገት ቆም ብሎ በአጠቃላይ የህይወቱ መሰረቶች ላይ ጥያቄ ሲያቀርብ ነው፡- ለምሳሌ " ህይወቴ ትርጉም፣ ዋጋ ወይም አላማ አለው ወይ?" ብሎ ሲጠይቅ። ይህ ጉዳይ በኅልውነት ፍልስፍና ከፍተኛ ቦት ተሰጥቶት የሚጠና ነው።
የኅልውና ቀውስ ብዙ ጊዜ የሚነሳው ባንድ ግለሰብ ህይወት ውስጥ ክፍተኛ ግምት የሚሰጣቸው ክንውኖች ሲፈጸሙ ነው፣ ለምሳሌ ያልን እንደሆን
በአለም ውስጥ ብቻየን ነኝ ብሎ ከማሰብ
አንድ ግለሰብ በርግጥም መሞቱ የማይቀር መሆኑን በርግጥ ሲረዳ
አንድ ሰው ህይወቱ ትርጉም ሆነ አላማ እንደሌለው ሲገነዘብ
አንድ ሰው ሙሉ ነጻነት እንዳለው ሲረዳ፣ ሃላፊነቱንም በዛው ልክ ሲቀበል ወይም ሲክድ
እጅግ አስደሳች ወይም እጅግ ጎጂ የሆነ ጉዳይ በግለሰብ ላይ ሲደርስ
በጋብቻ ወቀት፣ በፍቺ፣ መለያየት፣ የሚወዱት ሰው መሞት፣ አዲስ ፍቅረኛ፣ ልጆች አድገው ቤት ሲለቁ፣ 30 ወይም 40 ዓመት ሲሞላ፣ ወዘተ...
እንግዲህ ይህን ቀውስ ከሌሎች ለየት የሚያደርገው ጉዳይ አለ። አንድ ግለሰብ የራሱ ህይወት በጣም አስፈላጊ መሆኑን ለራሱ እያወቀ ነገር ግን አጠቃላይ የሰወች ኑሮ ትርጉም የለሽና አላማም የሌለው መሆኑን ሲገነዘብ በጭንቅላት ውስጥ ፍትጊያ ይፈጥራል። ይህ ፍትጊያ የከባቢው ባህልና እራሱ አይምሮአችን በደመነፈስ እኒህን ለመከላከል የፈጠራቸውን የመከላከያ መሳሪያወች ያሸንፋል። ስለዚህ የኅልውና ቀውስ በሁሉም ሰው በሁሉም ህብረተሰብ ኅልው በመሆን ብቻ የሚፈጠር መሰረታዊ ጥያቄ ነው። የኅልውነት ፍልስፍና እንግዲህ የሚለው፣ እያንዳንዱ ግለሰብ የየራሱን ህይወት ትርጉምና አላማ በማስቀመጥ ይህን ቀውስ በበቂ ሁኔታ መፍታት ይችላል።
መደብ : ኅልውነት
መደብ : ፍልስፍና
|
41867
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%B0%E1%8C%8D%E1%8B%B5%20%E1%8C%8D%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%8A%A5%E1%8C%8D%E1%8B%9A%E1%8A%A0%E1%89%A5%E1%88%84%E1%88%AD
|
አሰግድ ግብረእግዚአብሄር
|
አሰግድ ገብረእግዚአብሔር በማስታወቂያ ሚኒስቴር በልዩ ልዩ ክፍሎች ሰርቷል በጋዜጠኛነትም የሰንደቃላማችን ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅ እስከመሆን ደርሷል። በብሄራዊ ትያትር ቤትም የህዝብ ግንኙነት ክፍል ምክትል ሀላፊም ነበር።
እንደዛሬው የትያትር ጥበብ ሳይስፋፋ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ከሚሉ ጥቂት ተዋናዮች መካከል አንዱ አሰግድ ነበር። አምስት ለዜሮ፣ ግደይ ግደይ አለኝ፣ ሳይቋጠር ሲተረተር፣ ብቀላና ሁለት ወዶ በተባሉት ተውኔቶች ላይ ተጫውቷል። ሀምሌትና በቀይ ካባ ስውር ደባ ደግሞ በመድረክ ላይ ከሰራቸው መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በዛን ዘመን በኢትዮጵያውያን አርቲስቶች ከተሰሩት የውጪ ፊልሞች ደግሞ ፈረንጅ በተባለው ፊልም ላይ ተሳትፎ ችሎታውን አስመስክሯል።
የኢትዮጵያ ተዋናዮች
|
15647
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%95%20%E1%8D%8D%E1%8C%A5%E1%8A%90%E1%89%B5
|
የብርሃን ፍጥነት
|
የብርሃን ፍጥነት በ ምልከት ሲወከል፣ ለተፈጥሮ ህግጋት ጥናት ከፍተኛ አስተዋጾ ያለው የተፈጥሮ ቋሚ ቁጥር ነው። ብርሃን በቅጽበት ሳይሆን በተወሰነ ፍጥነት እንደሚጓዝ ቀደምት ሳይንቲስቶች የደረሱበት ጉዳይ ነው። የብርሃን ፍጥነት ለብርሃን ብቻ ሳይሆን ለብርሃን ቤተሰብ ለሆኑት ለኮረንቲና ማግኔት ማዕብሎች ያገለግላል። በአሁኑ ዘመን እንደተለካ፣ የብራሃን ፍጥነት በጥልቁ 299,792,458 ሜትር በሰኮንድ ነው። በሌላ አነጋገር አንድ የብርሃን ጨረር ከፀሐይ ተነስቶ መሬት ለመድረስ 8 ደቂቃ ይፈጅበታል ወይም ደግሞ አንድ የብርሃን ጨረር በየአንድ አንዷ ሰከንድ ወደ ሶስት መቶ ሚሊዮን የሚጠጋ ሜትር (300 ሺህ ኪሎ ሜትር) ይጓዛል።
ሥነ ፈለክ
|
42428
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B2%E1%8A%AB%E1%8A%91%E1%88%B5%20%28%E1%8B%A8%E1%88%9B%E1%88%8E%E1%89%B5%20%E1%89%B3%E1%8C%88%E1%88%B5%20%E1%88%8D%E1%8C%85%29
|
ሲካኑስ (የማሎት ታገስ ልጅ)
|
ሲካኑስ ጣልያናዊው መኖኩሴ አኒዩስ ዴ ቪቴርቦ በ1490 ዓ.ም. ባሳተመው ዜና መዋዕል ዘንድ፣ በጣልያን ሀገር የነገሠ ንጉሥ ነበር። የማሎት ታገስ ልጅ ይባላል። የቬቱሎኒያ ክፍል ለሲካኑስ አንደ ተሰየመ ይጨምራል። በርሱ ዘመን የፋይጦን ልጅ ሊጉር ሠፈረኞች ከኤሪዳኑስ (ፖ ወንዝ) አና ከኢስተር (ዳኑብ ወንዝ) መካከል ወዳለው ክፍል አንደ ላከ ይጽፋል። ከዚያ ሲካኑስ የቀድሞ ጣልያን ንጉሥ ያኑስ ሚስት ኣሬቲያ ወይም ሆርቺያ ለማክበር ኣምልኮቷን መሠረተ።
ከቲቤር ወንዝ ደቡብ የኖሩት ታላላቅ ሰዎች ወይም ጊጋንቴስ ወገን ተነሣ። ከሲካኑስ በኋላ ዔናቂ ሉኪ የሚባሉ ኣምባገነኖች ጣልያንን በግፍና ጭቆና ኦሲሪስ አፒስ አስካስወጣቸው ድረስ አንደ ገዙ ይጻፋል።
የጣልያን አፈታሪካዊ ነገሥታት
|
49646
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%8A%93%E1%8A%BD%E1%89%B0%E1%8A%95%E1%88%AC%20%E1%8A%A0%E1%88%95%E1%88%9E%E1%88%B5
|
ሰናኽተንሬ አሕሞስ
|
ሰናኽተንሬ አሕሞስ በላይኛ ግብጽ በ2ኛው ጨለማ ዘመን (17ኛው ሥርወ መንግሥት) ለአጭር ወራት ምናልባት 1567 ዓክልበ. አካባቢ በሂክሶስ ዘመን የገዛ ፈርዖን እንደ ነበረ ይታመናል።
እስከ 2004 ዓም ድረስ ስሙ «ሰናኽተንሬ» ብቻ ከካርናክ ፈርዖን ዝርዝርና በአንዳንድ መቃብር ተጽፎ ይታወቅ ነበር። በ2004 ዓም ተጨማሪ ቅርሶች ተገኝተው ሌላው ስሙ አሕሞስ (ያሕመስ)፣ የሔሩ ስምም መሪመዓት እንደ ሆነ ታወቀ። የተከታዩ የሰቀነንሬ ታዖ አባት፣ የካሞስና የ1 አሕሞስ አያት እንዲሁም የተቲሸሪ ባለቤት እንደ ሆነ ይገመታል፣ ይህ ግን እርግጥ አይደለም።
የሁለተኛው ጨለማ ዘመን ፈርዖኖች
|
23050
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B5%E1%88%AB%E1%8A%95%E1%88%B5%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B5%E1%8A%93%20%E1%88%98%E1%8C%88%E1%8A%93%E1%8A%9B%20%E1%88%9A%E1%8A%92%E1%88%B5%E1%89%B4%E1%88%AD
|
የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር
|
የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር (ሞታክ) በኢትዮጵያ መንግስት ስር ያለ የሚኒስቴር መስሪያ ቤት ነው። ዋና ፅሕፈት ቤቱ አዲስ አበባ ይገኛል።
የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር ከ2003 ጀምሮ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሆኖ የተዋቀረ ሲሆን የመገናኛው ዘርፍ በመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ስም ተዋቅሯል።
የውጭ ንባብ
(አማርኛ)የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር (
የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር (
የመገናኛ ሚኒስቴር
የኢትዮጵያ መንግስት ሚኒስቴሮች
የትራንስፖርት ሚኒስቴር
የኢትዮጵያ መገናኛ ሚኒስቴሮች
|
52606
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%BA%E1%8A%95%E1%8B%9E%20%E1%8A%A0%E1%89%A4
|
ሺንዞ አቤ
|
ሺንዞ አቤ (፣ አቤ ሺንዞ፣ []፣ መስከረም 21 ቀን 1954 - ጁላይ 8 2022) የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሊበራል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኤልዲፒ) ፕሬዝዳንት ከ2006 እስከ 2007 እና ከ2007 ጀምሮ ያገለገሉ የጃፓን ፖለቲከኛ ነበሩ። ከ2012 እስከ 2020 በጃፓን ታሪክ ረጅሙ ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ። አቤ እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2006 በጁኒቺሮ ኮይዙሚ ዋና የካቢኔ ፀሀፊ ሆኖ አገልግሏል እና በ2012 ለአጭር ጊዜ የተቃዋሚ መሪ ነበር።
አቤ በቶኪዮ ከአንድ ታዋቂ የፖለቲካ ቤተሰብ የተወለደ ሲሆን የጠቅላይ ሚኒስትር ኖቡሱኬ ኪሺ የልጅ ልጅ ነበር። ከሴይኪ ዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ለአጭር ጊዜ በሳውዝ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ከተከታተሉ በኋላ፣ አቤ በ1993 ምርጫ የተወካዮች ምክር ቤት ሆነው ተመርጠዋል። እ.ኤ.አ. በ2005 አቤ በኮይዙሚ ዋና የካቢኔ ፀሀፊ ሆኖ ተሾመ እና በሚቀጥለው አመት ጠቅላይ ሚኒስትር እና የኤልዲፒ ፕሬዝዳንት አድርጎ ተክቷል። ከጦርነቱ በኋላ የጃፓን ታናሽ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የመጀመሪያው የተወለደው በብሔራዊ አመጋገብ ልዩ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸውን አረጋግጠዋል ። አቤ በ2007 የምክር ቤት ምርጫ ፓርቲያቸው ከተሸነፈ በኋላ ብዙም ሳይቆይ በ በሽታ ምክንያት ከአንድ አመት በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ለቋል። አቤ ከማገገም በኋላ በ2012 የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር ሽገሩ ኢሺባን በማሸነፍ የኤልዲፒ ፕሬዝደንት በመሆን ያልተጠበቀ የፖለቲካ ጉዞ አድርጓል። ከሽገሩ ዮሺዳ እ.ኤ.አ. በ1948 ጀምሮ ን በ2014 እና 2017 ምርጫዎች ለተጨማሪ ድሎች በመምራት የጃፓን ረጅሙ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል። እ.ኤ.አ. በ 2020 አቤ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት የተነሱት የኮሊቲስ በሽታ ያገረሸባቸው ናቸው እና በዮሺሂዴ ሱጋ ተተክተዋል።
አቤ የፖለቲካ ተንታኞች እንደ ቀኝ ክንፍ የጃፓን ብሔርተኛ ሲሉ የገለጹለት ጠንካራ ወግ አጥባቂ ነበር። ከኒፖን ካይጊ ጋር በማያያዝ፣ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የምቾት ሴቶችን በመመልመል የመንግስት ማስገደድ ያለውን ሚና መካድን ጨምሮ፣ በጃፓን ታሪክ ላይ የነጋድያን አመለካከት ያዘ። ይህ አቋም በተለይ ከደቡብ ኮሪያ ጋር ውጥረት ፈጠረ። በእርሳቸው ጠቅላይ ሚኒስትርነት፣ በ2019 አቤ የጃፓን የኮሪያ አገዛዝን የሚመለከቱ ጉዳዮች ቀደም ሲል በ1965 በተደረገው ስምምነት የተፈቱ መሆናቸውን እና ተጨማሪ የካሳ ጥያቄ ደቡብ ኮሪያ ስምምነቱን ጥሳለች ሲል በ2019 በሁለቱ መካከል ያለው ግንኙነት የበለጠ እየሻከረ ሄደ። በዚያው አመት መጀመሪያ ላይ የአቤ መንግስት ከደቡብ ኮሪያ ጋር የንግድ ጦርነት የጀመረው የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በግዴታ ስራ ተጠቃሚ በሆኑ የጃፓን ኩባንያዎች ማካካሻ ሊደረግ ይገባል ብሏል። አቤ የጃፓን ወታደራዊ ፖሊሲዎች በተመለከተም እንደ ጠንካራ ሰው ይቆጠር ነበር። እ.ኤ.አ. በ 2007 የቻይናን ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ልዕለ ኃያል ሆና መምጣቷን ለመቃወም በመጀመሪያ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ዘመናቸው ከሌሎች ሶስት ሀገራት ጋር የኳድሪተራል ሴኩሪቲ ውይይት () አነሳሽ ነበር። የጃፓን የራስ መከላከያ ሃይል (ጃእመሃ) ሀገሪቱን ጦርነት እንዳታወጅ የከለከለውን ሰላማዊ የጃፓን ህገ መንግስት አንቀፅ 9ን በማሻሻል እንዲሻሻል አሳስቧል። እ.ኤ.አ. በ 2015 ወታደራዊ ማሻሻያዎችን አውጥቷል ፣ ይህም ጃፓን የጋራ ደህንነትን እንድትጠቀም እና ጃእመሃ ወደ ባህር ማዶ እንዲሰማራ ያስችለዋል ፣ ይህ ምንባቡ አወዛጋቢ እና ተቃውሞዎችን አጋጥሞታል። በኢኮኖሚ፣ የአቤ ፕሪሚየርነት የጃፓን የኢኮኖሚ ድቀት ለመመከት ባደረገው ሙከራ ይታወቃል፣ በቅፅል ስሙ “አቤኖሚክስ”፣ ውጤቱም የተለያየ ነው። አቤ ዩናይትድ ስቴትስ ከወጣች በኋላ የ ትራንስ-ፓሲፊክ አጋርነት (ትፓአ) ከ ትራንስ-ፓሲፊክ አጋርነት () አጠቃላይ እና ተራማጅ ስምምነት ጋር ወደ ነበረበት እንዲመለስ አድርጓል።
እ.ኤ.አ. ጁላይ 8 2022 አቤ ከጁላይ 10 ምርጫ በፊት በናራ የዘመቻ ንግግር ሲያደርግ በቀድሞ የጃፓን የባህር ኃይል ራስን መከላከል ኃይል መርከበኛ ተገደለ። ተጠርጣሪው አብይን ኢላማ ያደረገው ከውህደት ቤተክርስቲያን ጋር ስላለው ግንኙነት ነው።
|
15318
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%88%E1%88%85%E1%8A%92
|
ወህኒ
|
የወህኒ ተራራ በስሜን ጎንደር የሚገኝ ሲሆን በአጼፋሲለደስ ዘመን ለመጀምሪያ ጊዜ ለተገዳዳሪ የነገስታት ወንድ ዘሮች እንደ እስር ቤት አገልግሏል። ይህም እርስ በርስ ጦርነትን ከወደፊቱ ለማስቆም ነበር።
ፋሲል ልጁ ዳዊት ሲያምጽ ለመጀመሪያ ጊዜ በእስር ወደዚህ ተራራ ልኮታል። የዚህ ስርዓት ምንጭ ቀደምቱ የደብረ ዳሞ እና ግሸን አምባ ዘይቤ ነበር። አጼ ፋሲል ይህን ተራራ ለእስር ቤት ከተጠቀሙበት ጀመሮ እስከ ዘመነ መሳፍንት (በተለይ 1790) ድረስ አምባው በዚህ መልኩ አገልግሏል። በአሁኑ ዘመን የተለያዩ ሰወች ተራራውን ለመውጣት ሞክረው ከአንድ ሰው በስተቀር አልቻሉም ፤ በድሮው ዘመን ግን ቤ/ክርስቲያን እና ቤተ መንግስት በተራራው ላይ ተሰርቶ ነበር። ፍርስራሾቹም አሁን ድረስ በምኩራቡ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ተራሮች
የኢትዮጵያ ታሪክ
|
4002
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%88%80%E1%8A%95%E1%8B%B2%E1%88%B5%E1%8A%90%E1%89%B5
|
መሀንዲስነት
|
ምህንድስና ማለት የሳይንስ እና የሂሳብ መርሆችን በመከተል እንዲሁም የማስተዋል እና የምርምር ችሎታን በመጠቀም በተመጣጣኝ ወጪ ለሰው ልጆች ጥቅም ሊውሉ የሚችሉ ግንባታዎችን መቀየስ፣ ተቋማትን መስራት፣ የመገልገያ ቁሳቁሶችን መፍጠር እና ይተለያዪ የቴክኒክ ችግሮችን መፍትሔ ማግኘትን ያጠቃልላል። ይህንን አይነት ስራ የሚሰራ ሰው 'መሐንዲስ' ተብሎ ይጠራል። የምህንድስና ስራ የተለያዩ ዘርፎች ያሉት ሲሆን በተለምዶ ከሚታወቁት ዘርፎች ውስጥ ሲቭል፣ መካኒካል፣ ኤሌክትሪካል እና ኬሚካል ይጠቀሳሉ። የተክኖሎጂ ማደግ ተከትሎ በአሁኑ ወቅት የምህንድሲና ዘርፎች ሰፋ ያሉ ናቸው። አዲሶቹ የምህንድስና የትኩረት ዘርፎች ሁሉን አቀፍ (መልታይ ዲሲፕለናሪ) እና ውሱን በሆነ የተግባር አቅጣጫ (ስፐሲፊክ አፕልኬሽን) ላይ የተመሰረቱ ናቸው።
ከምህንድስና አይነቶች መካከል፦
ኤሌክትሪክ ምህንድስና
ህንጻ ምህንድስና
ኮምፒዩተር ምህንድስና
ሲቪል ኢንጂነሪንግ
|
37930
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%88%98%E1%89%80%20%E1%8A%A8%E1%89%A0%E1%8B%B0
|
ደመቀ ከበደ
|
ጋዜጠኛና ደራሲ ደመቀ ከበደ ጎጃም-ሞጣ በ1976ዓ.ም ተወለደ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በሞጣ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት፤የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በሞጣ ከፍተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። ለኪነ-ጥበብ ያለውን ልዩ ፍቅር ለማጎልበት በት/ቤት ክበባትና በአራት ዓይና ጎሹ የከያንያን ማህበር ከአባልነት እስከ መሪነት ተሳትፏል።ቤተሰቦቹ እንደአብዛኞቹ ቤተሰቦች ጎበዝ ተማሪነቱን አስተውለው ህክምና ወይም ምህንድስና እንዲያጠና ቢገፋፉትም የቋንቋ አስተማሪዎቹም ሆኑ የሃይስኩል ጓደኞቹ ባሳደሩበት ተፅእኖና በንባብ ፍቅር ባደረበት ስሜት ጋዜጠኝነትን አጥብቆ ወደደ። በተለይ ነጋሽ መሀመድን፣ መዐዛ ብሩን፣ በላይ በቀለንና ታደሰ ሙሉነህን እጅግ መውደዱ ለጋዜጠኝነት ልዩ ፍቅር እንዲያድርበት አድርጓል፤ ለበዓሉ ግርማ ደግሞ ፍቅሩ የትየለሌ ነው፡ እናም ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የሚወደውን ሙያ ለማጥናት ዩኒቨርሲቲ ገባ።
በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በጆርናሊዝምና ኮሙኒኬሽን በማዕረግ ተመርቋል። በዩኒቨርሲቲ ቆይታውም የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት (ጄኔራል አሴምብሊ) ሰብሳቢ፣የባህል ማዕከል የስነ-ዕሁፍ ዘርፍ ተጠሪ፣ የጆርናሊዝምና ኮሙኒኬሽን ክለብ መስራች ስራ አስፈፃሚ፣ የዩኒቨርሲቲው ጋዜጣና መፅሄት አዘጋጅ ሆኖ ከመስራቱም በላይ “የራስ ጥላ “ የተሰኘ መፅሀፍ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ እያለ አሳትሟል፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ባሳየው ከፍተኛ አፈፃፀም የ1999 ዓ.ም ከዓመቱ ምርጥ ተማሪዎች አንዱ በመሆን ከፕሬዝዳንቱ እጅ ሽልማት ተቀብሏል፡፡
ከዩኒቨርሲቲ ከወጣ በኋላም በሪፖርተር ጋዜጣ የባህልና ኪነ- ጥበብ አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል፡፡ በመቀጠልም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት /አዲስ አበባ/ ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ አዘጋጅነት ያገለገለ ሲሆን በ2002 ዓም ከሬድዮ ፋና የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኞች አንዱ በመሆን ከዋና ስራ አስፈፃሚው የገንዘብና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተቀብሏል፡፡
ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የስልጠና ፕሮግራም ማሻሻያ ክፍል ተ/ኃላፊ ሆኖ ሰርቷል፣ አሁን በድርጅቱ የዜና ዋና አዘጋጅ/አስተባባሪ/ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
ደራሲው በ2003 ዓ.ም በኢትዮጵያና በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በምልክት ቋንቋ፣ በብሬል፣ በኦዲዮ ሲዲና በቴክስት በማሳተም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትር ሚኒስትሮች፣ ምሁራን፣ታላላቅ ሰዎችና አርቲስቶች በተገኙበት አስመርቋል። የመፅሃፉን ማስታዎሻነት ለታሪክ ተመራማሪውና ለኢትዮጵያ ጥናት ተቋም መስራች ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት፣ለፊስቱላ ሆስፒታል መስራች ዶ/ር ካትሪን ሀምሊን፣ ለኦርኬስትራ ኢትዮጵያ መሰራችና ማሲንቆ ተጫዋች ሚስተር ቻርለስ ሳተን፣ ለኢትዮፒክስ ተከታታይ ሲዲ አሳታሚ ፍራንሲስ ፋልሴቶና በስማቸው ጎዳና ለተጠራላቸው ሚስተር ካላራቦስ ባምቢስ ሰጥቷል፣ በምረቃው እለት በክብር እንግድነት ከተገኙት ምሁራን አንዱ የነበሩት ፕሮፌሰር አንድሪያስ እሼቴ ደራሲው ያዘጋጀውን የማስታዎሻ ስጦታ ለፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት በክብር ሰጥተውለታል።
ደራሲና ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ ለታዋቂ ዘፋኞች ከሰጣቸው የግጥም ስራዎች በተጨማሪ በርካታ ለህትመት የተዘጋጁ ስራዎችን አዘጋጀቶ የህትመት ብርሃን እንዲያገኙ እየተጠባበቀ ነው።
የከዋክብት ጉማጅ-አጫጭር ታሪኮች
ሌዋታ- ረጅም ልቦለድ
የመጀመሪያዎቹ መጀመሪያ- የታላላቅ ኢትዮጵያውያን ታሪክ
ዘባሲል- ተረት፣ሳይንስ፣ሃይማኖትና ልቦለድ በአንድ ስንስል የተጣመሩበት ረጅም መፅሃፍ እና
አሁን ደግሞ የህፃናትን ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት አደይ አበባ የተሰኘ ተከታታይ የልጆች አዝናኝና አስተማሪ መፅሃፍ አዘጋጅቶ በህትመትና በስርጭት አብረውት የሚሰሩ አካላትን እየጋበዘ ይገኛል።
በ 2020 በኢትዮጵያ ባህርዳር ከተማ በተካሄደ የጣና ሽልማት መድረክ ላይ በኢትዮጵያ ፈጣን ወቅታዊና ሚዛናዊ መረጃ ማድረስ በሚለው ዘርፍ አሸናፊ ሆኖ ተሸልሟል።
|
12200
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B4%E1%88%9E%E1%8A%AD%E1%88%AB%E1%88%B2
|
ዴሞክራሲ
|
ዴሞክራሲ የፖለቲካ ሥርዓት ሲሆን ትርጓሜውም ሕዝባዊ መንግስት ማለት ነው። በሌላ አባባል ዲሞክራሲ ማለት ህዝብ የሚያስተዳድረውን አካል ያለምንም ተፅዕኖ ከመካከሉ መርጦ ሥልጣን የሚሰጥበት ሥርዓት ነው።
ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆነ
ዴሞክራሲ በተጠነሰሰበት ጥንታዊት ግሪክ ፣ ሰዎች ይኖሩ የነበረበት መሠረታዊ የፖለቲካ አሃድ (ዩኒት) ፣ ከተማዊ መንግስት ይባላል። ይህ በአሁን ዘመን ካለው አገር ወይንም ብሔራዊ መንግስት ይለያል። ከተማዊ መንግስታት፣ ለምሳሌ አቴና እንደ ከተማ አስተዳደርነቱ ፣ በቆዳ ስፋት አንስተኛ ስለነበር የዘመኑ ዲሞክራሲ በቀጥተኛ ተሳትፎ (በስብሰባ) ላይ የተመሰረተ ነበር። ነገር ግን ይህ ዓይነት አሰራር ከ፲፯ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ለተነሱት በንፅፅር ግዙፍ ለሆኑት ብሔረ መንግስታት እማይቻል ስለነበር (ማለት ከአገሪቱ ግዙፍ የቆዳ ስፋት አንጻር ሁሉን ዜጋ በየሳምንቱ ለስብሰባ መጥራት ስለማይቻል) በእንግሊዝ አገር ፓርላማ የተባለ አዲስ ሥርዓት ተፈጠረ። ይህም ማለት ሕዝቡ ተወካዮቹን (የፓርላማ ዓባላትን) ይመርጣል፤ ተመራጮችም መንግሥትን ይመሠርታሉ። ይህ ዓይነት ሥርዓት (ቀጥተኛ ያልሆነ ዴሞክራሲ) በመባል ይታዎቃል። በአሁኑ ሰአት አብዛሃኛዎቹ የአለም ሃገራት የሚጠቀሙበት የመንግስት መዋቅር ነው።
ዜግነትና ዴሞክራሲ
አንድ ሥርዓት ዲሞክራሲያዊ፣ በሌላ አነጋገግር ከሕዝብ ወይም በሕዝብ የቆመ ነው ከተባለ፣ ሕዝብ ማለት እዚህ ላይ ምንድን ነው? አብዛኛውን ጊዜ ሕዝብ ማለት ዜጋ ማለትን ሲዎክል፣ እስከ ሃያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ አብዛኞች ዲሞክራሲያዊ ሃገሮች ዜግነትን ትንሽ ለሆነ የህብረተሰብ ክፍል (ሴቶችን፣ ድሆችን፣ ዘሮችን ያገለሉ) ብቻ ያድሉ ነበር። እነዚህ ትንሽ ክፍሎች ብቻ እሚሳተፉበት ዴሞክራሲ በአሁኑ ዘመን ተቀባይነትን ያጣ ነው። ባሁኑ ዘመን፣ ዲሞክራሲ ማለት ብዙኃኑ ኅብረተሰብ መንግሥት የማዋቀር መብት አለው። የጥቂቶች መብት ደግሞ በህግ የተጠበቀ ነው።
ሥርዓተ ሕዝብ፣ ሥርዓተ ልሂቅ፣ ሥርዓተ ጥቂት
ፖለቲካዊ ዜግነት ሕጻናትን እንደማይጨምር አሁን ድረስ አብዛኞች ሃገራት የሚሰሩበት ነው። ይሁንና፣ በዚህ መንገድ አላግባብ ሌሎችም የሕዝብ አካላት እየተገለሉ ሄደው፣ ዴሞክራሲው ወደ ሌላ ዓይነት ሥርዓት ሊቀየር ይችላል። ለምሳሌ በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ የተከበሩ ሰዎች ብቻ እሚሳተፉበት ሥርዓት ሲፈጠር ሥርዓተ ልሂቅ ወይንም አሪስቶክራሲ ይባላል። በሆነ አጋጣሚ ዕድል አግኝተው ጥቂት ቡድኖች ብቻ በማህበረሰቡ ላይ በሚተላለፉ ውሳኔዎች ሲሳተፉ ሥርዓተ ጥቂት ወይንም ኦሊጋርኪ ይባላል። ይህን ሁኔታ ለማዎቅ አንድ አንድ ጊዜ አስቸጋሪ ይሆናል ምክንያቱም ሙሉ በሙሉ ዴሞክራሲያዊ በሆነ ሥርዓት ሳይቀር፣ ጊዜ አግኝተው በፖለቲካው የሚሳተፉ ግለሰቦች ከአጠቃላይ ዜጋ ጥቂት ስለሆኑ። ይሁንና በዲሞክራሲ፣ የመሳተፍ መብቱ ለሁሉም ዜጋ ምንጊዜም ያለ ነው፣ ይጠቀሙበት አይጠቀሙበት።
ዴሞክራሲ ለምን ተፈለገ?
እንደ ፈላስፋው ጆን ስቱዋርት ሚል ሦስት ምክንያቶች ይጠቀሳሉ፦
ሥልታዊ ምክንያት
ሕግ አርቃቂዎች የአንድን ሕብረተሰብ ጥቅም፣ መብት እና አስተሳሰብ በሚያረቁት ሕግ ውስጥ ግምት እንዲያስገቡ ከሌሎች የፖለቲካ ሥር ዓቶች በላይ ዴሞክራሲ ያስገድዳቸዋል። በዚህ ምክንያት ሰዎች በዚህ ሥርዓት ውስጥ የመጎዳታቸው ዕድል አንስተኛ ነው። ተመራማሪ ዓማርትያ ሴን ዋቢ ሲሰጥ «በማናቸው ዲሞክራሲያዊና ሉዓላዊ መንግስታት ከፍተኛ ርሃብ ተከስቶ አያቅም» ይላል።
ሥነ ዕውቀታዊ ምክንያት
ዴሞክራሲ አብዛኛውን ሕዝብ በውሳኔ አስጣጥ ላይ ስለሚያካፍል፣ ከሌሎች የፓለቲካ ሥርዓቶች በበለጠ ሥለ ሕዝቡ ጉዳይ ያዎቀ ሆኖ ይገኛል። በውሳኔ አሰጣጥ የሚካፈለው ሕዝብ መብዛት በሌላ ጎን ትክክለኛ ውሳኔ ላይ ለመድረስ እሚደረገውን ስራ ያግዛል፣ ተሳታፊዎችም ስለ ጉዳዮች የበለጠ የተተቸና የተብራራ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ይረዳል።
የዜጎችን ባሕርይ የማሻሻል ምክንያት
በዴሞክራሲ ሥርዓት ያሉ ሰዎች በውሳኔዎች ላይ ስለሚሳተፉ፤ ከሌሎች ሥርዓት ሰዎች በተለየ እራሳቸውን ችለው እንዲያስቡ፣ በሃሳባቸው ምክንያታዊ እንዲሆኑ እና የሌሎችን መብቶች ግምት ውስጥ እንዲያስገቡ ስለሚገደዱ በሥነ ምግባር እንዲሻሻሉ ይሆናሉ።
ከሚያስከትለው ጥቅም ውጭ ሌሎች ሥነ ምግባራዊ ጥቅሞች ይጠቀሳሉ። ለምሳሌ ሓርነት እና ዕኩልነት፣ እኩልነት፣ የሕግ የበላይነት፣ የመናገር መብት፣ ፍትህ ይጠቀሳሉ
በዴሞክራሲ ላይ የተነሱ ትችቶች
ፕላቶ የሥርዓተ ልሂቃን ዓይነት መንግስት ደጋፊ ስለነበር ዲሞክራሲን ከዚህ አቋሙ ተነስቶ ለመንቀፍ ሞክሯል። በእርሱ አስተሳሰብ በዲሞክራሲ ሥር ዓት ወደ ሥልጣን ላይ መውጣት እሚችሉት የምርጫ ሥር ዓቱን በማጭበርበር ወይንም በብልጥ ንግግር እና ስራ ሰውን በማታለል የተካኑ ሰዎች ይሆናሉ። ምርጫን እሚያሸንፉ ሰዎች ደግሞ የግዴታ መንግስታዊ ኣስተዳደር ላይ ብቁ ሆነው ስለማይገኙ፣ ዴሞክራሲ መንግስትን ለንደዚህ ያለ ግሽበት ይዳርጋል ይላል።
የእንግሊዙ ቶማስ ሆብስ በአንጻሩ የዘውድ ሥርዓትን በመደገፍ፤ የዴሞክራሲ ሥርዓት መንግስት እንዳይረጋጋ እሚያረጉ ተቃውሞዎችን ያበረታታል በማለት ይነቅፋል።
የዴሞክራሲ ተቋሞች
ምርጫ ተቋም
ዴሞክራሲ የመጣው የግሪክ ቃል ከሆኑት «ዴሞስ» ማለት «ህዝብ» እና «ክራቶስ» ማለት «ስልጣን» የመጣ ቃል ነው። በጥንታዊ የግሪክ ከተማ አቴንስ አገዛዝ ይተገበር ነበር።
ዋቢ ጽሑፎች
የፖለቲካ ጥናት
|
46315
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B4%E1%88%8C%E1%8C%8D%E1%88%AB%E1%8D%8D
|
ቴሌግራፍ
|
ቴሌግራፍ የመልእክት ግኑኝነት - የፅሁፍ ህትመት ማተሚያ መሳሪያ ቀደም ብሎ ዋና የመገናኛ መንገድ ነበር፤ ቀጥሎም ቴሌግራፍ ፈጣን ግኑኝነትን ከሩቅ ስፍራ ድረስ አስቻለ፤ የራዲዮ ስርጭት መጀመርም የቴሌግራፍን ዝና ቀነሰው እናም ሽቦ አልባ ቴሌግራፍ ብሎም ስልክ የቀጥታ እንድ ለአንድ ግኑኝነት መቻል ደረጃ ሲደረስ ፤መገናኛ ብዝኋን በቴሌቪዥን መስኮት ዋናው የግኑኝነት መንገድ ሆነ፡፡ በኢንተርኔት ዘመን ቴሌግረፊክ ወይንም የመልእክት ግኑኝነት በሽቦ መስመር ላይ በዘዴው እና በአጠቃቀሙ ጎልብቶ እና ቀሎ እነ ጋዜጣ፤ ራዲዮ፤ ቴሌቪዥን ፤ ስልክንም ጨምሮ በመጠቅለል ላይ ይገኛል።
የቴሌግራፍ ታሪክ
ቴልግራፊ(ከግሪክ «ቴሌ» ማለት ከርቀት፤ «ገራፋይን» ማለት መፃፍ) ሲሆን የረዥም ርቀት የፅሁፍ ወይንም የምልክት መልእክቶች ማስተላለፍን የሚወክል ሲሆን ይህም መልእክቱን የሚሸከም ወይንም የሚያደርስ አካልን አያካትትም፡፡
የኤኬክትሪክ ቴሌግራፍ፤ የኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ የኤሌክትሪክ ሲግናልን በተዘጋጀ የሽቦ መስመር ወይንም በራዲዮ ሞገድ መልክ መላክን ይገልፃል፤ ይህም አዲስ የተገኘውን የኤሌክትሪሲቲ ከስተት ማለትም ኃይሉን ማምረት፤ መቆጣጠር ሲቻል አብረው ያሉትንም እንደ፡ የኬሚካል ለውጦች፤ ብልጫታዎቹን፤ የማይለዋወጡ ቻረጆች የስበት ሀይል፤ የኤሌክትሪክ ንዝረት እና የማግኔቲዝም ጠባዩ ላይ ምርምር እና ክትትል ሲቀጥል ነው፡፡
የቴሌግራፍ አይነቶች እና ዕድገቱ
በጀርመኖቹ ፊዚሺያኖች የኤሌክትሮኬሚካል ቴሌግራፍ ዘዴ የሚጠቀመው በአንድ ወገን ብዙ ሽቦዎች እያንዳንዳቸው ልዩ የሆነ ስም ወይንም ፊደል የሚወክሉ አንድበአንድ በኤሌክትሪክ ቻረጅ ሲደረጉ በሌላኛው በኩል እነዚህ ሽቦዎች ጫፋቸው የኬሚካል እቃ ውስጥ ተነክረው ቻርጅ በተደረገው ሽቦ መስመር ያለው ኬሚካል በሚፈጥረው እንፋሎት መሰል ምልክት ወይንም በብል ትርጉም መስጠትን ይመስላል
ዴቪስ ሪሌይ () በማበል የሚታወቀውም ትንሽ ከረንት ፍሰት ትልቅ የኤሌክትሮማግኔት እንቅስቃሴን በማስነሰቱ ይህም የኤሌክትሪክ ሲገናል ማስተላለፍ ወይንም ቴሌግራፍ፤የኤሌክትሮማግኔትም መታወቅ እናም ጥቅል ሽቦዎችን በማብዛት ኢነሱሌትድ በሆነ ብረት ዙሪያ የመፈጠረውን የማገኔቲክ ኃይል ከፍ በማድረግ
ሳይንቲስቱ ሃንስ ክ. አረስትድ() በ1820 እ.ኤ.አ. የኤሌክትሪክ ዥረት የማግኔቲዝም ኃይል እንደሚፈጥር እና ይህም የደቡባዊ ዋልታ የሚያመለክት አመልካችን እንደሚያንቀሳቅስ፤ ቀጥሎም ጆ. ሽቫይገር() የተባለው ጋልቫኖሜትር ወይንም የኤሌክትሪክ ዝረትን ፍሰት አመልካች መሳሪያ በመፈልሰፉ፤ አ.ማ. አምፐርም() ጋልቫኖሜትሮችን በማሰባሰብ ልከ እንደ ኤሌክትሮኬሚካሎቹ ዎች በእያንዳንዱ ሽቦ ላይ የሚመጣውን የኤሌክትሪክ ፍሰት በማመልከት የቴሌግራፍ ጥቅም እንደሚገኝ አመልክቷል
ሳሙኤል ሞርስ () የሞርስ ኮድም () የሚባለውን ለእያንዳንዱ ፊደሎች የተለየ ድምፅ በመቀጠል በቴሌግራፍ ታዋቂ ነው
የጋውስ () ጋልቫኖሜትርም በዘዴው ተሸሽሎ ኮሚውታቶር በመጠቀም ፤ከቮልታይክ ፒል ወይንም ከባትሪ መሰል ይልቅ የኢንዳክሽን የኤሌክትሪክ ኃይል (ፐልስ) በማድረግ በኮሚውታቶሩ አማካኝነት የዝረት አመልካች ቀስቷን በፖዘቲቭ እና በኔጌቲቭ አቅጣጫ በማንቀሳቀስ በዚሁ ኮድ የተሰጠውን ፊደሎች ማስተላለፍ መቻሉ ሲሆን እነዚህ ፖሰቲቭ እና ኔጋቲቭ መጠኖችም ሊገኙ የቻሉት ጥቅል ሽቦዎችን በማግኔቱ ዙሪያ ወደ ላይ ችና ወደታች በማንቀሳቀስ ነበር፤ በዚህም ሰባት 7 ፊደሎችን በደቂቃ ማስተላለፍ ተችሎ ነበር፤
የቻርልስ ዊትሰቶን() ቴሌግራፍ አመለካች ቀስትን እንደ ሰዐት ቆጣሪ ገበታ ላይ መልእክቱን እንዲያመለክት ማድረግ ነበር ይህም የቴሌግራፍ መልእክቶችንም ከኮዳቸው ወደ ግልፅ ትርጎሜ ለማምጣት የሰለጠኑ ሰዋች ፍላጎት ያስቀረ ነበር እንዲሁም መልእክቱ በሚመጣበት ወቅት ተርጎሚዎች መኖር ነበረባቸው እናም በ1846 አሌክአንደር ባ.() የኬሚካል ቴሌግራፍን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ዥረት ሲግናል የብረት ጠቆሚን በወረቀት ላይ የቀለም ምልክት እንዲያደርግ በማድረግ ከዛም እነዚህን ምልክቶችንም በሌላ ጊዜ መተርጎም ያመለክታል፤ ቀጥሎም የፊደል ገበታ ያላቸው መሳሪያዎች (ኪ-ቦርድ) መልእክት የሚልኩ ቴሌግራፎችን በመጠቀም ፊደሎቹን ሲቀበሉ ወዲያውኑ በሞርስ ኮድ ማተም ተጀመር፤ ሌላውም በሞርስ ኮዶች መሰረት የኤሌክትሪክ ሲግናሉ ሲመጣ በታመቀ አየር በመጠቀም ቀዳዳዎችን በወረቀት ላይ በመብሳት ቀጥሎም መተርጎም ይከተላል ፡፡
የሽባውች የመጠነ አቃቢነት ወይንም ካፓሲታንስ እና ሽቦው በረዘመ ቁጥር የኃይሉ መጠን እንቅፋት ወይንም ረዚስታንስ እየጨመረ በመሄዱ የሚገኘውን የመልእክት ፍጥነት ላይ ተፅእኖ አስድሯል
ለዚህም ሲፎን መቀበያ"" የሚባ መሳሪያ በ…… የሚሰራ ፍጥነቱን ወደ 20 ፊደሎች በደቂቃ አድርሷታል
ኦሊቨር ሄቪሳይድም () የማስተላለፊያ መስመሩን የሲግናል መዛባት ለማጥፋት በሽቦው ላይ የዥረት አቃቢነት ወይንም ኢንደክታንስ ቢጨመርበት የሚለውን ሀሳብ አፈለቀ እነደዚሁም ይህ ኢንሱሌትድ ሽቦ የኤሌክትሮማግኔት ፀባዩን ከፍ በማድረግ ረዚስታንሱ የሚያመጣውን ጉድለት ቀንሶታል፤ ይህ ኢነሱሌተር ወይንም ኤልክትሪክ የማያስተላለፍ ፕላስቲክ መሰል ከኢሴያ ከ/አለም ከሚገኝ ዛፍ ጉታ ፐርቻ () እነደሚገኝ ታውቆ በስኮትላንድ ሀኪም ታውቆ ነበር እናም ይህ በእነ ፋራዳይ ለኤሌክትሪክ ኢነሱሌተርነት እንዲውል አደረጉት
ሌላው የቴሌግራፍ ተግዳሮት የነበረው የመላኪያ ፍጥነቱን መጨመር ነበር(ፊደሎች/በደቂቃ) ይህም በሰው የሚሰር እጅ ስራን ማስቀረት ይጨምራል፤ ለዚህም የድምፅ ሰራተኞችን በመዝግቦ በመተንተን… ሞርስ ኦፐሬተር የተበላው መሳሪያ ዶት እና ዳሽ ኮዶችን በመለየት በሚጠቀመው ዘዴ………
የቶማስ ኤዲሰንም መልቲፕሌክ ቴሌግፍ ፣ ሢግናሎችን በጊዜ በፍጥነት በመከፋፈል የሚገኘውን እስከ ቤል ቴሌፎን ዕያለ መሻሻል አሳይቷል
የአጠቃቀሙ ዕድገቱ
ጋውስ በ1835 በጀርመን የባቡር መስመር ጣቢያ የቴሌግራፍ መስመር ለትግበራ ውሎ ነበር
በ1840 ሞርስ የኤሌክትሪክ ቴሌግራፉን ለዕይታ ባቀረበበት ወቅት የታላከው መልእክት ፈጣሪ በመጀመሪያ ምን አለ “?” የሚል ትርጎሜ ይመስላል፤ እናም ለአሜሪካው ምክርቤት በፃፈው ማስታወሻ ሞርስ እንዲህ ብሎ ነበር - ይህን መሰሉ የፈጣን ግኑኝነት መሳሬያ ትልቅ ወጤት ያለው ስለሚሆን ስለዚህም ልክ እንደ አያያዛችን ለጥሩም ለመጥፎም ሊውል ይችላል"
ኮክ እና ዊትስቶን የኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ ካምፓኒ() መስርተው በ13ኪሜ ርዝመት ያለው ለንግድ ያዋለውን የቴሌግፍ መስመር በግሬት ዌስተርን ሬይልዌይ () አካባቢ ዘረጉ ይህም ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር
በ1850ወቹ በእንግሊዝ እና በ ፈረንሳይ መካከል የቴሌግራፍ መስመር ሲዘረጋ በመጀመሪያ ባይሳካም በሁለተኛ ሙከራ ግኑኘነት ማድረግ ተችሎል ቀጥሎም በ1860ዎቹ አትላንቲክ ውቂያኖስን ያቆረጠ የትሌግራፍ መስመር መዘርጋት ተችሎ በአሁጉራት መካከል ያለውን የጊዜ እና የቦታ ርቀት ከበደትን ያሳጣው ሆኗል፤ ዌስተርን ዩኒየን የመሳሰሉ ድርጅቶች ዋና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ነበሩ፤ እነደዚህም እያለ በፓሲፊክ ላይ የቴሌግራፍ ግኑኝነት በ 1902 ሲጠናቀቅ የቢሪቲሽ የባህር ውስጥ መስመር ዝርጋታ አብዛኛውን የወከለ ነበር፤ የዌስተርን ዩኒየን የቴሌግራፍ ግልጋሎት እስከ 2006 ድረስ ሲሰራ የነበረ ሲሆን የህንድም ተልግራፍ አገልግሎት እስከ 2013 ድረስ ጥቅም ላይ ውሎ ነበር፡፡
ኮክ እና ዊትስቶን የኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ ካምፓኒ() መስርተው በ13ኪሜ ርዝመት ያለው ለንግድ ያዋለውን የቴሌግፍ መስመር በግሬት ዌስተርን ሬይልዌይ () አካባቢ ዘረጉ ይህም ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር ↵↵-➞በ1850ወቹ በእንግሊዝ እና በ ፈረንሳይ መካከል የቴሌግራፍ መስመር ሲዘረጋ በመጀመሪያ ባይሳካም በሁለተኛ ሙከራ ግኑኘነት ማድረግ ተችሎል ቀጥሎም በ1860ዎቹ አትላንቲክ ውቂያኖስን ያቆረጠ የትሌግራፍ መስመር መዘርጋት ተችሎ በአሁጉራት መካከል ያለውን የጊዜ እና የቦታ ርቀት ከበደትን ያሳጣው ሆኗል፤ ዌስተርን ዩኒየን የመሳሰሉ ድርጅቶች ዋና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ነበሩ፤ እነደዚህም እያለ በፓሲፊክ ላይ የቴሌግራፍ ግኑኝነት በ 1902 ሲጠናቀቅ የቢሪቲሽ የባህር ውስጥ መስመር ዝርጋታ አብዛኛውን የወከለ ነበር፤ የዌስተርን ዩኒየን የቴሌግራፍ ግልጋሎት እስከ 2006 ድረስ ሲሰራ የነበረ ሲሆን የህንድም ተልግራፍ አገልግሎት እስከ 2013 ድረስ ጥቅም ላይ ውሎ ነበር፡፡
|
18615
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8C%8B
|
አጋ
|
አጋ (ወይም አካ) በሱመራዊ ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ በሱመር የኪሽ ከተማ ንጉሥ ነበረ።
አጋ በጊልጋመሽ ትውፊት ደግሞ ይጠቀሳል፤ የጊልጋመሽ ከተማ ኡሩክን እንደ ከበበ፣ ጊልጋመሽም እንዳሸነፈው ይላል።ከሦስተኛም ምንጭ የቱማል ጽሑፍ፣ ጊልጋመሽ ኒፑርን ከአጋ እንደ ያዘ መገመት ይቻላል።
የሱመራዊ ነገሥታት ዝርዝር፣ የጊልጋመሽ ትውፊት እና የቱማል ጽሑፍ ሁላቸው አጋ የኤንመባራገሲ ልጅና ተከታይ እንደ ነበር በማለት ይስማማሉ። ይህ ኤንመባራገሲ የኪሽ ንጉሥ ሲሆን ከሥነ ቅርስ በእውኑ እንደ ነገሠ ታውቋል። ስለዚህ አጋ እና ጊልጋመሽ እራሳቸው ታሪካዊ ነገሥታት እንደ ነበሩ ይታስባል። በአጭር አቆጣጠር ምናልባት 2370 ዓክልበ. ግድም ነገሠ። የሱመር ነገሥታት ዝርዝር ግን ለመጀመርያው ዘመን ብዙ ጊዜ የማይመስል ቁጥር አቅርቦ እንደ ሆነ፣ አጋ በኪሽ ለ625 ዓመታት እንደ ነገሠ ይላል።
የውጭ መያያዣ
የሱመር ነገሥታት
|
52406
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%8A%90%E1%89%B5%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A9
|
ትምነት ገብሩ
|
ትምነት ገብሩ: የተወለደችው1983/1984- ትምነት ገብሩ ኢትዮ-እሪትሪያዊ ኮምፕዊተር ሳይንቲስትና (በአልጎሪዝም አድልዎ እና በመረጃ ማዕድን ) ላይ የምትሰራ አሜሪካዊ የኮምፒውተር ሳይንቲስት ነች. ትምነት ለቴክኖሎጂ ልዩነት ተሟጋች እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ () ውስጥ የሚሰሩ ጥቁር ተመራማሪዎች ማህበረሰብ የሆነው የ , ተባባሪ መስራች ስትሆን ቴክኖሎጂን የመጠቀም ውጤቶቹን ለመፈተሽ በአለም ዙሪያ ካሉ ተመራማሪዎች ጋር በአፍሪካ እና በአፍሪካ ኢሚግሬሽን ላይ በማተኮር የሚሰራው የተከፋፈለ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ምርምር ኢንስቲትዩት () መስራች ነች። እ.ኤ.አ. በ2021 ትምነት ገብሩ በፎርቹን ከአለም 50 ታላላቅ መሪዎች አንዱዋ በመሆን ተሸልማለች።<
እ.ኤ.አ. በታህሳስ 2020 ገብሩ የስነምግባር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቡድን ቴክኒካል መሪ በመሆን ከጎግል ድንገተኛ ስራ መልቀቅ የተነሳ የህዝብ ውዝግብ ማዕከል ነበረች። የትላልቅ የቋንቋ ሞዴሎች ብዙ ስጋቶችን እና አድሎአዊ ጉዳዮችን የሚዘረዝር ወይም ሁሉንም የጎግል ደራሲያን ስም የሚያስወግድ ገና ያልታተመ ወረቀት እንድታወጣ ጋዜጣው ጠይቃ፣ ይህም ወረቀት በእነዚያ ስርዓቶች ውስጥ ያለውን አድሏዊነት የሚቀንስባቸውን የቅርብ ጊዜ ጥናቶችን ችላ ብላለች። በውሳኔው ላይ ግንዛቤን ጠየቃ፣ እና አለመታዘዝ የስራ መልቀቂያዋን ለመደራደር እንደሚያደርጋት አስጠንቅቃለች። ጎግል የስራ መልቀቂያዋን እንደተቀበለ በመግለጽ ስራዋን ወዲያውኑ አቋረጠ።
የመጀመሪያ ህይወት እና ትምህርት
ትምነት ገብሩ ተወዳ ያደገችው አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ነው። አባቷ በአምስት ዓመቷ ሞተ እና እናቷ አሳድጋለች። ሁለቱም ወላጆቿ ኤርትራ ናቸው። በመጨረሻ በዩናይትድ ስቴትስ የፖለቲካ ጥገኝነት አግኝታለች፣ ይህ ሁኔታ “አሳዛኝ ነው” ብላለች። ገብሩ በማሳቹሴትስ መኖር የጀመረችው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ለመከታተል ሲሆን ወዲያው በዘር ላይ የተመሰረተ መድልዎ መፈጸም እንደጀመረች ትናገራለች፣ አንዳንድ መምህራን ከፍተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ብትሆንም የተወሰኑ የከፍተኛ ምደባ ኮርሶችን እንድትወስድ አልፈቀዱላትም።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ ገብሩ ከፖሊስ ጋር ያጋጠማት አጋጣሚ በቴክኖሎጂ ስነ-ምግባር ላይ እንድታተኩር አድርጓታል። አንዲት ጥቁር ሴት ጓደኛዋ በቡና ቤት ውስጥ ጥቃት ተፈጽሞባታል፣ ገብሩ ፖሊስ ደውሎ ሪፖርት አድርጓል። ጓደኛዋ የጥቃቱን ዘገባ ከማስገባት ይልቅ ተይዞ ወደ ክፍል እንዲገባ መደረጉን ትናገራለች። ገብሩ ወቅቱን ወሳኝ ወቅት እና "የስርዓት ዘረኝነት ግልፅ ምሳሌ" ብሎታል።
በ2001 ገብሩ በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪዋን እና የሳይንስ ማስተር ዲግሪዋን በኤሌክትሪካል ምህንድስና፣ በ2017 የዶክትሬት ዲግሪዋን አግኝታለች።
ገብሩ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በ 2017 ውድድር ላይ ያቀረበች ሲሆን የኮምፒውተር ራዕይ ሳይንቲስቶች ስራቸውን ለኢንዱስትሪ እና ቬንቸር ካፒታሊስቶች አባላት ባቀረቡበት ወቅት ነው። ከሌሎች ስራ ፈጣሪዎችና ባለሀብቶች ጋር ተከታታይ ትብብር በማድረግ ውድድሩን አቶ ገብሩ አሸንፈዋል።
በ2016 በፒኤችዲ ፕሮግራሟ እና በ2018 ገብሩ በጀላኒ ኔልሰን የፕሮግራም ዘመቻ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች።
ገብሩ የዶክትሬት ዲግሪዋን እየሰራች እያለች ስለ የወደፊት ስጋት አሳትሞ የማያውቅ ወረቀት አዘጋጅታለች። በሜዳው ውስጥ የልዩነት እጦት አደጋዎችን ስትጽፍ ከፖሊስ ጋር ባላት ልምድ፣ የስነ ሕዝብ አወቃቀር እና በፕሮፐብሊካ የትንበያ ፖሊስ ምርመራ ላይ በማተኮር በማሽን መማሪያ ውስጥ የሰዎች አድሎአዊነት ትንበያ አሳይቷል። በወረቀቱ ላይ የሰከሩ ወንድ ተሰብሳቢዎች ወሲባዊ ትንኮሳ በሚያደርሱባቸው የኮንፈረንስ ስብሰባዎች ላይ ያጋጠሟትን ልምዷን በማሰላሰል "የወንድ ክለብ ባህል" የሚለውን አጣጥላለች።
ሙያ እና ምርምር
ገብሩ አፕልን የተቀላቀለው በ2004 በሃርድዌር ዲቪዚዮን ለድምጽ ክፍሎች ሰርክሪት በመስራት ሲሆን በሚቀጥለው አመት የሙሉ ጊዜ የስራ እድል ተሰጠው። ኦዲዮ መሐንዲስ ሆና ከሰራችው ስራ ስራ አስኪያጇ ዋየርድ "አትፍራ" እና በባልደረቦቿ በጣም የተወደደች መሆኗን ተናግራለች። ገብሩ በአፕል ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የሰውን ምስል መለየት የሚችል ሶፍትዌር ማለትም የኮምፒዩተር እይታን የመገንባት ፍላጎት አሳየች። ለመጀመሪያው አይፓድ የምልክት ማቀናበሪያ ስልተ ቀመሮችን ማዘጋጀቷን ቀጥላለች። በወቅቱ "በቴክኒካል አጓጊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ" ስትል ለክትትል ያለውን ጥቅም ግምት ውስጥ እንደማትገባ ተናግራለች።
ኩባንያውን ከለቀቀች ከረጅም ጊዜ በኋላ በ2021 የበጋው የ# እንቅስቃሴ በአፕል ሰራተኞች፣ ከገብሩ ጋር ያማከረችው ቼር ስካርሌትን ጨምሮ፣ ገብሩ “በጣም ብዙ አስጸያፊ ነገሮች” እንዳጋጠሟት እና “እንዴት እንደሚያስተዳድሩ ሁልጊዜ ትጠይቅ ነበር። [መ] ከትኩረት ብርሃን ለመውጣት" እሷ በአፕል ላይ ያለው ተጠያቂነት ረጅም ጊዜ ያለፈበት መሆኑን ገልጻ፣ በራዳር ስር መብረርን መቀጠል እንደማይችሉ አስጠንቅቃለች። አቶ ገብሩ ሚዲያው አፕልን እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን የሚዘግቡበትን መንገድ ተችተው፣ ፕሬስ ድርጅቶቹን ከህዝብ እይታ ለመጠበቅ ይረዳል ሲሉ ተችተዋል።
እ.ኤ.አ. በ2013 ገብሩ በስታንፎርድ የሚገኘውን የፌይ-ፌይ ሊ ቤተ ሙከራን ተቀላቀለ። በይፋ የሚገኙ ምስሎችን መረጃ ማውጣት ተጠቀመች። ስለ ማህበረሰቦች መረጃ ለመሰብሰብ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚያወጡትን የገንዘብ መጠን ለማወቅ ፍላጎት ነበራት። አማራጮችን ለመመርመር፣ ገብሩ ጥልቅ ትምህርትን ከጎግል ጎዳና እይታ ጋር በማጣመር የዩናይትድ ስቴትስ ሰፈሮችን ስነ-ሕዝብ ለመገመት፣ ይህም የሚያሳየው ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ባህሪያት እንደ የድምጽ አሰጣጥ ዘይቤ፣ ገቢ፣ ዘር እና ትምህርት ከመኪናዎች ምልከታ ሊወሰድ ይችላል። የፒክ አፕ መኪናዎች ቁጥር ከሴዳኖች ቁጥር ከበለጠ ህብረተሰቡ ለሪፐብሊካን ፓርቲ የመምረጥ ዕድሉ ሰፊ ነው። ከ15 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በብዛት ከሚኖሩባቸው 200 የአሜሪካ ከተሞች የተውጣጡ ምስሎችን ተንትነዋል። በቢቢሲ ኒውስ፣ ኒውስዊክ፣ ዘ ኢኮኖሚስት እና ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ተገኝተው ስራው በመገናኛ ብዙሃን በሰፊው ተዘግቧል።
እ.ኤ.አ. በ 2015 ገብሩ በሞንትሪያል ፣ ካናዳ በሜዳው ከፍተኛ ኮንፈረንስ የነርቭ መረጃ ማቀነባበሪያ ሲስተምስ () ተካፍሏል። ከ3,700 ተሳታፊዎች መካከል ጥቂቶች ጥቁር ተመራማሪዎች መካከል አንዷ እንደነበረች ገልጻለች። በሚቀጥለው ዓመት እንደገና ስትገኝ፣ ቆጠራን ያዘች፣ እና ጥቁር ወንዶች አምስት ብቻ እንደነበሩ እና ከ8,500 ተወካዮች መካከል ብቸኛዋ ጥቁር ሴት እንደነበረች ገልጻለች። ገብሩ ከባልደረባዋ ዶ/ር ረዲኤት አበበ ጋር በመሆን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚሰሩ የጥቁር ተመራማሪዎች ማህበረሰብን ብላክ ኢን አይ ኤስን መስርተዋል።
እ.ኤ.አ. በ2017 ክረምት ላይ ገብሩ ማይክሮሶፍትን በፍትሃዊነት ፣ ተጠያቂነት ፣ ግልፅነት እና ስነምግባር በ ) ቤተ ሙከራ የድህረ ዶክትሬት ተመራማሪ በመሆን ተቀላቀለ። እ.ኤ.አ. በ 2017 ገብሩ በፍትሃዊነት እና ግልፅነት ኮንፈረንስ ላይ ተናግሯል ፣ ቴክኖሎጂ ሪቪው በ ስርዓቶች ውስጥ ስላሉ አድልዎዎች እና በ ቡድኖች ውስጥ ልዩነቶችን መጨመር ችግሩን እንዴት እንደሚያስተካክለው ቃለ መጠይቅ አድርጎላቸዋል። ስኖው ከጃኪ ስኖው ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ "የብዝሃነት እጦት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና በተለይም የኮምፒዩተር እይታን የሚያዛባው እንዴት ነው?" እና አቶ ገብሩ በሶፍትዌር ገንቢዎች ውስጥ ያሉ አድልዎዎች እንዳሉ ጠቁመዋል። ገብሩ በማይክሮሶፍት በነበረበት ጊዜ የስርዓተ-ፆታ ሼዶች የተሰኘ ጥናታዊ ጽሁፍ አዘጋጅቷል፣ይህም በጋራ ደራሲ ዶ/ር ጆይ ቡኦላምዊኒ የሚመራውን ሰፊ የማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ተቋም ፕሮጀክት መጠሪያ ሆነ። ጥንዶቹ የፊት ለይቶ ማወቂያ ሶፍትዌርን መርምረዋል; ጥቁር ሴቶች ከነጭ ወንዶች በ 35% ያነሰ የመታወቅ እድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን ማወቁ.
ገብሩ ጎግልን የተቀላቀለችው እ.ኤ.አ. የቴክኖሎጂን ማህበራዊ ጠቀሜታ ለማሻሻል ያለውን አቅም ለማሻሻል በመፈለግ የሰው ሰራሽ የማሰብ ችሎታን አንድምታ አጥንታለች።
እ.ኤ.አ. በ2019 ገብሩ እና ሌሎች የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ተመራማሪዎች አማዞን የፊት መለያ ቴክኖሎጅን ለህግ አስከባሪ ኤጀንሲዎች መሸጥ እንዲያቆም የሚጠይቅ ደብዳቤ ተፈራርመዋል ፣ምክንያቱም ለሴቶች እና ለቀለም ሰዎች ያደላ ነው ። የአማዞን የፊት ለይቶ ማወቂያ ስርዓት ከማንኛውም የቴክኖሎጂ ኩባንያ የፊት ለይቶ ማወቂያ ሶፍትዌር የበለጠ ጠቆር ያለ ቆዳ ያላቸው ሴቶችን በመለየት ላይ ችግር ነበረበት። በኒውዮርክ ታይምስ ቃለ ምልልስ ላይ ገብሩ ፊትን ለይቶ ማወቅ በአሁኑ ጊዜ ለህግ ማስፈጸሚያ እና ለደህንነት ሲባል ጥቅም ላይ መዋል የማይችል አደገኛ መሆኑን እንደምታምን ተናግራለች።
ሽልማቶች እና እውቅና
ገብሩ፣ ቡኦላምዊኒ እና ኢኒዮሉዋ ዲቦራ ራጂ የፊት ለይቶ ማወቂያ ላይ ያለውን የአልጎሪዝም አድልዎ ችግር በማጉላት በ ምድብ የ ፈጠራዎች ሽልማት አሸንፈዋል። እ.ኤ.አ. በ 2021 በፎርቹን ከአለም 50 ታላላቅ መሪዎች መካከል ገብሩ ተካቷል ። ገብሩ እ.ኤ.አ.
|
52308
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%8B%88%E1%8B%AD%E1%8A%95
|
የኢትዮጵያ ወይን
|
በኢትዮጵያ የወይን ምርትን አጀማመር ወደኋላ ስናየው በመጀመሪያው ሺህ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ነው። የታሪክ ጸሃፊው ምሁሩ ሪቻርድ ፓንክረስት የአክሱማውያን ወይን ጠጅ ቀደምት ማጣቀሻዎች በ 4 ኛው ክፍለ ዘመን ገዥ ኢዛና ካቆሙት የድንጋይ ሃውልት ውስጥ በአንዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል ። የ አክሱማውያንን የ ወይን ማልማት ጥበብ በአክሱም በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የቆመው ታላቁ የአክሱም ሀውልት መሰረት ላይ የተቀረጹ ምስሎችም ይመሰክራሉ። ባህላዊው የማር ወይን ጠጅ ከጥንት ጀምሮ በሰፊው ተወዳጅነት ያገኘ ነበር።
የአሁኑ የወይን ማልማት ጥበብ በኢትዮጵያ የተጀመረው በ1956 በአዋሽ ወይን ፋብሪካ በስራ ፈጣሪዎቹ ሙሉጌታ ተስፋኪሮስ እና ራስ መስፍን ስለሺ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2014 የአዋሽ ወይን ፋብሪካ 10 ሚሊዮን ጠርሙሶች አመታዊ ምርት ነበረው አብዛኛዎቹ ደሞ በአገር ውስጥ ነበር የተሸጡት። እ.ኤ.አ. በ 2014 የፈረንሳይ መጠጥ ኮርፖሬሽን ካስቴል በኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ ዝዋይ አቅራቢያ ባለው 120 ሄክታር መሬት ላይ በርካታ የወይን ዝርያዎች ማምረት ጀመረ። እ.ኤ.አ. በ 2013 አመታዊ ምርቱ 3 ሚሊዮን ጠርሙሶች ነበር ከእነዚህም ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት በዋናነት ወደ ቻይና ተልከዋል።
በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ያለው የአየር ንብረት እና የመሬት አቀማመጥ ሁኔታዎች ለወይን ማልማት ተስማሚ ያደርጉታል። አመታዊ የዝናብ መጠን 650 ሚሜ አካባቢ ፣ የሙቀት መጠኑ በአማካይ 25 ዲግሪ ሴልሺየስ በዓመት እና ክልሉ በአሸዋማ አፈር የተሞላ ነው ይህ ደሞ ለወይን ምርት በጣም ተስማሚ ሁኔታዎች ናቸው። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከምድር ወገብ ጋር ባላት ቅርበት ምክንያት በአመት ሁለት ምርት መሰብሰብ ይቻላል። የኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች ምዕራባዊ ተዳፋት የሜዲትራኒያን የአየር ንብረት ስላላቸው ለወይን ማብቀል በጣም ምቹ ናቸው።
|
11258
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%88%E1%8B%B0%E1%88%A8
|
ገደረ
|
ገደረ ወይም ገደራት በግምት ከ3ኛው ክፍለ ዘመን በፊት በአክሱም የነገሰ የኢትዮጵያ ንጉሥ ነበር። የንጉሥ ገደረ ሠራዊት በደቡብ አረብ ስለመዝመቱ የሚናገሩ መረጃዎች ተገኝተዋል። ሆኖም የመንን በቁጥጥሩ ሥር አድርጎ መግዛቱን ለማረጋገጥ አያስችሉም። በሳባ ቋንቋ ተጽፎ በየመን የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ንጉስ ገደረ (ገደራት) ከሂምያር ቤተሰቦች ተቀናቃኝ ከሆነው ሓምዳ አኒድ ባላባት አል-ሃን፣ ናህፋን እና ከልጆቹ ሳይ-ሩውም፣ አውታር፣ እና ያሪም አይመን ጋር ወግኖ እንደነበርና ሆኖም ቆይቶ ወገንተኝነቱን ቀይሮ ከሂምያሮች ጎን እንደተሰለፈ ያመለክታል። የንጉስ ገደረ ዘመቻዎች ውጤቶች ባይታወቁም፡ ከሌላ ጽሑፍ በተገኘው መረጃ መሰረት፤ ናህፋን ወደ ሃበሻት (ሃበሻ) ሠራዊቱን እንዳዘመተና ከገደራት ጋር ባደረገው ውጊያ እንደቀናው መረጃው ይጠቁማል። በዚሁ ተመሳሳይ መረጃ መሰረት፡ የንጉሥ ገደረ ልጅ ባይጃ (በይጋ) በደቡብ አረብ ናይድና ዛፋር በተባሉ ቀጠናዎች ጦርነት ውስጥ እንደተሰለፈና ተሸንፎ ወደ ባሕር ጠረፍ ክልሎቹ እንዳፈገፈገ ያወሳል። የአክሱም ኃይላት ግን ዋዲ ሱርዱድ እና ዋዲ ሣሃም በተባሉት የስሜን የመን የባሕር ማዶ ቀጠናዎች እንቅስቃሴያቸውን ቀጥለው በጉራቲድ ነገስታት ኢልሳራህ ያህዱብ እና ያዚል ባይዪን በኃይል ተገፍተው እስኪለቁ ድረስ በአካባቢው ቆይተዋል። ንጉስ ገደረ በእርግጥ ደቡብ አረብን መግዛቱን የምያረጋግጥ ማረጋገጫ እስካሁን ባይገኝም የአክሱም ሠራዊት በደቡብ የመን ያደረገው ዘምቻና ቆይታ በወቅቱ በኢትዮጵያና በደቡብ አረብ ግዛቶችና ነገስታት መካከል ጠንካራ ግንኙነት እንደነበር ይረጋግጣሉ።
ዓዲ ገለሞ በተባለ በደቡብ ኤርትራ ከሚገኝ ስፍራ በቁፋሮ የተገኘው ከመዳብ በተሰራ ዘንግ ላይ የተገኘው የግዕዝ ጽሑፍ ላይ ገደረ፣ ነጋሲ አክሱም መሆኑን የሚናገር መልዕክት ይዟል። ይህ ንጉስ ገደረ ደቡብ አረብ ከዘመተው ገደረ (ገደራ) ጋር አንድ ስለመሆኑ እስካሁን ማረጋገጫ የለም። በ330 ዓመተ ዓለም አካባቢ በአካባቢው አግዱር የተባለ ንጉሥ ነግሶ እንደነበር ለምሳሌነት ማስቀመጥ ይገባል።
የኢትዮጵያ ባዮግራፊ መዝገበ ቃላት፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ኢትዮጵያ።
የኢትዮጵያ ነገሥታት
|
10091
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A8%E1%8A%A4%E1%89%BD%C2%B7%E1%8A%A0%E1%8B%AD%C2%B7%E1%89%AA%20%E1%89%AB%E1%8B%AD%E1%88%A8%E1%88%B5%20%E1%8C%8B%E1%88%AD%20%E1%89%B0%E1%88%B5%E1%88%9B%E1%88%9D%E1%89%B6%20%E1%88%88%E1%88%98%E1%8A%96%E1%88%AD
|
ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር ተስማምቶ ለመኖር
|
ከኤች·አይ·ቪ ጋር መኖር
ከኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ጋር መኖር ማለት ቫይረሱ በደሙ ውስጥ እንዳለ የተረዳ ሰው ራሱን አረጋግቶና ችግሩን እንደማንኛዉም የጤና ችግር በማየት ቫይረሱ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነሰ እና ለመከላከል በሕክምና፣ በአመጋገብ፣ እንዲሁም በባህርይ ላይ አስፈላጊ የሆኑ ለውጦችን በማምጣት ጥሩ ሕይወት መኖር ማለት ነው። አንድ ሰው ኤች·አይ·ቪ አለበት ማለት አሁኑኑ ታሞ ይተኛል ወይም በቅርቡ ሕይወቱ ያልፋል ማለት አለመሆኑን ማወቅ ተገቢ ነው። ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች የእድሜ ማራዘሚያ መድሀኒቶችን (ፀረ-ኤችአይቪ መዳኒቶች) በመጠቀም ለረጅም ዓመታት ጤናማ ሆነው ለመኖር ይችላሉ። አንዳንድ ሰዎች የበሽታዉ ምልክት ጨርሶ ሳይታይባቸው ከ15 ዓመት በላይ ከቫይረሱ ጋር መኖር እንደሚችሉ አንዳንድ ጥናቶችም ያመለክታሉ። ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ በደም ውስጥ በመኖሩ ምክንያት ሊሰማ የሚችለዉን ስሜት አውነታውን መቀበል መቻል በጣም አስፈላጊ ነው። ጥሩ ያልሆኑትን ስሜቶች ለማስወገድ የሚከተሉትን ምክሮች መቀበልና መተግበርም ተገቢ ነው።
ሁኔታዎች እያደር የተሻሉ እንደሚሆኑ ተስፋ ማድረግ፦ ፈታኝ የሆነ ሰሜት ሲሰማ ሁኔታዎች ሁሉ ከጊዜ ጋር እየተሻሻሉ እንደሚሄዱ ማመን በጣም ጠቃሚ ነው። የተሻለ ሁኔታ እንደሚኖር ተስፋ የሚሰጡ ብዙ መንገዶች አሉ። ለምሳሌ የራስን ጤንነት መጠበቅና የቀድሞውን የተረጋጋ ህይወት እንደገና መጀመር አንዱ መንገድ ነው።
ከኤች·አይ·ቪ ጋር ከሚኖሩ ሰዎች ጋር መመካከር፦ ማንኛውንም የሚሰማን ስሜት ወይም የህመም ምልክት፤ ሌሎችም ምናልባት ተመሳሳይ ስሜት እና ምልክት ሊኖራቸው ስለሚችል ከቫይረሱ ጋር ከሚኖሩ ሰዎች ጋር መመካከር ወይንም ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ወደመሠረቷቸው ማህበራት በመሄድ የምክር እርዳታ ማግኘት አስፈላጊ ነው።
ሁሌም የሚያስደስቱን ነገሮች ከማድረግ አለመቆጠብ፦ አንድ ሰው ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደሙ ውስጥ መኖሩን ካወቀ በኋላ የደረሰበትን ድንጋጤ ለማስወገድ ቀደም ሲል ያደርጋቸው የነበሩትን አስደሳች ስራዎችን በመቀጠል አሁን የተፈጠሩበትን የኀዘንና የብስጭት ሰሜቶችን መርሳት መቻል ይገባዋል። ዘወትር ሲያደርገው ያስደስቱት የነበሩትን ሥራዎች በቀጣይነት ማድረግ ኀዘን ወይም ጭንቀት ላይ ብቻ እንዳያተኩር ይረዳል።
አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ፦ ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰው ድካም ሊሰማዉና ሊጫጫነው ይችላል። በዚህ ጊዜ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ብርታትና ጥንካሬ ይሰጣል። ከፍተኛ የሰውነት እንቅስቃሴ ባይሆንም እንኳን ቀላል እርምጃዎችን ማዘውተር ለአእምሮና ለሰውነት ጤንነት በጣም አስፈላጊ ነው።
ጎጂ የሆኑ ቅፅበታዊ ለውጦችን በህይወት ላይ አለማድረግ፦ ሥራን አለመተው፣ ዘመድ ወዳጆችን አለመራቅ፣ ንብረቶችን አለመሸጥ። በእርግጥ አንድ ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖር ሰው የወደፊት እቅዱን ሊለውጥ ይችላል፤ ይህ ለውጥ ጫና ያልበዛበትና ውጤቱም ጠቃሚ መሆኑን አስቀድሞ መለየት ያስፈልጋል።
ባለሞያን ማማከር፦ ስለ ኤች·አይ·ቪ/ኤድስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመኖሪያ አካባቢያችን እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ማህበራትን ወይም ድርጅቶችን ማወቅ ጠቃሚ ነው። አንድ ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰዉ የጭንቀት እና የመከፋት ስሜት ካለቀቀው የህክምና ባለሞያዎች ወይንም አማካሪዎችን በስልክም ሆነ በአካል ማግኘትና ማማከር ያስፈልገዋል።
ያስታውሱ! ብቻዎን አይደሉም ፦ኢትዮጵያ ውስጥ ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ከአንድ ሚሊዮን ተኩል በላይ ሰዎች አሉ። በአሁኑ ጊዜ 12 በመቶ ገደማ የሚሆኑ ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ይኖራሉ። በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ዕድሜያቸው በ15 እና በ49 መካከል የሚገኙ ከ4 ከመቶ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ። አንድ ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ በደሙ ውስጥ ያለበት ሰው በቫይረሱ ለመያዝ ሆን ብሎ የሰራው ስህተት ስለሌለ ራሱን መውቀስ እና መጨነቅ የለበትም። ማድረግ ያለበት ነገር ቢኖር ለሌሎች ተጓዳኝ በሽታዎች እንዳይጋለጥ ራሱን እንዲጠብቅ ትምህርት ማግኘት እና ከኤች.አይ.ቪ ነፃ የሆኑ ሰዎች ለቫይረሱ እንዳይጋለጡ ስብዓአዊነት ተስምቶት ቅድመ ጥንቃቄዎችን ማድረግና፣ ከተቻለም ማስተማር።
ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸዉ አውቀው ከጥቂት ጊዜ በኋላ ያሉበትን የጤና ሁኔታ ተቀብለው ራሳቸውን በማረጋጋት ወደፊት በተሻለ መንገድ ለመኖር ምን ማድረግ እንዳለባቸው ማሰብ ይጀምራሉ። እራሰን አረጋግቶ ለመኖር ከዚ በታች የተጠቀሱት ጠቃሚ መመሪያዎች በዝርዝር ጠንቅቆ ማወቅ አጥጋቢ የሆነ የፀባይ እና የአኗኗር ለውጥ ለማምጣት ይረዳል፦
ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ በደም ዉስጥ መኖሩን በታወቀበት ጊዜ ሊገጥም የሚችለውን የጭንቀት እና የፍርሃት ስሜት እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል፤
አጋጣሚን ጠብቀው የሚመጡ የበሽታ ስሜት/ምልክቶች በሰውነት ላይ ሲታዩ መወሰድ ያለባቸውን ህክምና እና ጥንቃቄ፤
የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣ የራስን ንፅህና መጠበቅ እና የሰውነት እንቅስቃሴ የማድረግ አስፈላጊነትን፤
ጥንቃቄ ስለተሞላበት የግብረ ሥጋ ግንኙነት እና ስለወሊድ።
ተስፋ እና የወደፊት ህይወት
ከኤች.አይ.ቪ ጋር ኑሮን በሠላም ለረጅም እድሜ መምራት እንደሚቻል መገንዘብ አስፈላጊ ነው። እንዲሁም ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ህጋዊ መብታቸውን የሚያከብሩ ህግጋት እንዲደነግጉ ድጋፍን በመስጠት የራስን አስተዋፅኦ በማድረግ ተስፋን እውን ማድረግ። በተጨማሪም የዕለት ዜናዎችን በመከታተል፣ባለሞያዎችን ወይንም አማካሪዎችን በመጠየቅ በኤች.አይ.ቪ ላይ ያሉ አዳዲስ የህክምና እና የመድሀኒት ግኝቶችን መከታተልና ማወቅ ተስፋን ይሰጣል። ስለ ኤች.አይ.ቪ ዕውቀትን ማዳበርና ይበልጥ ማወቅ ራስን በደንብ ለመንከባከብ ይረዳል። አንድ ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰው ልጆች ካሉት ህመም ሲጠና ልጆችን የሚንከባከብ ሰው ቀድሞ ማዘጋጀት ያስፈልጋል።
ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ክትባት ወይም ፈዋሽ መድኀኒት ባይገኝለትም ምርምሩና ሙከራዉ እንደቀጠለ ነው። የዕድሜ ማራዘሚያ መድሃኒቶች (ፀረ-ኤችአይቪ መዳኒቶች) ቫይረሱ በደም ውስጥ የሚያደርገውን የስርጭት ፍጥነት ለመግታትና ለማስቆም የሚወሰዱ መድሃኒቶች ናቸው። በሰውነት ዉስጥ የሚገኘውን የኤች.አይ.ቪ ቁጥር መቀነስ ይችላሉ፤ መድሃኒቶቹ ቫይረሱን ከናካቴው ማጥፋት አይችሉም። መድሃኒቶቹን ያለ ህኪም ትዕዛዘና ፍቃድ መውሰድ በጤንነት ላይ ትልቅ ችግር ያስከትላል። የመድሃኒቶቹ ተጠቃሚ ሰው አንድ በቅርብ ሆኖ የሚከታተለው ብቃት ያለው የህክምና ባለሙያ ያስፈልገዋል።
የተመጣጠነ ምግብ መመገብ ሰውነታችንን እና የሰውነት የመከላከያ አቅማችንን እንደሚያጠነክር ሁሉ በቀላሉ ለበሽታ እንዳንጋለጥም ይጠቅመናል። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ስዎች በምግብ እና ውኀ ውስጥ ለሚገኙ በሽታን ወይም ህመምን ሊያስከትሉ ለሚችሉ ጀርሞች በቀላሉ የተጋለጡ በመሆናቸዉ፤ በቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጭ ሲመግቡ ንጽህናውን የጠበቀ የአመጋገብ ሥርዓት መከተልና የሚጠጣው ውሃ ንጹሀ መሆኑን ማረጋግጥም በጣም ጠቃሚ ነው። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ስዎች የተለያዩ ዓይነት ምግቦችን በመመገብ ያልተፈለገ የሰውነት ክብደት መቀነሰን ለመከላከል እና ጡንቻዎቻቸዉ እንደጠነከሩ እንዲቆዩ የሰውነት እንቅስቃሴ ማድረግ አለባቸው።
ሁሉም የምግብ ዓይነቶች የተለያዩ ጥቅሞች አላቸዉ። የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች በሚከተለው መሰረታዊ ምድቦች ተከፋፍለው ሊታዩ ይችላሉ።
ገንቢ ምግቦች፦ ባቄላ፤ አተር፣ ምስር፣ እንቁላል፣ ሥጋ፣ አሣ፣ ዶሮ፣ ወተት፣ አይብ እና ለውዝ ሰውነትን ለመገንባት የሚያስችሉ የምግብ ንጥረ ነገሮችን ይዘዋል።
ኃይል ሰጪ ምግቦች፦ ለሰውነት የሚያስፈልገውን ኃይል ሁሉ የምናገኝባቸው የምግብ አይነቶች እንደ በቆሎ፣ እንጀራ፣ ዳቦ፣ ድንች፣ ፓስታ፣ ሩዝ፣ ስንዴ፣ አጃ፣ ዳጉሳ፣ ማሽላ፣ ስኳር፣ ማርማላት፣ ማርጋሪን፣ ዘይት፣ ሲሆኑ በተጨማሪም እንደ ለውዝ እና አቮካዶ የመሳሰሉ የቅባት ምግቦችንም ያጠቃልላል።
የሰውነትን የመከላከል አቅም የሚያጎለብቱ ምግቦች፦ አትክልትና ፍራፍሬ መመገብ የሰውነታችንን አቅም በማጎልበት በሽታን በሚገባ ለመቋቋም ያስችላል፤ እንዲሁም እንደ ካሮት፣ ሰላጣ እና ጎመን የመሳሰሉ ምግቦችንም መመገብ ቫይታሚን ለማግኘት ይረዳናል።
የሰዉነትን የመከላከል አቅም ለማጎልበት፦
የምግብን የመፍጨት ሂደት ሊያውኩ የሚችሉ እንደ ቃሪያ፣ በርበሬ ወይም ሚጥሚጣ የመሳሰሉ እና ሌሎች ቅመማ ቅመም የበዛባቸውን ምግቦች በብዛት አለመመገብ፣ ለስለስ ያሉ እንደ አልጫ ወጥ ያሉ ምግቦችን መመገብ፣ ከህይለኛ ቅመሞች ይልቅ የጥብስ ቅጠልን የመሳሰሉ የምግብ ማጣፈጫዎች መጠቀም ያስፈልጋል።
ፍራፍሬ እና የአትክልት አመጋገባችንን መጨመር፣ እነዚህን የሰውነት የመከላከል አቅም የሚያጎለብቱ ምግቦች በቫይታሚንና በማዕድን የበለፀጉ በመሆናቸው ሰውነታችንን ከበሽታ ይከላከላሉ። በመሆኑም እንደ ቆስጣ እና ጎመን የመሳሰሉ በጣም አረንጓዴ የሆኑ የቅጠላቅጠል ምግቦችን፣ እንደ ዱባ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ፣ ማንጎ እና የመሳሰሉ ፍራፍሬዎችን በየቀኑ መመገብ ያስፈልጋል። በተጨማሪም ከጤፍ፣ ከጥቁር ስንዴ፣ ገብስ የተዘጋጁ ዳቦዎችን እና ሌሎች ምግቦችን መመገብ።
ዉኃ ለሰውነታቻን ከሚያሰፈልጉን ነገሮች አንዱ ነው። በየቀኑ ቢያንስ 8 ብርጭቆ ዉሃ መጠጣት ጠቃሚ ነው። የምንጠጣው ዉሃ ንፁህ መሆን አለበት። ከኤች. አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰው እንደ ተስቦ፣ ኮሌራ፣ ቢልሀርዚያ እና ጃርዲያ ለመሳሰሉት በተበከለ ውኃ አማካኝነት በሚተላለፉ በሽታዎች የተጋለጠ ስለሆነ በቀጥታ የህይቅ ወይም የምንጭ ውኃ ከመጠጣት ፈልቶ የቀዘቀዘ ውኃ መጠጣት በጣም አስፈላጊ ነው።
ሰዉነታችንን በጤንነት ለማቆየትና ቫይረሱ በጤና ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ቫይታሚን ኤ፣ ቢ6፣ ቢ12፣ ሲ፣ ዚንክ፣ አይረን፣ ኮፐር፣ ማንጋኒዝ፣ ማግኒዥየም እና ሴሊኒየም ጨዉ የመሳሰሉትን ሁሉ መመገብ ይጠቅማል።
የሰዉነትን የተፈጥሮ በሽታን የመከላከል አቅም በማጎልበት ረገድ ቫይታሚን ኤ፣ ሲ፣ ኢ፣ እና ከማዕድናትም ዚንክ በጣም ጠቃሚዎች ናቸው። እነዚህ የምግብ ንጥረ-ነገሮች በተፈጥሮ ከተለያዪ ምግቦች ዉስጥ ይገኛሉ።
አንዳንድ ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ ባለመመገባችን ምክንያት የሚከተለውን ክፍተት ለማካካስ በፋብሪካ የተዘጋጁ ቫይታሚኖችን እንወስድ ይሆናል። ቅድሚያ መስጠት የሚገባን የተመጣጠነ ምግብ በመመገብ ተፈላጊ የሆኑትን የምግብ ንጥረ ነገሮች ማግኘት ቢሆንም የቫይታሚን እንክብሎችን መውሰድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያት አሉ። በግምት ብዙ ቫይታሚኖችን መውሰድ ጤንነትን ስለሚያቃውስ የቫይታሚን እንክብ በሚወሰድበት ጊዜ በህክምና ባለሞያ ትዕዛዝ መሰረት መሆን አለበት።
በምግብ አዘገጃጀት እና አመጋገብ ምክንያት ሊከሰቱ ከሚችሉ በሽታዎች ራስን መከላከል
ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች በምግብ ምክንያት ለሚመጡ በሽታዎች የተጋለጡ ናቸዉ። አንዳንድ ጎጂ የሆኑ ጀርሞች ከጥሬ ስጋ፣ ምግቡን ከሚያዘጋጁ ሰዎች ወይም አብረዉ እንጀራ ከሚበሉ ሰዎች አፍና እጅ ንክኪ ሊሸጋገሩና የምንመገበውም ሊበከል ይችላል። ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖር ሰው በምግብ መመረዝ ሲታመም ለማዳን በጣም ከባድ ከመሆኑ ሌላ በሽታው በተደጋጋሚ ሊመላለስበት ይችላል። እንደ ኮሶ፣ ወስፋት እና አሜባ የመሳሰሉት በሽታዎች ከፍተኛ የጤና ችግርን እንዲሁም ሞትን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ከነዚ በሽታዎች አብዛኛዎቹ በቀጥታ በበሽታዎቹ ከተያዘ ሰው የሚተላለፉ ቢሆንም ባልበሰለ ወይም ንጽህናው ባልተጠበቀ ምግብ፣ በነፍሳት (ተባዮች) በተበከለ ምግብ፣ የምግብ አያያዝ ሥርዓትና ደንብን ባልተከተለ ሰው ተዘጋጅቶ በሚቀርብ ምግብ አማካይነት ሊተላለፉ ይችላሉ። ምግብን በደምብ ማብሰል ባክቴርያና ጀርሞች እንዲሞቱ ይረዳል። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ጥሬ ሥጋ ወይም ጥሬ ክትፎም ሆነ ለብለብ ክትፎ ባይመገቡ ይመረጣል። በተጨማሪም ከቤት ውጭ በሆቴሎችና ቡና ቤቶች ውስጥ መመገብ ምግቡ እንዴት እንደተዘጋጀ ስለማይታወቅ ለህመም ሊያጋልጥ ይችላል። ከተቻለ ከቤት ውጭ አለመመገብ፤ ካልሆነም ምግቡ እንዴት እንደተዘጋጀ እና ጥሬ የሆኑ የምግብ ውህዶች ማለትም ያልበሰለ ሥጋ፣ እንቁላል ወይም አትክልት የሌለበት መሆኑን ጠይቆ ማረጋገጥ ያስፈልጋል።
ዕፅ እና አልኮል
ዕፅም ሆነ አልኮል በብዛት መውሰድ የሰውነትን የተፈጥሮ በሽታን የመከላከል አቅም ያዳክማል። ጤናማ ሆኖ ለመኖርም ሆነ ጤንነትን ለመንከባከብ አልኮልንም ሆነ ዕፅን መጠቀምን እስከመጨረሻው መተው አማራጭ መንገድ ቢሆንም ይህንን ሁሉም ሰው በቀላሉ ሊያደርገው አይችልም። የሚወሰደው የሲጋራ፣ የዕፅ ወይም የአልኮል መጠንን በተቻለ መጠን መቀነስ ጤንነትን በተሻለ ሁኔታ ለመጠበቅም ይረዳል።
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ የተሻለ ጢና እንዲኖር ከመርዳቱ ሌላ የመጨነቅ፣ እና የድካም ስሜትን ይቀንሳል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴው ራስን ዘና የሚያደርግና የልብን ምት እንዲጪምር ተደርጎ መሠራት አለበት እንጂ እስኪደክሙ መሆን የለበትም። ተገቢውን የየአካል ብቃት እንቅስቃሴ መጠን ለማወቅ ቢቻል የስፖርት ባለሞያዎችን አስቀድሞ ማማከር የተሻለ ነው። በየቀኑ ከ30 እስከ 60 ደቂቃ ያህል በእግር መጓዝ የተሻለ ጤና እንዲኖረን ከሚረዱት የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች አንዱ ነው።
ወሲብና ፍቅር
አንድ ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ሰው ስለራሱ ጤና በተመለከተ መብቱ የተሰጠዉ ለራሱ በመሆኑ ለፈለገው ሰው መንገር፣ ካልፈለገ ደግሞ ያለመናገርም ውሳኔው በእጁ ነው። ነገር ግን ከዚህ ጋር በተያያዘ መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ አለ። በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ላይ የሰፈረ ድንጋጌ አንድ ሰው የሌላውን ሰው ጤንነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሆን ብሎ ይሁን በቸልተኝነት የሚጎዳ ተግባር ከፈጸመ እንደሚቀጣ ያስረዳል። ስለዚህ ከወሲብ ጓደኛ ጋር በሚኖር ግንኙነት ቫይረሱ ወደዛ ጓደኛ እንዳይተላለፍ ኮንዶም መጠቀም ያስፈልጋል ። ይህ ከሆነ ከኤች·አይ·ቪ ነፃ የሆነውን ወዳጅ ከቫይረሱ ለመጠበቅ ይረዳል። ከኤች·አይ·ቪ ጋር ነዋሪ መሆንን ለወሲብ/ፍቅር ጓደኛዎ አንዳንድ ጊዜ በቀጥታ ሌላ ጊዜ ደግሞ በተዘዋዋሪ መናገር ይቻላል። ለምሳሌ ስለቅድመ ወሲብ ጥንቃቄ ወይም ስለ ኤች·አይ·ቪ እና መተላለፊያ መንገዶች በማንሳት መነጋገር ይቻላል።
ወሊድ ( ኤችአይቪ ያለባት እናት)
አንዲት ሴት ኤች·አይ·ቪ በደሟ ውስጥ ቢኖርም እንኳን ልጆች ማፍራት ትችላለች። ተገቢውን ጥንቃቄ እና የህክምና ክትትል ካደረገች ከኤች·አይ·ቪ ነፃ የሆነ ጤነኛ ልጅ ሊኖራት ይችላል። ይሁን እንጂ ለኤች·አይ·ቪ የሚጋለጥም ልጅ ሊኖር ይችላል።
ልጅ ለመውለድ እቅድ ካለ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ማለት እና የህክምና ባለሞያን ማማከር ያስፈልጋል
የጤንነት ሁኔታ- በእርግዝና ወቅት በብዛትም ሆነ በጥራት የተሻለ የምግብ አቅርቦት መኖር አለበት። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ሰው ደግሞ ከፍ ያለ የምግብ መጠንና የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች ማግኘት ያስፈልገዋል።
ፅንሱን ከቫይረሱ መከላከል- ኤች·አይ·ቪ በደም ውስጥ መኖሩን አውቆ ልጅን ከኤች·አይ·ቪ ለመታደግ አስፈላጊውን እቅድ ማዉጣትና ተገቢውን ህክምና መከታተል የልጅን በቫይረሱ የመያዝ አጋጣሚ ለመቀነስ ይረዳል።
በደም ዉስጥ የኤች·አይ·ቪ መኖር- ወደፊት አንድ ወቅት ላይ የኤድስ ታማሚ ሊሆኑ እና አልጋ ላይ የመዋል አጋጣሚ ሊመጣ ይችላል። ስለዚህ ልጅዎ ያለ ተንከባካቢ እንዳይቀር ቀደም ብሎ ሁኔታዎችን ማመቻቸትም ያስፈልጋል።
ኤች·አይ·ቪ እና ሰብአዊ መብት
ከኤች·አይ·ቪ ጋር መኖር ከማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር አያሳንሰም። ኤች·አይ·ቪ በደም ውስጥ በመኖሩ በሰብአዊ ፍጡርነት ሊኖር የሚገባውን መብት ሊያጓድል የሚችል አንድም ምክንያት የለም። ይህም ማለት ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ማንኛውም ሰው እንደሌሎች
እንደማንኛውም ሰው ቫይረሱ በደሙ ያለበት ሰው የጤና አጠባበቅ አገልግሎት፣ ሥራ እና የትምህርት ዕድል የማግኘትና፣ በማህበራዊ ክንውኖች፣ ለምሳሌ፣ ዕድር፣ በዕምነት፣ በማህበራት ወይም የስፖርት ቡድን በመሳሰሉ ማህበራዊ ተቋማት አባል የመሆን መብት አለው።
ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ሰው ቤት የመከራየት ወይም ባለንብረት ለመሆን፣ የጤና፣ የህይወት ወይም የንብረት መድን የመግባት መብት አለው።
ከኤች·አይ·ቪ ጋር በሚኖሩ ሰዎች ላይ የሚደረግ መድልዎ ዋና ዋና መንስኤዎች አሉት፦ እነዚህም
ስለ ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ መተላለፊያ መንገዶች ዝቅተኛ ወይም የተሳሳተ መረጃ መኖር፤
በቂ ግንዛቤ ካለማግኘት ወይም ከተሳሳተ መረጃ ላይ በመመርኮዝ የሚመጣ ፍርሃት፤
ስለግብረ ስጋ ግንኙነት በግልጽ መነጋገር እንደ ነውር ስለሚቆጠር፤
በሥራ ቦታ ላይ ስለሚደርስ መድልዎ ማወቅ፦ አንድ ሰው ከኤች·አይ·ቪ ጋር በመኖሩ ምክንያት መገለል ወይም አድልዎ ከደረሰበት ከቀጣሪው ጋር በመነጋገር ወይም በፍርድ ቤት በመክሰስ ፍትህ የማግኘት መብት አለው። ሕግም ከለላና ጥበቃ ያደርግለታል። የኢፌዴሪ የኤች·አይ·ቪ/ኤድስ ፖሊሲ ማግለልና አድልዎን በግልጽ ይከለክላል።
የውጭ መያያዣዎች
1. አበሻ ኬር
2. የእንግሊዘኛ ውክፔዲያ
|
48313
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8C%8A%E1%88%B2%E1%8B%8D%E1%88%9D%E1%89%A3
|
አጊሲውምባ
|
አጊሲውምባ (ሮማይስጥ፦ ) በሮማዊው ታሪክ ጸሐፊ ቶለሚ ዘንድ በ1ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም. በዛሬው ደቡብ ቻድ አካባቢ የተገኘ ጥንታዊ አገር ነበር።
ቶለሚ (150 ዓም ግድም) እንደ ጻፈ፣ በ42 ዓም ሮማዊው አለቃ ፍላኩስ ሴፕቲሚዩስ እስከ ቻድ ሐይቅና ከዚያ ማዶ ደረሰ፣ አገሩም አጊሲውምባ ተባለ። አውራሪስና ጉማሬ በሐይቁ ዙሪያ የሞላበት አገር እንደ ነበረ ገለጸ። ከዚያ በ82 ዓም ሌላ ሮማዊ ተጓዥ ጁሊዩስ ማቴርኑስ በሁለተኛው ጉዞ እስከ አጊሲውምባ ድረስ ሄዶ አንድ አውራሪስ ይዞ እንደ ተመለሰ ተጽፏል። ከ75 እስከ 84 ዓም ድረስ የአጊሲውምባ ሕዝብ ለጋራማንቴስ ንጉሥ ተገዥ እንደ ነበር ጨመረ፤ ጋራማንቴስም በአሁኑ ደቡብ ሊብያ የተገኘ ብሔር ነበር።
ታሪካዊ አገሮች
የአፍሪካ ታሪክ
|
19883
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B4%E1%89%AA%E1%8B%B5%20%E1%88%81%E1%88%9D
|
ዴቪድ ሁም
|
ዴቪድ ሁም (ግንቦት 7 1711 - ነሐሴ 25 1776) የነበረ የስኮትላንድ ታሪከኛ እና ፈላስፋ ነበር። ሁም በዘመኑ ይታወቅ የነበረው በታሪክ ተመራማሪነት ነበር። የእንግሊዝ ታሪክ የሚሉ ትላልቅ መጻሕፍትን በዘመኑ ደርሶ ለህትመት አብቅቶ ነበር። አሁን ግን ሁም የሚታወቀው በዋና ፈላስፋነቱ ነው።
በፍልስፍና መጽሕፉ ላይ እንደሚያስረዳ ብዙው የሰው ልጅ አምኖ የሚቀበላቸው ነገሮች በ በምክንያት የተደገፉ አይደሉም። ይልቁኑ ከስሜትና ደመነፍስ የሚመነጩ ናቸው። ለምሳሌ አምክንዮ የአንድ ነገር መንስኤ ሌላ ነገር ነው ብሎ አይናገርም። ነገር ግን አንድ ክስተት ሲፈጠርና ከዚያ ቀጥሎ ሌላ ክስተት ሲፈጠር ስናይ የመጀመሪያው ክስተት ለሚቀጥለው ክስተት መንስኤ ነው ብለን በ"ስሜት" እንደመድማለን። በተመሳሳይ አንድ ሰው ሰናይ ግለሰብ እንደሆነ ምክንያት አይነግረንም። ይልቁኑ ያ ሰው ደግና ተግባቢ ሆኖ ስናየው በስሜት ሰናይ ነው እንላለን። እኒህ ነገሮች ከምክንያት አይመነጩም ብሎ ሁም ስለሚያምን ተጠራጣሪ ወይንም ኢ-ምክንዮት ፈላስፋ ተብሎ ይታወቃል።
ሁም ሃይማኖት ላይም ተጠራጣሪ ነበር። ሁም ሃይማኖተኛ ሰው አልነበረም። በተአምራትም አያምንም ነበር።
የሁም ዋና ዋና መጻሕፍት
በዚህ መጽሐፍ፣ ሁም ስለ ሰው ልጅ አዕምሮ በመተንተን እንዴት እንደሚሰራ ለመረዳት ይሞክራል። ስለ ሰው ልጅ እውቀት፣ ስለ መንስኤና ውጤት፣ ስለ የሰው ልጅ ስሜትምና ስለ ደግና ክፉ ይፈላስፋል።
በዚህች ትንሽ መጽሓፍ ውስጥ ከላይ የቀረበውን መጽሐፍ ሃሳቦች በማሳጠርና ለማንበብ እንዲመቹ በማድረግ ተንትኗል።
ትንሽና ለማንበብ ምቹ የሆነች መጽሐፍ ስትሆን የመጽሐፉ ትኩረት ስለ ደግና ክፉ ይተነትናል
በዚህ መጽሐፉ 3 ገጸ ባህርያት ስለ አምላክ ሲከራከሩ ይነበባል
የስኮትላንድ ሰዎች
|
15627
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%8C%E1%89%A5%E1%8A%92%E1%89%B5%E1%8B%9D
|
ሌብኒትዝ
|
ጎትፍሪድ ቪልሄልም ሌብኒትዝ ( 14 1716 እ.ኤ.አ.) የ17ኛው ክፍለ ዘመን የጀርመን የሒሳብ ሊቅ፣ ሳይንቲስት፣ ፈላስፋ፣ ፍርድ አጥኝና ባጠቃላይ መልኩ ሁለ ገብ ተመራማሪ ነበር።
ሌብኒዝ ከኢሳቅ ኒውተን ትይዩ ካልኩለስ የተባለውን የዕውቀት ዘርፍ ፈጥሯል። አሁን ድረስ ተማሪወች የሚጠቀሙበት የካልኩለስ የአጻጻፍ ስልት በዚህ ሰው የተፈለሰፈ ነው። ለኮምፒዩተር ስራ እጅግ ወሳኝ የሆነውን የሁለትዮሽ ቁጥር ስርዓት (ባይናሪ ቁጥር) ዘመናዊ ኮምፒዩተሮች ከመሰራታቸው 300 አመት በፊት ፈልስፏል።
በፍልስፍናው ዘርፍም ጠለቅ ያለ አስተዋጽኦ አበርክቷል። የሌብኒዝ ፍልስፍና እንደ ደካርት ፍልስፍና ቀልበኛ ይባላል። «ይህ ዓለም እግዚአብሔር ሊፈጥራቸው ይችላቸው ከነበሩ ዓለማት ሁሉ የተሻለ» ነው የሚለው ድምዳሜው የሌብኒዝን ፍልስፍና ብሩህ ተስፈኛ በሚባል መደብ ስር እንዲታወቅ አድርጎታል። የሌብኒዝ ፍልስፍና የቀደምት አውሮጳውያን የፍልስፍና ዘዴ ተብሎ የሚታወቀውን ስኮላስቲክ ወደ ኋላ የሚመለከትና ወደፊት ደግሞ በ20ኛው ክ/ዘመን ብቅ ያሉን ዘመናዊ ሥነ አምክንዮ እና ትንታኔአዊ ፍልስፍናን የተነበየ ነበር። በርግጥም ከደካርትና ከስፒኖዛ ጋር በመሆን ሌብኒዝ የ17ኛው ክፍለ ዘመን የአውሮጳ ዋና ቀልበኛ ፈላስፋ ነበር ቢባል ማጋነን አይሆንም።
ከዚህ በተጨማሪ ሌብኒዝ ለተፈጥሮ ህግጋት ጥናት እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ሥነ ህይወት ጥናቶች ከፍተኛ አስተዋጾችን አድርጓል። በህክምና፣ መሬት ጥናት፣ እድል ጥናት ፣ ታሪክ፣ ስነ ቋንቋ፣ ሥነ ምግባር፣ ሕግ፣ ፖለቲካ፣ ሥነ አዕምሮ፣ መረጃ ሳይንስ ላይ ህልቁ መሳፍርት ጽሁፎችን አቅርቧል። የሚያሳዝነው ግን እኒህ ሁሉ ጽሁፎቹ በመጽሄቶች ገጽና በደብዳቤውች ተሰባጥረው አንድ ላይ ስላልታተሙ እስካሁን ዘመን ድረስ የዚህ ሰው ስራ ስፋትና ወርዱ በርግጥም አይታወቅም።
ሌብኒዝ ከኒውተን ጋር "ማን ካልኩለስን ቅድሚያ ፈለሰፈ" በሚል ጥን አንስተው በእንግሊዝና በአውሮጳ ሳይንቲስቶች መካከል ከፍተኛ ሽኩቻ ነበር። በአሁኑ ዘመን ሁለቱም ሰወች ካልኩለስን ለየብቻቸው እንዳገኙ ይታመናል። ሌብኒዝ ብዙ ወዳጆች ቢያፈራም በኋለኛ ዘመኑ ብዙ ጠላቶች ስለነበሩት ሲሞት ካለጸሃፊው በስተቀር ለቀብሩ የመጣ አልነበረም። የዚህ ድንቅ ሰው ህይወት እንዲህ መፈጸሙ ብዙ ጸሃፊወችን እስከ አሁኑ ዘመን ሲያሳዝን ይኖራል።
የጀርመን ሰዎች
ሒሳብ ተመራማሪዎች
|
35058
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%86%E1%8A%85%E1%89%B0%20%E1%8A%A5%E1%8A%93
|
ኆኅተ እና
|
ኆኅተ እና መሰረታዊ ከሆኑት ኆኅተ አመክንዮዎች አንዱ ሲሆን ተግባሩም የአመክንዮ እናን ተግባር በተጨባጭ ቁስ መፈጸም ነው። ምንም እንኳ ኆኅተ አመክንዮዎች በተለያዩ ቁሶች ሊሰሩ ቢችሉም፣ በአሁኑ ዘመን እነዚህ ኆኅቶች የሚሰሩት ከኤሌክትሪክ አካላት ስለሆነ አስራሩ ከዚህ አኳያ ይመረምራል። ኆኅተ እና አምክንዮ-እናን በቁስ እንደመግልጹ፣ የዚህ ኆኅት ውጤት ከፍተኛ ቮልቴጅ እሚሆነው ሁለቱም ግቤትዎቹ ከፍተኛ ሲሆኑ ብቻ ነው። ከሁለቱ አንዱ ውይንም ሁለቱም ግቤቶች ትንሽ ከሆኑ የ እና ውጤት 0 ይሆናል ማለት ነው። ይህ ጸባይ ከጎን በሚታየው የዕውነታ ሠንጠረዥ ተብራርቶ ይታያል።
ከሠንጠረዡ እንደምንረዳ፣ የእና-ኆኅት ከሚቀርቡለት ሁለቱ ወይም ከዚያ በላይ ግቤቶች ትንሹን ይከተላል።
እና ግቤቶች ሲሆኑ ውጤት ሲሆን በአጠቃላይ ይህ ኆኅት የሚተገብረው አመክንዮ ነው ማለት ነው። የመጀመሪያው ምልክት እሚያሳየው ሁለት ማብሪያ ማጥፊያዎችን ሲሆን፣ ሁለቱም ማብሪያ ማጥፊያወች አንድ ላይ ካልበሩ ኤሌክትሪክ እንደምያስተላልፉ መገንዘቡ ይህ ዑደት የአምክንዮ-እናን እንደሚተገበር ያስረዳል።
የ እና-ሆኅት ከኆኅተ ኢእና ወይም ከኆኅተ ኢወይም ሊሰራ ይችላል። ለምሳሌ ከኢ-እና እንዲህ ይሰራል፦
ቁሳዊ አሰራሩ
የእና ኆኅት ብዙ ጊዜ የሚሰራው ከ ወይም ች ነው።
ኆኅተ አመክንዮ
|
22588
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%89%85%E1%88%98%E1%89%86
|
መቅመቆ
|
መቅመቆ () ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ
የእርሻም ሆነ የውድማ አረም ነው።
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር
የተክሉ ጥቅም
ድንቼው ቀይ ንክር ቀለም ይሠራል፣ የሴቶች እጅና እግር ለማጌጥ ነው። ድንቼው ሲበሠል ጠንካራ ቢጫ ንክር ቀለም ይሠራል፣ ይህም ለቅቤና ለቅመም ነው።
በባሕል መድሃኒት፣ ሥሩ በቋቁቻ ላይ በቀጥታ ይቀባል። ሥሩም ተደቅቆ በውሃ ተፈልቶ ለደም ብዛት ለማከም ይጠጣል። ሥሩም ለደም ብዛት ወይም ለጉሮሮ ብግነት ይኘካል። ሥሩ ተደቅቆ በወተትና ቅቤ ለእንቅርትና ለአሚባ በሽታ ይጠጣል።
የኢትዮጵያ እጽዋት
|
9952
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8B%AB
|
እስያ
|
እስያ (/ ፣ / በዋነኛነት በምስራቅ እና ሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ የምትገኝ የምድር ትልቁ እና በሕዝብ ብዛት የምትገኝ ናት። የዩራሺያን አህጉራዊ መሬት ከአውሮፓ አህጉር ጋር ትጋራለች፣ እና የአፍሮ-ኢውራሺያ አህጉራዊ መሬት ከአፍሪካ እና አውሮፓ ጋር ትጋራለች። እስያ 44,579,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (17,212,000 ስኩዌር ማይልስ)፣ ከምድር አጠቃላይ ስፋት 30 በመቶው እና ከምድር አጠቃላይ የገጽታ ስፋት 8.7% ያህሉን ይሸፍናል።ለብዙ የሰው ዘር መኖሪያ የሆነችው አህጉር ከረጅም ጊዜ በፊት የኖረችው የብዙዎቹ የመጀመሪያ ስልጣኔዎች ቦታ፡ 4.7 ቢሊዮን ህዝብዋ ከአለም ህዝብ 60% ገደማ ነው።
በአጠቃላይ እስያ በምስራቅ በፓስፊክ ውቅያኖስ፣ በደቡብ በህንድ ውቅያኖስ እና በሰሜን በአርክቲክ ውቅያኖስ የተከበበ ነው። በመካከላቸው ግልጽ የሆነ አካላዊ እና ጂኦግራፊያዊ መለያየት ስለሌለ የእስያ ድንበር ከአውሮፓ ጋር ታሪካዊ እና ባህላዊ ግንባታ ነው። በተወሰነ ደረጃ የዘፈቀደ ነው እና በጥንታዊ ጥንታዊነት ከመጀመሪያው ፅንሰ-ሀሳብ ጀምሮ ተንቀሳቅሷል። የዩራሺያ በሁለት አህጉራት መከፋፈል የምስራቅ - ምዕራብ የባህል፣ የቋንቋ እና የጎሳ ልዩነቶችን ያንፀባርቃል፣ አንዳንዶቹ በሰላማዊ መስመር ሳይሆን በስፔክትረም ይለያያሉ። በብዛት ተቀባይነት ያለው ድንበሮች እስያ ከሱዌዝ ካናል በስተምስራቅ ከአፍሪካ ይለያታል; እና ከቱርክ ስትሬት በስተ ምሥራቅ የኡራል ተራሮች እና የኡራል ወንዝ እና ከካውካሰስ ተራሮች በስተደቡብ እና በካስፒያን እና ጥቁር ባህሮች ከአውሮፓ ይለያሉ.
ቻይና እና ህንድ ከ1 እስከ 1800 ዓ.ም. በዓለም ላይ ትልቁ ኢኮኖሚ በመሆን ተፈራርቀዋል። ቻይና ትልቅ የኤኮኖሚ ሃይል ነበረች እና ብዙዎችን ወደ ምስራቃዊ ስቧል እና ለብዙዎች የህንድ ጥንታዊ ባህሎች አፈ ታሪክ ሀብት እና ብልጽግና ኤዥያንን በመምሰል የአውሮፓ ንግድን ፣ ፍለጋን እና ቅኝ ግዛትን ይስባል። ከአውሮፓ ወደ አሜሪካ የሚወስደውን የአትላንቲክ ተሻጋሪ መንገድ ኮሎምበስ ወደ ህንድ የሚወስደውን መንገድ ሲፈልግ በአጋጣሚ ማግኘቱ ይህን ጥልቅ መማረክ ያሳያል። የሐር መንገድ በኤሽያ ኋለኛ አገሮች ውስጥ ዋናው የምስራቅ-ምዕራብ የንግድ መስመር ሆነ የማላካ የባህር ዳርቻ እንደ ዋና የባህር መስመር ነው። እስያ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን (በተለይ የምስራቅ እስያ) እና ጠንካራ የህዝብ እድገት አሳይታለች፣ ነገር ግን አጠቃላይ የህዝብ ቁጥር እድገት ቀንሷል። እስያ የሂንዱይዝም፣ የዞራስተሪያኒዝም፣ የአይሁድ እምነት፣ የጃይኒዝም፣ የቡድሂዝም እምነት፣ የኮንፊሺያኒዝም፣ ታኦይዝም፣ ክርስትና፣ እስልምና፣ ሲክሂዝም እና ሌሎች በርካታ ሃይማኖቶች ጨምሮ የአብዛኛው የአለም ዋና ዋና ሃይማኖቶች መገኛ ነበረች።
ከግዙፉና ከልዩነቱ አንፃር የኤዥያ ጽንሰ-ሐሳብ-ከጥንታዊው ጥንታዊነት ጀምሮ ያለው ስም-ከሥጋዊ ጂኦግራፊ ይልቅ ከሰው ልጅ ጂኦግራፊ ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል። ባህሎች, አከባቢዎች, ኢኮኖሚክስ, ታሪካዊ ግንኙነቶች እና የመንግስት ስርዓቶች. በተጨማሪም ከምድር ወገብ ደቡብ በመካከለኛው ምስራቅ በሞቃታማው በረሃ፣ በምስራቅ ደጋማ አካባቢዎች እና በአህጉራዊው ማእከል እስከ ሳይቤሪያ ውስጥ ያሉ ሰፊ የከርሰ ምድር እና የዋልታ አካባቢዎች ያሉ በርካታ የተለያዩ የአየር ንብረት ሁኔታዎች አሏት።
ፍቺ እና ድንበሮች
እስያ-አፍሪካ ድንበር
በእስያ እና በአፍሪካ መካከል ያለው ድንበር ቀይ ባህር፣ የስዊዝ ባሕረ ሰላጤ እና የስዊዝ ካናል ነው። ይህ ግብፅን አህጉር ተሻጋሪ ሀገር ያደርጋታል፣ የሲና ባሕረ ገብ መሬት በእስያ እና የተቀረው የሀገሪቱ ክፍል በአፍሪካ ነው።
እስያ - አውሮፓ ድንበር
የብሉይ ዓለም የሶስትዮሽ ክፍፍል ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ጥቅም ላይ የዋለው እንደ አናክሲማንደር እና ሄካቴየስ ባሉ የግሪክ ጂኦግራፊዎች ምክንያት ነው። ዘመናዊው የሪዮኒ ወንዝ) በካውካሰስ ጆርጂያ (ከአፉ በፖቲ በጥቁር ባህር ዳርቻ ፣ በሱራሚ ማለፊያ እና በኩራ ወንዝ በኩል እስከ ካስፒያን ባህር ድረስ) ፣ አሁንም በሄሮዶተስ በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. በሄለናዊው ዘመን፣ ይህ የአውራጃ ስብሰባ ተሻሽሎ ነበር፣ እናም በአውሮፓ እና በእስያ መካከል ያለው ድንበር አሁን ታኒስ (የዘመናዊው ዶን ወንዝ) ተደርጎ ይቆጠር ነበር። ይህ እንደ ፖሲዶኒየስ፣ ስትራቦ እና ቶለሚ ባሉ የሮማውያን ዘመን ደራሲያን የተጠቀሙበት ስምምነት ነው።
በእስያ እና በአውሮፓ መካከል ያለው ድንበር በታሪክ በአውሮፓውያን ምሁራን ይገለጻል።የሩሲያ የዛርዶም ንጉስ ታላቁ ፒተር ታላቁ ፒተር የስዊድን እና የኦቶማን ኢምፓየር ተቀናቃኝ የይገባኛል ጥያቄዎችን ወደ ምስራቃዊ አገሮች በማሸነፍ እና የታጠቁ ተቃውሞዎችን ሲያሸንፍ የዶን ወንዝ ለሰሜን አውሮፓውያን አጥጋቢ አልነበረም። በሳይቤሪያ ነገዶች ፣ በ 1721 የተመሰረተው በ 1721 ወደ ኡራል ተራሮች እና ከዚያም በላይ የሚደርስ አዲስ የሩሲያ ኢምፓየር አቋቋመ ። የግዛቱ ዋና ጂኦግራፊያዊ ቲዎሪስት የቀድሞ የስዊድን እስረኛ ነበር ፣ በ 1709 በፖልታቫ ጦርነት ተወሰደ እና ተመድቧል ። ወደ ቶቦልስክ, ከፒተር የሳይቤሪያ ባለስልጣን ቫሲሊ ታቲሽቼቭ ጋር የተገናኘ እና ለወደፊት መጽሐፍ ለመዘጋጀት የጂኦግራፊያዊ እና አንትሮፖሎጂ ጥናቶችን ለማካሄድ ነፃነት ተፈቅዶለታል.
በስዊድን፣ ፒተር ከሞተ ከአምስት ዓመታት በኋላ፣ በ1730 ፊሊፕ ጆሃን ቮን ስትራለንበርግ የኡራል ተራሮችን የእስያ ድንበር አድርጎ የሚያሳይ አዲስ አትላስ አሳተመ። ታቲሽቼቭ ሀሳቡን ለቮን ስትራለንበርግ እንዳቀረበ አስታወቀ። የኋለኛው ደግሞ የኢምባ ወንዝን የታችኛው ወሰን አድርጎ ጠቁሟል። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ የኡራል ወንዝ እስኪያሸንፍ ድረስ በሚቀጥለው ክፍለ ዘመን የተለያዩ ሀሳቦች ቀርበዋል. ድንበሩ የኡራል ወንዝ ወደ ሚሰራበት ከጥቁር ባህር ወደ ካስፒያን ባህር ተወስዷል። በጥቁር ባህር እና በካስፒያን መካከል ያለው ድንበር ብዙውን ጊዜ በካውካሰስ ተራሮች ጫፍ ላይ ይደረጋል ፣ ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ ወደ ሰሜን ቢቀመጥም
የእስያ-ውቅያኖስ ድንበር
በእስያ እና በኦሽንያ ክልል መካከል ያለው ድንበር ብዙውን ጊዜ በማላይ ደሴቶች ውስጥ አንድ ቦታ ላይ ይደረጋል። በኢንዶኔዥያ የሚገኙት የማሉኩ ደሴቶች ብዙውን ጊዜ በደቡብ ምስራቅ እስያ ድንበር ላይ ከኒው ጊኒ ጋር ፣ ከደሴቶቹ በስተምስራቅ ፣ ሙሉ በሙሉ የኦሺኒያ አካል እንደሆኑ ይታሰባል። በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነደፉት ደቡብ ምስራቅ እስያ እና ኦሺኒያ የሚሉት ቃላት፣ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ብዙ የተለያዩ መልክዓ ምድራዊ ትርጉሞች ነበሯቸው። የትኛዎቹ የማሌይ ደሴቶች ደሴቶች እስያ እንደሆኑ ለመወሰን ዋናው ምክንያት በዚያ የሚገኙት የተለያዩ ኢምፓየሮች (ሁሉም አውሮፓውያን አይደሉም) የቅኝ ግዛት ይዞታዎች መገኛ ነው። ሉዊስ እና ዊገን "የደቡብ ምስራቅ እስያ" ወደ አሁን ድንበሮች መጥበብ ቀስ በቀስ ሂደት ነበር ይላሉ።
ቀጣይነት ያለው ትርጉም
ጂኦግራፊያዊ እስያ ከጥንት ግሪኮች ጀምሮ ፣ በሌሎች ባህሎች ላይ ተጭኖ በዓለም ላይ የአውሮፓ ፅንሰ-ሀሳቦች ባህላዊ ቅርስ ነው ፣ ትርጉሙ ምን ማለት እንደሆነ ትክክለኛ ያልሆነ ጽንሰ-ሀሳብ ነው። እስያ ከተለያዩ አይነት አካላት ባህላዊ ድንበሮች ጋር በትክክል አይዛመድም።
ከሄሮዶተስ ዘመን ጀምሮ ጥቂት የማይባሉ የጂኦግራፊ ባለሙያዎች የሶስት አህጉር ስርዓትን (አውሮፓ, አፍሪካ, እስያ) በመካከላቸው ምንም አይነት ተጨባጭ አካላዊ መለያየት የለም ብለው ውድቅ አድርገዋል. ለምሳሌ፣ በኦክስፎርድ የአውሮፓ የአርኪዮሎጂ ኤመርቲስ ፕሮፌሰር የሆኑት ሰር ባሪ ኩንሊፍ፣ አውሮፓ በጂኦግራፊያዊ እና በባህል ብቻ "የምዕራባዊው የእስያ አህጉር የላቀ" እንደነበረች ይከራከራሉ።
በጂኦግራፊያዊ አገላለጽ፣ እስያ የዩራሲያ አህጉር ዋና ዋና ምስራቃዊ አካል ነች ፣ አውሮፓ የመሬቱ ሰሜናዊ ምዕራብ ባሕረ ገብ መሬት ነች። እስያ፣ አውሮፓ እና አፍሪካ አንድ ነጠላ ቀጣይነት ያለው መሬት-አፍሮ-ኤውራሲያ (ከሱዌዝ ካናል በስተቀር) - እና አንድ የጋራ አህጉራዊ መደርደሪያን ይጋራሉ። ሁሉም ማለት ይቻላል አውሮፓ እና የእስያ ዋና ክፍል በዩራሺያን ፕላት ላይ ተቀምጠዋል ፣ በደቡብ በኩል በአረብ እና በህንድ ሳህን እና በሳይቤሪያ ምስራቃዊ ክፍል (ከቼርስኪ ክልል ምስራቅ) በሰሜን አሜሪካ ጠፍጣፋ ላይ።
ሥርወ ቃል
"እስያ" የሚባል ቦታ ሀሳብ በመጀመሪያ የግሪክ ሥልጣኔ ጽንሰ-ሐሳብ ነበር, ምንም እንኳን ይህ በአሁኑ ጊዜ በዚህ ስም ከሚታወቀው አህጉር ጋር ላይስማማ ይችላል. የእንግሊዘኛው ቃል የመጣው ከላቲን ስነ-ጽሑፍ ነው, እሱም ተመሳሳይ ቅርጽ አለው, "እስያ". በሌሎች ቋንቋዎች "እስያ" ከሮማን ኢምፓየር ከላቲን የመጣ ስለመሆኑ ብዙም እርግጠኛ አይደለም፣ እና የላቲን ቃል የመጨረሻው ምንጭ በእርግጠኝነት አይታወቅም ፣ ምንም እንኳን በርካታ ንድፈ ሐሳቦች ታትመዋል። እስያ የመላው አህጉር ስም አድርገው ከተጠቀሙባቸው የመጀመሪያዎቹ ክላሲካል ጸሐፊዎች አንዱ ፕሊኒ ነው። ይህ ዘይቤያዊ የትርጉም ለውጥ የተለመደ ነው እና በአንዳንድ ሌሎች የጂኦግራፊያዊ ስሞች ለምሳሌ እንደ ስካንዲኔቪያ (ከስካኒያ) ይታያል።
የነሐስ ዘመን
ከግሪክ ቅኔ በፊት የኤጂያን ባህር አካባቢ በግሪክ የጨለማ ዘመን ነበር፣ በዚህ መጀመሪያ ላይ የቃላት አጻጻፍ ጠፋ እና የፊደል አጻጻፍ አልተጀመረም። ከዚያ በፊት በነሐስ ዘመን የአሦር ኢምፓየር፣ የኬጢያውያን ግዛት እና የግሪክ የተለያዩ የሜይሴኒያ ግዛቶች መዛግብት እስያ እንደሚገኝ ጥርጥር የለውም፣ በእርግጠኝነት አናቶሊያ ውስጥ፣ ከሊዲያ ጋር ተመሳሳይ ካልሆነ ጨምሮ። እነዚህ መዝገቦች አስተዳደራዊ ናቸው እና ግጥም አያካትቱም.
የማሴኔያን ግዛቶች በ1200 ዓክልበ አካባቢ ባልታወቁ ወኪሎች ወድመዋል፣ ምንም እንኳን አንድ የአስተሳሰብ ትምህርት ቤት የዶሪያን ወረራ እስከዚህ ጊዜ ድረስ ቢመደብም። የቤተ መንግሥቶቹ መቃጠላቸው የማይሴኔያን የአስተዳደር መዛግብት የያዙ የሸክላ ጽላቶች በመጋገር እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል። እነዚህ ጽላቶች የተጻፉት ሊኒያር ቢ በተባለው የግሪክ ሲላቢክ ስክሪፕት ነው። ይህ ስክሪፕት የተፈታው በብዙ ፍላጎት ባላቸው አካላት ነው፣ በተለይም በወጣቱ የዓለም ጦርነት ጸሐፊ ሚካኤል ቬንተሪስ፣ በመቀጠልም በሊቁ ጆን ቻድዊክ ተረድቷል።
በጥንታዊው ፓይሎስ ቦታ በካርል ብሌገን የተገኘው ዋና መሸጎጫ በመቶዎች የሚቆጠሩ የወንድ እና የሴት ስሞች በተለያዩ ዘዴዎች የተፈጠሩ ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ በባርነት የተያዙ ሴቶች ናቸው (የህብረተሰቡ ጥናት በይዘቱ እንደሚያሳየው)። እንደ ልብስ ሥራ ባሉ ንግዶች ውስጥ ያገለግሉ ነበር እና አብዛኛውን ጊዜ ከልጆች ጋር ይመጡ ነበር። ከአንዳንዶቹ ጋር የተቆራኘው “የምርኮ ምርኮኞች” ኤፒሄት መነሻቸውን ያሳያል። አንዳንዶቹ የብሔር ስሞች ናቸው። በተለይም አንዱ፣ ፣ “የእስያ ሴቶችን” ይለያል።ምናልባት በእስያ ተይዘው ሊሆን ይችላል፣ነገር ግን ሌሎች ሚልጢያ፣ሚሊጢስ፣የግሪክ ቅኝ ግዛት የሆነችው፣በግሪኮች ለባሪያነት ያልተወረረች የሚሊጢን ይመስሉ ነበር። ቻድዊክ ስሞቹ እነዚህ የውጭ አገር ሴቶች የተገዙባቸውን ቦታዎች እንደሚመዘግቡ ይጠቁማል።ስሙም በነጠላ አስዊያ ነው፣ እሱም የአገሩን ስም እና ከዚያ የመጣች ሴትን ያመለክታል። የወንድነት ቅርጽ አለ, . ይህ አስዊያ በኬጢያውያን ዘንድ አሱዋ ተብሎ የሚጠራው፣ ልድያን ወይም "የሮማን እስያ"ን ያማከለ ክልል የተረፈ ይመስላል። ይህ ስም፣ አሱዋ፣ ለአህጉሪቱ “እስያ” መጠሪያ መነሻ ሆኖ ተጠቁሟል። የአሱዋ ሊግ በ1400 ዓክልበ አካባቢ በ1400 ዓ.ዓ አካባቢ በኬጢያውያን በቱድሃሊያ የተሸነፈ በምእራብ አናቶሊያ የግዛት ኮንፌዴሬሽን ነበር።
ክላሲካል ጥንታዊነት
የላቲን እስያ እና የግሪክ ተመሳሳይ ቃል ይመስላል። የሮማውያን ደራሲዎች እንደ እስያ ተርጉመዋል። ሮማውያን በምዕራብ አናቶሊያ (በአሁኗ ቱርክ) የምትገኝ እስያ ግዛት ብለው ሰየሙት። በዘመናዊቷ ኢራቅ ውስጥ ትንሽ እስያ እና እስያ ሜጀር ነበሩ። የስሙ የመጀመሪያ ማስረጃ ግሪክ እንደመሆኑ መጠን እስያ የመጣው ከ መሆኗ ሳይሆን አይቀርም፣ ነገር ግን ጥንታዊ ሽግግሮች፣ በሥነ-ጽሑፋዊ አውዶች እጥረት ምክንያት፣ በድርጊቱ ውስጥ ለመያዝ አስቸጋሪ ናቸው። በጣም የሚገመቱት ተሽከርካሪዎች እንደ ሄሮዶተስ ያሉ የጥንት ጂኦግራፊዎች እና የታሪክ ተመራማሪዎች ነበሩ ፣ ሁሉም ግሪክ ናቸው። የጥንት ግሪክ ቀደምት እና የበለጸገ የስሙን አጠቃቀም ያረጋግጣል።
የመጀመሪያው የእስያ አህጉራዊ አጠቃቀም ለሄሮዶቱስ (በ440 ዓክልበ. አካባቢ) የተነገረለት እሱ ስላፈለሰ ሳይሆን፣ ታሪኮቹ በማንኛውም ዝርዝር ሁኔታ ሊገልጹት ከቀደሙት ንባብ በመሆናቸው ነው። በጥንቃቄ ገልጾታል፣ ያነበበቸውን፣ አሁን ግን ሥራቸው የጠፋባቸውን የቀድሞ የጂኦግራፊ ባለሙያዎችን ጠቅሷል። በርሱም ከግሪክ እና ከግብፅ በተቃራኒ አናቶሊያ እና የፋርስ ኢምፓየር ማለት ነው።
ሄሮዶተስ የሦስት ሴቶች ስም “በተጨባጭ አንድ ለሆነ ትራክት የተሰጠ” (ኤውሮፓ፣ ኤዥያ እና ሊቢያ አፍሪካን በመጥቀስ) ለምን ሦስት የሴቶች ስሞች እንደተሰጡት ግራ እንዳጋባው ተናግሯል፣ አብዛኞቹ ግሪኮች እስያ የተሰየመችው በባለቤቱ ሚስት ስም እንደሆነ ገልጿል። ፕሮሜቴየስ (ማለትም ሄሲዮን)፣ ነገር ግን ልድያውያን ይህ ስም በሰርዴስ ላለው ነገድ ያስተላለፈው በኮቲስ ልጅ አሲየስ ነው ይላሉ። በግሪክ አፈ ታሪክ፣ “ኤዥያ” () ወይም “ኤሲ” () “የኒምፍ ወይም ታይታን የልድያ አምላክ” ስም ነበር።
በጥንቷ ግሪክ ሃይማኖት ቦታዎች ከጠባቂ መላእክት ጋር ተመሳሳይነት ባለው የሴት መለኮት ጥበቃ ሥር ነበሩ። ገጣሚዎቹ ተግባራቸውን እና ትውልዳቸውን በአምሳያ ቋንቋ ጨምረው በአስደሳች ታሪኮች ዘረዘሩ።ይህም ተከትሎ ተውኔት ደራሲያን ወደ ክላሲካል የግሪክ ድራማ ተለውጠው "የግሪክ አፈ ታሪክ" ሆነዋል። ለምሳሌ፣ ሄሲኦድ የቴቲስ እና የውቅያኖስን ሴት ልጆች ጠቅሷል፣ ከእነዚህም መካከል "ቅዱስ ኩባንያ"፣ "ከጌታ አፖሎ እና ወንዞች ጋር ወጣቶች በእጃቸው ያሉ" አሉ። ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹ ጂኦግራፊያዊ ናቸው-ዶሪስ, ሮዳ, ዩሮፓ, እስያ. ሄሲኦድ ያብራራል፡-
ሦስት ሺህ ንጹሕ ቁርጭምጭም የሌላቸው የውቅያኖስ ሴቶች ልጆች በሩቅና በሰፊ ተበታትነው ይገኛሉና፥ በየቦታውም ለምድርና ለጥልቁ ውኃ ያገለግላሉ።
ኢሊያድ (በጥንቶቹ ግሪኮች በሆሜር የተነገረው) በትሮጃን ጦርነት አሲዮስ በተባለው ጦርነት ሁለት ፍርጂያውያን (በሉቪያውያን የተካውን ነገድ) ጠቅሷል። እንዲሁም በሊዲያ ውስጥ ማርሽ እንደ የያዘ ማርሽ ወይም ቆላማ። ብዙ ሙስሊሞች እንደሚሉት፣ ይህ ቃል የመጣው የሙሴ አሳዳጊ እናት ከሆነችው ከጥንቷ ግብፅ ንግሥት እስያ ነው።
የእስያ ታሪክ እንደ የተለያዩ የባህር ዳርቻ ዳርቻዎች ታሪክ ሊታይ ይችላል-ምስራቅ እስያ ፣ ደቡብ እስያ ፣ ደቡብ ምስራቅ እስያ እና መካከለኛው ምስራቅ ፣ በመካከለኛው እስያ ረግረጋማ ውስጠኛ ክፍል የተገናኘ። የባህር ዳርቻው አካባቢ ለአንዳንድ የአለም ቀደምት የታወቁ ስልጣኔዎች መኖሪያ ነበር ፣እያንዳንዳቸውም ለም በሆነ የወንዝ ሸለቆዎች ዙሪያ ያደጉ። በሜሶጶጣሚያ፣ በኢንዱስ ሸለቆ እና በቢጫ ወንዝ የነበሩት ስልጣኔዎች ብዙ ተመሳሳይነት አላቸው። እነዚህ ስልጣኔዎች እንደ ሂሳብ እና ጎማ ያሉ ቴክኖሎጂዎችን እና ሀሳቦችን ተለዋውጠው ሊሆን ይችላል። እንደ ጽሑፍ ያሉ ሌሎች ፈጠራዎች በየአካባቢው በግለሰብ ደረጃ የተገነቡ ይመስላሉ. በእነዚህ ቆላማ አካባቢዎች የተገነቡ ከተሞች፣ ግዛቶች እና ኢምፓየሮች።
የመካከለኛው ስቴፕ ክልል ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የእስያ አካባቢዎች በፈረስ ላይ በተቀመጡ ዘላኖች ይኖሩ ነበር ። ከደረጃው ውስጥ በጣም ቀደምት የተለጠፈው መስፋፋት ኢንዶ-አውሮፓውያን ቋንቋቸውን ወደ መካከለኛው ምስራቅ፣ ደቡብ እስያ እና ቶቻሪያውያን ወደሚኖሩበት የቻይና ድንበሮች ያሰራጩ ናቸው። ሰሜናዊው የእስያ ክፍል፣ አብዛኛው ሳይቤሪያን ጨምሮ፣ ጥቅጥቅ ባለው ደኖች፣ የአየር ንብረት እና ታንድራ ምክንያት ለዳካ ዘላኖች በአብዛኛው ተደራሽ አልነበረም። እነዚህ አካባቢዎች በጣም ጥቂት ሰዎች አልነበሩም።
ማዕከሉ እና አከባቢዎቹ በአብዛኛው በተራሮች እና በረሃዎች ተለያይተዋል. የካውካሰስ እና የሂማላያ ተራሮች እንዲሁም የካራኩም እና የጎቢ በረሃዎች የእንጀራ ፈረሰኞች በጭንቅ ብቻ የሚሻገሩትን መሰናክሎች ፈጠሩ። የከተማው ነዋሪዎች በቴክኖሎጂ እና በማህበራዊ ደረጃ የላቀ ደረጃ ላይ የደረሱ ቢሆኑም፣ በብዙ አጋጣሚዎች የተጫኑትን የእግረኛ መንጋዎች ለመከላከል በወታደራዊ ዘርፍ ምንም ማድረግ አልቻሉም። ይሁን እንጂ ቆላማው አካባቢ ብዙ የፈረስ ጉልበትን የሚደግፍ በቂ ክፍት የሣር ሜዳዎች አልነበራቸውም; በዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች በቻይና፣ ህንድ እና መካከለኛው ምስራቅ ያሉትን ግዛቶች ያሸነፉ ዘላኖች ብዙውን ጊዜ ከአካባቢው እና ከበለጸጉ ማህበረሰቦች ጋር መላመድን አግኝተዋል።
የእስልምና ኸሊፋቶች የባይዛንታይን እና የፋርስ ግዛቶች ሽንፈት ወደ ምዕራብ እስያ እና የመካከለኛው እስያ ደቡባዊ ክፍሎች እና የደቡብ እስያ ምዕራባዊ ክፍሎች በ7ኛው ክፍለ ዘመን ወረራዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጓቸዋል። የሞንጎሊያ ኢምፓየር በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሰፊውን የእስያ ክፍል አሸንፎ ከቻይና እስከ አውሮፓ ድረስ ያለውን አካባቢ ያዘ። ከሞንጎል ወረራ በፊት የሶንግ ሥርወ መንግሥት ወደ 120 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች እንደነበሩ ይነገራል። ወረራውን ተከትሎ በተካሄደው 1300 የህዝብ ቆጠራ ወደ 60 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ሪፖርት አድርጓል።
በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ እጅግ አስከፊ ከሆኑት ወረርሽኞች አንዱ የሆነው ጥቁር ሞት በመካከለኛው እስያ በረሃማ ሜዳ ላይ እንደመጣ ይገመታል፣ ከዚያም በሃር መንገድ ተጉዟል።
የሩስያ ኢምፓየር ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ወደ እስያ መስፋፋት የጀመረ ሲሆን በመጨረሻም በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ሁሉንም ሳይቤሪያ እና አብዛኛው የመካከለኛው እስያ ክፍል ይቆጣጠራል። የኦቶማን ኢምፓየር አናቶሊያን፣ አብዛኛው መካከለኛው ምስራቅን፣ ሰሜን አፍሪካንና ባልካንን ከ16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ ተቆጣጠረ። በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን ማንቹ ቻይናን ድል በማድረግ የኪንግ ሥርወ መንግሥት አቋቋመ። እስላማዊው የሙጋል ኢምፓየር እና የሂንዱ ማራታ ኢምፓየር በ16ኛው እና በ18ኛው ክፍለ ዘመን እንደቅደም ተከተላቸው ህንድን በብዛት ተቆጣጠሩ። የጃፓን ኢምፓየር አብዛኛውን የምስራቅ እስያ እና አብዛኛው ደቡብ ምስራቅ እስያ፣ ኒው ጊኒ እና የፓሲፊክ ደሴቶችን እስከ ሁለተኛው የአለም ጦርነት ማብቂያ ድረስ ተቆጣጠረ።
የቻልኮሊቲክ ዘመን (ወይም የመዳብ ዘመን) የጀመረው በ4500 ዓ.ዓ ገደማ ነው፣ ከዚያም የነሐስ ዘመን በ3500 ዓክልበ ገደማ ጀመረ፣ የኒዮሊቲክ ባህሎችን በመተካት።
የኢንዱስ ሸለቆ ሥልጣኔ (አይቪሲ) የነሐስ ዘመን ሥልጣኔ ነበር (3300-1300 ዓክልበ. በሳል ጊዜ 2600-1900 ዓክልበ.) በዚህ ስልጣኔ ውስጥ ቀደምት የሂንዱይዝም አይነት እንደተደረገ ይቆጠራል። ከእነዚህ የስልጣኔ ታላላቅ ከተሞች መካከል ከፍተኛ የከተማ ፕላን እና ጥበባት የነበራቸው ሃራፓ እና ሞሄንጆ-ዳሮ ይገኙበታል። በ1700 ዓክልበ. አካባቢ የእነዚህ ክልሎች ውድመት መንስኤ አከራካሪ ነው፣ ምንም እንኳን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በተፈጥሮ አደጋዎች (በተለይ በጎርፍ) ነው። ይህ ዘመን በህንድ ውስጥ ከ1500 እስከ 500 ዓ.ዓ. አካባቢ ያለውን የቬዲክ ዘመንን ያመለክታል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የሳንስክሪት ቋንቋ አዳብሯል እና ቬዳስ ተጽፏል, ስለ አማልክት እና ስለ ጦርነቶች ተረቶች የሚናገሩ ድንቅ ዝማሬዎች. ይህ የቬዲክ ሃይማኖት መሠረት ነበር፣ እሱም በመጨረሻ የተራቀቀ እና ወደ ሂንዱይዝም የሚያድግ።
ቻይና እና ቬትናም የብረታ ብረት ሥራ ማዕከላት ነበሩ። ከኒዮሊቲክ ዘመን ጀምሮ፣ ዶንግ ሶን ከበሮ የሚባሉት የመጀመሪያዎቹ የነሐስ ከበሮዎች በ ትናም እና በደቡብ ቻይና በቀይ ወንዝ ዴልታ ክልሎች እና አከባቢዎች ተገኝተዋል። እነዚህ ከቬትናም ቅድመ ታሪክ ዶንግ ልጅ ባህል ጋር ይዛመዳሉ። ዘፈን ዳ የነሐስ ከበሮ ገጽ፣ ዶንግ ሶን ባህል፣ ቬትናም
በባን ቺያንግ፣ ታይላንድ (ደቡብ ምስራቅ እስያ) ከ2100 ዓክልበ. ጀምሮ የነሐስ ቅርሶች ተገኝተዋል።
በኒያንጋን የበርማ የነሐስ መሳሪያዎች ከሴራሚክስ እና ከድንጋይ የተሰሩ ቅርሶች ጋር ተቆፍረዋል። የፍቅር ጓደኝነት በአሁኑ ጊዜ ሰፊ ነው (3500-500 ዓክልበ.)
ጂኦግራፊ እና የአየር ንብረት
እስያ በምድር ላይ ትልቁ አህጉር ነው። ከምድር አጠቃላይ ስፋት 9 በመቶውን ይሸፍናል (ወይም ከመሬት ስፋቱ 30 በመቶው) እና ረጅሙ የባህር ዳርቻ ያለው ሲሆን በ62,800 ኪሎ ሜትር (39,022 ማይል)። እስያ በአጠቃላይ የዩራሺያን ምሥራቃዊ አራት-አምስተኛውን እንደያዘ ይገለጻል። ከሱዌዝ ካናል እና ከኡራል ተራሮች በስተምስራቅ እና ከካውካሰስ ተራሮች በስተደቡብ (ወይም ኩማ-ማኒች ዲፕሬሽን) እና ካስፒያን እና ጥቁር ባህሮች ይገኛሉ። በምስራቅ በፓስፊክ ውቅያኖስ ፣ በደቡብ በህንድ ውቅያኖስ እና በሰሜን በአርክቲክ ውቅያኖስ የተከበበ ነው። እስያ በ 49 አገሮች የተከፋፈለ ነው, ከእነዚህ ውስጥ አምስቱ (ጆርጂያ, አዘርባጃን, ሩሲያ, ካዛኪስታን እና ቱርክ) አቋራጭ አገሮች በከፊል በአውሮፓ ውስጥ ይገኛሉ. በጂኦግራፊያዊ አገላለጽ ሩሲያ በከፊል በእስያ ውስጥ ትገኛለች, ነገር ግን በባህላዊ እና በፖለቲካዊ መልኩ እንደ አውሮፓውያን ሀገር ይቆጠራል.
የጎቢ በረሃ ሞንጎሊያ ውስጥ ሲሆን የአረብ በረሃ አብዛኛውን የመካከለኛው ምስራቅን ክፍል ያቋርጣል። በቻይና የሚገኘው ያንግትዜ ወንዝ በአህጉሪቱ ረጅሙ ነው። በኔፓል እና በቻይና መካከል ያለው ሂማላያ በዓለም ላይ ካሉት የተራራ ሰንሰለቶች ሁሉ ረጅሙ ነው። ሞቃታማው የዝናብ ደኖች በአብዛኛው የደቡባዊ እስያ ክፍል ላይ ተዘርግተው የተንሰራፋ ሲሆን ሾጣጣ እና ደረቅ ደኖች በሰሜን በኩል ይገኛሉ.
የአየር ንብረት
እስያ በጣም የተለያየ የአየር ንብረት ባህሪያት አላት. የአየር ንብረት በሳይቤሪያ ከአርክቲክ እና ከሱባርክቲክ እስከ ደቡባዊ ህንድ እና ደቡብ ምስራቅ እስያ ሞቃታማ የአየር ጠባይ ይደርሳል። በደቡብ ምስራቅ ክፍሎች ላይ እርጥብ ነው ፣ እና በብዙ የውስጥ ክፍል ውስጥ ደረቅ ነው። በምድር ላይ ካሉት ትላልቅ የቀን ሙቀት ክልሎች መካከል አንዳንዶቹ በምዕራባዊ እስያ ክፍሎች ውስጥ ይከሰታሉ። የዝናብ ስርጭት በደቡባዊ እና ምስራቃዊ ክፍሎች ላይ የበላይነት አለው፣ ምክንያቱም ሂማላያ በመኖሩ በበጋ ወቅት እርጥበትን የሚስብ ዝቅተኛ የሙቀት መጠን እንዲፈጠር ያስገድዳል። የአህጉሪቱ ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች ሞቃት ናቸው። ሳይቤሪያ በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ ውስጥ በጣም ቀዝቃዛ ከሆኑት ቦታዎች አንዱ ነው, እና ለሰሜን አሜሪካ የአርክቲክ የአየር ብዛት ምንጭ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል. ለትሮፒካል አውሎ ንፋስ እንቅስቃሴ በምድር ላይ በጣም ንቁው ቦታ ከፊሊፒንስ ሰሜናዊ ምስራቅ እና ከጃፓን ደቡብ ይገኛል።
እ.ኤ.አ. በ 2010 በአለምአቀፍ ስጋት ትንተና ፋርም ማፕሌክሮፍት የተደረገ ጥናት 16 ለአየር ንብረት ለውጥ በጣም የተጋለጡ ሀገራትን ለይቷል ። የእያንዳንዱ ሀገር ተጋላጭነት የሚሰላው በሚቀጥሉት 30 ዓመታት ውስጥ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖ ያላቸውን 42 ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ አመልካቾችን በመጠቀም ነው። የእስያ አገሮች ባንግላዲሽ፣ህንድ፣ፊሊፒንስ፣ቬትናም፣ታይላንድ፣ፓኪስታን፣ቻይና እና ሲሪላንካ በአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ስጋት ካጋጠማቸው 16 አገሮች መካከል ይገኙበታል።አንዳንድ ለውጦች እየታዩ ነው። ለምሳሌ፣ በህንድ ሞቃታማ አካባቢዎች ከፊል ደረቃማ የአየር ጠባይ ባለባቸው አካባቢዎች፣ ከ1901 እስከ 2003 ባለው ጊዜ ውስጥ የሙቀት መጠኑ በ0.4 ዲግሪ ሴልሲየስ ጨምሯል። እ.ኤ.አ. በ2013 በአለም አቀፉ የሰብል ምርምር ኢንስቲትዩት ለከፊል-በረሃማ ትሮፒክስ () የተደረገ ጥናት ሳይንስን ለማግኘት ያለመ- የእስያ የግብርና ሥርዓቶች የአየር ንብረት ለውጥን እንዲቋቋሙ የሚያስችላቸው፣ ድሆችን እና አቅመ ደካሞችን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ድሆችን የሚደግፉ አቀራረቦች እና ቴክኒኮች። የጥናቱ ምክረ ሃሳቦች የአየር ንብረት መረጃ አጠቃቀምን ከማሻሻል እና የአየር ንብረትን መሰረት ያደረጉ የግብርና ምክር አገልግሎቶችን ከማጠናከር፣ የገጠር ቤተሰብን ገቢ ብዝሃነትን ከማበረታታት እና አርሶ አደሩ የደን ሽፋንን ለማሳደግ፣ የከርሰ ምድር ውሃን ለመሙላት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ርምጃዎችን እንዲወስድ ማበረታቻ መስጠት ነው። ታዳሽ ኃይልን ይጠቀሙ.
የደቡብ ምስራቅ እስያ መንግስታት () አሥሩ አገሮች - ብሩኒ ፣ ካምቦዲያ ፣ ኢንዶኔዥያ ፣ ላኦስ ፣ ማሌዥያ ፣ ምያንማር ፣ ፊሊፒንስ ፣ ሲንጋፖር ፣ ታይላንድ እና ቬትናም - በዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖዎች በጣም የተጋለጡ ናቸው ። ሆኖም የኤኤስያን የአየር ንብረት ቅነሳ ጥረቶች ከተጋረጡበት የአየር ንብረት አደጋዎች እና አደጋዎች ጋር የተመጣጠኑ አይደሉም።
|
16131
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A6%E1%88%AD%E1%8A%A8%E1%8A%93%20%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8B%9D
|
ቦርከና ወንዝ
|
ቦርከና ወንዝ በኢትዮጵያ፤ ወሎ ክፍለ ሀገር በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች የሚገኝ ታዋቂ ወንዝ ነው። ይህ ወንዝ የሚገብረው ለአዋሽ ወንዝ ነው።
የኢትዮጵያ ወንዞች
ከኩታበር ከተማ ነው የሚጀምረው።
የቦርከና ወንዝ ከሰሜን ወደ ደቡባዊ አቅጣጫ ደሴን፣ኮምቦልቻን፥ሀርቡንናከሚሴን እየሰነጠቀ በመፍሰስ ከሚሴ ከተማን ጥቂት እንዳለፈ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ ፊቱን በማዞር ቁልቁል ወደ አፋር ምድር ይንደረደራል ።
|
41366
|
https://am.wikipedia.org/wiki/1%20%E1%88%B3%E1%89%A3
|
1 ሳባ
|
1 ሳባ በጥንታዊ የኢትዮጵያ ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ ከንጉሥ ሆርካም ቀጥሎና ከንጉሥ ሶፋሪድ አስቀድሞ ለ30 ዓመታት የኩሽ መንግሥት (ኢትዮጵያ) ንጉሥ ነበረ። የነገሠበት ዘመን በየምንጩ የሚለያይ ነው፤ ለምሳሌ በተክለጻድቅ መኩሪያ ዝርዝር ከ2375 እስከ 2345 ዓክልበ. ነበረ። በሌላ ቁጠራ ከ2094 እስከ 2064 ዓክልበ. ነገሠ።
አለቃ ታዬ እንደ ጻፈው በ15ኛ ዓመቱ በግብጽና በሱዳን ላይ ረሃብ ስለ ጸና ከከነዓን ልጆች የሰማሪዎን (ሳምሪ) ተወላጅ ዋቶ እና ነገዱ (ወይጦ) ወደ ኩሽ ገቡ።
የኢትዮጵያ ነገሥታት
|
19881
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%88%A9%E1%8A%AD%20%E1%88%B5%E1%8D%92%E1%8A%96%E1%8B%9B
|
ባሩክ ስፒኖዛ
|
ባሩክ ስፒኖዛ (ህዳር 24፣ 1632 – የካቲት 21፣ 1677) የደች ፈላስፋ ሲሆን አመጣጡም ከፖርቱጋል አይሁድ ቤተሰብ ነበር። ባሩክ ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ታላላቅ የምክኑያዊነት ፈላስፋወች አንዱ እንደሆነ ስምምነት አለ። ሌሎች የዘመኑ ምክኑይዊነት አራማጆች ሌብኒዝ እና ደካርት ይጠቀሳሉ።
የህይወት ታሪክ
የስፒኖዛ አስተሳሰቦች በአይሁድ ህብረተሰብ ዘንደ የተጠላ ነበር። ስለሆነም በ1656 ከህብረተስቡ እንዲገለል ተደርጎ ነበር።
ቁልፍ ሐሳቦች
የስፒኖዛ ዋና ሃሳብ አምላክ እና ተፈጥሮ አንድ ናቸው የሚል ነበር። ተፈጥሮ ማለቱ እዚህ ላይ ማንኛው ህልው ነገር (ያለ ነገር) ይጠቀልላል። በጊዜው ይሰራበት የነበረውን የአዕምሮ እና አንጎል ክፍፍልን በመካድ ሁለቱም የአንድ አምላክ አዕላፍ ክፍላት አባል ናቸው አዋህዷል።
በተፈጥሮ ውስጥ ሰናይም ሆነ ዕኩይ የሆነ ነገር የለም ። ሰናይና እኩይ ትርጉም ያላቸው ለሰው ልጆች ብቻ ነው በማለት አስረድቷል። ለሰው ልጆች አንድ ኩነት (ክስተት) ሰናይ የሚሆነው ወደ ደስታ የሚመራው ሲሆን እና እኩይ የሚሆነው ደግሞ ለሃዘን ሲዳርገው ነው ብሎ አስረድቷል።
ስፒኖዛ ሁለት አይነት የሰው ልጅ አስተሳሰቦችንና ስሜቶችን ገልጿል፡
አንደኛው ተነሳሽ ሲባል፣ አንድ ሰው ከራሱ አመንጭቶ የሚፈጽመውን ተግባር ይገልጻል። አንድን ሰው የራሱን ተግባር በበለጠ በተረዳ ቁጥር፣ የበለጠ ተነሳሽ ይሆናል። ተነሳሽ ስሜቶች ለደስታና አምላክን ለማወቅ እንዲሁም ነጻነትን ለመቀዳጀት ያበቃሉ።
ሁለተኛው ፈዛዛ ሲባል፣ አንድ ሰው በሌሎች ሰወች ተፅዕኖ ስር ሲወድቅ ነው።
እንደ ስፒኖዛ አስተሳሰብ የሁሉ ሰው ግብ አምላክን በማወቅ መውደድ ነው (በሌላ አነጋገር፣ ተፈጥሮን በተቻለ መጠን ማውቅና መረዳት ነው)።
|
3284
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B3%E1%88%9C
|
ቅዳሜ
|
ቅዳሜ ከአርብ ቀጥሎ የሚገኝ የሣምንቱ የመጨረሻ ቀን ነው። አይሁድእና ሰባተኛ ቀን አድቬንቴስት ቤተክርስቲያን ሰንበትን የሚያከብሩበት ቀን ነው። እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ ከከርስቶስ ትንሳኤ በኋላ «ትልቁ» የሰንበት በአላቸው እሁድ ቢሆንም ቅዳሜንም «ቀዳሚ ሰንበት» በማለት ያከብራሉ። ስንበትን የሚያከብሩ ክርስትያኖችም ስላሉ ኣይህዶች የሚያከብሩት ቀን ነው ማለቱ ትክክል ኣይሆንም። ገና ኣይህዶች ሳይፈጠሩ ሰንበት ለሰው ተሰጠ ለኣዳምና ለሂዋን። ሰንበት የተጀመረው ገና ሃጢኣት በዚህ ኣለም ሳይገባ በኤደን ገነት ነበረ። ሰንበት የቃሉ መሰረት ሰባት ነው ። መጽሃፍ ቅዱስ ቅዳሜን ነው ሰንበት በሎ የሚጠራው እሁድን ኣይደለም።
|
52332
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%BB%E1%8A%95%E1%8C%8B%E1%8B%AD
|
ሻንጋይ
|
ሻንጋይ ቻይንኛ: ፣ የሻንጋይ አጠራር (የድምጽ ተናጋሪ )፣ መደበኛ ማንዳሪን አጠራር፡ [] (የድምጽ ማጉያ አዶሊስተን)) በቀጥታ ከሚተዳደሩ አራት ማዘጋጃ ቤቶች አንዱ ነው። የቻይና ህዝብ ሪፐብሊክ።[ሀ] ከተማዋ በያንግትዝ ወንዝ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ ትገኛለች፣ የሁአንግፑ ወንዝ በውስጡ ይፈስሳል። እ.ኤ.አ. በ2020 24.87 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ፣ በቻይና ውስጥ በሕዝብ ብዛት ያለው የከተማ አካባቢ ፣ በዓለም ላይ በጣም በሕዝብ የሚኖርባት ከተማ እና በምስራቅ እስያ ውስጥ ካሉት ዋና ከተማዎች የበለጠ የሀገር ውስጥ ምርት ያላት ብቸኛዋ ከተማ ነች። ሻንጋይ የፋይናንስ፣ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ምርምር፣ትምህርት፣ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ማኑፋክቸሪንግ፣ቱሪዝም፣ባህልና ማጓጓዣ ማዕከል ሲሆን የሻንጋይ ወደብ ደግሞ የዓለማችን እጅግ የተጨናነቀ የኮንቴይነር ወደብ ነው።
በመጀመሪያ የዓሣ ማጥመጃ መንደር እና የገበያ ከተማ ሻንጋይ በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን በአገር ውስጥ እና በውጭ ንግድ እና ምቹ የወደብ አቀማመጥ ምክንያት ጠቃሚነት አደገ። ከተማዋ ከመጀመሪያው የኦፒየም ጦርነት በኋላ ለአውሮፓ ንግድ ለመክፈት ከተገደዱ አምስት የስምምነት ወደቦች አንዷ ነበረች። የሻንጋይ ኢንተርናሽናል ሰፈራ እና የፈረንሳይ ኮንሴሽን በመቀጠል ተቋቋሙ። ከተማዋ ያበለፀገች ሲሆን በ1930ዎቹ የእስያ ዋና የንግድ እና የፋይናንስ ማዕከል ሆናለች። በሁለተኛው የሲኖ-ጃፓን ጦርነት ከተማይቱ የሻንጋይ ዋና ጦርነት ቦታ ነበረች። ከጦርነቱ በኋላ በ1949 ኮሚኒስቶች ዋናውን ምድር ከተቆጣጠሩ በኋላ የንግድ ልውውጥ በሌሎች የሶሻሊስት አገሮች ብቻ ተወስኖ የከተማዋ ዓለም አቀፍ ተጽእኖ ቀንሷል።
እ.ኤ.አ. በ 1990 ዎቹ ፣ በዴንግ ዚያኦፒንግ ከአስር አመታት በፊት ያካሄዱት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች የከተማዋን በተለይም የፑዶንግ አዲስ አካባቢን መልሶ ማልማት አስከትለዋል ፣ ይህም የገንዘብ እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመመለስ ይረዳል ። ከተማዋ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የዓለም አቀፍ ንግድ እና ፋይናንስ ማዕከል ሆና ብቅ አለች; በገቢያ ካፒታላይዜሽን በዓለም ላይ ካሉት ትልቁ የአክሲዮን ልውውጦች አንዱ የሆነው የሻንጋይ ስቶክ ገበያ እና የሻንጋይ ነፃ-ንግድ ዞን በዋናው ቻይና የመጀመሪያው ነፃ የንግድ ቀጠና ነው። እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ፣ ሻንጋይ በግሎባላይዜሽን እና የዓለም ከተሞች የምርምር አውታረ መረብ እንደ አልፋ+ (አለምአቀፍ የመጀመሪያ ደረጃ) ከተማ ተመድባለች እና በአለም አቀፍ የፋይናንሺያል ከኒውዮርክ ሲቲ እና ለንደን በስተጀርባ 3ኛ ተወዳዳሪ እና ትልቁ የፋይናንስ ማዕከል ተብላለች። የማዕከሎች መረጃ ጠቋሚ. በዓለም ላይ ካሉ ከማንኛውም ከተማዎች ትልቁ የሜትሮ አውታረ መረብ አለው ፣ በዓለም ላይ ካሉ ከማንኛውም ከተማዎች ስድስተኛ-ከፍተኛ የቢሊየነሮች ብዛት ፣ በዓለም ላይ ካሉት ከተሞች አምስተኛው ትልቅ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ፣ አምስተኛው ትልቁ የሳይንስ ምርምር ውጤት ከማንኛውም ከተማ። በዓለም ላይ ያለች ከተማ እና ከፍተኛ ደረጃ ያላቸው የትምህርት ተቋማት ፉዳን ዩኒቨርሲቲ ፣ ሻንጋይ ጂያኦ ቶንግ ዩኒቨርሲቲ ፣ ቶንግጂ ዩኒቨርሲቲ ፣ ምስራቅ ቻይና መደበኛ ዩኒቨርሲቲ ፣ ሻንጋይ ዩኒቨርሲቲ ፣ የሻንጋይ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚክስ ፣ እና የምስራቅ ቻይና የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ።
የሻንጋይ ኢኮኖሚ እያደገ የመጣውን የቻይና ‹የማሳያ ማሳያ› ተብሎ ተገልጿል ። እንደ አርት ዲኮ እና ሺኩመን ያሉ በርካታ የስነ-ህንፃ ቅጦችን የያዘ ከተማዋ በሉጂአዙይ የሰማይ መስመር፣ ሙዚየሞች እና የከተማ አምላክ መቅደስ፣ ዩ ጋርደን፣ የቻይና ድንኳን እና በቡንድ ዳር ያሉ ህንጻዎች ዝነኛ ሆና ትታወቃለች፣ ይህም የምስራቃዊ ፐርል ቲቪ ታወርን ያካትታል። ሻንጋይ በስኳር በበዛባቸው ምግቦች፣ ልዩ የሀገር ውስጥ ቋንቋ እና ደማቅ አለምአቀፋዊ ጨዋነት ትታወቃለች። እንደ አስፈላጊ ዓለም አቀፍ ከተማ ሻንጋይ የአዲሱ ልማት ባንክ መቀመጫ ናት በ ግዛቶች የተቋቋመው ባለብዙ ወገን ልማት ባንክ እና ከተማዋ በየዓመቱ ከ 70 በላይ የውጭ ተወካዮችን እና በርካታ አገራዊ እና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን ያስተናግዳል, ለምሳሌ የሻንጋይ ፋሽን ሳምንት, የቻይና ግራንድ ፕሪክስ እና ቻይናጆይ። ሻንጋይ በአለም ላይ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኝ የቱሪስት ከተማ ነች፣ በአለም ሰባተኛ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴሎች፣ እና በአለም ላይ ሁለተኛው ረጅሙ ህንፃ የሻንጋይ ታወር። እ.ኤ.አ. በ 2018 ሻንጋይ የመጀመሪያውን የቻይና ዓለም አቀፍ አስመጪ ኤክስፖ () አስተናግዶ ነበር፣ በዓለም የመጀመሪያው የማስመጣት ጭብጥ ያለው ብሄራዊ ደረጃ ኤክስፖ።
ሥርወ ቃል
|
15651
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%80%E1%8C%89%E1%88%AD
|
ፀጉር
|
ፀጉር በፕሮቲን የበለጸገ ከተባለ የሰውነት ክፍል ማደግ የሚጀምር አካል ነው። ይህ አካል በተለይም ኬራቲን () ከተባለው የፕሮቲን አይነት የተገነባ ነው። በአብዛሃኛው ጊዜ ፀጉር የአጥቢ እንስሳት መለያ ቢሆንም በአንዳንድ ነፍሳት ላይ ይታያል፤ ይህ ግን በሳይንስ ፀጉር አይባልም።
ጽጉር በእጅ ሲጐተት ከአይን እስከሚታይ ድረስ ያለመረዘሙ ለወንዶች የሚለው ደንብ፣ የተነሣ በፍትሐ ነገሥት ቀኖኖች ይገኛል ፤ «ጠጉርህ በአፍኣ በውጭ አይታይ» (ኢያስተርኢ ሥዕርትከ በአፍኣ) ሲል፤ በ1958 ዓም በብርሃንና ሰላም በታተመው በድሮ ፎቶ ኦፍሴት አማርኛ ነጥቦች ዘንድ፣ ይህ ማለት በገዛ እጅህ ተጎትቶ የራስህ ጽጉር ወይንም ሪዝህ በአይንህ እንዳይታይ የሚል ደንብ ነበር። (አለበለዚያ ለናዝራዊ ወይም ለባሕታዊ ለመኖኩሴ ግን የተፈጥሮ ጉንጉኖች ሥርዓት ከሙሴ አለ።) በእስልምና መጻሕፍት በተለይ ለጥቁሮች የተለየ ልምድ ኖሯል፣ በዚህም በኩል የወንድ ጸጉር ከጆሮ ይልቅ እንዳይዘረጋው የሚል ነው።
ተጨማሪ ይዩ
ሥነ አካል
ሥነ ሕይወት
|
13098
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%8C%E1%88%8A%E1%89%B5
|
ሌሊት
|
ሌሊት ፀሐይ ከጠለቀችበት እስከምትወጣበት ያለው ጊዜ ነው። ይህ ማለት ነጠላ ኮከብ ስለ ሆነ የፈለክዋ ግማሽ በራስዋ ጥላ ስትሆን ነው። ምድር በ፳፬ ሰዓት ውስጥ እየዞረች ነጠላ ፀሐይ እያላት በስተኋላው ጥላ ወይም ሌሊት ይሆናል ማለት ነው።
የፀሐይ ጮራ በጠፈር ተጉዞ ወደ ምድር የሚያንጸባርቀው እቃ እንደ ጨረቃ ሲነካ፣ ይበራል። የብርሃን ፎቶኖች እቃውን ሳይደርሱ ግን ወደ አይኑ አቅጣጫ ስለማይጓዙ አይታዩም፣ ስለዚህ በጨረቃ ዙሪያ ጮራ ቢኖርም ከምድር ጥቁር ብቻ ሊታይ ይቻላል።
|
13273
|
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B5%E1%88%8D%E1%8C%AB
|
ድልጫ
|
ድልጫ ህጻናት በክረምት ወራት የሚጫወቱት ጨዋታ ሲሆን፣ ዝናብ ከጣለ በኋላ የሰፈር ልጆች ተሰብስበው አንድ ምቹ ቦታ መርጠው ጭቃውን በማለስለስ ረጅም መስመር ይሰራሉ። ከዚያ ተራ በተራ ተንደርድረው መስመሩ ላይ በመንሸራተት በከፍተኛ ርዝመት የተንሸራተተ አሸናፊ ይሆናል። ይህ ጨዋታ ህጻናትን ለስራ የሚያነሳሳ፣ አካልዊ ጥንካሬን የሚያስተምርና ብሎም አብሮ መስራትን የሚያስተምር ነው።
ወላጆች የሚጠሉት የልጆቹ ልብስ በጭቃ ስለሚበላሽ ብቻ ነው።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.