text
stringlengths
4
267
ለይሁዳ ቤት ግን ምሕረት አደርጋለሁ፤ በቀስት፣ በሰይፍ፣ በጦርነት፣ በፈረሶች ወይም በፈረሰኞች ሳይሆን በአምላካቸው በይሖዋ አድናቸዋለሁ።”
ጎሜር፣ ሎሩሃማን ጡት ካስጣለች በኋላ ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደች።
ከዚያም አምላክ እንዲህ አለው፦ “ልጁን ሎአሚ ብለህ ጥራው፤ ምክንያቱም እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም፤ እኔም አምላካችሁ አይደለሁም።
“የእስራኤልም ሕዝብ ብዛት ሊሰፈር ወይም ሊቆጠር እንደማይችል እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናል። ‘ሕዝቤ አይደላችሁም’ ተብሎ በተነገራቸው ስፍራም ‘የሕያው አምላክ ልጆች’ ይባላሉ።
የይሁዳና የእስራኤል ሕዝብ ተሰብስበው አንድ ይሆናሉ፤ ለራሳቸውም አንድ መሪ ይሾማሉ፤ ከምድሪቱም ይወጣሉ፤ የኢይዝራኤል ቀን ታላቅ ይሆናልና።
“እስራኤልን ለመፈወስ በሞከርኩ ቁጥርየኤፍሬም በደል፣የሰማርያም ክፋት ይገለጣል። እነሱ ያታልላሉና፤ሌቦች ሰብረው ይገባሉ፤ የወራሪዎች ቡድን በውጭ ጥቃት ይሰነዝራል።
እነሱ ግን ክፉ ድርጊታቸውን ሁሉ እንደማስታውስ ልብ አይሉም። የገዛ ድርጊታቸው ከቧቸዋል፤የሠሩት ሥራ ሁሉ በፊቴ ነው።
ንጉሡን በክፋታቸው፣መኳንንቱንም አታላይ በሆነ ድርጊታቸው ያስደስታሉ።
ሁሉም አመንዝሮች ናቸው፤አንድ ዳቦ ጋጋሪ እሳቱን አንዴ ካቀጣጠለው በኋላ፣ያቦካው ሊጥ ኩፍ እስኪል ድረስ እሳቱን መቆስቆስ እንደማያስፈልገው የጋለ ምድጃ ናቸው።
በንጉሣችን ክብረ በዓል ቀን፣ መኳንንቱ ታመሙ፤በወይን ጠጅ የተነሳ በቁጣ ተሞሉ። ንጉሡ ለፌዘኞች እጁን ዘረጋ።
እንደ ምድጃ የሚነድ ልብ ይዘው ይቀርባሉና። ዳቦ ጋጋሪው ሌሊቱን ሙሉ ይተኛል፤በማለዳ ምድጃው እንደሚንበለበል እሳት ይንቀለቀላል።
ሁሉም እንደ ምድጃ የጋሉ ናቸው፤ገዢዎቻቸውንም ይውጣሉ። ነገሥታታቸው ሁሉ ወድቀዋል፤ከእነሱ መካከል ወደ እኔ የሚጮኽ ማንም የለም።
ኤፍሬም ከብሔራት ጋር ይቀላቀላል። እሱ እንዳልተገላበጠ ቂጣ ነው።
እንግዶች ጉልበቱን በዘበዙ፤ እሱ ግን ይህን አላወቀም። ራሱንም ሽበት ወረሰው፤ እሱ ግን ይህን ልብ አላለም።
የእስራኤል ኩራት በራሱ ላይ መሥክሮበታል፤ይህም ሁሉ ሆኖ ወደ አምላካቸው ወደ ይሖዋ አልተመለሱም፤እሱንም አልፈለጉትም።
ኤፍሬም ማስተዋል እንደሌላት ሞኝ ርግብ ነው። ግብፅን ተጣሩ፤ ወደ አሦርም ሄዱ።
የትም ቢሄዱ መረቤን በላያቸው እዘረጋለሁ። እንደ ሰማይ ወፎች ወደ ታች አወርዳቸዋለሁ። ለጉባኤያቸው በሰጠሁት ማስጠንቀቂያ መሠረት እገሥጻቸዋለሁ።
ከእኔ ስለሸሹ ወዮላቸው! በእኔ ላይ በደል ስለፈጸሙ ጥፋት ይምጣባቸው! እነሱን ለመዋጀት ዝግጁ ነበርኩ፤ እነሱ ግን በእኔ ላይ ውሸት ተናገሩ።
በአልጋቸው ላይ ሆነው ዋይ ዋይ ቢሉምእርዳታ ለማግኘት ከልባቸው ወደ እኔ አልጮኹም። ለእህላቸውና ለአዲስ ወይናቸው ሲሉ ሰውነታቸውን ይተለትላሉ፤በእኔም ላይ ዓመፁ።
ያሠለጠንኳቸውና ክንዳቸውን ያበረታሁ ቢሆንምክፉ ነገር በማሴር በእኔ ላይ ተነስተዋል።
አካሄዳቸውን ለወጡ፤ ከፍ ወዳለ ነገር ግን አይደለም፤ጅማቱ እንደረገበ ደጋን እምነት የማይጣልባቸው ሆነዋል። አለቆቻቸው እብሪተኛ ከሆነው አንደበታቸው የተነሳ በሰይፍ ይወድቃሉ። በዚህም ምክንያት በግብፅ ምድር መሳለቂያ ይሆናሉ።”
“ኤፍሬም በተናገረ ጊዜ ሰዎች ተንቀጠቀጡ፤በእስራኤል ነገዶች መካከል ትልቅ ቦታ ነበረው። ሆኖም ባአልን በማምለክ በደል በመፈጸሙ ሞተ።
አሁንም ተጨማሪ ኃጢአት ይሠራሉ፤በብራቸውም ለራሳቸው የብረት ምስሎች ይሠራሉ፤በጥበብ ጣዖቶችን ያበጃሉ፤ ሁሉም የእጅ ጥበብ ባለሙያ የሠራቸው ናቸው። ‘መሥዋዕት የሚያቀርቡት ሰዎች ጥጃዎቹን ይሳሙ’ በማለት ለእነሱ ይናገራሉ።
ስለዚህ እንደ ማለዳ ጉም፣ወዲያው እንደሚጠፋም ጤዛ ይሆናሉ፤አውሎ ነፋስ ከአውድማ ላይ ጠራርጎ እንደሚወስደው እብቅ፣በጭስ ማውጫም በኩል እንደሚወጣ ጭስ ይሆናሉ።
ይሁንና ከግብፅ ምድር አንስቶ እኔ አምላክህ ይሖዋ ነኝ፤ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ አታውቅም ነበር፤ከእኔም ሌላ አዳኝ የለም።
እኔ በምድረ በዳ፣ ድርቅ ባለበትም ምድር ተንከባከብኩህ።
በግጦሽ መሬታቸው ላይ ከበሉ በኋላ ጠገቡ፤በጠገቡም ጊዜ ልባቸው ታበየ። ከዚህም የተነሳ ረሱኝ።
ስለዚህ እንደ አንበሳ፣በመንገድም ዳር እንደሚያደባ ነብር እሆንባቸዋለሁ።
ግልገሎቿን እንደተነጠቀች ድብ ሆኜ እመጣባቸዋለሁ፤ደረታቸውንም እዘነጥላለሁ። በዚያ እንደ አንበሳ እውጣቸዋለሁ፤የዱር አውሬ ይቦጫጭቃቸዋል።
እስራኤል ሆይ፣ በእኔ ላይ ስለተነሳህ፣ረዳትህንም ስለተቃወምክ ያጠፋሃል።
‘ንጉሥና መኳንንት ስጠኝ’ ብለህ ነበር፤ታዲያ በከተሞችህ ሁሉ ያድንህ ዘንድንጉሥህ የት አለ? ገዢዎችህስ የት አሉ?
እኔም ተቆጥቼ ንጉሥ ሰጠሁህ፤በታላቅ ቁጣዬም አስወግደዋለሁ።
የኤፍሬም በደል ታሽጎ ተቀምጧል፤ኃጢአቱም ተከማችቷል።
ምጥ እንደያዛት ሴት ይሆናል። እሱ ግን ጥበበኛ ልጅ አይደለም፤የሚወለድበት ጊዜ ሲደርስ በቦታው ላይ አይገኝም።
ከመቃብር እጅ እዋጃቸዋለሁ፤ከሞትም እታደጋቸዋለሁ። ሞት ሆይ፣ መንደፊያህ የት አለ? መቃብር ሆይ፣ አጥፊነትህ የት አለ? ርኅራኄ ከዓይኔ ፊት ይሰወራል።
በቄጠማዎች መካከል ተመችቶት ቢያድግ እንኳየምሥራቅ ነፋስ ይኸውም የይሖዋ ነፋስ ይመጣል፤የውኃ ጉድጓዱ እንዲደርቅ፣ ምንጩም እንዲነጥፍ ለማድረግ ከበረሃ ይመጣል። ውድ የሆኑ ንብረቶቹ ሁሉ የሚገኙበትን ግምጃ ቤቱን ይበዘብዛል።
ሰማርያ በአምላኳ ላይ ስላመፀች ተጠያቂ ትሆናለች። በሰይፍ ይወድቃሉ፤ልጆቻቸው ይፈጠፈጣሉ፤የእርጉዝ ሴቶቻቸውም ሆድ ይቀደዳል።”
ከዚያም ይሖዋ እንዲህ አለኝ፦ “የእስራኤል ሕዝብ ሌሎች አማልክትን የሚከተሉና የዘቢብ ቂጣ የሚወዱ ሆነው ሳለ ይሖዋ እንደወደዳቸው ሁሉ፣ አንተም ሄደህ በሌላ ሰው የተወደደችውንና ምንዝር የምትፈጽመውን ሴት ዳግመኛ ውደዳት።”
በመሆኑም በ15 የብር ሰቅልና በአንድ ተኩል የሆሜር መስፈሪያ ገብስ ለራሴ ገዛኋት።
ከዚያም እንዲህ አልኳት፦ “ለብዙ ቀናት የእኔ ሆነሽ ትቀመጫለሽ። አታመንዝሪ፤ ከሌላ ሰውም ጋር ግንኙነት አታድርጊ፤ እኔም ከአንቺ ጋር ግንኙነት አልፈጽምም።”
ምክንያቱም የእስራኤል ሕዝብ ለረጅም ጊዜ ያለንጉሥ፣ ያለገዢ፣ ያለመሥዋዕት፣ ያለዓምድ፣ ያለኤፉድና ያለተራፊም ምስል ይኖራሉ።
ከዚያም በኋላ የእስራኤል ሕዝብ ተመልሰው አምላካቸውን ይሖዋንና ንጉሣቸውን ዳዊትን ይፈልጋሉ፤ በዘመኑም መጨረሻ ወደ ይሖዋና ወደ ጥሩነቱ እየተንቀጠቀጡ ይመጣሉ።
“እስራኤል ሆይ፣ ሐሴት አታድርግ፤እንደ ሌሎቹ ሕዝቦች ደስ አይበልህ። ምንዝር በመፈጸም ከአምላክህ ርቀሃልና። በየእህል አውድማ ላይ ለዝሙት አዳሪ የሚከፈለውን ደሞዝ ወደኸዋል።
ሆኖም የእህል አውድማውና የወይን መጭመቂያው አይመግባቸውም፤አዲሱም የወይን ጠጅ ይቋረጥባቸዋል።
በይሖዋ ምድር ላይ አይኖሩም፤ይልቁንም ኤፍሬም ወደ ግብፅ ይመለሳል፤በአሦርም የረከሰ ነገር ይበላሉ።
ከእንግዲህ ለይሖዋ የወይን ጠጅ መባ አያፈሱም፤መሥዋዕታቸውም አያስደስተውም። እንደ እዝን እንጀራ ናቸው፤የሚበሉትም ሁሉ ራሳቸውን ያረክሳሉ። ምግባቸው ለራሳቸው ብቻ ነውና፤ወደ ይሖዋ ቤት አይገባም።
የምትሰበሰቡበትና ለይሖዋ በዓል የምታከብሩበት ቀን ሲደርስምን ታደርጉ ይሆን?
እነሆ፣ ምድሪቱ በመውደሟ ለመሸሽ ይገደዳሉ። ግብፅ ትሰበስባቸዋለች፤ ሜምፊስ ደግሞ ትቀብራቸዋለች። ከብር የተሠሩ ውድ ንብረቶቻቸውን ሳማ ይወርሰዋል፤በድንኳኖቻቸውም ውስጥ እሾሃማ ቁጥቋጦ ይበቅላል።
ምርመራ የሚካሄድበት ጊዜ ይመጣል፤የበቀል ቀን ይመጣል፤እስራኤልም ይህን ይወቅ! የእነሱ ነቢይ ሞኝ፣ በመንፈስ የሚናገረውም ሰው እንደ እብድ ይሆናል፤ምክንያቱም በደልህ ብዙ ነው፤ በአንተም ላይ የሚደርሰው ጥላቻ በዝቷል።”
የኤፍሬም ጠባቂ ከአምላኬ ጋር ነበር። አሁን ግን የነቢያቱ መንገዶች ሁሉ እንደ ወፍ አዳኝ ወጥመዶች ናቸው፤በአምላኩ ቤት ጠላትነት አለ።
በጊብዓ ዘመን እንደነበረው፣ ጥፋት በሚያስከትሉ ነገሮች ተዘፍቀዋል። እሱ በደላቸውን ያስባል፤ በሠሩትም ኃጢአት የተነሳ ይቀጣቸዋል።
“እስራኤልን በምድረ በዳ እንዳለ ወይን ሆኖ አገኘሁት። አባቶቻችሁን ለመጀመሪያ ጊዜ ባፈራ የበለስ ዛፍ ላይ እንደ ጎመራ የበለስ ፍሬ ሆነው አየኋቸው። ሆኖም ወደ ፌጎር ባአል ሄዱ፤ለአሳፋሪውም ነገር ራሳቸውን አሳልፈው ሰጡ፤እንደወደዱትም ነገር አስጸያፊዎች ሆኑ።
የኤፍሬም ክብር እንደ ወፍ በሮ ይጠፋል፤መውለድ፣ ማርገዝም ሆነ መፀነስ የለም።
ልጆች ቢያሳድጉም እንኳአንድም ሰው እስከማይቀር ድረስ የወላድ መሃን አደርጋቸዋለሁ፤አዎ፣ ከእነሱ በራቅኩ ጊዜ ወዮላቸው!
በግጦሽ ስፍራ የተተከለው ኤፍሬም ለእኔ እንደ ጢሮስ ነበር፤አሁን ግን ኤፍሬም ልጆቹን ለእርድ አሳልፎ ይሰጣል።”
ይሖዋ ሆይ፣ ልትሰጣቸው የሚገባውን ስጣቸው፤የሚጨነግፍ ማህፀንና የደረቁ ጡቶች ስጣቸው።
“ክፉ ድርጊታቸውን ሁሉ በጊልጋል ፈጸሙ፤ እኔም በዚያ ጠላኋቸው። በሠሩት ክፉ ድርጊት የተነሳ ከቤቴ አባርራቸዋለሁ። ከእንግዲህ ወዲያ ፍቅሬን እነፍጋቸዋለሁ፤አለቆቻቸው ሁሉ እልኸኞች ናቸው።
ኤፍሬም ጉዳት ይደርስበታል። ሥራቸው ይደርቃል፤ አንዳችም ፍሬ አያፈሩም። ቢወልዱ እንኳ የሚወዷቸውን ልጆቻቸውን እገድላለሁ።”
እሱን ስላልሰሙትአምላኬ ይተዋቸዋል፤በብሔራትም መካከል ተንከራታች ይሆናሉ።
“ወንድሞቻችሁን ‘ሕዝቤ!’ እህቶቻችሁን ደግሞ ‘ምሕረት የተደረገልሽ ሴት!’ በሏቸው።
እናታችሁን ክሰሷት፤ እሷ ሚስቴ ስላልሆነች፣እኔም ባሏ ስላልሆንኩ ክሰሷት። ከእሷ ዘንድ ዘማዊነቷን፣ከጡቶቿም መካከል ምንዝሯን ታስወግድ፤
አለዚያ ራቁቷን አስቀራታለሁ፤ በተወለደችበት ቀን እንደነበረችውም አደርጋታለሁ፤እንደ ምድረ በዳ፣ውኃ እንደሌለበትም ምድር አደርጋታለሁ፤በውኃ ጥምም እገድላታለሁ።
ወንዶች ልጆቿ የምንዝር ልጆች ስለሆኑምሕረት አላደርግላቸውም።
እናታቸው አመንዝራለችና። እነሱን የፀነሰችው ሴት አሳፋሪ ድርጊት ፈጽማለች፤‘አጥብቀው የሚወዱኝን፣ደግሞም ምግቤንና ውኃዬን፣የሱፍ ልብሴንና በፍታዬን እንዲሁም ዘይቴንና መጠጤን የሚሰጡኝን ተከትዬ እሄዳለሁ’ ብላለችና።
ስለዚህ መንገዷን በእሾህ አጥር እዘጋለሁ፤መውጫ መንገድ እንዳታገኝምዙሪያዋን በድንጋይ አጥራለሁ።
አጥብቀው የሚወዷትን ተከትላ ትሄዳለች፤ ሆኖም አትደርስባቸውም፤ትፈልጋቸዋለች፤ ሆኖም አታገኛቸውም። ከዚያም ‘ተመልሼ ወደ መጀመሪያው ባሌ እሄዳለሁ፤ከአሁኑ ኑሮዬ ይልቅ የበፊቱ ይሻለኛልና’ ትላለች።
እህሉን፣ አዲሱን የወይን ጠጅና ዘይቱን የሰጠኋትእንዲሁም ለባአል አምልኮ የተጠቀሙበትን ብርና ወርቅበብዛት እንድታገኝ ያደረግኩት እኔ እንደሆንኩ አልተገነዘበችም።
‘ስለዚህ ሐሳቤን ቀይሬ፣ እህሌን በጊዜው፣አዲሱን የወይን ጠጄንም በወቅቱ እወስዳለሁ፤እርቃኗን የምትሸፍንበትንም የሱፍ ልብሴንና በፍታዬን እነጥቃታለሁ።
አሁንም ኀፍረተ ሥጋዋን አጥብቀው በሚወዷት ፊት እገልጣለሁ፤ከእጄም የሚያስጥላት ሰው አይኖርም።
ደስታዋን፣ በዓሏን፣ የወር መባቻዋንና ሰንበቷን ሁሉእንዲሁም የተወሰኑትን የበዓል ወቅቶቿን ሁሉ አስቀራለሁ።
“አጥብቀው የሚወዱኝ ውሽሞቼ ለእኔ የሰጡኝ ደሞዜ ናቸው” የምትላቸውን የወይን ተክሏንና የበለስ ዛፏን አወድማለሁ፤ጫካም አደርጋቸዋለሁ፤የዱር አራዊትም ይበሏቸዋል።
ለባአል ምስሎች መሥዋዕት ባቀረበችባቸው፣ በጉትቻዋና በጌጦቿ በተንቆጠቆጠችባቸውእንዲሁም አጥብቀው የሚወዷትን በተከተለችባቸው ቀናት የተነሳ ተጠያቂ አደርጋታለሁ፤እኔንም ረስታኝ ነበር’ ይላል ይሖዋ።
‘ስለዚህ አግባብቼ አሳምናታለሁ፤ወደ ምድረ በዳ እመራታለሁ፤ልቧን በሚማርክ መንገድ አናግራታለሁ።
ከዚያን ጊዜ አንስቶ የወይን እርሻዎቿን መልሼ እሰጣታለሁ፤የአኮርም ሸለቆ የተስፋ በር እንዲሆናት አደርጋለሁ፤በዚያም እንደ ልጅነቷ ጊዜናከግብፅ ምድር እንደወጣችበት ቀን መልስ ትሰጠኛለች።
በዚያም ቀን’ ይላል ይሖዋ፣‘ባሌ ብለሽ ትጠሪኛለሽ፤ ከእንግዲህ ጌታዬ ብለሽ አትጠሪኝም።’
‘የባአልን ምስሎች ስሞች ከአንደበቷ አስወግዳለሁ፤ስማቸውም ከእንግዲህ አይታወስም።
በዚያም ቀን ለእነሱ ጥቅም ስል ከዱር አራዊት፣ከሰማይ ወፎችና መሬት ለመሬት ከሚሳቡ ፍጥረታት ጋር ቃል ኪዳን አደርጋለሁ፤ቀስትን፣ ሰይፍንና ጦርነትን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ፤ያለስጋት እንዲያርፉም አደርጋለሁ።
ለዘላለም አጭሻለሁ፤በጽድቅ፣ በፍትሕ፣ በታማኝ ፍቅርናበምሕረት አጭሻለሁ።
በታማኝነት አጭሻለሁ፤አንቺም በእርግጥ ይሖዋን ታውቂያለሽ።’
‘በዚያም ቀን መልስ እሰጣለሁ’ ይላል ይሖዋ፤‘ለሰማያት መልስ እሰጣለሁ፤እነሱ ደግሞ ለምድር መልስ ይሰጣሉ፤
ምድር ደግሞ ለእህሉ፣ ለአዲሱ የወይን ጠጅና ለዘይቱ መልስ ትሰጣለች፤እነሱም ለኢይዝራኤል መልስ ይሰጣሉ።
በምድር ላይ ለራሴ እንደ ዘር እዘራታለሁ፤ደግሞም ምሕረት ላልተደረገላት ለእሷ ምሕረት አደርግላታለሁ፤ሕዝቤ ያልሆኑትን “እናንተ ሕዝቤ ናችሁ” እላቸዋለሁ፤ እነሱ ደግሞ “አንተ አምላኬ ነህ” ይላሉ።’”
“እስራኤል ፍሬ የሚሰጥ እየተበላሸ ያለ ወይን ነው። ፍሬው በበዛ መጠን መሠዊያዎቹንም በዚያው ልክ አበዛ፤ምድሩ የተሻለ ምርት ባስገኘ መጠን ይበልጥ ያማሩ የማምለኪያ ዓምዶችን ሠራ።
ልባቸው ግብዝ ነው፤በመሆኑም በደለኞች ናቸው። መሠዊያዎቻቸውን የሚሰባብር፣ ዓምዶቻቸውንም የሚያፈራርስ አለ።
እነሱም ‘ንጉሥ የለንም፤ ይሖዋን አልፈራንምና። ንጉሥ ቢኖረንስ ምን ሊያደርግልን ይችላል?’ ይላሉ።
ከንቱ ቃል ይናገራሉ፤ በሐሰት ይምላሉ፤ ቃል ኪዳንም ይገባሉ፤ስለዚህ የሚፈረደው ፍርድ በእርሻ ትልም ውስጥ እንዳለ መርዛማ አረም ነው።
የሰማርያ ነዋሪዎች በቤትአዌን ስላለው የጥጃ ጣዖት ስጋት ያድርባቸዋል። ሕዝቡም ሆኑ በእሱና በክብሩ ሐሴት ያደረጉት የባዕድ አምላክ ካህናትለእሱ ያዝናሉ፤ከእነሱ ተለይቶ በግዞት ይወሰዳልና።
ለአንድ ታላቅ ንጉሥ እንደሚቀርብ ስጦታ ወደ አሦር ይወሰዳል። ኤፍሬም ውርደት ይከናነባል፤እስራኤልም በተከተለው ምክር የተነሳ ያፍራል።
ሰማርያና ንጉሥዋ ተቆርጦ ውኃ ላይ እንደወደቀ ቅርንጫፍተጠራርገው ይጠፋሉ።
የእስራኤል ኃጢአት የሆኑት በቤትአዌን የሚገኙ ከፍ ያሉ የማምለኪያ ቦታዎች ይወድማሉ። መሠዊያዎቻቸውን እሾህና አሜኬላ ይወርሷቸዋል። ሰዎች ተራሮቹን ‘ሸሽጉን!’ ኮረብቶቹንም ‘በላያችን ውደቁ!’ ይሏቸዋል።
የእስራኤል ሰዎች ሆይ፣ ከጊብዓ ዘመን ጀምሮ ኃጢአት ሠርታችኋል። እነሱ በዚያ ጸንተዋል። በጊብዓ የተካሄደው ጦርነት የዓመፅን ልጆች አልፈጃቸውም።
በፈለግኩ ጊዜ እገሥጻቸዋለሁ። ሁለቱ በደሎቻቸው በላያቸው በሚጫኑበት ጊዜሕዝቦች በእነሱ ላይ ይሰበሰባሉ።
ኤፍሬም ማበራየት የምትወድ የተገራች ጊደር ነው፤በመሆኑም ያማረ አንገቷን አተረፍኩ። ሰውም ኤፍሬምን እንዲጋልብ አደርጋለሁ። ይሁዳ ያርሳል፤ ያዕቆብም መሬቱን ለእሱ ያለሰልሳል።
ለራሳችሁ የጽድቅን ዘር ዝሩ፤ ታማኝ ፍቅርንም እጨዱ። ይሖዋን መፈለግ የምትችሉበት ጊዜ ከማለፉ በፊት፣እሱም መጥቶ በጽድቅ መመሪያ እስኪሰጣችሁ ድረስያልለማውን መሬት ለራሳችሁ እረሱ።
እናንተ ግን ክፋትን አረሳችሁ፤ዓመፅን አጨዳችሁ፤የማታለልንም ፍሬ በላችሁ፤በገዛ ራሳችሁ መንገድ፣በተዋጊዎቻችሁም ብዛት ታምናችኋልና።
በሕዝባችሁ ላይ ሁከት ይነሳል፤እናቶች ከልጆቻቸው ጋር በተጨፈጨፉበት የውጊያ ቀንሻልማን፣ ቤትአርቤልን እንዳወደመ ሁሉ፣የተመሸጉ ከተሞቻችሁ በሙሉ ይወድማሉ።
ቤቴል ሆይ፣ ክፋትሽ ታላቅ ስለሆነ እንዲሁ ይደረግብሻል። ጎህ ሲቀድ የእስራኤል ንጉሥ ፈጽሞ ይጠፋል።”
“እናንተ ካህናት፣ ይህን ስሙ፤እናንተ የእስራኤል ቤት ሰዎች፣ በትኩረት አዳምጡ፤እናንተም የንጉሡ ቤት ሰዎች፣ አዳምጡ፤ፍርዱ እናንተንም ይጨምራልና፤ምክንያቱም ለምጽጳ ወጥመድ፣በታቦርም ላይ የተዘረጋ መረብ ሆናችኋል።
ከትክክለኛው መንገድ የራቁት ሰዎች ደም በማፍሰስ ወንጀል ተዘፍቀዋል፤እኔም ለሁሉም ማስጠንቀቂያ እሰጣለሁ።
ኤፍሬምን አውቀዋለሁ፤እስራኤልም ከእኔ የተሰወረ አይደለም። ኤፍሬም ሆይ፣ አሁን አንተ ሴሰኛ ሆነሃል፤እስራኤል ራሱን አርክሷል።