text
stringlengths
0
200
ዚታሪኩ ጜሑፍ ዘለግ ያለ ቢሆንም በአካባቢው ደሚሰብን ያሉትን በዝርዝር በዐይነ ኅሊና ዚሚያሳይ ነው።
ኚዚያም አንድ ግቢ ውስጥ አስገቡን ያለው ታሪኩ ኹኔታውን ያብራራል።
ግቢ ውስጥ እንደገባን ኚመኪናው ላይ እዚጉተቱ ካወሚዱን በኋላ ዚያዝነውን ዕቃ ፊት ለፊት እንድናስቀምጥ ካደሚጉን በኋላ በዚተራ እያስቆሙ እያመናጚቁ ፈተሹን።
ወንዶቜን ለብቻ ሎቶቜንም ለብቻ ካደሚጉን በኋላ ዚመጡት ወታደሮቜ ሁሉ ኹ ጊዜ በላይ ቆጠሩን።
ወደ ፊታቜን ሁለት ሰዎቜ መተው ቆሙ አንደኛው ዚእጅ ሜጉጥ ዚያዘ ሲሆን ሁለተኛው ሜመል ይዟል።
ባለመሣሪያው ዚአካባቢው ዚፀጥታ ክፍል ኃላፊ ሲሆን ባለሜመሉ ዚፖሊስ ኮሚሜን ነው።
ሁለቱ ሰዎቜ ወደኛ እንደቀሚቡ ወታደሮቹም ዙሪያቜንን ኹበው እጃ቞ውን ዚመሣሪያ቞ው መላጭ ላይ አደሹጉ በማለት ይቀጥላል ዚታሪኩ ጜሑፍ።
ወደ አካባቢው ዘመን ድራማን ለመሥራት ሲሄዱም ለ ኛ ጊዜያ቞ው እንደነበር ጜፏል።
ምክንያቱም ይላል ታሪኩ ምክንያቱም ጠቅላይ ሚኒስ቎ር ኃ ማሪያም ደሳለኝ ስለነበሩ ነው።
እኛም ኹጠቅላይ ሚኒስ቎ሩ ካሉበት ኬ ሜ እርቀት ላይ ነበርን።
ዳሩ መንግሥት ዚመንግስት ብቻ እንደሆነ ህዝብም ህዝብ እንደሆነ በአንድ ሀገር ሳንተያይ መኖር ኹጀምርን አመት አልፎናል ሲልም ጜሑፉን አጠቃሏል።
ዚዳዊት ጜሑፍፊ ዹዘመን ድራማ ፕሮዲውሰሮቜ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ለምን ቜግር ገጠማቾው
ዚቡድኑ አባላት ወደ ክልሉ ለቀሚጻ ዚገቡት ኹክልሉ መንግሥት እውቅና ውጪ በድብቅ ነው ብሏል ዳዊት።
ዳዊት ኚአካባቢው ዚጞጥታ ኃላፊ አገኘሁት ባለው መሹጃ ዹ ዘመን ድራማ ፕሮዲውሰሮቜ ውጭ ኹሚገኝ ድርጅት ጋር ግንኙነት አድርገዋል ይላል።
ዳዊት በጜሑፉ ማጠቃለያ ላይ ባሰፈሚው ዐሹፍተ ነገር ግን ኹላይ ዹገለጠውን ዚራሱን ክስ ዹሚቃሹን ጜሑፍ ጜፏል።
ሳያስፈቅዱ ለቀሚጻ መግባታ቞ው ብቻውን ኚጥርጣሬ በዘለለ ዹውጭ ኃይል ተባባሪ ናቾው ብሎ ለመደምደም አያበቃም በሚል።
ድርቅ ዚሚያጠቃው ዚሜንሌ ዞን ኹፊል ገጜታ ዹ ዘመን ድራማ ደራሲ መስፍን ጌታ቞ው ለዳዊት አጭር መልእክት በፌስቡክ አስፍሯል።
ስህተት በመሠራቱም በአግባቡ ይቅርታ ተጠይቀን ነው ዹተለቀቅነው ይላል መስፍን አክሎም ኹዛ በኋላም እስካሁን ድሚስ ሥራቜንን በስፍራው እዚሠራን እንገኛለን ብሏል።
ሜንሌ ኚድሬዳዋ በ ኪ ሜ ሜትር ርቀት ላይ ዚምትገኝ ኹተማ ነቜ።
ሁሌም ቢሆን ለእውነት ዋጋ መስጠት ትልቅነት ነው ሲል አጠቃሏል።
ይኜ በ ዘመን ድራማ ሠራተኞቜ ላይ ደሹሰ ዚተባለውን እንግልት ዹሚገልጾዉን መሹጃ በርካቶቜ በማኅበራዊ መገናኛ አውታሮቜ ተቀባብለውታል።
ጣና ሐይቅ ካለፉት አራት እና አምስት ዓመታት አንስቶ በመጀ አሹም ዚመወሚሩ ዜና በርካቶቜን አስደንግጧል።
አሹሙ በአፋጣኝ ካልተወገደ በዓባይ ምንጭነቱ ዚሚታወቀው ዚጣና ሐይቅን ሊያደርቀው ይቜላል ተብሏል።
ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ዶይ቞ ቬለ ኚዘገበበት በኋላ ዹበለጠ ትኩሚት ሊያገኝ እንደቻለ አንዳንድ አድማጮቻቜን ገልጠውልናል።
ዚሀገራቜን ህዝብ ተቆርቋሪነቱን በተለያዚ ማኅበራዊ ድሚ ገፅ እዚገለፀ ይገኛል በማለት ይጀምርና መፍትኄ ዹሚለውንም ሐሳብ አስፍሯል።
ጣናን ዹወሹሹው እምቊጭ ዹተሰኘው መጀ አሹም በኔ አስተሳሰብ ይህን አሹም ለማጥፋት ዹክልሉ መንግሥት ኹአቅሙ በላይ ዹሚሆን አይመስለኝም።
አሹሙን ለማጥፋት ይሚዳል በሚል ዚመፍትኄ ሐሳብ ዹሰጠን ሌላው ዚፌስቡክ ተኚታታያቜን ዚዑራኀል ልጅ ነኝ ዹሚል ዚፌስቡክ መጠሪያ አለው።
እንዲህ ይላል፩ ይህን አሹም ለማጥፋት እንደ ሌሎቜ አገራዊ ጉዳዮቜ በቮሌ በኩል ገንዘብ ዚሚሠበሠብበት መንገድ ቢመቻቜ መልካም ነዉ።
ይሄነው ላቀው በበኩሉፊ ጣናን ሐይቅ ፌደራሉ መንግሥት አይመለኹተውም እንዎ
ሕዳሎ ግድብ መለመኛ ሆኗል በጣናም ይለመና ሲል ጣና ሐይቅ እንደ ሕዳሎው ግድብ በመንግሥት በኩል ትኩሚት አልተሰጠዉም ዹሚል አስተያዚቱን ሰጥቷል።
ኧሹ ያገሬ ሕዝብ እንነሳ እንነጋገርበት ሌላ ሀገር አለን ወይ
ጣና ኹሌለ ባሕር ዳር እሚባል ነገር ተሚት ይሆናል ብሏል።
ታደሰ ወልደአብ በአጭር አሹፍተ ነገር ያሰፈሚው መልእክቱፊ ይህን ያኜል ጊዜ ለምን ዝም ተባለ
ገበሬዎቜ በሐይቁ ዙሪያ እምቊጭ ዚተባለውን አሹም ሲነቅሉ ዚሚያሳዩ ፎቶዎቜም በማኅበራዊ መገናኛ አውታሮቜ ይገኛሉ።
ኚፎቶዉ ጋር አሹሙን ለማጥፋት አስ቞ኳይ መፍትኄ እንደሚያሻው ዹሚጠቁሙ መልእክቶቜም ይነበባሉ።
ስፖርት ስፖርት መጋቢት ቀን ዓ ም ዚኢትዮጵያ ሎቶቜ ብሔራዊ ዚእግር ኳስ ቡድን ለጃፓኑ ዹኩሎምፒክ ውድድር ለመሳተፍ በድል ጎዳና እዚገሰገሱ ነው።
ዩጋንዳን በደርሶ መልስ ለ ዚሚቱት ሉሲዎቹ ኚምዕራብ አፍሪቃዊቷ ካሜሩን ጠንካራ ተፎካካሪዎቜ ጋር ይፋለማሉ።
ሣምንታዊ ዚስፖርት ዘገባ ዚኢትዮጵያ ሎቶቜ ብሔራዊ ዚእግር ኳስ ቡድን ለጃፓኑ ዹኩሎምፒክ ውድድር ለመሳተፍ በድል ጎዳና እዚገሰገሱ ነው።
ዚእንግሊዙ ማን቞ስተር ሲቲ በኀፍ ኀ ካፕ ድሉ ማግስት ለሻምፒዮንስ ሊግ ወሳኝ ፍልሚያ ራሱን እያዘጋጀ ነው።
በፕሬሚዚር ሊጉ ዋነኛ ተፎካካሪው ሊቹርፑልም ነገ ምሜት በተመሳሳይ ሰአት ለሻምፒዮንስ ሊግ ሩብ ፍጻሜ ወሳኝ ጚዋታውን ያኚናውናል።
በጁጂትሱ ዚትግል ስፖርት ኢትዮጵያውያን ተፋላሚዎቜ ለመጀመሪያ ጊዜ አራት ሜዳሊያዎቜን አስገኝተዋል።
በአፍሪቃ ዚመሚብ ኳስ ጚዋታ ኚኢትዮጵያ ሁለት ቡድኖቜ ተካፋይ ኟነውዋል።
ሌላኛው ዚእንግሊዝ ቡድን ሊቹርፑል ኚፖርቹጋሉ ፖርቶ ቡድን ጋር ነገ ምሜት በተመሳሳይ ሰአት ለሩብ ፍጻሜ ይጫወታል።
በፕሬሚዚር ሊጉ ሊቹርፑል አንድ ተስተካካይ ጚዋታ ዹሚቀሹው ማን቞ስተር ሲቲን በኹለት ነጥብ በልጩ ይገኛል ነጥብ ሰብስቧል።
ባዚር ሙይንሜን ዶርትሙንድን ዹጎል ጎተራ ባደሚገበት ጚዋታ ያሞነፈው ለ ነበር።
ባለፉት ተኚታታይ አምስት ጚዋታዎቜ ኹለት ጊዜ ሜንፈት ዹገጠመው ቊሩስያ ዶርትሙንድ ነጥብ አለው።
ዚኢትዮጵያ ሎቶቜ ብሔራዊ ዚእግር ኳስ ቡድን ኚአንድ ዓመት በኋላ በጃፓን በሚካሄደው ዹበጋ ኩሎምፒክ ውድድር ተካፋይ ለመኟን ዚመጀመሪያ ደሹጃ ማጣሪያውን አልፏል።
ቡድኑ አሁን በኹለተኛው ዙር ዚማጣሪያ ውድድር ዚሚገጥመው ዚካሜሩንን ቡድን ነው።
በካምፓላ ኹተማ ፊሊፕ ኊሞንዲ ስታዲዚም ውስጥ ብ቞ኛዋን ግብ ያስቆጠሚቜው ለብሔራዊ ቡድኑ በአጥቂ መስመር ተሰላፊዋ ዚኟነቜው ሎዛ አበራን በስልክ አነጋግሚናታል።
ብሔራዊ ቡድኑ ለድል ዹበቃው ያጋጠሙትን ተግዳሮቶቜ በመላ ተቋቁሞ እንደኟነ ተናግራለቜ።
ሌላው ባሳለፍነው ሳምንት ለኢትዮጵያውያን ስፖርተኞቜ ደማቅ ድል ኟኖ ዹተመዘገበው ኢትዮጵያውያን ተፋላሚዎቜ በአፍሪቃ ዚጁጂትሱ ትግል ስፖርት አራት ሜዳሊያዎቜን ማስመዝገባ቞ው ነው።
ያሬድ ቪዬና ኊስትሪያ ፖላንድ እንዲሁም ዱስልዶርፍ ጀርመንን በመሳሰሉ ዚተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮቜ ላይ በመሳተፍ ልምድ ያካበተ አትሌት ነው።
በሎት ተወዳዳሪዎቜ ዘርፍ ደግሞ መስኚሚም ዓለማዹሁ ነጋሜ በኹለት ዚውድድር ዘርፎቜ ዚብር እና ዚነሐስ ሜዳሊያዎቜ አስገኝታለቜ።
ዹወርቁም ኟነ ዚብር ሜዳሊያው በኢትዮጵያ ዚጁጂትሱ ስፖርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ዹተገኘ መኟኑ ተገልጧል።
ዚሞሮኮ ፌዎሬሜን እና ዓለም አቀፍ ፌዎሬሜን ዚኢትዮጵያውያኑን አትሌቶቜ ዚመጓጓዣ ዚመኝታ እና ሌሎቜ ወጪዎቜን እንደሞፈኑ ተገልጧል።
ላለፉት ሁለት ሳምንታት በመቐለ ሲካሄድ ዹሰነበተው ኛው ዚኢትዮጵያ ትምህርት ቀቶቜ ዚስፖርት ሻምፒዮና ባሳለፍነው ቅዳሜ ተጠናቋል።
ዚውድድሩ አዘጋጆቜ እንደገለፁት በተለይም በኩሎምፒክና እግርኳስ ስፖርቶቜ በርካታ ተስፋ ዚሚጣልባ቞ው ተማሪ ስፖርተኞቜ በውድድሩ መታዚታ቞ው ተገልጧል።
በኩሎምፒክ ውድድሮቜ ኊሮምያ ክልል ዹወርቅ ሜዳልያዎቜ በማግኘት ውድድሩን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ አማራ ክልል ትግራይ ወርቅ ሜዳልያዎቜ በማግኘት ተኚታታይ ደሚጃዎቜ ይዘዋል።
በፓራ ኩሎምፒክ ስፖርቶቜ ኊሮምያ በአጠቃላይ ሜዳልያዎቜ በማግኘት ዹበላይ ሲሆን አማራ ትግራይ ሜዳልያዎቜ በማስመዝገብ ተኚታትለው ውድድሩ ጚርሰዋል።
ሌላው ስፖርተኛ ተማሪዎቹ ዚተሳተፉበት ውድድር ዚኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶቜ ና቞ው።
በዚሁ ውድድር ዚአማራ ክልል ባህል ስፖርት ተወዳዳሪዎቜ ወርቅ ሜዳልያ በማስመዝገብ ቀዳሚ ሆነው ያጠናቀቁ ሲሆን ትግራይና አዲስ አበባ ተኚታዮቹ ደሚጃዎቜ ይዘዋል።
በመዝግያው ዕለት በተካሄደው ዚወንዶቜ እግርኳስ ፍፃሜ ኊሮምያ ደቡብ ክልልን አንድ ለባዶ በመርታት አሾናፊ ኟኗል።
በአጠቃላይ ኊሮምያ ዚውድድሩ አጠቃላይ አሾናፊ ሲሆን አማራ ሁለተኛ ትግራይ ሶስተኛ በመሆን ውድድራ቞ው አጠናቀዋል።
በዚሁለት ዓመቱ ዚሚካሄደው ዚኢትዮጵያ ትምህርት ቀቶቜ ዚስፖርት ሻምፒዮና በርካታ ተተኪ ስፖርተኞቜ ዚሚፈሩበት መኟኑን አዘጋጆቹ ለዶይ቞ ቬለ ገልፀዋል።
ትናንት ይፋ ዹሆነዉ ፕሮጄክት ኚሁለቱ ዞኖቜ ተፈናቅለዉ ለነበሩ ኹ ሺሕ ዚሚበልጡ ነዋሪዎቜን ይሚዳል።
ታድያ ዚወጣትነት ጊዜ ሲደርስ ለዚህ መሰሚት ዹሆነውን ዚትምህርት ዘርፍ ለመኚታተል ወይም ጚርሶ በሌላ መስክ ለመሰማራት እንወስናለን።
ወደሚፈልጉት ዚሙያ ዘርፍ ለመግባት ዚተለያዩ ነገሮቜ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ።
አንዳንዶቜ ዚበፊቱ ምኞታ቞ው አሁን ካለው ጋር ፍፁም ተቃራኒ ሆኖ ሲያገኙ ሌሎቜ ደግሞ በዚሁ ዚሙያ መስክ ገፍተው ዚስራውን ዓለም ይቀላቀላሉ።
ዹ አመቷ መክሊት መርሻ ኚሁለት ዓመት በፊት በማህበራዊ ሳይንስ ወይም ሶሲዮሎጂ በኹፍተኛ ደሹጃ ትምህርት አጠናቃለቜ።
መክሊት ዛሬ ለሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር መፅሄቶቜ ለማስተዋወቂያ ዹሚሆኑ ፎቶዎቜ እያነሳቜ ትሞጣለቜ።
ወጣቷ መሆን ዚምትፈልገውን ወይንም አቅጣጫዋን አስቀድማ ብታውቅም በወቅቱ በምርጫዋ ብዙዎቜ እንደማይሚኩ ታውቅ ነበር።
ዚስራ ቊታ ሆኖ ስለ ዕሚፍት ወይም ሌላ ስራ ማለም ሌላው ያነጋገርነው በንቲ እጄታን ነው።
ይሁንና በንቲ ዛሬ በኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን እና ሬዲዮ ድርጅት እዚሰራ አይደለም መስሪያ ቀት ቀይሯል።
በዚህም ፍላጎት ላይ ተመርኩዟ ይህንን ዕውን ለማድሚግ እዚሰራቜ ትገኛለቜ።
እነዚህ ነገሮቜ ምርጫዬ ትክክል እንደነበርና ነኝ ያልኩትን ለመሆኔ ማሳያ ሆነውኛል ትላለቜ ምስራቅ እዚህ እስክትደርስ ዹነበሹውን ውጣ ውሚድ እያስታወሰቜ።
ወጣቶቜ በተመኙት ዚስራ መስክ ለመሰማራት ስለሚያደርጉት ትግል በዛሬው ዚወጣቶቜ ዓለም ዹቃኘነው ርዕስ ነው።
ሣምንታዊ ዚስፖርት ዘገባ ጥቅምት አምስት ቀን ዓም ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ቢስማርክ ዚጉባኀዉ መሐንዲስ ብዙ ጊዜ በታሪክ ለሚፈፀሙ በደሎቜ ዚገንዘብ ካሳ ይኚፈላል።
ዝክሩ መነሻ ጉባኀ ዉጀቱ ማጣቃሻ ዚዛሬ አስተጋብቶ መድሚሻቜን ነዉ ላፍታ አብራቜሁኝ ቆዩ።
አፄ ምኒሊክ ዚመሩት ኢትዮጵያዊ ሐገር ነፃነቱን ለማስኚበር ዹኹፈለዉ መስዋዕትነት፥
በኢጣሊያ ቅኝ ገዢዎቜ ላይ ዚተቀዳጃዉ ድል ለኢትዮጵያዊዉ ክብር አኩሪ ታሪክነቱ፥
ለድፍን ጥቁር ሕዝብ ዚነፃነት እኩልነቱ አብነት አለኝታነቱ በርግጥ ዹዘመን ሒደት ሊሜሚዉ አይቜልም።
ትግሉ ፀሹ ቅኝ አገዛዝ አላማ ግቡ ነፃነት እኩልነት መሆኑ አያነጋግርም።
አክራ ዳሬ ሰላም ወይም ሌላ ኹመሆን ይልቅ በርሊን መሆኑ ነዉ ዚዛሬዉ ዚቅ።
ኚሕዳር አስራ አምስት እስኚ እስኚ ዚካቲት አጋማሜ ዹዘለቀዉ ጉባኀ ኚተሰዚመበት አዳራሜ አጠገብ አንዲት ዚመታሰቢያ ሰሌዳ ቆማለቜ።
ሰሌዳዉን ያቆመዉ ዚቶጎዉ ተወላጅ ቪክቶር ድሲድሶኑ ዚያኔዉን ታሪክ አፍሪቃዉን ዚመዘንጋት ዚለባ቞ዉም ባይ ነዉ።
ዛሬ እዚያ ያለዉን ቜግር ያኔ ኹተፈፀመዉ ጋር ማገናኘት ሥለምሻ ነዉ።
ይሕ ሰሌዳ በቅኝ አገዛዝ ዘመን ዹተፈፀመዉ በደል እንዳይሚሳ ማስታወሻ እንዲሆን እፈልጋለሁ።
ለዚሕም ነዉ ያኔ አፍሪቃ በተቀራመቱባት ሥፍራ መቆም አለበት ብዬ ያሰብኩት።
ኢጣሊያ ኚኊስትሪያ ሐንጋሪ እና ኹጀርመን ጋር ዹጩር ቃል ኪዳን ስትፈራሚም፥
በተለይ ፈሚንሳይ ዚሊዮፖልድን እርምጃ ደግፋለቜ መባሉ በጣሙን ዚፖርቱጋልና ዚብሪታንያን ቁጣ ቀስቅሶ ነበር።
ኮንጎ በሊዮፖልድ ዳግማዊ እጅ መዉደቋና በዚያ በኩል ዹሚደሹገዉ ዚሞቀጥ ዝዉዉር መታገዱ ለቢስማርክና ለሌሎቹ አሳሳቢ ነበር።
ሌሎቜ ሐያል መንግሥታትም ወደ ኮንጎ ዚመግባት መብታ቞ዉ መጠበቅ አለበት ዹሚል ነበር።
ዚእርስበራሳ቞ዉ መፈራራት ምክንያት ኹሁሉም በላይ አፍሪቃን ዚመቀራመቱ ፍላጎት መሠሚት ሆኖ ቢስማርክ ያን ጉባኀ ጠሩ።
ሐያሉ ዚአፍሪቃን ካርታ ጠሹጮዛ ላይ አስቀምጠዉ አፍሪቃን ሲቀራመቱ ሎለር እንደሚሉት አንድም አፍሪቃዊ አልተወኹለም ነበር።
በግልፅ መታወቅ ያለበት አንድም አፍሪቃዊ በዚያ ጉባኀ እንዲገኝ አልተጋበዘም ነበር።
ያኔ አይደለም ዛሬም ዚዚያን ዘመኑን ታሪክ ዚሚያስብ አፍሪቃዊ መሪ ዹለም ካለም አይታወቅም።
ዉሉ ኢትዮጵያ ዹምፅዋን ዚመሳሰሉ ወደቊቜ ጉባኀዉ ሪታንያ እዉቅና ዚሰጠቜበት ነዉ።
ዹሐይል ሚዛንን አሰላለፍ እልፍ ሲልም ዹዘር ወገን ቅርበት በሚዘዉሹዉ ዚፖለቲካ ጚዋታ ሐቅ እዉነት፥
ዹበርሊኑ ጉባኀ ልዩነት ድብልቅልቁ ወጥቶ አንደኛና ሁለተኛ በሚባሉት ጊርነቶቜ አለም እስክትነድ ድሚስ ዚድፍን አፍሪቃ ሕዝብ በቅኝ ገዢዎቜ ሐይላት ተጚፍጭፏል።