id
stringlengths
4
5
url
stringlengths
31
537
title
stringlengths
1
65
text
stringlengths
183
241k
49611
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A1%E1%88%BD%20%E1%89%A3%E1%88%AD%E1%8A%94%E1%8C%A3
ቡሽ ባርኔጣ
ቡሽ ባርኔጣ ከቡሽ ወይንም ከግንደ ብሌን የተሠራ ባርኔጣ ሲሆን በዓለም ዙሪያ በአንዳንድ ወታደራዊ ወግ ልብስ እንዲሁም በሕዝቡ መካከል የሚታይ ቄንጥ ነው። ከሕንድ ቡሽ (ሾላፒስ) የተሠሩት ባርኔጦች መጀመርያ በስፓኒሾች በፊሊፒንስ በ1840 ዓም አካባቢ ሲሆን፣ በሙቀት ሀገራት በገሞጂ በጣም ስለሚስማማ በቶሎ ወደ ፈረንሳይ፣ ብሪታንያ፣ ጣልያንና ጀርመን ኃያላት ተስፋፋ። በአንዳንዶች ዘንድ የቅኝ አገር ምልክት ቢታስብም፣ በተረፈ በበርካታ ሌሎች አገራት ተወዳጅነትና ሰፊ ጥቅም አግኝቷል። እስከ ዛሬ ድረስ በተለይ ለምሳሌ በቬትናም፣ ብሪታንያ፣ ካናዳ፣ አሜሪካ፣ ኔዘርላንድ፣ ቶንጋ በአንዳንድ ጭፍሮች ሊታይ ይችላል፣ እንዲሁም የክብር ዘበኞች በታይላንድ፣ ፊሊፒንስ፣ ሞናኮ፣ ዚምባብዌ እና ፖሊሶች ወይም የትራፊክ ፖሊሶች በስሪ ላንካ፣ ሕንድና ጣልያን የቡሽ ባርኔጣን ለብሰውታል። በኢትዮጵያም በተለይ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት እስከ 1967 ዓም ድረስ በክቡር ዘበኞች እንዲሁም በጃንሆይ እራሳቸው ይታይ ነበር። ቡሽ ባርኔጦች ብዙ ልዩ ልዩ ቅርጾች አሏቸው፣ በታይላንድ ዘበኞች በፎቶው እንደሚታይ አንዳንዴ አንድ ነጥብ በአናት ላይ አቁመዋል።
46044
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%8C%89%E1%8A%95%E1%8C%85
ብጉንጅ
ብጉንጅ ብጉር መስለ የቆዳ በሽታ ፡ የቆዳ ማበጥ ወይም መደደር ነው። ብጉንጅ አንድና ከዚያ በላይ የሆኑ የፀጉር መዉጫ ቀዳዳዎች በባክቴሪያ ምክንያት እንፌክሽን በሚፈጥርበት ወቅት ቆዳ ስር በመቆጣት፣መግል በመያዝና በማበጥ ህመም እንዲከሰት የሚያደርግ ችግር ነዉ፡፡ እብጠቱ በፍጥነት በማደግና በመግል በመሞላት የህመም ስሜቱ እንዲጨምር ያደርጋል፡፡ የህመሙ ምልክቶች ብጉንጅ በየትኛዉም የሰዉነት ክፍል ሊወጣ ቢችልም በብዛት ግን የሚታየዉ/የሚወጣዉ በፊት ቆዳ፣ አንገት፣ ብብት ስር፣ መቀመጫና ታፋ ላይ ነዉ፡፡ • ህመም ያለዉና ቀላ ያለ እብጠት መታየት • በእብጠቱ ዙሪያ የቀላና ያበጠ ቆዳ መታየት • እብጠቱ መግል እየሞላዉ ሲመጣ መጠኑ እየጨመረ መምጣት • ነጭ ወይም ቢጫ ነገር በእብጠቱ ጫፍ ላይ መታየት ከዚያን መፈንዳትና መግሉ መዉጣት የህክምና ባለሙያ ማይት የሚገባዎ መቼ ነዉ? የብጉንጁ መጠን አነስተኛ ከሆነ እርስዎ እራስዎ እንክብካቤ ማድረግ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የሚከተሉት የህመም ምልክቶች ካለዎት የህክምና ባለሙያዎን ያማክሩ፡፡ • ብጉንጅ የፊት ቆዳዎ ላይ ከወጣ • ከመጠን በላይ ካበጠ ወይም በፍጥንት ከተባባሰ • ትኩሳት ካለዎ • መጠኑ ከ5 ሳንቲሜትር በላይ ከሆነ • በሁለት ሳምንት ዉስጥ የማይድን ከሆነ • ከጠፋ በኃላ ተመልሶ ከመጣ ናቸዉ፡፡ ተጋላጭነትዎን የሚጨምሩ ነገሮች ምንም እንኳ ማንኛዉም ጤነኛ የሆነ ሰዉ ብጉንጅ ሊይዘዉ ቢችልም የሚከተሉት ነገሮች ግን ይበልጥ ተጋላጭ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ • ስታፍሎኮካል ባክቴሪያ እንፌክሽን ከያዘዉ ሰዉ ጋር የቅርብ ግንኙነት መኖር • የስኳር ህመም • የሰዉነት የበሽታ መከላከል መቀነስ ናቸዉ፡፡ የህይወት ዘይቤ ለዉጥና የቤት ዉስጥ ህክምና ትናንሽ ብጉንጆችን የሞቀ ዉሃ እላዩ ላይ በመያዝና በራሱ እንዲፈርጥ በመተዉ እራስዎ ሊያክሙትና እንዲሻሻል ማድረግ ይችላሉ፡፡ ስለሆነም • የሞቀ ነገር እላዩ ላይ መያዝ • ኮንታሚኔሽንን መከላከል፡- ብጉንጁን ከነኩ በኃላ እጅዎን በደንብ መታጠብ፡፡ ብጉንጅ የነኩ ልብሶች ካለዎና ብጉንጅ በተደጋጋሚየሚያስቸግርዎ ከሆነ ልብሱን በካዉያ መተኮስ • ብጉንጁን እራስዎ ያለማፍረጥ፡- ይህን ማድረግ ብጉንጅ ሌላ ቦታ እንዲዛመትያደርጋሉና፡፡
53948
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B3%E1%8C%8B%E1%89%B6%20%E1%8A%A9%E1%88%9D%E1%89%A4
ዳጋቶ ኩምቤ
ዳጋቶ ኩምቤ ቆልቻ ከታህሳስ 2022 ጀምሮ የኢትዮጵያ ፌዴራል ሰነዶች ምዝገባ እና ማረጋገጫ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በመሆን እያገለገሉ ያሉ ኢትዮጵያዊ ፖለቲከኛ ናቸው። ዳጋቶ የወላይታ ተወላጅ ሲሆን ከዚህ በፊትየወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆኖ አገልግሏል። ዳጋቶ ከዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት እስከ ወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ ድረስ አገልግሏል። ዳጋቶ በፈረንጆቹ ከ2018 ጀምሮ ለሁለት ዓመታት ያህል የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ ሆነው ሲሰራ ቆይተዋል። ከወላይታ የክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ስማቸው በጉልህ ከሚነሳቸው የቀድሞ አመራሮች ዳጋቶ ኩምቤ አንዱ ናቸው። ዳጋቶ በታህሳስ 2022 በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢፌዲሪ ሰነዶች ምዝገባ እና ማረጋገጫ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ። መደብ:የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
13829
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%8C%8B%20%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8C%A2%E1%8D%8B%E1%8A%96%E1%88%B5
ደጋ እስጢፋኖስ
ደጋ እስጢፋኖስ ጎጃም ጣና ሃይቅ ውስጥ በሚገኘው ደጋ ደሴት ውስጥ የሚገኝ ቤ/ክርስቲያን ሲሆን ወደ200 የሚጠጉ መነኮሳትን ያስተዳድራል። ቤ/ክርስቲያኑ የተቆረቆረው በ13ኛው ክፍለ ዘመን፣ በአጼ ይኩኖ አምላክ የወንድም ልጅ በሂሩተ አምላክ ነበር። ሂሩተ አምላክ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር በወሎ በሚገኘው ሃይቅ እስጢፋኖስ በአስተማሪያቸው እየሱስ ሞዓ የተማሩ የአንድ ክፍል ሰወች ናቸው። ቀደምቱ ደጋ እስጢፋንኖስ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በእሳት ሲቃጠል አሁን የቆመው ቤ/ክርስቲያን በምትኩ ተሰርቷል። በዚህ ምክንያት ከታሪክ አንጻር የቤ/ክርስቲያኑ ዋና መስዕብ ሆኖ የሚቀርበው ሳይቃጠል የተረፈው ቤተ-መዘክሩ ነው። በዚህ መዘክር የይኩኖ አምላክ፣ ቀዳማዊ ዳዊት፣ ዘርአ ያዕቆብ፣ ዘድንግል፣ ፋሲለደስና ባካፋ የደረቁ ቅሬቶች ይገኛሉ። አጼ ሃይለ ስላሴ በ1951 ደሴቲቱን ከጎበኙ በኋላ የነገስታቱ እሬሳ በመስታውት ሳጥን እንዲቀመጥ አደረጉ። የፋሲለደስ ቅሪት ከሌሎቹ ነገስታት በበለጠ መልኩ እስካሁን ብዙ ሳይበላሽ በመቆየቱ የፊቱን መልክ ከቅሪቱ መገንዘብ ይቻላል። መደብ : ጣና አብያተ ክርስቲያናት
11069
https://am.wikipedia.org/wiki/%C2%AB%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%8A%A8%E1%88%A0%E1%89%B0%E1%8B%8D%20%E1%8B%95%E1%8B%B5%E1%88%8D%C2%BB
«የተከሠተው ዕድል»
«የተከሠተው ዕድል» ማለት የአሜሪካ መንግሥት ግዛት ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጀምሮ እስከ ሰላማዊው ውቅያኖስ ድረስ መስፋፋቱ ልዩ ዕድል እንደ ነበር የሚል እምነት ነው። አንዳንዴም የተከሠተው እድል ደግሞ ስሜን አሜሪካ በሙሉ ከነካናዳ፣ ሜክሲኮ፣ ኩባና መካከለኛው አሜሪካ ጋራ ሁሉ እስከሚመጠት ድረስ የሚል ሰፊ ትርጉም ተሰጠው። ከዚህ በላይ ይኸው ፅንሰ ሀሣብ ሌሎችን ግዛቶች መግዛቱን ለማጽደቅ ተጠቅሞ ያውቃል። በተከሠተው ዕድል አራማጆች አስተያየት ዘንድ መስፋፋቱ ጥሩ ነገር ከመሆኑ በላይ ግልጽ (የተከሠተው) እና እርግጥኛ (ዕድል) ነው ብለው አመኑ። በመጀመርያ ዘይቤው የ19ኛው ክፍለ ዘመን ፖሊቲካዊ መፈክር ሆኖ በጊዜ ላይ ለአሜሪካ መንግሥት በአሕጉሩ ዳር እስከ ዳር መስፋፋት ተራ ታሪካዊ መግለጫ ሆነ። ዘይቤው መጀመርያ በተለይ በጃክሶኒያን ዴሞክራት ወገን በ1840ዎቹ አሁን ምዕራብ አሜሪካ ያለውን ማለት ኦሬጎን ግዛት፣ ቴክሳስ ሬፑብሊክና በዚያን ጊዜ ስሜን ሜክሲኮ የነበረውን በኃይል መያዙን ለመምዋገት ይጠቀም ነበር። ሁለተኛ በ1890ዎቹ በሪፐብሊካን ወገን ደጋፊዎች መሃል አሜሪካ አገር ከስሜን አሜሪካ ውጭ እንድትስፋፋ የሚያጸድቅ ሃልዮ እንዲሆን ተነሣ። በ20ኛ ክፍለ ዘመን ዘይቤው በአሜሪካ መሪዎች ዘንድ ቶሎ ከጥቅም ወደቀ፣ ዳሩ ግን አንዳንድ ተቺዎች እንደሚያምኑ፣ ልዩ ልዩ የተከሠተው እድል ረገዶች፣ በተለይም በዓለም ዙሪያ ዴሞክራሲ ለመግፋፋትና ለመከላከል ያለው አሜሪካዊ 'ተልዕኮ' የመኖሩ እምነት፣ እስካሁን በአሜሪካ ፖሊቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ላይ ተጽእኖ አሳድሮአል ይላሉ። የአሜሪካ ታሪክ
53539
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%88%8A%20%E1%88%80%E1%89%A2%E1%89%A5
ኤሊ ሀቢብ
ኤሊ ሀቢብ (እ.ኤ.አ. የካቲት 6፣ 1973 የተወለደ) የሊባኖስ ሥራ ፈጣሪ እና የአንግሃሚ ተባባሪ መስራች ነው፣ አንግሃሚ የመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ () ክልልን የሚያገለግል የሙዚቃ ዥረት መድረክ ነው። ሀቢብ ከንግድ አጋሩ ከኤዲ ማሩን ጋር በመሆን በአረቡ አለም የዲጂታል ሙዚቃ ኢንዱስትሪን በመቅረጽ ሚና ተጫውቷል። የመጀመሪያ ህይወት እና ትምህርት ኤሊ ሀቢብ ተወልዶ ያደገው ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ ነው። ከልጅነቱ ጀምሮ ለቴክኖሎጂ እና ሥራ ፈጣሪነት ፍላጎት አዳብሯል። በአካዳሚክ ሥራው በኮምፒዩተር ምህንድስና ለመቀጠል በመወሰን ከሊባኖስ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ () ዲግሪ አግኝቷል። እ.ኤ.አ. በ 2011 ኤሊ ሀቢብ እና ኤዲ ማሮን አ በ ክልል ውስጥ ያለውን ህጋዊ የሙዚቃ ዥረት አገልግሎት እጥረት ለመፍታት የሚል ራዕይን ሰንቀው አንግሃሚን መሰረቱ። አንጋሚን ከመመስረቱ በፊት ሃቢብ የሞባይል መልእክት መግቢያ በር አቅራቢ የሆነውን ን ጨምሮ በርካታ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን አቋቁሟል። በተጨማሪም በመካከለኛው ምስራቅ ካሉት ፈር ቀዳጅ ኩባንያዎች አንዱ በሆነው ናሃርኔት.ኮም ላይ የቺፍ ቴክኖሎጂ ኦፊሰር () ቦታን ያዘ። አንጋሚ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የዲጂታል ሙዚቃ ስርጭት ለማስፋት በህዳር 2012 ተጀመረ። መድረኩ እውቅና አግኝቶ በክልሉ ባለው ተጽእኖ ምክንያት ብዙ ጊዜ " (የመካከለኛው ምስራቅ የሙዚቃ ማህደር)" [ ተብሎ ይጠራ ነበር። አረብኛ እና አለምአቀፍ ሙዚቃን ጨምሮ ከ72 ሚሊዮን በላይ ዘፈኖችን የያዘ የተለያዩ የሙዚቃ አማራጮችን ይሰጣል። አንጋሚ ከ75 ሚሊዮን በላይ የተመዘገቡ ተጠቃሚዎችን ሲኖሩት፣ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ወርሃዊ ጅረቶችን አሳክቷል። አንጋሚ ወደ ብዙ ክፍላት ተከፋፍሏል። እነዚህም አንጋሚ ስቱዲዮ፣ ፣ ፣ እና ያካትታሉ። እ.ኤ.አ. በማርች 2021 አንጋሚ በኒውዮርክ የአክሲዮን ልውውጥ ናስዳቅ ከቪስታስ ሚዲያ አክዩዜስን ኩባንያ ጋር በመዋሃድ ከክልሉ በዓይነቱ የመጀመሪያ ኩባንያ በመሆን ታሪክ ሰርቷል። በዚህ ውህደት ወቅት የአንግጋሚ ዋጋ በ220 ሚሊዮን ዶላር መካከል እንደሚሆን ተገምቷል። አንጋሚ በተለያዩ የሽልማት መድረኮች ላይ ተሸልሟል፣ በ2017 ከፍተኛ ጀማሪዎች፣ ምርጥ ቴክኖሎጂ፣ የወርቅ ሽልማት ለፈጠራ፣ ለብራንድ ግንዛቤ የወርቅ ሽልማት፣ ለግንኙነት ግንባታ/ሲአርኤም የወርቅ ሽልማት፣ ለኔስካፌ ዘመቻ ከፍተኛ ሽልማት፣ በ2016 ለኢኖቬሽን እና የአረብ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች የብር ሽልማት ኤሊ ሀቢብ, ለሥራ ፈጠራ ስኬቶች ብዙ እውቅና አግኝቷል እነዚህም የሚከተሉትን ያካትታሉ: ኤሊ ሀቢብ እ.ኤ.አ. በ2012 እና በ2013 የሊባኖስ ከፍተኛ ስራ ፈጣሪ በመባል ተመስግኗል ። በዘርፉ ባሳየው ስኬት እ.ኤ.አ. በ 2013 ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኖ ተመረጠ ፣ ። እ.ኤ.አ. በ2018 በፎርብስ የሊባኖስ ከፍተኛ ሥራ ፈጣሪ ተብሎ ተሰይሟል። በሙዚቃ እና በመዝናኛ ዘርፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ እውቅና በመስጠት በመካከለኛው ምሥራቅ እና ሰሜን አፍሪካ ክልል የሚገኘው የኢንዱስትሪ ማህበር የ"የአመቱ ምርጥ ፈጣሪ" ሽልማት ሸልሞታል። ገልፍ ቢዝነስን ጨምሮ በተለያዩ መጽሄቶች ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጣሪ በሆኑ የአረቦች ዝርዝር ውስጥ ቀርቧል። በ 2023 ከፍተኛ ስራ ፈጣሪዎች እንደ አንዱ ሆኖ እውቅና አግኝቷል ኤሊ ሀቢብ፣ በአቡ ዳቢ የንግድ ምክር ቤት፣ እና የሊባኖስ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ውስጥ ያገለግላል።
13724
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%8B%AB%E1%88%B3%E1%88%AB%E1%8A%9D%20%E1%8A%90%E1%8B%8D
እያሳራኝ ነው
እያሳራኝ ነው አንድ ከዚህ በፊት የተረቡት ሰው መንገድ ላይ አግኝቷቸው ሊደብደብ ሲያባርራቸው እሳቸውም ሲሮጡ ቆይተው ሊደርስባቸው ሲሆን ቶሎ ብለው ሱሪያቸውን ፈተው ለመጸዳዳት ቁጭ ይላሉ። አለቃ በነበሩበት ዘመን ይትባሃሉ ሰው ጠላትም ቢሆን የሚገደለው፤ የሚደበደበው ከነሱሪው እንጂ ሱሪ አውልቆ አይደለም። ይሄ ወንድነትንም አያሰኝም። መለኛው አለቃ ይቺን ሰሩዋ። ሰውየውም ሊነርታቸው (ሊያሳራቸው) እስኪነሱ አጠገባቸው ቆሞ ይጠብቃል። እሳቸው ቁጭ እንዳሉ ሰውየው እንደቆመ ሁለቱን የሚያውቅ ሰው በመንገዱ ሲያልፍ ሰላም ብሏቸው የሁለቱ ነገር ገርሞት «ምን እያደረጋችሁ ነው?» ይላቸዋል። አለቃም ፈጠን ብለው «እያሳራኝ ነው።» ብለው መለሱ። ሊደበድባቸው የነበረው ሰውዬ በመልሳቸው ስቆ ትቷቸው ሄደ አሉ። መደብ : የኢትዮጵያ ቀልዶች
15768
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%8A%95%E1%8B%B4%E1%88%8D%E1%89%A5%E1%88%AE%E1%89%B5
ማንዴልብሮት
ቤንዋ ማንዴልብሮት (20 ህዳር 1924 – 14 ጥቅምት 2010 እ.ኤ.አ) ታዋቂ የ20 ና የ21ኛው ክፍለዘመን ሒሳብ ፈልሳፊና ተመራማሪ ነበር። የፍርክስክስ ጂዖሜትሪ አባት ተብሎ የሚታወቀው ይህ ሰው በዚህ በፈጠረው የሂሳብ ጥናት ዘርፍ ቅጥ የለሽና የተፈረካከሱ የጂዖሜትሪ ቅርጾችን ፣ በተለይ ባጎላናቸው (ቀረብ ብለን ባየናቸው ጊዜ ሁሉ) ከራሳቸው ጋር ተመሣሣይነት ያላቸውን ክስተቶችን በሂሳብ እኩልዮሽ ለመግለጽ ችሏል።ማንድልብሮት ፖላንድ አገር ተወልዶ በህጻንነቱ ፈራንሳይ አደገ ኋላም ቀሪ ዘመኑን በአሜሪካን አገር አሳለፈ። የአሜሪካና ፈረንሳይ ዜጋ ነበር። የፍርክስክስ ጂዖሜትሪ መፈጠር ከማንዴል ብሮት መነሳት በፊት የነበረው የሂሳብ ተማሪወች አስተሳሰብ እንዲህ ነበር፡ «በአለማችን ላይ የሚገኙ ቅርጾች እጅግ ውስብስብ፣ የጎረበጡ ፣ ፍርክስክስ ያሉና ቅጥ የሌላቸው ስለሆኑ በሂሳብ ቀመር ሙሉ ለሙሉ ለመግለጽ አይቻልም» ። በዚህ ምክንያት ሂሳብ ተማሪወች ትኩረት ሰጥተው ያጠኑት የነበረው በምናባቸው አስተካክለው ለፈጠሩዋቸው ቅርጾች፣ ለምሳሌ ለክብ፣ ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማዕዘን፣ ፓራቦላ ወዘተ ነበር። እኒህ እንግዲህ በጣም የተስተካከሉ የምናባዊ አለም ፍጥረቶች እንጂ በርግጥም በተፈጥሮ የማይገኙ ናቸው። የማንዴልብሮት ትልቁ ግኝት እንግዲህ ከዚህ ከምናባዊ አለም ወጥተን ወደ ገሃዱ አለም ስንገባ የምናገኛቸውን የተወሳሰቡ ቅርጾችን፣ ለምሳሌ ደመናን፣ ተራሮችን፣ የባህር ወደብን፣ ዛፎችን በሂሳብ ቀመር ማስቀመጫ ዘዴን ማግኘቱና በሂደት ማስተካከሉ ነበር። ይህ ስራው ለዘመናዊው የኬዖስ ጥናት መሰረት ሆነ። የፍርክስክስ ጂዖሜትሪ ጥናት መሰረት ማንዴልብሮት በ1960ወቹ በተሰኘው የአሜሪካን የኮምፒውተር አምራች ኩባንያ ተቀጥሮ ይሰራ ናበር። በዚህ ወቅት ኮምፒውተሮች በሚያደርጉት የመረጃ ልውውጥ ወቅት የሚነሱ ኤሌክትሪክ ረብሻወች ምክንያት አንዱ ኮምፒዩተር ወደ ሌላው የላከው መልዕክት ስህተት ሆኖ ይገኝ ነበር። ምንም እንኳ የስህተቶቹ ተፈጥሮ በጊዜው በሳይንቲስቶች ባይታወቅም ስህተቶቹ ግን ሁልጊዜ የሚፈጠሩ ሳይሆኑ እየተጠራቀሙ በየተወሰኑ የጊዜ ክፍሎች የሚፈጠሩ መሆኑ ተደረሰበት፣ ማለት ለተወሰነ ጊዜ ስህተት የሌለበት ስራ ይሰራና ብዙ ስህተት ያለበት ስራ ደግሞ ለቀጣዩ ጊዜ ይፈጠራል። እኒህን ጥርቅም ስህተቶች በቅርበት ሲመረምር በርግጥም ቅጥ አልባ ከመሆን ይልቅ ንድፍ () እንዳላቸው ተገነዘበ። ንድፋቸውም እንዲህ ነበር፡ ሁለት ሰዓት የኮምፒውተሮቹን ልውውጥ ብናስተውል፣ አንዱ ስዓት ምንም ስህተት ሳይኖር ካለፈ መጪው አንድ ሰዓት ደግሞ ስህተት ይኖረዋል። በተጨማሪ ስህተት የተገኘበትን ሰዓት በ20 በ20 ደቂቃ ብንከፍለው እና ብንመለከት፣ አንዱ 20 ደቂቃ ያለ ስህተት ሲያልፍ ቀጣዩ 20 ደቂቃ ስህተት ይይዛል። እንግዲህ ሰዓቶቹን እየከፋፈለ ባጎላ ቁጥር በሁሉም የማጉሊያ ዘርፍ የስህተት አቃፊው ሰዓት መጠን ከስህተት አልባው ይጊዜ መጠን ጋር ያለው ውድር () ምንጊዜም ቋሚ እንደሆነ ተገነዘበ። በሌላ አነገጋር የኤሌክትሪኩ ረብሻ በፈለግነው መጠን ባጎላነው ቁጥር እራሱን ደጋሚ መሆኑን አሳየ፣ ማለት እያንዳንዷ ትንሽ ክፍል በጎላች ቁጥር ከሷ በላይ ያለውን የትልቁን ክፍል መልክ/ይዘት/ቅርጽ ትደግማለች። ማንዴልብሮት ይህ "እራስን የመድገም" ባህርይ በሌሎች የተፈጥሮ ክስተቶች እንደሚታይ ማስተዋል ጀመረ። ለምሳሌ የጥጥ ዋጋን በጥንቃቄ ሲመረመር፣ የየቀኑ፣ የየወሩና የየአመቱ የጥጥ ዋጋ ቅጥ አልባ ቢሆንም ነገር ግን የየቀኑ ዋጋ ለውጥ ከየየወሩ የዋጋ ለውጥ እንዲሁም ከየየአመቱ ለውጥ ጋር አንድ አይነት እንደሆነ ለማወቅ ቻለ። የዛፎች ቅጠሎችም ልክ እንዳንጠለጠላቸው ዛፍ ተመሳሳይ ቅርንጫፍ እንዳላቸው በሌላ ወገን ደግሞ የባህር ጠረፎች ላይ የሚስተዋሉት ገባ ብለው ያሉ ሰላጤወች (ወደ ዋናው ምድር ገባ ያሉ ወደቦች) ቀረብ ተብለው ሲታዩ በራሳቸው ላይ እንደገና ገባ ያለ አንስተኛ ሰላጤ ይኖራል ሆኖም እኒህ አንስተኛ ሰላጤወች ቀርበው ሲታዩ ሌሎች አንስተኛ ስላጤወች አሏቸው፣ ወዘተ...። በ1967 ባሳተመው "የብሪታንያ የባህር ጠረፍ ርዝመት ስንት ነው?" በሚለው መጽሃፉ በርግጥም የእንግሊዝ ጠረፍ ህልቁ መሳፍርት ሰላጤወች ያሉትና ርዝመቱ እንደ አትኩረታችን እንደሚለያይ አሳይቷል። የዚህ ምክንያቱ ከላይ ከላዩ እንይ ከተባል ጠረፉን መለካት ቀላል ቢሆንም ቀረብ እያልን ስንሄድ በወደቡ ውስጥ ሰላጤወች እናገኛለን ከዚያ ስንቀርብ በበሰላጤው ውስጥ ሰላጤ እና እያለ ሄዶ በድንጋይ ውስጥ ድንጋይ እናገኛለን በድንጋዩ ውስጥ አሸዋ እያለ ህልቁ መሳፍርት ይጠጋል። ርዝመቱ እንግዲህ በተለምዶ ቢታወቅም በትክክል ግን አይታወቅም። እነዚህን እራሳቸውን የሚደግሙ ክስተቶች እና ሌሎች ተመሳሳይ ንድፎች በነበረው ሂሳብ መግለጽ እንደማይቻል ስላወቀ በቀጣዮቹ አመታት የፍርክስክስ ጂዖሜትሪን () ለዚህ ተግባር ፈጠረ። ፍራክታል የሚለውንም የሂሳብ ቃል በ1975 ሰየመ። የዚህ ጥናቱ ውጤት በአንዲት የሂሳብ ቀመር ተጠናቀቀ፣ ። ይቺ ቀመር የ ማንዴልብሮት ስብስብ በመባል ትታወቃለች። መጽሃፉ ታተመ በ1982 ዓ.ም፣ ከሌሎች የከፍተኛ ሂሳብ ጥናት መጽሃፎች በላይ የተሸጠውን (የተፈጥሮ ፍርክስክስ ጂዖሜትሪ ) የተባለውን መጽሃፉን አሳተመ። በዚህ መጽሐፉ «ደመና የኳስ ቅርጽ አይደለም፣ ተራሮች የአሎ አሎ ቅርጽ የላቸውም፣ የባህር ጠረፎች ክብ አይደሉም፣ የዛፍ ቅርፊት ለስላሳ ሳይሆን ሸካራ ነው፣ መብረቅ በቀጥተኛ መንገድ አይጓዝም» በማለት በጊዜው የነበረውን የሂሳብና ሳይንስ አስተያየት ተቸ። የድሮው ጂዖሜትሪ ለተፈጥሮ ክስተቶች ምንም ተስማሚ እንዳልነበር ያሳመነው ማንዴልብሮት በመጽሃፉ እንዴት ከላይ የተገለጹት ክስተቶችና የስቶክ ገበያ ዋጋ ልውውጥ፣ የፈሳሾች ንቅንቅ፣ የመሬት እንቅስቃሴወች፣ ምህዋሮች፣ የእንስሣቶች የቡድን ባህርይና ሙዚቃ ሳይቀር በፍርክስክስ ጂዖሜትሪ ናሙናቸው እንዴት እንዲሰራ አስረዳ። ይህ እጅግ ሃይለኛ የሆነ ሂሳብ ፣ በአለንበት የኮምፒውተሮች ዘመን የበለጠ ሃይልን ሊጎናጸፍ ቻለ። በአሁኑ ዘመን ፍርክስክስ ጂዖሜትሪን በመጠቀም እውነተኛ ተራሮችን፣ የባህር ወደቦችን፣ ዛፎችን፣ ደመናወችንና የሴል እድግትን በማስመሰል በኮምፒውተር ስዕልና ተንቀሳቃሽ ምስል መስራት ይቻላል። ከዚህ ሌላ የዲጂታል ምስልን ለመጭመቅ፣ ለመኪና ጎማወች በጣም ጥሩ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን ለመመራመር፣ ለአውሮፕላን ክንፍ አቅድ ለማውጣት፣ ሃኪም ቤት ሄዶ የሰውነትን ክፍል በራጅ ለማስነሳት ወዘተ... ከፍተኛ ግልጋሎት ይሰጣል። የፈረንሳይ ሰዎች ሒሳብ ተመራማሪዎች
16124
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%92%E1%89%B0%E1%88%AD%20%E1%8A%A1%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%8A%96%E1%89%AD
ፒተር ኡስቲኖቭ
ስር ፒተር አለክሳንደር ኡስቲኖቭ (ከሚያዚያ 1921 - መጋቢት 28 ቀን፣ 2004 እ.ኤ.አ.) የነበረ የእንግሊዝ ተዋናይ፣ ጸሃፊና ተውኔት ደራሲ ነበር። በተለይ ደግሞ ፊልም ሰሪ፣ ቲያትር አዘጋጅ እና ኦፔራ መሪ፣ ፊልም አዘጋጅ፣ መድረክ ተላሚ፣ ፊልም ደራሲ፣ ቀልደኛ፣ ኮሜዲያን፣ ጋዜጣ አዘጋጅ፣ መጽሔት አዘጋጅ፣ ራዲዮ አስተላላፊና ቴሌቪዥን አቅራቢ ነበር። ሰር ፒተር ኡስቲኖቭ በእናቱ በኩል የራሽያ ነገስታት ዘር ሲሆን በአባቱ በኩል ደግሞ የራሺያ፣ ጀርመንና ኢትዮጵያ ነገስታት ዘር ነው። በራሱ በኡስቲኖቭ አስተያየት ቅደመ አያቱ የአጼ ቴወድሮስ ልጅናት የሚል ሲሆን በአንዳንድ ተመራማሪወች ዘንድ ግን ቅድመ አያቱ ማግዳሊና ሀል የተባለች የወለተ እየሱስ (ካታሪና ሀል) ልጅ ናት። ወለተ እየሱስ የእቴጌ ጣይቱ አማካሪ የነበረች የቴወድሮስ መድፍ ሰሪ የነበረው ሞሪዝ ሆል የተሰኘ አይሁድ ሚስት ነበረች። ወለተ እየሱስ የጀርመኑ ሰዓሊ ኤድዋርድ ዛንደር እና እሳተ ወርቅ የተሰኘች የጎንደር ወታደር የነበርው መቃዶ ልጅ ናት። እጅግ ቅኔያዊ በሆኑ ንግግሮቹና ቀልዶቹ የታወቀው ይህ ሰው በቴሌቪዥን፣ በሌክቸርና በመሳሰሉት የህዝብ ስራወች ምንጊዜም አይጠፋም ነበር። በኋላም በነበረው የአይምሮ ብሩህነትና የዲፕሎማት ስራ አስተማሪ ሆኖ አገልግሏል፣ የዩኒሲኤፍም አምባሳደርና የአለም አቀፍ ፌዴራሊስት እንቅስቃሴም ፕሬዜዳንት ነበር። ፒተር ኡስቲኖቭ የአካዳሚ አዋርድስ፣ ኤሚ አዋርድስ፣ ጎልደን ግሎብስና ባፍታ አዋርድስን አሸናፊ ሲሆን የመንግስት ሽልማትንም ከእንግሊዝ፣ ፈረንሳይና ጀርመን አገሮች አግኝቷል። በ2004 ዓ.ም. ከሞተም በኋላ፣ የዱርሃም ዩኒቨርስቲ የድህረ ምረቃ ማህበረሰብን የኡስቲኖብ ኮሌጅ በማለት ሰይሟል። ዋቢ ጽሕፈት የእንግሊዝ ተዋናዮች መደብ :አጼ ቴዎድሮስ መደብ :የኢትዮጵያ ሰዎች የእንግሊዝ ጸሓፊዎች
37836
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8C%88%E1%8A%93%E1%8A%9B%E1%8A%93%20%E1%8A%A2%E1%8A%95%E1%8D%8E%E1%88%AD%E1%88%9C%E1%88%BD%E1%8A%95%20%E1%89%B4%E1%8A%AD%E1%8A%96%E1%88%8E%E1%8C%82%20%E1%88%9A%E1%8A%92%E1%88%B5%E1%89%B4%E1%88%AD
መገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
መገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በ2003 ዓ.ም. የተቋቋመ ሲሆን ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ኤጀንሲን ፣ የኢትዮጵያ ቴሌኮሚኒኬሽን ኤጀንሲን እና ከቀድሞው የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር የመገናኛ ዘርፉን በማዋሃድ የተመሰረተ ሲሆን በስሩ የኢትዮቴሌኮም ን እና የኢትዮጵያ ፖስታ ድርጅትን ያስተዳድራል። የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂን (መመቴክ) ራዕይ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኑሮና ህይወት በመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ሆኖ ማየት፣ የመመቴክ ተልዕኮ መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂን (መመቴክ) በማልማት እና በሁሉም ሥፍራ በስፋት በመጠቀም የህብረተሰቡን ኑሮ ማሻሻልና መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂን ለአገሪቱ እድገት የሚሰጠውን ድጋፍ ማሳደግ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ሚኒስቴሮች የመረጃና የመገናኛ ቴክኖዎሎጂ
47089
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8C%8B%E1%8B%9D%20%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%95%20%E1%88%9B%E1%8B%B5%E1%88%A8%E1%8C%8D
የጋዝ ብርሃን ማድረግ
የጋዝ ብርሃን ማድረግ በዘመናዊ ምዕራባውያን ፖሊቲካ ዘይቤ ሲሆን በአጠቃላይ «ማታለል» ማለት ነው። በተለይ «የጋዝ ብርሃን ማድረግ» አንድ ድርጊት አልተደረገም ብሎ ለማስመስል ማለት ነው። ተደረገ እንጂ የሚሉ ሁሉ ከዚያ እንደ እብዶች ወይም እንደ ተሳቱ ደግሞ ማስመስል ነው። የዘይቤው መነሻ ከአንድ 1930 ዓም ድራማ በእንግሊዝኛ «የጋዝ ብርሃን» መጣ። በዚህ ድራማ (በኋላም በ1936 ዓም ፊልም)፣ አንድ ውሸታም ባል ሚስቱን በጣም ረቂቅ በሆነ በጋዝ ብርሃን ያታላታል።
15805
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8D%E1%88%AD%E1%8B%B4%20%E1%8B%88%E1%8B%AD%E1%88%9D%20%E1%8D%88%E1%8A%95%E1%8C%A3%E1%8C%A3
ውርዴ ወይም ፈንጣጣ
ውርዴ በግብረ-ስጋ የሚተላለፍ የባክቴሪያ በሽታ ነው። ውርዴ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው የውርዴውን ቁስል በቀጥታ ከነኩት ነው። ውርዴ ብዙ ምልክቶች ሲኖሩት፣ የሌላ በሽታ ምልክቶች ሊመስሉና ሊያታልሉም ይችላሉ። ውርዴ ሦስት ደረጃ ኣሉት። 1ኛ ደረጃ፦ በተጋባ ከ10 እስከ 90 ቀናት ባሉት ውስጥ የበሽታው የመጀመሪያ ምልክቶች ይታያሉ። የውርዴ ቁስል ይወጣል፣ ካልታከመም የውርዴው ቁስል እየባሰ ይሄዳል። 2ኛ ደረጃ፦ በማንኛውም ቦታ ከቆዳ ላይ ቀይና ፍም የመሰለ ነገር ይወጣል። ግን ምንም የማሳከክ ስሜት የለበትም። ካልታከመ በሽታው እየባሰ ይሄዳል። 3ኛና የመጨረሻው ደረጃ፦ ከውጭ ያሉት ምልክቶች ሁሉም ይጠፋሉ። የበሽተኛው ገላ ስሜት መጥፋት ይጀምራል፣ ከኣእምሮ ድክመትም ይደርሳል፣ የኣካላት ማንቀሳቀስም ሊያቅት ይጀምራል። ሕክምና ካላገኘ ውርዴ ሞትን ያስከትላል። በመጀመሪያ ደረጃ የሚገኝ ውርዴ በቀላሉ ሊታከምና ሊድን ይችላል። ግን በሓኪም ትእዛዝ እንጂ ከፋርማሲ ማንም ሰው የሚገዛቸው መድሓኒቶች ባክተሪያውን ሊያጠፉት ኣይችሉም። ሓኪም የሚያዝዘው መድሓኒት ውርዴውን ቢያጠፋውም እንኳን በኣካል ላይ ለደረሰውጉዳትና ጠባሳ ለማከም ኣይቻል ይሆናል። ውርዴን መከላከል ይቻላል። እንደ ሌሎች የግብረ- ስጋ (ኤስቲዲ) በሽታዎች ውርዴም ከግብረ-ስጋ ፈጽሞ በመገለል፣ ወይም ሕመሙ ከሌለበት ሰው ብቻ ግብረ-ስጋን በመፈጸም ለመከላከል ይቻላል። ኮንዶምን በመጠቀም ግን ሕመሙን ለመከላከል ኣይቻልም።
19135
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A3%E1%89%B0%20%E1%8A%AA%E1%88%BE%E1%8A%95
አባተ ኪሾን
አቶ አባተ ኪሾ በሙስና ምክንያት ከስልጣን ወርደው በእሥር አራት ዓመት ያህል ካሳለፉ በኋላ በምህረት ከመለቃቀቸው በፊት ኢሕአዴግ ኢትዮጵያን ሲቆጣጠር በኢሕአዴግ ጥላ ሥር የሲዳማን ዴሞክራሲያዊ ድርጅትን በመመሥርታቸው የመጀመሪያው የደቡብ ኅብረት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት/ደ.ኅ.ዴ.ድ. ጸሃፊና በኢሕአዴግ ዘመነ መንግሥት የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት ነበሩ። አቶ አባተ የትምህርት ደረጃቸው በ1ኛ ደረጃ መምህርነት ኮርስ ከአዋሳ መህራን ማሰልጠኛ ተመርቀው የ5ኛ ክፍል ህብረተሰብ ሳይንስ አስተማሪ ነበሩ። የኢትዮጵያ ሰዎች
3893
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8C%8A%E1%8B%9B%20%E1%89%B3%E1%88%8B%E1%89%85%20%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8D%8A%E1%8A%95%E1%8A%AD%E1%88%B5
የጊዛ ታላቅ እስፊንክስ
የጊዛ ታላቅ እስፊንክስ በጊዛ ሜዳ ግብጽ (ካይሮ አጠገብ) የሚገኝ ታላቅና ጥንታዊ ሐውልት ነው። የእስፊንክስ ቅርጽ የአንበሣ ገላ እና ሰብዓዊ ራስ አለው። ነገር ግን የቅሉ ቅርጽ እንደ ዘመናዊ ሰዎች አይሆንም። 2900 ዓክልበ. ዓመታት ገደማ በፈርዖን ካፍሬ ዘመን እንደ ተሠራ ይታመናል። በመካከለኛው ዘመን ጸሐፊዎች በግብጻዊው እብን አብድ ኤል-ሀከም እና በፋርሳውያን አል-ታባሪና ሙሐመድ ቈንዳሚር መጻሕፍት ዘንድ፣ ፒራሚዶች፣ እስፊንክስ ወዘተ. ሁሉ የተሠሩ ከማየ አይህ በፊት በኖሩት ክፉ ዘሮች (የቃየልና የሴት ልጆች) ነበር ብለው ጻፉ። ጥንታዊ ግብፅ የግብፅ ህንጻዎች እና መዋቅሮች ሥነ ቅርስ
15424
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%8A%A8%E1%8B%9C
ተከዜ
ተከዜ ወንዝ ከላስታ ተራሮች በተለይ ቀጭን ተራራ ፈልቆ ወደ ምዕራብ በመፍሰስ አቅጣጫውን ቀይሮ ወደ ሰሜን ከሄደ በኋላ እንደገና ወደ ምዕራብ በመመለስ ከአጥባራ ወንዝ ጋር ሱዳን ውስጥ ተገናኝቶ በመጨረሻ ከአባይ (ናይል) ጋር ይደባቃል። በአጠቃላይ 608 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሲኖረው የተወሰነው ክፍሉ የአሁኑ ኤርትራንና ኢትዮጵያን ድንበር ይከልላል። የኢትዮጵያ ወንዞች ነጭ አባይ
13467
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8B%E1%8A%93%E1%8B%8D%20%E1%8C%88%E1%8C%BD%201
ዋናው ገጽ 1
ማንኛውንም የሙቀት መጠን የሚቆጣጠሩ ረቂቅ መሣሪያዎች፣ በአውሮፕላን ዋና አካል፣ በትንሹም ቢሆን፣ የመሰርጎድም ሆነ የመሰንጠቅ አደጋ ሲያጋጥም ወዲያው ወደ አንድ ማዕከላዊ የቁጥጥር ክፍል፣ የራዲዮ መልእክት ማስተላፍ የሚችል መሣሪያ፣ የጀርመኑ የምርምር ተቋም ጠበብት ሠርተው በተሣካ ሁኔታ መሞከራቸውን፣ ከፍራይቡርግ አስታወቁ። አንዳች የኤሌክትሪክ ኅይል ማስተላለፊያ ሽቦም ሆነ ባትሪ የማያስፈልጋቸውና በአኤሮፕላን አካል የሚጣበቁት እጅግ የረቀቁ መሣሪያዎች፣ ጉልበት የሚያገኙት በአኤሮፕላኑ ውስጥና ውጭ ባለው የሙቀት ልዩነት ነው። በውጭ ከዜሮ በታች ከ 20 እስከ 50 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሲሆን ቅዝቃዜው፣ በአኤሮፕላን ውስጥ ተሣፋሪዎች በሚቀመጡበት ክፍል ደግሞ ሙቀቱ፣ 20 ዲግሪ መሆኑ የታወቀ ነው። የፍራውንሆፈር የምርምር ተቋም ባልደረባ የሆኑት ዲርክ ኤብሊንግ እንዳስረዱት፣ በአኤሮፕላን አካል የሚያጋጥም እንከንን የሚጠቁሙት መሣሪያዎች የሚገለገሉት «ማይክሮፔልት » ከተባለው ኩባንያ ጋር በመተባበር በተሠሩ በሙቀት ልዩነት ኃይል በሚያገኙ ጉልበት አመንጪዎች ነው። ሙከራው አመርቂ ቢሆንም፣ በሙቀት ልዩነት የማይቋረጥ ኃይል በማመንጨት በማጠራቀም ፣ እንዲሁም እንከን በመጠቆም፤ አገልግሎት የሚሰጥ የተሟላ ረቂቅ መሣሪያ በተጨባጭ ሁኔታ ጥቅም እንዲሰጥ ገበያ ላይ መዋል የሚችለው በ 3 ዓመታት ውስጥ እንደሚሆን ነው የተገለጠው። በተጠቀሰው ዘዴ የሚሠሩ ረቂቅ መሣሪያዎች፣ ለበረራ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን፣ ለህንጻዎች ግንባታ፣ እንዲሁም ለህክምና አገልግሎት ሰፊ ጠቀሜታ እንደሚኖራቸው ነው የሚታመንበት። ረቂቅ የሆነ፣ ይህን መሰል ተቆጣጣሪ መሣሪያ በአንድ አትሌት ሸሚዝም ተጣብቆ አትሌቱ ልምምድ ሲያደርግ የልብ ትርታውን እንደሚለካ፣ የመስማት ችግር ያለባቸውን ሰዎች የሚረዱ ረቂቅ መሣሪያዎችም ወደፊት ከተጠቃሚው ሰው አካል በሚያገኙት የሙቀት ኃይል ሊሠሩ እንደሚችሉ የሚያጠራጥር አልሆነም። ዚህን በተረፈ፣ ፣ ህዝብ አመላላሽ አኤሮፕላኖች፣ ሞተራቸው በሚቃጠል ቤንዚን መሆኑ ቀርቶ በኤልክትሪክ ኀይል እንዲንቀሳቀስ ማድረጉ ይበልጥ አስተማማኝነት እንዳለው ነው የሚነገረው። በዩናይትድ እስቴትስ የተደረገ ሙከራ እንደሚያረጋግጠው፣ የአኤሮፕላንን ቀዛፊ ሞተር (ፕሮፔለር) ያለሳንክ ለማንቀሳቀስ፣ በነዳጅ ከሚንቀሳቀስ ሞተር ይልቅ፣ የኤሌክትሪክ ሞተር ምናልባት 10 ፣ ብሎም 20 እጥፍ ያህል ይበልጥ አስተማማኝ ነው የተባለው። በኤሌክትሪክ ኃይል የሚንቀሳቀስ ሞተር 95 ከመቶ ያህል እጅግ አስተማማኝ መሆኑ ሲነገርለት፣ ፣ በነዳጅ ኃይል የሚሠራው፣ አስተማማኝነቱ ፣ ከ 18 እስከ 23 ከመቶ መሆኑ ነው የተገለጠው። ከዚህም ሌላ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚበሩ አኤሮፕላኖች የድምፃቸው መጠን እጅግ ዝቅ ያለ በመሆኑ ፣ በአኤሮፕላን ማረፊያ ጣቢያዎች አሠራር ረገድም ለውጥ ሊያስከትል እንደሚችል ነው የሚታሰበው።
32695
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A0%E1%8C%80%E1%89%B5
በጀት
በጀት ማለት ለወደፊቱ የሚመጣን ገቢና ወጪ የሚተነብይ የንዋይ/ገንዘብ እቅድ ነው። በዚህ እቅድ ውስጥ ቁጠባ፣ ብድር እና ወጪ ይካተታሉ ። ግለሰቦች ወይንም ቢዝነሶች ገቢና ወጪያቸው ሲመረመር ከሞላ ጎደል ቋሚ ሆኖ ስለሚገኝ የበጀት ጥቅም ከዚህ ይመነጫል። ማለት፣ ቋሚ ገቢ ወጪ፣ ለወደፊት ይሚሆነን ለመተንበይ አመቺ ነው። ተንብዮ በበጀት መመራት ግለሰቦብ በገንዘባቸው/ንዋያቸው ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖራቸው ያደርጋል። አላስፈላጊ ወጭወችን ለመለየት እና በአቅም መኖርን ለማወቅ ይረዳል። የበጀት አሰራር ቅድሚያ መሰረት በመጀመሪያ ደረጃ ላለፉት ሁለት ወራት የነበረን የወጪ ዓይነቶች ማወቅ ያስፈልጋል። እማይታወቅ ከሆነ ከአሁኑ በመጀመር ለሁለት ወራት መመዝገብ መልካም ልማድ ነው። ለአንድ ወር እያንዳንዷን ወጪ ከላይ በተቀመጠው የበጀት ዓይነት መሰርት መመዝገብ ጥሩ ምክር ነው። የወር ደሞዝን ወይንም ሌላ አይነት ገቢን ለብቻው ማስላት፣ ሁለተኛው የበጀት አሰራር ደረጃ ነው። ከዚያ በኋላ፣ ወጪን ከገበሚ መቀነስና ውጤቱ ነጌቲቭ ከሆነ ያለ አቅም መኖርን ስለሚያመላክት ለወደፊት ይህ እንዳይሆን የወጪ ልማድን እንዴት ማስተካከል እንዳለብን ዘዴ መዘየድ። ውጤቱ ፖዚቲቭ ሆኖ ከተገኘ ግን ያለ ገቢ ከወጪ ስለሚበልጥ ተራፊውን ገንዘብ በየወሩ ወደ ሴቪንግ አካውንት ማስተላለፍ ጥሩ ተግባር ነው። ድህረ በጀት በየወሩ በጀቱ መጻፍና መመርመር ይኖርበታል ማለት ነው። ለየጊዜው እንዲስማማ ተደርጎ መሻሻልና መታደስም ይኖርበታል። ወጭና ገቢ በሂደት በሚገባ ከታወቀ በኋላ የወደፊቱን ማቀድ ቀላል ይሆናል። ወጪን ለመቀነስ ወጭን በዝርዝር ጽፎ በዚያ ዝርዝር መሰረት መመራት ከአላስፈላጊ ወጪ ያድናል። ዕዳና በጀት የበጀት ዋናው ጥቅም አንድ ግለሰብ በራሱ ገቢና ወጪ ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖረው ማስቻሉ ነው። ስለሆነም ግለሰቦች ዕዳ ውስጥ መግባት ሲጀምሩ በቶሎ እንዲያውቁ ይሆናሉ። ስለሆነም ችግሩ ከመባባሱ በፊት አስቀድመው እርምጃ ለመውሰድ ይችላሉ። አንድ ግለሰብ ዕዳ ውስጥ እየገባ መሆኑን መረዳት ሲጀመር መጀመሪያውኑ የዕዳውን አይነት መለየት አስፈላጊ ነው። ቅድሚያ ትኩረት አግኝተው መከፈል ያለባቸው እማይለወጡ ዕዳወች (ምሳሌ ሞርጌጅ፣ የቤት ኪራይ ..) እና ቀስ ብለው ሊከፍሉ የሚችሉ ተለዋዋጭ ዕዳዎች (ምግብ፣ የኤሌክትሪክ፣ ውሃ ና ሌሎች በጥንቃቄ ሊቀነሱ የሚችሉ ቢሎች) ተለየተው ሊታወቁ ይገባል። ዕዳዎቹ ከተለዩ በሗላ፣ ዕዳዎቹን ለማስወገድ መንገድ ማበጀት ተገቢ ነው። ለዚህ ተግባር እንዲረዳ «በደህና ጊዜ» በትንሽ በትንሹ ማጠራቀም ጥሩ ነው። ነገር ግን ይህ ተደርጎ ካልሆነ፣ ቀሪ እዳን ቀስ በቀስ ለመክፍል የሚያስችል ስምምነት ከዕዳ-ሰጪው ጋር መግባት ጥሩ ነው። ባንኮች የአንድ ግለሰብ ዕዳ ባለቤት ከሆኑ፣ ግለሰቡን ለመርዳት ፍላጎት ይኖራቸዋል፣ ምክንያቱም ከርሱ ነውና ገንዘብ የሚያገኙት። ለዚህ ተግባር እንዲረዳ ኮንሶሊዴሽን (ሁሉን ዕዳን በአንድ ላይ መሰብሰብ) እና ሪፋይናንሲንግ (ብድርን፣ በተራዘመ ጊዜ እንዲከፍሉ ማስቻል) የሚባሉ ሁለት መሳሪያወችን ባንኮች ይጠቀማሉ። እኒህን ማግኘት እዳ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይወጣ ይረዳሉ። ሆኖም እኒህ እድሎች ካልተገኙ ዴቢት ስፔሻሊስት የተሰኙ መካሪዎችን ማነጋገር ይቻላል። ተጨማሪ ንባብ በጀት የሚለው ቃል ከይት መጣ የአሜሪካ መንግስት የሸማች ህብረተሰብ ተከላካይ ተቋም በጀት አሰራር ትምህርት ኢንተርኔት ላይ በጀት መስሪያ ሶፍትዌር የአሜሪካ ኑሮ ዘዴ
13701
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%BB%E1%88%8B%E1%89%B8%E1%8B%8D%20%E1%8A%A0%E1%88%B8%E1%8A%93%E1%8D%8A
ቻላቸው አሸናፊ
ቻላቸው አሸናፊ የኢትዮጵያ ታዋቂ ዘፋኝ ሲሆን ብዙ ዘመናዊ የሙዚቃ ስራወችን በማቅረብ ይታወቃል። የህይወት ታሪክ የባህል ሙዚቃ ድምፃዊ ቻላቸው አሸናፊ የተለያዩ የባህል ሙዚቃዎችን በመጫወት ዝነኝነትን ያተረፈው ቻላቸው አሸናፊ የተወለደው በርከት ያሉ ባህላዊ የአዝማሪ ሙዚቃ ተጫዋቾች በፈለቁባት የጎንደሯ ደብረታቦር ከተማ በ1957 ዓ.ም ነበር። የስራ ዝርዝር ነይ መላ የኢትዮጵያ ዘፋኞች
49786
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%8B%B4
ሰዴ
ሰዴ ወረዳ በ ምስራቅ ጎጃም ዞን የሚገኝ ወረዳ ነው። በ2009 አ.ም 16 የደጋ ቀበሌዎችን በመያዝ ከ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ተቀንሶ የተመሰረተ ወረዳ ነው። የወረዳው ከተማ ሰዴ ይባላል። ሰዴ ከተማ ከ ሞጣ ያለው የመስመር ርቀት በ ቀራንዮ መስመር 32 ኪሎሜትር በ ቻክ መድኃኔዓለም በድሮው የእግር መንገድ 16 ኪሎሜትር ነው። ከተማው በቀደሙት ሰዎች ሰዴ ጊዎርጊስ እየተባለ ይጠራል። ይህ አጠራር በከተማው ከሚገኘው ጥንታዊ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዎርጊስ ቤተክርስቲያን ጋር የተያያዘ ነው። ሰዴ እሰከ 1974 በ ሞጣ አውራጃ ስር የ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አስተዳደር መቀመጫ ነበረች። የ ሰዴ ወረዳ በሰሜን የ ሁለት እጁ በምዕራብ ቢቡኝ በደቡብ ደባይ ጥላትግን በምስራቅ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ያዋስኑታል ። በወረዳው ሁለት ባንክ ማለትም መንግስታዊው የ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የግል ባንክ የሆነው አቢሲኒያ ባንክ በ 2011 አ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጡ ነው። በወረዳው ሶስት ጤና ጣቢያዎች ሰዴ ፣ ከርነዋሪ እና ጎይባ አግልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። ሰዴ ከተማ 1992 ዓ.ም የ ውሃ በ 2000 ዓ.ም ደግሞ የመብራት ተጠቃሚ ሆናለች ። አየር ንብረት የ ሰዴ ከተማ ከባህር ወለል በላይ 2550 ሜትር ከፍታ ላይ ትገኛለች። ከተማዋን ሰዴን ጨምሮ አብዛኛው ቀበሌዎች ደጋማ አየር ንብረት አላቸው። የ ሰዴ ከተማ የ ኬክሮስ እና ኬንትሮስ ( ላቲቲዪድ እና ሎንግቲዪድ መገኛው በ ላይ ነው። ሕዝብ ብዛት በ 2011 አም በነበረው መረጃ የወረዳው ህዝብ ብዛት 101763 ነበር። በ1999 አም ማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ባደረገው የ ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ በ ሰዴ ከተማ 2309 ( ሁለት ሺ ሶስት መቶ ዘጠኝ ) ጠቅላላ ሕዝብ ነበረ። ከነኚም መካከል 1296 ወንድ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ ሴቶች ነበሩ። ከ 1999 አም በፊት 1987 አም በተደረገው አገር አቀፍ ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ በ 408 አባዎራዎች ቤት የ ሰዴ ጠቅላላ ሕዝብ 1345 ነበረ። ከእነዚህ 533 ወንድ ሲሆኑ 812 ደግሞ ሴቶች ነበሩ። በዚህ ቆጠራ መሰረት አብዛኛው የ ከተማዋ ሕዝብ 94.6 % ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖት ተከታይ ሲሆን 5.4% ደግሞ ሙስሊም ነበሩ። ሰዴ የ 24 ሰዐት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆነች ጀምሮ የ የከተማዋ ህዝብ ብዛት ጨምሯል ። በተለይ ከተማዋ ራሷን ችላ የወረዳ ማዕከል ከሆነች ጀምሮ የከተማዋ ህዝብ ብዛት በአያሌ ጨምሯል። ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የሰዴ ወረዳ አስተዳዳሪዎች በቅደም ተከተል አቶ አብርሀም አያሌው አቶ መላኩ ከበደ ደመቀ ንጉሴ የኢትዮጵያ ወረዳዎች ስዩም ይዘንጋው ድንቁ () 20:29, 8 ዲሴምበር 2020 (
31391
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%93%E1%88%AD%E1%8C%A6%E1%88%8E%E1%8A%95
ፓርጦሎን
ፓርጦሎን በአየርላንድ ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ ከማየ አይኅ ጥቂት ክፍለ ዘመናት ቀጥሎ መጀመርያው በአይርላንድ ደሴት ላይ የደረሱት ሰፈረኞች መሪ ወይም ንጉሥ ነበር። የፓርጦሎን ስም በታሪክ መጻሕፍት መጀመርያው የሚታወቅ በ820 ዓ.ም. አካባቢ በሮማይስጥ በተጻፈው ሂስቶሪያ ብሪቶኑም («የብሪታንያውያን ታሪክ») ሊገኝ ይችላል። በዚሁ ጽሁፍ መሠረት፣ «ፓርጦሎሙስ» ከ1 ሺህ ሠፈረኞች (ወንዶችና ሴቶች) ጋር ደረሰ፣ እስከ 4 ሺህም ድረስ ቶሎ ተባዙ፣ ነገር ግን ድንገት በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁላቸው ከቸነፈር ሞተዋልና አገሩ እንደገና ባዶ ሆነ። ይኸው መጽሐፍ በአየርላንድኛ ትርጉም ደግሞ ቸነፈሩ በፓርጦሎን ሕዝብ ላይ የመጣበት ጠንቅ ፓርጦሎን ከኗሪ አገሩ ገና ሳይወጣ ወላጆቹን ገድሎአቸው ስለ ነበር የአምላክ ፍርድ ነው በማለት ይጨምራል። ከዚህ በላይ የፓርጦሎን መነሻ አገር እስኩቴስ እንደ ነበር፣ የማጎግ ተወላጅ እንደ ነበር ይታመን ነበር። የስኮት (በስኮትላንድና ቀድሞ በአይርላንድ የተገኘ) ብሔር ስም ከዚህ እስኩቴስ እንደ መጣ በድሮው መጻሕፍት በሰፊው ይጻፍ ነበር። በኋላ የተጻፉ ሌሎች የአይርላንድ ታሪክ መጻሕፍት ስለ ፓርጦሎን ብዙ ዝርዝር ጨምረዋል። በተለይ በ1100 ዓ.ም. ግድም በተጻፈው መጽሐፍ ሌቦር ገባላ ኤረን («የአይርላንድ ወረራዎች መጽሐፍ») ትውልዱ ፓርጦሎን ወልደ ስሩ ወልደ ባንባ ወልደ ማጎግ ይሠጣል። (ይህ ትውልድ ግን በየቅጂው እጅግ ይለያያል።) እርሱና ሦስት ልጆቹ (ላይግሊን፣ ስላንጋና ሩድራይግ) መሪዎች ሆነው 1 ሺህ ሠፈረኞች (ወንዶችና ሴቶች) ወደ አይርላንድ አመጡ። 7 ዓመት ከደረሱ በኋላ መጀመርያው የሞተው ሰው እሱም ፌአ ተብሎ ተቀበረ። 10 አመት ከደረሱ በኋላ የፓርጦሎን ሠራዊት በፎሞራውያን ላይ በማግ ኢጠ ውግያ አሸነፉ። እነዚህ ፎሞራውያን በመሪያቸው ኪቆል ግሪከንቆስ ተመርተው ከውጭ አገር የወረሩ መርከበኞች ነበሩ። ፓርጦሎን በአይርላንድ በደረሰበት ጊዜ 9 ወንዞች፣ 3 ሐይቆችና 1 ሜዳ ብቻ ነበሩ። በእርሱ ዘመን ግን 4 ተጨማሪ ሜዳዎች ተጣሩ፣ ከዚህ በላይ 7 ተጨማሪ ሐይቆች በተአምር ተፈጠሩ። በመጨረሻ ግን ፓርጦሎንና ሕዝቡ በሙሉ - 5 ሺህ ወንዶችና 4 ሺህ ሴቶች - በአንድ ሳምንት ውስጥ በቸነፈር አንድላይ ዓረፉ። (በሌላ ክፍል የጊላ ኮማይን ግጥም ሲጠቅስ ይህ የፓርጦሎን ወገን ከደረሰ 300 አመታት በኋላ ይለዋል።) ደሴቱም ከዚያ ለ30 አመት ባዶ ሆኖ ቀረ። ከዚህ በላይ ስለ ፓርጦሎን መንግሥት ብዙ ተጨማሪ ዝርዝሮች በሌቦር ገባላ ኤረን ይገለጻሉ። በ1620 ዓ.ም. ግድም የተቀነባበረው ምንጭ የአራቱ ሊቃውንት ዜና መዋዕሎች ደግሞ ተመሳሳይ ታሪክ ያቀርባል። አንዳንድ ዝርዝር ለምሳሌ የፎሞራውያን ቁጥር 800 እንደ ነበር ይጨምራል። በዚህ አቆጣጠር ፓርጦሎን 30 አመታት ከነገሠ በኋላ አረፈ፤ ሌሎቹ 9000 ሕዝብ ግን ከዚያ 270 ዓመታት በኋላ በቸነፈር ጠፉ። በ1625 ዓ.ም. አካባቢ የታተመው የሴጥሩን ኬቲን ታሪክ መጽሐፍ የአይርላንድ ታሪክ ደግሞ ስለ ፓርጦሎን ተመሳሳይ አፈ ታሪኮች የሚያቀርብ ነው። በእርሱ መጽሐፍ ፎሞራውያን ከካም ዘር የወጡ መርከበኞች ነበሩ። ከፓርጦሎን ሕዝብ በኋላ የደረሱት ወገኖች የነመድ፣ ፊር ቦልግ፣ ቱዋጣ ዴ ዳናን እና ሚሌሲያን ነገዶች ሁላቸው ከማጎግ ወይም ከጋሜር ዘር እንደ ነበሩ በአይርላንድ ልማዶች ይባላል። ከነዚሁ መጨረሻዎቹ የሚሌሲያን ነገድ የደረሱ ከእስፓንያ መሆኑ ይተረካል። የሚሌሲያንና የፓርጦሎን ታሪኮች ግን ትንሽ እንደ ተደናገሩ ይመስላል። ስለዚህ በብዙ ምንጮች ዘንድ የፓርጦሎን ወገን ከእስኩቴስ ወደ አይርላንድ የደረሰው እንደ ሚሌሲያን በሜድትራኒያን ባሕርና በእስፓንያ በኩል በመጓዝ እንደ ነበር ይጻፋል። ዋቢ መጽሐፍት የአየርላንድ አፈታሪካዊ ነገሥታት
35071
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%86%E1%8A%85%E1%89%B0%20%E1%8B%88%E1%8B%AD
ኆኅተ ወይ
ኆኅተ ወይ የ አመክንዮ ኆኅት አይነት ሲሆን ውጤቱ እውነት እሚሆነው ከሁለቱ ግቤቱ አንዱ ብቻና ብቻ እውነት ሲሆን ነው። በሌላ አነጋገር ሁለቱም ግቤቶቹ አንድ አይነት ከሆኑ ውጤቱ ምንጊዜም ውሸት ነው ማለት ነው። ለምሳሌ ወይ አለሚቱ ዋሽታለች ወይ ማሞ ዋሽቷል። ይህ አረፍተ ነገር እውነት እሚሆነው ከሁለቱ ሰዎች አንዳቸው ብቻና ብቻ ዋሽተው ሲገኙ ነው። ሁለቱም እውነት ተናግረው ከነበር ወይንም ሁለቱም ዋሽተው ከነበር አጠቃላይ አረፍተ ነገሩ ስህተት (ውሸት) ይሆናል ማለት ነው። ይህን ጉዳይ በኤሌክትሪክ ቮልት መስሎ የሚያሰላ የኤሌክትሪክ አካል ኆኅተ ወይ ይባላል። ኆኅተ አመክንዮ
41279
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A1%E1%89%83%E1%89%A2
ኡቃቢ
ዉቃቢ የሚለዉ ቃል አቃቢ ለወንድ አቃቢት ለሴት ከሚል የግእዝ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም "ከልካይ" "ጠባቂ" "ዘብ" ማለት ነው። ይህ ቃል እንደስም ሆኖ በሰዉ ላይ ለሚናገር የቅዱሳን መላእክት መንፈስ ያገለልላል። በኢትዮጵያም የአብዛኛዉ ህዝብ እምነት ሲሆን ከኦሪት የአምልኮ ስርአት ጋር የተያያዘ መልክ አለዉ። በታሪክ ዉርርስ ብቻ የተላለፈ እምነት ነዉ። ከራማ፤ ቃሉ፤ አወልያ፤ ቆሌ፤ የአባት እና የእናት-አምላክ የሚሉ መጠሪያዎችም ተለምዶአዊ ስሞች ናቸዉ። በኢትዮጵያ የባህል እምነት አምልኮ ዉስጥ ወሳኝ የእምነቱ አስፈጻሚ ነው።በተዋቀረ ስርአት የኦሮሞ ህዝብ ዋቄፈና ብሎ ያከብረዋል።
17032
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%99%E1%88%8B%E1%89%B1%20%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%89%B3%E1%8C%A5%E1%89%84
ሙላቱ አስታጥቄ
ሙላቱ አስታጥቄ አንጋፋ ኢትዮጵያዊ ሙዚቀኛ ሲሆን ኢትዮ ጃዝ የተባለውን የሙዚቃ ስልት በመፍጠር የኢትዮጵያን የጃዝ ሙዚቃ ዕድገት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያደረሰ ሰው ነው። ሙላቱ በዚህ ሥራው ከመወደዱና ከመደነቁም ሌላ በዓለም ላይ ብዙ የኢትዮ ጃዝ አፍቃሪዎችን አፍርቷል። በሥራውም የአብራውዝ ግራንት አሸናፊ ሆኗል። የህይወት ታሪክ ሙላቱ አስታጥቄ በጅማ ከተማ በ፲፱፻፴፭ ዓ/ም ተወለደ። የልጅነት ጊዜውን አዲስ አበባ ውስጥ ያሳለፈው ሙላቱ በትምህርቱ ጎበዝ ስለነበረ ቤተሰቦቹ ለትምህርት መሐንዲስነት (ኢንጅነሪንግ) አንዲያጠና ወደ ታላቋ ብሪታኒያ ቢላክም ውስጡ በነበረው የሙዚቃ ፍቅር ተልእኮው የሙዚቃ ሆነ። ብርቅዬው የሙዚቃ ቀማሪ ላለፉት ፵ ዓመታት በ'ጃዝ' ሙዚቃ ውስጥ ኖሯል። ኢትዮጵያን ለዓለም በ'ጃዝ' ያስተዋወቀው ሙላቱ አለማኛ ውስጥ በስሙ መንገድ ተሰይሞለታል፣ በአሜሪካም የበርክሊ የሙዚቃ ኮሌጅ የመጀመሪያው ጥቁር የሙዚቃ ተማሪ ነበር። ሙላቱ በዚሁ ኮሌጅ የአፍሪቃን ትምህርቶች ክፍል አማካሪነት ሹመት አግኝቷል። ሙላቱ አስታጥቄ «ብሮክን ፍላወር» የተባለው ፊልም ላይ ሙዚቃ በመሥራት ትልቅ አድናቆትን አግኝቷል። ይህም ለኢትዮ ጃዝ ሙዚቃ ዕድገትና በዓለም ላይም ትልቅ ደረጃ እንዲያገኝ ረድቶታል። ሙላቱ ለዓለም አቀፋዊ የሙዚቃ እድገት ስላደረገው ታላቅና ጉልኅ አስተዋፅፆ፤ በተጨማሪም በቀድሞ ኮሌጁ ተማሪዎች ላይ ስላሳደረው አርአያነት በቦስቶን የሚገኘው የበርክሊ የሙዚቃ ኮሌጅ ግንቦት ፬ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ሙላቱን የክብር ዶክቶሬት ዲግሪ ሸልሞታል። የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች
16649
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A0%E1%88%BB%E1%88%85%20%E1%89%B0%E1%8A%AD%E1%88%88%E1%88%9B%E1%88%AA%E1%8B%AB%E1%88%9D
በሻህ ተክለማሪያም
በሻህ ተክለማርያም ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ዜማ ደራሲ እና አቀናባሪ እንዲሁም የባህልና የዘመናዊ ሙዚቃን ያደራጁ ቀዳሚ ሰው ነበሩ። ብዙ ዜማዎችን ያቀናበሩ ሲሆኑ ፣ በገናናት የሚታወቁት፣ ሙሽራዬንና ያይኔ ተስፋ የተባሉትን ዜማና ጽሁፍ ያቀረቡ ነበሩ። በኢትዮጵያ ለሚገኙ ቲያትር ቤቶችና የኪነ ጥበብ ተቋማት የተቀናበረ የሀገረሰብ ሙዚቃ የመጀመሪያው ዘር የዘሩ ነበሩ። የህይወት ታሪክ አቶ በሻህ ተክለማርያም ከአባታቸው ከግራዝማች ተክለማርያም አጥናፈ ሰገድ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ የሺወርቅ ወልደ ጻዲቅ መጋቢት ፲፱፻፲፪ ዓ.ም. በባሌ ክፍለ ሀገር በጎባ ከተማ ተወለዱ። በ፬ ዓመት ዕድሜያቸው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የቤተ ክህነት ትምህርታቸውን ጀምረው ሳይጨርሱ በ፰ ዓመት ዕድሜያቸው በዳግማዊ ምኒልክና በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት በመግባት ዘመናዊውን ትምህርት ገብይተዋል። በድምጸ ሸጋነታቸው የሚታወቁት በሻህ ተክለማርያም በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ዘመናዊ የሚዚቃ ትምህርት ሲጀመር ትምህርታቸውን በመከታተል ቫዮሊንና ፒያኖን መጫወት ቻሉ። ጣልያን ኢትዮጵያን ሲወር በሻህ ተክለማርያም ከፍተኛ እሥርና እንግልት ደርሶባቸው ነበር። ከወረራው በኋላም አቶ በሻህ አርቲስቶችን በመመልመል የተለያዩ የኪነ ጥበብ ትርኢቶችን ከማዘጋጀታቸውም ባሻገር ለአገራችን ኪነ ጥበብ መዳበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። በፈረስይ ሐገር ለሙዚቃ ትምህርት ተልከው በቫዬሊን ክላሲካል ሙዚቃ ተመርቀዋል። ማስታወቂያ ሚኒስቴር ድምጽ መቅረጫ /ቴፕ ሪኮርደር/ ባልነበረው ጊዜ የዜማና የውዝዋዜ መሪ በመሆናቸው ተጫዋቾችን ስቱዲዮ ድረስ በመውሰድ በቀጥታ ዘፈኑን ለሕዝብ እንዲተላለፍ ያደረጉ ሲሆን በኋላም ማስታወቂያ ሚኒስቴር ቴፕ ሪኮርደር ሲያመጣ ዘፈኖችን በማሰባሰብ ቀርጸው ለትውልድ እንዲቆዩ ታሪካዊ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻፣ ገጽ 21 የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ሽልማት 1984
53311
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%8A%A9%E1%8A%93
አስኩና
በጉዋጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ከወረዳው ርእሰ ከተማ ከቲሊሊ በስተምስራቅ ይገኛል።አስኩና በተፈጥሮ ፀጋ የተዋበ እና ብዙ አይነት የእፅዋት ዝርያዎች ይገኙበታል።ይህ ቀበሌ ብዙ አመታትን ያስቆጠረ የሰው ልጅ የሰራው ማይመስል ግን በሰው ልጆች ድንቅ ጥበብ ከጭቃ የተሰራ እፁብ ድንቅ የሆነ ቤተ ክርስቲያንን አቅፎ ይዟል።ይህ ቤተ ክርስቲያን በውስጡ ብዙ ቅዱስ መፃህፋትን ይዟል።አስኩና በቆዳ ስፋቱ በጣም ብዙ ስፍራዎችን አጠቃሎ ይዟል።በተጨማሪም በውስጡ ብዙ ወንዞች በጣም ጣፋጭ የሆኑ ምንጮች ይገኛሉ።እንዲሁም ለመድሀኒትነት የሚጠቀሙበት የአምቦ ውሀ ይገኛል።በቀበሌው በጣም ብዙ የሆኑ ምርቶች ይበቅላሉ።በጣም በስፋት ከሚመረቱ ምርቶች ሰፊውን ስፍራ የሚይዘው የድንች ምርት ነው፣የድንች ምርት በአመት ሁለት ጊዜ ይመረታል፣ሰው ሁሌም አመት እስከ አመት ከድንች ተለይቶ አያውቅም።ከዚህ በተጨማሪም ጤፍ፣ስንዴ፣በቆሎ፣ገብስ፣ባቄላ እና አተር በስፋት ይመረታል።አስኩና ለኑሮ አመቺ በጣም አሪፍ አካባቢ ነው።በውስጡ ብዙ እፅዋቶችም ይገኛሉ።ከነዚህም መካከል ቀርከሃ፣ሾላ፣ቀጋ፣ውልክፋ፣አሽኩዋር፣እንጆሪ፣ኮርች፤ሆማ፣ቁልቋል፣ግራር፣ባህርዛፍ፣ስሚዛ፣ግራዋ፣ጨባ፣እና ሌሎች በርካታ እፅዋት ይገኙበታል።
3954
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%20%E1%8B%A8%E1%88%85%E1%8B%9D%E1%89%A5%20%E1%89%A5%E1%8B%9B%E1%89%B5
የዓለም የህዝብ ብዛት
የዓለም የህዝብ ብዛት በመሬታችን ላይ ያለውን የሰው ልጆች ቁጥር ይተምናል። በ1998 መጀመሪያ ላይ 6.5 ቢሊዮን እንደደረሰ ይገመታል። ከነዚህ ትምናዎች በመነሳት የዓለም ሕዝብ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን በፊት ታይቶ በማይታውቅ ፍጥነት ማደጉን እንደቀጠለ ይታያል። በአንዳንድ ግምቶች፣ እስከ አንድ ቢሊዮን ያህል እድሜያቸው ከአስራ አምስት እስክ ሃያ አራት የሚሆን ወጣቶች እንደሚገኙ ይታመናል። ከቅርብ ጊዜ በሗላ አሁን የምንኖርባት መሬት ልትጠፋ ስለምትችል የሰዉ ልጆችን ወደማርስ ለመላክ ሳይንቲስቶች በጥናት ላይ ናቸው:: የሰው ልጅ ጥናት
43009
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%8D%E1%8B%A9%20%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AD%E1%89%B5
ልዩ ትምህርት
የልዩ ፍላጎት ትምህርት ማለት ከመደበኛው ትምህርት በተለየ ሁኔታ የልዩ ትምህርት ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች እንደ እውቀታቸው መጠንና እንደ አስፈላጊነቱ በተለየ መልኩ ተዘጋጅቶ የሚሰጥ የትምህርት አይነት ነው። ልዩ ፍላጎት ትምህርት ራሱን በቻለ በልዩ ትምህርት ቤት ወይም በመደበኛ ትምህርት ቤት ውስጥ በሚገኙ የልዩ ፍላጎት ትምህርት መስጫ ክፍሎች ውስጥ ወይም በመደበኛ ትምህርት ቤት በመደበኛ ክፍሎች ውስጥ በልዩ ፍላጎት ትምህርት መምህር የሚሰጥ የትምህርት አይነት ነው።
43947
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A82003%20%E1%8B%93.%E1%88%9D.%20%E1%8D%89%E1%8A%A9%E1%88%BA%E1%88%9B%20%E1%8A%A0%E1%8B%B0%E1%8C%8B%20%E1%8B%8D%E1%8C%A4%E1%89%B5
የ2003 ዓ.ም. ፉኩሺማ አደጋ ውጤት
በመጋቢት ፪ 2003 ዓ.ም. አንድ የምድር መንቀጥቀጥ ጃፓንን መታ። ይህ ጹናሚ (ታላቅ ማዕበል) ፈጠረና ጹናሚው የፉኩሺማ ኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ጉዳትና አደጋ ሠራ። ከዚህ የተነሣ ብዙ የኒውክሌር ጨረራ እስካሁን እየወጣ ነው። ጨረራው እስካሁን በጃፓን ብዙ መቶ ሺህ ሰዎች ከቤቶቻቸው አሳድዷል። በፓሲፊክ ውቅያኖስ በሰፊ ክልል ምንም ዓሣ ወይንም የባሕር ሕይወት የለም። የተገኘውም ዓሣ ቢበላ በጨረራው ይበከላልና ለጤና መጥፎ ነው። ጨረራው በውኃ እስከ ካሊፎርኒያ ድረስ አሁን እየደረሰ ነው። የጨረራው ውጤት ለማከላከል በቴሮድም ላይ የኑክሌር ጨረራ መጥፎ ውጤት ለማከም፣ ሰዎች ፖታሼም አዮዲድ (የአዮዲንና የፖታሼም ውሑድ) ይጠቀማሉ። ኒውክሌር አደጋዎች
51009
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%89%A2%E1%88%8E%E1%8A%95%20%E1%89%A0%E1%88%B3%E1%88%8E%E1%8A%95
ባቢሎን በሳሎን
ባቢሎን በሳሎን ከታህሳስ 17፣ 2002 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ተአትር ለዕይታ የበቃ የኮመዲ ዘውግ ያለው የውድነህ ክፍሌ ድርሰት ሲሆን አዘጋጁ ደግሞ ተስፋዬ ገብረሐና ናቸው። በሕዝቡ ጥያቄ መሠረት በድጋሚ ወደ መድረክ መጋቢት 18 ቀን 2011 ዓ.ም ተመልሶም ነበር። ውብሸት እና ትዝታ አብሮ መኖርም ሆነ መለያየት ያልሆነላቸው ባልና ሚስት ናቸው። አንዱ የሌላውን እልህ ለማስወጣት ተግቶ እንቅልፍ ያጣል። በግድግዳ በከፈሉት ሳሌናቸው ውስጥ ተፈላጊነታቸውን እና ተደማጭነታቸውን ለማወጅ የቅናት የእልህ ጦር ይመዛሉ። ለማየሁ ታደሰ ሉሌ አሻጋሬ እመቤት ወልደገብርኤል (ራሄል ተሾመ) ህንፀተ ታደሰ እንድሪስ አህመድ ስናፍቅሽ ተስፋዬ ፍቃዱ ከበደ ዳንኤል ተገኝ የኢትዮጵያ ትያትር ድራማዎች
11738
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%AD%E1%88%8A%E1%88%89%20%E1%88%80%E1%89%A5%E1%89%B0-%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B5
አክሊሉ ሀብተ-ወልድ
ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሰው ሲሆኑ በ ጣልያን ወረራ ጊዜ አምስቱን ዓመት ሙሉ በፓሪስ የኢትዮጵያ ጉዳይ ፈጻሚ፤ በዠኔቭ በዓለም መንግሥታት ማኅበር የኢትዮጵያ ዋና ጸሐፊ ከድል በኋላም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት እና እስከ አብዮት ፍንዳታ ድረስም በዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስቴር ነበሩ። ከአብዮቱ ፍንዳታ በኋላ አቃቂ ታስረው ከቆዩ በኋላ ያለፍርድ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ከስልሳ ሰዎች ጋር በደርግ ተረሽነው ሞቱ። የተማሪነት ዘመናት አክሊሉ መጋቢት ፭ ቀን ፲፱፻፬ ዓ/ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቡልጋ ከተወለዱት አለቃ ሀብተወልድ ካብትነህ እና ከወይዘሮ ያደግድጉ ፍልፈሉ ተወልደው የአማርኛ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው የራጉኤል ቤተ ክርስቲያን አጠናቀቁ። ከዚያም በዳግማዊ ምኒልክ ትምሕርት ቤት ለሦስት ዓመታት ዘመናዊ ትምሕርት ከተከታተሉ በኋላ በ፲፱፻፲፯ ዓ/ም ወደ እስክንድርያ ትምሕርታቸውን እዚያ በሚገኘው የፈረንሳይ “ሊሴ” ትምህርት ቤት እንዲቀጥሉ በአልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መኮንን ተላኩ። እስክንድርያም እስከ ፲፱፻፳፫ ዓ/ም ከተማሩ በኋላ የሊሴ ትምሕርታቸውን አጠናቀው ለከፍተኛ ትምሕርት ወደ ፓሪስ እና ታዋቂው ሶርቦን ዩኒቨርሲቲ አምርተው የከፍተኛ የንግድ ሕግ እና ሽከታኪን () ትምሕርት ጀመሩ። ሶርቦን እስከ ፲፱፻፳፰ ዓ/ም ድረስ ተምረው የመጀመሪያ ሲማክቶ ጉላፕ በሸከታኪን እንዲሁም የ ሲማሕግ ጉላፕ () ተመርቀው ወጡ። ወዲያው ፋሽሽት ኢጣልያ ሀገራችንን ይወርና ወጣቱ አክሊሉ ሀብተወልድ ለውድ አገራቸው ነጻነት የአርበኝነት ትግላቸውን በቶፍካ () እና በገቢ ሰብሳቢነት እዚያው ፈረንሳይ አገር ተሰማሩ። በዓለም መንግሥታት ማኅበር የኢትዮጵያ ዋና ፀሐፊ በጦርነቱ ዋዜማ ኢትዮጵያ በዓለም መንግሥታት ማኅበር ሸንጎ ጣልያን በግፍ ልትወራት መነሳቷን እና በማኅበሩ ‘የጋራ ደህንነት’ ዋስትና () መሠረት አባላት አገሮች መሃል ገብተው ጣልያንን እንዲያስታግሱ በምትከረከርበት ጊዜ አክሊሉ በፈረንሳይ አገር ውስጥ ተማሪ ሆነው ሳሉ ለሀገራቸው የሚያደርጉትን ትግል በመመልከት ንጉሠ ነገሥቱ፤ በዠኔቭ የኢትዮጵያ ልዑካን መሪ ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም ሥር ዋና ፀሐፊ አደረጓቸው። ፊታውራሪው ያንጊዜ በፈረንሳይ፣ በብሪታንያ እና በዠኔቭ የኢትዮጵያ ዋና ልዑክ ነበሩ። ጦርነቱ በይፋ ከመጀመሩ በፊት ወደዠኔቭ እየሄዱ በኢትዮጵያ ስም ከጣልያን ጋር በዓለም መንግሥታት ማኅበር ሸንጎ ይሟገቱ የነበሩት እነዚህ ሁለቱ ስዎች ነበሩ። ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ወደአገራቸው ሲመለሱና ብላቴንጌታ ወልደ ማርያም በፓሪስ የኢትዮጵያ አምባሳዶር ሲሆኑ አክሊሉ የ”ፕሬስ አታሼ” ሆነው እንዲሠሩ ንጉሠ ነገሥቱ ቢያዟቸውም አምባሳደሩ “እምቢ ብለው አላስገባም አሉኝ። ቢሆንም እውጭ ሆቴል ቁጭ ብዬ እንደፕሬስ አታሼ ሆኜ ሥሠራ ነበር።” ( መስከረም ፲ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ለደርግ የምርመራ ኮሚሽን ‘ዓለም በቃኝ’ እስር ቤት ሆነው በላኩት የታሪክ ማስተወሻተው) የሚሉን አክሊሉ ሀብተወልድ በዚሁ ሥራ አፈ ቀላጤ () ሆነው ለጋዜጠኞች ማብራሪያ እና ቃለ ምልልስ በመስጠት የኢትዮጵያን አቋም እና የተሰነዘረባትን ግፈኛ ድርጊት ማስተዋወቃቸውን ቀጠሉ። ለመሆኑ ብላቴንጌታ ወልደ ማርያም ለምን ይሆን አክሊሉን አላስገባም ያሉት። ምናልባት ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ - ሁለተኛ መጽሐፍ” በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “በፓሪስ የኛ ሚኒስቴር የነበረው ብላቴንጌታ ወልደማርያም አየለ እኛን ከድቶ ለጣልያኖች በገባ ጊዜ በዓለም መንግሥታት ማኅበር የኢትዮጵያ ጸሐፊ አቶ አክሊሉ ሀብተወልድ በፓሪስ የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ጉዳይ አስፈጻሚ ሆኖ አገልግሎናል።” ብለው ያሠፈሩት ምክንያቱን ይጠቁም ይሆናል። በወቅቱ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበረው ፒዬር ላቫል እና የብሪታንያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሳሙኤል ሆር በ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፳፯ ዓ/ም በምስጢር ዶልተው አዘጋጅተውት የነበረውን፤ ኢትዮጵያን የሚበልጠውን አገር (ሐረርን፣ ሲዳሞን፣ ባሌን) ለጣልያን ሰጥታ ጎጃምን፣ ጎንደርን እና ትግሬን አስቀርታ ተጣልያን ጋር እንድትታረቅ የሚደነግገውን የ”ሆር-ላቫል” ስምምነት የሚባለውን ለጃንሆይ መስጠታቸው ሲሰማ አክሊሉ ሀብተወልድ ማዳም ታቡዴስ ለምትባለው የ”ራዲካል ፓርቲ” ጋዜጣ ኃላፊ ለነበረችው ታዋቂ ጋዜጠኛ በምስጢር ይገልጹላትና እሷ ሎንዶን ላይ በጋዜጣና በራዲዮ ይፋ አደረገችው። ጉዳዩ በብሪታንያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትልቅ ውዝግብና ሙግት ተደርጎበት ሆርም ምክር ቤቱን ይቅርታ እንዲጠይቅና ስምምነቱም እንዲወድቅ አድርጎታል። የጠላት ዘመን በሚያዝያ ወር ፲፱፻፳፰ ዓ/ም መደምደሚያ የፈረንሳይ የሕግ አውጪዎች ምክር ቤት አባላት ምርጫ በሚካሄድበት ጊዜ ወጣቱ አክሊሉ ለሦስቱ ዋና ፓርቲዎች የወቅቱ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስቴር የነበሩት ፒዬር ላቫል ሙሶሊኒን ለማስደሰት ሲል ኢትዮጵያን በመሸጥ “የጋራ ደህንነት” () የተባለውን የዓለም ጸጥታው ምክር ቤትን ዓላማ ማድከሙን፤ የኢትዮጵያ አቤቱታ እንዳይታይ እያደረገ እንደነ ሙሶሊኒና ሂትለርን እንዳበራታ ፣ በዚህም የዓለም ጦርነትን እንዲፋጠን ማድረጉን በዝርዝር ማስረዳትና ለፓርቲዎቹም የላቫልን መንግሥት ለመገልበጥ መሣሪያ መስጠት ለኢትዮጵያ ታላቅ ጥቅም እንደሚሰጥ በመገንዘብ በነዚህ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብሰባ እየተገኙ የኢትዮጵያን እሮሮ ማሰማት ጀመሩ። የፈረንሳይም ጋዜጦች እነኚህን ስብሰባዎች በሚዘግቡ ጊዜ የአክሊሉ ሀብተወልድን ንግግርም ጨምረው ሲያትሙ ሀገራቸው የደረሰባትን የግፍ ወረራ ለመላው የፈረንሳይ ሕዝብ ሲያስተዋውቁ ቆዩ። አዲስ የተመረጠውን የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሊዮን ብሎምን አነጋግረው ፈረንሳይ የሙሶሊኒ ፋሽሽት ኢጣልያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ያላትን ይዞታ መቼም ቢሆን እንደማያውቅ አረጋግጦላቸዋል። ወዲያው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በስደት ወደብሪታንያ ሲመጡ አክሊሉም በዚያው በፓሪስ የኢትዮጵያ ጉዳይ ፈጻሚ ሆነው ሲያገለግሉ ቆዩ። መስከረም ፲ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ለደርግ የምርመራ ኮሚሽን ‘ዓለም በቃኝ’ እስር ቤት ሆነው በላኩት የታሪክ ማስተወሻተው እንደነገሩን፤ “በ፲፱፻፴ ዓ/ም የእንግሊዝ ንጉሥና ንግሥት በግብዣ ለጉብኝት ፓሪስ በመጡ ጊዜ ተሌሎች አምባሳደሮች ጋር እኔም ተጠርቼ ሄጄ ነበር። በፕሮቶኮሉ ደንብ የኢትዮጵያና የጣልያን ጉዳይ ፈጻሚዎች አቀማመጣቸው ጎን ለጎን ስለነበር አጠገቡ በምሆንበት ጊዜያት ጣልያኑ በጣም ሲቆጣ እኔም ኃይለኛ ቃል ስለተናገርኩት ጠቡን ሁሉም ሰምተው የፕሮቶኮሉ ሹም በመካከላችን የሌላ አገር ጉዳይ ፈጻሚ አስቀመጠ።” ይላሉ በወቅቱ ጣልያኖች በኢትዮጵያ ላይ “ኋላቀር፤ ባርያ ሻጭ፤ አውሬዎች…. የኛ ተልዕኮ ኢትዮጵያን ማሰልጠን ነው….” እያሉ ፕሮፓጋዳቸውን ያዛምቱ ስለነበር የፈረንሳይ ሕዝብ ስሜቱን ለኛ ስሞታውን ወደነሱ አዙሮ ነበር። ይሄንን በዘለቄታማና ስኬታማ መንገድ ለመከላከል አክሊሉ (ሀ) ከልዩ ልዩ ጋዜጮች ጋር በመገናኘት እውነቱን በማስረዳት (ለ) ተነ ሙሴ ጃንጉል (በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሥር የፈረንሳይኛ ጋዜጣ ያቋቋመ) እና ከሌሎች ፈረንሳዮች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን የሚረዱ ሁለት ኮሚቴዎች ( እና ) በማቋቋምና በነዚህ ኮሚቴዎች በኩል የኢትዮጵያን ጉዳይ በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ፈረንሳዮች በማሰራጨት የሕዝብ ዕርዳታ ለማስገኘት ችለዋል። (ሐ) በነዚሁ ኮሚቴዎች ዕርዳታና መሥራችነት የኢትዮጵያን አቋምና የጣልያንን ግፍ በየጊዜው የሚያስረዳ “ኑቬል ደ ኤትዮፒ” (የኢትዮጵያ ዜና) የሚባል ጋዜጣ ተመሠርቶ እሳቸውም በየጊዜው በጋዜጣው ይጽፉ ነበር። ከድል በኋላ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሲያከትም የተሸናፊዎቹን የጀርመንን እና የጣልያንን ይዞታ፤ የካሳ ጉዳይ እና በድል ጊዜ ከጣልያን ወደ እንግሊዝ አስተዳደር ተላልፈው የነበሩትን የኤርትራን እና የኦጋዴንን ጉዳይ ለመወሰን በየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መሪነት “የሰላም ጉባዔ” በሚካሄድበት ጊዜ አቶ አክሊሉ ሀብተወልድ መጀመሪያ በፓሪሱ ጉባዔ በታዛቢነት በመጨረሻም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት አዲሱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በተመሠረተበት በሳን ፍራንሲስኮ ከተማ የኢትዮጵያን ልዑካን በመምራት ተሳትፈዋል። አክሊሉ ሀብተወልድን ትልቅ የዲፕሎማሲ ሰው መሆናቸውንና በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረኮች ለኢትዮጵያ ብዙ መታገላቸውን የሚያስመሰክርላቸው ዘመን የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ካከተመበት ጊዜ ጀምሮ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ በኅብረታዊ መንግሥት የመዋሐድ ጉዳይ እስከተፈረመበት ኅዳር ወር ፲፱፻፵፪ ዓ/ም ድረስ የነበረው ዘመን ነው። አክሊሉ በእንግሊዝና በኢጣሊያ ተሸንሽና የነበርቸውን አገራቸውን ረጅም ዓመት የፈጀ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በማድረግ አንድ ያደረጉ ታላቅ ዲፕሎማት እንደነበሩ ስለሳቸው ብዙም የተጻፈ መረጃ ማግኘት ቢያስቸግርም በአምባሳደር ዘውዴ ረታ የተጻፈው ‘የኤርትራ ጉዳይ’ የተባለው መጽሐፍ ስለኚህ ሰው ታላቅ ተጋድሎ በሰፊው ተዘርዝሮ ይገኛል :: አምባሳዶር ዘውዴ የኤርትራን ጉዳይ በተመለከተው በዓለም መድረክ ላይ ይካሄድ ስለነበረው ትግል ሲጽፉ ፤ በዚያን ጊዜ በአካባቢ ቡድን ብዛት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኃይል የነበራቸው የላቲን አሜሪካ አገሮች የጣልያን ወገን በመሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩን አክሊሉ ሀብተወልድን እጅግ በጣም ቢያናድዷቸው የተከተለውን ትንቢታዊ ንግግር ከማኅበሩ መድረክ ላይ አደርጉ፦ «በዚህ አጋጣሚ ለባልደረቦቼ የላቲን አሜሪካ አገሮች ተወካዮች፣ በተለይም ለአርጀንቲናው ልዑክ እጅግ በጣም ከባድ ፋይዳ ስላለው ጉዳይ የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ። ዛሬ አገሬ ከግብጽ እና ከላይቤሪያ ጋር ሆና እናንተ ከጣልያን ጋር በማደም የአፍሪቃን ሕዝቦች ለመጨቆን የምትጫወቱትን ሚና በጥንቃቄ እየተመለከትን ነው። በቅርብ ጊዜ ውስጥ ግን እዚህ ያለነው ሦስት አፍሪቃውያን አገሮች በአስር እጥፍ በዝተን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ ተገቢ መቀመጫችንን እንይዛለን። ያን ጊዜ እኛ እንደናንተ ሳይሆን፣ ለዓለም ሰላም ድጋፍ እና ፍትሐዊ ፍርድ ድምጻችንን እንደምናሰማ ጥርጣሬ የለኝም።» ሲሉ ስሜታዊ ንግግራቸውን አሰምተዋል። እውነትም ይሄንን በተናገሩ በአሥር ዐመታት ውስጥ አፍሪቃውያን አገሮች በማኅበሩ ውስጥ ትልቁ አኅጉራዊ ቡድን ለመሆን በቁ። ረዥሙ የስደት ዘመን ተጠናቀቀ በ፲፱፻፲፯ ዓ/ም መጀመሪያ ለትምሕርት ከአገራቸው፣ ከትምሕርታቸውም በኋላ በጣልያን የግፍ ወረራ ምክንያት አምስቱን ዓመታት አውሮፓ ቆይተው በተቻላቸውና በተሰጣቸውም መመሪያ ስለአገራቸው ሲታገሉ የኖሩት አክሊሉ፤ ከጠላትም ድል መደረግ በኋላ የሳቸው ዲፕሎማሲያዊ የትግል ሥራ እስከሚገባደድ ድረስ በድካም፤ በጭንቀት እና በህመምም ለብዙ ዓመታት በፓሪስ እና ኒው ዮርክ የኖሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከጥቂት የሥራ ጋደኞቻቸው ጋር በ፲፱፻፵፬ ዓ/ም ወደናፈቋት አገራቸው ተመለሱ። የኤርትራን ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስፈጽመው የተመለሱትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአገራቸው ሕዝብ በተለይም ኤርትራውያን በጣም ሞቅ ባለ ሁኔታ ተቀበሏቸው። ቀደም ብሎ ንጉሠ ነገሥቱ፣ እቴጌ መነን፣ ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ፣ አቶ ይልማ ደሬሳ እና የወለጋ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ የነበሩት ደጃዝማች መኮንን ደስታ የደስታ ቴሌግራም ተልኮላቸው ነበር። ሆኖም ንጉሠ ነገሥቱ መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፵፭ ዓ/ም የኤርትራን ከኢትዮጵያ ጋር በኅብረት መንግሥት መዋሐድ አስመልክተው ባደረጉት ንግግር አንዳንድ ኤርትራውያንን በስም ጠርተው ሲያመሰግኑ፤ ለዚህ ውጤት እጅግ ከፍ ያለ ትግል ያካሄዱትንና ታላቅ ዲፕሎማሲያዊ መስዋዕትነትን ላበረከቱት አክሊሉ ሀብተወልድ ግን በሕዝብ ፊት ምስጋና ያለማቅረባቸው ያሳዝናል። በሚያዝያ ወር ፲፱፻፵፯ ዓ/ም የአክሊሉ ዋና ደጋፊ የነበሩት እና እስከዚያ ጊዜ ድረስ በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ትልቅ ሥልጣን እና በንጉሠ ነገሥቱም ታማኝነትና ተሰሚነት የነበራቸው ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ፣ ትክክለኛ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከዚህ ቁልፍ ቦታ ተነስተው መጀመሪያ የአሩሲ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ ቀጥሎም የጋሙ ጎፋ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳድሪ ተደርጉ። አምባሳዶር ዘውዴ ረታ በመጽሐፋቸው ስለዚህ ጉዳይ ሲያወሱ፣ የኤርትራ ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሚካሄድበት ጊዜ አክሊሉ ሀብተወልድ የብሪታንያን የኤርትራ አቋም ነቅፈው በመዝለፋቸው የንጉሠ ነገሥቱ የግል ፀሐፊ የነበሩት እና የብሪታንያ ደጋፊ የሚባሉት አቶ ተፈራ ወርቅ (በኋላ ፀሐፊ ትዕዛዝ) ‘የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ አክሊሉ ለብሪታንያ ይቅርታ ይጠይቅ ሲሉ ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ግን ያደረገው አግባብ ነው ይቅርታ መጠየቅ የለበትም በሚል ጉዳይ ተከራክረዋል ሲሉን የፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ከሥልጣን መወገድ ምክንያት ዕውን ይሄ ይሆን ወይ? ሊያስብለን ይችላል። ባህሩ ዘውዴ ደግሞ በተባለው መጽሐፉ ላይ የፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ከሥልጣን መወገድ ዋና ምክኛት የነበሩት የግል ምስጢራዊ የስለላ ድር የዳበሩት እና በዚህም የሚያገኙትን መረጃዎች ለንጉሠ ነገሥቱ በማካፈል ይወደዱ የነበሩት የአክሊሉ ታላቅ ወንድም መኮንን ሀብተወልድ ናቸው ይለናል። እንዴት የፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ የመውደቅ ምክንያት እንደሆኑ ባያብራራልንም ምናልባት በዚሁ የምስጢራዊ ስለላ ድራቸው ‘ትልቅ ምስጢር አግኝተውባቸው ይሆን? ለማለት ያበቃናል። ትክክለኛ ምክንያቱ ይህም ይሁን ያ፣ የፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ መወገድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን አቶ አክሊሉን ግን ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር የሚያቀራርበውን በፀሀፊ ትዕዛዝ ማዕረግ የፅህፈት ሚኒስቴርና እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርነትን አፍርቶላቸዋል። የታኅሣሥ ግርግር በክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ ጄነራል መንግሥቱ ንዋይ እና በታናሽ ወንድማቸው አቶ ገርማሜ ንዋይ የተጸነሰሰውና ታኅሣሥ ፬ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ተጀምሮ ዓርብ ታኅሣሥ ፯ ቀን አሥራ አምስት መኳንንት፣ ሚኒስቴሮች እና የጦር መኮንኖች መረሸን ያከተመው የታኅሣሥ ግርግር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ፣ ለፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ በታላቅ ወንድማቸው አቶ መኮንን ሀብተወልድ መገደል ትልቅ የግል ሀዘን ላይ ቢጥላቸውም፤ በጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስቴርነት የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት ይመሩ የነበሩት የራስ አበበ አረጋይ በአመጸኞቹ እጅ መገደል ለሳቸው የጠላይ ሚኒስቴርነቱን ማዕርግ እና ሥልጣን አስገኝቶላቸዋል። በጠቅላይ ሚኒስቴርነት እና በፅሕፈት ሚኒስቴርነት በጥምር ሲያገለግሉ ዘመናዊውንና ጥንታዊውን ሥልጣናት በጃቸው በማግባት ለንጉሠ ነገሥቱ ቀርበው በተሰሚነት አብዮቱ እስከፈነዳ ድረስ ሠሩ። የአብዮት ፍንዳታ በ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የተቀጣጠለው አብዮታዊ ሽብር በተማሪዎች ሰልፍ፣ የወታደሮች እንቅስቃሴ እንዲሁም የዓለምን ዱኛ () ያናጋው የነዳጅ ማዕቀብ ሲለኮሱ የደርግ ሥልጣንም እየጎለመሰ መጣ። ወታደሮቹም መኮንኖችን ብቻ ሳይሆን የ መንግሥት ባለሥልጣናትንም ጭምር የማሠር ስልጣን እንደሚኖራቸው ንጉሠ ነገሥቱን አሳመኑ። በየካቲት ወር ጠቅላይ ሚኒስቴሩ አክሊሉ ሀብተወልድ ከነ ሚኒስቴሮቻቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ። ‘ተንፏቃቂው አብዮት’ ወዲያው ተተክተው የተሾሙትንም አዲስ ጠቅላይ ሚኒስቴር ልጅ እንዳልካቸው መኮንንም ከሥልጣን አውርዶ ከነ አክሊሉ ሀብተወልድ ጋር ከርቸሌ ከከተተ በኋላ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ባለቤቱን እራሳቸውን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ከሥልጣን አወረደ። ፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ከንጉሠ ነገሥቱ አዝማድ እና ቤተሰቦች፤ መሳፍንት እና መኳንንት፤ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ መኮንኖች ጋር በእስራት ከቆዩ በኋላ ያለክስም ያለፍርድ በኅዳር ወር ፲፱፻፷፯ ዓ/ም በተወለዱ በ ስድሳ ሦስት ዓመታቸው ከስልሳ ሰዎች ጋር ተረሽነው ሞቱ። የአክሊሉ ሀብተወልድ ጥቅሶች "… "የደረሰው ይድረስ ደካማ ሆኜ መታየት አልፈልግም :: የሀገሬን ጥቅምና መብት የሚነካ መስሎ ከታየኝ መናገሬን አልተውም ::" "…ሀገሬ ኢትዮጵያ በዓለም ሸንጎ ላይ ፍርድ ተነፍጓት ስታዝን የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም።…..ኢትዮጵያ ያለፉት ታሪኮቿ በትክክል እንዳስረዱት፤ለነፃነቷና ለመንቷ፤በኮሎኒያሊስቶች ጣሊአን ጋር በየጊዜዉ ስተዋጋ፤ያሸነፈችዉ ብቻዋን ነዉ። የተጠቃቺዉም ብቻዋን ስለሆነ፤አገሬ መቸዉንም ለሚደርስባት አደጋ ከማንም እርዳታ አገኛለሁ ብላ አትጠብቅም።ዛሬም ሆነ ነፃነቷን ለመጠበቅ፤ታሪኳን ለማስከበር አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረግ ያለባት፤እሷ ራሷ ብቻ ነች።…" “በዚህ አጋጣሚ ለባልደረቦቼ የላቲን አሜሪካ አገሮች ተወካዮች፣ በተለይም ለአርጀንቲናው ልዑክ እጅግ በጣም ከባድ ፋይዳ ስላለው ጉዳይ የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ። ዛሬ አገሬ ከግብጽ እና ከላይቤሪያ ጋር ሆና እናንተ ከጣልያን ጋር በማደም የአፍሪቃን ሕዝቦች ለመጨቆን የምትጫወቱትን ሚና በጥንቃቄ እየተመለከትን ነው። በቅርብ ጊዜ ውስጥ ግን እዚህ ያለነው ሦስት አፍሪቃውያን አገሮች በአስር እጥፍ በዝተን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ ተገቢ መቀመጫችንን እንይዛለን። ያን ጊዜ እኛ እንደናንተ ሳይሆን፣ ለዓለም ሰላም ድጋፍ እና ፍትሐዊ ፍርድ ድምጻችንን እንደምናሰማ ጥርጣሬ የለኝም።” ዋቢ ምንጮች ጦብያ መጽሔት ፪ኛ ዓመት ቁጥር ፮ መስከረም ፲፱፻፹፮ ዓ/ም የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
53081
https://am.wikipedia.org/wiki/Ethiopia%20national%20football%20team
Ethiopia national football team
የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ፣ በቅፅል ስሙ ዋሊያ ፣ ከዋልያ በኋላ፣ በወንዶች ዓለም አቀፍ እግር ኳስ ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክል ሲሆን የሚቆጣጠረው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የበላይ አካል ነው። ቡድኑ ከተመሰረተ ከ1943 ጀምሮ ኢትዮጵያን በመወከል በአህጉራዊ፣ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ሲሳተፍ ቆይቷል። ዋሊያዎቹ የሜዳቸውን ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደርጋሉ። ከዓለም 150ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ እና በ . በ 1957 በተጀመረው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ከተሳተፉት ሶስት ቡድኖች ( ከግብፅ እና ሱዳን ጋር) ኢትዮጵያ አንዷ ነበረች። ውድድሩን በ 1962 አሸንፏል, አስተናጋጁም ነበር. ይሁን እንጂ ስኬት ከ 1960 ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በጣም አስቸጋሪ ነበር. በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው መሪነት ቡድኑ ከ31 አመታት ቆይታ በኋላ ለ 2013 የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ፣ በቅፅል ስሙ ዋሊያ ፣ ከዋልያ በኋላ፣ በወንዶች ዓለም አቀፍ እግር ኳስ ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክል ሲሆን የሚቆጣጠረው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የበላይ አካል ነው። ቡድኑ ከተመሰረተ ከ1943 ጀምሮ ኢትዮጵያን በመወከል በአህጉራዊ፣ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ሲሳተፍ ቆይቷል። ዋሊያዎቹ የሜዳቸውን ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደርጋሉ። ከዓለም 150ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ እና በ . በ 1957 በተጀመረው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ከተሳተፉት ሶስት ቡድኖች ( ከግብፅ እና ሱዳን ጋር) ኢትዮጵያ አንዷ ነበረች። ውድድሩን በ 1962 አሸንፏል, አስተናጋጁም ነበር. ይሁን እንጂ ስኬት ከ 1960 ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በጣም አስቸጋሪ ነበር. በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው መሪነት ቡድኑ ከ31 አመታት ቆይታ በኋላ ለ 2013 የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን፣ በቅፅል ስሙ ዋሊያ ፣ ከዋልያ በኋላ፣ በወንዶች ዓለም አቀፍ እግር ኳስ ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክል ሲሆን የሚቆጣጠረው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የበላይ አካል ነው። ቡድኑ ከተመሰረተ ከ1943 ጀምሮ ኢትዮጵያን በመወከል በአህጉራዊ፣ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ሲሳተፍ ቆይቷል። ዋሊያዎቹ የሜዳቸውን ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደርጋሉ። ከዓለም 150ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ እና በ . በ 1957 በተጀመረው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ከተሳተፉት ሶስት ቡድኖች ( ከግብፅ እና ሱዳን ጋር) ኢትዮጵያ አንዷ ነበረች። ውድድሩን በ 1962 አሸንፏል, አስተናጋጁም ነበር. ይሁን እንጂ ስኬት ከ 1960 ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በጣም አስቸጋሪ ነበር. በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው መሪነት ቡድኑ ከ31 አመታት ቆይታ በኋላ ለ 2013 የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል።
15307
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%88%9C%E1%8A%95%20%E1%89%B0%E1%88%AB%E1%88%AB
ሰሜን ተራራ
የ ስሜን ተራራ በሰሜን ጎንደር የሚገኝ የተራሮች ሰንሰለት ሲሆን ከኢትዮጵያ ከፍተኛው ተራራ ራስ ዳሸን በዚሁ ሰንሰለት መካከል ይገኛል። ይህ የተራራ ሰንሰለት ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ እንስሳቶችን (እንደ ዋልያ፣ ቀይ ቀበሮ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ፣ ወዘተ...) የመሳስሉ ዝርያዎችን አቅፎ ይዟል። የጥንቱ ግሪክ ጸሐፊ በድርሰቶቹ ውስጥ የግሪኮቹ አማልዕክት በረዶ በበዛበት የኢትዮጵያ ተራሮች እረፍታቸውን እንደሚያሳልፉ መዝግቧል። በአንድ አንድ ተመራማሪወች ዘንድ ይህ ተራራ የስሜን ተራሮች ሰንሰለት ነው ተብሎ ይታመናል። የኢትዮጵያ ተራሮች
13177
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%B3%E1%8B%B5%E1%88%AB%E1%89%B2%E1%8A%AD
ኳድራቲክ
ኳድራቲክ ተብሎ የሚታወቀው የሂሳብ እኩልዮሽ ይህን ይመስላል፦ ተለዋዋጭ ዋጋን ሲወክል ደግሞ ቋሚ ዋጋን ይወክላል። በነገራችን ላይ ≠ 0 አለዚያ = 0 ከሆነ ስሌቱ ሊኒያር እኩልዮሽ ወይም ቀጠተኛ እኩልዮሽ ይሆናል ማለት ነው። እኩልዮሹን እውነት ለማድረግ ተለዋዋጭ ዋጋው በሚከተለው አይነት ሊሰላ ይገባል፡ - ከቋሚ ዋጋወቹ በዚህ መንገድ ሁለቱን መልሶች ካገኘን በኋላ እኩልዮሹን ፈታን ወይንም መልሱ አገኘን ብለን እንናገራለን ማለት ነው።
18791
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%88%AA%E1%8B%8D%20%E1%8C%86%E1%8A%95%E1%88%B0%E1%8A%95
አንድሪው ጆንሰን
አንድሪው ጆንሰን (እንግሊዝኛ: ) የአሜሪካ አስራ ሰባተኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕረዝዳንቱ ሥልጣን ላይ የወጡት እ.አ.አ. በ1865 ሲሆን በስልጣን ዘመናቸው ምክትል ፕሬዝዳንት አልሾሙም ነበር። ፕሬዝዳንቱ በመጀመሪያ የዴሞክራቲክ ናሽናል ዩኒዬን ፓርቲ በኋላ የናሽናል ዩኒዬን ፓርቲ በመጨረሻ ከምንም ፓርቲ ውጭ የነበሩ ሲሆን ከሥልጣን የወረዱት እ.አ.አ. በ1869 ነበር። አስራ አምስተኛ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች ዝርዝር የአሜሪካ መሪዎች
15927
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%85%E1%88%8D%E1%8B%8D%E1%8A%90%E1%89%B5
ኅልውነት
አብዛኞች ሃይማኖቶችና ፍልስፍናወች የሰው ልጅ ኅይወት ትርጉም (አላማ) አለው ብለው ያምናሉ። ስለሆነም ይህን አላማ ወይም ለማስፈጸም ወይም ደግሞ ለማግኘት ሲጥሩ ይታያሉ። ከዚህ በተጻራሪ በኅልውነት ፍልስፍና የሰው ልጅ ህይወት ከመፈጠሩ (ኅልው ከመሆኑ) በፊት የተጻፈ ትርጉምም ሆነ አላማ የለውም። ስለሆነም የፍልስፍና አትኩሮት መሆን ያለበት «እያንዳንዱ ግለሰብ ለህይወቱ እንዴት ትርጉምና አላማ መስጠት አለበት?» የሚል ነው። የኅልውነት ፍልስፍና አባት ነው የሚባለው ሶረን ኬርከጋርድ እንዳስቀመጠው «እያንዳንዱ ግለሰብ ለህይወቱ ትርጉም የመስጠት እንዲሁም ይህን ህይወቱን በሃቀኝነትና በሙሉ ስሜት የመምራት ኃላፊነት አለበት።» ይህ ሲሆን ታዲያ ተስፋ መቁረጥ፣ የኅልውና ድንጋጤ፣ ባይተዋርነት፣ ድብርትና መሰረተ ቢስነት የተባሉ የኅልውና ቀውሶች የሰውን ልጅ ይጋረጣሉ፣ እኒህን እንቅፋቶችን የማሸነፍ ዘዴ መቀየስ የኅልውነት ፍልስፍና አይነተኛ አትኩሮት ነው። የሰው ልጅ ህይወት ትርጉም የለሽና አላማውም የማይታወቅ ሲሆን ትርጉም አለው እምንለው እያንዳንዱ ግለሰብ ለህይወቱ በራሱ እጅ ትርጉም (አላማ) እስከሰጠው ድረስ ብቻ ነው። በሌላ አባባል ኅልውና ከምንነት ቀዳሚ እንጂ ተከታይ አይደለም። ይሄ የኅልውነት ፍልስፍና ዋና ቁልፍ ሃሳብ ነው፣ ትርጉሙም እንዲህ ነው፡ አንድ ግለሰብ ከመፈጠሩ (ኅልው ከመሆኑ) በፊት "ምንነቱ" አልተጻፈም ስለዚህ የግለሰቡ "ምንነት" ኅልው ከሆነ በኋላ በሚያደርጋቸው የኑሮ ምርጫወች ይፈጥራል፦ እያንዳንዱ ግለሰብ በንቃተ ህሊናው የራሱን ዋጋና የራሱን የህይወት ትርጉም ይጽፋል። በዚህ ተቃራኒ አንድ ህንጻ ቢገነባ ህንጻው ለምን ግልጋሎት እንደሚጠቅም ከወደፊት ተጠንቶ ነው። ስለዚህም ህንጻው ኅልው ከመሆኑ በፊት "ምንነት" አለው እንላለን። አላማው/ግልጋሎቱ/ምንነቱ ከኅልውነቱ ቀደመ። እንዲሁ አንድ ቢላዋ ከመሰራቱ በፊት ለመክተፍ እንደሚያገለግል፣ ይህም የመኖሩ (ኅልውናው ) ዋና አላማ መሆኑ ይታወቃል። በኅልውነት ፍልስፍና የሰው ልጅ እንደዚያ አይደለም። የሰው ልጅ፣ ጀርመን አገርም ሆነ ሱዳን፣ ፊሊፒንስም ሆነ አሜሪካ፣ ከመፈጠሩ በፊት የህይወቱ "ምንነት" አይታወቅም። ከተፈጠረ በኋላ በሚያደርገው ምርጫወች ምንነቱ ይታወቃል። ከመፈጠሩ በፊት "ምንነቱ" አለመታወቁ የሰው ልጅ ለሰራው ስራ ሁሉ ሙሉ ነጻነት እንዲኖረው ያደርጋል፣ ስለዚህም ለያንዳንዱ ድርጊቱ ሙሉ ተጠያቂነት ይኖረዋል። ይህ ጉዳይ የኅልውና ድንጋጤ በያንዳንዱ ግለሰብ ላይ ይፈጥራል። ለምሳሌ አንድ ሰው ከገደል ጫፍ ላይ ቢቆም ሁለት ድንጋጤወች ይጋፈጡታል፣ አንደኛው «ወድቄ ብከሰከስስ» የሚል ሲሆን ሁለተኛውና ለምንነጋገርበት ርዕስ ጠቃሚ የሆነው ደግሞ «ምናልባት እራሴን ብወረውርስ» የሚል ፍርሃቻ ናቸው ። በዚህ አጣብቂኝ ግለሰቡ "ምንም የሚይዘኝ ነገር የለም" ወይም ደግም "በተፈጥሮየ እራሴን እንዳልወረውር የሚጠብቀኝ እንዲሁ በተቃራኒው እራሴን እንድወረወር የሚገፋፋኝ እድል እጣ ፈንታ የለኝም፣ ሁለቱም እራሴ በማደርገው ምርጫ የሚወሰን ነው" የሚለውን መሰረታዊ የሰው ልጅ ነጻነት ይረዳል። ይህ የመመረጥ ሙሉ ነጻነትና የሚያስከተለው ሙሉ ሃላፊነት በሰው ልጅ ላይ ድንጋጤን ይፈጥራል። የኅልውና ድንጋጤ እንደሌሎች የፍራቻ አይነቶች ሳይሆን አብሮ ከሰው ልጅ ሙሉ የመምረጥ ነጻነት ጋር ምንጊዜም የሚገኝ ነው። ኅልውነት በ19ኛውና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በተነሱ የአውሮጳ (ፈረንጅ) ፈላስፎች የተጠና የፍልስፍና አይነት ነው። ለዚህ የፍልስፍና አይነት ከፍተኛ አስተዋጾ ካደረጉ ውስጥ ዶስቶቭስኪ፣ ኒሺ፣ ዦን-ፖል ሳርት፣ ኬርከጋርድ፣ ካሙ ይገኙበታል። መደብ :ፍልስፍና
31374
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8C%E1%88%AD%E1%8C%89%E1%88%B5%20%E1%8B%B1%E1%89%A5%E1%8B%B4%E1%89%B3%E1%89%85
ፌርጉስ ዱብዴታቅ
ፌርጉስ ዱብዴታቅ ከ240 እስከ 241 አም ድረስ የአየርላንድ ከፍተኛ ንጉሥ ነበር። በአይርላንድ ታሪኮች ዘንድ ቀዳሚው ሉጋይድ ማክ ኮን ከተገደለ በኋላ፣ ለአንድ አመት ከፍተኛ ንጉሥነቱን ያዘ፤ ከዚያ ኮርማክ ማክ አይርት ፈርጉስን በውግያ ገደለውና ከፍተኛ ንጉሥ ሆነ። የቲገርናቅ ዜና መዋዕል (1080 ዓም ተቀነባብሮ) የፈርገስ ዘመን በ239 እንደ ጀመረ ቢለንም፣ ሉጋይድ ግን ከ210 ጀመሮ ለ፴ ዓመታት እንደ ገዛ ይላል። በዚህ አቆጣጠር የፈርገስ ዓመት 240-241 ዓም መሆን አለበት። የአየርላንድ አፈታሪካዊ ነገሥታት
48772
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B8%E1%8A%AE%E1%88%8B%E1%89%B3
ቸኮላታ
ቸኮላታ ከካካዎ ዛፍ () ዘሮች ውጥ (ካካው) የተሠራ ጣፋጭ ከረሜላ አይነት ነው። ብዙ ስኳር ሳይጨመር ግን የቸኮላታ ጻዕም መራራ ነው። ቸኮላታ መጠጥ እና የካካዎ ዛፍ ከጥንት ጀምሮ በሜክሲኮ ታውቀዋል፤ ስያሜውም «ቸኮላታ» እና በአለሙ ልሳናት የተዛመዱት ቃላት ሁላቸው ከናዋትል ስም «ሾኮላትል» ደርሰዋል። የተቀደሠ መጠጥ እንደ ሆነ ይቆጥሩትም ነበር። ከ1520 ዓም በኋላ የካካው ዘር ወደ አውሮፓ ገብቶ፣ እዛም በጣም ተወደደ። ዛሬ በመላው አለም አብዛኛው ካካው በምዕራብ አፍሪካ ይመረታል። ቸኮላታ ግን ለለማዳ እንስሶች በተለይም ለድመት፣ ለውሻ፣ ለከብት ጤና የሚጎዳ ወይም የሚገድል መርዝ ነው።
38158
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%8A%AB%E1%88%AE%E1%88%B5
ኢካሮስ
ኢካሮስ እንደ ጥንቱ ግሪክ አፈ ታሪክ የታላቁ እጅ ጥበበኛ የ ዴድለስ ልጅ ነበር። ስለ ኢካሮስ ከተነገሩ ዋና ታሪኮች አንዱ ይኖሩበት የነበረውን ደሴት በረው እንዲያመልጡ፣ ዴደለስ ለልጁና ለራሱ ከሰምና ከወፎች ላባ አራት ክንፎች እንደሰራና ክንፎቻቸውን እየለበሱ እያለ ዳዲለስ ልጁን ኢካሮስን እንዲህ ብሎ እንዳስጠነቀቀው ነበር፦ «ወደ ፀሐይዋም ሆነ ወደ ባሕሩ እንዳትጠጋ፣ ይልቁኑ የኔን የበረራ መስመር ተከተል።» አባትና ልጅ ክንፋቸውን እያራገቡ መብረር ሲጀምሩ ኢካሮስ ልቡ እንደሸፈተና በኋላም መሬትን እየለቀቁ ወደ አየሩ ሲቀዝፉ ኢካሮስ በደስታ እራሱን መቆጣጠር እንዳቃትው ታሪኩ ያትታል። የአባቱን ምክር ረስቶ፣ ወደ ሰማይ፣ ወደ ላይ ፀሐይን ተጠግቶ በመብረሩም ክንፉን አጣብቆ የያዝው ሰም በመቅለጡ ኢካሮስ ወደ ባሕሩ ወደቆ እንደተከሰከሰ አፈታሪኩ ያትታል። ይህ ባሕር እስከ አሁን ዘመን የኢካሮስ ባሕር ወይንም ኢካርያ ይባላል። አንድ አንድ ታሪክ አጥኘወች የዚህን አፈታሪክ መልዕት ሰዎች ከመጠን ያለፈ የገንዘብ፣ የስልጣልን፣ የመታዎቅ ወዘተ...ፍላጎት ባደረባቸው ጊዜ ውድቀታቸውም በዚያው ልክ ይፋጠናል እሚል ነው። የግሪክ አፈታሪክ
44362
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%8B%E1%89%A5%E1%88%AB%E1%8B%B6%E1%88%AD
ላብራዶር
ላብራዶር ሪትሪቨር ተብለው የሚታወቁት ውሻዎች ላብራዶር እንዲሁም ላብ በሚሉትም ስሞች ይጠራሉ። እነኝህ ውሻዎች ሪትሪቨር (የታደኑ እንስሳትን ወደ አዳኙ የሚያመጡ) ከሚባለዉ ዝርያ ውስጥ የሚካተቱ ናቸው። በባህሪያቸው የተለሳለሱ ሲሆኑ ከህጻናት እና ከአዛውንቶች ጋራ በጥሩ ሁነታ ይግባባሉ። ላብራዶሮች ስፖርት ወዳድና ተጫዋች ሲሆኑ በብዙ የውሻ ባለቤቶች ዘንድ ተመራጭ ናቸው። በብዙ ሃገሮች የእርዳታ ዉሻን ሚና ይሚጫወቱት እነዚህ ውሻዎች በተለይም አይነ-ስውራንን እና ከኦቲዝም ጋራ የሚኖሩ ሰዎችን እንዲሁም የህግ አስከባሪ ባለሙያዎችን እንዲያግዙ ማሰልጠን ይቻላል። ሰውነታቸው ከትላልቆች ተርታ የሚመደበው እነዚህ ውሻዎች በብዛት ክብደታቸው ለወንዶች ከ29-36ኪግ ለሴቶች ድግሞ ከ25-32ኪግ ድረስ ይመዝናል። ለላብራዶሮች ተቀባይ ተብለው የተመዘገቡት ቀለሞች ጥቁር፥ ቢጫ (ከሽሮ እስከ ቀላ ያለ ቀበሮ) እና ቡናማ ግራጫ (ከመካከለኛ እስከ ጥቁር ቡኒ) ናቸው። ለማዳ እንስሶች
47214
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A6%E1%8C%A6
ኦጦ
ማርኩስ ሳልዊዩስ ኦጦ ለአጭር ዘመን ለ፫ ወር ከጥር ወር 61 ዓም ጀምሮ የሮሜ መንግሥት ቄሣር ነበር። የአራቱ ቄሣሮች ዓመት ሁለተኛው ንጉሥ ነበረ። ኦጦ በ24 ዓም በጣልያን ተወለደ። በሮሜ ግቢ፣ ነጉሥ ኔሮን እንደ ጎበዝ ወጣት ቆጠረው። ኔሮን ግን ሚስቱን ከቃመ በኋላ ኦጦን ወደ ሉሲታኒያ (ፖርቱጋል) እንደ አገረ ገዥ ላከው። የጋሊያ ሉግዱኔንሲስ (ፈረንሳይ) እና የሂስፓኒያ ታራኮኔንሲስ (ስፔን) ክፍላገራት አገረ ገዦች በአመጽ ሲነሡ ኦጦም ከጸረ-ኔሮን ወገን ጋራ ተባበረ። ኔሮን ራሱን ከገደለ በኋላ የሂስፓኒያ አገረ ገዥ ጋልባ ቄሣር ሆነ። በጥር ወር 61 ዓም የጌርማኒያ ሥራዊት በጋልባ ላይ አመጹበትና የጌርማኒያ አገረ ገዥ ዊቴሊዩስ ንጉሥ እንዲሆን አዋጁ። ጋልባ በሮሜ ቆይቶ አልጋ ወራሹ ሉኪዩስ ካልፒኒዩስ ፒሶ እንዲሆን ሰየመው። በዚህ ኦጦ በተለይ ተናደደ፣ አልጋ ወራሽነቱን ለራሱ መኝቶ ነበርና። የሮሜ ሥራዊት ደግሞ ኦጦን ደገፈውና በጋልባ ላይ አመጹ። ጋልባ በድካምነቱ በቃሬዛ ተሸክሞ ሲቀርብላቸው ገደሉትና ያንጊዜ ኦጦ ለአጭር ወራት በፈንታው የሮሜ ቄሣር ሆነ። መልኩ ለኔሮን ተመሳሳይነት ስለነበረው በሮሜ ዜጎች መኃል እንደ አዲሱ ኔሮን ተወደደ። የኔሮንም ሰዶማዊ «ባል» ስፖሩስ ለራሱ «አገባ»። ከዚያ ኦጦ የጋልባን ሰነዶች አንብቦ የዊቴሊዩስ ሥራዊት ከጌርማኒያ ቶሎ እንደሚደርስ ተረዳ። የዊቴሊዩስ ወገን ወደ ጣልያን ገብቶ አሸንፎም ኦጦ ብሔራዊ ጦርነት እንዳይስፋፋ እንደ ኔሮን ራሱን እንደ ገደለ ይባላል። ስለዚህ በፈንታው ዊቴሊዩስ በሚያዝያ የሮሜ ቄሣር ሆነ። የሮሜ ሰዎች
18332
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%98%E1%8B%8B%E1%88%AA%20%E1%88%B0%E1%8A%95%E1%88%B0%E1%88%88%E1%89%B5
ዘዋሪ ሰንሰለት
ዘዋሪ ሰንሰለት የሰንስለት አይነት ሲሆን ብቃቱ እስከ 98% የሚደርስ ሃይል አስተላላፊ ማሽን ነው። ጥቅሙም ለመኪና፣ ለሞተርሳይክል፣ ለአመላላሾች፣ ለማተሚያ መሳሪያወች፣ ወዘተ.. ውስጣዊ ሃይል አመላላሽነት ነው። ይህን ማሽን ሃንስ ሬኖልድ በ1880 ፈጠረው ይባል እንጂ በ16ኛው ክፍለዘመን ይኖር የነበረው ሊዮናርዶ ዳቪንቺ የዚህን አይነት መሳሪያ ትልም እንደሳለ እስከማስረጃው አሁን ድረስ ይገኛል። መደብ :ማሽን
51110
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8A%A4%E1%88%8D
ኢትኤል
አባታችን አዳም በዕለተ አርብ በነግህ ከተፈጠረ በኋላ እናታችን ሔዋን በሳምንቱ አርብ በዘመናችን አነጋገር 3 ሰዓት ላይ ከግራ ጎኑ ተፈጠረች። በገነትም 7 ዓመት ከ3 ወር ከ 17 ዕለታት ካሳለፉ በኋላ ሕግን ተላልፈው እፀ በለስን በመብላታቸው ከገነት ተባረሩ። በዚህ ግዜ አምላካችን እግዚአብሔር ለአዳም የተስፋ ቃል ሰጠው፤ እርሱም ከልጅ ልጅህ ተወልጀ ከ5 ቀን ከመንፈቅ በኋላ አድንሃለሁ የሚል ቃል ነበረ። ይህ የተስፋ ቃልና ከመላእክት ለአዳም የተሰጡትን ስጦታዎች አዳምና የልጅ ልጆቹ ሲቀባበሉት ቆይቶ ከካሕኑ መልከጼዴቅ እጅ ላይ ደረሰ። ከመልከጼዴቅ አንዳንዶቹ ለአብርሃም ተሰጠ ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ለኢት-ኤል ተሰጠ ይላሉ። 🔰መልከጼዴቅም ኢት-ኤልን እንዲህ አለው፦ “ ይህን የዕንቁ እንክብል ውሰድ፤ ሄደህም በአባይ ወንዝ መነሻ ኑሮህን መስርት። እንክብሉ በርሃብና በመከራ ወቅት ይጠቁራል፤ በጥጋብና በመልካም ወቅቶች ደግሞ ያበራል፤ ኢትዮጵያውያን የሚሆኑ ትውልዶችህ ይህን ዕንቁ ተንከባክበው እንዲጠብቁ እዘዛቸው። የሰላሙ ንጉሥ መወለዱንም አንድ ብሩህ ኮከብ ከሰማይ ያመላክታቸዋል፤ ጨረሮቹም ንጉሡ ወደ ሚወለድበት አቅጣጫ ይፈነጥቃሉ። በተወለደበት ቦታ ላይ ሲደርሱ ኮከቡ ንቅናቄውን ያቆማል። ነግሥታቱ ልጆችህም በዚያ ለንጉሡ ‘አንተ የዘላለም አምላክ ነህ’ ብለው ይስገዱለት። ልዩ የሆነውንም የኢትዮጵያ ‘ዮጵ’ የተባለውን ቢጫ ወርቅ፤ እንዲሁም ዕንጣንና ከርቤ ለሰላሙ ንጉሥ ገጸ-በረከት ያቅርቡለት። ” 🔰ከዚህ በኋላ ደሸት(ዘረ ደሸት) 1400-1600 ቅ.ል.ክ ላይ በጣና ዳር ሆኖ ሲጸልይና ከዋክብትን ሲመራመር ድንግል ከነልጅዋ በራእይ ተመለከተ፤ እርሱንም በወርቅና በብር ሰሌዳ ላይ ጽፎ ለትውልድ አስተላለፈ። ከነሸምሸልና ከነ ቀራሚድ በኋላ ደሸት ጣና አከባቢ ጎጃም ውስጥ ደሸት በተባለ ስፍራ ላይ ይኖር ነበረ። ሰብአ ሰገሎች ማን ናቸው ? ( ስለ ሰብአ ሰገሎች ከማብራራታችን በፊት የስማቸውን አንድምታ ማወቅ ይኖርብናል። #ሰብእ ማለት በግእዝ ቋንቋ #ሰው ማለት ሲሆን #ሰገል ማለት ደግሞ #ጥበብ ፈላስፋ እንደማለት ነው። በእንግሊዘኛው ሐዲስ ኪዳን ‘’ ይላቸዋል፤ በብዙ ቁጥር ሲሆን ደግሞ ‘’ ይላቸዋል። እነዚህ ነገሥታት በሥነ-ከዋክብት እውቀት ላይ የተራቀቁ እንደነበሩ ሁሉም ተመራማሪዎች ይስማሙበታል። በቀደምቱ ዓለም ደግሞ ሥነ-ጠፈር፥ ሥነ-ከዋክብትንና ሥነ ሕክምናን ከዓለም አስቀድማ ያጠናችና ጥበቡን ያስተላለፈች ቅድስት ምድር ኢትዮጵያ እንደነበረች ብዙዎች ይስማማሉ። 🔰ተመራማሪው ሉስያን “ ” በማለት ኢትዮጵያ በሥነ ከዋክብትና በተለያዩ ዘርፎች ገናና ጥበብ ከነበራቸውን ሀገራት ውስጥ ተጠቃሽ ናት። 🔰መምሕር መስፍን ሰሎሞን “7 ቁጥር” በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “ ባቢሎን፥ ግሪክ፥ ሕንድ፥ ኢትዮጵያ፥ ሮም፥ ቻይናና ፋርስ በቀደመው ዓለም 7 የሥነ-ጠፈር አጥኚ ሀገራት ናቸው” በማለት አስፍረዋል። ነገር ግን ስለ ሰብአ ሰገል መነሻ ስፍራ አንድ ወጥ የሆነ አስተሳሰብ የለም፤ ትልቅ ጥናት የሚያስፈልገው የታሪክ ክስተት ነው። አንዳንዶቹ በፋርስ ከነበረ “” ማኅበረሰብ የመጡ ናቸው ይላሉ፤ ይሄም “” የሚለው ስያሜ የመጣበት ማኅበረሰብ እንደሆነ ይገመታል። አንዳንዶቹ የፋርስ ሰዎች ናቸው በማለት ዘረ-ደሸት የተባለ ሰው በፋርስ ይኖር ነበረ ይላሉ፤ ይህ ግን በጣም አስቂኝ ነገር ነው ዘረ-ደሸትን ከዞሮአስተር ጋር እያየያዙት ነው። በሀገራችን ደሸት የተባለ ቦታ አሁን ድረስ ጣና አከባቢ ይገኛል። ታዲያ ይህንን ታሪክ ከኢትዮጵያ በማውጣት ለሌላ ዓለም እየሰጡ ነው፤ ልክ የትሮይ ጦርነትን ኢትዮጵያውያን ተዋግተው ታሪኩ ግን ለግሪክ እንደተሰጠው የታሪክ መዛባትና ስርቆት ማለት ነው። 🔰ታላቁ የቤተ-ክርስቲያናችን ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ ሰብአ ስገል 3 ሲሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነበሩ ብለው “የኢትዮጵያ እምነት በ፫ቱ ሕግጋት” በተባለው መጽሐፋቸው ላይ አስፍረው አልፈዋል። በርካታ የታሪክ ተመራማሪዎች ቁጥራቸው 3 ናቸው በማለት ስማቸውን እንዲህ በማለት ይዘረዝራሉ። ሜልኩ[ሜልኪዮር]- የፐርሽያ ንጉሥ ፥ ማንቱሲማር[ጋስፓር]- የሕንድ ንጉሥና በዲዳስፋ የኢትዮጵያ ንጉሥ በሚለው ስያሜ በርካታ ተመራማሪዎች ይስማማሉ። ተመራማሪዎቹ ሰብአ ሰገል 3 ናቸው ያሉበት ዋና ምክንያት ወርቅ፥ ዕጣንና ከርቤን በመገበራቸው ነው። 🔰ከምዕራባውያን ተመራማሪዎች ውስጥ ዊልያም ሊዮ ሀንስበሪና ኢሀርፐር ጆንሰን “” በተባለው ጽሁፋቸው ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ናቸው ቁጥራቸውም 3 ናቸው ይላሉ። አንዳንድ ተመራማሪዎች 3 ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ 12 ናቸው እያሉ የየራሳቸውን ማስረጃዎች ያቀርባሉ። ☑️ሰብአ ሰገል ኢትዮጵያዊ ለመሆናቸው ማስረጃዎች ( ሰብአ ሰገሎች ኢትዮጵያዊ ናቸው ከሚሉት ውስጥ አለቃ አያሌው ታምሩ፥ አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ፥ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ፥ መሪ ራስ አማን በላይ እንዲሁም ከላይ የተጠቀሱት ዊልያም ሊዮ ሀንስበሪና ኢሀርፐር ጆንሰን ተጠቃሽ ናቸው። እኒህ መረጃ አድርገው የሚያቀርቧቸው ማስረጃዎች ውስጥ ትንቢተ ኢሳያስ 60፥ 6 ላይ ያለው ቃል ዋነኛው ነው፤ ነገሥታቱ የሳባ ነገሥታት ናቸው ብቻ ስለሚል ነገሥታቱ የሳባ ነገሥታት ናቸው ማለት እኒህ ነገሥታት የተነሱት ከኢትዮጵያ ነው ማለት ነው። እንዲሁም መዝ. 71፥ 9-10 ላይ “በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፤ ጠላቶቹም አፈር ይልሳሉ” በሚለው ቃል ላይ “ኢትዮጵያ” ብሏልና እነዚህ ሰብአ ሰገል ኢትዮጵያዊ ናቸው ብለው ማስረጃ ያቀርባሉ። ከላይ የተጠቀሰው የደሸት ታሪክም አንዱ ማስረጃ ሲሆን ዋናው ማስረጃ ደግሞ ኢትዮጵያ ከዓለም ብቸኛዋ ወርሃ ተኅሣሥን ከሰብአ ሰገል ጋር አያይዛ የሰየመች መሆኑ ነው። ታኅሣሥ ትርጉሙ የማሰስ የመፈለግ ወር ማለት ነውና። ስለ ሰብአ ሰገል በመጽሐፍ ቅዱስ በማቴ. 2 ላይ የተነገረ ሲሆን ከምሥራቅ መጡ ይላል እንጂ ስማቸውን አይዘረዝርም። ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳና መሪ ራስ አማን በላይ በሰብአ ሰገል ዙሪያ ተመሳሳይ አመለካከቶች ሲኖራቸው ሰብአ ሰገል 12 ናቸው የተነሱትም ከኢትዮጵያ ነው ይላሉ። 🔰የእያንዳንዱን ነገሥታት ስምም በመጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ብለው አስፍረዋል። 1- የጎንጂ ንጉሥ አጎጃ ጃቦን ዮጵ ወርቅ ይዞ ተነሣ 2- አቦል 3- ቶና 4- በረካን 3ቱ የአጎጃ ጃቦን ወንድም የዳጋ ነገሥታት ነበሩ። 5- የሱዳንና የአረብ ንጉሥ መሊ አቡሰላም 6- የሰገልና የማጂ ንጉሥ መጋል 7- የኤውላጥ[ኦጋዴን]ና የሶማሊያ ንጉሥ መቃዲሽ ከርቤ ይዞ ተነሣ 8- የአዳል ንጉሥ አውርና 9- የአፋር ንጉሥ ሙርኖ ዕጣን ይዘው። 10- የአዘቦ ንጉሥ አጋቦን 11- የኑባው ንጉሥ ሀጃቦንና 12- በሳባ ከተማ በሃማሴን ይቀመጥ የነበረው አርስጣ ናቸው። ሰብአ ሰገል 12 መሆናቸው ከ12ቱ ሐዋርያት ጋር የተያያዘ መለኮታዊ ምስጢር አለው በማለት 2ቱ ተመራማሪውች የኢትዮጵያ ትንሣኤ ታሪክና ስውሩና ያልተነገረው የኢትዮጵያውያንና የአይሁዳውያን ታሪክ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ አስፍረዋል።አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ በመጽሐፋቸው ላይ ሰብአ ሰገል 3 ነገሥታትና 2 ልዑላን ናቸው በማለት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ናቸው ይሉንና እኒህ ነገሥታት ኢትዮጵያዊ ናቸው፤ ቀለማቸው ግን ነጭ ሊኖር ይችላል። ያ ኢትዮጵያዊነታቸውን አይፍቅም። ኢትዮጵያዊ ከአንድ እናትና አባት 4 አይነት ቀለም ያላቸው የተለያዩ አበባ የመሰሉ ልጆችን ይወልዳሉና ይላሉ በጥናታቸው ላይ። 🔰አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ የነገሥታቱን ስምና የትውልድ ቦታ እንዲህ በማለት ያብራሩታል። 1- ናሁ አዳም(ከወንድሙ ጋር) ተነሳ ከኢትዮጵያ 2- ራይናስ(ከወንድሙ ጋር) ከምሥር 3- አሕራም ከየመን ኮከቡን ያዩት በነገሡ በ13ኛው ዕለት ሲሆን የጉዞው መሪ ከ3ቱ ኢትዮጵያውያን ውስጥ እስከ መካከለኛው ምሥራቅ ይገዛ የነበረው ናሁ አዳም ነው ይላሉ። ~ በአጠቃላይ በሰብአ ሰገል ማንነት ላይ ሁሉም ተመራማሪዎች ቢያንስ ከ3 ወይንም ከ12 አንዱ ኢትዮጵያዊ ነው በማለት ይስማማሉ። 🔰ከላይ የጠቀስናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ የትንቢተ ኢሳያስና የመዝሙረ ዳዊት አገላለጾችና አንድምታዎች በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሥነ-ጠፈር ምርምር የተራቀቀች መሆኗ ሰብአ ሰገል ኢትዮጵያዊ ናቸው ወደሚለው ጥናት ይወስደናል። በዚያም ሆነ በዚህ ሰብአ ሰገል ውስጥ አንዱ ወይንም ከዚያ በላይ የሆኑት ኢትዮጵያዊ ናቸው የሚለው ሃሳብ ሁሉንም ተመራማሪዎች ያስታርቃል። ☑️ሰብአ ሰገል የተመለከቱት ኮከብ ምን አይ ከጠዋቱ ፀሐይ እንደወጣች ልክ ሦስት ጫማ በዘመናችን አነጋገር ከጠዋቱ 3 ሰዓት እንደሆነ ጂራቱ 13 ክንድ የሚያህል 7 ሕብረ ቀለማት ያለው በጣም የሚያምር ጂራታም ኮከብ ከምሥራቅ በኩል ወጥቶ በኢትዮጵያና በዓለም ላይ አበራ፤ ይህንን ኮከብ የሚያዩት ለማየት ከአምላካችን #ሥላሴ የተፈቀደላቸው ብቻ ናቸው። ይላሉ አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ። 🔰በተመሳሳይ የታኅሣሡ ስንክሳር “ልውጥ ኮከብ” ይለዋል፤ ይህም የሚቀያየር የሚሰወር ኮከብ ለማለት ሲሆን አንድም ሕብረ ቀለሙን ለመግለጽም ነው። ሰብአ ሰገል በመሃል ከተማ በሚገቡበት ጊዜ ኮከቡ ይሰወራቸው ነበር ይላል። ኮከቡ አንዴ ሕጻን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን አንዴ ደግሞ ራስ፥ እጅና እግር ያለውን ሰው ይመስል ነበረ። ይህ ኮከብ የታየው ክርስቶስ ከመወለዱ ከ2 ዓመታት በፊት ነበረ፤ ይሄም ቀድሞ በቅድስት ሥላሴ ፈቃድ የተከናወነ ጎዞ መሆኑን ያመለክተናል። ምክንያቱም ከ2 ዓመት በኋላ በቤተልሔም ስለሚደርሱ ነው። 🔰ስለ ኮከቡ ምንነት በቤተክርስቲያን አስተምሕሮ መሰረት ሁሉም አንድ ወጥ ሃሳብ አላቸው፤ ‘ኮከቡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ነው’ የሚል። ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን ኮከብ በቀን አይታይምና ኮከብ ዝቅ ብሎ እነርሱ ባሉበት ደረጃ አይጓዝም የሚል ነው። ኮከብ የተባለው በምስጢራዊ አነጋገር ነው ይላሉ መተርጉማነ መጻሕፍት። ☑️የሰብአ ሰገል ጉዞ[ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም] ( ሰብአ ሰገል ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም የሄዱት ስዊዝ ካናል ከመከፈቱ በፊት መንገድ ነበረ በዚያ ነው። ከቦታው ለመድረስም 2 ዓመት ፈጅቶባቸዋል። በትርክቶች መሰረት ሲነሱ 12 ነገሥታት ሲሆኑ ኢየሩሳሌም ግን የደረሱት 3ቱ ናቸው ይባላል፤ ምክንያቱም ስንቅ ስላለቀባቸውና ጦር ስለ ተነሳባቸው ነው ይላሉ። ይህ ግን በኢትዮጵያ መዛግብት ዘንድ ተቀባይነት የለውም። ሰብአ ሰገል ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ከተማዋ ተሸበረች እነ ሄሮድስ ደነበሩ፤ ለወረራ የመጡ መስሏቸው ነበረና ኢትዮጵያውያን ሮማውያንን ከጥንት ጀምሮ አይቀጡ ቅጣት ይቀጧቸው ነበረና። እነርሱም ለንጉሡ ልንሰግድለትና ሥጦታ ልንሰጥ መጣን ሲሉ ሄሮድስ ተደሰተ ለርሱ መስሎት ነበረና፤ ለርሱ አለመሆኑን ሲረዳ ግን ተበሳጨ ከእኔ ውጭ የይሁዳ ንጉሥ አለ እንዴ በሚል ተናደደ። እነርሱንም ንጉሡን ስታገኙት ንገሩኝ እኔም መጥቼ እንድሰግድለት አላቸው። 🔰ሰብአ ሰገል ከበረቱ በደረሱ ጊዜ ኮከቧ ቆመች[ ከላይ መልከጼዴቅ ያለውን ይመልከቱ] ወደ ውስጥም ገብተው ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስና ለእናቱ ለድንግል ማርያም ሰግደው ዮጵ ወርቅ፥ ዕጣን፥ ከርቤ፥ ቅባት፥ አክሊል፥ ዘውድ፥ በትረ መንግሥት፥ በትረ መስቀልና ሽቶ ሥጦታ አበረከቱ። ☑️ሰብአ ሰገል ከዚህ ሁሉ በኋላ አስቀድሞ የአምላክን ሰው መሆን ለድንግል ማርያም ባበሰራት በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ትእዛዝ በነፋስ ኃይል በብርሃን ሰረገላ በስውር ዓለምን ዙረው ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ከተመለሱ በኋላ የአምላክን ሰው መሆን የምስራች ለኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ አበሰሩ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች በመሆን ሰበኩ። ከዚህ በኋላ ዋልድባ[አርምኃ ደጋ] በመግባት ከአበው ጋር በመቀላቀል አምላክን ሲያገለግሉ ኖሩ። 😲ሰብአ ሰገል በሕይወት ይኖራል እንጂ አልሞቱም፥ ቅዱስ ገብርኤል ጌታን ዳግም እስከምታዩት ድረስ አትሞቱም ብሏቸዋልና አሁን እንደነ ነብዩ ሄኖክ፥ ቅዱስ ኤልያስ፥ ቅዱስ ያሬድ፥ ቅዱስ ነአኩቶለአብ፥ አቡነ አረጋዊ እንዲሁም ሌሎች ቅዱሳን ተሰውረው ይገኛሉ። ፨ኢትኤል ኢትዮጵያን የሰራ ድንቅ ጥበበኛ መሪ ነበር። ተጻፈ በኃይለሚካኤል ደሣለኝ - - መንገደ ጥበብ / ዩቲዩብ ቻናል።
15395
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AD%E1%89%A5%E1%8B%B0%E1%89%B5
ክብደት
ክብደት በአንድ ቁስ ላይ የመሬት ስበት የሚያሳርፍበት የጉልበት መጠን ማለት ነው። መሬት ላይ የአንድ ነገር ክብደት ከነገሩ ግዝፈት በንዲህ መልኩ ይለካል፦ ክብደት ነው የነገሩ ግዝፈት ነው ^2 ሲሆን በመሬት ስበት ምክንያት የሚፈጠረው የቁሶች ፍጥንጥነት ነው; በርግጥ ቁሶች በመሬት ብቻ ሳይሆን የሚሳቡት በሌሎችም ቁሶች ይሳባሉ። ይህ ክስተት ግስበት ይሰኛል። ለምሳሌ በጨረቃ ወይም ፀሐይ ወይም ማርስ። ባጠቃላይ መልኩ ቁሶች በግስበት ሜዳ ውስጥ ሲገኙ የሚያርፍባቸው የስበት ጉልበት ክብደት ተብሎ ይታወቃል። የግስበት መጠን ከአንድ ቁስ መካከለኛ ቦታ እየራቅን በሄድን ቁጥር በርቀቱ ስኩየር መጠን ግስበቱ እየደበዘዘ ይሄዳል። በዚህ ምክንያት የግስበቱ ሜዳ ደከመ እንላለን። የመሬትም ስበት ከባህር ወለል ተነስተን ወደ ተራራማው የምድር ክፍል እየወጣን ስንሄድ ግስበቷ እየደበዘዘ ይሄዳል። ስለዚህም የአንድ ቁስ ክብደት በተራራ ላይ ሲቀንስ በባህር ወለል ላይ ይጨምራል። ይህ ጸባይ ከግዝፈት ጋር ይለያያል። የአንድ ነገር ግዝፈት የትም ቦታ አንድ አይነት ነው።
14745
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%AD%E1%8C%8E%E1%89%A3
አርጎባ
አርጎባ ኢትዮጵያ በደቡብ እስከ ባሌ በምስራቅ እስከ ሐርር፣ አፋር ሰሜን ወሎ ትግራይ ክፍል ድረስ የሚኖሩ አርጎብኛ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎችን የሚገልጽ ቃል ነው። አርጎባ በአፋር ዞን 3 የአርጎባ ልዩ ወረዳ፣ አዋሽ ሠባት ኪሎ፣ ወረርና የመሳሰሉት፣ በአማራ ሰሜንሸዋ (ምንጃር - መልካጅሎ፣ ጮባ፣ በረኸት፣ አሳግርት፣ ሸዋ ሮቢት፣ አጣዬ፣ ጣርማበርና የመሳሰሉት፣ በደቡብ ወሎ ዞን ምስራቃዊ ክፍሎች፣ ቃሉና አካባቢውእና ኦሮሚያ ልዩ ዞን እንዲሁም በኦሮሚያና ሀረሪ ክልሎች በስፋት ይኖራሉ። አርጎባ የሚለው ስያሜ «በወቅቱ የነበሩ አፄዎች አረብ ገባ ብለው የአርጎባ ማህበረሰብን መጠርያ ከአርጎባ ጋር ያያልዙታል። ይህ የብሄረሰቡ ትክክለኛ መጠርያ ሳይሆን ሊሉ የፈለጉት ውጫዊ ናቸው ለማለት ነው። አርጎባዎች መቶ በመቶ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ናቸው። በእርሻ በንግድና በሽመና ይተዳደራሉ። ኢትዮጵያ ይኖር የነበረ ጥንታዊ ህዝብ ነው። በተለይ በ13ኛው እና በ14ኛው ክፍለ ዘመንየወላሽማ ስርወ መንግስትን ማለትም የይፋት ወላስማ ሥርወ መንግስት እና የአደል ወላስማ ስርወ መንግስት ያስተደደረ ንግድን መስርቶ ይኖር የነበረ በኢትዮጵያ የመጀመርያውን እስላማዊ መንግስትን የመሰረተ ከዚያም በሁለተናዉ ሂጅራ በነብዩ መሃመድ የእስልምና እምነት ተከታዮች ከቁርሾች ጋር በነበረው ግጭት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ አረቦችን ተቀብሎ ያስተናገደ ሃይማኖታቸውንም የተቀበለ የኢትዮጵያ የመጀመርያው የሙስሊም ማህበረሰብ ነው ማለት ይቻላል። የአርጎባ ህዝብ ባህላዊ እና መንፈሳዊ መሪዎች አሉት፦ ሱልጣን፣ ጋራድ፣ ኢማም፣ አሚር፣ ወዚር፣ ቃዲ፣ ሸህ፣ አባ ጋር፤አባዬ፤አቦኝ… የሚባሉ የሽማግሌዎችና የወጣቶች መሪዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔሮች
50403
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B6%E1%88%B5
ቅዱስ ገብረክርስቶስ
ገብረክርስቶስ የቆንስታቲኖፕሉ ንጉስ ቲወዲሰይስ ልጅ የነበረ ጻድቅ ነው። የዚህ ጻዲቅና መባዓ ጽዮን የተባለው የኢትዮጵያ ጻዲቅ ገድሎች ተከለ ሃይማኖት በተባለ ሃብታምና ሚስቱ ወለተ ጽዮን አነሳሽነት ምክሖ ጊዮርጊስ በተባለ ፀሐፊ በአንድ መጽሃፍ እንዲጻፉ ተደረገ ። ይህ መጽሐፍ እጅግ በተዋቡ ደማቅ ስዕሎች ያሸበረቀ ሲሆን ሰአሊው "ኢግናጦስ" የሚባል ሰው ሊሆን ይችላል በማለት ታሪክ ተመራማሪው ዋሊስ በጅ ገምቷል መጽሃፉ በዓፄ ቴወድሮስ መቅደላ ላይ ሊያሠሩት ለነበረው ቤ/ክርስቲያናቸው እንደስጦታ አዘጋጅተውት በመሃሉ በእንግሊዞች ተወስዶ እንግሊዝ አገር ውስጥ ይገኛል ። የመጀመሪ ሕይወት ታሪኩ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ወላጅ አባቱ የቍስጥንጥንያው ንጉሥ ቴዎዶስዮስና እናቱ ንግሥት መርኬዛ በስለት ያገኙት ብቸኛ ልጃቸው ስለሆነ ሃይማኖትን እያስተማሩት በምግባር በእጅጉ ተንከባክበው አሳድገውታል፡፡ የአባቱን ንግሥና በመውረስ ቍስጥንጥንያን እንዲገዛላቸው በመፈለግ ወላጆቹ ለአካለ መጠን ሲደርስ የሮሙን ንጉሥ ሴት ልጅ አጋቡት፡፡ እርሱ ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም የተዘጋጀ ነበርና የሠርጉ ዕለት ሌሊት የእርሱንም ሆነ የሙሽይቱን ድንግልና እንደጠበቀ ላንቺም ለእኔም ይህ ነገር የሚጠቅመን አይደለም ብሎ ከጫጉላ ቤት ወጥቶ በመርከብ ተሳፍሮ ሩቅ ሀገር በመሄድ በቤተክርስቲያን ተቀምጦ ከነዳያን ጋር ተደባልቆ በመለመን ለምኖ ያገኘውንም ለሌሎች እየመጸወተ በጾም በጸሎት ተጠምዶ 15 ዓመት ኖረ፡፡ የዓላማው መታወቅ እመቤታችን ተገልጻ ለአንድ የቤተክርስቲያኑ አገልጋይ የገብረ ክርስቶስን ጽድቅ ብትነግረው ምሥጢሩን ለሀገሩ ሁሉ አዳረሰበት፡፡ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስም ‹‹ግብሬ ታወቀ፣ ከዚህ ውዳሴ ከንቱ ልሽሽ›› በማለት ወደሌላ ሀገር በመርከብ ሲጓዝ ፈቃደ እግዚአብሔር መርከቢቱን ያለ አቅጣጫዋ ወስዶ አባቱ ደጅ አደረሰው፡፡ ማንነቱን እንደደበቀና ዓለምን ምን ያህል እንደናቃት ይረዳ ዘንድ በአባቱና በንጉሡ ደጅ የኔ ቢጤ ለማኝ ሆኖ ለአባቱ ውሾች የሚሰጠውን ፍርፋሪ እየተመገበ አሁንም 15 ዓመት ሙሉ በትዕግስት ተቀመጠ፡፡ የአባቱ አሽከሮች እንኳን እጣቢና ቆሻሻውን ሁሉ እየደፉበት ሲያሠቃዩት የአባቱ ውሾች ግን የእግሩን ቁስል ይልሱለት ነበር፡፡ በአጠቃላይ ገብረ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የታላቅ ንጉሥ ልጅ ሲሆን ነገር ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ ስለ ጽድቅ ተሰዶ እየለመነ ያገኘውን እየመጸወተ በጾም በጸሎት እየተጋደለ 30 ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፡፡ በመጨረሻም ጌታችን እመቤታችንን፣ ቅዱሳን መላእክትን ሁሉ፣ ከገብረ ክርስቶስ በፊት የነበሩ ነቢያትን ሁሉ፣ ሐዋርያትን፣ ጻድቃንን፣ ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ መጥቶ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ ከጌታችን ጋር አብረውት የመጡት ሁሉ በታላቅ ክብርና ምስጋና እያመሰገኑት ጌታችን ክብርት ነፍሱን በእቅፉ ተቀብሎ አሳርጓታል፡፡ የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ በቅዳሴ ላይ ሳሉ ከንጉሡ ቤት ሄደው የገብረ ክርስቶስን ሥጋ እንዲያመጡ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ በትእዛዝ መጣላቸውና ሄደው ቢያዩ የገብረ ክርስቶስን ሥጋ በንጉሥ አባቱ ደጅ ወድቆ አገኙት፡፡ በገብረ ክርስቶስም እጅ ላይ በጥቅል ወረቀት የተጻፈ ደብዳቤ ነበርና ወስደው ሊያነቡት ሲሞክሩ ወረቀቱ አልላቀቅ ብሎ ፈጽሞ እምቢ አላቸው፡፡ ብዙ ምሕላና ጸሎት ከተደረገ በኋላ ወረቀቱ ከእጁ ላይ ተላቀቀና ሲነበብ ገብረ ክርስቶስ ስለ አምላኩ ፍቅር ብሎ ለ30 ዓመታት ያሳለፈውን እጅግ አሠቃቂ መከራ በተለይም በአባቱ ደጅ ማንም ሳያውቀው ያሳለፈውን እጅግ አሳዛኝ መከራና በኀዘን የሚያስለቅሰውን ታሪኩን በራሱ እጅ በዝርዝር ጽፎት ተገኝቷል፡፡ ንጉሡ አባቱና ንግሥት እናቱም ይህንን ልጃቸው የጻፈውን መልእክት ባነበቡ ጊዜ የሚሆኑት ጠፋቸው፡፡ በጣም የሚገርመው ደግሞ ወላጆቹ ሚስት አድርገው ያመጡለት የሮሙ ንጉሥ ሴት ልጅ ለባሏ ታማኝ ሆና 30 ዓመት ሙሉ በእናት አባቱ ቤት በትዕግስት ስትጠብቀው መኖሯ ነው፡፡ እርሷም ታሪኩ ሲነበብ ብትሰማ እንደ ዕብድ ሆነች፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስን ሥጋውን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱ እጅግ አስገራሚ ተአምራት በድውያን ሕመምተኞች ላይ ተፈጽሟል፡፡ ከተአምራቱ የተነሣ መንገዱ በሕዝብ ተጨናንቆ አላሳልፍ ቢላቸው ንጉሡ በመንገድ ዳር ወርቅ እየበተነ ሰው ወርቁን ለማንሳት ሲሄድ በፍጥነት ወደ ቤተ ክርስቲያን አድርሰውታል ፡፡ ከገድለ ገብረክርስቶስ የተወሰዱ ጥንታዊ ስዕሎች
4196
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%83%E1%8B%AD%E1%88%9B%E1%8A%96%E1%89%B5
ሃይማኖት
ሃይማኖት አንድ ሕብረተሠብ የሚያምንባቸው ጽኑ እምነቶች መሠረት ነው። በዓለም ውስጥ በርካታ ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች አሉ። ዋና ዓለማዊ ሃይማናቶች ክርስትና፣ እስልምና፣ አይሁድና፣ የሕንዱ ሃይማኖት እና ቡዲስም ናቸው። እነዚህ ሃይማኖቶች በአንዳንድ አገር በይፋ የመንግሥት ሃይማኖት ሁኔታ አላቸው። ከነዚህ መጀመርያ ሦስቱ. ክርስትና፣ እስልምናና አይሁድና፣ ሁላቸው ከአብርሐም ስለ ተነሡ፣ «አብርሃማዊ ሃይማኖቶች» ተብለዋል። ሒንዱኢዝምና ቡዲስም ግን ከሕንድ ተነሡና «ሕንዳዊ» ወይም «ዳርማዊ ሃይማኖቶች» ተብለዋል። ሌሎች ሃይማኖቶች በአሁኑ ሰዓት በየትም አገር የመንግሥት ሃይማኖት ባይሆኑም፣ ባለፉት ዘመናት በታሪክ መንግሥታት ይኖራቸው ነበር፦ በተለይ ዛርጡሽና፣ ጃይኒስም፣ ሲኪስም፣ ዳዊስም፣ የኮንግ-ፉጸ ትምህርት፣ ሺንቶና የተለያዩ ኗሪ ወይም አረመኔ ሃይማኖቶች የቀድሞ መንግሥታት ነበሯቸው፤ የጠፉት ሃይማኖቶች ማኒኪስም እና አሪያኒስም ደግሞ የቀድሞ መንግስታት ነበሯቸው። በተጨማሪ መቸም መንግስት ያልነበረላቸው በርካታ ሌሎች አነስተኛ ሃይማኖቶች ወይም እምነቶች አሉ ወይም በታሪክ ተገኝተዋል። በአንዳንድ አስተሳሰብ ማርክሲስም-ሌኒኒስም በሃይማኖት ፈንታ የአንዳንድ መንግሥት ፍልስፍና፣ ትምህርት ወይም ርዕዮተ ዓለም በመሆኑ በውኑ እንደ አንድ ሃይማኖት መቆጠሩ ተገቢ ነው።
40392
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%89%E1%88%9D%E1%8A%92%20%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B3%E1%88%8D%20%E1%8B%B6%E1%89%BD%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%8B%B5
አሉምኒ ፖርታል ዶችላንድ
አሉምኒ ፖርታል ዶችላንድ ከትርፍ ነፃ የሆነና በጀርመን አገር ስልጠና ላደረጉ ሰዎች የተዘጋጀ ማህበራዊ ድረ ገፅ ነው። ማንኛውም በጀርመን አገር ጥናት፤ ሪሰርች ያደረገ፤ ስራ የስራ ወይም በጀርመን አገርም ሆነ በውጭ አገር ማንኛውንም አይነት የቋንቋም ሆነ ሌላ አይነት ስልጠና ያደረገ አሉምኑስ ሊጠቀምበት የሚችል ድረ ገፅ ነው። ፖርታሉ ለግልም ሆነ ሙያን ላስመለከተ ጉዳይ የተዘጋጀ ነው። ስኮላርሺፕ ላገኙም ሆነ ላላገኙ፤ በአለም አቀፍ የጥናት ፕሮግራሞች ለተሳተፉም ሆነ ላላልተሳተፉ ግለሰቦች ክፍት የሆነ መድረክ ነው። የግል ድርጅቶች በነፃ ድረ ገፁን ለመጠቀም ይችላሉ። ፕሮጀክቱ በአምስት የጀርመን አገር ድርጅቶች እንዲሁም በጀርመን አገር መንግስት ትብብር ተዘጋጅቷል። የአሉምኒ ፖርታል ዶችላንድ ድረ ገፅ በእንግሊዝኛ እና በጀርመንኛ ቋንቋ ተዘጋጅቷል። ኰሚውኒቲው ውስጥ በተለያዩ ቋንቋዎች መልእክት መለዋወጥ ይቻላል። አሉምኒ ፖርታል ዶችላንድ ለጀርመን አሉምኒዎች ከሎሎች አሉምኒዎች እንዲሁም ከጀርመን አገር ጋር ግንኙነት ካላቸው ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንዲኖራቸው ይረዳቸዋል። ከተለያዩ የኰሚውኒቲ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ፖርታሉ አለም አቀፍ የሆኑ የስራ እንዲሁም የሙያ ማታወቂያዎችን ባህልን ትምህርትን ሳይንስን ኢኮኖሚን ያስመለከተ የስነ ፅሁፍ ክፍል አለም አቀፍ የሆኑ ዝግጅቶችን ያስመለከተ ክፍል በተጨማሪም ጀርመንኛ ቋንቋን መማሪያ መሳሪያዎች ያስመለከቱ ፕሮራግሞችን አካቷል። አሉምኒ ፖርታል ለድርጅቶች በጀርመን አገር የሰለጠኑ አለም አቀፍ የሆኑ ኤክስፐቶችን ማግኛ መንገድ ሊሆናቸው ይችላል። ድረ ገፁ እነዚህ ድርጅቶች ኤክስፐርቶችን እንዲሁም ቢዝነስ ፓርትነሮችን የሚያገኙበት መድረክ ነው። አሉሚኒዎች ለረዥም ጊዜ ከአገር ውጭ በመሄድ የስራ ልምዳቸውን ለማዳበር ሙከራ ሲያደጉ ቆይተዋል። ይህም ቢሆን ወደ 80% የሚደርሱ ወደ ጀርመን አገር ለጥናት ከሚሄዱት መካከል ወደ 14,000 የሚጠጉት የራሳቸውን ወጪ ችለው የሚንቀሳቀሱ ናቸው። ከነዚህ ግሩፖች ጋር ግንኙት ለመፍጠር አስቸጋሪ ሙከራ ነበር። አሉምኒ ፖርታል ዶችላንድ ከማንኛውም ድርጅት ለሚመጡ ለጀርመን አገር አሉምኒዎች የተዘጋጀ ድረ ገፅ ነው። ዋነኛው አላማ እነዚህን ግለሰቦች ነፃ ትምህርት ሰጪ ድርጅቶችን እንዲሁም በጀርመን አገር የሰለጠኑ ተቀጣሪዎችን የሚፈልጉ ድርጅቶን አንድ ላይ ማምጣት ነው። የፕሮጀክቱ ፅንሰ ሃሳብ ከተጀመረበት 2008 እ.ኤ.አ. ጀምሮ 65.977 አባላት 1.369 ድርጅቶች 306 ዩኒቨርቲዎች 392 ክፍት የራ ቦታ ማስታወቂያዎች 3.876 የግል ፐሮፋይሎች 915 ግሩፖችን 1.541 ብሎጎችን አጠቃሎ ይዟል ( 2013 እ.ኤ.አ.) የድረ ገፁ ውስጣዊ ይዘት አሉምኒ ፖርታል ዶችላንድ ሁለት ክፍሎች አሉት፤ ኦንላይን ኮሚኒቲ እና ኢንፎ ፖይንት። ኦንላይን ኮሚኒቲ የማህበራዊ መገናኛ ክፍል ነው። ይህ ክፍል ፖርታሉ ውስጥ ለተመዘገቡ አባሎች ብቻ ክፍት ሲሆን እነዚህ አባሎች ከሌሎች አባሎች እንዲሁም ከድርጅቶች ጋር በግሩፖች በብሎጎች በፕሮፋይሎች በተጨማሪም በፎረሞች ወዘተ በመጠቀም ሃሳባቸውን ለመለዋወጥ የሚችሉበትን መንገድ ፈጥሮላቸዋል። ኢንፎ ፖይንት ላልመዘገቡ አባላትም ክፍት የሆነ መድረክ ነው። ይህ መድረክ ውስጥ ከጀርመን አገር ጋር ግንኙነት ያላቸውን መልእቶች ማግኘት ይቻላል። ተጠቃሚዎች የጀርመንኛ ቋንቋ ችሎታቸውን የጎተ ኢንስቲቲዩት በሚሰጣቸው ፕሮግራሞች በመጠቀም ለማሻሻል ይችላሉ። በኢንፎ ፖይንት ውስጥ ሙያቸውን ወይም ትምህርታቸውን ለመቀጠል የሚፈልጉ ግለሰቦች እንዲሁም አለም አቀፍ ስራ የሚፈልጉ የተለያየ ኢንፎሜሽን ለማግኘት ይችላሉ። የኤዲቶሪያል ክፍሉ ውስጥ ስለ ኢኮኖሚ ሳይንስ ጥናት ባህል እና ወዘተ ማንበብ ይቻላል። የጀርመን ድርጅቶች በኢንፎ ፖይንት በመጠቀም በጀርመን አገር ውስጥ የሰለጠኑ አዲስ ተቀጣሪዎችን ለማግኘት ይችላሉ። ድርጅቹ አሉምኒ ፖርታል ውስጥ ከተመዘገቡ በኋላ ክፍት የስራ ቦታቸውን ማስተዋወቅ ሬዙሜዎችን ማመሳሰል እንዲሁም ድርጅታቸውን ያስመለከቱ አዲስ ዜናዎችን በነፃ ማስተዋወቅ ይችላሉ። አጋሪ ድርጅቶች አምስቱ ዋነኛ ከትርፍ ነፃ የሆኑ አሉምኒ ፖርታል ዶችላንድን በመፍጠር በመደገፍ እንዲሁም በማስተዋወቅ እየረዱ ያሉ ድርጅቶች የሚቀጥሉት ናቸው፤ አሌክሳንደር ፎን ሁምቦልት ፋውንዴሽን ( ሴንተር ፎር ኢንተርናሽናል ማይግሬሽን ኤንድ ዴቨሎፕመንት ( የጀርመን የእድገት ትብብር ድርጅት [ የጀርመን የትምህርት እና የሙያ ልውውጥ ፕሮግራም ( ጎተ ኢንስቲቲዩት [ በቁጥር ከአስር የበለጡ ስራቴጂክ አባሮች ከላይ የተጠቀሱትን የአሉምኒ ፖርታል ዶችላንድን ስፖንሰሮች በመደገፍ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል የጀርመን አገር ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ የጀርመን አገር ትምህርት ሚኒስትር እንዲሁም የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደ ፍሪድሪሽ ኤበርት ኮንራድ አደናወር እና ሃይንሪሽ ቦል ድርጅቶች ይገኙበታል። ሌሎች ሊንኮች
19320
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%AE%E1%88%AD%E1%8B%AB%20%E1%8A%90%E1%8C%88%E1%88%A5%E1%89%B3%E1%89%B5%20%E1%8B%9D%E1%88%AD%E1%8B%9D%E1%88%AD
የኮርያ ነገሥታት ዝርዝር
ማስታወሻ፦ ከ200 ዓክልበ. አስቀድሞ የነበሩት የኮርያ ነገሥታት በታሪክ ሊቃውንት ዘንድ ከአፈ ታሪካዊ ሁኔታ በላይ የላቸውም። የጎጆሰን ስርወ መንግሥት በኮርያዊ ተውፊት መሠረት ዳንጉን ዋንገም በኮርያ የደረሰው በቻይና ጥንታዊ ንጉሥ ያው 25ኛው አመት ሲባል ይህ የሆነው በኮርያ ሊቃውንት አቆጣጠር በ2341 ዓ.ም. ነበረ። የጊጃ ሥርወ መንግሥት በአፈ ታሪክ የቻይና ንጉሥ ዦው ዉ በ1134 አክልበ. ግድም ጊጃን በጎጆሰን ዙፋን አስቀመጠው። ይህ ታሪክ ቀድሞ በቻይናም ሆነ በኮርያ ሊቃውንት የተቀበለ ሲሆን፣ አሁን ግን የቻይና ሊቃውንት ሲቀበሉት ብዙ የኮርያ ሊቃውንት አይቀበሉትም፤ የፊተኛው 47 ነገሥታት እስከ 203 ዓክልበ. ድረስ እንደ ነገሡ ያደርጋሉ እንጂ። ሙንሰውንግ (ጊጃ) (1134 – 1090 ዓክልበ.) ጃንግህየ ግየውንግህዮ ጎንግጀውንግ ሙንሙ ቴዎን ግየውንግቻንግ ህውንግፕየውንግ ቸውርዊ ሰውንህየ ኡያንግ ሙንህየ ሰውንግደክ ዶሄ ሙንየውል ቻንጉክ ሙሰውንግ ጀውንግየውንግ ቸውንህዮ ሱዶ ኊያንግ ቦንጊል ደውክቻንግ ሱሰውንግ የውንገውል ኢልሚን ጀሰ ቸውንጉክ ዶጉክ ህየውክሰውንግ ኋራ ሰውልሙን ግየውንግሱን ጋደውክ ሳምህዮ ህየውንሙን ጃንግፕየውንግ ጆንግቶንግ ኤ (ጁን)
13122
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%80%E1%8C%A5%E1%89%83%E1%8C%AD
ቀጥቃጭ
የኢትዮጵያን ባህላዊ የብረትና ነሓስ እቃዎች እንዴት እንደሚሰሩ የሚያውቅና በተግባርም የሚተረጉም ምሁር ቀጥቃጭ ይባላል። ግን ያን የሚያደርጉና ይህን የመሰለ የጅ ጥበብ ያላቸው እነኚህ ባለሙያዎች በህብረተሰቡ ዘንድ የተናቁና የተገፉ ናቸው ይህ ደግሞ ከጥንት ጀምሮ የመጣ ነው የሚገርመው ነገር አሁንም ድረስ እነዚህ ወርቅ እጅ ያላቸው ማህበረሰቦችን በተለያየ መንገድ በተለያየ ስያሜ ይጠሯቸዋል በተለይ በጉራጌ ክልል ውስጥ እነዚህ ጥበበኞችን (ነፉረ )እያሉ ነው የሚጠሯቸው ይህ ማለትም ብረት ቀጥቃጭን ቡዳ ከሰው የማይቀላቀል ይሉቱል ባጠቃላይ የጎነ ሰብ እያሉ ይጠሩታል ይሄ ማለት ደግሞ በሀገሩ ላይ መብት የሌለው እና የተገፋ ነው ማለት ነይ እኔ ከሁሉም የሚገርመኝ ደግም እነሱ በሰሩት ቢላዋ አርደው ከትፈው እየበሉ እነሱ በሰሩት ምጣድ ቆልተው ጋግረው እየበሉ እነሱ በሰሩት ድስት ሰርተው አብስለው እየበሉ ይሏቸዋል የተናቁ ታድያ ምን ይሉታል ጥበበኛውን ንቆ ጥበቡን ማድነቅ በጃቸው ጥበብ በተሰራ መሳርያ እየተጠቀሙ እነሱን መግፋት ታድያ እስኪ ፍረድ ይሄ ምን የሚሉት ነገር ነው ይህ ማለት ልጅን ወዶ እናትን መጥላት ነው ለኔ ወገኔ ንቃ ይሄኮ ጥበብ ነው ይሄኮ እድገት ነው ይሄ ማለት ባደጉት ሀገራት የተከበረ ስራ ነው ታድያ ለምን እኛ እርስ በርሳችን ያንተ ዘር ይሄ የኔ ደግሞ ይሄ እያልን ያንተጎሳ የዘቀጠ የኔ ደግሞ ከፍ ያል እየተባባልን እስከመቼ እንኖራለን እኛ ሁላችንም ያዳም እና የሄዋን ዘሮች ነን ስለዚህ ጥንት አባቶቻችን ባለመማርና በለማወቅ በፈጠሩት አፈታሪ እኛም ተተብትበንበታል ወገኔ ንቃ ይሄ ሙያ ነው !!!!!!!!!!!! የኢትዮጵያ ባልትና
18264
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%89%A1%E1%89%A5
ደቡብ
ደቡብ የሚለው ቃል ስም፣ የስም ገላጭ ወይም የግሥ ገላጭ ሊሆን ይችላል፣ ከአራቱ ዋና ዋና የአቅጣጫ መጠሪያዎች አንዱ ነው። ይህ አቅጣጫ ለሰሜን ተቃራኒ ሲሆን ለምስራቅ እና ለምዕራብ ደግሞ ቀጤ ነክ ነው። እንደ ስምምነት ሁኖ የማንኛውም ካርታ የታችኛው ክፍል ደቡብ ተደርጎ ይወሰዳል። ደግሞ ይዩ፦ ደቡብ ዋልታ
44096
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%88%AD%E1%8A%AB%E1%89%A5-%E1%8B%B3%E1%88%99
ኢርካብ-ዳሙ
ኢርካብ-ዳሙ ከ2115-2109 ዓክልበ. ግድም የኤብላ ንጉሥ ነበር። የኤብላ ጽላቶች የተባሉት ሰነዶች ክምችት ይህን ዘመን ይጠቅላል። የማሪ ንጉሥ ኢብሉል-ኢል ከኤብላ ብዙ መሬት በጦርነት ይዞ ነበር። በኢርካብ-ዳሙ መጀመርያው ዓመት ግን የኤብላ ሻለቃ ኤና-ዳጋን ኢብሉል-ኢልን አሸንፎ አዲስ ንጉሥ ኒዚ በማሪ ዙፋን አነሣ። በቅርብ ጊዜ ግን ኤና-ዳጋን እራሱ የማሪን ንጉሥነት ማዕረግ ያዘ። ኢርካብ-ዳሙ ደግሞ ከሐማዚ ንጉሥ ዚዚ ጋራ ስምምነት እንደ ተዋዋለ ይዘገባል። የእስያ ታሪክ
33763
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%88%B5%E1%89%B5%20%E1%89%A0%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%20%E1%8B%99%E1%88%AA%E1%8B%AB
ኢትዮጵስት በዓለም ዙሪያ
ኢትዮጵስት በዓለም ዙሪያ የኢትዮጵያ ጥናት ፡ ይህ ጥናት አጠቃላይ የሆነ የኢትዮጵያ የታሪክ ፣ የጆግራፊ፣ የዘር፣ የቋንቋ፣ የስነፅሁፍ፣ የባሕል፣ የተፈጥሮ ሐብት፣ የኤኮኖሚ፣ የፖለቲካና የሶሻል፣ ጥናቶችን ያጠቃልላል። ይህ ነጻ የሆነ ሳይንሳዊ ጥናት በቅርቡ ተጠናክሮ የቀጠለ ቢሆንም በቅድመ ጥናቶች የተደረጉ ስራወች እንደሚያሳዮት ጥናቶች የተከሃዱት ባጠቃላይ ፖቶሎጅካል የታሪክ፣ የቋንቋ፣ የባህልና በሀገሪቱ የሚኖሩ ጎሳወችን በተመለከተ ነበር። በመጀመሪያ የኢትዮጵስት ጥናተቶች የወጡት በ17ኛዉ ክፍለ ዘመን መጨረሻ ሲሆን በ20ኛዉ ክፍለ ዘመን በአዉሮፓዉያን ቋንቋ በመጀመሪያ ጊዜ በኢጣሊያንኛ ከዚያም በፈረንሳይኛና በእንግሊዝኛ ስለትዮጵያ ጥናታዊ ጽሑፎች ብቅ ማለት ጀመሩ። ስለዚህም እንደምሳሌ የሚጠቀሰዉ ‘የኢትዮጵያ ጥናት‘ በሚል // በኢጣሊኛ ቋንቋ የሚታተም ጽሑፍ ነበር። የኢትዮጵስት የኢትዩጵያ ጥናት የሚለዉ ሀሳብ በተለይም ከመጀመሪያዉ ዓለም አቀፍ የኢትዮዽያ የጥናት ኮንፍረስ በሁዋላ ታዋቂ ሆኗል። {1959 በሮም ኢጣሊ} በአሁኑ ጊዜ ከ16 ያላነሱ ኮንፍረንሶች ተካሂደዋል። በነዚህም ኮንፍረንሶች ላይ አያሌ ኢትዮጵስት ምሁራን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ብዛት ያላቸዉ ጥናቶችን አቅርበዋል። በመካከለኛዉ ዘመን ኢትዮዽያ የሚባለዉ አካባቢ በተጨማሪ ‘የቅዱስ ዮሐንስ የክርስቲያኖች ሀገር በሚል በብዛት ይታወቅ ነበር። እንዲሁም አቢሲንያ በመባልም ይታወቃል። በ4ኛዉ ክፍለዘመን ክርስትና በአክሱም በመስፋፋቱ በኢትዮጵያና በኗሪወቿ ለይ ከፍተኛ ለዉጥ አስከትሏል። ለዉጭዉም ዓለም ትኩረትን አሳይቷል። ስለሆነም የቤዛንቲያን፣ የአርሚያን፣ የሮማዉያን ፣የፖርትጋል ኤፔስ ኮፖሳት በ6ኛዉ ክፍለዘመን በኢትዮዽያ ጉብኝቶችን አድርገዋል። አረቦች ከኢትዮዽያና ከሕዝቦቿ ጋር በጥሩ ሁኔታ ይተዋወቃሉ። ይሄም እስልምና ከመፈጠሩ በፊት በነበረዉ የንግድና የባህል ልዉዉጦችና ግንኙነቶች ነበር። ከእስልምና በሁዋላም ቢሆን ችግር ባጋጠማቸዉ ጊዜ የመሐመድ ተከታዮች በስደት ወደ ኢትዮጽያ መጥተዋል። የአረብ የታወቁ የጆግራፊና የታሪክ ጽሐፊወች ያኩቢ፣ ማሱዲ፣ኢባን ሀያካሊያ፣ ያኩዬታ፣ ኢባን ሱኢዳ ከ9ኛዉ እስከ 14ኛዉ ክፍለዘመን በተደረጉ የጥናት ስራወቻቸዉ በጣም ከፍተኛ ታሪካዊ ዋጋ ያላቸዉና ስለ መካከለኛዉ ዘመን ኢትዮጽያ ታሪክ፣ ጆግራፊ፣ ኤትኖግራፊ የተጻፉ ስራወቻቸዉ ከፍተኛ የታሪክ ማጣቀሻወች ናቸዉ። በመካከለኛዉ ዘመን አዉሮፓዉያን በተከታታይ ወደ ኢትዮጽያ ትኩረት አድርገዉ ነበር። ይሄዉም በ12ኛዉ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነዉ። ለዚህም ዋናዉ ምክንያት በዓለም ላይ ከፍተኛ የሆነ የእስልምና መስፋፋት ስለነበር ይህንን ለመቋቋም በሚደረገዉ ትግል አጋዠ ለማድረግና የጋራ ግንባር ለመፍጠር ነበር። በዚህ የእስልምና መስፋፋት ዘመን ይህች የቅዱስ ዬሐንስ የክሪስታኖች ሀገር በሚል የምትታወቀዉ ኢትዮጵያ የበኩሏን አስተዋጦ አድርጋለች። ኢትዮጵያ በዚያን ጊዜ በእየሩስዓለምና በሮም የኢንፎርሜሽን ሴንተሮች ቤተክሪስታኖች ነበሯት።እንዲሁም በዚያን ጊዜ ካይሮ ታለቅ የንግድ ሴንተር ስለነበረች ኢትዮጵያም ታለቅ የንግድ ግንኙነት ስለነበራት እንደ ኢንፎርሜሽን ሴንተር ትገለገልበት ነበር። 16ኛዉና17ኛዉን ክፍለዘመን አዲሱ የኢትዮጵያ ጥናት የታሪክ ዘመን በማለት መጥራት ይቻለል። ይሄዉም የፖርቱጋሎች ወደ ኢትዮጵያ መምጣትና እንዲሁም የጽሐፋቸዉ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸዉ የታሪክ ማስታወሻወችና መጽሐፍት ናቸዉ። ከነዚህም መካከል፡ አለባሪሽ ‘እዉነተኛ ታሪክ ስለ ቅዱስ ዩሐንስ የቅዱሳን ሀገር’ ካሽታኑዩዝ “የፖርትጋሎች ጉዞ ታሪክ በአቢሲኒያ’ እንዲሁም ፖርቱጋልን ያገለግል በነበተዉ የእስፓኒሽ ተወላጅ ፓይሱ ‘የኢትዮጽያ ታሪክ’ በመጀመሪያ አጠቃሎ የታተመዉ በ1945/46 እነዚህ የፖርቱጋል አገር ጎብኝወችና ታርክ ጸሐፊወች ኢትየጵያንና የሕዝቦቿን ታሪክ ለአዉሮፓዉያን በማስተዋወቅ ታላቅ ሚና ተጫዉተዋል ወይም ቀደምትነት ነበራቸዉ። በ17ኛዉ ክፍለዘመን መጨረሻ በአዉሮፓና በሌሎችም አገሮች ስለኢትዮዽያ ስለመሬቷ ለምነት፣ ስለሕዝቦቿ አኗኗር፣ ስለቋንቋዋና ባሕሏ ብዙ ጥናታዊ ስራወች ተሰርተዋል። ሆኖም እነዚህ ስራወች ብዙወቹ ስተቶች ያሉባቸዉና ያልተስተካከሉ ነበሩ። በአዉሮፓ የኢትዮጵያ ጥናት መስራች ተብሎ የሚታወቀዉ ኢትዮጵስት ጀርመናዊዉ ተመራማሪ ፔሩ ሉዶልፍ ነዉ። የሱ ስራወችም የኢትዮጵያ ታሪክ መዝገበ ቃላቶች ናቸዉ ማለት ይቻላል። ስራወቹም በተለያዩ የታሪክ ክፍሎች ላይ የተመሰረቱ ናቸዉ። ለምሳሌ ኤትኖግራፊ/ሕዝብ /፣ ጆግራፊ፣ ታሪክ፣ ፍልስፍና ሌሎችም ነበሩበት። የእሱ የኢንፎርሜሽን ምንጭም ለብዙ ዓመታት በሮም ይኖሩ የነበሩት ኢትዮጵያዊ ቄስ መነኩሴ ግሪጎሪ ናቸዉ። ፔሩ ሉዶልፍ ታላላቅ ስራወቹን በፍራንክፈርት አሳትሟል ከእነዚህም መካከል። ‘የኢትዮጵያ ታሪክ’ ፣ ‘አጠቃላይ የሆነ እርማት ከኢትዮጵያ ታሪክ’ ፣ ‘የግዝ ቋንቋ ሰዋሰዉ /ግራመር/ ፣ ‘የአማርኛ ሰዋሰዉ /ግራመር/ና መዝገበ ቃላት’ ፣ ‘የግዝ ስነጽሑፍ መስፋፋትና መዝገበ ቃላት’ የሚሉ ናቸዉ። የፔሩ ሉዶልፍ መጸረሐፍትና ስራወች በፈረንሳይ፣ በእንግሊዝና በሌሎችም የአዉሮፓዉያን ቋንቋወች ተተርጉመዉ ነበር። ለረጅም ጊዜም እንደ ቋንቋ መዝገበ ቃላትና የታሪክ መማሪያነት አገልግለዋል። ‘የኢትዮጵያ ታሪክ’ የሚለዉ መጽሐፍ በራሽያን ቋንቋ ተተርጉሞ ለታላቁ ፔትሮስ /ጴጥሮስ/ አንደኛ በስጦታ ተሰጧቸዉ ነበር። ከፔሩ ሉዶልፍ በሁዋላ በኢትዮዽያ ጥናት ላይ መዳከም ታይቶ የነበር ቢሆንም በ18ኛዉ ክፍለዘመን መጨረሻና በ19ኛዉ ክፍለዘመን መጀመሪያ እንግሊዛዊያን ዠ- ቦርዩስ እና ገ- ሶልት አዲሱን የኢትዮጵያ ጥናት ጀመሩት። እረጅም ጊዜ የፈጀ ጉብኝትም አደረጉ ብዙ ጥናቶችንም አቀረቡ ቦርዩስ አባይ ከጣና ይፈልቃል አለ። በ1790 ጉብኝቱ በጻፈዉ ጽሑፍ ብዙ የጆግራፊ፣ የኤትኖግራፊ፣የታሪክ ሪኮርዶችን ለመጥቀስ ሞክሯል። ብዙ የኢትዮጵያ የጅ ጽሑፎችንም ሰብስቧል። በሁዋላም ለኦክፎርድና ለማንችስተር ዩንበርስቲወች ሰጧቸዋል። ሶልት ሁለት ጊዜ ያህል ኢትዮጵያን ጎብኝቷል በስራወቹ ትኩረት ያደረገዉ በሰሜን ኢትዮዽያ በተለይም በአክሱም በሚገኙት ሐወልቶችና ጸረሑፎች ላይ ነበር። በ19ኛዉ ክፍለዘመን ኢትዮጵስትና የኢትዮጵያ ጥናት በፍጥነት ተቀይሯል። ብዙ ጥናታዊ ተቋማትም ተመስርተዋል። በአዉሮፓ በሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶች ላይም መሰረታዊ የሆኑ ሳይንሳዊ ምርምሮችና ጥናቶች ተካሂደዋል። እንዲሁም ብዙ ጥናታዊ ጉዞወች ወደ ኢትዮዽያ ተደርገዋል። በተደረጉትም ጉዞወች በርካታ ጥናቶች ተካሂደዋል። ስለ ሴሜትክና ኩሸቲክ ቋንቋወች ጥናቶች ተደርገዋል። በ19ኛዉ ክፍለዘመን አጋመሽ ጀርመናዊዉ ተመራማሪ አ-ዲሊማን መሪነት ስለ ጥንታዊ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ስለ መካከለኛዉ ዘመን ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ስለግዕዝ ቋንቋ ሰዋሰዉ /ግራመር/ ስለ ሊቶግራፊና ሌሎችም ጥናቶችን አካሂደዋል። በነዚህና በመሳሰሉት ስራወች ላይ ከፍተኛ አስተዋጾ ያደረጉ ተመራማሪወችም፡ ፈ- ፐሪቶሪዮስ፣ ኦ- ሙቲቦክስ፣ ከ- ቢትሊድ፣ እንዲሁም አዉስትሪያዊዉ ኤ- ሊትማን ይገኙበታል።ኤ- ሊትማን በ1905፣1906 በአክሱም የተካሄደዉን የአርኪኦሎጅ ምርምርና የተመራማሪወች ቡድን መርቷል። የዚህ ጥናት ዉጤት በአራት ቶሞች በ1913 ታትሟል። ብዙ የአርኪኦሎጅና የኢፖግራዊ ስራወች ስለ ጥንታዊ ኢትዮጵያ ይዟል። ኤ- ሊትመን ሌላ የጥናት ቡድንም በኢትዮጵያ መርቷል። ይህ የጥናት ቡድን ስለስነጽሑፍና ስለፍልስፍና ጥናት ያደረግ ሲሆን፤ በተለይ በትግሬኛ ቋንቋ ላይም ጥናት አካሂዷል። ኤ- ሊትማን በብራሴል ዩንበርስቲ በሴሚቶሎጅ ፋኮሊቴት ስለ ኢትዮጵያ ያስተምር ነበር። በኢጣሊያ የኢትዮጵያ ጥናት በኢጣሊያ የኢትዮዽያ ጥናት መስራች ኢትዮጵስት ኢ- ገቢድ ነበር። ይህ ሰዉ ብዙ የቋንቋ የጥናት ጽሑፎችን ያበረከተ ነዉ። የሱ ተማሪ የነበረዉ ኮንቴኢኦሲን በኢትዮጵያ ኤትኖግራፊ ሕዝብና ቋንቋን በሚመለከት ስፊ ጥናቶችን አካሂዷል። የትግሬኛና የሀረሬኛ ቋንቋወችንም ይናገር ነበር። ኢጣሊ በኢትዮጵያ ሁለትዮሽ ባሕሪ ያለዉ ጥናት ስታካሂድ ቆይታለች። በቋንቋወችና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ የሚደረገዉ ጥናት በጣም ተዳክሞ የኢጣሊያን የቅኝ ግዛት ታሪክ በተመለከተና የቅኝ ግዛት መስፋፋትን በተመለከተ ብዙ ስራወች ተካሂደዋል። በ1941ዓም በሮም የኢትዮጵያ ጥናት ጆርናል ይታተም ነበር። // ለዚህ ከፋተኛ አስተዋጦ ያደረጉ ምሁራን፡ራይኒሮ፣ ፐሮካች፣ ተሩሊትስ፣ ናቸዉ። በኢጣሊያ ስለ ኢትዮጵያ ጥናት የሚካሄድባቸዉ ተቋማት የኢትዮጵያ ሴንቴር በኢጣሊያ፣ የምስራቃዊያን ጥናት ፋኮሊቴት በሮምና እንዲሁም በኒኦፖሎስ ዩንበርስቲ ነበር። በማከታተልም ኤ- ቺሩሊ የተባለዉ በሁለት ተከታታይ ጽሑፎች ጥናቱን አዳብሮታል እነዚህም ‘ኢትዮዽያ በፓላስታይን’ ፣ ‘የኢትዮዽያ ስነጽሑፍ ታሪክ’ ፣ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ጥናት በ19ኛዉ ክፍለዘመን መጨረሻ በመጀመሪያዉ አጋማሽ በ20ኛዉ ክፍለዘመን መጀመሪያ ኢትዮጵስት ዠ- ጋሊቢ የኢትዮጵያን ጥናት በፈረንሳይ መሰረተ። ዠ-ጋሊቢ በፈረንሳይ ዩንበርስቲ ሴሚቶሎግና ፕሮፌሰር ቢሆንም ጥናት በሚያደርግበት ጊዜ የፋኮሊቲዉ ሃላፊ ፈ- ሞንዶን ቢዳይ ይባል ነበር። ከዚያም ታዋቂዉ ሴሚቶሎግና የቋንቋ ምሁር ኢትዮጵስት መ- ኮኤን እነሱን በመተካት ፋኮሊቲዉን ይመራዉ ነበር። በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ጥናት በተለያዩ የፓሪስ ዩንበሪስቲወች የምስራቅ ቋንቋወች ፋኮሊቲወች ጥናቶች ይካሄዳሉ፣ ጥናት ከአካሄዱ ምሁራን መካከል፣ የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡ ሊክላን፣ አንፈሬ፣ ካኮ፣ ቱቢኦና፣ ዶርስስ ይገኙባቸዋል። በራሽያ የኢትዮጵያ ጥናት በ19ኛዉና በ20ኛዉ ክፍለዘመን በዓለም አቀፍ ኢትዮጵስቶች መካከል የራሽያ ተመራማሪወች ከፍተኛዉን ቦታ ይዘዉ ይገኛሉ። ይህም በታሪክ፣ በሐይማኖት፣ በአርኪኦግራፊ፣ በቋንቋ ከፍተኛ አስተዋጦ አድርገዋል። እነዚህ ከፍተኛ አስተዋጦ ያደረጉ ምሁራኖች፣ ቦሎቶብ፣ ኮባሌብስኪ፣ ኢሊሴባ፣ ባሮቢትስና፣ ቡልታቢች፣ አርታሞኖባ፣ እና ሌሎችም ሲሆኑ ከቅድመ አብዮት ስራወች መካከል ስለ ኢትዮጵያ ከፍተኛ በታ የሚይዘዉ ቱራዬብ መሰረታዊ የሆኑ የታሪክና የቋንቋ ጥናቶችን አካሂዷል። ከነዚህም መካከል፡ “የኢትዮዽያ ጥናት አርኪኦሎጅካል ማጣቀሻ” “የአቢሲኒያ ስብስቦች 15ኛዉና16ኛዉ ክፍለዘመን” የሚሉ ሲሆኑ ቱራዬብ በዘመኑ በምስራቃዊ ጥናት ታዋቂ በነበረዉ የሐርከፍ ዩንበርስቲ ከታዋቂዉ የምስራቃዊያን ምሁር ከዶርኖም ጋር በመሆን የኢትዮጵን ቋንቋ ያስተምር ነበር። የኢትዮጵያን ጥናት በመቀጠልም የቱራዬብ ተማሪ የነበረዉ ኢትዮጵስት ኮራትኮብስኪ ብዙ ስራወችን አበርክቷል። በታሪክና በስነጽሑፍ ጥናት ከተሰሩት ስራወች መካከል በተለይም አማረኛ ቋንቋን በተመለከተ ዩሽማኖብ ከሚጠቀሱት ዉስጥ አንዱ ነዉ። በባቢሎብ የተመራዉ የቦታኒክና የአግሮኖሚ ኢክስፖዴሽን ኢትዮዽያ የእርሻን ምርት በመጠቀም የመጀመሪያዋ አገር መሆኗን አረጋግጧል ኢትዮዽያ በጣም ጥንታዊና የእርሻ ስራትን ቀድማ የጀመረች ሀገር ነች በማለት አረጋግጠዋል። የዚህ ጥናት ስራወች በራሽያ በ1930 በሊቢና፣ ሊሶብስኪ፣ኦሊዴሮጌ፣ በሚባሉ ምሁራን ተመራማሪወች ታትመዋል። በኢትዮጵስቶች የተሰሩ የኢትዮዽያ ጥናታዊ ስራወች ወደ አዉሮፖዉያን ቋንቋ በብዛት መተርጎም የጀመሩት በ20ኛዉ ክፍለዘመን ነዉ። እነዚህም ስራወች የተተረጎሙት ለብዙ ዘመን በአዉሮፖ በኖሩት ሰወች ነዉ። የታወቁት ጽሐፊ አፈወርቅ ገብረእየሱስ በኢጣሊያን ቋንቋ መጽሐፍቶችን አሳትመዋል። ‘የአማረኛ ቋንቋ ሰዋሰዉ /ግራመር/1905}፣ ‘የአማረኛ ግስ’ ከሁለተኛዉ ዓለም ጦርነት በፊት አለቃ ታዬ ገብረመድሕን በጀርመን ይሰሩ ነበር። አለቃ ታዬ ‘የኢትዮዽያ ሕዝብ ታሪክ’ የሚል መጽሐፍ ጽፈዋል። እንዲሁም ተክለ ማሪያም መሀሪ በግዝ ቋንቋ ጥሩ ስራወችን አሳትመዉ ነበር። ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት በሁዋላ የተክለ ጻድቅ መኩሪያ ጥናታዊ ስራወች ከ1951ዓም ጀምሮ መታተም ጀመረ። በኢትዮጵያዊዉ ምሁር ተሰማ ሀብተወልደሚካኤል ለመጀመሪያ ጊዜ መሰረታዊ የሆነ የአማረኛ መዝገበ ቃለትም ተጻፈ። በ1950ዓም አዲሱ የኢትዮጰያ ጥናት ምራፍ ተጀመረ ማለት ይቻላል። ብዙ ኢንስቲቲዉቶችና ተቋማትም መቋቋም ጀመሩ። እንደዚሁም ብዙ የጥናት ተቋማት በተከታታይ ዓለማቀፍ የጥናት ኮንፍረንሶች መካሄድ ጀመሩ። ኢትዮጵያን በተመለከተ በሰፊዉ የአንትሮፖሎጅ፣ የአርኪኦሎጅ፣ የኢትኖግራፊ፣ የሰነጽሑፍ፣የሶሽኦሎጅ ጥናቶች በስፊዉ መካሄድ ተጀመረ። እንዲሁም የጥናት መስኮች እየተስፋፉ በዘመናዊ የሶሻልና የኢኮኖሚ፣ የዓለም አቀፍ ግንኙነቶችን የተለያዩ ቋንቋወችንና ጎሳወችን በሚመለከት በሰፊዉ ጥናቶች ይካሄዳሉ። በራሽያ ዉስጥ ስለኢትዮጵያ ጥናት የሚያደርጉ ተቋመትና ምሁራን በጣም በርካታወች ናቸዉ። ከነዚህም ዉስጥ ‘የአፍሪካ ጥናት ኢኒስቲቲዉት፣ ሳንክ ፒተርስቡርግ ዩንበርስቲ ኤትኖግራፊ ፋኮሊቴት፣ የዓለም ስነጽሑፍ ኢኒስቲቲዉት፣ የራሽያ አካዳሚ የምስራቅ ፋኮሊቴትና ሌሎችም። በመካከለኛዉ ክፍለ ዘመን በኢትዮዽያ ታሪክ ላይ ጥናት ያካሄዱ ራሽያዊ ምሁራን ኮቦሻኖብ፣ ቼርንትሶብ፣ ሲሆኑ በዘመናዊ የኢትዮዽያን ታሪክ ላይ ጥናት ያደረጉ ምሁራን፣ ባሲን፣ ራይት፣ተራፊሞብ፣ ትስኪን፣ያግያ፣ ናቸዉ። እንዲሁም ኢትዮጵያ ከራሽያ፣ ከጆርጅያና፣ ከአርሜንያ ጋር የነበሯትን ግንኙነቶች በሚመለከት ጥናት ያደረጉ ምሁራን፣ ማቻራደዜ እና ቶፑዝያን፣ ሲሆኑ ስለኢትዮጵያ ከአረብ የታሪክ ምንጮችን በተመለከተ ጥናት ያደረጉ ምሁራን፣ ቡኒያቶብ ነበሩ። በሌሎች ዘመናዊ የሶሻልና የኢኮኖሚ ጉደዮች ላይ ጥናት ያደረጉ ምሁራንም ጋሊፔሪን፣ ኮኪየብ፣ ሸራዬብ፣ ሼርር ናቸዉ። ቋንቋን በተመለከተ ጥናት ያካሄዱ ምሁራን፣ጋንኪን እና ቲቶብ ናቸዉ። የኢትዮጵያን ስነጽሑፍ በተመለከተ ጥናት ያካሄዱ ምሁራን፣ ቦሊፔ፣ ፓፕሼባ፣ ቱተሩሞባ ሲሆኑ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ጥናት ታላቅ አስተዋጦ ከአደረጉት ኢትዮጵስት ምሁራን መካከል በተለይ የሚከተሉት ጉልህ ቦታ ይይዛሉ። ማንቲሊኒችኮ፣ ባርተንትስኪና እንዲሁም የቼህ ምሁራን የሆኑት ፔትራቾክ፣ ቼርን ናቸዉ። በታላቋ ብርታኒያ የኢትዽያ የጥናት በታላቋ ብርታኒያ የኢትዽያ የጥናት ሴንተር በለንደን ዩንበርስቲ የምስራቅ ፋኮሊቴትና በኦክስፎርድና በማንችስተር ዩንበርስቲ ጥናቶች ይካሄዳሉ። የለንደን ዩንበርስቲ የኦሪንታልና የአፍሪካ ጥናት በሚል ቡሊቴን ያሳትማል። ስለኢትዮዽያ የታወቁት ኢትዮጵስት ሪቻርድ ፓንክረስት ብዙ ስራወቻቸዉን አሳትመዋል። ሌሎች እንግሊዛዊ አትዮጵስቶች ፔሬም፣ ኡሊንዶፍ ናቸዉ። በአሜሪካ ስለኢትዮጵያ ጥናት በአሜሪካ ስለኢትዮጵያ ጥናት የተጀመረዉ ከሌሎች አካባቢወች ጋር ሲነጣጠር በቅርቡ ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ በብዛት ስራወች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ። በአሜሪካ ስለኢትዮጵያ ጥናት የሚያደርጉ ሴንተሮች ወይም ተቋማት፡ በሜችጋን የንቨሪስቲና በካሊፎርኒያ የንቨሪስቲ የአፍሪካ ጥናት ማዕከል እና ሌሎችም ስለኢትዮጵያ ጥናቶችን ያካሂዳሉ። ከ1977ዓም ጀምሮ የሜችጋን ዩንቨሪስቲ “የኢትዮጵስቶች ማስታወሻ” በሚል እትሞችን ያወጣ ነበር። // እንዲሁም በኒዉጀርሲ ዩንቨሪስቲ ከ1978ዓም ጀምሮ “የአፍሪካ ቀንድ “በሚል ጆርናል ያሳትሙ ነበር። / በኢትዮጵያ ጥናት እድገት ዉስጥ ዋናዉና ታላቅ ቦታ ሊሰጠዉ የሚገባዉ በኢትዮጵያ የተቋቋሙት የጥናት ተቋማትና የአርኪኦሎጅ ኢኒስቲቲዉት የአርኪኦሎጆ አናላይዝ በሚል እትመቶችን ያወጣ ነበር። ፣ ሌላዉ ተቋም በአዲስ አበባ ዩንበሪስቲ የተከፈተዉ የኢትዮዽያ ጥናት ኢኒስትቲዉት ሲሆን ይህ ጠቋም የኢትዮዽያ ጥናት ጆርናልን ማሳተም ጀምሯል። ከ1974ዓም አብዮት ፍንዳታ በሁዋላ በኢትዮጵያ ጥናት ተቋማት ላይና እንዲሁም በሕብረተሰቡ ላይ መሰረታዊ ለዉጦች ተካሂደዋል። የኢትዮዽያ ጥናት ኢኒስትቲዉት የአደረጃጅት ለወጥ አካሂዷል። ተቃሙ ከፍተኛ የሆኑ ታላላቅ ጥናቶችን ስለኢትዮጵያ ማካሄድ ጀምሮ። ለዚህም ተቋም የታወቁት የታሪክ ምሁረና ተመራማሪ ኢትዮጵስት ታደሰ ታምራት በሃላፊነት ተመድበዉ ነበር። የተቋሙ ዋና ሴንተር የነበረዉን የአማረኛ ቋንቋ አካዳሚ የኢትዮጵያ ቋንቋወች አካዳሚ በሚል በመተካት አያሌ ጥናቶችን በኢትዮጵያ በሚገኙ ብሔርና ብሔረሰቦች ፎልክሮች፣ ቋንቋወችና ባሕሎች ላይ ጥናቶችን አካሂዷል። እንዲሁም መዝገበ ቃላቶችንና የሳይንስና የቴክኖሎጅ ቴርሚኖችን እያሳተመ ያወጣል። አልፋቤት ለሌላቸዉ ቋንቋወች አልፋቤቶች እንዲቀረጡ ያደርጋል፣ለአላቸዉም እንዲሻሻሉ ጥናቶችን ያቀርባል። በዚህ ተቋም ዉስጥ የታወቁት የቋንቋ ምሁራን ፕሮፊሰሮች፣ አምሳሉ አክሊሉ፣ አሰፋ ገ/ማሪያም እና ሌሎችም ምሁራን በተቋሙ ይሰሩ ነበር። ሌላዉ ተቋም ታሪካዊ ሐዉልቶችንና ቅርሶችን ለመንከባከብና ለመጠበቅ የተቋቋመዉ የባሕልና የቅርሶች ጥናት መዕከል /ሴተር/ ነዉ። የኢትዮጵያ ጥናት በሌሎች የአዉሮፖ አገሮችም በኒዜርላንድና በስዉዘርላንድ ዩንበሪስቲወች ጥናቶችን ያካሂዳሉ። እንዲሁም የስራኤል የቴላቢብ ዩንበሪስቲም ስለኢትዮዽያ ጥናቶችን ያካሂዳል። ዓለም አቀፍ የኢትዮዽያ ጥናት ኢትዮጵስቶች ኮንፍረንስ የተካሄደባቸዉ አመታትና ሀገሮች/ከተማወች። 1ኛዉ ኮንፍረንስ በኢጣሊ ሮም 1959ዓም 2ኛዉ ኮንፍረንስ በኢንግሊዝ ማንችስተር 1963ዓም 3ኛዉ ኮንፍረንስ በኢትዮዽያ አዲስ አበባ 1966ዓም 4ኛዉ ኮንፍረንስ በኢጣሊ ሮም 1972ዓም 5ኛዉ ኮንፍረንስ በኒዘርላንድ ኒትሳ 1977ዓም 6ኛዉ ኮንፍረንስ በእዝራኤል ቴላአቢብ 1980ዓም 7ኛዉ ኮንፍረንስ በሱዲን ሉዋንዳ ዩንበሪስቲ 1982ዓም 8ኛዉ ኮንፍረንስ በኢትዮዽያ አዲስ አበባ 1984ዓም 9ኛዉ ኮንፍረንስ በራሽያ ሞስኮ 1986ዓም
34217
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%8D%88%E1%8C%A5%E1%88%AE%20%E1%8C%AD%E1%88%9B%E1%88%AA
የተፈጥሮ ጭማሪ
የተፈጥሮ ጭማሪ በሰው ልጅ ጥናት በኩል ከአንድ አገር (ወይም ክፍላገር ወዘተ.) ጥሬ ልደት መጠን ቁጥር (ልደቶች በየሺህ ሕዝብ በየዓመቱ) የዚያው አገር ጥሬ ዕረፍት መጠን (እረፍቶች በየሺህ ሕዝብ) ሲቀነስ የሚገኘው የሕዝቡ ጭማሪ መጠን ነው። ይህ መጠን ግን «የተፈጥሮ» በመባሉ የሰው ልጅ ፍልሰቶች (ሰዎች ከአንድ አገር ወደ ሌላ የሚዛወሩበት መጠን) ቸል ይላል። የጥሬ ዕረፍት መጠን ከጥሬ ልደት መጠን ይልቅ ሲበዛ፣ ጭማሪ ሳይሆን የተፈጥሮ ቅነሳ አለ። አሁን በተለይ በምሥራቅ አውሮጳና በጃፓን ውስጥ ብዙ ልደቶች ስለሌሉ የተፈጥሮ ቅነሳ አለ፤ የሕዝብ ቁጥር በየዓመቱ ይቀነሳል። ሆኖም በአንዳንድ አገር የፍልሰቱ መጠን ከፍ ያለ በመሆኑ (ብዙ ሰዎች ወደዚያው አገር በመግባት ከመውጣት በላይ)፣ በጠቅላላ የኗሪዎቹ ቁጥር በየዓመቱ ይጨመራል። ከሁሉ ይልቅ የሆነው ቅነሳ ግን በሃይቲ ነው። በሃይቲ የልደት መጠን እጅግ ከፍተኛ ቢሆንም፣ የዕረፍት መጠን ግን ከዚያ እንኳን ይበዛል፤ ስለዚህ በጠቅላላ ቅነሳ አለ። በአፍሪቃ ግን ከእረፍቶቹ ይልቅ ብዙ ልደቶች ስላሉ የተፈጥሮ ጭማሪ አለ፤ የሕዝቡም ቁጥር እየበዛ ነው። ከአገራት ከሁሉ ከፍተኛ የሆነው የጭማሪ መጠን ለኒጄር ነው። የሰው ልጅ ጥናት
12109
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AE%E1%88%A8%E1%88%9B%E1%88%BD
ኮረማሽ
ኰረማሽ በአማራ ክልል ውስጥ፤ በሰሜን ሸዋ በ ላይ የምትገኝ ወረዳ ናት። ከአዲስ አበባ በምሥራቅ በኩል ሰማንያ አምሥት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ሥፍራ ስትሆን፣ በ ‘ስምጥ ሸለቆ’ () ምሥራቃዊ ፍንጭ አናት ላይ ያላት ገዥ ይዞታ ከአፋር (የቀድሞው አዳል) እና ከሶማሌ በኩል በታሪክ ዘገባ ይመነጩ የነበረቱን እስላማዊ አጥቂዎች ለመከላከል የተመቸች ቦታ በመሆኗ የተመሠረተች ጥንታዊ ምሽግ ናት። ከፊት ለፊትዋ የመገዘዝ ተራራ፤ እንኮይ፤ ሰንበሌጥ፤ ቡልጋ እና ወደ ምሥራቅ የደረቂት እና አማሪት ወንዞች ከከሰም ወንዝ ጋር ሲቀላቀሉ እንዲሁም የመስኖ ዘንባባ ተራራ እና የመስኖ ማርያም ቤተ ክርስቲያን፤ ሜዳማው የሾላ ገበያ ወደደቡብ ምሥራቅ ደግሞ ከማዶ የክርስቶስ ሰምራ ትውልድ አገር እና ምንጃር ቁልጭ ብለው ይታያሉ። የአካባቢው ቃለ ታሪክ ሥፍራዋ በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አያት ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እንደተመሠረተች ሲያረጋግጥ፤ የልጅ ልጃቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ደግሞ የሸዋ ንጉሥ በነበሩ ጊዜ እስካሁን ድረስ ያለውን ታላቅ የመሣሪያ ምሽግ እና በግቢው ውስጥ ያሉትን አሥራ አንድ ቤቶች እንዳሠሩ ብዙ የጽሑፍና የቃል ታሪኮች እንዲሁም ሕንጻዎቹ እራሳቸው ምስክር ናቸው። ከነኚህ አሥራ አንድ ሕንጻዎች ሁለቱ በ ፲፱፻፸፯ ዓ/ም በሉተራን ኃይማኖታዊ ተልዕኮ ልገሣ ታድሰው የ ጥራ ጥሬ እና የ እህል ምርት ማከማቻ ጎተራ ሆነዋል። ሌሎቹ ቤቶች የወረዳው ፍርድ ቤት፤ የቤተ ክህነት ጽ/ቤት ፤ የወረዳው የፖሊስ ጽ/ቤት እና የመሳሰሰሉ መንግሥታዊ ቢሮዎችን ይዘዋል። በጥቅምት ወር ፲፱፻፱ ዓ/ም አዲስ በተመሠረተው የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እና የራስ ተፈሪ መኮንን መንግሥት ላይ ጦርነት አውጀው ከወሎ የዘመቱትን የልጅ እያሱ አባት ንጉሥ ሚካኤልን ሊከላከል የተሰለፈው የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠራዊት ጥቃቱን ያደራጀው እዚሁ ኮረማሽ ላይ ሲሆን፡ ኋላም ዓርብ ጥቅምት ፲፯ ቀን ራስ ተፈሪና ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሰገሌ ሜዳ ላይ ንጉሥ ሚካኤልን ድል ያደረጉት ከዚሁ ደጀን ቦታ ነው። በዚች ወረዳ ውስጥ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ያስገነቡት የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ይገኛል። በ፳፻፩ ዓ/ም ከ ዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የኤሌክትሪክ መሥመር ተዘርግቶ ለዚች መንደርና ለአካባቢው የቡልጋ ሕዝብ የልማት መስፋፊያ ጮራ ተገልጾለታል። በዘመናዊ መልክ የተገነባው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በተመረቀበት ዋዜማ፣ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ባለው የአሥራ ሦስት ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ ላይ በሳምንት ሁለት ጊዜ፤ ማለትም ሐሙስ እና ቅዳሜ ለገበያ የሚያመች የሕዝብ መመላለሻ የአውቶቡስ መሥመር አገልግሎቱን ጀምሮ፣ በተለይም ቆለኞቹ ምርታቸውን ወደ ገበያ በማቅረብ ላይ የነበረባቸውን የእግር ጉዞ እንግልት ቀንሶላቸዋል። ወደፊትም ገብያቸውን ሐሙስ ገበያ ድረስ ከመሄድ እዚችው ኰረማሽ ላይ ለመመሥረት ተስፋ ሰጥቷቸዋል። ለ የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምረቃ ሥነ ስርዐት የተጓዙ እንግዶች በዚሁ የአውቶቡስ አገልግሎት ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ቢያንስ የሦስት ሰዐት የእግር ጉዞ ቀርቶላቸዋል። ዋቢ ምንጮች የኢትዮጵያ ወረዳዎች
35984
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8B%9D%E1%8C%88%E1%89%A0%E1%8D%A1%E1%89%83%E1%88%8B%E1%89%B5%E1%8D%A1%E1%89%A0%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%8A%85%E1%88%AD%E1%8A%9B%E1%8D%A2
መዝገበ፡ቃላት፡በአምኅርኛ።
መዝገበ ቃላት በአምኅርኛ። በጀርመናዊው ጸሐፊ እዮብ ሉዶልፍ እና ኢትዮጵያዊው አባ ጎርጎርዮስ ትብብር የተደረሰ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ነው። በላቲን ቋንቋ ግምገማ የተካሄደበት ይህ መጽሐፍ በ1690 ዓ.ም. ሊታተም በቅቷል። ደግሞ ይዩ የውጭ ማያያዣ እውነተኛ የቀለም ቅጅውን ለመመልከት ጉግል 17ኛ ክፍለ ዘመን አማርኛ ሥነ ጽሑፍ አባ ጎርጎሪዮስ ኢዮብ ሉዶልፍ
12372
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8A%9D%20%E1%8C%8D%E1%8B%9B%E1%89%B5
ቅኝ ግዛት
ቅኝ ግዛት ማለት የአንድ ሃገር ህዝቦች የሌላውን ሃገር ህዝቦች በቁጥጥር ስር በማዋል የሚደረግ ግዛትን የማስፋፋት ስራት ነው። በዋናነት ቅኝ ግዛት የሚገለጸው ከ15ኛው እስከ 20ኛ ክ/ዘመን ያለውን የአውሮፓ ሀገሮች የአፍሪካን፣ ሰሜን አሜሪካን እና የእስያ ሃገሮች የተቆጣጠሩበትን ዘመን ነው። ጣሊያን ኢትዮጵያ ላይ የቅኝ ግዛት ሙከራ ከአንዴም ሁለት ጊዜ ያደረገች ሲሆን ጀግኖቹ ኢትዮጵያውያ አርበኞች ባደረጉት የሞት ሽረት ተጋድሎ አሸንፈው ባንዲራዋ በነፃነት ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አድርገዋል። የፖለቲካ ጥናት
53339
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%88%B5%E1%88%A3%E1%89%B5%20%E1%8C%A5%E1%8A%93%E1%89%B5
የእንስሣት ጥናት
የእንስሳት ጥናት. ሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ ይህን አድርጓል። ስለዚህ እሱን ለመምሰል ከፈለግህ እንስሳትን ማጥናት አለብህ። እንስሳት አስደሳች ናቸው. ዓሣ ነባሪዎች በዓለም ላይ ትልቁ ዓሣ ነባሪ ናቸው። ያ አስደሳች ነው። በጎች ካፖርትና አልጋ ለመሥራት ሱፍ አላቸው። የአልጋ ስራ ሶስት ሱፍ እና ሶስት እንጨት ነው.
45790
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%8B%AB%E1%88%B1%20%E1%8D%AD%E1%8A%9B
ኢያሱ ፭ኛ
'''ልጅ እያሱ እና ደጃች ተፈሪ መኮንን ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ከበርካታ ሙስሊም ባላባቶች ጋር የተነሳቸው ፎቶግራፎች አሉ፡፡ ለምሳሌ ሀረር ውስጥ ገራድ አብዱላሂ አሊ ሳዲቅ ከሚባል የሀረር ገዥ ቤተሰብ ጋር የተነሳው ፎቶግራፍ በብዙ ስፍራዎች ተለጥፎ አይቼዋለሁ፡፡ አንዳንድ ምንጮች ያ ፎቶግራፍ ልጅ እያሱን ለመወንጀል “” በሚባለው የፈጠራ ጥበብ የተሰራ ነው የሚል ታሪክ ያስነብባሉ። ለምሳሌ “የሃያኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ” የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ “ፎቶውን የሰራው ዝነኛው እንግሊዛዊ ወታደር ቶማስ ለውሬንስ (በዓለም ታሪክ መጻሕፍት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቅ) ነው” በማለት ጽፈዋል። ሆኖም የልጅ እያሱ የልጅ ልጅ የሆኑት ፕሮፌሰር ግርማ ዮሐንስ እያሱ እንደዚህ ዓይነት ፎቶዎች እርግጠኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ከአስር ዓመታት በፊት “ጎህ” ለተሰኘ መጽሔት በሰጡት ቃለ-ምልልስ ገልጸዋል። ፕሮፌሰር ግርማ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገሩ እንዲህ ነበር ያሉት። “ከሼኮችና ከሌሎችም ጋር የተነሱአቸው ፎቶግራፎች ብዙዎች አሉ። ስለዚህ ከቄስ ጋር መነሳትም የተለመደ ነበርና ልጅ እያሱ ሁለቱንም እኩል አድርጎ ለማየት የነበራቸው ፖሊሲ አካል ነው”። (ጎህ መጽሔት፣ ቅጽ 1፣ ቁጥር 5፣ ጥቅምት 1993፣ ገጽ 13) በቅርብ ጊዜ ስለልጅ እያሱና የአፋሮች ግንኙነት የጻፉት አራሚስ ሁመድ ሱሌ ( የተባሉ ምሁር ልጅ እያሱ ከአፋር ባላባቶችም ጋር እኝህን መሰል ፎቶግራፎች መነሳቱን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ፎቶው “ፎርጅድ” አልነበረም ማለት ነው። ሁለቱ ምሁራን (ፕሮፌሰር ግርማ እና አራሚስ ሁመድ ሱሌ) በትክክል እንደገለጹት ልጅ እያሱ ፎቶግራፉን የተነሳበት ዓላማ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ከክርስቲያን ወገኖቻቸው ጋር እኩል መሆናቸውን ለማሳየት በሚል ነው። ታዲያ ልጅ እያሱ በመናፍቅነት በተከሰሰበት ወቅት እንዲህ ዓይነት ፎቶዎች እየተለቀሙ እንደማስረጃ ቀርበውበት ነበር። ይህ የልጅ እያሱ መስለም በዘመኑ ብዙ የተባለለት ቢሆንም እስከ አሁን ድረስ ከአፍ ታሪክ የበለጠ ማስረጃ ሊቀርብለት አልቻለም። የእርሱ የስልጣን ባለጋራ የሆኑት ራስ ተፈሪ መኮንን (አጼ ኃይለ ሥላሴ) በጻፉት “ህይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ” የተሰኘው ግለ-ታሪካቸው ውስጥ የእያሱ ወንጀሎች በማለት ከዘረዘሯቸው አስራ አንድ ነጥቦች መካከል አስሩ አቀራረባቸው ቢለያይም ይዘታቸው አንድ ነው። ይኸውም የልጅ እያሱ መስለም ነው። እነዚህ ነጥቦች የልጅ እያሱን አራት ሴቶች ማግባት፣ መስጊድ ገብቶ መስገድና ቁርአን ማንበብ፣ መስጊድ ማሰራት፣ በኢትዮጵያ ባንዲራ ላይ “ላኢላሃ ኢለላህ” የሚል ጽሁፍ ማስጠለፍ ወዘተ… የመሳሰሉት ናቸው። ይሁንና የልጅ እያሱ የልጅ ልጅ የሆኑት ፕሮፌሰር ግርማ ዮሐንስ “እነዚህ ሁሉ የፈጠራ ክሶች ናቸው” ነው የሚሉት። በተለይ ከተፈሪ መኮንን ጋር ከተዋጉ በኋላ ተሸንፈው በሸሹበት የአፋር በረሃ ያስጠለሏቸው የዘመኑ የአፋር ሱልጣን አቡበከር የወንድም ልጅ የሆኑት ሀንፍሬ አሊሚራህ ስለልጅ እያሱ ፍጹም ክርስቲያን መሆን ምስክርነታቸውን እንደሰጡአቸው ይገልጻሉ። አራሚስ ሁመድ ሱሌ የተባሉት ምሁርም የፕሮፌሰር ግርማን አባባል የሚያጠናክር ምስክርነት ሰጥተዋል። እኝህ ምሁር እንደጻፉት ክርስቲያኑ ልጅ እያሱ በአፋር ምድር ሳለ በክርስትና እምነቱ ከመጽናቱም በላይ አገልጋዮቹ የሰሩለትን የማሽላ ጠላ ይጠጣ ነበር። ስለዚህ ልጅ እያሱ ሙስሊሙን ከክርስቲያኑ ጋር እኩል ለማድረግ ጥረት ከማድረጉ ውጪ ለራሱ ክርስቲያን ሆኖ ነው የኖረው ማለት ነው። ሆነም ቀረ ግን የእያሱ መስለም እርሱን ከስልጣን ለማውረድ የተደረገው ትግል ማጠንጠኛ ሆኖ ነው ያረፈው። ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ክሱ በዚህ ስልት የተቀናበረው እያሱን በህዝቡና በጦር ሀይሉ ዘንድ ለማስጠላት አመቺ መሳሪያ ሆኖ በመገኘቱ ነው ይላሉ። እንደ ፕሮፌሰሩ ገለጻ ልጅ እያሱ ቀጨኔ መድኃኒዓለምን የመሳሰሉ ደብሮችን እንዳልተከለ ሁሉ ከፍ ብሎ የሚወራው መስጊዶችን ማሰራቱ ነው። ለክሱ ማስረጃ አምጡ በሚባልበት ጊዜ “ድሮውንስ ከሙሐመድ ዓሊ ልጅ ምን ይጠበቅ ኖሯል?!” የሚል ቃለ አጋኖ ይደሰኮር ነበር። “ይሁንና” ይላሉ ፕሮፌሰር ባህሩ “ለሸዋ መኳንንት የእያሱ አደገኛነት የፖለቲካ የበላይነታቸውን ከመፈታተኑ ላይ ነበር። ስለዚህ የመናፍቅነቱ ክስ የመነጨው ለሃይማኖት ከመጨነቅ ሳይሆን ለተፈጠረው የፖለቲካ ስጋት ርዕዮተ ዓለማዊ ሽፋን ሆኖ ለማገልገል ካለው አመቺነት ነው።” (ባህሩ ዘውዴ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847-1983፡ ገጽ 134-135) በልጅ እያሱ ላይ የሚደረገው ዱለታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰው ልጅ እያሱ አባቱን “ንጉሥ ሚካኤል” በማለት በወሎና በትግሬ ላይ ባነገሠበት ጊዜ ነው። የሸዋ መኳንንት ራስ ሚካኤል ሰሜን ኢትዮጵያን በቀጥታ ሌላኛውን የኢትዮጵያ ክልል በልጁ በኩል መቆጣጠሩን አሰመሩበት። በመሆኑም የሸዋ መኳንንት “ይህ ወጣት ከቤተ መንግሥቱ ጠራርጎ ሳያስወጣን እንቅደመው” በማለት መሯሯጥ ጀመሩ። የዚህ አድማ ዋነኛ መሪና አቀናባሪ የጦር ሚኒስትሩ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ ስለመሆኑ ምሁራን የሚስማሙበት ሐቅ ነው። ከዚህ በፊት እንዳጫወትኳችሁ ልጅ እያሱ የዕድሜ ልክ ባላንጣው ሊሆን የበቃውን ደጃች ተፈሪ መኮንንን በጋብቻ ጠልፎ ዝም ሊያሰኘው ሞክሮ ነበር። ይሁንና ተፈሪ የእያሱ እህት ልጅ የሆነችውን ወ/ሮ መነን አስፋውን ቢያገባም ሁለቱ ወጣቶች ፍጹም ሊጣጣሙ አልቻሉም። ተፈሪ የዘመኑ ሀብታም ክፍለ ሀገር የነበረው ሀረርጌ የዕድሜ ልክ ግዛቴ ነው ብሎ ያስብ ነበር። እያሱ ደግሞ ተፈሪ በሀረር ሀብት መበልጸጉን አልወደደውም። በተለይም ደጃች ተፈሪ ከባቡር መስመር መዘርጋት ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ የሀገሪቱ መንግሥት ግምጃ ቤት አለኝታ ሊሆን የበቃውን የድሬዳዋ ጉምሩክ ገቢ በቀጥታ ሊቆጣጠረው መቻሉ ለልጅ እያሱ አልተዋጠለትም። ነገር ግን ከዚህ ክስተት በላይ እያሱን በተፈሪ ላይ ያነሳሳው የልጅ እያሱን ስም የሚያጠፋ ሚስጢራዊ ደብዳቤ ለእንግሊዝ መንግሥት ተጽፎ መገኘቱ ነው። ይህንን ደብዳቤ የጻፉት የደጃች ተፈሪ መኮንን ጸሓፊና አንድ ማንነቱ በውል ያልተገለጸ ሌላ ሰው ናቸው። ደብዳቤው በማን ትዕዛዝ እንደተጻፈ ግን የታሪክ ሰነዶች በይፋ የሚገልጹት ነገር የለም። ልጅ እያሱ “ትዕዛዙን ያስተላለፈው ተፈሪ መኮንን ነው” ባይ ነው። በዚህም ወደ አዲስ አበባ አስጠርቶት ስለጉዳዩ ቢጠይቀው ደጃች ተፈሪ ከነገሩ ንጹህ መሆኑን በመሀላ ገለጸለት። ቢሆንም እያሱ አላመነውም። በመሆኑም በሁለቱ መካከል የነበረው ቅራኔ በጣም ተባባሰ። ነገሮች በዚህ ላይ እንዳሉ ልጅ እያሱ ተፈሪ መኮንንን ወደ አዲስ አበባ አስጠርቶት እርሱን ሳያነጋግር ወደ ሀረር ወረደ። ከሀገሬው ህዝብ ጋር ከተማከረ በኋላም ደጃች ተፈሪ መኮንንን ከሀረር ገዥነቱ ሻረው። በምትኩም የከፋ ገዥ አድርጎ ሾመውና በአስቸኳይ ወደ ተሾመበት ክልል እንዲሄድ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጠው። የድሬ ዳዋ ጉምሩክንም ወዳጁ በነበረው ሶሪያዊው ሀሲብ ይዲልቢ ስር እንዲሆን አደረገው። የልጅ እያሱ እርምጃ ተፈሪን በጣም አስደነገጠው። “ይህ መስፍን ሊውጠኝ እያመቻቸኝ ነው” በማለት እንዲያስብም አደረገው። ስለዚህ ደጃች ተፈሪ ወደ ከፋ መሄዱን ተወና አዲስ አበባ ሆኖ የሚበጀውን መንገድ ማፈላለግ ጀመረ። ልጅ እያሱ በትዕዛዝ ላይ ትዕዛዝ ቢያዥጎደጉድለትም ደጃች ተፈሪ ልዩ ልዩ ሰበቦችን እያመካኘ በዋና ከተማይቱ ሰነበተ። የእያሱንም ልብ ለማቀዝቀዝ የስጋ ዘመዱ የሆነውን ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴን (የኋለኛው ራስ እምሩ) የቃልና የጽሑፍ መልዕክት አስጨብጦ ልጅ እያሱ ወደሚገኝበት ድሬዳዋ ላከው። እያሱም የተፈሪን መልዕክት ከሰማ በኋላ እንዲህ አለ። “ደጃች ተፈሪ አሳቡ ሁሉ ሌላ ነው። ያንዳንድ ወስላቶች ነገር እየሰማ ወዲያ ወዲህ ቢል ብርቱ ነገር ያገኘዋል። የአዲስ አበባ ወስላታ ሁሉ ፍሬ ያለው መስሎታል።” (ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ “ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ”፣ በኢትኦጵ መጽሔት የቀረበ ጽሁፍ፣ ጥቅምት 1993፣ ገጽ 37) ይህ የልጅ እያሱ አነጋገር በሁለቱ ልዑላን መካከል የነበረው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ያመላክታል። የእያሱ ንግግር ለደጃች ተፈሪ ጆሮ ከደረሰው በኋላ ተፈሪ በስውር ማድባቱን ትቶ እያሱን ከስልጣን ለመፈንገል የሚዶልቱትን መኳንንት በይፋ ተቀላቀለ። በአስገራሚ ፍጥነትም የዱለታውን መሪነት ከፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ እጅ የሁለቱ ወጣቶች መገፋፋት ይፋ ሆኗል። ቀጣዩ ነገር “ማን ቀድሞ አጥቅቶ የአሸናፊነቱን ዘውድ ይቀዳጃል” የሚለው ብቻ ነበር። የሸዋና የምዕራብ ኢትዮጵያ ባላባቶች በተፈሪ ዙሪያ ተሰልፈዋል። የወሎ፣ የአፋር፣ የኦጋዴንና የሀረርጌ ባላባቶች የእያሱን ጎራ ተቀላቅለዋል። ቢሆንም ሁለቱ ጎራዎች በራሳቸው ወኔ ፍልሚያውን መጀመር አልቻሉም። የመጨረሻውን ፍልሚያ ለማስጀመር ሌላ ስውር እጅ አስፈልጓል። የዘመኑ ታላላቅ ቅኝ ገዥዎች እጅ! እንግሊዝ፣ ኢጣሊያና ፈረንሳይ ሁለቱ ልዑላን ሲጣሉ መጀመሪያ ላይ አይተው እንዳላዩ ሆነው ስራቸውን ማከናወኑን ነበር የመረጡት። ከቆይታ በኋላ ግን የልጅ እያሱ የእኩልነት ፖሊሲ (በሁሉም ኢትዮጵያዊያን መካከል እኩልነትን ለማስፈን በሚል የሚወስዳቸው እርምጃዎች) የነርሱን ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን ተገነዘቡ። የጠረፍ አካባቢ ገዥዎች ከቅኝ ገዥዎች ጋር ለሚያደርጉት ውጊያ የሞራል ድጋፍ የሚሰጥ መሆኑ አስቀየማቸው። በተለይ እንግሊዝ ሶማሌላንድን ከብሪታኒያ አገዛዝ ነጻ ለማውጣት ለ30 ዓመታት ሲዋጋ ለኖረው ሰይድ አብዱሌ ሐሰን የተሰኘ የኦጋዴን ሶማሊዎች ብሔራዊ ጀግና የመሳሪያ ድጋፍ በገፍ ማቅረቡ ቅኝ ገዥዎቹን በጣም አስበረገጋቸው። “ይህ ወጣት ዝም ተብሎ ከተተወ ከዚህ አካባቢ ሊያስነቅለን ነው” እንዲሉም አደረጋቸው። አልፎ ተርፎም ልጅ እያሱ በዘመኑ ከነዚህ ቅኝ ገዥዎች ጋር በአንደኛው የዓለም ጦርነት የሚዋጉትን ጀርመንና ቱርክን የመደገፍ አዝማሚያ ማሳየቱ ሶስቱ ሀያላን እርሱን ከስልጣን ለመንቀል በሚደረገው ትግል በቀጥታ እንዲሳተፉ አነቃነቃቸው። በመሆኑም ሀያላኑ ጳጉሜ 1908 የእያሱን የጠላትነት እርምጃ በማስመልከት በጻፉት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አድማውን መቀላቀላቸው ይፋ ሆነ። ከመጋረጃ ጀርባ ኩዴታ ጠንስሰው ወደ ተግባር መለወጥ ላቃታቸው የሸዋ መኳንንት ኩዴታው ወደ ተግባር የሚለወጥበትንም ስልት አስጨበጧቸው። በተለይ በእያሱ ላይ የቀረበው የመናፍቅነት ክስ ትክክል መሆኑን ለማስረገጥ የእያሱን መስለም የሚያሳዩ ፎቶግራፎችን እያባዙ በአዲስ አበባና በሌሎችም ከተሞች አሰራጩ። ይህ ውጥረት በተፈጠረበት ወቅት ልጅ እያሱ ኦጋዴን ነበር። ከበረሃ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ በቤቱ ላይ የተለኮሰውን እሳት እንዲያጠፋ ወዳጆቹ መልዕክት ቢሰዱለት “የሸዋን መኳንንት በአፉ ላይ ብሸናበት የሚናገረኝ የለም” የሚል የንቀት መልስ መለሰላቸው። በዚህም የስልጣን ፍጻሜውን አቃረበው። ታዲያ እያሱ የጠላቶቹን አሰላለፍ በደንብ የተገነዘበው አይመስልም። በርሱ ሐሳብ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ለማመጣጠን የሚወስዳቸውን እርምጃዎች የሚቃወሙት የሸዋ መኳንንት ብቻ ነበሩ። ነገሩ ግን እንዲያ አልነበረም። ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ እንደሚሉት ልጅ እያሱ ፖሊሲውን በግልጽ ባለማብራራቱ ተራው ህዝብ እንኳ ሀገሩን ለማስለም ሌት ተቀን የሚደክም አድርጎ ነው የወሰደው። በዚህ ላይ እነ ደጃች ተፈሪ በቆንስሎቹ ድጋፍ እያሱ የሚገለበጥበትን የሀሰት ክስ ቀምመው ሲያቀርቡለት ህዝቡም እንደ መኳንንቱ “ድሮስ ከሙሐመድ ዓሊ ልጅ” አለና አረፈው። በመሆኑም ሰፊው ህዝበ ክርስቲያን ለዱለታው ድጋፉን ሰጥቷል። የእያሱ እጣ አሳዛኝ የሚሆነው ድሮ የሚገብሩለት ሁሉ በዚህ ቀውጢ ጊዜ ሲከዱት ነው። በተለይ በስልጣን ዘመኑ መጀመሪያ ላይ በወሰዳቸው ተራማጅ እርምጃዎች ተደስተው በርሱ ዙሪያ የተሰለፉት ለውጥ ናፋቂ ምሁራን በዚህ የፈተና ወቅት የገቡበት ሳይታወቅ ከጎኑ ጠፍተዋል። አንዳንዶቹ ጭራሽ ከርሱ ጎራ ተነጥለው እርሱን ወደ መንቀፍ ገብተዋል። ለዚህም ምሳሌ የሚሆነው የነጋድራስ አፈወርቅ ገብረኢየሱስ ነገር ነው። ነጋድራስ አፈወርቅ ልጅ እያሱን በስልጣን ዘመኑ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያ ተስፋና የለውጥ ሀዋሪያ አድርገው እንዳላንቆለጳጰሱት ሁሉ በዚህ የመከራ ወቅት እንዲህ የሚል ስንኝ መቋጠራቸውን ታሪክ አዋቂዎች በትውስታቸው መዝግበዋል። ሙሐመድ እያሱ ለገመ በራሱ እያሱ ሙሐመድ አልጋ ሲሉት አመድ። (ብርሃኑ ድንቄ፣ ቄሳርና አብዮት፣ 1986፣ ገጽ 30) እንግዲህ የልጅ እያሱ ውድቀት እውን ሆነ። ለሶስት ዓመታት የነገሠበትን አልጋ ከውጪና ከውስጥ በተሸረበበት ሴራ አጣ። መስከረም 17/1909 ዓ.ል. ዘውዲቱ ምኒልክ ንግሥተ ነገሥታት ተብላ ዙፋኑ ላይ ስትቀመጥ ደጃች ተፈሪ መኮንን “ራስ” ተብሎ የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ ሆነ። ይህ ሁሉ ሲከናወን ኢላማ የሌለው ተኩስ አልፎ አልፎ ከመሰማቱ በስተቀር አዲስ አበባ ሰላም ነበረች (አንዳንዶች 17 ሰዎች ሞተዋል በማለት ጽፈዋል)። የልጅ እያሱ ከስልጣን መውረድ ዜና የተሰማው እያሱ ጅጅጋ እያለ ነው። የዜናውን መሰማት ተከትሎ የእያሱ ደጋፊዎች በሚበዙባቸው ሀረርና ድሬ ዳዋ ታላቅ ረብሻ ተነሳ። የደጃች ተፈሪ መኮንን ደጋፊዎች የተባሉት እየተሳደዱ ተፈጁ። እያሱ በከተሞቹ ደርሶ ሁኔታውን ካረጋጋ በኋላ በአሻጥር የተወሰደበትን ዙፋን ለማስመለስ ከከተሞቹ ነዋሪዎች ጋር ተማከረ። በዚህም የህዝቡን ድጋፍ ካገኝ በኋላ በሸዋ ላይ ለመዝመት መዘጋጀት ጀመረ። ይሁንና ዝግጅቱን ሳያጠናቅቅ እነ ራስ ተፈሪ የላኩት 15,000 ጦር ወደ ሀረርጌ እየመጣ መሆኑ ታወቀ። ልጅ እያሱም የሸዋውን ጦር ለመግጠም ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ገሠገሠ። ሁለቱ ሀይሎች ሚኤሶ አጠገብ ተገናኙ። ትልቅ ውጊያም አደረጉ። በጦርነቱ የሸዋው ሀይል ድል ስለቀናው ልጅ እያሱ ወደ አፋር በረሃ ሸሸ። የልጅ እያሱ አባት (ራስ ሚካኤል) የልጁን ስልጣን ለማስመለስ 100,00 ጦር አስከትቶ ወደ ሸዋ ዘመተ። ነገር ግን እርሱም እንደ ልጁ ሰገሌ ላይ ተሸነፈ። ልጅ እያሱ የሰገሌውን መርዶ ከሰማ በኋላ በሽሽት ነው የኖረው ለማለት ይቻላል። በመቅደላና በደሴ አነስተኛ ውጊያዎችን ቢያደርግም በለስ ሊቀናው አልቻለም። ከዚያም ወደ አውሳ በረሃ ሄዶ ከወዳጁ ከሱልጣን አቡበከር ጋር ለጥቂት ዓመታት ኖረ። ነገር ግን ጠላቶቹ እዚያም እንዲቆይ አልፈቀዱለትም። ከሀረርጌና ከወሎ ትልቅ ጦር ቢያዘምቱበት ወደ ትግራይ ሸሸ። በትግራይ ውስጥ ለጥቂት ወራት ከቆየ በኋላ በ1915 ተያዘና ፍቼ ታሰረ። እዚያ እያለ የጎጃሙ ራስ ሀይሉ ተክለሀይማኖት እስር ቤቱን ሰብሮ ሊያስወስደው መሆኑ ስለተወራ ሌላ ቦታ እንዲዛወር ተወሰነ። በመሆኑም ወደ ሀረርጌ ተወስዶ ጋራ ሙለታ አምባ ላይ በተሰራለት እስር ቤት እንዲታሰር ተደረገ። በዚህ አምባ ላይም ለአስር ዓመታት ያህል በእስር ከቆየ በኋላ ጥቅምት 1928 መሞቱ ይፋ ሆነ። ልጅ እያሱ ሚካኤል የስልጣን ዘመኑ በእንቆቅልሽ የተመላ ነው። መንግሥቱን ያስተዳደረበት ዘይቤ፣ ከስልጣን የወረደበት ሁኔታ፣ በእስር ላይ ያሳለፈው ህይወትና የሞተበትም ሁኔታ እንቆቅልሽ ነው። ሌላው ይቅርና የተቀበረት ቦታ እንኳ እስከ አሁን ድረስ በትክክል አይታወቅም። እንቆቅልሽ በእንቆቅልሽ! ተሸዋረጋ የሚወለድ ልጅ እምብዛም አይከፋ እምብዛም አይበጅ ትንሽ ወደኋላ ይቀረዋል እንጅ። ባሽከሮቹ ክፋት ደግሞም ባጋፋሪ ዘውዱ ሲዞር አየን ወደ ልጅ ተፈሪ። እያሱ የሚባል አንድ ልጅ ተወልዶ የአባቶቹን መሬት አደረገው ባዶ። መች ባንተ ይሆናል ምኒልክ ንጉሡ አንተ አስበህ ነበር ልትሰጠው ለእያሱ እንኳን ሊነግሥና ይያዛል ለነፍሱ በራስ መኮንን ልጅ ትጠፋለች ነፍሱ ተጌታ ተፈርዷል ዘውዲቱ ሊነግሱ። የልጅ እያሱ ሰው የአባሻንቆ ሎሌ ተለቀለቀለት መወቂያው ሰገሌ። ሰገሌ ሜዳ ላይ የመጣብን መርዶ በቀኝ እጁ ካራ በግራው ብርንዶ። (የወሎው ሼኽ ሑሴን ጂብሪል ስለልጅ እያሱ ተናግረውታል ከተባለው ትንቢት: ምንጭ፣ ቦጋለ ተፈሪ በዙ፡ “ትንቢተ ሼኽ ሑሴን ጅብሪል”፣ አዲስ አበባ፣ 1985) ከወሒድ ዑመር
16343
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9E%E1%8A%9D%20%E1%89%A3%E1%88%8D%E1%8A%93%20%E1%88%9A%E1%88%B5%E1%89%B5
ሞኝ ባልና ሚስት
ሁለት ሞኝ ባልና ሚስት አብረው ይኖሩ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን እንጨት ለቀማ ወደ ጫካ በመንገድ ሲሄዱ፣ ከጫካ የሚመለስ አንድ ሰው አገኙ። ከዚያም እንዲህ ብለው ነገሩት። እዚያ የሚታየው ቤት ውስጥ እንዳትገባ፣ ረሰተን ሳንዘጋ ወጥተን ነው። እቤት ውሰጥ የምንጠቀምባቸውና ያካበትናቸው ነብረቶቻችን በሙሉ በቤት ውስጥ እዳለ ነው። አደራ ወደዚያ ሒደህ ንብረቶቻችንን እዳትነካ ብለው ጉዟቸውን ቀጠሉ። አንጨት ለቅመው ሲመለሱ በቤታቸው ውስጥ ሰባራ ገል እንኳን የሌለበት ባዶ ቤት ሆኖ አገኙት። ብዙም ሳይቆዩ ቀደም ሲል አደራ እዳትነካብን ያሉት ሰው ቤት ውሰጥ ምንም ሳያሰቀር ዘርፏቸው መሔዱን ሲያረጋገጡ፣ ዱላዎቻቸውን በመያዝ ከጫካ ሲመለስ አግኝተውት የነበረውን ሰው መፈለግ ጀመሩ። ከብዙ ፍለጋ በኋላ ስለደከማቸው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በመንገድ ላይ ሌላ ሰው አገኙ። ያገኙትን ሰው አስቁመው በል የወሰድኸውን ንብረታችንን አሁኑኑ መልስ፣ አለበለዚያ በምታየው በያዝነው ዱላ ቀጥቅጠን እንገድልኻለን ሲሉት፣ ሰዎቹ ስለምን ንብረት እንደምታወሩ አልገባኝም፣ ከገበያ የገዛሁነትን ዕቃ ወደሱቄ አድርሼ ከብቶቼን ለማምጣት ወደ ሜዳው እየወረድሁ ነው። ሲላቸው ጭራሽ ወደሱቅህ ወስደህ ልትቸበችብልን ነው፣ እያሉ በያዙት ዱላ ቀጥቅጠው ገደሉት። ይባላል። [ተሻሻሎ ተፃፈ - ማማሩ በዛብህ - ሚያዚያ/2014 ዓ.ም.] [መደብ:የኢትዮጵያ ቀልዶች]
43708
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D
ማርያም
ድንግል ማርያም በክርስትናና፣ በእስልምና እምነቶች መሠረት የከበረችው የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። በክርስትና እምነት የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ማለትም የወልድ እናት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር ኃይል በሥላሴ ምርጫ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንደ ወለደችው ይታመናል ። በእግዚአብሔር ህሊና ከፍጥረት በፊት እንደነበረች ኦዘ-ም፡፫ ቁ፡፲፭ ያስረዳል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማርያምን በጣም ከመወደዷ የተነሳ ከ፻ በላይ በሰየመቻት ስሞቿ ትጠራታለች (የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች):: አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ። ሙስሊሞች ደግሞ መሪማ የኢየሱስ (ኢሳ) እናት ይልዋታል። በአለም ላይ ፫ ታላላቅ እምነቶች ዘንድ እስዋም ልጅዋም ትልቅ ክብርና ቅድስና በተለይ ለልጇ መመለክ ገንዘባቸው ነው። >ውዳሴ ማርያም እንድምታ >ቅዳሴ ማርያም እንድምታ >ከድረገጾችዎ አንዱን ለማየት እዚህላይ ይጫኑ ወይም ይህን ይጫኑ በክርስትና እምነት ድንግል ማርያም ሰው ሁኖ የመጣዉ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ከእግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንዱ ተወላዲ ማለትም (ወልድ) ሲሆን ፣ ወላዲ ደግሞ (አብ) ነው ፣ ቀጥሎም ሰራጺ (መንፈስ ቅዱስ) ይሆናል ፤ በተጨማሪ ወልድ ጌታ ወይም ክርስቶስ፡መሢሕ ይባላል። እናቱ ማርያም እግዚአብሔር የተባለውን ወልድ ለመውለድ ስለ ተመረጠች እና ብቁ ሆና ስለተገኘች ከሴቶች ሁሉ ይልቅ ብጹዕት ፣ ቅድስት ፣ በግሪክ ቴዎቶከስ ማለትም የእግዚአብሔር እናት ትባላለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከ 34 ዓ.ም ጀምራ ክርስትናን በኢትዮጵያ ምድር የሰበከች ጥንታዊት ቤተክርስቲያን ሥትሆን ምድቧም ከ ኦርዮንታል አብያተ ክርስቲያናት ነው:: እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥላሴ አካላት አንዱ ወልድ፣ አምላክ ነው::ይህ አምላክም ወይም እግዚአብሔር ወልድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ::በሌላ አገላለጽ አምላክ ሰው ሆነ::በዚህም ምክንያት ቅድስት ድንግል ማርያምን የጌታ እናት ወይም የእግዚአብሔር እናት(ወላዲተ አምላክ) ትባላለች:: ቤተክርስቲያኗ ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም አምላክ ፣ ወልደ አምላክ ፣ ወልደ ማርያም ፣ ወልድ፣ ቃል ብላ ትጠራዋለች:: ድንግል ማርያምን ደግሞ እመቤት ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ፣ እግዝእትነ ማርያም ፣ የጌታ እናት ፣ ወላዲተ አምላክ ፣ ቅድስት፣እመ ብርሃን ፣ እመ አምላክ፣ንጽሕተ ንጹሃን ቅድስተ ቅዱሳን፣ጽዮን ወዘተ በማለት ትጠራታለች::ቅድስት ድንግል ማርያምን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከአዳም በደል ወይም ከጥንተ አብሶ ነጻ ሆና በአዳም ባህርይ እንደ እንቁ ስታበራ የኖረች አደፍ ጉድፍ የሌለባት ፣ ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ የነጻች ፣ እንደሆነች ታምናለች። በሌላው ወገን ጥንተ አብሶ ነበራት ለዚህም ማስረጅያ "ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም" ተብሎ የሚጠራው በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ቁጥር 47 እግዚአብሔርን "መድኃኒቴ" ብላ ማመስገነዋ ነው የሚሉም አሉ ። ሁለቱም ወገን ግን እግዚአብሔር ወልድ ሥጋዋን ከተዋሃደ በፊት እንዳነጻት ማደሪያው እንድትሆን እንዳስጌጣት ከወለድችሁም በኋላ በድንግልኗና በንፅህኗ እንደኖረች፣ ለዘለዓለም በዚሁ ሁኔታ ጸንታ እንደምትኖር ያምናሉ። ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነች፣ የሰማይ የምድር ንግስት ፣ እንደሆነች ቤተክርስቲያን ታስተምራለችና ። አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ። ይህም መንፈስ ቅዱስ የሞላባት ወልድ የተዋሀዳት አብ የመረጣት ፍፁምነት የተገለፀባት ከሰው ሁሉ ተለይታ መከበር የሚገባት መሆኑዋን አረጋግጦ ያስረዳል ። ጸሎተ ማርያም ሉቃስ ም፩ ፣ ፵፯ - ፶፭ ነፍሴ፡ጌታን፡ታከብረዋለች፥መንፈሴም፡በአምላኬ፡በመድኀኒቴ፡ሐሴት፡ታደርጋለች፤ የባሪያዪቱን፡ውርደት፡ተመልክቷልና።እንሆም፥ከዛሬ፡ዠምሮ፡ትውልድ፡ዅሉ፦ብፅዕት፡ ይሉኛል፤ ብርቱ፡የኾነ፡ርሱ፡በእኔ፡ታላቅ፡ሥራ፡አድርጓልና፤ስሙም፡ቅዱስ፡ነው። ምሕረቱም፡ለሚፈሩት፡እስከ፡ትውልድና፡ትውልድ፡ይኖራል። በክንዱ፡ኀይል፡አድርጓል፤ትዕቢተኛዎችን፡በልባቸው፡ዐሳብ፡በትኗል፤ ገዢዎችን፡ከዙፋናቸው፡አዋርዷል፤ትሑታንንም፡ከፍ፡አድርጓል፤ የተራቡትን፡በበጎ፡ነገር፡አጥግቧል፤ባለጠጋዎችንም፡ባዷቸውን፡ሰዷቸዋል። ለአባቶቻችን፡እንደ፡ተናገረ፥ለአብርሃምና፡ለዘሩ፡ለዘለዓለም፡ምሕረቱ፡ትዝ፡እያለው፡ የቅድስት ድንግል ማርያም ትውልድ ቅድስት ድንግል ማርያም አባቷ ኢያቄም እናቷ ደግሞ ሃና ይባላሉ::የተፀነሰቸው በእለተ እሁድ ነሐሴ ፯ ቀን ሲሆን የተወለደቸውም ግንቦት ፩ ነው::እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም የተወለደችበት እለት በአባት እናቷ ቤት ፍስሃ ደስታ ተደረገበት ፤ ቤቱንም ብርሃን መላው ፤ በ፰ኛውም ቀን ማርያም ብለው አወጡላት::ስለምን ማርያም ብለው አወጡላት ቢሉ:እነሆ በዚህ አለም ከሚመገቡት ሁሉ ምግብ ለአፍ የሚጥም ለልብ የሚመጥን ማር ነው:በገነትም በህይወት የተዘጋጁ ጻድቃን ቅዱሳን ያም የሚባል ምግብ አላቸው ::ከዚ ሁሉ የበለጥሽ የከበርሽ ነሽ ሲሉ ስለዚህ ማርያም ብለው አወጡላት:: እመቤታችን ማርያም ለእናት ለአባቷ አንዲት ስትሆን የተወለደቸው በጸሎት በመሆኑና የስለት ልጅ በመሆኗ እናትና አባቷ ለእግዚአብሔር በተሳሉት መሰረት ፫ ዓመት ሲሞላት ወደ ቤተመቅደስ ወሰደው ለካህኑ ለዘካርያስ አስረከቧት::እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደች በሦስት ዓመቷ እናቷ ሐና አባቷ ኢያቄምን፡- “ይህች ብላቴና ሆዷ ዘመድ ሳይወድ፣ አፏ እህል ሳይለምድ “ለእግዚአብሔር በገባነው ቃል መሠረት ወስደን ለቤተ መቅደስ አንሰጣትምን?” ‘የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሳ’ እንዲሉ አንዳች ነገር ብትሆንብን ከልጃችንም ከእግዚአብሔርም ሳንሆን እንዳንቀር” አለችው፡፡ እርሱም፡- “ፍቅርሽ ይለቅልሽ ብዬ ነው እንጂ እኔማ ፈቃዴ አይደለምን?” አላት፡፡ወላጆቿ ይህን ተነጋግረው እንዳበቁ ሕጻን ልጃቸውን ማርያምን ወስደው ለቤተ መቅደስ ሰጧት፡፡ በዚያን ጊዜ የነበረው ሊቀ ካህናት ዘካርያስ ይባላል፤ እርሱም ስለ ምግቧ ነገር ሊያስወስን መጥቅዕ (ደወል) ደውሎ ሕዝቡን ሰብስቦ እየተወያዩ ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል የሰማይ ኅብስትና የሰማይ ጽዋ ይዞ ከሰማይ ወርዶና ረብቦ ታየ፡፡ብላቴናይቱንም መልአኩ ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ደግሞ ጋርዶ በሰው ቁመት ያህል ከምድር አስለቅቆ ከፍ አድርጓትና መግቧት ዐረገ፡፡ ከዚህ በኋላ ካህናቱና ሕዝቡ “የምግቧ ነገር ከተያዘልንማ ከሰው ጋር ምን ያጋፋታል” ብለው ሕጻን ማርያምን ከወላጆቿ ተቀብለው ወደ ቤተ መቅደስ አግብተዋት በዚያ ፲፪ ዓመት ኖራለች፡፡ይህም ሲደመር ጠቅላላ ፲፭ ዓመት ሆናት ማለት ነው::በዚህ ስዓት አይሁድ ከበተመቅደስ ትውጣልን ብለው አመለከቱ ፤ ለጻድቁ ለቅዱስ ዮሴፍም እንዲጠብቃት ታጨች ፤ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አበሰራት::በ ፲፭ አመቷ እግዚአብሔር ወልድን ፀነሰች:: የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች:- የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን «እስመ ስሙ ይመርህ ኀበ ግብሩ» በማለት ስም ግብርን ሁኔታን ማንነትን ይገልጻል ይላሉ፡፡በዚህም መሰረት ቤተክርስቲያኗ ለስመ ድንግል ማርያም ዘርፍ /ቅጽል/ አልያም ምትክ አድርጋ የምትጠቀምባቸው ምሥጢራዊና ረቂቅ ትርጉም ያላቸው ንጽሕናዋን፣ ቅድስናዋን፣ ድንግልናዋን፣ ብፅእናዋን ወዘተ የሚመሰክሩ በርካታ ስሞች ሰይማላታለች፡፡ከነዚህም መካከል ከብዙ በጥቂቱ:ምልዕተ ጸጋ ፣ እምነ /«ም» ጠብቆ ይነበብ/ ጽዮን ፣እመ ብርሃን ሰአሊተ ምሕረት ፣እመቤታችን ፣ቤዛዊተ ዓለም፣ ወላዲተ አምላክ ፣ኪዳነ ምሕረት ወዘተ.. ቅድስት ድንግል ማርያም በ 64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ እንደ ልጇ በሦስተኛው ቀን ማረጓን ቤተክርስቲያኑ ታስተምራለች:: ቅድስት ድንግል ማርያም በኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተአምረ ማርያም በሚባለው የጸሎት መጽሓፍ ቅድስት ድንግል ማርያም በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው በሕፃንነቱ ልጇን ጌታ ኢየሱስን እንዳይገድሉባት ከምድረ እስራኤል ስትሸሽ በግብጽ አልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ደርሳለች። ጌታ ኢየሱስ በእግሩ በመረገጡ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ከአረጋዊው ከቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ከዘመዳቸው ከቅድስት ሰሎሜ ጋር በእንግድነት በመቀመጡ ምድረ ኢትዮጵያን ባርኳታል። እመቤታችንን በጭንቀቷ ሰዓት ይቺ ምድርና ሕዝቦቿ ስለተቀበሏት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአደራነት ወይም በአሥራትነት ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደሰጣት ቤተ ክርስቲያኒቷ ታስተምራለች። በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ዘንድ እጅግ በጣም ልዩ ተወዳጅነትና ፍቅር ያላት በተለምዶ እንኳን እምዬ እናታችን እመቤታችን ወይም በመዓረግ ስሞቿ ኪዳነ ምሕረት ወላዲተ አምላክ እመብርሃን ተብላ ትጠራለች። ከኃይማኖትም ባሻገር በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ባህልም ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ ቦታ አላት። ለምሳሌ አንዲት እርጉዝ ሴት ልትወልድ ስትል «ድንግል ማርያም ትቅረብሽ» ስትወልድም «እንኳን ማርያም ማረችሽ» በአራስ ቤትም ሳለች «ድንግል ማርያም በሽልም ታውጣሽ» ትባላለች። አንድ ሰው ገላው ላይ ሲወለድ የነበረ ጥቁር ምልክት ቢኖረው «ድንግል ማርያም እዚህ ስምሃለች» ይባላል። >ጾመ ፍልሰታ ፍልሰታ የሚለው ቃል የሚገልጸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለቆ መሔድን መሰደድን መፍለስን ያመለክታል። ይህም የእመቤታችንን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ስር ከነበረበት መነሳቱን ለማመልከት ይነገራል። ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን መነሳቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙ ከነሐሴ 8 ቀን አስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ሲጾም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው። ኃይማኖታዊ መሠረት እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተጸንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች# <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት : ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እምቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር : ዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷ ዓመት ዕድሜዋ በ፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በእድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፰ ነው የመልክአ ማርያም ቁጥርም ፷ ነው። ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሳ፣ አረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ፡ ደግሞ አሁን እሷም ተነሳች፣ አረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል :: የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑሯቸዋል ። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ ስከ ነሐሴ ፲ ቀን ድረስ ሁለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በ ሦስተኛውም ቀን ተነስታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ስርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሳኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንንም ትንሳኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው አረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብ» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነስታ አርጋልች» በማለት ሁኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህገረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው። በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሳኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከሁለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሳኤዋንና እርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ አዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ። የእመቤታችን ትንሳኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ዉሀ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምዕመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነስ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እምቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች። ንጉስ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፩ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውብቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ ወዳጄ ...ዉበቴ»" የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት # ክቡር ዳዊት መዝሙር ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን እረፍቷን ትንሳኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም። የማርያምን ድንግል ሁና እየሱስን ወይንም እነሱ እንደሚሉት ኢሳ (አ.ሰ)ን እንደወለደች ብሎም በነሱ እምነት አራት ተብለዉ ከተጠቀሱ ምርጥ ሴቶች ዉስጥ አንድዋ ነች። ነገር ግን ኢሳን የአላህ መልዕክተኛ ነዉ ሲሉት፣ አላህም ፈጣሪዉ እንጅ ልጁ አይደለም ባዮች ናቸው። በቁርአን ምክንያት አምላክ አይወልድም አይወለድም፤ ይህም ለአላህ የማይገባው ሥራ ነው ይላሉ።
50779
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%89%B1
መቱ
መቱ በደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የንግድ ከተሞች መካከል አንዷ ስትሆን በኦሮሚያ ክልል የኢሉባቦር ዞን ዋና ከተማ ነች። ከሶር ወንዝ አጠገብ የምትገኘው ይህች ከተማ 8 ° 18′ 160 35 ° ላቲትዩድና ሎንጊትዩድ እንዲሁም 1605 ሜትር ከፍታ አላት። መቱ አዲሱ ህገ-መንግስት እስከ ፀደቀበት ጊዜ ድረስ ከ1978 ዓ/ም በፊት የቀድሞው ኢሉባቦር ክፍለ አገር ዋና ከተማ ነበረች ። መቱ ከ1930ዎቹ ጀምሮ የቡና ንግድ ዋና ገበያ ስለሆነች ከአካባቢው አርሶአደሮች ሰብሉን ለመግዛት በከተማዋ በርካታ የውጭ ዜጎች ይኖራሉ ። ከዚያው ጊዜ ጀምሮ ከተማዋ ከጎሬ እና አዲስ አበባ ጋር በስልክ የተገናኘች ነች። የከተማዋ የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጭ በአቅራቢያው የሚገኘው የሶር ወንዝ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው ። ኦሮሚያ ክልል
53968
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%88%9B%E1%88%86%E1%8B%AD%20%E1%8C%BD%E1%8C%8C%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A9
እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ
እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ (ከምንኩስናቸው በፊት ይጠሩበት በነበረው ስማቸው የውብዳር ገብሩ) ታኅሣሥ 4 ቀን 1915 ዓ.ም. አዲስ አበባ ነበር የተወለዱት። ገና የስድስት ዓመት ሕጻን ሳሉ ከታላቅ እኅታቸው ከሥንዱ ገብሩ ጋር ወደ ስዊትዘርላንድ ሔደው “ሞንት ሚራል” በተባለ አካዳሚ ትምህርት ይጀምራሉ። በትምህርት ቤቱ ውስጥ ከቀለም ትምህርቱ በተጓዳኝ ቫየሊን እና ፒያኖ አጥንተዋል። የውብዳር ገብሩ 11 ዓመት ሲኾናቸው፣ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ። በዚህ ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወራ ነበር። ከንቲባ ገብሩም መላ ቤተሰባቸውን ይዘው ወደ ጎሬ ለመሠደድ ተገደዱ። የእኅቶቻቸው እና የእርሳቸው ትምህርት ተቋርጦ ከደስታ ገብሩ እና ከገነት ገብሩ ጋር በስደት ቆይተዋል። እማሆይ ጽጌ ማርያም የጽሕፈት መኪና መምታት ተምረው ስለነበረ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ለጥቂት ጊዜ በጸሐፊነት ሠርተዋል። ሙዚቃን በከፍተኛ ደረጃ ለመማር ቁርጥ ውሳኔ ላይ የደረሱት ከዚህ ጊዜ በኋላ ነበር። ይህን ውሳኔያቸውን በማስታወሻቸው እንዲህ ሲሉ አስፍረውታል። “እንደገና አባባን አስቸግሬ፤ ጃንሆይን እንዲለምኑልኝ አስደርጌ ወደ ውጪ ሀገር ሔጄ የሙዚቃ ትምህርቴን እንድቀጥል ተፈቅዶልኝ ወደ ካይሮ ሔድኩኝ። ትካዜ እንደ ጓደኛ አይለየኝም ነበር። ብዙ የፍቅር መጻሕፍትን ስለማነብ ስለ ሰው ልጅ ጥሩ አስተሳሰብ አልነበረኝም። ሰው አታላይ ነው፣ ውሽታም ነው በማለት ሰውን እምብዛም አላምንም ነበር።” ይላሉ እማሆይ። ለከፍተኛ የሙዚቃ ትምህርት ወደ ግብጽ ሔደው “ቬሉኑስ ኮንሰርቫቶሪ ኦፍ ሉቺኒያ” በተባለው የሙዚቃ ትምህርት ቤት አሌክሳንደር ኮንትሮቪች በተባለ ፖላንዳዊ የሙዚቃ መምህር ሥር ትምህርታቸውን ተከታትለዋል። አሌክሳንደር ኮንትሮቪች ኋላ ላይ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ፤ በዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትዕዛዝ የክብር ዘበኛ ሙዚቃን አደራጅቶ፤ በ1948 ዓ.ም. የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኦርኬስትራ ሙዚቀኞች በመምራት ከፍተኛ አስተዋጽዖ የነበረው የሙዚቃ ባለሙያ ነበር። እማሆይ ከትምህርታቸው በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው የሙዚቃ ቅማሬዎቻቸውን ማዘጋጀት ጀመሩ። “በዚህ ጊዜ ውስጥ” ይላሉ ወንድማቸው ኮ/ል ዳዊት ገብሩ። “በዚህ ጊዜ ውስጥ ከዕለታት አንድ ቀን የንጉሣዊ በተሰብ የኾኑ አንድ ሰው ለኹለት ዓመት ትምህርት ወደ እንግሊዝ እንድትሔድ የቅድሞሽ ቢከፍሉላትም፣ የይለፍ ወረቀቱን ኹሉ ይዛ ሳለ፣ ‘ከበላይ የመጨረሻ ፈቃድ አልተገኘም’ ተብላ ቀረች። ይህ ልክ በእኔ የደረሰብኝ ዓይነት ነው፤” ይላሉ ኮ/ል ዳዊት ገብሩ በመጽሐፋቸው። “አባቴ በ1922 ዓ.ም. …ለትምህርት ወደ ጀርመን ሊልኩኝ ቢያስቡም፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ሳህሌ ጸዳሉ ተመሳሳይ ዕግድ በማድረግ የትምህርት ዕድሌን አጨናግፈውብኛል። እኔ ብዙ ስላየሁ ቻልኩት እኅቴ ግን አልቻለችውም።” በማለት አጋጣሚውን በኀዘን ይገልፁታል። በወጣትነታቸው በወሰኑት በዚህ የምንኩስና ሕይወት አባትታቸው እና እናታቸው ከፍተኛ ኀዘን ላይ ወደቁ። ብዙም አልቆዩ፤ እማሆይ በመነኮሱ በኹለት ዓመታቸው አባታቸው ከንቲባ ገብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ከዚያ በኋላ እማሆይ ሙሉ ጊዜያቸውን ለሙዚቃ ቅማሬ እና ለመንፈሳዊው ግልጋሎት ብቻ ወሰኑ። የመጀመሪያ ቅማሬያቸውን ለማስቀረጽ ወሰኑ። የዚህ ሙዚቃ የማስቀረጹ ውሳኔ፤ የራሱ የኾነ ምክንያት ነበረው። “ቅማሬዬን በሸክላ ለማስቀረጽ ያነሳሳኝ ዐቢይ ምክንያት ነበር። ጎንደር በነበርኩበት ጊዜ በየቤተክርስቲያኑ የማይጠገበውን ማኅሌት ሰምቼ ስመለስ፤ እደጅ የአገር ቤት ተማሪዎች በየሜዳው ጥቅልል ብለው ተኝተው አያለሁ። ብጠይቅ ሌሊት ቤተክስቲያን ያደሩ ናቸው፣ ጥግና ቤት የሌላቸው። በዚህም ልቤ ተነካ፣ አዘንኩ። እኔ ሀብት የለኝ፤ ያለችኝ ያቺው ሙዚቃዬ። ስለዚህ አስኪ ሙዚቃዬን ላስቀርጽ እና ሽያጩን እነዚህ ልጆች ገብተው በነጻ የሚያድሩበት ቤት ላቋቁም አልኩ። መከረኞቹም አሉ ሸክላውም ተቀረጸ። ነገር ግን ተንኮለኛ አይጠፋምና ለሽያጭ ከመቅረቡ በፊት እንጉሡ ጆሮ ስለ ደረሰ ሐሳቡ መና ቀረ መሞከሬ ግን አልቀረም።” ይህንን በመሰለ “እርሳቸው ያልተረጋጋ” በሚሉት ሕይወት እስከ 1975 ዓ.ም. ከቆዩ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሔዱ። እማሆይ በደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት ከሦስት ዐሥርት ዓመታት በላይ ኖረዋል። ላለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት ስላሉበት ኹኔታ ምንም ዓይነት ዐዲስ ዜና ተሰምቶ ስለማይታወቅ በሕይወት መኖራቸውን የተጠራጠሩ ብዙዎች ነበሩ። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን፣ ሥራዎቻቸው የታላቅ ሙዚቀኞችን ቀልብ መሳብ ጀመረ። በወጣትነታቸው ብዙ መሥዋዕትነት የከፈሉለት፣ ማንም ልብ ሳይለው የዘሩት የረቂቅ ሙዚቃ የቅማሬ ዘር፤ ዛሬ ላይ ብዙዎች እርሳቸውን ብለው፣ የእርሳቸውን ሙዚቃ እንዲያጠኑ እያደረገ ነው። የዓለም ታላላቅ የዜና የዓለም ታላላቅ የዜና አውታሮችም ከ2013 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ ስለ እማሆይ ሙዚቃዎች አዳዲስ ነገሮችን ማቅረብ ጀምረዋል። በ2013ቱ የኢየሩሳሌም የባህል ክብረ በዓል ከተከናወኑ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በእማሆይ ሕይወት ታሪክ እና የሙዚቃ ሥራዎች ዙሪያ ያተኮሩ ተግባራት ነበሩ። ባለኹለት ጥራዝ መጻሕፍትን በእማሆይ የሕይወት እና የሙዚቃ ሥራዎች ላይ መታተም ችለዋል። የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን በኖታ የያዘ ባለ 146 ገጽ መጽሐፍም ታትሟል። እንደ ናዳቭ ሀርፐር ያሉ የእስራኤል ታላላቅ ሙዚቀኞች ስለ እማሆይ ሥራዎች ጥልቀት ምስክርነት እየተሰጡ ይገኛሉ። በወጣትነት ዕድሜ የተሠራ የአስተውሎት ሥራ የኋላ ኋላ የራሱ ትንሣኤ ይኖረዋል። የእማሆይ ጽጌ ማርያም ሕይወት በሙዚቃ በብዙ ተፈትነዋል። ከመንፈሳዊ ሕይታቸው ጋር የሚቃረን የሚመስላቸው አንዳንዶች፣ ሙያቸውን እና የሙዚቃ ፍቅራቸውን አጣጥለውባቸዋል። የሕይወታቸውን አቅጣጫ ፍጹም በማይገመት መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም ነው። ከሀገራቸው አሰድዶ በሌላ በዓት ተነጥለው እንዲኖሩ ያደረገ ነው። ግን ከዚህ ኹሉ በኋላ የስማቸውን ትንሣኤ ዕድለኛ ኾነው፣ ከዘጠኝ ዐሥርት ዓመታት በኋላ በታላቅ ክብር ከብዙዎች ብድራቱን አግኝተውበታል። በቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር ቤት ከንጉሠ ነገሥቱ ብቻ በቀር ማንም በትዕግሥት ሊያዳምጠው ያልቻለው ኮንሠርታቸው፤ ሐምሌ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ሥራዎቻቸውን በሚጫወቱ ወጣቶች አማካኝነት ከ1800 በላይታዳሚያን በተገኙበት በአድናቆት ተመልካች አግኝቷል። ገና ያልተደመጡት አዳዲሶቹ ስድስት ክላሲካል ቅማሬዎቻቸው በትልቅ ኦርኬስትራ ሊቀርቡ ዝግጅት እየተደረገ ነው። ውልደት እና እድገት የውብዳር ገብሩ 11 ዓመት ሲኾናቸው፣ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ። በዚህ ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወራ ነበር። ከንቲባ ገብሩም መላ ቤተሰባቸውን ይዘው ወደ ጎሬ ለመሠደድ ተገደዱ። የእኅቶቻቸው እና የእርሳቸው ትምህርት ተቋርጦ ከደስታ ገብሩ እና ከገነት ገብሩ ጋር በስደት ቆይተዋል። ዚህ በኋላ የወጣቷ፣ በሙዚቃ ብዙ የመግፋት ጉጉት የነበራት የየውብዳር ገብሩ የሕይወት መስመር ሌላ አቅጣጫ ያዘ። የዚህ ዕድል መሰናከል ምን እንዳስከተለ የእማሆይ ማስታወሻ እንዲህ ይገልፀዋል።“የመጨረሻ ዕድሌ በመሰበሩ፣ መንፈሴ ተሰባብሮ፣ ሞትን ብቻ ፈለግኹ። ከ15 ቀን በላይ እህል ውኃ ሳልቀምስ ጥቁር ባዶ ቡና ብቻ እየጠጣሁ ስሰነብት፤ ያው የሞት ጥላ በላዬ ላይ ሲያንዣብብ፣ የመጨረሻ ቁርባን እንዲሰጠኝ ጠይቄ አንድ ቄስ እስከነበርኩበት ምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም አጠገብ እነበረው ሆስፒታል ድረስ መጥተው አቆረቡኝ። የዚህ ዓለም ፍቅር እና የመኖር ፍላጎት ከኅሊናዬ ፈጽሞ ተወገደ፤” ይላሉ። በቤተሰቦቻቸው ርብርብ ሕይወታቸው በቤተሰቦቻቸው ርብርብ ሕይወታቸው ተርፎ ጥቂት የተጽናኑት እማሆይ፤ ቤተሰቦቻቸውን አዘናግተው ወደ ግሼን ደብረከርቤ ተጓዙ። “ለኹለት ዓመታት አንድ ቀን ሳይቋረጥብኝ ሰዓታቱንም፣ ቅዳሴውንም ሥራውንም ከዘለቅሁት በኋላ ስቆረጠልኝ። የኹለት ወር ፈቃድ እና ደመወዝ ይዤ ከአንድ ዓመት በፊት ከእናቴ ከወ/ሮ ካሣዬ ጋር ሔጄበት ወደነበረው ወደ ግሼን ማርያም ተጓዝኩ። ወደዚያ ስሔድ ግን ነፋስ መለወጥ አለብኝ ብዬ አባባን እና እናቴን አስፈቅጄ ነው። እነርሱ ምንም አልጠረጠሩም ነበረና ለሽርሽር የምሄድ መስሏቸው ፈቀዱልኝ።” ይላሉ። ከዚያም ለግሼኑ አቡነ ሚካኤል መመንኮስ እንደሚፈልጉ ይነግሯቸዋል። “ዘመዶችሽ በኋላ መጥተው ቢያስቸግሩስ?” ቢሏቸው፤ “በነፍሴ የሚያዝባት ሰው ካለ እኔ ሌላ የለም።” ስላሉዋቸው ምንኩስናው ተፈቀደላቸው። ከምንኩስናው በፊት በጸጉር የመላጨቱ ሥነ ሥርዓት ወቅት የተከሰተው ነገር እዚህ ላይ ሳይጠቀስ አይታለፍም። “ከእንክብካቤ እቅፍ ውስጥ ወጥቶ ተሞነጫጭሮ ትከሻዬ ላይ የተዘረገፈውን ፀጉሬን ዐይተው አቡነ ሚካኤል፤ ‘ይህ ጠጉር ደግሞ መላጨት አለበት፤ ’ አሉኝ። ቀጠል አድርጌ ኧረ እርሱስ ግድ የለም አልኳቸውና አባ ደሳለኝ የሚባሉትን የደሴ ግቢ መርቆርዮስ አስተዳዳሪ እንዲላጩኝ ጠየቅኳቸው። አባ ደሳለኝ ሲላጩኝ እጃቸው ለብዙ ጊዜ ሲያርፍ ‘ምን ኾነው ነው?’ ብዬ ዘወር ብዬ ሳያቸው፤ ዕንባ አውጥተው ሲያለቅሱ ዐየሁና ‘ምነው አባቴ ምን ኾኑ?’ ብላቸው፤ ‘አባቴ እንኳን ሲሞት አላለቀስኩም፣ እንዲያው አዝኜ ነው’ አሉኝ። እኔም ‘ምን ለፀጉሩ ነው ይህንን ያህል የሚያዝኑት’ ብዬ ቀለድኩባቸው። እንኳንስ ፀጉር ሌላም በነበረኝ ለጌታዬ የምሰጠው አልኳቸው።” ይላሉ። በዚህ ዕለት ማግስት የምንኩስና ሥርዓቱ ተፈጸመላቸው። ይህ ሲኾን ዕድሜያቸው 20ዎቹ መጀመሪያ ላይ ነበር። የዓለም ታላላቅ የዜና አውታሮችም ከ2013 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ ስለ እማሆይ ሙዚቃዎች አዳዲስ ነገሮችን ማቅረብ ጀምረዋል። በ2013ቱ የኢየሩሳሌም የባህል ክብረ በዓል ከተከናወኑ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በእማሆይ ሕይወት ታሪክ እና የሙዚቃ ሥራዎች ዙሪያ ያተኮሩ ተግባራት ነበሩ። ባለኹለት ጥራዝ መጻሕፍትን በእማሆይ የሕይወት እና የሙዚቃ ሥራዎች ላይ መታተም ችለዋል። የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን በኖታ የያዘ ባለ 146 ገጽ መጽሐፍም ታትሟል። እንደ ናዳቭ ሀርፐር ያሉ የእስራኤል ታላላቅ ሙዚቀኞች ስለ እማሆይ ሥራዎች ጥልቀት ምስክርነት እየተሰጡ ይገኛሉ። የእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ህልፈትን ተከትሎ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ "ዝክረ እማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ" የተሰኘ የመታሰቢያ መረሃ ግብር በቀጣዩ 15 ቀናት ውስጥ እንደሚዘጋጅ መምህር ዕዝራ አባተ ለቢቢሲ ገልጸዋል። በዚህ የመታሰቢያ መረሃ ግብር ላይ "በተቻለ መጠን እማሆይን ጽጌማሪያም የሚያስታውስ መሰናዶ በያሬድ ሙዚቃ ትምህር ቤት ይከናወናል" ብለዋል መምህሩ። ይህ መሰናዶ "ወጣቶች እንዲያስታውሷቸው" ያለመ እንደሆነ ዕዝራ ተናግረዋል። አያይዘው እንደገለጹት የመሰናዶው ዋነኛ ይዘት የእማሆይ ጽጌማርያም ሙዚቃዊ አበርክቶ ይሆናል። "በዋነኛነት ትምህርታዊ አበርክቷቸው ላይ የሚያተኩር ይሆናል። በኢትዮጵያ ሙዚቃ ያላቸውን አስተዋጽኦም ይዳስሳል" ሲሉ አስረድተዋል። በዚህ የመታሰቢያ መረሃ ግብር ላይ ሙዚቀኞች እንዲሁም መምህራን ይሳተፉበታል ተብሎ እንደሚጠበቅም መምህር ዕዝራ አባተ ለቢቢሲ ገልጸዋል። ታዋቂ ስራዎች ማያ ከእማሆይ አሳዛኝ ቅንብሮቻቸውን እንደምትወድ ብሎም ሦስቱን ለይታ እንደምትወዳቸው ትናገራለች። "በእርግጥ ይሄ አሁን ላይ ያለ እንጂ እንደጊዜው፣ እንደ አየር ሁኔታው እና እንደ ስሜቴ ሊቀያየር ይችላል (ሳቅ)" ትላለች ማያ። ዘ ጋርዲያንስ ኦፍ ጌትሰማኔ፣ ጎልጎታ እና ጄሩሳሌም አሁን ላይ የምትወዳቸው እና የምታዳምጣቸው የእማሆይ ቅንብሮች ናቸው። "ዘ ጋርዲያንስ ኦፍ ጌትሰማኔ በሕብረ ቀለማት የተንቆጠቆጠ፣ ኮርድስ እና ፎልስ ሩር ኤግዞቲክ ፍላወር።
49618
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%98%E1%8B%8B%E1%8C%8B%E1%89%B5%20%E1%8B%88%E1%8B%AD%E1%88%9D%20%E1%88%98%E1%88%B8%E1%88%BD%20%E1%88%98%E1%88%8D%E1%88%B5
የመዋጋት ወይም መሸሽ መልስ
የመዋጋት ወይም መሸሽ መልስ አሜሪካዊው መምህር ዶ/ር ዋልተር ካኖን በ1908 ዓም የገለጠ ሃልዮ ነው። በመላምቱ ዘንድ እንስሶች አደጋ ባጋጠሙበት ጊዜ በቅጽባት እንዲዘጋጁ ለመርዳት የእድገንጥር ጐርፍ ከአዕምሮና ከኩላትጌ ዕጢ (አድሬናል ግላንድ) ያገኛሉ። ይህ ሁሉ እንስሳ በአደጋ ሰዓት እንዲዘጋጅ ስለሚረዳ፣ ለእንስሳው ጥቅም እንደተለማ ይታስባል። ይህም በእድገ-ንጥር (ሆርሞን) እንደ ተሠለጠነ ይባላል። ነገር ግን ለሰው ልጆች በተያዘ፣ የተዘረዘሩት ውጤቶች ሁሉ ምንም ጠቃሚ አይደሉም። ባጭሩ የሽብር ፍዳ ምልክቶች ናቸው፦ የልብ ምት ማፋጠን፣ የፊኛ መፈታት፣ ዋግምቦ እይታ - የዘርፋዊ እይታ ፈዘዛ፣ የብሌን መስፋት፣ የቀላ ፊት፣ ደረቅ አፍ፣ የሆድ መፍጨት ቆይታ፣ የጆሮ መስማት ቅንሰት እነዚህም ውጤቶች ደግሞ በእድገ-ንጥሮች እንደ ተሠለጠኑ ይባላል። ስለዚህ በተቃራኒ ለሰው ልጆች ጠቃሚ የሆኑት ውጤቶች ቢሠለጠኑ ኖሮ እንዲህ ይሆናሉ፦ ልቡ ሳይሸበር በጸጥታ መወሰን፣ የፊኛ መጠበቅ፣ ዓይኑን አለማጭበርበርና በቶሎ ትክተቱን ማግኘት፣ የጆሮ ፈጣን ማዳመጥና ማስተዋል፣ ወደ ኋለ የሚቀር ጎጂ ደመነፍስን መቆጣጠር። ስነ ልቡና
42246
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%B0%E1%88%9B%E1%88%B5%E1%89%86%20%E1%88%B0%E1%8A%90%E1%8B%B5
የደማስቆ ሰነድ
የደማስቆ ሰነድ በቁምራን ዋሻዎች ከ1938 ዓ.ም ጀምሮ ከተገኙት ብራናዎች መካከል አንዱ ሲሆን ከዚያ በፊት ሌላ ቅጂ በካይሮ በ1889 ዓ.ም. ተገኝቶ ይታወቅ ነበር። ስለ መጨረሻ ቀን ሲነበይ እንዲህ ይላል። «የጽድቅ መሪ» ከተሰበሰበበት ቀን ጀምሮ ከድተው ለሐሣዊዉ የተሰለፉ ሁሉ እስከ መጥፋታቸው ድረስ አርባ ዓመት ያህል ይሆናል። የውጭ መያያዣ የደማስቆ ሰነድ የደማስቆ ሰነድ - ሌላ ትርጒም ሥነ ጽሁፍ ሥነ ቅርስ
52317
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%A5%E1%89%A0%E1%89%83%20%E1%89%B5%E1%8B%95%E1%8B%9B%E1%8B%9D
ጥበቃ ትዕዛዝ
የጥበቃ ትዕዛዝ በለንደን የሜትሮፖሊታን ፖሊስ አገልግሎት የስፔሻሊስት ኦፕሬሽን ዳይሬክቶሬት ውስጥ ካሉት ትዕዛዞች አንዱ ነው። ትዕዛዙ በመከላከያ ደህንነት ላይ የተካነ ሲሆን ሁለት ቅርንጫፎች አሉት እነሱም የሮያልቲ እና የስፔሻሊስት ጥበቃ (ራኤስፒ) ፣ ለንጉሣዊ ቤተሰብ ጥበቃ እና ለመንግስት ባለስልጣናት የቅርብ ጥበቃ ፣ እና የፓርላማ እና የዲፕሎማቲክ ጥበቃ (ፓዲፒ) ፣ የመንግስት ህንፃዎች ፣ ባለስልጣናት እና አንድ ወጥ የሆነ ጥበቃን ይሰጣል ። ዲፕሎማቶች።ከአብዛኞቹ የብሪታንያ የፖሊስ መኮንኖች በተቃራኒ፣ ብዙ የጥበቃ አዛዥ አባላት በተግባራቸው ጊዜ የጦር መሳሪያ ይይዛሉ እና ሁሉም የተፈቀዱ የጦር መሳሪያ መኮንኖች ናቸው። በኤፕሪል 2015 (የአውሮፓ የቀን መቁጠሪያ) የጥበቃ ትእዛዝ ቅርንጫፎች እና የደህንነት ትዕዛዝ አካላት በሁለት የተለያዩ ቅርንጫፎች በመከላከያ ትእዛዝ ቁጥጥር ስር ተዋህደዋል-የሮያልቲ እና የስፔሻሊስት ጥበቃ (ራኤስፒ; የሮያልቲ ጥበቃ እና የልዩ ባለሙያ ጥበቃ ውህደት) እና የፓርላማ እና የዲፕሎማቲክ ጥበቃ (ፓዲፒ; የዲፕሎማቲክ ጥበቃ ቡድን እና የዌስትሚኒስተር የደኅንነት ትዕዛዝ ቤተ መንግሥት ውህደት)። የንጉሣዊ ቤተሰብ እና የልዩ ባለሙያ ጥበቃ የሮያሊቲ እና የስፔሻሊስት ጥበቃ (ራኤስፒ) የተመሰረተው የሮያልቲ ጥበቃ ትእዛዝ ከልዩ ጥበቃ ትእዛዝ ጋር በሚያዝያ 2015 ውህደትን ተከትሎ ነው። መምሪያው ሶስት የስራ ቦታዎች አሉት ለንጉሣዊ ቤተሰብ አባላት፣ የመንግስት ሚኒስትሮች (ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ) እና የጎበኘ የሀገር መሪዎች ጥብቅ ጥበቃ። ለንጉሣዊ ቤተሰብ አባላት እና የመንግስት ሚኒስትሮች የሞባይል የታጠቁ ጥበቃን የሚያቀርበው የልዩ አጃቢ ቡድን በለንደን፣ ዊንዘር እና ስኮትላንድ ውስጥ ባሉ የንጉሣዊ መኖሪያ ቤቶች የታጠቁ ጥበቃ። በመጀመሪያ፣[መቼ?] የሮያሊቲ ጥበቃ መኮንኖች በረዳት ኮሚሽነር “ሀ” ትዕዛዝ በቀጥታ ቢመጡም ለአስተዳደራዊ ዓላማ ከ “” ክፍል ጋር ተያይዘዋል። የሮያሊቲ ጥበቃ ቅርንጫፍ እንደ የተለየ ልዩ ባለሙያተኛ ክፍል በ1978 ተመሠረተ። የፓርላማ እና የዲፕሎማሲ ጥበቃ የፓርላማ እና የዲፕሎማቲክ ጥበቃ (ፓዲፒ) የተመሰረተው የዲፕሎማቲክ ጥበቃ ቡድን ከዌስትሚኒስተር ዲቪዥን ቤተ መንግስት ጋር በሚያዝያ 2015 ውህደትን ተከትሎ ነው። ፓዲፒ የታጠቁ እና ያልታጠቁ ኤምባሲዎችን፣ ሚሲዮኖችን እና የፓርላማ እስቴትን ጥበቃ ያደርጋል። እንዲሁም ለከፍተኛ የመንግስት ሚኒስትሮች የመኖሪያ ቤት ጥበቃን ይሰጣሉ እና በዳውኒንግ ስትሪት እና በኒው ስኮትላንድ ያርድ የመዳረሻ ቁጥጥር እና ደህንነት ሃላፊነት አለባቸው። ፓዲፒ በ2017 በዌስትሚኒስተር በተፈጸመ ጥቃት የተገደለው የፖሊስ ኮንስታብል ኪት ፓልመር ጂኤም የሚሰራበት ትእዛዝ ነበር።
32004
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8C%BD%E1%88%90%E1%8D%88%E1%8D%A1%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AD%E1%89%B5%E1%8D%A1%E1%8B%98%E1%88%8D%E1%88%B3%E1%8A%95%E1%8D%A1%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%8A%85%E1%88%AB%E1%8D%A2
መጽሐፈ፡ትምህርት፡ዘልሳን፡አምኅራ።
መጽሐፈ፡ትምህርት፡ዘልሳን፡አምኅራ። በጀርመናዊው ጸሐፊ እዮብ ሉዶልፍ እና ኢትዮጵያዊው አባ ጎርጎርዮስ ትብብር የተደረሰ የአማርኛ ሰዋሰው ነበር። በላቲን ቋንቋ ግምገማ የተካሄደበት ይህ መጽሐፍ በ1686 ዓ.ም. ሊታተም በቅቷል። መጽሐፉ፣ ከተለያዩ የሰዋሰው ጥናቶች በተጨማሪ የሉቃስ 11፡1-13 ትርጓሜን፣ አባ ጎርጎሪዮስ ስለ ቅድስት ማርያም የደረሱትን ምስጋና፣ ግጥሞችና የለተ ተለት ንግግሮችን መዝግቦ ይገኛል። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኙት አብዛኞቹ የአማርኛ ቃላት በርግጥም የአሁን ዘመን አማርኛን ለሚናገር ሰው እንግዳ አይደሉም። ሆኖም አልፎ አልፎ ለየት ያሉ የፊደላት አቀነባበር ይታያል። በአሁን ጊዜ «አ»ን የሚጠቀሙ ቃላት «ሐ»ን ሲጠቀሙ ይታያሉ፣ በአ እና ዐ ም መካከል ልዩ አጠቃቀም ይታያል። ሀ፣ ሐ እና ኅ እንዲሁ አገባብቸው ውሱንና የጠራ መሆኑ ግልጽ ነው። በተረፈ አንድ አንድ ፊደላት ከአሁኑ ዘመን በተለይ መልኩ ሲቀረጹ ይታያሉ። ለምሳሌ ጨ ፊደል ጠ ሆኖ ከጎንና ጎኑ መያዣ ያለው ፊደል ሆኖ ቀርቧል። የመጽሐፉ ሙሉ ገጾች ከታች ቀርበዋል ፦ 17ኛ ክፍለ ዘመን አማርኛ ሥነ ጽሑፍ አባ ጎርጎሪዮስ ኢዮብ ሉዶልፍ
22748
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AE%E1%88%B6
ኮሶ
ኮሶ () ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው። የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር ባብዛኛው የደጋ ዛፍ ከ2000 ሜትር ከፍታ በላይ ይገኛል። የተክሉ ጥቅም መልካም ማጌጫ ዛፍ ነው። የደረቁ ሴቴ አበቦች ከሁሉ የተጠቀመው የኮሶ ጥገኛ ትል ማስወገጃ ነው። በገበያ በሰፊ ይሸጣል። የኮሶ መጠን ብርቱ ስለሆነ እንደሰውዬው ጤና ሁናቴ መጠኑ መስተካከል ኣለበት። ከልክ በላይ መጠን ቢወሰድ ሊገድል ይችላል፣ በተደጋጋሚ ቢጠቀም ዕውርነት እንደሚፈጥር ይታሠባል። የኢትዮጵያ እጽዋት የመድኃኒት እጽዋት ኮሶ በሽታ
48553
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%86%E1%88%8E%E1%8A%AE%E1%88%B5%E1%89%B5
ሆሎኮስት
ሆሎኮስት ማለት በ2ኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ የአዶልፍ ሂትለር ወገን ናዚዎች በአይሁድና በሌሎች ያደረጉት እልቂት ነበር። ስያሜው በግሪክኛ /ሆሎካውስቶስ/ ትርጒሙ የተቃጠለ መስዋዕት ነው። ስድስት ሚሊዮን ያህል አይሁዶች ተገደሉ። በተጨማሪ ምናልባት አምስት ሚሊዮን ስላቮች ተገደሉ። በሂትለር ርዕዮተ አለም በመከተል ናዚዎቹ እነዚህን ዘሮች መጥፎዎች እንደ ነበሩ ይሉ ነበርና። የአውሮፓ ታሪክ
1531
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8D%8D%E1%88%AA%E1%89%83
አፍሪቃ
አፍሪቃ (አፍሪካ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ1,869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 56 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ126 ሚሊዮን እና በ120 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) 0ኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። አፍሪካ ከሌላው ዓለም ይልቅ የታወቀው በጣም ትንሽ ነው። ኤውሮጳውያን ደኅና አድርገው አፍሪካን አልመረመሩትም። ከሕዝቡ የሚበልጡት ሻንቅሎች ናቸው። ከነዚህም ብዝዎቹ በነገድ የተለያዩ ናቸው። ዓየሩ ሙቀት ያለው ስለ ሆነ፣ ለመጠጊያቸው የሚፈልጉት ትንሽ ጎጆና ትንሽ ልብስ ነው። ስለዚህ ቤታቸው የተዋረደ ነው። ቅጠላቅጠሉን ጎጆ ሠርተው በትንሽ ቤት ይኖራሉ። መቸውንም ልብሳቸው አንዲት ቁራጭ ጨርቅ ናት፤ በወገባቸውም ይጠመጥሟታል። ከሻንቅሎቹ በቀር ደግሞ ሌሎች አያሎች የአፍሪካ ዘሮች አሉ። ከግብፅ ጀምሮ እስከ ሐበሻ ድረስ ያሉት ባላገሮች የጥንት ግብፃውያንነታቸውን ሳይለቁ ከቱርኮችና ከዐረቦች ከሌሎችም የተቀላቀሉ ናቸው። ሰሐራ የሚባለውን ልክ የሌለውን በረሃና በዙሪያው ያለውን አውራጃ ሁሉ ጨምረው ፈረሶቻቸውንና ግመሎቻቸውን ይዘው ለማሰማራት ወይም ለመዝረፍ ከአንዱ ወዳንዱ የሚዞሩ አረቦች ይዘውታል። አፍሪካ በመላው ወደ ሥልጣኔ ያልደረሰ ነው ተብሎ ይታሰባል፤ ከሕዝቡ የሚበዙት እስላሞች ናቸው። በመካከለኛው አፍሪካ አንበሳ፤ ዝሆን፣ አውራሪስ፣ የሜዳ አህያና ሌሎችም አራዊት ይገኙበታል። በደኑ ሁሉ ጦጣና ዝንጀሮ ይንጫጩበታል። በጫካው ውስጥ ዘንዶና ሰጎን ሞልተዋል። በሜዳው አጋዘንና ድኩላ፣ የሜዳ ፍየል ተሰማርተው ይታያሉ። በየወንዙና በየባሕሩ ጎማሬ ይታያል። አዞ በረጋ ውሃ ውስጥ ትኖራለች። አዕዋፍም በየስፍራው ሁሉ ይታያሉ። ዋቢ ምንጮች
13421
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%92%E1%88%BA
ኒሺ
ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ (ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900) ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ሲሆን አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። እርግጥ ኒሺ፣ በነበረበትም ሆነ በኋላ ዘመኑ ብዙ ተቃዋሚወች ቢነሱበትም በዚያው ልክ ብዙ ሰወች ስራወቹን እንደ ታላቅ የፍልስፍና እና ስነ ጽሁፍ ስራ ይወስዷቸዋል። ኒትሸ አብዛኛው ጽሁፉ የሚያተኩረው ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ምክንያት እሱ ይኖርበት የነበረውን ዘመን የጀርመን ሥነ ምግባር (ኤቲክስ) በመንቀፍ ብዙ ጽፎአል። ሠናይ እና እኩይ (ጥሩና መጥፎ) ተብለው ተለይተው ይሰራባቸው የነበሩትን የጊዜውን ሥነ ምግባር ዋጋወች በመተቸት ሰወች አዲስ ሥነ ምግባር ፈጥረው ለሁሉም ምግባር አዲስ የሠናይነትና እኩይነት (ጥሩ እና መጥፎ) ዋጋ እንዲሰጡ በጽሑፎቹ ብዙ ሞክሯል።በዚህ መሰረት፣ ለምሳሌ፣ በክርስቲያኖች ዘንድ የሚሰራበትን ለደካሞች ማዘንን ሠናይነት ተቃውሟል። በሱ አስተያየት ደካሞች ሲታዘንላቸው የበለጠ ይዳከማሉ የሚል ነው ምክንያቱም በሱ አስተያየት ደካሞቹ በጠንካሮቹ ላይ የበለጠ ጥገኛ በመሆን መላው ህብረተሰብ ይዳከማል የሚል ነው። በተጨማሪም፣ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ተጨባጩን አለም መገንዘብ እና ክሁሉ በላይ ስለዚሁ ዓለም ማተኮር አለበት ብሏል። ሰማይና ሌሎች አለማትን በማጣጣል፣ የሰው ልጅ እነዚህን አይነት አለሞች የሚፈጥረው አሁን ያለበትን ተጨባጩ የውኑ አለም ችግሮች መፍታት ሲያቅተው ለመፈርጠጥ ነው በማለት የሰው ልጅ ስለዚህ ምድር ብቻ እንዲያስብ ይወተውታል። ኒሽ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል አጥብቆ ያምናል። በኒሺ ፍልስፍና፣ አንድ እራሱን ያሽነፈ ሰው በጣም የተለወጠ እና የተሻለ ስለሚሆን "ሱፐር ማን" ወይም "የበላይ ሰው" እንዲባል ሰይሟል። የበላይ ሰው እንግዴህ ጠንካራና በሌሎች ሰወች "ሠናይ" እና "እኩይ" ወይም ደግሞ "ጥሩ" ና "መጥፎ" ዋጋወች የማይመራ፣ ይልቁኑ የራሱን ሥነ ምግባር የሚፈጥር ነው። ዋና ዋና ሓሳቦቹ የበላይ ሰው የሃይል ፈቃድ አፖሎና ዳይኖስየስ የጌታና ባሪያ ሥነ ምግባር የእጣ ፈንታ ፍቅር ዘላለማዊ ድግግሞሽ የኒሽ ትጽኖ የናዚ ጀርመን መሪ የነበረው ሂትለር የኒሽን ጽሁፍ ያነብ እንደነበር ታሪክ የሚያውቀው ሲሆን፣ ምንም እንኳ አንድ አንድ ሰወች እንደሚሉት የኒሽን ስራ ሂትለር የመረዳት አቅሙ ባይኖረውም፣ ነገር ግን የፈላስፋውን ሃሳቦች በጥራዝ ነጠቅ ለራሱ ስራወች ትክክልነት እንደማማካኛ ይጠቀም ነበር። ኒሽ የአጻጻፉ ዘዴው እጅግ ሃይለኛና ስሜት ቀስቃሽ ነበር፣ በዚህ ምክንያት አንድ አንዶች የጀርመን ስነ ጽሁፍ አባት ይሉታል። ኒሽ እድሜው እየጎለመሰ በሄደ ጊዜ፣ በበሽታ መሰቃየት ጀመረ። በሽታውን ለማስታገስ ከጀርመን ወደ ጣሊያን ሄዶ የተወሰነ ጊዜ ያሳልፍ ነበር። አንድ ቀን በቱሪን ከተማ ጣሊያን በመንገድ ሲዘዋወር አንድ ፈረስ በባለቤቱ በአለንጋ ሲደበደብ አይቶ ሲሮጥ ሄዶ ከፈርሱ ላይ ተጠመጠመ። ከዚያን ጊዜ ወዲህ ሙሉ በሙሉ አበደ፣ ጽሁፍም መጻፍ አቋረጠ። በዚህ ጊዜ እድሜው አርባ አመቱ ነበር። እብደቱና ከዚያም በፊት ሲያሰቃየው የነበረው በሽታ መንሴ ወይም ቂጥኝ ወይም ደግሞ የአይምሮ ነቀረሳ ነው ተብሎ በአሁኑ ጊዜ ይታመናል። ጽሁፎቹና ስራው አሁን ድረስ ዝናን ያተረፉ፣ በዚያው ልክ የሚጠኑ ናቸው።
3500
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%8B%8A%E1%8B%98%E1%88%AD%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%8B%B5
ስዊዘርላንድ
ስዊዘርላንድ፣ በይፋ የስዊስ ኮንፌዴሬሽን፣ በምዕራብ፣ መካከለኛው እና ደቡብ አውሮፓ መገናኛ ላይ ያለ ወደብ የለሽ ሀገር ነች። አገሪቱ በ26 ካንቶን የተዋቀረች የፌደራል ሪፐብሊክ ነች፣ በበርን ላይ የተመሰረተ የፌዴራል ባለስልጣናት ያሏት። ስዊዘርላንድ በደቡብ ከጣሊያን፣ በምዕራብ ከፈረንሳይ፣ በሰሜን ከጀርመን እና በምስራቅ በሊችተንስታይን ትዋሰናለች። በጂኦግራፊያዊ ሁኔታ በስዊስ ፕላቶ፣ በአልፕስ ተራሮች እና በጁራ መካከል የተከፋፈለ ሲሆን በአጠቃላይ 41,285 ኪ.ሜ. (15,940 ካሬ ማይል) እና የመሬቱ ስፋት 39,997 ኪ.ሜ. (15,443 ካሬ ማይል) ይሸፍናል። ምንም እንኳን የአልፕስ ተራሮች የግዛቱን ትልቁን ቦታ ቢይዙም በግምት 8.5 ሚሊዮን የሚሆነው የስዊዘርላንድ ህዝብ በአብዛኛው በደጋው ላይ ያተኮረ ነው ፣ ትላልቅ ከተሞች እና ኢኮኖሚያዊ ማዕከሎች ባሉበት ፣ ከእነዚህም መካከል ዙሪክ ፣ጄኔቫ ፣ ባዝል እና ላውዛን ናቸው። እነዚህ ከተሞች እንደ ፣ ፣ ፣ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መቀመጫ፣ የፊፋ ዋና መሥሪያ ቤት፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሁለተኛ ትልቁ ጽሕፈት ቤት እንዲሁም የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤቶች ያሉባቸው በርካታ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ቢሮዎች ናቸው። ለአለም አቀፍ ሰፈራዎች. የስዊዘርላንድ ዋና ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎችም በእነዚህ ከተሞች ውስጥ ይገኛሉ። በመካከለኛው ዘመን መገባደጃ ላይ የድሮው የስዊስ ኮንፌዴሬሽን መመስረት የተገኘው በኦስትሪያ እና በቡርገንዲ ላይ በተደረጉ ተከታታይ ወታደራዊ ስኬቶች ነው። የስዊዘርላንድ ከቅድስት ሮማን ግዛት ነፃ ወጥታ በ1648 በዌስትፋሊያ ሰላም ውስጥ በይፋ እውቅና አገኘ። እ.ኤ.አ. የ 1291 የፌዴራል ቻርተር በስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቀን የሚከበረው የስዊዘርላንድ መስራች ሰነድ ነው። ከ 16 ኛው ክፍለ ዘመን ተሐድሶ ጀምሮ ስዊዘርላንድ የታጠቁ የገለልተኝነት ፖሊሲን ጠብቃለች; ከ 1815 ጀምሮ ዓለም አቀፍ ጦርነት አላደረገም እና እስከ 2002 ድረስ የተባበሩት መንግስታትን አልተቀላቀለችም. ቢሆንም, ንቁ የውጭ ፖሊሲን ይከተላል. በአለም አቀፍ የሰላም ግንባታ ሂደቶች ውስጥ በተደጋጋሚ ይሳተፋል። ስዊዘርላንድ የቀይ መስቀል መፍለቂያ ናት፣ በዓለም ካሉት አንጋፋ እና ታዋቂ የሰብአዊ ድርጅቶች አንዱ ነው። እሱ የአውሮፓ ነፃ ንግድ ማህበር መስራች አባል ነው ፣ ግን በተለይም የአውሮፓ ህብረት ፣ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ወይም የዩሮ ዞን አካል አይደለም ። ሆኖም በ አካባቢ እና በአውሮፓ ነጠላ ገበያ በሁለትዮሽ ስምምነቶች ይሳተፋል። ስዊዘርላንድ በአራቱ ዋና ዋና የቋንቋ እና የባህል ክልሎች፡ ጀርመንኛ፣ ፈረንሣይኛ፣ ጣልያንኛ እና ሮማንሽ እንደተገለፀው የጀርመን እና የፍቅር አውሮጳ መስቀለኛ መንገድን ትይዛለች። ምንም እንኳን አብዛኛው ህዝብ ጀርመንኛ ተናጋሪ ቢሆንም የስዊዘርላንድ ብሄራዊ ማንነት ግንኙነቱ የጋራ ታሪካዊ ዳራ፣ የጋራ እሴቶች እንደ ፌዴራሊዝም እና ቀጥተኛ ዲሞክራሲ እንዲሁም የአልፓይን ተምሳሌትነት ነው። በቋንቋ ልዩነት ምክንያት ስዊዘርላንድ በተለያዩ የአፍ መፍቻ ስሞች ትታወቃለች፡ ] (ጀርመንኛ);[ማስታወሻ 5] ስዊስ (ፈረንሳይኛ); ] (ጣሊያን); እና ፣ ] (ሮማንሽ)። በሳንቲሞች እና ማህተሞች ላይ፣ የላቲን ስም፣ - በተደጋጋሚ ወደ "ሄልቬቲያ" የሚታጠረው - ከአራቱ ብሄራዊ ቋንቋዎች ይልቅ ጥቅም ላይ ይውላል። የበለጸገች አገር፣ በአዋቂ ሰው ከፍተኛው ስምንተኛ-ከፍተኛ የነፍስ ወከፍ ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አላት፤ እንደ የግብር ቦታ ተቆጥሯል ። እሱ በአንዳንድ ዓለም አቀፍ መለኪያዎች ፣ ኢኮኖሚያዊ ተወዳዳሪነት እና የሰው ልማትን ጨምሮ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። እንደ ዙሪክ ፣ጄኔቫ እና ባዝል ያሉ ከተሞቿ ምንም እንኳን በአለም ላይ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ቢኖራቸውም በኑሮ ጥራት ከአለም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2020፣ አይኤምዲ የሰለጠነ ሰራተኞችን በመሳብ ስዊዘርላንድን ቀዳሚ አድርጓል። በዓለም አቀፍ ደረጃ አምስተኛውን ተወዳዳሪ አገር አስቀምጧል ሥርወ ቃል የእንግሊዝኛው ስም ስዊዘርላንድ በ 16 ኛው እስከ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ጥቅም ላይ የዋለ ለስዊስ ሰው ጊዜ ያለፈበት ቃል ስዊዘርላንድን የያዘ ውህድ ነው። የእንግሊዘኛ ቅፅል ስዊስ ከፈረንሣይ ስዊስ የተገኘ ብድር ነው፣ እሱም ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ጥቅም ላይ ይውላል። ስዊዘርላንድ የሚለው ስም ከአለማኒክ ሽዊዘር የመጣ ነው፣ በመነሻውም የሽዊዝ ነዋሪ እና ተዛማጅ ግዛቱ፣ ከዋልድስተቴ ካንቶኖች አንዱ የሆነው የብሉይ ስዊስ ኮንፌዴሬሽን አስኳል ነው። ስዊዘርላንድ ከ 14 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ጥቅም ላይ የዋለው "ኮንፌዴሬቶች" ከሚለው ቃል ጎን ለጎን ከ 1499 የስዋቢያን ጦርነት በኋላ ስዊዘርላንድ ለራሳቸው ስም መቀበል ጀመሩ ። የስዊዘርላንድ የመረጃ ኮድ፣ ፣ ከላቲን (እንግሊዝኛ፡ ) የተገኘ ነው። ሽዊዝ የሚለው ስም እራሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመሰከረው በ972 ነው፣ እንደ ኦልድ ሃይ ጀርመናዊ ስዊትስ፣ በመጨረሻም ምናልባት ከስዊድን 'ለመቃጠል' የተቃጠለውን እና የተጸዳውን የደን ቦታ በመጥቀስ ከስዊድን ጋር ይዛመዳል። ለመገንባት. ይህ ስም በካንቶን የበላይነት ወደሚገኝበት አካባቢ ተስፋፋ እና ከ 1499 የስዋቢያን ጦርነት በኋላ ቀስ በቀስ ለመላው ኮንፌዴሬሽን ጥቅም ላይ መዋል ጀመረ። የስዊዝ ጀርመናዊው የአገሪቷ ስም ሽዊዝ ከካንቶን እና ሰፈራው ጋር ተመሳሳይ ነው ፣ ግን የተወሰነውን አንቀፅ በመጠቀም ( ፣ ግን በቀላሉ ለካንቶን እና ከተማ) ይለያል። ረጅም [] የስዊዘርላንድ ጀርመን በታሪካዊ እና ዛሬም ብዙ ጊዜ ⟨⟩ ከ ⟨⟩ ይልቅ ⟨⟩ ይጽፋል፣ የሁለቱን ስሞች የመጀመሪያ ማንነት በጽሁፍም ይጠብቃል። የላቲን ስም ነበር እና በ 1848 የፌዴራል ግዛት ምስረታ በኋላ ቀስ በቀስ አስተዋወቀ, ወደ ናፖሊዮን ሄልቬቲክ ሪፐብሊክ ወደ ኋላ , 1879 ጀምሮ ሳንቲሞች ላይ ታየ, 1902 ውስጥ የፌዴራል ቤተ መንግሥት ላይ የተጻፈው እና 1948 በኋላ ኦፊሴላዊ ማኅተም ጥቅም ላይ ለምሳሌ የ የባንክ ኮድ "" ለስዊስ ፍራንክ እና የሀገሪቱ ከፍተኛ ደረጃ ጎራ "." ሁለቱም ከስቴቱ የላቲን ስም የተወሰዱ ናቸው)። ሄልቬቲካ ከሮማውያን ዘመን በፊት በስዊዘርላንድ አምባ ላይ ከሚኖረው ከሄልቬቲ የተገኘ የጋሊሽ ጎሳ ነው። ሄልቬቲያ በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን የስዊስ ኮንፌዴሬሽን ብሔራዊ ሰው ሆኖ በ 1672 በጆሃን ካስፓር ዌይሰንባክ ተውኔት ታየ በአካባቢው በጣም የታወቁት የባህል ጎሳዎች ከኒውቸቴል ሀይቅ በስተሰሜን በሚገኘው በላ ቴኔ አርኪኦሎጂካል ቦታ የተሰየሙት የሃልስታት እና የላ ቴኔ ባህሎች አባላት ነበሩ። የላ ቴኔ ባህል ያደገው እና ​​ያደገው በኋለኛው የብረት ዘመን ከ450 ዓክልበ. አካባቢ ነው፣ ምናልባትም በግሪክ እና ኢትሩስካን ስልጣኔዎች በተወሰነ ተጽእኖ ስር ሊሆን ይችላል። በስዊስ ክልል ውስጥ ካሉት በጣም አስፈላጊ የጎሳ ቡድኖች አንዱ ሄልቬቲ ነው። በጀርመናዊ ጎሳዎች በየጊዜው ትንኮሳ በደረሰበት በ58 ዓክልበ ሄልቬቲ የስዊዝ አምባን ትቶ ወደ ምዕራብ ጋሊያ ለመሰደድ ወስኗል፣ነገር ግን የጁሊየስ ቄሳር ጦር ዛሬ በምስራቅ ፈረንሳይ በሚገኘው የቢብራክቴ ጦርነት በማሳደድ አሸነፋቸው። ወደ መጀመሪያው የትውልድ አገሩ ። በ15 ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ አንድ ቀን ሁለተኛው የሮማ ንጉሠ ነገሥት የሆነው ጢባርዮስ እና ወንድሙ ድሩሰስ የአልፕስ ተራሮችን ድል አድርገው ከሮም ግዛት ጋር አዋህደው ያዙ። በሄልቬቲ የተያዘው አካባቢ - የኋለኛው ስሞች - በመጀመሪያ የሮማ ጋሊያ ቤልጂካ ግዛት እና ከዚያም የጀርመኒያ የላቀ አውራጃ አካል ሆነ ፣ የዘመናዊው ስዊዘርላንድ ምስራቃዊ ክፍል ደግሞ ወደ ሮማ ግዛት ሬቲያ ተቀላቀለ። በጥንት ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ሮማውያን ቪንዶኒሳ የሚባል ትልቅ የጦር ካምፕ ጠብቀው ቆይተዋል፣ አሁን በአሬ እና ሬውስ ወንዞች መጋጠሚያ ላይ፣ የብሩግ ወጣ ገባ በሆነችው በዊንዲሽ ከተማ አቅራቢያ ውድመት ደረሰ። የመጀመሪያው እና ሁለተኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም በስዊዘርላንድ አምባ ላይ ለሚኖሩ ህዝቦች የብልጽግና ዘመን ነበር። እንደ ፣ እና ያሉ በርካታ ከተሞች እጅግ አስደናቂ መጠን ላይ ደርሰዋል፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ የግብርና ግዛቶች () በገጠር ተመስርተዋል። በ260 ዓ.ም አካባቢ፣ ከራይን በስተሰሜን ያለው የአግሪ ዲኩሜትስ ግዛት መውደቅ የዛሬዋን ስዊዘርላንድ ወደ ኢምፓየር ድንበር ምድር ቀይሯታል። በአላማኒ ጎሳዎች ተደጋጋሚ ወረራ የሮማውያንን ከተሞች እና ኢኮኖሚ ውድመት አስከትሏል፣ ይህም ህዝቡ በሮማውያን ምሽጎች አቅራቢያ መጠለያ እንዲያገኝ አስገድዶ ነበር፣ ለምሳሌ በኦገስታ ራውሪካ አቅራቢያ እንደ ካስትራም ራውራሰንስ። ኢምፓየር በሰሜን ድንበር (ዶና-ኢለር-ራይን-ሊምስ ተብሎ የሚጠራው) ሌላ የመከላከያ መስመር ገነባ። አሁንም በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ፣ የጨመረው የጀርመን ግፊት ሮማውያን የመስመር መከላከያ ጽንሰ-ሐሳብን እንዲተዉ አስገደዳቸው። የስዊዘርላንድ አምባ በመጨረሻ ለጀርመን ጎሳዎች መኖሪያ ክፍት ሆነ። በመካከለኛው ዘመን መጀመሪያ ከ 4 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ የዘመናዊቷ ስዊዘርላንድ ምዕራባዊ ስፋት የቡርጋንዲን ነገሥታት ግዛት አካል ነበር። አለማኒ በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን የስዊዝ አምባን እና በ 8 ኛው ክፍለ ዘመን የአልፕስ ተራሮች ሸለቆዎችን ሰፈረ ፣ አልማንኒያ ፈጠረ። የአሁኗ ስዊዘርላንድ ስለዚህ በአሌማንኒያ እና በቡርገንዲ ግዛቶች መካከል ተከፈለች። በ 504 ዓ.ም ክሎቪስ 1 በአለማኒ ላይ በቶልቢያክ ድል እና በኋላም የቡርጋንዳውያን የፍራንካውያን የበላይነትን ተከትሎ በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢው ሁሉ የተስፋፉ የፍራንካውያን ግዛት አካል ሆነ። በቀሪው 6ኛው፣ 7ኛው እና 8ኛው ክፍለ ዘመን፣ የስዊስ ክልሎች በፍራንካውያን የበላይነት (በሜሮቪንግያን እና ካሮሊንግያን ስርወ መንግስት) ቀጥለዋል። ነገር ግን በሻርለማኝ ስር ከተስፋፋ በኋላ የፍራንካውያን ኢምፓየር በ 843 በቬርዱን ስምምነት ተከፋፈለ። የአሁኗ ስዊዘርላንድ ግዛቶች በመካከለኛው ፍራንሢያ እና በምስራቅ ፍራንሢያ ተከፋፈሉ በ1000 ዓ.ም አካባቢ በቅድስት ሮማ ግዛት ሥር እስኪቀላቀሉ ድረስ። እ.ኤ.አ. በ1200፣ የስዊዘርላንድ አምባ የሳቮይ፣ የዛህሪንገር፣ የሀብስበርግ እና የኪበርግ ቤቶችን ግዛቶች ያካትታል። አንዳንድ ክልሎች (፣ ፣ ፣ በኋላ ዋልድስተተን በመባል የሚታወቁት) ኢምፓየር በተራራ መተላለፊያዎች ላይ ቀጥተኛ ቁጥጥር እንዲደረግ የኢምፔሪያል አፋጣኝ ፍቃድ ተሰጥቷቸዋል። በ1263 የኪበርግ ሥርወ መንግሥት ወድቋል። በ1264 ዓ.ም. የሀብስበርግ መንግሥት በንጉሥ ሩዶልፍ (በ1273 የቅዱስ ሮማ ንጉሠ ነገሥት) የኪይበርግ መሬቶችን በመያዝ ግዛታቸውን እስከ ምሥራቃዊው የስዊስ አምባ ድረስ ያዙ።የድሮው የስዊስ ኮንፌዴሬሽን በመካከለኛው የአልፕስ ተራሮች ሸለቆ ማህበረሰቦች መካከል ጥምረት ነበር። በተለያዩ ካንቶኖች በሚገኙ መኳንንት እና ፓትሪሻኖች የሚመራው ኮንፌዴሬሽን የጋራ ፍላጎቶችን ማስተዳደር እና ጠቃሚ በሆኑ የተራራ ንግድ መስመሮች ላይ ሰላምን አረጋግጧል። በ1291 የወጣው የፌደራል ቻርተር በኡሪ፣ ሽዊዝ እና ዩንተርዋልደን የገጠር ማህበረሰቦች መካከል የተስማማው የኮንፌዴሬሽኑ መስራች ሰነድ ነው፣ ምንም እንኳን ተመሳሳይ ጥምረት ከብዙ አሥርተ ዓመታት በፊት የነበረ ቢሆንም። እ.ኤ.አ. በ 1353 ሦስቱ ኦሪጅናል ካንቶኖች ከግላሩስ እና ዙግ እና ከሉሰርን ፣ ዙሪክ እና የበርን ከተማ ግዛቶች ጋር ተቀላቅለው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ድረስ የነበረውን የስምንት ግዛቶችን “አሮጌ ኮንፌዴሬሽን” ፈጠሩ። መስፋፋቱ ለኮንፌዴሬሽኑ ሥልጣንና ሀብት እንዲጨምር አድርጓል። እ.ኤ.አ. በ 1460 ፣ ኮንፌዴሬቶች አብዛኛው ግዛት ከራይን በስተደቡብ እና በምዕራብ እስከ አልፕስ እና የጁራ ተራሮች ፣ በተለይም በ 1470 ዎቹ ውስጥ በቻርልስ ዘ ቦልድ ኦፍ ቡርጋንዲ ላይ ከሀብስበርግ (የሴምፓች ጦርነት ፣ የናፍልስ ጦርነት) ድል በኋላ ። እና የስዊዘርላንድ ቅጥረኞች ስኬት. እ.ኤ.አ. በ1499 ከስዋቢያን ንጉሠ ነገሥት ማክስሚሊያን 1ኛ የስዋቢያን ሊግ ጋር በስዊዘርላንድ በተደረገው ጦርነት በስዊዘርላንድ የተቀዳጀው ድል በቅድስት ሮማ ኢምፓየር ውስጥ ነፃነትን አስገኝቷል። በ 1501 ባዝል እና ሻፍሃውሰን የድሮውን የስዊስ ኮንፌዴሬሽን ተቀላቀለ።የድሮው የስዊስ ኮንፌዴሬሽን በነዚህ ቀደምት ጦርነቶች የማይሸነፍ ዝና አግኝቷል፣ነገር ግን የኮንፌዴሬሽኑ መስፋፋት እ.ኤ.አ. በ1515 በስዊዘርላንድ በማሪኛኖ ጦርነት ሽንፈት ገጥሞታል። ይህ የስዊዘርላንድ ታሪክ “ጀግና” እየተባለ የሚጠራውን ዘመን አበቃ። በአንዳንድ ካንቶኖች የዝዊንጊ ተሐድሶ ስኬት በ1529 እና ​​1531 (የካፔል ጦርነቶች) በካንቶናዊ መካከል የሃይማኖት ግጭቶች እንዲፈጠሩ አድርጓል። በ1648 በዌስትፋሊያ ሰላም፣ የአውሮፓ አገሮች ስዊዘርላንድ ከቅድስት ሮማ ግዛት ነፃ መውጣቷንና ገለልተኝነቷን የተገነዘቡት ከእነዚህ የውስጥ ጦርነቶች ከአንድ መቶ ከሚበልጡ ዓመታት በኋላ ነበር። በስዊዘርላንድ የጥንት ዘመናዊ ጊዜ ውስጥ የፓትሪያል ቤተሰቦች እያደገ የመጣው አምባገነንነት ከሠላሳ ዓመታት ጦርነት በኋላ ከደረሰው የገንዘብ ችግር ጋር ተዳምሮ በ 1653 የስዊዝ የገበሬዎች ጦርነት ምክንያት ሆኗል ። ከዚህ ትግል በስተጀርባ በካቶሊክ መካከል የተፈጠረው ግጭት ። እና የፕሮቴስታንት ካንቶኖች በ 1656 በቪልመርገን የመጀመሪያ ጦርነት እና በቶገንበርግ ጦርነት (ወይም የቪልመርገን ሁለተኛ ጦርነት) በ 1712 ተጨማሪ ብጥብጥ ፈነዳ። ናፖሊዮን ዘመን በ1798 አብዮታዊው የፈረንሳይ መንግስት ስዊዘርላንድን ወረረ እና አዲስ የተዋሃደ ህገ መንግስት ደነገገ። ይህም የአገሪቱን መንግሥት ያማከለ፣ ካንቶኖቹን በሚገባ በማጥፋት፣ በተጨማሪም ሙልሃውሰን ፈረንሳይን ተቀላቀለ እና የቫልቴሊና ሸለቆ ከስዊዘርላንድ በመለየት የሲሳልፓይን ሪፐብሊክ አካል ሆነ። ሄልቬቲክ ሪፐብሊክ በመባል የሚታወቀው አዲሱ አገዛዝ በጣም ተወዳጅ አልነበረም. ወራሪ የውጭ ጦር የዘመናት ወግ ገድቦና አጠፋው፤ ስዊዘርላንድ ከፈረንሳይ ሳተላይት ግዛት ያለፈ ነገር አልነበረም። እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 1798 የኒድዋልደን አመፅ የፈረንሣይ ኃይለኛ አፈና የፈረንሳይ ጦር ጨቋኝ መገኘት እና የአካባቢው ህዝብ ወረራውን የመቋቋም ምሳሌ ነበር። በፈረንሳይና በተቀናቃኞቿ መካከል ጦርነት በፈነዳበት ጊዜ የሩሲያና የኦስትሪያ ኃይሎች ስዊዘርላንድን ወረሩ። ስዊዘርላንድ በሄልቬቲክ ሪፐብሊክ ስም ከፈረንሳይ ጋር ለመፋለም ፈቃደኛ አልሆነም። እ.ኤ.አ. በ 1803 ናፖሊዮን በፓሪስ ከሁለቱም ወገኖች መሪ የስዊስ ፖለቲከኞች ስብሰባ አዘጋጀ ። የሽምግልና ህግ ውጤቱ ነው፣ እሱም የስዊስ ራስን በራስ የማስተዳደርን ባብዛኛው ወደነበረበት ይመልሳል እና የ19 ካንቶን ኮንፌዴሬሽን አስተዋወቀ። ከአሁን በኋላ፣ አብዛኛው የስዊስ ፖለቲካ የካንቶኖችን ራስን በራስ የማስተዳደር ባህል ከማዕከላዊ መንግስት ፍላጎት ጋር ማመጣጠን ያሳስበዋል። እ.ኤ.አ. በ 1815 የቪየና ኮንግረስ የስዊስ ነፃነትን ሙሉ በሙሉ እንደገና አቋቋመ ፣ እናም የአውሮፓ ኃያላን የስዊስ ገለልተኝነቶችን በቋሚነት እውቅና ለመስጠት ተስማምተዋል። የስዊዘርላንድ ወታደሮች በጌታ ከበባ ሲዋጉ እስከ 1860 ድረስ የውጭ መንግስታትን አገልግለዋል። ስምምነቱ ስዊዘርላንድ የቫሌይስ፣ የኒውቸቴል እና የጄኔቫ ካንቶኖችን በመቀበል ግዛቷን እንድትጨምር አስችሎታል። ከአንዳንድ ጥቃቅን ማስተካከያዎች በስተቀር የስዊዘርላንድ ድንበሮች አልተቀየሩም። ዘመናዊ ታሪክ ስዊዘርላንድ በሁለቱም የዓለም ጦርነቶች አልተወረረችም። በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ስዊዘርላንድ የሶቪየት ዩኒየን አብዮታዊ እና መስራች ቭላድሚር ኢሊች ኡሊያኖቭ (ቭላዲሚር ሌኒን) መኖሪያ ነበረች። እ.ኤ.አ. እስከ 1917 ድረስ እዚያው ቆየ። በ1917 በግሪም-ሆፍማን ጉዳይ የስዊዘርላንድ ገለልተኝነት በቁም ነገር ተጠራጥሮ ነበር፣ ነገር ግን ያ ብዙም አልቆየም። እ.ኤ.አ. በ1920 ስዊዘርላንድ ከማንኛውም ወታደራዊ መስፈርቶች ነፃ እንድትሆን በጄኔቫ የሚገኘውን የመንግስታቱን ሊግ ተቀላቀለች። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት፣ ዝርዝር የወረራ እቅዶች በጀርመኖች ተዘጋጅተው ነበር፣ ስዊዘርላንድ ግን ጥቃት አልደረሰባትም። በጦርነቱ ወቅት ትላልቅ ክስተቶች ወረራ ስላዘገዩ ስዊዘርላንድ በወታደራዊ መከላከያ፣ ለጀርመን በሰጠችው ስምምነት እና መልካም ዕድል በመጣመር ነፃ ሆና መቀጠል ችላለች። በጄኔራል ሄንሪ ጉይሳን ለጦርነቱ ጊዜ ዋና አዛዡን የተሾመው የጦር ኃይሎች አጠቃላይ ቅስቀሳ ታዝዟል። የስዊዘርላንድ ወታደራዊ ስትራቴጂ የኢኮኖሚውን እምብርት ለመጠበቅ በድንበር ላይ ከሚገኝ የማይንቀሳቀስ የመከላከያ ዘዴ ወደ የተደራጀ የረጅም ጊዜ መጥፋት እና መውጣት ወደ ጠንካራ እና በጥሩ ሁኔታ ወደተከማቸ የአልፕስ ተራሮች ከፍታ ወደ ሬዱይት ተለወጠ። ስዊዘርላንድ በግጭቱ ውስጥ ለሁለቱም ወገኖች የስለላ አስፈላጊ መሰረት ነበረች እና ብዙ ጊዜ በአክሲስና በተባባሪ ኃይሎች መካከል የሚደረጉ ግንኙነቶችን አስታራቂ ነበር። የስዊዘርላንድ ንግድ በሁለቱም አጋሮች እና በአክሲዎች ታግዷል። ለናዚ ጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ብድር ማራዘም እንደ ወረራ ግምት እና እንደ ሌሎች የንግድ አጋሮች አቅርቦት ይለያያል። እ.ኤ.አ. በ 1942 በቪቺ ፈረንሳይ በኩል ያለው ወሳኝ የባቡር ሐዲድ ከተቋረጠ በኋላ ስዊዘርላንድ (ከሊችተንስታይን ጋር) በአክሲስ ቁጥጥር ስር ከሰፊው ዓለም ሙሉ በሙሉ ተለይታ ከነበረች በኋላ ቅናሾች ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደረሱ። በጦርነቱ ወቅት ስዊዘርላንድ ከ300,000 በላይ ስደተኞችን አስገብታለች እና በጄኔቫ የሚገኘው አለም አቀፍ ቀይ መስቀል በግጭቱ ወቅት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ጥብቅ የኢሚግሬሽን እና የጥገኝነት ፖሊሲዎች እና ከናዚ ጀርመን ጋር ያለው የገንዘብ ግንኙነት ውዝግብ አስነስቷል፣ ግን እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ድረስ አልነበረም። በጦርነቱ ወቅት የስዊዘርላንድ አየር ሃይል የሁለቱም ወገኖች አውሮፕላኖችን በማሳተፍ በግንቦት እና ሰኔ 1940 11 የሉፍትዋፍ አውሮፕላኖችን በመተኮስ ከጀርመን ዛቻን ተከትሎ የፖሊሲ ለውጥ ካደረገ በኋላ ሌሎች ሰርጎ ገቦችን አስገድዶ ነበር። በጦርነቱ ወቅት ከ100 በላይ የህብረት ቦንብ አውጭዎች እና ሰራተኞቻቸው ከ1940 እስከ 1945 ባለው ጊዜ ውስጥ ስዊዘርላንድ በተባበሩት መንግስታት በቦምብ ተመታ የሰው ህይወት እና ንብረት ወድሟል። በቦምብ ከተጠቁት ከተሞችና ከተሞች መካከል ባዝል፣ ብሩስዮ፣ ቺያሶ፣ ኮርኖል፣ ጄኔቫ፣ ኮብሌዝ፣ ኒደርዌንገን፣ ራፍዝ፣ ሬኔንስ፣ ሳሜዳን፣ ሻፍሃውሰን፣ ስታይን አም ራይን፣ ተገርዊለን፣ ታይንገን፣ ቫልስ እና ዙሪክ ይገኙበታል። 96ኛውን የጦርነት አንቀፅ የጣሰውን የቦምብ ፍንዳታ በአሰሳ ስህተት፣ በመሳሪያዎች ብልሽት፣ በአየር ሁኔታ እና በቦምብ አውሮፕላኖች የተደረጉ ስህተቶች መሆናቸውን የህብረት ሃይሎች አብራርተዋል። ስዊዘርላንዳውያን የቦምብ ፍንዳታዎቹ ከናዚ ጀርመን ጋር ኢኮኖሚያዊ ትብብር እና ገለልተኝነታቸውን እንዲያቆሙ በስዊዘርላንድ ላይ ጫና ለመፍጠር ታስቦ ነው ሲሉ ስጋት እና ስጋት ገለጹ። የወታደራዊ ፍርድ ቤት ክስ በእንግሊዝ የተካሄደ ሲሆን የዩኤስ መንግስት ለቦምብ ጥቃቱ ማካካሻ 62,176,433.06 በስዊስ ፍራንክ ከፍሏል። ስዊዘርላንድ ለስደተኞች ያላት አመለካከት የተወሳሰበ እና አወዛጋቢ ነበር። በጦርነቱ ወቅት በናዚዎች ከፍተኛ ስደት የደረሰባቸውን አይሁዶች ጨምሮ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩትን ጨምሮ 300,000 የሚደርሱ ስደተኞችን ተቀብሏል። ከጦርነቱ በኋላ የስዊዘርላንድ መንግስት ክሬዲቶችን ወደ ውጭ በመላክ ሽዌይዘርስፔንዴ በሚባለው የበጎ አድራጎት ፈንድ በኩል ለማርሻል ፕላን በመለገስ የአውሮፓን ማገገም ይረዳዋል፣ ይህ ጥረት በመጨረሻ የስዊስ ኢኮኖሚን ​​ተጠቃሚ አድርጓል። በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት የስዊዘርላንድ ባለስልጣናት የስዊዝ የኒውክሌር ቦምብ ግንባታን ግምት ውስጥ አስገብተው ነበር። በፌዴራል የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዙሪክ እንደ ፖል ሸርረር ያሉ ግንባር ቀደም የኑክሌር ፊዚክስ ሊቃውንት ይህንን ተጨባጭ ሁኔታ አቅርበውታል። እ.ኤ.አ. በ 1988 የፖል ሸርረር ኢንስቲትዩት የኒውትሮን መበታተን ቴክኖሎጂዎችን ቴራፒዩቲካል አጠቃቀምን ለመመርመር በስሙ ተመሠረተ ። በመከላከያ በጀት እና በሥነ ምግባራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ የፋይናንስ ችግሮች ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንዳይመደብ አግደዋል እና የ 1968 የኑክሌር መስፋፋት ስምምነት እንደ ትክክለኛ አማራጭ ታይቷል ። በ1988 የኑክሌር ጦር መሣሪያዎችን ለመገንባት የቀሩት እቅዶች በሙሉ ወድቀዋል ስዊዘርላንድ ለሴቶች የመምረጥ መብት የሰጠች የመጨረሻዋ ምዕራባዊ ሪፐብሊክ ነበረች። አንዳንድ የስዊስ ካንቶኖች በ 1959 ይህንን አጽድቀዋል ፣ በፌዴራል ደረጃ ፣ በ 1971 እና ከተቃውሞ በኋላ ፣ በመጨረሻው ካንቶን አፕንዘል ኢንነርሮድ (ከሁለት የቀሩት ላንድስጌምአይንድ ፣ ከግላሩስ ጋር) በ 1990 ውስጥ ተገኝቷል ። በፌዴራል ደረጃ፣ ሴቶች በፍጥነት በፖለቲካዊ ጠቀሜታ ጨምረዋል፣ የመጀመሪያዋ ሴት ሰባት አባላት ባሉት የፌደራል ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚ ከ1984 እስከ 1989 ያገለገሉት ኤልሳቤት ኮፕ፣ እና የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት ሩት ድሪፈስ በ1999 ዓ.ም. ስዊዘርላንድ በ1963 የአውሮፓ ምክር ቤትን ተቀላቀለች። በ1979 ከበርን ካንቶን የወጡ አካባቢዎች ከበርኔዝ ነፃነታቸውን አግኝተው አዲሱን የጁራ ካንቶን ፈጠሩ። እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 18 ቀን 1999 የስዊዘርላንድ ህዝብ እና ካንቶኖች ሙሉ በሙሉ የተሻሻለውን የፌዴራል ሕገ መንግሥት ደግፈዋል። እ.ኤ.አ. በ 2002 ስዊዘርላንድ የተባበሩት መንግስታት ሙሉ አባል ሆና ቫቲካን ከተማ ሙሉ በሙሉ የተባበሩት መንግስታት አባልነት የሌላት የመጨረሻዋ ሰፊ እውቅና ያለው ሀገር ሆና ቀረች። ስዊዘርላንድ የኢኤፍቲኤ መስራች አባል ናት ግን የአውሮፓ ኢኮኖሚክ አካባቢ አባል አይደለችም። የአውሮፓ ህብረት አባልነት ማመልከቻ በግንቦት 1992 ተልኳል፣ ነገር ግን ኢኢአ በታህሳስ 1992 ውድቅ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ ስዊዘርላንድ በኢ.ኢ.ኤ ላይ ህዝበ ውሳኔ የጀመረች ብቸኛ ሀገር ነች። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአውሮፓ ህብረት ጉዳይ ላይ በርካታ ህዝበ ውሳኔዎች ተካሂደዋል; በዜጎች ተቃውሞ ምክንያት የአባልነት ማመልከቻው ተሰርዟል. ቢሆንም፣ የስዊስ ህግ ከአውሮፓ ህብረት ህግ ጋር ለመጣጣም ቀስ በቀስ እየተስተካከለ ነው፣ እና መንግስት ከአውሮፓ ህብረት ጋር በርካታ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርሟል። ስዊዘርላንድ፣ ከሊችተንስታይን ጋር፣ ኦስትሪያ ከገባችበት እ.ኤ.አ. . ይህች ሀገር በባህላዊ መልኩ እንደ ገለልተኛ እና ወደ የበላይ አካላት ለመግባት ፈቃደኛ እንደሌላት ይቆጠራል። እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 2020 ከአውሮፓ ህብረት ነፃ የሰዎች ዝውውር የሚፈቅደውን ስምምነት ለማቆም ድምጽ እንዲሰጥ የሚጠይቅ ህዝበ ውሳኔ በስዊዘርላንድ ህዝቦች ፓርቲ (ኤስ.ፒ.ፒ.) አስተዋወቀ። ነገር ግን፣ መራጮች የኢሚግሬሽንን መልሶ ለመቆጣጠር የተደረጉ ሙከራዎችን ውድቅ በማድረግ የቀረበውን ጥያቄ ከ63-37 በመቶ በሆነ ልዩነት በማሸነፍ። የመሬት አቀማመጥ በሰሜን እና በደቡብ የአልፕስ ተራሮች በምዕራብ-መካከለኛው አውሮፓ፣ ስዊዘርላንድ በ41,285 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (15,940 ስኩዌር ማይል) ስፋት ላይ እጅግ በጣም ብዙ የመሬት አቀማመጥ እና የአየር ንብረትን ያጠቃልላል። የህዝብ ብዛት ወደ 8.7 ሚሊዮን (2020 እ.ኤ.አ.) ነው። እ.ኤ.አ. በ2019 አማካይ የህዝብ ብዛት 215.2 ነዋሪዎች በካሬ ኪሎ ሜትር (557/ስኩዌር ማይል) ነበር።: 79 በትልቁ ካንቶን በአከባቢው ግራውዩንደን፣ ሙሉ በሙሉ በአልፕስ ተራሮች ላይ ተኝቶ፣ የህዝብ ጥግግት በአንድ ካሬ ኪሎ ሜትር ወደ 28.0 ነዋሪዎች ይወርዳል (73 /ስኩዌር ማይል):: 30 ትልቅ የከተማ ዋና ከተማ ባለችው ዙሪክ ካንቶን ውስጥ መጠኑ 926.8 በካሬ ኪሎ ሜትር (2,400/ስኩዌር ማይል) ነው።፡ 76 ስዊዘርላንድ በኬክሮስ 45° እና 48° እና በኬንትሮስ 5° እና 11° ሠ መካከል ትገኛለች። በውስጡም ሶስት መሰረታዊ የመሬት አቀማመጥ ቦታዎችን ይዟል፡ የስዊስ ተራሮች ወደ ደቡብ፣ የስዊስ ፕላቶ ወይም መካከለኛው አምባ እና በምዕራብ የጁራ ተራሮች። የአልፕስ ተራሮች የሀገሪቱን አጠቃላይ ስፋት 60% የሚሆነውን በመሃልኛው እና በደቡባዊው የሀገሪቱ ክፍል የሚያቋርጡ ከፍተኛ የተራራ ሰንሰለቶች ናቸው። አብዛኛው የስዊስ ህዝብ በስዊስ ፕላቶ ውስጥ ይኖራል። በስዊዘርላንድ ተራሮች ላይ ከሚገኙት ከፍተኛ ሸለቆዎች መካከል፣ ብዙ የበረዶ ግግር በረዶዎች ይገኛሉ፣ በድምሩ 1,063 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (410 ካሬ ማይል)። ከእነዚህም በአራቱ ካርዲናል አቅጣጫዎች ወደ መላው አውሮፓ የሚፈሱ እንደ ራይን፣ ኢንን፣ ቲሲኖ እና ሮን ያሉ የበርካታ ዋና ዋና ወንዞች ዋና ውሃ ይመነጫል። የሃይድሮግራፊክ አውታረመረብ በመካከለኛው እና በምዕራብ አውሮፓ ውስጥ በርካታ ትላልቅ የንፁህ ውሃ አካላትን ያጠቃልላል ፣ ከእነዚህም መካከል የጄኔቫ ሀይቅ (በፈረንሳይኛ ሌ ላክ ሌማን ተብሎም ይጠራል) ፣ ኮንስታንስ ሀይቅ (በጀርመን ቦደንሴ በመባል ይታወቃል) እና ማጊዮር ሀይቅ ይገኙበታል። ስዊዘርላንድ ከ 1500 በላይ ሀይቆች ያላት ሲሆን 6% የአውሮፓ ንጹህ ውሃ ክምችት ይዟል. ሐይቆች እና የበረዶ ግግር ከብሔራዊ ክልል 6 በመቶውን ይሸፍናሉ። ትልቁ ሀይቅ በምዕራብ ስዊዘርላንድ ከፈረንሳይ ጋር የሚጋራው የጄኔቫ ሀይቅ ነው። ሮን የጄኔቫ ሀይቅ ዋና ምንጭ እና መውጫ ሁለቱም ነው። ሐይቅ ኮንስታንስ ሁለተኛው ትልቁ የስዊስ ሀይቅ ነው እና ልክ እንደ ጄኔቫ ሀይቅ፣ በኦስትሪያ እና በጀርመን ድንበር ላይ ባለው የራይን መካከለኛ ደረጃ ነው። ሮን በፈረንሣይ ካማርጌ ክልል ወደ ሜድትራንያን ባህር ሲፈስ እና ራይን ወደ ሰሜን ባህር በኔዘርላንድ ሮተርዳም 1,000 ኪሎ ሜትር (620 ማይል) ይርቃል ፣ ሁለቱም ምንጮች ከእያንዳንዳቸው 22 ኪሎ ሜትር (14 ማይል) ብቻ ይለያሉ። በስዊስ ተራሮች ውስጥ ሌላ ከስዊዘርላንድ አርባ ስምንቱ ተራሮች በከፍታ ወይም ከዚያ በላይ በ4,000 ሜትሮች (13,000 ጫማ) ከባህር ላይ ይገኛሉ።በ4,634 (15,203 ጫማ) በሞንቴ ሮዛ ከፍተኛው ነው፣ ምንም እንኳን ማተርሆርን (4,478 ሜትር ወይም 14,692 ጫማ) ብዙውን ጊዜ እንደ ትልቁ ይቆጠራል። ታዋቂ. ሁለቱም የሚገኙት ከጣሊያን ጋር ድንበር ላይ በሚገኘው የቫሌይስ ካንቶን ውስጥ በፔኒን አልፕስ ውስጥ ነው። 72 ፏፏቴዎችን የያዘው ከጥልቅ የበረዶ ግግር ላውተርብሩነን ሸለቆ በላይ ያለው የበርኔስ ተራሮች ክፍል ለጁንግፍራው (4,158 ሜትር ወይም 13,642 ጫማ) ኢገር እና ሞንች እና በክልሉ ውስጥ ላሉት በርካታ ውብ ሸለቆዎች የታወቀ ነው። በደቡብ ምስራቅ በረዥሙ ኤንጋዲን ሸለቆ፣ በ ካንቶን የሚገኘውን የቅዱስ ሞሪትዝ አካባቢን የሚያጠቃልለውም ይታወቃል። በአጎራባች በርኒና አልፕስ ከፍተኛው ጫፍ ፒዝ በርኒና (4,049 ሜትር ወይም 13,284 ጫማ) ነው። በሕዝብ ብዛት የሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል፣ ከጠቅላላው የአገሪቱ ክፍል 30% የሚሆነው፣ የስዊስ ፕላቱ ተብሎ ይጠራል። ብዙ ክፍት እና ኮረብታ መልክአ ምድሮች፣ ከፊል በደን የተሸፈኑ፣ ከፊል ክፍት የግጦሽ መሬቶች፣ አብዛኛውን ጊዜ የግጦሽ መንጋ ወይም አትክልት እና የፍራፍሬ ማሳዎች አሉት፣ ግን አሁንም ኮረብታ ነው። ትላልቅ ሀይቆች እዚህ ይገኛሉ, እና ትልቁ የስዊስ ከተማዎች በዚህ የአገሪቱ አካባቢ ይገኛሉ. በስዊዘርላንድ ውስጥ ሁለት ትናንሽ አከባቢዎች አሉ፡ የጀርመን ነው፣ ካምፒዮን ዲ ኢታሊያ የጣሊያን ነው። ስዊዘርላንድ በሌሎች አገሮች ኤክስክላቭ የላትም። የአየር ንብረት የስዊስ የአየር ንብረት በአጠቃላይ መጠነኛ ነው፣ ነገር ግን በአከባቢዎቹ መካከል በጣም ሊለያይ ይችላል፣ በተራራ አናት ላይ ካለው የበረዶ ሁኔታ አንስቶ እስከ በስዊዘርላንድ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ባለው በሜዲትራኒያን አቅራቢያ እስከ ጥሩ የአየር ሁኔታ ድረስ። በስዊዘርላንድ ደቡባዊ ክፍል አንዳንድ ቀዝቃዛ-ጠንካራ የዘንባባ ዛፎች የሚገኙባቸው አንዳንድ ሸለቆዎች አሉ። የበጋ ወቅት ወቅታዊ ዝናብ ሲኖር ሞቃታማ እና እርጥብ ይሆናል, ስለዚህ ለግጦሽ እና ለግጦሽ ተስማሚ ናቸው. በተራሮች ላይ ያለው አነስተኛ እርጥበት ያለው ክረምት ለሳምንታት የተረጋጋ ሁኔታዎችን ረጅም ክፍተቶች ማየት ይችላል። በተመሳሳይ ጊዜ, የታችኛው መሬቶች በተገላቢጦሽ ይሰቃያሉ, በእነዚህ ወቅቶች, ስለዚህ ለሳምንታት ምንም ፀሐይ አይታዩም. ፎህን ተብሎ የሚጠራው የአየር ሁኔታ ክስተት (ከቺኑክ ንፋስ ጋር ተመሳሳይ ውጤት ያለው) በዓመቱ ውስጥ በማንኛውም ጊዜ ሊከሰት የሚችል እና ባልተጠበቀ ሞቃት ነፋስ ተለይቶ የሚታወቅ ሲሆን ይህም በዝናብ ጊዜ በጣም ዝቅተኛ አንጻራዊ እርጥበት ያለው አየር ወደ አልፕስ ተራሮች ሰሜን ያመጣል. በአልፕስ ተራሮች ደቡባዊ ፊት ላይ ጊዜያት። ይህ በአልፕስ ተራሮች ላይ በሁለቱም መንገድ ይሰራል ነገር ግን ከደቡብ ቢነፍስ ለሚመጣው ንፋስ ገደላማ እርምጃ የበለጠ ውጤታማ ነው። ከደቡብ ወደ ሰሜን የሚሄዱ ሸለቆዎች ምርጡን ውጤት ያስከትላሉ። ዝቅተኛ ዝናብ በሚያገኙ የውስጠኛው የአልፕስ ሸለቆዎች ሁሉ በጣም ደረቅ ሁኔታዎች ይቀጥላሉ ምክንያቱም የሚመጡ ደመናዎች ወደ እነዚህ ቦታዎች ከመድረሳቸው በፊት ተራሮችን ሲያቋርጡ ብዙ ይዘታቸውን ያጣሉ ። እንደ ያሉ ትላልቅ የአልፕስ አካባቢዎች ከቅድመ-አልፓይን አካባቢዎች የበለጠ ደረቅ ሆነው ይቆያሉ, እና በቫሌይስ ዋና ሸለቆ ውስጥ, ወይን ወይን እዚያ ይበቅላል. በጣም ሞቃታማው የአየር ሁኔታ በከፍታ ተራራማ አካባቢዎች እና በቲሲኖ ካንቶን ብዙ ፀሀይ ባለበት እና ከጊዜ ወደ ጊዜ ከባድ ዝናብ በሚዘንብበት አካባቢ ይቀጥላል። የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ በመጠኑ ይሰራጫል፣ በበጋ ከፍተኛ ነው። መኸር በጣም ደረቅ ወቅት ነው ፣ ክረምቱ ከበጋ ያነሰ ዝናብ ይቀበላል ፣ ነገር ግን በስዊዘርላንድ ውስጥ ያለው የአየር ሁኔታ በተረጋጋ የአየር ንብረት ስርዓት ውስጥ አይደለም። ምንም ጥብቅ እና ሊገመቱ የሚችሉ ወቅቶች ሳይኖሩባቸው ከአመት ወደ አመት ሊለያዩ ይችላሉ. ስዊዘርላንድ ሁለት የመሬት አከባቢዎችን ይይዛል-የምእራብ አውሮፓ ሰፊ ደኖች እና የአልፕስ ኮንፈር እና ድብልቅ ደኖች። የስዊዘርላንድ ስነ-ምህዳሮች በተለይ በቀላሉ ሊበላሹ ይችላሉ፣ ምክንያቱም በረጃጅም ተራሮች የሚለያዩት ብዙ ስስ ሸለቆዎች ብዙውን ጊዜ ልዩ የሆነ ስነ-ምህዳር ይፈጥራሉ። ተራራማ አካባቢዎች እራሳቸውም ለጥቃት የተጋለጡ ናቸው፣ ብዙ የእጽዋት ዝርያዎች በሌላ ከፍታ ላይ የማይገኙ እና ከጎብኚዎች እና ከግጦሽ ግጦሽ ይደርስባቸዋል። የአልፕስ አካባቢ የአየር ንብረት፣ ጂኦሎጂካል እና መልክአ ምድራዊ ሁኔታዎች በተለይ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ የሆነውን በጣም ደካማ ሥነ-ምህዳር እንዲኖር ያደርጋሉ። ቢሆንም፣ በ2014 የአካባቢ አፈጻጸም ኢንዴክስ መሰረት፣ ስዊዘርላንድ አካባቢን በመጠበቅ ከ132 ሀገራት አንደኛ ሆና ትገኛለች፣ ይህም በአካባቢ ማህበረሰብ ጤና ላይ ባላት ከፍተኛ ውጤት፣ በታዳሽ የሃይል ምንጮች (ሃይድሮ ፓወር እና የጂኦተርማል ኢነርጂ) ላይ ከፍተኛ ጥገኛ በመሆኗ እና የአካባቢ ጥበቃን በመቆጣጠር ረገድ ስዊዘርላንድ ቀዳሚ ሆናለች። በ2020 ከ180 ሀገራት ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሀገሪቱ እ.ኤ.አ. ከ1990 ጋር ሲነፃፀር በ 2030 የ ልቀትን በ 50% ለመቀነስ ቃል ገብታለች እና በ 2050 ዜሮ ልቀት ላይ ለመድረስ እቅድ አውጥታ እየሰራች ነው። ነገር ግን፣ በስዊዘርላንድ የባዮአፓሲቲ ተደራሽነት ከአለም አማካይ እጅግ ያነሰ ነው። እ.ኤ.አ. በ2016 ስዊዘርላንድ በግዛቷ ውስጥ ለአንድ ሰው 1.0 ግሎባል ሄክታር ባዮአፓሲቲ ነበራት፣ ይህም ከአለም አማካይ በ1.6 ሄክታር በአንድ ሰው 40 በመቶ ያነሰ ነው። በተቃራኒው, በ 2016, 4.6 ግሎባል ሄክታር ባዮኬጅ - የፍጆታ ሥነ-ምህዳራዊ አሻራቸውን ተጠቅመዋል. ይህ ማለት ስዊዘርላንድ ከያዘችው 4.6 እጥፍ ያህል ባዮአፓሲቲ ተጠቅመዋል ማለት ነው። ቀሪው ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት እና አለም አቀፍ የጋራ ንብረቶችን (እንደ በከባቢ አየር በካይ ጋዝ ልቀቶች) ከመጠን በላይ ከመጠቀም የመጣ ነው. በውጤቱም, ስዊዘርላንድ የባዮካፓሲቲ እጥረት እያካሄደች ነው. ስዊዘርላንድ የ2019 የደን መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ኢንቴግሪቲ ኢንዴክስ አማካይ 3.53/10 ነጥብ ነበራት፣ ይህም በአለም ከ172 ሀገራት 150ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
52626
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%AA%E1%88%BA%20%E1%88%B1%E1%8A%93%E1%8A%AD
ሪሺ ሱናክ
ሪሺ ሱናክ (/ /፤ ግንቦት 12 ቀን 1980 ተወለደ) ከ2020 እስከ 2022 የውጪ ቻንስለር ሆኖ ያገለገለ ብሪቲሽ ፖለቲከኛ ነው፣ ከዚህ ቀደም ከ2019 እስከ 2020 የግምጃ ቤት ዋና ፀሀፊ ሆኖ አገልግሏል። የኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ አባል። ከ2015 ጀምሮ ለሪችመንድ (ዮርክ) የፓርላማ አባል () ነው። በደቡብ ምስራቅ አፍሪካ በህንድ ዲያስፖራ ውስጥ ካደጉት ከፑንጃቢ ሂንዱ ወላጆች በሳውዝሃምፕተን የተወለደ ሱናክ በዊንቸስተር ኮሌጅ ተምሯል። በመቀጠል በሊንከን ኮሌጅ ኦክስፎርድ ፍልስፍናን፣ ፖለቲካን እና ኢኮኖሚክስን () አነበበ እና በኋላም በካሊፎርኒያ ከሚገኘው ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የ ምሁር ሆነ። በስታንፎርድ ሲማር የወደፊት ሚስቱን አክሻታ ሙርቲን አገኘው፣ ኢንፎሲስን የመሰረተው የሕንድ ቢሊየነር ነጋዴ የ ሴት ልጅ። ሱናክ እና ሙርቲ በብሪታንያ 222ኛ ባለጸጎች ሲሆኑ እ.ኤ.አ. በ2022 በድምሩ 730 ሚሊዮን ፓውንድ ሀብታቸው። ከተመረቀ በኋላ ለጎልድማን ሳችስ እና በኋላም በሄጅ ፈንድ ኩባንያዎች የህፃናት ኢንቨስትመንት ፈንድ አስተዳደር እና ጭብጥ አጋሮች ውስጥ አጋር ሆኖ ሰርቷል። ሱናክ በ 2015 አጠቃላይ ምርጫ በሰሜን ዮርክሻየር ለሪችመንድ (ዮርክ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመረጠ። በቴሬዛ ሜይ ሁለተኛ መንግስት ለአካባቢ አስተዳደር የፓርላማ ምክትል ፀሀፊ በመሆን አገልግለዋል። ለሜይ ብሬክሲት የመውጣት ስምምነት ሶስት ጊዜ ድምጽ ሰጥቷል። ሜይ ከስልጣን ከወጣች በኋላ ሱናክ የኮንሰርቫቲቭ መሪ ለመሆን የቦሪስ ጆንሰን ዘመቻ ደጋፊ ነበር። ጆንሰን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙ በኋላ ሱናክን የግምጃ ቤት ዋና ጸሐፊ አድርጎ ሾመው። ሱናክ በፌብሩዋሪ 2020 ከለቀቁ በኋላ ሳጂድ ጃቪድን የ ቻንስለር አድርገው ተክተዋል። እንደ ቻንስለር ሱናክ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሰጠው የፋይናንስ ምላሽ እና በኢኮኖሚው ተፅእኖ፣ የኮሮና ቫይረስ የስራ ማቆያ እና ለእርዳታ መብላትን ጨምሮ። በፓርቲጌት ቅሌት መካከል፣ በብሪታንያ ታሪክ ውስጥ የመጀመርያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ቻንስለር በመሆን ቢሮ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ህጉን በመጣስ ማዕቀብ የተጣለባቸው በመቆለፊያ ጊዜ የኮቪድ-19 ደንቦችን በመጣስ የቅጣት ማስታወቂያ ከተሰጣቸው በኋላ ነው። በመልቀቂያ ደብዳቤው ላይ በእራሱ እና በጆንሰን መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ፖሊሲ ልዩነት በመጥቀስ በጁላይ 5 2022 ቻንስለርነቱን ለቋል። በጁላይ 8 2022፣ በኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ አመራር ምርጫ ጆንሰንን ለመተካት እጩነቱን አስታውቋል። እ.ኤ.አ. ጁላይ 20፣ በኮንሰርቫቲቭ የፓርላማ አባላት መካከል በመጀመሪያ ድምጽ ሰጥቷል፣ እና አሁን በሊዝ ትረስ ላይ የፓርቲ አባላት በፖስታ ድምጽ በመወዳደር ላይ ነው፣ ውጤቱም በሴፕቴምበር 5 2022 ይገለጻል። የመጀመሪያ ህይወት እና ትምህርት ሱናክ በ12 ሜይ 1980 በሳውዝሃምፕተን ተወለደ የፑንጃቢ ዝርያ ካላቸው የሂንዱ ወላጆች ያሽቪር እና ኡሻ ሱናክ። ከሦስት ወንድሞችና እህቶች መካከል ትልቁ ነው። አባቱ ያሽቪር ተወልዶ ያደገው በኬንያ ቅኝ ግዛት እና ጥበቃ (በአሁኑ ኬንያ) ሲሆን እናቱ ኡሻ በታንጋኒካ (በኋላ የታንዛኒያ አካል የሆነችው) ተወለደች። አያቶቹ የተወለዱት በፑንጃብ ግዛት፣ ብሪቲሽ ህንድ ሲሆን ከምስራቅ አፍሪካ ከልጆቻቸው ጋር በ1960ዎቹ ወደ እንግሊዝ ተሰደዱ። ያሽቪር አጠቃላይ ሐኪም ነበር፣ እና ኡሻ በአካባቢው የሚገኝ ፋርማሲስት የሚመራ ፋርማሲስት ነበር። ሱናክ በስትሮድ ትምህርት ቤት፣ በሮምሴ፣ ሃምፕሻየር፣ እና ዊንቸስተር ኮሌጅ፣ የወንዶች ገለልተኛ አዳሪ ትምህርት ቤት፣ ዋና ልጅ እና የት/ቤቱ ወረቀት አርታኢ በሆነበት የመሰናዶ ትምህርት ቤት ገብቷል። በበጋው የዕረፍት ጊዜ በሳውዝአምፕተን ውስጥ የካሪ ቤት አገልጋይ ነበር። በሊንከን ኮሌጅ ኦክስፎርድ ፍልስፍና፣ ፖለቲካ እና ኢኮኖሚክስ () አንብቦ በ2001 በአንደኛ ደረጃ ተመርቋል። ገና ዩኒቨርሲቲ እያለ፣ በኮንሰርቫቲቭ ዘመቻ ዋና መሥሪያ ቤት ተለማምዶ ሠራ። እ.ኤ.አ. በ2001 ከወላጆቹ ጋር ለቢቢሲ ዘጋቢ ፊልም ሚድል ክፍልስ፡ ራይስ ኤንድ ስፕራውል ተጠይቀው ነበር፡ በዚህ ወቅትም እንዲህ ሲል ተናግሯል፡- “እኔ መኳንንት የሆኑ ጓደኞች አሉኝ፣ የከፍተኛ ክፍል ጓደኞች አሉኝ፣ የስራ መደብ የሆኑ ጓደኞች አሉኝ ደህና ፣ የሥራ ክፍል አይደለም ። እ.ኤ.አ. በ 2006 የፉልብራይት ምሁር ከነበረበት ከስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተቀበለ። የንግድ ሥራ ሱናክ ከ2001 እስከ 2004 ባለው ጊዜ ውስጥ ለኢንቨስትመንት ባንክ ጎልድማን ሳችስ ተንታኝ ሆኖ ሰርቷል። ከዚያም በሴፕቴምበር 2006 አጋር በመሆን ለሄጅ ፈንድ አስተዳደር ድርጅት ዘ ህጻናት ኢንቨስትመንት ፈንድ አስተዳደር ሰርቷል። በጥቅምት 2010 የጀመረው 700 ሚሊዮን ዶላር በአስተዳደሩ ስር የጀመረው የተባለው አዲስ የሄጅ ፈንድ ድርጅት። በአማቹ የህንድ ነጋዴ ባለቤትነት የተያዘው የካታማራን ቬንቸርስ የኢንቨስትመንት ድርጅት ዳይሬክተርም ነበሩ። የቀድሞ የፖለቲካ ሥራ የፓርላማ አባል ሱናክ በጥቅምት 2014 ዌንዲ ሞርተንን በማሸነፍ ለሪችመንድ (ዮርክ) የወግ አጥባቂ እጩ ሆኖ ተመርጧል። ወንበሩ ቀደም ሲል የፓርቲው መሪ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩት ዊልያም ሄግ የተያዙት ሲሆን በሚቀጥለው አጠቃላይ ምርጫ መወዳደርን መርጠዋል። መቀመጫው በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ካሉ በጣም አስተማማኝ የኮንሰርቫቲቭ መቀመጫዎች አንዱ ሲሆን በፓርቲው ከ 100 ዓመታት በላይ ተይዟል. በዚሁ አመት ሱናክ የጥቁር እና አናሳ ብሄረሰብ () የምርምር ክፍል የመሀል ቀኝ አስተሳሰብ ታንክ የፖሊሲ ልውውጥ ሃላፊ ነበር፣ ለዚህም በዩኬ ውስጥ ባሉ ማህበረሰቦች ላይ ሪፖርት አቅርቧል። እ.ኤ.አ. በ2015 በተካሄደው አጠቃላይ ምርጫ በ19,550 አብላጫ ድምፅ ለምርጫ ክልሉ የፓርላማ አባል ሆነው ተመርጠዋል። በ2015-2017 ፓርላማ ውስጥ የአካባቢ፣ ምግብ እና ገጠር ጉዳዮች ምርጫ ኮሚቴ አባል ነበር። በጁን 2016 የአውሮፓ ህብረት አባልነት ህዝበ ውሳኔ ላይ ሱናክ ብሬክሲትን (እንግሊዝ ከአውሮፓ ህብረት ለቃ) ደገፈ። በዚያው ዓመት፣ ከ በኋላ ነፃ ወደቦችን ማቋቋምን የሚደግፍ የፖሊሲ ጥናት ማእከል (የ ቲንክ ታንክ) ሪፖርት ጻፈ፣ እና በሚቀጥለው ዓመት ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የችርቻሮ ቦንድ ገበያ መፍጠርን የሚደግፍ ዘገባ ጻፈ። . ሱናክ በ2017 አጠቃላይ ምርጫ እንደገና ተመርጧል፣ አብላጫ ድምጽ 23,108 ጨምሯል። እ.ኤ.አ. በጥር 2018 እና ጁላይ 2019 መካከል የፓርላማ አባል የመንግስት ፀሐፊ ሆነው አገልግለዋል ። ሱናክ በወቅቱ ለጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ የብሬክዚት መልቀቂያ ስምምነት በሶስቱም ጊዜያት ድምጽ ሰጥተዋል እና በማንኛውም የመልቀቂያ ስምምነት ላይ ሁለተኛ ህዝበ ውሳኔን ተቃወሙ። እ.ኤ.አ. በ 2019 የኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ አመራር ምርጫ ቦሪስ ጆንሰንን ደግፏል እና በሰኔ ወር በዘመቻው ወቅት ለጆንሰን ጥብቅና ለመቆም ከፓርላማ አባላት ሮበርት ጄንሪክ እና ኦሊቨር ዶውደን ጋር በታይምስ ጋዜጣ ላይ አንድ ጽሑፍ ጽፈዋል ። የግምጃ ቤት ዋና ጸሐፊ ሱናክ በቻንስለር ሳጂድ ጃቪድ ስር በማገልገል በጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ጁላይ 24 ቀን 2019 የግምጃ ቤት ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሾሙ። በማግስቱ የፕራይቪ ካውንስል አባል ሆነ። ሱናክ በ2019 አጠቃላይ ምርጫ በ27,210 አብላጫ ድምፅ በድጋሚ ተመርጧል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሱናክ በሁለቱም የቢቢሲ እና የአይቲቪ የሰባት መንገድ የምርጫ ክርክሮች ወግ አጥባቂዎችን ወክሏል። የውጭ ጉዳይ ቻንስለር ሱናክ የኤክቼከር ቻንስለር ሆኖ ከመሾሙ በፊት ባሉት ሳምንታት ውስጥ በፕሬስ ውስጥ ብዙ መግለጫዎች በሱናክ የሚመራ አዲስ የኢኮኖሚ ሚኒስቴር ሊቋቋም እንደሚችል ጠቁመዋል ፣ ይህም በካንስለር ሳጂድ ጃቪድ በግምጃ ቤት ውስጥ ያለውን ኃይል እና ፖለቲካዊ ተፅእኖ ለመቀነስ ። ሱናክ በዶሚኒክ ኩሚንግስ የተወደደ የጆንሰን ታማኝ ታማኝ እንደሆነ ይታሰብ እና በ2019 የምርጫ ክርክር ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩን በብቃት የወከለው እንደ “የወጣ ኮከብ” ሚኒስትር ይታይ ነበር። እ.ኤ.አ. በፌብሩዋሪ 2020 ጃቪድ ቻንስለር ሆኖ እንደሚቆይ እና ሱናክ የግምጃ ቤት ዋና ፀሃፊ ሆኖ እንደሚቆይ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋና አማካሪ ኩምንግስ ፣ “እንዲከታተሉት” ጃቪድ ሱናክ በየካቲት 13 2020 የካቢኔ ማሻሻያ አካል ሆኖ ወደ ቻንስለር ከፍ ብሏል፣ ከሱ በፊት የነበረው ጃቪድ በተመሳሳይ ቀን ከስልጣን መልቀቁን ተከትሎ። ጃቪድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጆንሰን ጋር ባደረጉት ውይይት ከኤክስቼከር ቻንስለርነታቸው ተነስተዋል። በስብሰባው ወቅት ጆንሰን በኩምንግስ በተመረጡ ግለሰቦች ለመተካት ሁሉንም አማካሪዎቻቸውን በግምጃ ቤት ውስጥ እንዲያሰናብቱ ቅድመ ሁኔታ አቅርበው ነበር። ጃቪድ ሥራውን በመልቀቅ ለፕሬስ ማኅበር እንደተናገረው “ለራሱ የሚያከብር ሚኒስትር እነዚህን ውሎች አይቀበልም” ሲል ተናግሯል። አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች የሱናክን ሹመት ግምጃ ቤቱ ከዳውኒንግ ስትሪት ነፃ መውጣቱን የሚያመላክት እንደሆነ አድርገው ይመለከቱት ነበር ፣ የፋይናንሺያል ታይምስ የፖለቲካ ተንታኝ ሮበርት ሽሪምሌይ ፣ “ጥሩ መንግስት ብዙውን ጊዜ በከፍተኛ ሚኒስትሮች እና በተለይም በቻንስለር - መቻል ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ ተከራክረዋል ። መጥፎ ሀሳቦችን መዋጋት". የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሱናክ የመጀመሪያ በጀት የተካሄደው በ11 ማርች 2020 ነው። ይህ የ30 ቢሊዮን ፓውንድ ተጨማሪ ወጪ ማስታወቂያን ያካተተ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 12 ቢሊዮን ፓውንድ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖን ለመቀነስ ተመድቧል። ወረርሽኙ የፋይናንስ መዘዝን ሲያስገኝ አንዳንድ ሰራተኞች ለግምጃ ቤት የገቢ ድጋፍ እርምጃዎች ብቁ መሆን ባለመቻላቸው የቻንስለር ሱናክ እርምጃዎች ትችት ደርሰዋል። የሊበራል ዴሞክራቶች ተጠባባቂ መሪ ኤድ ዴቪ፣ ሰዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የፓርላማ አባላት ቻንስለርን ካነጋገሩ በኋላ “የሕልማቸው ሥራ ወደ ቅዠት እየተቀየረ” ኢፍትሐዊ በሆነ መንገድ “እንዲደርቁ” እየተደረጉ ነው ብለዋል። የቅጥር ጥናት ኢንስቲትዩት እንዳስታወቀው 100,000 ሰዎች አዲስ ሥራ በመጀመራቸው በጣም ዘግይተው በሥራ ማቆየት መርሃ ግብር ውስጥ ለመካተት ምንም ዓይነት የመንግሥት እርዳታ ለማግኘት ብቁ ሊሆኑ እንደማይችሉ የብሪቲሽ እንግዳ ተቀባይ ማህበር የግምጃ ቤት መረጣ ኮሚቴ ከ 350,000 እስከ በዘርፉ 500,000 ሠራተኞች ብቁ አልነበሩም። ሱናክ በወረርሽኙ ላይ ውሳኔዎችን ያሳለፈ የካቢኔ ሚኒስትሮች (እንዲሁም ጆንሰን ፣ ማት ሃንኮክ እና ሚካኤል ጎቭን ጨምሮ) ኮሚቴ አካል ነበር። ሱናክ ከጆንሰን ጋር በፓርቲ ላይ በመገኘታቸው ተቀጡ እንጂ መግለጫ አላቀረቡም ወይም ስራቸውን አልለቀቁም። የሥራ ማቆየት እቅድ እ.ኤ.አ. ማርች 17 ፣ ሱናክ 330 ቢሊዮን ፓውንድ ለንግድ ድርጅቶች የአደጋ ጊዜ ድጋፍ እና እንዲሁም ለሰራተኞች የችኮላ እቅድ አስታውቋል ። የብሪታንያ መንግስት እንዲህ አይነት የሰራተኞች ማቆያ ዘዴ ሲፈጥር ይህ የመጀመሪያው ነው። መርሃግብሩ በማርች 20 ቀን 2020 ለቀጣሪዎች 80% የሰራተኛ ደሞዝ እና የቅጥር ወጪዎችን በየወሩ ለመክፈል ድጎማ የሚሰጥ ሲሆን ይህም በአንድ ሰው በወር እስከ £2,500 ድረስ ይፋ ሆነ። ወጪው ለማስኬድ በወር 14 ቢሊዮን ፓውንድ እንደሚሆን ተገምቷል። የኮሮና ቫይረስ የስራ ማቆያ መርሃ ግብር መጀመሪያ ላይ ለሶስት ወራት ተካሂዶ ወደ ማርች 1 ተመለሰ። ለሶስት ሳምንታት የተራዘመውን የሀገሪቱን መቆለፊያ ተከትሎ እቅዱ በሱናክ እስከ ሰኔ 2020 መጨረሻ ድረስ ተራዝሟል። በግንቦት መጨረሻ ሱናክ እቅዱን እስከ ኦክቶበር 2020 መጨረሻ ድረስ አራዘመ። የስራ ማቆያ መርሃ ግብሩን ለማራዘም ውሳኔ ተደረገ። ከ1930ዎቹ ጀምሮ ያልታዩ የጅምላ ድጋፎችን፣ የኩባንያ ኪሳራዎችን እና የስራ አጥነት ደረጃዎችን ለማስወገድ ወይም ለማዘግየት። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 31 ቀን 2020 በእንግሊዝ ለሁለተኛ ጊዜ መቆለፉ ከታወጀ በኋላ እስከ ታህሳስ 2 ቀን 2020 ተጨማሪ ማራዘሚያ ተገለጸ፣ ይህ በኖቬምበር 5 2020 እስከ ማርች 31 ቀን 2021 ድረስ ረዘም ያለ ማራዘሚያ ተደረገ። እስከ ኤፕሪል 30 ቀን 2021 ተጨማሪ ማራዘሚያ በሱናክ ተገለጸ። በ17 ዲሴምበር 2020። እ.ኤ.አ. በ2021 የዩናይትድ ኪንግደም በጀት እ.ኤ.አ. በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ በእቅዱ ላይ የተደረጉ ለውጦችን ተከትሎ የሰሜን አየርላንድ የችርቻሮ ኮንሶርቲየም ዳይሬክተር እንደገለፁት ንግዶች በማይገበያዩበት ጊዜ ደመወዝ እንዲከፍሉ መጠየቁ ተጨማሪ ጫና ነው ፣የአነስተኛ ንግዶች ፌዴሬሽን ቻንስለር ማስታወቁ ተገርሟል ። ሲጨርስ የመርሃግብሩ መለጠፊያ የሰሜን አየርላንድ ኢኮኖሚ ሚኒስትር ዳያን ዶድስ እንደተናገሩት በእቅዱ ላይ የተደረጉ ለውጦች ለአንዳንድ ሴክተሮች በተለይም በእንግዶች እና በችርቻሮ ዘርፍ መቼ እንደሚከፈቱ እርግጠኛ ካልሆኑት በጣም ከባድ ሊሆን ይችላል ፣ የፋይናንስ ሚኒስትሩ ኮኖር መርፊ በበኩላቸው በኢኮኖሚው ማገገሚያ ላይ በጣም ቀደም ብሎ ነው ብለዋል ። በነሀሴ 15 80,433 ድርጅቶች በእቅዱ መሰረት የይገባኛል ጥያቄ የቀረበባቸውን £215,756,121 መልሰዋል። ሌሎች ኩባንያዎች ማንኛውንም የትርፍ ክፍያ ለማካካስ በሚቀጥለው ክፍያ አነስተኛ መጠን ያለው የገንዘብ ድጋፍ ጠይቀዋል። የኤች.ኤም.ኤም ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣኖች £3.5 ቢሊዮን በስህተት ወይም ለአጭበርባሪዎች የተከፈለ ሊሆን እንደሚችል ያምኑ ነበር። በእቅዶቹ ላይ ማጭበርበር ሰኔ 2020፣ የማጭበርበር አማካሪ ፓነል የበጎ አድራጎት ድርጅት ሊቀመንበር ዴቪድ ክላርክ እና ከፍተኛ የነጮች አንገት የወንጀል ባለሙያዎች ቡድን በመንግስት ግብር ከፋይ ላይ የማጭበርበር አደጋን ለማስጠንቀቅ ለሱናክ፣ ለብሔራዊ ኦዲት ቢሮ እና ለሌሎችም ደብዳቤ ጻፉ። የሚደገፉ የማነቃቂያ እቅዶች. የመረጃ ማዛመጃ ማጭበርበርን ለመከላከል፣ለመከላከል እና ለመለየት የሚቀበሉ ኩባንያዎች ስም እንዲታተም ጠይቀዋል። በሴፕቴምበር 2020 የመንግስት ሚኒስትሮች ስለ ቢቢኤልኤስ እና የወደፊት ፈንድ ያሳሰባቸው የመንግስት ብሪቲሽ ቢዝነስ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኪት ሞርጋን በፋይናንስ ድጋፍ እቅዶች ላይ የማጭበርበር አደጋ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ወጣ። በዲሴምበር 2020፣ ባንኮች እና ብሔራዊ የወንጀል ኤጀንሲ የን በማጭበርበር አላግባብ መጠቀም እንዳሳሰባቸው ተዘግቧል። እ.ኤ.አ. በጥር 2021፣ እንደዘገበው ለተመሳሳይ የለንደን የፋይናንስ ተቋም ይሰሩ የነበሩ ሶስት የከተማ ሰራተኞች በቁጥጥር ስር የዋሉት በተጭበረበረ በድምሩ 6 ሚሊዮን ፓውንድ ነው። ኤንሲኤ ሰዎቹ ማጭበርበርን ለመፈጸም ያላቸውን "ልዩ እውቀት" ተጠቅመው ተጠርጥረው ነበር ብሏል። ይህ የዉስጥ አዋቂ ማጭበርበር በጁን 2020 ለሱናክ በተላከው ደብዳቤ ላይ የተገለጸ አደጋ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2022 የመረጃ ነፃነት ጥያቄ ለብሪቲሽ ቢዝነስ ባንክ፣ የመንግስት አካል የብድር መመለሻ ዘዴን የሚያስተዳድረው አካል፣ አንድ አምስተኛ ማለት ይቻላል፣ ወይም እ.ኤ.አ. ሰኔ 27 ቀን 2022 193,000 ቢዝነሶች የመክፈያ ውሎቻቸውን ማሟላት አልቻሉም። የዩኬ መንግስት £4.9 ቢሊዮን የተመለሱ ብድሮች በማጭበርበር ሊጠፉ እንደሚችሉ ገምቷል። ለእርዳታ ምግብ ይበሉ በሀምሌ ወር ተጨማሪ የ30 ቢሊዮን ፓውንድ ወጪን ይፋ አድርጓል ይህም የቴምብር ቀረጥ በዓል፣ ለእንግዶች ተጨማሪ እሴት ታክስ (ተጨማሪ እሴት ታክስ) የመስተንግዶ ዘርፍ ቅነሳ፣ ከመብላት መውጣት እና ከስራ ማቆያ ጉርሻ ጋር የተያያዘ እቅድ አውጥቷል። ለቀጣሪዎች. ኢት ኦው ቶ ርዳታ ኦውት በመስተንግዶ ኢንዱስትሪ ውስጥ ለመደገፍ እና የስራ እድል ለመፍጠር ተገለጸ። መንግስት በተሳታፊ ካፌዎች፣ መጠጥ ቤቶች እና ሬስቶራንቶች የምግብ እና የለስላሳ መጠጦችን በ50% በነፍስ ወከፍ እስከ £10 ድጎማ አድርጓል። ቅናሹ ከሰኞ እስከ እሮብ በየሳምንቱ ከኦገስት 3 እስከ 31 ይገኛል። በአጠቃላይ እቅዱ 849 ሚሊዮን ፓውንድ ለምግብ ድጎማ አድርጓል። አንዳንዶች ዕቅዱ የእንግዳ ተቀባይነት ኢንዱስትሪውን በማሳደግ ረገድ ስኬታማ እንደሆነ አድርገው ይመለከቱታል፣ ሌሎች ግን አይስማሙም። ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ አንፃር፣ በዋርዊክ ዩኒቨርሲቲ የተደረገ ጥናት እንዳመለከተው እቅዱ በኮቪድ-19 ኢንፌክሽኖች ከ8 በመቶ እስከ 17 በመቶ ከፍ እንዲል አስተዋጽኦ አድርጓል። በሴፕቴምበር 2020 በ የሕዝብ አስተያየት፣ ሱናክ በኤፕሪል 1978 ከሠራተኛ ዴኒስ ሄሌይ ጀምሮ ከማንኛውም የብሪታኒያ ቻንስለር ከፍተኛውን እርካታ አግኝቷል። በሴፕቴምበር 26 ፣ ሱናክ እንደሚያስከተለው አስከፊ ኢኮኖሚያዊ መዘዞች እና ለዚያም ሊደርስበት ባለው ሀላፊነት የተነሳ የስራ መልቀቂያ ማስፈራሪያውን በመቃወም ለሁለተኛ ጊዜ መዘጋቱን ተቃውሟል ። የማርች 2021 በጀት እ.ኤ.አ. በማርች 2021 ባወጣው በጀት እ.ኤ.አ. በ2020/2021 የበጀት ዓመት ጉድለቱ ወደ 355 ቢሊዮን ፓውንድ ከፍ ማለቱን አስታውቋል፣ ይህም በሰላም ጊዜ ከፍተኛው ነው። በጀቱ የኮርፖሬሽኑ የታክስ መጠን በ2023 ከ19 በመቶ ወደ 25 በመቶ መጨመር፣ ከቀረጥ ነፃ በሆነው የግል አበል ላይ ለአምስት ዓመታት መቆየቱ እና ከፍተኛ የገቢ ግብር ገደብ እና የፉርሎፍ እቅዱን እስከ መጨረሻው ማራዘምን ያጠቃልላል። የመስከረም ወር. ሱናክ በ1974 ከሄሌይ ጀምሮ የኮርፖሬሽኑን የግብር ተመን ያሳደገ የመጀመሪያው ቻንስለር ነበር። ቋሚ የቅጣት ማስታወቂያ በኤፕሪል 12 2022 ሱናክ በመቆለፊያ ጊዜ የኮቪድ-19 ደንቦችን በመጣስ የተወሰነ የቅጣት ማስታወቂያ ተሰጥቶ ነበር። ሌሎች በርከት ያሉ ደግሞ ጆንሰንን ጨምሮ ቋሚ የቅጣት ማሳሰቢያዎችን ተቀብለዋል። ሱናክ በብሪታንያ ታሪክ ውስጥ በስልጣን ላይ እያሉ ህጉን ጥሰው የተገኙ የመጀመሪያው ቻንስለር ሆነዋል። የሚኒስትሮች ፍላጎቶች ምዝገባ እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2020 ሱናክ የሚስቱን እና የቤተሰቡን የገንዘብ ፍላጎት በሚኒስትሮች መዝገብ ላይ ከፍተኛ መጠን እንዳላሳወቀ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፣ ይህም በህንድ ኩባንያ ኢንፎሲስ ውስጥ የተካተተውን 1.7 ቢሊዮን ፓውንድ የአክሲዮን ድርሻን ጨምሮ። ሱናክ ከኃላፊነቱ ጋር "ተዛማጅ" የሆኑ ፍላጎቶችን እና "ግጭት ይፈጥራል ተብሎ የሚታሰበውን" ፍላጎቶች ለማወጅ በሚኒስቴር ህጉ መሰረት ይጠየቃል. የሚኒስትሮች ጥቅም ገለልተኛ አማካሪ ሱናክ ምንም አይነት ህግጋትን አልጣሰም ብሎ ደመደመ። ቡድን 7 የታክስ ማሻሻያ በሰኔ 2021 በለንደን ላንካስተር ሃውስ በሱናክ በተዘጋጀው የጂ7 ስብሰባ የታክስ ማሻሻያ ስምምነት ተፈረመ ይህም በመርህ ደረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ዝቅተኛ ግብር በመልቲናሽናልስ እና በመስመር ላይ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ላይ ለመመስረት ይፈልጋል። በጥቅምት 2021፣ የታክስ ማሻሻያ ዕቅድን ለመቀላቀል ስምምነት ተፈራርሟል የታቀደ አረንጓዴ ቀረጥ እንደ ቻንስለር ሱናክ በግላቸው የአረንጓዴ ቀረጥ ለመጣል የፔትሮል እና የናፍታ ዋጋ እንዲጨምር ለማድረግ በ2050 የግሪንሀውስ ጋዝ ልቀትን ወደ ዜሮ ለመቀነስ እቅዱን ለመክፈል ይረዳ ነበር። በ , የመንገድ ትራንስፖርት ብክለትን, እንዲሁም የማጓጓዣ, የህንጻ ማሞቂያ እና የናፍታ ባቡሮች, በአንድ ላይ ከ 40% በላይ የዩኬ የካርቦን ልቀትን ለመጨመር ፈለገ. ሃሳቡ በመጨረሻ በቦሪስ ጆንሰን ውድቅ ተደረገ, እሱም ለተጠቃሚዎች ወጪ መጨመር እንደማይፈልግ ለባለስልጣናቱ መመሪያ ሰጥቷል የኑሮ ውድነት በጥቅምት 2021 ሱናክ ሶስተኛውን የበጀት መግለጫ ሰጥቷል። ከሳይንስ እና ከትምህርት ጋር በተያያዙት ከፍተኛ ወጪ ተስፋዎችን አካትቷል። ሱናክ የፀደይ መግለጫውን እ.ኤ.አ. ማርች 23 ቀን 2022 ሰጥቷል። ከ -19 ወረርሽኝ ማገገም በሩሲያ ዩክሬን ወረራ ተስተጓጉሏል ብሏል። የነዳጅ ቀረጥ ቆርጧል፣ በሃይል ቆጣቢ መሳሪያዎች ላይ ተ.እ.ታን በማንሳት (እንደ ሶላር ፓነሎች እና ኢንሱሌሽን ያሉ) እና ለአነስተኛ ቢዝነሶች የሚሰጠውን የብሔራዊ ኢንሹራንስ ክፍያ ቀንሷል እና በሚያዝያ ወር የታቀደውን የብሔራዊ ኢንሹራንስ ጭማሪ ሲቀጥል ቀዳሚውን ደረጃ ከመሠረታዊው ጋር ለማጣጣም ቃል ገብቷል ። ከጁላይ ጀምሮ የግል የገቢ አበል። በ2024 የገቢ ታክስን ለመቀነስ ቃል ገብቷል።የበጀት ሃላፊነት ጽህፈት ቤት ከ1940ዎቹ ጀምሮ የግብር ጫናው ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚደርስ ተናግሯል። ሱናክ ለችግር የተጋለጡ ሰዎች የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለመርዳት የተወሰነ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል። እ.ኤ.አ. በኤፕሪል 2022 የሌበር መሪ ኬይር ስታርመር ሱናክ በኑሮ ውድነት ምክንያት ከተራ ሰዎች ትግል ጋር ግንኙነት እንደሌለው ተናግረዋል ። ክሪፕቶ ምንዛሬዎች እና ኤንኤፍቲዎች እንደ ቻንስለር ሱናክ ከእንግሊዝ ባንክ የቴክኖሎጂው የፋይናንሺያል መረጋጋት ቢፈራም ለእለት ተእለት ክፍያ የሚውልበትን አዲስ ህግ በመግፋት ላይ ነበር። እ.ኤ.አ. በኤፕሪል 2022 ሱናክ በዩናይትድ ኪንግደም የሚደገፈው የማይበገር ማስመሰያ (ኤንኤፍቲ) እንዲፈጥር ለሮያል ሚንት አዘዘው በበጋ 2022 የሚወጣ። የባለቤቱ እና የግሪን ካርዱ መኖሪያ ያልሆነ ሁኔታ የሱናክ ሚስት አክሻታ ሙርቲ መኖሪያ ያልሆነ ደረጃ አላት ይህም ማለት በዩኬ ውስጥ ስትኖር በውጪ የምታገኘውን ገቢ ግብር መክፈል የለባትም። ደረጃውን ለማስጠበቅ ወደ 30,000 ፓውንድ ትከፍላለች፣ ይህም በዩኬ ውስጥ በግምት 20 ሚሊዮን ፓውንድ የሚገመት ግብር ከመክፈል እንድትቆጠብ ያስችላታል። የሚዲያ ውዝግብ ተከትሎ፣ በኤፕሪል 8፣ በአለም አቀፍ ገቢዎ ላይ የዩኬን ግብር እንደምትከፍል አስታውቃለች፣ በመግለጫው ላይ ጉዳዩ "ለባለቤቴ ትኩረት የሚስብ እንዲሆን" እንደማትፈልግ ተናግራለች። በኤፕሪል 10 ላይ የእርሷን የግብር ሁኔታ ዝርዝር ማን እንደ ሾለከ ለማወቅ የኋይትሆል ጥያቄ መጀመሩ ተገለጸ። እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 11 ቀን 2022 ዘ ጋርዲያን “ኬይር ስታርመር ቤተሰቦቹ የራሳቸውን የግብር እዳ እየቀነሱ እያለ ለተራ ብሪታንያውያን ቀረጥ እየጣለ ነው በሚል ምክንያት ሪሺ ሱናክን 'ግብዝነት' በማለት ከሰሰው። በዚህ ጊዜ አካባቢ ሪፖርት ማድረግ ሱናክ እ.ኤ.አ. በ2000ዎቹ ያገኘውን የአሜሪካ ቋሚ ነዋሪ ካርድ እስከ 2021 ድረስ መያዙን እንደቀጠለ፣ ቻንስለር ከነበረ በኋላ ለ18 ወራት ጨምሮ፣ ይህም የአሜሪካን የግብር ተመላሽ ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ አጋልጧል። በሁለቱም የሚስቱ የግብር ሁኔታ እና የመኖሪያ ሁኔታው ​​ላይ በተደረገው ምርመራ ሱናክ የሚኒስትሮችን ህግ እንዳልጣሰ አረጋግጧል የስራ መልቀቂያ እ.ኤ.አ. ጁላይ 5 2022 ሱናክ በ ላይ በቀረበው የፆታዊ ትንኮሳ ውንጀላ ዙሪያ ሳጂድ ጃቪድ ከጤና ፀሐፊነት ከለቀቁ በኋላ ከቻንስለርነት ስራቸውን ለቀቁ። በሱናክ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤው ላይ “ህዝቡ መንግስትን በአግባቡ፣ በብቃትና በቁም ነገር እንዲመራ በትክክል ይጠብቃል። ይህ የመጨረሻው የሚኒስትር ስራ ሊሆን እንደሚችል እገነዘባለሁ፣ ነገር ግን እነዚህ መመዘኛዎች መታገል ተገቢ ናቸው ብዬ አምናለሁ እናም ለዚህ ነው ስራዬን የምለቅቀው። በሚቀጥለው ሳምንት ስለ ኢኮኖሚው የጋራ ንግግራችን ለመዘጋጀት አቀራረባችን በመሠረቱ በጣም የተለያየ እንደሆነ ግልጽ ሆኖልኛል። ከተጨማሪ የስራ መልቀቂያ በኋላ፣ ጆንሰን በጁላይ 7 ከኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ መሪነት ተነሳ። የአመራር ጨረታ እ.ኤ.አ. ጁላይ 8 ቀን 2022 ሱናክ ጆንሰንን ለመተካት በኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ አመራር ምርጫ እንደ እጩ እንደሚቆም አስታውቋል። ጆንሰንን ይደግፉ የነበሩ ወግ አጥባቂ ፖለቲከኞች ሱናክን “ጠቅላይ ሚኒስትሩን በማውረድ ግንባር ቀደም” ሲሉ ተችተውታል፣ ጃኮብ ሪስ-ሞግ ደግሞ “ከፍተኛ የታክስ ቻንስለር” ብለውታል። ጎራ ለመጀመሪያ ጊዜ በ የተመዘገበው በታህሳስ 23 2021 ሲሆን በጁላይ 6 2022 የተመዘገበ ሱናክ ቻንስለርነቱን ከለቀቀ ከሁለት ቀናት በኋላ ነው። የቀድሞው ጎራ ወደ ሁለተኛው እንደ ማዞሪያ ሆኖ ይሰራል የህዝብ ምስል እ.ኤ.አ. በ 2020 መጀመሪያ ላይ ፣የኤክስቼኩር ቻንስለር ሆነው ከተሾሙ በኋላ ፣ ሱናክ በአንፃራዊ ጨለማ ውስጥ በሕዝብ ንግግር ላይ ደረሰ። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ የመጀመሪያ ደረጃዎች እሱ በብሪቲሽ ፖለቲካ መስፈርቶች በጣም ታዋቂ ነበር ፣ በአንድ ተንታኝ “ከቶኒ ብሌየር የጅምላ ዘመን ጀምሮ ከማንኛውም ፖለቲከኛ የተሻሉ ደረጃዎች” እንዳለው ሲገለጽ። የተለያዩ ምርጫዎች እንደሚያሳዩት ሱናክ በ2020 በኮንሰርቫቲቭ ደጋፊዎች እና በሌሎች በርካታ ብሪታንያውያን ዘንድ ተወዳጅ ሆኖ ቆይቷል።በዚህ ጊዜ ውስጥ የኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ ጠቅላይ ሚኒስትር እና መሪ ለመሆን ተመራጭ ሆኖ በሰፊው ይታይ ነበር። ሱናክ በማህበራዊ ድህረ ገጾች እና በመጽሔቶች ላይ የጾታ ስሜትን የሚስብ ሆኖ በመሳለቅ እና በመሳቅ በመከተል የአምልኮታዊ ሚዲያ የሆነ ነገር ፈጠረ። በ2021 ለሱናክ ያለው ህዝባዊ አመለካከት በሰፊው አዎንታዊ ሆኖ ቆይቷል፣ ምንም እንኳን ታዋቂነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ሄደ። እ.ኤ.አ. በ2022 መጀመሪያ ላይ፣ የኑሮ ውድነቱ እያደገ የህዝቡ ትኩረት እየሆነ በመምጣቱ የሱናክ ምላሽ እንደ ቻንስለር ኦፍ ኤክስቼከር፣ በቂ እንዳልሆነ ተገንዝቦ አንዳንድ ዝቅተኛ የማጽደቅ ደረጃ አሰጣጡን አግኝቷል። የሱናክ ቤተሰብ የፋይናንስ ጉዳዮች ሲፈተሹ ይህ ውድቀት ቀጠለ የግል ሕይወት ሱናክ በነሀሴ 2009 የህንዱ ቢሊየነር ኤን አር ናራያና ሙርቲ ልጅ የሆነችውን አክሻታ ሙርቲን አገባ። በብሪታንያ ካሉት ሀብታም ሴቶች አንዷ አድርጓታል። እ.ኤ.አ. በ2022 ሩሲያ በዩክሬን ላይ ያደረገችውን ወረራ ተከትሎ በሱናክ እና በቤተሰቡ ላይ ትችት አስከትሎ የነበረ ቢሆንም፣ በሚያዝያ ወር ላይ ግን የሩሲያ ቢሮውን እንደሚዘጋ አስታውቋል። በሁለቱ የጄሚ ኦሊቨር ሬስቶራንት ንግዶች፣ ዌንዲ በህንድ፣ ኮሮ ኪድስ እና ዲግሜ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ላይ አክሲዮኖች አሉት። ሱናክ እና ሙርቲ በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ ተገናኙ; ሁለት ሴት ልጆች አሏቸው. የአባቷ የኢንቨስትመንት ኩባንያ ካታማራን ቬንቸርስ ዳይሬክተር ናቸው። የሚኖሩት በኪርቢ ሲግስተን ማኖር በሰሜን ዮርክሻየር በኖርዝለርተን አቅራቢያ በሚገኘው በኪርቢ ሲግስተን መንደር ነው። እንዲሁም በማዕከላዊ ለንደን ውስጥ በኬንሲንግተን ውስጥ የሜውስ ቤት፣ በሎንዶን ኦልድ ብሮምፕተን መንገድ ላይ ያለ አፓርታማ እና በሳንታ ሞኒካ ፣ ካሊፎርኒያ ውስጥ የሚገኝ የቤት ውስጥ አፓርታማ አላቸው። ሱናክ የሂንዱ እምነት ተከታይ ነው፣ እና በብሃጋቫድ ጊታ በሚገኘው የኮመንስ ቤት የፓርላማ አባል በመሆን ቃለ መሃላ ፈጸመ። ቲቶቶለር ነው። እሱ ቀደም ሲል የምስራቅ ለንደን ሳይንስ ትምህርት ቤት ገዥ ነበር። ሱናክ ኖቫ የሚባል ላብራዶር አለው። የሱናክ ወንድም ሳንጃይ የሥነ ልቦና ባለሙያ ነው። እህቱ ራኪ የተባበሩት መንግስታት አለም አቀፍ የትምህርት ፈንድ የትምህርት ፕላን ስትራቴጂ እና እቅድ ዋና መሪ ነች። ሱናክ ከትምህርት ዘመናቸው ጀምሮ ከሚያውቃቸው የ የፖለቲካ አርታኢ ጄምስ ፎርሲት ጋር የቅርብ ጓደኛሞች ናቸው። ሱናክ ከጋዜጠኛ አሌግራ ስትራትተን ጋር በፎርሲት ሰርግ ላይ ምርጥ ሰው ነበር እና አንዳቸው ለሌላው ልጆች አማልክት ናቸው። እ.ኤ.አ. በኤፕሪል 2022 ሱናክ እና ባለቤቱ ከ11 ዳውኒንግ ስትሪት ወደ አዲስ የታደሰ የቅንጦት የምዕራብ ለንደን ቤት እንደሄዱ ተዘግቧል። በእሁድ ታይምስ የሪች ሊስት 2022 የእንግሊዝ ባለጸጎች ደረጃ ሱናክ እና ሙርቲ 222ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።በአጠቃላይ ሀብታቸው 730 ሚሊየን ፓውንድ ይገመታል።
2482
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B1%20%E1%8A%83%E1%8B%AD%E1%88%88%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D
መንግስቱ ኃይለ ማርያም
ይህን ታሪክ የጸፍው ግለሰብ የመንግስት ሀይለማሪያ ቀንደኛ ደጋፊ እንደሆነ ከፁሁፉ አንጸር መርዳት አያዳግትም ትክክለኛውን ታሪክ ከምንጭ ጋር እንደሚያስተካክልው ተስፍ አደርጋለሁ። መንግሥቱ ኀይለማሪያም በግንቦት 27 በ1929 እ.ኤ.አ. በአዲስ አበባ ተወለዱ። አባታቸው ሃምሳዓለቃ ሃይለማሪአም ወልዴ፣ እናታቸው ብዙነሽ ተሰማ ነበሩ የአሁኑ መንግስት እና ብዙ የምእራባውያን መንግስታት እሱን እንደ ኮሚኒስት ተኮር አምባገነን አድርገው የሚቆጥሩት ሲሆን የቀድሞው አምባገነን ሮበርት ሙጋቤ የጥገኝነት ጥያቄውን ከተቀበሉ ወዲህ ወደዚምባብዌ ተሰዷል ፡፡ ምንም እንኳን መንግስት እንደዚህ ያሉ ክሶችን በተደጋጋሚ ቢክድም በ 2006 በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ፍ / ቤት በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሷል ፡፡ ሆኖም በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል እንዲከሰስ በሄግ አልተከሰሰም ፡፡ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም' ከ1966 እስከ 1983 ዓ.ም. (1974 እስከ 1991 እ.ኤ.አ.) ለ17 ዓመታት የኢትዮጵያ መሪ ነበሩ። ወደ ስልጣን የወጡት በደርግ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን በመገልበጥ ሲሆን የአብዮቱ መሪ ሆነው ከቆዩ በኋላ በመለስ ዜናዊ በሚመራው በኢሓዴግ ሽምቅ ተዋጊ ቡድን እና በአሜሪካው የቀድሞው የሲአይኤ ዳሪክተር ሃርማንኮህ እርዳታ በ1983ዓ.ም ከስልጣን ተወገዱ። በአሁኑ የሀገሩ መንግስት እና በአብዛኞቹ የምዕራባውያን አገራት የኮሚኒስት አምባገነን ተደርጎ ፣ ይህ መፈንቅለመንግስት በሲአይኤ ስውር ዘዴ የተከናወነ ሲሆን የህወሓትና የሻእብያው መሪ ከሱዳን በቦይን 777 ከቀድሞው ከሲአይኤ ዳሪክተር ከ ሃርማንኮህ ጋር ታጅበው አዲስ አበባ ገብተዋል። ይህነው የኮሎኔል መንግሰቱ ኃይለማርያም የመንግሰቱ ግልበጣ ሳቦታጅ!! መንግስቱ ኃይለማርያም ያላሰበው ግልበጣ ተቀናብሮበት ያለአማራጭ በአየርላይ ቀረ እንጂ በራሱ ፍላጎት ሸሽቶ ዚምቡዋቤ ተሸሸገ የሚለው አባባል ከእውነት የራቀነው። ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም በቃላቸው የሚገኙ አገር ወዳድ ጀግና ሰው እንደነበሩ እናውቃለን። መንግሥቱ ኃይለማሪያም ወደ ርዕሰ ብሄርነት ሥልጣን ብቅ ሲሉ ገና የ፫፯ ዓመት ወጣት የነበሩ ሲሆኑ በሀረር የ3ኛ ክፍለ ጦር የመሳሪያ ግምጃ ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር። በወቅቱ በክፍለ ጦሩ አዛዥ የነበሩት ጀነራል ሓይሌ ባይከዳኝ የሚባሉ ኮ/ መንግስቱን በባህሪያቸው በመጠርጠራቸው ከአጠገባቸው ዞር ለማድረግ ወደ ኦጋዲን አዛውረዋቸው እንደ ነበር ይነገራል። በእዚያም ጥቂት ጊዜ በኋላ ለትምህርት ወደ አሚሪካ ሜሪላንድ ለወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት ተላኩ። ከትምህርት ሲመለሱም በ3ኛ ክፍለ ጦር የመሳሪያ ግምጃ ቤት ሃላፊ ሆነው ተሾሙ። ከዛም በደረጃ እድገት ካገኙ በሁዋላ የአፄ ኃይለስላሴን ጨቋኝ አገዛዝ ለመገርሰስ የደርግ ኩዴታን መሰረቱ በመኮንኖች ህብረት የተመሰረተው ደርግ በአብዛኛው ተደማጭነትና የፓለቲካ ብስለት በነበራቸው በቆራጥነታቸው ታዋቂ በሆኑት በመንግስቱ ኃይለማርያም ስልታዊ አደረጃጀት ተቀናብሮ የንጉሱን ወንበር ገለበጡት ይህ በሆነ ወቅት በነበረው አለመረጋጋት በከተማው የተኩስ ልውውጥ ተደረጎነበር። የመጀመርያውን ስልጣን በመያዝ የደርግ ሊቀመንበር ሆነው የተሾሙት ጀኔራል አማን አምዶም ነበሩ። በተለያየ አመታት በተለያየ ክህደትና አሻጥር የተገኙ አመራሮች ከስልጣን ሲወገዱ ቆይተው በአራ0ተኛው ዙር ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ የመጀመርያው ፕሬዚዳንት ለመሆን በቅተዋል። ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት ሶማሊያየዚያድባሬ መንግስት በሶቭየቶች ተደግፋ ሀገራችንን ድንገት ወረረች። በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩትን ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተርን ፈጣን ወታደራዊ እርዳታ ጠይቀው እሳቸውም የንጉሱ የቅርብ ወዳጅ ስለነበሩ በስዊስ ባንክ ያለውን የኢትዮጵያ ሃብት ለመንግስቱ ኃይለማርያም ከሰለመስጠት በተደረገው ውይይት የአሜሪካ እጅ ስለነበረበት መንግስቱ ነጮችን በ73 ሰአት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ አድርጎ ስለነበር በዚህ ቂም ጥያቄውን ሳይቀበሉ ቀሩ። በእዚህም ምክንያት አማራጭ ያጣው ደርግና መንግሥቱ ሀገሪቱ በከፍተኛ ስጋት ላይ በመውደቋ የግድ ወደ ሞስኮ መሳሪያ ልመና ልኡካን ላኩ። በሌላ በኩል ሞስኮ ከሶማሊያ ጋር ጥቅምዋን በማወዳደር ለመንግስቱ መሳሪያ መስጠት ካስፈለገ በፊርማ ሶሻሊስት ካምፐ መግባቱን እንዲያረጋግጡ ስለ ጠየቀች ኮ/መንግሥቱ ይህን በማድረጋቸው በይፋ የሚመሩት አብዩት የሌኒኒስት ማርክሲስት መሆኑን በአዋጅ አሳወቁ። ኮ/መንግሥቱ የቼጉቬራና የሶቬቱን ማርክሲዝም አሜሪካ ለወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት በተላኩበት ዘመን ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ሃር ሳይመለሱ ወደ ሞስኮ በማምራት የራሻን ሶሻሊዝም በግላቸው ተምረው ነበር፣ወደ አገር ሲመለሱም ንጉሱ በዚህ ድርጊታቸው ለሁለት አመት በኦጋዴን በረሃ በቅጣት እንዲቆዩ ተደርጎነበር። የመንግስቱ ስለሶቪየት ሶሸሰሊዝም ፖለቲካ እውቀት የሚያውቁት የቅርብ መኮንኖች በደርግ ኩዴታው የነቃውንና ብስለት ያለውን ደፋሩን መንግስቱ ኃይለማረወያምን ነበር በአደራጅነት የመደቡት። ከስምምነቱም በሁዋላ በ፪ ወር ጊዜ ውስጥ የብዙ ሚሊዮን ዶላር ታንክና የጦር መሣሪያ እርዳታ ማግኘት ብቻ ሳይሆን በሞስኮ በኩል የኩባን የጦር አማካሪዎች በማግኘታቸው የወራሪውን የሶማሊያን ኃይል መመከት ችለዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አሜሪካ የጭንቅ ጊዜ ጥያቄ መላሽ ሆና ባለመገኘትዋና በንጉሱ ስም በስዊስ ባንክ የተቀመጠውን በትሪሊዮን የሚቆጠር ዶላርና ወርቅ የስዊስ ባንክ ለኢትዮጵያ መንግስት እንድትመልስ መንግስቱ ኃይለማረወያም ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ በማድረጓ የአሜሪካ ትብብር በመኖሩ ምክንያት መንግስቱ ኃይለማርያም በስልጣን እስከቆዩበት ዘመን ሁሉ በዋና ጠላትነት ተፈርጀዋል። አንዳንድ ሚሲዮናዊያንንም ከአገር አባረሩ። በንጉስ ኃይለስላሴ ፊርማ በስዊስባንክ የነበረው የኢትዮጵያ ሃብት እስካሁን አልተመለሰም። አብይ አህመድ ይህን የመጠየቅ ወኔ የለውም፣ምፅዋእት ከመለመን በቀር። በወቅቱ በአገር ውስጥ ግንባር ቀደም ተቃናቃኝና ተቃዋሚ ከነበረው ከኢህአፓ ጋር የከተማ ለከተማ ውጊያና መገዳደል ተጀመረ። ሁለቱም ወገኖች ቀን በቀን ግድያም ለብዙ ወጣትና አዋቂ እልቂት ምክንያት ሆኑ። መንግሥቱ ኃ/ማሪያም በወታደራዊ አመራር ውስጥ የተከስተው የስልጣን ዝቀጠትና ምግባረ ብልሹነት፤ የደህንነቱ ክፍል በሁለት ቢላዋ መብላት፣ ተደማምሮ ውድቀታቸውን እንዳፋጠነው የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። የመንግስቱን አስተዳደር ለውድቀት ያበቃው የኮሎኔሉ አምባገነን አመራር ነው የሚሉት ተቀናቃኞቻቸውና በሁለት ቢለዋ እየበሉ አገርን ለመሸጥ ያስማሙ የነበሩ በወቅቱ (በመኢሶን) ውስጥ ተሰግስገው የነበሩ የኦነግ ስውር ባንዳ መኮንኖችና የ() እና የ () ሰላዮችና አገር በሆድና በስልጣን የሸጡ የመንግስቱ ተቀናቃኞች መረጃን አሾልኮ ለተቃዋሚ ኃይሎች አሳክፎ በመስጠት እንደሆነ ይታወቃል። በመንግስቱ ኃይለማርያምላይ የተቀነባበረ የ 16 ግዜ የመግደል ሙከራ ተደርጎባቸው አምልጠዋል። ጠላቶቻቸው ከውስጥና ከውጭ ብዙ ስለነበሩ ለ17 አመታት ቀንና ሌሊት ሲዋጉ አገርን በልማት በምርት ዘመቻ፣በትምህርትዘመቻ፣እንዲሁም ስራአጥነትንና ሴተኛ አዳሪነትን ለማስወገድ የኢንዱስትሪ ስራዎችን በመክፈትና በማስፋፋት መሬትን ለአራሹ በመሰከፋፈል፣ ለደሃው ህዝብ ርካሽ የቤትክራይን በመደንገግ፣ለአገራቸው ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ታላቅ መሪናቸው። ይህን በጎ ተግባራቸውን ለመናገር የሚያንቃቸው የግል ጥቅማቸውን ከአገር ጥቅም ይልቅ አብልጠው የሚወዱ ተቀናቃኝ ሰዎች ብቻ ናቸው። መንግሥቱ (የቀድሞው) ርዕሰ ብሔር ማንኛውም መሪ ላይ ሊከሰት የሚችል ስህተት ነው የፈፀሙት...ስለ ሐገር ስለ ብሔራዊ ክብር እና ኩራት ግን እርሳቸው ! ከፊት ቢሠለፉ የሚገባቸውና የሚያምርባቸው ናቸው። የኮሎኔል መንግስቱን ህይወት ተቀጥፋ ለማየት የጓጉና የፎከሩ ሁሉ ቀድመዋቸው ሞተዋል!! የእድሜ በለፀጋው ጓድ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሦስት ልጆች አባት ሲሆኑ 3ስቱም ልጆቻቸው ዶክተሮች ናቸው። ዛሬ የ 83 አመት አዛውንት ሆነው በሃራሬ በህይወት ይገኛሉ። ማህበራዊ አውታረ መረቦች መንግስቱ በፌስቡክ
35817
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%89%80%E1%89%A5
ማዕቀብ
ማዕቀብ የፖለቲካና የኢኮኖሚ እገዳ ሲሆን ሕጋዊ በሆነ ውሳኔ ኃይል ተጠቅሞ አንድን ሰው፣ ሀገር ወይም ተቋም ከያዘው አፈንጋጭ አስተሳሰብ ወይም ድርጊት እንዲመለስ፣ የሚጠበቅበትን መስመር እንዲከተል ወይም ለትክክለኛው ሕግ ተገዥ እንዲሆን ለማድረግ በፖለቲካና በኢኮኖሚ እገዳ አማካይነት የሚወሰን ቅጣት ነው። ይህ ዓይነቱ ቅጣት በተለይ የሚጣለው ዓለም አቀፋዊ ውሳኔዎችን በማያከብር ወገን ላይ ሲሆን በሙሉ ተፈጻሚነት ሊያገኝ የሚችለው የውሳኔው ደጋፊዎች ቅጣቱ ከተጣለበት ወገን ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚና የፖለቲካ ግንኙነት ሲያቋርጡና እንዲሁም ሕገወጥ ድርጊቱን በማንኛውም ቦታና ጊዜ በማጋለጥና በማውገዝ ነው። የማርክሲዝም ሌኒኒዝም መዝገበ ቃላት ፤ ፲፱፻፸፰፤ ገጽ 89 የፖለቲካ ጥናት
52507
https://am.wikipedia.org/wiki/The%20Defenders
The Defenders
(የተከሳሽ ጠበቃዎች) ከ1961 እስከ 1965 እ.ኤ.አ. ድረስ የተሠራ አሜሪካዊ የፍርድ ቤት ድራማ ነው። የተከሳሽ ተበቃዎቹ ቡድን አባትዬው ሎረንስ ፕረስቶን እና ልጁ ኬኔስ ፕረሥቶን ሲሆኑ በፍርድ ቤት አጥር ግቢ ውስጥ በተለይ ውስብስብ በኾኑት ጉዳዮች ልዩ ሙያ አላቸው። 132 ክፍሎች ተሠሩ። ተከታታይ ፊልሞች የቴሌቪዥን ትርዒት የአሜሪካ ፊልሞች
3404
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%B3%E1%88%9B
አዳማ
ናዝሬት ወዲህ ይመራል። ለእስራኤል ከተማ፣ ናዝሬት፣ እስራኤልን ይዩ። ኣዳማ በአማርኛ ናዝሬት በኦሮሚያ ክልል ለኦሮሚያ በዋና ከተማነት የሚያገለግል የኢትዮጵያ ከተማ ነው። በምስራቅ ሸዋ ዞን በላቲቱድና ሎንጂቱድ ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ ምዕራብ 100 ኪሎመትር ላይ ይገኛል። እንደ ሲቲ ፖፑሌሽን መረጃ አዳማ ከተማ የ456,868 ሰዎች መኖሪያ ስትሆን ሲሆን ከኗሪዎቿ 223,560 ወንዶችና 233,308 ሴቶች ናቸው። አዳማ በትራንስፖርት ማእከልነት የታወቀ ከተማ ነው። ከተማው በአዲስ አበባና በድሬዳዋ መንገድ ላይ ይገኛል። አዲስ አበባ ጅቡቲና አሰብ (ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በፊት ኢትዮጵያ አሰብን ስትጠቀም) የሚመላለሱ ቁጥራችው ከፍ ያሉ የጭነት መኪኖች የሚያልፉት በአዳማ ነው። ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ የሚሄደው ምድር ባቡርም አዳማን ያቋርጣል። የኢትዮጵያ ከተሞች
50003
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%81%E1%88%B6%E1%89%BD%20%E1%8C%A5%E1%8A%93%E1%89%B5%20%E1%88%B3%E1%8B%AD%E1%8A%95%E1%88%B5%20%E1%8B%88%E1%8B%AD%E1%88%9D%20%E1%88%9D%E1%88%85%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%88%B5%E1%8A%93
የቁሶች ጥናት ሳይንስ ወይም ምህንድስና
የቁሶች ጥናት ሳይንስ ወይም ምህንድስና በሲቪል ምህንድስና ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ሚና ይይዛል። የቁሶች ጥናት ሳይንስ ወይም ምህንድስና የቁሶችን ተፈጥሮዋዊ ባህሪ የሚያጠና የሳይንስ ወይም የምህንድስና ዘርፍ ነው። ለግንባታ ከሚውሉ ቁሳቁሶች ውስጥ ኮንክሪት፣ የአስፋልት ኮንክሪት፣ እንደ ብረት እና አልሙኒየም ያሉ ጠንካራ ብረታ ብረቶች ፣ የፕላስቲ ውጤቶችና የመሳሰሉት ይገኙበታል። የቁሶች ጥናት የግንባታ አካላትን ከተለያየ ጥቃት ለመከላከል የሚውሉ ቅባቶችና የመከላከያ ንጣፎችን፣ እንዲሁም አንድን የብረት አይነት ከሌላ የብረት አይነት ጋር በማደባለቅ ለግንባታ ተስማሚ የሆነ ሌላ አይነት የብረት አይነት ማምረት የመሳሰሉ ስራዎችንም ያጠቃልላል። የቁሶች ጥናት የትግበራ ፊዚክስና () የኬሚስትሪ እውቀቶችን የያዘ የምህንድስና ዘርፍ ነው። በቅርቡ እየተስፋፋ የመጣው የናኖ ሳይንስ ወይም ቴክኖሎጂን (ናኖ ሳይንስ የአንድን ቁስ የአቶምና የሞሎኪዮል አወቃቀር በመቀየር በተፈጥሮ የማይገኙ ለየት ያለ ባህሪ ያላቸውን ቁሶች ለመስራት የሚደረግ ጥረት ነው) ደረጃ ተንተርሶ በአሁኑ ጊዜ የቁሶች ጥናት ከፍተኛ የሆነ የምርምር ድርሻን ይዞ ይገኛል። የቁሶች ጥናት ምህንድስና በምርምር ምህንድስናና የግንባታ አካላት ከጥቅም ውጪ የመሆን መንስኤን ለማጥናት በሚደረጉ ስራዎች ላይ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። ቁሶች ጥናት ሳይንስ
9607
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%8C%B8
ተረት ጸ
ጸሀይ ሳለ ሩጥ አባት ሳለ አጊጥ ጸሀይ ብልጭ ወፍ ጭጭ ሲል ጸሀይ ካልወጣ ከሰፈረበት አይነሳ አንበጣ ሴት ምክንያት አታጣ ጸሀይ የጠዋት አዱኛ የሽበት ጸሀይ ያየውን ሰው ሳያየው አይቀርም ጸሀይና ንጉስ ሳለ ሁሉም አለ ጸሎት በጽሞና ነገር በደመና ጸሎት በፍቅር ሀይማኖት በምግባር ጸሎት ከፍቅር ሀይማኖት ከምግባር ይበጃል ጸሎት ከፍቅር ሀይማኖት ከግብር ጸሎት ያለፍቅር ሀይማኖት ያለግብር አይረባም ጸጸት እያደር ይመሰረት ጻድቃን ሳይቀጣጠሩ ይገናኛሉ ጻድቃን ሳይቀጣጠሩ ይገናኛሉ ሀጥአን ግን በተቃጠሩበት ይተጣጣሉ ጽዋ በተርታ ስጋ በገበታ ጽድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ ጽድቁ ቀርቶብኝ በውሉ በኮነነኝ ጽድቅ ለመንኳሽ ቀኝ ለከሳሽ ጽድቅ እንደ ላሊበላ እድሜ እንደ ማቱሳላ ይስጥህ ጽህፈት በብራና ዘፈን በበገና ጾማ ጾማ ለጸሎተ ሀሙስ እርጎ ትልስ ጾም ገዳፊና ሰው ጠባቂ ለጥቂት ይሳሳታል
13752
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%88%8D%E1%89%A3%20%E1%88%9B%E1%88%BB%E1%8B%8D%20%E1%88%9A%E1%8A%AB%E1%8A%A4%E1%88%8D
የተልባ ማሻው ሚካኤል
የተልባ ማሻው ሚካኤል አለቃ ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር ሲመለሱ ያው የግድ የአባይን በረሀ ማቋረጥ ነበረባቸው። አብረዋቸው የነበሩ መንገደኞች በቃ የአባይ ሽፍታ ሊዘርፈን ነው ብለው ሲያለቃቅሱ። አለቃ ብራችሁን ሰብስቡና አምጡ ብለው - መንገድ ሲሄዱ ተልባ እየወቀጡ የሚበሉበት ሙቀጫ ውስጥ ብሩን በሙሉ ይጨምሩና አፉን ወትፈው፤ ሙቀጫውን የቤተ ክርስቲያን ጨርቅ አልብሰው ለአንዱ መንገደኛ እንደታቦት አሽክመው ሲጓዙ ሽፍቶቹ ዘንድ ይደርሳሉ። ሽፍቶቹም ብቅ ብቅ ይሉና «ምንድናችሁ?» ይላሉ። አለቃም ፈጠን ብለው «ታቦት ልናስገባ ይዘን የምንመጣ መንገደኞች ነን» ይላሉ። አንዱ ሽፍታም «የታቦቱ ስም ማን ነው?» ይላል። አለቃም «የተልባ ማሻው ሚካኤል ነው» ብለው መለሱ። ሽፍቶቹም ተሳልመው መንገደኞቹም በሰላም በረሀውን አለፉ። የኢትዮጵያ ቀልዶች
12901
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B5%E1%88%98%E1%89%B5
ድመት
ድመት አንስተኛ ስጋ በሊታ እንስሳ ስትሆን እቤት ውስጥ አይጥና የመሳሰሉትን ተውሳኮች ለመያዝ ታገለግላለች። ድመት በአሁኑ ጊዜ ከሁሉም እንስሳ በላይ በቤት እንስሳነቱዋ ተፈላጊነትን ያላት ናት። ተመራማሪወች የድመትን ለማዳነት ቢያንስ ቢያንስ 9500 ዓመት እንደሚሞላው ሊያረጋግጡ ችለዋል። የቤት እንስሳ ድመቶች እንዳሉ ሁሉ በየዱሩም የሚላወሱ፣ ምግባቸውን አድነው መብላት የሚችሉ ድመቶችም አሉ። ለማደን እንዲረዳቸውም አይናቸው የሰው ልጅ ማየት ከሚችልበት 1/6ኛ ብርሃን ውስጥ እንኳ ይሰራል፣ ጆሮዋቸውም ከሰውና ከውሻ ይልቅ በጣም ሃይለኛ ነው፣ አፍንጫቸውም እንዲሁ። የድመቶች ድክመት ምንድን ነው፣ ስኳር ስኳር የሚልን ነገር መቅመስ አይችሉም፣ ከዚ በተረፈ አይናቸው ከአረንጓዴና ሰማያዊ ቀለማት ውጭ መለየት አይችልም። ለምሳሌ ቀይና አረንጓዴ ለድመት አንድ አይነት ቀለም ነው። ደግሞ ይዩ የድመት አስተኔ የውጭ ማያያዣዎች ለማዳ እንስሶች የዱር አራዊት
31254
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A6%E1%8B%B5%E1%89%A5%E1%8A%AB%E1%8B%B5
ቦድብካድ
ቦድብካድ በአይርላንድ አፈ ታሪክ ምናልባት በ366 ግድም የአየርላንድ ከፍተኛ ነጉሥ ነበር። በ17ኛው ክፍለ ዘመን የታተሙት የአይርላንድ ታሪኮች እንዳሉት የቦድብካድ ዘመን ፩ ቀን ከግማሽ ብቻ ነበር። ቅድመኞችሁ ታሪኮች ግን ቦድብካድ ንጉሡን ኡጋይነ ሞር ከገደለ በኋላ፣ የኡጋይነ ልጅ ሎጋይረ ሎርክ ቦድብካድን ገድሎ በቀጥታ ከፍተኛ ንጉሥ ሆነ። በተለይ የላውድ አቆጣጠሮች (1014 ዓም ተቀነባብሮ) እና የድሮ አቆጣጠር በመከተል፣ ይህ ዘመን በ366 ዓክልበ. ይሆናል። በኋላ የታዩት ታሪኮች ግን ከዚያ በፊት ያደርጉታል። የአየርላንድ አፈታሪካዊ ነገሥታት
10335
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%88%A8%E1%8C%80%20%E1%8A%A8%E1%89%A0%E1%8B%B0
ደረጀ ከበደ
ደረጀ ከበደ እውቅ የክርስቲያን ዘማሪ፡ የዘመራቸው መዝሙሮች አብዛኛዎቹ ከሕይወቱ ገጠመኝ ጋር የተያያዘ በመሆኑ ልዩ ያረገዋል ደረጀ ከበደ የመጀመሪያ ቋንቋው አማርኛ ቢሆንም በኦሮምኛም ዘምሮአል ። ደረጀ በተለይ በውብ ድምጸ ቅላጤው ሲዘምር የሰሚውን ጆሮና ልብ ያነቃቃል። ዝማሬዎቹ የአብዛኞችን ህይወት ለውጠዋል፥ አፅናንተዋል፥ አንፀዋል የክህደት ትምህርቶችን ገስፀዋል በኢትዮጵያ የፕሮቴስታንት አማኞች ዘንድ በመንግስታት ለተጎዱ ህዝቦች መብት መቆም() መቃወም የሚያስገፋና መጥፎ ስሞችን የሚያሰጥ ሲሆን ዶ/ደረጀ ከበደ ግን በዝማሬዎቹም በዩትዩብ የምስል ቪዲዮ ኢሰብዐዊነትን ማጋለጡ ለየት ከማድረጉም በልይ ከብዙ ታዋቂ የፕሮቴስታንት አባቶች ጋርም ያመሳስለዋል። ዶ/ር ደረጀ ከበደ የመጀመሪያ ዲግሪውን በአግሮ ኢኮኖሚክስ - በክርስቲያን ትምርህት የማስተርስ ዲግሪ -በ አዲክሽን ስተዲስ የማስተርስ ዲግሪ እና በሄልዝ ሳይንስ በዶክትሬት ተመርቆ እየሠራ ይገኛል።
46168
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%AD%E1%8A%A5%E1%88%B5%20%E1%8A%A3%E1%88%8D%E1%89%A3
ርእስ ኣልባ
ርእስ ማለት የኣንድ ነገር የበላይ የሆነ ፣ መሰረት ፣ መጀመሪያ ፣ ልክ እስትንፋስ ማለት ነው። ብዙ ጊዜ ርእስ ያለው ነገር ቁም ነገር ኣለበት። ለምሳሌ ሰው ትንፋሽ ኣለበት፣ ሕይወት ያላቸው ነገሮች ሁሉ እስትፋስ ኣለባቸው። ሰው ሁሉ ፈጣሪ ያለበት (ያመነ) ዶሞ የተረጋጋ መንፈስ ኣለበት። ርእስ ያለው ነገር ሁሉ መጀመሪያዊ ኣለበት ይሆናል። ዳኝነት ቅንነት ሃቀኝነት የእኩሉነት በሕይወቱ ይታያሉ። በማን በርእስ (በራስ) ያለበት። የሌለበት ደሞ ያው እንደ ጅረት ውሃ ሰው እየጎዳ ራሱን እየጎዳ ይሄዳል። ኣያቋርጥም መግፋት እያተላተመ ከዚያም ከዚህም። ርእስ ኣልባ ባዶ ቁጥር ቁጭ እያተረፈ ከማንም እየቀነሰ ከሰው ራስንም እየደከመ።
38374
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%8A%E1%8A%A9%E1%88%AD%E1%8C%89%E1%88%B5%20%28%E1%8B%A8%E1%8C%A5%E1%88%AB%E1%8A%AD%E1%8B%AB%20%E1%8A%95%E1%8C%89%E1%88%A5%29
ሊኩርጉስ (የጥራክያ ንጉሥ)
ሊኩርጉስ (ሉኮርጎስ) በግሪክ አፈታሪክ የጥራክያ ንጉሥ ነበር። ከትሮያን ጦርነት አስቀድሞ እንደ ገዛ በብዙ ጽሐፊዎች ከነሆሜር ተጽፎዋል። ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ እንደሚለን፣ ይህ ሊኩርጉስ አምባ ገነን ሆኖ ከአለቆቹ አንድ ሞፕሶስ የተባለውን ከመንግሥቱ አባረረው። በተጨማሪ የእስኩቴስን ሰው ሲፑሉስን አባረረው። ከዚህ ጥቂት ጊዜ በኋላ ግን አማዞኖች የተባሉት ሴት ወታደሮች ከሊብያ አንስተው አገሩን ወረሩ። ያንጊዜ ሞፕሶስና ሲፑሉስ ከስደት ተመልሰው ሠራዊታቸው ከአማዞኖች ጋር በተዋገው ውግያ ንግሥታቸው ሚሪና ተገደለችና ተሸነፉ። በኋላ ዘመን ግን አፒስ ዲዮኔሶስ በየአገሩ ስለ ግብርና እያስተማረ ተዛውሮ ከእስያ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ሲፈልግ ሊኩርጉስ ግን አቃወመው። ኦሲሪስ ግን ሊኩርጉስን ገደለውና በፈንታው አለቃውን ማሮን አገረ ገዥ አደረገው። የግሪክ አፈታሪክ
16993
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%88%E1%88%8B%E1%8A%95%20%E1%89%B0%E1%88%B0%E1%88%9B
ገላን ተሰማ
ገላን ተሰማ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ዘፋኝ ነው። የህይወት ታሪክ ገላን ተሰማ ተወልዶ ያደገው በወለጋ ኖኖ ሲሆን ወደ አዲስ አበባ የመጣው በአስር ዓመቱ ነው። በ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. በክብር ዘበኛ ጋራዥ ክፍል ተቀጥሮ ሲሰራ ቆይቶ ከሶስት ዓመታት በኋላ ወደ ቲያትር ክፍሉ ተዛውሮ በመሰልጠን ዳንኪረኛ ለመሆን ችሏል። ገላን እስከ ዛሬ ድረስ የተለያዩ ዜማዎችን ተጫውቷል። ከእነርሱም መካከል «እንደ ተመኘኋት» የተባለችውን ዜማ በይበልጥ ይወዳታል፤ ገላን በወቅቱ የክብር ዘበኛ አርቲስቶች የዳንኪራ መምህር ነበር። ገላን በዳንኪርተኛነቱ እጅግ የተደነቀና የተፈጥሮ ስጦታ ያለው ነው። የኢትዮጵያ ዘፋኞች
32638
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A4%E1%88%8C%E1%8A%AD%E1%89%B5%E1%88%AA%E1%8A%AD%20%E1%8A%A5%E1%88%9D%E1%89%85
የኤሌክትሪክ እምቅ
የኤሌክትሪክ እምቅ አንድ የኤሌክትሪክ መስክ በተንሰራፋበት ኅዋ ነጥቦች ላይ ያለው እምቅ አቅም ነው። ስለሆነም ከኤሌክትርክ እምቅ አቅም ጋር ይለያያል፣ ምክንያቱም የኤሌክትሪክ እምቅ አቅም የሚለካው አንድ ቻርጅ በአንድ የኤሌክትሪክ መስክ ውስጥ ባለው አቀማመጥ ምክንያት የሚፈጠር ነውና። በሌላ አነጋገር ኤሌክትሪክ እምቅ የመስክ ባህርይ ሲሆን፣ ኤሌክትሪክ እምቅ አቅም ደግሞ በመስክ ውስጥ ያለ ቻርጅ ባህርይ ነው። ስለዚህ በአንድ የኅዋ ነጥብ ላይ ተንጣሎ የሚገኝ ቻርጅ የተወሰነ የኤሌክትሪክ እምቅ አቅም ቢኖረው፣ ያንን አቅም ለቻርጁ በማካፈል የመስኩ ኤሌክትሪክ እምቅ ይገኛል ማለት ነው። የኤሌክትሪከ እምቅ ከኤሌክትሪክ እምቅ አቅም ጋር ያለው ዝምድና የኤሌክትሪክ መስክ ከኤሌክትሪክ ጉልበት ጋር ካለው ዝምድና ጋር ተመሳሳይ ነው ። አንድ መፈተኛ ቻርጅ በምትገኝበት የኤሌክትሪክ መስክ ውስጥ የኤሌክትሪክ እምቅ አቅሟ ቢሆን፣ በዚያ ቦታ ላይ መስኩ ያለው ዬለክትሪከ እምቅ እንዲህ ይሰላል። ቀመሩ እንደሚያስረዳ የእምቁ መንስዔ በነጥቡ ላይ የሚገኝ የኤሌክትሪክ መስክ ነው። ስለሆነም የእምቁ መጠን ሙሉ በሙሉ የሚወሰነው በመስኩ ጥንካሬ ነው እንጅ እዛ ነጥብ ላይ ባለ ቻርጅ አይደለም። ሆኖም የኤሌክትሪክ እምቅ ያለ መፈተኛ-ቻርጅ፣ በቀጥታ፣ ከመስኩ ጥንካሬ ሊሰላ ይችላል። ይሄውም የሚደረገው በተሰጠ የኤሌክትሪክ መስክ ውስጥ ባሉ ሁለት ነጥቦች መካከል የመስመር ጥረዛ በማካሄድ ነው። በሒሳብ ቋንቋ፡ ከላይ የተሰጠው ቀመር በነጥቦች እና መካከል ያለውን የአቅም ልዩነት ሲናገር፣ አንድን መፈተኛ ፖዚቲቭ ቻርጅ ከ ወደ ለመውሰድ የሚያስፈልገውን አቅም ይናገራል። ልዩነቱ (ቮልቴጅ) ፖዚቲቭ ከሆነ፣ ስራ መስራት ያሰፈልጋል፣ ልዩነቱ ነጌቲቭ ከሆነ፣ መስኩ እራሱ ቻርጁን ወደ ስለሚወስደው ስራ መስራት አላስፈላጊ ነው ማለት ነው። ከሁለቱ ነጥቦች አንዱን እንደ ዜሮ የኤሌክትሪክ አቅም በመውሰድ የአቅም ልዩነቱን እንደ የሌላኛው ነጥብ ኤሌክትሪክ አቅም መውሰድ ይቻላል። የኤሌክትሪክ አቅም ስኬላር መስክ ነው። ማለት ለእያንዳንዱ የህዋ ነጥብ ዋጋ ሲሰጥ፣ ነገር ግን አቅጣጫ የለውም። የኤሌክቲሪክ እምቅ በ ወይንም ሊወከል ሲችል፤ መለኪያ መስፈርቱ ቮልት ወይንም ጁልስ በ ኩሎምብ ነው። የኤሌክትሪክ እምቅ ጽንሰ ሐሳብ ብዙ ጥቅም ሲኖረው፣ በተለይ የኤሌክትሪክ መስክን ለማስላት አይነተኛ መሳሪያ ነው። የመደመር (ንብብሮሽ) ስርዓት ከብዙ ስብስብ ኤሌክትሪክ መስኮች የሚፈጠር የኤሌክትሪክ አቅም የእያንዳንዳቸው መስኮች አቅም ድምር ውጤት ነው። ማለት፦- በነጥብ ቻርጅ መስክ የሚነሳ የኤሌክትሪክ እምቅ በ ርቀትላይ፣ በነጥብ ቻርጅ ምክንያት የሚፈጠር የኤሌክትሪክ እምቅ, እንዲህ ይሰላል፦ እዚህ ላይ 0 የ የኤሌክትሪክ ቋሚ ቁጥር ናት። ይህ ቀመር የኩሎምብ እምቅ በመባል በሌላ ስም ይታወቃል። የቀመሩ መስራት ምስጢር 3 እውነታወችን ያዘለ ነው፡ 1ኛ፣ በነጥብ ቻርጅ ምክንያት የሚፈጠር ጉልበት መስክ ራዲያል አቅጣጫ ስላለው፣ ምንጊዜም ከተመረጠ መንገድ ጋር ያለው የ የጥላ ብዜቱ ዋጋ የሚኖረው በራዲየስ አቅጣጫ ነው። በክቡ ጠርዝ ላይ ያለው ጥላ ብዜት 0 ነው። 2ኛ፡ የኤሌክትሪክ መስክ ጽኑ ጉልበት አይነት ስለሆነ፣ ለመጠረዝ የምንመርጣቸው ማናቸውም መንገዶች እኩል ውጤት ይሰጡናል፡፡ ስለሆነም ከሁሉ ቀላል የሆነውን የራዲስ ታካኪ መስመርና የክብ ጠርዝ መምረጥ፣ የቀመሩን ስራ ላይ የመዋል ሁኔታ ውሱን አያደርገውም። ብዙ ነጥብ-ቻርጆች ቢሰበሰቡ፣ የኒህ ስብስብ መስክ ኤሌክትሪክ እምቅ፣ የእያንዳንዱ ነጥብ-ቻርጅ እምቅ ድምር ውጤት ነው። ቋሚ ኤሌክትሪክ መስክ ልዩነት (ቮልቴጅ) በቋሚ የኤሌክትሪክ መስክ ውስጥ ነጥብ ላይ የሚገኘው ኤሌክትሪክ እምቅ እንዲህ ይሰላል ን ከ0 እምቅ ነጥብ ጋር የሚያገናኝ ማናቸውም፣ ነሲብ መንገድ ሊሆን ይችላል ። ማለት እላይ የተሰጠው ጥረዛ በሚመረጥ መንገድ አይቀያየርም። ልክ የድንጋይ እምቅ አቅም በቁመቱ እንጂ በተጓዘበት መንገድ እንደማይወሰን። ስለሆነም የቋሚ ኤሌክትሪክ መስክ ጽኑ ጉልበት ኮንሰርቫቲቭ ጭረር መስክ ይሰኛል ማለት ነው። ከኤሌክትሪክ አቅም ወደ ኤለክትሪክ መስክ ከላይ እንደሚታየው ከተሰጠ የኤሌክትሪክ መስክ ተነስቶ የመስመር ጥረዛ በመጠቀም የኤሌክትሪክ አቅምን ስኬላር መስክ ማግኘት ይቻላል። በተገልባጭ፣ ከተሰጠ የኤሌክትሪክ አቅም ተነስቶ የኤሌክትሪክ መስክን የቬክተር መስክን ማስላት ይቻላል። ለዚህ የሚረዳ የሒሳብ ቀመር አቀበት ይሰኛል። የኤሌክትሪክ መስክ
18805
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AB%E1%88%8D%E1%89%AA%E1%8A%95%20%E1%8A%A9%E1%88%8A%E1%8C%85
ካልቪን ኩሊጅ
ካልቪን ኩሊጅ (እንግሊዝኛ: ) የአሜሪካ ሠላሳኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕረዝዳንቱ ሥልጣን ላይ የወጡት በቀዳሚው በዋረን ሃርዲንግ መሞት በ1923 እ.ኤ.አ. ሲሆን ሁለተኛ ዘመን (አራት ዓመታት) በምርጫ አገኝተው በጠቅላላ ፮ ዓመታት ገዙ። በስልጣን ዘመናቸው ምክትል ፕሬዝዳንት ሁነው የተሾሙት ቻርልስ ዳውዝ ናቸው። ፕሬዝዳንቱ የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የነበሩ ሲሆን የለሴ ፈርና የትንሽ መንግሥት ወዳጅ ነበሩ። ለተጨማሪ ዘመን ምርጫ ዕጩ መሆን ስላልወደዱ ከሥልጣን የወረዱት በ1929 እ.ኤ.አ. ነበር። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች ዝርዝር የአሜሪካ መሪዎች
13264
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%8B%AD
ብይ
ብይ የኢትዮጵያ ህጻናት ትንሽ ድቡልቡል ነገርን (ከእስክፒቶ ቀፎ በማቅለጥና በጅ በማበልበል የሚሰራ ወይም ደግሞ ለዚሁ ተብሎ ከሚሰራ "ብይ" ወይም ከኩቺኔታ ኳሶች የሚሰራ) የተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ በመክተትና ከዚያም የተቃራኒን ብዮች በማጥቃትና በ"መብላት" የሚጫወቱት ነው። ጎበዝ የብይ ተጫዋች ጉድጓድ መግባትና ከዚያም የባላጋራውን ብይ አነጣጥሮ በመምታት መብላት ሳይሆን አንድ አንድ ጊዜም የተቃራኒውን ብይ መስበር ወይም መፈርካከስን ያጠቃልላል። ይህ ጨዋታ ለህጻናት ብዙ ትምህርት ይሰጣል። በክፍለ ሀገር ያሉ ህፃናት ብይ ከጭቃ በመስራት ይጫወቱ ነበር። መደብ ጨዋታ
50400
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%88%8B%E1%8C%85
ቅላጅ
በአማራ ክልል በአዊ ዞን በዚገም ወረዳ የምትገኘዋን የቅላጅ ከተማ ታሪካዊ አመሠራረትና አጠቃላይ ገፅታ በከፊል የከተማ ታሪካዊ አመሰራረት ኢትዮጵያ ሀገራችን ቀደምነት ታሪክ ካለቸው ከተሞች አመሰራረት ከታየባቸው ሀገሮች አንዷ ነች። ነገር ግን ኢትዮጵያ ቀደምነት ያላቸው ከተሞች የታዩበት ሀገር ትሁን እንጂ ከራሷ የእድገት ሁኔታ ጋር በተያየዘ የከተሞች እድገት እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ ድረስ ከዚህ ግባ በሚባል አልነበረም። ነገር ግን ስልጣኔ ወደ ሀገራችን መግባት ከጀመረበት ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቄያ አካባቢ ጣሊያን ሀገራችን ከወራራበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ከተሞች መቆራቆር እንደ ጀመሩና እድገታቸውም በዚያው ልክ እያደገ እንደሄደ የተለያዩ ጥንታዊ ፅሑፎች ያስረዳሉ። ታሪክን ማወቅ ያለፈው ትውልድ የሰራቸውን መልካም ነገሮችን ቀምሮና የአሁኑና ሞች ትውልድ በአግባብ እንዲጠቅምባቸው ለማድረግ መጥፎዎች ደግሞ ታሪክ ሁነው እንዲቀሩ ለማድረግ ይረዳል። ከዚህ አንፃር የቅላጅ ከተማን ቀደምት ታሪክ በመደሰስ ከተማዋ የት ተነስተ የት እንዳደረሰች በታሪኩ መዘክርነትነት የመቀመጥ ቅርስ ማስቀመጥ ታሪክን ለማወቅና ወደ ፊት በከተማዋ ላይ ሰፋ ያለ ጥናት ለሚዘጋጅ መነሻ እንዲሆን ለማሳወቅ የፅሑፍ ማስረጃ ከሀገር ሽማግሌዎች በመጠየቅና ውይይት ማድረግ የከተማዋን ታሪክ ለመደሰስ ሞክረናል። ከተማዋ እንቅስቃሴ የጀመረችው በንግስት ዘውዲቱ ዘመነ መንግስት ቢሆንም በይፋ የተመሰረተችው ግን በአፄ ኃይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት የዚገም ምክትል ወረዳ ገዢ በነበሩበት በፊታውራሪ ደረሶ ተሰማ በ1925 ዓ/ም እንዳሆነ አረጋዊያን ያስረዳሉ። በዝርዝር ታሪኳም እንዲህ ነው። የዚገም ግዛት በምስራቅ በኩል ከዳሞት ግዛት ጋር ይወስን ነበር። በሁለቱም ግዛቶች ድንበር ጫፍ ላይ ደግሞ አካኮ የምትበል ገበያ ነበረች። ይህች ገበያ በርካታ ገቢ የተገኘው ከዚገም እና ከዳሞት ግዛት እየመጡ ይገበያዩበት የነበረች ሲሆን በሁለቱም ድንበርተኞች አጎራባች ግዛቶች ማዕከል በሚነሳ ግጭት/አለማግባባት/ ዳሞቶች ገበያ መጠው የዚገም ሰው ገድሎ ድንበራቸው ቅርብ ስለነበረ ወደ ዳሞት ግዛት ይገባሉ። ዚገሞች ከሠው ግዛት ቢገቡ የሰው ግዛት ጥሶ ለገቡ ዋስትና የለም። የዚገሞች እንዲህ ከዳሞት የመጣን ገበያተኞች ገድሎ ወደ ራሳቸው ግዛት ይመጣሉ። ዳሞቶች የሰው ግዛት ጥሶ ቢገቡ ከላይ የተጠቀሰው ዕጣ ይገቡና ሟቹ ካልሆነም የአካኮ ገበያ በድንበር ላይ መሆን ከገበያ ማዕከልነት ባለፈ የግጭት ማዕከል የሆነችው ከመምጣቷ ፊታውራሪ ደረሶ ተሰማ ገበያውን ከነበረችበት በመነሳት እና ማክሰኞ ትውል የነበረችውን የማቻ ገበያ በአንድ ላይ በማድረግ አሁን ዋና ገበያው ከሚገኝበት የከተማዋ ደቡብ ጫፍ ላይ ቅዳሜ ቅዳሜ ቀን እንዲውል አድርጓል። በ1925 ዓ/ም ገበያውን እንደመሰረቱትና ከተማዋ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በይፋ እንደተመሰረተችው የከተማዋ ዕድ ጠቢብ አዛውንቶች በሰፊው ያስረዳሉ። ከተማዋም ከተመሰረተች ጊዜ ጀምሮ ምክትል ግዢ ደረጃነትን ይዛ እንደነበረች የፓርላማ ተወካይ እንደነበሩት ያስረዳሉ። የዚገም ምክትል ግዢ የነበሩት ፊታውራሪ ደረሶ ተሰማ ልጅ ልጅ ተሰማ ደረሶ ቅላጅ ከተማ የመጀመሪያ የፓርላማ ተወካይ ሁነው እንደተመረጡም አዛውንቶች በትዝታ ያስታውሳሉ። አማራ ክልል
52339
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%AE%E1%8A%93%E1%88%B5%20%E1%8B%B0%E1%88%B3%E1%88%88%E1%8B%8D
ዮናስ ደሳለው
ዮናስ ደሳለው ዮናስ ደሳለው አቶ ዮናስ ደሳለው በድሮው ጎጃም ጠቅላይ ግዛት አገው ምድር አውራጃ በአሁኑ ፈግታ ለኮማ ወረዳ ልዩ ስሙ አዲስ ቅዳም ከተማ 01 ቀበሌከአባታቸው መ/ር ደሳለው በሪሁን እና ከእናታቸው መ/ርት ጥሩእመቤት ዳኛው ጥቅምት 06/2012 ዓ.ም ተወለደ። ተወለዶ አቅማ ሄዋን እስኪደረስ ድረስ ከአያቱ ጋር አደገ።ከዚያህ በሆላ ወደ አባቱ ዘንድ መኖር ስለፈለገ በፊቱ አጣራር ኮክራ አውራጃ በአሁኑ ፋግታ ለኮማ ወረዳ ኮሪጎሃና ቀበሌ ቸዋሲ ኪ/ምህረት ኑሮውን መስርተው የሚኖሩ ታዋቂ እና ዝናኛ አከበባውን ህብረተሰብ ወይም ማህበረሰብ የሚያከብሩ ታላቅ ሰው ናቸው።
39063
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%98%E1%88%B5%E1%8C%88%E1%8A%95%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%AC
ተመስገን ገብሬ
ተመስገን ገብሬ የተወለዱት በጎጃም ጠቅላይ ግዛት በደብረ ማርቆስ ከተማ በ፲፱፻፪ ዓ/ም ነው፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ የቤተ ክህነት ትምህርት ተከታትለዋል፡፡ ቤተሰባቸው ካህናት ከመሆናቸውም በላይ ጎበዝ ተማሪ ነበሩ። ጉብዝናቸው በዘመናዊ ትምህርት ሲከታተሉም ጎልቶ ወጥቷል፡፡ ከጎጃም አዲስ አበባም በመምጣት በስዊድን]] ሚሲይናዊ ትምህርት ቤት ተማሩ በወቅቱ ሀገሪቱ ካፈራቻቸው ጎበዝ ተማሪዎች አንዱ ነበሩ፡፡ ተመስገን በጋዜጠኝነት ሙያ ከመሥራታቸውም በላይ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ቦታ ተመድበው አገልግለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በኢጣሊያ በተወረረችበት ወቅት በአርበኝነት ከጠላት ጋር ተፋልመዋል፡፡ በኋላም ወደ ሱዳን ተሰደው ገዳሪፍ ውስጥ እያሉ ኢትዮጵያዊያንን በልዩ ልዩ መልክ አስተምረዋል፡፡ ጣሊያን ከለቀቀች በኋላ የዘመናዊ አስተሳሰብና ዕድገት ዓላማዋ ዕውን እንዲሆንም ፍፁም የለውጥ አርበኛ ሆነው ሠርተዋል። ተመስገን፣ ኅዳር ፳፪ ቀን ፲፱፻፵፩ ዓ/ም በ አዲስ አበባ ነፃነት ማተሚያ ቤት “የጉለሌው ሰካራም” በሚል ርዕስ ያሳተሙት ድርሰታቸው የመጀመሪያው፣ የታተመ የአማርኛ አጭር ልብ-ወለድ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ የጉለሌው ሰካራም ከመታተሙ በፊት ስለ የካቲቱ ፋሺስታዊ ጭፍጨፋ (ግፊቱን በቀመሱት አርበኛው ደራሲ አገላለጽ፣ ‹‹ዓለም በድንገት ተለውጣ፣ አዲስ አበባም ኢጣሊያኖች ኢትዮጵያውያንን የሚያርዱበት ቄራ ሆና ነበር፡፡››) “የካቲት ፲፪” በሚል ርዕስ እና “ሊቀ-ጠበብት እውነቱ” የተሰኙ ሁለት አጫጭር ልብወለዶችን በጋዜጣ ላይ አውጥተዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ‹‹ሕይወቴ›› የተሰኘውን ግለታሪካቸውን ያዘጋጁት አርበኛው አቶ ተመስገን ገብሬ በአምስቱ ዓመት የፋሺስት ወረራ ጊዜም በደረሱት ‹‹በለው በለው አትለውም ወይ፤ የጥቁር አንበሳ አይደለህም ወይ›› በሚለው መዝሙራቸውም ይታወሳሉ፡፡ ማጣቀሻ እና ዋቢ ምንጮች የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች በየአመቱ የካቲት 12 ቀን ሲደርስ ከማስታውሳቸው የዚህች አገር ባለውለተኞች መካከል ተመስገን ገብሬ አንዱ ነው፡፡ ይህ ሰው ሀገሩ ኢትዮጵያ በፋሽስቶች እንዳትወረር ብዙ ትግል አካሂዷል፡፡ ከወረራው በኋላም በአርበኝነት ተሰማርቶ የፋሽስቶችን ግብአተ-መሬት ካፋጠኑ የኢትዮጵያ ታላላቅ ደራሲያን መካከል ከግንባር ቀደሞቹ አንዱ ነው፡፡ ተመስገን ገብሬ በ1901 ዓ.ም ጐጃም ደብረማርቆስ ከተማ ነው የተወለደ፡፡ ታህሳስ 15 ቀን 1941 ዓ.ም በ40 ዓመቱ አረፈ፡፡ በትምህርቱ እጅግ ጐበዝ የሚባል በመሆኑ ገና በ15 ዓመቱ የቅኔ መምህር ሆኖ ነበር፡፡ በቤተ-ክህነት ትምህርት በዚህ እድሜ የቅኔ መምህር የሆነ ሰው ከተመስገን ሌላ አልተገኘም ይባላል፡፡ ይህ ሰው በ1918 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ መጥቶ የዘመናዊ ትምህርቱን በስዊድሽ ሚስዮን ተከታትሎ ጨርሷል፡፡ በ1920ዎቹ ውስጥ ጣሊያን ኢትዮጵያን ከመውረሯ በፊት ወረራው ለኢትዮጵያ እንደማይቀር በማወቅ በየአደባባዩ ሕዝብን እየሰበሰበ አንድ እንዲሆንና ጠላትን እንዲመክት ያስተምር ነበር፡፡ በአንድነቷ የጠነከረች ኢትዮጵያን ለመመስረት ብርቱ ትግል አድርጓል፡፡ ተመስገን የኤርትራ ድምፅ የሚሰኝ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅም ነበር፡፡ የአልጋ ወራሽ አስፋው ወሰን ኃይለስላሴ የቤት ውስጥ መምህርም ነበር፡፡ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው አጭር ልቦለድ የሚባለው የጉለሌው ሰካራም መጽሐፍም ደራሲ ነው፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ችሎታውና በአፃፃፍ ቴክኒኩ እጅግ የተዋጣለት ደራሲ መሆኑን ሃያሲያን ይናገራሉ፡፡ ተመስገን ገብሬ በኢጣሊያ ወረራም በፋሽስቶች ሊገደሉ ከሚፈለጉ ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዱ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም አብርሃ ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶም ግራዚያኒ ላይ ቦምብ ወርውረው ካቆሰሉት በኋላ ፋሽስቶች 30 ሺ ያህል የሚገመት የአዲስ አበባን ሕዝብ ጨፍጭፈዋል፡፡ ጣሊያኖች እነ አብርሀ ደቦጭ ግራዚያኒን ለመግደል ያሴሩት በተመስገን ገብሬ ግፊት ነው ብለው በማመናቸው በዋና ጠላትነት ይፈልጉት ነበር፡፡ በዚያን ወቅት ተመስገንም በአጋጣሚ በፋሽስቶች እጅ ይወድቃል፡፡ ግን ተመስገን ገብሬ መሆኑን አላወቁም፡፡ ስሙን ሸሸጋቸው፡፡ እሱንም ሊገድሉት እስር ቤት ባስገቡት ወቅት ጣሊያኖች ኢትዮጵያዊያኖችን ሲጨፈጭፉ በዓይኑ አይቷል፡፡ ከዚህም ጭፍጨፋ በተአምር አምልጦ ወደ ሱዳን ይሰደዳል፡፡ ተመስገን ገብሬ ይህን የየካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም የተደረገውን ጭፍጨፋ እና በአጠቃላይ በርሱ ሕይወት ዙሪያ ያለውን ውጣ ውረድ ሕይወቴ በሚል ርዕስ ፅፎታል፡፡ ይህን መጽሀፍ በ2000 ዓ.ም የአርትኦት ስራውን የሰራነውና እንዲታተም ያደረግነው እኔ እና ደረጀ ገብሬ እንዲሁም የተመስገን ገብሬ ልጅ ሲስተር ክብረ ተመስገን መሆናችንን በዚህ አጋጣሚ መጥቀስ እወዳለሁ፡፡ ከዚሁ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰነውን ክፍል በመውሰድ በወቅቱ ምን ዓይነት ግፍ እንደተፈፀመ ለማስታወስ እሞክራለሁ፡፡ ተመስገን ጭፍጨፋውን በተመለከተ በወቅቱ ለንደን ለሚገኙት ለጃንሆይም ያየውን ጽፎላቸው ሲያነቡት አልቅሰዋል፡፡ ምን ይሆን ለጃንሆይ የፃፈላቸው? ከብዙ በጥቂቱ የሚከተለውን ይመስላል፡- “ከሦስት ቀን የከተማ ጥፋት በኋላ ከሆለታ የመጡ የፋሽስት አውሬዎች በሚመለሱበት ካሚዮን በኋላው በኩል አቶ አርአያን እግራቸውን ጠርቅመው አሰሯቸው፡፡ ካሚዮኑ ሳይጐትታቸው “እኔ ወደ ሰማይ እንድገባ ሰማይ ተከፍቶ ይጠብቀኛል፡፡ እየሱስንም በዚያ አየዋለሁ፡፡ ደስ ይለኛል፡፡ ደስ ይለኛል፡፡ ደስ ይለኛል!” የሚለውን የሚሲዮን መዝሙር ዘመሩ፡፡ ፋሽስቶቹም የተሻለውን መዝሙር ብትሰማ ይሻልሃል አሏቸውና ዱኪ ዱኪ የሚለውን መዝሙራቸውን ዘመሩ፡፡ ካሚዮኑም ሞተሩን አስነስቶ ሲነዳ ታስረው ቁመው ነበርና ያን ጊዜ ዘግናኝ አወዳደቅ አቶ አርአያ ወደቁ፡፡ ካምዮኑም እየፈጠነ ጐተታቸው፡፡ ከአዲስ አበባ እስከ ሆለታ አርባ ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ ካምዮኑ ከዚያ ሲደርስ ያ ከካሚዮኑ ጋር የታሰረው እግራቸው ብቻ እንደተንጠለጠለ ነበርና የካሚዮኑ ነጂ ከካሚዮኑ ፈታና ለውሾች ወረወረው፡፡ እኔንም ያለሁበትን ቤት ሰብረው ከዚያ ቤት ያለነውን አውጥተው ከየመንደሩም ሕዝቡን አጠራቅመው ኑረዋል፡፡ ከዚያም መሐል ጨመሩን፡፡ ስምንት መትረየስ በዙሪያችን ጠምደዋል፡፡ በዚያም ቦታ ቁጥራቸው በብዙ የሆኑ ሐበሾችን አስቀድመው ገለዋቸዋል፡፡ ሬሣቸውም ተቆላልፎ በፊታችን ነበረ፡፡ እኛንም በዚያ ሊገድሉን ተዘጋጁ፡፡ ለመትረየስም ተኩስ እንድንመች ያንዳችንን እጅ ካንዱ ጋር አያይዘው አሰሩን፡፡ አሥረውን ወደ መተኰሱ ሳይመለሱ አንድ ታላቅ ሹም መጣ፡፡ የርሱም ፖለቲካ ልዩ ነበረ፡፡ ፋሽስቶች የሚያደርጉትን የሰላማዊ ሕዝብ መግደል፤ ሕፃናቶችን ከአባትና እናታቸው ጋራ በቤት ዘግቶ ማቃጠል መልካም ብሎ ቢወድ እንኳን እኒያ ቦምብ በቤተ-መንግስቱ ስብሰባ የወረወሩት ሐበሾች ሳይታወቁ እንዲቀሩ አይወድም ነበርና ስለዚህ ካሚዮኖች ይዞ እየዞረ ፋሽስቶች የሚገድሉትን እያስጣለ ወደ እስር ቤት ለምርመራ ይወስድ ኑረዋል፡፡ እኛንም እንዲተኮስብን ታሰረን ከቆምንበት ከቅዱሰ ጊዮርጊስ ጠበል አጠገብ ካለው ሸለቆ እስራታችንን አስፈትቶ በአምስተ ረድፍ ወደላይኛው መንገድ ለመድረስ ስንሄድ በአካፋ ራሳቸውን የተፈለጡ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ ምራቄ ደረቀ፡፡ በካሚዮኑ ወደ እስር ቤት አስወሰደን፡፡ ለጊዜው እስር ቤት ያደረጉት ማዘጋጃ ቤትን ነበር፡፡ ከማዘጘጃ ቤቱ በር ስንደርስ በአምስት ካምዮን ያጠራቀመንን ሰዎች በዋናው መንገድ እንድንቆም አዘዘን፡፡ ዙሪያችንንም ከበው በሳንጃ እየወጉን ጨፍቅ ብለን በመንገዱ ቆምን፡፡ ከወደኋላችን ትልቁን የጣሊያን ካሚዮን በላያችን ላይ ነዱብን፡፡ አስራ ስምንት ቆስለው አልተጨረሱም፤በሳንጃ ጆሮአቸውን ወጓቸው፡፡ በአንድ ጊዜ ማለት አርባ ስምንት ሰዎች ጨፈለቀ፡፡ ተካሚዮኑ ወደኋላ ያፈገፈጉትን እሥረኞች ዙሪያውን ሳንጃ መዘው የቆሙት ወጓቸው፡፡ እኔም በካምዮኑ ጉልበቴን መታኝ፡፡ ያን ጊዜ የቆሰልሁት እስከ ዛሬ ለምጥ ይመስላል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስትያን ተቃጥሎ ኑሯል፡፡ እንደ ማታ የፀሐይ ጮራ ከምዕራብ በኩል ይታያል፡፡ በለሊት ወስደው ከገደሉት በእስር ቤት የቀረው ያንሳል፡፡ ነገር ግን በዚህ ለመግደል ሲያወጡ የሚበልጥ በዚያ በር ያገቡ ነበር፡፡ በበነጋው ከተደበደበው ሕዝብ ከኪሱ የተገኘውን እየቆጠሩ ለሹሙ አስረከቡ፤ እኔም ከጽሕፈት ቤቱ ፊት ለፊት ነበርሁ፡፡ የደበደቧቸውን የሐበሾችን የጋብቻ ቀለበታቸውን በሲባጐ እንደ መቁጠሪያ ሰክተው ደርድረው በአንገታቸው አግብተው አቀረቡት፡፡ አንዱ ቆጥሮ መዝኖም እስኪያስረክብ ሌላው ገና ባንገታቸው ነበር፡፡ ንፁህ የሆነውንም ልብስ በካምዮን አምጥተውት ነበርና አየቆጠሩ እስኪረከቡ፤ ገናም ሳይገቡ ገፈዋቸው ኖሯል፡፡ ስለዚህም ከጥቂቶች በቀር ሙሉው ልብስ በደም አልተበላሸም፡፡ በመሬትም ጣል ጣል እያደረጉ እየቆጠሩ እስኪረከቡ የጥቂቶች ልብሶች ገና እስከ ትኩስ ደም ኑረው ከመሬት መልሰው ሲያነሱዋቸው አፈር እና ግብስባሱን እየያዙት ሲነሱ አየሁ፡፡ ይህን ባዬ ጊዜ አንዱ ብድግ ብሎ እንደ እብድ ተነሳ፡፡ “እርሷን አሁን ከመሬት አፈር ይዛ የተነሳችውን ደም እግዚአብሔር አየ፤ ሊፈርድ ነው፡፡ ይህ ክፉ ስራችሁ በጭካኔ ሕዝቡን የሰው ሕይወት በማጥፋት ትጫወታላቸሁ፡፡ የገደላችኋቸው ወገኖቻችን ቀለበት በሲባጐ ሰክታችሁ መዝናችሁ ወሰዳችሁ፡፡ ደማችንን መሬቱ መጠጠው፤ ሬሳውም እንደ ገለባ ተከመረ፡፡ ስትገድሉ እግዚአብሔር ሊፈርድባችሁ ነው፡፡ ይኸው አሁን የእግዚአብሔር ሚዛን ሞላ፡፡ እንግዲህ ኢትዮጵያን ከቶ አትገዙም፡፡ እኔንም አሁን ልትገድለኝ ነው” አላቸው፡፡ ገናም ነገሩን ሳይጨርስ አምስት ቦምብ ተወረወረ፡፡ በአጠገቡ ያሉ ሁሉ ተቆላልፈው ሰማንያ ሰዎች ወደቁ፡፡ ካሚዮንም ሬሳውን ለመውሰድ አመጡ፡፡ ሬሳውን በአንድ ካሚዮን ከወሰዱ በኋላ ሌሎች ካሚዮኖችም ቁስለኞችን ለመውሰድ አመጡ፡፡ በብርቱም የቆሰሉትን እያነሱ ወስደው ከእስር ቤት በር በመትረየስ ተኰስዋቸው፡፡ በጥቂት የቆሰሉት ሰዎች ግን ቁስላቸውን አየሸሸጉ እንደ ደህና እየመሰሉ በእስረኛው መሐል ተሸሸጉ፡፡ ኢጣሊያኖችም እየበረበሩ ጥቂትም ቆስሎ ቢሆን ልትታከሙ ነው እያሉ እየመረጡ ከበር ገደሏቸው፡፡ ቁስል የሌላቸውንም እየነዱ ሲያወጡ “እረ እኛ ጤነኛ ነን አልቆሰልንም” እያሉ ቢጮሁ “አይሆንም ትታከማለህ፤ ቆስላችኋል” ብለው እየጐተቱ አውጥተው ከማዘጋጃ ቤት በር ሲደርሱ የሳንቃውን ቋሚ ዘንግ የሚመስሉትን ብረቶች በሁለት እጃቸው አንቀው ይዘው አልወጣ አሉ፡፡ በእንጨት ላይ እያሰለፉ ገደሏቸው፡፡ ቀኑ ብርቱ ፀሐይ ነበር፡፡ በዚያ እስር ቤት በማዘጋጃ ቤት ሜዳ ነበርና ብርቱ ክቢያ ተከበን ታላቅ ፍርሃት ነበር፡፡ ውሃና መብልም አላገኘንም፡፡ በሦስተኛው ቀን ጊዜውም ስድስት ሰዓት ሲሆን አስራ ሰባት ሰዎች በውሃ ጥማቱ ሞቱ፡፡ ይህም ቀን ጨለመ፡፡ እህልና ውሃ ሳናገኝ ሦስተኛው ቀን ነበርና ገንዘብም አየተቀበሉ በኰዳቸው ጣሊያኖች ለእስረኞች ውሃ መሸጥ ጀመሩ፡፡ ሕይወታችንም በዚህ ስቃይ ውስጥ ታንቃ ስንጨነቅ መሸ፤ እንጂ ለቀን ቀኑ ረጅም ነበር፡፡ ከዚያ ረሐብና ውሃ ጥማት እንዲገድሉን መርጠን ነበር፡፡ ይህንንም ከልክለውን ሁለት ካሚዮን አምጥተው ከዚህ ወደሚሰፋ እስር ቦታ ሊወስዱን እየቆጠሩ ስሙን እየፃፉ 30ውን አሳፈሩት፡፡ እንደተናገርኩት እኔ በጽህፈት ቤቱ በር አጠገብ ስለነበርኩ እስረኛውን አየቆጠሩ አያሳፈሩ መጓዝ የጀመሩ ከወዲያ በኩል ነበርና ስለዚህ የኔ መሄዴ ዘግይቶ ነበር፡፡ ብዙ የሚያሳዝን ቁም ነገሮች በመዘግየቴ አየሁ፡፡ ሦስት ሴቶች በወሊድ ተጨንቀው ኖረዋል፡፡ ሊወልዱም ቦታ አላገኙምና በአስረኛው ግፊ ተጨፍልቀው ሞተዋል፡፡ ሦስቱም ከትንንሽ ህፃናቶቻቸው ጋር ሬሳቸው ወድቆ አየሁት፡፡ በውሃ ጥማትና በረሃብ እነርሱም በቦምብ ከገደሉት ከሞተው ሰውና ከሬሳው ብዛት የተነሳ እኒህን በወሊድ የሞቱትን ያስተዋላቸው አልነበረም፡፡ እኔንም ሊገድሉኘ ስሜን በሊስት ይዘው ይፈልጉኝ ነበርና ስሜን ፅፈው ሊያሳፍሩኝ ሲሉ ሌላ ስም ነገርኳቸው፡፡ በካሚዮንም እስረኛውን ወደወሰዱበት ስፍራ አጓዙን፡፡ በመንገድም የካሚዮኑ መብራት በሚወድቅበት እንመለከት ነበር፡፡ መንገዱ ሁሉ ሬሳ ተሞልቶ ነበር፡፡ በገደሏቸው በሐበሾች ሬሳ ተሞልቶ ነበር፡፡ ዝም ብለው በላዩ ይነዱበት ነበር፡፡ በሬሳው ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን ሬሳውን ደግሞ በካሚዮናቸው በጨፈለቁት ወቅት በሰው ሬሳ መንገዱ ተበላሽቶ ያስጸይፍ ነበር፡፡ ከመንገዱም ዳር የወደቁትን ሬሶች የካሚዮኑ ብርሃን በወደቀባቸው ጊዜ ድመቶች ጐንጫቸውን ነክሰው ጺማቸውን እያራገፉ ሲበሏቸው አየሁ፡፡ ካሚዮኑ ከእስር ቤቱ በር ፊት በር በሚባለው በደረሰ ጊዜ ከካሚዮን እንድንወርድ አደረጉን፡፡ በኋላ በኩል ከነበሩት መጀመሪያ የወረዱትን ቦምብ ወርውረው ገደሏቸው፡፡ የቀረነው አንወርድም ብለን ራሳችንን በውስጥ በሸሸግን ጊዜ በኋላ በኩል ነጂው በሚቀመጥበት በኩል መትረየስ አምጥተው አስገብተው ተኩሰውብን ሞላዎችን ገደሏቸው፡፡ የቀረነው እየዘለልን ከካሚዮን ወረድን፡፡ ለጥይቱ ፈርተው በኋላ በኩል ሸሽተው ነበርና የወረደም የለም፡፡ የእስር ቤቱ በር ክፍት ስለነበር እየፈጠንን ሩጠን ተጨመርን፡፡ ሌሊቱንም ሁሉ እስረኛውን እያጋዙት ሲጨምሩት አደሩ፡፡ ይህም ቦታ ጠፍ ሁኖ የኖረ ነበረና ሳማና ልት የሚባለው ምንስ ወራቱ መጋቢት ቢሆን ቅጠሉ ለምልሞ ነበር፡፡ በታላቅ ረሃብና ውሃ ጥማት የተጨነቀው እስረኛ ያንን መራራ ቅጠል በላ፡፡ ሲጠጣ ይህን ቅጠል ያሳደሩ ስሩን እየገፈፉ በሉ፡፡ እኔም ምን የሚበላ ነገር ይህ ፍጥረት አገኘ? ባገኘው ህይወት ነው ብዬ ወደሚያላምጡት ሰዎች ሔድሁ፡፡ የሚያውቀኝ ሰው አገኘሁና ከዚያ ስር ቆፍሮ ሰጠኘ፡፡ እኔም ወስጄ ለባልንጀሮቼ አካፈልኋቸው፤ለውሃ ጥማት ይህን ማላመጥ መድሃኒት ነው ብሎ ነግሮኝ ነበርና ለውሃ ጥማት መድሃኒት ነው ብዬ ነገርኋቸው፡፡ ከፊላችንም መራራ አንደሚጣፍጥ ይህን እያላመጥን እስከ አራት ሰዓት ቆየን፡፡ ዛሬ ቀኑ አሁድ ነበር፡፡ የተያዝንበትም አርብ በስምንት ሰዓት ነበር፡፡ ከዚያ እስከ ዛሬ እህል የሚባል እንኳን ለመብል ማግኘት ቀርቶ ያየን የለም፡፡ ፀሐይ በዚህ ቀን ሲተኩስ ሰው ሁሉ ልቡሱን እያወለቀ በራሱ ላይ ተከናነበው፡፡ በዚህም መከናነብ የፀሐይ ትኩሳት ሲበርድ ውሃውን ጥማት መከላከል የሚችሉ መስሏቸው ነበር፡፡ ከሌላው እስር ቤት በቀር በዚህ እስር ቤት ውስጥ የነበረው አስረኛ እነሱ ጣሊያኖች እንደገመቱት 18 ሺ ነበር፡፡ ከረሐቡና ከጥማቱ የተነሳ እስረኛውም ሁሉ መናገር አይችልም ነበር፡፡ ነፍሱ ገና አለቀው እያለች ነው እንጂ ሁሉም ደክሞ ይጠራሞት ነበር፡፡ ለመተንፈስ እስከማይችል ድረስ ያ ትልቁ ሰፊ ሜዳ ጠቦ ነበር፡፡ አንዱ እየተጋፋ መጣ፡፡ ጠርሙስ በእጁ ነበር፡፡ ፊቱ ክስመት ገብቶ ነበር፡፡ ከአጠገባችን ቆሞ ሊናገረን ፈለገ፡፡ ገና ከንፈሩን ማላቀቅ ግን አፈልቻለም፡፡ ከውሃ ጥማት የተነሳ ረድኤት በማፈልግ ዓይን በሚያሳዝን ተኩሮ ወደ አኛ ተመለከተ፡፡ በታላቅ ችግር በውሃ ጥማት የተያያዘውን ከንፈር አላቀቀው፡፡ ደካማ በሆነ ድምፅ “እባካችሁ! እባካችሁ!” ሲል ሰማነው፡፡ ነገሩን የሚለውን አጥርተን አልሰማነውም ነበርና ልንሰማው እንድንችል ወደ እኛ በጣም ቀረበ፡፡ እ…ባካችሁ ከአናንተ ጭብጦ የሌላችሁ ሽንቱን በዚህ ጠርሙስ ይስጠኝ ወንድሞቼ ሁለቱ በውሃ ጥማት ሞቱ፤ እኔም ልሞት ነኝ፤ እባክዎ ጭብጦ ባይኖርዎ ሽንትዎን አባክዎ ጌታ ይስጡኝ” ብሎ ልመናውን ወደ አቶ ገብረመድህን አወቀ አበረታው፡፡ አቶ ገብረመድህን አወቀም “እኔም አንዳንተ ነኝ፡፡ ውሃ ከጠጣሁ ሦስተኛ ቀኔ ነው፡፡ ከዬት ሽንት አመጣለሁ?” እኛንም አልፎ እየዞረ ሲለምን አልቆየም፡፡ አስከ መጨረሻው ደክሞት ነበር፡፡ መናገርም አቃተው፡፡ አንድ ድንጋይም በአጠገባችን ተንተርሶ ጥቂት ጊዜ ተጋድሞ በሕይወቱ ቆየ፡፡ በመጨረሻም ግን እንደ እንቅልፍ በሞት ያችን ድንጋይ እንደተንተራሰ አሸለበ፡፡ በዚህ ቀን በውሃ ጥማት ከመቶ በላይ እሰረኛ ከጥዋት እስከ ሰባት ሰዓት ሞቱ፡፡ ሬሳቸውንም ካሚዮኖች መጥተው ወሰዱት፡፡ በዚህ ጊዜ የእስር ቤቱ ሹም ቲሊንቲ ሎዊጂ ኮርቦ የሚባለው በዚያ እስር ውስጥ ገብቶ የተጠሙትን ነፍሳቸው አልላቀቅ ያላቸውን አይቷቸው ኑሯል፡፡ በኰዳው ውሀ ይዞ መጣ፡፡ ቲሊንቲም የኮዳውን ውሃ ለእስረኛው መሸጡን ሰማን፡፡ ገንዘብም ይዤ ሄድሁ፡፡ የሚሸጠው እሱ ብቻ ስለሆነ ካጠገቡ መድረስ አይቻልም፡፡ የተጠማው ብዙ ሕዝብ ውሃ ለማግኘት ዙሪያውን ከቦት ይጋፋ ነበር፡፡ ገዥውም ፋታ አያገኝም ነበር፡፡ በቀኝ እጁ ሽጉጡን አውጥቶ፤ በግራ እጁ በተጠማው ሰው በአፉ ውስጥ ትንሽ ጠብ ያደርግለታል፡፡ የኢጣሊያ አንድ ኰዳ ሁለት ጠርሙስ ተኩል ይይዛል፡፡ ቲሊንቲ አንዱን ኰዳ ውሃ ለሃያ አምስት ሰው አስጠጥቶ ሃያ አምስት ብር ለአንድ ኮዳ ተከፈለው፡፡ የአቶ ስለሺ አሽከርም በጣም ተጠምቶ ነበር፡፡ አንድ ብር በቲሊንቲ ግራ እጅ አኖረ፡፡ እሱም ከኰዳው አጠጣው፡፡ ቲሊንቲም ውሃውን አቀረበና በአፉ አፈሰሰበት፡፡ ጠጪውም ስላልረካ ኮዳውን ቲሊንቲን ቀልጥፎ ሲያቃናው በሁለት እጁ ከአፉ አስጠግቶ ያዘው፡፡ ቲሊንቱም ሽጉጡን በዓይኑ መሐል ተኮሰበት፡፡ ሳይውጠው ገና በጉንጩ የነበረው ሲወድቅ በአፉ ፈሰሰ፡፡ ቲሊንቲም ደጋግሞ ተኩሶ ጨረሰው፡፡ እርሱን በተኰሰው ጊዜ አሳልፎ ክንዱን ያንዱን ሰው አቁስሎት ስለነበር የቆሰለው ብር እንኳ ቢሰጠው እንዲሁ ያለ ዋጋ አጠጣው፡፡ ይህንም በውሃ ጥማት የሆነውን ታላቅ እልቂት እንዲቀር ውሃ በሸራ ቧንቧ ኢጣሊያኖች ከታሰርንበት ድረስ አስገብተው በ120 በርሜል ሞሉልን፡፡ እኒያ ሁለት ሹማምንቶች ማርሻሎና ቲሊኒቲ ሎዊጂ ኮርቦ እስረኛውን እያካፈሉ ከዚያ ወዲህ ያለው ይጠጣ እያሉ ሲከላከሉ አንድ ጊዜ እስረኛው እንደ ናዳ ተንዶ ጥሷቸው ሄደና ውሃም የቻለውን ያህል ይጠጣ አለ፡፡ በርሜሉንም ገና ያላየው ነበር፡፡ እነርሱም በዚህ ግፊት እኒህ ውሃ ሲሸጡ የዋሉ ሹማምንቶች ተድጠው ሞተው ኑረዋል፡፡ የሹማምንቶቻቸውን ሞት ስላወቁ ሰው ላይ ቦምብ ይወረውሩበት ጀመር፡፡ በበርሜሎች ዙሪያ ሬሳው ተከመረ፡፡ በቦምብ የተመቱት የጥቂቶችም ሬሳ በበርሜሎች ውሃ ውስጥ ገባ፡፡ ደማቸው ተቀላቀለበት፤ ሰውም ከላያቸው ላይ ሳይፀየፍ ይጠጣ ነበር፡፡ ልብሶቸውንም በበርሜሉ ውሃ እየነከሩ አምጥተው የተነከረውን ልብስ እንደ ጡት ጠቡት፡፡ በደከሙት ባልጀሮች አፍም እየጨመቁላቸው ቤዛ ሆኑ፡፡ ከተወረወረብንም ቦምብ ብዛት የተነሳ የሞተው ሬሳ በበርሜሎች ዙሪያ ተቆልሎ ነበርና ሰው ቢሄድም ሬሳው ወደ በርሜሉ እንደማያደርሰው አወቀ፤ ከመሄድም ታገሰ፡፡ ሦስት መትረየስ አግብተው ጠምደው ተኮሱብን፡፡ ውሃ ለእስረኛ ሲሸጡ ውለው እግዜር ፈርዶባቸው የተዳጡትንም የሹማምነቶቻቸውን በቀል ተበቀሉን፡፡ አምስት ካሚዮን አመላልሰው አንድ ሺ አምስት መቶ የሚያህል እስረኛ ሞተ፡፡ ሬሳውንም በካሚዮን እስኪያወጡ ድረስ ፈፅሞ ጨለመ፡፡ በኢጣሊያ ፋሽስት የተያዘ ሳይገደል በህይወት ፊት ምንድን ነው? መብልና ውሃ የሰጡን ሹማምንቶች ወደ ቤታቸው በተመለሱ ጊዜ ቁጣቸውን አድሰው በዙሪያው በውድሞው ያሉ ፋሽስቶች በሰው ህይወት ሊጫወቱ ቦምብ ይወረውሩብን ጀመረ፡፡ ግን የቁጣ ምክንያት አልነበራቸውም፡፡ በዙሪያው ከሚወረወር ቦምብ ለመሸሽ የማይደረስበት መሃከለኛውን ቦታ ለመያዝ እርስ በርሳችን ተጨናንቆ ተጋፍቶ ቆሞ ሳለ በዙሪያ ዳር የሚወረወሩት ቦምቦች ከመሀል አወራወራቸው ሊያደርሳቸው ስለማይችል በዳር በኩል ዙሪያውን ያሉትን ጨፈጨፏቸው፡፡ የቀረውም ከመሀል ሆኖ ለቦምብ ውርውራ ስለአቃታቸው መትረየሱን ለመሀል ጠምደው ተኮሱብን፡፡ ከጥይት ለመዳን የፈለገ ሲተኛ የቆመው ህዝብ ጨፈለቀው፡፡ የቆመውን መትረየስ ጠረገው፡፡ የቆሰለና ያልቆሰለ የሞተና ደህነኛ እስኪጠባ ድረስ ተቆላልፎ አደረ፡፡ ሰኞ በበነጋው ሌላ ሹም መጥቶ ደህናውንና የቆሰለውን በአንድ በኩል ለየው፤ የሞተውን ሬሳ ግን በካሚዮን ማጓዝ ጀመረ፡፡ ግን በዚያ ማታ በቦምብ የገደሏቸውን ሬሳውን ሳይወስዱ ስለቀሩ ወደ በሩ ሲል ወዳለው ማዕዘን አንድ ሴት እስከ ልጇ የታሰረች በቦመብ ተመታ ሞታ ኑሯል፡፡ ልጇ ደህና ነበረ፡፡ የእናቱንም ሬሳ ሌሊትን ሁሉ በደረቷ ላይ ተሰቅሎ ገና በሕይወት እንዳለች ሁሉ ይጠባት ነበር፡፡ እሰረኞችም ምንስ በእንዲህ ያለ ጭንቅ ተይዘው፤ በውሃ ረገድ ባይረዳዱ የዚህ ሕፃን ስቃይ ልባቸውን አንቀሳቀሰው፡፡ ይህን ሕፃን አንስተው ትናንት በግፍ ልጇ ለተዳጠባት ሴት እባክሽ አጥቢው ብለው ሰጧት፡፡ ያችም ሴት ለልጇ ምትክ እንዳገኘች ደስ ብሏት አልተቀበለችም፡፡ እንዲያውም ወርውራ ጣለችው፡፡ ነገ ኢጣሊያኖች በቦምብ ለሚገድሉት ለማሳደግ አላጠባም፡፡ ለመትረየስና ለሳንጃም አላሳዳግም ብላ ወረወረችው፡፡ በዚያ ብርቱ ፀሐይ ተንጋሎ ወድቆ ብርቱ ለቅሶ አለቀሰ፡፡ እኔም አንስቼ እናቱ ሬሳ ላይ አስቀመጥኩት፡፡ እናቱንም አንዳገኘ ሁሉ ደስ ብሎት ለቅሶውንም አቆመ፡፡ ወዲያውም በካሚዎን ሬሳውን መውሰድ ጀመሩ፡፡ የዚህን ህፃን እናቱ በካሚዎን ሬሳዋን ፋሽስቶች ወስደው ሲያገቡ አንዱ ኦፊሰር የሆነ ፋሽስት ይህን ህፃን ታቅፎ በእውነት ሲያለቅስ አየነው፡፡ እነዚህ የካቶሊክ ካህናት የሃይማኖት ወገናቸውን ሁሉ አስፈትተው ይዘው ሄዱ፡፡ የዛኑ ለት ማታውኑ የቀረነውን እስረኞች በካምዮን ጭነው ወደ ሆለታ ወሰዱን፡፡ እዛም ስንደርስ በጫካው አውርደው ተኮሱብን፡፡ እኔም አጠገቤ ያለው ሰው ተመቶ ሲወድቅ አብሬው ወደቅሁ፡፡ ጣሊያኖችም ጨርሰናቸዋል ብለው ትተውን ሄዱ፡፡ እኔም ካምዮኑ መሄዱን አረጋግጨ በሆዴ እየተንፏቀቅሁ ከዛ እሬሳ መሃል ወጥቸ በጨረቃ ብርሃን ወደ እትቴ በዛብሽ ቤት ሄድኩ፡፡ እዛም እንደደረስሁ በምክር ወደ ጐጃም እንዴት እንደምደርስ አሰላን፤ እርስዋም ልብሷን አለበሰችኝና ሻሽዋንም አስራልኝ ማሰሮ አሳዝላኝ በጨረቃ ብርሃን ጉዞየን ወደ ጐጃም አቀናሁ፡፡ የማውቀው የአባይን በረሃ በለሊት እየተጓዝሁ በቀን እየተደበቅሁ እማርቆስ ገባሁ፡፡ እዛም እናቴንና እህቴን በሌላ መንደር አገኘኋቸው፡፡ እናቴ “በቤቱ በምበላበት ገበታ ዙሪያውን ልጆቼና አባቴ ከበው ይቀመጡ ነበር፡፡ ዛሬ ግን በዚያው ገበታ ዙሪያና በዚያው ቤት ብቻየን እቀመጣለሁ፡፡ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ እንደ ቀመሰው መራራ ውኃ፤ ሕይወቴ ሁሉ መራራ ሆነ፡፡ ሕይወቴ ሁሉ እንዲህ ለኃዘን ከሆነ ለምን ሰው ሆንሁኝ?” አለች፡፡ እናቴን በእንዲህ ያለ ኃዘን ባየሁ ጊዜ ከቶ የተራበው ሰውነቴ እጅግ መብል ሊወስድ አልቻለም፡፡ በባቢሎን ወንዝ ዳር ተቀምጠው እሥራኤል ጽዮንን እያሰቡ ያለቅሱ እንደ ነበር ልንበላ በከበብነው ገበታ ዙሪያ ፈረንጆች የገደሏዋቸውን አያቴንና አራቱን ወንድሞቼን እያሰበች እናቴ አለቀሰች፡፡ እናቴ ገና ከአንድ ወር በፊት በገበታ ዙሪያ አብረዋት ይከቡ የነበሩትን ልጆቿን ፈረንጆቸ ሲገድሉባት ይቀመጡበት የነበረውን ቦታ ባዶውን ስታይ በአጭር ጊዜ እንዴት ልትረሳቸው ይሆንላታል? ይቀመጡበት የነበረው የገበታው ዙሪያና ይተኙበት የነበረው ክፍል ባዶነት እንደ ሐውልት ቁሞ ነበር፡፡ ወደ መብል ስትቀመጥ ባዶ የሆነውን ዙሪያ ወደመኝታ ቤት ስትሔድ ባዶውን አልጋ ማየት ለእናቴ እጅግ ኅዘን ነበር፡፡ ስለዚህም እናቴ ያን ቤት ትታ ሌላ ቤት ተከራይታ ነበር፡፡ እንዲሁ የእናቴ ዕንባ በጐንጮችዋ ላይ ሲወርድ ባየሁ ጊዜ ነጮች ያፈሰሱትን የወንድሞቸን ደም ያህል የቀረበውን መብል ቆጠርሁ፤ ለመብላትም ፈቃዴ ተዘጋ፤ ምንም እንኳ ተርቤ ብሰነብት፡፡ ከዚሀ በኋላ የቀረበው ሁሉ መብል ተነሣ፡፡ እኔ ከነጮች እንድሸሽ አጎቴ የሰጠኝን ፈረስ አቀረበልኝ፡፡ ጠጉሬ የከተማ ሰው ቁርጥ ነበርና እንደ ውጭ ባላገር እንድመስል እኅቴ እያበላለጠች ስትቆርጥልኝ አዘገየችኝ፡፡ ገና ከተዘንቦው በኩል ስትቆርጥልኝ አያሌ የነጭ ወታደሮች ቤቱን ከበቡት፡፡ እናቴ ከድንጋጤ የተነሣ አእምሮዋ ሳይቀር ጠፋባት፤ አጎቴና እኅቴ ከቤት ወጥተው ነገሩ ምንድን ነው? ብለው ጠየቋቸው፡፡ ብርጋዴሩ የያዘውን ሊስት አየና… እፈልጋለሁ አለ፡፡ በጣም ያስደንቅ ነበር፡፡ በሊስት የተያያዘው ስም በፍፁም የእኔ ስም ነው፡፡ ግን ያባቱ ስም አሥራት ይባል ነበር፡፡ የእኔ አባት ስም ሌላ .. ነበር፡፡ እህቴም የሚፈልጉትን ሰው ቤቱን እንደ ተሳሳቱ ነገረቻቸው፡፡ ብራጋዴሩ ሊስቱን እንደገና አየና ከአጎቱ ጋር ይኖራል እንጂ ለእርሱ ቤት የለውም ብሎ ነገራት፡፡ አዎን ያ ሰው ደግሞ ከአጎቱ ጋር ይኖር ነበርና አዎን ከአጎቱ ጋር ነው ብላ ነገረችው፤ ወታደሮቹም ሔደው ያንን ቤት ከበቡት፡፡ መንደረተኛውን ሁሉ እንዳይወጣና አንዳይገባ ከለከሉ፡፡ ያን ለመያዝ ከዚያም ጫጫታ ሆነ፡፡ በዚህ ጊዜ ለማምለጥ ቅጽበት ጊዜ አገኘሁ፡፡ ኮርቻ ለመጫንና ለመለጎም ጊዜ አልነበረም፤ በፈረሱ ያለ ኮርቻ ያለ ልጓም ተቀመጥሁና ጋለብሁ፡፡ ጠጉሬን ግማሹን ተቆርጨ ግማሹን ሳልቆረጥ አመለጥሁ፡፡ ይህም ዛሬ ተረት ይመስላል፡፡ ሕይወቴ ከነጮች በማምለጥ ለሩጫና ለሽሽት ብቻ ሆነ፡፡ በፊቴም ሁሉ ተስፋና መጽናኛ የለም፤ ዙሪያውም ሁሉ ከሌሊት የባሰ ጨለማ ሆነብኘ፡፡ በሀገራችን እያባረሩ ለሚያድኑን ለነጮች የምታበራይቱ ፀሐይ ግን በሃገራችን ሰማይ ታበራ ነበር፡፡ ስለዚህም ለሚያዳኑን ለእነርሱ የሚያምረው የበጋ ብርሃን ለምታደነው ለእኔ የክረመት ጨለማ ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ አእምሮው ጮሌ የሆነ ዕውር ከእኔ የተሻለ ነበር፡፡ ወዴት እንደምሸሽ ከቶ አላውቅም ነበር፡፡ ወዴት እንድጋልብ ሳላውቅ ፈረሱን ወደ ቀጥታው እንዲጋልብ ለቀቅሁት፡፡ በማዶው በኩል በተራራው ግርጌ ተፋጥኜ ካለፍሁ በኋላ አርባ ማይል እንደ ተጓዝሁ ከራዕዩ እንደ ተመለሰ ሰው ሆንሁ፡፡ ለጥቁር ሕዝብ በሰላም የተሰማራበትን ነጮቹ በማደን የማያባርሩበትን አዲሱን ክበብ አየሁ፡፡ አዲስ ምድርና አዲስ ሰማይ ያህል መሰለኝ፡፡ በዚያም ጠባቂ የሌለው በግ ጥቁሩ ሕዝብ ተሰማርተዋል፡፡ ጠባቂው በእንግሊዝ አገር ነው፡፡ ቀበሮው ከዚህ አስቀድሞ አልገባም ነበር፡፡ የዘር ወራት ነበርና ሁሉም ደርሶ ነበር፡፡ ያን ሃገር ነበረና የዘራውን ሊበላ በተስፋ ይዘራ ነበር፡፡ ገና ነጮች ሃገሩን አልወረሩትም ነበርና በመስኩ ከብቱ ተሰማርቶ ነበር፡፡ እናቶች በቤታቸው ናቸው፡፡ ሕፃናቶችም በመንደራቸው አንደ ማለዳ ወፎች እየተንጫጩ ይጫወታሉ፡፡ በግ ጠባቂው በጎችን ይመለከታል፡፡ ከብቶችን የማያረባው ዘላን ከብቶችን ይከተላል፡፡ ወደ መንደራቸው ጠባቂዎች ከመንጋዎቻቸው ጋር ይጓዛሉ፡፡ ወርቅ የሚመስለው የፀሐይ ጮራ በተራራዎች ላይ ተዘርግቷል፡፡ ገበሬዎች በሚያርሱበት ቦታ ጅራፍ ብቻ ይጮሃል፡፡ የኤውሮፓ ማሰልጠኛ ቦንብና መድፍ መትረየስ ድምፅ አይሰማም፡፡ በነጮች ወራሪ የሣር ክዳን አንድ ጎጆ የተቃጠለ አመድ የለምና ንፋሱም አመድ አያበንም፡፡ በወንዙ ዳር የተተከሉ ለጋ ሸንበቆዎች በወታደር አልተጣሱም፡፡ ገና ንፋሱ ያወዛውዛቸዋል፡፡ ባላገሮች በሃገራቸው ላይ በፍፁም ፀጥታ ይኖራሉ፡፡ እንዲህ ያለ ጥቁር ሕዝብ ከሰላሙ ጋር የሚኖርበት አዲስ አገር አገኘሁ፡፡ የሰላም የሰላም የሰላም ሃገር፡፡ ነጮች ወራሪዎች አልረገጥዋትም፤በድንገት ግን አደጋ ጥሎ ለመወረር ገና ሳያዩዋቸው በሚስጥር መግባት ጀምረዋል፡፡ በቤቴ ለመኖር የነበረኝ ሰላም በነጮች ከተቀጠቀጠ ሁለት ዓመት ያህል ሆኖ ነበርና በሀገራቸው በሰላም እንዲሁ የሚኖሩትን ሰዎች በማየቴ ካለፈው ዓመት በፊት እንዴት በሰላም ከበቴ እኖር እንደነበር አሳሰበኝ፡፡ በሰሩት ቤት መኖር! ሰማይ ቢከፈት ከዚህ የበለጠ ስጦታ በምድር ሊዘንብ በቻለ፡፡ ሕዝብ በሀገር ውስጥ በሰላም መኖር ሕፃናትን በሰላመ ማሳደግ ቤተሰብን መረዳት ከዚህም ጋራ በሰሩት ቤት በሰላም መኖር! ከዚህ የበለጠ የበረከት ፍሬ መሬት ልትሰጥ ትችላለችን? ሰው በሕይወቱ የሚመኘውና ሊኖረው የሚፈልገው ይህ ብቻ ነው፡፡ የነጮች ወራሪዎች በረገጧት ሃገር ሁሉ ለሕያው ነፍስ የሚያስፈልገው የሰላም ኑሮ የለም ነበር፡፡ ከወራሪዎች ድንግል በነበረችው ከዚህች አውራጃ ሃገር በደረስሁ ጊዜ አዲስ ሌላ አለም ያየሁ ያህል መሰለኝ፡፡ ያልታደለችው ኢትዮጵያ በእርግጥ ሰፊ ሃገር ናት፡፡ ወራሪዎችም ባንድ ጊዜ በሙሉዋ ሊጎርሷት አልቻሉም ነበርና በየከተማ አጠገብ ያሉትን ሃገሮች በቦምብ በመርዝና ቤቶችን በማቃጠል ያልታደለውን ፍጥረት ገና ያመነዥኩ ነበር፡፡ በተራራዎችና በአፋፎች የኢጣልያኖች መድፎች እንደ ክረምት ነጎድጓድ ይጮሃሉ፡፡ ባለ ከብቶች ከከብታቸው ጋር የሚኖርባቸው ጠፍጣፋ ሃገሮች በጉም እንደሚጋረዱ የተራራ እግሮች በመርዝ ጢስ ታፍነዋል፡፡ ከዓመት አራት ጊዜ ፍሬዋን ትሰጥ የነበረች ሃገር ያለ አዝመራ ሆነች፡፡ ለመታጨድ የደረሱ አዝመራዎችን የሰለጠኑት ነጮች በእሳት ቦምብ ሲያቃጥሉት፤ ዝሆኖች አንበሶች አንደሚኖሩባት በረሃ የገበሬዎች አዝመራ ተቃጠለ፡፡ ቅጠልያ የሆነችው ሃገር ከቃጠሎው የተነሣ እንደ ነብር ቆዳ ዝንጉርጉር ሆነች፡፡ ከጠፍጣፋው ሃገር ሸሽተው በተራራ ሰዎቸ ተሰማሩ፡፡ የተሰማሩበት ጫካ ሳይቀር ተቃጠለ፤ ከነጮች የሥልጣኔ ቦምብና መርዝ የሚሸሹ የአፍሪካ ሕፃናቶች ለሊት ሲባንኑ መርዝ! መርዝ! መርዝ! እያሉ በዕንቅልፋቸው እየጮሁ ያለቅሱ ነበር፡፡ በዚህም ሁሉ ያ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ ለመቁረጥ ብቻ ሆነ፡፡
13729
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%88%E1%89%83%20%E1%8C%8D/%E1%88%A8%E1%8A%83%E1%8A%93%20%E1%89%A0%E1%8C%A3%E1%88%9D%20%E1%8A%A0%E1%8C%AD%E1%88%AD%20-%20%E1%8B%B5%E1%8A%95%E1%8A%AD%E1%8B%AC%20%E1%88%B0%E1%8B%8D%20%E1%8A%93%E1%89%B8%E1%8B%8D
አለቃ ግ/ረኃና በጣም አጭር - ድንክዬ ሰው ናቸው
አለቃ ግ/ረኃና በጣም አጭር - ድንክዬ ሰው ናቸው ሚስታቸው ወይዘሮ ማዘንጊያሽ ደግሞ ሲበዛ 1ሜትር ከ80 ናቸው። መንገድ ውለው ወደቤታቸው ሲመለሱ ወይዘሮ ማዘንጊያሽ ሠማዩን አይተው አለቃ ዝናብ ሊዘንብ ነው መሰለኝ ይሏቸዋል። ከዚያ አለቃ ከኋላቸው ኩስ ኩስ እያሉ ሲመልሱላቸው! «እኔ ምን አውቃለሁ ለሰማዩ ቅርቡ አንቺ ነሽ» አሏቸው ይባላል። መደብ : የኢትዮጵያ ቀልዶች
3915
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%A8%E1%88%AD%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%8B%B5%20%E1%88%AA%E1%8D%90%E1%89%A5%E1%88%8A%E1%8A%AD
አየርላንድ ሪፐብሊክ
ይህ ገጽ በቀጥታ በእንግሊዝኛ ከተመሳሳዩ ገጽ የተወሰዱ ምንጮችን ይጠቀማል። እባክዎን የእኔን ትርጉሞች ለማሻሻል ያግዙ!አየርላንድ ወይም / (ያዳምጡ) ፤ አይሪሽ: ኤይሬ [] (ያዳምጡ)፤ ኡልስተር-ስኮትስ: አየርላን በሰሜን-ምዕራብ አውሮፓ በሰሜን አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ የምትገኝ ደሴት ናት። ከታላቋ ብሪታንያ በምስራቅ በሰሜን ቻናል፣ በአይሪሽ ባህር እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ቻናል ተለያይቷል። አየርላንድ የብሪቲሽ ደሴቶች ሁለተኛዋ ትልቅ ደሴት ናት፣ በአውሮፓ ሶስተኛዋ ትልቁ እና በአለም ሃያኛዋ ነች። በጂኦፖለቲካዊ መልኩ፣ አየርላንድ በአየርላንድ ሪፐብሊክ (በይፋ አየርላንድ ተብሎ የሚጠራው)፣ የደሴቲቱን አምስት ስድስተኛ ክፍል በሚሸፍን ገለልተኛ መንግስት እና የዩናይትድ ኪንግደም አካል በሆነችው በሰሜን አየርላንድ መካከል ተከፋፍላለች። እ.ኤ.አ. እስከ 2022 ድረስ ፣ የመላው ደሴት ህዝብ ብዛት ከ 7 ሚሊዮን በላይ ነው ፣ 5.1 ሚሊዮን በአየርላንድ ሪፐብሊክ እና 1.9 ሚሊዮን በሰሜን አየርላንድ ውስጥ ይኖራሉ ፣ ይህም በአውሮፓ ውስጥ በሕዝብ ብዛት ከታላቋ ብሪታንያ ቀጥሎ ሁለተኛዋ ነች። የአየርላንድ ጂኦግራፊ በአንፃራዊነት ዝቅተኛ የሆኑ ተራሮችን በማእከላዊ ሜዳ ዙሪያ ያቀፈ ሲሆን በርካታ ወንዞችም ወደ ውስጥ ይዘልቃሉ። ለምለሙ እፅዋት ከሙቀት ጽንፍ የፀዱ መለስተኛ ግን ተለዋዋጭ የአየር ንብረት ውጤት ነው። አብዛኛው አየርላንድ እስከ መካከለኛው ዘመን መጨረሻ ድረስ ጫካ ነበር። ዛሬ ዉድላንድ የደሴቱን 10% ያህሉን ይይዛል፣ ከአውሮፓ አማካኝ ከ33% በላይ ከሆነ፣ አብዛኛዎቹ ተወላጅ ያልሆኑ የኮንፈር እርሻዎች ናቸው። የአየርላንድ የአየር ንብረት በአትላንቲክ ውቅያኖስ ተጽዕኖ ስለሚኖረው በጣም መጠነኛ ነው እና ክረምቱ እንደዚህ ላለው ሰሜናዊ ክፍል ከሚጠበቀው በላይ ለስላሳ ነው ፣ ምንም እንኳን የበጋው ወቅት በአህጉራዊ አውሮፓ ካሉት የበለጠ ቀዝቃዛ ነው። የዝናብ እና የደመና ሽፋን በብዛት ይገኛሉ። ጌሊክ አየርላንድ ብቅ ያለችው በ1ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም. ደሴቱ ከ 5 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በክርስትና እምነት ተከታይ ነበር. ከ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የአንግሎ ኖርማን ወረራ በኋላ እንግሊዝ ሉዓላዊነቷን ተናገረች። ነገር ግን፣ የእንግሊዝ አገዛዝ እስከ 16ኛው–17ኛው ክፍለ ዘመን ቱዶር ድል ድረስ በመላው ደሴት ላይ አልዘረጋም፣ ይህም ከብሪታንያ በመጡ ሰፋሪዎች ቅኝ ግዛት እንዲገዛ አድርጓል። በ1690ዎቹ የፕሮቴስታንት እንግሊዛዊ አገዛዝ ስርዓት የካቶሊክ አብላጫውን እና ፕሮቴስታንት ተቃዋሚዎችን በቁሳዊ መልኩ ለመጉዳት ተዘጋጅቶ በ18ኛው ክፍለ ዘመን ተራዝሟል። እ.ኤ.አ. በ 1801 በሕብረት ሥራ ፣ አየርላንድ የዩናይትድ ኪንግደም አካል ሆነች። በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የነፃነት ጦርነት ተከትሎ የደሴቲቱ ክፍፍል ተከስቷል ፣ ይህም የአየርላንድ ነፃ ግዛት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ፣ ይህም በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት እየጨመረ ሉዓላዊ ሆነ ፣ እና የዩናይትድ ኪንግደም አካል የሆነችው ሰሜን አየርላንድ። ሰሜን አየርላንድ ከ1960ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ እስከ 1990ዎቹ ድረስ ብዙ ህዝባዊ አመፅ ታይቷል። እ.ኤ.አ. በ 1998 ከጥሩ አርብ ስምምነት በኋላ ይህ ቀነሰ ። በ 1973 የአየርላንድ ሪፐብሊክ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብን ስትቀላቀል ዩናይትድ ኪንግደም እና የሰሜን አየርላንድ አካል እንደዚሁ አደረጉ። እ.ኤ.አ. በ 2020 ፣ ዩናይትድ ኪንግደም ፣ ሰሜናዊ አየርላንድ ፣ ያኔ የአውሮፓ ህብረትን () ን ትታለች። የአየርላንድ ባህል በሌሎች ባህሎች ላይ በተለይም በሥነ-ጽሑፍ መስክ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል. ከዋናው የምዕራባውያን ባህል ጎን ለጎን በጌሊክ ጨዋታዎች፣ በአይሪሽ ሙዚቃ፣ በአይሪሽ ቋንቋ እና በአይሪሽ ዳንስ እንደተገለጸው ጠንካራ አገር በቀል ባህል አለ። የደሴቲቱ ባህል ከታላቋ ብሪታንያ ጋር ብዙ ባህሪያትን ይጋራል፣ የእንግሊዘኛ ቋንቋን ጨምሮ፣ እንደ ማህበር እግር ኳስ፣ ራግቢ፣ የፈረስ እሽቅድምድም፣ ጎልፍ እና ቦክስ የመሳሰሉ ስፖርቶች። ሥርወ ቃል አየርላንድ እና ኤይሬ የሚሉት ስሞች ከድሮው አይሪሽ ኤሪዩ የወጡ ሲሆን በአይሪሽ አፈ ታሪክ ውስጥ አምላክ የሆነው አምላክ በዘጠነኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ተመዝግቧል። የኤሪዩ ሥርወ-ቃል አከራካሪ ነው ነገር ግን ከፕሮቶ-ኢንዶ-አውሮፓ ሥር * የመጣ ሊሆን ይችላል፣ የሚፈሰውን ውሃ ያመለክታል።
9599
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%8B%98
ተረት ዘ
ዘላለም ከመፍሳት አንዴ መቅዘን ዘመነ ግልምቢጥ ውሻ ወደ ሰርዶ አህያ ወደ ሊጥ ዘመነ ግርምቢጥ ውሻ ወደ ሰርዶ አህያ ወደ ሊጥ ዘመን እንደንጉሱ አውድማ እንደንፋሱ ዘመን የሚወልደውን ንጉስ የሚፈርደውን ዘመን የሚወልደውን ንጉስ የሚፈርደውን የሚያውቅ የለም ዘመን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ዘመን የወለደው ንጉስ የወደደው ዘመን ያነሳው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ዘመደ ብዙ ጠላሽ ቀጭን ነው ዘመደ ብዙ ጠላው ቀጭን ነው ዘመዱን ያማ ገማ ዘመዱን ያማ ለራሱ ገማ ዘመዱን ያማ እራሱ ገማ ዘመድ ሲጣላ ያረክሳል ዘመድ ሲፈራ ላሊበላ ሲኮራ ዘመድ በዘመዱ አይጨክንም ሆዱ ዘመድ ቢረዳዳ ችግርም ባልጎዳ ዘመድ ቢረዳዳ ችግርም አይጎዳ ዘመድና መድሀኒት የተቸገሩ ለት ዘመድና መድሀኒት በተቸገረ ቀን ይፈለጋል ዘመድና ሚዛን ከወገብ ይይዛል ዘመድና እሳት በሩቅ ዘመድና ሳንቲም ከመንገድ ወድቀው ሳንቲሙን አነሱ ዘመድን ጥለው ዘመድና ዋንጫ እያለቀሰ ይመጣ ዘመድና ገንዘብ ሳያስቡት ይገኛል ዘመድና ፍየል ቤት አጥፊ ነው ዘመድን ከዘመድ ጋር ማማት ዳቦ እንደመግመጥ ነው ዘመድን ከዘመድ ጋር ማማት ጮማ እንደመቁረጥ ይቆጠራል ዘመድን የሚወጉበት ጦር ጀንፎው አይለቀቅም ዘመድን የሚወጉበት ጦር ጅንፎው አይለቀቅም ዘመድ ከዘመዱ አህያ ካመዱ ዘመድ ያረጀ በልቶ ያፈጀ ዘመዶችዋ ሁሉ ይሏታል ግንድ አልብስ ዘምቶ ተወረሰ ዘምቶ ያረጀ በልቶ ያፈጀ ዘረፋና ቀን ካልተሻሙበት ያልቃል ዘሩ የጣቴ ምድሩ ያባቴ ዘር ልትበደር ሂዳ እህል ሲሸት መጣች ዘር ከልጓም ይስባል ዘር ከልጓም ይጠቅሳል ዘር ከልጓም ይስባል ዘር ከበረከት ትውልድ ከምርቃት ዘርቶ መቃም ወልዶ መሳም ዘርቶ ያልበላ አምላክን ጠላ ዘር የጣቴ ምድሩ ያባቴ ዘባራቂ ላባ ቀረሽ እብድ አስተኔ ዘባራቂ ይወዳል ምራቂ ዘቅዝቀው ቢቀብሩት ቀና ብሎ አደገ ዘንዶ የዳገት በረዶ ዘንጋዳ ከቆረጡት አገዳ ሚስት ከፈቷት እዳ ዘንጋዳ ተቆረጡት አገዳ እዳኛ ከደረሱ እዳ ዘንጋዳና ወታደር በመከር ጊዜ ይታይ ነበር ዘንጋዳ የገለበጠ አባቱን የገላመጠ ዘንዶ የዳገት በረዶ ዘንግ ከተተከለ ልብ ተከፈለ ዘኬውን ሲቋጥር አነቀው ነብር ዘጠኝም ቢታለብ ለኔ ያው ገሌ ነው ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለው ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለው አለ ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለው አለው ዘጠኝ ጠጥቶ አስረኛውን የወደደ በሙሉ ነደደ ዘጠኝ ጠጥቶ አስር የወደደ በሙሉ ተናደ ዘጥ ዘጥ አቁማዳ ቂጥ ዘገየች ከረመች ቆይታ መጣች ዘፈን በበገና ነገር በዋና ዘፈን በከበሮ አዋጅ በደበሎ ዘፈን በገና ነገር በዋና ዘፈን አለ በገና ነገር አለ በዋና ዘፈን አለ በገና ነገር አለ ዋና ዘፍኖ አያምር እንኳን አልቅሶ ዛሬ ጠምቃ ፈጀችው ጠልቃ ጠልቃ ዛሬ የትላንት ነገ ነበረች ዛሬ ደግሞ የነገ ትላንት ትሆናለች ዛር ልመና ሳይያዙ ገና ከተያዙ ብዙ ነው መዘዙ ዛብ የሌለው ፈረሰኛ ምሳ የሌለው ኮሰኛ ዛፍ ሲወድቅ ከግንዱ ሰው ሲቸገር ከዘመዱ ዛፍ በሌለበት እንቧጮ አድባር ይሆናል ዛፍ እራሱን ያውቃል ዛፍ ዝናብ ያስጥላል ትልቅ ሰው ከዳ ያስጥላል ዛፍ ያለቅርንጫፍ አይደምቅም ሰው ያለሰው አይከበርም ዛፎች ቢጠፉ ቁጥቋጦች ተሰለፉ ዛፎች ቢጠፉ ቁጥቋጦች ዛፎች ነን አሉ ዛፎች አለቁ እና ግራሮች ዛፍ ሆኑ ዜማ በሀሌ ነገር በምሳሌ ዝሆኑ ሳለ ዱካውን ዝሆን ለቀንድ ባላባት ለትውልድ ዝሆን ማለት ከሞኝ ያስቆጥራል ዝሆንም ለሆዱ ድምቢጥም ለሆዱ ወደ ወንዝ ወረዱ ዝሆን ቂጡን ተማምኖ ግንድ ይውጣል ዝሆን ቢያንቀላፋ ዛፍ ተደግፎ ነው ዝሆን እንሆት ፍለጋው ወዴት ዝሆን እንሆ ፍለጋው ወዴት ዝሆን ጥርሱን አዝመራ ገብሱን ዝሆንና ዝሆን ቢጣሉ የሚጎዳው ሳሩ ዝሆን የዋለችበትን ትመስላለች ዝም ባለ አፍ ዝምብ አይገባበትም ዝም ብትል ባትከበርም ችላ ትባልበታለህ ዝምታ ለበግም አልበጃት አስራ ሁለት ሆና አንድ ነብር ፈጃት ዝምታ ራሱ መልስ ነው ዝምታ ራሱን የቻለ መልስ ነው ዝምታ ወርቅ ነው ዝምታ ወርቅ ነው መናገር ብር ነው ዝም አይነቅዝም ዝም ያለ ተንኮለኛ ይመስላል እንብላ ያለ ስስታም ይመስላል ዝርክርክ ከወንፊት የባሰ ዝክዝክ ዝቅ ቢል ከገብርዬ ከፍ ቢል ከዚያ ሰውዬ ዝባድን ከውሻ እምነትን ከባለጌ አትሻ ዝናር የሌለው ነፍጠኛ አለንጋ የሌለው ፈረሰኛ ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ዝናብ ለዘር ጠል ለመኸር ዝናብ ሊጥል ሲል ይነፋፍሳል ዝናብ ሊጥል ሲል ይነፍሳል ዝናብ ሲያባራ ከዋሻ ምን ሊሻ ዝናብ ሲያባራ ዋሻ ምን ያሻ ዝናብ ሳይመጣ ሁሉ ቤት እንግዳ ባይመጣ ሁሉ ሴት ዝናብ ሳይመጣ ገና የውሀን መንገድ መጥረግ ደህና ዝናብ ከደመና ነገር ከዋና ዝናብ ካልጣለ ሁሉ ቤት እንግዳ ካልመጣ ሁሉ ሴት ዝናብ ካባራ ወደ ዋሻ ዝናብና ልጅ ሲጠሉት ያከብር ዝናብ ዘነበ ቢለው ከደጅህ እየው ዝንብ ሩቅ አይበር ሜዳ አደግ ዱር አይደፍር ዝንብ ሩቅ አይበር የሜዳ ልጅ ዱር አይደፍር ዝንብ ሳያቆሙ ዝግን አይቅሙ ዝንብ ሳይቅሙ ዝግን አይቅሙ ዝንብ ቢሰበሰብ መግላሊት አይከፍትም ዝንብ ቢሰበሰብ ጋን አይከፍትም ዝንብ ካይን ጭራ ከዘባን ዝንጀሮ መቀመጫዬ ይብሳል አለች ዝንጀሮ የመቀመጫዬ ይቅደምልኝ አለች ዝንጀሮ ሰው ነበር ይላሉ ድሮ ዝንጀሮ ቢሰበሰብ ውሻን አይመክትም ዝንጀሮ እንሳሳቅ ካልሽ ነዶዬን መልሽ ዝንጀሮና ጥዋ ካፉ ነው የሚያዝ ዝንጀሮና ጥዋ ክፉ ነው የሚይዝ ዝንጀሮን በበግ ለውጠኝ ቢለው ጣፍጩን ትቼ አልማጩን ዝንጀሮ የራሷን ጠባሳ ሳታይ በባልንጀራዋ ሳቀች ዝንጀሮ የቂጧን መላጣ ሳታይ በባልንጀራዋ ትስቃለች ዝንጅብል ማን ቢሉህ ማነኝ ትል ዞር አሉ አልሸሹም ዞሮ ዞሮ መዝጊያው ጭራሮ ዞሮ ዞሮ እራቱ ጥሬ ዞሮ ዞሮ የዶሮ አንገት በማሰሮ ዞሮ ዞሮ የዶሮ አንገት ከማሰሮ]]
15722
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%89%85%E1%8B%B0%E1%88%8B
መቅደላ
መቅደላ ወይም በአሁኑ ስሙ አምባ ማርያም የሚባለው አምባ፣ ወሎ ውስጥ የሚገኝ በአጼ ቴወድሮስ ዘመን ለዋና ከተማነት ታጭቶ በመካከሉ በእንግሊዞች ጦርነት ወቅት የተቃጠለ ከተማ ነው። በአሁኑ ወቅት በአካባቢው 1899 ሰወች ይኖራሉ። መቅደላ አምባ እና ዓፄ ቴዎድሮስ መቅደላ አምባ ለመድረስ ከደሴ ከተማ በስተምዕራብ ፻፳፰ ኪ/ሜ ርቀት ላይ ከምትገኘው የተንታ ከተማ በስተሰሜን ምስራብ ፳፱ ኪ/ሜ መጓዝን ይጠይቃል፡፡ ጥንት ከመቅደላ ደብረ ታቦር ከዚያም ወደጣና ሐይቅ ዳርቻ የሚያዘልቅ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ጐብኝዎች የሚታወቅ የእግር መንግድ ነበር፡፡ ግን ልክ እንደ ጥንታዊው የላሊበላ ሰቆጣ መንገድ ሁሉ መስመሩ ከተዘጋ ዘመናት ተቆጥረዋል። መቅደላ ሲነሳ ዓፄ ቴዎድሮስ መታወሳቸው የማይቀር ነው፡፡ የመቅደላ አምባ ዙሪያ ገባውን ከርቀት ለመቆጣጠር የሚያስችል በመሆኑና በዘመኑ የፖለቲካ ከርሰ-ምድር ሁነኛ ሥፍራ ላይ በመገኘቱ ከፍተኛ ቁልፋዊ ጥቅም ነበረው፡፡ ይህ ጠቀሜታ ደግሞ በወቅቱ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ለሚጥር ንጉሥና ባለሟሎቹ የሚሰወር አልነበረም። በንጉሠ ነገሥቱ የፖለቲካ ሥልጣን መባቻ ለሰባት ወራት የተካሄደው የወሎ ዘመቻ የተጠናቀቀውም በመቅደላ መያዝ ነበር፡፡ ዓፄ ቴዎድሮስ ከጎንደር በኋላ የሥልጣን ማእከላቸውን ለጊዜው ወደ ደብረ ታቦር ከዚያም ወደመቅደላ በማዞር ለተቀረው ግዛት ዓርዓያ ሊሆን የሚችል የአስተዳደር ሥርዓት ለማቆም ጥረት የጀመሩት በዚሁ ሥፍራ ነበር፡፡ በርካታና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች፣ ብዛት ያላቸው ገድሎች፣ መጻሕፍትና ድርሳናት እንዲሁም የንጉሠ ነገሥቱ የግል የክብር ዕቃዎች በሥርዓት ተሰድረው ይቀመጡ የነበረው በመቅደላ ግምጃ ቤት ነበር። በዘመኑ ፲፭ መድፎች፣ ፯ ሞርታሮች፣ ፲፩ ሺ ፷፫ የተለያዩ ጠመንጃዎች፣ ፰፻፸፭ ሽጉጦችና ፬፻፹፩ ሳንጃዎች፣ ፭፻፶፭ የመድፍና የሞርታር አረሮች እንዲሁም ፹፫ ሺ ፭፻፷፫ የተለያዩ ጥይቶች በመቅደላው ግምጃ ቤት እንደነበሩ መረጃዎች ይገልፃሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን ለታሪክ መዘክርነት በቦታው ከሚገኙት ቅርሶች አንዱ ‘ሴባስቶፖል’ የተባለው የንጉሠ ነገሥቱ ትልቅ መድፍ እና ዓፄ ቴዎድሮስ ጊዜያዊ ቤተ መንግሥት ፍርስራሽና የመቃብር ቦታዎች ናቸው፡፡ መጽሐፍቱ፣ ድርሳናቱ፣ የወርቅና ብር ዋንጫዎች፣ አክሊሎችና ሌሎች የንጉሠ ነገሥቱ የግል ሀብቶች የነበሩ ቅርሶች ሁሉ ከመቅደላው ጦርነትና ከዓፄ ቴዎድሮስ እረፍት በኋላ በደላንታ ሜዳ ለጨረታ ተሰጥተው በ ናፒዬር የተመራው የእንግሊዝ ሠራዊት ተቀራምቷቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ከንጉሠ ነገሥቱ አናት ላይ የተሸለተውን ሹሩባ ፀጉር ጨምሮ ሌሎች ቅርሶች በእንግሊዝ አገር የተለያዩ የሥነ-ቅርስ መዘክሮች ውስጥ ተቀምጠው ይገኛሉ። ከዓርዓያዊ የአስተዳደር ማዕከልነትና ግምጃ ቤትነት ባሻገር የንጉሠ ነገሥቱ ወህኒ ቤትም የሚገኘው በመቅደላ ነበር፡፡ በእጅ ተይዘው በሞት ያልተቀጡ ጠንካራ የሥልጣን ተቀናቃኞች፣ ምርኮኞችና አማጽያን ከመቅደላ ነዋሪዎች ጥቂቶቹ ነበሩ። ከእነዚህም አንዱ የኋላው ንጉሠ ነገሥት የያኔው ደጃዝማች ምኒሊክ ናቸው። ምኒልክ ለ አሥራ አንድ ዓመታት የመቅደላ እስረኛ ነበሩ። አጼ ቴዎድሮስ ከእንግሊዝ መንግሥት ጋር በነበራቸው ጠብ እልህ ውስጥ ገብተው በጎንደር ይኖሩ የነበሩ የውጭ ዜጎችን ሰብስበው ያጎሩት በመቅደላው ወህኒ ቤት ነበር፡፡ በመጨረሻም የመቅደላ አምባ የአጼ ቴዎድሮስ ሥልጣን መደላደል ምልክት የመሆኑን ያህል የፍጻሜያቸውም ተምሳሌት ሆኗል። ሁሉም ነገር አብቅቶ የማይቀረው ፍፃሜ ሲቀርብ ራሳቸውን በክብር ያጠፉት በዚሁ በቅደላ አምባ ነው፡፡ የመቅደላ አምባ ከአጼ ቴዎድሮስ ሞት በኋላም እስረኞች የሚታገቱበት ሥፍራ መሆኑ አልቀረም። ከሰገሌ ጦርነት አምስት ዓመት ቀደም ብሎ በታኅሣሥ ወር ፲፱፻፫ ዓ/ም የወሎው ራስ ሚካኤል አልጋ ወራሽነት ታጭተው የነበሩትን የልጃቸውን የልጅ ኢያሱን ሥልጣን ለማጠናከርና ሁኔታዎችን ለመቆጣጠር ወደ ስምንት ሺህ የሚደርስ የወሎ ሠራዊትን አስከትለው ወደ አዲስ አበባ ከዘመቱ በኋላ ይደርሳል ተብሎ የተፈራው ግጭት በአቡኑ እና በእጨጌው ገላጋይነት በርዶ ራስ ሚካኤል ወደ ወሎ ሲመለሱ ከአመጹት መካከል አንዱ ናቸው ያሏቸውን ራስ አባተ ቧ ያለውን ወደ መቅደላ በመውሰድ ለአምሥት ዓመታት በእስር አቆይተዋቸዋል፡፡ ከሰገሌ ጦርነትም በኋላ ልጅ ኢያሱ እራሳቸው ከማዕከላዊው መንግሥት በሸሹበት ጊዜ እዚሁ መቅደላ ላይ ለጥቂት ጊዜ መሽገው እንደነበር ታሪክ ይዘግባል። ታሪኩን ለሚያውቅ የመቅደላ ጉብኝት ልዩ ስሜት ይፈጥርበታል፡፡ ሁሉም ጐብኝ ግን የቴዎድሮስን ፍፃሜ በዓይነ ህሊናው ማስተዋሉ አይቀርም፡፡ በመቅደላ አምባ አካባቢ ሊጐበኙ ከሚችሉ ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶች መካከል በ፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሐ ወአጽብሐ ዘመነ መንግሥት መተከሉ የሚነገርለት የሰላምጌ ሥላሴ፣ በአጼ ላሊበላ ዘመን ከአንድ አለት ተፈልፍሎ የተሠራው የፉል አምባ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን፣ በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዓፄ ይስሐቅ ዘመነ መንግሥት መመሥረቷ የሚታመነው የመቅደላ ማርያምና በ፳ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በንጉሥ ሚካኤል የተሠራው የተንታ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ዋናዎቹ ናቸው፡፡ በውስጣቸውም የኢትዮጵያን ጥንታዊነት የሚዘክሩና በርካታ ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ይዘዋል። ዋቢ ምንጭ “አማራ ክልልና መስህቦቿ” የኢትዮጵያ ተራሮች የኢትዮጵያ ከተሞች አጼ ቴዎድሮስ
49917
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A5%E1%8C%8D%E1%8B%9A%E1%8A%A0%E1%89%A5%E1%88%94%E1%88%AD%20%E1%88%B0%E1%88%8B%E1%88%9D%E1%8A%93%20%E1%88%B5%E1%88%9D%E1%88%9D%E1%8A%90%E1%89%B5
የእግዚአብሔር ሰላምና ስምምነት
የእግዚአብሔር ሰላምና ስምምነት ወይም በሮማይስጥ /ፓክስ ኤት ትሬውጋ ደይ/ በዓለም ታሪክ መጀመርያው የታወቀ ሕዝባዊ የሰላም እንቅስቃሴ ነበር። «የእግዚአብሔር ሰላም» መጀመሪያ በ981 ዓም በአሁኑ ፈረንሳይ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪነት የታወጀ ነበር። ከንጉሡ ካሮሉስ ማግኑስ መንግሥት በኋላ በምዕራብ ፍራንኪያ ወይም ፈረንሳይ፣ የመኳንንት ወገን በሕዝብ ላይ ብዙ መግደልና ዝርፊያ ያድርጉ ነበር። ይህን ለማቃወም፣ በመጀመርያ ቤተክርስቲያኑ በድሆች፣ በቄሶችና በአብያተ ክርስቲያን ላይ ግፍ ማድረጉን ቢከለክሉም ትንሽ ረዳ። በኋላ ከ1033 ዓም በኋላ «የእግዚአብሔር ስምምነት» በአንዳንድ ቀን ከሳምንት መግደልን ከለከለ። ይህንም የሚጥሰው ተወግዞ እራሱ የሚከተለው ግብ ይሆን ነበር። በየጥቂቱ በክፍለዘመናት ላይ ግፍ የተከለከለባቸው ቀኖች ተስፋፉ፣ በመጨረሻም ግፍ ሁሉ በሙሉ ሳምንት ተከለከለ። የአውሮፓ ታሪክ
16894
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%88%AE
መሮ
መሮ ከፌሮ ብረት ቁራጭ የሚሰራ እና በተለይም እንጨትን ለመፈልፈል እና ለመብሳት የሚያገለግል ሹል ብረት ነው። ይህ ብረት ለማገር፣ ጠርብ፣ አውራጅ ወይንም ሌላ የመዋቅር አይነቶች መብሻነት አልያም ደግሞ እንደ ግንብ ላሉ መዋቅሮች መፈልፈያነት ይጠቅማል። ይህ መሳሪያ በመዶሻ ወይንም መርቴሎ እየተመታ መዋቅሮቹን እንዲፈለፍል ወይም ወደ ውስጥ እንዲገባ ይደረጋል።
52418
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A6%E1%88%AA%E1%88%B5%20%E1%8B%AC%E1%88%8D%E1%89%B5%E1%88%B2%E1%8A%95
ቦሪስ ዬልትሲን
ቦሪስ ኒኮላይቪች የልሲን (ሩሲያኛ: ; የካቲት 1 ቀን 1931 - 23 ኤፕሪል 2007) የሩሲያ እና የሶቪየት ፖለቲከኛ ከ 1991 እስከ 1999 የሩሲያ ፌዴሬሽን የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት ሆኖ ያገለገሉ ። የሶቪየት ኮሚኒስት ፓርቲ አባል ነበሩ። ዩኒየን ከ1961 እስከ 1990። በኋላም እንደ ፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ የቆመ ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ በርዕዮተ ዓለም ከሊበራሊዝም እና ከሩሲያ ብሔርተኝነት ጋር የተቆራኘ ተደርጎ ይቆጠር ነበር። ዬልሲን የተወለደው በቡቱካ ፣ ኡራል ክልል ፣ ከድሃ ቤተሰብ ነው። ያደገው በካዛን, ታታር ውስጥ ነው. በኡራል ስቴት ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ከተማረ በኋላ በግንባታ ላይ ሠርቷል. ኮሚኒስት ፓርቲን ተቀላቀለ። እሱ በደረጃው ከፍ ብሏል እና በ 1976 የፓርቲው የስቨርድሎቭስክ ክልል ኮሚቴ የመጀመሪያ ጸሐፊ ሆነ ። ዬልሲን በመጀመሪያ የሶቪየት መሪ ሚካሂል ጎርባቾቭ የፔሬስትሮይካ ማሻሻያ ደጋፊ ነበር። በኋላም ማሻሻያው በጣም መጠነኛ ነው በማለት ተችተው ወደ መድበለ ፓርቲ ተወካይ ዴሞክራሲ እንዲሸጋገር ጠይቀዋል። እ.ኤ.አ. በ 1987 ከፓርቲው አስተዳደር የፖሊት ቢሮ አባልነት የለቀቁ የመጀመሪያው ሰው ነበሩ ፣ ይህም ተወዳጅነቱን ፀረ-መመስረቻ ሰው አድርጎታል ። እ.ኤ.አ. በ 1990 የሩሲያ ጠቅላይ ሶቪየት ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ እና በ 1991 የሩሲያ ሶቪየት ፌደሬሽን ሶሻሊስት ሪፐብሊክ () ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ ። ዬልሲን ከተለያዩ የሩሲያ ብሔርተኛ ካልሆኑ መሪዎች ጋር ተባብሮ ነበር፣ እና በዚያው ዓመት በታህሳስ ወር የሶቪየት ኅብረት መደበኛ መፍረስ ላይ ትልቅ ሚና ነበረው። የሶቪየት ኅብረት ሲፈርስ፣ የራሺያ ፌዴሬሽን፣ ራሱን የቻለ መንግሥት ሆነ። በዚያ ሽግግር ዬልሲን በፕሬዚዳንትነት ቦታ ላይ ቆይቷል። በኋላም በ1996ቱ ምርጫ በድጋሚ ተመረጡ፣ ተቺዎችም ሰፊ ሙስና አለባቸው ሲሉ ነበር። ዬልሲን የኢኮኖሚ ድንጋጤ ሕክምናን፣ የሩብልን የገበያ ምንዛሪ መጠን፣ አገር አቀፍ የፕራይቬታይዜሽን እና የዋጋ ቁጥጥርን በማንሳት የሩሲያን የዕዝ ኢኮኖሚ ወደ ካፒታሊስት ገበያ ኢኮኖሚ ለውጦታል። ኢኮኖሚያዊ ተለዋዋጭነት እና የዋጋ ግሽበት ተፈጠረ. በኢኮኖሚው ሽግግር ወቅት ጥቂት የማይባሉ ኦሊጋርኮች አብዛኛውን የሀገሪቱን ንብረትና ሀብት ያገኙ ሲሆን ዓለም አቀፍ ሞኖፖሊዎች ገበያውን መቆጣጠር ጀመሩ። እ.ኤ.አ. በ 1993 ዬልሲን የሩሲያ ፓርላማ ሕገ-መንግሥታዊ ባልሆነ መልኩ እንዲፈርስ ካዘዘ በኋላ ሕገ መንግሥታዊ ቀውስ ተፈጠረ ። የየልሲን ታማኝ ወታደሮች ፓርላማውን ከገቡ በኋላ የትጥቅ አመጽ ካቆሙ በኋላ ቀውሱ አበቃ። ከዚያም የፕሬዚዳንቱን ሥልጣን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሰፋ አዲስ ሕገ መንግሥት አቀረበ። በሩሲያ ካውካሰስ ውስጥ የመገንጠል ስሜት ወደ መጀመሪያው የቼቼን ጦርነት፣ የዳግስታን ጦርነት እና ሁለተኛው የቼቼን ጦርነት ከ1994 እስከ 1999 አመራ። በአለም አቀፍ ደረጃ ይልሲን ከአውሮፓ ጋር አዲስ ትብብርን አበረታች እና ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ስምምነቶችን ተፈራረመ። ውስጣዊ ግፊት እየጨመረ በመምጣቱ እ.ኤ.አ. በ 1999 መጨረሻ ላይ ሥልጣናቸውን ለቀቁ እና በተመረጡት ምትክ ቭላድሚር ፑቲን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ከቢሮ ከወጡ በኋላ ዝቅተኛ መገለጫቸውን ይዘዋል እና በ 2007 ህይወታቸው ሲያልፍ መንግስታዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጽሟል ። ዬልሲን አከራካሪ ሰው ነበር። በአገር ውስጥ በ1980ዎቹ መጨረሻ እና በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ በፕሬዚዳንትነታቸው በፈጠሩት ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶች ዝናቸው ተጎድቶ የነበረ ቢሆንም፣ በሩሲያ ሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኝ ሥራውን ለቋል። ሶቭየት ኅብረትን በማፍረስ፣ ሩሲያን ወደ ተወካይ ዴሞክራሲ በማሸጋገር እና አዳዲስ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል ነፃነቶችን ለአገሪቷ በማስተዋወቅ ላበረከተው ሚና ምስጋናና ትችት ደረሰበት። በአንፃሩ በኢኮኖሚ አስተዳደር እጦት፣ ከፍተኛ የሆነ የእኩልነት እና የሙስና እድገትን በመቆጣጠር እና አንዳንዴም ሩሲያ እንደ ትልቅ የዓለም ኃያል ሀገር ያላትን አቋም በማሳጣት ተከሷል።
32412
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%93%E1%8D%96%E1%88%8C%E1%8B%8E%E1%8A%95%20%E1%89%A6%E1%8A%93%E1%8D%93%E1%88%AD%E1%89%B5
ናፖሌዎን ቦናፓርት
ናፖሌዎን ቦናፓርት (ፈረንሳይኛ፦ ) 1761-1813 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ አብዮት መጨረሻ አለቃና መሪ ነበሩ። ከ1796 እስከ 1807 ዓ.ም. ድረስ 1 ናፖሌዎን ተብለው የፈረንሳይ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ 1795 ናፖሊዮን ቦናፓርት የተባለ አንድ ወጣት ወታደር የቱሊሪስ ቤተ መንግስትን እየወረረ ያለውን የፓሪስ ህዝብ እንዲያስወግድ ታዘዘ። ናፖሊዮን ፣ ቀድሞውኑ በ 1795 ፣ ሙሉ ስራውን የሚገልፅ ምኞት እና ጨካኝነት ጥምረት ያሳያል ። ህዝቡ ወደ ቱሊሪስ እየገሰገሰ ሲሄድ ናፖሊዮን ዓይኑን ሳያንጸባርቅ ወታደሮቹን ወደ ህዝቡ እንዲተኩስ አዘዘ። ሕዝቡ በፍጥነት ተበታተነ; ይህ በዳይሬክተሩ ላይ ሊደርስ የሚችለው ስጋት፣ የወቅቱ የፈረንሳይ መንግስት፣ ተወግዷል። ይህ ሰው ከየት መጣ? የናፖሊዮን ቀደምት ወታደራዊ ድሎች በ1796–97 በነበሩት እጅግ አስደናቂ ወታደራዊ ድሎች ግን በጣም የታወቀ ነበር። በነዚያ ዓመታት ሁሉንም ሰሜናዊ ኢጣሊያ ድል በማድረግ ሀብስበርግ ግዛቶቻቸውን እንዲለቁ እና ኔዘርላንድንም እንዲቆጣጠሩ አስገደዳቸው። ወደ ግብፅ ወታደራዊ ጉዞ በማምራት በዚያ የሚገኘውን የብሪታንያ አቋም ለማዳከም ፈልጎ ነበር፣ ምንም እንኳን በግብፅ ያደረገው ዘመቻ እሱ ያሰበውን ውጤት ባያመጣም ተከታታይ አስደናቂ ወታደራዊ ድሎችን አስመዝግቧል። ይህ በፈረንሳይ ውስጥ በጣም ትልቅ ሽፋን ተሰጥቶታል. ይህ ወታደራዊ ጉዞ ብቻ አልነበረም; እያንዳንዷን እንቅስቃሴ የሚከታተል የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ አድርጎ አሁን የምናስበውን ነገር ወስዷል። መፈንቅለ መንግስት ናፖሊዮንን ወደ ስልጣን አመጣ እ.ኤ.አ. በህዳር 1799 የተወሰኑ የማውጫው አባላት የታደሰ አክራሪነት እና የንጉሳዊ አገዛዝን ተደጋጋሚ ስጋቶች ለመቋቋም የሚያስችል የተረጋጋ መንግስት እንዲመሰርቱ ለመርዳት ወደ ናፖሊዮን ዞሩ። የዳይሬክተሩ ሁለት አባላት ወደ ናፖሊዮን ቀርበው ደካማውን መንግስት ለመገልበጥ እና ለፈረንሳይ አዲስ መንገድ ለመቅረጽ የሚያስችል ጠንካራ አገዛዝ ለመመስረት ከሱ እና ከወንድሙ ሉዊስ ጋር አሴሩ ። ይህ መፈንቅለ መንግስት ህዳር 9 ቀን 1799 ተፈፀመ። የተቋቋመው አዲስ መንግስት ስልጣን በሶስት ቆንስላዎች እንዲካፈል ጥሪ አቅርቧል። ወደ አብዮቱ ወይም ወደ አሮጌው አገዛዝ የማይመለስ፣ ነገር ግን ቆንስላዎች ወደ ሮም ግዛት የሚመለሱ የቃላት አገባቦችን አስቀድመው አይተዋል። ሥልጣን በሦስትዮሽ ሊጋራ ነበር፣ እና ናፖሊዮን የመጀመሪያ ቆንስላ፣ ፣ በመጀመሪያ በእኩል ደረጃ መሆን ነበረበት። በዚህ ጊዜ ስለ እሱ ሁለት ነገሮች ቀድሞውኑ ግልጽ ነበሩ። አንደኛው ትልቅ ምኞቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ታላቅ ችሎታው ነበር። ይህንን ከሰራዊቱ ጋር ባደረገው ግንኙነት ማለትም በሰሜናዊ ጣሊያን ከሚገኙት ወታደሮቹ፣ ከግብፅ ወታደሮቹ ጋር ባደረገው ግንኙነት እና እንዲሁም ሁሉም ዓይነት ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከሰዎች ጋር በተገናኘ በተናጥል ከፍተኛ ውበት፣ ኃይል እና ሞገስ አሳይቷል። በዚህ ትሪምቪራይት ውስጥ ሁለቱን አጋሮቹን እና እንዲሁም የገዥው አካል የህግ አውጭ አካላትን በፍጥነት እንደሚያሸንፍ እንቆቅልሽ አልነበረም። የፈረንሳይ ኢምፓየር በጣም ታዋቂ ማርሻል የፈረንሣይ መሪዎች የአውሮፓ ታሪክ
1831
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%20%E1%88%AC%E1%8B%AD%E1%8A%95%20%E1%88%9C%E1%8A%A8%E1%88%AD%E1%88%B5
ኢትዮ ሬይን ሜከርስ
ኢትዮ ሬይን ሜከርስ () በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ ምንድነው? ኢትዮ ሬይን ሜከርስ ሃገራችንን አረንጓዴ ለማልበስ የተቋቋመ ቡድን ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። የውጭ መያያዣ የኢትዮ ሬይን ሜከርስ ድረገጽ (አማርኛ እና እንግሊዝኛ - የኢትዮጵያ ድርጅቶች