text
stringlengths
4
267
አንተ በቋጥኝ መሸሸጊያ ውስጥ የምትኖር፣መኖሪያህን በከፍታ ቦታ ላይ ያደረግክ፣በልብህ ‘ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይችላል?’ የምትል፣የልብህ እብሪት አታሎሃል።
መኖሪያህን እንደ ንስር ከፍ ብታደርግወይም ጎጆህን በከዋክብት መካከል ብትሠራ እንኳእኔ ከዚያ አወርድሃለሁ” ይላል ይሖዋ።
“ሌቦች ወደ አንተ ቢመጡ፣ ዘራፊዎች በሌሊት ቢገቡ(ታላቅ ጥፋት በደረሰብህ ነበር!) የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለም? ደግሞስ ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡጥቂት ቃርሚያ አያስቀሩም?
ኤሳው ምንኛ ተበረበረ! የተደበቀው ውድ ሀብቱ ምንኛ ተፈለገ!
እስከ ድንበሩ ድረስ እንድትሄድ አስገደዱህ። አጋሮችህ ሁሉ አታለውሃል። ከአንተ ጋር ሰላማዊ ግንኙነት የነበራቸው ሰዎች አይለውብሃል። ከአንተ ጋር የሚበሉ ሰዎች ከሥርህ መረብ ይዘረጉብሃል፤አንተ ግን አታስተውለውም።
በዚያ ቀን” ይላል ይሖዋ፣“ጥበበኞችን ከኤዶም አላጠፋም?ማስተዋልንስ ከኤሳው ተራራማ ምድር አላስወግድም?
ቴማን ሆይ፣ ተዋጊዎችሽ ይሸበራሉ፤ምክንያቱም እያንዳንዳቸው ታርደው ከተራራማው የኤሳው ምድር ይወገዳሉ።
በወንድምህ በያዕቆብ ላይ በተፈጸመው ግፍ የተነሳኀፍረት ትከናነባለህ፤ለዘላለምም ትጠፋለህ።
ዳር ቆመህ ትመለከት በነበረበት ጊዜ፣እንግዶች ሠራዊቱን ማርከው በወሰዱበትናየባዕድ አገር ሰዎች በበሩ ገብተው በኢየሩሳሌም ላይ ዕጣ በተጣጣሉበት ጊዜ፣አንተም ልክ እንደ እነሱ አደረግክ።
በወንድምህ ቀን ይኸውም ወንድምህ ክፉ ነገር በደረሰበት ቀን መፈንደቅ አይገባህም ነበር፤የይሁዳ ሕዝብ በጠፋበት ቀን ሐሴት ማድረግ አልነበረብህም፤ደግሞም በጭንቀታቸው ቀን በእብሪት መናገር አይገባህም ነበር።
በጥፋታቸው ቀን ወደ ሕዝቤ በር መምጣት አልነበረብህም፤በጥፋቱ ቀን በደረሰበት መከራ መፈንደቅ አይገባህም ነበር፤ደግሞም ጥፋት በደረሰበት ቀን ሀብቱን መውሰድ አልነበረብህም።
የሚሸሹትን የይሁዳ ሰዎች ለመግደል መንታ መንገድ ላይ መቆም አይገባህም ነበር፤በጭንቀቱም ቀን በሕይወት የተረፉትን አሳልፈህ መስጠት አልነበረብህም።
ይሖዋ በብሔራት ሁሉ ላይ የሚነሳበት ቀን ቀርቧልና። አንተ በእሱ ላይ እንዳደረግከው በአንተም ላይ ይደረጋል። በሌሎች ላይ ያደረግከው ነገር በገዛ ራስህ ላይ ይመለሳል።
እናንተ በቅዱሱ ተራራዬ ላይ እንደጠጣችሁ፣ልክ እንደዚሁ ብሔራት በሙሉ ዘወትር ይጠጣሉ። ይጠጣሉ፤ ደግሞም ይጨልጡታል፤ፈጽሞ እንዳልነበሩም ይሆናሉ።
ያመለጡት ግን በጽዮን ተራራ ላይ ይሆናሉ፤እሱም የተቀደሰ ይሆናል፤የያዕቆብ ቤት ሰዎችም የራሳቸው የሆኑትን ነገሮች ይወርሳሉ።
የያዕቆብ ቤት እሳት፣የዮሴፍም ቤት ነበልባል ይሆናል፤የኤሳው ቤት ደግሞ እንደ ገለባ ይሆናል፤እነሱም ያቃጥሏቸዋል፤ ይበሏቸዋልም፤ከኤሳውም ቤት የሚተርፍ አይኖርም፤ይሖዋ ራሱ ተናግሯልና።
እነሱ ኔጌብንና የኤሳውን ተራራማ ምድር፣ሸፌላንና የፍልስጤምን ምድር ይወርሳሉ። የኤፍሬምን መሬትና የሰማርያን መሬት ይወርሳሉ፤ቢንያምም ጊልያድን ይወርሳል።
እስከ ሰራፕታ ድረስ ያለው የከነአናውያን ምድር፣ከዚህ የመከላከያ ግንብ በግዞት የተወሰዱት ሰዎች ይኸውም የእስራኤል ሕዝብ ይዞታ ይሆናል። በሰፋራድ የነበሩት ከኢየሩሳሌም በግዞት የተወሰዱ ሰዎችም የኔጌብን ከተሞች ይወርሳሉ።
ሕዝቡን የሚታደጉ ሰዎችም በኤሳው ተራራማ ምድር ላይ ለመፍረድወደ ጽዮን ተራራ ይወጣሉ፤ንግሥናውም የይሖዋ ይሆናል።”
የይሖዋ ቃል ወደ አሚታይ ልጅ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣ፦
“ተነስተህ ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድና በእሷ ላይ የፍርድ መልእክት አውጅ፤ ክፋታቸውን አስተውያለሁና።”
ዮናስ ግን ከይሖዋ ፊት ኮብልሎ ወደ ተርሴስ ለመሄድ ተነሳ፤ ወደ ኢዮጴም ወረደ፤ ከዚያም ወደ ተርሴስ የምትሄድ መርከብ አገኘ። ከይሖዋም ፊት ሸሽቶ፣ በመርከቡ ውስጥ ከነበሩት ጋር ወደ ተርሴስ ለመሄድ የጉዞውን ዋጋ ከፍሎ ተሳፈረ።
ከዚያም ይሖዋ በባሕሩ ላይ ኃይለኛ ነፋስ አመጣ፤ ከባድ ማዕበል ስለተነሳ መርከቧ ልትሰበር ተቃረበች።
መርከበኞቹ እጅግ ከመፍራታቸው የተነሳ እርዳታ ለማግኘት እያንዳንዳቸው ወደየአምላካቸው ይጮኹ ጀመር። የመርከቧንም ክብደት ለመቀነስ በውስጧ የነበሩትን ዕቃዎች ወደ ባሕሩ መጣል ጀመሩ። ዮናስ ግን ወደ መርከቧ ውስጠኛ ክፍል ወርዶ ተኝቶ ነበር፤ ጭልጥ ያለ እንቅልፍም ወስዶት ነበር።
የመርከቧ አዛዥ ወደ እሱ ቀርቦ እንዲህ አለው፦ “እንዴት ትተኛለህ? ተነስተህ ወደ አምላክህ ጩኽ! ምናልባት እውነተኛው አምላክ ለእኛ አስቦ ከጥፋት ያድነን ይሆናል።”
ከዚያም እርስ በርሳቸው “ይህ መከራ የደረሰብን በማን ምክንያት እንደሆነ ማወቅ እንድንችል፣ ኑ ዕጣ እንጣጣል” ተባባሉ። በመሆኑም ዕጣ ተጣጣሉ፤ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወደቀ።
እነሱም እንዲህ አሉት፦ “ይህ መከራ የደረሰብን በማን ምክንያት እንደሆነ እባክህ ንገረን። ሥራህ ምንድን ነው? የመጣኸው ከየት ነው? አገርህስ የት ነው? ከየትኛውስ ሕዝብ ነህ?”
እሱም መልሶ “እኔ ዕብራዊ ነኝ፤ ባሕሩንና የብሱን የፈጠረውን የሰማያትን አምላክ ይሖዋን የምፈራ ሰው ነኝ” አላቸው።
በዚህ ጊዜ ሰዎቹ የባሰ ፈሩ፤ “ያደረግከው ነገር ምንድን ነው?” ብለው ጠየቁት። (ሰዎቹ ዮናስ ነግሯቸው ስለነበር ከይሖዋ ፊት እየሸሸ እንዳለ አወቁ።)
የባሕሩ ማዕበል እያየለ በመሄዱ “ባሕሩ ጸጥ እንዲልልን በአንተ ላይ ምን ብናደርግ ይሻላል?” አሉት።
እሱም “አንስታችሁ ወደ ባሕሩ ጣሉኝ፤ ባሕሩም ጸጥ ይልላችኋል፤ ይህ ከባድ ማዕበል የመጣባችሁ በእኔ የተነሳ መሆኑን አውቃለሁና” በማለት መለሰላቸው።
ሰዎቹ ግን መርከቧን ወደ የብስ ለመመለስ በኃይል ቀዘፉ፤ ይሁንና ማዕበሉ ይበልጥ እያየለባቸው ስለሄደ ሊሳካላቸው አልቻለም።
ከዚያም ወደ ይሖዋ በመጮኽ እንዲህ አሉ፦ “እንግዲህ ይሖዋ ሆይ፣ በዚህ ሰው ምክንያት እንዳንጠፋ እንለምንሃለን! ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ደስ እንዳሰኘህ ስላደረግክ ለንጹሕ ሰው ደም ተጠያቂ አታድርገን!”
ከዚያም ዮናስን አንስተው ወደ ባሕሩ ጣሉት፤ ባሕሩም መናወጡን አቆመ።
በዚህ ጊዜ ሰዎቹ ይሖዋን እጅግ ፈሩ፤ ለይሖዋም መሥዋዕት አቀረቡ፤ ስእለትም ተሳሉ።
ይሖዋም ዮናስን እንዲውጠው አንድ ትልቅ ዓሣ ላከ፤ ዮናስም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በዓሣው ሆድ ውስጥ ቆየ።
ከዚያም የይሖዋ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ እንዲህ ሲል ወደ ዮናስ መጣ፦
“ተነስተህ ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የምነግርህንም መልእክት በመካከሏ አውጅ።”
ዮናስም የይሖዋን ቃል በመታዘዝ ተነስቶ ወደ ነነዌ ሄደ። ነነዌ እጅግ ታላቅ ከተማ የነበረች ስትሆን በእግር የሦስት ቀን ያህል መንገድ ታስኬድ ነበር።
ዮናስም ወደ ከተማዋ ገብቶ የአንድ ቀን መንገድ ከተጓዘ በኋላ “ነነዌ በ40 ቀን ውስጥ ትደመሰሳለች” ብሎ አወጀ።
የነነዌም ሰዎች በአምላክ አመኑ፤ ከትልቁም አንስቶ እስከ ትንሹ ድረስ ጾም አወጁ፤ ማቅም ለበሱ።
የነነዌ ንጉሥ መልእክቱን በሰማ ጊዜ ከዙፋኑ ተነስቶ ልብሰ መንግሥቱን አወለቀ፤ ማቅም ለብሶ አመድ ላይ ተቀመጠ።
በተጨማሪም በመላው ነነዌ አዋጅ አስነገረ፤“ንጉሡና መኳንንቱ ያወጡት ድንጋጌ፦ ሰውም ሆነ እንስሳ፣ ከብትም ሆነ መንጋ ምንም ነገር አይቅመስ። ምግብ አይብሉ፤ ውኃም አይጠጡ።
ሰውም ሆነ እንስሳ ማቅ ይልበስ፤ ሁሉም አጥብቆ ወደ አምላክ ይጩኽ፤ ክፉ መንገዳቸውንና የሚፈጽሙትን ግፍ ይተዉ።
እኛ እንዳንጠፋ፣ እውነተኛው አምላክ ሊያመጣው ያሰበውን ነገር እንደገና በማጤን ከሚነደው ቁጣው ይመለስ እንደሆነ ማን ያውቃል?”
እውነተኛው አምላክ ያደረጉትን ነገር ይኸውም ከክፉ መንገዳቸው እንዴት እንደተመለሱ አየ፤ በእነሱም ላይ አመጣዋለሁ ያለውን ነገር መልሶ በማጤን ጥፋቱን ከማምጣት ተቆጠበ።
ከዚያም ዮናስ በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደ ይሖዋ ጸለየ፤
እንዲህም አለ፦ “ተጨንቄ ሳለሁ ወደ ይሖዋ ተጣራሁ፤ እሱም መለሰልኝ። በመቃብር ጥልቅ ውስጥ ሆኜ እርዳታ ለማግኘት ጮኽኩ። አንተም ድምፄን ሰማህ።
ወደ ጥልቁ፣ ወደ ታችኛው የባሕሩ ወለል በጣልከኝ ጊዜፈሳሹ ውኃ ዋጠኝ። ማዕበሎችህና ሞገዶችህ ሁሉ በላዬ አለፉ።
እኔም ‘ከፊትህ አባረርከኝ! ቅዱስ የሆነውን ቤተ መቅደስህን ዳግመኛ እንዴት መመልከት እችላለሁ?’ አልኩ።
ውኃው ዋጠኝ፤ ሕይወቴንም አደጋ ላይ ጣለው፤ጥልቁ ውኃ ከበበኝ። የባሕር አረም ራሴ ላይ ተጠመጠመ።
ወደ ተራሮች መሠረት ሰመጥኩ። የምድር መቀርቀሪያዎች ለዘላለም ተዘጉብኝ። ይሖዋ አምላኬ ሆይ፣ አንተ ግን ሕይወቴን ከጉድጓዱ ውስጥ አወጣህ።
ሕይወቴ እየተዳከመች ስትሄድ ይሖዋን አስታወስኩ። ጸሎቴም ወደ አንተ፣ ቅዱስ ወደሆነው ቤተ መቅደስህ ገባ።
ለማይረቡ ጣዖቶች ያደሩ ሰዎች ታማኝ ፍቅር የሚያሳያቸውን ይተዋሉ።
እኔ ግን በምስጋና ድምፅ መሥዋዕት አቀርብልሃለሁ። የተሳልኩትን እከፍላለሁ። መዳን ከይሖዋ ነው።”
በኋላም ይሖዋ ዓሣውን አዘዘው፤ ዓሣውም ዮናስን በደረቅ ምድር ላይ ተፋው።
ሆኖም ይህ ጉዳይ ዮናስን ፈጽሞ አላስደሰተውም፤ በመሆኑም እጅግ ተቆጣ።
ወደ ይሖዋም እንዲህ ሲል ጸለየ፦ “ይሖዋ ሆይ፣ በገዛ አገሬ ሳለሁ ያሳሰበኝ ጉዳይ ይህ አልነበረም? መጀመሪያውኑም ወደ ተርሴስ ለመሸሽ የሞከርኩት ለዚህ ነበር፤ አንተ ሩኅሩኅና መሐሪ አምላክ፣ ለቁጣ የዘገየህና ታማኝ ፍቅርህ የበዛ፣ አዝነህም ጥፋት ከማምጣት የምትቆጠብ እንደሆንክ አውቃለሁና።
አሁንም ይሖዋ ሆይ፣ በሕይወት ከመኖር ይልቅ መሞት ስለሚሻለኝ እባክህ ግደለኝ።”
ይሖዋም “እንዲህ መቆጣትህ ተገቢ ነው?” ብሎ ጠየቀው።
ከዚያም ዮናስ ከከተማዋ ወጥቶ በስተ ምሥራቅ በኩል ተቀመጠ። በዚያም ለራሱ መጠለያ ሠርቶ በከተማዋ ላይ የሚደርሰውን ነገር ለማየት በጥላው ሥር ተቀመጠ።
በዚህ ጊዜ ይሖዋ አምላክ፣ ዮናስ ራሱን እንዲያስጠልልባትና ከሥቃዩ እንዲያርፍ ሲል አንዲት የቅል ተክል ከበላዩ እንድታድግ አደረገ። ዮናስም በቅል ተክሏ እጅግ ተደሰተ።
ይሁን እንጂ እውነተኛው አምላክ በሚቀጥለው ቀን፣ ማለዳ ላይ አንድ ትል ላከ፤ ትሉም የቅል ተክሏን በላት፤ ተክሏም ደረቀች።
ፀሐይ መውጣት ስትጀምር አምላክ የሚያቃጥል የምሥራቅ ነፋስ አመጣ፤ ፀሐይዋም የዮናስን አናት አቃጠለችው፤ እሱም ተዝለፈለፈ። እንዲሞትም ለመነ፤ ደግሞ ደጋግሞም “በሕይወት ከምኖር ብሞት ይሻለኛል” አለ።
አምላክም ዮናስን “ስለ ቅል ተክሏ እንዲህ መቆጣትህ ተገቢ ነው?” ሲል ጠየቀው። እሱም “መቆጣት ሲያንሰኝ ነው፤ እንዲያውም ብሞት ይሻለኛል” አለ።
ይሖዋ ግን እንዲህ አለው፦ “አንተ በአንድ ሌሊት አድጋ በአንድ ሌሊት ለጠፋችው፣ ላልደከምክባት ወይም ላላሳደግካት የቅል ተክል አዝነሃል።
ታዲያ እኔ ትክክልና ስህተት የሆነውን ነገር ለይተው የማያውቁ ከ120,000 በላይ የሚሆኑ ሰዎችና በርካታ እንስሶቻቸው ለሚኖሩባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ ላዝን አይገባም?”
በይሁዳ ነገሥታት በኢዮዓታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞረሸታዊው ወደ ሚክያስ የመጣው እንዲሁም ሚክያስ ስለ ሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም በራእይ ያየው የይሖዋ ቃል ይህ ነው።”
“እናንተ ሕዝቦች ሁላችሁም ስሙ! ምድርና በውስጧ ያሉ ሁሉ፣ በትኩረት ያዳምጡ፤ይሖዋ ቅዱስ በሆነው ቤተ መቅደሱ ነው። ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ በእናንተ ላይ ይመሥክርባችሁ።
እነሆ፣ ይሖዋ ከስፍራው ይወጣል፤ወደ ታች ወርዶ የምድርን ከፍ ያሉ ቦታዎች ይረግጣል።
በእሳት ፊት እንዳለ ሰምናበገደል ላይ እንደሚወርድ ውኃተራሮቹ ከሥሩ ይቀልጣሉ፤ሸለቆዎቹም ይሰነጠቃሉ።
ይህ ሁሉ የሆነው በያዕቆብ ዓመፅ፣በእስራኤልም ቤት ኃጢአት የተነሳ ነው። ለያዕቆብ ዓመፅ ተጠያቂው ማን ነው? ሰማርያ አይደለችም? በይሁዳ ለሚገኙት ከፍ ያሉ የማምለኪያ ቦታዎችስ ተጠያቂው ማን ነው? ኢየሩሳሌም አይደለችም?
ሰማርያን በሜዳ እንደሚገኝ የፍርስራሽ ክምር፣ወይን እንደሚተከልበትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ እወረውራለሁ፤መሠረቶቿንም አራቁታለሁ።
የተቀረጹ ምስሎቿ በሙሉ ይደቅቃሉ፤ለዝሙት አዳሪነቷ የተሰጧት ስጦታዎች ሁሉ በእሳት ይቃጠላሉ። ጣዖቶቿን ሁሉ እደመስሳለሁ። እነዚህን ሁሉ ነገሮች የሰበሰበችው ለዝሙት አዳሪነቷ በተከፈላት ደሞዝ ነው፤አሁን ደግሞ እነዚህ ነገሮች በሌላ ቦታ ላሉ ዝሙት አዳሪዎች ክፍያ እንዲሆኑ ይወሰዳሉ።”
ከዚህ የተነሳ ዋይ ዋይ እላለሁ፤ ደግሞም አላዝናለሁ፤ባዶ እግሬንና ራቁቴን እሄዳለሁ። እንደ ቀበሮዎች አላዝናለሁ፤እንደ ሰጎኖችም አለቅሳለሁ።
ቁስሏ ሊፈወስ አይችልም፤እስከ ይሁዳ ድረስ ተሰራጭቷል። መቅሰፍቱ እስከ ሕዝቤ በር፣ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ተዛምቷል።
“በጌት አታውሩት፤ከቶም አታልቅሱ። በቤትአፍራ በአፈር ላይ ተንከባለሉ።
የሻፊር ነዋሪዎች ሆይ፣ እርቃናችሁን ሆናችሁ በኀፍረት ተሻገሩ። የጻናን ነዋሪዎች አልወጡም። በቤትዔጼል ዋይታ ይኖራል፤ ለእናንተ ድጋፍ መስጠቱንም ያቆማል።
የማሮት ነዋሪዎች መልካም ነገርን ተጠባበቁ፤ይሁንና ከይሖዋ ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም በር የወረደው ክፉ ነገር ነው።
የለኪሶ ነዋሪዎች ሆይ፣ ፈረሶቹን ከሠረገላው ጋር እሰሩ። ለጽዮን ሴት ልጅ የኃጢአት መጀመሪያ ነበራችሁ፤በእናንተ ውስጥ የእስራኤል ዓመፅ ተገኝቷልና።
ስለዚህ ለሞረሸትጋት የመሰነባበቻ ስጦታ ትሰጫለሽ። የአክዚብ ቤቶች ለእስራኤል ነገሥታት ማታለያ ነበሩ።
የማሬሻህ ነዋሪዎች ሆይ፣ ድል አድራጊውን ገና አመጣባችኋለሁ። የእስራኤል ክብር እስከ አዱላም ድረስ ይመጣል።
ለምትወዷቸው ልጆቻችሁ ፀጉራችሁን ተቆረጡ፤ ራሳችሁንም ተላጩ። እንደ ንስር ተመለጡ፤ልጆቻችሁ በግዞት ተወስደውባችኋልና።”
ወዮልኝ! የበጋ ፍሬ ከተሰበሰበናወይን የሚሰበሰብበት ጊዜ አብቅቶቃርሚያ ከተለቀመ በኋላየሚበላ የወይን ዘለላ እንደማያገኝ ሰው ሆኛለሁ፤በጣም የምመኘውን፣ በመጀመሪያው ወቅት የሚደርሰውን በለስም አላገኘሁም።
ታማኝ ሰው ከምድሪቱ ጠፍቷል፤ከሰው ልጆችም መካከል ቅን የሆነ የለም። ሁሉም ደም ለማፍሰስ ያደባሉ። እያንዳንዱም የገዛ ወንድሙን በመረብ ያጠምዳል።
እጆቻቸው መጥፎ ነገር በማድረግ የተካኑ ናቸው፤ገዢው የሆነ ነገር እንዲደረግለት ይጠይቃል፤ፈራጁ ክፍያ ይጠይቃል፤ታዋቂ የሆነው ሰው የራሱን ፍላጎት ይገልጻል፤እነሱም አንድ ላይ ሆነው ያሴራሉ።
ከእነሱ መካከል የተሻለ የተባለው እንደ እሾህ ነው፤እጅግ ቅን የተባለው ደግሞ ከእሾህ ቁጥቋጦ የከፋ ነው። ጠባቂዎችህ የተናገሩለት፣ አንተ የምትጎበኝበት ቀን ይመጣል። እነሱ አሁን ይሸበራሉ።
ባልንጀራህን አትመን፤ወይም በቅርብ ወዳጅህ አትታመን። በእቅፍህ ለምትተኛው ስለምትናገረው ነገር ተጠንቀቅ።
ወንድ ልጅ አባቱን ይንቃልና፤ሴት ልጅ በእናቷ ላይ ትነሳለች፤ምራት ደግሞ በአማቷ ላይ ትነሳለች፤የሰው ጠላቶቹ ቤተሰቦቹ ናቸው።
እኔ ግን ይሖዋን በጉጉት እጠባበቃለሁ። የሚያድነኝን አምላክ በትዕግሥት እጠብቃለሁ። አምላኬ ይሰማኛል።
ጠላቴ ሆይ፣ በእኔ ላይ በደረሰው ነገር ሐሴት አታድርጊ። ብወድቅም እንኳ እነሳለሁ፤በጨለማ ውስጥ ብቀመጥም ይሖዋ ብርሃን ይሆንልኛል።
በእሱ ላይ ኃጢአት ስለሠራሁለእኔ እስኪሟገትልኝና ፍትሕ እንዳገኝ እስከሚያደርግ ድረስየይሖዋን ቁጣ ችዬ እኖራለሁ። እሱ ወደ ብርሃን ያወጣኛል፤እኔም የእሱን ጽድቅ አያለሁ።
“አምላክህ ይሖዋ የት አለ?”ስትለኝ የነበረችው ጠላቴም ታያለች፤ ኀፍረትም ትከናነባለች። ዓይኖቼም ያዩአታል። በዚያን ጊዜ በጎዳና ላይ እንዳለ ጭቃ የምትረገጥ ቦታ ትሆናለች።
የድንጋይ ቅጥሮችሽ የሚገነቡበት ቀን ይሆናል፤በዚያ ቀን ድንበሩ ይሰፋል።
በዚያ ቀን ከአሦርና ከግብፅ ከተሞች፣ከግብፅ አንስቶ እስከ ወንዙ ድረስ፣ከባሕር እስከ ባሕር፣ ከተራራም እስከ ተራራ ድረስ ያሉ ሰዎችወደ አንቺ ይመጣሉ።
ምድሪቱም ከነዋሪዎቿና ከሠሩት ነገር የተነሳባድማ ትሆናለች።
ሕዝብህን ይኸውም በጫካ ውስጥ በፍራፍሬ እርሻ መካከል ብቻውን ያለውን፣የርስትህን መንጋ እንደ እረኛ በበትር ጠብቅ። እንደ ድሮው ዘመን በባሳንና በጊልያድ ይሰማሩ።
“ከግብፅ ምድር በወጣችሁበት ዘመን እንደነበረውድንቅ ሥራዎችን አሳያችኋለሁ።
ብሔራትም ያያሉ፤ ታላቅ ኃይል ቢኖራቸውም ያፍራሉ። እጃቸውን በአፋቸው ላይ ይጭናሉ፤ጆሯቸው ይደነቁራል።
እንደ እባብ አፈር ይልሳሉ፤በምድር ላይ እንደሚሳቡ እንስሳት እየተንቀጠቀጡ ከምሽጎቻቸው ይወጣሉ። በፍርሃት ተውጠው ወደ አምላካችን ወደ ይሖዋ ይመጣሉ፤አንተንም ይፈሩሃል።”