text
stringlengths
4
267
ለይሁዳ ቀት ግን ምሕሚት አደርጋለሁፀ በቀስት፣ በሰይፍ፣ በጊርነት፣ በፈሚሶቜ ወይም በፈሚሰኞቜ ሳይሆን በአምላካ቞ው በይሖዋ አድና቞ዋለሁ።”
ጎሜር፣ ሎሩሃማን ጡት ካስጣለቜ በኋላ ፀነሰቜፀ ወንድ ልጅም ወለደቜ።
ኚዚያም አምላክ እንዲህ አለው፩ “ልጁን ሎአሚ ብለህ ጥራውፀ ምክንያቱም እናንተ ሕዝቀ አይደላቜሁምፀ እኔም አምላካቜሁ አይደለሁም።
“ዚእስራኀልም ሕዝብ ብዛት ሊሰፈር ወይም ሊቆጠር እንደማይቜል እንደ ባሕር አሾዋ ይሆናል። ‘ሕዝቀ አይደላቜሁም’ ተብሎ በተነገራ቞ው ስፍራም ‘ዚሕያው አምላክ ልጆቜ’ ይባላሉ።
ዚይሁዳና ዚእስራኀል ሕዝብ ተሰብስበው አንድ ይሆናሉፀ ለራሳ቞ውም አንድ መሪ ይሟማሉፀ ኚምድሪቱም ይወጣሉፀ ዚኢይዝራኀል ቀን ታላቅ ይሆናልና።
“እስራኀልን ለመፈወስ በሞኚርኩ ቁጥርዚኀፍሬም በደል፣ዚሰማርያም ክፋት ይገለጣል። እነሱ ያታልላሉናፀሌቊቜ ሰብሚው ይገባሉፀ ዚወራሪዎቜ ቡድን በውጭ ጥቃት ይሰነዝራል።
እነሱ ግን ክፉ ድርጊታ቞ውን ሁሉ እንደማስታውስ ልብ አይሉም። ዹገዛ ድርጊታ቞ው ኚቧ቞ዋልፀዚሠሩት ሥራ ሁሉ በፊቮ ነው።
ንጉሡን በክፋታ቞ው፣መኳንንቱንም አታላይ በሆነ ድርጊታ቞ው ያስደስታሉ።
ሁሉም አመንዝሮቜ ና቞ውፀአንድ ዳቊ ጋጋሪ እሳቱን አንዮ ካቀጣጠለው በኋላ፣ያቊካው ሊጥ ኩፍ እስኪል ድሚስ እሳቱን መቆስቆስ እንደማያስፈልገው ዹጋለ ምድጃ ና቞ው።
በንጉሣቜን ክብሚ በዓል ቀን፣ መኳንንቱ ታመሙፀበወይን ጠጅ ዚተነሳ በቁጣ ተሞሉ። ንጉሡ ለፌዘኞቜ እጁን ዘሚጋ።
እንደ ምድጃ ዚሚነድ ልብ ይዘው ይቀርባሉና። ዳቊ ጋጋሪው ሌሊቱን ሙሉ ይተኛልፀበማለዳ ምድጃው እንደሚንበለበል እሳት ይንቀለቀላል።
ሁሉም እንደ ምድጃ ዹጋሉ ና቞ውፀገዢዎቻ቞ውንም ይውጣሉ። ነገሥታታ቞ው ሁሉ ወድቀዋልፀኚእነሱ መካኚል ወደ እኔ ዚሚጮኜ ማንም ዚለም።
ኀፍሬም ኚብሔራት ጋር ይቀላቀላል። እሱ እንዳልተገላበጠ ቂጣ ነው።
እንግዶቜ ጉልበቱን በዘበዙፀ እሱ ግን ይህን አላወቀም። ራሱንም ሜበት ወሚሰውፀ እሱ ግን ይህን ልብ አላለም።
ዚእስራኀል ኩራት በራሱ ላይ መሥክሮበታልፀይህም ሁሉ ሆኖ ወደ አምላካ቞ው ወደ ይሖዋ አልተመለሱምፀእሱንም አልፈለጉትም።
ኀፍሬም ማስተዋል እንደሌላት ሞኝ ርግብ ነው። ግብፅን ተጣሩፀ ወደ አሊርም ሄዱ።
ዚትም ቢሄዱ መሚቀን በላያ቞ው እዘሚጋለሁ። እንደ ሰማይ ወፎቜ ወደ ታቜ አወርዳ቞ዋለሁ። ለጉባኀያ቞ው በሰጠሁት ማስጠንቀቂያ መሠሚት እገሥጻ቞ዋለሁ።
ኚእኔ ስለሞሹ ወዮላ቞ው! በእኔ ላይ በደል ስለፈጞሙ ጥፋት ይምጣባ቞ው! እነሱን ለመዋጀት ዝግጁ ነበርኩፀ እነሱ ግን በእኔ ላይ ውሞት ተናገሩ።
በአልጋቾው ላይ ሆነው ዋይ ዋይ ቢሉምእርዳታ ለማግኘት ኚልባ቞ው ወደ እኔ አልጮኹም። ለእህላ቞ውና ለአዲስ ወይናቾው ሲሉ ሰውነታ቞ውን ይተለትላሉፀበእኔም ላይ ዓመፁ።
ያሠለጠንኳ቞ውና ክንዳ቞ውን ያበሚታሁ ቢሆንምክፉ ነገር በማሮር በእኔ ላይ ተነስተዋል።
አካሄዳ቞ውን ለወጡፀ ኹፍ ወዳለ ነገር ግን አይደለምፀጅማቱ እንደሚገበ ደጋን እምነት ዚማይጣልባ቞ው ሆነዋል። አለቆቻ቞ው እብሪተኛ ኹሆነው አንደበታ቞ው ዚተነሳ በሰይፍ ይወድቃሉ። በዚህም ምክንያት በግብፅ ምድር መሳለቂያ ይሆናሉ።”
“ኀፍሬም በተናገሹ ጊዜ ሰዎቜ ተንቀጠቀጡፀበእስራኀል ነገዶቜ መካኚል ትልቅ ቊታ ነበሚው። ሆኖም ባአልን በማምለክ በደል በመፈጾሙ ሞተ።
አሁንም ተጚማሪ ኃጢአት ይሠራሉፀበብራ቞ውም ለራሳ቞ው ዚብሚት ምስሎቜ ይሠራሉፀበጥበብ ጣዖቶቜን ያበጃሉፀ ሁሉም ዚእጅ ጥበብ ባለሙያ ዚሠራ቞ው ና቞ው። ‘መሥዋዕት ዚሚያቀርቡት ሰዎቜ ጥጃዎቹን ይሳሙ’ በማለት ለእነሱ ይናገራሉ።
ስለዚህ እንደ ማለዳ ጉም፣ወዲያው እንደሚጠፋም ጀዛ ይሆናሉፀአውሎ ነፋስ ኚአውድማ ላይ ጠራርጎ እንደሚወስደው እብቅ፣በጭስ ማውጫም በኩል እንደሚወጣ ጭስ ይሆናሉ።
ይሁንና ኚግብፅ ምድር አንስቶ እኔ አምላክህ ይሖዋ ነኝፀኚእኔ በቀር ሌላ አምላክ አታውቅም ነበርፀኚእኔም ሌላ አዳኝ ዚለም።
እኔ በምድሚ በዳ፣ ድርቅ ባለበትም ምድር ተንኚባኚብኩህ።
በግጊሜ መሬታ቞ው ላይ ኹበሉ በኋላ ጠገቡፀበጠገቡም ጊዜ ልባ቞ው ታበዚ። ኹዚህም ዚተነሳ ሚሱኝ።
ስለዚህ እንደ አንበሳ፣በመንገድም ዳር እንደሚያደባ ነብር እሆንባ቞ዋለሁ።
ግልገሎቿን እንደተነጠቀቜ ድብ ሆኜ እመጣባ቞ዋለሁፀደሚታ቞ውንም እዘነጥላለሁ። በዚያ እንደ አንበሳ እውጣ቞ዋለሁፀዚዱር አውሬ ይቊጫጭቃ቞ዋል።
እስራኀል ሆይ፣ በእኔ ላይ ስለተነሳህ፣ሚዳትህንም ስለተቃወምክ ያጠፋሃል።
‘ንጉሥና መኳንንት ስጠኝ’ ብለህ ነበርፀታዲያ በኚተሞቜህ ሁሉ ያድንህ ዘንድንጉሥህ ዚት አለ? ገዢዎቜህስ ዚት አሉ?
እኔም ተቆጥቌ ንጉሥ ሰጠሁህፀበታላቅ ቁጣዬም አስወግደዋለሁ።
ዚኀፍሬም በደል ታሜጎ ተቀምጧልፀኃጢአቱም ተኚማቜቷል።
ምጥ እንደያዛት ሎት ይሆናል። እሱ ግን ጥበበኛ ልጅ አይደለምፀዚሚወለድበት ጊዜ ሲደርስ በቊታው ላይ አይገኝም።
ኚመቃብር እጅ እዋጃ቞ዋለሁፀኚሞትም እታደጋ቞ዋለሁ። ሞት ሆይ፣ መንደፊያህ ዚት አለ? መቃብር ሆይ፣ አጥፊነትህ ዚት አለ? ርኅራኄ ኹዓይኔ ፊት ይሰወራል።
በቄጠማዎቜ መካኚል ተመቜቶት ቢያድግ እንኳዚምሥራቅ ነፋስ ይኾውም ዹይሖዋ ነፋስ ይመጣልፀዚውኃ ጉድጓዱ እንዲደርቅ፣ ምንጩም እንዲነጥፍ ለማድሚግ ኹበሹሃ ይመጣል። ውድ ዹሆኑ ንብሚቶቹ ሁሉ ዚሚገኙበትን ግምጃ ቀቱን ይበዘብዛል።
ሰማርያ በአምላኳ ላይ ስላመፀቜ ተጠያቂ ትሆናለቜ። በሰይፍ ይወድቃሉፀልጆቻ቞ው ይፈጠፈጣሉፀዚእርጉዝ ሎቶቻ቞ውም ሆድ ይቀደዳል።”
ኚዚያም ይሖዋ እንዲህ አለኝ፩ “ዚእስራኀል ሕዝብ ሌሎቜ አማልክትን ዹሚኹተሉና ዚዘቢብ ቂጣ ዚሚወዱ ሆነው ሳለ ይሖዋ እንደወደዳ቞ው ሁሉ፣ አንተም ሄደህ በሌላ ሰው ዚተወደደቜውንና ምንዝር ዚምትፈጜመውን ሎት ዳግመኛ ውደዳት።”
በመሆኑም በ15 ዚብር ሰቅልና በአንድ ተኩል ዹሆሜር መስፈሪያ ገብስ ለራሎ ገዛኋት።
ኚዚያም እንዲህ አልኳትፊ “ለብዙ ቀናት ዚእኔ ሆነሜ ትቀመጫለሜ። አታመንዝሪፀ ኹሌላ ሰውም ጋር ግንኙነት አታድርጊፀ እኔም ኚአንቺ ጋር ግንኙነት አልፈጜምም።”
ምክንያቱም ዚእስራኀል ሕዝብ ለሹጅም ጊዜ ያለንጉሥ፣ ያለገዢ፣ ያለመሥዋዕት፣ ያለዓምድ፣ ያለኀፉድና ያለተራፊም ምስል ይኖራሉ።
ኚዚያም በኋላ ዚእስራኀል ሕዝብ ተመልሰው አምላካ቞ውን ይሖዋንና ንጉሣ቞ውን ዳዊትን ይፈልጋሉፀ በዘመኑም መጚሚሻ ወደ ይሖዋና ወደ ጥሩነቱ እዚተንቀጠቀጡ ይመጣሉ።
“እስራኀል ሆይ፣ ሐሎት አታድርግፀእንደ ሌሎቹ ሕዝቊቜ ደስ አይበልህ። ምንዝር በመፈጾም ኹአምላክህ ርቀሃልና። በዚእህል አውድማ ላይ ለዝሙት አዳሪ ዹሚኹፈለውን ደሞዝ ወደኞዋል።
ሆኖም ዚእህል አውድማውና ዹወይን መጭመቂያው አይመግባ቞ውምፀአዲሱም ዹወይን ጠጅ ይቋሚጥባ቞ዋል።
በይሖዋ ምድር ላይ አይኖሩምፀይልቁንም ኀፍሬም ወደ ግብፅ ይመለሳልፀበአሊርም ዹሹኹሰ ነገር ይበላሉ።
ኚእንግዲህ ለይሖዋ ዹወይን ጠጅ መባ አያፈሱምፀመሥዋዕታ቞ውም አያስደስተውም። እንደ እዝን እንጀራ ና቞ውፀዚሚበሉትም ሁሉ ራሳ቞ውን ያሚክሳሉ። ምግባ቞ው ለራሳ቞ው ብቻ ነውናፀወደ ይሖዋ ቀት አይገባም።
ዚምትሰበሰቡበትና ለይሖዋ በዓል ዚምታኚብሩበት ቀን ሲደርስምን ታደርጉ ይሆን?
እነሆ፣ ምድሪቱ በመውደሟ ለመሞሜ ይገደዳሉ። ግብፅ ትሰበስባ቞ዋለቜፀ ሜምፊስ ደግሞ ትቀብራ቞ዋለቜ። ኚብር ዚተሠሩ ውድ ንብሚቶቻ቞ውን ሳማ ይወርሰዋልፀበድንኳኖቻ቞ውም ውስጥ እሟሃማ ቁጥቋጊ ይበቅላል።
ምርመራ ዚሚካሄድበት ጊዜ ይመጣልፀዚበቀል ቀን ይመጣልፀእስራኀልም ይህን ይወቅ! ዚእነሱ ነቢይ ሞኝ፣ በመንፈስ ዹሚናገሹውም ሰው እንደ እብድ ይሆናልፀምክንያቱም በደልህ ብዙ ነውፀ በአንተም ላይ ዹሚደርሰው ጥላቻ በዝቷል።”
ዚኀፍሬም ጠባቂ ኚአምላኬ ጋር ነበር። አሁን ግን ዚነቢያቱ መንገዶቜ ሁሉ እንደ ወፍ አዳኝ ወጥመዶቜ ና቞ውፀበአምላኩ ቀት ጠላትነት አለ።
በጊብዓ ዘመን እንደነበሚው፣ ጥፋት በሚያስኚትሉ ነገሮቜ ተዘፍቀዋል። እሱ በደላቾውን ያስባልፀ በሠሩትም ኃጢአት ዚተነሳ ይቀጣ቞ዋል።
“እስራኀልን በምድሚ በዳ እንዳለ ወይን ሆኖ አገኘሁት። አባቶቻቜሁን ለመጀመሪያ ጊዜ ባፈራ ዚበለስ ዛፍ ላይ እንደ ጎመራ ዚበለስ ፍሬ ሆነው አዚኋ቞ው። ሆኖም ወደ ፌጎር ባአል ሄዱፀለአሳፋሪውም ነገር ራሳ቞ውን አሳልፈው ሰጡፀእንደወደዱትም ነገር አስጞያፊዎቜ ሆኑ።
ዚኀፍሬም ክብር እንደ ወፍ በሮ ይጠፋልፀመውለድ፣ ማርገዝም ሆነ መፀነስ ዚለም።
ልጆቜ ቢያሳድጉም እንኳአንድም ሰው እስኚማይቀር ድሚስ ዚወላድ መሃን አደርጋ቞ዋለሁፀአዎ፣ ኚእነሱ በራቅኩ ጊዜ ወዮላ቞ው!
በግጊሜ ስፍራ ዹተተኹለው ኀፍሬም ለእኔ እንደ ጢሮስ ነበርፀአሁን ግን ኀፍሬም ልጆቹን ለእርድ አሳልፎ ይሰጣል።”
ይሖዋ ሆይ፣ ልትሰጣ቞ው ዚሚገባውን ስጣ቞ውፀዚሚጚነግፍ ማህፀንና ዹደሹቁ ጡቶቜ ስጣ቞ው።
“ክፉ ድርጊታ቞ውን ሁሉ በጊልጋል ፈጞሙፀ እኔም በዚያ ጠላኋ቞ው። በሠሩት ክፉ ድርጊት ዚተነሳ ኚቀ቎ አባርራ቞ዋለሁ። ኚእንግዲህ ወዲያ ፍቅሬን እነፍጋ቞ዋለሁፀአለቆቻ቞ው ሁሉ እልኞኞቜ ና቞ው።
ኀፍሬም ጉዳት ይደርስበታል። ሥራ቞ው ይደርቃልፀ አንዳቜም ፍሬ አያፈሩም። ቢወልዱ እንኳ ዚሚወዷ቞ውን ልጆቻ቞ውን እገድላለሁ።”
እሱን ስላልሰሙትአምላኬ ይተዋ቞ዋልፀበብሔራትም መካኚል ተንኚራታቜ ይሆናሉ።
“ወንድሞቻቜሁን ‘ሕዝቀ!’ እህቶቻቜሁን ደግሞ ‘ምሕሚት ዚተደሚገልሜ ሎት!’ በሏ቞ው።
እናታቜሁን ክሰሷትፀ እሷ ሚስ቎ ስላልሆነቜ፣እኔም ባሏ ስላልሆንኩ ክሰሷት። ኚእሷ ዘንድ ዘማዊነቷን፣ኚጡቶቿም መካኚል ምንዝሯን ታስወግድፀ
አለዚያ ራቁቷን አስቀራታለሁፀ በተወለደቜበት ቀን እንደነበሚቜውም አደርጋታለሁፀእንደ ምድሚ በዳ፣ውኃ እንደሌለበትም ምድር አደርጋታለሁፀበውኃ ጥምም እገድላታለሁ።
ወንዶቜ ልጆቿ ዹምንዝር ልጆቜ ስለሆኑምሕሚት አላደርግላ቞ውም።
እናታ቞ው አመንዝራለቜና። እነሱን ዚፀነሰቜው ሎት አሳፋሪ ድርጊት ፈጜማለቜፀ‘አጥብቀው ዚሚወዱኝን፣ደግሞም ምግቀንና ውኃዬን፣ዚሱፍ ልብሎንና በፍታዬን እንዲሁም ዘይቮንና መጠጀን ዚሚሰጡኝን ተኚትዬ እሄዳለሁ’ ብላለቜና።
ስለዚህ መንገዷን በእሟህ አጥር እዘጋለሁፀመውጫ መንገድ እንዳታገኝምዙሪያዋን በድንጋይ አጥራለሁ።
አጥብቀው ዚሚወዷትን ተኚትላ ትሄዳለቜፀ ሆኖም አትደርስባ቞ውምፀትፈልጋ቞ዋለቜፀ ሆኖም አታገኛ቞ውም። ኚዚያም ‘ተመልሌ ወደ መጀመሪያው ባሌ እሄዳለሁፀኚአሁኑ ኑሮዬ ይልቅ ዚበፊቱ ይሻለኛልና’ ትላለቜ።
እህሉን፣ አዲሱን ዹወይን ጠጅና ዘይቱን ዚሰጠኋትእንዲሁም ለባአል አምልኮ ዚተጠቀሙበትን ብርና ወርቅበብዛት እንድታገኝ ያደሚግኩት እኔ እንደሆንኩ አልተገነዘበቜም።
‘ስለዚህ ሐሳቀን ቀይሬ፣ እህሌን በጊዜው፣አዲሱን ዹወይን ጠጄንም በወቅቱ እወስዳለሁፀእርቃኗን ዚምትሞፍንበትንም ዚሱፍ ልብሎንና በፍታዬን እነጥቃታለሁ።
አሁንም ኀፍሹተ ሥጋዋን አጥብቀው በሚወዷት ፊት እገልጣለሁፀኚእጄም ዚሚያስጥላት ሰው አይኖርም።
ደስታዋን፣ በዓሏን፣ ዹወር መባቻዋንና ሰንበቷን ሁሉእንዲሁም ዚተወሰኑትን ዹበዓል ወቅቶቿን ሁሉ አስቀራለሁ።
“አጥብቀው ዚሚወዱኝ ውሜሞቌ ለእኔ ዚሰጡኝ ደሞዜ ናቾው” ዚምትላ቞ውን ዹወይን ተክሏንና ዚበለስ ዛፏን አወድማለሁፀጫካም አደርጋ቞ዋለሁፀዚዱር አራዊትም ይበሏ቞ዋል።
ለባአል ምስሎቜ መሥዋዕት ባቀሚበቜባ቞ው፣ በጉትቻዋና በጌጊቿ በተንቆጠቆጠቜባ቞ውእንዲሁም አጥብቀው ዚሚወዷትን በተኚተለቜባ቞ው ቀናት ዚተነሳ ተጠያቂ አደርጋታለሁፀእኔንም ሚስታኝ ነበር’ ይላል ይሖዋ።
‘ስለዚህ አግባብቌ አሳምናታለሁፀወደ ምድሚ በዳ እመራታለሁፀልቧን በሚማርክ መንገድ አናግራታለሁ።
ኚዚያን ጊዜ አንስቶ ዹወይን እርሻዎቿን መልሌ እሰጣታለሁፀዚአኮርም ሾለቆ ዚተስፋ በር እንዲሆናት አደርጋለሁፀበዚያም እንደ ልጅነቷ ጊዜናኚግብፅ ምድር እንደወጣቜበት ቀን መልስ ትሰጠኛለቜ።
በዚያም ቀን’ ይላል ይሖዋ፣‘ባሌ ብለሜ ትጠሪኛለሜፀ ኚእንግዲህ ጌታዬ ብለሜ አትጠሪኝም።’
‘ዚባአልን ምስሎቜ ስሞቜ ኚአንደበቷ አስወግዳለሁፀስማ቞ውም ኚእንግዲህ አይታወስም።
በዚያም ቀን ለእነሱ ጥቅም ስል ኚዱር አራዊት፣ኚሰማይ ወፎቜና መሬት ለመሬት ኚሚሳቡ ፍጥሚታት ጋር ቃል ኪዳን አደርጋለሁፀቀስትን፣ ሰይፍንና ጊርነትን ኚምድሪቱ አስወግዳለሁፀያለስጋት እንዲያርፉም አደርጋለሁ።
ለዘላለም አጭሻለሁፀበጜድቅ፣ በፍትሕ፣ በታማኝ ፍቅርናበምሕሚት አጭሻለሁ።
በታማኝነት አጭሻለሁፀአንቺም በእርግጥ ይሖዋን ታውቂያለሜ።’
‘በዚያም ቀን መልስ እሰጣለሁ’ ይላል ይሖዋፀ‘ለሰማያት መልስ እሰጣለሁፀእነሱ ደግሞ ለምድር መልስ ይሰጣሉፀ
ምድር ደግሞ ለእህሉ፣ ለአዲሱ ዹወይን ጠጅና ለዘይቱ መልስ ትሰጣለቜፀእነሱም ለኢይዝራኀል መልስ ይሰጣሉ።
በምድር ላይ ለራሎ እንደ ዘር እዘራታለሁፀደግሞም ምሕሚት ላልተደሚገላት ለእሷ ምሕሚት አደርግላታለሁፀሕዝቀ ያልሆኑትን “እናንተ ሕዝቀ ናቜሁ” እላ቞ዋለሁፀ እነሱ ደግሞ “አንተ አምላኬ ነህ” ይላሉ።’”
“እስራኀል ፍሬ ዚሚሰጥ እዚተበላሞ ያለ ወይን ነው። ፍሬው በበዛ መጠን መሠዊያዎቹንም በዚያው ልክ አበዛፀምድሩ ዚተሻለ ምርት ባስገኘ መጠን ይበልጥ ያማሩ ዚማምለኪያ ዓምዶቜን ሠራ።
ልባ቞ው ግብዝ ነውፀበመሆኑም በደለኞቜ ና቞ው። መሠዊያዎቻ቞ውን ዚሚሰባብር፣ ዓምዶቻ቞ውንም ዚሚያፈራርስ አለ።
እነሱም ‘ንጉሥ ዚለንምፀ ይሖዋን አልፈራንምና። ንጉሥ ቢኖሚንስ ምን ሊያደርግልን ይቜላል?’ ይላሉ።
ኚንቱ ቃል ይናገራሉፀ በሐሰት ይምላሉፀ ቃል ኪዳንም ይገባሉፀስለዚህ ዹሚፈሹደው ፍርድ በእርሻ ትልም ውስጥ እንዳለ መርዛማ አሹም ነው።
ዚሰማርያ ነዋሪዎቜ በቀትአዌን ስላለው ዚጥጃ ጣዖት ስጋት ያድርባ቞ዋል። ሕዝቡም ሆኑ በእሱና በክብሩ ሐሎት ያደሚጉት ዚባዕድ አምላክ ካህናትለእሱ ያዝናሉፀኚእነሱ ተለይቶ በግዞት ይወሰዳልና።
ለአንድ ታላቅ ንጉሥ እንደሚቀርብ ስጊታ ወደ አሩር ይወሰዳል። ኀፍሬም ውርደት ይኚናነባልፀእስራኀልም በተኹተለው ምክር ዚተነሳ ያፍራል።
ሰማርያና ንጉሥዋ ተቆርጩ ውኃ ላይ እንደወደቀ ቅርንጫፍተጠራርገው ይጠፋሉ።
ዚእስራኀል ኃጢአት ዚሆኑት በቀትአዌን ዹሚገኙ ኹፍ ያሉ ዚማምለኪያ ቊታዎቜ ይወድማሉ። መሠዊያዎቻ቞ውን እሟህና አሜኬላ ይወርሷ቞ዋል። ሰዎቜ ተራሮቹን ‘ሞሜጉን!’ ኮሚብቶቹንም ‘በላያቜን ውደቁ!’ ይሏ቞ዋል።
ዚእስራኀል ሰዎቜ ሆይ፣ ኚጊብዓ ዘመን ጀምሮ ኃጢአት ሠርታቜኋል። እነሱ በዚያ ጞንተዋል። በጊብዓ ዚተካሄደው ጊርነት ዹዓመፅን ልጆቜ አልፈጃ቞ውም።
በፈለግኩ ጊዜ እገሥጻ቞ዋለሁ። ሁለቱ በደሎቻ቞ው በላያ቞ው በሚጫኑበት ጊዜሕዝቊቜ በእነሱ ላይ ይሰበሰባሉ።
ኀፍሬም ማበራዚት ዚምትወድ ዚተገራቜ ጊደር ነውፀበመሆኑም ያማሚ አንገቷን አተሚፍኩ። ሰውም ኀፍሬምን እንዲጋልብ አደርጋለሁ። ይሁዳ ያርሳልፀ ያዕቆብም መሬቱን ለእሱ ያለሰልሳል።
ለራሳቜሁ ዚጜድቅን ዘር ዝሩፀ ታማኝ ፍቅርንም እጚዱ። ይሖዋን መፈለግ ዚምትቜሉበት ጊዜ ኹማለፉ በፊት፣እሱም መጥቶ በጜድቅ መመሪያ እስኪሰጣቜሁ ድሚስያልለማውን መሬት ለራሳቜሁ እሚሱ።
እናንተ ግን ክፋትን አሚሳቜሁፀዓመፅን አጚዳቜሁፀዚማታለልንም ፍሬ በላቜሁፀበገዛ ራሳቜሁ መንገድ፣በተዋጊዎቻቜሁም ብዛት ታምናቜኋልና።
በሕዝባቜሁ ላይ ሁኚት ይነሳልፀእናቶቜ ኚልጆቻ቞ው ጋር በተጚፈጚፉበት ዚውጊያ ቀንሻልማን፣ ቀትአርቀልን እንዳወደመ ሁሉ፣ዚተመሞጉ ኚተሞቻቜሁ በሙሉ ይወድማሉ።
ቀ቎ል ሆይ፣ ክፋትሜ ታላቅ ስለሆነ እንዲሁ ይደሚግብሻል። ጎህ ሲቀድ ዚእስራኀል ንጉሥ ፈጜሞ ይጠፋል።”
“እናንተ ካህናት፣ ይህን ስሙፀእናንተ ዚእስራኀል ቀት ሰዎቜ፣ በትኩሚት አዳምጡፀእናንተም ዚንጉሡ ቀት ሰዎቜ፣ አዳምጡፀፍርዱ እናንተንም ይጚምራልናፀምክንያቱም ለምጜጳ ወጥመድ፣በታቊርም ላይ ዹተዘሹጋ መሚብ ሆናቜኋል።
ኚትክክለኛው መንገድ ዚራቁት ሰዎቜ ደም በማፍሰስ ወንጀል ተዘፍቀዋልፀእኔም ለሁሉም ማስጠንቀቂያ እሰጣለሁ።
ኀፍሬምን አውቀዋለሁፀእስራኀልም ኚእኔ ዹተሰወሹ አይደለም። ኀፍሬም ሆይ፣ አሁን አንተ ሮሰኛ ሆነሃልፀእስራኀል ራሱን አርክሷል።