Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet Duplicate
id
stringlengths
4
5
url
stringlengths
38
537
title
stringlengths
2
65
text
stringlengths
3.43k
241k
39063
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%98%E1%88%B5%E1%8C%88%E1%8A%95%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%AC
ተመስገን ገብሬ
ተመስገን ገብሬ የተወለዱት በጎጃም ጠቅላይ ግዛት በደብረ ማርቆስ ከተማ በ፲፱፻፪ ዓ/ም ነው፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ የቤተ ክህነት ትምህርት ተከታትለዋል፡፡ ቤተሰባቸው ካህናት ከመሆናቸውም በላይ ጎበዝ ተማሪ ነበሩ። ጉብዝናቸው በዘመናዊ ትምህርት ሲከታተሉም ጎልቶ ወጥቷል፡፡ ከጎጃም አዲስ አበባም በመምጣት በስዊድን]] ሚሲይናዊ ትምህርት ቤት ተማሩ በወቅቱ ሀገሪቱ ካፈራቻቸው ጎበዝ ተማሪዎች አንዱ ነበሩ፡፡ ተመስገን በጋዜጠኝነት ሙያ ከመሥራታቸውም በላይ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ቦታ ተመድበው አገልግለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በኢጣሊያ በተወረረችበት ወቅት በአርበኝነት ከጠላት ጋር ተፋልመዋል፡፡ በኋላም ወደ ሱዳን ተሰደው ገዳሪፍ ውስጥ እያሉ ኢትዮጵያዊያንን በልዩ ልዩ መልክ አስተምረዋል፡፡ ጣሊያን ከለቀቀች በኋላ የዘመናዊ አስተሳሰብና ዕድገት ዓላማዋ ዕውን እንዲሆንም ፍፁም የለውጥ አርበኛ ሆነው ሠርተዋል። ተመስገን፣ ኅዳር ፳፪ ቀን ፲፱፻፵፩ ዓ/ም በ አዲስ አበባ ነፃነት ማተሚያ ቤት “የጉለሌው ሰካራም” በሚል ርዕስ ያሳተሙት ድርሰታቸው የመጀመሪያው፣ የታተመ የአማርኛ አጭር ልብ-ወለድ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ የጉለሌው ሰካራም ከመታተሙ በፊት ስለ የካቲቱ ፋሺስታዊ ጭፍጨፋ (ግፊቱን በቀመሱት አርበኛው ደራሲ አገላለጽ፣ ‹‹ዓለም በድንገት ተለውጣ፣ አዲስ አበባም ኢጣሊያኖች ኢትዮጵያውያንን የሚያርዱበት ቄራ ሆና ነበር፡፡››) “የካቲት ፲፪” በሚል ርዕስ እና “ሊቀ-ጠበብት እውነቱ” የተሰኙ ሁለት አጫጭር ልብወለዶችን በጋዜጣ ላይ አውጥተዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ‹‹ሕይወቴ›› የተሰኘውን ግለታሪካቸውን ያዘጋጁት አርበኛው አቶ ተመስገን ገብሬ በአምስቱ ዓመት የፋሺስት ወረራ ጊዜም በደረሱት ‹‹በለው በለው አትለውም ወይ፤ የጥቁር አንበሳ አይደለህም ወይ›› በሚለው መዝሙራቸውም ይታወሳሉ፡፡ ማጣቀሻ እና ዋቢ ምንጮች የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች በየአመቱ የካቲት 12 ቀን ሲደርስ ከማስታውሳቸው የዚህች አገር ባለውለተኞች መካከል ተመስገን ገብሬ አንዱ ነው፡፡ ይህ ሰው ሀገሩ ኢትዮጵያ በፋሽስቶች እንዳትወረር ብዙ ትግል አካሂዷል፡፡ ከወረራው በኋላም በአርበኝነት ተሰማርቶ የፋሽስቶችን ግብአተ-መሬት ካፋጠኑ የኢትዮጵያ ታላላቅ ደራሲያን መካከል ከግንባር ቀደሞቹ አንዱ ነው፡፡ ተመስገን ገብሬ በ1901 ዓ.ም ጐጃም ደብረማርቆስ ከተማ ነው የተወለደ፡፡ ታህሳስ 15 ቀን 1941 ዓ.ም በ40 ዓመቱ አረፈ፡፡ በትምህርቱ እጅግ ጐበዝ የሚባል በመሆኑ ገና በ15 ዓመቱ የቅኔ መምህር ሆኖ ነበር፡፡ በቤተ-ክህነት ትምህርት በዚህ እድሜ የቅኔ መምህር የሆነ ሰው ከተመስገን ሌላ አልተገኘም ይባላል፡፡ ይህ ሰው በ1918 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ መጥቶ የዘመናዊ ትምህርቱን በስዊድሽ ሚስዮን ተከታትሎ ጨርሷል፡፡ በ1920ዎቹ ውስጥ ጣሊያን ኢትዮጵያን ከመውረሯ በፊት ወረራው ለኢትዮጵያ እንደማይቀር በማወቅ በየአደባባዩ ሕዝብን እየሰበሰበ አንድ እንዲሆንና ጠላትን እንዲመክት ያስተምር ነበር፡፡ በአንድነቷ የጠነከረች ኢትዮጵያን ለመመስረት ብርቱ ትግል አድርጓል፡፡ ተመስገን የኤርትራ ድምፅ የሚሰኝ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅም ነበር፡፡ የአልጋ ወራሽ አስፋው ወሰን ኃይለስላሴ የቤት ውስጥ መምህርም ነበር፡፡ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው አጭር ልቦለድ የሚባለው የጉለሌው ሰካራም መጽሐፍም ደራሲ ነው፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ችሎታውና በአፃፃፍ ቴክኒኩ እጅግ የተዋጣለት ደራሲ መሆኑን ሃያሲያን ይናገራሉ፡፡ ተመስገን ገብሬ በኢጣሊያ ወረራም በፋሽስቶች ሊገደሉ ከሚፈለጉ ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዱ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም አብርሃ ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶም ግራዚያኒ ላይ ቦምብ ወርውረው ካቆሰሉት በኋላ ፋሽስቶች 30 ሺ ያህል የሚገመት የአዲስ አበባን ሕዝብ ጨፍጭፈዋል፡፡ ጣሊያኖች እነ አብርሀ ደቦጭ ግራዚያኒን ለመግደል ያሴሩት በተመስገን ገብሬ ግፊት ነው ብለው በማመናቸው በዋና ጠላትነት ይፈልጉት ነበር፡፡ በዚያን ወቅት ተመስገንም በአጋጣሚ በፋሽስቶች እጅ ይወድቃል፡፡ ግን ተመስገን ገብሬ መሆኑን አላወቁም፡፡ ስሙን ሸሸጋቸው፡፡ እሱንም ሊገድሉት እስር ቤት ባስገቡት ወቅት ጣሊያኖች ኢትዮጵያዊያኖችን ሲጨፈጭፉ በዓይኑ አይቷል፡፡ ከዚህም ጭፍጨፋ በተአምር አምልጦ ወደ ሱዳን ይሰደዳል፡፡ ተመስገን ገብሬ ይህን የየካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም የተደረገውን ጭፍጨፋ እና በአጠቃላይ በርሱ ሕይወት ዙሪያ ያለውን ውጣ ውረድ ሕይወቴ በሚል ርዕስ ፅፎታል፡፡ ይህን መጽሀፍ በ2000 ዓ.ም የአርትኦት ስራውን የሰራነውና እንዲታተም ያደረግነው እኔ እና ደረጀ ገብሬ እንዲሁም የተመስገን ገብሬ ልጅ ሲስተር ክብረ ተመስገን መሆናችንን በዚህ አጋጣሚ መጥቀስ እወዳለሁ፡፡ ከዚሁ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰነውን ክፍል በመውሰድ በወቅቱ ምን ዓይነት ግፍ እንደተፈፀመ ለማስታወስ እሞክራለሁ፡፡ ተመስገን ጭፍጨፋውን በተመለከተ በወቅቱ ለንደን ለሚገኙት ለጃንሆይም ያየውን ጽፎላቸው ሲያነቡት አልቅሰዋል፡፡ ምን ይሆን ለጃንሆይ የፃፈላቸው? ከብዙ በጥቂቱ የሚከተለውን ይመስላል፡- “ከሦስት ቀን የከተማ ጥፋት በኋላ ከሆለታ የመጡ የፋሽስት አውሬዎች በሚመለሱበት ካሚዮን በኋላው በኩል አቶ አርአያን እግራቸውን ጠርቅመው አሰሯቸው፡፡ ካሚዮኑ ሳይጐትታቸው “እኔ ወደ ሰማይ እንድገባ ሰማይ ተከፍቶ ይጠብቀኛል፡፡ እየሱስንም በዚያ አየዋለሁ፡፡ ደስ ይለኛል፡፡ ደስ ይለኛል፡፡ ደስ ይለኛል!” የሚለውን የሚሲዮን መዝሙር ዘመሩ፡፡ ፋሽስቶቹም የተሻለውን መዝሙር ብትሰማ ይሻልሃል አሏቸውና ዱኪ ዱኪ የሚለውን መዝሙራቸውን ዘመሩ፡፡ ካሚዮኑም ሞተሩን አስነስቶ ሲነዳ ታስረው ቁመው ነበርና ያን ጊዜ ዘግናኝ አወዳደቅ አቶ አርአያ ወደቁ፡፡ ካምዮኑም እየፈጠነ ጐተታቸው፡፡ ከአዲስ አበባ እስከ ሆለታ አርባ ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ ካምዮኑ ከዚያ ሲደርስ ያ ከካሚዮኑ ጋር የታሰረው እግራቸው ብቻ እንደተንጠለጠለ ነበርና የካሚዮኑ ነጂ ከካሚዮኑ ፈታና ለውሾች ወረወረው፡፡ እኔንም ያለሁበትን ቤት ሰብረው ከዚያ ቤት ያለነውን አውጥተው ከየመንደሩም ሕዝቡን አጠራቅመው ኑረዋል፡፡ ከዚያም መሐል ጨመሩን፡፡ ስምንት መትረየስ በዙሪያችን ጠምደዋል፡፡ በዚያም ቦታ ቁጥራቸው በብዙ የሆኑ ሐበሾችን አስቀድመው ገለዋቸዋል፡፡ ሬሣቸውም ተቆላልፎ በፊታችን ነበረ፡፡ እኛንም በዚያ ሊገድሉን ተዘጋጁ፡፡ ለመትረየስም ተኩስ እንድንመች ያንዳችንን እጅ ካንዱ ጋር አያይዘው አሰሩን፡፡ አሥረውን ወደ መተኰሱ ሳይመለሱ አንድ ታላቅ ሹም መጣ፡፡ የርሱም ፖለቲካ ልዩ ነበረ፡፡ ፋሽስቶች የሚያደርጉትን የሰላማዊ ሕዝብ መግደል፤ ሕፃናቶችን ከአባትና እናታቸው ጋራ በቤት ዘግቶ ማቃጠል መልካም ብሎ ቢወድ እንኳን እኒያ ቦምብ በቤተ-መንግስቱ ስብሰባ የወረወሩት ሐበሾች ሳይታወቁ እንዲቀሩ አይወድም ነበርና ስለዚህ ካሚዮኖች ይዞ እየዞረ ፋሽስቶች የሚገድሉትን እያስጣለ ወደ እስር ቤት ለምርመራ ይወስድ ኑረዋል፡፡ እኛንም እንዲተኮስብን ታሰረን ከቆምንበት ከቅዱሰ ጊዮርጊስ ጠበል አጠገብ ካለው ሸለቆ እስራታችንን አስፈትቶ በአምስተ ረድፍ ወደላይኛው መንገድ ለመድረስ ስንሄድ በአካፋ ራሳቸውን የተፈለጡ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ ምራቄ ደረቀ፡፡ በካሚዮኑ ወደ እስር ቤት አስወሰደን፡፡ ለጊዜው እስር ቤት ያደረጉት ማዘጋጃ ቤትን ነበር፡፡ ከማዘጘጃ ቤቱ በር ስንደርስ በአምስት ካምዮን ያጠራቀመንን ሰዎች በዋናው መንገድ እንድንቆም አዘዘን፡፡ ዙሪያችንንም ከበው በሳንጃ እየወጉን ጨፍቅ ብለን በመንገዱ ቆምን፡፡ ከወደኋላችን ትልቁን የጣሊያን ካሚዮን በላያችን ላይ ነዱብን፡፡ አስራ ስምንት ቆስለው አልተጨረሱም፤በሳንጃ ጆሮአቸውን ወጓቸው፡፡ በአንድ ጊዜ ማለት አርባ ስምንት ሰዎች ጨፈለቀ፡፡ ተካሚዮኑ ወደኋላ ያፈገፈጉትን እሥረኞች ዙሪያውን ሳንጃ መዘው የቆሙት ወጓቸው፡፡ እኔም በካምዮኑ ጉልበቴን መታኝ፡፡ ያን ጊዜ የቆሰልሁት እስከ ዛሬ ለምጥ ይመስላል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስትያን ተቃጥሎ ኑሯል፡፡ እንደ ማታ የፀሐይ ጮራ ከምዕራብ በኩል ይታያል፡፡ በለሊት ወስደው ከገደሉት በእስር ቤት የቀረው ያንሳል፡፡ ነገር ግን በዚህ ለመግደል ሲያወጡ የሚበልጥ በዚያ በር ያገቡ ነበር፡፡ በበነጋው ከተደበደበው ሕዝብ ከኪሱ የተገኘውን እየቆጠሩ ለሹሙ አስረከቡ፤ እኔም ከጽሕፈት ቤቱ ፊት ለፊት ነበርሁ፡፡ የደበደቧቸውን የሐበሾችን የጋብቻ ቀለበታቸውን በሲባጐ እንደ መቁጠሪያ ሰክተው ደርድረው በአንገታቸው አግብተው አቀረቡት፡፡ አንዱ ቆጥሮ መዝኖም እስኪያስረክብ ሌላው ገና ባንገታቸው ነበር፡፡ ንፁህ የሆነውንም ልብስ በካምዮን አምጥተውት ነበርና አየቆጠሩ እስኪረከቡ፤ ገናም ሳይገቡ ገፈዋቸው ኖሯል፡፡ ስለዚህም ከጥቂቶች በቀር ሙሉው ልብስ በደም አልተበላሸም፡፡ በመሬትም ጣል ጣል እያደረጉ እየቆጠሩ እስኪረከቡ የጥቂቶች ልብሶች ገና እስከ ትኩስ ደም ኑረው ከመሬት መልሰው ሲያነሱዋቸው አፈር እና ግብስባሱን እየያዙት ሲነሱ አየሁ፡፡ ይህን ባዬ ጊዜ አንዱ ብድግ ብሎ እንደ እብድ ተነሳ፡፡ “እርሷን አሁን ከመሬት አፈር ይዛ የተነሳችውን ደም እግዚአብሔር አየ፤ ሊፈርድ ነው፡፡ ይህ ክፉ ስራችሁ በጭካኔ ሕዝቡን የሰው ሕይወት በማጥፋት ትጫወታላቸሁ፡፡ የገደላችኋቸው ወገኖቻችን ቀለበት በሲባጐ ሰክታችሁ መዝናችሁ ወሰዳችሁ፡፡ ደማችንን መሬቱ መጠጠው፤ ሬሳውም እንደ ገለባ ተከመረ፡፡ ስትገድሉ እግዚአብሔር ሊፈርድባችሁ ነው፡፡ ይኸው አሁን የእግዚአብሔር ሚዛን ሞላ፡፡ እንግዲህ ኢትዮጵያን ከቶ አትገዙም፡፡ እኔንም አሁን ልትገድለኝ ነው” አላቸው፡፡ ገናም ነገሩን ሳይጨርስ አምስት ቦምብ ተወረወረ፡፡ በአጠገቡ ያሉ ሁሉ ተቆላልፈው ሰማንያ ሰዎች ወደቁ፡፡ ካሚዮንም ሬሳውን ለመውሰድ አመጡ፡፡ ሬሳውን በአንድ ካሚዮን ከወሰዱ በኋላ ሌሎች ካሚዮኖችም ቁስለኞችን ለመውሰድ አመጡ፡፡ በብርቱም የቆሰሉትን እያነሱ ወስደው ከእስር ቤት በር በመትረየስ ተኰስዋቸው፡፡ በጥቂት የቆሰሉት ሰዎች ግን ቁስላቸውን አየሸሸጉ እንደ ደህና እየመሰሉ በእስረኛው መሐል ተሸሸጉ፡፡ ኢጣሊያኖችም እየበረበሩ ጥቂትም ቆስሎ ቢሆን ልትታከሙ ነው እያሉ እየመረጡ ከበር ገደሏቸው፡፡ ቁስል የሌላቸውንም እየነዱ ሲያወጡ “እረ እኛ ጤነኛ ነን አልቆሰልንም” እያሉ ቢጮሁ “አይሆንም ትታከማለህ፤ ቆስላችኋል” ብለው እየጐተቱ አውጥተው ከማዘጋጃ ቤት በር ሲደርሱ የሳንቃውን ቋሚ ዘንግ የሚመስሉትን ብረቶች በሁለት እጃቸው አንቀው ይዘው አልወጣ አሉ፡፡ በእንጨት ላይ እያሰለፉ ገደሏቸው፡፡ ቀኑ ብርቱ ፀሐይ ነበር፡፡ በዚያ እስር ቤት በማዘጋጃ ቤት ሜዳ ነበርና ብርቱ ክቢያ ተከበን ታላቅ ፍርሃት ነበር፡፡ ውሃና መብልም አላገኘንም፡፡ በሦስተኛው ቀን ጊዜውም ስድስት ሰዓት ሲሆን አስራ ሰባት ሰዎች በውሃ ጥማቱ ሞቱ፡፡ ይህም ቀን ጨለመ፡፡ እህልና ውሃ ሳናገኝ ሦስተኛው ቀን ነበርና ገንዘብም አየተቀበሉ በኰዳቸው ጣሊያኖች ለእስረኞች ውሃ መሸጥ ጀመሩ፡፡ ሕይወታችንም በዚህ ስቃይ ውስጥ ታንቃ ስንጨነቅ መሸ፤ እንጂ ለቀን ቀኑ ረጅም ነበር፡፡ ከዚያ ረሐብና ውሃ ጥማት እንዲገድሉን መርጠን ነበር፡፡ ይህንንም ከልክለውን ሁለት ካሚዮን አምጥተው ከዚህ ወደሚሰፋ እስር ቦታ ሊወስዱን እየቆጠሩ ስሙን እየፃፉ 30ውን አሳፈሩት፡፡ እንደተናገርኩት እኔ በጽህፈት ቤቱ በር አጠገብ ስለነበርኩ እስረኛውን አየቆጠሩ አያሳፈሩ መጓዝ የጀመሩ ከወዲያ በኩል ነበርና ስለዚህ የኔ መሄዴ ዘግይቶ ነበር፡፡ ብዙ የሚያሳዝን ቁም ነገሮች በመዘግየቴ አየሁ፡፡ ሦስት ሴቶች በወሊድ ተጨንቀው ኖረዋል፡፡ ሊወልዱም ቦታ አላገኙምና በአስረኛው ግፊ ተጨፍልቀው ሞተዋል፡፡ ሦስቱም ከትንንሽ ህፃናቶቻቸው ጋር ሬሳቸው ወድቆ አየሁት፡፡ በውሃ ጥማትና በረሃብ እነርሱም በቦምብ ከገደሉት ከሞተው ሰውና ከሬሳው ብዛት የተነሳ እኒህን በወሊድ የሞቱትን ያስተዋላቸው አልነበረም፡፡ እኔንም ሊገድሉኘ ስሜን በሊስት ይዘው ይፈልጉኝ ነበርና ስሜን ፅፈው ሊያሳፍሩኝ ሲሉ ሌላ ስም ነገርኳቸው፡፡ በካሚዮንም እስረኛውን ወደወሰዱበት ስፍራ አጓዙን፡፡ በመንገድም የካሚዮኑ መብራት በሚወድቅበት እንመለከት ነበር፡፡ መንገዱ ሁሉ ሬሳ ተሞልቶ ነበር፡፡ በገደሏቸው በሐበሾች ሬሳ ተሞልቶ ነበር፡፡ ዝም ብለው በላዩ ይነዱበት ነበር፡፡ በሬሳው ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን ሬሳውን ደግሞ በካሚዮናቸው በጨፈለቁት ወቅት በሰው ሬሳ መንገዱ ተበላሽቶ ያስጸይፍ ነበር፡፡ ከመንገዱም ዳር የወደቁትን ሬሶች የካሚዮኑ ብርሃን በወደቀባቸው ጊዜ ድመቶች ጐንጫቸውን ነክሰው ጺማቸውን እያራገፉ ሲበሏቸው አየሁ፡፡ ካሚዮኑ ከእስር ቤቱ በር ፊት በር በሚባለው በደረሰ ጊዜ ከካሚዮን እንድንወርድ አደረጉን፡፡ በኋላ በኩል ከነበሩት መጀመሪያ የወረዱትን ቦምብ ወርውረው ገደሏቸው፡፡ የቀረነው አንወርድም ብለን ራሳችንን በውስጥ በሸሸግን ጊዜ በኋላ በኩል ነጂው በሚቀመጥበት በኩል መትረየስ አምጥተው አስገብተው ተኩሰውብን ሞላዎችን ገደሏቸው፡፡ የቀረነው እየዘለልን ከካሚዮን ወረድን፡፡ ለጥይቱ ፈርተው በኋላ በኩል ሸሽተው ነበርና የወረደም የለም፡፡ የእስር ቤቱ በር ክፍት ስለነበር እየፈጠንን ሩጠን ተጨመርን፡፡ ሌሊቱንም ሁሉ እስረኛውን እያጋዙት ሲጨምሩት አደሩ፡፡ ይህም ቦታ ጠፍ ሁኖ የኖረ ነበረና ሳማና ልት የሚባለው ምንስ ወራቱ መጋቢት ቢሆን ቅጠሉ ለምልሞ ነበር፡፡ በታላቅ ረሃብና ውሃ ጥማት የተጨነቀው እስረኛ ያንን መራራ ቅጠል በላ፡፡ ሲጠጣ ይህን ቅጠል ያሳደሩ ስሩን እየገፈፉ በሉ፡፡ እኔም ምን የሚበላ ነገር ይህ ፍጥረት አገኘ? ባገኘው ህይወት ነው ብዬ ወደሚያላምጡት ሰዎች ሔድሁ፡፡ የሚያውቀኝ ሰው አገኘሁና ከዚያ ስር ቆፍሮ ሰጠኘ፡፡ እኔም ወስጄ ለባልንጀሮቼ አካፈልኋቸው፤ለውሃ ጥማት ይህን ማላመጥ መድሃኒት ነው ብሎ ነግሮኝ ነበርና ለውሃ ጥማት መድሃኒት ነው ብዬ ነገርኋቸው፡፡ ከፊላችንም መራራ አንደሚጣፍጥ ይህን እያላመጥን እስከ አራት ሰዓት ቆየን፡፡ ዛሬ ቀኑ አሁድ ነበር፡፡ የተያዝንበትም አርብ በስምንት ሰዓት ነበር፡፡ ከዚያ እስከ ዛሬ እህል የሚባል እንኳን ለመብል ማግኘት ቀርቶ ያየን የለም፡፡ ፀሐይ በዚህ ቀን ሲተኩስ ሰው ሁሉ ልቡሱን እያወለቀ በራሱ ላይ ተከናነበው፡፡ በዚህም መከናነብ የፀሐይ ትኩሳት ሲበርድ ውሃውን ጥማት መከላከል የሚችሉ መስሏቸው ነበር፡፡ ከሌላው እስር ቤት በቀር በዚህ እስር ቤት ውስጥ የነበረው አስረኛ እነሱ ጣሊያኖች እንደገመቱት 18 ሺ ነበር፡፡ ከረሐቡና ከጥማቱ የተነሳ እስረኛውም ሁሉ መናገር አይችልም ነበር፡፡ ነፍሱ ገና አለቀው እያለች ነው እንጂ ሁሉም ደክሞ ይጠራሞት ነበር፡፡ ለመተንፈስ እስከማይችል ድረስ ያ ትልቁ ሰፊ ሜዳ ጠቦ ነበር፡፡ አንዱ እየተጋፋ መጣ፡፡ ጠርሙስ በእጁ ነበር፡፡ ፊቱ ክስመት ገብቶ ነበር፡፡ ከአጠገባችን ቆሞ ሊናገረን ፈለገ፡፡ ገና ከንፈሩን ማላቀቅ ግን አፈልቻለም፡፡ ከውሃ ጥማት የተነሳ ረድኤት በማፈልግ ዓይን በሚያሳዝን ተኩሮ ወደ አኛ ተመለከተ፡፡ በታላቅ ችግር በውሃ ጥማት የተያያዘውን ከንፈር አላቀቀው፡፡ ደካማ በሆነ ድምፅ “እባካችሁ! እባካችሁ!” ሲል ሰማነው፡፡ ነገሩን የሚለውን አጥርተን አልሰማነውም ነበርና ልንሰማው እንድንችል ወደ እኛ በጣም ቀረበ፡፡ እ…ባካችሁ ከአናንተ ጭብጦ የሌላችሁ ሽንቱን በዚህ ጠርሙስ ይስጠኝ ወንድሞቼ ሁለቱ በውሃ ጥማት ሞቱ፤ እኔም ልሞት ነኝ፤ እባክዎ ጭብጦ ባይኖርዎ ሽንትዎን አባክዎ ጌታ ይስጡኝ” ብሎ ልመናውን ወደ አቶ ገብረመድህን አወቀ አበረታው፡፡ አቶ ገብረመድህን አወቀም “እኔም አንዳንተ ነኝ፡፡ ውሃ ከጠጣሁ ሦስተኛ ቀኔ ነው፡፡ ከዬት ሽንት አመጣለሁ?” እኛንም አልፎ እየዞረ ሲለምን አልቆየም፡፡ አስከ መጨረሻው ደክሞት ነበር፡፡ መናገርም አቃተው፡፡ አንድ ድንጋይም በአጠገባችን ተንተርሶ ጥቂት ጊዜ ተጋድሞ በሕይወቱ ቆየ፡፡ በመጨረሻም ግን እንደ እንቅልፍ በሞት ያችን ድንጋይ እንደተንተራሰ አሸለበ፡፡ በዚህ ቀን በውሃ ጥማት ከመቶ በላይ እሰረኛ ከጥዋት እስከ ሰባት ሰዓት ሞቱ፡፡ ሬሳቸውንም ካሚዮኖች መጥተው ወሰዱት፡፡ በዚህ ጊዜ የእስር ቤቱ ሹም ቲሊንቲ ሎዊጂ ኮርቦ የሚባለው በዚያ እስር ውስጥ ገብቶ የተጠሙትን ነፍሳቸው አልላቀቅ ያላቸውን አይቷቸው ኑሯል፡፡ በኰዳው ውሀ ይዞ መጣ፡፡ ቲሊንቲም የኮዳውን ውሃ ለእስረኛው መሸጡን ሰማን፡፡ ገንዘብም ይዤ ሄድሁ፡፡ የሚሸጠው እሱ ብቻ ስለሆነ ካጠገቡ መድረስ አይቻልም፡፡ የተጠማው ብዙ ሕዝብ ውሃ ለማግኘት ዙሪያውን ከቦት ይጋፋ ነበር፡፡ ገዥውም ፋታ አያገኝም ነበር፡፡ በቀኝ እጁ ሽጉጡን አውጥቶ፤ በግራ እጁ በተጠማው ሰው በአፉ ውስጥ ትንሽ ጠብ ያደርግለታል፡፡ የኢጣሊያ አንድ ኰዳ ሁለት ጠርሙስ ተኩል ይይዛል፡፡ ቲሊንቲ አንዱን ኰዳ ውሃ ለሃያ አምስት ሰው አስጠጥቶ ሃያ አምስት ብር ለአንድ ኮዳ ተከፈለው፡፡ የአቶ ስለሺ አሽከርም በጣም ተጠምቶ ነበር፡፡ አንድ ብር በቲሊንቲ ግራ እጅ አኖረ፡፡ እሱም ከኰዳው አጠጣው፡፡ ቲሊንቲም ውሃውን አቀረበና በአፉ አፈሰሰበት፡፡ ጠጪውም ስላልረካ ኮዳውን ቲሊንቲን ቀልጥፎ ሲያቃናው በሁለት እጁ ከአፉ አስጠግቶ ያዘው፡፡ ቲሊንቱም ሽጉጡን በዓይኑ መሐል ተኮሰበት፡፡ ሳይውጠው ገና በጉንጩ የነበረው ሲወድቅ በአፉ ፈሰሰ፡፡ ቲሊንቲም ደጋግሞ ተኩሶ ጨረሰው፡፡ እርሱን በተኰሰው ጊዜ አሳልፎ ክንዱን ያንዱን ሰው አቁስሎት ስለነበር የቆሰለው ብር እንኳ ቢሰጠው እንዲሁ ያለ ዋጋ አጠጣው፡፡ ይህንም በውሃ ጥማት የሆነውን ታላቅ እልቂት እንዲቀር ውሃ በሸራ ቧንቧ ኢጣሊያኖች ከታሰርንበት ድረስ አስገብተው በ120 በርሜል ሞሉልን፡፡ እኒያ ሁለት ሹማምንቶች ማርሻሎና ቲሊኒቲ ሎዊጂ ኮርቦ እስረኛውን እያካፈሉ ከዚያ ወዲህ ያለው ይጠጣ እያሉ ሲከላከሉ አንድ ጊዜ እስረኛው እንደ ናዳ ተንዶ ጥሷቸው ሄደና ውሃም የቻለውን ያህል ይጠጣ አለ፡፡ በርሜሉንም ገና ያላየው ነበር፡፡ እነርሱም በዚህ ግፊት እኒህ ውሃ ሲሸጡ የዋሉ ሹማምንቶች ተድጠው ሞተው ኑረዋል፡፡ የሹማምንቶቻቸውን ሞት ስላወቁ ሰው ላይ ቦምብ ይወረውሩበት ጀመር፡፡ በበርሜሎች ዙሪያ ሬሳው ተከመረ፡፡ በቦምብ የተመቱት የጥቂቶችም ሬሳ በበርሜሎች ውሃ ውስጥ ገባ፡፡ ደማቸው ተቀላቀለበት፤ ሰውም ከላያቸው ላይ ሳይፀየፍ ይጠጣ ነበር፡፡ ልብሶቸውንም በበርሜሉ ውሃ እየነከሩ አምጥተው የተነከረውን ልብስ እንደ ጡት ጠቡት፡፡ በደከሙት ባልጀሮች አፍም እየጨመቁላቸው ቤዛ ሆኑ፡፡ ከተወረወረብንም ቦምብ ብዛት የተነሳ የሞተው ሬሳ በበርሜሎች ዙሪያ ተቆልሎ ነበርና ሰው ቢሄድም ሬሳው ወደ በርሜሉ እንደማያደርሰው አወቀ፤ ከመሄድም ታገሰ፡፡ ሦስት መትረየስ አግብተው ጠምደው ተኮሱብን፡፡ ውሃ ለእስረኛ ሲሸጡ ውለው እግዜር ፈርዶባቸው የተዳጡትንም የሹማምነቶቻቸውን በቀል ተበቀሉን፡፡ አምስት ካሚዮን አመላልሰው አንድ ሺ አምስት መቶ የሚያህል እስረኛ ሞተ፡፡ ሬሳውንም በካሚዮን እስኪያወጡ ድረስ ፈፅሞ ጨለመ፡፡ በኢጣሊያ ፋሽስት የተያዘ ሳይገደል በህይወት ፊት ምንድን ነው? መብልና ውሃ የሰጡን ሹማምንቶች ወደ ቤታቸው በተመለሱ ጊዜ ቁጣቸውን አድሰው በዙሪያው በውድሞው ያሉ ፋሽስቶች በሰው ህይወት ሊጫወቱ ቦምብ ይወረውሩብን ጀመረ፡፡ ግን የቁጣ ምክንያት አልነበራቸውም፡፡ በዙሪያው ከሚወረወር ቦምብ ለመሸሽ የማይደረስበት መሃከለኛውን ቦታ ለመያዝ እርስ በርሳችን ተጨናንቆ ተጋፍቶ ቆሞ ሳለ በዙሪያ ዳር የሚወረወሩት ቦምቦች ከመሀል አወራወራቸው ሊያደርሳቸው ስለማይችል በዳር በኩል ዙሪያውን ያሉትን ጨፈጨፏቸው፡፡ የቀረውም ከመሀል ሆኖ ለቦምብ ውርውራ ስለአቃታቸው መትረየሱን ለመሀል ጠምደው ተኮሱብን፡፡ ከጥይት ለመዳን የፈለገ ሲተኛ የቆመው ህዝብ ጨፈለቀው፡፡ የቆመውን መትረየስ ጠረገው፡፡ የቆሰለና ያልቆሰለ የሞተና ደህነኛ እስኪጠባ ድረስ ተቆላልፎ አደረ፡፡ ሰኞ በበነጋው ሌላ ሹም መጥቶ ደህናውንና የቆሰለውን በአንድ በኩል ለየው፤ የሞተውን ሬሳ ግን በካሚዮን ማጓዝ ጀመረ፡፡ ግን በዚያ ማታ በቦምብ የገደሏቸውን ሬሳውን ሳይወስዱ ስለቀሩ ወደ በሩ ሲል ወዳለው ማዕዘን አንድ ሴት እስከ ልጇ የታሰረች በቦመብ ተመታ ሞታ ኑሯል፡፡ ልጇ ደህና ነበረ፡፡ የእናቱንም ሬሳ ሌሊትን ሁሉ በደረቷ ላይ ተሰቅሎ ገና በሕይወት እንዳለች ሁሉ ይጠባት ነበር፡፡ እሰረኞችም ምንስ በእንዲህ ያለ ጭንቅ ተይዘው፤ በውሃ ረገድ ባይረዳዱ የዚህ ሕፃን ስቃይ ልባቸውን አንቀሳቀሰው፡፡ ይህን ሕፃን አንስተው ትናንት በግፍ ልጇ ለተዳጠባት ሴት እባክሽ አጥቢው ብለው ሰጧት፡፡ ያችም ሴት ለልጇ ምትክ እንዳገኘች ደስ ብሏት አልተቀበለችም፡፡ እንዲያውም ወርውራ ጣለችው፡፡ ነገ ኢጣሊያኖች በቦምብ ለሚገድሉት ለማሳደግ አላጠባም፡፡ ለመትረየስና ለሳንጃም አላሳዳግም ብላ ወረወረችው፡፡ በዚያ ብርቱ ፀሐይ ተንጋሎ ወድቆ ብርቱ ለቅሶ አለቀሰ፡፡ እኔም አንስቼ እናቱ ሬሳ ላይ አስቀመጥኩት፡፡ እናቱንም አንዳገኘ ሁሉ ደስ ብሎት ለቅሶውንም አቆመ፡፡ ወዲያውም በካሚዎን ሬሳውን መውሰድ ጀመሩ፡፡ የዚህን ህፃን እናቱ በካሚዎን ሬሳዋን ፋሽስቶች ወስደው ሲያገቡ አንዱ ኦፊሰር የሆነ ፋሽስት ይህን ህፃን ታቅፎ በእውነት ሲያለቅስ አየነው፡፡ እነዚህ የካቶሊክ ካህናት የሃይማኖት ወገናቸውን ሁሉ አስፈትተው ይዘው ሄዱ፡፡ የዛኑ ለት ማታውኑ የቀረነውን እስረኞች በካምዮን ጭነው ወደ ሆለታ ወሰዱን፡፡ እዛም ስንደርስ በጫካው አውርደው ተኮሱብን፡፡ እኔም አጠገቤ ያለው ሰው ተመቶ ሲወድቅ አብሬው ወደቅሁ፡፡ ጣሊያኖችም ጨርሰናቸዋል ብለው ትተውን ሄዱ፡፡ እኔም ካምዮኑ መሄዱን አረጋግጨ በሆዴ እየተንፏቀቅሁ ከዛ እሬሳ መሃል ወጥቸ በጨረቃ ብርሃን ወደ እትቴ በዛብሽ ቤት ሄድኩ፡፡ እዛም እንደደረስሁ በምክር ወደ ጐጃም እንዴት እንደምደርስ አሰላን፤ እርስዋም ልብሷን አለበሰችኝና ሻሽዋንም አስራልኝ ማሰሮ አሳዝላኝ በጨረቃ ብርሃን ጉዞየን ወደ ጐጃም አቀናሁ፡፡ የማውቀው የአባይን በረሃ በለሊት እየተጓዝሁ በቀን እየተደበቅሁ እማርቆስ ገባሁ፡፡ እዛም እናቴንና እህቴን በሌላ መንደር አገኘኋቸው፡፡ እናቴ “በቤቱ በምበላበት ገበታ ዙሪያውን ልጆቼና አባቴ ከበው ይቀመጡ ነበር፡፡ ዛሬ ግን በዚያው ገበታ ዙሪያና በዚያው ቤት ብቻየን እቀመጣለሁ፡፡ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ እንደ ቀመሰው መራራ ውኃ፤ ሕይወቴ ሁሉ መራራ ሆነ፡፡ ሕይወቴ ሁሉ እንዲህ ለኃዘን ከሆነ ለምን ሰው ሆንሁኝ?” አለች፡፡ እናቴን በእንዲህ ያለ ኃዘን ባየሁ ጊዜ ከቶ የተራበው ሰውነቴ እጅግ መብል ሊወስድ አልቻለም፡፡ በባቢሎን ወንዝ ዳር ተቀምጠው እሥራኤል ጽዮንን እያሰቡ ያለቅሱ እንደ ነበር ልንበላ በከበብነው ገበታ ዙሪያ ፈረንጆች የገደሏዋቸውን አያቴንና አራቱን ወንድሞቼን እያሰበች እናቴ አለቀሰች፡፡ እናቴ ገና ከአንድ ወር በፊት በገበታ ዙሪያ አብረዋት ይከቡ የነበሩትን ልጆቿን ፈረንጆቸ ሲገድሉባት ይቀመጡበት የነበረውን ቦታ ባዶውን ስታይ በአጭር ጊዜ እንዴት ልትረሳቸው ይሆንላታል? ይቀመጡበት የነበረው የገበታው ዙሪያና ይተኙበት የነበረው ክፍል ባዶነት እንደ ሐውልት ቁሞ ነበር፡፡ ወደ መብል ስትቀመጥ ባዶ የሆነውን ዙሪያ ወደመኝታ ቤት ስትሔድ ባዶውን አልጋ ማየት ለእናቴ እጅግ ኅዘን ነበር፡፡ ስለዚህም እናቴ ያን ቤት ትታ ሌላ ቤት ተከራይታ ነበር፡፡ እንዲሁ የእናቴ ዕንባ በጐንጮችዋ ላይ ሲወርድ ባየሁ ጊዜ ነጮች ያፈሰሱትን የወንድሞቸን ደም ያህል የቀረበውን መብል ቆጠርሁ፤ ለመብላትም ፈቃዴ ተዘጋ፤ ምንም እንኳ ተርቤ ብሰነብት፡፡ ከዚሀ በኋላ የቀረበው ሁሉ መብል ተነሣ፡፡ እኔ ከነጮች እንድሸሽ አጎቴ የሰጠኝን ፈረስ አቀረበልኝ፡፡ ጠጉሬ የከተማ ሰው ቁርጥ ነበርና እንደ ውጭ ባላገር እንድመስል እኅቴ እያበላለጠች ስትቆርጥልኝ አዘገየችኝ፡፡ ገና ከተዘንቦው በኩል ስትቆርጥልኝ አያሌ የነጭ ወታደሮች ቤቱን ከበቡት፡፡ እናቴ ከድንጋጤ የተነሣ አእምሮዋ ሳይቀር ጠፋባት፤ አጎቴና እኅቴ ከቤት ወጥተው ነገሩ ምንድን ነው? ብለው ጠየቋቸው፡፡ ብርጋዴሩ የያዘውን ሊስት አየና… እፈልጋለሁ አለ፡፡ በጣም ያስደንቅ ነበር፡፡ በሊስት የተያያዘው ስም በፍፁም የእኔ ስም ነው፡፡ ግን ያባቱ ስም አሥራት ይባል ነበር፡፡ የእኔ አባት ስም ሌላ .. ነበር፡፡ እህቴም የሚፈልጉትን ሰው ቤቱን እንደ ተሳሳቱ ነገረቻቸው፡፡ ብራጋዴሩ ሊስቱን እንደገና አየና ከአጎቱ ጋር ይኖራል እንጂ ለእርሱ ቤት የለውም ብሎ ነገራት፡፡ አዎን ያ ሰው ደግሞ ከአጎቱ ጋር ይኖር ነበርና አዎን ከአጎቱ ጋር ነው ብላ ነገረችው፤ ወታደሮቹም ሔደው ያንን ቤት ከበቡት፡፡ መንደረተኛውን ሁሉ እንዳይወጣና አንዳይገባ ከለከሉ፡፡ ያን ለመያዝ ከዚያም ጫጫታ ሆነ፡፡ በዚህ ጊዜ ለማምለጥ ቅጽበት ጊዜ አገኘሁ፡፡ ኮርቻ ለመጫንና ለመለጎም ጊዜ አልነበረም፤ በፈረሱ ያለ ኮርቻ ያለ ልጓም ተቀመጥሁና ጋለብሁ፡፡ ጠጉሬን ግማሹን ተቆርጨ ግማሹን ሳልቆረጥ አመለጥሁ፡፡ ይህም ዛሬ ተረት ይመስላል፡፡ ሕይወቴ ከነጮች በማምለጥ ለሩጫና ለሽሽት ብቻ ሆነ፡፡ በፊቴም ሁሉ ተስፋና መጽናኛ የለም፤ ዙሪያውም ሁሉ ከሌሊት የባሰ ጨለማ ሆነብኘ፡፡ በሀገራችን እያባረሩ ለሚያድኑን ለነጮች የምታበራይቱ ፀሐይ ግን በሃገራችን ሰማይ ታበራ ነበር፡፡ ስለዚህም ለሚያዳኑን ለእነርሱ የሚያምረው የበጋ ብርሃን ለምታደነው ለእኔ የክረመት ጨለማ ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ አእምሮው ጮሌ የሆነ ዕውር ከእኔ የተሻለ ነበር፡፡ ወዴት እንደምሸሽ ከቶ አላውቅም ነበር፡፡ ወዴት እንድጋልብ ሳላውቅ ፈረሱን ወደ ቀጥታው እንዲጋልብ ለቀቅሁት፡፡ በማዶው በኩል በተራራው ግርጌ ተፋጥኜ ካለፍሁ በኋላ አርባ ማይል እንደ ተጓዝሁ ከራዕዩ እንደ ተመለሰ ሰው ሆንሁ፡፡ ለጥቁር ሕዝብ በሰላም የተሰማራበትን ነጮቹ በማደን የማያባርሩበትን አዲሱን ክበብ አየሁ፡፡ አዲስ ምድርና አዲስ ሰማይ ያህል መሰለኝ፡፡ በዚያም ጠባቂ የሌለው በግ ጥቁሩ ሕዝብ ተሰማርተዋል፡፡ ጠባቂው በእንግሊዝ አገር ነው፡፡ ቀበሮው ከዚህ አስቀድሞ አልገባም ነበር፡፡ የዘር ወራት ነበርና ሁሉም ደርሶ ነበር፡፡ ያን ሃገር ነበረና የዘራውን ሊበላ በተስፋ ይዘራ ነበር፡፡ ገና ነጮች ሃገሩን አልወረሩትም ነበርና በመስኩ ከብቱ ተሰማርቶ ነበር፡፡ እናቶች በቤታቸው ናቸው፡፡ ሕፃናቶችም በመንደራቸው አንደ ማለዳ ወፎች እየተንጫጩ ይጫወታሉ፡፡ በግ ጠባቂው በጎችን ይመለከታል፡፡ ከብቶችን የማያረባው ዘላን ከብቶችን ይከተላል፡፡ ወደ መንደራቸው ጠባቂዎች ከመንጋዎቻቸው ጋር ይጓዛሉ፡፡ ወርቅ የሚመስለው የፀሐይ ጮራ በተራራዎች ላይ ተዘርግቷል፡፡ ገበሬዎች በሚያርሱበት ቦታ ጅራፍ ብቻ ይጮሃል፡፡ የኤውሮፓ ማሰልጠኛ ቦንብና መድፍ መትረየስ ድምፅ አይሰማም፡፡ በነጮች ወራሪ የሣር ክዳን አንድ ጎጆ የተቃጠለ አመድ የለምና ንፋሱም አመድ አያበንም፡፡ በወንዙ ዳር የተተከሉ ለጋ ሸንበቆዎች በወታደር አልተጣሱም፡፡ ገና ንፋሱ ያወዛውዛቸዋል፡፡ ባላገሮች በሃገራቸው ላይ በፍፁም ፀጥታ ይኖራሉ፡፡ እንዲህ ያለ ጥቁር ሕዝብ ከሰላሙ ጋር የሚኖርበት አዲስ አገር አገኘሁ፡፡ የሰላም የሰላም የሰላም ሃገር፡፡ ነጮች ወራሪዎች አልረገጥዋትም፤በድንገት ግን አደጋ ጥሎ ለመወረር ገና ሳያዩዋቸው በሚስጥር መግባት ጀምረዋል፡፡ በቤቴ ለመኖር የነበረኝ ሰላም በነጮች ከተቀጠቀጠ ሁለት ዓመት ያህል ሆኖ ነበርና በሀገራቸው በሰላም እንዲሁ የሚኖሩትን ሰዎች በማየቴ ካለፈው ዓመት በፊት እንዴት በሰላም ከበቴ እኖር እንደነበር አሳሰበኝ፡፡ በሰሩት ቤት መኖር! ሰማይ ቢከፈት ከዚህ የበለጠ ስጦታ በምድር ሊዘንብ በቻለ፡፡ ሕዝብ በሀገር ውስጥ በሰላም መኖር ሕፃናትን በሰላመ ማሳደግ ቤተሰብን መረዳት ከዚህም ጋራ በሰሩት ቤት በሰላም መኖር! ከዚህ የበለጠ የበረከት ፍሬ መሬት ልትሰጥ ትችላለችን? ሰው በሕይወቱ የሚመኘውና ሊኖረው የሚፈልገው ይህ ብቻ ነው፡፡ የነጮች ወራሪዎች በረገጧት ሃገር ሁሉ ለሕያው ነፍስ የሚያስፈልገው የሰላም ኑሮ የለም ነበር፡፡ ከወራሪዎች ድንግል በነበረችው ከዚህች አውራጃ ሃገር በደረስሁ ጊዜ አዲስ ሌላ አለም ያየሁ ያህል መሰለኝ፡፡ ያልታደለችው ኢትዮጵያ በእርግጥ ሰፊ ሃገር ናት፡፡ ወራሪዎችም ባንድ ጊዜ በሙሉዋ ሊጎርሷት አልቻሉም ነበርና በየከተማ አጠገብ ያሉትን ሃገሮች በቦምብ በመርዝና ቤቶችን በማቃጠል ያልታደለውን ፍጥረት ገና ያመነዥኩ ነበር፡፡ በተራራዎችና በአፋፎች የኢጣልያኖች መድፎች እንደ ክረምት ነጎድጓድ ይጮሃሉ፡፡ ባለ ከብቶች ከከብታቸው ጋር የሚኖርባቸው ጠፍጣፋ ሃገሮች በጉም እንደሚጋረዱ የተራራ እግሮች በመርዝ ጢስ ታፍነዋል፡፡ ከዓመት አራት ጊዜ ፍሬዋን ትሰጥ የነበረች ሃገር ያለ አዝመራ ሆነች፡፡ ለመታጨድ የደረሱ አዝመራዎችን የሰለጠኑት ነጮች በእሳት ቦምብ ሲያቃጥሉት፤ ዝሆኖች አንበሶች አንደሚኖሩባት በረሃ የገበሬዎች አዝመራ ተቃጠለ፡፡ ቅጠልያ የሆነችው ሃገር ከቃጠሎው የተነሣ እንደ ነብር ቆዳ ዝንጉርጉር ሆነች፡፡ ከጠፍጣፋው ሃገር ሸሽተው በተራራ ሰዎቸ ተሰማሩ፡፡ የተሰማሩበት ጫካ ሳይቀር ተቃጠለ፤ ከነጮች የሥልጣኔ ቦምብና መርዝ የሚሸሹ የአፍሪካ ሕፃናቶች ለሊት ሲባንኑ መርዝ! መርዝ! መርዝ! እያሉ በዕንቅልፋቸው እየጮሁ ያለቅሱ ነበር፡፡ በዚህም ሁሉ ያ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ ለመቁረጥ ብቻ ሆነ፡፡
9724
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%88%8D%E1%8A%AE
አምልኮ
አምልኮ ወይም አምልኮት የሚለው ቃል "መለክ" ማለትም "መገዛት" ከሚል የግዕዝ ቃል የሚመነጭ ሲሆን በሙሉ ሁለንተና የሚቀርብ ልመና፣ ስእለት፣ ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ስግደት፣ መገዛት ፣ አገልግሎት ማለት ነው። መለኮት በባሕርይ የበላይና ገዢነትን ስለሚያመለክት ለሰውና ለፍጡር አይሆንም። ዕብራውያን /ኤል/ ወይም /ኤሎሃ/ የሚሉትን አረቦች /ኢላህ/ ይላሉ። ሁሉም የመለኮት ሥልጣን ያሳያል። በዚህ መልክ ከሄድን ከፈጣሪ ውጪ የማምክ ተግባር የጣዖት አምልኮ ይባላል። «አምልኮ» የሚለው ቃል በእብራይስጥ /አባድ/ ሲሆን በግሪክ ደግሞ /ላትሬኦ/ ነው፤ ይህም ለአንዱ አምላክ ብቻ በሙሉ ሁለንተና የሚቀርብ ልመና፣ ስእለት፣ ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ስግደት፣ መገዛት ፣ አገልግሎት ነው፤ ይህም አምልኮ ለአንድ አምላክ ብቻ እንደሚገባ የመለኮታዊ ትምህርት ቅሪት ባለበት ባይብል ላይ ሰፍሯል፦ ዘዳግም 6፥13 አምላክህን ያህዌህን ፍራ እርሱንም #አምልክ በስሙም ማል። ዘዳግም 10፥20 አምላክህን ያህዌህን ፍራ፥ እርሱንም #አምልክ ከእርሱም ተጣበቅ፥ በስሙም ማል። ዘዳግም 13፥4 አምላካችሁን ያህዌህን ተከተሉ፥ እርሱንም ፍሩ፥ ትእዛዙንም ጠብቁ፥ ቃሉንም ስሙ፥ እርሱንም ፥ ከእርሱም ጋር ተጣበቁ። ኢያሱ 24፥14 አሁንም ያህዌህን ፍሩ፥ በፍጹምም በእውነተኛም ልብ #አምልኩት አባቶቻችሁም በወንዝ ማዶ በግብፅም ውስጥ ያመለኩአቸውን አማልክት ከእናንተ አርቁ፥ ያህዌህንም አምልኩ ። ሳሙኤል ቀዳማዊ 12፥20 ሳሙኤልም ሕዝቡን አለ። አትፍሩ በእውነት ይህን ክፋት ሁሉ አደረጋችሁ ነገር ግን ያህዌህን በፍጹም ልባችሁ #አምልኩት እንጂ ያህዌህን ከመከተል ፈቀቅ አትበሉ። ሳሙኤል ቀዳማዊ 7፥3 ሳሙኤልም የእስራኤልን ቤት ሁሉ። በሙሉ ልባችሁ ወደ ያህዌህ ከተመለሳችሁ እንግዶችን አማልክትና አስታሮትን ከመካከላችሁ አርቁ፥ ልባችሁንም ወደ ያህዌህ አቅኑ፥ እርሱንም ብቻ #አምልኩ … ብሎ ተናገራቸው። ማቴዎስ 4፥10 ያን ጊዜ ኢየሱስ፦ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ #አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና አለው። ልብ አድርግ አንድ ማንነት ብቻ ያለው አንድ አምላክ መሆኑን ለማመልከት «እርሱን» ብቻ አምልክ በሚል በገላጭ () የተጠፈነገ ነጠላ ተውላጠ ስም እንጂ «እነርሱ» የሚል የለም፤ ታዲያ ሶስት ማንነቶች ያሉባቸውን ምስልና ሃውልት አበይት በሚባሉት በኦርቶዶክስ፣ በካቶሊክ እና በአንግሊካን አብያተ-ክርስቲያናት ለምን ይሰገዳል፣ እጣን ይጨሳት፣ ይሸረገዳል፣ ይጎባደዳል? ይህ የጣኦት አምልኮ ካልሆነ ምን እንበለው? ወገኖቻችን፦ “ለስእልና ለሃውልት የአምልኮ ስግደት ሳይሆን የፀጋ ስግደት ነው የምናደርሰው” ይላሉ፤ እርግጥ ነው የአክብሮት ስግደት ባይብል ላይ ለመላእክትና ለሰዎች አይተናል፤ ግን የት ቦታ ነው ለማይሰማና ለማይለማ ምስልና ሃውልት ስገዱ የተባለው? ከዚያ ይልቅ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም ተብሏል፦ ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ #አትስገድላቸው፥ #አታምልካቸውምም፤ የሚገርመ የአገራችን ሰዎች እንዲህ ይፀልያሉ፦ “ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”ተሰቀለበት [[መስቀል]ም እስገዳለው” የዘወትር ጸሎት «መስቀል» እንጨት፣ ብር፣ ወርቅ ወይም ብረት አይደለምን? ይህንን ቀርፆ ለእርሱ መስገድ የጣኦት ክፍል አይደለምን? ሥላሴን በጀሶ ቀርፆ ወደ እነርሱ አምላኬ እያሉ መለማመን ባእድ አምልኮ አይደለምን? ኢሳይያስ 44፥17 #የቀረውንም #እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ #ይሰግዳል ወደ እርሱም #እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። ኢሳይያስ 45፥20 እናንተ ከአሕዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ፥ ተሰብስባችሁ ኑ በአንድነትም ቅረቡ፤ #የተቀረጸውን #የምስላቸውን #እንጨት የሚሸከሙና ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ #የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም። ኤርምያስ 10፥2-5 ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ “የአሕዛብን መንገድ አትማሩ ከሰማይ ምልክትም አትፍሩ፤ አሕዛብ ይፈሩታልና። “የአሕዛብ ልማድ” ከንቱ ነውና፤ ዛፍ ከዱር ይቈረጣል፥ በሠራተኛም እጅ በመጥረቢያ ይሠራል። በብርና በወርቅ ያስጌጡታል፥ እንዳይናወጥም በችንካርና በመዶሻ ይቸነክሩታል። እንደ #ተቀረጸ ዓምድ ናቸው እነርሱም አይናገሩም፤ መራመድም አይቻላቸውማን ይሸከሙአቸዋል። ክፉ መሥራትም አይቻላቸውምና፥ ደግምም መልካም ይሠሩ ዘንድ አይችሉምና አትፍሩአቸው። የሥላሴ፣ የመላእክት፣ የቅዱሳን ምስልና ሃውልት ክፉ መሥራትም አይቻላቸውም፤ ደግምም መልካም ይሠሩ ዘንድ አይችሉም፤ ካልቻሉ ለምን ይሰገድላቸዋል? ይህ የእኛ የሙስሊሞች ጥያቄአችን ብቻ ነው እንጂ ነቀፌታ ወይም መዘርጠጥ አይደለም፤ አላህ ከእርሱ ሌላ ሰዎች የሚያመልኩአቸውን ጣዖታት አትስደቡ ብሎናል፤ ምክንያቱም ድንበርን በማለፍ ያለእውቀት አላህን ይሰድባሉና፦ 6፥108 እነዚያንም ከአላህ ሌላ “የሚጠሩዋቸውን” َ ጣዖታት አትስደቡ፤ ድንበርን በማለፍ ያለእውቀት አላህን ይሰድባሉና። “ዒባዳ” የሚለው ቃል “ዓበደ َ “አመለከ” ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን “አምልኮ” ማለት ነው፤ አምልኮ የሚገባው አንዱ አምላክ አላህ ብቻ ነው፤ መልእክተኞችም የተላኩበት ጭብጥ ይህ ነው፦ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ “አላህን #አምልኩ ፤ ጣዖትንም ራቁ” በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤ 21:25 ከአንተ በፊትም፣ እነሆ “ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና #አምልኩኝ ِ ” በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢሆን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም። ለናሙና ያክል እነዚህ መልእክተኞች፦ 23:23 ኑሕንም ወደ ሕዝቦቹ በእርግጥ ላክነው፡፡ ወዲያውም «ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን #አምልኩ ፡፡ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ አትጠነቀቁምን» አላቸው፡፡ 11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ አላህን #አምልኩ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፤ እናንተም ቀጣፊዎች እንጂ ሌላ አይደላችሁም። 7:73 ወደ ሠሙድም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ! አላህን #አምልኩ ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ ምንም አምላክ የላችሁም፤ 29:16 ኢብራሂምንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ፦ አላህን #አምልኩ ፤ ፍሩትም፤ ይሃችሁ የታውቁ ብትሆኑ ለናንተ በላጭ ነው። 11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ አላቸው ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን #አምልኩ ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም፤ 2:83 የእስራኤል ልጆችንም ጥብቅ ኪዳን አላህን እንጂ ሌላን #አታምልኩ ፤ … በማለት በያዝንባቸው ጊዜ አስታውሱ፡፡ 5:72 አልመሲሕም አለ፦ የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን #አምልኩ” ፤ 11:2 እንዲህ #በላቸው ፦ አላህን እንጂ ሌላን #አታምልኩ ፤ እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስስጠንቂ እና አብሳሪ ነኝ። ቁርአን ሲሶው የሚናገረው ስለ ኢባዳ ነው፣ ይህ የቁርአን አንድ ሶስተኛው የአምልኮ ጭብጥ በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ የተወሳ ነው፣ ለቀድሞቹ ነቢያት የመጣው የተውሂድ ትምህርት ነው በቁርአን ውስጥ የመጣው፣ በፊት ለነበሩት መልክተኞች የተባለው “አምልኩኝ” ሲሆን በነብያችን የተባለው ይህ ነው፤ ይህ ለእሳቸው እና ከእሳቸው በፊት የነበረው የተውሒድ መገሰጫ ነው፦ 26:196 እርሱም ቁርኣን በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ “የተወሳ” ነው፡፡ 23:68 የቁርኣንን ንግግሩንም አያስተነትኑምን ወይስ ለመጀመሪያዎቹ አባቶቻቸው ያልመጣ ነገር መጣባቸውን? 41:43 ከአንተ በፊት ለነበሩት መልክተኞች የተባለው “ቢጤ” እንጅ ለአንተ ሌላ አይባልም፤ 21:24 ይልቁንም ከእርሱ ሌላ አማልክት ያዙን? አስረጃችሁን አምጡ፤ *ይህ እኔ ዘንድ ያለው መገሠጫ፣ ከኔ በፊትም የነበረው መገሠጫ ነው* በላቸው። በእውነቱ አብዛኞቻቸው እውነቱን አያውቁም፤ ስለዚህ እነርሱ እንቢተኞች ናቸው َ ። በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ ፈጣሪ “ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ” ብሎ የተናገረ አምላክ ዛሬም በዘመናች እኔን ብቻ አምልኩ ብሎ በተከበረው ቃሉ ይናገራል፦ 29:56 እላንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፤ እኔንም ብቻ #አምልኩኝ ِ ። 24:55 በእኔ ምንንም የማያጋሩ ሆነው #ያመልኩኛል ፤ ከዚያም በኋላ የካደ ሰው እነዚያ እነርሱ አመጠኞች ናቸው። 51:56 ጋኔንንና ሰውን #ሊያመልኩኝ ِ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም። 21:92 ይህች ሕግጋት አንዲት መንገድ ስትኾን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ እኔም ጌታችሁ ነኝና #አምልኩኝ ِ ። 6:102 ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ ስለዚህ #አምልኩት ُ ፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው፡፡
15399
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B8%E1%8B%8B
ሸዋ
ሽዋ በኢትዮጵያ ገጸ ምድር መሃል ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ሥፍራ ነው። ለብዙ መቶ ዓመታት በሉዐላዊነት በራሱ መሪዎች ሲተዳደር የኖረ የኢትዮጵያ አካል ሲሆን፣ ርዕሰ ከተማው እስከ ፲፰፻፹፱ ዓ/ም በሰሜን ሸዋ ውስጥ በየጊዜው በተለያዩ ሥፍራዎች ሲፈራረቅ ቆይቶ ባለፉት መቶ በላይ ዓመታት ግን አዲስ አበባ ሆናለች። ደብረ ብርሃን፤ አንኮበር፤ አንጾኪያ፤ ልቼ እና እንጦጦ በተለያዩ ጊዜያት የሸዋ ርዕሰ ከተማዎች ነበሩ። የሸዋ ገጸ ምድር እምብርት ባሁኗ ኢትዮጵያ መሃል የሚገኙት ተራራዎች ናቸው። በአህመድ ግራኝ ወረራ ጊዜ የባሌ ክፍለ ሀገር ከተወሰደ በኋላ የሸዋ ድንበር የኢትዮጵያ የደቡብ-ምሥራቅ ድንበር ነበር። የግዛቱ ተራራማነት የተፈጥሮ መከላከያ በመሆን ከውጭ ወረራ ለመላ አገሪቱ ደጀን የነበረና በፍትህ የአስተዳደር ዝናውም ለሌላ የኢትዮጵያ ዜጋዎች መጠጊያና መሸሸጊያም ነበር። አንዳንዴም በወራሪ ሕዝቦች ምክንያት ከቀሪው የኢትዮጵያ ግዛቶች ተግንጥሎም አብዛኛው የሰሜን ሸዋ ግዛቶች፣ ማለትም ሰላሌ(ግራሪያ)፤መርሃቤቴ፤ ደራ፤ መንዝ፤ ተጉለት፤ ይፋት፤ ምንጃር እና ቡልጋ ሕዝብ ክርስቲያን አማራ እና ኦሮሞዎች ናቸው። ደቡብ እና ምሥራቅ ሸዋ ግን አብዛኛው የኦሮሞ ብሔር እና የእስላም ኃይማኖት ተከታዮች ናቸው። በሰሜን ሸዋ ብዙ ታሪካዊ አብያተ ክርሲያናት እና ገዳማት ይገኛሉ። ከነዚህም በዋናነት የሚጠቀሰው፣ አቡነ ተክለ ኃይማኖት በሰላሌ ወረዳ የመሠረቱት ታዋቂው የደብረ ሊባኖስ ገዳም ይገኙበታል። የሰላሌ ታዋቂ ሰው : ቀደምት ታሪክ ሸዋ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪክ የተመዘገበችው በ896 እ.ኤ.አ. በተመሠረተውና ዋና ከተማውን ወለላ ()ላይ አድርጎ በነበረው የእስላም ግዛት ውስጥ ነው በማለት በኢትዮጵያ ታሪክ ዘጋቢዎች ይታመናል። ከነዚህም አንድ፣ ስለ ኢትዮጵያ ብዙ ትምህርታዊ መጽሐፍትን የደረሰው ሀንቲንግፎርድ () ነው። ይህ ግዛት ወደ ፲፪፻፸፮ ዓ/ም በይፋቱ ሱልጣን ሥር ተጠቃለለ። በቅርብ ጊዜ በፈረንሳይ የሥነ-ቅርስ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ሦስት ቦታዎች የሸዋ እስላማዊ ንጉዛት(በዘውድ የሚተዳደር ግዛት) የከተማ ማእከላት ናቸው ተብለው ተገምተዋል። አጼ ይኩኖ አምላክ የዘመኑን የዛግዌ ስርወ መንግሥት በመቃወም ሲነሱ ከክርስቲያን አማራዎች አገር ከሸዋ እንደተነሱ እና ቀድሞውንም የአክሱም ነገሥታት በጉዲት መነሳት ሥልጣናቸውን ሲለቁ ከዛች ንግሥት በመሸሽ ተከታዮቻቸውንና ቤተ ሰባቸውን ደብቀው የኖሩት በዚሁ በሸዋ ውስጥ ነበር። እንዲሁም ክብረ ነገሥት (አንቀጽ 39) እንደሚለው፣ ሸዋ የአጼ ቀዳማዊ ምኒልክ ክፍላገር ሆኖ ነበር። ሆኖም አንዳንድ ዘመናዊ ሊቃውንት የዳሞትና የአክሱም መንግሥታት ሥልጣን እስከ ሸዋ ድረስ ወደ ደቡብ እንዳልተዘረጋ የሚል ጥርጣሬ አለባቸው። በ፲፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መላው ክርስቲያን ኢትዮጵያ በአህመድ ግራኝ ሠራዊት (አዳል) በተወረረ ጊዜ ሸዋ ተመልሶ የእስላም አገር ሆነ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እስከ ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ የሸዋ ታሪክ እምብዛም ባይዘገብም አጼ ልብነ ድንግል እና ልጆቻቸው በወረራ ጊዜያት ሸዋን መሸሻቸው አድርገውት እንደነበር ተጽፏል። የሸዋ ነገሥታት ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በይኵኖአምላክ ጊዜ ከደብረ ሊባኖስ ወደ ሐይቅ በመጡት በአባ ተክለሃይማኖት እገዛ እንደተመሠረተ ይታመናል። የአኵስም ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በዮዲት ጕዲት ተንኮታኩቶ ወደመጥፋት ደርሶ ነበረ። የዮዲት ጕዲት ጦር በሸዋ ጭፍሮች ከተሸነፈ ወዲህም ሰሎሞናዊው ሥርወ መንግሥት አላንሰራራም ነበር። ይኵኖአምላክም ከንግሥናው በፊት በይፋት፣ በመርሐ ቤቴ፣ በተጕለትና በመንዝ ኖሯል። ከይኵኖአምላክም ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት ውስጥ 99 ሀገራትን (በሓውርት) ያስገበረው ዓምደ ጽዮን ደማቅ ታሪክ ካላቸው ነገሥታት መሃል አንዱ ነው። ከግራኝ ይማም አሕመድ በኋላ ጎንደር መናገሻ ከመሆኗ ጋራ ተያይዞ የሸዋ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት ለጎንደሩ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት መሠረት ሆኗል። ከዚያም በኋላ በ17ኛው ክ/ዘመን ነጋሢ ይፋት አካባቢ ያለውን ቦታ ይቆጣጠር ጀመር። በይፋዊ ታሪክ፣ የነጋሢ አባት ልብሰ ቃል (በመንዝ የአጋንቻ ጌታ) በአጼ ልብነ ድንግል ታናሽ ልጅ በያዕቆብ በኩል የሚመጣ በአባት በኩል የዘር ሐረግ ያለው ነው ይላል። ይህም ማለት ከሰለሞን ስርወ መንግስት ጋር የተያያዘ ነው ማለት ነው። በዚህ መሰረት የጎንደር ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት ከሸዋ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በኋላ የመጣና ያበበ ነው ማለት ይቻላል። የሸዋ መሪዎች ማዕረጋቸው ደግሞ በሸዋ ብቻ የሚገኘው መርዕድ አዝማች ነበር። የነጋሢ ልጁ ስብስትያኖስ የመጀመሪያው መርዕድ አዝማች ነበር። ተከታታይ መሪዎች ይሄንን ማዕረግ ሲጠቀሙበት ቆይተው የመርዕድ አዝማች ወሰን ሰገድ ልጅ ሣህለ ሥላሴ በአባታቸው ወንበር ሲቀመጡ ንጉሠ ሸዋ ተባሉ። ከሳቸውም በኋላ ልጃቸው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ለስምንት ዓመታት ነግሠው ጥቅምት ፴ ቀን ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ሲያርፉ ልጃቸው አቤቶ ምኒልክ ገና ሕጻን ነበሩ። ወዲያው በዓፄ ቴዎድሮስ ተማርከው መቅደላ ከኖሩ በኋላ አምልጠው ሸዋ ሲገቡ በአባታቸው ወንበር ንጉሠ ሸዋ ተብለው ነገሡ።ከርሳቸው በኋላ ቀዳማዊ ግርማዊ ኃይለ ሥላሴ የሸዋ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት የመጨረሻው ንጉሥ ናቸው። በ፲፱፻፳፫ ዓ/ም የንጉሠ ነገሥትነቱ በትረ ሥልጣን ወደ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሲዘዋወር፤ አልጋ ወራሽነቱን እና የጥንቱን የሸዋ መሳፍንት ማዕርግ ለልጃቸው አስፋ ወሰን ሰጥተዋቸው ልዑል መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ተባሉ። የሸዋ አማርኛ በተለምዶ የሸዋ አማርኛ የሚባለው ርቱዕ አማርኛ ነው። አሁን ላይ በመላው የኢትዮጵያ ክፍላተ ሀገራት ቅቡልነት አግኝቷል። ለአማርኛ መዝገበ ቃላት መዳበርም የሸዋ ሊቃውንት የማይተካ ድርሻ አበርክተዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የቆየ ታሪክ ካላቸው አካባቢዎች አንዱ የሰሜን ሸዋ ዞን ነው፡፡ ፲፭ሺ ፱፻ ነጥብ ፺፯ ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው የሰሜን ሸዋ ዞን በሁለት የከተማ አስተዳደሮችና በሃያ ሁለት ወረዳዎች ተከፋፍሎ ፪ ነጥብ ፫ ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርበት ሲሆን ውርጭ፣ ቆላ፣ ደጋና ወይና ደጋ የአየር ንብረቶችን አካቶ ይዟል። አዋሳኞቹም በምዕራብ፣ በደቡብ ምዕራብ፣ በደቡብና ደቡብ ምስራቅ ኦሮሚያ ክልል፣ በሰሜን ምስራቅ አፋር፣ በሰሜን ደቡብ ወሎና ኦሮሚያ ዞኖች ናቸው። ዞኑ ከቅድመ ታሪክ ጀምሮ እስከ ታሪክ ዘመን ያሉ አሻራዎች የሚገኙበት ስለመሆኑ የሥነ ቅርስ ግኝቶች ይጠቁማሉ። ከ፲፪፻፸ ዓ/ም እስከ ፲፭፻፳፯ ዓ/ም ድረስ «የሰሎሞን ስርወ መንግሥት» የመራሄ መንግሥቱ ዋና ማዕከል እንደነበረም የተለያዩ የታሪክ ምንጮች ይገልፃሉ። የሰሜን ሸዋ ምሥራቃዊ ክፍል ከ፰፻፸፪ ዓ/ም ጀምሮ ዋነኛው የእስልምና ስርወ መንግሥት መቀመጫ ከመሆኑ ባሻገር ከ፲፪ኛው እስከ ፲፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ የይፋት ስርወ መንግሥት የማዕከላዊ መንግሥቱ ተቀናቃኝ ኃይል እስከመሆን ደርሶ ነበር። በመጨረሻም ከሌሎች ታሪካዊ ሁኔታዎች ጋር ተደማምሮ በ፲፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የእስልምናው ኃይል በግራኝ አህመድ መሪነት በማየሉና በማሸነፉ ማዕከላዊ መንግሥቱ ከሸዋ ወደ ጎንደር ለመዛወር ተገዷል። በ፲፮፻፺፮ ዓ/ም በመንዝ የተንቀሳቀሰው የሸዋ ስርወ መንግሥት እንደገና ማዕከላዊ መንግሥቱ ወደ ሸዋ በመመለሱ በዘመናዊ ታሪካችን ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በእነዚህ የታሪክ ሂደቶችም ሰሜን ሸዋ የበርካታ ጥንታዊ የታሪክና የባህል ነፀብራቅ የሆኑ አሻራዎች ባለቤት ሊሆን ችሏል። ታሪካዊ ቦታዎች ደብረ ብርሃን - በ፲፬፻፵፮ ዓ/ም በዓፄ ዘርአ ያዕቆብ የተቆረቆረችውና ስያሜዋን ያገኘችው የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና ከተማ አንጎለላ - ከደብረ ብርሃን ከተማ በስተ ምዕራብ አሥር ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና ሸዋን ከ ፲፰፻፭ ዓ/ም እስከ ፲፰፻፵ ዓ/ም ባስተዳደሩት ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የተመሠረተችው የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ የትውልድ ቦታ። የቁንዲ ከተማ - ረጅሙን የዞኑን ተራራ ተንተርሳ የምትገኘው የቁንዲ ከተማ ሌላዋ ታሪካዊ ቦታ ናት። ከተማዋ የተመሰረተችው በመርዕድ አዝማች ወሰን ሰገድ ነው። ከአንኮበር አሥር ኪሎ ሜትር ሲቀር በምትገኘው ቁንዲ የሚገኘው ቤተ መንግሥት በግንብ የተከበበ እንደነበረ በዙሪያው የሚታየው ፍርስራሽ ያረጋግጣል። የቁንዲ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንም የዚያን ዘመን የእደ ጥበብ ውጤት ያንፀባርቃል። አልዩ አምባ - የአንኮበር ታሪክ ሲዘከር የስምጥ ሸለቆ አካል የሆነችው የአልዩ አምባ ከተማና የአብዱል ረሱል የእስልምና መቃብር ሥፍራ አብረው የሚጠቀሱ ናቸው። አልዩ አምባ ከአንኮበር ከተማ አሥራ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ቁልቁል ሲወረድ ትገኛለች። አልዩ አምባ እንደ ሐረር በግንብ የተከበበች ስትሆን በምስራቅ፣ በደቡብና በምዕራብ በሮች አሏት። ከመካከለኛው ዘመን ጀምሮ እስከ ፳ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ድረስ በኢትዮጵያ ታሪክ ጥንታዊ ከሚባሉት የቀረጥ ኬላዎችና የንግድ ማዕከል አንደኛዋ ነበረች። የፈረንሲስ ዲፕሎማት ሮቺ ሄሪኮርት እንደፃፈው ከ፲፭፻ እስከ ፲፯፻ የሚጠጉ ግመሎች የአገር ውስጥ ምርት ወደውጭ ያጓጉዙባት ነበር። በ፲፰፻፴፬ ዓ/ም እና ፲፰፻፴፭ ዓ.ም በአገራችን መጀመሪያ የሆነው የቀረጥ ውል የተፈረመው በአልዩ አምባ ገበያ መሠረት ነው። በከተማዋ ከፐርሽያ ( ኢራን) ፣ ከህንድና ከአረብ አገሮች የሚመጡ በርካታ የውጭ አገር ዜጎች ይኖሩባት እንደነበርም ጎብኝዎች ጽፈውላታል። በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመን የቀረጥ መሥሪያ ቤት ሲከፈት በአልዩ አምባ የጉምሩክ ጽሕፈት ቤት ሥራውን እንዲጀምር ተደርጎ ነበር። ስልክም ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ ከእንጦጦ እስከ አልዩ አምባ ድረስ መስመር ተዘርግቶለት ነበር። አልዩ አምባ የተዳከመችው የባቡር ሐዲድ በከተማዋ ማለፍ ባለመቻሉና ወደ ድሬ ዳዋ በመዛወሩ መሆኑ ይነገራል። ዛሬ የአልዩ አምባ ገበያ አብዛኛዎቹን አርጎባዎች ይዞ የአፋርንና አማራ ብሔረሰቦችን ያገናኛል። ሳላይሽ የጦር መሳሪያ ግምጃ ቤት - (ኮረማሽ ከደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ ዋናውን መንገድ ተከትሎ አምሣ አራት ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ ሐሙስ ገበያ ላይ ወደግራ በመታጠፍ አሥራ ሦሥት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የኮረማሽ ከተማ ይገኛል። የዳግማዊ ምኒልክ የመሳሪያ ግምጃ ቤቶች፣ አሰራራቸው የዕንቁላል ቅርጽ የሆነ አስራ አራት ሕንጻዎች አሉ። ቤቶቹ ከአድዋ ድል ማግስት ለጦር መሣሪያ ማከማቻነት ተብለው የተሰሩ ሲሆን የቦታው የተፈጥሮ አቀማመጥ የጐብኝን ቀልብ ይስባል። የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቶቹ ቀደም ሲልም ለአፈንጋጭ ባለሥልጣናት እስር ቤት በመሆን አገልግለዋል። ከእስረኞቹ መካከልም ልጅ ኢያሱ ይጠቀሳሉ። የአቡኑ ከተማ ሰላ ድንጋይ - ከደብረ ብርሃን በስተሰሜን ሰባ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች። ለሠላሳ ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ፓትሪያርክ የነበሩት ግብፃዊው አቡነ ማቴዎስ መንበረ ጵጵስናቸው በዚችው በሰላ ድንጋይ ነበር። በ፲፰፻፸፭ ዓ/ም እሳቸው ያሠሩት የሰላ ድንጋይ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ አደጋ ቢፈርስም እንደገና በ፲፱፻ ዓ/ም በዳግማዊ ምኒልክ ልዩ ትዕዛዝ ተሠርቶ ምኒልክ ባሉበት በአቡኑ ተባርኳል። የቤተክርስቲያኑ ሕንፃ የውስጥ አሠራር ውበት ዓይንን የሚማርክና የዘመኑን የሕንፃ ሥራ ልዩ ችሎታ የሚመሰከር ነው። በውስጡም ከግብጽ የመጣውን የአቡነ ማቴዎስ መቀመጫ ጨምሮ በርካታ የታሪክና የባህል ቅርሶች ይገኙበታል። ሰላ ድንጋይ የንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የትውልድ ሥፍራም ናት። በእናታቸው በወይዘሮ ዘነበወርቅ እንደተሰራችና በስማቸውም የምትጠራው ሰገነት ከተሰራች ብዙ ዘመናት አስቆጥራለች። ሰላ ድንጋይ የአብዛኛዎቹ የሸዋ ነገሥታት ሚስቶችና እቁባቶች መቀመጫ ስለነበረች የወይዘሮዎች ከተማ በመባልም ትታወቃለች። ባልጭ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን - የሚገኘው ከደብረ ብርሃን ፪፻፷ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ባልጭ ከተማ ነው። ቤተ ክርስቲያኑ የተመሠረተው በ፲፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዓፄ ገላውዲዎስ ሲሆን ዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸ዎቹ አሳድሰውታል። በቅድስቱ ግድግዳ ላይ የተሳሉት ጥንታዊ የፈትል ስእሎች ከመንፈሳዊ መግለጫነት ባሻገር ደጃዝማች ምኒሊክ በልጅነታቸው በዓፄ ቴዎድሮስ ሲማረኩ፣ በ፲፰፻፶፯ ዓ.ም ከመቅደላ ሲያመልጡና በኋላም በፍቼ ከተማ ከዓፄ ዮሐንስ ጋር ያካሄዱትን ስምምነት የሚገልጹ ናቸው። በመካነ ፈውስነቱ በአገራችን ስሙ እየገነነ የመጣው የሸንኮራ ዮሐንስ ፀበልም የሚገኘው ከባልጭ ከተማ የአሥራ አምስት ደቂቃ የእግር ጉዞ በኋላ ነው። ፀበሉ ቀደም ሲል በሽተኞችን ያድን እንደነበር ይነገር እንጅ ቀሳውስትና የፀበሉ አስተዳዳሪዎች ግን ከ፲፱፻፶፯ ዓ.ም ጀምሮ ዝናው እንደታወቀ ይናገራሉ። ፀበሉ የሚገኝበት አካባቢ ዳገታማና ቁልቁለት በመሆኑ ከአዲሱ ዩሐንስ ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ አጠገብ ሆኖ ሲመለከቱት የአካባቢውን አስደናቂ መልክአ ምድራዊ አቀማመጥና በተፈጥሮ ውበት የታደለውን የመስህብ ሥፍራ ማየት ያስደስታል። ወፍ ዋሻ ደን - በሰሜን ሸዋ ከሚገኙ የተፈጥሮ መስህብ ስፍራዎች መካከል የወፍ ዋሻ ደን አንዱ ነው። ደኑ አምስት ወረዳዎችን፡- ጣርማበር፣ ቀወትን፣ አንኮበርን፣ ላሎማማንና ጌራቀያን የሚያካልል ሲሆን አሥራ ሰባት ሺህ ሄክታር የሚጠጋ የቆዳ ስፋት አለው። ደኑ ጎሽ ሜዳ፣ ወፍ ዋሻና ጓሳ በተባሉ የጉብኝት ሥፍራዎች የተከፋፈለ ነው። የጣርማ በር ዋሻ - ሰው ሰራሽ የሆነው የጣርማ በር ዋሻ የወፍ ዋሻ ደን አካል ነው። ከ፲፱፻፳፱ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፴፪ ዓ/ም ባሉት ዓመታት በኢጣልያኖች የተሠሩት የጣርማ በር ዋሻዎች ሶስት ሲሆኑ ትልቁ የ ፮፻፵፪ ሜትር ርዝመት አለው። የአገራችን ረጅሙ የመሬት ውስጥ መንገድ ከመሆኑም በተጨማሪ ሰሜን ኢትዮጵያን ከደቡብ ጋር የሚያገናኝ ዋና ጐዳና ነው። የጐዜ መስጊድ - ከደብረ ብርሃን ከተማ ፺፫ ኪሎ ሜትር ርቃ ከምትገኘው የሸዋሮቢት ከተማ በስተ ምዕራብ ላይ ይገኛል። የጐዜ መስጊድ በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የይፋት ስርወ መንግሥት ከፍተኛ ደረጃ በደረሰበት ዘመን ከተሠሩት አርባ መስጊዶች ውስጥ አንዱና የመጨረሻው መሆኑ ይነገራል። ከ፭፻ ዓመታት በላይ እድሜ እንዳለው የሚነገርለት ይህ መስጊድ አሠራሩ አራት ማዕዘን ሲሆን ግድግዳውና ጣራው ባልተጠረቡ ድንጋዮች የተገነባ ነው። የድንጋዩን ክዳን የተሸከሙት አራት አግዳሚ የጣውላ ወራጆች ሲሆኑ ምሰሶዎቹ አራት ናቸው። መስጊዱ የአርጐባ መንደሮች በስተግርጌው አድርጎ ከኮረብታ ላይ ይገኛል። በዙሪያው ጥንታዊ የመቃበር ሥፍራ፣ የድሮ ነዋሪዎች የውሃ ማጠራቀሚያ ጉድጓዶች እንዲሁም በውስጥ የቆዩ የሃይማኖቱ መሪዎች አራት ጦሮች አሉ። ቀደም ሲል በመስጊዱ ዙሪያ የአርጐባ ማኅበረሰብ አባላት ይኖሩ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ኮረብታውን ለቀው ከግርጌው መንደራቸውን መሥርተው ይኖራሉ። ይሁን እንጅ ዛሬም ቢሆን መስጊዱ ዋነኛ የእምነት ቦታቸው ነው። በታላቁ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው ይህ መስጊድ የአርጐባን ብሔረሰብና በአካባቢ ያለውን ውብ የተፈጥሮ መስህብ በስተግርጌው አድርጎ ሲታይ ዓይንን ይማርካል። የሙሽራ ድንጋዮች - በተለምዶ የሙሽራ ድንጋዮች በመባል የሚታወቁት ትክል ድንጋዮች ከአጣዬ ከተማ በምዕራብ በኩል ፳፩ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ልዩ ሥፍራው ገድሎ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ይገኛሉ። ገድሎ ሜዳ ደጃዝማች ምኒልክ በ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም ከመቅደላ እስር ቤት አምልጠው ሲሄዱ በምትካቸው በዓጼ ቴዎድሮስ ተሹመው ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ጦርነት ያደረጉበት ሥፍራ ነው። ጦርነቱም በዓፄ ምኒልክ አሸናፊነት ተጠናቋል። “ሙሽራ ድንጋዮች” በገድሎ ሜዳ ምዕራባዊ ዳርቻ ላይ የሚገኙ የሰው ቅርጽ ያላቸው ትክል ድንጋዮች ናቸው። ትክል ድንጋዮቹ ቆመውና ካሉበት ሳይነሱ የሚገኙ ፳፩፣ በሥፍራው ወድቀው የሚገኙ ፪፣ ከሥፍራው ተነስተው ገበሬዎች ለእርሻ ድንበር መለያ የተጠቀሙባቸው ፵፬ ናቸው። የሙሽራ ድንጋዮች ስያሜቸውን ያገኙበት በአንድ ወቅት በመንገድ ላይ እያሉ ሙሽሮችና ሠርገኞች ባደረጉት ከልክ ያለፈ ጭፈራ እግዚአብሔርን በማሳዘናቸው ተረግመው ወደ ቤታቸው ሳይመለሱ ወደ ድንጋይነት ተቀይረው በዚያው እንደቀሩ ይነገራል። የሙሽራ ድንጋዮች ታሪካዊ አመጣጥ ከላይ በተገለጸው አኳኋን የተለየ ጥንታዊ ሰዎች ለአንድ ዓላማ ያቆሟቸው ትክል ድንጋዮች ናቸው ተብሎ ይታመናል። ምናልባትም ከአክሱም ዘመን በፊት ጀምሮ ሲያያዝ የመጣ የእደ ጥበብ ውጤት እንደሆነ ይገመታል። የሙሽራ ድንጋዮች በአብዛኛው ከደቡብ ኢትዮጵያ የጥያ ትክል ድንጋዮች ጋር ተመሳሳይነት አላቸው። እነዚህ ምስጢርን ያዘሉ የታሪካችን አሻራዎች ለጥናትና ምርምር የሚጋብዙና ለተመልካች ደግሞ የሚያዝናኑ ናቸው።
52821
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%AD%E1%88%B1%E1%88%9D%20%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%A5%E1%89%B5
አክሱም መንግሥት
የአክሱም መንግሥት (ኤርትሪያ) መንግሥተ አክሱም (ግዕዝ) በ1ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ–ሐ. በ960 ዓ.ም የአክሱም ወይም የአክሱም ንጉስ ኢንዱቢስን የሚያሳይ የአክሱማይት ገንዘብ ንጉሥ የሚያሳይ ምንዛሬ የአክሱም መንግሥት በከፍተኛ ደረጃ በ6ኛው ክፍለ ዘመን የአክሱም መንግሥት በከፍተኛ ደረጃ በ6ኛው ክፍለ ዘመን ካፒታል ኤርትራ አክሱም ኩባር/ጃርማ (ከ800 ዓ.ም. በኋላ) የተለመዱ ቋንቋዎች (ከ1ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ) ክርስትና (ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፤ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በኋላ በይፋ) አክሱማይት አምልኮተ አምልኮ (ከ350 በፊት ይፋ የሆነ) የአጋንንት ስም(ዎች) አክሱማይት፣ ኢትዮጵያዊ፣ አቢሲኒያ የመንግስት ንጉሳዊ አገዛዝ • ሐ. 100 ዛ ሃቃላ (በመጀመሪያ የታወቀው) • ሐ. 940 ዲል ናኦድ (የመጨረሻ) ታሪካዊ ዘመን ክላሲካል ጥንታዊነት እስከ መጀመሪያው የመካከለኛው ዘመን • የተቋቋመ በ 1 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ • ቀደምት የደቡብ አረቢያ ተሳትፎ 3 ኛው ክፍለ ዘመን • የሜሮን ድል • የኢዛና ወደ ክርስትና መቀየሩ • የሂሚያራይት መንግሥት ወረራ • ቀደምት የሙስሊም ወረራዎች 7 ኛው ክፍለ ዘመን • በንግስት ጉዲት ተደምስሷል ሐ. በ960 ዓ.ም 1,250,000 ኪሜ2 (480,000 ካሬ ማይል) ምንዛሬ ምንዛሬ የቀደመው በ ተሳክቷል። የዛግዌ ሥርወ መንግሥት የሲሚን መንግሥት የሸዋ ሱልጣኔት ዛሬ በከፊል የአክሱም መንግሥት (ግእዝ፡ መንግሥተ አክሱም፣ )፣ እንዲሁም የአክሱም መንግሥት ወይም የአክሱም ኢምፓየር በመባል የሚታወቀው፣ በሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ እና በደቡብ አረቢያ ላይ ያተኮረ መንግሥት ከጥንት ጀምሮ እስከ መካከለኛው ዘመን መጀመሪያ ድረስ ያለ መንግሥት ነበር። የአሁኗ ኤርትራን፣ ሰሜናዊ ጅቡቲን እና ምስራቃዊ ሱዳንን የሚሸፍን ሲሆን በንጉሥ ካሌብ ዘመነ መንግስት ወደ ደቡብ አረቢያ አብዛኛው ክፍል ዘልቋል። አክሱም ለብዙ መቶ ዘመናት የመንግሥቱ ዋና ከተማ ሆና ስታገለግል በ9ኛው ክፍለ ዘመን ግን የንግድ ትስስር በመቀነሱ እና በተደጋጋሚ የውጭ ወረራ ምክንያት ወደ ጃርማ ተዛወረ። ከቀደምት የዲኤምቲ ስልጣኔ በመነሳት መንግስቱ የተመሰረተው በ1ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ሳይሆን አይቀርም። የቅድመ-አክሱማዊ ባህል በከፊል የዳበረው ​​በደቡብ አረቢያ ተጽዕኖ ምክንያት ነው፣ በጥንቷ ደቡብ አረቢያ ስክሪፕት አጠቃቀም እና በጥንታዊ ሴማዊ ሀይማኖት ልምምዶች ላይ ይታያል። ነገር ግን የግእዝ ፊደል በ4ኛው ክፍለ ዘመን ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን መንግሥቱ በሮም እና በህንድ መካከል ባለው የንግድ መስመር ላይ ዋና ኃይል እየሆነ ሲመጣ ወደ ግሪኮ-ሮማን የባህል ሉል በመግባት ግሪክን እንደ ቋንቋ መጠቀም ጀመረ። የአክሱም መንግሥት በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአክሱም ኢዛና ሥር ክርስትናን የመንግሥት ሃይማኖት አድርጎ የወሰደው በዚህ ነው። አክሱማውያን ወደ ክርስትና መምጣታቸውን ተከትሎ የሃውልት ግንባታ አቆሙ። የአክሱም መንግሥት በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከነበሩት አራት ታላላቅ ኃያላን መንግስታት ከፋርስ፣ ሮም እና ቻይና ጋር በመሆን በፋርስ ነቢይ ማኒ ነበር። ከኢንዱቢስ የግዛት ዘመን ጀምሮ አክሱም እስከ ቂሳርያ እና ደቡባዊ ህንድ ባሉ ቦታዎች የተቆፈሩትን የራሱን ሳንቲሞች ያወጣል። ግዛቱ በጥንት ዘመን መስፋፋቱን ቀጠለ፣ ሜሮንን በመቆጣጠር በጣም አጭር ጊዜ ወሰደ፣ ከርሱም "ኢትዮጵያ" የሚለውን የግሪክ አገላለጽ የወረሰ ነው። የአክሱማውያን የቀይ ባህር የበላይነት ያበቃው በአክሱም ካሌብ ዘመነ መንግስት ሲሆን በባይዛንታይን ንጉሠ ነገሥት ጀስቲን ቀዳማዊ ትዕዛዝ የአይሁድ ንጉሥ በዱ ኑዋስ በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለውን ስደት ለማስቆም በየመን የሚገኘውን የሂሚያራይት መንግሥት ወረረ። ከሂያር ጋር በመቀላቀል፣ የአክሱም መንግሥት በግዛቱ ትልቁ ነበር። ሆኖም ግዛቱ በአክሱማይት-ፋርስ ጦርነቶች ጠፍቷል። የመንግሥቱ አዝጋሚ ማሽቆልቆል የጀመረው በ7ኛው ክፍለ ዘመን ነው፣ በዚህ ጊዜ ምንዛሪ ማውጣት አቆመ። የፋርስ (በኋላም ሙስሊሞች) በቀይ ባህር ውስጥ መገኘታቸው አክሱምን በኢኮኖሚ እንዲሰቃይ አድርጓቸዋል፣ እናም የአክሱም ከተማ ነዋሪ ቁጥር ቀንሷል። ከአካባቢያዊ እና ውስጣዊ ሁኔታዎች ጎን ለጎን, ይህ የመቀነስ ምክንያት ነው. የአክሱም የመጨረሻዎቹ ሶስት መቶ ዘመናት እንደ ጨለማ ዘመን ተቆጥረዋል፣ እናም እርግጠኛ ባልሆኑ ሁኔታዎች መንግስቱ በ960 አካባቢ ፈራረሰ። በጥንት ዘመን ከነበሩት ዋና ዋና ግዛቶች መካከል አንዱ ቢሆንም፣ የአክሱም መንግሥት በመካከለኛው ዘመን ሁሉ ኢትዮጵያ ተገልላ በነበረችበት ጊዜ ጨለማ ውስጥ ወደቀች። ሀ የኢዛና ድንጋይ ኢዛና ወደ ክርስትና መግባቱን እና ሜሮንን ጨምሮ በአካባቢው ያሉትን የተለያዩ ህዝቦች መገዛቱን መዝግቧል። አክሱማዊት መንህር በባላው ካላው (መተራ) ሰናፌ አቅራቢያ የአክሱም መንግሥት በኤርትራና የሚገኝ የንግድ ግዛት ነበር። ከ100-940 ዓ.ም ገደማ ነበረ፣ ከአይረን ዘመን ፕሮቶ-አክሱማይት ዘመን ሐ. ከክርስቶስ ልደት በፊት በአራተኛው ክፍለ ዘመን ታዋቂነትን ለማግኘት በአንደኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም. በአክሱም መጽሃፍ መሰረት የግዛቱ የመጀመሪያ ዋና ከተማ ማዛብር የኩሽ ልጅ ኢቲዮጲስ ነው የተሰራችው ዋና ከተማዋ በኋላ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ወደ አክሱም ተዛወረች። መንግሥቱ በአራተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ "ኢትዮጵያ" የሚለውን ስም ይጠቀም ነበር. የአክሱም ኢምፓየር በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛዎቹ የኤርትራ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ፣ በምእራብ የመን - የግብፅን ጀልባ ዲዛይን በመጠቀም የወረረውን - እና አንዳንድ የምስራቅ ሱዳን ክፍሎች ይስፋፋ ነበር። የግዛቱ ዋና ከተማ አሁን በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኝ አክሱም ነበረች። ዛሬ ትንሽ ማህበረሰብ፣ አክሱም ከተማ በአንድ ወቅት የተጨናነቀች ዋና ከተማ፣ የባህል እና የኢኮኖሚ ማዕከል ነበረች። ሁለት ኮረብታዎች እና ሁለት ጅረቶች በከተማይቱ ምስራቅ እና ምዕራብ ይገኛሉ; ምናልባት ይህንን አካባቢ ለማስተካከል የመነሻ ተነሳሽነት ሊሆን ይችላል። ከከተማው ውጭ ባሉት ኮረብታዎች እና ሜዳዎች ላይ የአክሱማውያን መቃብር ስቴሊ ወይም ሐውልት የሚባሉ የተንቆጠቆጡ የመቃብር ድንጋዮች ነበሯቸው። ሌሎች ጠቃሚ ከተሞች የሃ፣ ሃውልቲ-መላዞ፣ ማታራ፣ አዱሊስ እና ቆሃይቶ፣ የመጨረሻዎቹ ሶስት ከተሞች አሁን በኤርትራ ይገኛሉ። በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በኤንዱቢስ የግዛት ዘመን፣ የራሷን ገንዘብ ማውጣት የጀመረች ሲሆን በማኒ ከሳሳንያን ኢምፓየር፣ ከሮማ ኢምፓየር እና ከቻይና "ሶስት መንግስታት" ጋር በዘመኑ ከነበሩት አራት ታላላቅ ኃያላን መንግስታት አንዱ ተብሎ ተሰየመ። አክሱማውያን በ325 ወይም 328 ዓ.ም በንጉሥ ኢዛና ክርስትናን እንደ መንግሥታዊ ሃይማኖት የወሰዱ ሲሆን አክሱም የመስቀልን ምስል በሳንቲሞቹ ላይ የተጠቀመች የመጀመሪያዋ ሀገር ነች። በ3ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ (ምናልባትም ከ240-260 ዓ.ም.) አካባቢ፣ በሴምብሮውተስ የሚመሩት አክሱማውያን ሴሴይን አሸነፉ፣ ሴሴያ የአክሱም መንግሥት ገባር ሆነ። በ330 አካባቢ፣ የአክሱም ኢዛና ሠራዊቱን እየመራ ወደ ሜሮ ግዛት በመግባት ከተማዋን ራሷን ወረረች። አንድ ትልቅ የድንጋይ ሐውልት እዚያው ቀርቷል፣ ወረራውም በኢዛና ድንጋይ ላይ የተያያዘ ነው።
15696
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%B2%E1%8B%B3%E1%88%9B%20%E1%89%A3%E1%88%95%E1%88%8B%E1%8B%8A%20%E1%88%90%E1%8B%AD%E1%88%9B%E1%8A%96%E1%89%B5
የሲዳማ ባሕላዊ ሐይማኖት
የሲዳማ ባህላዊ ሐይማኖት ሲዳማ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል አንዱ ሲሆን፡ ቀድሞ የሲዳሞ ክፍለ አገር ይባል በነበረው እና በአሁኑ ጊዜ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት አካል በሆነው ሲዳማ ዞን ውስጥ የሚገኝ ህዝብ ነው። ህዝቡ ከሲዳማ ዞን ውጪ በአጎራባቹ የኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖች ውስጥ ይኖራል። የህዝብ ብዛቱም ከአራት ሚሊዮን በላይ እንደሆነ የተለያዩ ዶክመንቶች ያመለክታሉ። ሲዳማዎች የአፍሮ - እስያቲክ ግንድ ካላቸው እና በሰሜን አፍሪካ፣ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ እስያ ከሚነገሩ 375 ቋንቋዎች አንዱ የሆነ እና ከኩሽ ወይም ከኩሺቲክ የቋንቋ ቤተሰብ የሚመደብ ቋንቋ ይናገራሉ። ከቋንቋቸው ባሻገር እንደሌሎቹ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ሁሉ የራሳቸው የሆነ ባህል፣ እምነት፣ አስተዳደራዊ ስርዓት፣ መገበያያ ገንዘብ፣ የጊዜ እና ዘመን አቆጣጠር ስርዓት እና ሌሎች ማህበራዊ እሴቶች ያሉት ህዝብ ነው። ሲዳማዎች ለዘመናት ከአባት ወደ ልጅ እያወረሱ ካቆዩት እሴቶቻቸው መካከል ባህላዊ ሐይማኖት ይገኝበታል። በሐይማኖቱ መሰረት ሲዳማዎች በማጋኖ ( አምላክ ወይም እግዚአብሔር) ያምናሉ። ማጋኖ ፣ ሐላሌ ( እውነት) እና አካካ ( አባቶች፣ አያቶች፣ ቅድመ አያቶች) የእምነታቸው ምሰሶዎች ናቸው። በእነዚህ ሶስቱ ምሰሶዎች ላይ እና በእምነቱ አጠቃላይ ጽንሰ ሐሳብ ላይ አንዳንድ ሀሳቦችን ከማንሳት በፊት ስለአካኮዎች ወይም አባቶች፣ አያቶች፣ ቅድመ አያቶች ወይም ስለሲዳማ ጎሳዎች ትንሽ ልበል። ሲዳማዎች ከመካከለኛው ምስራቅ ባህርን ተሻግረው ወደ አፍሪካ ቀንድ መምጣታቸውን፣ በመጀመሪያ «ዳዋ» 1 ከሚባል ቦታ ላይ መስፈራቸውን ቀጥሎም በባሌ አድርገው አሁን ወዳሉበት አከባቢ መምጣታቸውን የብሔሩ ሽማግሌዎች ይተርካሉ። በትረካቸውም አሁን ወዳሉበት አከባቢ እንዲመጡ ያደረጋቸው የአባታቸው ጉዛዜ መሆኑን ይናገራሉ። እንደሽማግሌዎቹ ገለፃ፡ ሲዳማዎች የሁለት አባቶች ልጆች ሲሆኑ፡ ቡሼ የሚባለው አንደኛው አባታቸው ሲሞት ከመቃራቸው ጉድጓድ የሚወጣው አፈር ከተቀበሩ በሃላ ሲመለስ ከመሬት ከፍ ወይም ዝቅ ከሚል ቦታ እንዳይቀብራቸው በተናዘዙት መሰረት የአባታቸውን ሬሳ በተለያዩ አካባቢዎች እና ቦታዎች ለመቅበር ሞክረው ስላልተሳካላቸው መጀመሪያ ከሰፈሩበት አካባቢ ተነስተው በባሌ አድርገው እግሬ መንገዳቸውን የአባታቸውን ሬሳ እየቀበሩ እያወጡ ዛሬ ወዳሉበት አከባቢ መጥተዋል። በአከባቢውም የአባታቸውን ሬሳ ሲቀብሩ በተናዘዙት መሰረት ከመቃብር ጉድጓድ የወጣው አፈር ወደ መቃብሩ ሲመለስ ከመሬት እኩል በመሆኑ የአባታቸው የመጨረሻ የመቃብር ቦታ ሆነ። ከአባታቸው የመቃብር አከባቢ መራቅ ያልፈለጉት ሲዳማዎችም በአከባቢው ሰፍረው እስከአሁን ይኖራሉ። እንግዲህ ስለሲዳማዎች አባት ኑዛዜ አፍጻጸም ያለምክንያት አይደለም ያነሳሁት፡ በብሔሩ ባህላዊ ሐይማኖት መሰረት የእርሱ የመቃብር ቦታ እና ሌሎች መሰል የጎሳ አባቶች መቃብሮች በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ቦታ ስላላቸው ነው። ወደታች በስፋት አነሳዋለሁ። ለባህላዊ ሐይማኖቱ መሰረት የሆነው ሌላው ማጋኖ ነው። ከላይ እንዳነሳሁት የሐይማኖቱ ተከታዮች በማጋኖ ( አምላክ ወይም እግዚአብሔር ) ያምናሉ። ለማጋኖ፤ ካላቃ (ፈጣሪ)፣ ካሊቃ (ሃያል ሁሉን ቻይ) እና ሐላላንቾ (እውነተኛ) በማለት ሶስት ገጽታዎችን ይሰጡታል። ከዚህም በተጨማሪ ማጋኖ፤ እውነተኛ ወዳጅ፣ ለልጆቹ የሚሳሳ፣ የሚራራ፣ ሲያጠፉ የሚገጽጽ፣ ሀጢኣያታቸው የሚምር ሩህሩህ አባት ነው ይላሉ። በሐይማኖቱ ማጋኖ አምሳያ የለውም። በአምሳሉ የተቀረጹ ወይም የቆሙ ወይም መልኩን የሚያሳዩ ቁሶች የሏቸውም፤ ነገር ግን ቀን በቀን ከመሃከላቸው እንደሚገኝ ያምናሉ። ስሙ በራሱ የሚፈራ እና የሚከበር በመሆኑ ለመልካም ስራ ካልሆነ ለክፉ ተግባራት ማለትም ለማታለሊያነት፣ ውሸት ለመናገር፣ ወዘተ አይጠራም። ለክፋት ስሙን ማንሳት ወይም መጥራት ማጋኖን ያስቆጣል ተብሎ ይታመናል። ማጋኖ የሰውን ልጅ ከአፈር ፈጥሮ ትንፋሹን ከሰጠው በኋላ ወደ ሰማይ አረገ። ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ከፈጠው የሰው ልጅ ጋር በሐላሌ አማካይነት ይገናኝ ነበር። ሐላሌም በሰው እና በካሊቃ መካከል እንደድልድይ ሆነ ስለ ሰው ልጅ ያማልዳል ነበር። የእምነቱ ተከታዮች እንደምሉት ከሆነ፤ ሐላሌ ሲዳማዎች ከፈጣሪያቸው ጋር የሚገናኙበት ብቸኛው ድልድይ በመሆኑ ታላቅ ክብር እና ዋጋ ይሰጡት ነበር። በመጀመሪያ ላይ ሐላሌ በአይን የምታይና በእጅ የምዳሰስ፤ ሰዎች በሚያሹት ወቅት በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ የሚገኝ ብሎም በሰው ልጆች መካከል የሚመላለስ ነበር። ሐላሌ ለሲዳማዎች ቅርብ ከመሆኑ እና ሲዳማዎችም ለሐላሌ ካላቸው ክብር የተነሳ በእርሱ ይተዳደሩ ነበር፤ ሐላሌም ሲዳማን ያስተዳድር ነበር። ነገር ግን ከብዙ ዓመታት በኋላ የሰው ልጆች በክፋት፣ ጥላቻ፣ ተንኮል ፣ ክህደት እና በሌሎች ክፉ ተግባራት እየተሰማሩ የፈጣሪን ትዕዛዛት እየጣሱ ሲመጡ፤ ሐላሌ ከመሃከላቸው መመላለስን እና ማስተዳደሪን ትቶ ወደ ፈጣሪ ወይም ካሊቃ ዘንድ ለመሄድ ተነሳ። ሐላሌ ከመካከላቸው እንደማይኖር እና ጥሏቸው ወደ ካሊቃ (ማጋኖ) እንደሚሄድ የተረዱ እና ከእንግዲህ ከፈጣሪ ጋር እንደት ሆኖ እንደምገናኙ ያልተረዱት የእምነቱ ተከታዮች ሐላሌ ለማን ጥሏቸው እንደሚሄድ ጠየቁት። ሐላሌም ከእንግዲህ ከካሊቃ ጋር የምትገናኙት በአባቶቻችሁ በኩል ነው። አባቶቻችሁ ከፈጣሪ ጋር ያገናኟችሃል፣ ስለእናንተ ፈጣሪን ይማለዱላችሃል ብሏቸው ወደ ሰማይ አረገ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሐይማኖቱ ተከታዮች በሞት የተለዮቸው አባቶቻቸው፣ አያቶቻቸው፣ ቅድመ አያቶቻቸው ከማጋኖ ጋር ይኖራሉ ብለው አመኑ፤ ከማመንም በላይ ከማጋኖ ጋር ለመገናኘት አባቶቻቸውን መጠቀም ጀመሩ። በእምነቱ ፊልስፊና መሰረት «እኔ ከእኔ በላይ አባቴ ፣ ከአባቴ በላይ ቀደሚት አባቶቼ፣ ከቀደሚት አባቶቼ በላይ ካሊቃ (ማጋኖ)» ተብሎ ይታመናል። ከእምነቱ ጋር በተያያዘ እና በሌሎች ማህበራዊ ምክንያቶች የተነሳ ሲዳማዎች ለአባቶች እና ለአረጓውያን የተለየ አክብሮት አላቸው። እንግዲህ ሐላሌ ወደ ካሊቃ ካረገበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ አባቶች የእምነቱን ተከታዮች ከፈጣሪ ያገናኛሉ፣ ያስታርቃሉ፣ ስለእነርሱ ይማለዳሉ።ከዚህም ባሻገር የማህበረሰቡ ስነ ምግባር ወይም የግብረገብነት እና ሐይማኖታዊ ሕግጋት መከበራቸውን ይቆጣጠራሉ። የአባቶቻቸው የመቃብር ቦታም የእምነቱ ስነስርዓት ማካሄጃ ቦታ ሆነው ያገለግላሉ። ከላይ ከመግቢያዬ ላይ እንዳነሳሁት፤ የሲዳማ ጎሳዎች አባቶች በተለይ ሁለቱ የሲዳማ ዘር የተነሳባቸው አባቶች መቃብር ቦታዎች በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ቅዱስ ቦታዎች ናቸው። በሲዳምኛ ሞጎ ተብለው የሚታወቁት የአባቶች እና ቅድመ አባቶች ወይም የአካኮች መቃብሮች፤ ታጥረው በጥንቃቄና በንፅህና የተያዙ፣ የእምነቱ ተከታዮች ፈጣሪውን ለማምለክ የሚሰባሰብባቸው፣ እንዲሁም ፈጣሪን መማጸኛ መስዋዕቶችን የሚያቀርቡበት ቅዱስ ስፍራ ነው። በእነዚህ በትላልቅ ዛፎች በተሞሉ 2 ቅዱስ ስፍራዎች የእምነቱ መሪዎች ይኖራሉ። በጥቅሉ ቃዶ ተብሎ የሚጠሩት እነዚህ የእምነቱ መሪዎች በቁጥር አራት ሲሆኑ፤ ከስራ ሐላፊነታቸው አንፃር ጋና፣ ቃሪቻ፣ ዎማ እና ጋዳላ ይባላሉ። ከላይ እንዳነሳሁት የእምነቱን ተከታዮች ከፈጣሪ ወይም ከካሊቃ ጋር እንደድልድይ ሆኖ ያገናኛቸው የነበረው እና ያስተዳድራቸው የነበረው ሐላሌ ወደ ካሊቃ ከሄደ በሃላ ከፈጣሪ ጋር የማገናኘቱን ስራ ለአባቶች ስሰጥ ህዝቡን የማስተዳደር ስራ ሐላሌን ተክቶ እንዲሰሩ ከእምነቱ ተከታዮች መካከል ለተመረጡ ሰዎች ተሰጥቷል። ሐላፊነቱን የወሰዱት እነዚሁ ቃዶዎች ናቸው። የእምነቱ ተከታዮች ከእምነቱ እና ከእለትለት ማህበራዊ ኑሮ ጋር በተገናኘ የሚገጥሟቸውን ችግሮች እና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ መንፈሳዊ ማበረታቻዎችን እና ማህበራዊ ፍትሕ ለማግኘት ወደነዚህ ቅዱስ ቦታዎች በመሄድ ቃዶዎቹን ያገኟቸዋል። ቃዶዎቹም ሐላፊነት ከተቀበሉበት ጊዜ ጀምሮ ከቅዱስ ቦታዎቹን እየተንከባከቡ እድሜ ልካቸውን እዛው ይኖራሉ በምትካቸው ሌላ ቃዶ የሚመረጠው ሲሞቱ ብቻ ነው። አራቱም የተለያየ የስራ ሐላፊነቶች ሲኖሯቸው፤ አንደኛው በሌላኛው ስራ ላይ ጠልቃ መግባት አይችሉም። ከዚህም በተጨማሪ እነርሱ በምሰጡት ውሳኔዎች ላይ ማንኛውም ውጫዊ አካል ጠልቃ መግባት አይችልም። እንግዲህ የሲዳማ ባህላዊ ሐይማኖትን በተመለከተ በጣም በጥቂቱ ይህንን የሚመስል ሲሆን፤ ባህላዊ ሐይማኖቱ እንደሌሎቹ የዓለማችን ትላልቅ ሐይማኖቶች ሁሉ የራሱ የሆኑ ሕጎች ያሉት፣ የራሱ የሆነ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ያሉት፣ በብዙ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት፣ የራሱ የሆነ ማምለኪያ ስፍራ ያለው እና በራሱ ሙሉ የሆነ ነው። የሲዳማ ባሕላዊ ሐይማኖት የኢትዮጵያ ብሔር ነው። የኢትዮጵያ ብሔሮች
49937
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%90%E1%8A%93%20%E1%8B%88%E1%8A%A2%E1%8B%AB%E1%89%84%E1%88%9D
ሐና ወኢያቄም
ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን አባቶች እንደሚያስተምሩት አዳምና ሔዋን እግዚአብሔር አትብሉ ያላቸውን የዕፀ በለስን ፍሬ በሰይጣን ምክር ተታለው በበሉ ጊዜ ፣ ከተድላ ገነት ወጡ ፤ በፈጣሪ ፍርድም ተቀጡ ። እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን ከገነት አስወጥቶ በአንጻርዋ (በትይዩ) በደብረ ቅዱስ አኖራቸው ፤ ስለምን ቢሉ ፣ ገነትን እያስታወሱና በሩቅ እያዩ እንዲያዝኑ ፣ በዚያውም ፣ "ወደ ቀድሞው ቤታችን ወደ ገነት ይመልሰን ይሆን? " እያሉ እንዲጸጸቱ ና ወደ ነበሩበት ለመመለስ እንዲተጉ በአጠቃላይ ገነት መንግሥተ ሰማያት እንዳልጠፋች ፣ ሕልም እንዳልሆነች በእርግጥ እንዳለች በአይምሮ እንዲቀረፅ ሲል አደረገው። አዳምና ሕይዋን በደብረ ቅዱስ ከዕለታት አንድ ቀን አዳም ፣"እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ፣ ገነትን ያህል ቦታ ያጣሁት በአንቺ ምክኒያት እኮ ነው" ሲል ሔዋንን ተቆጣትና ፊት ነሣት ። በዚያም ጊዜ ሔዋን ደንግጣ ከአዳም ሸሽታ ሄደች ። አዳምም ብቻውን እያዘነና እየጸለየ ሳለ ፣ የእግዚአብሔር መልአክ ወደ አዳም መጥቶ ፣ "ከሚስትህ ጋር ተጣልተህ፣እስዋንም አባረህ እንዴት ትጸልያለህ? ሂድና ታረቃት" አለው ። አዳምም ፣ "እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ፣ ገነትን ያህል ቦታ ያጣሁት በእርስዋ ምክኒያት ስለ ሆነ አልታረቅም" አለው ። መልአኩም ፤ "በእርስዋ ምክንያት ያጣኸውን ብታጣ ከፈጣሪህ ጋር መታረቂያህ እስዋ ናትና ታረቃት" አለው ። አዳም ግን ፣ "አይሆንም አለና ጸሎቱን ቀጠለ" ። መላኩም እንደገና ወደ አዳም መጥቶ ፣ "እግዚአብሔር የቂመኛን ጸሎት አይቀበልምና በመጀመሪያ ከሚስትህ ታረቅ" አለው ። አዳምም ለመልአኩ መልሶ ፣ "አንተው ሂደህ ብታመጣልኝሳ?" ብሎ ለመነው ። መላኩም አዳም ፈቃደኛ መሆኑን ሲያውቅ ፣"እንዳባረርሃት አንተው ሂድና አምጣት እንጃ፤ እኔ ምን ባይ ነኝ " ሲል መለሰለት ። በዚያን ጊዜ አዳም ሄዶ ከሔዋን ታረቀ ፣ መለሳትም ። ከታረቁ በኋላ ከዚህም ጊዜ ጀምሮ ሁለቱም ሲጫወቱ ሔዋን አዳምን ፣ "እግዚአብሔር አምላካችን እንደተጣላን ይቀር ይሆን? አይታረቀንም ብለህ?" ስትል ጠየቀችው ። አዳምም ፣ "እግዚአብሔር መሐሪ ነውና ይታረቀን ነበር ። ዳሩ ግን አንቺ አለሽና ምን ይሆናል" አላት ። በዛም ጊዜ ሔዋን ፣ "ከእንግዲህ ወዲህ ካንተ ፈቃድ አልወጣም" አለችው ። ይህንንም ከተባባሉ በኋላ ሁለቱም እግዚአብሔርን ለመለመን ሱባኤ ገቡ ። አዳምና ሔዋን ሱባኤያቸውን ሲፈጽሙ እግዚአብሔር ተገለጠላቸውና ፣ "አዳም ሆይ ፤ከሰማየ ሰማያት ወርጄ ፣ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ እኔ አድንሃለሁ" አለው ። አዳምም ፣ "እግዚአብሔር ሆይ ፣ መቼ ነው የምታድነኝ?"ሲል ጠየቀው ። "አምስት ቀን ተኩል ሲፈፀም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ፣ በመንደርህ ተመላልሼ ፣ ተሰቅዬና ሞቼ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ሰጠው ፤ ቃል ኪዳንም ገባለት ።። "አምስት ቀን ተኩል" በእግዚአብሔር አቆጣጠር ነው "አምስት ሺህ ከአምስት መቶ ዓመት" ማለት ነው ። አዳምም በዚህ ተስፋ እየተጽናና ዘጠኝ መቶ ሠላሳ ዓመት ከኖረ በኋላ አንቀላፋ (ሞተ) ዘፍጥ.፭፥፩-፭ ። አጭር የዘር ሀረግ ለአዳም የተሰጠው ተስፋም ሲወርድ ሲዋረድ ቴክታና በጥሪቃ ከተባሉ የዳዊት ዘር ከሆኑት ከድንግል ማርያም አያቶች ደረሰ ። በዮሴፍ ሀረገ ትውልድ በኩል በአጭሩ ሲቆጠር አኪንም ኤልዮድን ወለደ ፤ ኤልዮድም አላዛርን ወለደ ፤ አላዛርም ማትያስን ወለደ ፤ ማትያስም ያዕቆብን ወለደ ፤ ያዕቆብም ዮሴፍን ወለደ ፤ ዮሴፍም በዕድሜ ሽምግልና እያለ አምላክን ለመውለድ ትንቢት የተነገረላትን ድንግል እንዲጠብቃት (እንዲያጫት) በእግዚአብሔር መልአክ ታዘዘ ማቴ.፩፥፲ ። ከዳዊት ዘር ሐረግ ትውልድ የተወለዱት የቅድስት ድንግል ማርያም ቅድም አያቶች ቴክታና በጥሪቃ በጣም የበዛ ሀብት ነበራቸው ። ነገር ግን ልጅ ስላልወለዱ በሀብታቸው ብዛት እምብዛም አይደሰቱም ነበር ። እግዚአብሔርን ግን ፍሬ እንዲሰጣቸው ሱባኤ እየገቡ ይጸልዩ ነበር ። በአንድ ወቅት ቴክታና በጥሪቃ ሱባኤ ገብተው ሳለ ራእዪ ያያሉ ፤ ራእዪውም አንዲት ነጭ እንቦሳ ጥጃ ከበረታቸው ስትወጣ ይህችም እንቦሳ ሌላይቱን እንቦሳ ስትወልድ ፣ እንዲሁ እየተዋለዱ እስከ አምስተኛይቱ እንቦሳ ይደርሳሉ ፤ አምስተኛይቱ እንቦሳ ግን ጨረቃ መሰል እንቦሳ ትወልዳለች ፤ ጨረቃይቱም ፀሐይን ትወልዳለች ። ይህንንም ራእዪ በዘመናቸው ለነበረው መፈክረ ሕልም (ሕልም ፈቺ) ሄደው ነገሩት ። እሱም ፣ "ደጋግ ልጆች ትወልዳላቹህ ። የጨረቃው ራእዪም ከሰው በላይ የሆነች ልጅ ትወልዳላቹህ ። የፀሐዩ ነገር በርቶ አልተገለጸልኝም እንደ ነብይና እንደ ንጉሥ የመሰለ ልጅ ከቤታቹህ ይወለዳል" ብሎ ነገራቸው ። የማይቀረው የአምላክ ቃል ከዚህም በኋላ ቴክታ ፀነሰች ፤ ወለደችም ስምዋንም ሄኤማን ብላ ጠራቻት ። ሄኤማን ማለት "ስለቴ ደረሰ ፤ እንደ ስለቴ ሆነልኝ" ማለት ነው ። ከዚያም ሄኤማን ዴርዴን ፣ ዴርዴን ቶና ፣ ቶና ሲካርን ወለዱ ፣ ሲካር ሄርሜላን ፤ ሄርሜላ ሐናን ወለደች ። ኢያቄምና ሐናም እንደ ሳሙኤል ወላጆች እንደ ሐናና ሕልቃና በእግዚአብሔር ፊት ደጋጎች ነበሩ ። ሁለቱ ጻድቃን ነበሩ ነገር ግን ልጅ ስላልወለዱ ልጅ እንዲያገኙ ወደ እግዚአብሔር ይጸልዩ ነበር ፤ እንዲህ ሲሉ "ሴት ልጅ ብንወልድ በቤተ መቅደስ እየኖረች እግዚአብሔርን እንድታገለግል ፤ ወንድ ልጅ ቢወለድ እንደ ነብዩ ሳሙኤል የእግዚአብሔር ካህን ሆኖ ዕድሜው ሙሉ እንዲያገለግል ለእግዚአብሔር ስዕለት አርገን እናቀርባለን" ብለው ብፅዓት ገቡ ። ሐናና ኢያቄምም በሱባኤ ቆይተውና ስዕለታቸው ተናግረው ሐምሌ ፳፱ ቀን ወደ ቤታቸው ተመለሱ ። ሐምሌ ፴ ቀን ሁለቱም ሕልም አዩ ። ሐና ለኢያቄም ፥ "ፀመር (ግምጃ) ሲያስታጥቁህ ፣ የእጅህም መቋሚያም ለምልማ አብባና አፍርታ ፍሬዋን ሰው ሁሉ ሲመገብ አየሁ" ብላ ነገረችው ። ኢያቄም በበኩሉ ፣ "ርግብ ጸዐዳ (ነጭ ርግብ) ሰባቱን ሰማያት ሰንጥቃ ወርዳ በራስሽ ላይ ስታርፍ ፣ በቀኝ ጆሮሽም ገብታ በማሕፀንሽ ስታድር አየሁ" ብሎ ነገራት ። ስለዚህ በዚህ እግዚአብሔር በገለጸላቸው ራእዪ መሠረት ነሐሴ ፯ ቀን ሐና ፀነሰች ። ሐና ድንግል ማርያምን በፀነሰች ጊዜ የመውለጃዋ ቀን እስኪደርስ የታዘዘ መልአክ ሕፃንዋን ከማንኛውም ክፉ ነገር ይጠብቃት ነበር ። ከተፀነሰችበት ቀን ጀምሮ ምንም ርኩሰት እንዳይነካት መልአኩ ጠበቃት ፤ በሐሳብም በሥጋም ድንግል ሆና ለዘላለም እንደምትኖር የተነገረላት ናትና ። ወላዲተ አምላክ ሐና ቅድስት ድንግልን በፀነሰችበት ወራት ታላቅ ደስታ ተደረገ ። ብዙ በሽተኞችም የሐናን ልብስ እየዳሰሱ ተፈወሱ ፣ ብዙ እውሮችም ልብስዋን እየነኩ ዓይኖቻቸው በሩላቸው ። ተአምራቱን ያዩ ምቀኞች ሰዎች ግን ቀንተው ሐናን ሊጣሉዋት ወሰኑ በድንጋይም ሊወግሩዋት ተስማሙ ። የእግዚአብሔርም መልአክ ለኢያቄም ተገልጾ "ወደ አድባረ ሊባኖስ ተራሮች ይዘሃት ውጣ" አለው ። ኢያቄምም መልአኩ እንዳዘዘው ወደ ሊባኖስ ተራሮች ይዝዋት ወጣ ። በዚያም አንድ ዋሻ ውስጥ ሳለች ወለደች ። ድንግል ማርያም በተወለደችበት ሰዓት ዋሻው በረቂቅ ሰማያዊ ብርሃን ተሞላ ፤ የሰማይ መላእክትም እግዚአብሔርን ሲየመሰግኑ ተሰሙ ፣ በሊባኖስ ተራሮች ጫፍ ብርሃናት እንደ ችቦ ሲበሩ ከሩቅ ታዩ ። የተስፋ ዋዜማ በድንግል መወለድም የአዳም ተስፋው ሊፈፀም ዋዜማው ተጀመረ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" ተብሎ የተነገረለት ተስፋ ሊፈፀም መሠረት ተጣለ ። ሊቃውንት ይህን አስመልክተው "አዳም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የመዳን ተስፋው ባንቺ በኩል ይሆናል" ብለው የሚያመሰግኑበት ዘመን (ዘመነ ሐዲስ) ሊጀመር አዋጅ ተነገረ ። "መሠረቶችዋ በቅዱሳን ተራሮች ናቸው" ሲል ዳዊት የተናገረው ድንግል ማርያም ከአብርሃምና ከዳዊት ዘር መወለድዋን ለመግለፅ ነው መዝ.፹፮፥፩ እንዲሁም በመዝ.፵፬፥፲፪-፲፯ ፣ በሰለሞን መኃይልም ፣ በራእዪም በትንቢተ ኢሳያስ ... በብዙ መጽሐፍት የተተነበየላት ናት ። ከ፴፫ቱ የእመብርሃን በዓላት ሁሉ የልደት በዓሏ የበለጠ መሆኑን ራሷ ቅድስት ድንግል ማርያም ፣ በቀን ሺህ ጊዜ "ሰአሊ ለነ ቅድስት" እያለ ለሚጸልይ ለአንድ ባሕታዊ እንደነገረች የቤተክርስቲያን አባቶች ይተርካሉ (ትርግዋሜ ቅዳሴ ማርያም ምዕራፍ አንድ) ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ።
10298
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%83%E1%8B%AD%E1%88%88%E1%88%9B%E1%88%AA%E1%8B%AB%E1%88%9D%20%E1%8B%B0%E1%88%B3%E1%88%88%E1%8A%9D
ኃይለማሪያም ደሳለኝ
አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በወላይታ አውራጃ በቦሎሶ ወረዳተወለዱ። የ1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአከባቢያቸው የአየርላንድ ካቶሊክ ሚሺን ባቋቋመው ት/ቤት እንደፈጸሙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወላይታ ሶዶ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፈጽመው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢንጂነሪንግ ከተመረቁ በኋላ በአርባምንጭ ውኃ ተቋም አስተማሪ ሆነው እያገለገሉ ሳሉ የማስትሬት ዲግሪያቸውን በፊንላንድ ተምፔ ዩኒቨርስቲ በጽዳት ወይም ሳኒቴሺን አጠናቀው አገር ቤት በመመለስ በአርባምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ዲን ሆነው አገልግለዋል። ከዚያም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በም/ፕሬዚዳንት፣ በፕሬዚዳንትና የኢሕአዴግ ዋና ጸሃፊ ሆነው አገልግለዋል። ተማሪ በነበሩ ጊዜ የደርግ ደጋፊ የነበሩት አቶ ሃይለማርያም፣ የማስተርስ ትምህርታቸውን ጨርሰው ሲመለሱ የመንግስት ለውጥ ስለነበረ፣ እሳቸውም የአቁዋም ለውጥ አርገው የገዚው መንግስት ደጋፊ መሆን ጀመሩ። የስልጣን ጥማታቸውንም ለማርካት፣ ከፖፑ በላየ ካቶሊክ እንደሞባለው፣ እሳቸውም የዘር ፖለቲካውን ከወያኔ ባለስልጣኖች በላይ ማናቸስ ጀመሩ። ባለቤታቸው ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ከአከባቢያቸው ከወላይታ ዞን ሲሆኑ በኢኮኖሚክስና በሥራ ሃላፊነት ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ ሲሆኑ ባለቤታቸው ወደ አዲስ አበባ እስከመጡበት ድረስ የደቡብ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ቢሮ /የባለቤታቸው/ ልዩ አማካሪና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል። ወ/ሮ ሮማን ከሃይስኩል እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድሕረ ምረቃ ድረስ ከባለቤታቸው ጋር አብረዋቸው በከፍተኛ ትምሕርት ዘልቀዋል። ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅት መሥርተው በኃላፊነት ከሰሩ በህዋላ ወደ ዩ.ኤን.ዲ.ፒ. ዓለም አቀፍ መሥሪያ ቤት ተዛውረው ሲሰሩ ቆይተው ከህዳር ወር ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የቀዳሚ ወይዘሮ ቢሮ ተረክበዋል። በዚህም ሥራ መስክ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያ ና የጎጂ ልማዶችና ባህሎች ማስወገጃ ሰሚናሮች ላይ እየተገኙ ንግግር በማድረግና ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛሉ። አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኢሕአዴግ መንግስትና የወላይታ ሕዝብ በቋንቋ ምክንያት በተፈጠረው ውዝግብ ጊዜ የ"ወጋጎዳ" ቋንቋ የወላይታ ልጆች ተገደው እንዲማሩ ጫና አርገዋል ተብለው በሌሎች የአከባቢያቸው ጎሳዎች ዘንድ አለመወደዳቸው ጥቁር ነጥብ በታሪካቸው ጥሎ እንዳለፈ ይነገራል። እንዲሁም በደቡብ ክልል የክልል ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩ ጊዜ በጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ትዕዛዝ የበላይ አለቃቸውና የክልሉን ፕሬዚዳንት የነበሩትን አቶ አባተ ኪሾን ከስልጣን የሚያስወግድ ደብዳቤ በገዛ እጃቸው የጻፉና በምትካቸው ራሳቸውን ተክተዋል እየተባሉም ይተቻሉ። ይሁን እንጂ በመንግሥት ሚዲያ በኋላ እንደተነገረው አቶ አባተ ኪሾ በሙስና ምክንያት ከስልጣን መወገዳቸው ተዘግቦአል። በዚህም የተነሳ በጊዜው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መስተዳድር አስተዳደራቸውና እውቅናቸው እይደበዘዘ ስለመጣ የአካከባቢው ተወላጆች በተደጋጋሚ በሚቀሰቅሱት ተቃውሞች ከሥልጣናቸው ተነስተው ወዲያውኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ አማካሪ ሆነው በታላቁ ቤተመንግሥት አከባቢ ቆይተው በ2003 በ8ኛው የኢሕአዴግ ጠቅላላ ስብሰባ ላይ የቀድሞውን ብሄረ አማር ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ መሪ አቶ አዲሱ አበበን በመተካት የኢሕአዴግ ምክትል ሊቀመንበር ለመሆን በቅተዋል። በተጨማሪም የደቡብ ክልላዊ መንግሥት የኢሕአዴግ ሊቀመንበር በመሆናቸው በፓርቲው ታሪክ የመጀመሪያው በትጥቅ ትግል ያልተሳተፉ ከፍተኛ ባለሥልጣን መሆን ብቻ ሳይሆን ከመለስ ዜናዊ ቀጥሎ ያለውን 2ኛውን ትልቅ ቦታ በጣም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመቆናጠጣቸውም በላይ የኢትዮጵያ 24ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። ይህም በመሆኑ፡ ከሶስት ትላልቅ ብሄሮች ውጪ ማለትም አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ ብሄር አባል ያልሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የደቡብ ተወላጅና ከኦርቶዶክስ እምነትተከታይ ውጪ ፕሮተስታንትየውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው እ.ኤ.አ ኦገስት 22 /2012 ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አቶ ኃ/ማሪያም ወደ ተጠባባቂ ጠ/ሚኒስትርነት ማዕረግ ከፍ ብለው ለአንድ ወር ያህል ከቆዩ በኋላ የገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የፓርቲው ሊቀመንበርና ባለሙሉ ስም ጠ/ሚኒስትር እንዲሆኑ በመመረጣቸው እስከ 2015 ምርጫ ቀጣዩ የኢትዮጵያ መሪ በመሆን በኢትዮጵያ ታሪክ መዝገብ ላይ ስማቸውን አኑረዋል። የሚከተለው አስረጅ ከአይጋ ፎረም የተወሰደ ነው የ47 ዓመቱ አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ በአረካ ከተማ ነው የተወለዱት ። የወጣትነት ዘመናቸውንም በዚህ በተወለዱበት ሰፍራ ያሳለፉ ሲሆን ፥ በ1980 ዓመተ ምህረት የባችለር ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና አግኝተዋል። ገና በወጣትነት ዘመናቸው የያኔውን የአርባምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የዛሬውን አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲን በመምህርነት አገልግለዋል ። በተቋሙ ቆይታቸው ባገኙት ነፃ የትምህርት እድልም ወደ ፊንላንድ በማቅናት ከታምፔሬ የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በስነ ንፅህና ምህንድስና የማስተርስ ድግሪያቸውን ተከታትለዋል ። ከተመለሱም በኋላ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዲን በመሆን ለ13 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን ፥ በነዚህ ጊዜያት ውስጥም ከአሜሪካው አዙሳ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ በድርጅት አመራር የማስተርስ ድግሪ አግኝተዋል ። አቶ ሀይለማሪያመ ደሳለኝ በ1990ዎቹ መግቢያ ላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ አባል በመሆን በአገሪቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ መሳተፍ ጀምረዋል ። የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስትን በምክትል ርእሰ መስተዳደርነት ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ሀይለማሪያም በ1998 ለአራት ዓመታት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሆነው ሰርተዋል ። በመቀጠልም አቶ ሀይለማሪያም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆን የተንቀሳቀሱ ሲሆን ፥ በምክር ቤቱ የመንግስት ጉዳዮች ተጠሪ ሚኒስትርም ነበሩ ። ከዚህ በተጓዳኝም በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አማካሪም ሆነው የሰሩ ሲሆን ፥ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች ፣ የህዝብ አደረጃጀትና ተሳትፎ ልዩ አማካሪም ሆነው የሰሩባቸው ጊዜያቶች ነበሩ ።ከ2002 አገር አቀፍ መርጫ በኋላም በድጋሚ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ሆነው የተመረጡ ሲሆን ፥ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ካቢኔ ውስጥም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነትና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ተሹመው በማገልገል ላይ ይግኛሉ ። በፓርቲያቸው ውስጥ ባላቸው እንቀስቃሴም የኢህአዴግ አባል በሆነው ድርጅታቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ንቅናቄ / ደኢህዴን/ ሊቀመንበር በመሆን ከ10 ዓመት ለሚበልጥ ጊዜ እየሰሩ ይገኛሉ ። የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልም ሲሆኑ ፥ ከሁለት ዓመት በፊት የድርጅቱ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ምክትል ሊቀመንበር ሆነውም ተመርጠዋል ። ከወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ጋር ትዳር መስርተውና ሶሳት ልጆች አፈርተው እየኖሩ የሚገኙት አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ዛሬ የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል። በፓርቲው አሰራርም መሰረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ያገለግላሉ። የኢትዮጵያ መሪዎች የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
19140
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%89%A5%E1%88%B5%E1%89%A5
ስብስብ
ስብስብ ሲባል ተለይተው ሊዘርዘሩ የሚችሉ ነገሮች ክምችት ማለት ነው። ሥነ ስብስብ የሒሳብ ጥናት መሰረት ከመሆኑ የተነሳ በአሁኑ ወቅት በሁሉም የሂሳብ ዘርፎች ሰርጾ ይገኛል። ስለሆነም ከመዋዕለ ህጻናት እስከ ዩኒቨርስቲወች ድረስ የስብስብ ጥናት እንደ ትምህርት ይሰጣል። ከላይ እንደተጠቀሰው ስብስብ ማለቱ ጥርት ብለው የተለዩ ነገሮች (የየቅል ነገሮች) ክምችት ማለት ነው። እኒህ የተከማቹ ነገሮች፣ እያንዳንዳቸው፣ የስብስቡ አባል ይሰኛሉ። የአንድ ስብስብ አባላት ማናቸውም አይነት ነገር ሊሆኑ ይችላሉ ፦ ሰወች፣ ቁጥሮች፣ ፊደሎች፣ ሌሎች ስብስቦች፣ ወዘተ... ። ስብስቦች፣ በእንግሊዝኛ ፊደላት ካፒታል ሌተር ይሰየማሉ። ስብስብ እና ስብስብ እኩል ናቸው የሚባሉት ሁለቱም ስብስቦች አንድ አይነትና አንድ አይነት ብቻ ስብስብ ሲኖራቸው ነው። ስብስብን የመግለጫ መንገዶች ስብስብን በሁለት አይነት መንገድ መግልጽ ይቻላል። አንደኛው ቃላትን በመጠቀም የስብስቡን አባላት በመወሰን ነው። ምሳሌ፡- ማለት የመጀመሪያዎቹ አራት መቁጠሪያ ቁጥሮች ስብስብ ነው ማለት የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ቀለማት ስብስብ ነው ሁለተኛው መንገድ የስብስቡን አባላት አንድ-ባንድ በመዘርዘር ይሆናል። ለዚህ ተግባር እንዲጠቅም አባላቱን በብራኬት መክበብና የእንግሊዝኛ ኮማ በአባላቱ መካከል በማስቀመጥ ነው። ለምሳሌ = {ቀይ, ቢጫ, አረንጓዴ} የስብስብ አባላት፣ እያንዳዳቸው በጠራ ሁኔታ የተለያዩ (የየቅል) መሆን አለባቸው። አባላቱ ቢደጋገሙ ምንም ለውጥ አያመጡም። በሌላ አነጋገር የአንድ ሰብስብ ሁለት አባላቱ አንድ አይነት ሊሆኑ አይችሉም። የስብስብ አባላት አደራደር ቅደም-ተከተል የለውም። እንደፈለገ ሊደረደር ይችላል። እንዲህ የሆነበት ምክንያት የስብስብ ጽንሰ ሐሳብ ዋና አላም ማን/ምን የሰብስቡ አባል ነው የሚለውን ጥያቄ ለመመልስ ስለሆነ ነው። ስለዚህም የሚከተሉት ስብስቦች እኩል ናቸው። የአንድ ስብስብ አባላት ብዙ ከሆኑና የአባላቱ ይዘት ግልጽ ከሆነ ሁሉንም አባላት መጻፍ አያስፈልግም። ለዚህ ተግባር መጠቀም ይቻላል። በብራኬት መንገድ እያንዳንዱን አባላት ሳይዘረዝሩ ስብስቡን መግለጽም ይቻላል። ለምሳሌ = {የካርታ ጨዋታ ምልክቶች} ማለቱ እኒህ ምልክቶች አባላቱ የሆነ ስብስብ ማለቱ ነው። በአጠቃላይ መልኩ ስብስብ መስሪያ አጻጻፍ የሚባለውን ዘዴ በመጠቀም ስብስቦችን በብራኬት ተጠቀመን እንዲህ መስራት እንችላለን፡፡ ለምሳሌ መቁጠሪያ ቁጥር ሲሆን; 0 ≤ እዚህ ላይ የ ምልክት ትርጓሜው "ሆኖ ሲያበቃ" እንደማለት ነው። ከላይ የተጠቀሰው ምሳሌ ሲነበብ የሁሉም ቁጥሮች 2 − 4, ስብስብ ሆኖ ሲያበቃ ደግሞ በ0 እና 19 መካከል ያለ መቁጠሪያ ቁጥር ነው"። ነገር የስብስብ አባል ከሆነ ይህ ኩነት እንዲህ ይወከላል ። በሌላ በኩል የስብስብ አባል ካልሆነ እንዲህ ይወከላል ። ሌላ ከበድ ያለ ምሳሌ ለመውሰድ ያክል = {ቀይ, ቢጫ አረንጓዴ}, እና መቁጠሪያ ቁጥር ነው; እና 0 ≤ እና 285 ∈ ; ነገር ግን እና ሰማያዊ ∉ ታህታይ ስብስብ ማናቸውም የስብስብ አባላት የስብስብ አባላት ከሆኑ፣ የ ታህታይ ስብስብ ነው እንላለን። ሲጻፍ ( ሲነበበ ስብስብ ውስጥ ይገኛል)። በዚህ ትይዩ እንዲህ በለንም መጻፍ እንችላለን , ሲነበብ የ ላዕላይ ስብስብ ነው ወይም ስብስብ ን ይጠቀልላል። የ ታህታይ ስብስብ ሆኖ ነገር ግን ሁለቱ ስብስቦች እኩል ካልሆኑ , የ ደንበኛ ታህታይ ስብስብ ይሰኛል፣ በሒሳብ ምልክት ሲጻፍ ። ሌሎች ደራሲያን ይህን ምልከት ይጠቀማሉ። ስብስብ የስብስብ ታህታይ ስብስብ ነው የሁሉ ወንዶች ስብስብ የሁሉ ሰወች ስብስብ ታህታይ ስብስብነው። ባዶ ስብስብ የማናቸውም ስብስብ ታህታይ ስብስብ ነው። ሁሉም ስብስብ በበኩሉ የራሱ ስብስብ ታህታይ ስብስብ ነው። ሁለት ስብስቦች እኩል እንደሆኑ ለማረጋገጥ የሚያገለግል መምሪያ ሐሳብ ይኼ ነው፦ ሁለት ስብስቦች እኩል የሚሆኑት እና ሲሆኑና ሲሆኑ ብቻ ነው። የስብስብ ብዛት የስብስብ ብዛት የምንለው የአንድ ስብስብ አባላትን ብዛት ነው። ለምሳሌ የስብስብ ብዛት በሒሳብ ምልክት እንዲህ ይወከላል፡ ። ለምሳሌ፡ ስብስብ የፈረንሳይ ባንዲራ ቀለሞች ስብስብ ቢሆን፣ የ ብዛት ሲሰላ ነው፣ ምክንያቱም የፈረንሳይ ባንዲራ ቀለሞች 3 ናቸውና። ባዶ ስብስብ የምንለው ልዩ ስብስብ በውስጡ ምንም አባላት የሉትም ስለሆነም ብዛቱ ዜሮ ነው እንላለን። ምልክቱም ይሄ ነው፡ ∅ ወይም ። ለምሳሌ ጎናቸው አራት የሆኑ ሶስት ማዕዘኖች ስብስብ ዜሮ አባላት ስላሉት ባዶ ስብስብ ይባላል። በተጻራሪ አንድ አንድ ስብስቦች አእላፍ ብዛት አሏቸው። ለምሳሌ የቁጥሮች ስብስብን ብንወሰድ አእላፍ አባላት አሉት። አንድ አንድ አእላፋት ከሌሎች አእላፋት የሚበልጡበት ሁኔታ ይገኛል። ለምሳሌ የውኑ ቁጥር ብዛት ከመቁጠሪያ ቁጥር ብዛት ይበልጣል፣ ምንም እንኳ ሁለቱም ብዛታቸው አእላፍ ቢሆንም። በተጻራሪ አንድ አንድ እኩል የማይመስሉ አዕላፎች እኩል ሆነው ይገኛሉ። ለምሳሌ የመስመር ቁራጭ ና የተቆረጠበት መስመር እኩል ብዛት አላቸው፣ ማለት እኩል የነጥብ ብዛት አላቸው። እኒህንና እኒህ የመሰሉ እንግዳ የአእላፍ ጠባዮች የተጠኑት በጆርጅ ካንተር ነበር። ርቢ ስብስቦች(ፓወር ሴት) የስብስብ ርቢ ስብስብ የምንለው ማናቸውንም የስብስብ ታህታይ ስብስቦች አቅፎ የሚይዝን ስብስብ ነው። ማለት ከ አባላት የሚሰሩ ማናቸውንም ስብስቦችና ባዶ ስብስብን ይይዛል። አንድ ብዛቱ አእላፍ ያልሆነ (አባላቱ የሚያልቁ) ስብስብ ብዛቱ ቢሆነ የርቢ ስብስቡ ብዛት 2 ነው። የርቢ ስብስብ እንዲህ ይወከላል ስብስብ ቢሰጠን፣ ርቢ ስብስቡ ይሄ ነው . የመጀመሪያው ስብስብ ብዛት 3 ሲሆን የርቢ ስብስቡ ብዛት 23 = 8 ነው። መሰረታዊ የስብስብ መተግበሪያወች ከተሰጠ ስብስብ ወይም ስብስቦች ሌሎች ስብስቦች ለመፍጠር የተለያዩ መተግበራዊያወች ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥ ዋና ዋናዎቹ እኒህ ናቸው ውሁድ ስብስብ ሁለት ስብስቦች "ሊደመሩ" ይችላሉ። መደመርን መተግብሪያ ውህድ ስብስብ ሲሆን፣ የ እና ውህድ እንዲህ ይጻፋል ። ትርጓሜውም በ ወይም በ የሚገኙ ሁሉም አባላት ስብስብ ማለት ነው። አንድ አንድ መሰረታዊ የውህድ ስብስብ ጸባዮች: የጋራ ስብስብ የሁለት ስብስቦችን የጋራ አባላት በመውሰድ እንዲሁ አዲስ ስብስብ መፍጠር ይቻላል። የ እና የጋራ ስብስብ እንዲህ ይወከላል ፤ ትርጓሜውም በ እና በ ውስጥ የሚገኙ የጋራ አባላቶች ስብስብ ማለት ነው። ከሆነ እና የየቅል ስብስብ ይሰኛሉ። የጋራ ስብስብ መሰረታዊ ጸባዮች: የሚሆነው ከሆነና ከሆነ ብቻ ነው። የስብስብ ውጭ ሁለት ስብስቦች ሊቀናነሱ ይችላሉ። (ወይም ) ማለቱ ማናቸውም በ ውስጥ ኖረው ነገር ግን በ የማይገኙ አባላት ስብስብ ማለቱ ነው። በአንድ አንድ ስሌቶች ማናቸውም ስብስቦች የአቃፊያቸው አለም አቀፍ ስብስብ አባል እንደሆኑ ተደርገው ሊወሰዱ ይችላሉ። ይህ ሁሉን አቃፊ ስብስብ እንዲህ ይወከላል፡ ። በዚህ ጊዜ የ ውጭ ወይንም የ ተቃርኖ ይሰኛል። አለም አቀፉ ስብስብ የመቁጠሪያ ቁጥሮችን ቢወክል, ደግሞ ተጋማሽ ቁጥሮችን, ኢተጋማሽ ቁጥሮችን ቢወክል, መሰረታዊ የውጭ ስብስብ ጸባዮች: የእና የ ሚዛናዊ ውጭ ስብስብ እንዲህ ይተረጎማል። ለምሳሌ የ እና ሚዛናዊ ውጭ ስብስብ ነው። ካርቴዣን ብዜት እያንዳንዷን የአንድ ስብስብ አባላት ከሌላው ስብስብ አባላት ጋር በማያያዝ አዲስ ስብስብ መፍጠር ይቻላል። የ ስብስብ እና ካርቴዥያዊ ብዜት እንዲህ ይወከላል ፤ ትርጓሜውም የቅደም ተከተል ጥንዶች() ስብስብ ሆኖ ሲያበቃ፣ እዚህ ላይ የስብስብ አባል ሲሆን ደግሞ የስብስብ አባል ነው ማለት ነው።ብብ መሰርታዊ የካርቴዢያዊ ብዜት ጸባዮች: እና አላቂ ስብስቦች ቢሆኑ የብዛታቸው ጸባይ እንዲህ ነው የስነ ስብስብ ቦታ በሂሳብ ጥናት የስብስብ ኅልዮት (ትምህርት) ለሁሉ የሒሳብ ትምህርት መሰረት እንደሆነ ይታመናል። ለምሳሌ አልጀብራ፣ ቡድን ሂሳብ፣ መስክ ሂሳብ፣ ቀለበት ሂሳብ በሙሉ አንድ አይነት ወም ሌላ አይነት ስብስቦች ሲሆኑ የሚለያዩትም በአንድ ወይም በሌላ መተግብሪያ (ኦፕሬሽን) ስር መዘጋታቸው ብቻ ነው። በሌላ ጎን የስብስብ ኅልዮት ለዝምድና ሂሳብ መሰረት ነው። ይሄም ለፈንክሽንና ሌሎች ጽንሰ ሃሳቦች አስፈላጊ ነው። ተጨማሪ ንባብ የውጭ ድረ ገጾች ሥነ ስብስብ ሥነ አምክንዮ
48862
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%93%E1%8D%93%20%E1%8D%8D%E1%88%AB%E1%8A%95%E1%88%B2%E1%88%B5%E1%8A%AE%E1%88%B5
ፓፓ ፍራንሲስኮስ
ፓፓ ፍራንሲስኮስ ወይም ፖፕ ፍራንሲስ፣ ልደት ስም ሖርጌ ማሪዮ ቤርጎልዮ (1929 ዓም አርጀንቲና ተወለዱ) ከ2005 ዓም ጀምሮ የሮሜ ፓፓ ወይም የሮማን ካቶሊክ መሪ ናቸው።ከ 2013 (አውሮፓውያን) ጀምሮ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ እና የቫቲካን ከተማ ግዛት ሉዓላዊ ገዥ ናቸው። ፍራንሲስ የኢየሱስ ማኅበር አባል ለመሆን የመጀመሪያው ጳጳስ ነው፣ የመጀመሪያው ከአሜሪካ፣ የመጀመሪያው ከደቡብ ንፍቀ ክበብ፣ በ 8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከገዛው ሶርያዊ ጎርጎርዮስ ሳልሳዊ በኋላ ከአውሮፓ ውጪ የመጀመሪያው ጳጳስ ነው። በቦነስ አይረስ፣ አርጀንቲና የተወለደው ቤርጎሊዮ በወጣትነት ጊዜ የኬሚስትነት ሙያ ከማሰልጠን በፊት በምግብ ሳይንስ ላብራቶሪ ውስጥ በቴክኒሻንነት ከመስራቱ በፊት በባውንተርነት እና በፅዳት ሰራተኛነት ለተወሰነ ጊዜ ሰርቷል። ከከባድ ሕመም ካገገመ በኋላ በ1958 የኢየሱስ (የጀሱሳውያን) ማኅበር አባል ለመሆን ተነሳሳ። በ1969 የካቶሊክ ቄስ ሆኖ ተሹሟል፤ ከ1973 እስከ 1979 በአርጀንቲና ውስጥ የየየሱሳውያን ጠቅላይ ግዛት የበላይ ሆኖ ተሾመ። እ.ኤ.አ. በ1998 የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ እና በ2001 በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ካርዲናል ፈጠሩ። በታህሳስ 2001 በአርጀንቲና በተፈጠረው ሁከት የአርጀንቲና ቤተ ክርስቲያንን መርተዋል። የኔስቶር ኪርችነር እና የክርስቲና ፈርናንዴዝ ደ ኪርችነር አስተዳደሮች እንደ ፖለቲካ ተቀናቃኝ አድርገው ይመለከቱት ነበር። እ.ኤ.አ. ለአሲሲው ቅዱስ ፍራንሲስ ክብር ሲል ፍራንሲስን የጵጵስና ስም አድርጎ መረጠ። በአደባባይ ህይወቱ በሙሉ፣ ፍራንሲስ በትህትናው፣ በእግዚአብሔር ምህረት ላይ አፅንዖት በመስጠት፣ በአለም አቀፍ ደረጃ እንደ ጳጳስ ታይነት፣ ለድሆች ተቆርቋሪነት እና በሀይማኖቶች መካከል ውይይት ለማድረግ ባለው ቁርጠኝነት ይታወቃሉ። ለጵጵስናው ከቀደምቶቹ ያነሰ መደበኛ አቀራረብ እንደነበረው ይነገርለታል፡ ለምሳሌ ቀደምት ሊቃነ ጳጳሳት ይገለገሉበት በነበረው የሐዋርያዊ ቤተ መንግሥት የጳጳሳት አፓርታማዎች ውስጥ ከመኖር ይልቅ በዶሙስ ሳንክታ ማርቴ የእንግዳ ማረፊያ ውስጥ መኖርን መርጧል። ፍራንሲስ ውርጃን፣ ቀሳውስትን አለማግባትን እና የሴቶችን መሾም በተመለከተ የቤተክርስቲያኗን ትውፊታዊ አመለካከቶች ይጠብቃሉ፣ ነገር ግን በዲቁናነት ዕድል ላይ ውይይት ጀምሯል እና ሴቶችን በሮማን ኪዩሪያ የዲያስትሪክት ሙሉ አባላት አድርጓል። ቤተክርስቲያኑ ለኤልጂቢቲ ማህበረሰብ አባላት የበለጠ ክፍት እና እንግዳ ተቀባይ መሆን እንዳለባት ይጠብቃል። ፍራንሲስ ያልተገራ የካፒታሊዝም እና የነፃ ገበያ ኢኮኖሚክስ፣ የፍጆታ ተጠቃሚነት እና ከመጠን በላይ እድገትን የሚተቹ እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ተሟጋቾች የሉዳቶ ሲ' አዋጅ የጵጵስና ስልጣናቸው ትኩረት ነው። በአለምአቀፍ ዲፕሎማሲ, በዩናይትድ ስቴትስ እና በኩባ መካከል ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ለማደስ እና በአውሮፓ እና በመካከለኛው አሜሪካ የስደተኞች ቀውሶች ወቅት የስደተኞችን ጉዳይ ደግፏል. ከ 2018 ጀምሮ እሱ የሕዝባዊነት ተቃዋሚ ነው።ኢኩሜኒዝምን ማስፋፋቱን ጨምሮ፣ እንዲሁም በሲቪል የተፋቱ እና እንደገና የተጋቡ ካቶሊኮች ከአሞሪስ ላቲሺያ እትም ጋር እንዲተባበሩ ማድረጉን ጨምሮ በብዙ ጥያቄዎች ላይ ከሥነ-መለኮት ወግ አጥባቂዎች ትችት ገጥሞታል። የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ጆርጅ ማሪዮ ቤርጎሊዮ ታኅሣሥ 17 ቀን 1936 (አውሮፓዊ) ወይም በኢትዮጵያ 1929 በቦነስ አይረስ ሰፈር ፍሎሬስ ተወለደ። እሱ የማሪዮ ሆሴ ቤርጎሊዮ እና ሬጂና ማሪያ ሲቮሪ የአምስት ልጆች ታላቅ ነበር። ማሪዮ ቤርጎሊዮ በጣሊያን ፒዬድሞንት ግዛት በፖርታኮማሮ (የአስቲ ግዛት) የተወለደ ጣሊያናዊ ስደተኛ አካውንታንት ነበር። ሬጂና ሲቮሪ በቦነስ አይረስ የተወለደች የቤት እመቤት ነበረች። የማሪዮ ሆሴ ቤተሰቦች ከቤኒቶ ሙሶሎኒ ፋሺስታዊ አገዛዝ ለማምለጥ በ1929 ጣሊያንን ለቀው ወጡ። ማሪያ ኤሌና ቤርጎሊዮ (በ1948 ዓ.ም.) እንደተናገረችው፣ የጳጳሱ ብቸኛ ሕያው ወንድም እህት፣ እነሱ በኢኮኖሚያዊ ምክንያቶች አልተሰደዱም። ሌሎች ወንድሞቹ አልቤርቶ ሆራሲዮ ፣ ኦስካር አድሪያን (1938 - ሟች) እና ማርታ ሬጂና ነበሩ። ሁለት የልጅ ልጅ የሆኑት አንቶኒዮ እና ጆሴፍ በትራፊክ ግጭት ሞቱ። የእህቱ ልጅ ክሪስቲና ቤርጎሊዮ በስፔን ማድሪድ ውስጥ ሰአሊ ነው። በስድስተኛ ክፍል ቤርጎሊዮ በቦነስ አይረስ ግዛት ራሞስ ሜጂያ በሚገኘው የዶን ቦስኮ የሽያጭ ሰዎች ትምህርት ቤት ዊልፍሪድ ባሮን ደ ሎስ ሳንቶስ አንጄልስ ተምሯል። በቀድሞው የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ስም የተሰየመውን ን በቴክኒካል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሎ በኬሚካል ቴክኒሻን ዲፕሎማ ተመርቋል (አንዳንድ ሚዲያዎች በስህተት እንደዘገቡት በኬሚስትሪ የማስተርስ ዲግሪ አይደለም)። በዚ ብቃቱ፣ በሂኪቲየር-ባችማን ላብራቶሪ የምግብ ክፍል ውስጥ በአስቴር ባሌስቲሪኖ ስር ሰርቶ ለብዙ አመታት አሳልፏል። ቤርጎሊዮ በኬሚካል ቴክኒሻንነት ከመስራቱ በፊት እንደ ባር ቆጣቢ እና እንደ ጽዳት ፎቆችም ሰርቷል። የ21 ዓመት ልጅ እያለ ለሕይወት አስጊ በሆነ የሳንባ ምች እና በሦስት የሳይሲስ በሽታ ተሠቃይቷል። ብዙም ሳይቆይ የሳንባ ክፍል ተቆርጧል። ቤርጎሊዮ የሳን ሎሬንዞ ደ አልማግሮ የእግር ኳስ ክለብ የዕድሜ ልክ ደጋፊ ነው። ቤርጎሊዮ የቲታ ሜሬሎ፣ ኒዮሪያሊዝም እና ታንጎ ዳንስ ፊልሞች አድናቂ ነው፣ የአርጀንቲና እና የኡራጓይ ባህላዊ ሙዚቃ ሚሎንጋ በመባል ይታወቃል። ጀሱት ቤርጎሊዮ የክህነት ጥሪውን ያገኘው የፀደይ ቀንን ለማክበር በጉዞ ላይ እያለ ነው። ኑዛዜ ለመሄድ በቤተ ክርስቲያን በኩል አለፈ፣ እናም በካህኑ ተመስጦ ነበር። ቤርጎሊዮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሴሚናሪ ኢንማኩላዳ ኮንሴፕሲዮን ሴሚናሪ በቪላ ዴቮቶ ቦነስ አይረስ ከተማረ በኋላ ከሦስት ዓመታት በኋላ ወደ ኢየሱስ ማኅበር ጀማሪ መጋቢት 11 ቀን 1958 ገባ። ያገኛትን ልጅ አፍቅሮ ሃይማኖታዊ ሥራውን ለመቀጠል በአጭሩ ተጠራጠረ። እንደ ጀማሪ ጀማሪ በሳንቲያጎ፣ ቺሊ የሰው ልጅን አጥንቷል። በኢየሱስ ማኅበር ውስጥ ከጀመረ በኋላ፣ ቤርጎሊዮ መጋቢት 12 ቀን 1960 ዓ.ም የሃይማኖታዊ ሙያውን የድህነት፣ የንጽሕና እና የሥርዓት አባል ታዛዥነትን በፈጸመ ጊዜ በይፋ ኢየሱሳዊ ሆነ። እ.ኤ.አ. በ1960 ቤርጎሊዮ በቦነስ አይረስ ግዛት ሳን ሚጌል ከሚገኘው ከኮሌጂዮ ማክስሞ ደ ሳን ሆሴ የፍልስፍና ፈቃድ አገኘ። ከ1964 እስከ 1965 በሳንታ ፌ በሚገኘው ኮሌጂዮ ዴ ላ ኢንማኩላዳ ኮንሴፕሲዮን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስነ-ጽሁፍ እና ስነ ልቦና አስተምሯል።በ1966 በቦነስ አይረስ በሚገኘው ኮሌጆ ዴል ሳልቫዶር ተመሳሳይ ኮርሶችን አስተምሯል። ፕሬስባይቴሬት እ.ኤ.አ. በ1967 ቤርጎሊዮ የነገረ መለኮት ትምህርቱን በፋኩልታዴስ ደ ፊሎሶፊያ ጀመረ እና በታህሳስ 13 ቀን 1969 በሊቀ ጳጳስ ራሞን ሆሴ ካስቴላኖ የክህነት ማዕረግ ተሹሟል። በዚያ ለነበረው ክፍለ ሀገር የጀማሪዎች አለቃ ሆኖ አገልግሏል እና የነገረ መለኮት መምህር ሆነ። ቤርጎሊዮ የመጨረሻውን የመንፈሳዊ የስልጠና ደረጃውን በአልካላ ዴ ሄናሬስ፣ ስፔን አጠናቀቀ እና የመጨረሻውን የኢየሱስዊት ቃል ኪዳን ገባ። እ.ኤ.አ. የዮም ኪፑር ጦርነት። የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በ1980 የተማሩበት የሳን ሚጌል የፍልስፍና እና ስነ መለኮት ፋኩልቲ ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ። ይህንን አዲስ ሹመት ከመውሰዱ በፊት፣ እ.ኤ.አ. በ1980 የመጀመሪያዎቹን ሶስት ወራት በአየርላንድ እንግሊዘኛ ለመማር አሳልፏል፣ በዱብሊን ሚልታውን የስነመለኮት እና የፍልስፍና ተቋም ውስጥ በጄስዊት ማእከል ቆየ። እ.ኤ.አ. እስከ 1986 ድረስ በሳን ሚጌል ለስድስት ዓመታት አገልግሏል ፣ በጄሱሳዊው ጄኔራል ፒተር ሃንስ ኮልቨንባች ውሳኔ ፣ በኢየሱስ ማኅበር ውስጥ ካለው ዓለም አቀፋዊ የማህበራዊ ፍትህን ከማጉላት አዝማሚያ ጋር በሚስማማ ሰው ተተካ ። በታዋቂው ሃይማኖታዊ እና ቀጥተኛ የአርብቶ አደር ሥራ ላይ. በጀርመን ፍራንክፈርት በሚገኘው የሳንክት ጆርጅገን የፍልስፍና እና የነገረ መለኮት ምረቃ ትምህርት ቤት የመመረቂያ ርእሶችን በማጤን ብዙ ወራት አሳልፏል። የጀርመናዊውን/ ጣሊያናዊውን የሃይማኖት ምሁር ሮማኖ ጋርዲኒ ሥራ በመቃኘት ላይ ተሰማርቷል፣ በተለይም በ1925 በዴር ጌንሣትዝ ሥራው ላይ ያሳተመውን 'ንፅፅር' ጥናት። ነገር ግን፣ በኮርዶባ ለሚገኘው የጄሱስ ማህበረሰብ መናዘዝ እና መንፈሳዊ ዳይሬክተር ሆኖ ለማገልገል ያለጊዜው ወደ አርጀንቲና ሊመለስ ነበረበት። በጀርመን በአውስበርግ የሚገኘውን ሜሪ ፣ ዩኒት ኦቭ ኖትስ የተሰኘውን ሥዕል አይቷል እና የሥዕሉን ቅጂ ወደ አርጀንቲና አመጣ እና አስፈላጊ የማሪያን አምልኮ ሆነ። በሣሌዥያ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረበት ጊዜ፣ ቤርጎሊዮ በዩክሬን ግሪክ ካቶሊክ ቄስ ስቴፋን ክዝሚል ተማክሮ ነበር። ቤርጎሊዮ ብዙ ጊዜ ከክፍል ጓደኞቹ ከሰአታት በፊት ተነስቶ ለ ቅዳሴን ለማገልገል። በ 1992 ቤርጎሊዮ ከየየሱሳውያን መሪዎች እና ሊቃውንት ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ፣የቤርጎሊዮን “አለመስማማት” ስሜት ፣ የካቶሊክ ኦርቶዶክሱን እና የነፃነት ሥነ-መለኮትን በመቃወም እና በሠራው ሥራ በ 1992 በጄሱሳውያን ባለሥልጣናት እንዳይኖር ተጠየቀ ። የቦነስ አይረስ ረዳት ጳጳስ። እንደ ኤጲስ ቆጶስነቱ ለጄሱሳዊ አለቃው ተገዥ አልነበረም። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ, እሱ ኢየሱስ ቤቶችን አልጎበኘም እና ጳጳስ ሆኖ እስከተመረጠበት ጊዜ ድረስ "ከኢየሱሳውያን የራቀ" ነበር. ቅድመ-ጳጳስ ኤጲስ ቆጶስ ቤርጎሊዮ በ1992 የቦነስ አይረስ ረዳት ጳጳስ ተብሎ ተሰይሟል እና በጁን 27 ቀን 1992 የአውካ ጳጳስ ፣ የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አንቶኒዮ ኳራሲኖ ፣ ዋና ገዳም ሆነው ቀደሱ። እንደ ኤጲስ ቆጶስነት መሪ ቃል መረጠ። በማቴዎስ 9፡9-13 ላይ “በምሕረት አይቶ ስለ መረጠው” ከሚለው የቅዱስ በዴ ስብከት የተወሰደ ነው። ሰኔ 3 ቀን 1997 ቤርጎሊዮ የመተካት መብት ያለው የቦነስ አይረስ አስተባባሪ ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ተሾመ። እ.ኤ.አ. በዚ ተግባር፣ በርጎሊዮ አዲስ አድባራትን ፈጠረ እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጽ/ቤቶችን በአዲስ መልክ አዋቅሮ፣ ለሕይወት ደጋፊ የሆኑ ተግባራትን መርቷል፣ እና የፍቺ ኮሚሽን ፈጠረ። እንደ ሊቀ ጳጳስ የቤርጎሊዮ ዋና ተነሳሽነቶች አንዱ የቤተክርስቲያንን መገኘት በቦነስ አይረስ ሰፈር ውስጥ ማሳደግ ነው። በእሱ መሪነት, በድሃ መንደሮች ውስጥ እንዲሰሩ የተመደቡት ካህናት ቁጥር በእጥፍ ጨምሯል. ይህ ሥራ "የድሆች ጳጳስ" ተብሎ እንዲጠራ አድርጎታል. ቤርጎሊዮ የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ወቅት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን አክሲዮኖች በተለያዩ ባንኮች በመሸጥ ሒሳቡን ወደ መደበኛው ዓለም አቀፍ ባንኮች ተቀይሯል። በባንክ የነበረው አክሲዮን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ወደ ከፍተኛ ወጪ እንዲሸጋገር አድርጓታል፣ በዚህም ምክንያት ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለኪሳራ እየተቃረበ ነበር። የባንኩ መደበኛ ደንበኛ እንደመሆኖ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በከፍተኛ የፊስካል ዲሲፕሊን ውስጥ እንድትገባ ተገድዳለች። እ.ኤ.አ. ህዳር 6 1998 የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ሳለ፣ በአርጀንቲና ላሉ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ለሌላቸው የምስራቅ ካቶሊኮች ተራ ተባሉ። ሜጀር ሊቀ ጳጳስ በርጎሊዮ የሼቭቹክ ዩክሬንኛ የግሪክ ካቶሊካዊ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ፣ ሥርዓት እና መንፈሳዊነት እንደሚረዳና ሁልጊዜም የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ጊዜ ለምስራቅ ካቶሊኮች እንደ ተራ ነገር “የአርጀንቲና ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅ ነበር” ብለዋል። በ2000 ቤርጎሊዮ ብቸኛው የቤተ ክርስቲያን ባለሥልጣን ነበር በ1972 የአርጀንቲናውን አብዮት ወታደራዊ አምባገነን መንግሥት በመቃወም በካህንነት ከታገደው ከጄሮኒሞ ፖዴስታ ከቀድሞው ጳጳስ ጋር ያስታረቀ። በዚያው ዓመት ቤርጎሊዮ የአርጀንቲና ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በ1970ዎቹ በቆሸሸው ጦርነት ወቅት “በአምባገነኑ ዘመን ለተፈፀሙት ኃጢአት የሕዝብን የንስሐ ልብስ መልበስ አለባት” ብሏል። ቤርጎሊዮ እንደ እስር ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የጡረተኞች መኖሪያ ቤቶች ወይም ሰፈር ባሉ ቦታዎች የእግር መታጠብን የቅዱስ ሀሙስ ስነ ስርዓት ማክበርን ልማዱ አድርጎታል። እ.ኤ.አ. በ2007፣ በነዲክቶስ 16ኛ ከሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ በፊት የነበሩትን የቅዳሴ ቅጾች ለመጠቀም አዲስ ሕግ ካወጡ ከሁለት ቀናት በኋላ፣ ብፁዕ ካርዲናል ቤርጎሊዮ በዚህ ያልተለመደ የሮማውያን ሥርዓት ለሳምንታዊ ቅዳሴ የተወሰነ ቦታ አቋቋሙ። በየሳምንቱ ይከበር ነበር። እ.ኤ.አ. ህዳር 8 ቀን 2005 ቤርጎሊዮ የአርጀንቲና ኤጲስ ቆጶስ ኮንፈረንስ ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ ለሦስት ዓመታት ። በኅዳር 11 ቀን 2008 ለሌላ የሶስት ዓመት የሥራ ዘመን ተመረጠ። የኮሚሽኑ ቋሚ የአስተዳደር አካል አባል ሆኖ ቆይቷል። ፣ የአርጀንቲና ጳጳሳዊ ካቶሊካዊ ዩኒቨርሲቲ የኮሚቴው ፕሬዝዳንት እና የቅዱስ ቤተመቅደሶች እንክብካቤ የቅዳሴ ኮሚቴ አባል። በርጎሊዮ የአርጀንቲና ካቶሊካዊ ጳጳሳት ጉባኤ መሪ በነበረበት ወቅት በቆሻሻ ጦርነት ወቅት ቤተ ክርስቲያናቸው ሰዎችን ከጁንታ ለመከላከል ባለመቻሏ የጋራ ይቅርታ ጠይቀዋል። በታህሳስ ወር 2011 75 ዓመት ሲሞላቸው ቤርጎሊዮ የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ሆነው መልቀቂያቸውን ለጳጳስ በነዲክቶስ 16ኛ በቀኖና ሕግ አስረከቡ።ነገር ግን ምንም አስተባባሪ ሊቀ ጳጳስ ስላልነበራቸው በቫቲካን የሚሾመውን ሰው በመጠባበቅ በቢሮው ቆዩ እ.ኤ.አ. በጥቅምት 14 ቀን በዚያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመደበኛነት ተጭኗል። ለሥነ ሥርዓቱ ወደ ሮም ሲሄድ እሱና እህቱ ማሪያ ኤሌና አባታቸው የተወለደበትን ሰሜናዊ ኢጣሊያ መንደር ጎበኙ። እንደ ካርዲናል፣ ቤርጎሊዮ በሮማን ኩሪያ ውስጥ ለአምስት የአስተዳደር ቦታዎች ተሾመ። እሱ የመለኮታዊ አምልኮ እና የቅዱስ ቁርባን ተግሣጽ ጉባኤ፣ የካህናት ጉባኤ፣ የተቀደሰ ሕይወት ተቋማት ጉባኤ እና ሐዋርያዊ ሕይወት ማኅበራት ጉባኤ፣ የቤተሰብ ጳጳሳዊ ምክር ቤት እና የላቲን አሜሪካ ኮሚሽን አባል ነበሩ። በዚያው ዓመት ብፁዕ ካርዲናል ኤድዋርድ ኤጋን በሴፕቴምበር 11 ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ወደ ኒውዮርክ ሲመለሱ፣ ቤርጎሊዮ በጳጳሳት ሲኖዶስ ውስጥ በሪተርተር (ዘጋቢ ፀሐፊ) ተክተው እንደ ካቶሊካዊ ሄራልድ ገለጻ፣ “እንደ ሰው ክፍት ሆኖ ጥሩ ስሜት ፈጠረ። ወደ መግባባት እና ውይይት" ብፁዕ ካርዲናል ቤርጎሊዮ በግላዊ ትሕትና፣ በአስተምህሮ ወግ አጥባቂነት፣ እና ለማህበራዊ ፍትህ ባለው ቁርጠኝነት ይታወቃሉ። ቀላል የአኗኗር ዘይቤ በትሕትና እንዲታወቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። እሱ በኦሊቮስ ከተማ ውስጥ ባለው የሚያምር ጳጳስ መኖሪያ ውስጥ ሳይሆን በትንሽ አፓርታማ ውስጥ ይኖር ነበር። የህዝብ ማመላለሻ ወስዶ የራሱን ምግብ ያበስል።በሮም የነበረውን ጊዜ ለ"መብረቅ ጉብኝት" ወስኗል። ለሊሴው ቅድስት ቴሬሴ ያደሩ እንደነበር ይታወቃል፣ እና በጻፋቸው ደብዳቤዎች ላይ የእርሷን ትንሽ ምስል "ታላቅ ሚስዮናዊት ቅድስት" በማለት ጠርቷታል። ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጆን ፖል ዳግማዊ በኤፕሪል 2 2005 ከሞቱ በኋላ ቤርጎሊዮ በቀብራቸው ላይ ተገኝተው የጵጵስና ሹመትን ለመተካት እንደ አንዱ ተደርገው ይቆጠሩ ነበር። በ2005 ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት 16ኛን በመረጠው የጳጳስ ጉባኤ እንደ ካርዲናል መራጭ ተሳትፈዋል። በብሔራዊ የካቶሊክ ዘጋቢ፣ ጆን ኤል አለን ጁኒየር በ2005 የጉባኤው ግንባር ቀደም ተዋናይ እንደነበር ዘግቧል። በሴፕቴምበር 2005 ሊምስ የተሰኘው የኢጣሊያ መጽሔት ቤርጎሊዮ በዚያ ጉባኤ ብፁዕ ካርዲናል ራትዚንገር 2ኛ እና ዋና ተፎካካሪ እንደነበር ገልጿል። እና በሶስተኛው ድምጽ 40 ድምጽ አግኝቷል, ነገር ግን በአራተኛው እና ወሳኝ ድምጽ ወደ 26 ወድቋል. የይገባኛል ጥያቄዎቹ የተመሠረቱት በጉባኤው ላይ ተገኝተው ያልታወቁ የካርዲናሎች ንብረት ናቸው በሚባል ማስታወሻ ደብተር ላይ ነው። እንደ ጣሊያናዊው ጋዜጠኛ አንድሪያ ቶርኒዬሊ፣ ይህ የድምጽ ቁጥር ለላቲን አሜሪካ ፓፓቢል ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ አልነበረውም። ላ ስታምፓ እንደዘገበው በምርጫው ወቅት ቤርጎሊዮ ከራትዚንገር ጋር በቅርበት ይከራከር ነበር፣ ካርዲናሎቹ እንዳይመርጡለት በስሜት ተማፅኖ እስኪያቀርብ ድረስ።እንደ ቶርኒዬሊ ገለጻ ቤርጎሊዮ ይህን ጥያቄ ያቀረበው ስብሰባው በምርጫው ላይ ብዙ እንዳይዘገይ ለመከላከል ነው። ጳጳስ ። እንደ ካርዲናል፣ ቤርጎሊዮ የታማኝ ማኅበራት በመባል የሚታወቀው የካቶሊክ ወንጌላዊ እንቅስቃሴ ከሆነው ከቁርባን እና ነፃ አውጪ ጋር የተያያዘ ነበር። በጣሊያን የበጋ ወራት መጨረሻ ላይ በተካሄደው የሪሚኒ ስብሰባ ተብሎ በሚጠራው አመታዊ ስብሰባ ላይ አንዳንድ ጊዜ ብቅ ብሏል። እ.ኤ.አ. በ2005፣ ካርዲናል ቤርጎሊዮ በሳን ፓትሪሲዮ ቤተክርስትያን እልቂት ለተገደሉ ስድስት የፓሎቲን ማህበረሰብ አባላት የድብደባ - ሶስተኛው የቅድስና ደረጃ ጥያቄን ፈቀዱ። በተመሳሳይ ጊዜ ቤርጎሊዮ በግድያዎቹ ላይ ምርመራ እንዲደረግ አዘዘ ይህም በብሔራዊ መልሶ ማደራጀት ሂደት ፣ አርጀንቲና ላይ ይገዛ የነበረው ወታደራዊ ጁንታ በሰፊው ተከሷል ።
12916
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%95%E1%89%A5%E1%88%AB%E1%8B%8D%E1%8B%AB%E1%8A%95%20%E1%89%B3%E1%88%AA%E1%8A%AD
የዕብራውያን ታሪክ
በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት የዕብራውያን ታሪክ በዔቦር ተወላጅ በአብርሃም (መጀመርያ አብራም ተብሎ) ይጀምራል። ከአብርሃም እስከ ሙሴ እንደ ብሉይና ሐዲስ ኪዳን አቆጣጠር አብርሃም (አብራም) ለአዳም ፳፩ኛ ትውልድ ነው። የተወለደውም ከአርፋክስድ ወገን በከለዳውያን ከተማ በከላውዴዎን ዑር ነው። ኦሪት ዘፍጥረት 11፡31 እንደሚለው፣ ይህ አብራም ከአባቱ ከታራ ቤተሠብ ጋራ ከዑር ተነሥተው ወደ ከነዓን ይሄዱ ዘንድ በካራን አገር ተቀመጡ። ስለዚህ ዑርና ካራን የተለያዩ ቦታዎች ናቸው። የከለዳውያን ዑር የሚባለው ስፍራ በአርፋክስድ ርስት ሲሆን፣ አብርሃም የደረሰበት ሥፍራ ካራን ግን በአራም ርስት በፓዳን-አራም ወይም አራም-ናሓራይም (አራም በሁለቱ ወንዞች መካከል ወይም መስጴጦምያ) ተገኘ። አብርሃም በዚህ ስፍራ በልማድም በዝምድናም ተሳስሮ አብሮ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር ተገለጠለትና እንዲህ ሲል አዘዘው። «ካገርህ ውጣ፤ ከዘመዶችህም ካባትህም ቤት ተለይ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ፤ ታላቅም ሕዝብ አደርግኻለሁ። ለበረከትም ትሆናለህ» (ዘፍ፡ ም፡ ፲፪፡ ቁ፡ ፩-፲።) ይህ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት ምናልባት 2119 ዓመት ግድም ነው። እንግዲህ አብርሃም በአንዱ እግዚአብሔር በቻ ለማምለክና እሱና ዘሩ ለእግዚአብሔር የተመረጡ እንዲሆኑ የተጠራበት ዘመን ነበር። ከዚህም ዘመን አስቀድሞ፣ ኦሪት ዘፍጥረትና መጽሐፈ ኩፋሌ እንደሚተርኩት፣ አሕዛብ ሁሉ እንደየኖኅ ልጆች ወገኖች ከባቢሎን ግንብ ሥፍራ ከሰናዖር ወደየአገራቸው ተበትነው ነበር። የካም ልጅ ከነዓን ግን የኩፋሌ ውላቸውን ፈርሶ ወደ ማዶ ባሕር በመርከብ ለመጓዝ ፈቃደኛ ሳይሆን በአርፋክስድ (በሴም) ርስት ተቀመጠና በልጁ ሲዶና ስም ከተማ ሠራ። በዚያው ዘመን አሕዛብ ሁሉ በስኅተት ተመርተው ወደ ጣኦት ቢዞሩም በከነዓን የተነሡት ሕዝቦች ልማድ በተለይ እግዚአብሔርን እንዳስጠላው ይላል። አብርሃም ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ ታዘዘ ከወገኖቹ ከከለዳውያን ተለይቶ ቤተሰቡን ይዞ ወንድሙን ሎጥን፤ ከነቤተሰቡ አስከትሎ ወደ ከነዓን አገር (ዛሬ ኢየሩሳሌም ወይም ፓለስቲን ወደሚባለው) ሄዶ ተቀመጠ። በዚያም ሲኖር ከሸመገለ በኋላ ይስሐቅን ከሚስቱ ከሳራ፤ እስማኤልን ከገረዱ ከአጋር ወለደ። ነገር ግን ከገረዱ የተወለደው ወደ ፊት ለአብርሃምና ለዘሩ የተመደበውን አገርና ዕድል አይወርስም ተብሎ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ እስማኤልን ከነናቱ አስወጥቶ ወደ ፋራን በረሓ (ዐረብ) ሰደዳቸው። ዛሬ እስላሞች ሁሉ ዓረቦች በእስማኤል በኩል የአብርሃም ልጆችና ወራሾች ናቸው ይላሉ። በተለይ ፳ኤሎች ግን በአብርሃም ልጅነት የሚመኩት በደንበኛው ልጁ በይስሐቅ በኩል የመጣውን ትውልድ በመከተል ነው። አንዳንድ ክርስቲያን ደግሞ እንደ ዮሐንስ ምጥምቁ ቃል መዳን በአብርሃም ተወላጅነት የሚሰጥ አይደለም ባዮች ናቸው። (ማቴ 3፡9፤ ሉቃስ 3፡8) ይስሐቅም ከሚስቱ ከርብቃ ኤሳውንና ያዕቆብን ወለደ። ያዕቆብ የኤሳው ታናሽ ሆኖ ሳለ ብኵርናን በምስር ወጥ ከኤሳው ከገበየ በኋላ ዐሥራ ሁለቱን የእስራኤልን የነገድ አባቶች ወለደ። ከዐሥራ ሁለቱም አንዱ ከብንያም በላይ የመጨረሻው ልጅ ዮሴፍ ነው። በዛሬ አባቶች ዘንድ እንደ ተለመደ ትንሹን ዮሴፍን አባቱ ያዕቆብ ከሌሎቹ አብልጦ ይወደው ነበርና በዚሁ ቅናት የያዛቸው ወንድሞቹ ከምድያም በከነዓን በኩል ወደ ግብፅ ለሚሔድ ነጋዴ ዮሴፍን ሸጡት። ገዥውም ዮሴፍን ይዞ ወደ አገሩ ወደ ግብፅ ከገባ በኋላ ለጶጢፋር ሸጠው። ጶጢፋርም በቤቱ እንደ አሽከር አድርጎ አስቀመጠው። ጌታውም ለጉዳዩ ወደ ውጭ በሔደበት ሰዓት የጌታው ሚስት ለሥጋ ፈቃድ ተመኘችውና ጠየቀችው። እሱም «ጌታዬ ባያይ እግዚአብሔር ያያል» የሚል የሚያስደነግጥ መልስ ሰጠና እንቢ አላት። እሷ ግን ሳታፍር ሳትደነግጥ ለማስገደድ ልብሱን ብትይዘው ልብሱን ተወላትና ወደ ውጭ ሸሸ። ከዚህ በኋላ ጌትዮው ከመንገድ ሲገባ «ይኸ ለአሽከርነት ያመጣኸው ዕብራዊ ካላነቅሁሽ ብሎ ስንተናነቅ ብጮኽበት ልብሱን ጥሎኝ ሔደ» ብላ አሳየችው። ጌትዮም ነገሩን ሳይመረምር የሚስቱን ቃል ብቻ በማመን ጻድቁን እንደ ኅጢአተኛ እወህኒ ቤት አገባው። ከዚህ ከወህኒ ቤት በሕልም አፈታት ምክንያት ወጥቶ ከግብፅ ንጉሥ ከፈርዖን ጋራ ተዋወቀና ባለሟል ሆነ። ቀጥሎም ዮሴፍ የንጉሡ የፈርዖን እንደራሴ ለመሆን በቃ። በዚህ ዘመን ግብፅን ይገዙ የነበሩት የመካከለኛው መንግሥት ፈርዖኖች ነበሩ። በዚህ ዘመን በከነዓን አገር ረኃብ ተነሥቶ ነበርና፤ የሚሸመት እኽል ለመፈለግ የሸጡት ወንድሞቹ ከከነዓን ወደ ግብፅ መጡ። እሱም ወንድሞቹን ዐወቃቸው፤ የሚፈልጉትንም እኽል ሰጣቸው። የአባቱንም ሕይወት ጠይቆ ከተረዳ በኋላም ከአባታቸው ከያዕቆብና ከሚስቶቻቸው ጋራ ከከነዓን ወደ ግብፅ መጥተው እንዲቀመጡ ነገራቸው። ከዚህ በኋላ ከእግዚአብሔር ለአባታቸው ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጣቸውን አገራቸውን ከነዓንን ትተው ያዕቆብና ልጆቹ በድምሩ ፸ ነፍስ ሆነው ግብፅ መጥተው ተቀመጡ። ወደ ግብጽ የወረዱበት ጊዜ፣ በመጽሐፈ ኩፋሌ ሲቆጠሩ፣ ከፍጥረት 2172 ዓመታት አለፉ፣ ይህም ከክርስቶስ ልደት በፊት 1900 ዓመታት ያህል ነው። ዮሴፍ ካለፈ በኋላ፣ በአባይ ወንዝ አፍ ወይም በጌሤም ለትንሽ ጊዜ ለእጭታዊ (ለ13ኛው ሥርወ መንግሥት) ተገዥ 14ኛ ሥርወ መንግሥት ተነሣ፤ እነዚህ ከከነዓን የደረሱ ሴማዊ እረኞችና ነጋዴዎች ሲባሉ የዕብራውያን ዘመን በግብጽ ሊያብራራ ይችላል። ከሙሴ እስከ ዳዊት በግብፅ ፻ ዓመት ያኽል እንደ ተቀመጡ ዘራቸው በረከተና የግብፅን መንግሥት እማሥጋት ደረሱ። ስለዚህ በበረከቱበት በመጨረሻ ጊዜ የነበረው የግብፅ ንጉሥ በእስራኤሎች ላይ በኃዘን እስኪጮሁ ድረስ አገዛዝ አጸናባቸው። ይህ ጭቆና ሙሴ በተወለደበት ሰዓት ያህል ጀመረ። እግዚአብሔር ግን ለበረከት ትሆናላችው ብሎ ለራሱ አምልኮ የመረጣቸው ሕዝቦች ናቸውና ሥቃያቸውን ተመልክቶ አዘነላቸው። ሙሴም አድጎ ወደ ምድያም ሸሽቶ የያህዌን ራዕይ በደብረ ሲና ላይ አይቶ ሕዝቡ ከግብጽ እንዲያመልጡ ታዘዘ። በሙሴም አማካይነት በልዮ ልዮ ተአምራት ከግብፅ አወጣቸው። ፈርዖኑም ከግብጽ በር ስያባርራቸው ሥራዊቱ በታላቅ ተዓምር በቀይ ባሕር ጠፋ። የዚህ ፈርዖን መታወቂያ በሰፊ ተከረክሯል። ለምሳሌ ዳግማዊ ራምሴስ እንደ ነበር የሚያስቡ ብዙ አሉ። ሆኖም ይህ ፈርዖን የገዛ በ1200 ዓክልበ. ግድም ስለ ሆነ፣ ከዳዊት ዘመን በፊት ለእስራኤል ዘመነ መሳፍንት (በመጽሐፈ መሳፍንት) ከዘጸዓት በኋላ ጊዜው አይበቃም። በመጽሐፈ ኩፋሌ ቁጥጥር ከግብጽ ታሪክ ጋር ሲስማማ፣ ዘጸዓት የሆነው በ1661 ዓክልበ. ስለ ሆነ የጠፋው ፈርዖን መርነፍሬ አይ (ከ13ኛው ሥርወ መንግሥት) ይመስላል። በመርነፍሬ አይ ዘመን መጨረሻ፣ ዕብራውያን የወጡበት ዓመት፣ የግብጽ ኃይል እጅግ ደክሞ አንድ አሞራዊ ወገን «ሂክሶስ» ወይም 15ናው ሥርወ መንግሥት ወደ ግብጽ ስሜን ወረረ፤ እነዚህ ከከነዓን ስለ ደረሱ ብዙ ጊዜ ከእብራውያን ጋር ተደናግረዋል። ኢያሱ ወልደ ነዌ ከነዓንን እያሸነፈው፣ ሂክሶስ መላውን ግብጽ ያሸነፉ ተዋጊዎች ነበሩ፣ በ1548 ዓክልበ. ፈርዖኑ አህሞስ ሂክሶስን ከግብጽ አባረራቸው እንጂ ይህ የእብራውያን ዘጸአት አልነበረም። ለእስራኤል ወደ ፊትም የሚተዳደሩበትን ሕግ በሙሴ አማካይነት ሰጣቸው። ከዚያም በኢያሱ መሪነት የከነዓንን ነገሥታት አሸንፈው ለአባታቸው ወደ ተሰጠው ወደ ከነዓን አገር ገቡ። በአብርሃምና በያዕቆብ ጊዜ ያንድ የትልቅ ሰው ቤተሰብ ብቻ የነበሩት አሁን ግን ከያዕቆብ እስከ ሳሙኤል ድረስ ፷፻ ዓመት በሚያኽል ጊዜ ውስጥ በርክተው በበረቱባቸው ጊዜዎች መንግሥት ለማቆም በቁ። መጽሐፈ መሳፍንት እንደሚተርክ፣ በሌሎች ወቅቶች በአረመኔ ጎረቤታቸው በአሕዛብ ጣኦታት ከተሳሳቱ በኋላ፣ አይሁዶች ለጊዜ ተገዥ ይሆኑ ነበር። በየተራ ለሶርያ፣ ለሞአብ፣ ለአሞን፣ ለምድያም ወዘተ. ይገዙ ነበር፣ እያንዳንዱም ጊዜ ዕብራውያን ወደ እግዜር በተመለሱበት ወቅት የሚያድናቸው ፈራጅ ወይም አለቃ ይልካቸው ነበር። ጎቶንያል፣ ናዖድ፣ ዲቦራና ባራክ፣ ጌዴዎንም በዚህ አይነት ነበሩ፣ የአረመኔ ሃይሎችን ያሸንፉ ነበር። በነዚህም ክፍለዘመናት በሥነ ቅርስ በተገኙት በሌሎች ታሪካዊ ሰነዶች እንደሚታወቅ፣ «ሃቢሩ» ወይም «አፒሩ» የተባለ ብርቱ ወገን ከከነዓናዊ ጎረቤቶቻቸው ጋራ ይታገሉ ነበር፤ ሆኖም የነዚህ «ሃቢሩ» መታወቂያ ለዘመናዊ ምዕራባውያንና አይሁዳውያን ሊቃውንት የ«ሚኒማሊስም» (ክህደት) ፍልስፍና ተከታዮች ስለ ሆኑ አጠያያቂ ጉዳይ ሆኗል። ከጌዴዎን ቀጥሎ አቢሚለክ ለሦስት ዓመታት (1252-1249 ዓክልበ. ያህል) የእስራኤላውያን አምባገነን በሴኬም ተደረገ። በእርሱ አስተዳደር ግን ሃይማኖታቸው የአረመኔ ጣኦት በአልብሪት አምልኮት ሆነ። መጨረሻውም በእርስ በርስ ጦርነት ደረሰ (መሳፍንት 9)። በሚከተሉት ፈራጆች ዘመን ዕብራውያን በተለይ በገለዓድና ኤፍሬም ሠፈሮች ይጠቀሳሉ እንጂ መላውን አገር እንዳልያዙ ይመስላል። በ1155 ዓክልበ. ግን እንደገና ፍልስጥኤም በርቶ እስራኤልን ይገዛ ጀመር። በ1135 ዓክልበ. በፍልስጥኤማውያን ሥር እየቆዩ ሶምሶን የእስራኤላውያን አለቃ ሆነ። በ1115 ዓክልበ. ኤሊ የእስራኤል ፈራጅ ሆነ። በ1076 ዓክልበ. ፍልስጥኤማውያን ታቦትን ማረኩ፤ በሚከተለው አመት ግን ሳሙኤል አስመለሰው። ስለዚህ በመጀመሪያ ጊዜ በነጌዴዎን፤ በነሶምሶን በመሳፍንቱ፤ ከዚያም በነኤሊ፤ በነሳሙኤል በካህናቱ ሲተዳደሩ ቆይተው በመጨረሻ እንደ ጎረቤቶቻቸው እንደ ፍልስጥኤማውያን፤ እንደ ሞዓባውያንና እንደ አሶራውያን «ንጉሥ» ይደረግልን ብለው ጠየቁና በእግዚአብሔር ፈቃድ በ1055 ዓክልበ. ሳሙኤል ሳኦል የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን አደረገ። ከዳዊት እስከ ባቢሎን ምርኮ ከዚያም ዳዊት ቀጥሎም ልጁ ሰሎሞን ነገሠ። በዳዊትና በሰሎሞን ዘመነ መንግሥት የእስራኤል ልጆች መንግሥታቸው ታላቅ መሆኑ በሁሉ ዘንድ ታወቀ። እነዚህ የእስራኤል ዘሮች ምንም እንኳን ቀድሞ በግብፅና በሲና በረሓ በኋላም በአገራቸው በከነዓን ሳሉ አንዳንድ ጊዜ አብረው በአሉት ሕዝብ ልማድና አምልኮ እየተዋጡ ጣዖት ማምለካቸው ባይቀር ከአብርሃም ጀምሮ እስከዚህ እስከ ሰሎሞን መንግሥት ድረስ፤ ከሰሎሞን ጀምሮም እስከ ዛሬ ድረስ በአንዱ በእግዚአብሔር ያመልካሉ። በሰሎሞንም ጊዜ ለእግዚአብሔር ትልቅ ቤተ መቅደስ ተሠራ። ስለዚህ የእውነተኛው እግዚአብሔርና የነሱም የዳዊትና ይልቁንም የሰሎሞን ስም በዓለም ታወቀ። ከክርስቶስ ልደት በፊት በሺ ዓመት ላይ ንግሥታችን ንግሥተ ሳባ የሰሎሞንን ጥበብ ለማየት ወደ ይሁዳ ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም የሔደቸው በዚህ ምክንያት ነው። ነገር ግን ከዚያ ወዲህ የተነሡት የሰሎሞን ተከታዮች አንዳንድ ነገሥታት የጎረቤቶቻቸውን የጢሮስንና የሲዶናን የባቢሎንንም አማልክት ብኤልንና ሞሎክን እያመለኩ እግዚአብሔርን አሳዘኑት። አንዱ ንጉሥ ተነሥቶ ለጣዖት አትስገድ አታምልክ፤ የሰገድህ አንደ ሆነ በአሕዛብ እጅ ትወድቃለህ የሚለውን የኦሪትን ቃል በካህናቱና በነቢያቱ አፍ ለሕዝቡ እያስነበበ ጣዖታቱን እንዲያጠፉና ሕዝቡ እውነተኛውን እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ ሲያደርግ፤ አንዱ ንጉሥ ደግሞ የማይታየውን እውነተኛውን እግዚአብሔርን ከማምለክ የሚታየውን ሐሰተኛውን ጣዖት ማምለክ ስለ መረጠና ሕዝቡም ስለ ተከተለው እስራኤል ከአምላካቸው ከእግዚአብሔር ተጣሉ። የውድቀታቸውም ዋዜማ ሲሆን ወደ ሁለት መከፈል ጀመሩ። ከሙሴ ጀምሮ እስከ ሰሎሞን ድረስ በ፩ መሪ ይተዳደሩ የነበሩት አሁን በሮብዓም ዘመን ወደ ሁለት ተከፈሉና ዐሥሩ ነገዶች ከኢየሩሳሌም በሰሜን በኩል ያለውን ሰማርያን ያዙ። የመጀመሪያውም ንጉሣቸው ኢዮርብዓም ሆነ። ሁለቱ የይሁዳና የብንያም ወገኖች በታችኛው በዚሁ በኢየሩሳሌም ቀርተው ለየብቻ ይተዳደሩ ጀመር። ስማቸውም የላይኛው የእስራኤል መንግሥት የታችኛው የይሁዳ መንግሥት ይባል ጀመር። እነዚህ ወደ ሁለት የተከፈሉት መንግሥታት አንዳንድ ጊዜ እየተጣሉ እርስ በራሳቸው ሲዋጉ፤ አንዳንድ ጊዜ እየተፋቀሩ አንድ ሆነው የእስራኤልን መንግሥት ጠላት አሶርን የይሁዳን መንግሥት ጠላት ባቢሎንን ሲወጉ ብዙ ዘመን በነጻነት ቆዩ። ከዚህ ቀጥሎ ግን ነፃነታቸው በአሶርና በባቢሎን ተደምስሶ በሰማርያ ከነገሡት ነገሥታት እነአክዓብ (አሐብ) በይሁዳ ከነገሡት እነሮብዓም፤ እነምናሴ «እኔ ነኝ አምላካችሁ ከባርነት ቤት ከምድረ ግብፅ ያወጣኋችሁ፤ ከኔ በቀር ለሌሎች አማልክት አትስገዱ» ያለውን ችላ እያሉ ሞሎክንና ብዔልን እያመለኩ ስለ አስቸገሩት፤ በወሰናቸው ያሉት በእርሱ የማያመልኩት የአሶርና የባቢሎን መንግሥታት እንዲያይሉባቸው አደረገ። ስለዚህ በሰሜን ያለውን የእስራኤልን መንግሥት አሶራውያን፤ በደቡብ በኩል ያለውን የይሁዳን መንግሥት ባቢሎናውያን በጦርነት ደመሰሱት። በሰሎሞን ጊዜ አምሮ የተሠራውም ቤተ መቅደስ ፈረሰ። የዚህ ቤተ መቅደስና የነገሥታቱም መሣሪያ ከነገሥታቱና ከሕዝቡ ጋራ በምርኮ ወደ ባቢሎን ተጋዘ። ወደ ኢየሩሳሌምም ከባቢሎን ከአሶር ከሰማሪያ ድብልቅ ዘሮች ከሰሜን፤ የኤዶምያስ ሰዎች ከደቡብ እየመጡ በየቀኑ ተሰደዱበት። ከባቢሎን ምርኮ እስከ ኢየሱስ ልደት እንግዲህ እሰከ አሁን ድረስ ምንም እንኳን በየስፍራቸው የሰዎቹ መኖር የታወቀ ቢሆን ፋርሶችም ግሪኮችም ሮማውያንም ታናሽ እስያንና የአፍሪካን ሰሜን ወረው ገና በገናንነት አልተነሡም። ነገር ግን ከኋላ ከረጅም ጊዜ በግምት ከ፬ ሺሕ ዓመት ጀምሮ እስከ አሁን እስከ ፮ኛው መቶ ዓመት ድረስ ከክርስቶስ ልደት በፊት የታወቁም ሥልጣኔም ኃይልም ያላቸው ግብፅ፤ አሶር፤ ባቢሎን፤ ኢትዮጵያ (ናፓታ)፤ ህንድ፤ ቻይና ናቸው። ነገር ግን በኋላ የታናሽ እስያን አገሮችና ግብፅን እስራኤሎችን ጭምር ቀጥቅጦ የገዛውን በነናቡከደነጾር ጊዜ የገነነውን የባቢሎንን መንግሥት የሚጥል የፋርስ መንግሥት ተነሣ። ከፋርስ በፊት ጎረቤቱ የሜዶን (ሚድያ) መንግሥት ለጥቂት ዘመን አይሎ ነበር። እስከ ባቢሎንና እስከ አሶር እስከ ኢየሩሳሌምም ደርሶ ነበር። ፋርስንም የራሱ ግዛት አድርጎት ነበር። ነገር ግን ፋርሶች ጊዜ ሲመቻቸው ከውስጣቸው ቂሮስ የሚባለውን ብልኅ ንጉሥ ባነገሡ ጊዜ የሜዶንም የአሶርም የባቢሎንም ትልቅነት ወደ ውድቀት ማዘንበል ጀመረ። ቂሮስ ከክርስትና በፊት በ፭፻፶ ዓመት በፋርስ ላይ ነገሠና መጀመሪያ የሜዶንን ቀጥሎ የልድያን መንግሥት አሸንፎ ያዘ። ከዚያም በናቡናኢድ ዘመነ መንግሥት ትልቁን የባቢሎንን ከተማ በ፭፻፴፰ ዓመት ከቦ አስጨነቀ። በመጨረሻም በጦር ኃይል አሸንፎ ያዘና ትልቁን የባቢሎንን ግዛት የፋርስ የአውራጃ ግዛቱ አደረገው። ከዚህ በኋላ በናቡከደናጾር ጊዜ በምርኮ የሄዱት የኢየሩሳሌም (የእስራኤል) ሹማምንት ተፈትተው ሁሉም ተሰብስበው ድል አድራጊው ቂሮስ ፊት በቀረቡና ባያቸው ጊዜ አዘነላቸው። ስለዚህ ምርኮኞቹ ፳ኤሎች አለቆቻቸውን ዕዝራን ነሕምያን ዘሩባቤልን ይዘው በነፃነት ወደ አገራቸው ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመለሱ ፈቀደላቸው። ከኢየሩሳሌም ቤተ መንግሥትና ከቤተ መቅደስም ተዘርፎ በባቢሎን ከተማ ለጊዜው የተገኘውን ንዋየ ቅድሳት ይዘው ሄደው የፈረሰውን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ መልሰው እንዲሠሩ አዘዛቸው። ከራሱም እርዳታ ጨመረላቸው። እስራኤሎችም ቂሮስን ተሰናብተው በሹማምንት በነዘሩባቤል በሊቀ ካህናቱም እየተመሩ በደስታ ወደ አገራቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው የከተማውንና የቤተ መቅደሱን ሥራ ጀመሩ። ሥራውንም እጅ በእጅ ብለው ቅጥሩን ሠርተው አዳረሱት። ዳሩ ግን በመካከሉ የሚያሳዝን ነገር መጣ። «እነዚህ ሰዎች ከተማቸውንና ቅጥራቸውን ሠርተው ከፈጸሙ በኋላ አይታዘዙልህም፤ የቀድሞ ታሪካቸውንም ስንመረምር አዋኪ ሰዎች መሆናቸውን ተረድተናል» ብለው ነገረ ሠሪዎችና የፋርስ መንግሥት ተመልካቾች ለንጉሡ ላኩ። ንጉሡም ምንም ደግና ብልኅ ቢሆን በእንደዚህ ያለ ዘውዱንና ገዥነቱን በሚያሠጋ ነገር መገንገኑ አይቀርምና ሥራው ይቁም የሚል ትእዛዝ አስተላለፈ። ቢሆንም በቂሮስም በዳርዮስም ጊዜ ሲከለከልም ሲፈቀድም በቀን ብዛት የኢየሩሳሌም ከተማና ቤተ መቅደስ ተሠርቶ አለቀ። ይህ ሁሉ በብሉይ ኪዳን በመጽሐፈ ነገሥትና በመጽሐፈ ዕዝራ በመጽሐፈ ዜና መዋዕል፤ በመጽሐፈ መቃያንና በዜና አይሁድም ተጽፏል። የፋርስ መንግሥት በቂሮስና በነዳርዮስ ዘመን ቅልቅ የንጉሠ ነገሥት መንግሥት ሆኖ እስከ ፫፻፴፬ ዓመት ድረስ ከቆየ በኋላ በዚህ ዘመን ከመቄዶንያ (ግሪክ) ትልቁ እስክንድር ተነሥቶ ጦሩን ይዞ ከመጨረሻው ከፋርስ ንጉሥ ከዳርዮስ ፫ኛ ጋራ ተጋጥሞ አሸንፏል። እስክንድርም የዳርዮስን ጦር ካሸነፈ በኋላ የፋርስና የግዛቱ የባቢሎን የአሶር የፓለስቲን የግብፅ ባለቤት ሆኖ፤ እስከ ህንድ ወንዝ ድረስ ገፍቷል። እስክንድር በነገሠ በ፲፫ በተወለደ በ፴፫ ዓመቱ ስለ ሞተ ግዛቱን «ዲያዶክ» የሚባሉት የጦር አለቆች ተከፋፍለው እስከ ሮማውያን መምጣት ድረስ ገዝተዋል። በፓለስቲን ያሉት እስራኤሎች ከባቢሎን ወደ ፋርስ፤ ከፋርስ ወደ ግሪክ (ከገዥ ወደ ገዥ) ከዚያም ወዲህ ቶሎሜውስ (በጥሊሞስ) በሚባሉት በግብፅ ገዥዎች ቀጥሎ ደግሞ ሴሌውሲድ በሚባሉት በሶርያ ነገሥታት ውስጥ ጥገኛም ተገዥም እየሆኑ ከክርስቶስ ልደት በፊት የሁለቱንና የአንደኛውን መቶ ዓመት ጊዜያቸውን አሳለፉ። ቶሎሜውስና ሴሌውኩስ የሚባሉት የትልቁ እስክንድር ፪ የጦር አለቆች ነበሩ። እስክንድር ከሞተ በኋላ ቶሎሜውስ በግብፅ ነገሠና ቶሎሜይ የተባለውን፤ ሴሌውኩስ በአሶርና በባቢሎን ነግሦ ሴሌውሲድ የተባለውን ቤተ መንግሥት (ዲናስቲ) የመሠረቱ ናቸው። ከዚህ በኋላ ሮማውያን ከኢጣሊያ ተነሥተው እነሺፒዮኔ የአፍሪካን፤ ሰሜን፤ እነማሪዮ እነቼዛሬ ኦታቪያኖ የፈረንሳዊን የኤስፓኝን የእንግሊዝን (ጋልያና ብሪታንያን ኤስጳንያን)፤ እነሲላ እነፓምፔዎ የባልካንን አገሮችና የታናሽ እስያን መንግሥታት ሲወሩ ፓምፔዎ (ዮሐንስ መደብር ፉምፍዮስ የሚለው) እንደ ኤውሮፓ አቆጣጠር በ፷፪ ዓመት ላይ ድል አድርጎ ፓለስቲንን ያዘ። ከዚህ በኋላ በ፳፱ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት ሮማውያንን ካዩ ጁሊዎ ቼዛሬ አታቪያኖ የሚሉት በኋላ ግርማ ያለው ጠቅላይ አለቃ ለማለት «አውግስጦስ» የሚባል የማዕረግ ስም የተጨመረለት፤ እኛ ኢትዮጵያውያን በዚሁ ይዞታ አውግስጦስ ቄሳር የምንለው በሮማ ነገሠ። ከአውግስጦስ ቄሳር ንጉሥ ቀደም ብሎ በዮልዩስ ቄሳር ጊዜ በሮማ የበላይ ገዥነት ውስጥ ትልቁ ሄሮድስ የሚባለው ንጉሥ ተብሎ ከሮማ ምክር ቤት በአርባ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት ተፈቅዶ በይሁዳ (ፓለስቲን) ተሾሟል። ሄሮድስ የኤዶምያስ ተወላጅ ነው። የኤዶምያስም ዘር ከያዕቆብ ታላቅ ወንድም ከኤሳው ትውልድ የመጣ ነው ይባላል። ሄሮድስ በይሁዳ በነገሠ ጊዜ የግሪክና የሮማን ሥልጣኔ በአገሩ ለማስገባት ፈቃደኛ ሆነ። በሮማ የነገሠውን አውግስጦስ ቄሳርንም ከልቡ ይወደው ነበርና በቀያፉ በታች በባሕር ዳር የምትገኘዋን ከተማ አሠርቶ ለእርሱ ስም መታሰቢያ እንድትሆን ቂሳርያ ብሎ ሰየማት። በዚህ ሁሉ ምክንያት ሄሮድስ በሮማውያን ዘንድ የታመነና የተወደደ ሆኖ በፓለስቲን በንጉሥነት ብዙ ጊዜ ቆየ። እንዲሁም ምንም እንኳን ባህሪዮና ምግባሩ እንደ ወገኖቹ እንደ ኤዶምያስ ቢሆን፤ ሃይማኖቱ ወደ እስራኤል የሚያደላ ስለነበር የአይሁድን ሃይማኖትና ልማድ ያከብርና ነበርና እነሱም እርሱን ይፈሩትና ያከብሩት ነበር። ዛሬ ግን በክርስቲያኖች ዘንድ ጌታችን የተወለደ ጊዜ ንጉሥ የሚሆን ሕፃን ተወለደ ማለትን ሰምቶ ከኔ በቀር ማን ንጉሥ ሊሆን ነው ብሎ ጌታችንን አብሮ ያገኘ መስሎት ብዙ ሕፃናት በማስፈጀቱ ለወዳጁ ለሄሮድያዳ ሲል የዮሐንስ መጥምቁን ራስ በማስቆረጡ እንደ ትልቅ ጨካኝና አመፀኛ የተቆጠረ ሰው ነው። ይህ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚገኘው የ፳ኤሎች ታሪክ ነው። የእስያ ታሪክ መጽሐፍ ቅዱስ
44524
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A4%E1%88%BD%E1%8A%91%E1%8A%93%20%E1%88%95%E1%8C%8D%E1%8C%8B%E1%89%B5
የኤሽኑና ሕግጋት
የኤሽኑና ሕግጋት በሁለት ጽላቶች በ1937 እና 1939 ዓ.ም. በኢራቅ ተገኙ። ምናልባት 1775 ዓክልበ. አካባቢ እንደ ኤሽኑና ሕግ ፍትሕ ሆነው ወጡ፤ የትኛው ንጉሥ እንዳወጣቸው ግን እርግጥኛ አይደለም። ከነዚህ ሕገጋት ብዙዎቹ የሐሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ. ግድም) ይመስላሉ፤ እንዲሁም ብዙዎቹ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 በሕገ ሙሴ (1661 ዓክልበ. ግድም) መልስ አገኙ። ሆኖም ከነዚህ ሕጎች መካከል ያላቸው ልዩነቶች ደግሞ ጥቂት አይደሉም። ሌሎችም ሕግጋት ነበሩ፤ ነገር ግን ጽሑፊ በፍርስራሽ ሆኖ በሙሉ ሊነበብ አይቻልም። ከተረፉት ሕግጋት መሃል፦ §1) ለአንድ ሰቀል (፱ ግራም ያህል) ብር መግዣው፦ 1 ጉር (300 ሊተር ያህል) ገብስ 3 ሊተር የሩስቱም ዘይት 12 ሊተር የሰሊጥ ዘይት 15 ሊተር ጮማ 40 ሊተር «የወንዝ ዘይት» 6 ምና (=3.24 ኪሎግራም) ሱፍ 2 ጉር ጨው 1 ጉር የድስት አመድ 3 ምና (1.62 ኪሎግራም) መዳብ 2 ምና (1.08 ኪሎግራም) የተሠራ መዳብ §2) 1 ሊተር የሰሊጥ ዘይት ለ30 ሊተር ገብስ መደበኛ ነው፤ 1 ሊተር ጮማ ለ25 ሊተር ገብስ፤ 1 ሊተር «የወንዝ ዘይት» ለ8 ሊተር ገብስ §3) የጋሪ ኪራይ ከነነጂው፣ ከነበሬው፦ 100 ሊተር ገብስ፣ ወይም 1/3 ሰቀል ብር፣ ለአንድ ቀን ይሆናል። §4) የመርከብ መጓጓዣ ኪራይ ለ1 ጉር ይዘት 2 ሊተር ገብስ ነው፤ <...> ሊተር የመርከበኛው ኪራይ ለአንድ ቀን ነው። §5) መርከበኛ ቸልተኛ ሆኖ መርከቡ ከሰመጠበት፣ የይዘቱን ዋጋ በሙሉ ይከፍላል። §6) ሰው አለግባብ የሌላውን ሰው መርከብ ከወሰደ፣ 10 ሰቀል ብር ይክፈል። §7) ምርቱን ያመረተው ዋጋ 20 ሊተር ገብስ፣ ወይም 12 ቅንጣት ብር (0.6 ግራም) ይሆናል። §8) ያመነሸው ዋጋ 10 ሊተር ገብስ ነው። §9) ሰው ለሠራተኛ ምርቱን ለማምረት ፩ ሰቀል ብር ከሰጠው፣ ሠራተኛው ግን ሥራውን ካልጨረሰው፣ በሠራተኛው ላይ የ10 ሰቀል ብር ቅጣት አለ። §9 ሀ) የማጭድ ኪራይ 15 ሊተር ገብስ ነው፣ ለባለቤቱም ይመልስ። §10) የአህያ ኪራይ 10 ሊተር ገብስ፣ የነጂውም ኪራይ 10 ሊተር ገብስ፣ ለአንድ ቀን ይሆናል። §11) የሠራተኛው ኪራይ (ደሞዝ) 1 ሰቀል ብር እና ለሥንቁ 60 ሊተር ገብስ ለአንድ ወር ይሆናል። §12) ማንኛውም ሰው በዜጋ እርሻ፣ በሰብሉ ከተያዘ፦ በመዓልት ከሆነ 10 ሰቀል ብር ይክፈል። በሌሊት በሰብሉ የተያዘው፣ ይሙት በቃ። §13) ማንኛውም ሰው በዜጋ ቤት ውስጥ ከተያዝ፦ በመዓልት ከሆነ 10 ሰቀል ብር ይክፈል። በሌሊት በቤቱ የተያዘው፣ ይሙት በቃ። §15) ነጋዴው ብር፣ ገብስ፣ ሱፍ ወይም የሰሊጥ ዘይት ከባርያ እጅ አይቀበለም። §17/18) የሰው ልጅ የሙሽሪት ማጫ ብር ለአማቱ ካመጣ፦ (ሀ) ከዚያ ከሁለቱ አንዱ ካረፈ፣ አማቱ ማጫዋን ይመልስ፤ (ለ) ሙሽሪት ወደ ቤተሠቡ ከገባች፣ ከዚያም (ልጅ ሳይወለድ) ከሁለቱ አንዱ ካረፈ፣ ያመጣው ጥሎሽ አይወጣም፤ ትርፉን ብቻ ይወስዳል። §18 ሀ) ጥሎሹም ለ፩ ሰቀል ብር የ36 ቅንጣት (1.8 ግራም) ወለድ አገድ አለው፤ ለ፩ ጉር ገብስ የ40 ሊተር ወለድ አገድ አለ።. §19) የሚከፍለው ሰው በአውድማ ይቀበል። §22) ሰው በሌላ ሰው ላይ ምንም የእዳ ነገር ሳይኖረው፣ ሆኖም የሌላውን ገረድ ከያዘ፣ የገረድ ጌታ በአምላክ ይማል፣ «አንተ በኔ ላይ ምንም ነገር የለህም»፤ ገረዱን የያዘው ሰው እንደ ገረዲቱ ዋጋ ይክፈል። §23/24) ሰው በሌላ ሰው ላይ ምንም የእዳ ነገር ሳይኖረው፣ ሆኖም የሌላውን ገረድ ከያዘ፣ በቤቱም እንድትሞት ካደረገ፣ እርሱ ለገረዲቱ ጌታ ፪ ገረዶች ይተካ። §25) ሰው በአማቱ ቤት ከታጨ፣ አማቱ ግን በድሎት ልጂቱን ለሌላ ከሰጠ፣ የልጅቱ አባት ፪ እጥፍ የማጫዋን ብር ይመልሳል። §26) ሰው ለሴት ልጅ የማጫዋን ብር ካመጣ፣ ሌላ ግን ያለ ወላጆች ፈቃድ በግድ ከያዛት፣ የሕይወት ጉዳይ ነው፤ ይሙት በቃ። §27) ሰው ወላጆቿን ሳይጠይቅ ሴት ልጃቸውን ከያዘ፦ (ሀ) ከዚያም የሠርግ ሥነ ሥርዓትና ውል ካልፈጸመ፣ ለአንድ አመት ሙሉ እቤቱ ውስጥ ብትኖርም፣ «ሚስት» አትሆንም። (ለ) ከዚያም የሠርግ ሥነ ሥርዓትና ውል ከፈጸመ፣ «ሚስት» ነች። በሌላ ሰው ጭን ከተያዘች፣ ይሙት በቃ ጉዳይ ነው። §29) ሰው በጦርነት ጊዜ ከተማረከ፣ በሌላ አገር ለረጅም ጊዜ ከኖረ፣ ሌላ ሰው ደግሞ ሚስቱን አግብቶ ልጅ ከወለደችለት፣ ቢሆንም ሰውዬው በተመለሰበት ጊዜ ወደ ሚስቱ ሊመለስ ይችላል። §30) ሰው ከተማውን ከጠላ፣ ከሸሸ፣ ሌላ ሰው ደግሞ ሚስቱን ከወሰደ፣ ሰውዬው በተመለሰበት ጊዜ ምንም ይግባኝ ማለት የለውም። §31) ሰው የሌላውን ሰው ገረድ በወሲብ ከያዘ፣ 1/3 ምና (20 ሰቀል ወይም 180 ግራም) ብር ይክፈል፤ ገረዲቱም የጌታዋ ሆና ትቅር። §32) ሰው ልጁን ለአሳዳጊነት ከሰጠ፣ ለሦስት ዓመት ስንቅ በቂ ምግብ፣ ዘይትና ልብስ ካላቀረበለት፣ 10 ምና ለልጁ አሳዳጊነት ይክፈል፣ ልጁም ለርሱ ይመልሳል። §33) ገረድ ያለ ሕግ ልጇን ለሌላ ሴት ልጅ አሳዳጊነት ከሰጠችው፣ እሱም አድጎ ጌታው ካወቀው፣ ጌታው ይዞት ሊውሰደው ይችላል። §36/37) ሰው ንብረቱ እንዲጠበቅ አደራ ቢያኖር፣ አደራ ያለው ባልንጀራ ማንም ሌባ እቤቱ ሳይገባ ንብረቱ እንዲጠፋ ካደረገ፣ ባልንጀራው ንብረቱን ለሰውዬው ይተካል። ከቤቱም ቢሰረቅ፣ የባለቤት ማጣት ነው፣ ባለቤቱ በቤተ መቅደስ ለሰውዬው በአምላክ ይማል፦ «የኔና ያንተ ንብረት አንድላይ ጠፍተዋል፣ እኔ አልከፋሁም አልበደልኩም።» ይማልና ምንም ዕዳ አይሆንበትም። §39) ሰው ድሃ ሆኖ ቤቱን ከሸጠ፤ ገዢው በፈቃዱ በሚሸጥበት ቀን ባለቤቱ ሊገዛው ይችላል። §40) ማንም ሰው ባርያ፣ ገረድ፣ በሬ፣ ወይም ሸቀጥ ከገዛ፣ ለማናቸውም ዋጋ፣ ማን እንደ ሸጠው ሊያስረዳ ካልቻለ እርሱ እራሱ ሌባው ነው። §42) ሰው የሌላውን አፍንጫ ከቈረጠ፣ ፩ ምናን ይክፈል፤ ለዓይን፦ ፩ ምና፤ ለጥርስ፦ 1/2 ምና (፴ ሰቀል)፤ ለዦሮ - 1/2 ምና። ለጥፊ፦ 10 ሰቀል ብር ይክፈል። §43) ሰው የሌላውን ጣት ከቈረጠ፣ 2/3 ምና ይክፈል። §44/45) ሰው ሌላውን በጠብ ወደ ምድር ጥሎት እጁን ከሰበረ፣ 1/2 ምና ብር ይክፈል። እግሩን ከሰበረ፣ 1/2 ምና ይክፈል። §46) ሰው ሌላውን ከመታ ክሳዱን አጥንት ከሰበረ፣ 2/3 ምና ብር ይክፈል። §47) ሰው ሌላውን በጠብ ከጎዳው፣ 10 ሰቀል ብር ይክፈል። ) ሰው በጠብ የሌላ ሰው ልጅ መሞት ካደረገበት፣ 2/3 ምና ብር ይክፈል። §49) ሰው ከተሰረቀ ባርያ ጋር፣ ከተሰረቀች ገረድ ጋር ከተገኘ፣ ባርያ ለባርያ፣ ገረድ ለገረድ መተካት አለበት።: §50) ማንም ሹም ከዜጋ የሸሸውን ባርያ፣ የሸሸችውን ገረድ፣ የባዘነውን በሬ ወይም አህያ ወደ ኤሽኑና ካላመጣው ወይም ካላመጣት፣ በቤቱም ውስጥ ከጠበቀው፣ ከአንድ ወር በላይ ካለፈ፣ ቤተ መንግሥት በስርቆት ይከሰዋል። §51) የባርነት ምልክት ያለበት የኤሽኑና ባርያ ወይም ገረድ ከኤሽኑና በር ያለ ጌታቸው አይወጡም። §52) የመንገደኛ ባርያ ወይም ገረድ ወደ ኤሽኑና በር ገብቶ የባርነት ምልክት ይቀበላል፣ በጌታውም አደራ ይቆያል። §53) በሬ ወግቶ በሬን ከገደለ፣ ሁለቱ ባለቤቶች የደኅናውን በሬ ዋጋና የሞተውን በሬ ሬሳ በትክክል ይካፈሉ። §54/55) በሬ ተዋጊ ከሆነ፣ ኃላፊውም ለባለቤቱ ቢመሰክርለት፣ እሱ ግን በሬውን ባይጠብቀው፣ ሰውንም ቢገድል፣ የበሬው ባለቤት 2/3 ምና ብር ይክፈል። ባርያን ወግቶ ቢገድል፦ 15 ሰቀል ብር ይክፈል። §56/57) ውሻ ተዋጊ ከሆነ፣ ኃላፊውም ለባለቤቱ ቢመሰክርለት፣ እሱ ግን ውሻውን ባይጠብቀው፣ ሰውንም ቢገድል፣ የውሻው ባለቤት 2/3 ምና ብር ይክፈል። ባርያን ወግቶ ቢገድል፦ 15 ሰቀል ብር ይክፈል። §58) ግድግዳ ሊወድቅ ቢል፣ ኃላፊው ለባለቤቱ ቢመሰክለት፣ እሱ ግን ግድግዳውን ካልጠነከረ፣ ግድግዳውም ወድቆ የሰውን ልጅ ከገደለ፦ የሕይወት ጉዳይ ነው፤ በንጉሥ ድንጋጌ ነው።
End of preview. Expand in Data Studio
README.md exists but content is empty.
Downloads last month
580