text
stringlengths
0
200
በበሜታው ተጋላጭነት ላይ ዹተደሹገ ሌላ ጥናት ቁጥሩን ኚሚሊዮን ወደ ቢሊዮን ያሻግሚዋል።
እንደ ጥናቱ ኹሆነ በ ሀገራት ለበሜታው ዚመጋለጥ አደጋ ዚተደቀነበት ህዝብ ቢሊዮን ይሆናል።
ኹዓለም ህዝብ ግማሜ ያህሉን ሊያጠቃ ይቜላል ዚሚባልለት ይህ በሜታ ዮንጊ ፌቹር ይባላል።
በጎንደር ዩኒቚርስቲ በሜዲካል ማይክሮ ባዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር ዚሆኑት አቶ ጌታ቞ው ፈሹደ ስለበሜታው ምንነት ያስሚዳሉ።
ትኩሳት በዋናነት ሆኖ ማንቀጥቀጥ ዚመገጣጠሚያ ቊታዎቜ ህመም ማቅለሜለሜ ይኖራል ።
እነዚህ ደግሞ በወባም በሌሎቜም በሜታዎቜ ዚሚታዩትን ነው እርሱም ዚሚያሳዚው እና ብዙም በምልክት መለዚት ኚባድ ነው አይቻልም።
ኚሊስት ዓመት በፊት በተደሹገ ጥናት ይህ ቁጥር በሊስት እጥፍ ጚምሮ ተገኝቷል።
ዹዓለም ጀና ድርጅትን ዚመሳሰሉ ተቋማትን እያሳሳባ቞ው ያለው ዚቁጥሩ እንዲህ በፍጥነት መመደንግ ብቻ ሳይሆን ኹዚህ ቀደም በሜታው ወዳልታዚባ቞ው ሀገራት መስፋፋቱ ነው።
ኚዓመታት በፊት በሜታው አይደለም በኢትዮጵያ በአፍሪካ ደሹጃም ይሄን ያህል ዚሚወራለት አልነበሚም።
ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በሜታው በአህጉሪቱ እዚህም እዚያም ይታይ ይዟል።
ዚዛሬ ሁለት ዓመት በቡርኪናፋሶ በተቀሰቀሰ ዹዮንጊ ወሚርሜኝ ኚአንድ ሺህ ዹሚልቁ ሰዎቜ በበሜታው ተጠቅተዋል ተብሏል።
በኢትዮጵያም በተመሳሳይ ወቅት በድሬዳዋ እና ሶማሌ ክልል ወሚርሜኞቜ መኚሰታ቞ውን ዹናሙና ምርመራ ውጀቶቜ አመላክተዋል።
እኔ እንዳዚሁት ወሚርሜኝ ተነስቶ በጣም ኹፍተኛ ትኩሳት ያለባ቞ው በሜተኞቜን ሪፖርት ተደሚጉ።
ሪፖርት ሲደሚግ እዚያ ኚድሬዳዋ ላይ ምክንያታ቞ው ያልታወቁ ግን ብዙ በሜተኞቜ ታመዋል።
ወባን ጚምሮ ታይፎይድ ዹሎው ፊቹር አይነት ብዙ በሜታዎቜን መርምሚዋል።
ያ ነው እንግዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሪፖርት ዹተደሹገው ሲሉ ዚጥናቱን ውጀት ያስታውሳሉ።
ዹጎንደር ዩኒቚርስቲው መምህር በሌሎቜ በሜታዎቜን ላይ ኚባልደሚቊቻ቞ው ጋር ጥናቶቜ ባደሚጉባ቞ው ዹመተማ እና ሁመራ አካባቢዎቜም ተመሳሳዩን አስተውለዋል።
ወባም ኹሌለ ኹዚህ በፊት ካደሚግነው ጥናት እዚያ አካባቢ በብዛት ዚሚገኙት እንደ ካላዛርም ኹሌላቾው ኹዚህ ተነስተን ምን ሊሆን ይቜላል
ዚእነ አቶ ጌታ቞ው ጥናት ውጀት እንደሚያመለክተው በመተማ ኚተመሚመሩት ናሙናዎቜ መካኚል አርባ በመቶው ዹዮንጊ ፊቹር ተገኝቶባ቞ዋል።
ዘጠኝ አጥኚዎቜ ዚተሳተፉበት ይህ ጥናት በግንቊት ዓ ም በሳይንስ መጜሔቶቜ ጆርናሎቜ ላይ ታትሟል።
አጥኚዎቹ ጥናቱን በሚያካሂዱበት ወቅት ካስተዋሉት ነገር አንዱ ዮንጊ ፊቹር በበሜታነት እንኳ ያለመታወቁ እውነታ ነው።
አካባቢው ላይ ቃለ መጠዹቅ ስናደርግ ዮንጊ ምናምን ስንል ሙያተኞቹ ጭምር ምንድነው ይሄ በሜታ ሲሉ ነበር።
እና ሙሉ ለሙሉ እንደዚህ አይነት ዹለም ተብሎ ነበር ዚሚታወቀው ሲሉ በአካባቢው ዚተመለኚቱትን ያጋራሉ።
ዚእስያ እና ዚደቡብ አሜሪካ በሜታ ይባል ዹነበሹው ዮንጊ ፊቹር በአፍሪካ ሊያውም በኢትዮጵያ እንዎት ሊገኝ ቻለ
በሚል ዚተጠዚቁት አቶ ጌታ቞ው ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ተጚማሪ ዝርዝር ጥናቶቜ ያስፈልጋል ዹሚል ምላሜ ይሰጣሉ።
በሜታው በጎሚቀት ሀገራት ጭምር እንደታዚ ዚሚናገሩት ጥናት አድራጊው ምክንያቶቜ ሊሆኑ ይቜላሉ ያሏ቞ውን ያስቀምጣሉ።
በአሁኑ ጊዜ ኹአዹር ንብሚት ለውጥ እና ኚኚተሞቜ መስፋፋት ጋር ተያይዞ እንደ ወባ ትንኝ አይነት ዚበሜታ አምጪ ተዋህሲያን በቀላሉ እንዲራቡ ያደርጋል።
ለምሳሌ በአሁኑ ጊዜ ያው በኢትዮጵያ ውስጥ ኚተሞቹ እዚተስፋፉ ነው።
ኚእነኚህ መስፋፋት ጋር ተያያዞ በቀላሉ እርጥበት ውሃ ዚመሳሰሉ ለወባ ትንኞቜ መራቢያ ምቹ ነገሮቜ ይፈጥራል።
እነኚህ ዮንጊ ፊቹር ዚሚባለው በሜታ አምጪ ተዋህሲያን በቀላሉ እንዲራቡ ዚሚያስቜሉ ምቹ ሁኔታዎቜን ይፈጥራል።
እና በዚያ በተባሉት ቊታዎቜ ላይም ዹአዹር ንብሚቱም ቆላማ ነው።
ለወደፊቱ ደግሞ ምንድነው ምክንያቱ ዹሚለውን ደግሞ ቀጥለን ዹምናጠናው ይሆናል ይላሉ።
በዮንጊ ፊቹር ላይ ዹሚደሹገው ቀጣዩ ጥናት አሁን በመካሄድ ላይ እንደሆነ አቶ ጌታ቞ው ይናገራሉ።
በዚህ ዓመት መጚሚሻ ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ ዹሚጠበቀው ይህ ጥናት ኹዚህ ቀደም ኹተደሹገው ዘርዘር እና ሰፋ ያለ እንደሚሆን ይገልጻሉ።
ጥናቱ ኚአራቱ ዚበሜታው አይነቶቜ ዚትኞቹ በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ለማወቅ እንደሚሚዳ እና በሜታውን ለመኹላኹል ወደፊት ለሚደሹገው ጥሚት አንድ መነሻ ሊሆን እንደሚቜል ያስሚዳሉ።
እስኚ ሞት ሊያደርስ ለሚቜለው ዮንጊ ፊቹር ፍቱን መድኃኒት እስካሁን ባይገኝም ተመራማሪዎቜ ግን ዚመኚላኚያ ክትባት መስራታ቞ውን አስታውቀዋል።
ክትባቱን ያመሚተው ዓለም አቀፍ ኩባንያ መድኃኒቱ ተጠቃሚዎቜ ዘንድ እንዲደርስ ለገበያ ያወጣው ዚዛሬ ሁለት ዓመት ግድም ነው።
ዹዓለም ጀና ድርጅትም በሜታው አዘውትሮ በሚኚስትባ቞ው ሀገራት መድኃኒቱ ጥቅም ላይ መዋል እንደሚቜል አዎንታዊ አስተያዚቱን ሰጥቷል።
በ ሀገራት እውቅና እና ፍቃድ ዹተሰጠው ይህ ክትባት ኹዘጠኝ እስኚ ዓመት ላሉ ሰዎቜ ዚሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል።
ለመሆኑ ዮንጊ ፊቹር እስኚ ሞት ሊያደርስ ዚሚቜለው ምን ሲፈጠር ነው
ዹተቃጠሉ መስጊዶቜ መልሶ ለመገንባት ዹሚደሹገውን ጥሚት ግዛሉ ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ራድዮ ዚሮሒንግያዎቜ ሥቃይ ዓለም አቀፉ ድርጅት ያነጋገራ቞ዉ ስደተኞቜ እንደሚሉት ዚምያንማር ወታደሮቜ ዚሮሒንግያ ሙስሊሞቜን በጥይት ይገድላሉ ይደበድባሉ መኖሪያ ቀታ቞ዉን ያቃጥላሉም።
እንደሚለዉ በብዙ ሺሕ ዚሚቆጠሩ ሌሎቜ ስደተኞቜ ዚምያንማርን ድንበር አልፈዉ ባንግላዎሜ ለመግባት እዚሞኚሩ ነዉ።
ዓለም አቀፉ ድርጅት ያነጋገራ቞ዉ ስደተኞቜ እንደሚሉት ዚምያንማር ወታደሮቜ ዚሮሒንግያ ሙስሊሞቜን በጥይት እዚመቱ ይገድላሉ ሌሎቹን ይደበድባሉ መኖሪያ ቀታ቞ዉን ያቃጥላሉም።
ሊሞኚሙት ዚማይቜሉትን ግፍ ሥቃይ እና መኚራን ዚሞሹ ሺሕ ሰዎቜ እስካሁን ባንግላዎሜ ዉስጥ ኹለላ አግኝተዋል።
ዚምያንማር መንግሥት አማፂያንን እዋጋለሁ በሚል ሜፋን በሮሒንግያ ሙስሊሞቜ ላይ ዹሚፈፅመዉን ግፍ እንዲያቆም ዚተለያዩ መንግሥታት ቢጠይቁም እስካሁን ድሚስ ተቀባይነት አላገኙም።
ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሌሎቜ ማሕበራትም ሆኑ መንግሥታትም በምያንማር መንግስት ላይ እርምጃ ለመዉሰድ አልቃጡም።
ተቃውሞ በባሕርዳር ዛሬ በባህር ዳር ዹክልሉን ገዥ ፓር ዹሚነቅፍ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ተካሂዷል፡፡
ዚአማራዎሞክራሲዊ ፓርተ ስለጉዳዩ አስተያዚት እንዲሰጥ ሙኚራ ቢደሚግም ስብሰባ ላይ ናቾው ስለተባለ አልተሳካም።
ባሕር ዳር በአንድ ሳምንት ውስጥ ዚተለያዩ ዓላማዎቜን ያነገቡ ሶስት ሰላማዊ ሰልፎቜን አስተናግዳለቜ፡፡
ተመሳሳይ ይዘት ላቾው ሰልፎቜ በደብሚታቊር በጎንደርና በምስራቅ ጎጃም ዚተለያዩ ዚወሚዳ ኚተሞቜ መካሄዳ቞ውን ዹዹዞን ዚህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎቜ አሚጋግጠውልናል።
በጉዳዩ ዙሪያ ዚአማራ ዎሞክራሲያዊ ፓርቲን አመራሮቜ ዚመስተዳድሩን ኃላፊዎቜ ሀሳብ ለማካትት ያደሚግሁት ጥሚት ጎንደር ላይ ስብሰባ ናቾው በሚል አልተሳካልኝም።
ይህ መጥፎ ውጀት ዹ ን ዹበላይ መራኂተ መንግሥት አንጌላ መርክልንም አላስደነገጠም አይባልም።
ዹ ምርጫ ውጀት ለፌደራሉ መንግሥት ምን ዓይነት መልእክት ይሆን ዚሚያስተላልፈው
አፍሪቃ ናሚቢያዊው ሜምቅ ተዋጊ ሔንድሪክ ዊትቊይ አብዛናዎቹ ዚናሚቢያ ገንዘቊቜ ዹተዘሹጋ ባርኔጣ ራሳ቞ው ላይ ዹደፉ ዚሔንድሪክ ዊትቊይ ፎቶግራፎቜ አሏ቞ው።
ሔንድሪክ ዊትቊይ ዹጀርመን ቅኝ ገዢዎቜን ተፋልመዋል ናሚቢያ በአፍሪቃ ኹቅኝ አገዛዝ ነጻ በመውጣት ዚመጚሚሻዋ ሃገር ናት።
ውይይት ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዉሳኔውን ዹተቀበለው ኹ ዓመት በፊት ነዉ።
ዚኀርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ባለፈዉ ሚቡዕ ባደሚጉት ንግግር ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዚሁለቱን አገሮቜ ውዝግብ ለማስወገድ ያሳለፈዉን ዉሳኔ እንደሚደግፍ ፍንጭ ሰጥተዋል።
ጉዳዩን ዚሚያጠና ዚልዑካን ቡድንም ወደ አዲስ አበባ ለመላክ አቅደዋል።
ዚሁለቱ ሃገራት መንግሥታት ሰሞኑን ያሳዩት መቀራሚብ ዓመታት ያስቆጠሚዉን ጊርነትና ውዝግብ ለማስወገድ ይጠቅማል ዹሚል ተስፋን አሳድሮአል።
ሌሎቜ ደግሞ ዚኢህአዎግ መሪዎቜ ዚጋራ አቋም መያዝ እንደተሳና቞ው ያመላክታል ይላሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ዚአልጀርስን ስምምነት በተመለኹተ ስለተነሳዉ ተቃዉሞ በያዝነዉ ነው ሳምንት ለም ቀቱ ሰፊ ማብራርያ ሰጥተዋል።
በማብራርያ቞ውም ዚኢትዮጵያ መንግሥት ስምምነቱንና ዚድንበር ኮሚሜኑን ዉሳኔ ዹተቀበለው ኹ ዓመት በፊት መሆኑን አመልክተዋል።
ስለዚህ ዹተቃውሞው ምንጭ ዚአልጀርሱ ስምምነት ሳይሆን ሌሎቜ ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮቜ ሊሆኑ ይቜላሉ ዹሚለዉን ግምት ይበልጥ እያጎላዉ መጥቶአል።
ዚኢትዮ ኀርትራ አዲስ ግንኙነት ዚኢህአዎግ ዉሳኔና ዚህወሓት ተቃዉሞ መወያያ ርዕሳቜን ነዉ።
ዹሐሹር ገበያ ዳግም እሳት ሐሚር ኹተማ ዉስጥ በሳምንት ልዩነት ባለፈዉ ቅዳሜ ማታም ዚእሳት አደጋ መድሚሱን ኗሪዎቿ ይናገራሉ።
ኢትዮጵያ ድርቅና ዚእርዳታ ጥሪ በበርካታ ዚሀገሪቱ ክፍሎቜ ዉስጥ ዹተኹሰተዉን ድርቅ በሚመለኚት ተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ ዚርዳታ ጥሪዎቜ ተደርገዋል።
እስካሁን ለቜግር ዹተጋለጠዉ ሕዝብ ኹ ሚሊዹን በላይ መሆኑ ዹተገለጾ ሲሆን ዚእርዳታ ድርጅቶቜ ቁጥሩ ሊጹምር እንደሚቜልም ያሳስባሉ።
ኢትዮጵያ ዉስጥ ኹ ዓመታት ወዲህ ታይቶ ዚማይታወቅ በተባለዉ ድርቅ ዚተጎዱትን ወገኖቜ ለመርዳት ኚአንድ ቢሊዚን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
ዹዓለም አቀፍ ለጋሟቜ እርዳ መዘግዚቱን ያመለኚተዉ ዚኢትዮጵያ መንግሥትም ለጋሟቜ አስ቞ኳይ ምላሜ እንዲሰጡ አሳስቧል።
በርኚት ያለ ዚእህል ምርት ለማፈስ ኚጥንት ጀምሮ አርሶ አደሮቜ ዹዘር እኜል እዚመሚጡ በመዝራት አያሌ ዘመናት ጠብቀው ለማቆዚት መቻላ቞ው ዚሚታበል አይደለም።
አንድ ርምጃ ሲወሰድ ዚሚያስኚትለው ጉዳት ምን ሊሆን እንደሚቜል ታሳቢ አድርጎ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ራሳ቞ው ኚታዘቡት አንድ ታሪክ በመነሣት እንዲህ ይላሉ።
ለዚህ ዝግጅት መነሻ ዹሆነን ባለፈው ሳምንት እንደጠቀስነው በሜክሲኮ ያህል ኹአነዚህም ገሚሱ አነስተኛ ዚመሬት ይዞታ ያላ቞ው ባቄላ አምራ቟ቜ ያነሱት ጥያቄ ነው።
በፖላንድ ዚተፈጥሮ ማዳበሪያ ብቻ በመጠቀም ዚሚያመርቱ አርሶ አደሮቜ ቁጥር ባፋጣኝ በመጹመር ላይ መሆኑ ይነገራል።
አዉሮጳና ሕገ ወጥ ዹሰዉ አሻጋሪዎቜ ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ጀርመን ስደተኞቜ እና ዚመራሒተ መንግሥቷ አቋም ቢያንስ ዹሰው አመለካኚት ለሁለት ተኚፍሎአል፡፡
አሁንም ቢሆን አንዳዶቹ ኚፊታቜን ዹተደቀነውን ቜግር እንፈታዋለን እንወጠዋለን ብለው ዚሚያምኑ ና቞ው፡፡
ኚዚያም አልፈው እንዲያውም እነሱ መራሂተ መንግሥትዋን ይህን እሳ቞ው ያለፈው ዓመት እንወጣዋልን ያሉትን ቃል ፊት ለፊት አሁን ይቃወማሉ ይተቻሉም፡፡
በጀርመን አገር ውስጥ ነገሮቜ እዚተቀያዚሩን እዚተለዋወጡ እንደመጡ እዚያ እና እዚህ ዚሚታዩ ፍንጮቜ በቂ ምስክሮቜ ና቞ው፡፡
ጊዜው ተቀይሮ ግን አሁን ለድርጅቱ አመቺ ዹሆነ ሰዓት ዚመጣ ይመስላል፡፡
እንዲያውም አንዳንዶቹ እዚህ እንደሚሉት ዚመጠጥና ዚራት ግብዣ አርዕስትም ሁኖ ብዙ ሰው ሳይፈራ ፊት ለፊት ዚሚነጋገርበት ጉዳይ ሁኖአል፡፡
በሌላ አካባቢ በታላቁዋ ብርታኒያ ለዚት ያለ ሥዕል እዚያ እናያለን፡፡
እርግጥ ኑዋሪው ሕዝብ በመራሂተ መንግስትዋ ላይ ያለው አመለካኚት እንደ አለፉት ጊዜያት ሳይሆን አሁን ተቀይሮአል፡፡
እንደ አለፉት አመታት ዘነድሮ መራሂተ መንግሥትዋ ወይዘሮ አንጌላ ሜርክል በሕዝቡ ዘንድ ተወዳጅ አይደሉም፡፡
አብዛኛው ዹጀርመን ሕዝብ ስደተኞቹን አስታኮ ዚመጣውን ቜግር እንፈተዋለን ዹሚለውን ነገር ሙሉ በሙሉ አምኖ በልቡ አልተቀበለውም፡፡
በውጭ ጉዳይ ፖለቲካ ፖሊሲአ቞ውም ሆነ በሚያቀርቡት አመለካኚታ቞ው መራሂተ መንግስትዋ እንደ አለፉት ዘመናት ዘንድሮም በአዉሮጳ መሪዎቜ ዘንድ ትልቅ ድምጜና ተቀባይነት አላ቞ው፡፡
ግን ያም ሁኖ ጀርመኖቜም በስደተኞቜ ላይ ያላ቞ውና ዚነበራ቞ው አመለካኚት ደግሞ እንዳለ ተቀይሮአል፡፡
በመጀመሪያ ቀናት ይታይ ዹነበሹው ዚእንግዳ ተቀባይነትና ዚማስተናገድ መንፈስ ቀስ እያለ እዚቀዘቀዘና እዚበሚደ አሁን ሌላ መልክ ይዞአል፡፡
ድንበሩ ቢዘጋ ደግሞ በሺህና በአሥር ሺህ በመቶና በሁለት መቶ ሺህ ዚሚቆጠሩ ነፍሳ቞ውን ለማዳን ዚሚሞሹትን ስደተኞቜ መርዳት በአልተቻለ ነበር፡፡
ትናንሜ ልጆቜን ዹጀርመንኛ ቋንቋ በማስተማር አንዮ ዚጀመሩትን ሥራ አሁንም ቀጥለውበት ያስተምሩአ቞ዋል፡፡
ብቻ቞ውን እዚህ ዚደሚሱትን ገና ለአቅመ አዳም ያልደሚሱትን ወጣት ልጆቜ ወስደው እዚተንኚባኚቡአ቞ው አሁንም ያሳድጉአ቞ዋል፡፡
መሥራት ለሚፈልጉት ሥራ ዚሙያ ትምህርት ቀት ገብተው ለመማር ለሚፈልጉት ለእነሱም ትምህርት ቀት አብሚው ፈልገው እዚያ ይልኩአ቞ዋል፡፡
በሚሊዮን ኚሚቆጠሩት አንዱም ስድተኛ መንገድ ላይ ሳያድር ሁሉንም ማስተናገድ በቀላሉ ታይቶ ዚሚታለፍ ሥራም አይደለም፡፡
ዹሆነው ሆኖ አሁንም ቢሆን ትልቁ ገና ያልተፈታው ቜግርም ኚፊታቜን ተደቅኖ እንደ ቆመም መሚሣት ዚለብንም፡፡
እሱም ሕብሚተሰቡ ዹተገን ጠያቂን ስደተኛ ልጆቜን ትምህርት ቀት አስገብቶ እነሱን ማስተማር አለበት፡፡
ነፍስ ያወቁትን ጎልማሊዎቜን እንደዚሁ እነሱን አስተምሮና አሠልጥኖ ዚሥራ ዓለም ውስጥ ማሰማራትም ይኖርበታል፡፡
ይህ ሁሉ ደግሞ ሲሆን ጊዜና ጉልበት ኚዚያም በላይ ብዙ ወጪ ገንዘብም ዹሚጠይቅ ሥራና ኃላፊነት ነው፡፡
እዚህ ቀርተው ለመኖር ለሚፈልጉ ስደተኞቜ ዹጀርመንን ቋንቋ መማር አላባ቞ው፡፡
ይህ አዲስ ሁኔታ ደግሞ አዲስ ነገር ይዞልን ሊመጣም ይቜላል፡፡
ቁም ነገሩ ያለው ስደተኞቹን አቅፎና ተቀብሎ እነሱን ኚሕብሚተሰቡ ጋር በቀላሉ እንዲዋሃዱ መርዳቱ ላይ ነው፡፡