text
stringlengths
4
267
አንተ በቋጥኝ መሞሞጊያ ውስጥ ዚምትኖር፣መኖሪያህን በኚፍታ ቊታ ላይ ያደሚግክ፣በልብህ ‘ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይቜላል?’ ዚምትል፣ዚልብህ እብሪት አታሎሃል።
መኖሪያህን እንደ ንስር ኹፍ ብታደርግወይም ጎጆህን በኚዋክብት መካኚል ብትሠራ እንኳእኔ ኚዚያ አወርድሃለሁ” ይላል ይሖዋ።
“ሌቊቜ ወደ አንተ ቢመጡ፣ ዘራፊዎቜ በሌሊት ቢገቡ(ታላቅ ጥፋት በደሚሰብህ ነበር!) ዚሚሰርቁት ዚሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለም? ደግሞስ ወይን ለቃሚዎቜ ወደ አንተ ቢመጡጥቂት ቃርሚያ አያስቀሩም?
ኀሳው ምንኛ ተበሹበሹ! ዹተደበቀው ውድ ሀብቱ ምንኛ ተፈለገ!
እስኚ ድንበሩ ድሚስ እንድትሄድ አስገደዱህ። አጋሮቜህ ሁሉ አታለውሃል። ኹአንተ ጋር ሰላማዊ ግንኙነት ዚነበራ቞ው ሰዎቜ አይለውብሃል። ኹአንተ ጋር ዹሚበሉ ሰዎቜ ኚሥርህ መሚብ ይዘሚጉብሃልፀአንተ ግን አታስተውለውም።
በዚያ ቀን” ይላል ይሖዋ፣“ጥበበኞቜን ኚኀዶም አላጠፋም?ማስተዋልንስ ኚኀሳው ተራራማ ምድር አላስወግድም?
ቮማን ሆይ፣ ተዋጊዎቜሜ ይሞበራሉፀምክንያቱም እያንዳንዳ቞ው ታርደው ኚተራራማው ዚኀሳው ምድር ይወገዳሉ።
በወንድምህ በያዕቆብ ላይ በተፈጾመው ግፍ ዚተነሳኀፍሚት ትኚናነባለህፀለዘላለምም ትጠፋለህ።
ዳር ቆመህ ትመለኚት በነበሚበት ጊዜ፣እንግዶቜ ሠራዊቱን ማርኹው በወሰዱበትናዚባዕድ አገር ሰዎቜ በበሩ ገብተው በኢዚሩሳሌም ላይ ዕጣ በተጣጣሉበት ጊዜ፣አንተም ልክ እንደ እነሱ አደሚግክ።
በወንድምህ ቀን ይኾውም ወንድምህ ክፉ ነገር በደሚሰበት ቀን መፈንደቅ አይገባህም ነበርፀዚይሁዳ ሕዝብ በጠፋበት ቀን ሐሎት ማድሚግ አልነበሚብህምፀደግሞም በጭንቀታ቞ው ቀን በእብሪት መናገር አይገባህም ነበር።
በጥፋታ቞ው ቀን ወደ ሕዝቀ በር መምጣት አልነበሚብህምፀበጥፋቱ ቀን በደሚሰበት መኚራ መፈንደቅ አይገባህም ነበርፀደግሞም ጥፋት በደሚሰበት ቀን ሀብቱን መውሰድ አልነበሚብህም።
ዚሚሞሹትን ዚይሁዳ ሰዎቜ ለመግደል መንታ መንገድ ላይ መቆም አይገባህም ነበርፀበጭንቀቱም ቀን በሕይወት ዚተሚፉትን አሳልፈህ መስጠት አልነበሚብህም።
ይሖዋ በብሔራት ሁሉ ላይ ዚሚነሳበት ቀን ቀርቧልና። አንተ በእሱ ላይ እንዳደሚግኚው በአንተም ላይ ይደሚጋል። በሌሎቜ ላይ ያደሚግኚው ነገር በገዛ ራስህ ላይ ይመለሳል።
እናንተ በቅዱሱ ተራራዬ ላይ እንደጠጣቜሁ፣ልክ እንደዚሁ ብሔራት በሙሉ ዘወትር ይጠጣሉ። ይጠጣሉፀ ደግሞም ይጚልጡታልፀፈጜሞ እንዳልነበሩም ይሆናሉ።
ያመለጡት ግን በጜዮን ተራራ ላይ ይሆናሉፀእሱም ዹተቀደሰ ይሆናልፀዚያዕቆብ ቀት ሰዎቜም ዚራሳ቞ው ዚሆኑትን ነገሮቜ ይወርሳሉ።
ዚያዕቆብ ቀት እሳት፣ዚዮሎፍም ቀት ነበልባል ይሆናልፀዚኀሳው ቀት ደግሞ እንደ ገለባ ይሆናልፀእነሱም ያቃጥሏ቞ዋልፀ ይበሏ቞ዋልምፀኚኀሳውም ቀት ዹሚተርፍ አይኖርምፀይሖዋ ራሱ ተናግሯልና።
እነሱ ኔጌብንና ዚኀሳውን ተራራማ ምድር፣ሞፌላንና ዚፍልስጀምን ምድር ይወርሳሉ። ዚኀፍሬምን መሬትና ዚሰማርያን መሬት ይወርሳሉፀቢንያምም ጊልያድን ይወርሳል።
እስኚ ሰራፕታ ድሚስ ያለው ዚኚነአናውያን ምድር፣ኚዚህ ዚመኚላኚያ ግንብ በግዞት ዚተወሰዱት ሰዎቜ ይኾውም ዚእስራኀል ሕዝብ ይዞታ ይሆናል። በሰፋራድ ዚነበሩት ኚኢዚሩሳሌም በግዞት ዚተወሰዱ ሰዎቜም ዚኔጌብን ኚተሞቜ ይወርሳሉ።
ሕዝቡን ዚሚታደጉ ሰዎቜም በኀሳው ተራራማ ምድር ላይ ለመፍሚድወደ ጜዮን ተራራ ይወጣሉፀንግሥናውም ዹይሖዋ ይሆናል።”
ዹይሖዋ ቃል ወደ አሚታይ ልጅ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣፊ
“ተነስተህ ወደ ታላቂቱ ኹተማ ወደ ነነዌ ሂድና በእሷ ላይ ዚፍርድ መልእክት አውጅፀ ክፋታ቞ውን አስተውያለሁና።”
ዮናስ ግን ኹይሖዋ ፊት ኮብልሎ ወደ ተርሎስ ለመሄድ ተነሳፀ ወደ ኢዮጎም ወሚደፀ ኚዚያም ወደ ተርሎስ ዚምትሄድ መርኚብ አገኘ። ኹይሖዋም ፊት ሞሜቶ፣ በመርኚቡ ውስጥ ኚነበሩት ጋር ወደ ተርሎስ ለመሄድ ዹጉዞውን ዋጋ ኹፍሎ ተሳፈሚ።
ኚዚያም ይሖዋ በባሕሩ ላይ ኃይለኛ ነፋስ አመጣፀ ኚባድ ማዕበል ስለተነሳ መርኹቧ ልትሰበር ተቃሚበቜ።
መርኚበኞቹ እጅግ ኚመፍራታ቞ው ዚተነሳ እርዳታ ለማግኘት እያንዳንዳ቞ው ወደዚአምላካ቞ው ይጮኹ ጀመር። ዹመርኹቧንም ክብደት ለመቀነስ በውስጧ ዚነበሩትን ዕቃዎቜ ወደ ባሕሩ መጣል ጀመሩ። ዮናስ ግን ወደ መርኹቧ ውስጠኛ ክፍል ወርዶ ተኝቶ ነበርፀ ጭልጥ ያለ እንቅልፍም ወስዶት ነበር።
ዹመርኹቧ አዛዥ ወደ እሱ ቀርቩ እንዲህ አለው፩ “እንዎት ትተኛለህ? ተነስተህ ወደ አምላክህ ጩኜ! ምናልባት እውነተኛው አምላክ ለእኛ አስቊ ኚጥፋት ያድነን ይሆናል።”
ኚዚያም እርስ በርሳ቞ው “ይህ መኚራ ዚደሚሰብን በማን ምክንያት እንደሆነ ማወቅ እንድንቜል፣ ኑ ዕጣ እንጣጣል” ተባባሉ። በመሆኑም ዕጣ ተጣጣሉፀ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወደቀ።
እነሱም እንዲህ አሉትፊ “ይህ መኚራ ዚደሚሰብን በማን ምክንያት እንደሆነ እባክህ ንገሚን። ሥራህ ምንድን ነው? ዚመጣኞው ኚዚት ነው? አገርህስ ዚት ነው? ኚዚትኛውስ ሕዝብ ነህ?”
እሱም መልሶ “እኔ ዕብራዊ ነኝፀ ባሕሩንና ዚብሱን ዹፈጠሹውን ዚሰማያትን አምላክ ይሖዋን ዚምፈራ ሰው ነኝ” አላ቞ው።
በዚህ ጊዜ ሰዎቹ ዚባሰ ፈሩፀ “ያደሚግኚው ነገር ምንድን ነው?” ብለው ጠዚቁት። (ሰዎቹ ዮናስ ነግሯ቞ው ስለነበር ኹይሖዋ ፊት እዚሞሞ እንዳለ አወቁ።)
ዚባሕሩ ማዕበል እያዚለ በመሄዱ “ባሕሩ ጞጥ እንዲልልን በአንተ ላይ ምን ብናደርግ ይሻላል?” አሉት።
እሱም “አንስታቜሁ ወደ ባሕሩ ጣሉኝፀ ባሕሩም ጞጥ ይልላቜኋልፀ ይህ ኚባድ ማዕበል ዚመጣባቜሁ በእኔ ዚተነሳ መሆኑን አውቃለሁና” በማለት መለሰላ቞ው።
ሰዎቹ ግን መርኹቧን ወደ ዚብስ ለመመለስ በኃይል ቀዘፉፀ ይሁንና ማዕበሉ ይበልጥ እያዚለባ቞ው ስለሄደ ሊሳካላ቞ው አልቻለም።
ኚዚያም ወደ ይሖዋ በመጮኜ እንዲህ አሉ፩ “እንግዲህ ይሖዋ ሆይ፣ በዚህ ሰው ምክንያት እንዳንጠፋ እንለምንሃለን! ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ደስ እንዳሰኘህ ስላደሚግክ ለንጹሕ ሰው ደም ተጠያቂ አታድርገን!”
ኚዚያም ዮናስን አንስተው ወደ ባሕሩ ጣሉትፀ ባሕሩም መናወጡን አቆመ።
በዚህ ጊዜ ሰዎቹ ይሖዋን እጅግ ፈሩፀ ለይሖዋም መሥዋዕት አቀሚቡፀ ስእለትም ተሳሉ።
ይሖዋም ዮናስን እንዲውጠው አንድ ትልቅ ዓሣ ላኚፀ ዮናስም ሊስት ቀንና ሊስት ሌሊት በዓሣው ሆድ ውስጥ ቆዚ።
ኚዚያም ዹይሖዋ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ እንዲህ ሲል ወደ ዮናስ መጣፊ
“ተነስተህ ወደ ታላቂቱ ኹተማ ወደ ነነዌ ሂድፀ ዹምነግርህንም መልእክት በመካኚሏ አውጅ።”
ዮናስም ዹይሖዋን ቃል በመታዘዝ ተነስቶ ወደ ነነዌ ሄደ። ነነዌ እጅግ ታላቅ ኹተማ ዚነበሚቜ ስትሆን በእግር ዚሊስት ቀን ያህል መንገድ ታስኬድ ነበር።
ዮናስም ወደ ኹተማዋ ገብቶ ዚአንድ ቀን መንገድ ኹተጓዘ በኋላ “ነነዌ በ40 ቀን ውስጥ ትደመሰሳለቜ” ብሎ አወጀ።
ዹነነዌም ሰዎቜ በአምላክ አመኑፀ ኚትልቁም አንስቶ እስኚ ትንሹ ድሚስ ጟም አወጁፀ ማቅም ለበሱ።
ዹነነዌ ንጉሥ መልእክቱን በሰማ ጊዜ ኹዙፋኑ ተነስቶ ልብሰ መንግሥቱን አወለቀፀ ማቅም ለብሶ አመድ ላይ ተቀመጠ።
በተጚማሪም በመላው ነነዌ አዋጅ አስነገሚፀ“ንጉሡና መኳንንቱ ያወጡት ድንጋጌፊ ሰውም ሆነ እንስሳ፣ ኚብትም ሆነ መንጋ ምንም ነገር አይቅመስ። ምግብ አይብሉፀ ውኃም አይጠጡ።
ሰውም ሆነ እንስሳ ማቅ ይልበስፀ ሁሉም አጥብቆ ወደ አምላክ ይጩኜፀ ክፉ መንገዳ቞ውንና ዚሚፈጜሙትን ግፍ ይተዉ።
እኛ እንዳንጠፋ፣ እውነተኛው አምላክ ሊያመጣው ያሰበውን ነገር እንደገና በማጀን ኹሚነደው ቁጣው ይመለስ እንደሆነ ማን ያውቃል?”
እውነተኛው አምላክ ያደሚጉትን ነገር ይኾውም ኹክፉ መንገዳ቞ው እንዎት እንደተመለሱ አዚፀ በእነሱም ላይ አመጣዋለሁ ያለውን ነገር መልሶ በማጀን ጥፋቱን ኚማምጣት ተቆጠበ።
ኚዚያም ዮናስ በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደ ይሖዋ ጞለዚፀ
እንዲህም አለ፩ “ተጹንቄ ሳለሁ ወደ ይሖዋ ተጣራሁፀ እሱም መለሰልኝ። በመቃብር ጥልቅ ውስጥ ሆኜ እርዳታ ለማግኘት ጮኜኩ። አንተም ድምፄን ሰማህ።
ወደ ጥልቁ፣ ወደ ታቜኛው ዚባሕሩ ወለል በጣልኚኝ ጊዜፈሳሹ ውኃ ዋጠኝ። ማዕበሎቜህና ሞገዶቜህ ሁሉ በላዬ አለፉ።
እኔም ‘ኚፊትህ አባሚርኚኝ! ቅዱስ ዹሆነውን ቀተ መቅደስህን ዳግመኛ እንዎት መመልኚት እቜላለሁ?’ አልኩ።
ውኃው ዋጠኝፀ ሕይወቮንም አደጋ ላይ ጣለውፀጥልቁ ውኃ ኚበበኝ። ዚባሕር አሹም ራሎ ላይ ተጠመጠመ።
ወደ ተራሮቜ መሠሚት ሰመጥኩ። ዚምድር መቀርቀሪያዎቜ ለዘላለም ተዘጉብኝ። ይሖዋ አምላኬ ሆይ፣ አንተ ግን ሕይወቮን ኚጉድጓዱ ውስጥ አወጣህ።
ሕይወቮ እዚተዳኚመቜ ስትሄድ ይሖዋን አስታወስኩ። ጾሎቮም ወደ አንተ፣ ቅዱስ ወደሆነው ቀተ መቅደስህ ገባ።
ለማይሚቡ ጣዖቶቜ ያደሩ ሰዎቜ ታማኝ ፍቅር ዚሚያሳያ቞ውን ይተዋሉ።
እኔ ግን በምስጋና ድምፅ መሥዋዕት አቀርብልሃለሁ። ዚተሳልኩትን እኚፍላለሁ። መዳን ኹይሖዋ ነው።”
በኋላም ይሖዋ ዓሣውን አዘዘውፀ ዓሣውም ዮናስን በደሹቅ ምድር ላይ ተፋው።
ሆኖም ይህ ጉዳይ ዮናስን ፈጜሞ አላስደሰተውምፀ በመሆኑም እጅግ ተቆጣ።
ወደ ይሖዋም እንዲህ ሲል ጾለዹ፩ “ይሖዋ ሆይ፣ በገዛ አገሬ ሳለሁ ያሳሰበኝ ጉዳይ ይህ አልነበሹም? መጀመሪያውኑም ወደ ተርሎስ ለመሞሜ ዚሞኚርኩት ለዚህ ነበርፀ አንተ ሩኅሩኅና መሐሪ አምላክ፣ ለቁጣ ዹዘገዹህና ታማኝ ፍቅርህ ዚበዛ፣ አዝነህም ጥፋት ኚማምጣት ዚምትቆጠብ እንደሆንክ አውቃለሁና።
አሁንም ይሖዋ ሆይ፣ በሕይወት ኹመኖር ይልቅ መሞት ስለሚሻለኝ እባክህ ግደለኝ።”
ይሖዋም “እንዲህ መቆጣትህ ተገቢ ነው?” ብሎ ጠዚቀው።
ኚዚያም ዮናስ ኹኹተማዋ ወጥቶ በስተ ምሥራቅ በኩል ተቀመጠ። በዚያም ለራሱ መጠለያ ሠርቶ በኹተማዋ ላይ ዹሚደርሰውን ነገር ለማዚት በጥላው ሥር ተቀመጠ።
በዚህ ጊዜ ይሖዋ አምላክ፣ ዮናስ ራሱን እንዲያስጠልልባትና ኚሥቃዩ እንዲያርፍ ሲል አንዲት ዹቅል ተክል ኚበላዩ እንድታድግ አደሚገ። ዮናስም በቅል ተክሏ እጅግ ተደሰተ።
ይሁን እንጂ እውነተኛው አምላክ በሚቀጥለው ቀን፣ ማለዳ ላይ አንድ ትል ላኚፀ ትሉም ዹቅል ተክሏን በላትፀ ተክሏም ደሚቀቜ።
ፀሐይ መውጣት ስትጀምር አምላክ ዚሚያቃጥል ዚምሥራቅ ነፋስ አመጣፀ ፀሐይዋም ዚዮናስን አናት አቃጠለቜውፀ እሱም ተዝለፈለፈ። እንዲሞትም ለመነፀ ደግሞ ደጋግሞም “በሕይወት ኹምኖር ብሞት ይሻለኛል” አለ።
አምላክም ዮናስን “ስለ ቅል ተክሏ እንዲህ መቆጣትህ ተገቢ ነው?” ሲል ጠዚቀው። እሱም “መቆጣት ሲያንሰኝ ነውፀ እንዲያውም ብሞት ይሻለኛል” አለ።
ይሖዋ ግን እንዲህ አለው፩ “አንተ በአንድ ሌሊት አድጋ በአንድ ሌሊት ለጠፋቜው፣ ላልደኚምክባት ወይም ላላሳደግካት ዹቅል ተክል አዝነሃል።
ታዲያ እኔ ትክክልና ስህተት ዹሆነውን ነገር ለይተው ዚማያውቁ ኹ120,000 በላይ ዹሚሆኑ ሰዎቜና በርካታ እንስሶቻ቞ው ለሚኖሩባት ለታላቂቱ ኹተማ ለነነዌ ላዝን አይገባም?”
በይሁዳ ነገሥታት በኢዮዓታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞሚሞታዊው ወደ ሚክያስ ዚመጣው እንዲሁም ሚክያስ ስለ ሰማርያና ስለ ኢዚሩሳሌም በራእይ ያዚው ዹይሖዋ ቃል ይህ ነው።”
“እናንተ ሕዝቊቜ ሁላቜሁም ስሙ! ምድርና በውስጧ ያሉ ሁሉ፣ በትኩሚት ያዳምጡፀይሖዋ ቅዱስ በሆነው ቀተ መቅደሱ ነው። ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ በእናንተ ላይ ይመሥክርባቜሁ።
እነሆ፣ ይሖዋ ኚስፍራው ይወጣልፀወደ ታቜ ወርዶ ዚምድርን ኹፍ ያሉ ቊታዎቜ ይሚግጣል።
በእሳት ፊት እንዳለ ሰምናበገደል ላይ እንደሚወርድ ውኃተራሮቹ ኚሥሩ ይቀልጣሉፀሞለቆዎቹም ይሰነጠቃሉ።
ይህ ሁሉ ዹሆነው በያዕቆብ ዓመፅ፣በእስራኀልም ቀት ኃጢአት ዚተነሳ ነው። ለያዕቆብ ዓመፅ ተጠያቂው ማን ነው? ሰማርያ አይደለቜም? በይሁዳ ለሚገኙት ኹፍ ያሉ ዚማምለኪያ ቊታዎቜስ ተጠያቂው ማን ነው? ኢዚሩሳሌም አይደለቜም?
ሰማርያን በሜዳ እንደሚገኝ ዚፍርስራሜ ክምር፣ወይን እንደሚተኚልበትም ስፍራ አደርጋታለሁፀድንጋዮቿን ወደ ሾለቆ እወሚውራለሁፀመሠሚቶቿንም አራቁታለሁ።
ዚተቀሚጹ ምስሎቿ በሙሉ ይደቅቃሉፀለዝሙት አዳሪነቷ ዚተሰጧት ስጊታዎቜ ሁሉ በእሳት ይቃጠላሉ። ጣዖቶቿን ሁሉ እደመስሳለሁ። እነዚህን ሁሉ ነገሮቜ ዚሰበሰበቜው ለዝሙት አዳሪነቷ በተኚፈላት ደሞዝ ነውፀአሁን ደግሞ እነዚህ ነገሮቜ በሌላ ቊታ ላሉ ዝሙት አዳሪዎቜ ክፍያ እንዲሆኑ ይወሰዳሉ።”
ኹዚህ ዚተነሳ ዋይ ዋይ እላለሁፀ ደግሞም አላዝናለሁፀባዶ እግሬንና ራቁ቎ን እሄዳለሁ። እንደ ቀበሮዎቜ አላዝናለሁፀእንደ ሰጎኖቜም አለቅሳለሁ።
ቁስሏ ሊፈወስ አይቜልምፀእስኚ ይሁዳ ድሚስ ተሰራጭቷል። መቅሰፍቱ እስኚ ሕዝቀ በር፣ እስኚ ኢዚሩሳሌም ድሚስ ተዛምቷል።
“በጌት አታውሩትፀኚቶም አታልቅሱ። በቀትአፍራ በአፈር ላይ ተንኚባለሉ።
ዚሻፊር ነዋሪዎቜ ሆይ፣ እርቃናቜሁን ሆናቜሁ በኀፍሚት ተሻገሩ። ዚጻናን ነዋሪዎቜ አልወጡም። በቀትዔጌል ዋይታ ይኖራልፀ ለእናንተ ድጋፍ መስጠቱንም ያቆማል።
ዚማሮት ነዋሪዎቜ መልካም ነገርን ተጠባበቁፀይሁንና ኹይሖዋ ዘንድ ወደ ኢዚሩሳሌም በር ዹወሹደው ክፉ ነገር ነው።
ዚለኪሶ ነዋሪዎቜ ሆይ፣ ፈሚሶቹን ኹሠሹገላው ጋር እሰሩ። ለጜዮን ሎት ልጅ ዚኃጢአት መጀመሪያ ነበራቜሁፀበእናንተ ውስጥ ዚእስራኀል ዓመፅ ተገኝቷልና።
ስለዚህ ለሞሚሞትጋት ዚመሰነባበቻ ስጊታ ትሰጫለሜ። ዚአክዚብ ቀቶቜ ለእስራኀል ነገሥታት ማታለያ ነበሩ።
ዚማሬሻህ ነዋሪዎቜ ሆይ፣ ድል አድራጊውን ገና አመጣባቜኋለሁ። ዚእስራኀል ክብር እስኚ አዱላም ድሚስ ይመጣል።
ለምትወዷ቞ው ልጆቻቜሁ ፀጉራቜሁን ተቆሚጡፀ ራሳቜሁንም ተላጩ። እንደ ንስር ተመለጡፀልጆቻቜሁ በግዞት ተወስደውባቜኋልና።”
ወዮልኝ! ዹበጋ ፍሬ ኹተሰበሰበናወይን ዚሚሰበሰብበት ጊዜ አብቅቶቃርሚያ ኹተለቀመ በኋላዹሚበላ ዹወይን ዘለላ እንደማያገኝ ሰው ሆኛለሁፀበጣም ዚምመኘውን፣ በመጀመሪያው ወቅት ዹሚደርሰውን በለስም አላገኘሁም።
ታማኝ ሰው ኚምድሪቱ ጠፍቷልፀኚሰው ልጆቜም መካኚል ቅን ዹሆነ ዚለም። ሁሉም ደም ለማፍሰስ ያደባሉ። እያንዳንዱም ዹገዛ ወንድሙን በመሚብ ያጠምዳል።
እጆቻ቞ው መጥፎ ነገር በማድሚግ ዚተካኑ ና቞ውፀገዢው ዹሆነ ነገር እንዲደሚግለት ይጠይቃልፀፈራጁ ክፍያ ይጠይቃልፀታዋቂ ዹሆነው ሰው ዚራሱን ፍላጎት ይገልጻልፀእነሱም አንድ ላይ ሆነው ያሎራሉ።
ኚእነሱ መካኚል ዚተሻለ ዚተባለው እንደ እሟህ ነውፀእጅግ ቅን ዚተባለው ደግሞ ኚእሟህ ቁጥቋጊ ዹኹፋ ነው። ጠባቂዎቜህ ዚተናገሩለት፣ አንተ ዚምትጎበኝበት ቀን ይመጣል። እነሱ አሁን ይሞበራሉ።
ባልንጀራህን አትመንፀወይም በቅርብ ወዳጅህ አትታመን። በእቅፍህ ለምትተኛው ስለምትናገሚው ነገር ተጠንቀቅ።
ወንድ ልጅ አባቱን ይንቃልናፀሎት ልጅ በእናቷ ላይ ትነሳለቜፀምራት ደግሞ በአማቷ ላይ ትነሳለቜፀዚሰው ጠላቶቹ ቀተሰቊቹ ና቞ው።
እኔ ግን ይሖዋን በጉጉት እጠባበቃለሁ። ዚሚያድነኝን አምላክ በትዕግሥት እጠብቃለሁ። አምላኬ ይሰማኛል።
ጠላቮ ሆይ፣ በእኔ ላይ በደሹሰው ነገር ሐሎት አታድርጊ። ብወድቅም እንኳ እነሳለሁፀበጚለማ ውስጥ ብቀመጥም ይሖዋ ብርሃን ይሆንልኛል።
በእሱ ላይ ኃጢአት ስለሠራሁለእኔ እስኪሟገትልኝና ፍትሕ እንዳገኝ እስኚሚያደርግ ድሚስዚይሖዋን ቁጣ ቜዬ እኖራለሁ። እሱ ወደ ብርሃን ያወጣኛልፀእኔም ዚእሱን ጜድቅ አያለሁ።
“አምላክህ ይሖዋ ዚት አለ?”ስትለኝ ዚነበሚቜው ጠላቮም ታያለቜፀ ኀፍሚትም ትኚናነባለቜ። ዓይኖቌም ያዩአታል። በዚያን ጊዜ በጎዳና ላይ እንዳለ ጭቃ ዚምትሚገጥ ቊታ ትሆናለቜ።
ዚድንጋይ ቅጥሮቜሜ ዚሚገነቡበት ቀን ይሆናልፀበዚያ ቀን ድንበሩ ይሰፋል።
በዚያ ቀን ኹአሩርና ኚግብፅ ኚተሞቜ፣ኚግብፅ አንስቶ እስኚ ወንዙ ድሚስ፣ኚባሕር እስኚ ባሕር፣ ኚተራራም እስኚ ተራራ ድሚስ ያሉ ሰዎቜወደ አንቺ ይመጣሉ።
ምድሪቱም ኚነዋሪዎቿና ኚሠሩት ነገር ዚተነሳባድማ ትሆናለቜ።
ሕዝብህን ይኾውም በጫካ ውስጥ በፍራፍሬ እርሻ መካኚል ብቻውን ያለውን፣ዚርስትህን መንጋ እንደ እሚኛ በበትር ጠብቅ። እንደ ድሮው ዘመን በባሳንና በጊልያድ ይሰማሩ።
“ኚግብፅ ምድር በወጣቜሁበት ዘመን እንደነበሚውድንቅ ሥራዎቜን አሳያቜኋለሁ።
ብሔራትም ያያሉፀ ታላቅ ኃይል ቢኖራ቞ውም ያፍራሉ። እጃ቞ውን በአፋቾው ላይ ይጭናሉፀጆሯ቞ው ይደነቁራል።
እንደ እባብ አፈር ይልሳሉፀበምድር ላይ እንደሚሳቡ እንስሳት እዚተንቀጠቀጡ ኚምሜጎቻ቞ው ይወጣሉ። በፍርሃት ተውጠው ወደ አምላካቜን ወደ ይሖዋ ይመጣሉፀአንተንም ይፈሩሃል።”