text
stringlengths
4
267
ዚርስቱን ቀሪዎቜ ኃጢአት ይቅር ዚሚል፣ በደላቾውንም ዚሚያልፍእንደ አንተ ያለ አምላክ ማን ነው? እሱ ለዘላለም አይቆጣምፀታማኝ ፍቅር በማሳዚት ደስ ይሰኛልና።
ዳግመኛ ምሕሚት ያሳዚናልፀ በደላቜንን በቁጥጥሩ ሥር ያደርጋል። ኃጢአታ቞ውን ሁሉ ወደ ጥልቅ ባሕር ትጥላለህ።
በጥንት ዘመን ለአባቶቻቜን በማልክላቾው መሠሚትለያዕቆብ ታማኝነትን፣ለአብርሃም ደግሞ ታማኝ ፍቅርን ታሳያለህ።
እንዲህ አልኩፊ “እናንተ ዚያዕቆብ መሪዎቜናዚእስራኀል ቀት ገዢዎቜ፣ እባካቜሁ ስሙ። ትክክል ዹሆነውን ነገር ማወቅ አይገባቜሁም?
ሆኖም እናንተ መልካም ዹሆነውን ትጠላላቜሁፀ ክፉ ዹሆነውን ደግሞ ትወዳላቜሁፀዚሕዝቀን ቆዳ ትገፍፋላቜሁፀ ሥጋ቞ውንም ኚአጥንቶቻ቞ው ትለያላቜሁ።
ዚሕዝቀንም ሥጋ ትበላላቜሁፀቆዳ቞ውንም ትገፍፋላቜሁፀአጥንቶቻ቞ውንም ትሰባብራላቜሁፀበድስት ውስጥ እንዳለ አጥንትና በአፍላል ውስጥ እንዳለ ሥጋ ትቆራርጧ቞ዋላቜሁ።
በዚያን ጊዜ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ይጮኻሉፀእሱ ግን አይመልስላ቞ውም። ክፉ ድርጊት በመፈጞማ቞ው፣በዚያን ጊዜ ፊቱን ይሰውርባ቞ዋል።
ሕዝቀ እንዲባዝን በሚያደርጉ፣በጥርሳ቞ው ሲነክሱ ‘ሰላም!’ እያሉ በሚያውጁ፣አፋ቞ው ላይ ዚሚያደርጉት ነገር በማይሰጣ቞ው ሰው ሁሉ ላይ ግን ጊርነት በሚያውጁ ነቢያት ላይ ይሖዋ እንዲህ ይላል።”
‘ሌሊት ይመጣባቜኋልፀ ራእይም አታዩምፀጚለማ ብቻ ይሆንባቜኋልፀ ሟርትም አታሟርቱም። ፀሐይ በነቢያቱ ላይ ትጠልቅባ቞ዋለቜፀቀኑም ወደ ጹለማ ይለወጥባ቞ዋል።
ባለ ራእዮቜ ኀፍሚት ይኚናነባሉፀሟርተኞቜም ይዋሚዳሉ። ኹአምላክ ዘንድ መልስ ስለማይኖርሁሉም አፋቾውን ይሞፍናሉ።’”
እኔ በበኩሌ ለያዕቆብ ዓመፁን፣ ለእስራኀልም ኃጢአቱን እንድነግርበይሖዋ መንፈስ ኃይልን፣ፍትሕንና ብርታትን ተሞልቻለሁ።
ፍትሕን ዚምትጞዚፉና ቀና ዹሆነውን ነገር ሁሉ ዚምታጣምሙ፣እናንተ ዚያዕቆብ ቀት መሪዎቜ፣ዚእስራኀልም ቀት ገዢዎቜ፣ እባካቜሁ ይህን ስሙፀ
ጜዮንን ደም በማፍሰስ፣ ኢዚሩሳሌምንም በዓመፅ ዚምትገነቡ፣ ስሙ።
መሪዎቿ በጉቩ ይፈርዳሉፀካህናቷ በክፍያ ያስተምራሉፀነቢያቷም በገንዘብ ያሟርታሉ። ያም ሆኖ “ይሖዋ ኚእኛ ጋር አይደለም? ምንም ዓይነት ጥፋት አይደርስብንም” እያሉ በይሖዋ ይመካሉ።
ስለዚህ በእናንተ ዚተነሳጜዮን እንደ እርሻ ትታሚሳለቜፀኢዚሩሳሌም ዚፍርስራሜ ክምር ትሆናለቜፀዚቀቱም ተራራ፣ በጫካ እንዳሉ ኹፍ ያሉ ቊታዎቜ ይሆናል።
“መጥፎ ነገር ለሚሞርቡናበአልጋ቞ው ላይ ሆነው ክፉ ነገር ለሚያውጠነጥኑ ወዮላ቞ው! ጠዋት ሲነጋ ያሰቡትን ይፈጜማሉፀምክንያቱም ይህን ዚሚያደርጉበት ኃይል በእጃ቞ው ነው።
እርሻን ይመኛሉፀ ነጥቀውም ይይዙታልፀቀቶቜንም ይመኛሉፀ ደግሞም ይወስዳሉፀዚሰውን ቀት፣ዚሰውንም ርስት አታለው ይወስዳሉ።
ስለዚህ ይሖዋ እንዲህ ይላል።” ‘እነሆ፣ በዚህ ወገን ላይ ጥፋት ላመጣ አስቀአለሁፀ እናንተም ኹዚህ ጥፋት አታመልጡም። ኚእንግዲህ ወዲህ በትዕቢት አትመላለሱምፀ ይህ ዚጥፋት ጊዜ ነውና።
በዚያም ቀን ሰዎቜ እናንተን አስመልክተው ምሳሌ ይናገራሉፀበእናንተም ዚተነሳ አምርሹው ያለቅሳሉ። እንዲህ ይላሉ፩ “እኛ ፈጜሞ ጠፍተናል! ዚሕዝቀን ድርሻ ለሌሎቜ ሰጥቷልፀ ኚእኔም ወስዶታል! እርሻዎቻቜንን ለኚዳተኛው ይሰጣል።”
ስለዚህ በይሖዋ ጉባኀ ውስጥ፣ምድሪቷን ለማኹፋፈል በገመድ ዚሚለካ ሰው አይኖርህም።
“አትስበኩ!” ብለው ይሰብካሉፀ“እነዚህን ነገሮቜ መስበክ አይገባ቞ውምፀውርደት አይደርስብንም!”
ዚያዕቆብ ቀት ሆይ፣ “ዹይሖዋ መንፈስ አይታገሥም? እነዚህንስ ነገሮቜ ያደሚገው እሱ ነው?” ሲባል ሰምተሃል? ቀና በሆነ መንገድ ለሚሄዱ ዹገዛ ቃሌ መልካም ነገር አያስገኝም?
ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ዹገዛ ሕዝቀ ጠላት ሆኖ ተነስቷል። ኚጊርነት እንደሚመለሱ ሰዎቜ በልበ ሙሉነት ኚሚያልፉት ላይዚሚያምሚውን ጌጥ ኚልብሱ ጋር በይፋ ገፈፋቜሁ።
ዚሕዝቀን ሎቶቜ ኚሚያምሚው ቀታ቞ው አፈናቀላቜኋ቞ውፀክብሬን ኚልጆቻ቞ው ለዘላለም ወሰዳቜሁ።
ተነሱና ኹዚህ ሂዱፀ ይህ ዚማሚፊያ ቊታ አይደለምና። ኚርኩሰት ዚተነሳ ጥፋት ይመጣልፀ ጥፋቱም ኚባድ ነው።
አንድ ሰው ነፋስንና ማታለያን ተኚትሎ ቢሄድና “ስለ ወይን ጠጅና ስለ መጠጥ እሰብክላቜኋለሁ” ብሎ ውሞት ቢናገር ይህ ሰው ለዚህ ሕዝብ ተቀባይነት ያለው ሰባኪ ይሆናል!
ያዕቆብ ሆይ፣ ሁላቜሁንም በእርግጥ እሰበስባለሁፀኚእስራኀል ዚቀሩትን ያላንዳቜ ጥርጥር አንድ ላይ እሰበስባለሁ። በጉሹኖ ውስጥ እንዳለ በግ፣በግጊሜ መስክ ላይ እንዳለም መንጋ በአንድነት አኖራ቞ዋለሁፀቊታውም በሕዝብ ሁካታ ይሞላል።’
ዚሚሰብሚውም ኚፊታ቞ው ይሄዳልፀእነሱም ሰብሚው በበሩ በኩል ያልፋሉፀ በዚያም ወጥተው ይሄዳሉ። ንጉሣ቞ው በፊታ቞ው ያልፋልፀይሖዋም ኚፊታ቞ው ይሄዳል።”
“አንቺ ጥቃት ዚተሰነዘሚብሜ ሎት ልጅ ሆይ፣አሁን ሰውነትሜን ትተለትያለሜፀዙሪያቜንን ተኚበናል። ዚእስራኀልን ፈራጅ ጉንጩን በዱላ ይመቱታል።
ኚይሁዳ አእላፋት መካኚል በጣም ትንሜ ዚሆንሜውቀተልሔም ኀፍራታ ሆይ፣ምንጩ ኚጥንት፣ ኹሹጅም ዘመን በፊት ዚሆነ፣በእስራኀል ገዢ ዹሚሆን ኚአንቺ ይወጣልኛል።
ስለዚህ ልትወልድ ዚተቃሚበቜው ሎት እስክትወልድ ድሚስአሳልፎ ይሰጣ቞ዋል። ዚቀሩት ወንድሞቹም ወደ እስራኀል ሕዝብ ይመለሳሉ።
እሱ በይሖዋ ብርታትና በአምላኩ በይሖዋ ስም ታላቅነት ይነሳልፀመንጋውንም እንደ እሚኛ ይጠብቃል። እነሱም በዚያ ያለስጋት ይቀመጣሉፀበዚያን ጊዜ ታላቅነቱ እስኚ ምድር ዳርቻ ይደርሳልና።
እሱም ሰላም ያመጣል። አሊራዊው ምድራቜንን ኹወሹሹና ዚማይደፈሩ ማማዎቻቜንን ኚሚገጠበእሱ ላይ ሰባት እሚኞቜን፣ አዎ ኹሰው ልጆቜ መካኚል ስምንት አለቆቜን እናስነሳበታለን።
እነሱ ዹአሩርን ምድር በሰይፍ ይቀጣሉፀዚናምሩድንም ምድር መግቢያዎቜ ይቆጣጠራሉ። አሊራዊው ምድራቜንን ሲወርና ክልላቜንን ሲሚግጥእሱ ይታደገናል።
ዚተሚፉት ዚያዕቆብ ወገኖቜ በብዙ ሕዝቊቜ መካኚል፣ኚይሖዋ ዘንድ እንደሚወርድናሰውን ተስፋ እንደማያደርግወይም ዹሰው ልጆቜን እንደማይጠባበቅ ጠል፣በአትክልትም ላይ እንደሚወርድ ካፊያ ይሆናሉ።
በዱር እንስሳት መካኚል እንዳለ አንበሳ፣በሚያልፍበት ጊዜ እዚሚጋገጠና እዚሰባበሚ እንደሚሄድ፣በበግ መንጎቜ መካኚል እንዳለ ደቩል አንበሳ፣ዚተሚፉት ዚያዕቆብ ወገኖቜም በብሔራት፣በብዙ ሕዝቊቜም መካኚል እንዲሁ ይሆናሉፀሊያስጥል ዚሚቜልም አይኖርም።
እጅህ ኚባላጋራዎቜህ በላይ ኹፍ ኹፍ ትላለቜፀጠላቶቜህም ሁሉ ይወገዳሉ።”
“በዚያም ቀን” ይላል ይሖዋ፣“ፈሚሶቜህን ኚመካኚልህ አስወግዳለሁፀ ሠሚገሎቜህንም አጠፋለሁ።
በምድርህ ላይ ዚሚገኙትን ኚተሞቜ እደመስሳለሁፀዚተመሞጉ ስፍራዎቜህንም ሁሉ አፈራርሳለሁ።
ጥንቆላህን አስወግዳለሁፀኚእንግዲህም አስማተኛ በመካኚልህ አይኖርም።
ዚተቀሚጹ ምስሎቜህንና ዓምዶቜህን ኚመካኚልህ አስወግዳለሁፀኚእንግዲህም ወዲህ ለእጆቜህ ሥራ አትሰግድም።
ዚማምለኪያ ግንዶቜህንም ኚመካኚልህ እነቅላለሁፀኚተሞቜህንም እደመስሳለሁ።
ታዛዥ ያልሆኑትን ብሔራት፣በቁጣና በንዎት እበቀላለሁ።”
በዘመኑ መጚሚሻዚይሖዋ ቀት ተራራኚተራሮቜ አናት በላይ ጞንቶ ይቆማልፀኚኮሚብቶቜም በላይ ኹፍ ኹፍ ይላልፀሕዝቊቜም ወደዚያ ይጎርፋሉ።
ብዙ ብሔራትም ሄደው እንዲህ ይላሉ፩ “ኑፀ ወደ ይሖዋ ተራራናወደ ያዕቆብ አምላክ ቀት እንውጣ። እሱ ስለ መንገዶቹ ያስተምሚናልፀበጎዳናዎቹም እንሄዳለን።” ሕግ ኚጜዮን፣ዚይሖዋም ቃል ኚኢዚሩሳሌም ይወጣልና።
እሱ በብዙ ሕዝቊቜ መካኚል ይፈርዳልፀበሩቅ ካሉ ኃያላን ብሔራት ጋር በተያያዘም ሁሉንም ነገር ያቀናል። እነሱ ሰይፋቾውን ማሚሻ፣ጊራ቞ውንም ማጭድ ለማድሚግ ይቀጠቅጣሉ። አንዱ ብሔር በሌላው ብሔር ላይ ሰይፍ አያነሳምፀኚእንግዲህ ወዲህ ጊርነት አይማሩም።
እያንዳንዱም ኹወይኑና ኚበለስ ዛፉ ሥር ይቀመጣልፀዚሚያስፈራ቞ውም አይኖርምፀዚሠራዊት ጌታ ዹይሖዋ አፍ ተናግሯልና።
ሕዝቊቜ ሁሉ፣ እያንዳንዳ቞ው በአምላካ቞ው ስም ይሄዳሉፀእኛ ግን በአምላካቜን በይሖዋ ስም ለዘላለም እንሄዳለን።
“በዚያ ቀን” ይላል ይሖዋ፣“ዚሚያነክሰውን እሰበስባለሁፀደግሞም ዚተበተኑትንናያንገላታኋ቞ውን ሰዎቜ አንድ ላይ እሰበስባለሁ።
ዚሚያነክሰው ዹተወሰኑ ቀሪዎቜ እንዲኖሩት አደርጋለሁፀወደ ሩቅ ስፍራ ዹተወሰደውንም ኃያል ብሔር አደርገዋለሁፀይሖዋም ኹአሁን ጀምሮ ለዘላለምበጜዮን ተራራ በእነሱ ላይ ንጉሥ ሆኖ ይገዛል።
አንተም ዹመንጋው ማማ፣ዚጜዮን ሎት ልጅ ጉብታ ሆይ፣አንተ ወዳለህበት ይመለሳልፀ አዎ፣ ዚመጀመሪያው ግዛትህ፣ዚኢዚሩሳሌም ሎት ልጅ መንግሥት ይመለሳል።
አሁንስ ድምፅሜን ኹፍ አድርገሜ ዚምትጮኺው ለምንድን ነው? ንጉሥ ዚለሜም?ወይስ አማካሪሜ ጠፍቷል?ልትወልድ እንደተቃሚበቜ ሎት ዚምትሠቃዪው ለዚህ ነው?
ዚጜዮን ሎት ልጅ ሆይ፣ ልትወልድ እንደተቃሚበቜ ሎትተንፈራገጪፀ አቃስቺምፀአሁን ኹኹተማ ወጥተሜ በሜዳ ትሰፍሪያለሜና። እስኚ ባቢሎን ድሚስ ትሄጃለሜፀበዚያም ይታደግሻልፀበዚያ ይሖዋ ኚጠላቶቜሜ እጅ ይዋጅሻል።
አሁንም ብዙ ብሔራት በአንቺ ላይ ይሰበሰባሉፀእነሱም ‘ዚሚኚሰቜ ትሁንፀዓይኖቻቜንም ይህ በጜዮን ላይ ሲደርስ ይመልኚቱ’ ይላሉ።
ይሁንና ዹይሖዋን ሐሳብ አያውቁምፀዓላማውንም አይሚዱምፀእሱ ገና እንደታጚደ እህል ወደ አውድማ ይሰበስባ቞ዋልና።
ዚጜዮን ሎት ልጅ ሆይ፣ ተነስተሜ እህሉን ውቂፀቀንድሜን ወደ ብሚት፣ሰኮናሜንም ወደ መዳብ እለውጣለሁናፀአንቺም ብዙ ሕዝቊቜን ታደቂያለሜ። በማጭበርበር ያገኙት ትርፍ ለይሖዋ ዹተወሰነ እንዲሆን፣ሀብታ቞ውም ለምድር ሁሉ ጌታ ብቻ እንዲውል ታደርጊያለሜ።”
ይሖዋ ዹሚለውን እባካቜሁ ስሙ። ተነሱፀ በተራሮቜ ፊት ሙግታቜሁን አቅርቡፀኮሚብቶቜም ቃላቜሁን ይስሙ።
ተራሮቜ ሆይ፣ እናንተ ጜኑ ዚምድር መሠሚቶቜ፣ዚይሖዋን ሙግት ስሙፀይሖዋ ኚሕዝቡ ጋር ሙግት አለውናፀኚእስራኀልም ጋር ይኚራኚራልፊ
“ሕዝቀ ሆይ፣ ምን ያደሚግኩህ ነገር አለ? ያደኚምኩህስ ምን አድርጌ ነው? እስቲ መሥክርብኝ።
ኚግብፅ ምድር አወጣሁህፀኚባርነትም ቀት ዋጀሁህፀሙሎን፣ አሮንንና ሚርያምን በፊትህ ላክሁ።
ሕዝቀ ሆይ፣ ዚሞዓብ ንጉሥ ባላቅ ያሎሚብህን ነገር፣ዚቢዖር ልጅ በለዓምም ዹሰጠውን መልስ እባክህ አስታውስፀዚይሖዋን ዚጜድቅ ሥራ ታውቅ ዘንድኚሺቲም እስኚ ጊልጋል ድሚስ ዹሆነውን ነገር አስታውስ።”
በይሖዋ ፊት ምን á‹­á‹€ ልቅሚብ? ኹፍ ባለ ስፍራ በሚኖሹው አምላክ ፊት ምን á‹­á‹€ ልስገድ? ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠሉ መባዎቜናዚአንድ ዓመት ጥጃዎቜ á‹­á‹€ ልቅሚብ?
ይሖዋ በሺህ በሚቆጠሩ አውራ በጎቜወይስ በእልፍ ዚዘይት ፈሳሟቜ ደስ ይለዋል? ለሠራሁት በደል ዚበኩር ወንድ ልጄን፣ለሠራሁትም ኃጢአት ዹሆዮን ፍሬ ላቅርብ?
ሰው ሆይ፣ መልካም ዹሆነውን ነግሮሃል። ይሖዋ ኹአንተ ዹሚፈልገው ምንድን ነው? ፍትሕን እንድታደርግ፣ ታማኝነትን እንድትወድናልክህን አውቀህ ኹአምላክህ ጋር እንድትሄድ ብቻ ነው!
ዹይሖዋ ድምፅ ኹተማዋን ይጣራልፀጥበበኞቜ ስምህን ይፈራሉ። ዚበትሩን ድምፅና ቅጣቱን ዚወሰነውን ስሙ።
ክፉ በሆነ ሰው ቀት፣ በክፋት ዹተገኘ ሀብትእንዲሁም አስጞያፊ ዹሆነ ጎዶሎ ዚኢፍ መስፈሪያ አሁንም አለ?
አባይ ሚዛንና ዚተዛቡ ዚድንጋይ መለኪያዎቜ ዚያዘ ኚሚጢት እዚተጠቀምኩንጹሕ ሥነ ምግባር ሊኖሹኝ ይቜላል?
ባለጞጎቿ በግፍ ዹተሞሉ ና቞ውፀነዋሪዎቿም ውሞት ይናገራሉፀምላሳ቞ው በአፋቾው ውስጥ አታላይ ነው።
“ስለዚህ መትቌ አቆስልሃለሁፀኚኃጢአትህ ዚተነሳ አጠፋሃለሁ።
ትበላለህፀ ግን አትጠግብምፀሆድህም ባዶ ይሆናል። ዚምትወስዳ቞ውን ነገሮቜ ጠብቀህ ማቆዚት አትቜልምፀጠብቀህ ያቆዚኞውንም ነገር ሁሉ ለሰይፍ አሳልፌ እሰጠዋለሁ።
ዘር ትዘራለህፀ ሆኖም ዚምታጭደው ነገር አይኖርም። ዚወይራ ፍሬ ትጚምቃለህፀ ሆኖም ዘይቱን አትጠቀምበትምፀደግሞም አዲስ ወይን ትጚምቃለህፀ ሆኖም ዹወይን ጠጅ አትጠጣም።
ዚኊምሪን ደንቊቜና ዚአክዓብን ቀት ሥራ ሁሉ ትኚተላላቜሁናፀምክራ቞ውንም ተኚትላቜሁ ትሄዳላቜሁ። ስለዚህ አንተን መቀጣጫ፣ነዋሪዎቿንም ማፏጫ አደርጋለሁፀዚሰዎቜንም ፌዝ ትሞኚማላቜሁ።”
በነነዌ ላይ ዹተላለፈ ፍርድፊ ዚኀልቆሻዊው ዹናሆም ዚራእዩ መጜሐፍ ይህ ነው፩
ይሖዋ እሱ ብቻ እንዲመለክ ዹሚፈልግና ዹሚበቀል አምላክ ነውፀይሖዋ ይበቀላልፀ ቁጣውንም ለመግለጜ ዝግጁ ነው። ይሖዋ ባላጋራዎቹን ይበቀላልፀለጠላቶቹም ቁጣ ያኚማቻል።
ይሖዋ ለቁጣ ዹዘገዹ ነውፀ ኃይሉም ታላቅ ነውፀይሁንና ይሖዋ ተገቢውን ቅጣት ኚመስጠት ፈጜሞ ወደኋላ አይልም። መንገዱ በአደገኛ ነፋስና በወጀብ ውስጥ ነውፀደመናት ኚእግሩ በታቜ እንዳለ አቧራ ና቞ው።
ባሕሩን ይገሥጻልፀ ያደርቀዋልምፀወንዞቹንም በሙሉ ያደርቃ቞ዋል። ባሳንና ቀርሜሎስ ይጠወልጋሉፀዚሊባኖስ አበባዎቜም ይጠወልጋሉ።
ኚእሱ ዚተነሳ ተራሮቜ ይንቀጠቀጣሉፀኮሚብቶቜም ይቀልጣሉ። ኚፊቱም ዚተነሳ ምድር፣ዚብስና በላዩ ዚሚኖሩት ሁሉ ይናወጣሉ።
በቁጣው ፊት ማን ሊቆም ይቜላል? ዚንዎቱን ትኩሳት ሊቋቋም ዚሚቜልስ ማን ነው? ቁጣው እንደ እሳት ይፈስሳልፀዓለቶቜም ኚእሱ ዚተነሳ ይፈሚካኚሳሉ።
ይሖዋ ጥሩ ነውፀ በጭንቀትም ቀን መሞሞጊያ ነው። እሱን መጠጊያ ማድሚግ ዚሚፈልጉትን ያውቃል።
ጠራርጎ በሚወስድ ጎርፍ ስፍራዋን ፈጜሞ ያጠፋልፀጠላቶቹንም ጹለማ ያሳድዳ቞ዋል።
በይሖዋ ላይ ዚምታሎሩት ምንድን ነው? እሱ ፈጜሞ ያጠፋል። ጭንቀት ዳግመኛ አይመጣም።
እርስ በርሳ቞ው እንደ እሟህ ተጠላልፈዋልናፀመጠጥ ጠጥተው እንደሰኚሩ ሰዎቜ ና቞ውፀሆኖም እንደደሚቀ ገለባ እሳት ይበላ቞ዋል።
በይሖዋ ላይ ክፉ ነገር ዚሚያሎር፣ኚንቱ ምክርም ዚሚሰጥ ኚመካኚልሜ ይወጣል።
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ምንም እንኳ ዹተሟላ ኃይል ያላ቞ውና ብዙዎቜ ቢሆኑምይቆሚጣሉፀ ደግሞም ይጠፋሉ። መኚራ አሳይቌሃለሁፀ ኚዚያ በኋላ ግን መኚራ አላመጣብህም።
አሁንም ቀንበሩን ኹአንተ ላይ እሰብራለሁፀእስራትህንም እበጥሳለሁ።
ይሖዋ አንተን በተመለኹተ እንዲህ ሲል አዟልፊ‘ኚእንግዲህ ስምህን ዚሚያስጠራ አይኖርም። ዚተቀሚጹትን ምስሎቜና ኚብሚት ዚተሠሩትን ሐውልቶቜ ኚአማልክትህ ቀት አስወግዳለሁ። ዹተናቅክ ስለሆንክ መቃብር አዘጋጅልሃለሁ።’
እነሆ ምሥራቜ ይዞ ዚሚመጣ፣ሰላምንም ዚሚያውጅ ሰው እግር በተራሮቜ ላይ ነው። ይሁዳ ሆይ፣ በዓሎቜሜን አክብሪፀ ስእለትሜን ፈጜሚፀኚእንግዲህ ወዲህ ዚማይሚባ ሰው በመካኚልሜ አያልፍምና። እንዲህ ያለው ሰው ሙሉ በሙሉ ይወገዳል።”
ለደም አፍሳሿ ኹተማ ወዮላት! በማታለልና በዝርፊያ ዚተሞላቜ ናት። ኹማደን ቩዝና አታውቅም!
ዹአለንጋ ድምፅና ዚመንኮራኩር ኳኳ቎ ይሰማልፀፈሚሶቜ ሲጋልቡና ሠሚገሎቜ ሲፈተለኩ ይታያል።
ፈሚስ ጋላቢው ይጋልባልፀ ሰይፉ ያንጞባርቃልፀ ጊሩ ያብሚቀርቃልፀዚተገደሉት በጣም ብዙ ና቞ውፀ ዚአስኚሬን ክምር ይታያልፀሬሳው ስፍር ቁጥር ዚለውም። አስኚሬኖቹም ያደናቅፏ቞ዋል።
ይህ ዹሆነው ዝሙት አዳሪዋ በምትፈጜመው በርካታ ዚአመንዝራነት ተግባር ዚተነሳ ነውፀእሷ ብሔራትን በምንዝሯ፣ ወገኖቜንም በጥንቆላዋ ዚምታጠምድ፣ዚምታምርና ዚምትማርክ እንዲሁም በጥንቆላ ዚተካነቜ ናት።
“እነሆ፣ በአንቺ ላይ ተነስቻለሁ” ይላል ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋፀ“ቀሚስሜን እስኚ ፊትሜ ድሚስ እገልበዋለሁፀብሔራትም እርቃንሜን፣መንግሥታትም ነውርሜን እንዲያዩ አደርጋለሁ።
ቆሻሻ እደፋብሻለሁፀዚተናቅሜ አደርግሻለሁፀማላገጫም እንድትሆኚ አደርጋለሁ።
አንቺን ዚሚያይ ሁሉ ኚአንቺ ይሞሻልፀደግሞም ‘ነነዌ ወድማለቜ! ዚሚያዝንላት ማን ነው?’ ይላል። አንቺን ዚሚያጜናና ኚዚት ማግኘት እቜላለሁ?
አንቺ በአባይ ዚመስኖ ቊዮቜ አጠገብ ኚነበሚቜው ኹኖአሞን ትሻያለሜ? እሷ በውኃ ዚተኚበበቜ ነበሚቜፀባሕሩም ሀብት ያስገኝላት፣ እንደ ቅጥርም ሆኖ ያገለግላት ነበር።
ኢትዮጵያና ግብፅ ገደብ ዚለሜ ዹኃይል ምንጮቿ ነበሩ። ፑጥና ሊቢያውያን ሚዳቶቿ ነበሩ።
ይሁንና እሷም እንኳ በግዞት ተወሰደቜፀተማርካም ሄደቜ። ልጆቿም በዚመንገዱ ማዕዘን ተፈጠፈጡ። በተኚበሩ ሰዎቿ ላይ ዕጣ ተጣጣሉፀታላላቅ ሰዎቿም ሁሉ በእግር ብሚት ታሰሩ።
አንቺም ትሰክሪያለሜፀደግሞም ትሰወሪያለሜ። ኚጠላት ዚምትሞሞጊበት ቊታ ትፈልጊያለሜ።
ምሜጎቜሜ ሁሉ ዚመጀመሪያዎቹን ዹበሰሉ ፍሬዎቜ እንደያዙ ዚበለስ ዛፎቜ ና቞ውፀዛፎቹ ኹተነቀነቁ ፍሬዎቹ ሹግፈው በበላተኛ አፍ ውስጥ ይወድቃሉ።
እነሆ፣ ወታደሮቜሜ በመካኚልሜ እንዳሉ ሎቶቜ ና቞ው። ዚምድርሜ በሮቜ ለጠላቶቜሜ ወለል ብለው ይኚፈታሉ። ዚበሮቜሜን መቀርቀሪያዎቜ እሳት ይበላ቞ዋል።