text
stringlengths
0
200
ዚትምህርት ደሹጃህ ግልጜነትህ ወይም ለመስራት ዚምትፈልገውን ወደጎን በመተው በትግሉ ውስጥ ዚተጫወትኚውን ሚና ይጠይቁኃል።
በ እና ዓም በብዙ አፍሪቃውያት ሀገራት ውስጥ ተቃውሞ ተካሂዷል።
በዚምባብዌ እና በዎሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ወጣቶቜ በተጠሉት ፕሬዚደንቶቻ቞ው አንፃር በተደጋጋሚ ተቃውሞ አድርገዋል ።
በሮኔጋል እና በቡርኪና ፋሶም ተቃዋሚዎቜ አምባገነን መሪዎቻ቞ውን ኚስልጣን አባሚዋል።
በሌሎቜ አፍሪቃውያትሀገራት ግን ተቃውሞዎቹ ያን ያህል አልተሳኩም ይላሉ ፕሮፌሰር ዛካሪያ ማምፒሌ።
በዚህ ፈንታ ድምፃ቞ውን ለማሰማት ሌላ አማራጭ ያፈላልጋሉ ማለት ነው።
ትልቁ አደጋ ግን ተቃውሞው እንዎት እንደሚካሄድ እና ምን እንደሚያስኚትል መተንበይ አለመቻሉ ነው።
እቅዱ በአፍሪቃ ዚወጣቶቜ ሰነድ ዚተቀመጡትን ዓላማዎቜ ኚግብ ዚማድሚስ እና ዚወጣቱንም አቅም በፖለቲካው እና በልማቱ ዘርፍ ዚማጎልበት ዓላማ ይዞ ተነስቷል።
ይሁን እንጂ ዚዚምባብዌ ተወላጇ ዚመብት ተሟጋቜ ሊንዳ ማዜሪሬ በሰነዱ ስለተቀመጡት አማላይ ቃላት መስማት አትፈልግም።
ኮሚሜነር ዘይኑ ለጋዜጠኞቜ በሰጡት መግለጫ ፖሊስ ኢንጅንዚሩ በሞቱበት ቊታ ዚነበሩ ማስሚጃዎቜ እና መሚጃዎቜን ዚሚሰጡ ሰዎቜን ይዞ እዚመሚመሚ ነው ብለዋል።
ዚአሟሟታ቞ውን ሁኔታ ዚሚያሳይ ዚምርመራ ውጀት ፈጥነን ለማቅሚብ ርብርብ እያደሚግን ነው።
ዉይይቱ ሲያበቃ ዛሬ ኚቀትር በኋላ ዹነበሹዉን ጋዜጣዊ መግለጫ ዚተኚታተለዉን ዚብራስልስ ወኪላቜን ገበያዉ ንጉሮን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ዚገበያ ማዕኹሉ አሁን በሚገኝበት መብራት ኃይል በተባለው ቊታ እንኳ ቃጠሎ ሲገጥመው ሁለተኛ ጊዜው ነው ፡፡
ዚገበያ ማዕኹሉ አሁን በሚገኝበት መብራት ኃይል በተባለው ቊታ እንኳ ቃጠሎ ሲገጥመው ሁለተኛ ጊዜው ነው፡፡
መልካም እንደልሆነ አጋጣሚ ደግሞ በሁለቱም ዹአደጋ ክስተት ንብሚታ቞ው ተቃጥሎ ዚተጎዱ ወገኖቜ አሉ ፡፡
በሌላ በኩል ነጋዎዎቹ መደበኛ ስራ቞ውን ለመጀመር ዚብድር ገንዘብ እዚተመቻ቞ ስለመሆኑ መስማታ቞ውን ገልፀዋል ፡፡
ምንም እንኳን እስካሁን ተግባራዊ ባይደሚግም ብድር ኚቜግሩ አገግሞ ወደ ስራ ለመግባት አያስቜልም ዚሚሉት ነጋዎዎቜ መንግሥት ዹተለዹ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
ብድር ጫና ይፈጥራል ዹሚል ቅሬታ ስለመነሳቱ ያነሳሁላ቞ው ኃላፊው አብዛኞቹ ቀደም ሲል ኹተቋሙ ዚወሰዱትን ብድር ዚመለሱ መሆናቾውን አሹጋግጠናል ብለዋል ፡፡
ዚገበያ ማዕኹሉ መልሶ ግንባታ እዚተካሄደ በሚገኝበት ቊታ ተገኝቌ እንደተመለኚትኩት እንዳንዶቹ ሱቆቜ በር በመግጠም ሥራ ለመጀመር ጥሚት እያደሚጉ መሆናቾውን ተመልክቻለሁ ፡፡
ባህል ሪታ ፓንክኞርስት ዚኢትዮጵያ ባለውለታ አዲስ አበባ ላይ ትዳር ዚመሰሚቱት ዚኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪዎቜ በትዳር ኹ ዓመታት በላይ ዘልቀዋል።
ወ ሮ ሪታ ፓንክኞርስት በቀተ መፅሕፍት ባለሙያነታ቞ው በብሔራዊ ቀተ መፅሕፍት አገልግለዋል።
በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ሕያዉ ሆነዉ ሲታወሱ ይኖራሉ ሀገራቜን ሀገሯ ህዝባቜን ህዝቧ ኑሯቜን ኑሮዋ ሆኖ ስታገለግለን እድሜዋን ጚርሳ ኚእኛው ዘንድ አሚፈቜ።
ደህና ሁኚ ይላል ጋዜጠኛ ዚትነበርክ ታደለ በፌስቡክ ድሚገፁ ያስቀመጠዉ ጜሑፍ።
ባለቀታ቞ዉ አጋፋዉ ዚኢትዮጵያ ዚታሪክ ተመራማሪ ዚፕሮፊሰር ሪቻርድ ፓንክኞርስት ኚሁለት ዓመት በፊት ኹዚህ ዓለም በሞት መለዚታ቞ዉ ይታወሳል።
በዚህ ዝግጅታቜን ዚሪታ ፓንክኞርስትን ዚሕይወት ታሪክና በኢትዮጵያ ሳሉ ያበሚኚቱትን አስተዋፅኊ እንቃኛለን።
በጎርጎሚሳዉያኑ ዓ ም በሩሜንያ ዚተወለዱት ወ ሮ ሪታ ፓንክኞርስት በ ዓመታ቞ዉ ኚወላጆቻ቞ዉ ጋር ወደ እንጊሊዝ ተሰደዱ።
ታዳጊዋ ሪታ በእንጊሊዝ ሃገር ካምብሪጅ ኹተማ በሚገኝ ዚልጃገሚዶቜ ት ቀት ዹአንደኛ እና ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ዉን ተኚታትለዋል።
ዹኹፍተኛ ትምህርታ቞ዉን በኊክስፎድ ዩንቚርስቲ ፈሚንሳይኛና ሩስያንኛን በሚያካትተዉ ዹዘመናዊ ቋንቋቜ ጥናት በማስተርስ ዲግሪ ተመርቀዋል።
ሪታ ዹኹፍተኛ ትምህርታ቞ዉን እንዳጠናቀቁ በመጀመርያ ዚተቀጠሩት ቻተም ሃዉስ በሚገኘዉ ፕሬስ ቀተ መፅሕፍት ዉስጥ ነዉ።
ኚዝያም ሪታ ዚዝያን ግዜ ዹፍቅር ጓደኛቾዉ ሪቻርድን እና ዚሪቻርድን እናት ሲልቪያ ፓንክኞርስትን ተኚትለዉ ወደ ኢትዮጵያ በጎርጎሚሳዉያኑ ዓ ም ይመጣሉ።
ዚሪታ ፓንክኞርስት ልጅ አሉላ ፓንክኞርስት ስለእናቱ ማንነት እንዲነግሚን ቀጠሮ ልንይዝ ዚደወልነት በለቅሶ ላይ ሳለ ነበር።
እንድያም ሆኖ ለነገ ቀጠሹንና ግንቊት ዚእናቱ ግባዕተ መሬት ኹተፈፀመ ኚአንድ ቀን በኋላ በስልክ ስለናቱ አጫወተን።
እናቱ ሪታ በብሪታንያ ዹኹፍተኛ ትምህርታ቞ዉን አጠናቀዉ በመፀሐፍ ትርጉም በቋንቋ አስተማሪነት እንዲሁም በቀተ መፅሐፍ ዉስጥ ሲሰሩ ሳለ ሪቻርድን ይተዋወቃሉ።
ሪታ እና቎ አባ቎ን እንደ አጋጣሚ ለንደን ኹተማ ላይ ተዋዉቃዉ ነበር።
አባ቎ ኚእና቎ጋር ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ መወሰኑን ነግሮ አብራ እንድትመጣ ጋበዛት እስዋም ወድያዉኑ ኚሱ ጋር ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ ወሰነቜ።
እናት እና አባትዋ ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ መወሰንዋን ሲሰሙ በጣም ሰግተዉ ነበር።
በዚሁ ዓመት እናትና አባ቎ እዚሁ አዲስ አበባ ጋብቻ቞ዉን ፈፀሙ።
ሚዜዎቻ቞ዉ ሜትር አር቎ስት አፈወርቅ ተክሌ እና መንግስቱ ለማ ነበሩ።
አዲስ አበባ ላይ ትዳር ዚመሰሚቱት ዚኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪዎቜ በትዳር ኹ ዓመታት በላይ ዘልቀዋል።
በሹጅም ዓመታት ዚስራ ዘመናቾው ወ ሮ ሪታ ዚኢትዮጵያን ባሕል ዚኢትዮጵያውያን ሎቶቜ ታሪክን እንዲሁም በኢትዮጵያ ዚቀተ መፅሕፍት ታሪክና ዕድገትን መርምሹዋል ዘክሚዋል።
ወደ ለንደን ዚተሰደዱት በወቅቱ በሃገሪቱ በነበሹዉ አስኚፊ ሁኔታ ልጆቻቜንን ለማሳደግ ኚባድነ ነበር ዹሚል ስጋት አድሮባ቞ዉ ስለነበሚ ነዉ።
እግሚ መንገድዋን አባ቎ ሪቻርድ በሚያዘጋጀዉ ኢትዮጵያን ኊብዘርቬሜን በተባለዉ መጜሔት ላይ በጜሑፍ ታግዘዉ ነበር።
በቀተ መጻሕፍት በተለይ ዚአጌ ቎ድሮስ በብራና ላይ ዹተፃፉ ደብዳቀዎቜን እና ጜሑፎቜን በተመለኹተ ዚተለያዩ ጜሑፎቜን በማቅሚብ አስተዋዉቃለቜ።
አቶ አሉላ በቀይ ሜብር ጊዜ ወላጆቌ እኛን ይዘዉ ወደ ብሪታንያ ተሰደዉ ነበር ብለኞኛል እስ቎ ስለ ስደት ታሪክ ንገሹን
ኑሮዋ቞ዉ ሙሉ በሙሉ እዚሁ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ዉስጥ ነበር።
ደርግ ወደ ስልጣን በመጣ ጊዜ መጀመርያ ሁኔታዉ ተቀይሮ ብሩህ ተስፋ ይመስል ነበር ።
አማን አብዶ ዚአባ቎ ተማሪ ነበር በጣም ጎበዝ ተማሪ በጣም ዚሚያደንቀዉ ተማሪ ነበር።
አካባቢዉ ላይ ታንኮቜ ገብተዉ አማን አብዶ በተገደለ ጊዜ እና ሁኔታዉ አሳሳቢ እዚሆነ ሄደ።
አባ቎ እንግሊዝ ለንደን እንደገባ ስራ አልነበሹዉም ኚዝያም ለንደን በሚገኝ ዩንቚርስቲ ዚአፍሪቃ ጥናት ተቋም ዉስጥ ለማስተማር ዚአንድ ዓመት ኮንትራት አገኘ።
እና቎ም በቀተ መፅሐፍት ጉዳይ ሞያ በለንደን በአንድ ዩንቚርስቲ ዉስጥ ስራን ጀመሚቜ።
እንድያም ሆኖ ወላጆቌ ለንደን ይኑሩ እንጂ ሃሳባ቞ዉ ወደ ኢትዮጵያ ነበር።
በዝያዉ በለንደን ሲኖሩ ዚመጀመርያዉ ዚኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ዹዓለም አቀፍ ጉባኀ ለንደን ላይ እንዲጀመር አብሚዉ ነበር ስራን ዚሰሩት።
ኚዝያም አባ቎ ወደ ኢትዮጵያ ዚመመለስ እድልን ሲያገኝ ለመመለስ ፈለገ።
ኚዝያም አባ቎ ተመልሶ በአዲስ አበባ ዩንቚርስቲ በኢትዮጵያ ጥናት ተቋም ማገልገል ጀመሚ።
እና቎ም እንዲሁ ዚተለያዩ ዚጥናት ጜሑፎቜን እንዲሁም ዚተማሪዎቜ ዚመመሚቅያ ጜሑፎቜን አርትዓይ በማድሚግ ሥራን መስራት እገዛን ጀመሚቜ።
ለምሳሌ ለኢትዮጵያዉያን ወጣት ተማሪዎቜ በዹዉጭ ትምህርት እድል እንዲያገኙ በአንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ዉስጥ በመስራት ትልቅ እገዛን አድርጋለቜ።
በተለይ ግቢዋ ዉስጥ ዚምትተክላ቞ዉን ዚተለያዩ ተክሎቜ አበቊቜ በጣም ትወድ ነበር።
በዚህም ወጣት አታክልተኞቜን ለማበሚታታት በሚደሹገዉ እንቅስቃሎ ኹፍተኛ ስተዋጟን አበርክታለቜ።
በሃገሪቱ በሚካሄድ ዚአትክልት ትርኢት ዉድድር ላይ በዳኝነት ወንበር ላይ ትቀመጥ ነበር።
ወ ሮ ሪታ ፓንክኞርስት ባለፉት ስድስት አምስት ዓመታት ኚባለቀታ቞ዉ ጋር በመሆን ዚኢትዮጵያ ታሪካ቞ዉን መፃፍ ጀምሹዉ ነበር።
ኢትዮጵያን ወዳጅዋ ሲቭሊያ ፓንክኞርስት ለኢትዮጵያ ሰርተዉ እዉቀት ፍቅርን አስተላልፈዉ አልፈዋል።
ዚፓንክኞርስት ቀተሰቊቜ ለኢትዮጵያዉያ ያበሚኚቱት ኹፍተኛ አስተዋፅዖ ትዉልድ ሲማርበት እንዲሁም በስራ቞ዉ በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ሕያዉ ሆነዉ ሲታወሱ ይኖራሉ።
አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኚገዢው ፓርቲ ዹተለመደ ይትባህል ወጣ ባለ መልኩ ያቀሚቡት ንግግር ብዙዎቜ ተስፋ እንዲሰንቁ አድርጓ቞ዋል፡፡
ኹሀገር ውስጥም ሆነ ኹውጭ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በቶሎ ማሻሻያዎቜን እንዲተገብሩ ዹሚጠይቁ ደጋግመው ዚሚያነሱት አንድ ጉዳይ አለ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ፡፡
ባለፈው ዚካቲት ወር ዚታወጀው ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ድንጋጌ ለስድስት ወር እንደሚቆይ ቢቀመጥም ጠያቂዎቹ ግን አሁኑኑ ይነሳ ባይ ና቞ው፡፡
ይህንን አቋማቾው በይፋ ካሳወቁት መካኚል ዚኢትዮጵያ መንግስት ሁነኛ አጋር ዚሚባሉት አሜሪካ እና ዚአውሮፓ ህብሚት ይገኙበታል፡፡
ዚአሜሪካንን ፈለግ ዹተኹተለ ዚሚመስለው ዚአውሮፓ ህብሚትም አዋጁ በቶሎ እንዲነሳ ፍላጎቱን ገልጿል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ኹተማ ፖሊስ መምሪያ ለ ቀናት ያህል ታስሮ ባለፈው ሳምንት ተለቅቋል፡፡
በእስር በቆዚበት ዚፖሊስ መምሪያ ውስጥ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁን ጥሳቜኋል በሚል ወደ ገደማ ተጠርጣሪዎቜ ታስሚው መመልኚቱን ይናገራል፡፡
አብዛኞቹ ዚተኚሰሱበትን ጉዳይ ግን እንኳ በቅጡ እንደማያውቁ እና ሲያዙም ድብደባ እንደተፈጞመባ቞ው እንደነገሩት ይገልጻል፡፡
ዚፉሪ ዹወንጀል መኹላኹል ኃላፊ ኮማንደር አዹለ ደበላ እና ዚፉሪ ዚትራፊክ ፖሊስ ኃላፊ አለ፡፡
አብዛኞቹ ዚመጡት ኚአዲስ አበባ እና ኚአዲስ አበባ ዙሪያ ነው፡፡
ለምሳሌ አንድ አማሹ ዚሚባል መካኒሳ ጋር ዚተያዘ ፌስ ቡኩን እያዚ ዚኮሎኔል ደመቀን ፎቶ አጋርተሃል ተብሎ ነው ዚመጣው፡፡
በሙሉ በአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ተይዘው እኛ ዚነበርንበት ፖሊስ ጣቢያ ያሉ ኚቀታ቞ው ኚስራ ቊታ቞ው እና ኚመንገድ ላይ ዚተያዙ ና቞ው፡፡
እነርሱ አሁን ኚእኛ ዹተለዹ ዚሚያደርጋ቞ው ኹፍተኛ ድብደባ ተፈጜሞባ቞ዋል በተያዙበት ዚመጀመሪያ እና ሁለተኛ ቀን ላይ፡፡
አሁን ሲያዩን አስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ኚመውጣቱ በፊት በአመጜ ወቅት ላይ ተሳትፎ ነበራቜሁ ነው፡፡
ኚአዲስ አበባ በስተሰሜን ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ባህር ዳርም ተርጣሪዎቜ ዚተያዙበት ሁኔታ ተመሳሳይ እንደሆነ ዹዓይን እማኞቜ ይናገራሉ፡፡
ዚባህር ዳር ዩኒቚርስቲው መምህር እና ጓደኞቻ቞ው በቆዩበት ፖሊስ ጣቢያ በአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ዚታሰሩ ቁጥራ቞ው ወደ ዹሚጠጉ ሰዎቜ እንዳጋጠሟ቞ው ይናገራሉ፡፡
ባህር ዳር ኹነማ ኹደሮ ኹነማ ጋር በነበሹው ጚዋታ ዕለት ሚብሻ ፈጥራቜኋል ተብለው ተይዘው ዚነበሩ ወደ ወይም ልጆቜ ነበሩ፡፡
እንዲዚህ አይነት በትንንሜ ጉዳዩቜ ጜሁፍ በኪሳቜሁ ይዛቜሁ ስ቎ድዚም ተገኝታቜኋል ተብሎ ዚታሰሩ ልጆቜ ነበሩ፡፡
እንደዚህ አይነት ልጆቜ ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ ብዙ እስሚኛ ነው ዚነበሚው፡፡
ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ማስፈጞሚያ መመሪያ በመላው ሀገሪቱ ዚሚተገብሩ ብሎ ክልኚላዎቜን ዹዘሹዘሹ ሲሆን ለተወሰኑ ቊታዎቜ ደግሞ አራት ክልኚላዎቜን አስቀምጧል፡፡
አዋጁን እና መመሪያውን ዚፈተሹ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ ተቋማት ክልኚላዎቹ አሻሚ ትርጉም ያላ቞ው እና ግልጜነት ዚሚጎድላ቞ው ናቾው ሲሉ ይተቻሉ፡፡
መመሪያ ተብሎ ዚወጣውን ዚኢትዮጵያ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈጞሚያ ደንብ ስታዚው ህግ በሚያሚቅቁ ሰዎቜ ተጜፏል ብሎ ለመናገር በጣም ነው ዚሚያሳፍሚው፡፡
ስለ አመክኖያዊ ትስስራ቞ው መሬት ላይ ሲተገበሩ ስለሚያመጡት ውጀት ምን ያህል ተጚባጭ ናቾው
ምን ያህል ኹሰው እና ኚማህበሚሰብ ዹቀን ተቀን መስተጋብር ጋር አብሚው ይሄዳሉ ስለሚለው ጉዳይ ብዙም ትኩሚት ዹተሰጠ አይመስለኝም፡፡
ለህግ ደንቊቜ አሹቃቀቅ ምንም ክብር በሌለው ሁኔታ ዹተሹቀቀ አይነት ነው፡፡
ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ላይ ያሉ ድንጋጌዎቜ በስፋት ዚተቀመጡ እና አሻሚዎቜ ዹሆኑ ና቞ው፡፡
ምርመራ ለምን ያህል ጊዜ ያህል ይካሄዳል ዚሚሉት እንደዚሁ ዚሉም፡፡
ታሳሪዎቹ አላግባብ መታሰራ቞ውን ዚት አቀት ማለት እንደሚቜሉ ለማወቅ ተ቞ግሚዋል።
በአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ወቅት ዚሚወሰዱ እንደዚህ አይነት እርምጃዎቜን ዚመኚታተል እና ዚመቆጣጠር ተግባር ያለው መርማሪ ቊርድ ግን ስራዚን እያኚናወነንኩ ነው ይላል።
መርማሪ ቊርዱ በአዋጁ ዚሚወሰዱ እርምጃዎቜ ኢ ሰብዓዊ መሆናቾውን ካመነ እርምጃውን እንዲያስተካክል ለኮማንድ ፖስቱ ሀሳብ እንደሚሰጥ ተደንግጓል፡፡
ቊርዱ ኹተሰጠው ስልጣን እና ተግባር አንዱ በአዋጁ ምክንያት ዚታሰሩ ግለሰቊቜን እና ዚታሰሩበትን ምክንያት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ ማድሚግ ነው፡፡
አራማጆቜ አክቲቪስቶቜ ግን በዚአካባቢው ዚታሰሩ ሰዎቜ በቊርዱ ኹተጠቀሰው በጣሙኑ እንደሚልቅ ይሟገታሉ።
ዚቊርዱ ሰብሳቢ በባለፈው ሳምንት መግለጫ቞ው ኚህብሚተሰቡ ኚሚደርሷ቞ው ጥቆማዎቜ ብዙዎቹ ሰዎቜ እዚታሰሩ ያሉት በቂም በቀል ነው ዹሚል እንደሆነ አስሚድተዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ ኢህአዎግ በስልጣን ላይ በቆዚባ቞ው ዓመታት ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ሲያውጅ ዹአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜው ነው፡፡
ባለፈው ዓመት ታውጆ ዹነበሹው ተመሳሳይ ድንጋጌ ለ ወር ኹቆዹ በኋላ እንዲነሳ ተደርጓል፡፡
በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት አማካኝነት በዚካቲት ዚታወጀው ዹአሁኑ ድንጋጌ ሕገ መንግስቱን እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ኹአደጋ ለመኹላኹል በሚል እንደነበር ይታወሳል፡፡
ዹአምቩው ዩኒቚርስቲ መምህር ኢትዮጵያ አሁን ባለቜበት ነባራዊ ሁኔታ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንም ባይ ና቞ው።
መቀመጫ቞ውን ዋሜንግተን ዲሲ ያደሚጉት ዚሰብዓዊ መብቶቜ ህግ ባለሙያው አቶ ዩሎፍ ተመሳሳይ አስተያዚት አላ቞ው፡፡