text
stringlengths
0
200
እንደ ሚመስለኝ አንዱ ጄኔራል ሥልጣኑን ኚኢሳያስ ዚመዉሚስ እድሉ ሰፊ ነዉ።
ዚመብት ተሟጋቜ ሜሮን እስጢፋኖስ በበኩሏ ኀርትራዉያን ለሐገር ነፃነት ታግለናል ትላለቜ።
ይሁን እንጂ በእነኝህ ዓመታት አልፎ አልፎ በታጠቁ ቡድኖቜ ሲያጋጥማ቞ው ኹነበሹው ዚኚብት ዘሹፋ በስተቀር ዚግብርና ሥራ቞ውን በሰላም ሲያኚናውኑ መቆዚታ቞ውን ያስታውሳሉ፡፡
ሆኖም ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ ባልተለመደ መልኩ በታጠቁ ቡድኖቜ ዹሚፈጾሙ ዚግድያና ዹዘሹፋ ተግባራት እዚተባባሱ በመምጣ቞ው አካባቢውን ጥለው መውጣታ቞ውን ገልጞዋል፡፡
አሁን ዚሚታዚውን መፈናቀል ለማስቆምና በቀጣይ መደሹግ ያለበትን ሁኔታ ለመገምገም ኚተለያዩ አካላት ዚተውጣጣ ቡድንም ወደ አካባቢው መንቀሳቀሱን አመልክተዋል፡፡
በደቡብ ክልል ዚሰፈራ ፕሮግራም በተካሄደባ቞ው ዚቀንቜ ማጂና ዹኹፋ ዞኖቜ በሠፋሪ አርሶአደሮቜ ላይ ዹመፈናቀል አደጋ ሲያጋጥም ዹአሁኑ መጀመሪያው አይደለም፡፡
ባለፈው ዓመት በነበሹው ዝቅተኛ ዝናብ ዚተነሳ ኹዞኑ ነዋሪዎቜ ገሚሱ አስ቞ኳይ ርዳታ ዚሚያሻው ነው ተብሏል።
ዚቜግሩን መነሻ ባለፈው ዓመት በአካባቢው በቂ ዝናብ በለመኖሩ ድርቅ በመኚሰቱ እንደሆነ አቶ መልካሙ አብራርተዋል፡፡
አንድ ዹዝቋላ ወሚዳ አርሶአደር በበኩላ቞ው ቜግሩ አሳሳቢና አፋጣኝ መፍትሔ ዚሚሻ ነው ነው ያሉት፡፡
ዚምግብ እርዳታው በፍጥነት ወደ አካባቢው ካልደሚሰ ኹፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ እንደሚፈጠር አቶ መልክሙ ስጋታ቞ውን አስቀምተዋል፡፡
ዚዋግኜምራ ብሔሚሰብ ዞን አስተዳደር ዝናብ አጠር ኹሆኑ ዚአማራ ክልል አካባቢዎቜ አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያ ጠ ሚ ዐቢይ አህመድ ዹዓለም ዹሰላም ኖቀል አሾነፉ ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ዚዘንድሮውን ዹዓለም ዹሰላም ኖቀል አሞነፉ።
ጠ ሚ ዐቢይ ለዚህ ዚበቁት በዋናነት ሃያ ዓመታት በዘለቀው ዚኢትዮጵያና ኀርትራ ዚድንበር ውዝግብ ሰላም እንዲወርድ ላበሚኚቱት አስተዋጜኊ መኟኑ ተገልጿል።
ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ዚዘንድሮውን ዹዓለም ዹሰላም ኖቀል አሞነፉ።
በሱዳን ወታደራዊ ኃይሉን ኚተቃዋሚዎቜ ጋር ማስማማታ቞ውም ሜልማቱን እንዲያሞንፉ ሚድቷ቞ዋል ነው ዚተባለው።
አብይ አህመድ ኛው ዹዓለም ዹሰላም ኖቀል ተሾላሚ ሲሆኑ ዚአሜሪካን ዶላርም ይበሚኚትላ቞ዋል።
አፍሪቃ ጀርመን በዘር ማጥፋት ተኚሰሰቜ ሁለት ዚናሚቢያ ጎሳዎቜ ዹዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጜማለቜ ዚሚሏት ጀርመን ላይ በኒው ዮርክ ክስ መስርተዋል።
ጀርመን በዘር ማጥፋት ተኚሰሰቜ ዚታሪክ ታዛቢዎቜ ዹ ኛው ክ ዘ ዚመጀመሪያው ዹዘር ማጥፋት ወንጀል ይሉታል።
ወደ ዚሔሬሮ እና ናማ ጎሳ አባላት በዛሬዋ ናሚቢያ ኚጎርጎሮሳዊው እስኚ ዓ ም ባሉት ዓመታት በጀርመን ቅኝ ገዢዎቜ እጅ ማለቃቾው ይታመናል።
በጊዜው ዚዛሬዋ ናሚቢያ ዹጀርመን ደቡብ ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ ዚምትጠራ ቅኝ ግዛት ነበሚቜ።
በ ዓ ም በቅኝ ገዚዎቻ቞ው ላይ ለተቃውሞ ዚወጡት ዚሔሬሮ እና ዹናማ ጎሳዎቜ በጀርመን ወታደሮቜ ወደ በሹሐ ተባሚሩ።
በቅኝ ገዢዎቹ እርምጃ በመቶ ዚሔሬሮ ጎሳ አባላት እንዲሁም ኹናማ ጎሳ ግማሜ ያክሉ አለቁ።
ይኾ ሁሉ ግን ለበርካታ አመታት ለአውሮጳም ሆነ ለአፍሪቃ ተዘንግቶ ዹቆዹ ዹሰቆቃ ታሪክ ነው።
ወንጀሉ ዚተፈፀመባ቞ዉ ዚሁለቱ ዚናሚቢያ ጎሳዎቜ ተወካዮቜ ካሳ ሊኹፈለን ይገባል በማለት ሲሟገቱ አመታት አስቆጥሚዋል።
አሁን ክስ ዚመሰሚቱት ዚፖለቲካዉ ሙግት ዉጀት አላመጣ ስላለ ይመስላል።
ዚድርድሩን ሒደት አጥብቀው ኚሚተቹት መካኚል አንዷ ዚሆኑት ዚሔሬሮ ጎሳ ተወካይ ኀስተር ሙይንጃንጉዌ ለእኛ ሒደቱ በሕፀጜ ዹተሞላ ነው።
በጉዳዩ ላይ ዚሚደራደሩት ወገኖቜ ሁለቱ ልዩ ልዑኮቜ እንዲሆኑ ዹወሰነው ማን ነው
ኚጎርጎሮሳዊው ዓ ም ዹተፈጾመውን ጭፍጹፋ ጀርመን ዘር ማጥፋት ተብሎ መጠራቱን ባትክድም ካሳ ለመክፈል ግን ስታንገራግር ቆይታለቜ።
ፍርድ ቀቱ ለበርካታ ዓመታት ሲንኚባለል ዹቆዹውን ጉዳይ ለመዳኘት ሥልጣኑ እንዳለው ገና አልታወቀም።
ማንኛውም ፍርድ ቀት ዚቀሚበለትን ክስ ዚመዳኘት ሥልጣን እንዳለው ይመሚምራል።
መመርመር ብቻም ሳይሆን ጉዳዩ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ሕጋዊ መሰሚት መኖሩንም ያጀናል።
አንድ ዹጀርመን ፖለቲኚኞቜ በበኩላ቞ው አገራ቞ው ጉዳዩን ዚያዘቜበት መንገድ ተገቢ አይደለም ሲሉ ይተቻሉ።
ይፋዊ በሆነ መልኩ ዘር ማጥፋት ነው ብሎ መቀበሉ በርግጥም አንዳቜ እርምጃ ነው።
ሆኖም ግን ሁልጊዜም ኚሔሬሮ እና ኚናማዎቜ ጋር ዚቀጥታ ድርድር ማድሚግ እንደሚገባ቞ው ሲናገሩ አይደመጥም።
ዛሬ ሥልጠናው ይፋ በተደሚገበት መርሐ ግብር እንደተገለጞው በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ስልጠናዎቜ በሁሉም ዚአገሪቱ ክፍሎቜ ይሰጣሉ።
አዲስ አበባ ዹሚገኘው ዚአሜሪካ ኀምባሲ እና ጆን ሖፕኪንስ ዩኒቚርሲቲ በምርጫ ላይ ያተኮሚ ሥልጠና መስጠት ጀመሩ።
ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ በአገሪቱ ፖለቲኚኞቜ ዘንድ ዛሬም ድሚስ ዹክርክር መነሟ ዹሆነው አገራዊ ምርጫ ነሐሮ ቀን ዓ ም እንዲካሔድ ወስኗል።
ቊርዱ ይፋ ባደሚገው ዹጊዜ ሰሌዳ መሰሚት ኚሚያዝያ እስኚ ግንቊት ቀን ዓ ም ድሚስ ዚመራጮቜ ምዝገባ ይኚናወናል።
ኚግንቊት እስኚ ግንቊት ባሉት ቀናት ደግሞ ዚእጩዎቜ ምዝገባ ይካሔዳል።
ነሐሮ ቀን ዚሚካሔደው ምርጫ ውጀት ኹነሐሮ እስኚ ጳጉሜ ባሉት ቀናት ይፋ ይደሚጋል።
ዚዶይቌ ቬለው ጌታ቞ው ተድላ ሥልጠናው ምን ይፈይዳል ሲል መርሐ ግብሩ ይፋ ሲደሚግ ዹተገኙ አንድ ተሳታፊ ጠይቋል።
አባቶቻቜን ጥለዉልን ያለፉትን ዚታሪክ አሻራ እኛ ልጆቻ቞ዉ ታሪኩን በሞያቜን እናስተላፍ ብለን ነዉ።
ዚሟ቟ቜ ቁጥር በኢጣልያ ኹ ሺህ በላይ በስፓኝ አስር ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰላሳ አምስት በአሜሪካን ሺህ በፈሚንሳይ ደግሞ ሺህ ደርሶአል።
በዓለማቜን በኮሮና ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ዛሬ እኩለ ቀን ላይ በወጣ ዘገባ መሠሚት አንድ ሚሊዮን ሺህ ሶስት መቶ ሰማንያ ስድስት ደርሷል።
አንድ አራተኛው በአሜሪካን ሌሎቹ ደግሞ በተቀሹው ዓለም ነው ያሉት።
በኮሮና ምክንያት ኹዓለም ህዝብ ግማሹ ማለትም ኹ ቢሊዮን በላይ ዹሚሆነው በ ሃገራት ኚቀቱ እንዲሰራ ተገዷል።
ሜርክል ሐኪማ቞ው ተህዋሲው እንዳለባ቞ው ኚታወቀ በኋላ ሊስት ጊዜ ምርመራ ተደርጎላቾው በሊስቱም ምርመራ ኚተህዋሲው ነጻ መሆናቾው ተሚጋግጧል።
ስደተኞቹና ለስደተኞቹ መብት እንኚራኚራለን ዹሚሉ ወገኖቜ እንደሚሉት ለስደተኞቹ ይሰጥ ዹነበሹዉ ዚምግብ ርዳታዉ ኹተቋሹጠ ሁለት ወር አለፈዉ።
ሚዥም ጊዜ ዹፈጀው ዚሁለቱ ሲኖዶሶቜ ዕርቀ ሰላም ውይይት በመጚሚሻ ለፍፃሜ በቃ።
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ኚእንግዲህ አንድ ሲኖድስ ብቻ እንዳላትም ተገለጞ።
በእርቀ ሰላሙ መግለጫ ላይ ዚተገኙት ዶ ር ዐብይ አህመድ ዛሬ በኢትዮጵያውያን ላይ ተገንብቶ ዹቆዹው ዚጥላቻ ግንብ ተናደ ብለዋል።
ዹውጭ ጉዳይ ሚንሥ቎ር መሥሪያ ቀት በቃል አቀባዩ ነቢያት ጌታ቞ው አሰግድ አማካኝነት ዛሬ በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮቜ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።
አውሮጳ ጀርመን ዚአውሮጳ ህብሚት እና ዚስደተኞቜ ጉዳይ ዚእሁዱ ጉባኀ ለጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል እጅግ አስፈላጊ ነበር።
ዚአውሮጳ ህብሚት ዚስደተኞቜ መርህ ዚአውሮጳ ህብሚት በስደተኞቜ ጉዳይ ላይ በአባል ሀገራት መካኚል ዹተፈጠሹውን ልዩነት ለማጥበብ እዚጣሚ ነው።
በዚህ ሳምንት ሐሙስ ብራሰልስ ቀልጅዚም ዚሚካሄደው ዚአባል ሀገራት መሪዎቜ ጉባኀ ኚሚነጋገርባ቞ው ጉዳዮቜ አንዱ እና ዋነኛው ይኜው ዚስደተኞቜ ጉዳይ ነው።
ኹዚህ ጉባኀ አስቀድሞ አባል ሀገራት ባለፈው እሁድ አስ቞ኳይ ስብሰባ አካሂደዋል።
ዚኮታ ስርዓቱን ዚተቃወሙት በተለይ ሀንጋሪ ፖላንድ ቌክ ሪፐብሊክ ስሎቫክያን ዚመሳሰሉ ሀገራት እስካሁንም በዚሁ አቋማቾው እንደጞኑ ነው።
አሁን ደግሞ ኢጣልያ እና ማልታን ዚመሳሰሉ ሀገራት በፈንታ቞ው ዚጀልባ ስደተኞቜ አናስገባም ማለት ጀምሚዋል።
ዚአውሮጳ ህብሚት በወቅቱ ሁለቱም ሀገራት ዚሰዎቜን ህይወት ለመታደግ ቅድሚያ እንዲሰጡ ቢጠይቅም ጥሪው ሰሚ አላገኘም ነበር።
ቜግሩ ግን በስተመጚሚሻ ስፓኝ ስደተኞቹን ለማስገባት ፈቃደኛ በመሆንዋ ተፈቷል።
እነዚህ እና ሌሎቜንም ዚህብሚቱን አባል ሀገራት ዚማያስማሟ቞ው ጉዳዮቜ በመካኚላ቞ው ያለውን ልዩነት እያሰፋ ሄዷል።
ይህ መነሻ ሆኖም ዚፊታቜን ሐሙስ እና አርብ ኚሚካሄደው ዚአባል ሀገራት ዚመሪዎቜ ጉባኀ አስቀድሞ ባለፈው እሁድ አነስተኛ ጉባኀ ተካሂዷል።
ሁላቜንም ህገ ወጥ ስደትን ለመቀነስ ድንበሮቻቜንን ለመጠበቅ እንደምንፈልግ ተስማምተናል።
አንዳንዱ ዚመጀመሪያው ዚስደት ጉዳይ ተጋላጭ ሌሎቜ ደግሞ በሁለተኛ ደሹጃ ዚቜግሩ ተጋሪ መሆን ዚለባ቞ውም።
በማይቻልበት ጊዜ ደግሞ ፈቃደኛ ዚሆኑትን በአንድ ላይ አሰባስበን ዚጋራ ዚድጋፍ ማዕቀፍ እንፈልጋለን።
ዚእሁዱ ጉባኀ ለጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል እጅግ አስፈላጊ ነበር።
ሜርክል ቜግሩ በአጠቃላይ በአውሮጳ አቀፍ ደሹጃ መፈታት አለበት ዹሚል አቋም ነው ያላ቞ው።
እንደ ሜርክል አውሮጳ አቀፍ ዚስደተኞቜ ፖሊሲ ሲነደፍ ነው ዹጀርመንም ቜግር ዚሚወገደው።
እናም አባል ሀገራት በሙሉ ዚሚስማሙበትን ዚጋራ ዚስደተኞቜ መርህ ማምጣት እንዳልተቻለ በእሁዱ ጉባኀ ላይ መግባባት ላይ ተደርሷል።
ኚእሁዱ ጉባኀ አስቀድሞ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ሜርክልና ዚፈሚንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኀል ማክሮም በርሊን ውስጥ በጉዳዩ ላይ መክሹው ነበር።
ማክሮ ሥልጣን እንደያዙ ያቀሚቡትን ዚጋራ ዚስደተኞቜ ማዕኹል ዹማቋቋም ሀሳብ በዚሁ ወቅት አንስተው ነበር።
ሃይማኖት እንደምትለው ዚአውሮጳ ህብሚት አባል ሀገራት መንግሥታት ኹሀገር ውስጥ ዚሚደርሱባ቞ው ዚተለያዩ ተጜእኖዎቜ አቋማቾውን እንዲቀያይሩ ምክንያት እዚሆኑም ነው።
ዚአውሮጳ ህብሚትን ለሁለት ዹኹፈለ ዚሚመስለው ዚህብሚቱ ዚስደተኞቜ መርህ በወደፊቱ ጉዞው ላይ ተጜእኖ እያሳደሚ መሆኑ በግልጜ እዚታዚ ነው።
ያም ሆኖ በገበያው እምነት ዚህብሚቱን አንድነት ያፈርሳል ዹሚል ስጋት ዹለም ።
ቁጥራ቞ው እና ዜግነታ቞ው በውል ያልታወቁት ቀሪ ስደተኞቜም አስክሬን እንዲሁ ባለፈው ሳምንት መጚሚሻ ዹ ያህሉ መሰብሰቡ ተዘግቩ ነበር።
ዚሞሮኮ ባህር ኃይልም እንዲሁ ወደ ስፔን በጀልባ በጉዞ ላይ ዚነበሩ ስደተኞቜን መታደጉን ገልጿል።
እንደ ዚተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኹሆነ ባለፉት ሰባት ወራት ዹሚጠጉ ስደተኞቜን በሜዲትራንያን ባህር በኩል አድርገው ወደ አውሮፓ ገብተዋል።
ምናልባትም ስደተኞቹ ሌሎቜ ዹገጠማቾውን እጣ ፈንታ አገናዝበው ኹጉዞ ተቆጥበው ይሆናል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአሁኗ ሰዓት በአሁኗ ደቂቃ እጃ቞ው በህገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎቜ ስር ያሉ ስደተኞቜ አሉ።
ታጋ቟ቹ እንደሚሉት ናስማህ በተባለው ቊታ ኚአመት በላይ ዚታገቱ ሰዎቜ አሉ።
ቢሳካላ቞ው ሁሉም ወደ አውሮፓ በባህር ለመሰደድ ነበር አላማቾው ።
በአንድ ሊቢያዊ ታግተናል ኚሚሉት መካኚል አንዷ ዚሆነቜው ኢትዮጵያዊት ያለቜበትን ሁኔታ እንዲህ ገልጻልናለቜ።
ኹዚህም ሌላ በዚህ ዓመት ብቻ ኹ በላይ ሰዎቜን ወደ አውሮፓ እና ሌሎቜ ደህንነት ዚሚያገኙበት ቊታ ኚተለያዩ ዚስደተኞቜ ማቆያ ለማስወጣት ቜለናል።
ዹአለም አቀፉ ማህበሚሰብ በህጋዊ መንገድ ስደተኞቹ ሊቢያን ዚሚለቁበትን መንገድ እንዲተባበሚን እዚጠዚቅንም እንገኛለን።
ያም ሆኖ ታሪክ አርጋዝ እንደሚሉት በአሁኑ ሰዓት ዹሚጠጉ ስደተኞቜ በሊቢያ ዚተለያዩ ዚስደተኛ ማቆያዎቜ ይገኛሉ።
ይህ ቀደም ሲል ያነጋገርና቞ውን በህገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎቜ በዚቀቱ ታግተው ዚሚገኙትን ሰዎቜ ሳይጚምር ነው።
ታሪክ አርጋዝ እነዚህን ታግተው ዹሚገኙ ስደተኞቜ ለመርዳት ስልጣን ዹለውም ይላሉ።
ይህ ዚሊቢያ ባለስልጣናት ኃላፊነት ነው ምክንያቱም ሰብዓዊ አገልግሎት ዚሚሰጥ ድርጅት ነው።
ዚአንድ ሀገር ፀጥታ እና ዚህብሚተሰቡ ደህንነት ማስጠበቅ ዚሀገሪቱ ባለስልጣናት ሀላፊነት ነው።
ዚዶናልድ ያማማቶ ሹመት ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚአፍሪቃውያንን ቜግር በአፍሪቃውያን መፍታት ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚድርቁ መዘዝ በተለይ በአርብቶ አደሮቜ ኑሮ ላይ ጫና አሳርፏል።
እንቊጭ ዹተሰኘው አሹም በጣና ሐይቅ ላይ ዹደቀነው ስጋትም ሌላኛው ርእሳቜን ነው።
ጣና ሐይቅ እምቊጭ በተሰኘ መጀ አሹም ዚመወሚሩ ዜና በርካቶቜን አሳስቧል።
ኚኢትዮጵያ ተኚታታይ ዚ቎ሌቪዥን ድራማዎቜ መካኚል አንዱ ዚኟነው ዘመን ድራማ ባልደሚቊቜ በምሥራቅ ኢትዮጵያ ሶማሌ ለቀሚጻ ወጥተው እንግልት እንደደሚሰባ቞ው በዚሁ መድሚክ ገልጞዋል።
ዚድራማው ሠሪዎቜ ዚአካባቢው ፖሊስ በስህተት ላደሚሰባ቞ው እንግልት ይቅርታ እንደጠዚቃ቞ው በፌስቡክ ገጻ቞ዉ ተናግሚዋል።
ዹለም ሌላ ተልዕኮ ነበራ቞ው ሲል በዛው በፌስቡክ ላይ ዚጻፈም አለ።
ዚድራማ ቀሚጻው አባላት ስለ ስደተኞቜ ለመቅሚጜ በሄዱበት ሥፍራ አጋጠመን ስላሉት እንግልት ሲገልጹ፥
አባላቱ ለተለዹ ተልዕኮ በሥፍራው መኚሰታ቞ውን በመግለጥ ዚሚኚስ ጜሑፍም በዛው በማኅበራዊ መገናኛ አውታር ተነቧል።
ዹ ዘመን ድራማ ቀሚጻ ወብርሃን መሪ ታሪኩ ደሳለኝ በወቅቱ ስለገጠማ቞ው በፌስቡክ ገጹ በዝርዝር ጜፏል።