text
stringlengths
0
200
ዚተመድና መንግሥታዊ ያልሆኑት ድርጅቶቜ ብይኑ በጎሳዎቜ መካኚል ግጭቱን እንደገና ይቀስቅስ ይሆናል በሚል ሰግተው ነበር።
በአንፃሩ ሁሉ ሰላም እንደነበር ዚሌንዱ ጎሳ ቃል አቀባይ ፍራንስዋ ዳዳ ገልጟዋል።
ጊዜ ራሱ በጎሳዎቹ መካኚል ያለው ልዩነት እንዲቆም ድርሻ አበርክቶዋል።
ጊርነት እስኚሌለ ድሚስ ሕዝቡ ባለፉት ዓመታት ዚደሚሰበትን በደል ሚስቶዋል።
ይህንን ብንልም ግን በደስታ እንፈነድቃለን ማለት አይደለም ምክንያቱም ኚሳሟቜ እኛ አልነበርንምና።
ምንም እንኳን ዚትኛውም ኚባድ ቅጣት ዚግዳጁ ምልመላ ሰለባ ዚሆኑት ሕፃናት ዚደሚሰባ቞ውን ዚዕድሜ ልክ ሥቃይ ባይቀንስም።
ጥያቄው ዚብዙ ሕፃናትን ሕይወት ላበላሾ ግለሰብ ትክክለኛው ቅጣት ዚቱ ነው ዹሚለው ነው።
በመግቢያው መግለጫቜን እንዳስታወቅነው፡ ኹፍተኛው ዚእሥራት ቅጣት እንዲበዚንባ቞ው ነው ዚምንጥሚው።
ዚኢሬቻ በዓል አኚባበር በአዲስ አበባ ኢሬቻ በዓል ዛሬ በአዲስ አበባ ለግምት ዚሚያስ቞ግር በርካታ ህዝብ በተገኘበት ተኚብሯል።
ዚኢሬቻ በዓል ዛሬ በአዲስ አበባ ለግምት ዚሚያስ቞ግር በርካታ ህዝብ በተገኘበት ተኚብሯል።
ዚመስኚሚም ቀን ዓ ም ዹዜና መጜሔት ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዹሰመርጃም ሬጌ ዹሙዚቃ ትርኢት ኛ ዓመት መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
በፌደራል ማሚሚያ ቀቶቜ ኹ በላይ እንዲሁም በቀጠሮ ታራሚዎቜ መኖራ቞ውን ኚፌደራል ማሚሚያ ቀቶቜ ኮሚሜን ዹተገኘው መሹጃ ይጠቁማል።
በዚህ ሳምንት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ መነጋገሪያ ኚኟኑ ነጥቊቜ መካኚል አራት ጉዳዮቜ ጎልተው ወጥተዋል።
ዚአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ ሥላሎ ዚኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዎሬሜን ፕሬዚዳንት ኟኖ መመሚጥ አንደኛው ርእስ ነው።
ዚአትሌት ምሩጜ ይፍጠር ዚጀንነት ኹኔታን በተመለኹተ ዚቀሚቡ ዘገባዎቜም አነጋጋሪ ኟነዋል።
ዚዶናልድ ትራምፕ ባልተጠበቀ መልኩ ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ፕሬዚዳንት ኟነው መመሚጥ በስፋት አነጋጋግሯል።
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብሚ ሥላሎ ዚኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዎሬሜን ፕሬዚዳንት በመኟን መመሚጡ በማኅበራዊ ዹመገናኛ ዘዎዎቜ መነጋገሪያ ኟነው ኚቆዩ ጉዳዮቜ አንዱ ነበር።
ዘካርያስ ዘላለም በትዊተር ማኅበራዊ መገናኛ ገጹ ባሰፈሚው ጜሑፉፊ ኃይሌ ገብሚ ሥላሎ በርካት ጉዳዮቜ ተቆልለው ይጠብቁታል።
ኚእነዚያም መካኚል በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዎሬሜን ዚተንሰራፋው ሙስና እና አትሌቶቜን ስልታዊ በኟነ መልኩ መበደል ይገኝበታል።
ሰማኾኝ ጋሹ አበበ ዚኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዎሬሜን ፕሬዚዳንት ምርጫን በፌስቡክ ገጹ እንደሚኚተለው ተቜቷል።
ዚኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዎሬሜን አትሌት ኃይሌ ገብሚሥላሎን ዚፌዎሬሜኑ ፕሬዚዳንትነት አድርጎ መርጊታል።
ግለሰቡ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ በሕዝባዊ ትግሉ ላይ ዚሚሰጣ቞ዉ አስተያዚቶቜ እንደሚጠቁሙት ኚስርአቱ ጋር ዹጠበቀ ቁርኝት አንዳለዉ ነዉ።
እንዲመሚጥ ያስደሚገዉም ይህ ለስርአቱ ያለዉ ድጋፍ ነዉ ሲል ጜፏል።
ሰማኾኝ በመቀጠል ጜሑፉን ሲያብራራፊ ስርአቱ ኚደሚሰበት ዚፖለቲካ ኪሳራ ለመዉጣት እንዲህ አይነት ቁማር መጫወቱ ዹሚጠበቅ ነዉ።
ገብሚ እግዚአብሔር ገብሚ ማርያም ዚኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዎሬሜን አዲሱ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚ቎ አባል ነው።
ፌዎሬሜኑ በቀድሞ ታላቅ አትሌቶቜ በመመራት ዚባዚር ሙይንሜንን ሞዮል እዚተኚተለ ነው ብሏል።
ናታሊ አሚዮት በትዊተር ቀጣዩን ባስነበበቜው መልእክቷፊ ንጉሡ እርቃኑን ነው።
ዶ ር ቎ድሮስ በግልጜ ዚሕወሃት ተጚማሪ ማጭበርበር እና ሐፍሚት ነው ብላለቜ።
እንዳልካ቞ው ኃይለሚካኀል ግሎባል ቮይስ በተባለ ድሚ ገጜ ላይ ያሰፈሚውን ዘለግ ያለ ጜሑፍ ትዊተር ገጹ ላይ አካፍሏል።
ዹሚለውን ዚዶ ር ቎ድሮስ አድሃኖም ጥያቄ እና አወያዩ ጥያቄውን በድጋሚ ለማብራራት መሞኚራ቞ው ዚሚያሳፍር መኟኑን አካቷል።
ዚኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሜን ድሚ ገጜ አድራሻ ዚያዘ ዜና ሚቡዕ ጥቅምት ቀን ዓም ኢንተርኔት ላይ ሰፍሮ ይገኛል።
ዜናው በእንግሊዝኛ ቋንቋ ዚተጻፈ ሲኟንፊ ዕውቁ ዚኢትዮጵያ አትሌት ምሩጜ ይፍጠር አርፏል ይላል።
በቅድሚያም ዜና ሚፍት ሲል ዹሚንደሹደሹው ዚስፖርት ዜና ኚኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሜን ድሚ ገጜ እንደተሰሚዘ ዚሚያመለክተው ዹተፈለገው መሹጃ አልተገኘም ዹሚል መልእክትም ይነበባል።
አጥናፍ ብርሐኔ በትዊተር ገጹ ዚመንግሥት መገናኛ አውታሮቜ በሚዥም ርቀት ታዋቂው አትሌት ምሩጜ ይፍጠር አርፏል በማለት ሰዉን አሳስተዋል ሲል ጜፏል።
ዚአብይ አጠር ያለው ስላቃዊ ጜሑፉፊ ዚፖለቲካ ትንታኔ ነፍስሜን በሠላም ያሳርፈው ዹሚል ነው።
ዘላለም ክብሚት በትዊተር ገጹ ዚሪፐብሊካኖቜ ፓርቲ መለያ ዚኟነውን ቀይ ቀለም ኚኢትዮጵያ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በማነጻጞር አጠር ያለ መልእክት አስተላልፏል።
ዚምርጫ መዘርዝር ውጀቱን ለማሳዚት ዹቀሹበው ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ካርታን በስፋት አልብሶ ዚሚታዚው ቀይ ቀለም ሪፐብሊካኖቜ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በስፋት ማሾነፋቾውን ያመለክታል።
ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ቀይ ዞን ኹሚል ጜሑፍ ጋር በቀይ ቀለም ዹተዋጠ ዚኢትዮጵያ ካርታም ኹጎኑ ሰፍሯል።
ዘላለም፩ ኚዩናይትድ ስ቎ትስ እና ኚኢትዮጵያ ካርታ ጋር ያያዘው አጭር ጜሑፍ ቀይ በቀይ ዹሆነ ጊዜ ይላል።
ዚብዥታው ምንጭ ዚመንግሥት መገናኛ አውታሮቜ ዘገባ እንደኟነ ብዙዎቜ ጜፈዋል።
በሳምንቱ ውስጥ ዹተኹናወነ ወይም ዹሚኹናወን አንድ ዓቢይ ፖለቲካዊ ጉዳይን ያስተነትናል።
ኚኀኮኖሚው ዓለም ለዓለም በተለይ ለኢትዮጵያ ኀኮኖሚያዊ ሂደቶቜ ትኩሚት ዚሚሰጥ ዝግጅት ነው።
ዚባህል መድሚክ በተለይ ዚኢትዮጵያውያን ዚኪነ ጥበብ ስራዎቜን እንዲሁም በጀርመን አውሮጳ እና በሌሎቜ ባህሎቜ መካኚል ዹሚደሹገውን ግንኙነት ዚሚያስቃኝ ሳምንታዊ ዝግጅት ነው።
ዚወጣቶቜ ዓለም ወጣት ኢትዮጵያውያንን ዚሚመለኚቱ እና ዚሚያዝናኑ አርዕስትን እያነሳ ኚሚመለኚታ቞ው ጋር በሚደሹግ ውይይት ዹሚጠናቀር ሳምንታዊ ዝግጅት ነው።
ኢንክሪፕሜን በመሹጃ እና ግንኙነት ዘርፍ ማንኛውም መልእክት ኚላኪው ወደ ተቀባዩ ኚመድሚሱ አስቀድሞ ዚሚያልፍበት መንገድ አለው።
መልእክቱ ካልተቆለፈ በስተቀር ኚላኪ እና ኚተቀባይ ውጪ መሀል መንገድ ላይ በሊስተኛ ወገን ሊበሹበር ይቜላል።
በእርግጥ አንድ መልእክት ኚላኪ እና ኚተቀባዩ ውጪ በሊስተኛ ወገን ተለይቶ እንዳይታወቅ ማድሚጊያ ዚመቆለፊያ ሒደት አለ በእንግሊዝኛው ይሰኛል።
ኢንክሪፕሜን ኹመደበኛው ዚመስመር ስልክ ውጪ ዚኢንተርኔት ዹመገናኛ መግባቢያን በመጠቀም ዚኢንተርኔት መሚብ ውስጥ ዚስልክ ጥሪ ዹማኹናወን እና ሰነዶቜን ዹመላክ ስልትን ይጠቀማል።
አቶ ሰለሞን ሙሉጌታ ካሳ ዚስነ ቮክኒክ ኹፍተኛ አማካሪ እና ዚሶፍትዌር አበልጻጊ ና቞ው።
ቮክ ቶክ ዹተሰኘውን ዚኢቢ ኀስ ቎ሌቪዥን ፕሮግራም በማዘጋጀትም ያቀርባሉ።
ኢንክሪፕሜን በጥቅሉ ምንነቱ ሳይታወቅ በሆነ መንገድ ተቆልፎ ዹተላኹ መልእክት ተቀባዩ ጋር ብቻ ሲደርስ ግልጜ ሆኖ እንዲፈታ ዚማድሚግ ሒደት ነው።
ዚዲጂታሉ ዘመን ዚጀመሚበት ዚመጀመሪያ ዓመታት አካባቢ ተቆልፈው ይላኩ ዚነበሩ መልእክቶቜ በቀላሉ ሊፈቱ ዚሚቜሉ ነበሩ።
ዚኮምፒውተሮቜ መስፋፋት እና መርቀቅ ግን ዹተቆለፈው መልእክት እጅግ ውስብስብ እንዲሆን እና በቀላሉ እንዳይፈታ ለማድሚግ አግዘዋል።
በተለይ ዚኢንተርኔት ዹመገናኛ መግባቢያን በመጠቀም ዚኢንተርኔት ጥሪ አገልግሎት መጀመሩ መልእክቶቜ ዹበለጠ እንዲቆለፉ አስቜሏል።
በዓለማቜን መልእክቶቜን ቆልፎ ዹመላክ ጥበብ ዚዲጂታሉ ዘመን ብቻ ያመጣው አዲስ ነገር አይደለም።
መልእክት ቊለፋ በሮማን ኢምፓዚር ዘምን ጭምር ጥቅም ላይ ዹነበሹ ጥበብ ስለመሆኑ ዚታሪክ ድርሳናት ይጠቅሳሉ።
ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ትልቁ እና አንደኛው ነገር ምሥጢራዊነትን መጠበቅ መሆኑን አቶ ሰለሞን ተናግሚዋል።
ዚጥሚቱ ምንጭ በእርግጥ ዘርፈ ብዙ እና ሰፊ ነው ኹማጭበርበር አንስቶ ዚፖለቲካ ተልዕኮ እስኚ ማስፈጞም ሊደርስ ይቜላል።
ለመሆኑ ዚመልእክት ቊለፋ እንደ ቫይበር ዋትስአፕ ስካይፕ መሮንጀር እና በመሳሰሉት ዚመልእክት መቀበያ ወይም መላኪያ ማስተናበሪያዎቜ ዚሚሠራው እንዎት ነው
ያን ዚሚያደርገውም መልእክት ላኪው እና ተቀባዩ ጋር ዹሚገኘው አፕሊኬሜን ነው።
ዚጋራ ቊልፍ ኖሮ ቊልፉን ዚሚያውቁ አካላት ብቻ ሊፈቱት ዚሚቜሉት ዹቊለፋ አይነት ወይንም አንደኛው ነው።
በዚህ ዘዮ ዹተቆለፈውን መልእክት ለመፍታት ላኪው እና ተቀባዩ ተመሳሳይ መቆለፊያ እና መፍቻ ዘዮን ነው ዚሚጠቀሙት።
ሆኖም ቊልፉ ኚላኪ እና ተቀባይ ኚወጣ ዚመልእክቱ ምሥጢር በሊስተኛ ወገን በቀላሉ ሊፈታ ይቜላል።
ሌላኛው ዘመናዊ ዹቊለፋ አይነት በመልእክት ላኪው እና ተቀባዩ መካኚል ብቻ ዹሚመሰጠር ነው።
መልእክቱን ዹሚቀበለው ሰው ላኪውም ዚራሳ቞ው ዹግል ቊልፍ ይኖራ቞ዋል መፍቻ ቊልፍ መቀባበል አያስፈልግም።
ይህ ዘዮ ይፋ ዹሆነው እንደ ጎርጎሪዮሳስ አቆጣጠር በ ነው።
በኢንተርኔቱ ዓለም ሙሉ ዲጂታል መሹጃ አገልግሎት ዚሚሰጡ ማስተናበሪያዎቜ በርካታ ና቞ው።
ዹቊለፋ ስልት በመጠቀም ዚኢንተርኔት ጥሪን ዚሚያስተናግዱ ማስተናበሪያዎቜ ግን አይነታ቞ው በሁለት ይኚፈላል።
አንደኛው ኚላኪው እና ተቀባዩ ውጪ አገልግሎት ሰጪው እንኳን መልእክቱን ማዚት ዚማይቜልበት ነው።
ዹዚህ ተጠቃሚዎቜ ለአብነት ያኜል ዋትስአፕ እና ዹአፕል አይ ሜሮጅ ይጠቀሳሉ።
ሌሎቹ እንደነ ትዊተር ሀንግ አውት ዚፌስቡክ መሮንጀር ስካይፕ ዚመሳሰሉት ሲሆኑ እነሱም እንደነዋትስአፕ ዹቁለፋ ስልትን ይጠቀማሉ።
ሆኖም ለዚት ዚሚያደርጋ቞ው ዚአፕሊኬሜኖቹ ባለቀቶቜ ያልተቆለፈው መልእክት ዚሰነድ ማኚማቻ ቋታ቞ ውስጥ መገኘቱ ነው።
ደም መታዚቱ በራሱ በሜታ ሳይሆን ምልክት ነዉ ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
አፍሪቃ በግድያ ዹተጠሹጠሹዉ ኀርትራዊ ኀርትራዊዉ ፍራንክፈርት ባቡር ጣቢያ ዚነበሩ እናት ልጅን በፍጥነት በሚጓዝ ባቡር ፊት ገፍትሮ ጥሏ቞ዋል።
እናትዚዋ ኚባቡሩ ሐዲድ ተንኚባላ ስታመልጥ ዚስምት ዓመቱ ሕፃን ግን እዚያዉ ሞቷል።
ዹጀርመን ዚፌደራል ፖሊስ አዛዥ ዲተር ሮማን ዛሬ እንዳስታወቁት ሰዉዬዉ ሲዊዘርላንድ ዉስጥ አንዲት ጎሚቀቱን በጩቀ ለመዉጋት በማስፈራራት ወንጀል ሲታደን ነበር።
አቃቀ ሕግ ዚግድያና ድርብ ዚግድያ ሙኚራ ክስ ለመመስሚት እዚተዘጋጀ ነዉ።
ኹ ጀምሮ ሲዊትዘርላንድ ዉስጥ እንደኖሚ ባለትዳርና ዹ ልጆቜ አባት እንደሆነም ተነግሯል።
ኀርትራዊዉ ፍራንክፈርት ባቡር ጣቢያ ዚነበሩ እናት ልጅን በፍጥነት በሚጓዝ ባቡር ፊት ገፍትሮ ጥሏ቞ዋል።
ፖሊስ እንዳስታወቀዉ ኀርትራዊዉ ሌላ ሎትዮ ወደ ሐዲዱ ለመገፍተር ሞክሮ አልተሳኚለትም።
አደጋዉን ካደሚሰ በኋላ ለማምለጥ ሲሮጥ ባካባቢዉ በነበሹዉ ሕዝብና እርፍት ላይ በነበሹ ፖሊስ ርብርብ ተይዟል።
ኩነግ በሰጠው መግለጫመንግስት እዚወሰደ ነው ባለው መብቶቜን ዚሚጥሱ እርምጃዎቜ ሃገሪቱን ወዳልተፈለገ ቜግር ሊያመራት ይቜላል ሲል አስጠንቅቋል።
መንግሥት ዚዜጎቜን ዚመደራጀት ዚመሰብሰብ እና በነጻነት ዚመንቀሳቀስ መብት ሊያኚብር ይገባል ሲል ዚኊሮሞ ነጻነት ግንባር ኩነግ አሳሰበ።
መንግሥት ዚዜጎቜን መሰሚታዊ ዚዎሞክራሲ መብቶቜ መጣሱን ዚሚቀጥል ኹሆነ ግን ነገሮቜ ወደማይፈልጉት አስ቞ጋሪ ሁኔታ ሊያስገባ ይቜላል ብለዋል።
መንግስት ዚሰብዓዊ መብትን ጚምሮ ዚመደራጀት በነጻነት ዚመንቀሳቀስ እና ዚመስበሰብ መብቶቜን ነጻ እንዲያደርግ እና እነዚህኑ ኚሚያደናቅፉ ተግባራት እንዲቆጠብ እንጠይቃለን።
ይህ ካልሆነ ግን ሀገሪቷ ወደማይፈለግ ዚጥፋት መንገድ እዚሄደቜ መሆኗን ለማስታወስ እና መንግስት አካሄዱንም ሆነ መዋቅሩን እንዲያስተካክል እናሳስባለን።
አቶ ዳውድ አያይዘውም ዚመንግስት መዋቅርም ሆነ ባለስልጣናቱ ዹሕግ ዚበላይነትን አክብሚው መንቀሳቀስ ይኖርባ቞ዋል ብለዋል።
አንዳንድ ዚገዢው ፓርቲ አባላት ዹቀደመውን መንግስት ለመመለስ እያደሚጉ ካለው እንቅስቃሎያ቞ው ይቆጠቡ ሲሉም ጠይቀዋል።
በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዹተቀሰቀሰውን ዚኮሚና ወሚርሜን ለመግታት ሁሉም ርብርብ እንዲያደርግም አቶ ዳውድ በዚሁ ወቅት ጠይቀዋል።
በጉራጌ ዞን በተቀሰቀሰ ግጭት ሰዎቜ መገደላቾውን ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ ተናገሩ አውዲዮውን ያዳምጡ።
ሪቻርድ ፎን ቫይሎኚር ተኛው ዹጀርመን ፕሬዝዳንት መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ኢትዮጵያ ካለፉት ጥቂት ሳምንታት ወዲህ በፍጥነት ዚሚለዋወጡ ክስተቶቜን እያስተናገደቜ ነው።
በነዚህ ጊዜያት ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዚሚወስዳ቞ው እርምጃዎቜም ዚዜጎቜን ልብ እያንጠለጠሉ እና ብዙ ጥያቄዎቜን እያስነሱ ነው።
ማን ይተካ቞ዋል ዹሚለውም ኹመላ ምት በስተቀር እስካሁን ቁርጥ ያለ መልስ አላገኘም።
ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳይ አነጋግሮ ሳያበቃ በማግሥቱ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉ ሌላው ካለፈው ሳምንት አንስቶ ዚሚያጠያይቅ ዐብይ ክስተት ሆኖ ዘልቋል።
አዋጁ ኹተደነገገ በኋላም ህብሚተሰቡ ሌሎቜ ጥያቄዎቹ እንዲመለሱ በመጠዹቅ አድማ ማካሄዱን ቀጥሎ ነበር ዚሰነበተው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣን እለቃለሁ ካሉ በኋላ ዹሰው ሳይሆን ዚስርዓት ለውጥ ነው ዹምንፈልገው ዹሚሉ ዚሜግግር መንግሥት ጥያቄዎቜ እዚቀሚቡ ነው።
ዹአዹር ንብሚት ለውጥ ተሟጋ቟ቹ ኚባቢ አዹርን ጠብቁ ዚድንጋይ ኹሰል ቊፋሮን አቊሙ ሲሉም መፈክር አስተጋብተዋል።
በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ዹአዹር ንብሚት ለውጥ ተሟጋ቟ቜ መንግሥታት ዹዓለም ሙቀት መጹመርን ለመግታት ርምጃዎቜን መውሰድ እንዲጀምሩ በጀርመን ቩን ኹተማ ባካሄዱት ሰልፍ ጠዚቁ፡፡