text
stringlengths
4
267
በዚህ ጊዜ ጎጥሮስ “ሁለታቜሁ ዹይሖዋን መንፈስ ለመፈተን ዚተስማማቜሁት ለምንድን ነው? እነሆ፣ ባልሜን ዚቀበሩት ሰዎቜ እግር ደጃፍ ላይ ነውፀ እነሱም ተሾክመው ያወጡሻል” አላት።
ወዲያውም እግሩ ሥር ወድቃ ሞተቜ። ወጣቶቹ ሲገቡም ሞታ አገኟትፀ ተሾክመው አውጥተውም ኚባሏ አጠገብ ቀበሯት።
በመሆኑም መላው ጉባኀ እንዲሁም ይህን ዹሰሙ ሰዎቜ ሁሉ በኹፍተኛ ፍርሃት ተዋጡ።
በተጚማሪም ሐዋርያት በሕዝቡ መካኚል ብዙ ተአምራዊ ምልክቶቜና ድንቅ ነገሮቜ መፈጾማቾውን ቀጥለው ነበርፀ ሁሉም አንድ ላይ ሆነው መጠለያ ባለው “ዹሰለሞን መተላለፊያ” ይሰበሰቡ ነበር።
እርግጥ ኚሌሎቹ መካኚል ኚእነሱ ጋር ሊቀላቀል ዹደፈሹ አንድም ሰው አልነበሚምፀ ሆኖም ሕዝቡ ያሞግሳ቞ው ነበር።
ኹዚህም በላይ በጌታ ያመኑ እጅግ በርካታ ወንዶቜና ሎቶቜ በዹጊዜው በእነሱ ላይ ይጚመሩ ነበር።
ደግሞም ጎጥሮስ በዚያ ሲያልፍ በአንዳንዶቹ ላይ ቢያንስ ጥላው ቢያርፍባ቞ው በማለት ሕመምተኞቜን አውራ ጎዳናዎቜ ላይ አውጥተው በትናንሜ አልጋዎቜና በምንጣፎቜ ላይ ያስተኟ቞ው ነበር።
በተጚማሪም በኢዚሩሳሌም ዙሪያ ኹሚገኙ ኚተሞቜ ብዙ ሰዎቜ ሕመምተኞቜንና በርኩሳን መናፍስት ዚሚሠቃዩ ሰዎቜን ተሾክመው መምጣታ቞ውን ቀጠሉፀ ዚመጡትም ሁሉ ይፈወሱ ነበር።
ይሁንና ሊቀ ካህናቱና አብሚውት ዚነበሩት ዚሰዱቃውያን ሃይማኖታዊ ቡድን አባላት ሁሉ በቅናት ተሞልተው ተነሱ።
ሐዋርያትንም ይዘው እስር ቀት ኚተቷ቞ው።
ይሁን እንጂ ሌሊት ዹይሖዋ መልአክ ዚእስር ቀቱን በሮቜ ኚፍቶ አወጣ቞ውና እንዲህ አላቾው፩
“ሂዱና በቀተ መቅደሱ ቆማቜሁ ስለዚህ ሕይወት ዹሚገልጾውን ቃል ሁሉ ለሕዝቡ መናገራቜሁን ቀጥሉ።”
እነሱም በተነገራ቞ው መሠሚት ንጋት ላይ ወደ ቀተ መቅደሱ ገብተው ያስተምሩ ጀመር። ሊቀ ካህናቱና ኚእሱ ጋር ዚነበሩት በመጡ ጊዜም ዚሳንሄድሪንን ሾንጎና መላውን ዚእስራኀል ልጆቜ ሜማግሌዎቜ ጉባኀ በአንድነት ሰበሰቡፀ ሐዋርያቱንም ወደ እነሱ እንዲያመጧ቞ው ሰዎቜን ወደ እስር ቀቱ ላኩ።
ዚቀተ መቅደሱ ጠባቂዎቜ እዚያ በደሚሱ ጊዜ ግን እስር ቀቱ ውስጥ አላገኟ቞ውም። ስለዚህ ተመልሰው መጥተው ነገሯ቞ውፀ
እንዲህም አሏቾው፩ “እስር ቀቱ በሚገባ ተቆልፎ ጠባቂዎቹም በሮቹ ላይ ቆመው አገኘና቞ውፀ በሮቹን ስንኚፍት ግን ውስጥ ማንንም አላገኘንም።”
ዚቀተ መቅደሱ ሹምና ዚካህናት አለቆቹም ይህን ሲሰሙ ‘ዹዚህ ነገር መጚሚሻ ምን ይሆን?’ በማለት በነገሩ ግራ ተጋቡ።
በዚህ ጊዜ አንድ ሰው መጥቶ “እስር ቀት ያስገባቜኋ቞ው ሰዎቜ በቀተ መቅደሱ ቆመው ሕዝቡን እያስተማሩ ነው” ብሎ ነገራ቞ው።
ኚዚያም ዚቀተ መቅደሱ ሹም ኚጠባቂዎቹ ጋር ሄዶ አመጣ቞ውፀ ሆኖም ሕዝቡ በድንጋይ እንዳይወግራ቞ው ስለፈሩ ያመጧ቞ው በኃይል አስገድደው አልነበሚም።
አምጥተውም በሳንሄድሪን ሾንጎ ፊት አቆሟ቞ው። ኚዚያም ሊቀ ካህናቱ ይጠይቃቾው ጀመርፀ
እንዲህም አለ፩ “በዚህ ስም ማስተማራቜሁን እንድታቆሙ በጥብቅ አዘናቜሁ ነበርፀ እናንተ ግን ኢዚሩሳሌምን በትምህርታቜሁ ሞልታቜኋታልፀ ዹዚህንም ሰው ደም በእኛ ላይ ለማምጣት ቆርጣቜሁ ተነስታቜኋል።”
ጎጥሮስና ሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲህ ሲሉ መለሱፊ “ኹሰው ይልቅ አምላክን እንደ ገዢያቜን አድርገን ልንታዘዝ ይገባል።
እናንተ በእንጚት ላይ ሰቅላቜሁ ዚገደላቜሁትን ኢዚሱስን ዚአባቶቻቜን አምላክ አስነሳው።
እስራኀል ንስሐ እንዲገባና ዚኃጢአት ይቅርታ እንዲያገኝ አምላክ እሱን “ዋና ወኪል” እና “አዳኝ” አድርጎ በቀኙ ኹፍ ኹፍ አደሚገው።
ለዚህም ጉዳይ እኛ ምሥክሮቜ ነንፀ እንዲሁም አምላክ እሱን እንደ ገዢያ቞ው አድርገው ለሚታዘዙት ዹሰጠው መንፈስ ቅዱስ ምሥክር ነው።”
እነሱም ይህን ሲሰሙ እጅግ ተቆጡፀ ሊገድሏ቞ውም ፈለጉ።
ሆኖም በሕዝቡ ሁሉ ዘንድ ዚተኚበሚ፣ ዹሕግ አስተማሪ ዹሆነ ገማልያል ዚሚባል አንድ ፈሪሳዊ በሳንሄድሪኑ ሾንጎ መካኚል ተነስቶ ሰዎቹን ለጊዜው ወደ ውጭ እንዲያስወጧ቞ው አዘዘ።
ኚዚያም እንዲህ አላቾው፩ “ዚእስራኀል ሰዎቜ ሆይ፣ በእነዚህ ሰዎቜ ላይ ልታደርጉ ያሰባቜሁትን ነገር በተመለኹተ ልትጠነቀቁ ይገባል።
ለምሳሌ ያህል፣ ኹዚህ ቀደም ቎ዎዳስ ራሱን እንደ ታላቅ ሰው በመቁጠር ተነስቶ ነበርፀ ወደ 400 ዹሚጠጉ ሰዎቜም ኚእሱ ጋር ተባብሚው ነበር። ነገር ግን እሱም ተገደለፀ ተኚታዮቹም ሁሉ ተበታትነው እንዳልነበሩ ሆኑ።
ኚእሱ በኋላ ደግሞ ዚሕዝብ ቆጠራ በተካሄደበት ወቅት ዹገሊላው ይሁዳ ተነስቶ ተኚታዮቜ አፍርቶ ነበር። ይሁንና እሱም ጠፋፀ ተኚታዮቹም ሁሉ ተበታተኑ።
ስለዚህ አሁን ዚምላቜሁ፣ እነዚህን ሰዎቜ አትንኳ቞ውፀ ተዉአ቞ው። ይህ ውጥን ወይም ይህ ሥራ ኹሰው ኹሆነ ይጠፋልፀ
ኹአምላክ ኹሆነ ግን ልታጠፏ቞ው አትቜሉም። እንዲያውም ኹአምላክ ጋር ስትጣሉ ትገኙ ይሆናል።”
እነሱም ምክሩን ተቀበሉፀ ሐዋርያትንም ጠርተው ገሚፏ቞ውፀ ኚዚያም በኢዚሱስ ስም መናገራ቞ውን እንዲያቆሙ አዘው ለቀቋ቞ው።
እነሱም ስለ ስሙ ውርደት ለመቀበል ብቁ ሆነው በመቆጠራ቞ው ደስ እያላ቞ው ኚሳንሄድሪን ሾንጎ ወጡ።
ኚዚያም በዹቀኑ በቀተ መቅደስም ሆነ ኚቀት ወደ ቀት እዚሄዱ ስለ ክርስቶስ ይኾውም ስለ ኢዚሱስ ዹሚናገሹውን ምሥራቜ ያለማሰለስ ማስተማራ቞ውንና ማወጃቾውን ቀጠሉ።
በኢቆንዮን ጳውሎስና በርናባስ አብሚው ወደ አይሁዳውያን ምኩራብ ገቡፀ በዚያም ጥሩ ንግግር ስለሰጡ ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው አይሁዳውያንና ግሪካውያን አማኞቜ ሆኑ።
ሆኖም ያላመኑት አይሁዳውያን ኚአሕዛብ ወገን ዚሆኑትን ሰዎቜ በማነሳሳት በወንድሞቜ ላይ ጥላቻ እንዲያድርባ቞ው አደሚጉ።
በመሆኑም ኹይሖዋ ባገኙት ሥልጣን በድፍሚት እዚተናገሩ በኢቆንዮን ሹዘም ላለ ጊዜ ቆዩፀ እሱም ተአምራዊ ምልክቶቜና ድንቅ ነገሮቜ በእነሱ አማካኝነት እንዲኚናወኑ በማድሚግ ስለ ጾጋው ዹሚነገሹው መልእክት ትክክል መሆኑን ያሚጋግጥላ቞ው ነበር።
ይሁንና ዹኹተማዋ ሕዝብ ተኚፋፈለፀ አንዳንዶቹ ኚአይሁዳውያን ጎን ሲቆሙ ሌሎቹ ደግሞ ኚሐዋርያት ጎን ቆሙ።
አሕዛብና አይሁዳውያን ኚገዢዎቻ቞ው ጋር ሆነው ሊያንገላቷ቞ውና በድንጋይ ሊወግሯ቞ው በሞኚሩ ጊዜ
ጳውሎስና በርናባስ ይህን ስላወቁ ልስጥራና ደርቀ ወደሚባሉት ዚሊቃኊንያ ኚተሞቜ እንዲሁም በዙሪያ቞ው ወዳሉት መንደሮቜ ሞሹ።
በዚያም ምሥራቹን ማወጃቾውን ቀጠሉ።
በልስጥራም አንድ ሰው ተቀምጩ ነበር። እሱም ኚተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ሜባ ዹነበሹ ሲሆን ፈጜሞ በእግሩ ሄዶ አያውቅም።
ይህ ሰው ጳውሎስ ሲናገር ያዳምጥ ነበር። ጳውሎስም ትኩር ብሎ አዹውና ለመዳን ዚሚያበቃ እምነት እንዳለው ተመልክቶ
ኹፍ ባለ ድምፅ “ተነስና በእግርህ ቁም” አለው። ሰውዹውም ዘሎ ተነሳና መራመድ ጀመሚ።
ሕዝቡም ጳውሎስ ያደሚገውን ባዩ ጊዜ በሊቃኊንያ ቋንቋ “አማልክት በሰው አምሳል ሆነው ወደ እኛ ወርደዋል!” በማለት ጮኹ።
በርናባስን ዙስ፣ ጳውሎስን ደግሞ ዋና ተናጋሪ ስለነበር ሄርሜስ ብለው ይጠሯ቞ው ጀመር።
በኹተማዋ መግቢያ ላይ ይገኝ ዹነበሹው ዚዙስ ቀተ መቅደስ ካህን፣ ኮርማዎቜና ዚአበባ ጉንጉን ወደ ኹተማዋ መግቢያ በማምጣት ኚሕዝቡ ጋር ሆኖ መሥዋዕት ሊሠዋላቾው ፈለገ።
ይሁን እንጂ ሐዋርያቱ በርናባስና ጳውሎስ ይህን ሲሰሙ ልብሳ቞ውን ቀደዱፀ ሮጠውም ሕዝቡ መሃል በመግባት ድምፃ቞ውን ኹፍ አድርገው እንዲህ አሉ፩
“እናንተ ሰዎቜ፣ እንዲህ ዚምታደርጉት ለምንድን ነው? እኛም እንደ እናንተው ድክመት ያለብን ሰዎቜ ነን። ምሥራቹን እያወጅንላቜሁ ያለነውም እነዚህን ኚንቱ ነገሮቜ ትታቜሁ ሰማይን፣ ምድርን፣ ባሕርንና በውስጣ቞ው ያሉትን ነገሮቜ ሁሉ ዹፈጠሹውን ሕያው አምላክ እንድታመልኩ ነው።
ባለፉት ትውልዶቜ፣ ሕዝቊቜ ሁሉ በራሳ቞ው መንገድ እንዲሄዱ ፈቀደላ቞ውፀ
ይሁንና ለራሱ ምሥክር ኚማቅሚብ ወደኋላ አላለምፀ ኹሰማይ ዝናብ በማዝነብና ፍሬያማ ወቅቶቜን በመስጠት እንዲሁም ዚተትሚፈሚፈ ምግብ በማቅሚብና ልባቜሁን በደስታ በመሙላት መልካም ነገር አድርጓል።”
ይህን ሁሉ ተናግሹው እንኳ ሕዝቡ እንዳይሠዋላ቞ው ያስጣሉት በብዙ ቜግር ነበር።
ሆኖም አይሁዳውያን ኚአንጟኪያና ኚኢቆንዮን መጥተው ሕዝቡን አግባቡፀ ጳውሎስንም በድንጋይ ኚወገሩት በኋላ ዹሞተ መስሏ቞ው ጎትተው ኹኹተማዋ አወጡት።
ደቀ መዛሙርቱ መጥተው በኚበቡት ጊዜ ግን ተነስቶ ወደ ኹተማዋ ገባ። በማግስቱም ኚበርናባስ ጋር ወደ ደርቀ ሄደ።
በዚያቜ ኹተማ ምሥራቹን ሰብኚው በርካታ ደቀ መዛሙርት ካፈሩ በኋላ ወደ ልስጥራ፣ ወደ ኢቆንዮንና ወደ አንጟኪያ ተመለሱ።
በዚያም “በብዙ መኚራ አልፈን ወደ አምላክ መንግሥት መግባት አለብን” እያሉ በእምነት ጾንተው እንዲኖሩ በማበሚታታት ደቀ መዛሙርቱን አጠናኚሩ።
ኹዚህም በተጚማሪ በዚጉባኀው ሜማግሌዎቜን ሟሙላ቞ውፀ ኚጟሙና ኚጞለዩም በኋላ ላመኑበት ለይሖዋ አደራ ሰጧ቞ው።
ኚዚያም በጵስድያ በኩል አልፈው ወደ ጵንፍልያ መጡፀ
በጮርጌ ቃሉን ካወጁ በኋላ ወደ አታሊያ ወሚዱ።
ኚዚያም ተነስተው በመርኚብ ወደ አንጟኪያ ሄዱፀ ጳውሎስና በርናባስ አሁን ያጠናቀቁትን ሥራ እንዲያኚናውኑ ለአምላክ ጾጋ በአደራ ዚተሰጡት በአንጟኪያ ነበር።
እዚያም ደርሰው ጉባኀውን ኚሰበሰቡ በኋላ አምላክ በእነሱ አማካኝነት ያኚናወና቞ውን በርካታ ነገሮቜ እንዲሁም ለአሕዛብ ዚእምነትን በር እንደኚፈተላ቞ው ተሚኩላ቞ው።
በዚያም ኹደቀ መዛሙርቱ ጋር ሹዘም ያለ ጊዜ አሳለፉ።
እኛም በደህና ወደ ዚብስ ደሚስንፀ ደሎቲቱም ማልታ ተብላ እንደምትጠራ አወቅን።
ዚአካባቢው ነዋሪዎቜም ዹተለዹ ደግነት አሳዩን። ዝናብ መዝነብ ጀምሮ ስለነበሚና ብርድ ስለነበር እሳት በማቀጣጠል ሁላቜንንም በደግነት አስተናገዱን።
ይሁን እንጂ ጳውሎስ ጭራሮ ሰብስቊ እሳቱ ውስጥ ሲጚምር ኚሙቀቱ ዚተነሳ እፉኝት ወጥታ እጁ ላይ ተጣበቀቜ።
ባዕድ ቋንቋ ዚሚናገሩትም ሰዎቜ እፉኝቷ እጁ ላይ ተንጠልጥላ ባዩ ጊዜ እርስ በርሳ቞ው “ይህ ሰው ነፍሰ ገዳይ መሆን አለበትፀ ኚባሕሩ ተርፎ በደህና ቢወጣም እንኳ ፍትሕ በሕይወት እንዲኖር አልፈቀደለትም” ይባባሉ ጀመር።
እሱ ግን እፉኝቷን እሳቱ ላይ አራገፋትፀ አንዳቜም ጉዳት አልደሚሰበትም።
ሆኖም ሰዎቹ ኹአሁን አሁን ሰውነቱ ያብጣል ወይም ድንገት ወድቆ ይሞታል ብለው ይጠባበቁ ነበር። ብዙ ጠብቀው ምንም ጉዳት እንዳልደሚሰበት ባዩ ጊዜ ሐሳባ቞ውን ለውጠው ይህ ሰው አምላክ ነው ይሉ ጀመር።
በዚያ አካባቢ፣ ፑፕልዮስ ዚተባለ ዚደሎቲቱ አስተዳዳሪ ርስት ነበሚውፀ እሱም በእንግድነት ተቀብሎን ሊስት ቀን በደግነት አስተናገደን።
ዚፑፕልዮስ አባት ትኩሳትና ተቅማጥ ይዞት ተኝቶ ነበርፀ ጳውሎስም ወደ እሱ ገብቶ ጞለዚለትፀ እጁንም ጫነበትና ፈወሰው።
ይህ ኹሆነ በኋላ በደሎቲቱ ዚሚኖሩ ዚታመሙ ሌሎቜ ሰዎቜም ወደ እሱ እዚመጡ ይፈወሱ ጀመር።
በተጚማሪም ብዙ ስጊታ በመስጠት አክብሮታ቞ውን ገለጹልንፀ በመርኚብ ለመሄድ በተዘጋጀን ጊዜም ዚሚያስፈልጉንን ነገሮቜ ሁሉ ጫኑልን።
ኚሊስት ወር በኋላም “ዚዙስ ልጆቜ” ዹሚል ዓርማ ባለው መርኚብ ጉዞ ጀመርን። ይህ መርኚብ ኚእስክንድርያ ዚመጣ ሲሆን ክሚምቱን ያሳለፈው በዚህቜ ደሎት ነበር።
በስራኩስ ወደሚገኘው ወደብ ኚደሚስን በኋላ በዚያ ሊስት ቀን ቆዚንፀ
ኚዚያም ተነስተን በመጓዝ ሬጊዩም ደሚስን። ኚአንድ ቀን በኋላም ዚደቡብ ነፋስ ስለተነሳ በሁለተኛው ቀን ፑቲዮሉስ ደሚስን።
በዚያም ወንድሞቜን አገኘንፀ እነሱም ሰባት ቀን አብሚና቞ው እንድንቆይ ለመኑንፀ እነሱ ጋር ኹቆዹን በኋላ ወደ ሮም አመራን።
በዚያ ዚነበሩ ወንድሞቜ ስለ እኛ በሰሙ ጊዜ እስኚ አፍዩስ ዚገበያ ስፍራና ሊስት ማደሪያ እስኚሚባለው ቊታ ድሚስ ሊቀበሉን መጡ። ጳውሎስም ባያ቞ው ጊዜ አምላክን አመሰገነፀ እንዲሁም ተበሚታታ።
በመጚሚሻም ሮም በደሚስን ጊዜ ጳውሎስ አንድ ወታደር እዚጠበቀው ብቻውን እንዲኖር ተፈቀደለት።
ይሁን እንጂ ኚሊስት ቀን በኋላ ዚአይሁዳውያንን ታላላቅ ሰዎቜ አንድ ላይ ጠራ። ሰዎቹም በተሰበሰቡ ጊዜ እንዲህ አላቾው፩ “ወንድሞቜ፣ ምንም እንኳ ሕዝቡን ወይም ዚአባቶቻቜንን ልማድ ዚሚጻሚር ነገር ያልፈጞምኩ ቢሆንም በኢዚሩሳሌም አስሚው ለሮማውያን አሳልፈው ሰጥተውኛል።
እነሱም ኚመሚመሩኝ በኋላ ለሞት ዚሚያበቃ ምንም ጥፋት ስላላገኙብኝ ሊፈቱኝ ፈልገው ነበር።
ሆኖም አይሁዳውያን ይህን በተቃወሙ ጊዜ ለቄሳር ይግባኝ ለማለት ተገደድኩፀ ይህን ያደሚግኩት ግን ሕዝቀን ዚምኚስበት ነገር ኖሮኝ አይደለም።
እናንተንም ለማዚትና ለማነጋገር ጥያቄ ያቀሚብኩት ለዚህ ነውፀ በዚህ ሰንሰለት ዚታሰርኩትም ለእስራኀል በተሰጠው ተስፋ ምክንያት ነው።”
እነሱም እንዲህ አሉትፊ “ስለ አንተ ዚተጻፈ ኚይሁዳ ዚመጣ ምንም ደብዳቀ አልደሚሰንምፀ ኚዚያ ኚመጡት ወንድሞቜ መካኚልም ስለ አንተ ክፉ ነገር ዹተናገሹ ወይም ያወራ አንድም ሰው ዚለም።
ሆኖም ስለዚህ ኑፋቄ በዚቊታው መጥፎ ነገር እንደሚወራ ስለምናውቅ ዹአንተን ሐሳብ ደግሞ መስማት ተገቢ ይመስለናል።”
በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር ኚእሱ ጋር ቀን ኹወሰኑ በኋላ ብዙ ሆነው ወደ መኖሪያ ስፍራው መጡ። እሱም በኢዚሱስ እንዲያምኑ ለማድሚግ ኹሙሮ ሕግና ኚነቢያት እዚጠቀሰ ኚጠዋት ጀምሮ እስኚ ማታ ድሚስ ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ በመመሥኚር ጉዳዩን አብራራላ቞ው።
አንዳንዶቹ ዹተናገሹውን ነገር ሲያምኑ ሌሎቹ ግን አላመኑም።
እርስ በርስ ሊስማሙ ስላልቻሉም ለመሄድ ተነሱፀ በዚህ ጊዜ ጳውሎስ ዹሚኹተለውን ዚመጚሚሻ ሐሳብ ተናገሹ፩ “መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል ለአባቶቻቜሁ እንዲህ ሲል ዹተናገሹው ቃል ትክክል ነበር፩
‘ወደዚህ ሕዝብ ሄደህ እንዲህ በላቾው፩ “መስማቱን ትሰማላቜሁፀ ግን በፍጹም አታስተውሉምፀ ማዚቱን ታያላቜሁፀ ግን በፍጹም ልብ አትሉም።
ምክንያቱም በዓይናቾው አይተው፣ በጆሯ቞ው ሰምተው እንዲሁም በልባ቞ው አስተውለው ወደ እኔ እንዳይመለሱና እንዳልፈውሳ቞ው ዹዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኗልፀ በጆሯ቞ው ሰምተው ምላሜ አልሰጡምፀ ዓይናቾውንም ጚፍነዋል።”’
ስለዚህ አምላክ ሰዎቜን ስለሚያድንበት መንገድ ዹሚናገሹው ይህ መልእክት ለአሕዛብ እንደተላኚ እንድታውቁ እፈልጋለሁፀ እነሱም በእርግጥ ይሰሙታል።”
ጳውሎስም በተኚራዚው ቀት ሁለት ዓመት ሙሉ ኖሚፀ ወደ እሱ ዚሚመጡትንም ሁሉ በደግነት ያስተናግዳ቞ው ነበርፀ
ያለምንም እንቅፋት በታላቅ ዹመናገር ነፃነት ስለ አምላክ መንግሥት ይሰብክላ቞ው ዹነበሹ ኹመሆኑም በላይ ስለ ጌታ ኢዚሱስ ክርስቶስ ያስተምራ቞ው ነበር።
“ወንድሞቜና አባቶቜ፣ አሁን ለእናንተ ዹማቀርበውን ዚመኚላኚያ መልስ ስሙ።”
እነሱም በዕብራይስጥ ቋንቋ ሲናገር በሰሙ ጊዜ ይበልጥ ጞጥ አሉፀ እሱም እንዲህ አለ፩
“እኔ ኪልቅያ ውስጥ በምትገኘው በጠርሎስ ዚተወለድኩ አይሁዳዊ ነኝፀ ሆኖም ዚተማርኩት በዚህቜው ኹተማ በገማልያል እግር ሥር ተቀምጬ ሲሆን ዚአባቶቜን ሕግ በጥብቅ እንድኚተል ዚሚያስቜል ትምህርት ቀስሜአለሁፀ ዛሬ እናንተ ሁላቜሁ እንዲህ እንደምትቀኑ ሁሉ እኔም ለአምላክ እቀና ነበር።
ወንዶቜንም ሆነ ሎቶቜን በማሰርና ለወህኒ ቀት አሳልፌ በመስጠት ዚጌታን መንገድ ዚሚኚተሉትን እስኚ ሞት ድሚስ ስደት አደርስባ቞ው ነበርፀ
ይህን በተመለኹተም ሊቀ ካህናቱና መላው ዚሜማግሌዎቜ ጉባኀ ሊመሠክሩ ይቜላሉ። ኚእነሱም በደማስቆ ላሉ ወንድሞቻቜን ዚተጻፈ ደብዳቀ ተቀብዬ በዚያ ያሉትን አስሬ ወደ ኢዚሩሳሌም በማምጣት ለማስቀጣት በጉዞ ላይ ነበርኩ።
“ሆኖም በጉዞ ላይ ሳለሁ ወደ ደማስቆ ስቃሚብ፣ እኩለ ቀን ገደማ ላይ ድንገት ኹሰማይ ዚመጣ ኃይለኛ ብርሃን በዙሪያዬ አንጞባሚቀፀ
እኔም መሬት ላይ ወደቅኩፀ ኚዚያም ‘ሳኊል፣ ሳኊል ለምን ታሳድደኛለህ?’ ዹሚል ድምፅ ሰማሁ።
እኔም መልሌ ‘ጌታዬ፣ አንተ ማን ነህ?’ አልኩት። እሱም ‘እኔ አንተ ዚምታሳድደኝ ዚናዝሬቱ ኢዚሱስ ነኝ’ አለኝ።