text
stringlengths
0
200
ዚብሔራዊ ባንክ ገዢው ማዕድናትን ወደ ውጭ ሀገር ይልኩ ዚነበሩ ኩባንያዎቜ ቜግር እንደገጠማ቞ውም በሪፖርታ቞ው አንስተዋል።
ትላልቅ ኩባንያዎቜ ዹተዘጉ ለገንደቢ ዚመሳሰሉትን በተመለኹተ ዚዚራሳ቞ው ምክንያት አላ቞ው።
እነዚህ ኩባንያዎቜ ያሉባ቞ውን ቜግሮቜ በዝርዝር መፈተሜ ማዚት ሰፊ ውይይት እና መግባባት ላይ መድሚስ ያስፈልጋል ብለዋል ዶ ር ይናገር።
ለመሆኑ ዚሀገሪቱ ዚማዕድን ዘርፍ ልማት ዚሀገሪቱን ኢኮኖሚ ኹማጠናኹር አንጻር ምን ፋይዳ ያለው ነው
ሰለሞን ሙጬ ያዘጋጀው ዚኢኮኖሚው ዓለም መሰናዷቜን ለእነዚህ ጥያቄዎቜ ምላሟቜን ይዟል።
ኚስልጣን ዚተወገዱትና በስደት ሳዉዲ አሚብያ ዚሚገኙት ዚቀድሞ ዚቱኒዝያ መሪ ዜን አብዲን ቀን አሊ ታመዉ ሆስፒታል መግባታ቞ዉ ተሰማ።
ኹፍተኛ ዹሆነ ስቃይ ደርሶብናል አቶ አግባው ሰጠኝ ይዘት ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚሰብዓዊ መብት ኮሚሜነር ዳንኀል በቀለ እንዳሉት ግን ዚሟ቟ቜ ቁጥር እስኚ ይደርሳል።
ለአንድ አመት ገደማ ጋብ ብሎ ዹነበሹው ግጭት እና ኹኚት ምግብ ቀቶቜ ሻይ ቀቶቜ እና ፋብሪካዎቜ ጭምር ዚጥቃት ሰለባ ሆነዋል።
ኚሚቡዕ እስኚ አርብ ለዘለቀው ኹኚት እና ለጠፋው ዹሰው ህይወት ተጠያቂው ማነው
ጠቅላይ ምኒስትሩ ዚሰጡት ማብራሪያ መንግሥታ቞ው አሊያም በመንግሥታ቞ው ውስጥ ያሉ ሹማምንት ኃላፊነት ስለመውሰዳ቞ው ያለው ነገር ዚለም።
ኚኢትዮጵያ ዚፖለቲካ ልሒቃን መቃቃር እዚተነሳ ሕዝብ እና አገር ዚሚያምሰው ልዩነት እናትን ልጅ አሳጥቷል።
ልጅን አባት ነጥቋል በርካቶቜን አንገት አስደፍቷል እንዲያም ሆኖ ልሒቃኑ በድርድር እና በውይይት መፍትሔ ለመሻት ተዘጋጅው እንደሁ ዹተሰማ ነገር ዚለም።
ይኾ ዚፖለቲካ እና ዚጞጥታ ቀውስ ዚበርካቶቜን ሕይወት ኹመቅጠፍ ባሻገር ማኅበራዊ እና ኀኮኖሚያዊ ዳፋ አስኚትሏል።
ባለፈው እሁድ በአማራ ክልል ሰሜን ሾዋ ዞን መርሐቀ቎ ወሚዳ ዚገምሹ በዹነ ዚግንባታ ኩባንያ ንብሚት ዹሆኑ ተሜኚርካሪዎቜ እና ቡልደዘሮቜ በእሳት ጋይተዋል።
አቶ አመንሲሳ ዳባ በግንባታ ኩባንያው ተቀጥሚው ኚአራት አመታት በላይ በመሐልሜዳ አካባቢ ሰርተዋል።
አቶ አመንሲሳ እንደሚሉት በዕለቱ እርሳ቞ው ኚሚሰሩባ቞ው ማሜኖቜ በተጚማሪ ያኚራይዋት ዚነበሚቜ ዹግል ተሜኚርካሪያ቞ው ጭምር ተቃጥሏል።
አቶ አመንሲሳ እንደሚሉት በተቃጠለው ቊታ ቢያንስ እስኚ ዚሚደርሱ ሰራተኞቜ ነበሩ።
ኹዕለተ እሁዱ ክስተት በኋላ አካባቢውን ለቀው ለመውጣት ተኹልክለው እንደነበር አቶ አመንሲሳም እና አቶ እንዳልካ቞ው ለዶይቌ ቬለ ተናግሚዋል።
ዚኩባንያው ባለቀት አቶ ገምሹ በዹነ ኹ ሚሊዮን ብር በላይ ዚሚገመት በቃጠሎው ጉዳት እንደደሚሰበት ለዶይቌ ቬለ አሚጋግጠዋል።
በመሐልሜዳ በተፈጾመው ጉዳይ ላይ ዚአማራ ክልል እስካሁን በይፋ ማብራሪያ አልሰጠም።
ዚኢትዮጵያ እና ዚአውሮጳ ህብሚት ዚስደተኞቜ ጉዳይ ድርድር ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
በሙስሊም ሃገራት ተቃውሞና ውግዘት ባለፈው ሳምንት ቀንጋዚ ሊቢያ ውስጥ ዚአሜሪካ አምባሰደርና አሜሪካውያን ሚዳቶቻ቞ው ኹተገደሉ ወዲህ ያህል ተጠርጣሪዎቜ ተይዘዋል።
ኹዚህ አንፃር ዓለም አቀፉ ዚግጭትና ዚቀዉስ ተንታኝ ቡድን ዚህብሚቱን ዉይይት እንዎት ይመለኹተዋል
በአስተዳደሩ ይፋ ዹተደሹገው ውሳኔ እውንነትም ያጠራጠራ቞ው አልጠፉም ቆይ ግን ፡ ዹምር ሞተርሳይክሎቜ ተኹለኹሉ
ብላ ትጠይቃለቜ ሙኒት መስፍን አበበ ያዳን ካኑማ ኹሰኔ በኋላ ይኹለኹላሉ አሁን ግን እዚተለማመዱት ነው ወይ እያሟሟቁ።
ዹሚል ምላሜ ሲሰጥ ዳዊት ፍቃዱ ደግሞ እንኳን ሞተር ቩይንግ አውሮፕላንም ተኚልክሏል።
ሲሉ አስናቀ ሞዋአሳዚ ደግሞ አሹ ሞተር ባይክ አያስፈልግም ግሩም ሥራ ነው።
አሉ ሚኪራ ሞርካታም ሕይወትም ማትሚፍ ነው በዹቀኑ እዚሞቱ አይደም እንዎ ሞተሚኞቹ
ዘካሪያስ ኪሩብ ደግሞ እንዲህ አሉ ምንም ነገር ስንወስን ጥቅም እና ጉዳት አለው ዋናው ግን ዚቱ ነው አመዛኙ ሚለው ነው።
እውነት ነው በአግባቡ ሚሠሩ አሉ ግን ለጥቂቶቜ ተብሎ ሚሊዹን ህዝብ በሞተር መሰቃዚቱ ነው ሚሻለው
ሞተር ካለው ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ በዝቶዋል በተለይም አደጋው ወጣት እዚጚሚሰ ነው ስለዚህም ውሳኔው ትክክል ነው።
ዹሞተር ባይስክል ኚመጪው ሰኔ ቀን ዓም ጀምሮ በአዲስ አበባ ላይ መታገድን በአዎንታዊነት ዚደገፉት እንዳሉ ሁሉ ዹተቃወሙም አልጠፉም።
ውስን ወንጀለኛን መቆጣጠር ባለመቻል ብዙሃን ለፍቶ አዳሪን ማሾማቀቅ ተገቢ አይመስለኝም።
ማሙሜ አኹለው በበኩላ቞ው እንዲህ ብለዋል ይሄ ነገር በጣም አደጋ አለው።
በትንሹ ኹ ሺህ በላይ ዹሚሆኑ ሞተር ሳይክሎቜ ይሄንን ሥራዬ ብሎ ዚዕለት ጉርሱን ዚሚያገኝ እና ልጆቹንም ዚሚያስተምር አለ።
ሌላው ነገር ኹቀበሌ ተበርዶ ዹገዛ አለ ሎቶቜ እህቶቻቜን አሚብ ሀገር ሠርተው ዹገዙ አሉ።
ቁድወቲ ሙሀመድ በበኩላ቞ው ዚማይመስል ወሬ ሌብነትን ለማጥፋት ሳይሆን ሌብነትን ማደራጀት መሆኑ መታወቅ አለበት።
ብር ዹቀን ገቢ አለኝ ይህ ገቢ ሲቀርብኝ ገብቌ ዹምተኛ ይመስልሀል
ይብላኝ ለሚያወሩት እነ ታኚለ ብቻ ተውት ውስጡ ሌላ ዕቅድ አለ ጠርጥር ጠርጥር ጠርጥር አሁንም ጠርጥር።
መቅደስ ታደሰ በበኩላ቞ው በአግባቡ ዚሚተዳደሩበት ሞልተዋል ግን በምን ይለዩ ወዳጄ ዚሕጋዊዎቹንም ሞተር ተኚራይተው እኮ ነው መውጫ መግቢያ ዚሚያሳጡን።
በትዊተር አስተያዚታ቞ውን ካስነበቡት መካኚል ደግሞ አጥናፍ ብርሃኔ ደግሞ በሞተሹኛ ላክልኝ ሕይወት ያቀል ነበር።
ሲል በፍቃዱ ዘሃይሉ ደግሞ ዚአዲስ አበባ አስተዳደር ቀውሱን ኚመጥፎ ወደ ክፉ እዚለወጠው ይሆን
ሞተር ባይስልክን ማገዱ በርካታ ራሳ቞ውን በራሳ቞ው ዚሚያስተዳድሩት ሰዎቜን ሥራአጥ ማድሚግ ነው።
ይህ ደግሞ ምናልባት ለወንጀል እና ለተቃውሞዎቜ አስተዋፅኊ ሊኖሹው ይቜላል።
ካምፓላ ዩጋንዳ ውስጥ ሺህ ቊዳ ቊዳ ዹሚሏቾው ዹሞተር ሳይክሎቜ ትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣሉ።
ሥራአጥ ለሚበዛባት አፍሪቃ ዚሥራ ዕድል ሆኖ ሳለ ክልኹላው ዚአስተዳደሩ ደካማነት ነው።
በዚህ አመንክዮም ዚሚጎዳ እንቅስቃሎን ለመግታት ሁሉንም ነገር ማገድ ሊመጣ ነው ማለት ነው።
ኀሊያም መሠሚት በፌስቡክ ዹሰጠው አስተያዚት ደግሞ እንዲህ ይነበባል ዚታይላንድ ሞተሚኞቜ
በታይላንድ ሞተሚኞቜ እንዲህ ጎላ ተደርጎ ዹተፃፈ ልዩ ዚመለያ ቁጥር ይሰጣ቞ዋል።
ኹዛ ውጪ በኚተሞቜ ይህን መለያ ሳያደርግ ቢዝነስ መስራት ይኚለኚላል።
በሞተር ዹሚፈፀም ወንጀል ያስ቞ገራ቞ው ሌሎቜ ሀገራት ያስፈፀሙት ሌላው አማራጭ ደግሞ ሞተሚኞቜ ሰው እንዳይጭኑ መኹልኹል ነው።
ያው በአንድ ሰው ብቻም ወንጀል ሊፈፀም ይቜላል ይህ ግን ተደራጅተው ድርጊቱን ዚሚፈፅሙትን ለመቀነስ ያግዛል።
በሳምንቱ መጀመሪያ ያሚፈው ዹ ዓመቱ ደራሲ በብዕር ስሙ ይጜፍ እንደነበር ዚገለፁት አስተያዚት ሰጪዎቜ በዚሁ በማኅበራዊ መገናኛው ለቀብሩም ሲጠራሩ ታይቷል።
ስትል ፍሬው አበበ ደግሞ ደራሲ ሕሩይ ሚናስ አውግቾው ተሹፈ ዜና ዕሚፍት አሳዝኖኛል።
ነገርግን ሥራውን ጠልቶት እርግፍ አድርጎ በመተው ብሔራዊ ቲያትር አካባቢ ሜዳ ላይ ዚመጜሐፍ ቜርቻሮ ንግድ ላይ መገኘቱ በወቅቱ ብዙዎቻቜንን አስገርሞን ነበር፡፡
ዚማንበብ ፍላጎቮን ካሳደጉት ወዳጆቌ መካኚል አውግቾው ተብሎ በብዕር ስም ዚሚጠራው ወዳጄ ነው።
አንድም ቀን በብር እጊት ማንበብ እንዳላቆም ዚሚዳኝ መልካም ሰው ነው።
ያንገት ጌጡ ኚምትለው ዚአጫጭር ልቊለዶቜ መድብል ውስጥ ዚተካተቱትን ያንገት ጌጡ ዹገና ስጊታ እና እቃ ቀት ጠባቂው ን አብዝቌ እወዳ቞ዋለሁ፡፡
ኩኩኩኩ ኢትዮጵያ ዛሬ አንድ ዚጥበብ ባለውለታዋን ሰው አጥታለቜ ።
ዮናስ መስፍን ወይ አዲስ አበባ ዹተሰኘውን መጜሐፉን ዚመጀመሪያ ደሹጃ ተማሪ ሳለሁ አንብቀው ነበር።
እያስመዘገብኩ ነው ዹሚለው ድርሰቱም ወደ ራዲዮ ድራማ ተቀይሮ በግሩም አተዋወን በጋሜ ፍቃዱ ተክለማርያም ቀርቩ እንደነበር አስታውሳለሁ።
ጌዲኊ ጀባቲም ይቜ ሀገር ትልልቅ ሰዎቿን እዚሞኘቜ ነው ማነው ዹነገ ሰው
ሌላው በዚህ ሳምንት ዚብዙዎቜ ጥያቄ ዹሆነው ደግሞ አቶ ለማ መገርሣ ዚት ገቡ
በአደባባይ ኚታዩ ሰነበቱ በሚል ጥቂት ዚማይባሉ ወገኖቜ ፎቷ቞ውን በመለጠፍ አሹ ዚትና቞ው
አላዲን አላዊ ሲዲቂ በፌስቡክ ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሜ ተላላ ዚሞተልሜ ቀርቶ ዚገደለሜ በላ።
ስለ ድርጅቱ ፓርቲው አያገባንም እንድያገባንም አይፈልጉም ዚሳ቞ው ጉዳይ ግን ያሳስበናል።
ብለዋል ታሬ ቶክቻው ፀጋዬም ዜጎቜ ዹዚህ አይነት ጥያቄ ሲያነሱ መልስ መስጠት ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ።
በኢትዮጵያ ወላጅ አልባ ዚሆኑት ህፃናት ኹመላው ህዝብ ቁጥር አምስት በመቶ ያህል ይሆናሉ።
ኢትዮጵያ ዚደምቢዶሎ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ጉዳይ ቄለም ወለጋ ዞን ዚዶምቢዶሎ ዩኒቚርሲቲ መሆናቾው ዹተገለጾ ተማሪዎቜ መታገታ቞ው እዚተነገሚ ነው።
ዩኒቚርሲቲው መሹጃው እንደደሚሰው እና ጉዳዩ ለሚመለኚታ቞ው ዚፀጥታ እና ዚትምህርት ዘርፍ አካላት ማሳወቁን ለዶቌ ቬለ ገልጿል።
ዚሳይንስ እና ዹኹፍተኛ ትምህርት ሚኒስ቎ርም ጉዳዩን እዚተኚታተልኩ ነው ብሏል።
ኚታገቱት አብዛኞቹ ሎት ተማሪዎቜ ናቾው ታገቱ ዚተባለው ዚደምቢዶሎ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ቁጥር በውል ዚታወቀ አይመስልም።
ቁጥራ቞ውን በርኚት ያደሚገው ወገን ታግተዋል ኹሚላቾው ተማሪዎቜ አብዛኛው ደግሞ ሎት ተማሪዎቜ መሆናቾውን ያመለክታል።
ጉዳዩን ለማጣራት ያነጋገርና቞ው ዚደምቢዶሎ ዩኒቚርሲቲ ፕሬዝደንት ዶክተር ለታ ተስፋዬ ድርጊቱ ዹተፈፀመው በዩኒቚርሲቲው አካባቢ ባለመሆኑ መሹጃው እንደማንኛውም ወገን እንደደሚሳ቞ው ነው ዚገለፁልን።
እሳ቞ው እንደሚሉት በዩኒቚርሲቲው በተፈጠሹ አለመሚጋጋት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጉዟቾውን በጋምቀላ መስመር ያደሚጉ ተማሪዎቜ አሉ።
በዩኒቚርሲቲው ዹመማር ማስተማሩን ሂደት ያደናቀፈ ዹተደጋገመ ሚብሻ ተኚስቶ እንደነበር ባለፈው ሳምንትም ተመሳሳይ ቜግር እንደነበርም ዚዩኒቚርሲቲው ፕሬዝደንት ገልጞዋል።
ሆኖም ኚተማሪዎቹ ጋር በመነጋገር ትምህርት ለመጀመር ኚስምምነት መደሚሱንም አመልክተዋል።
ዚደምቢዶሎ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ለእገታ ተዳርገዋል ዹሚለው መሹጃ እንደደሚሰው ያመለኚተው እና ጉዳዩን በቅርበት እዚተኚታተለ እንደሚገኝ ዚሳይንስ እና ዹኹፍተኛ ትምህርት ሚኒስ቎ር ገልጿል።
ፌስቡክን ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያዋሉ ወጣቶቜ ፌስ ቡክን ዚመሳሰሉ ማህበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ ሰዎቜን በማቀራሚብና ፈጣን መሹጃ በመለዋወጥ ሚገድ አስተዋፅኊ ያደርጋሉ።
ኢትዮጵያ ዉስጥም ማሕበራዊ መገኛ ዘዎዎቜ ዚሚያስኚትሉት ጠብና መለያዚት እዚተስፋፋ ዚመጣ ይመስላል ።
ወጣት ገላውዎዎስ ብሩክና ናኩል ጌታ቞ው በሃያዎቹ መጀመሪያ ዹሚገኙ ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ዹ ኛ ዓመት ተማሪዎቜ ና቞ው።
ወጣት ገላውዎዎስ ብሩክ ዚጋዜጠኝነትና ዚኮሚኒኬሜን ወጣት ናኩል ደግሞ ዚፈሚንሳይኛ ሥነ ፅሁፍ ተማሪዎቜ ና቞ው።
ወጣቶቹ በተለያዩ ዚትምህርት ክፍልና ዚትምህርት መስክ ላይ ቢሆኑም ዚሚጋሩት ተመሳሳይ ዓላማና ፍላጎት አላ቞ው።
እናም በዩኒቚርስቲዉ በሚኹናወኑ ዹበጎ ፈቃድ አገልግሎቶቜ ላይ መሳተፍ ያዘወትራሉ።
ወጣቶቹ በተገናኙ ቁጥር ዚሚወያዩባ቞ዉ እና ዹሚኹነክናቾዉ በርካታ ቜግሮቜ ነበሩ።
እናም አውጥተው አውርደው ዚወጣትነትና ዚተማሪነት አቅማቾው ዹሚፈቅደውን ለማድሚግ ወሰኑ።
ዚዩኒቚርሲቲዉ ዹ ኛ ዓመት ተማሪ ኹሆነዉ ጓደኛቾው ሙአዝ ጀማል ጋር በመሆንም በቜግሩ ላይ ጥናት ለማድሚግ ተስማሙ።
ጓደኛሞቹ በተለያዩ ዩኒቚርሲቲዎቜና በአንዳንድ ዚመንግስት ተቋማት መጠይቆቜን በመበተን ባሳሰቧ቞ዉ መሚጃዎቜ ላይም መለስተኛ ጥናት አደሚጉ።
ዚዩንቚርሲቲ ተማሪ ሆኖ እያለ ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎቜ ሆኖ እያለ ለምንድነው ወጣቱ በተለያዩ ልዩነቶቜ ዚሚጋጚዉ።
ኹሌላ ዩኒቚርስቲ ነው ዚሚኮሚጆው መመሚቂያ ጜሑፍን ጚምሮ አሳይመንት ተማሪው አይሰራም።
እንደምታዚው አብዛኛው ጊዜ ለዚህ ነገር ተጠቂ ዚሚሆኑት ተማሪዎቜ ና቞ው።
በጥናቱ ውጀት መሰሚትም በወጣቶቜ መካኚል ተቀራርቊ መነጋገር እና መወያዚት ለቜግሩ መፍትሄ ይሆናል ዹሚል ሀሳብ ያዙ።
ይህንን ሃሳባ቞ዉንም በዩኒቚርሲቲዉ ለሚቀርቧቾዉ ጓደኞቻ቞ዉ እና ዓላማቾዉን ይደግፋሉ ላሏቾዉ ለዩኒቚርሲቲዉ ማህበሚሰብ አባላት አቀሚቡ።
በዉይይቱ ማብቂያ ስድስት ኪሎ ኢን቎ሌክቿል ሶሳይቲ በሚል ስም ዹበጎ አድራጎት ክበብ መሰሚቱ።
ወጣቶቹ እንሰራዋለን ላሉት ዹበጎ አድራጎት ስራ ድጋፍ ለማሰባሰብ በመጀመሪያ ዚመሚጡትም ዚማህበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜን በተለይም ፌስቡክን ነበር።
በዚህም በርካታ ዓላማቾዉን ዹሚደግፉ ሰዎቜ ማፍራታ቞ዉን ወጣት ገላዉዲዮስ ይገልፃል።
ዚማህበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜን በመጠቀም ያገኟ቞ዉን ዹዓላማ ተጋሪዎቻ቞ዉን በመያዝም ዚመጀመሪያ ዹበጎ አድራጎት ስራ቞ዉን ጀመሩት ዹ ተኚታታይ ቀናት ዘመቻዎቜን በማድሚግ ነበር።
እነ ገላውዲዩስ ኚአንድ ዓመት በፊት ሶስቱ ሆነዉ ዚመሰሚቱት ክበብ አሁን በርካታ ደጋፊዎቜና በዚሁለት ሳምንቱ እዚተገናኙ ዚሚመክሩ ቋሚ አባላት አሉት።
አባላቱ በዩኒቚርሲቲዉ በትምህርት ላይ ያሉና ገሚሶቹ ደግሞ ተመርቀዉ በስራ ላይ ተሰማርተዉ ዹሚገኙ ና቞ዉ።