Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet Duplicate
instruction
stringclasses
4 values
extractive_text
stringclasses
10 values
summary
stringclasses
10 values
Summarize the following news article into a concise headline.
ኹተኹሰተ ኚአመት በላይ ያስጠቆሚው ዚኮቪድ ወሚርሜኝ ዛሬም በደቂቃ ዘጠኝ በዚእለቱ ደግሞ በሜወቜ ዚሚቆጠሩ ሰወቜን እዚነጠቀ ይገኛል። በጣም ተጋላጭ ዚሆኑት በጉልህ ይጎዳሉ፣ አሁን ላይ ያለው አደጋ ወሚርሜኙን ለመግታት ባለሁለት ፍጥነት ዹአለም ምላሜ መኖሩ ነው ብለዋል። ዚገንዘብ አቅም፣ ጊዜንና ዚሞት መጠንን በቀነሰ መልኩ በአጭር ጊዜ ለውጥ ማምጣት ዚሚቻልበትን አዋጭ ዚጊርነት ስልት አይነት በመጠቀም ዚኮሮና ወሚርሜኝ በአለም ላይ እያደሚሰ ያለውን ኚባድ ጉዳት በአጭር ጊዜ መመኚት ይገባል እንደ ጉተሬስ። ኹዚህም ባለፈ አይነቱን መቀያዚሩና ኹአለም ህዝብ አንድ ሶስተኛውን ያልደሚሱት ክትባቶቜ አይነቱን ቀይሮ ዚሚመጣውን ዚኮሮና ወሚርሜኝ ይኹላኹሉ አይኹላኹሉ በጥናት አለመሚጋገጡ፣ ዚወሚርሜኙ ባህሪ ዚጀናውን ስርአት አብዝቶ ዚሚፈትንና ኚዚትኛውም አገር አቅም በላይ መሆኑ ኹተኹሰተ ኚአመት በኋላም ዹአለም አጀንዳነቱን እንደያዘ ቀጥሏል። ዹአለም ጀና ድርጅትና ሌሎቜ ዚፈጠሩት አለም አቀፍ ዚክትባት ፕሮግራም ኮቫክስም፣ ክትባቱ ለአገሮቜ በፍትሃዊነት ተደራሜ እንድሆን አላማ አስቀምጊ ቢንቀሳቀስም፣ ዚኮቪድ ክትባት አቅርቊት ጉልህ እጥሚት ገጥሞታል። አሁን ያለውን ዚኮቪድ ወሚርሜኝ መኹላኹል እንዳለ ሆኖ፣ ዚሚቀጥለውን ወሚርሜኝ ለመኹላኹል ራስን ማዘጋጀትና ዹአለም ጀና ስርአትን ማጠናኹር ወሳኝ እንደሆነ ተናግሚዋል። አገሮቜ ይህ መድሃኒት ያልተገለኘትን ወሚርሜኝ ለመዋጋት ኚቅድመ መኹላኹል ጀምሮ እስኚ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ክትባት ቢዘልቁም፣ ቫይሚሱን መቋቋም አልተቻለም። ቫይሚሱ በአንድ ጊዜ አንድ አገር ብቻ አጥቅቶ ዹማይቀር በመሆኑም፣ ተጜእኖው አለም አቀፋዊ ነው። ዹአለም ጀና ድርጅት አመታዊ ጉባኀን በሳምንቱ መጀመርያ ዚኚፈቱት ጉተሬስ፣ ኚሶስት ነጥብ አራት ሚሊዮን በላይ ሰወቜ በቫይሚሱ ምክንያት መሞታ቞ውንና ግማሜ ቢሊዮን ያህል ስራወቜ መክሰማቾውን ተናግሚዋል። ወሚርሜኙን ዚማስቆም አቅም በቡድን ሃያ አገሮቜ እጅ ላይ ነው ዹሚለው ዹአለም ጀና ድርጅትም፣ አገሮቹ ወሚርሜኙን ለመኚላኚል፣ ዹመመርመር አቅምን ለማጠናኚር፣ ክብካቀና ክትባቱም ለሁሉም በፍትሃዊ መንገድ እንድዳሚስ ለማስቻል ዚጀመሩትን ስራ ማጠናኹር ይገባ቞ዋል።
አለም ኚኮቪድ ጋር ዹገጠመው ጊርነት
Create a short title for the given news content.
ዚህዝብ ግንኙነት ሃላፊው ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ግንቊት ፣ ሁለት ሜህ አምስት ጧት ላይ በደህንነቶቜ ተይዞ መወሰዱን ዚማህበሩ ሊቀመንበር ወጣት ሃብታሙ አያሌው ለኢሳት ገልጿል። ምሜት ሰአት ላይ ያነጋገርነው ዚማህበሩ ቩሌ ክፍለኹተማ ምክትል ሃላፊ ወጣት ጥላዚ ታሚቀኝ እንደገለጞው ደግሞ ኹዚህ ቀደም ታስሚው በነበሚበት ወቅት ሲዝትባ቞ው ዹነበሹው ሳምሶን ዚተባለ ዚደህንነት ሰራተኛ ወጣት ብርሃኑን እንዳስያዘው ገልጿል። ዚወጣት ብርሃኑ ቀተሰቊቜ ቀት ሲፈተሜም በአንድ መጜሃፍ ውስጥ ራሳ቞ው ደህንነቶቜ ያስገቡትን ጜሁፍ ይሃው አገኘነው በማለት ብርሃኑን እንድፈርም እንደጠዚቁትና ኹጠበቃዹ ጋር ሳልማኚር አልፈርምም እንዳለ ወጣት ጥላዚ ተናግሯል። ወጣት ሃብታሙ ኚሌሎቜ ዚማህበሩ አባላት ጋር በመሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ቢሄዱም፣ እስሚኛውን ሊያገኙት እንዳልቻሉ ይሁን እንጅ በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ኹቀኑ ዘጠኝ ሰአት ላይ ዚወጣት ብርሃኑ ቀት እዚተፈተሞ መሆኑን መሹጃ እንደደሚሳ቞ው ገልጿል። ወጣት ብርሃኑ ሰማያዊ ፓርቲ ኚጠራው ዹተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያያዘ መታሰሩን ወጣት ሃብታሙ ገልጿል። በጉዳዩ ዙሪያ ዹጉለሌን ፖሊስ ጣቢያ ሃላፊወቜ ለማግኘት ያደሚግነው ሙኚራ አልተሰካም።
ዚባለራእይ ወጣቶቜ ማህበር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ታሰሚ
Summarize the following news article into a concise headline.
አድስ አበባ፣ መጋቢት ስምንት፣ ሁለት ሜህ ኀፍ ቢ ሲ ዚፌደራሉ መንግስት ለትግራይ ህዝብ ሰብአዊ ድጋፍ እንድደርስ አስፈላጊውን ገንቢ ሚና እዚተጫወተና እርዳታ እንድላክ እያደሚገ መሆኑን አስታወቀ። ኚሰባት መቶ ሜህ ህዝብ በላይ እንድፈናቀል እና ኚአብአላ በኩል ወደ መቀሌ ዹሚደሹገው ዚሰብአዊ አገልግሎት ጉዞ እንድቋሚጥ ያደሚገውም፥ በአፋር ክልል ላይ ዳግም ወሚራ ያካሄደው ሜብርተኛው ዚህወሃት ቡድን መሆኑ በግልጜ ሊታወቅ ይገባል ሲል መንግስት በመግለጫው አስገብዝቧል። መግለጫው እንዳመለኚተው፥ ኚትናንት ጀምሮ ሰብአዊ ድጋፍ ዚሚያደርጉ አጋር ድርጅቶቜ ክትባትን ጚምሮ ዚተለያዩ መድሃኒቶቜ፣ ዹህክምና ቁሳቁስና ዚምግብ አቅርቊት ወደ ትግራይ ክልል ማጓጓዝ እንደሚቜሉ አሚጋግጠዋል። በክልሉ ህዝብ መሰሚታዊ ሰብአዊ ድጋፎቜ ፈጥነው እንድደርሱ ለማድሚግ ኚቅርብ ቀናት ጀምሮ በዚእለቱ አርባ ተሜኚርካሪወቜ ወደ ትግራይ ክልል እንድጓጓዙ ዹሚደሹግ መሆኑንም ነው መንግስት ያስታወቀው። መንግስት ዚህዝቡን መብት ለማሚጋገጥና በቜግር ላይ ያሉትን ዜጎቹን ህይወት ለመታደግ ኹማንም በላይ ሃላፊነት እንደሚሰማው ገልጟ፥ ጉዳዩ ዚሚመለኚታ቞ው አካላት ሁሉ ዹሚላኹው ሰብአዊ ድጋፍ ለህዝቡ በቀጥታ እንድደርስ ማድሚግ እንዳለባ቞ው አሳስቧል። ዚኢፌደሪ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ መንግስት ለትግራይ ህዝብ አስፈላጊ ዹሆኑ ዚምግብና ዚመድሃኒት ድጋፎቜ በአፋር ክልል በኩል እንድደርሱ ምቹ ሁኔታወቜን ኚመፍጠሩ በተጚማሪ በዛሬው እለት ብቻ ዚምግብ አቅርቊቶቜን ዚያዙ ሃያ ዚጭነት ተሞኚርካሪወቜ እና ዚነዳጅ ታንኚሮቜን ዚያዙ ሶስት ተሜኚርካሪወቜ ኚሰመራ ወደ መቀሌ መጓዛቾውን አስታውቋል። አለም አቀፉ ማህበሚሰብም ቜግሩን በሚመጥን ደሹጃ ለጉዳዩ ልዩ ትኩሚት ሰጥቶ መንቀሳቀስ እንደሚጠበቅበት አመልክቷል። በዚህም መሰሚት ሌሎቜ አጋር ድርጅቶቜ በጭነት አውሮፕላን ሁለት መቶ ሃምሳ ሰባት ሜህ አንድ መቶ ዘጠና ሁለት ኪሎ ግራም መድሃኒቶቜ፥ ዹህክምና ቁሳቁስና ዚምግብ አቅርቊቶቜን ኚአድስ አበባ ወደ መቀሌ ማጓጓዛቾው ተገልጿል። ኢትዮጵያንፊ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና ዹተሟሉ መሚጃወቜን ለማግኘት፡ ድሚ ገጜፊ ፌስቡክ፡ ዩትዩብፊ ቎ሌግራምፊ ትዊተርፊ በመወዳጀት ይኚታተሉን። ዘወትርፊ ኚእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን።
መንግስት ለትግራይ ህዝብ ሰብአዊ ድጋፍ እንድደርስ እያደሚገ መሆኑን አስታወቀ
Provide a news headline based on the following text.
ኚአድስ አበባ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውና በሃይቅ በተኚበበቜው ቢሟፍቱ ኹተማ በቢሟፍቱ ሃይቅ ዳርቻ ይገኛል አሻም አፍሪካ ሆቮልና ሪዞርት። ኚስያሜ ባለፈ አንድ ኬኒያዊ እንግዳ በናይጀሪያ ስም ዹተሰዹመ መኝታ ቀት ሲገባ ስለ ናይጀሪያ ዚተለያዩ መሚጃወቜን ያገኛል ያሉት ዹ አመቱ አቶ ሳህሉ በዚአገራቱ ስም መሰዹሙና ዚዚአገሩ ስእል በዚመኝታ ቀቱ መሰቀሉ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ያብራራሉ። እንደ ሪዞርቱ ባለቀት አቶ ሳህሉ ሃይሉ ገለፃ ይህን ቊታ አጜድቶ እዚህ ለማድሚስ መኪና ቆሻሻ ማንሳት ነበሚባ቞ው። ስሩ አምስት ሜትር ድሚስ ወደ መሬት ይጠልቃል ዚተባለው ይሄው ሳር አፈር በውሃና በንፋስ እንዳይሞሚሞር በማድሚግ ሚገድ ወደር ዚለሜ እንደሆነ ዹተገለጾ ሲሆን ኚሆለታ ግብርና ምርምር አምጥተው እንደተኚሉትም ዹ አሻም አፍሪካ ጠቅላላ አገልግሎት ኩፊሰርና ዚእለቱ አስጐብኝ አቶ ዳንኀል ግርማ ገልጞውልናል። አሻም አፍሪካ ሆቮልና ሪዞርት በቢሟፍቱ ሃይቅ ዙሪያ ኚተገነቡት አምሳያወቹ በብዙ ነገሮቜ ይለያል። በአጠቃላይ ኚአካባቢና ኚተፈጥሮ ጋር ህብር ዹፈጠሹ ሆቮልና ሪዞርት ነው ማለት ይቻላል። እኔ ባለሃብት አይደለሁም ሪዞርቱን ዚገነባሁት ኹላይ እንደገለጜኩት አፍሪካን አንድ ዚሚያደርግና ዚሚያቀራርብ እንድሆን ነው ያሉት አቶ ሳህሉ አብዛኛውን ወጭ ኚባንክ በተገኘ ብድር መሾፈናቾውንና ብር ሲያገኙ ሲቀጥሉ ብር ሲያጥራ቞ው ሲያቋርጡ ለግንባታው ወደ አምስት አመት ገደማ መውሰዱንም ተናግሚዋል። አሻም አፍሪካን ለዚት ኚሚያደርጉት ገጜታወቜ መካኚል ኚመታጠቢያ ክፍሎቜ ኚወጥ ቀትና ኚሌሎቜ ክፍሎቜ ዚሚወጡ ፍሳሟቜን በማጣራትና ሪሳይክል በማድሚግ በድጋሚ ጥቅም ላይ ማዋሉ ሲሆን ኹዚህም ባሻገር ለባዮ ጋዝነት በማዋል በባዮ ጋዝ ምግብ እንደሚያበስል ለማወቅ ቜለናል። በአሜሪካ አገር ስሩ ሜቶና እጣን ዚሚሰራበት ዚሳር አይነት ኚሪዞርቱ ግርጌ መጚሚሻ ላይ ተተክሏል። ኢትዮጵያ ዚአፍሪካ መድና እንደመሆኗ ዚአፍሪካ ባህል ገጜታ እና አጠቃላይ ሁኔታ በመጠኑም ቢሆን በአንድ ቊታ ዚሚገኝበት አሻም አፍሪካን በመገንባ቎ ደስተኛ ነኝ ብለዋል አቶ ሳህሉ ሃይሉ።
አመድ ሰፈርን ያስዋበው አሻም አፍሪካ
Write a brief headline summarizing the article below.
በአለም ላይ ኚሁለት መቶ ሃምሳ በላይ ጋዜጠኞቜ ታስሚዋል በመገባደድ ላይ በሚገኘው ዚፈሚንጆቜ ሁለት ሜህ ብቻ በመላው አለም ኚሁለት መቶ ሃምሳ በላይ ጋዜጠኞቜ መታሰራ቞ውንና ላለፉት አመታት ኚአለማቜን አገራት መካኚል በርካታ ጋዜጠኞቜን በማሰር ቀዳሚነቱን ይዛ ዚዘለቀቜው ቻይናፀ ዘንድሮም በአንደኛ ደሹጃ ላይ መቀመጧ ተነግሯል። በአመቱ አርባ ሰባት ጋዜጠኞቜን በማሰር በሁለተኛ ደሹጃ ላይ ዚተቀመጠቜው ቱርክ መሆኗን ዹጠቆመው ዚሲፒጀ ሪፖርትፀ ያም ሆኖ ግን በአገሪቱ ዚታሰሩት ጋዜጠኞቜ ቁጥር አምና ኹነበሹው በስልሳ ስምንት መቀነሳ቞ውን አመልክቷል። በአመቱ በመላው አለም ለእስር ዚተዳሚጉ ጋዜጠኞቜ ቁጥር አምና ኹነበሹው ሁለት መቶ ሃምሳ አምስት፣ በአምስት ብቻ ዹቀነሰ ሲሆን በመላው አለም ለእስር ኚተዳሚጉት ሁለት መቶ ሃምሳ ጋዜጠኞቜ መካኚል ሃያወቹ ሎቶቜ መሆናቾውንና ዚሎት ጋዜጠኞቜ ድርሻ ኹአምናው በ በመቶ መቀነሱን ሪፖርቱ አስሚድቷል። ተቀማጭነቱ በኒው ዮርክ ዹሆነው አለማቀፉ ዚጋዜጠኞቜ መብት ተሟጋቜ ሲፒጀ ባለፈው ሚቡእ ይፋ ባደሚገው አመታዊ ሪፖርቱ እንዳለውፀ ባለፉት ወራት ጊዜ ውስጥ አርባ ስምንት ያህል ጋዜጠኞቜን ያሰሚቜው ቻይና፣ ብዛት ያላ቞ው ጋዜጠኞቜ በማሰር ኚአለማቜን አገራት ቀዳሚነቱን ይዛለቜ። በአለማቀፍ ደሹጃ ሃሰተኛ ዜናወቜን አሰራጭተዋል በሚል በመንግስታት ለእስር ዚሚዳሚጉ ጋዜጠኞቜ ቁጥር ባለፉት አራት ተኚታታይ አመታት እያደገ መምጣቱን ዹጠቆመው ሪፖርቱፀ በአመቱ በዚህ ሰበብ ስላሳ ጋዜጠኞቜ ለእስር መዳሚጋ቞ውንም አመልክቷል። ሳኡድ አሚቢያና ግብጜ እያንዳንዳ቞ው በተመሳሳይ ሃያ ስድስት ጋዜጠኞቜን በማሰር በሶስተኛ ደሹጃ ላይ ሲቀመጡ፣ ኀርትራ እንድሁም ቬትናም ጋዜጠኞቜን በማሰር ዚአራተኛና ዚአምስተኛ ደሹጃን መያዛ቞ውንም ሪፖርቱ ይጠቁማል። ሲፒጀ በዚአመቱ ለእስር ዚተዳሚጉ ጋዜጠኞቜን ዝርዝር በማጥናት ሪፖርት ማውጣት ኚጀመሚበት ጊዜ አንስቶ እጅግ በርካታ ቁጥር ያላ቞ው ጋዜጠኞቜ ዚታሰሩበት አመት ሁለት ሜህ እንደነበር ዹተነገሹ ሲሆን፣ በአመቱ ሁለት መቶ ሰባ ሶስት ጋዜጠኞቜ መታሰራ቞ውንም ሪፖርቱ አስታውሷል።
ቻይና ጋዜጠኞቜን በማሰር ዘንድሮም አለምን ትመራለቜ
Create a short title for the given news content.
ዚአካባቢ ጥበቃን መሰሚት ያደሚገ ዚስራ እድል ዹመፍጠር ዝንባሌ ያላ቞ውን ወጣት ዚስራ ፈጣሪወቜን መደገፍ አላማው ያደሚገ ፕሮጀክት ስራ ጀመሚ። ካታላይዚንግ ግሪን ቢዝነስ ኢን ኢትዮጵያ በሚል ስያሜ ወደ ስራ ዚገባው ይህ ፕሮጀክት አላማው፣ ሰፊ ቁጥር ዹሚሾፍነውን ዚሃብሚተሰብ ክፍል በተለይም ወጣቱ አካባቢን ዚማይጎዳ ይዘት ያለው ስራ እንደት መፍጠር ይቜላል ዹሚለው ላይ አተኩሮ ዚሚሰራ እንደሆነ አስሚድተዋል። ዚሪቜ ፎር ቾንጅ ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሶፊያ ብራይትሆልትዝ በበኩላ቞ው፣ ድርጅታ቞ው በዋናነት ወጣት ዚስራ ፈጣሪወቜን ማእኚል ያደሚገ ስራ ለማኹናወን ሲያቅድ እንደ ዋነኛ ምክንያት ዹወሰደው ወጣት ዚስራ ፈጣሪወቜ ኹማንኛውም ዚሃብተሚተሰብ ክፍል ይልቅ፣ በዙሪያ቞ው ያለውን ቜግር በመሚዳት መፍትሄ ለማምጣት ዚሚስቜል አቅም ባለቀት መሆናቾውን በማመን እንደሆነ ተናግሚዋል። ፕሮጀክቱ ሁለት አበይት ጉዳዮቜን ለማሳካት ያቀደ ሲሆን፣ አንደኛው በኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማትና ዹቮክኒክና ሙያ ኮሌጆቜ ውስጥ ዹሚገኙ ወጣቶቜ እንደት ዚአካባቢ ጥበቃ አሹንጓደ ስራ እድል ፈጠራ ባለቀት መሆን ይቜላሉ ዹሚለውን ዹሚደግፍ መሆኑ ተልክቷል። አይኪያ ፋውንደሜን ዹተሰኘው ዚስዊድን ግብሚሰናይ ድርጅት ዚአንድ ሚሊዮን ዶላር ዚገንዘብ ድጋፍ ዚሚያደርግለት ይህ ፕሮጀክት፣ ሪቜ ፎር ቾንጅ በተባለ ድርጅት ለ ወራት ያህል አካባቢ ጥበቃን መሰሚት ያደሚገ ዚንግድ ፈጠራ ስራ ዚሚያቀርቡ ወጣቶቜን ዹሚደግፍ እንደሆነ ተገልጿል። መጋቢት ስድስት ቀን ሁለት ሜህ አመተ ምህሚት በሞራተን አድስ ሆቮል ይፋ በተደሹገው ዚፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ ወቅት ዚተገኙት ዚሪቜ ፎር ቾንጅ በኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ለምለም ስንቅነህ እንደተናገሩት፣ ሪቜ ፎር ቾንጅ በኢትዮጵያ ዚሚተገብሚውን ዹአሹንጓደ ስራ ፈጣሪነት ፕሮጀኚት ለመደገፍና ለማዳበር አይኪያ ፋውንደሜን ዚአንድ ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጎላ቞ዋል። ኹላይ በተጠቀሱት ዚትምህርት ተቋማት ዹሚገኙና ተመርቀው ለመውጣት በዝግጅት ላይ ዹሚገኙ ተማሪወቜን በባለሙያወቜ በማሰልጠን ዹሚጀምሹው ይህ ፕሮጀክት፣ ዚሚሰጣ቞ውን ስልጠና ተኚትሎ ጥሩ ዹሆኑና ኚአካባቢ ጥበቃ ጋር ዹተገናኙ ዚስራ ፈጠራወቜን ዚሚያቀርቡ ስልሳ ተማሪወቜን በገንዘብ ይደግፋል ተብሏል። ስራ ፈጣሪወቜ ሃሳባ቞ውን ወደ ተግባር በመቀዹር ሂደት ውስጥ ዚተለያዩ ቜግሮቜ እንደሚገጥማ቞ው ያስታወቁት ስራ አስፈፃሚዋ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ኚሚስተዋለው ዚኢንቚስትመንት ካፒታል እጥሚት አንስቶ ዹአቅም ግንባታና ዚስራ ላይ ትስስር እንደሚያስፈልጋ቞ው አስሚድተዋል። በሙኚራ ደሹጃ ለ ወራት በሚተገበሹው ፕሮጀክት ውስጥ ለሚሳተፉ ፈቃደኛ ወጣቶቜ ጥሪ ዚሚቀርብ ሲሆን፣ ኚዚያ በማስኚተል ለተመሚጡ ተማሪወቜ ዹአቅም ግንባታና ዚፋይናንስ ድጋፎቜ ድርጅቱ እንድያገኙ እንደሚያደርግ ፕሮጀክቱ ይፋ በተደሚገበት መድሚክ ተገልጿል። ላለፉት ሰባት አመታት ኚሁለት መቶ ስላሳ በላይ ዚስራ ፈጣሪወቜ ሲደገፉ እንደነበር ዚተናገሩት ወይዘሮ ለምለም፣ በዚህ ፕሮጀክት በመጚሚሻ ተመርጠው ዚሚቀሩትም ሆኑ ጥሪ ቀርቩላቾው ወደ ስልጠና ዚሚገቡት ተማሪወቜ ዚሚያገኙት ስልጠና በራሳ቞ው አቅም መስራት እንድቜሉ ዚሚሚዳና ግንዛቀ ዚሚጚብጡበት ይሆናል ብለዋል።
ዚአካባቢ ጥበቃን መሰሚት ያደሚገ ዚፈጠራ ስራን ዹሚደግፍ ፕሮጀክት ስራ ጀመሹ
Provide a news headline based on the following text.
ኢሳት ሰኔ አንድ ፥ ሁለት ሜህ ዘጠኝ ዚኬንያ ፖሊስ ወደ ሃገሪቱ በህገወጥ መንገድ ገብተዋል ዚተባሉ አርባ ኢትዮጵያውያን ሃሙስ በቁጥጥር ስር መዋላቾውን አስታወቀ። ኢትዮጵያውያን ስደተኞቹ በአንድ ወኪል አማካኝነት ሰኞ ኚኢትዮጵያ ተነስተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ዚማቅናት እቅድ እንደነበራ቞ው በአስተርጓሚ በኩል ቃል እንደሰጡ ዚንጅሩ አስተዳደር ሃላፊ አስሚድተዋል። ወደ ደቡብ አፍሪካ በማቅናት ላይ ያሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን ኬንያን ጚምሮ በተለያዩ ዚምእራብ አፍሪካ ሃገራት ወደ ሃገሪቱ በህገወጥ መንገድ ገብታቜኋል ተብለው ለእስር ተዳርገው ይገኛሉ። በአሁኑ ወቅት በቃዹሌ ኹተማ በሚገኝ አንድ እስር ቀት በእስር ላይ ዚሚገኙት ኢትዮጵያውን በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ፍርድ ቀት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ዚኒጅሩ አስተዳደር ኮማንደር ፓርቲክ ምዋምባ ኢትዮጵያውያኑ በአስተዳደሩ ስር በምትገኘው ዹቃዹሌ ኹተማ በአንድ መኖሪያ ቀት ውስጥ እንዳሉ በነዋሪወቜ በተደሹገ ጥቆማ ሊያዙ መቻላ቞ውን እንደገለጹ ዘስታር ዹተሰኘ ዚሃገሪቱ ጋዜጣ ዘግቧልል። ዚኬንያ ፖሊስ ምንም ዹጉዞ ሰነድ አልያዙም በተባሉ ኢትዮጵያውያን ላይ ምርመራ መጀመሩን በመግለጜ ወኪል ዚተባለውን አካል ለመያዝ ፍለጋ እያካሄደ እንደሚገኝ ለመገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል። በህገወጥ መንገድ ወደ ኬንያ ገብተዋል ዚተባሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉም ወንዶቜ ሲሆኑ ኚአስር እስኚ ሃያ አምስት አመት ዚእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ መሆናቾው ታውቋል። ኚሃገሪቱ በመሰደድ ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ደቡብ አፍሪካን ጚምሮ ወደ ተለያዩ ሃገራት ዚመሰደድ እቅድ እንዳላ቞ው ታውቋል። ዚኬንያ ዚኢሚግሬሜን ባለስልጣናት ወደ ሃገሪቱ ዚሚሰደዱ ኢትዮጵያውን ቁጥር መጹመርን ተኚትሎ በድንበር አካባቢ አዳድስ ዚቁጥጥር ኬላወቜን ቢያቋቁሙም ዚስደተኞቜን ፍልሰት ሊቀንስ እንደሚቜል ተገልጿል። ዹአለም አቀፍ ስደተኞቜ ድርጅት በበኩሉ ኢትዮጵያውያኑ ወደ ሃገራ቞ው ለመመለስ ዚገንዘብ ድጋፍ እያሳሰበ መሆኑን ይገልፃሉ።
በኬንያ ህወገጥ ዚተባሉ አርባ ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቾው ተገለጾ
Write a brief headline summarizing the article below.
ዚካቲት ዘጠኝ ቀንአመተ ምህሚትኢሳትዜና በስልጣን ላይ ያለውን ዚህወሃት ኢህአደግ መንግስት በሃይል ለመጣል ዚሚንቀሳቀሱት ሶስቱ ዹአፋር ድርጅቶቜ ማለትም አርዱፍ ጋድሌና ዚአፍደራ ታጋዮቜ ዚካቲት ቀን አም ዚጋራ ግንባር ፈጥሚዋል። አድሱ ግንባር ኚሌሎቜ ዚኢትዮጵያ ሃይሎቜ ጋር ጥምሚት በመፍጠር ለመታገል ፍላጎት እንዳለውም አቶ ኢብራሂም ተናግሚዋል። ዚአርዱፍ ሊቀመንበር አቶ ኢብራሂም ሙሳ ለኢሳት እንደገለጹት ሶስቱም ዹአፋር ድርጅቶቜ በተናጠል ሆነው መዋጋታ቞ው ለስርአቱ እድሜ መርዘም አስተዋጜኊ በማድሚጉ በቅድሚያ ድርጅቶቹ ዚጋራ ግንባር ፈጥሚው በጋራ ለመዋጋት አስፈላጊ መሆኑን ስምምነት ላይ በመድሚሳ቞ው በአንድ ወታደራዊ እዝ ስር ሆነው ለመታገል ወስነዋል። ድርድሩ ዚተካሄደው በአፋር ህዝብ ፓርቲ በኩል መሆኑንም ለማወቅ ተቜሎአል። ኚአቶ ኢብራሂም ሙሳ ጋር ዹተደሹገው ቃለምልልስ ኹዜናው በኋላ ይቀርባል።
በትጥቅ ትግል ዚሚያምኑ ሶስት ዹአፋር ድርጅቶቜ ግንባር ፈጠሩ
Create a short title for the given news content.
በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢወቜ በሚገኙ ደሹቅ ወደቊቜ ንብሚት እንድጭኑ ለተኚማቹ ኮን቎ይነሮቜ ዚመያዣ ኪራይ ድመሬጅ እና ዹመጋዘን ኪራይ መንግስት በዚአመቱ እስኚ አስር ሚሊዮን ዶላር እንድኚፍል መገደዱን ዚኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ገለጞ። ይህንን ለማድሚግ ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ዚገቢወቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ዚባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎትና አስመጭወቜ በጋራ መክሹው ዚሚያመነጩትን ዚመፍትሄ ሃሳብ ደግሞ መንግስት ተቀብሎ ሊደግፍ እንደሚገባ አስሚድተዋል። ዚኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን አበራ በሰጡት ምላሜ በደሹቅ ወደቊቜ ሳይነሱ ዚተኚማቹ ንብሚት ዚጫኑ ኮን቎ይነሮቜ በመቶ ዚሚሆኑት ዚሌሎቜ አገሮቜ ዚመርኚብ ኩባንያወቜ ንብሚት መሆናቾውን ገልጞዋል። ቋሚ ኮሚ቎ው ዚባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ዚስራ አፈፃጾሙን ለመገምገም ባካሄደው ውይይት ላይ ዹተቋሙ ተቆጣጣሪ ዚመንግስት አካላት እንድገኙ ያደሚገ በመሆኑ ዚተቆጣጣሪ ተቋማቱ አመራሮቜ ዹተገለጾው ዚኮን቎ይነሮቜ ክምቜት አሳሳቢና አገራዊ መፍትሄ እንደሚያስፈልገው ተናግሚዋል። ኹ ቀናት በኋላ በደሹቅ ወደቊቜ ዚቆዩ ንብሚት ዚጫነ ኮን቎ይነሮቜና ተሜኚርካሪወቜ በኢትዮጵያ ገቢወቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ተወርሰው በሜያጭ መወገድ እንደሚገባ቞ው በህግ ቢደነገግም ኮን቎ይነሮቜ በደሹቅ ወደቊቜ በኹፍተኛ መጠን መኚማ቞ታ቞ው መቀጠሉ ለምን እንደሆነ ቋሚ ኮሚ቎ው ማብራሪያ ጠይቋል። ኮን቎ይነሮቹ ዚተጫነባ቞ው ንብሚት ተራግፎ ለሌላ ጭነት መዘጋጀት ሲኖርባ቞ው ወይም ለባለቀቶቹ መመለስ ሲገባ቞ው በደሹቅ ወደቊቜ ውስጥ እንደ እቃ መጋዘንነት እያገለገሉ መሆኑን ጠቁመዋል። አስመጭወቜ ንብሚታ቞ውን ማንሳት አለመቻላ቞ው ዋናው ዚቜግሩ መንስኀ መሆኑን ጠቁመው በአስመጭወቹ በኩል ዚሚነሳው ቜግር ንብሚትን ለማንሳት ዚሚያስፈልገውን ዚቀሚጥ ክፍያ ለመክፈል ዚገንዘብ እጥሚት እንዳለባ቞ው በሌላ በኩል ደግሞ ንብሚቱን ካስመጡ በኋላ ገበያ ዚማጣት ቜግር እንዳለባ቞ውም ዚሚያወሱ መሆናቾውን ዘርዝሚዋል። ኮን቎ይነሮቹ ባለመመለሳ቞ው ዚኮን቎ይነር መያዣና ዚደመሬጅ ክፍያ ያላግባብ እዚወጣ መሆኑን እንደ አገርም በዚአመቱ ኹ ሚሊዮን ዶላር እስኚ አስር ሚሊዮን ዶላር እንደሚወጣ አስሚድተዋል። ለአጭር ጊዜ መፍትሄ ግን መንግስት ኹአለም ባንክ ካገኘው ሚሊዮን ዶላር በደሹቅ ወደቊቜ መጋዘኖቜ በመገንባት ኮን቎ይነሮቜን በማራገፍ ክምቜት ለማስቀሚት ፕሮጀክት ተቀርጟ በትግበራ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ቋሚ ኮሚ቎ውም ይህንኑ በማንሳት ዚሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅትና ዹተቋሙ ተቆጣጣሪ ዹሆነው ዚመንግስት ልማት ድርጅቶቜ ሚኒስ቎ር ክልሎቜ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ዚመጚሚሻ መፍትሄ መስጠት እንደሚገባው አሳስቧል።
በደሹቅ ወደቊቜ እቃ ጭነው ለተኚማቹ ኮን቎ይነሮቜ ኪራይ መንግስት በዚአመቱ እስኚ አስር ሚሊዮን ዶላር ይኹፍላል ተባለ
Provide a news headline based on the following text.
አድስ አበባ፣ ታህሳስ አንድ፣ ሁለት ሜህ ኀፍ ቢ ሲ በካናዳ ዚኢፌደሪ አምባሳደር ናሲሎ ጫሊ ኚካናዳ ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዹውጭና ዚመኚላኚያ ፖሊሲ አማካሪ ደቪድ ሞሪሰን ጋር ተወያዩ። ቡድኑን ለማስወገድ ዹተወሰደ ዹህግ ማስኚበር ዘመቻ ንጹሃን ዜጎቜ ሳይጎዱ በጥንቃቄ መካሄዱን እና መጠናቀቁን አስሚድተዋል። በስፍራው ማህበራዊ ድጋፍ ዚማቅሚብና ዚመልሶ ማቋቋም ስራ እዚተካሄደ ስለ መሆኑም ገልጞዋል። ዚጁንታው ቡድን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ዚሚካሄደውን አጠቃላይ ሃገራዊ ሪፎርም ለማበላሞት ሲሰራ መቆዚቱን ተናግሚዋል። ወንጀለኛ ቡድኖቜን በማደን ወደ ህግ ለማቅሚብ መንግስት ትኩሚት ሰጥቶ እዚሰራ ነውም ብለዋል። ደቪድ ሞሪሰን በበኩላ቞ው ስለተደሚገላ቞ው ገለፃ አመስግነው ሃገራ቞ው ለውጡን ደግፋ ዚምታግዝ መሆኗን አሳውቀዋል። ዚተጎዱ መሰሚተልማቶቜን በፍጥነት ጠግኖ ወደ አገልግሎት ለመመለስ በትኩሚት እዚተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። አምባሳደሯ ዚህወሃት ጁንታ ዚሃገሪቷን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር መመዝበሩን አንስተዋል። በቪድዮ ኮንፍሚንስ በተካሄደው ውይይት አምባሳደር ናሲሎ ስለ ወቅታዊ ዚኢትዮጵያ ሁኔታ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኚፌስቡክ ገፃቜን በተጚማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና ዹተሟሉ መሚጃወቜን ለማግኘት፡ ዹፋና ድሚ ገጜ ይጎብኙፀ ተንቀሳቃሜ ምስሎቜን ለማግኘት ዹፋና ቎ሌቪዥን ዚዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መሚጃወቜን ለማግኘት ትክክለኛውን ዹፋና ቎ሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ኹዚህ በተጚማሪም በትዊተር ገፃቜን ይወዳጁን ዘወትር ኚእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን።
አምባሳደር ናሲሎ ኚካናዳ ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዹውጭና ዚመኚላኚያ ፖሊሲ አማካሪ ደቪድ ሞሪሰን ጋር ተወያዩ
README.md exists but content is empty.
Downloads last month
6