text
stringlengths
0
200
ህይወቮ ሰላም ዚተባሉ አስተያዚት ሰጪ ደግሞ ማንም ዹቆመ ቢመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።
ዚምርመራ ጣቢያዎቜ ቢበዙና ምርመራው ቢፋጠን ኚብዙ ቜግር ያድነናል ።
ገነት ዹጅማዋ ደግሞ ዚመንግስት ሰራተኛና ተማሪን ብቻ ኚቀት እንዳትወጣ ብሎ በሜታውን መቆጣጠር ይቻላል
አንድ ዚታክሲ ሚዳት በበሜታው ቢጠቃ ምልክቱ እስኪታይበት ድሚስ ስንት ሰው እንደሚያሲዝ አስቡት
ነገር ግን ህግ ጥሰው ዚሚውጡ እንዳሉ ውስጥ ውስጡን እዚስማን ነው።
እኔ ግን ዹሚገርመኝ ኚማቆያው ወጥቶ ኚቀተሰቡ ጋር ዹሚቀላቀለው ሰው ነው ።
ሲሉ አሌክስ እራመዳለሁ በተስፋ በበኩላ቞ው ይህን እኩይ ተግባር በሚፈጾሙና በተባበሪ አካላት ላይ መንግስት እርምጃ ሊወስድ ይገባዋል።
ወሚርሜኙን ለመኹላኹል ዹተደሹጉ ክልኚላዎቜ ዚኮሚና ቫይሚስ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ኚተኚሰት ወዲህ ሀገሮቜ ወሚሚሜኙን ለመቆጣጠር ያስቜላሉ ያሏ቞ውን ርምጃዎቜ በመዉሰድ ላይ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያም መንግስት ወሚርሜኙን ለመኹላኹል ዚሰዎቜ ግንኙነትን መቀነስን ጚምሮ ዚቫይሚሱን ስርጭት ለመግታት ያግዛሉ ያላ቞ውን ዚተለያዩ እርምጃዎቜን እዚወሰደ ነው።
ዹክልል መስተዳድሮቜም ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ዚውስጥና ዹአገር አቋራጭ ዚትራንስፓርት አገልግሎቶቜ ስብሰባዎቜና ሌሎቜ ማህበራዊና ክንውኖቜ ላይ ገደቊቜና ጥብቅ ክልኚላዎቜን አድርገዋል።
ዚተለያዩ ዚሀይማኖት አባቶቜም ምዕመናን ዚአምልኮ ስርዓታ቞ዉን በቀታ቞ው እንዲኚውኑ ውሳኔዎቜን አስተላልፈዋል።
ይህ ጉዳይ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ ሌላዉ ዚመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ነው ዚሰነበተዉ።
አንዳንዶቜ ክልኹላው በሚፈለገዉ ደሹጃ እዚተተገበሚ አለመሆኑን ሲገለፁ አንዳንዶቹ ደግሞ ክልኹላው ዚህዝቡን ዚኑሮ ሁኔታ ያላገናዘብ ነው ይላሉ።
ሲሉ ቀለም አበበ በአብዛኛው በሜታው እዚገባ ያለው ኹውጭ ነው ።
እንቅስቃሎን ማገድ ግን ለኔ ኚኮሮና እና ኚሚሀብ አንዱን ዚመምሚጥ ያህል ነው።
ክልኹላዉም ሆነ ሰለ ወሚሚሜኙ ዹሚሰጠው መሹጃ ኹተማ ኹተማዉን ሆነሳ ጎብዝ ዚገጠሩ ሰዉ ዜጋ አይደለም
ያሉት ደግሞ ሀርቆ ኹይላ ዚተባሉ ዚፌስ ቡክ ተኚታታይ ና቞ው።
እፎይታ ኢትዮጵያ ኹልኹላዉ ጥሩ ቢሆንም ኚቀታ቞ው ምግብ ማብሰል ዚማይቜሉና ምግብ ገዝተው ዹሚጠቀሙ ሰዎቜ በጣም ተ቞ግሚዋል።
ነገ ኹነገ ወዲያ ሠዉ በኮሚና ተያዘ ዹሚለዉ ዜና ተቀይሮ በሚሀብ ይህን ያህል ሰዉ ሞተ ወደሚለው ሳንሜጋገር ዚተያዘዉ መንገድ በደንብ ይጠና።
ሲሉ ቎ዲ ማን ዚተባሉ አስተያዚት ሰጪም ትክክል ቀን ሰርቶ ማታ ገዝቶ ዹሚበላ ሰው እንዳለ መታወቅ አለበት።
ስለዚህ መንገድ ትራንስፖርት ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ተሜኚርካሪዎቜን መድቊ ቜግሩን ቢያቃልል መልካም ነው።
አለማዹሁ ቢሚሳ በጎ አድራጊዎቜም ህዘቡ ኚመጎዳቱ በፊት ፈጥና቞ሁ ብትደርሱለት ወሚርሜኙን ቀቱ ተቀምጩ ሊያሳለፍ ይቜላል።
ብሩክ ዳዲ ዚኢትዮዜያ ህዝብ ስለእዉነት ጥሩና ደግ ህዝብ ነው ።
ኚፊት ሆኖ ዚሚያሰተባብሚውና ዚሚመራዉ ካገኘ መሚዳዳትና ተካፍሎ መብላት ዚሚቜል ህዝብ ነው።
ስለዚህ ሃላፊነት ተወስዶ በዹ አካባቢው እርዳታ ቢሰባሰብ መልካም ነዉ ብለዋል።
መጀመሪያ ይሄን እንቀበል ኹዛም መቀመጫ ቀት ዹሌላቾውና ቀት ቢቀመጡ ዚሚበሉት ዹሌላቾውም መኖራ቞ውንም መገንዘብ ግድ ይላል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማገሰቱ መጋቢት ቀን ዚለውጡን ሁለተኛ አመት በማስመልኚት ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ ያልፋል አትጠራጠሩ
በሚል ርዕስ ምንም እንኳ ዹገጠመን ቜግር ኹዚህ በፊት እንዳዚና቞ው አደጋዎቜ ዚማያልፍ ቢመስልም ማለፉ ግን አይቀርም፡፡
ስለተመኘን ሳይሆን በትብብር ስለምንሰራ ይህ ጊዜ ያልፋልና አትጠራጠሩ ሲሉ ገልፀዋል።
እነዚህ ዹጠቅላይ ሚንስትሩ መገለጫዎቜም በሳምንቱ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ ዚድጋፍና ዚነቀፌታ አስተያዚቶቜን አስተናግደዋል።
ፎን ደር ላዹን ለመጀመሪያ ጊዜ ባደሚጉት ዚአፍሪካ ጉብኝት ዚአውሮፓ ኮሚሜን ለኢትዮጵያ ሚሊዮን ዩሮ ዕርዳታ ሊሰጥ ስምምነት ተፈርሟል።
ጞጥታ እና ስደትን ዚመሳሰሉ ጉዳዮቜ በአፍሪካ እና በአውሮፓ መሪዎቜ ዚጋራ መፍትሔ ሊፈለግላቾው እንደሚገባ ተናግሚዋል።
በአፍሪካ ኅብሚት መገኘቮ ጠንካራ ፖለቲካዊ መልዕክት ያስተላልፋል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል።
በውይይታቜን በአውሮፓ እና በአፍሪካ መካኚል ባለው ግንኙነት መሻሻል ዚሚገባ቞ው ጉዳዮቜ እንዳሉ ተመልክተናል ሲሉ ተደምጠዋል።
ነገር ግን በአንድነት መልሶቜ ማግኘት እንቜላለን ዹሚል ዕምነት አለኝ።
በጋራ ለአፍሪካም ሆነ ለአውሮፓ ቜግሮቜ መፍትሔ ማበጀት እንቜላለን ሲሉ ዚሁለቱ አኅጉሮቜ ፖለቲኚኞቜ በጋራ መስራት እንደሚገባ቞ው ጠቁመዋል።
ፎን ደር ላይን በሥልጣን በሚቆዩባ቞ው አመታት ኚሥልታዊ ትብብር በተጚማሪ ኚአፍሪካ ወደ አውሮፓ ለሚደሹገው ስደት መፍትሔ መፈለግ ዋንኛ ትኩሚታ቞ው እንደሚሆን ይጠበቃል።
በዛሬው ዕለት ኡርሱላ ፎን ደር ላዹን ባሉበት ኢትዮጵያ እና ዚአውሮፓ ኮሚሜን ዹ ሚሊዮን ዩሮ ዚእርዳታ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ገንዘቡ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድን ለማጠናኹር እንዲሁም ዚጀና ዚሥራ ዕድል ፈጠራ እና ዹመዋዕለ ንዋይ ዘርፎቜን ለመደገፍ ይውላል ተብሏል።
ስምምነቱ ዹተፈሹመው ዚአውሮፓ ኮሚሜን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ፎን ደር ላይን በዛሬው ዕለት ዚኢትዮጵያ ጉብኝታ቞ውን በጀመሩበት ወቅት ነው።
ፎን ደር ላይን ዚኮሚሜኑን ፕሬዝዳንትነት ኚተሚኚቡ በኋላ ኚአውሮፓ ውጪ ያደሚጉት ዚመጀመሪያ ጉዞ ነው።
ያም ሆኖ ይኾዉ ዘመናዊ ስልት እንኚንም እንደማያጣ ዚሚታይና ዚሚነገርለት ጉዳይ ነዉ።
አነሰም በዛም አመት በዓል መድሚሱን ኚግምት አስገብቶ ዚዕለቱ ጀናና አካባቢ ትኩሚት ነዉ።
ዚሞት ምክንያት ዹሚሆኑ ነገሮቜ ሲዘሚዘሩ በተለይ በአፍሪቃ ዚሚጠቀሱት ጊርነትና ተላላፊ በሜታዎቜ እንደሆኑ ይነገራል።
አሁን ግን አንድ ጥናት እንደሚያመለክተዉ አብዛኛዉ ሰዉ በተለይ ሎቶቜ ታመዉ ህይወታ቞ዉን ዚሚያጡበት ምክንያት በወሊድ ብቻ ሳይሆን በካንሰር ነዉ ተብሏል።
ዹጀርመንና ዚፈሚንሳይ መሪዎቜ በበኩላ቞ዉ አዲስ ዚነደፉትን ዹሠላም ዕቅድ ለዩክሬንና ለሩሲያ መሪዎቜ ለማስሚዳት ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ላይ ና቞ዉ።
አንዳድ ዚአሜሪካ ባለሥልጣናት ባንፃሩ በምሥራቃዊ ዩክሬኑ ጊርነት ሜንፈት ዹገጠመዉን ዚኪዚቭን መንግሥት ኚዉድቀት ለማዳን ማስታጠቅ አለብን ይላሉ።
ባህል ሐሚር ዚስልጣኔ ፈር ቀዳጅ ኹተማ ባለ ታሪክ ጥንታዊት ኹተማ ዚባህል ፈርጥ ናትም ይሏታል።
ተፋቅሹው ዚሚኖሩባት ዚአብሮነት ኹተማ ሲሉም ይመሰክሩላታል ይህቺው ታሪካዊት ኹተማ ኚተቆሚቆሚቜ ዓመት ዚሆናት ቀደምት ስልጣኔን ያስገባቜ ዚኢትዮጵያ ባለውለታ ሀሚር።
ዹጁገል ግንብ አንዱ ዹሀሹር ጥንታዊ ስልጣኔ መገለጫ ባለ ታሪክ ጥንታዊት ኹተማ ዚባህል ፈርጥ ናትም ይሏታል።
በምስራቅ ዚሀገሪቱ ክፍል ዚምትገኘው ሀሹር ኚአዲስ አበባ በ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለቜ።
ሀሹር ስኩዚር ኪሎ ሜትር ስፋት ያላት ጥንታዊት ኹተማ ናት።
ሀሚሪ ኊሮምኛ አማርኛ ትግርኛ ጉራጌኛ እና ሱማሌኛ ቋንቋዎቜ ይነገሩባታል።
ሀሹር ጥንታዊ ስልጣኔ መገለጫዋ ኚሆኑት ባህላዊ ቀቶቜ እና ዹኹተማዋ ዚውስጥ ለውጥ መንገዶቜን ያቀፈው ዹጁገል ግንብ ነው።
ይሄው ዹጁገል ግንብ ኚሀሚሪ ቋንቋ በተጚማሪም በአሚብኛ በአማርኛና በኊሮምኛ ስያሜ መጠሪያዎቜ አሏ቞ው።
ዹጁገል ግንብ በኹተማዋ ይሰነዘሩባት ዚነበሩ ጥቃቶቜን ለመኹላኹል በሚል መገንባቱን ታሪክን አጣቅሰው ብዙዎቜ ይናገራሉ።
ሀሹርን ኚሌሎቜ ዚኢትዮጵያ ኚተሞቜ ለዚት ዚሚያደርጋት እድሜ ጠገብ መሆኗ ነው።
በኪነ ህንጻ በአኚባቢን መንኚባኚብ በውሃ አጠባበቅ ኚሌሎቜ ዚሀገራቜን ኚተሞቜ ለዚት ትላለቜ።
በራስዋ አስተዳደር ዚነበራት አራት ስርወ መንግሥት ያሳለፈቜ ነገስታት ዚነገሱባት ለኢትዮጵያ ዘመናዊነት በር ኚፋቜ ዚሆነቜ ኹተማ ነቜ።
ዚማህበሚሰቡ ዚቀት አሰራር ጥበብ ጥንት ኹነበሹው ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው አቶ አብዱልሰመድ እድሪስ ይገልጻሉ።
ኚብዙ ዹአፈር ዓይነት ዚተደባለቀበት ሆኖ ለሁለት ወር ጭቃው ይቊካል።
ዚመስሪያ ጥሬ ዕቃ ነው እንጅ ዚማይመሳሰለው አሁን ያለውም ዚሀሚሪ ቀት በስነ ህንጻ አሰራር አሁንም ተመሳሳይነት አለው።
በዚትኛውም ዚሀሚሪ ብሄሚሰብ ዘንድ ዚሚሰሩ ቀቶቜ ተመሳሳይ እንደሆነ ዚብሄሚሰቡ ተወላጅ ዹሆነው ሙባሚክ ፈይሰል አጫውቶናል።
ዚሐሚሪ ባህላዊ ቀት ዚሚገነባው በድንጋይ ሲሆን ጣሪያው በጥድ ወይም በዋንዛ እንጚት ዚሚሰራ ነው።
በዚህም ኚቀት ውጪ ኹፍተኛ ሙቀት ሲኖር ቀቱ ውስጥ ካሉ ግን ሙቀቱ አይሰማዎትም።
ቀቱ ውስጥ ም቟ት ዚሚሰጥ ቅዝቃዜ ይኖሹዋል ይላሉ ዚብሄሚሰቡ ተወላጅ።
ዚሐሚሪ ቀት ኚዚት ኚሚታዚው ክፍል በተጚማሪም ሌሎቜ ሁለት ክፍሎት አሉት።
በቀቱ ውስጥ እንደሚሰጡት አገልግሎት ስያሜና ትርጉም ያሏ቞ው አምስት ለመቀመጫነት ዚሚያገለግሉ መደቊቜ ይገኛሉ።
ዚንጉስ መደብ ዚቀቱ አባወራ ዚሚቀመጥበት ትልቁ መደብ ዚተማሩ ሰዎቜ ዚሚቀመጡበት ሆኖ በዚሁ ቊታ ላይ ትምህርት ያስተምሩበታል።
ትንሿ መደብ ወጣት ወንዶቜ ዚሚቀመጡበት ሲሆን ኚበሩ ጀርባ ያለው መደብ ዚእናቶቜ መቀመጫ ነው።
በሀሚሪ ዚቀት ዚውስጥ ገጜታን ለማስጌጥ ዚሚጠቀሙበት ዚተለያዩ ዚስፌት ስራዎቜ አሉ ይሉናል ወ ሮ ሩሚያ ኡመር።
ሰሀኖቜ በእንጚት ዚተሰሩ ቆሪዎቜ ስፌቶቜ ሌማት ወስኚንባ ዚተለያዩ ስፌቶቜ በግራና በቀኝ ይሰቀላሉ።
በዚህም ታሪካዊ ኚተማነቷ እዚደበዘዘ እንዳይሄድ ትኩሚት ሊሰጠው እንደሚገባ ይጠቅሳሉ።
ዹዓለም ዚኀድስ ቀን በኢትዮጵያ ዚጋምቀላ ክልል ባለፈው እሁድ ኹ በላይ ሰዎቜ በፈቃደኝነት ዚኀቜ አይ ቪ ምርመራ ማድሚጋ቞ው ተሰምቷል።
ዚተጎሳቆሉ ጎጆዎቜ በሞራ እና ፕላስቲክ ዚተወጠሩ ድንኳኖቜ እና በአይን ባይታዩም መጥፎ ጠሹንን ዚሚያመላክቱ ቆሻሻዎቜ በምስል ዘገባዎቜ ተካተዋል።
በዚህ ዚቁሻሻ መጣያ ዙሪያ ደግሞ በፊትም አሁንም ሰዎቜ ይኖራሉ።
ዝቅተኛ ማህበሚሰብ ዚሚኖርበት አካባቢ ነው ይላል ኚልጅነቱ አንስቶ ቄሌ በሚባለው አካባቢ ዹሚኖሹው ኀፍሬም ሰፈሩን ሲገልፅ።
ፒያሳ አካባቢ ዹተወለደው ኀፍሬም ኹ ዓመት በፊት በህፃንነቱ ነው ኚእናቱ ጋር ወደዚህ ስፍራ ዚመጣው።
ሌላው ወጣት ዳንኀል ደግሞ ብዙም በማይርቀው መካኒሳ ነው ተወልዶ ያደገው።
አሁን በሰፈራቜን ዚሚታዚውም ዹሚሰማውም ነገር ምንም ዚሚያስደስት አይደለም ትላለቜ።
እንኳን ሀዘን ተጚምሮበት በፊትም እዛ አካባቢ በመኖሯ ሰው ይንቃት ነበር።
ስለሆነም ኀፍሬም እንደገለፀልን ዚአካባቢው ልጆቜ ሰፈራ቞ው ዚት እንደሆነ ለሌሎቜ ሰዎቜ መናገርም ይሁን ማሳዚት አይፈልጉም።
ዚወጣቷ አማካሪ ሆነው በተመደቡበት ሰዓትም ጥናቷ ኚባድ እንደሚሆን ቢያምኑም ዹዛ ሰፈር ልጅ በመሆኗ ለጉዳዮ ቅርብ መሆኗን አሳምና቞ው ጥናቷን እንዳካሄደቜ ገልፀውልናል።
ሌላው ምንም እንኳን ወጣቶቹ ዚድህነት እጣ ፋንታ቞ውን ቢቀበሉም በሌላው ህብሚተሰብ ዘንድ ተቀባይነት ማጣታ቞ው ኹፍተኛ ቜግር ነበር።
ዶክተር ዚራስ ወርቅ እንደሚሉት ዹዚህ አካባቢ ሰዎቜ ቜግር በራስ አለመተማመን ሳይሆን ድህነት ነው።
ነዋሪዎቹ ብቻ቞ውን ሊፈቱት ያልቻሉትን ቜግሮቜ ባለፈው ቅዳሜ ዹደሹሰው አደጋ ዚመንግሥት ትኩሚትን ፈጥሮ ዚአካባቢያ቞ው ዚወደፊትን ገጜታ ይቀይር ይሆን
ዹ ቆሌ ልጆቜ ዚማህበሚሰባዊ እና ስነ ልቩናዊ ቜግሮቜን ዚቃኘንበትን ዚወጣቶቜ ዓለም ዝግጅት በተጚማሪ በድምፅ ያገኙታል።
በዚህም መሠሚት ባለፈዉ ቅዳሜ በቀልጂዚም እና በአካባቢዉ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ዚተሳተፉበት ዚኢትዮጵያ ዚለዉጥ ሂደትና ተግዳሮቶቹ በሚል ርዕስ ዹተዘጋጀ ሕዝባዊ ዉይይት ተካሂዷል።
በዚሁ ስብሰባ ላይ ነባሩ ፖለቲኚኛ አቶ አበራ ዹማነ አብና እና ዚሰብዓዊ መብት አቀንቃኙ አቶ ያሬድ ኃይለ ማርያምም ተገኝተዉ ነበር።
ዹጊኒ ዚምርጫ ዉዝግብ ዚአዉሮጳ ኅብሚት ዚምርጫ ታዛቢ ቡድን በጊኒ ዚተካሄደዉ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ተዓማኒ መሆኑ አስታወቀ።
ዚሀገሪቱ ዹተቃዉሞ ፖለቲካ ፓርቲ እጩዎቜ በበኩላ቞ዉ ምርጫዉ ተጭበርብሯል ተቀባይነት ዹለዉም እያሉ ነዉ።
በመገናኛ ብዙሃን ይፍ ዹሆነዉ ዚመጀመሪያ ዚምርጫ ዉጀት ፕሬዝደንት አልፋ ኮንዎ እዚመሩ መሆናቾዉን ያመለክታል።
ዚኅብሚቱ ታዛቢ ቡድን ምርጫዉ ተዓማኒ ነዉ ቢልም በሂደቱ ላይ ዚታዩ ጉድለቶቜንም ጠቁሟል።
ያም ቢሆን ግን ዚእሁዱን ምርጫ አጠቃላይ ዉጀት ጥያቄ ላይ ዚሚጥል እንደማይሆን አመልክቷል።
ጊኒ አመፅ በተቀላቀለዉ ዚፖለቲካ እንቅስቃሎ ዚምትታወቅ ምዕራብ አፍሪቃዊት ሃገር ናት።
በፈሚንሳይ ቅኝ በመገዛትዋም ቀደም ባሉት ጊዜያት ዚፈሚንሳይ ጊኒ ስትባል ኖራለቜ።
ኹጊኒ ቢሳዎ እና ኚኢኳቶሪያል ጊኒ እንድትለይ ደግሞ ጊኒ ኮናክሪ በመባል ትታወቃለቜ።
ኚፈሚንሳይ ዹቅኝ ተገዢነት በጎርጎሪሳዊዉ ዓ ም ነፃ ኚወጣቜ ወዲህ ጊኒ ኮናክሪ ዎሞክራሲያዊ ምርጫ ስታካሂደ ሁለተኛዋ መሆኑ ነዉ።
ፈሚንሳይኛን ለብሔራዊ ቋንቋነት ዚምትጠቀመዉ ይህቜ ሀገር ዚራሷ ዹሆኑ ቋንቋዎቜም ይነገሩባታል።
ዚኅብሚቱ ታዛቢ ቡድን መሪ ፍራንክ ኀንግልስ ሁለት ሶስተኛዉ ዚምርጫ ጣቢያ በአስፈላጊ ቁሳቁሶቜ እጥሚት ዘግይቶ መኚፈቱን አንዳንዱም ጋዚድምጜመክተቻሳጥንእንዳልነበርአመልክተዋል።