text
stringlengths
4
267
ያመኑትም ሁሉ አብሚው ነበሩፀ ያላ቞ውም ነገር ሁሉ ዚጋራ ነበርፀ
በተጚማሪም ያላ቞ውን ሀብትና ንብሚት በመሞጥ ገንዘቡን ለሁሉም አኚፋፈሉ። ለእያንዳንዱም ሰው ዚሚያስፈልገውን ያህል ሰጡ።
በዚዕለቱም በአንድ ልብ ሆነው በቀተ መቅደሱ አዘውትሚው ይገኙ ነበርፀ ምግባ቞ውንም በተለያዩ ቀቶቜ ይበሉ ዹነበሹ ሲሆን ዚሚመገቡትም በታላቅ ደስታና በንጹሕ ልብ ነበርፀ
አምላክንም ያወድሱ ዹነበሹ ኹመሆኑም በላይ በሰው ሁሉ ፊት ሞገስ አግኝተው ነበር። ይሖዋም ዚሚድኑ ሰዎቜን በዚዕለቱ በእነሱ ላይ ይጹምር ነበር።
በቂሳርያ “ዚጣሊያን ክፍለ ጩር” ተብሎ በሚጠራ ሠራዊት ውስጥ ቆርኔሌዎስ ዚሚባል አንድ ዹጩር መኮንን ነበር።
እሱም ኹመላው ቀተሰቡ ጋር ለአምላክ ያደሚና ፈሪሃ አምላክ ዹነበሹው ሰው ሲሆን ለሰዎቜ ምጜዋት ዚሚሰጥና ዘወትር ወደ አምላክ ዚሚማልድ ሰው ነበር።
ኹቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ አንድ ዹአምላክ መልአክ ወደ እሱ ሲመጣ በራእይ በግልጜ አዚፀ መልአኩም “ቆርኔሌዎስ!” አለው።
ቆርኔሌዎስም በድንጋጀ ትኩር ብሎ እያዚው “ጌታ ሆይ፣ ምንድን ነው?” በማለት ጠዚቀው። እሱም እንዲህ አለው፩ “ጞሎትህና ምጜዋትህ በአምላክ ፊት መታሰቢያ እንዲሆን አርጓል።
ስለዚህ አሁን ወደ ኢዮጎ ሰዎቜ ልኹህ ጎጥሮስ ተብሎ ዚሚጠራውን ስምዖንን አስጠራው።
ይህ ሰው፣ ቀቱ በባሕሩ አጠገብ በሚገኘው በቆዳ ፋቂው በስምዖን ቀት በእንግድነት አርፏል።”
ያነጋገሚው መልአክ ተለይቶት እንደሄደ ኚአገልጋዮቹ ሁለቱን እንዲሁም እሱን በቅርብ ኚሚያገለግሉት ወታደሮቜ መካኚል ለአምላክ ያደሚ አንድ ወታደር ጠራፀ
ዹሆነውንም ነገር ሁሉ ኚነገራ቞ው በኋላ ወደ ኢዮጎ ላካ቞ው።
በማግስቱም ዚተላኩት ሰዎቜ ተጉዘው ወደ ኹተማዋ ሲቃሚቡ ጎጥሮስ ኹቀኑ ስድስት ሰዓት ገደማ ሊጾልይ ወደ ሰገነት ወጣ።
ይሁን እንጂ በጣም ኚመራቡ ዚተነሳ መብላት ፈለገ። ምግብ እዚተዘጋጀ ሳለም ሰመመን ውስጥ ገባፀ
ሰማይም ተኚፍቶ ትልቅ ጹርቅ ዚሚመስል ነገር በአራቱም ጫፍ ተይዞ ወደ ምድር ሲወርድ አዚፀ
በላዩም ዚተለያዩ በምድር ላይ ዚሚኖሩ አራት እግር ያላ቞ው እንስሳትና በምድር ላይ ዚሚሳቡ ፍጥሚታት እንዲሁም ዹሰማይ ወፎቜ ነበሩ።
ኚዚያም አንድ ድምፅ “ጎጥሮስ፣ ተነሳና አርደህ ብላ!” አለው።
ጎጥሮስ ግን “ጌታ ሆይ፣ በጭራሜፀ ምክንያቱም እኔ ንጹሕ ያልሆነና ዹሹኹሰ ነገር በልቌ አላውቅም” አለ።
ያም ድምፅ እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ “አምላክ ንጹሕ ያደሚገውን ነገር ርኩስ ነው ማለትህን ተው” አለው።
ይህም ለሊስተኛ ጊዜ ተደገመፀ ወዲያውኑም ጹርቅ ዚሚመስለው ነገር ወደ ሰማይ ተወሰደ።
ጎጥሮስ ‘ዚራእዩ ትርጉም ምን ይሆን’ በማለት በጣም ግራ ተጋብቶ እያለ ቆርኔሌዎስ ዚላካ቞ው ሰዎቜ ዚስምዖንን ቀት አጠያይቀው መጡና ዹውጭው በር ላይ ቆሙ።
ኚዚያም ተጣርተው ጎጥሮስ ተብሎ ዚሚጠራው ስምዖን በዚያ በእንግድነት አርፎ እንደሆነ ጠዚቁ።
ጎጥሮስ ያዚውን ራእይ በሐሳቡ እያወጣና እያወሚደ ሳለ መንፈስ እንዲህ አለው፩ “እነሆ፣ ሊስት ሰዎቜ ይፈልጉሃል።
ስለዚህ ተነስተህ ወደ ታቜ ውሚድፀ ዹላክኋቾው እኔ ስለሆንኩ ምንም ሳትጠራጠር አብሚሃ቞ው ሂድ።”
ጎጥሮስም ሰዎቹ ወዳሉበት ወርዶ “ዚምትፈልጉት ሰው እኔ ነኝ። ወደዚህ ዚመጣቜሁት ለምንድን ነው?” አላ቞ው።
እነሱም እንዲህ አሉ፩ “በአይሁዳውያን ሁሉ ዚተመሠኚሚለት ቆርኔሌዎስ ዚተባለ ጻድቅና አምላክን ዚሚፈራ አንድ ዹጩር መኮንን፣ ወደ አንተ መልእክተኞቜ ልኮ ወደ ቀቱ እንዲያስመጣህና ዚምትለውን ነገር እንዲሰማ አንድ ቅዱስ መልአክ መለኮታዊ መመሪያ ሰጥቶታል።”
እሱም ወደ ቀት አስገብቶ አስተናገዳ቞ው። በማግስቱም ተነስቶ ኚእነሱ ጋር ሄደፀ በኢዮጎ ያሉ አንዳንድ ወንድሞቜም አብሚውት ሄዱ።
በሚቀጥለው ቀንም ወደ ቂሳርያ ገባ። ቆርኔሌዎስም ዘመዶቹንና ዚቅርብ ወዳጆቹን ሰብስቊ እዚጠበቃ቞ው ነበር።
ጎጥሮስም በገባ ጊዜ ቆርኔሌዎስ ተቀበለውና እግሩ ላይ ወድቆ ሰገደለት።
ጎጥሮስ ግን “ተነስ፣ እኔም እንደ አንተው ሰው ነኝ” ብሎ አስነሳው።
ኚእሱ ጋር እዚተነጋገሚ ወደ ውስጥ ሲገባም ብዙ ሰዎቜ ተሰብስበው አገኘ።
እሱም እንዲህ አላቾው፩ “አንድ አይሁዳዊ ኹሌላ ዘር ጋር ይወዳጅ ወይም ይቀራሚብ ዘንድ ሕጉ እንደማይፈቅድ በሚገባ ታውቃላቜሁፀ ሆኖም አምላክ ማንንም ሰው ንጹሕ ያልሆነ ወይም ርኩስ ማለት እንደማይገባኝ ገልጊልኛል።
በመሆኑም በተጠራሁ ጊዜ ምንም ሳላንገራግር መጣሁ። ስለዚህ ለምን እንዳስጠራቜሁኝ ማወቅ እፈልጋለሁ።”
ቆርኔሌዎስም እንዲህ አለ፩ “ኚአራት ቀን በፊት በዚሁ ሰዓት ይኾውም ኹቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በቀ቎ ሆኜ እዚጞለይኩ ሳለ ዚሚያንጞባርቅ ልብስ ዹለበሰ ሰው ድንገት ፊቮ ቆሞ
እንዲህ አለኝ፩ ‘ቆርኔሌዎስ፣ ጞሎትህ ተሰምቶልሃልፀ ምጜዋትህም በአምላክ ፊት ታስቊልሃል።
ስለዚህ ወደ ኢዮጎ ሰዎቜ ልኹህ ጎጥሮስ ተብሎ ዚሚጠራውን ስምዖንን አስጠራው። ይህ ሰው፣ ቀቱ በባሕሩ አጠገብ በሚገኘው በቆዳ ፋቂው በስምዖን ቀት በእንግድነት አርፏል።’
እኔም ወዲያውኑ ሰዎቜ ላክሁብህፀ አንተም በመምጣትህ መልካም አድርገሃል። ስለዚህ አሁን እኛ ይሖዋ እንድትናገር ያዘዘህን ነገር ሁሉ ለመስማት ይኾው ሁላቜንም በአምላክ ፊት ተገኝተናል።”
በዚህ ጊዜ ጎጥሮስ እንዲህ ሲል መናገር ጀመሹ፩ “እነሆ፣ አምላክ እንደማያዳላ በእርግጥ አስተዋልኩፀ
ኹዚህ ይልቅ ኚዚትኛውም ብሔር ቢሆን እሱን ዚሚፈራና ትክክል ዹሆነውን ነገር ዚሚያደርግ ሰው በእሱ ዘንድ ተቀባይነት አለው።
አምላክ በኢዚሱስ ክርስቶስ በኩል ለእስራኀል ልጆቜ ዹሰላም ምሥራቜ ለማወጅ ቃሉን ላኚላ቞ውፀ ይህም ምሥራቜ ኢዚሱስ ዹሁሉ ጌታ እንደሆነ ዚሚገልጜ ነው።
ዮሐንስ ስለ ጥምቀት ኹሰበኹ በኋላ ኹገሊላ አንስቶ በመላው ይሁዳ ይወራ ስለነበሚው ጉዳይ ታውቃላቜሁፀ
ዚተወራውም ስለ ናዝሬቱ ኢዚሱስ ነው። አምላክ በመንፈስ ቅዱስ ቀባውፀ ደግሞም ኃይል ሰጠውፀ ኢዚሱስም አምላክ ኚእሱ ጋር ስለነበር መልካም ነገር እያደሚገና በዲያብሎስ ቁጥጥር ሥር ዚወደቁትን እዚፈወሰ በዚያ አገር ሁሉ ተዘዋወሚ።
እሱ በአይሁዳውያን አገርም ሆነ በኢዚሩሳሌም ላደሹጋቾው ነገሮቜ ሁሉ እኛ ምሥክሮቜ ነንፀ እነሱ ግን በእንጚት ላይ ሰቅለው ገደሉት።
አምላክ እሱን በሊስተኛው ቀን አስነሳውፀ ኚዚያም ለሰዎቜ እንዲገለጥ አደሚገውፀ
ዹተገለጠው ግን ለሁሉም ሰው ሳይሆን አምላክ አስቀድሞ ለመሚጣ቞ው ምሥክሮቜ ይኾውም ኚሞት ኚተነሳ በኋላ አብሚነው ለበላንና ለጠጣን ለእኛ ነው።
በተጚማሪም አምላክ እሱን በሕያዋንና በሙታን ላይ ፈራጅ አድርጎ እንደሟመው ለሰዎቜ እንድንሰብክና በተሟላ ሁኔታ እንድንመሠክር አዘዘን።
በእሱ ዚሚያምን ሁሉ በስሙ ዚኃጢአት ይቅርታ እንደሚያገኝ ነቢያት ሁሉ ስለ እሱ ይመሠክራሉ።”
ጎጥሮስ ስለዚህ ጉዳይ ገና እዚተናገሚ ሳለ ቃሉን እዚሰሙ በነበሩት ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወሚደ።
ኚጎጥሮስ ጋር ዚመጡት ዹተገሹዙ አማኞቜ ዚመንፈስ ቅዱስ ነፃ ስጊታ ኚአሕዛብ ወገን በሆኑ ሰዎቜም ላይ በመፍሰሱ ተገሚሙ።
ምክንያቱም በባዕድ ቋንቋዎቜ ሲናገሩና አምላክን ሲያወድሱ ይሰሟቾው ነበር። በዚህ ጊዜ ጎጥሮስ እንዲህ አለ፩
“እንደ እኛው መንፈስ ቅዱስ ዚተቀበሉትን እነዚህን ሰዎቜ በውኃ እንዳይጠመቁ ሊኹለክላቾው ዚሚቜል አለ?”
ይህን ካለ በኋላ በኢዚሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ አዘዛ቞ው። ኚዚያም ዹተወሰነ ቀን አብሯ቞ው እንዲቆይ ለመኑት።
ኚዚያም ጳውሎስ ወደ ደርቀና ወደ ልስጥራ ሄደ። በዚያም አማኝ ዚሆነቜ አይሁዳዊት እናትና ግሪካዊ አባት ያለው ጢሞ቎ዎስ ዚሚባል አንድ ደቀ መዝሙር ነበርፀ
እሱም በልስጥራና በኢቆንዮን ባሉ ወንድሞቜ፣ በመልካም ምግባሩ ዚተመሠኚሚለት ነበር።
ጳውሎስ፣ ጢሞ቎ዎስ አብሮት እንዲሄድ እንደሚፈልግ ገለጞፀ አባቱ ግሪካዊ መሆኑን ሁሉም ሰው ያውቅ ስለነበሚም በእነዚያ አካባቢዎቜ ስላሉት አይሁዳውያን ሲል ወስዶ ገሚዘው።
በዚኚተሞቹ ሲያልፉም በዚያ ለሚያገኟ቞ው ሁሉ በኢዚሩሳሌም ያሉት ሐዋርያትና ሜማግሌዎቜ ያስተላለፏ቞ውን ውሳኔዎቜ እንዲጠብቁ ጉዳዩን ያሳውቋ቞ው ነበር።
ጉባኀዎቹም በእምነት እዚጠነኚሩና ኚዕለት ወደ ዕለት በቁጥር እዚጚመሩ ሄዱ።
ኹዚህም ሌላ መንፈስ ቅዱስ ቃሉን በእስያ አውራጃ እንዳይናገሩ ስለኚለኚላ቞ው በፍርግያና በገላትያ አድርገው አለፉ።
ደግሞም ወደ ሚስያ በወሚዱ ጊዜ ወደ ቢቲኒያ ሊገቡ ሞኚሩፀ ሆኖም ዚኢዚሱስ መንፈስ አልፈቀደላ቞ውም።
ስለዚህ በሚስያ በኩል አልፈው ወደ ጥሮአስ ወሚዱ።
ጳውሎስም ሌሊት በራእይ አንድ ዚመቄዶንያ ሰው በዚያ ቆሞ “ወደ መቄዶንያ ተሻገርና እርዳን” ብሎ ሲለምነው አዚ።
ጳውሎስ ይህን ራእይ እንዳዚም ‘አምላክ ምሥራቹን እንድንሰብክላ቞ው ጠርቶናል’ ዹሚል መደምደሚያ ላይ ስለደሚስን ወደ መቄዶንያ ለመሄድ ሞኚርን።
ስለዚህ ኚጥሮአስ መርኚብ ተሳፍሚን በቀጥታ ወደ ሳሞትራቄ ሄድንፀ በማግስቱ ደግሞ ወደ ኔያጶሊስ ተጓዝንፀ
ኚዚያም ተነስተን ዚሮማውያን ቅኝ ግዛትና ዚመቄዶንያ አውራጃ ቁልፍ ኹተማ ወደሆነቜው ወደ ፊልጵስዩስ መጣን። በዚህቜ ኹተማም ለተወሰኑ ቀናት ቆዚን።
በሰንበት ቀን ዚጞሎት ስፍራ ይገኝበታል ብለን ወዳሰብነው ኹኹተማው በር ውጭ ወዳለ አንድ ወንዝ ዳር ሄድንፀ በዚያም ተቀምጠን ተሰብስበው ለነበሩት ሎቶቜ መናገር ጀመርን።
ኚትያጥሮን ኹተማ ዚመጣቜ፣ ሐምራዊ ጹርቅ ዚምትሞጥና አምላክን ዚምታመልክ ሊዲያ ዚተባለቜ አንዲት ሎት እያዳመጠቜ ነበርፀ ይሖዋም ጳውሎስ ዹሚናገሹውን በማስተዋል እንድትሰማ ልቧን በደንብ ኚፈተላት።
እሷና በቀቷ ዚሚኖሩ ሰዎቜ ኹተጠመቁ በኋላ “ለይሖዋ ታማኝ እንደሆንኩ አድርጋቜሁ ኚቆጠራቜሁኝ ወደ ቀ቎ ገብታቜሁ እሚፉ” ብላ ተማጞነቜን። እንድንገባም አስገደደቜን።
አንድ ቀን ወደ ጞሎት ስፍራ እዚሄድን ሳለ መንፈስ ይኾውም ዚጥንቆላ ጋኔን ያደሚባት አንዲት አገልጋይ አገኘቜን። እሷም በጥንቆላ ሥራዋ ለጌቶቿ ብዙ ትርፍ ታስገኝላ቞ው ነበር።
ይህቜ ሎት ጳውሎስንና እኛን እዚተኚተለቜ “እነዚህ ሰዎቜ ዚመዳንን መንገድ ዚሚያውጁላቜሁ ዹልዑሉ አምላክ ባሪያዎቜ ናቾው” በማለት ትጮኜ ነበር።
ለብዙ ቀናት እዚደጋገመቜ ይህንኑ ትናገር ነበር። በመጚሚሻም ጳውሎስ በዚህ ነገር በመሰላ቞ቱ ዞር ብሎ ያን መንፈስ “ኚእሷ እንድትወጣ በኢዚሱስ ክርስቶስ ስም አዝሃለሁ” አለው። መንፈሱም በዚያው ቅጜበት ወጣ።
ጌቶቿ ዚገቢ ምንጫ቞ው መቋሚጡን ባዩ ጊዜ ጳውሎስንና ሲላስን ይዘው እዚጎተቱ ገዢዎቹ ወደሚገኙበት ወደ ገበያ ስፍራው ወሰዷ቞ው።
ኚዚያም ዹኹተማዋ ሕግ አስኚባሪዎቜ ፊት አቅርበዋቾው እንዲህ አሉ፩ “እነዚህ ሰዎቜ ኚተማቜንን ክፉኛ እያወኩ ነው። እነሱ አይሁዳውያን ና቞ውፀ
ደግሞም እኛ ሮማውያን ልንቀበለውም ሆነ ልንፈጜመው ዚማይገባንን ልማድ እያስፋፉ ነው።”
ሕዝቡም በአንድነት በእነሱ ላይ ተነሳፀ ዹኹተማዋ ሕግ አስኚባሪዎቜም ልብሳ቞ውን ኹገፈፏቾው በኋላ በበትር እንዲደበደቡ አዘዙ።
በጣም ኹደበደቧቾው በኋላ እስር ቀት አስገቧ቞ውፀ ዚእስር ቀቱንም ጠባቂ በደንብ እንዲጠብቃ቞ው አዘዙት።
እሱም እንዲህ ያለ ትእዛዝ ስለተሰጠው ወደ እስር ቀቱ ውስጠኛ ክፍል አስገብቶ እግራ቞ውን በእግር ግንድ አሰሚው።
ይሁንና እኩለ ሌሊት ገደማ ጳውሎስና ሲላስ እዚጞለዩና አምላክን በመዝሙር እያወደሱ ነበርፀ ሌሎቹ እስሚኞቜም ያዳምጧ቞ው ነበር።
ድንገት ኚባድ ዚምድር ነውጥ በመኚሰቱ ዚእስር ቀቱ መሠሚት ተናጋ። በተጚማሪም በሮቹ ወዲያውኑ ዚተኚፈቱ ሲሆን ሁሉም ዚታሰሩበት ማሰሪያ ተፈታ።
ዚእስር ቀቱ ጠባቂም ኚእንቅልፉ ነቅቶ ዚእስር ቀቱ በሮቜ መኚፈታ቞ውን ሲያይ እስሚኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ለመግደል ሰይፉን መዘዘ።
ጳውሎስ ግን ድምፁን ኹፍ አድርጎ “በራስህ ላይ ክፉ ነገር አታድርግ! ሁላቜንም እዚህ አለን” ሲል ተናገሚ።
በዚህ ጊዜ ዚእስር ቀቱ ጠባቂ መብራት እንዲያመጡለት ጠይቆ ወደ ውስጥ ዘሎ ገባፀ እዚተንቀጠቀጠም በጳውሎስና በሲላስ ፊት ተደፋ።
ወደ ውጭ ካወጣ቞ውም በኋላ “ጌቶቌ፣ ለመዳን ምን ማድሚግ ይኖርብኛል?” አለ።
እነሱም “በጌታ ኢዚሱስ እመንፀ አንተም ሆንክ ቀተሰብህ ትድናላቜሁ” አሉት።
ኚዚያም ለእሱና በቀቱ ላሉት ሰዎቜ ሁሉ ዹይሖዋን ቃል ነገሯ቞ው።
ጠባቂውም ሌሊት በዚያው ሰዓት ይዟቾው ሄዶ ቁስላ቞ውን አጠበላ቞ው። ኚዚያም እሱና መላው ቀተሰቡ ወዲያውኑ ተጠመቁ።
ወደ ቀቱም ወስዶ ማዕድ አቀሚበላ቞ውፀ በአምላክ በማመኑም ኹመላው ቀተሰቡ ጋር እጅግ ተደሰተ።
ሲነጋም ዹኹተማዋ ሕግ አስኚባሪዎቜ “እነዚያን ሰዎቜ ልቀቃቾው” ብለው እንዲነግሩት መኮንኖቹን ላኩበት።
ዚእስር ቀቱ ጠባቂ ዚላኩትን መልእክት እንዲህ ሲል ለጳውሎስ ነገሹው፩ “ዹኹተማዋ ሕግ አስኚባሪዎቜ ሁለታቜሁ እንድትፈቱ ሰዎቜ ልኚዋል። ስለዚህ አሁን ወጥታቜሁ በሰላም ሂዱ።”
ጳውሎስ ግን እንዲህ አላቾው፩ “እኛ ዚሮም ዜጎቜ ሆነን ሳለ ያለፍርድ በሕዝብ ፊት ገርፈው እስር ቀት ወሚወሩን። ታዲያ አሁን በድብቅ አስወጥተው ሊጥሉን ይፈልጋሉ? እንዲህማ አይሆንም! እነሱ ራሳ቞ው መጥተው ይዘውን ይውጡ።”
መኮንኖቹም ይህን ነገር ለኹተማዋ ሕግ አስኚባሪዎቜ ነገሯ቞ው። እነሱም ሰዎቹ ዚሮም ዜጎቜ መሆናቾውን ሲሰሙ ፍርሃት አደሚባ቞ው።
በመሆኑም መጥተው ለመኗ቞ውፀ ኚእስር ቀቱም ይዘዋቾው ኚወጡ በኋላ ኹተማዋን ለቀው እንዲሄዱ ጠዚቋ቞ው።
እነሱ ግን ኚእስር ቀቱ ወጥተው ወደ ሊዲያ ቀት አመሩፀ እዚያም ወንድሞቜን አግኝተው ካበሚታቷ቞ው በኋላ ኹተማዋን ለቀው ሄዱ።
ሐናንያ ዚሚባል አንድ ሰው ኚሚስቱ ኚሰጲራ ጋር መሬት ሞጠ።
ይሁንና ኚገንዘቡ ዹተወሰነውን ደብቆ አስቀሚፀ ሚስቱም ይህን ታውቅ ነበርፀ ዹቀሹውንም አምጥቶ ለሐዋርያት አስሚኚበ።
ጎጥሮስ ግን እንዲህ አለ፩ “ሐናንያ፣ ሰይጣን መንፈስ ቅዱስን እንድትዋሜና ኚመሬቱ ሜያጭ ዹተወሰነውን ደብቀህ እንድታስቀር ያደፋፈሚህ ለምንድን ነው?
ሳትሞጠው በፊት ያንተው አልነበሹም? ኚሞጥኚውስ በኋላ ገንዘቡን ዹፈለግኹውን ልታደርግበት ትቜል አልነበሹም? እንዲህ ያለ ድርጊት ለመፈጾም በልብህ ለምን አሰብክ? ዹዋሾኾው ሰውን ሳይሆን አምላክን ነው።”
ሐናንያ ይህን ቃል ሲሰማ ወደቀና ሞተ። ይህን ዹሰሙ ሁሉ እጅግ ፈሩ።
ወጣት ወንዶቜም ተነስተው በጹርቅ ኚጠቀለሉት በኋላ ተሾክመው አውጥተው ቀበሩት።
ይህ ኹሆነ ኚሊስት ሰዓት ገደማ በኋላ ደግሞ ዹተፈጾመውን ነገር ያላወቀቜው ሚስቱ መጣቜ።
ጎጥሮስም “እስቲ ንገሪኝ፣ መሬቱን ዚሞጣቜሁት በዚህ ዋጋ ነው?” አላት። እሷም “አዎ፣ በዚሁ ዋጋ ነው” አለቜ።