text
stringlengths
707
989
### Text: በከተራ በዓል ላይ በደረሱ የኤሌክሪክ አደጋዎች 2 ወጣቶች ሞቱ።ትላንት በአማራ ክልል በሰቆጣ እና በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሸረሮ ከተሞች የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት በደረሰ የኤሌክትሪክ አደጋ የ2 ወጣቶች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አሰታውቋል።የሰቆጣ ከተማ ፖሊስ ፅህፈት ቤት በከተማው የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት ታቦታቱን ከፀሃይ የሚከላከል ጥላ ከኤሌክትሪክ ጋር በመነካካቱ 0በተከሰተ የኤሌክትሪክ አደጋ የአንድ ወጣት ህይወት ወድያው አልፏል።በሌሎች ጥላውን በመግፈፍ ላይ በነበሩ ስምንት ወጣቶች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወጣቶች በሰቆጣ ተፈራ ሃይሉ መታሰቢያ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።በተመሳሳይ0በኦሮሚያ0ክልል0ሰሜን0ሸዋ0ዞን0ደብረሊባኖስ0ወረዳ0ሸረሮ0ከተማ0ለጥምቀት0በዓል0ማድመቂያ0ሰንደቅ0ዓላማ0ለመስቀል0የሞከረ0የ240ዓመት0ወጣት0ህይወቱ0ማለፉን0የወረዳው0ፖሊስ0አስታውቋል።ወጣቱ0ፎቅ0ላይ0ሆኖ0የወረወረው0ገመድ0330ኪሎ0ዋት0የኤሌክትሪክ0ኅይል0ማስተላለፊያ0ገመድ0ላይ0በማረፉ0በእርጥብ0እንጨት0ለማንሳት0ሲሞክር0በኤሌክትሪክ0ሀይል0ተገፍተሮ0ሊወድቅ0ችሏል።ወጣቱ ወደ ሽረሮ ጤና ጣቢያ ቢወሰድም ከ30 ደቂቃ በኃላ ህይወቱ አልፏል። ### Response:
### Text: ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ አገራት ውስጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደብዛቸው መጥፋቱ ተገለጸ።ከ44 ሺህ በላይ ሰዎች በአሁኑ ወቅት በመላው አፍሪካ እንደጠፉ መረጋገጡን የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አይሲአርሲ ዓለም አቀፉን የመጥፋት ቀንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።ከነዚህም ውስጥ 45 በመቶ የሚሆኑት ህፃናት ናቸው ብሏል።ከነዚህ ከጠፉት 82 በመቶ ያህሉ በግጭት ከሚናጡ ከተባሉ ሰባት አገሮች ብቻ መሆናቸውን ድርጅቱ አስታውቋል።በአፍሪካ ውስጥ ከጠፉት ሰዎች ጠቅላላ ቁጥር ከግማሽ በላይ ናይጄሪያውያን ናቸው። በአገሪቱ ውስጥ ወደ 24 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች መጥፋታቸው ተመዝግቧል።በርካቶች የጠፉ ሰዎች ቁጥር የተመዘገበባቸው ሌሎች አገሮች ኢትዮጵያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ሶማሊያ ፣ ሊቢያ ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ካሜሩን ይገኙበታል።ድርጅቱ እንዳመለከተው ባለፈው ዓመት በተከሰቱ ግጭቶችና በሌሎች የጥቃት ዓይነቶች አህጉሪቱ የጠፉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጿል።በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወረርሽኝ ምክንያት በተጣሉ ገደቦች የጠፉ ተጎጂዎችን ለማግኘት እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማቀላቀል የሚደረገውን ጥረት እያደናቀፉ እንደሆነ ቢገልፅም የጠፉ ሰዎች የተረሱ ሰዎች አይደሉም ብሏል። ቢቢሲ ### Response:
### Text: ዛሬ የዓለም ምግብ ፕሮግራም አልሚ ምግብን ጨምሮ ህይወት አድን ፍጆታዎችን የጫኑ 47 ተሸከርካሪዎች ወደ ትግራይ ጉዞ መጀመራቸውን አሳውቋል።ከ47ቱ ተሽከርካሪዎቹ በተጨማሪ ለመሰረታዊ አገልግሎቶች የሚውል ነዳጅ የጫኑ 3 ተሽከርካሪዎች ወደ ክልሉ በመጓዝ ላይ ይገኛሉ።ከሁሉም ባለስልጣናት በተደረገው ድጋፍ እስካሁን ጉዞው የተሳካ እና መልካም የሚባል እንደሆነ ጠቁሟል።ለሰብዓዊነት ተብሎ ግጭት የማቆም ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ እስካሁን ድረስ ወደ 26 ተሸከርካሪዎች ብቻ ናቸው ወደ ክልሉ የገቡት።የዓለም ምግብ ፕሮግራም በክልሉ በችግር ላይ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን የሰብዓዊ ፍላጎት ለማሟላት በየዕለቱ 100 ተሽከርካሪዎች ወደ ክልል መግባታ እንዳለባቸው ከዚህ ቀደም መግለፁ ይታወሳል።በሌላ መረጃ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምቤት በ ስር ዛሬ በኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ በዝግ ይመክራል። በስብሰባው ላይ የሰብአዊ ጉዳዮች ም ዋና ጸሃፊ ማርቲን ግሪፍትስ ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።የዛሬውን ስብሰባውን የጠየቁት የ3 የምክር ቤቱ አባላት ጋቦን፣ ጋና እና ኬንያ ናቸው። በ3 ብቻ በኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ ስብሰባ ሲጠየቅ ይህ የመጀመሪያው መሆኑን ተመድን ዋቢ አድርጎ አል ዓይን አስነብቧል። ### Response:
### Text: ታላቁና ታሪካዊው የፈረንሳይ ካቴድራል ኖትር ዳም በእሳት እየጋየ ነው። በፓሪስ እምብርት የሚገኘው ይህ ካቴድራል ግንባታው በ1345 ዓም የተጠናቀቀ፣ 128 ሜትር ርዝመትና 69 ሜትር ቁመት ያለው የ4ኛው ክፍለ ዘመን አስደናቂው የፈረንሳይን የጎቲክ ሥነ ሕንፃ ምጥቀት የሚንፀባረቅበት የካቶሊክ ካቴድራል ነው። ኖትር ዳም ማለት እመቤታችን እንደማለት ነው።ይህ ታሪካዊ ካቴድራል ድንቁ ደራሲ ቪክቶር ሂጎ በ1831 ባሳተመው ወይም በሚለው ልብወለድ መፅሃፉ ዝናው ከናኘ በኋላ በአለማችን ከፍተኛ ጎብኚዊች መሳብ የቻለና በአመት 13 ሚሊዮን ቱሪስቶች የሚመለከቱት አስደናቂ ቦታ ሆኗል።የፈረንሳይ አብዮት ባመጣባቸው ጣጣ የመፍረስና የመዘረፍ ዕጣ እንደደረሰባቸው አብዛኞቹ የፈረንሳይ ካቴድራሎች ኖትር ዳምም የተጎዳ ቢሆን ከአብዮት በኋላ ወደ ስልጣን የመጣው ናፖሊዮን ቦናፓርት ካቴድራሉን ከታደጉት የሃገሪቱ መሪዎች በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ ነው።ኖትር ዳም የፓሪስ ሃገረ ስብከት መንበር በመሆኑ የከተማይቱ ሊቀ ጳጳስ ሚሼል ኦፐቲ መቀመጫም ነው። ይህ ታሪካዊ ገዳም በእድሳት ላይ በሚገኝበት በአሁኑ ወቅት በደረሰ የእሳት አደጋ በሚያሳዝን ሁኔታ በመውደም ላይ ይገኛል። እስካሁን የአደጋው መንስዔ በትክክል አልታወቀም። ### Response:
### Text: ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው የትምህርት አይነቶችም ይፈተሹ ዝቅተኛ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው የፈተና ውጤቶች ዳግም እንዲታዩ የ ቤተሰብ አባላት ጠይቀዋል። አስተያየት ከሰጡት መካከል በመምህርነት ሞያ የሚያገለግሉ አንድ የቤተሰባችን አባል ይህን ብለዋል ብዙሃኑ ትኩረቱን ያደረገው ዝቅተኛ በሚባለው ውጤት ነው ነገር ግን የማይጠበቅ እንዲሁም ተመሳሳይ ውጤቶች ችላ ተብለዋል ይህ ተገቢ አይደለም። አንዳንዱ ያየናቸው ውጤቶች ኖርማል አይመስሉም። ተማሪ የራሱ ያልሆነውን ውጤት የኔ አይደለም እንዳለው ሁሉ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው የትምህርት አይነቶች ላይ እንዲታይለት መጠየቅ አለበት። እንደ ትውልድ ያልሰራንበት ውጤት ሲቀመጥልንም ለምን ብለን መጠየቅ አለብን። ይህን መሰሉ አሰራር በመምህርነት ህይወቴ አልገጠመኝም፡ ኤጀንሲው ችግሩን መርምሮ መፍትሄ እንደሚሰጥ ይህ ችግር እንዲፈጠር ያደረጉና ያጠፉ አካላትን መንግስት በህግ እንደሚጠይቅ አምናለሁ ብለዋል።ፎቶውየአንዳንድ ትምህርት ቤቶችን የመፈተኛ ቁጥር እያስገባን የተመለከትነውን ውጤት ያሳያል። እና ትምህርቶች ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቦባቸዋል። እንዴት የአንዳንድ ተማሪዎች ውጤት 100 እና 99 ሆኖ ነው የተመዘገበው። ### Response:
### Text: በሀገሪቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግጭት እንዳይከሰት በሚደረገው ጥረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ሥራ በቂ አይደለም ተባለ። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምክር ቤት ጉባኤ የ45ቱም ዪንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። ጉባኤው በዩንቨርሲቲዎች ሠላም፣ በምርምር፣ መማር ማስተማር እና ቴክኖሎጂ ላይ እንደሚያተኩር ተገልጿል።የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕር ሂሩት ወልደማርያም በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት በትምህርት ተቋማቱ የሚስተዋለውን አለመረረጋት ለመፍታት በሚደረገው ርብርብ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ድጋፍ በቂ አይደለም ብለዋል፡፡ በአሁኑ ሰዐት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቆራረጠ ትምህርት እየሰጡ እንደሚገኙ የተናገሩት ሚኒስትሯ ወጥ የሆነ መማር ማስተማር እንዲኖር ክልሎች እና ከተሞች በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በአማራና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ዩንቨርሲቲዎች ከፍተኛ አለመረጋጋት የሚታይባቸው ናቸው ተብሏል፡፡ በነዚህ ተቋማት ግጭት እንዲከሰት የተጠና ድጋፍ የሚያደርጉ አካላት መኖራቸውንም ፕሮፌሰር ሂሩት አስታውቀዋል፡፡ ምሁራን ለችግሮቹ የመፍትሄ ሀሳብ እንዲያመጡም ተጠይቋል፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች ሳውዲ አረቢያ ዓለም አቀፍ በረራዎች ለቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት እንዲታገዱ ትዕዛዝ አስተላልፋለች። በሳውዲ በአሁን ሰዓት በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ 86 ሰዎች ይገኛሉ። የቫይረሱ ስርጭት እየተገታባት ነው በተባለችው ቻይና በ24 ሰዓት ውስጥ የተመዘገበው የ13 ሰዎች ሞት ነው። በቫይረሱ ደግሞ መጠቃታቸው የተነገረው 11 ሰዎች ብቻ ናቸው። በአሜሪካ የብራዚል አምባሳደር በተደረገላቸው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ቫይረሱ እንደሚገኝባቸው ተረጋግጧል። በስፔን በ24 ሰዓት ውስጥ የ66 ሰዎች ሞት መመዝግቡን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 133 ደርሷል። በአሜሪካ ዋሽንግተን ስቴት በ24 ሰዓት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ የስድስት ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ፖላንድ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ወደሀገሯ የሚገቡ የውጭ ሀገር ዜጎችን ለማገድ መወሰኗ ተሰምቷል። ፖላንድ ውስጥ በ24 ሰዓት አዲስ 16 የኮሮና ቫይረስ ኬዝ ተመዝግቧል። ዴንማርክ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለውጭ ሀገር ዜጎች ደንበሯን እንደዘጋች በይፋ አሳውቃለች። ዴንማርክ ውሥጥ 804 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል። በፈረንሳይ በኮሮና ቫይረስ የ18 ሰዎች ሞት መመዝገቡን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 79 ደርሰዋል። በሀገሪቱ ከ3661 በላይ ተጠቂዎች አሉ። ### Response:
### Text: ከሀዋሳ ማረሚያ 103 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋልየሀዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ሙንጣሽ ብርሃኑ በማህበረሰቡ የጥንቃቄ መጓደል እና የምርመራ ስራዎች በስፋት በመከናወናቸው ምክንያት በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እየጨመረ መምጣቱን ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ተናግረዋል።እስካሁን በከተማው ምርመራ ከተደረገላቸው ከ7000 በላይ ሰዎች መካከል 800 የሚደርሱት በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።በሀዋሳ ማዕከላዊ ማረሚያ ተቋም 510 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 103 የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። 3ቱ ከውጭ የገቡ አገልግሎት ሰጪዎች ናቸው። በቫይረሱ የተያዙ ተለይተው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የውጭ ዜጎች ፣ የቀን ሰራተኞች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቷል።የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ዶር ማቴ መንገሻ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዙሪያ አሃዛዊ መረጃ ባይሰጡም በከተማይቱ በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ ከፓርኩ ከተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው።ይህም በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ካለው የሰዎች ብዛት፣ የስራ ባህሪ አንፃር የሚፈጠሩ መነካካቶች ወረርሽኙን ሊያስፋፋ ይችላል የሚል ስጋት ማሳደሩን ዶር ማቴ መንገሻ ለጀርመን ድምፅ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: 15 ሚሊዮን ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ የሉም።የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል በህተምቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት በሰሜን ወሎ በሰሜን ጎንደር በዋግኽምራ ከፊል ደቡብ ወሎ ከፊል ደቡብ ጎንደር በከፈተው ጦርነት እና ወረራ ሳቢያ ከ15 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ርቀዋል።በተጨማሪ በጦርነቱ ምክንያት 277 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ መውደሙን ከ1 ሺህ 300 በላይ በከፊል ተጎድተዋል የትምህርት ቁሳቁሶች ተሰርቋል፣ ወድሟል፣ ቁሳቁሶች ከጥቅም ውጭ ሆኗል ።የክልሉ ትምህርት ቢሮ ተፈናቅለው በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎች ትምህርት እንዲቀጥሉ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ አመቻቻለሁ ብሏል።ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ጌታቸው ተፈናቅለው የሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃቸውን ይዘው ባለመምጣታቸው ምክንያት ባሉበት አካባቢ ሁሉ በሚፈልጉበት ትምህርት ቤት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲመዘገቡ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።በሌላ በኩል የምስራቅ ጎጃም ዞን ባለፈው ወር 10 ሺ ተፈናቃይ ተማሪዎችን የምግብ ወጪያቸውን ጨምሮ ለመቀበል ባደረገው ጥሪ እስካሁን 235 ተማሪዎች መመዝገቡን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ለቪኦኤ አሳውቋል። ### Response:
### Text: የወላይታ ክልልነት ጥያቄትላንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አሕመድ ክልል የመሆን ጥያቄ ካቀረበው የወላይታ ዞን ባለሥልጣናት እና የማህበረሰቡ ተወካዮች ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በውይይቱ የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቢ የሰላም ምኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የደቡብ ክልል ርዕሰመስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው እና የሐይማኖት መሪዎች ጭምር ተገኝተው ነበር። ለውይይቱ በኃላ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትዊተር «ፍሬያማ ውይይት አድርገናል» እንደነበር አይዘነጋም። በውይይቱ የተሳተፈው እና የላጋ የተባለው የወላይታ ወጣቶች ማኅበራዊ ንቅናቄ መሥራቾች አንዱ የሆነ አቶ አሸናፊ ከበደ «ወላይታ ራሱን ችሎ ክልል ከመሆን ሌሎች አማራጮች ይኖራሉ አይኖሩም የሚሉ ጉዳዮች እና ሌሎች ተያያዥ አማራጭ የሆኑ ጉዳዮች ምንድናቸው እዚያ ላይ እንወያይ» ማለታቸውን ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ተናግሯል።0ተሳታፊዎች «የአስራ አምስት ሚሊዮን የዎላይታ ሕዝብ አቋም እና ፍላጎት ህገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት የዎላይታ ሕዝብ ራሱን ችሎ በራሱ ክልል የመሆን አማራጭ ተወዳዳሪ እና አቻ የለውም» የሚል ምላሽ ለጠቅላይ ምኒስትሩ እንደሰጡ አሸናፊ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ አስረድቷል።0 12022 የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ### Response:
### Text: የህዝብ ተወካዮች ምቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የምቤቱ አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል።አቶ ታገሰ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡አዋጁ ለአፈጉባኤውና ለአፈጉባኤው ጽቤት በሰጠው ስልጣን እንዲሁም በአዋጁ በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ከቀረቡት 632 ዕጩዎች መካከል 42ቱ መለየታቸውን ተናግረዋል፡፡በቀረቡ 42 ዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከአማካሪዎች ጋር ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡በቀጣይ ሳምንት ደግሞ የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምቤት አመራር አካላት በሚገኙበት በዕጩዎች የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ ላይ ምክክር ተደርጎ ግብአት የሚሰበሰብ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡በማስከተልም በምቤቱ ድረገጽና በማህበራዊ ሚዲያ የእጩዎችን ማንነት በመግለጽ በቂ ግብአት ከተሰበሰበ በኋላ ሰብሳቢና ምሰብሳቢን ጨምሮ 11ዱ ዕጩ ኮሚሽነሮች ለምቤቱ ቀርቦ ከፀደቀና ዕጩዎች ከተሰየሙ በኋላ ወደ ስራ እንደሚገባም ገልጸዋል። ### Response:
### Text: 9ኛው ዙር የጥንዶች ፌስቲቫል የፊታችን ጳጉሜ 4 በሃዋሳ ሴንትራል ሆቴል ሊካሄድ ነው።ይህን በዓይነቱ የተለየ ዝግጅት የሚያዘጋጀው አሼ ታለንት ፕሮፋይል ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሲሆን ድርጅቱ ይህን ፌስቲቫል ላለፉት 8 ዓመታት በተሳካ ሁኔታ ሲያካሂድ ቆይቷል። በዚህ ዝግጅት የፍቅር ህይወት ተሞክሮዎች ይቀርባሉ እንዲሁም የተለያዩ አዝናኝ እና የሰርፕራዝ ዝግጅቶች ይኖራሉ።አሼ ታለንት ፕሮፋይል ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ከዚህ ዝግጅት በተጨማሪ ሌሎች 11 ዝግጅቶችንም ያዘጋጃል። በተለይ በሀዋሳ እና በመላው ደቡብ ክልል የሚታወቀው ውበታችንን ከሱስ እንጠብቀው በሚል መርህ በሚያዘጋጀው አንቲ ድራግ የቁንጅና ውድድር ነው። ከዚህ ባለፈም በደቡብ 1009 ዘውትር ዓርብ ምሽት ከ23 የታለንት ፕሮፋይል የጥበብ ምሽት ዝግጅት እንዲሁም እሁድ ምሽት ከ121 የፍቅር ምሽት የተሰኙ ፕሮግራሞችን ያዘጋጃል። የድርጅቱ ዋና መቀመጫ ሀዋሳ ሲሆን አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተለያዩ አጋሮች እና ተወካዮች አሉት። ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሬድዮ ዝግጅቶቹን በ 916 በኩል ማድመጥ ትችላላችሁ።ለተጨማሪ መረጃ የድርጅቱን መስራች እና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ አሸናፊ ግዛውን በተከታዮቹ አድራሻዎች ማግኘት ትችላላችሁ 0911 09 38 51 ### Response:
### Text: አርቲስት ተዘራ ለማ በድንገተኛ የልብ ህመም ህይወቱ አለፈ አርቲስት ተዘራ ለማ እስካሁን ከ20 በላይ ፊልሞች ላይ የተለያዩ ገፀ ባህሪያትን ተጫውቷል። ውሳኔ፣ ከኩርባው በስተጀርባ፣ ፍቅር ባጋጣሚ ፣ታሰጨርሺኛለሽ፣ ፍቅር በይሉኝታ፣አልወድሽም፣ ወንድሜ ያዕቆብ፣ ኢንጂነሩ፣ ጥቁር እና ነጭ፣ ፍፃሜው፣ ሀማርሻ፣ ሰውዬው፣ የፍቅር ቃል፣ ቪዳ፣ ባዶ ነበር፣ ፀሀይ የወጣች ቀን፣ ጣምራ፣ የበኩር ልጅ፣ እሷን ብዬ፣ ጉደኛ ነች፣ ሰበበኛ፣ ዘውድና ጎፈር በመሰራት ላይ ያሉ እና በቅርብ የሚወጡ ታላቁ ሩጫ ፣ ሰንሰለት ፣ እስክትመጪ ልበድ እና ሌሎችም ይጠቀሳሉ።በ በኩር ልጅ ፊልምም ባሳየው የገፀ ባህሪይ አጨዋወት በ9ኛው የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ላይ የአመቱ ምርጥ ተዋናይ ተብሎ ተሸልሟል። በፍቅር ቃል ፊልም ላይም እንዲሁ ባሳየው ብቃት ከእነ ቤተሰቡ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።በ1954ዓም ፍቼ የተወለደው አርቲስት ተዘራ ለማ እድገቱ እዚሁ መዲናችን አዲስ አበባ ርቼ አካባቢ ነው ይህ አርቲስት ወደ ጥበቡ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በፊልም፣ በቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ ፣ በትያትር እና በልዩ ልዩ ማስታወቂያዎች ላይ ሰርቷል። በተወለደ በ57 አመቱ አርቲስት ተዘራ ለማን በድንገተኛ ህመም ከእዚህ አለም በሞት ተለይቷል። ### Response:
### Text: በፌስቡክ የሚለቀቁ የሀሰት መረጃዎችንና የሀሰት ዜና ማጋለጥ ላይ የተሰራ አንድ ጥናት ይፋ ተደርጓል በኦፒያን አጥኚ ድርጅት ተጠንቶ ቀረበ የተባለው ጥናት 49 የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በድምራቸው 295 ሚሊየን ተከታይ ያላቸው የተካተቱበት ሲሆን ጥናቱ እነዚህ ገጾች ከጥር 2011 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 22 ድረስ 260000 ፖስቶችን ለቀዋል ያለ ሲሆን 178 ሚሊየን ግብረመልሶችንም አስተናግደዋል ተብሏል፡፡ በጥናቱ የሐሰት መረጃ ፣ የሃሰተ መረጃ፣ የውሸት ዜና ፣ ሕሶት ዜና የተሰኙ ቁልፍ ቃላት ለጥናቱ ውለዋል፡፡ከጥናቱ በተገኘው መረጃ መሰረት 56 ስለ ሀሰተኛ መረጃ ጥቆማዎችን በመስጠትም ሆነ ጠቅላላ ግንዛቤ በመፍጠር ሲሰራ የነበረው የጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡ ይህም በጥናቱ በድምር ከተጠቀሰው 295 ሚሊየን ተከታዮች መካከል 88ሺ ተከታይ ብቻ ያለው ገጽ ሲሆን የመድረስ አቅሙ ግን ወደ 30 ሚሊየን እንደሚደረስ በጥናቱ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን ብሔራዊ ሚዲያዎች የሆኑት ለምሳሌ እንደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ያሉት ሚዲያዎች በሀሰተኛ ዘገባዎች ላይ ያላቸው ተጽዕኖ 6 ብቻ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከዚህም ባለፈ እነዚህ ሚዲያዎች አልፎ አልፎም የተሳሳተ ዘገባን ሲሰሩም ይስተዋላል በማለት ጥናቱ ይጠቁማል፡፡ ### Response:
### Text: በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የተፈጸመውን ሰውን አቃጥሎ የመግደል ድርጊት የሚመረምር የወንጀል ምርመራ ቡድን ወደ አካባቢው መተከል ዞን ረቡዕ መሰማራቱን ተሰምቷል።ይህ ቡድን 5 አባላት ያሉት ሲሆን ከፍትህ ሚኒስቴር እና ፌደራል ፖሊስ በተውጣጡ መርማሪዎች የተዋቀረው ነው።በዚህ የምርመራ ቡድን ውስጥ ከፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ ሶስት ባለሙያዎች መካተታቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።ቀሪ ሁለቱ አባላት ከፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የተወከሉ ናቸው። የወንጀል ምርመራው በሁለቱ የፌደራል ተቋማት የሚከናወን መሆኑን እና የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት የአጋዥነት ሚና እንደሚኖረው ኢትዮጵያ ኢንሳይደር 20226436 የየፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።በመተከል ዞን፣ ጉባ ወረዳ፣ አይሲድ ቀበሌ ከሁለት ሳምንት በፊት የተፈጸመው በህይወት ያለን ሰው አቃጥሎ የመግደል ድርጊት በመንግስት የጸጥታ አባላት ተሳትፎ ጭምር መከናወኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኢሰመኮ ባለፈው እሁድ አስታውቆ እንደነበር አይዘነጋም።መንግስትም ማንነታቸው ምንም ይሁን ምን ድርጊቱን የፈፀሙ አካላትን አጣርቶ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቃል ቀብቶ እንደነበር ይታወሳል። ### Response:
### Text: ወደ መልካም ስራችን እንመለስበኔትዎርክ መቋረጥ ምክንያት ለእህት እና ወንድሞቻችን እንዲሁም ለልጆቻችን ተገቢውን ነገር ሳናደርግ ቆይተናል1ስም ሳምራዊትአረጋ እድሜ 22የአድማስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪበደረሰባት ድንገተኛ የኩላሊት ህመም በአልጋ ላይ የወደቀች እህታችንልጃችን2ስም ምህረቱመንግስቴ ከ8ተኛ ክፍል ትምህርቱን አቋርጦ ለ11አመታት በየሆስፒታሉ ሲንከራተት የቆየ በሰው እቅፍ ካልሆነ መንቀሳቀስ የማይችል ሲመገብም ሆነ ለተፈጥሮ ግዳጅ መቀመጥ የማይችል በከፋተኛ የአጥንት ቁስለት እየተሰቃየ ከግራታፋው 5 የተለያዩ ቁስለቶች ፈሳሽ የሚፈሰው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ውጭ ሀገር እንዲታከም ሪፈር የፃፈለት 12ሚሊየን ብር የተጠየቀ ነገር ግን ወላጁን በሞት ያጣና ምንም ገቢ የሌለው አሳዛኝ የ21 አመት ታዳጊ3ስም ካሊድኡመር የ16 አመት ታዳጊ በኩላሊት ህመም የሚሰቃይ ልጃችንወንድማችንበ አተባባሪነት 1የጋራ የባንክ አካውንት እንዲከፍቱ ተደርጓል።1000278664612 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ400000 ብር ለማሰባሰብ የታቀደው ገንዘብበትንሹ 40 ሺ አባላት ተሳታፊ እንድትሆኑ እንማፀናለን 10 ብር 40000 የ አባላት=400000 ብርእስካሁን የተገኘው 48000 ብርየሞባይል ባንኪንግ ተጠቅችሁ አሁኑኑ ድጋፋችሁን ታደርጉ ዘንድ እንማፀናለን ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ህወሓት በውጫሌ እና ጭፍራ አካባቢዎች በፈፀመው ጥቃት 30 የሚሆኑ ንፁሃንን መገደላቸውን አስታወቀ።30 ንፁሃን የተገደሉት ህወሓት ከሰሞኑ በውጪሌ እና ጭፍራ አካባቢዎች ላይ በፈፀመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት መሆኑ ተገልጿል።ይህን ያሳወቁት የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶር ለገሰ ቱሉ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው።ዶር ለገሰ አሸባሪው ህወሓት ወሮ በያዛቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ላይ ንጹሀንን በግፍ እየገደለ ነው። ከሰሞኑም ቡድኑ በከባድ መሳሪያ በፈጸመው ድብደባ በውጪሌ እና ጭፍራ አካባቢዎች ንጹሀንን ገድሏል ብለዋል።ሚኒስትሩ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፍረስ አዲስ ስልት ጀምሯል ያሉ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ተኩስ በከፈተባቸው አካባቢዎች ኢትዮጵያን የማፍረስ ህልሙን ለማሳካት የህዝብ ማዕበል ስልትን እየተከተለ የትግራይ ህጻናትን እያስፈጀ ነው ብለዋል። መንግስት በተረጋጋና በተጠና ሁኔታ እርምጀ ይወስዳል ሲሉም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።ሚኒስትሩ ይሄ ጦርነት የማይመለከተው ሰው ስለሌለ አሸባሪው ህወሓት በአሁኑ ወቅት የከፈተውን ጦርነት ሁሉም ወገን ከመከላከያ ጎን በመሆን ይመክት ሲሉም ጥሪ ማቅረባቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል። ### Response:
### Text: ድሬ የድሬዳዋ ፖሊስ በአሽከርካሪነት ተመድቦ ከሚሰራበት ድርጅት እንዲያሽከረክር የተሠጠውን መኪና ሰርቆ በ290 ሺህ ብር የሸጠው ተጠርጣሪ ግለሰብን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ። ተጠርጣሪው ግለሰብ በተሰኘ የመንገድ ስራ ድርጅት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ ነበር።የካቲት 29 ቀን 2015 ዓም ከምሽቱ ሶስት ሠዓት ላይ የድርጅቱን የስራ ኃላፊዎች ወደቤታቸው ካስገባቸው በኋላ ያለማንም ፍቃድ ተሸከርካሪውን ከሌሎች ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ወደ አዲስ አበባ በመውሰድ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመተውን ተሸከርካሪ ለአንድ ግለሰብ በ290 ሁለት መቶ ዘጠና ሺ ብር ሽጧጣ።የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመ ከሁለት ቀን በኋላ ከድርጅቱ መኪና እንደጠፋ ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ ከተጠርጣሪው አድራሻ በመነሳት ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪውን በሌላ ሰው እጅ በአዳማ ከተማ ሲሽከረከር በቁጥጥር ስር ሊያውለው መቻሉ አሳውቋል።በአሁኑ ወቅት ተሽከርካሪውን ሰርቆ የሸጠውን አሽከርካሪ እና የገዛውን ግለሰብ ጨምሮ 5 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን ድሬ ፖሊስ ገልጿል።የድሬ ፖሊስ መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለንብረታቸው ተገቢውን ክትትል ማድረግ እንዳለባቸው መልእክት አስተለልፏል። ድሬፖሊስ ### Response:
### Text: አዋጁ የወጣው በምክንያት ነውበዶክተር ያቤፅ ከበደየህብረተሰብ ጤና ባለሞያድብቅ ጦርነት የከፈተብንን የኮሮና ቫይረስ እንዴት እንዋጋ የባለሙያ ምክሮችን በአግባቡ መተግበር ስርጭቱን ይቀንሰዋል አዎከበዓሉ ወዲህ የሚታየው መዘናጋት እጅጉን እያሳሰበን ነው። የምርመራ ምህዳሩ ገና እየሰፋበት ባለበት ስዓት ህብረተሰቡ እያሳየው ያለው መዘናጋት ወደ የማንወጣው ትግል ውስጥ ሊከተን ነው።የእጅ ጓንትን ማድረግ ለህብረተሰቡ የተሳሳተ የደህነት ስሜትን በመስጠት ለበለጠ መዘናጋት ያጋልጣቸዋል በአብዛኛው የሚረዳው የጤና ባለሙያዎችን ሲሆን እዲሁም ስራቸው ከግብይት እና ልውውጥ ጋር ለተያያዘዙ የህብረተሰብ ክፍል ነው።የባንክ አገልግሎት በሚሰጥባቸው አካባቢዎች፣ በገበያዎች፣ በትራንስፖርት መሳፈሪያ ቦታዎች፣ በትራንስፖርት ውስጥ፣ በሱቆች፣ በመድሀኒት መሸጫ አካባቢዎች ፣ ህዝባዊ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ቦታዎች እና ሌሎች ህዝብ በሚበዛባቸው መሰል አካባቢዎች የሚገኝ ማንኛውም ሰው አፍና አፍንጫው ላይ መሸፈኛ የማድረግ ግዴታ አለበት።እነኚህን እና የእጅ ንፅህናን መጠበቅ ባጠቃላይ የእኛ ህዝብ ላለው የኑሮ መስተጋብር የቫይረሱን ስርጭት ይቀንሰዋል።እባካቹህ ለራሳችሁ አስቡ ለእኛም አስቡ ### Response:
### Text: ከቀናት በፊት በአፍጋኒስታን ካቡል ኤርፖርት አካባቢ የሽብር ጥቃት ሊያደርስ መሆኑን መረጃዎች መውጣታቸው ተከትሎ አካባቢው ላይ ውጥረት ስለመንገሱ ሪፖርት መደረጉ ይታወሳል።በወቅቱ የአሜሪካ ኤምባሲ የደህንነት ስጋት እንዳለ ተናግሮ ነገር ግን ስጋቱ ምን እንደሆነ ሳይጠቅስ ከአፍጋኒስታን የሚወጡ የአሜሪካ ዜጎች እና ሌሎችም ወደ አካባቢው እንዳይሄዱ አስጠንቅቆ ነበር።አሁን ደግሞ በርካታ ሃገራት ካቡል አየር ማረፊያ የሽብር ጥቃት ሊኖር ስለሚችል ዜጎቻቸው ወደ አየር ማረፊያ እንዳይሄዱ አስጠንቅቀዋል።አውስትራሊያ፣ አሜሪካ ፣ ዩናይትድ ኪንግደም ለዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ ከሰጡ መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሱ ናቸው።ከአየር ማረፊያው ውጪ ያሉ ሰዎች አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ ተነግሯቸዋል።የተለያዩ ሃገራት ከተቀመጠላቸው የነሃሴ 25 ቀነ ገደብ በፊት ዜጎቻቸውን ከአፍጋኒስታን ለማስወጣት እየተሯሯጡ ነው።እስካሁን ባለው ሪፖርት መሰረት ከ 14 ጀምሮ 82300 ሰዎች ከአፍጋኒስታን የወጡ ሲሆን ከነዚህ መካከል 19000 ማክሰኞ ዕለት ተው ከካቡል የወጡት። ዛሬ በተገኘው መረጃ አሜሪካ አሁንም 1 ሺህ 500 የሚደርሱ ዜጎቿን ከአፍጋኒስታን አላስወጣችም።መረጃው ከቢቢሲ፣ ሲኤን ኤን እንዲሁም ከቪኦኤ የተገኘ ነው። ### Response:
### Text: የትራንስፖርት ታሪፍ0 ጭማሪ አልተደረገም️ዛሬ በስራ ላይ የሚውለውን የነዳጅ ዋጋ መጨመር ተከትሎ ምንም አይነት የትራንስፖርትታሪፍ 0 ጭማሪ እንደማይኖር የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገለፀ።የአዲስ አበባም ሆነ የክልሎች የትራንስፖርት ታሪፍ ባለበት እንደሚቀጥልም ባለስልጣኑ አስታውቋል።በባለስልጣኑ የፖሊሲ ጥናትና የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ መብራቱ እንደገለፁት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነውን የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ ተከትሎ ምንም አይነት የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ አልተደረገም።በህዳር ወር የነዳጅ ማስተካከያ በተደረገበት ወቅት የአገር አቋራጭ ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማስተካከያ ስለተደረገና የአዲስ አበባውም የዛሬ አመት አካባቢ መሰረታዊ ማስተካከያ ያደረገ ስለሆነ የሚኖር ማስተካከያ አለመኖሩን ነው ያስታወቁት።የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ አካላት ይህንን አውቀው ምንም አይነት ጭማሪ ማድረግ እንደሌለባቸው ባለስልጣኑ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።ህብተረተሰቡ በቀድሞው ታሪፍ መሰረት የአገልግሎት ክፍያውን እንዲፈፅም አሳውቀዋል።የንግድ ሚኒስቴር ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: የባህር ዳርዘማ ወንዝፈለገብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተገኙበት በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል፡፡ ፕሮጀክቶቹን በተመለከተ ኮንትራት አንድ የባህርዳር ዜማ ወንዝ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ የመንገዱ ርዝመት 925 ኪሜ የመንገድ ግንባታውን ሲያካሂድ የቆየው የስራ ተቋራጭ ሲኖ ሃይድሮ የተባለ የቻይና ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት የምህንድስና ቁጥጥርና የማማከር ስራውን ሲያካሂድ የቆየው አማካሪ ድርጅት፡ አገር በቀሉ ኔት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፕሮጀክቱን ለማካሄድ ወጪ የሆነው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን 129281875099 ብር የግንባታ ወጪው የተሸፈነው ሙሉ በሙሉ የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል። ኮንትራት ሁለት ዜማ ወንዝ ፈለገብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ የመንገዱ ርዝመት 8283 ኪሜ የመንገድ ግንባታውን ሲያካሂድ የቆየው የስራ ተቋራጭ ሲአርሲጂ የምህንድስና ቁጥጥርና የማማከር ስራውን ሲያካሂድ የቆየው አማካሪ ድርጅት አይከን ኢንጂነሪንግ ፕሮጀክቱን ለማካሄድ ወጪ የሆነው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን 1244361000 ብር የግንባታ ወጪው የተሸፈነው፡ ሙሉው የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል፡፡ የትራንስፖርት ሚንስቴር ### Response:
### Text: የእሳት አደጋ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ልዩ ቦታው ትቅደም ትምህርት ቤት ጀርባ በሚገኘውና ሾላ ገበያ ዶሮ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ የንግድ ሱቆች ላይ የእሳት አደጋ ደረሰ።የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መቆጣጠር እና መከላከል ባለስልጣን ከፍተኛ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቶ ማሞ እንዳስታወቁት የእሳት አደጋው ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ ነው የደረሰው።በእሳት አደጋውም በንብረት እና በሰው ላይ ጉዳት ደርሷል ያሉት አቶ ንጋቱ የደረሰው የጉዳት መጠን እየተጣራ መሆኑን ገልፀዋል።በአሁኑ ጊዜም ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች በአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መቆጣጠር እና መከላከል ባለስልጣን እና በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል አምቡላንሶች ተወስደው ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ገልፀዋል።7 የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎች፣ 2 ቦቴዎች እሳቱን የማጥፋት ስራው ላይ ተሰማርተዋል ብለዋል 2 አምቡላንሶችም አደጋ የደረሰባቸውን ሰዎች ለመርዳት መሰማራታቸውን በመጥቀስ።በአሁኑ ጊዜም እሳቱ በቁጥጥር ስር መዋሉንም አቶ ንጋቱ አስታውቀዋል።የእሳት አደጋው መንስኤም እስካሁን አለመታወቁን እና በመጣራት ላይ እንደሚገኝም ነው አቶ ንጋቱ ያስታወቁት። ### Response:
### Text: ወንጀል ነክ መረጃ️ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰዉ ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሽ ሳሙኤልጎችልወልደመስቀል በ1996 ዓም የወጣዉን የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 555ለ ስር የተመለከተዉን ድንጋጌ ተላልፎ በፈፀመዉ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ተከሷል፡፡ተከሳሽ በሌላ ሰዉ አካል ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ሰኔ 2 ቀን 2010 ዓም በግምት ከምሽቱ 1230 ሲሆን በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታዉ በግ ተራ ተብሎ ከሚጠራዉ አካባቢ የግል ተበዳይ አብርሀም ታፈረን በቦክስ በመምታት የላይኛዉ የፊት ለፊት አራት ጥርሶቹ እንዲወልቁ ያደረገ በመሆኑ በፈፀመዉ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ነዉ፡፡ተከሳሽ ከላይ በክስ ዝርዝሩ አደረክ የተባልኩትን ድርጊት አልፈፀምኩም ሲል የእምነት ክህደት ቃሉን ቢሰጥም ዐቃቢ ህግ 4 የሰዉ ምስክሮችንና የሰነድ የማስረጃዎቹን አጠናቅሮ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡መዝገቡን የተመለከተዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የየካ ምድብ የወንጀል ችሎትም ተከሳሽ ጥፋተኛ ነዉ ሲል ታህሳስ 08 ቀን 2011 ዓም በዋለዉ 3ተኛ ወንጀል ችሎት በቅጣት ዉሳኔው ተከሳሽን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል በማለት በ2 አመት ከ9 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡ምንጭ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ### Response:
### Text: ኢር ታከለ ኡማ በቦሌ ክከተማ በመንግሥት በጀት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነቡ በርካታ ፕሮጀክቶችን ስራ አስጀምረዋል፡፡ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው እነዚህ ፕሮጀክቶች የከተማ አስተዳደሩ ተቋማትን በአንድ አከባቢ በመገንባት ለህብረተሰቡ ምቹ እና ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጡ ታስቦ የተገነቡ ናቸው፡፡ዛሬ ከተመረቁ ፕሮጀክቶች መካከል 10 ጤና ጣቢያ ፣ 98 የንግድ ሼዶች ፣ 9 የአንደኛ እና ሁለተኛ የመማርያ ትቤቶች ፣ 6 የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎች እና 13 የወሳኝ ኩነት ማዕከላት ይገኙበታል፡፡በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ኢር ታከለ ኡማ የከተማ አሰተዳደሩ የህብረተሰቡን አቅም ባገናዘበ መልኩ ጥራት ያለው ትምህርትን በመንግስት ትቤቶች ለመስጠት ከምን ጊዜውም በላይ ጠንክሮ እየሰራ እንደሆነም ጠቅሰዋል፡፡በ2012 የትምህርት ዘመን የከተማ አስተዳደሩ 600ሺ ለሚሆኑ በከተማዋ ውስጥ ለሚገኙ የመንግስት ትቤት ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ደብተር ፣ እስክርቢቶ ፣ እርሳስ እና የመሳሰሉትን እንደሚያቀርብም አስታውቀዋል፡፡በመጨረሻም የከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጀው የክረምት የበጎ አድራጎት ስራ ላይ የአከባቢው ነዋሪዎች ፣ ወጣቶች እና መምህራን እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና በምዕራብ ሸዋ ዞን ጅባት ወረዳ ዛሬ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። በአደጋው 38 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱም ተገልጿል።በምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ማኔጅመንት ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ተሰማ ብሩ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ዛሬ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ላይ ነው። አርባ ሰዎችን አሳፍሮ ከኖኖ ወረዳ በመነሳት ወደ አምቦ ከተማ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 337423 ኦሮ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው አደጋው ሊደርስ የቻለው።አደጋው በጅባት ወረዳ ጋሞ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጆሬ በተባላ አካባቢ መድረሱን የገለጹት ኮማንደር ተሰማ፣ በእዚህም የሁለት መምህራን ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በ48 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። የመኪናው አሽከርካሪ ለጊዜው መሰወሩንና ክትትል እየተደረገበት መሆኑንም ተናግረዋል። እንደኮማንደር ተሰማ ገለጻ በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው ተሰጥቷል። ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 11 ሰዎችም በአምቦ ሆስፒታል የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። ### Response:
### Text: 251994780288 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን በማስፈጸም ሂደት ድምጽ ሰጪዎች ጥያቄና አስተያየት መቀበያ የስልክ መስመር አዘጋጅቷል፡፡በመሆኑም በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ መረጃ መስጠት የምትፈልጉ ወይም ጥያቄ ያላችሁ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰአት ድረስ በ 251994780288 የስልክ መስመር በመደወል አስተያየታችሁን መስጠትም ሆነ ጥያቄዎችን መጠየቅ ትችላላችሁ፡፡ ቦርዱ ጥያቄዎችን በመመለስ አስተያየቶችን ተቀብሎ ከግምት ውስጥ በማስገባት ሂደቱን የተሻለ እንዲሆን ጥረት ያደርጋል፡፡1 ከምርጫ ሂደቱን ሊያስተጓጉሉ የሚችሉ እና ከምርጫ ጋር የተገናኙ የጸጥታ ችግሮች ለመጠቆም2 በመራጭነት ለመመዝገብ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመጠቆም3 በመራጭነት የምዝገባ ሂደት የደረሰ ተጽእኖ ካለ ለማሳወቅ4 በምርጫ ጣቢያ አካባቢ የተከለከሉ ተግባራትን ለመጠቆም በምርጫ ጣቢያው እና በ200 መቶ ሜትር ዙሪያ መገኘት የሚችሉት ሁለት ህጋዊ ወኪል ፣ ሁለት ቅሬታ ሰሚ፣ የቦርዱ አስፈጻሚዎች፣ ፍቃድ የተሰጣቸው ታዛቢዎችና ሚዲያዎች ብቻ ሲሆኑ ማንኛውም አይነት ማስታወቂያ ወይም ባነር መስቀል፣ የታጠቀ ሃይል መገኘት የተከለከለ ነው5 ስለህዝበ ውሳኔው ሂደት ያሉ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ### Response:
### Text: በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረውን የሳይበር ጥቃት ማክሸፍ ተቻለ ዛሬ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረውን የሳይበር ጥቃት ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ መቻሉን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡የፋይናንስ ተቋሞችን የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ኔትወርኩን ከ15 እስከ 20 ደቂቃዎች ለማቋረጥ ተገድዶ እንደነበር የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ወርቁ ጋቸና ተናግረዋል፡፡ተመሳሳይ ችግሮችን ለማክሸፍ ኤጀንሲው ከኢትዮ ቴልኮም ጋር በመሆን እየሰራ መሆኑንም ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡በኤጀንሲ ውስጥ ኢትዮ ሰርት የሚባል የፋይናንስ ተቋማትን ለ24 ሰዓት የሚከታተል እና አዲስ ጥቃቶች ሲቃጡ የመከላከል ተግባር ያለው ክፍል መኖሩን ገልጸዋል፡፡ በዚሁ ክፍል ጥቃቱ ሳይደርስ መከላከል መቻሉን ኢንጅነር ወርቁ ተናግረዋል፡፡ስራው ብዙ ጊዜ የተለመደውና የኔትወርክ ለውጥ የሚደረገው ብዙ ሰው ኢንተርኔት በማይጠቀምበት ሰአት ምሽት እንደነበር የተገለጸ ሲሆን ዛሬ ላይ የተፈጠረው አስቸኳይ ስለነበር ቀን ላይ እርምጃው መወሰዱን ተጠቁሟል፡፡ ጥቃቱ ከየት እንደተሰነዘረ ዝርዝር ጉዳዮችን እየተመለከቱ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ኢቢሲ ### Response:
### Text: ሶማሊያ በጎረቤታችን ሶማሊያ አልሸባብ የሽብር ቡድን በፈፀመው ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎች ሲገደሉ 7 ተሽከርካሪዎች በቡድኑ ተቃጥለዋል።የሶማሊያ ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ጨካኙ የሽብር ቡድን ትላንት ምሽት በሂራን ክልል 20 ሰዎችን ገድሎ ምግብና ሌሎች የንግድ ሸቀጦችን ጭነው ለማሃስ ወረዳ የአካባቢው ነዋሪዎች ይዘው ሲጓዙ የነበሩ 7 ተሽከርካሪዎችን አቃጥሏል ብሏል።አንድ0የአካባቢው ባለስልጣናት ደግሞ ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል0 ጥቃቱ የተፈፀመው በክልሉ ዋና ከተማ በለድዋይ እና በማሃስ ወረዳ መካከል ባለው ጎዳና ላይ መሆኑን ገልፀው 22 ሰዎች መገደላቸውን አስረድተዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው ምግብ ጭኖ ይጓዝ በነበረ ልዑክ ላይ መሆኑን አመልክተው ቡድኑ 17 ሰዎች እዛው ገድሎ ተጎጆዎቹን ሊረዱ በመጡ ሲቪሎች እና ቆፋሪዎች ላይ በተቀበረ ፈንጂ በማነጣጠር 5 ሰዎችን ገድሏል ብለዋል።አልሻባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ሲሆን በጥቃቱ 20 የአካባቢውን ታጣቂዎች መግደሉን ገልጿል።የሶማሊያ መንግስት ባወጣው መግለጫ ጥቃቱን አጥብቆ አውግዞ አረመኔ እና አሳፋሪ ሲል ገልጿል።መንግስት ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጎን እንደሚቆም ገልጾ ለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት ጠንከር ያለ ምላሽ እንደሚሰጥ ቃል መግባቱን ቪኦኤ ዘግቧል። ### Response:
### Text: የምክር ቤቱ አጀንዳዎች ምንድናቸው የጉራጌ ዞን ምቤት ነገ መስከረም 7 ቀን 2015 ዓም 4ኛ ዙር 8ኛ ዓመት 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ለማካሄድ ለምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርቧል።በጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎች የ2014 ዓም የአስተዳደር ምክር ቤት እቅድ አፈጻጸም0 የዞኑ ፍርድ ቤት የ2014 ዓም ማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማ የ2015 የመንግስት የምክርቤቱና የፍርድ ቤት አመታዊ እቅድ እና የ2015 የዞኑ አመታዊ በጀት ላይ በመምከር ዉሳኔ ማሳለፍ እንደሆነ የምቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አርሺያ አህመድ ተናግረዋል።ከላይ ከተጠቀሱት አጀንዳዎች ውጪ ሌላ የተለየ አጀንዳ አለመኖሩን አፈጉባኤዋ ገልፀዋል።በጉባኤው ላይ መያዝ የሚገባቸው አጀንዳዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የተያዙ መሆናቸውንና ጉባኤው የሚመራው በህገመንግስቱ መነሻነት ከፌደራልና0 ከክልል ህገመንግስት መነሻ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምቤት በተዘጋጀው የአሰራር ስነምግባር መሰረት መሆኑን አስረድተዋል።የጉራጌ ዞን ምቤት የደቡብ ክልላዊ መንግስትን ለ2 በሚከፍለው የክላስተር አደረጃጃት ላይ ተወይይቶ የቀረበውን የክላስተር አደረጃጀት በአብላጫ ድምፅ ውድቅ ካደረገበት የባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር አስቸኳይ ጉባኤ ወዲህ ለስብሰባ ሲቀመጥ የነገው የመጀመሪያ ይሆናል። ### Response:
### Text: 2013 ዛሬ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የምርጫ ቅስቀሳ የምርጫ ዘመቻ የሚጀምርበት ቀን ነው።ፖርቲዎች እያደረጉ ያሉትን እንቅስቃሴ ደውለን ጠይቀናል። ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ህብር ኢትዮጵያ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለህብር ኢትዮጵያ ፓርቲ የደወለ ሲሆን አመራሮቹ ዛሬ የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልጀመሩ ገልፀዋል።ነገር ግን ፓርቲው ምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ለመጀመር ሰፋ ያለ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ አሳውቆናል።በዚህ ሳምንት የምርጫ ቅስቀሳ እንደሚጀምር ተገልጾልናል። የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ኢህአፓ የፓርቲውን አመራሮች በስልክ አግኘተን ያነጋገርናቸው ሲሆን ኢህአፓ ለምርጫ ቅስቀሳ ዛሬ እንዳልጀመረ ገልፀውልናል።ነገር ግን ኢህአፓ ለምርጫ ቅስቀሳ የሚሆን ቅድመ ሁኔታዎችን የማመቻቸት እንዲሁም ሌሎች ሰፊ ዝግጅቶችን እያደረገ እንደሚገኝ አሳውቆናል።በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥም ወደቅስቀሳ ይገባል። የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲት ፓርቲ ኢሶዴፓበቅርቡ ከመድረክ በይፋ ለተለያየው ኢሶዴፓ የምርጫ ቅስቀሳውን በተመለከተ ጥያቄ አቅርበን ነበር ዛሬ ምርጫ ቅስቀሳ እንዳልጀመር ገልጾልናል።ፓርቲው ወደፊት ቀስ ብሎ የምርጫ ቅስቀሳውን እንደሚጀምር አሳውቆናል። ### Response:
### Text: በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አሕመድ መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና በሰጡበት ወቅት ነው።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተማሪዎቹ እንኳን ደስ ያላችሁ ካሉ በኋላ የተሰጣቸውን ፈተና በአግባቡ መስራት በመቻላቸው ኢትዮጵያን የሚያግዙ 273 ተማሪዎች ተገኝተዋል በዚህም ደስታ ይሰማናል ብለዋል፡፡ተማሪዎቹ እጅግ ዘመናዊ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉና ለኢትዮጵያ እና አፍሪካ የሚደርሱ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።ዶር ዐቢይ ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀዋል በተለይ ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁ ብለዋል። ኤፍቢሲ ### Response:
### Text: ጨፌ ኦሮሚያየኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ለማመገርሳ የ6 ወራት የስራ አፈጻጸምን ለጨፌ ኦሮሚያ ያቀረቡ ሲሆን፣ በሪፖርታቸው የመሬት ወረራና ሕግ ወጥ ግንባታን ለመከላከል ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ ህዝቡ የሕግየበላይነትን የማስከበር ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት ባለፉት 6 ወራት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡ የክልሉ መንግስት ሰላምእንዲኖር እየሰራ ቢሆንም በክልሉ አንዳንድ አከባቢዎች የጸጥታ ችግሮች መከሰታቸውን የገለጹት አቶ ለማ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ችግሩ እንዲከሰት ያደረጉ አካላትን ወደ ሕግ የማቅረብ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል፡፡በተለይ በጉጂና በምዕራብ ጉጂ ዞኖች የተከሰቱትን የጸጥታችግሮች በትዕግስትና በሳል አመራር በመስጠት ሁኔታው ወደ ሰላም እንዲመጣ መደረጉን አቶ ለማ በሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡ ህዝቡ ከመጣው ለውጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ ስራዎች መሰራታቸውንም አቶ ለማ ገልጸዋል፡፡ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በተሰራው ስራ የተለያዩ ፓርቲዎች ወደ አገር ገብተው የፖለቲካ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ ### Response:
### Text: ክልላዊ ቤተ ክህነት ፅህፈት ቤት የማቋቋም ጥያቄ የቤተ ክርስቲያኗ የዶግማና የቀኖና ትውፊት ለውጥ ሳይኖር አስተዳደራዊ ችግሮችን ለመፍታት መዋቅር የማበጀት ጥያቄ ነው የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ፅህፈት ቤት አደራጅ ኮሚቴ ቢቢሲአማርኛ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ፅህፈት ቤት በክልል ደረጃ እንዲዋቀር የቀረበው ጥያቄ ምላሽ ቅዱስ ሲኖዶሱ በ30 ቀናት ውስጥ እንዲያሳውቃቸው ይህ ተግባራዊ ካልሆነ ግን አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ፅህፈት ቤት አደራጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ ቀሲስ በላይ መኮንን አስታውቀዋል።በዛሬው ዕለት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ኮሚቴው ባለ ስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያወጣ ሲሆን ቅዱስ ሲኖዶሱ ክልላዊ ፅህፈት ቤቱን ጥያቄ የሚቀበለው ከሆነ የሰው ኃይል አመዳደቡም ሆነ አፈፃፀሙ ይህ አደራጅ ኮሚቴና ጠቅላይ ቤተ ክህነት በጋራ የሚወስኑት እንደሚሆን ተገልጿል።በተጠየቀው መሰረት አስቸኳይ ምላሽ የማያገኝ ከሆነ የምዕመኑን ጥያቄ ለመመለስ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ኮሚቴው አስጠንቅቋል። እርምጃው ምን እንደሆነ በዚህ ወቅት ግልፅ ባያደርጉም ከዚህ ቀደም እንደተናገሩት በራሳቸው ክልላዊ ቤተ ክህነት ፅህፈት ቤት እናቋቁማለን ማለታቸው የሚታወስ ነው።ተጨማሪ ያንብቡ 09013 ### Response:
### Text: ስራ ፈላጊዎች እንዳትጨበረበሩ ተጠንቀቁከቲክቫህ አባል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለተለያዩ የሥራ መደቦች ክፍት የስራ መደቦችን ይፋ ያደረገ ሲሆን እአአ ታህሳስ 152020 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ካምፓሶች የ ን ለፈተና ያቀረቡትን የእጩዎች ዝርዝር ከየየራሳቸው የስልክ ቁጥር ጋር በማያያዝ በድርጅቱ ኢኮሥኮ ጠርቷል።ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ነው የምደውለው የሚል ሰው በ ኢኮሥኮ ቴሌግራም ገጽ ላይ ከተያያዙት የእጩዎች ዝርዝር ውስጥ የስልክ ቁጥሮችን በመጠቀም እየደወለ ከኮርፖሬሽኑ ጋር ስምምነት ለመፈረም የደመወዛችሁን 50 ወደ 6000 ገደማ መክፈል አለባችሁ እያለ ገንዘቡን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ እንዲያስገቡለት የባንክ ቁጥሩን ይሰጣል።ሥራውን ለማግኘት እና የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለዚህ ግልሰብ ለማስቀመጥ ፍላጎት ያላቸው ብዙ ተጋላጭ ሠራተኞች አሉ ብዬ አምናለሁ፡፡ ባለቤቴ ጋር ደውሎ 6000 ብር እንድታስገባ ነገራት ይህንንም በስልኳ ቀድታዋለች። የቲከቫህ አባላት እንዳይታለሉ እላለሁ። የግለሰቡ የስልክ ቁጥር ፣ የባንክ አድራሻውን መዝግበው የቤተሰባችን አባላት ልከዋል። ከላይ የምታዳምጡት የተቀዳው የስልክ ንግግር ነው ### Response:
### Text: በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአስከፊ ችግር ውስጥ ናቸው የሶማሌ ክልልየሶማሌ ክልላዊ መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ በሶማሌ እና አፋር ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በሚገኙ አካባቢዎች ላይ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአስከፊ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ ገልጿል።ክልሉ ከግጭቱ ጋር በተያያዘ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።ከመኖሪያ ቀዬአቸው የተፈናቀሉት ዜጎች በአሁኑ ወቅት በሲቲ ዞን ኤረር ወረዳ አስቡሊ እና በድዌይ በሚባል አካባቢ የተሰባሰቡ ቢሆንም በክረምቱ ከባድ ዝናብ ምክንያት መንገዶች በመቆራረጣቸውና ወደ አካባቢው ተሽከርካሪ ሊገባ ባለመቻሉ ምንም አይነት የእለት ደራሽ እርዳታ0ለማቅረብ አልተቻለም ብሏል።በአሁኑ ወቅት ተፈናቃዮቹ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ ያለው የክልሉ መንግስት ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመቀናጀት አፋጣኝ እርዳታ ለማቅረብ ጥረትና ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል።ለዚህም የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ እና ምርዕሰ መስተደድር ኢብራሂም ኡስማን የተካተቱበት የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ልኡካን ቡድን ተፈናቃዮች በሚገኙበት በሲቲ ዞን በመገኘት ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስ በማስተባበር ላይ ይገኛሉ ሲል ክልሉ አሳውቋል። ### Response:
### Text: ለግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአዲስ መልክ ፍቃድ ሊሰጥ መሆኑን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳውቋል። የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ለግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአዲስ መልክ ፍቃድ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።ባለሥልጣኑ ከህዳር 30 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ አዲስ ለሚከፈቱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፍቃድ መስጠት ማቆሙ ይታወቃል።ባለሥልጣኑ አዲስ ፈቃድ የሚያገኙ ተቋማት ማሟላት የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች የሚደነግጉ መመሪያዎች ዝግጅት ማጠናቀቁን የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡የተሻሻሉት መመሪያዎቹ ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል።ከዚህ ቀደም ፈቃድ የነበራቸውን ጨምሮ ሁሉም የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሙሉ እንደ አዲስ ምዝገባ መፈጸም እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል።ምዝገባው በዘንድሮ ዓመት የሚጠናቀቅ ሲሆን በ2016 ዓም አዲስ ፍቃድና የእድሳት አገልግሎት መስጠት ሊጀመር እንደሚችል ዋና ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡በኢትዮጵያ 360 የሚጠጉ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን መረጃ ያሳያል። ### Response:
### Text: የሚዘጉ መንገዶች ማስታወሻከጥር 28 እስከ የካቲት 2 ቀን 2012 ዓም የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ እና ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ ስለሚካሄድ ጉባኤው ተጠናቆ እንግዶች እስከሚ ሸኙ ድረስ ከትራፊክ ፖሊስ ሞተር ብስክሌቶች ውጪ ማንኛውም ባለ ሁለት እግር ሞተር ብስክሌት በአጃብ መስመር ውስጥ ማለትም፡1 ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወሎ ሰፈር ኦሎምፒያ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግስት ግቢ ገብርኤል መታጠፊያ ሸራተን አዲስ አራት ኪሎ2 ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወሎ ሰፈር ኦሎምፒያ ጋዜቦ በአዲሱ መንገድ ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ ቡልጋርያ ማዞሪያ አፍሪካ ህብረት3 ከፓርላማ መብራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በብሄራዊ ቤተመንግስት በፍልውሃ ብሄራዊ ቲያትር ሜክስኮ አደባባይአፍሪካ ህብረት4 ከአራት ኪሎ በሸራተን ሆቴል ሐራምቤ ሆቴል ብሔራዊ ቲያትር መብራት ወይም አንድነት መብራት ሰንጋ ተራ ዋቢ ሸበሌ ሜክስኮ አደባባይ ትምባሆ ሞኖፖል አፍሪካ ህብረት5 ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወሎ ሰፈር ኦሎምፒያ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተመንግስት ግቢ ገብርኤል መታጠፊያ አራት ኪሎ እንግዶች በአጀብ በሚያልፉበት ወቅት ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ### Response:
### Text: መስከረም 162013 ዓምአጫጭር የኮቪድ19 መረጃዎች በኮሮና ቫይረስ መባባስ ምክንያት የኢንግላንድ እና የዌልስ መጠጥ ቤቶች ከሃሙስ ጀምሮ ደንበኞቻቸው በጊዜ አስተናግደው እየዘጉ ናቸው። በስኮትላንድ ትላንት ጀምሮ ከማታ አራት ሰዓት በኃላ ምግብና መጠጥ ቤቶች እንዲዘጉ ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ፈረንሳይ ውስጥ ካለፈው ሰኔ ወር ወዲህ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ታመው ጽኑ ህክምና ክፍል የሚገቡ ህሙማን ቁጥር ሃሙስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንድ ሽህ አልፏል። ባለፉት 24 ሰዓት በህንድ ተጨማሪ 1093 ሰዎች ሲሞቱ 85468 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ብራዚል ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት 836 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 32670 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 1 ሚሊዮን እየተጠጋ ነው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 32771253 ደርሰዋል። ክትባት በስፋት ከመሰራጨቱ በፊት በቫይረሱ የሚሞቱ ሰዎች ሁለት ሚሊዮን ሊደርሱ ይችላሉ ብሏል። የድርጅቱ የድንገተኛ ቡድን መሪ ዶር ማይክ ራየን እንዳሉት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ካልተባበረ የሟቾች ቁጥር ሊጨምርም ይችላል። ፈለክ የፊት ማስክ ለኮቪድ19 መከላከያ የሰራቸው የአፍንጫና አፍ መሸፈኛ ማስክ የውጤታማነት የብቃት ማረጋገጫ አግኝቷል። ### Response:
### Text: ጨረታውተሰርዟል 30 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የወባ አጎበር ግዢ ጨረታ ተሰረዘ።የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር 30 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት በኬሚካል የተነከረ የወባ መከላከያ አጎበር ግዢ በኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩል ግዢ እንዲፈጸም ጥያቄ አቅርቦ ነበር።በዚህም መሰረት ዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ ወጥቶ ተጫራቾች ቀርበው አሸናፊውን ቢለይም በጨረታው ሂደት ላይ ቅሬታ መቅረቡን ተከትሎ ሚኒስቴሩ ማጣራት በማድረግ ጨረታውን እንዲሰረዝ ማድረጉን አሳውቋል።የጤና ሚኒስቴር በሌሎች ተቋማት የማጣራት ስራ መሰራቱን እንዲሁም ደግሞ በራሱ ባደረገው የማጣራት ስራ በጨረታ ሂደቱ ላክ የተፈጸመ ህገወጥ ድርጊት እንዳላገኘ ገልጿል።ነገር ግን የብቃት ማረጋገጫ እና ምዝገባ ጋር በተያያዘ በግብርና ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በህግ የተሰጠ ነገር ግን የስልጣን መደራረብ የነበረ መሆኑን እና የጨረታ መገምገሚያ መስፈርት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ቀርቦ ባለበት ሁኔታ ሂደቱን ከማስቀጠል የፋይናንስ ድጋፍ በሚያደርገው ድርጅት አማካኝነት ግዢው እንዲፈጸም ማድረግ ለሚኒስቴሩ የተሻለ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን በመገንዘብ ጨረታው እንዲሰረዝ ተደርጓል፡፡ተጨማሪ ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል ### Response:
### Text: ሞያሌ በሞያሌ ከተማ ዛሬም ውጥረት እንዳለ ተሰምቷል። ትላንት በሞያሌ ጉሙሩክ መጋዘን የእሳት ቃጠሎ መደረሱ አይዘነጋም።ትላንት በቀኑ 630 በሞያሌ ጉምሩክ መጋዘን ቃጠሎ 8 መኪናዎች ሙሉ በሙሉ ሲወድሙ እጅግ በርካታ ኮምፒተሮች ተዘርፈዋል። ለጊዜው መነሻው ምን እንደሆነ ባይታወቅም የተደራጁ እና የታጠቁ ሀይሎች ወረራ ፈፅመው የፈፀሙት ተግባር ነው ተብሏል።የተደራጁት ሀይሎች ቤንዚን አርከፍክፈው መጋዘኑን ከማቃጠል በተጨማሪ በርካታ ንብረቶችን ዘርፈዋል። እንዲሁም የፀጥታ ሀይላትን ሲከላከሉ እንደነበር ታውቋል።ክስተቱ ድንገተኛ በመሆኑ የፌደራልና መከላከከያ ሀይሎች ሁኔታውን መቆጣጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።በቃጠሎው ወ ቅት የእሳት አደጋ መከያከያ ባለመኖሩ መጋዘኑን ከወድመት ለመከላከል አስቸጋሪ ሆኖ ነበር።ህብረተሰቡ እሳቱን ለማጥፋት ሙከራ ለማድረግ ቢፈልግም የተደራጁት ሰዎች አርፋችሁ ተቀመጡ ካልሆነ የናተንም ቤት እናቃጥላለን በማለት አስፈራርተዋል።ዛሬም ድባቡ ጥሩ እንዳልሆነ ተሰምቷል። ጥዋት ተኩስ ነበር ኬላ ላይም ፍተሻ እንዳይደረግ ሲሞከር ተስተውሏል።የሞያሌ ጉምሩክ ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቋል።ምንጭ አቶ ጫንያለው ፋጂየሞያሌ ገቢዎችና ጉምሩክ ቅርጫፍ ስራ አስኪያጅ ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ ስምምነት ላይ ባይደረስም የውሃ ሙሌቱን ታከናውናለችየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልኢትዮጵያ በጋራ የመጠቀምና አብሮ የማደግ መርህን የምትከተል ሀገር ናት፡፡ ይሁንና በራሷ የተፈጥሮ ሀብት ለመጠቀም የሌሎችን ፈቃድ ወይም ይሁንታ የማግኘት ግዴታ የለባትም፡፡በዘንድሮው የክረምት ወቅት ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውሃ ለመያዝ የምትሰራው ስራ 60 በመቶ የሚሆነው የሃገራችን ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ የተጀመረውን ጥረት ያግዛል፡፡ በአንፃሩ በጋራ ተጠቃሚነት ለማታምነው ግብፅ ከእኔ ብቻ ልኑር የዘመናት ግትር አስተሳሰቧ እንድትወጣና በፍትሃዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነት ምህዋር ላይ እንድትሽከረከር ያደርጋታል፡፡ግብፅ በቀጠናውም ሆነ በአህጉሪቱ ላይ ሁለንተናዊ ብልጫን መያዝ ስለምትፈልግ ግድቡ ውሃ እንዳይያዝ ዓለም አቀፍ ተቋማትን በመጠቀም ተፅዕኖ ለማሳደር ስትሞክር ትታያለች፡፡ ይህም ድርጊቷ የሃገራችንን ውሳኔ የሚቀለብስ ባይሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ በሃገራቱ መካከል ፍጥጫ እየተካረረ እንዲመጣ አድርጓል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኃላፊነቱን ወስዶ የኢትዮጵያ ፣ የሱዳንና የግብፅ መሪዎችን በመጋበዝ ዓርብ ምሽት ሰኔ 19 ቀን 2012 ዓም ውይይት ማድረጋቸው በዚህ መነሻነት ነው 0629 ### Response:
### Text: ኢዴፓ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በላከው ደብዳቤ አቶ ልደቱ አያሌው የአስም እና የልብ ህመም እንዳለባቸው በመግለፅ ፍፁም ለጤናቸው አስጊ በሆነ ሁኔታ በቢሾፍቱ እስር ቤት ውስጥ መታሰራቸውን አሳውቋል።ኢዴፓ የአቶ ልደቱ መርማሪን ጨምሮ አምስት 5 ፖሊሶች በእስር ቤቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አቶ ልደቱ እራሳቸው አረጋግጠውልኛል ብሏል።ይህ ሁኔታ ከአቶ ልደቱ የጤና ሁኔታ አንፃር ለኮቪድ19 ይበልጥ ተጋላጭ የሚያደርጋቸው ቢሆንም ምንም አይነት ጥንቃቄ በማይደረግበት እስር ቤት ውስጥ አሁንም እንዲታሰሩ በመደረጉ ህይወታቸው አደጋ ላይ ወድቋል ሲል አስታውቋል።ፓርቲው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ከሰላማዊ የትግል መስመር ውጭ ለአንድም ቀን ተንቀሳቅሶ እንደማያውቅና በአመፅና በነውጥ ዘላቂ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ይገነባል ብሎ እንደማያምን በደብዳቤው ገልጿል።ነገር ግን መንግስት በህግ ማስከበር ስም ከሁከትና ብጥብጥ ጋር ግንኙነት የሌለውን የተለየ ሃሳብ በማራመዱ የፓርቲውን የብሄራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ልደቱን በግፍ አስሮታል ብሏል።ኢዴፓ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የፃፈውን ደብዳቤ መሉ ሃሳብ ከላይ ባሉት ምስሎች ማንበብ ትችላላችሁ። ### Response:
### Text: 5 አስደሳች ዜና በዓለማችን ላይ እጅግ ታዋቂ የሆነው ቢግ 5 የግንባታ ንግድ ትርዒት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው። ኤግዚቢሽኑ ከግንቦት 10 እስከ 12 ቀን 2015 ዓም በአዲስ አበባ የሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል። በከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ዕውቅና እና ድጋፍ ያለው ብሎም ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ከ100 በላይ የዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ ስመጥር የዘርፉ ባለሙያዎች እና ግብዓት አቅራቢዎች የሚሳተፉበት ይህ ታላቅ ዐውደ ርዕይ ሊያመልጥዎት አይገባም ምን ይሄ ብቻ ቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ አውደ ርዕይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ተከታታይ የሙያ ዕድገት ፕሮግራምን በማቅረቡ ኩራት ይሰማዋል። ከ20 በላይ የግንባታው ኢንደስትሪ ላይ ያተኮሩ ሙያዊ ንግግሮች በሚደረጉበት እና ዓለም አቀፋዊ የሙያ የምስክር ወረቀቶች0 በሚሰጡበት ኢግዚቢሽን ላይ የዘርፉ ባለሙያዎች በፕሮጀክት ማኔጅመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ሕንጻ ንድፍ እና ዲዛይን፣ ምሕንድስና እና መሰል ሙያዎች ላይ የ ነጥባቸውን ማሳደግ የሚችሉበት ትልቅ ዕድል ተመቻችቷል። በዘርፉ ያልዎትን ዕውቀት ለማሳደግ እና በዘርፉ ካሉ ባለሙያዎች ጋር ትውውቅዎን ለማስፋት ይህ ወርቃማ ዕድል አያምልጥዎ የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል መስፈንጠሪያውን ይከተሉ 5 ### Response:
### Text: ለወገን ደራሽ ወገን ነው ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ለጋዜጠኛ ብሩክ እንዳለ የህክምና ወጪ 30ሺ ብር ሰጠለ4 ዓመታት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በመዝናኛ ክፍል አገልግሎል፡፡ በዚህም በርካታ የሃገራችን ምሁራንና ታዋቂ ግለሰቦችንና አርቲስቶችን ቃለምልልስ በማድረግ ታዋቂነትን አትርፏል፡፡በቅርቡ ግንቦት 2009 ዓም ላይ ተወዳጁን ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ቴዲ አፍሮ ለኢቢሲ ቃለምልልስ አድርጎ ሳይተላለፍ በመቅረቱ የተነሳ በገዛ ፍቃዱ ስራውን መልቀቁ የሚታወስ ነው፡፡ጋዜጤኛ ብሩክ እንዳለ ላለፋት 9ወራት ባጋጠመው የዲስክ መንሸራተት ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች ሲታከም የቆየ ቢሆንም የዲስክ መንሸራተቱ ነርቩን የተጫነው በመሆኑ ህክምናው ሃገር ውስጥ የማይቻል በመሆኑ ለህክምና የሚሆነው ገንዘብ እዚሁ ሃገር ውስጥ በመጨረሱ የወገንን እጅ ማየቱ ግድ ሆነበት ስለዚህ ለወገን ደራሽ ወገን ነውና በሃገር ውስጥና በባህር ማዶ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን የጋዜጤኛውን ህይወት ለመታደግና ውጭ ሄዶ እንዲታከም ድጋፍ እንድታደርጉለት በእግዚአብሔር ስም እንማፀናለንየጋዜጠኛ ብሩክ እንደለ የባንክ አካውንት↪️የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000043925648 በስልክ ማግኘት የምትፈልጉበ↪️09 10 88 09 50 መደወል ትችላላችሁ ### Response:
### Text: ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን ሶስት ባልደረቦቹ ትግራይ ክልል ውስጥ መገደላቸውን ሪፖርት አደረገ። የባልደረቦቹን ሞት ማረጋገጫ ከሰማ በኃላ ሃዘን ላይ መሆኑ ገልጿል።የደንገተኛ ጊዜ አስተባባሪ ማሪያ ኸርናዴዝ ረዳት አስተባባሪ ዮሀንስ ሃለፎም ረዳ፣ ሹፌር ቴድሮስ ገብረማርያም ገሚካኤል ትላንት ከሰዓት ጉዞ እያደረጉ እያለ ግንኙነታቸው ተቋርጦ ነበር።ዛሬ ጥዋት ባዶ መኪናቸው ተገኝቷል ከመኪናው በትንሽ ሜትር ርቀት ደግሞ ህይወታቸው አልፎ አስክሬናቸው ተገኝቷል። ጥቃቱን ያወገዘ ሲሆን ጥቃቱ በማን እንደተፈፀመ ግን በሪፖርቱ ላይ ያለው ነገር የለም።ማሪያ ፣ ዮሃንስ እና ቴድሮስ ትግራይ ክልል ውስጥ ለሰዎች ድጋፍ በመስጠት ላይ ነበሩ ለዚህ ስራ ክፍያቸው ይህ ነፍሳቸውን መንጠቅ መሆኑ ሊታሰብ የማይችል ነው ብሏል ።ስለሰራተኞቹ ማሪያ ኸርናዴዝ ከማድሪድ ስፔን ሀገር የመጣች የ35 ዓመት ሴት ስትሆን ከ ጋር በመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ፣ በየመን ፣ ሜክሲኮ፣ በናይጄሪያ ሰርታለች። ዮሃንስ ሃለፎም ረዳ ዕድሜው 31 ሲሆን ከኢትዮጵያ ነው ድርጅቱን የተቀላቀለው የካቲት ወር ላይ ነበር። ቴድሮስ ገብረማርያም ገብረሚካኤል ዕድሜው 31 ሲሆን ከኢትዮጵያ ነው ከግንቦት ወር ጀምሮ የድርጅቱ ሹፌር ነበር። ### Response:
### Text: ኮምቦልቻና ደሴ ኤሌክትሪክ ዛሬ ማግኘት እንዲችሉ በርብርብ እንሰራለን የኢኤኃ የጥገና ባለሙያዎች በሸዋ ሮቢት ኮምቦልቻ መስመር የተጎዳውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት የሚጠግነው የጥገና ቡድን አባላት የኮምቦልቻና ደሴ ከተሞች ዛሬ ኤሌክትሪክ ማግኘት እንዲችሉ በርብርብ እንሰራለን ብለዋል።የጥገና ቡድኑ ትናንት ምሽት የጥገና ሂደቱን፣ በየከተሞቹ የደረሰውን ጉዳትና የህብረተሰቡን ስሜት የተመለከተ አጠቃላይ ግምገማ ካደረገ በኋላ ዛሬ የኮምቦልቻና ደሴ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ የቻለውን ያህል ጥረት እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል፡፡የጥገና ቡድኑ ትናንት ከካራቆሬ ከሜሴ ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ አድርጓል።የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ የቴክኒክ ቡድኑ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከሸዋሮቢት እስከ ከሚሴ ያለውን መስመር ጠግኖ ለአገልግሎት ለማብቃት ያደረገውን ጥረት አድንቀዋል፡፡አቶ ሀብታሙ ከባድ መስዋዕትነት በመክፈል የህዝቡን ችግር ለመፍታት ያደረጋችሁትን ርብርብ ተቋማችንና ህብረተሰቡ ሁሌም ሲያስታውሰው ይኖራል ብለዋል፡፡ ምንጭ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ### Response:
### Text: ከዘር ማጥፋት እልቂት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ 2 ሺህ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ በመስጠት የተጠረጠረው ግለሰብ ተያዘ።እአአ በ1994 በሩዋንዳ በነበረው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ ከጥቃት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ ሁለት ሺሕ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፏል በሚል የተጠረጠረው ግለሰብ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መያዙን የሩዋንዳውን የዘር ማጥፋት የሚከታተለው፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጦር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።የቀድሞው የፖሊስ አባል፣ ፉልጌንሴ ካይሼማ፣ ፍቤቱ በይፋ ክሥ ከመሠረተበት ካለፉት 22 ዓመታት ጀምሮ በሽሽት ላይ ነበር።በተመድ የተቋቋመው ችሎት፣ ሥራውን ለሩዋንዳ በማስረከቡ፣ ካይሼማ ለሩዋንዳ ተላልፎ እንደሚሰጥ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል።የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ካይሼማ ያለበትን ለሚጠቁም፣ የአምስት ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።ሌላው የዘር ማጥፋቱ ጠንሳሽ የተባለው ፌሊሲን ካቡጋ፣ ከ26 ዓመታት ሽሽት በኋላ ከሦስት ዓመት በፊት በፈረንሳይ ውስጥ መያዙ ይታወቃል።እአአ በ1994 በሩዋንዳ፣ በአክራሪ ሁቱዎች በተፈጸመ የዘር ማጥፋት፣ 800ሺሕ የሚሆኑ ቱትሲዎች መገደላቸው ይታወሳል። ቪኦኤ ሩዋንዳ ### Response:
### Text: ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለሶስት ሰዎች የክብር ዶክትሬት ሰጠዶክተር ሰገነት ቀለሙ፣ ፕሮፌሰር ሃንስ ማትሰን እና ማርክ ጌልፋንድ ናቸው በባህርዳር የኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት የክብር ዶክትሬታቸውን አግኝተዋል፡፡ዶክተር ሰገነት ቀለሙ በልዩ መሪነትና ተመራማሪነት ዘርፍ የተመረጡ ሲሆን ናይሮቢ የሚገኘው ዓለማቀፉ የነፍሳት ግብረ አካል እና ሥነምኅዳር የመጀመሪያዋ ሴት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ከ25 ዓመታት በላይ በሰሜን አሜሪካና በላቲን አሜሪካ በርካታ ምርምሮችን ሠርተዋል፡፡ በዓለማቀፍ ደረጃ ዕፅዋትን በሚያጠፉ በሽታዎች ላይ ሳይንሳዊ ምርምር በማድረግ ቀዳሚ ሴት ተመራማሪ በመሆናቸውም በርካታ ሽልማቶችን አሸንፈዋል፡፡ ስዊድናዊው ፕሮፌሰር ሃንስማትሰን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና በምሥራቅ አፍሪካ የመሬት አስተዳደር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡አሜሪካዊው ማርክ ጌልፋንድ በበኩላቸው በኢትዮጵያና በሌሎች ታዳጊ ሀገራት የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምሕንድስና እና የሒሳብ ትምህርቶች ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው ድጋፍ ያደረጉ ምሁር ናቸው፡፡ በባሕር ዳር፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባና በሌሎችም 12 ዩኒቨርሲቲዎችና አካባቢዎች የስቲም ማዕከላት እንዲከፈቱ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ### Response:
### Text: ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ እስር ቤቶች ይታወቁ የነበረው በአካል ላይ ጥቃት በማድረስ፣ አሰቃቂ የማሰቃየት ተግባር በመፈጸም ጭምር ነበረ ዶክተር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ኢትዮጵያ ውስጥ ከአንድ ዓመት በፊት አዲስ የፖለቲከ ምዕራፍ ተከፍቷል። የተፈጠረውን መልካም ዕድል በመጠቀም በአገር ውስጥ የዴሞክራሲ ተቋማትን በአዲስ መልክ ለማደራጀትና ለማጠናከር ለሚደረገው ስራ የበኩሌን አስተዋጽኦ ለማበርከት የቀረበልኝን ጥሪ በበጎ መልክ ለመቀበል ወስኛለሁ። አሁን የደረስንበት ምዕራፍ በብዙ ትግል የተገኘ ነው። ብዙ ሰዎች ህይወታቸውን፣ ደህንነታቸውን፣ አካላቸውን፣ ንብረታቸውን ያጡበት ሂደት ነው። በመሆኑም በእዚህ ወቅት ያለን ሰዎች ደግሞ ይህንን ጊዜ በኃላፊነት ስሜት ተረክበን የምንችለውን አስተዋጽኦ ማድረግ አለብን። ወደእዚህ ተመልሼ በእዚህ ስራ ላይ ለመሰማራት የወሰንኩትም በእዚሁ ስሜት ነው። የዴሞክራሲ ተቋማት ተብለው የሚታሰቡት እንደምርጫ ቦርድ፣ የሰብአዊ መብት ኮሚሽንና የመሳሰሉት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ በመንግስት ስር ሆነው የመንግስት መጠቀሚያ መሳሪያ ወይንም የፕሮፖጋንዳ መሳሪያ እየሆኑ ሲያገለግሉ እንደነበሩ ይታወቃል። 11032 ምንጭ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ### Response:
### Text: በወላይታ ዞን በተከሰተው አለመረጋጋት በትንሹ ከ10 በላይ ሰዎች ሞተዋል። የቲክቫህ ኢትዮጵያ ኦቶና ሆስፒታል አባላት እንደገለፁት ደግሞ እስካሁን ባሉበት ሆስፒታል ብቻ ከ80 በላይ ሰዎች ተጎድተው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።ዛሬም በወላይታ ሶዶ እንዲሁም በሌሎችም ከተሞች የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት እንደተዘጋ ነው። ከበርካታ የወላይታ ዞን የቲክቫህ አባላት ጋር መገናኘት አልቻልንም።የወላይታ ሶዶ፣ አረካ፣ ቦዲቲ ቲክቫህ አባላት በስልክ ደውለው ያለውን ሁኔታ ያሳወቁ ሲሆን አሁንም የትንራስፖርት ፣ የንግድ እንቅስቃሴ የለም አንዳንድ ቦታ ውስጥ ለውስጥ አልፎ አልፎ ሱቆች ክፍት ናቸው ፣ ባንክ ቤቶች ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ፣ የሰዎች እንቅስቃሴ ግን ይታያል ካለፈው ቀን የተሻለ መረጋጋት አለ ብለዋል።የየከተማው ነዋሪ በተፈጠረው ክስተት ክፉኛ ልቡ ተሰብሯል በዚህ ምክንያት እንደዋዛ ህይወታቸው በተቀጠፈውና በተጎዱት ወጣቶች ምክንያትም መሪር ሀዘን ላይ ይገኛል ብለዋል።ከሶስቱም ከተሞች ወሶዶ፣አረካ፣ ቦዲቲ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ማረጋገጥ እንደቻልነው አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፀጥታ አስከባሪዎች መከላከያ ሰራዊትና የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። ### Response:
### Text: ጀርመን በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ ከቀረበላት አገራዊ የምክክር ሂደቱን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አሳውቃለች።ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው ኢትዮጵያ በሚገኙት አምባሳደሯ ነው።በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አወር ለኢዜአ በሰጡት ቃል የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር የአገሪቷን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት ጥሩ የመፍትሔ አማራጭ ነው ብለዋል።በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ጥያቄ ከቀረበላት የፌዴራል ስርዓት የምትከተለው ጀርመን በሚቻለው አቅም ሁሉ አገራዊ የምክክር ሂደቱን ለመደገፍ ዝግጁ ናት ሲሉ አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉትን ውስጣዊ ችግሮች በመፍታት መፍትሔ ለማበጀት በጋራ መምከር ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሩ ኢትዮጵያ የምታካሂደው አገራዊ ምክክር ሁሉንም አሳታፊና አካታች ሆኖ ሲካሄድ ልዩነቶችን በመነጋገርና በመፍታት በቀላሉ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ያስችላል ብለዋል።በአገራዊ ምክክሩ ለጋራ ችግሮች መንስኤ የሆኑ ጉዳዮች ምንድን ናቸው የሚለውን ቁልፍ ጥያቄ በማንሳትና በግልጽ መነጋገር የጋራ መፍትሔ ማምጣት ይቻላል ሲሉም አክለዋል።አምባሳደር ስቴፈን የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የምክክር ሂደቱን ሁሉን አቀፍ ለማድረግ እየሰራ መሆኑ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ### Response:
### Text: በኔፓል የመንገደኞችአውሮፕላን ተከስክሶ በርካቶች ህይወታቸው አለፈ።72 ሰዎች አሳፍሮ የነበረ የመንገደኞች አይሮፕላን በማዕከላዊ ኔፓል የአውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ ተከስክሶ እስካሁን ባለው 40 አስከሬኖች መገኘታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ማሳወቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።አውሮፕላኑ ንብረትነቱ የ የቲ አየር መንገድ ሲሆን ከካትማንዱ ተነስቶ ወደ ቱሪስት መዳረሻ ከተማ ወደሆነችው ፖክሃራ ያቀና ነበር። አውሮፕላኑ ፖክሃራ ኤርፖርት አቅራቢያ ነው የተከሰከሰው።በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨ አንድ ቪዲዮ አውሮፕላኑ በአንድ በርካታ ሰዎች በሚኖሩበት መንደር አካባቢ ዝቅ ብሎ ሲበር አሳይቷል።በአውሮፕላኑ ውስጥ ቢያንስ 15 የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 68 ተሳፋሪዎች እና አራት የበረራ አባላት ነበሩ ተብሏል።ከተሳፋሪዎቹ ውስጥ 53ቱ የኔፓል ዜጎች መሆናቸው ተነግሯል። በተጨማሪ አምስት ህንዳውያን፣ አራት ሩሲያውያን ሁለት ኮሪያውያን አንድ የአየርላንድ ፣ አንድ የአውስትራሊያ፣ አንድ የአርጀንቲና እና አንድ የፈረንሣይ ዜጎች በአውሮፕላኑ ውስጥ እንደነበሩም ተጠቁሟል።ከአውሮፕላን መከስከሱ በኃላ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ፑሽፓ ካማል ዳሃል ካቢኔያቸውን ለአስቸኳይ ስብሰባ መጥራታቸው ታውቋል። ### Response:
### Text: ኦፌኮ️መንግስት በየአካባቢው እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን ህብረተሰቡን በማሳተፈና0 ህግን መሰረት በማድረግ0 ሊፈታው እንደሚገባ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ0 ሊቀመንበር ዶር መረራ ጉዲና ገለፁ።የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ወቅታዊ የሀገሪቱን ሁኔታ በተመለከተ አባላቶቹና ደጋፊዎቹ0 የተሳተፉበት ሲምፖዚየም በአዲስ አበባ አካሂዷል።ሊቀመንበሩ ዶክተር መረራ ጉዲና ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ወጣቶች ትውልድ በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች እየተስተዋሉ ባሉ ችግሮችና0 የሀገር አንድነትን ሊያፈርሱ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ መሆን የለባቸውም።ዶክተር መረራ የሀገር አንድነትን የበለጠ ለማጠናከር በአፋጣኝ ብሄራዊ መግባባትን ሊፈጥር የሚችል መድረክ እንዲመቻች አሰስበዋል።እንዲሁም አሁን በሀገሪቱ እየተስተዋለ ያለውን ለውጥም በፍጥነት ወደ ሁሉም አካባቢዎች ማዳረስ እንደሚገባ ነው ሊቀመንበሩ ዶክተር መረራ ጉዲና የተናገሩት። ወጣቱ ሁሌም ለለውጥ ተሰላፊ መሆኑን የገለፁት ሊቀመንበሩ ነገ የተሻለ እንዲሆን የወጣቱ ሀላፊነት እንደሆነ ተናግረዋል።ከዚህ ባለፈ ወጣቱ የአንድ ድርጅት አገልጋይ0 ሳይሆን የህዝብ ውክልና በመያዝ ትግሉን በአንድነት መቀጠል አለበት ብለዋል።© ### Response:
### Text: በሃገሪቱ የኮሌራ ወረርሽኝ በተከሰተባቸው ክልሎች ከፍተኛ ተጋላጭነት ያላቸውን የህረተሰብ ክፍሎች በመለየት በቀጣይ ሳምንታት የኮሌራ ክትባት እንደሚሰጥ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዊት አስታወቀ፡፡ኢንስቲትዊቱ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ በአሁኑ ወቅት በሃገሪቱ 770 ሺህ ክትባቶች መኖራቸውን ገልጿል፡፡እስአሁን በሃገሪቱ 5 ክልሎች በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽ ምክንያት 15 ሰዎች ሕወታቸው አልፏል፡፡የኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲትዊት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር በየነ ሞገስ እንደገለፁት ለወረርሽኙ ከፍተኛ ተጋላጭ የሆኑ አካላትን በዳሰሳ ጥናት በመለየት በቀጣይ ሳምንታት ክትባት ይሰጣል፡፡በቀጣይ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ የሚከታተል ግብረ ሃይል ከክልል ርእሰ መስተዳድሮችና ከንቲባዎች ጀምሮ በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች የማቋቋም ስራ እንደሚሰራ ዶክተር በየነ ሞገስ ግልፀዋል፡፡በሽታን ቶሎ ለመቆጣጠር መድኃኒቶችና የህክምና ግብአቶች በሁሉም ክልሎች ወደሚገኙ የኢትዮያ የመድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ መጋዘኖች እንዲከማች ተደርጓ፡፡ በተጨማሪም ለዚሁ በሽታ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የሰው ኃይልም እየሰለጠነ ይገኛል፡፡ ### Response:
### Text: በድሬዳዋ ለደረሰው ግጭት የተሳሳቱ መረጃዎች ዋነኛ ምክንያት ናቸው ተባለ በቅርቡ በድሬዳዋ ተከስቶ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ላደረሰው ግጭት መነሻ በዋነኛነት ተሳሳቱ ምረጃዎች ወደ ግለሰቦች መድረሳቸው መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አስታወቀ። ምክር ቤቱ 43ኛ መደበኛ ጉባዔውን ያካሔደ ሲሆን በጉባዔውም ላይ ከተማዋን ሰላም በሚመለከት ሰፊ ውይይት ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል።በጉባዔው ላይ በተለያዩ ጊዜያት በማኅበራዊ ድህረ ገጾችም ሆነ በተወሰኑ ቡድኖች የሚነዙ የተሳሳቱ መረጃዎች ሳቢያ የአስተዳደሩ ነዋሪ ሰላሙን እንዲያጣ አይነተኛ ሚና መጫወቱን የተናገሩት የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፈጡም ሙስጠፋ አመራሩ ይሄንን እታች ድረስ ወርዶ በማጣራትና ትክክለኛ መረጃን ለኅብረተሰቡ በመስጠት ህዝቡን የማረጋጋት ስራ እንዲሰሩ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡በድሬዳዋ በተከሰቱት ግጭቶች እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ110 ሰዎች መኖራቸው በሪፖርቱ የተገለጸ ሲሆን በማስረጃ በተደገፈ ምርመራ 51 ተጠርጣሪዎች ተለይተው በልዩ ሁኔታ እየተመረመሩ እንደሚገኙና በቀጣይም የምርመራው ሂደቱን ውጤት በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶና የእስልምና ኃይማኖቶች ሰባኪያን፣ መምህራንና0ምሁራን ግጭቶችን በትብብር ለመፍታት የሚያስችል0 ውይይት አደረጉ። ውይይቶቹ መሬት ላይ ወርደው አንዱ እምነት ለአንዱ ደጀን በመሆን ችግሮችን ለመፍታት እስከ ወረዳ ድረስ ተደራሽ እንደሚሆን አስታውቀዋል።የኃይማኖቶች ትብብርና የጋራ መድረክ 0ለሕዝቦች ሰላምና አንድነት በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረኩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የጴጥሮሳዊያን የቤተ ክርስቲያን ክብርና መብት አስጠባቂ ኅብረትና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ የተዘጋጀ ነው።ውይይቱን አስመልክተውም የጴጥሮሳዊያን የቤተ ክርስቲያን ክብርና መብት አስጠባቂ ኅብረት ሰብሳቢ ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑና የሙሰሊሞች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዑስታዝ አቡበከር አህመድ በጋራ 0መግለጫ ሰጥተዋል።በመግለጫቸውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አገሪቷ ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ግጭቶች እየተባባሱና ኃይማኖታዊ መልክ እየያዙ በመምጣታቸው፣ ከየትኛውም ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ውጭ አማኙ ማኅበረሰብ ውስጥ የማይጠበቁ ጥፋቶች መከሰታቸውን ተከትሎ ግጭቶችን በጋራ ለመፍታት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ወደወለጋ፣ወደኢሉባቦር ኦፌኮ ድጋፍ የለውምመሪዎቹም ጃዋርን ጨምሮ ወደዛ ላይሄዱ ይችላሉ የሚሉ ስጋቶች አሉ ተብለው ኬላ በተሰኘ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ የተጠየቁት አቶ ጃዋር መሃመድ የሰጡት ምላሽምንሄደው ድጋፍ ያለን ቦታ ብቻ አይደለም። ምንሄደው ድጋፍ ለማጠናከር ነው። እኛ በሁሉም ወረዳ ላይ ህዝባችንን ማነጋገር እንፈልጋለን። ግን ሰዉ ይረሳል እንጂ በጣም ነገሮች በተጧጧፉበት እና መንግስት በጣም በተዳከመበት፣ በሌለበት ወቅት እኔና በቀለ እስከ አሶሳ ድረስ ሰው ማንም በማይሄድበት፣ የመንግስት ባለስልጣን ሀገር ጥሎ በጠፋበት ወቅትም ስንሄድ ነበር። አሁንም ወደምዕራብ እንሄዳለን። ምዕራብና ደቡብ እንደሚታወቀው ካለው ግጭት ጋር ተያይዞ ህጋዊ ያልሆነ ኮማንድ ፖስት አለ። ያ ኮማንድ ፖስት እንዲነሳ በህጉ እናደርጋለን። እኛ ብቻ አይደለንም ጥምረት ፈጥረን እየሰራን ነው ያለነው ከኦነግ ጋር፣ ከኦብፓ ጋር አብረን ወደፊት የምናደርገው እንቅስቃሴ ይኖራል። የማንሄድበት ዞን አይኖርም። ኦሮሚያ ውስጥ ብቻ አይደለም ወደ ተለያዩ ክልሎች የመሄድ እቅድ አለን። ደፍሮ ለሚለውም የተያያዝነው ትግል እንጂ ዳንስ አይደለም። ስለዚህ ሁሉም ቦታ እንሄዳለን። ስንሄድ ደግሞ በተጨባጭ ይታያል። ### Response:
### Text: በመተከል ዞን ሽፍቶች ተቆጣጥረውት የነበረ ቦታ እንደነበር እና ቡድኑ ላይ በተወሰደ እርምጃ ቦታዎቹን ማስለቀቅ እንደተቻለ ተሰማ።በዞኑ በሽፍቶች ቁጥጥር ስር የነበሩት ቦታዎች የትኞቹ እንደነበሩ ግን በግልፅ አልተብራራም።ይህ መረጃ ይፋ የሆነው ዛሬ በዶር ዐቢይ ተቋቁሞ የመተከል ዞንን የፀጥታ እና የሕግ ማስከበር ሥራ የተረከበው ግብረኃይል የሁለት ሳምንት ስራውን መገምገም በጀመረበት ወቅት ነው።ግብረኃይሉ በመተከል ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ የወረዳ እና ቀበሌ የሥራ ኃላፊዎች እንዲነሱ፣ ወንጀል ያለባቸውም በሕግ እንዲጠየቁ እየተደረገ ነው ብሏል።አዲስ የሚመረጡ የሥራ ኃላፊዎች ሕዝብ መምራት የሚችሉት በሕዝብ ፊት ቀርበው ተቀባይነት ሲያገኙ ብቻ ነው ተብሏል።ትምህርት ቤቶችን የመማር ማስተማር ማስጀመር፣ የጤና ተቋማትን ሙሉ በሙሉ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እና ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው መመለስ የቀጣዮቹ ሁለት 2 ሣምንታት ሥራ እንደሚሆንም ተግልጿል።በጠሚሩ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የፀጥታ እና የሕግ ማስከበር ሥራውን በ1 ወር ጊዜ አጠናቅቆ ለአስተዳደሩ ለማስረከብ ዕቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በዚህ ጉዳይ ያሰራጨው መረጃ ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: ብሊንከን ከጠሚ ዶር ዐቢይ ጋር በስልክ መነጋገታቸውን ገለፁ።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አሕመድ ጋር በስልክ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን ጁላይ 6 ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።አቶ ብሊንከን በግጭት ላይ ባሉ ሁሉም ወገኖች ዘንድ አስቸኳይና ዘላቂ ተኩስ የማቆሙን አስፈላጊነት አንስተው ማሳሰባቸውንና የተከዜ ድልድይ መፍረስንም አስመልክቶ ማውገዛቸውን ጠቅሰዋል።0በተጨማሪ የኤርትራ ጦርና የአማራ ሚሊሺያ ከትግራይ ሙሉ በሙሉ ለቅቀው እንዲወጡ ሰብዓዊ እርዳታን ለሚሹ ረድኤት ለመድረስ ሙሉ ተደራሽነት እንዲኖር በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂ በሆኑት ላይ ግልፅ የሆነ ሂደት እንዲዘረጋ የኢትዮጵያን የውስጥ ወሰኖችንም ሆነ ዓለም አቀፍ ድንበር በኃይል ወይም ሕገ መንግሥቱን በመጣስ መለወጥ እንደሌለበት ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፍኖ ያለውን የጎሳና ፖለቲካ ክፍፍሎች ሁሉን አቀፍ በሆነ ዘላቂ መፍትሔ የሚያስገኝ ፖለቲካዊ ውይይት እንዲካሔድ በተባበሩት መንግሥታት ፀጥታ ምክር ቤት የተመከረበትን ግብር ላይ እንሲያውሉ ያበረታቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።የስልክ ንግግሩን አስመልክቶ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ እስካሁን የተሰጠ መግለጫ የለም።ምንጭ ### Response:
### Text: የበጎ ሰው ሽልማት ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደው የ2011ዓም የበጎ ሰው ሽልማት ስነስርዓት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል እየተካሄደ ነው። በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅን ዘውዴና የጤና ሚኒስትር ዶክተር አሚር አማንን ጨምሮ የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።ለዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት በዘጠኝ ዘርፎች 291 ዕጩዎች የተጠቆሙ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም 27 ሰዎች የመጨረሻ ዕጩ ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገልጿል። በዛሬው ዕለትም በዘጠኝ ዘርፎች ለመጨረሻ ዕጩ ከቀረቡት ሶስት ሶስት ዕጩዎች ውስጥ የመጨረሻ አሸናፊዎች ይፋ እየተደረገ ይገኛል። በዚህ መሰረትም እስካሁን በመምህርነት ዘርፍ ወይዘሮ ህይወት ወልደመስቀል፣በቅርስና ባህል ጥበቃ ዘርፍ አቶ አብደልፈታህ አብደላበሳይንስ ዘርፍ ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሰውበንግድ ስራ ፈጠራ ዘርፍ አቶ ነጋ ቦንገርበመንግስታዊ የስራ ተቋማት ሃላፊነት ዘርፍ አቶ ግርማ ወንዳፍራሽበበጎ አድራጎት ዘርፍ ዶክተር አብዱላዚዝ ኢብራሂም አሸናፊ መሆናቸው ይፋተደርጓል።የበጎ ሰው ሽልማት ዋና አላማ በኢትዮጵያ በጎ የሰሩ እና ለሌሎች አራያ ሊሆኑ የሚችሉ ሰዎችን ማበረታታት እና እውቅና መስጠት ነው። ### Response:
### Text: ወቅታዊ መረጃዎች 1 ተመድ ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረግ ትግራይ ዉስጥ በተለያዩ አካባቢዎች የሚታየዉ ውጊያ ነገሩን አክብዶታል ሲል አስታውቋል።2 ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ዛሬ ለሮይተርስ በላኩት መልዕክት በመቐለ የኤርትራ ወታደሮች እየፈፀሙት ባለው ዝርፊያ ምክንያት ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጎ ነበር ብለዋል።3 ጦርነት ሸሽተው ወደ ሱዳን የተሰደዱ ኢትዮጵያዊያንን ለመመለስ ከሀገሪቱ መንግስት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።4 የህወሓት አመራሮችን ወርቅአምባ አካባቢ በ6 በረት ለበስ ዙሪያውን ኮማንዶ እየጠበቃቸው እንደሆነ መከላከያ ሰራዊት አረጋግጧል። በአሁን ሰዓት በዚህ አካባቢ ዶር ደብረፅዮን ፣ አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ አቦይ ስብሃት ፣ አቦይ ፀሃዬ ፣ ሌሎችም ሀገር መከላከያ ሰራዊት የማያውቃቸው አካላት አሉ።5 መከላከያ ሰራዊት መቐለ ከተማን የማረጋጋት ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።0በሌላ በኩል በመቐለ የህወሓት አመራሮች ቤት በተደረገ ብርበራ ለጥፋት አላማ የሚውሉ የጦር መሳሪያዎች መገኘቱ ተገልጿል።የአቶ ጌታቸው ረዳ፣ የአቶ ስዩም መስፍን፣ የአቶ አባይ ፀሃዬ ፣ መኖሪያ ቤት ህጉ በሚፈቅደው መሰረት ብርበራ ተደርጓል ብሏል ሰራዊቱ።በዝርዝር ይመልከቱ 12043 ### Response:
### Text: የነዳጅ ምርት ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እየገባ ነው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርከፍተኛ መጠን ያለው የነዳጅ ምርት ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እየገባ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ እሸቴ አስፋው ለፋና ቴሌቪዥን አሳውቀዋል።አቶ እሸቴ ቀድሞ ይገባ ከነበረው 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የነዳጅ ምርት በአሁኑ ሰዓት 3 ሚሊየን ሊትር በቀን ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ ይገኛል ብለዋል ለቴሌቪዥን ጣቢያው።በተጨማሪ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ዲፖዎች በቂ ክምችት ያላቸው በመሆኑ በአቅርቦት ላይ ምንም ስጋት እንደሌለ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚታዩት ሰልፎች መኖራቸውን የተናገሩ ሲሆን ይህ የተፈጠረው አፋር አካባቢ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምከንያት መሆኑን ጠቅሰው አሁን ላይ ችግሩ በመቀረፉ ነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪዎች በብዛት ወደ ሀገር እየገቡ ናቸው ብለዋል።ይሁን እንጂ አንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች እጥረት እንዲፈጠር የሚያደረግ ተግባር እያከናወኑ መሆኑን ሚኒስትሩ ባደረገው ቁጥጥር በማረጋገጡ ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠቡ አሳስበዋል። አያይዘውም ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪም ይሁን የአቅርቦት ችግር ባለመኖሩ ሁሉም ተረጋግቶ ስራውን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። ### Response:
### Text: ቅዱስ ፓትርያርኩ ለህክምና ከሄዱበት አሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ሲገቡ አቀባበል ይደረግላቸዋል።ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሕክምናቸውን አጠናቀው ነገ ጷጉሜን 1 ቀን 2014 ዓም ወደ ኢትዮጵያና ወቅዱስ መንበራቸው ይመለሳሉ።ቅዱስ ፓትራርኩ ወደ ኢትዮጵያና ወቅዱስ መንበራቸው መመለሳቸውን ተከትሎ ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ጀምሮ አቀባበል እንደሚደረግላቸው ታውቋል።የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በጤና ወደ መንበራቸው መመለሳቸው የቤተ ክርስቲያን ደስታ ነው ያለ ሲሆን በዚሁ መጠን ይፋዊ አቀበበል ዝግጅት ተደርጓል ሲል አሳውቋል።የቅዱስነታቸውን ወደ አገር ቤት መመለስን አስመልክቶ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የአቀባበል ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲሰራ የቆየ ሲሆን አሁን ላይ የአቀባበል ቅድመ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ለማወቅ ተችሏል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስነታቸው ወደ ሀገራቸውና ወቅዱስ መንበራቸው መመለስን ተከትሎ ነገ ለሚደረገው አቀባበል ሁሉም ሚዲያዎች ጥዋት 1 ሰዓት ላይ ቦሌ ኤርፖርት እንዲገኙላት ጥሪ አቅርባለች። ### Response:
### Text: ነገ የሚዘጉ መንገዶች 1442ኛው ኢድአል አድሐ አረፋ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጀት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።በአዲስ አበባ ስታዲዮም በሚኖረው የጠዋት ስግደት ምክንያት ከማለዳው 11 ሰዓት ጀምሮ የስግደቱ ሥነሥርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የተወሰኑ መንገዶች ለጊዜዉ ለትራፊክ ዝግ ይሆናሉ።በዚህም መሰረት ከመገናኛ እና ከ22 ለሚመጡ ኡራኤል አደባባይ ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ ከሪቼ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ 4ኛ ክፍለ ጦር ከጦር ኃይሎች ወደ ስታዲዮም ሜክሲኮ አደባባይ ከመርካቶ በበርበሬ በረንዳ በተክለ ሐይማኖት ወደ ስታዲዩም ለሚመጡ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስከሞላ ማሩ በጌጃ ሰፈር ወደ ስታዲዩም ለሚመጡ ጎማ ቁጠባ ከፒያሳ ወደ ስታዲዮም ለሚመጡ ቴዎድሮስ አደባባይ ከ4ኪሎ በፊት በር ወደ መስቀል አደባባይ ጊቢ ገብርኤል የሚወስዱ እና በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ መጋቢ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።ፖሊስ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ትብብር እንዲያደርጉ የጠየቀ ሲሆን በተጠቀሱት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሸከርካሪን አቁሞ መሔድ የተከለከለ መሆኑን አሳስቧል። ### Response:
### Text: ጀርመን ከ መጋዘን ህወሓት የፈፀመውን በኃይል የነዳጅ ክምችት የመውሰድ ድርጊት አፀያፊ ስትል አወገዘች።የጀርመን መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ለ5 ወራት የዘለቀው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱና ጦርነቱ እንደገና መጀመሩ በእጅጉ እንዳሳዘነው ገልጿል።በግጭቱ ውስጥ ያሉ ሁሉም አካላት አሁኑኑ መሳሪያቸውን አስቀምጠው ወደ ተኩስ አቁም በፍጥነት መመለስ አለባቸው ብሏል። ግጭቱ ሊፈታ የሚችለው በድርድር ጠረጴዛ ዙሪያ ብቻ ነው ያለው የጀርመን መንግስት የአፍሪካ ህብረት የማሸማገል ጥረቶችን አሁንም መደገፉን እንደሚቀጥል እና ይህም ስራ አሁን መጠናከር እንዳለበት ገልጿል።የትግራይ፣ የአማራ እና የአፋር ህዝብ በቂ ስቃይ ደርሶበታል ያለው የጀርመን መንግስት ሴቶች እና ህጻናትን ጨምሮ በጣም ብዙ ንፁሃን ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል ወይም ለከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሰለባ ሆነዋል ብሏል።ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ተገደዋል ሚሊዮኖችም በረሃብ እየተሰቃዩ ነው ሲል የጀመን መንግስት ገልጿል።ከዚህም ዳራ አንፃር ህወሓት አስቸኳይ ህይወት አድን ሰብአዊ እርዳታን ለማከፋፈል የሚውልን ነዳጅ መውሰዱ አስጸያፊ ነው ስትል አውግዛለች። ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና️የወልቂጤ ከተማ እግርኳስ ክለብን በአምበልነት እያገለገለ የነበረው መዝገቡ ወልዴ በድንገተኛ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትናንት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።ታኅሳስ 16 በ1982 ዓም የተወለደው መዝገቡ ወልዴ የእግርኳስ ህይወቱን ከፕሮጀክት አንስቶ ህይወቱ እስከምታልፍ ድረስ በደቡብ ክልል ፕሮጀክት ቀጥሎም ወልቂጤ ከተማ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ክለቡን በአምበልነት ለ11 ዓመታት አገልግሏል። በ2007 ለሲዳማ ቡና የመጫወት እድልም አግኝቷል፡፡ብዙም ሳይቆይ ወደ መጀመሪያ ክለቡ በድጋሚ ተመልሷል። በዚህ ዓመት ለኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን መጫወት ችሎም ነበር።በክለቡ እና በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ በነበረው መልካም ባህርይ አንቱታ ያተረፈው መዝገቡ ከእግርኳሱ በተጨማሪ በትምህርቱ ገፍቶ በ2002 ከመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪ ማግኘት ችሎ ነበር።የመዝገቡ ስርዓተ ቀብር ዛሬ በወልቂጤ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡ ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በተጫዋቹ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገለጿል። የውልቂጤ እግር ኳስ ቡድንም ተጫዋቹ ይለብሰው የነበረውን 2 ቁጥር ማልያም ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት እንዳይለበስ መወሰኑ ታውቋል፡፡ምንጭ፡ሶከር ኢትዮጵያ ### Response:
### Text: የጎዳና ተዳዳሪዎቹን ሕይወት ያጠፋው ግለሰብ ተቀጣ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ የሦስት ሰዎችን ሕይወት በተመሳሳይ አጥፍተዋል የተባሉት ግለሰብ አንድ ሰው ላይ ሙከራ አድርገዋል በአዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ኸለት ልዩ ሥሙ አሜን ሆስፒታል ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ሚሊዮን ዘሪሁን የተባለ የጎዳና ተዳዳሪ በሌላ ጎዳና ተዳዳሪ ላይ በበቀል ስሜት በመነሳሳት በፈፀመው የግድያ ወንጀል ተፈረደበት።ሟች በራሱ ላይ በተጫነበት ከፍተኛ መጠን ያለውን ድንጋይ፣ የራስ ቅል አጥንት መሰባበር እና የአንጎል ወደ ውጪ መውጣት ደርሶበት ሕይወቱ ያለፈ ሲሆን፣ ተከሳሽ በከባድ የሰው ግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብሏል።የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ሲመለከት በቆየው መዝገብ ላይ እንደተረጋገጠው፣ ተከሳሽ ሟች እና ጓደኞቹ ጋር የጉልበት ሥራ በመሥራት የተገኘውን ገንዘብ ሳይከፍሉኝ ቀርተዋል በጋራም በመሆን ድብደባ ፈጽሞብኛል በሚል ምክንያት በቂም በመነሳት ወንጀሉን ፈፅሟል። በዚህ ምክንያትም ሟች የሚያድርበትን አካባቢ ሲያጠና ከቆየ በኋላ በግምት ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ሲሆን ሟች በጎዳና ላይ የግንብ አጥር ስር ተኝቶ ባለበት ቦታ በጭካኔ ሕይወቱ እንዲልፍ አድርጓል በሚል ተከሷል። 11273 ### Response:
### Text: ሶስተኛው የግድቡ ሙሌት በሂደት ላይ ይገኛል ኢር ክፍሌ ሀሮዛሬ የ2ኛው ተርባይን ኃይል ማመንጫ ማብሰሪያ ስነስርዓት ላይ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢር ክፍሌ ሀሮ ከተናገሩት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ በያዝነው ዓመት በ2014 ለማከናወን ከተያዙ አብይ እቅዶች መካከል በሁለት ዩኒት ማለትም በሁለት ታርባይንና ጀነሬተሮች ኃይል ማመንጨት አንዱ ሲሆን ይህ እቅድ ተሳክቶ በ2ቱም ዩኒቶች ኃይል ማመንጨት ተችሏል።ከለውጡ በኃላ በፕሮጀክቱ ላይ የማስተካከያ እርምጃ ከተወሰደ በሶስት ዓመታት ውስጥ በግድቡ ውስጥ መተከል የነበረባቸው የውሃ ማስተላለፊያ የብረታብረት ስራዎችን በማጠናቀቅ የመካከለኛውን የግድብ ከፍታ ከሃያ አምስት ሜትር ወደ መቶ ሜትር ማድረስ ተችሏል።እንደዚሁም የግድቡን ግራና ቀኝ በትንሹ እስከ ስድስት አርባ አምስት የደረሰም አለ ወይም ከባህር ጠለል በላይ እስከ ስድስት አርባ አምስት ወይም መቶ አርባ አምስት ሜትር ከመሰረት ከፍ ያለ በተጨማሪ በትንሹ እስከ መቶ አስራ አንድ ሜትር ከፍ በማድረግ ሁለት ሙሊቶችን ማከናወን የተቻለ ሲሆን ሶስተኛውሙሊትበሂደት ላይ ይገኛል ። ከምንም ደረጃ ተነስቶ ሁለት ተርባይኖች እና ጄነሬተሮች በመትከል ኃይል ማመንጨት ተችሏል። ### Response:
### Text: የቁጥሩ ነገር የአባ ዱላ ንግግርና የመንግሥት ሚዲያዎች ደጋግሞ ቁጥር መቀያየር በጣም ጥርጣሬን የሚያጭር ቢኾንም በትክክል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተወካዮች ምክር ቤት አባላቱ ስለ መጽደቁም ኾነ ውድቅ ስለ መደረጉ ማረጋገጫ ማግኘት አልተቻለም፡፡ቀጥሮቹ እነዚህ ናቸው ጠቅላላ የፓርላማ አባላት ቁጥር 547 አባዱላ 8 ያህሉ ስለሞቱ እና በህመም ምክንያት ስለቀሩ ቁጥሩ 539 ነው ብሏል ዛሬ የተገኙ አባላት 441 የመንግሥት ሚዲያዎች ቁጥሩን አሁን ወደ 490 አሳድገውታል አዋጁ እንዲጸድግ የደገፉ 346 የመንግሥት ሚዲያዎች ቁጥሩን አሁን ወደ 395 አሳድገውታል አዋጁን የተቃወሙ 88 ብዙዎቹ የኦሕዴድ አባላት ድምጸ ተአቅቦ ያደረጉ 7 አዋጁን ለማፅደቅ የሚያስፈልግ የድጋፍ ድምጽ፡ 23ኛቁልፉ ጥያቄ 23ኛው ድምጽ ታሳቢ የሚደረገው ከተገኙ የፓርላማ አባላት 441 ነው ወይስ ከጠቅላላው የፓርላማ አባላ ቁጥር 547 ነው የሚል ነው፡፡ከተገኙ አባላት አንጻር ከኾነ ሕግ ፀድቋል ማለት ይቻላል ውጤቱ ታሳቢ የሚደረገው ከጠቅላላ የፓርላማ አባላት ቁጥር አንጻር ከኾነ ሕጉ ውድቅ ኾኗል ማለት ነው፡፡በነገራችን ላይ ሪፖርተር ከሰሞኑ ሕገመንግሥቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን በተመለከተ የሕግ ክፍተት አለበት ብሎም ነበር፡፡ምንጭ አክመል ነጋሽ ### Response:
### Text: ተክለ ብርሃን አምባዬ በ73 ሚሊዮን ብር ግብር ስወራ ተከሰሰየፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽንን ጨምሮ አምስት ከፍተኛ ተቋራጮችን በግብር ስወራ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በስምንተኛ እና ዐስረኛ ወንጀል ችሎቶች ክስ መሰረተ።በኢትዮጵያ ካሉ የደረጃ አንድ ተቋራጮች መካከል እንዲሁም ከፍተኛ አቅም ካላቸው መካከል የሆነው ተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን፣ ከ 2005 እስከ 2008 ባለው ጊዜ መክፈል የነበረበት እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች የተገኘ 703 ሚሊዮን ብር የትርፍ ግብር ባለመክፈሉ ክሱ ተመሥርቷል።የንግድ ግብሩ ግዢ ባልተፈፀመባቸው ሐሰተኛ ደረሰኞች በመጠቀም የተሰወረ እንደሆነ እና ደረሰኞቹንም የቆረጡት ድርጅቶች በአካል የሌሉ መሆናቸውን ጠቅሶ ነው ዐቃቤ ሕግ ክሱን የመሠረተው። ከተለያዩ ፕሮጀክቶች ከ 25 ሚሊዮን እስከ አንድ ሚሊዮን ብር የሚደርስ ገቢን ድርጅቱ ሰውሯልም ሲል ዐቃቤ ሕግ ክሱን አሰምቷል።በተጨማሪም ከተለያዩ አገልግሎቶች የተሰበሰበ ሦስት ሚሊዮን ብር የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ በተመሳሳይ ከ 2005 እስከ 2008 ባለው ዓመት ለመንግሥት ሳይከፍሉ ቀርተዋል ሲልም ነው ዐቃቤ ሕግ ክሱን በስምንተኛ የጉምሩክ ችሎት የመሠረተው። 1202 አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ### Response:
### Text: 19 የኮሮና ቫይረስ አስጊ የሚባል ደረጃ ላይ ደርሷል ዶር ቴድሮስ አድሃኖምየኮሮና ቫይረስ አስጊ የሚባል ደረጃ ላይ እና ዓለም አቀፍ ስጋት ሊሆን የሚችልበት አቅም ላይ መድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ገለፁ። የዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም አስተያየት የተሰማው በተለያዩ የዓለም ሀገራት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ባለበት ወቅት ነው። ባለፉት ሁለት ቀናት ከቻይና በበለጠ በሌሎች ሀገራት አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች መገኘታቸውም ተጠቁሟል። በአሁኑ ወቅት ከቻይና ውጭ ኢራን እና ጣሊያን የቫይረሱ መገኛ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ቫይረሱም ከእነዚህ ሃገራት ወደ ሌሎች ሀገራት በሚያቀኑ ሰዎች አማካኝነት እየተሰራጨ ነው ተብሏል። ዶር ቴድሮስ በሰጡት አስተያየት በቀሪው ዓለም እየታየው ያለው ነገር አሁን ላይ ትልቅ ትኩረት የምንሰጠው ነው ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ የዓለም መንግስታት ቫይረሱን ለመቆጣጠር በፍጥነት እና በጥንካሬ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባም አሳስበዋል። ወቅቱ የፍርሃት ሳይሆን ቫይረሱን የመቆጣጠር እና የሰዎችን ህይወት የምናተርፍበት ጊዜ ነውም ብለዋል ዶክተር ቴድሮስ በንግግራቸው። ቢቢሲ ኤፍቢሲ ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ ተጨማሪ 19 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧልባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4044 የላብራቶሪ ምርመራ አስራ ዘጠኝ 19 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ሶስት መቶ ስድስት 306 ደርሷል፡፡ቫይረሱ የተገኘባቸው 15 ወንድ እና 4 ሴት ናቸው። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ከ16 እስከ 55 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 2 ሰዎች ከአዲስ አበባ ሲሆኑ፣ 2 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል ጊንጪ ከተማ፣ ደንዲ ወረዳ፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ 3 ሰዎች ከትግራይ ክልል ማይ ካድራና ሰቲት ሁመራ ለይቶ ማቆያ፣ 1 ሰው ከአማራ ክልል መተማ ለይቶ ማቆያ እና 11 ሰዎች ከሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ ናቸው። የዕለቱ ታማሚዎች የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው 15 በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው 2 የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው 2ተጨማሪ መረጃ በትላትናው ዕለት አንድ 1 ሰው ከኦሮሚያ ክልል ከበሽታው ያገገመ ሲሆን አጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ አስራ ሶስት 113 ደርሷል። ### Response:
### Text: አራቱ ጋዜጠኞች በዋስትና ተፈቱ።በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት ኪሎ ከተማ በሚገኝ የፖሊስ ማሰልጠኛ ካምፕ ለ49 ቀናት በእስር ላይ የቆዩት አራት የኢትዮ ፎረም እና የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኞች በዋስትና ተፈተዋል።በዛሬው ዕለት ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኞች የኢትዮ ፎረም አዘጋጁ ያየሰው ሽመልስ እና ባልደረባው አበበ ባዩ፣ የአውሎ ሚዲያ ዋና አዘጋጅ በቃሉ አላምረው እንዲሁም በሚዲያው በተንታኝነት ይሳተፍ የነበረው ፋኑኤል ክንፉ ናቸው። የአራቱን ጋዜጠኞች የምርመራ የጊዜ ቀጠሮ ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ፍቤት እያንዳንዳቸው ተጠርጣሪዎች 5000 ብር ዋስትና አስይዘው እንዲፈቱ ውሳኔ አሳልፎ የነበረው ከትላንት በስቲያ ሰኞ በዋለው ችሎት ነበር። የጋዜጠኞቹ ቤተሰቦች ለዋስትና የተጠየቀውን ገንዘብ የዚያኑ ዕለቱ ከፍለው ቢያጠናቅቁም ተጠርጣሪዎቹ ላለፉት 2 ቀናት ሳይፈቱ ቆይተዋል። ዛሬ ጠዋት ሁለት ሰዓት ገደማ አራቱን ጋዜጠኞች ጨምሮ 8 ተጠርጣሪዎች በእስር ላይ ከቆዩበት የአዋሽ ሰባት ኪሎ ከተማ የፖሊስ ማሰልጠኛ ካምፕ መፈታታቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኞች ረፋድ 530 ገደማ አዲስ አበባ መግባታቸው ታውቋል።የመረጃው ባለቤት ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ### Response:
### Text: የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን️የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ባደረገው ከ8ዐ ሺ በላይ የአሜሪካ ዶላርን ጨምሮ ድርሃም፣ የሳዑዲ ሪያል፣ የሱዳን ፓውንድ እና ከ271 ሺ ብር በላይ መያዙን አስታወቀ፡፡የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ያደረገውን ጥናት መነሻ በማድረግ ሁለቱ ተቋማት ታህሳስ 14 እና 152011 በጋራ በቦሌ ክፍለ ከተማ ባደረጉት የኦፕሬሽን ገንዘቡ መያዙ ተገልጿል፡፡ጉዳዩ እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሰታውቋል፡፡ከተያዙት ገንዘቦች በተጨማሪ በሕገወጥ መንገድ በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተዋል ያሏቸውን ልዩ ልዩ ቁሰቁሶችና በአንድ ሥፍራ ብቻ የተገኙ 1 ሺህ 23 የውኃ ቆጣሪዎች ተይዘው ሕጋዊነታቸውን ለማረጋገጥ የምርመራ ሥራ እየሰራ መሆኑን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ከዚህ ቀደም በተደረጉ ተመሳሳይ የኦፕሬሽን ሥራዎች ከፍተኛ የውጪ ሀገር ገንዘቦች መያዛቸውን ኮሚሽኑ አስታውሶ ወደፊትም ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመግታት ተግባሩ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ሕብረተሰቡ ለኮሚሽኑ ሥራ ስኬታማነት እያደረገ ላለው ትብብር ምሥጋናውን እያቀረበ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: ነገ የካቲት 272011 በእጣ ለተመዝጋቢዎች የሚተላለፈው የ4060 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዝርዝር እና በዕጣው ለመግባት የሚያስፈልገው የቁጠባ መጠንሀ ለ2ኛው ዙር የ4060 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ዝግጁ የሆኑ የቤቶች ዝርዝር በቁጥር1 ባለ 1 መኝታ = 30602 ባለ 2 መኝታ = 103223 ባለ 3 መኝታ = 5194በጠቅላላ ለ2ኛው ዙር ለዕጣ ዝግጁ የሆኑ 18576 የ4060 ቤቶች ናቸውለ በ4060 የቤት ልማት ፕሮግራም እየቆጠቡ ያሉ ተመዝጋቢዎች1 በባለ 1 መኝታ = 116992 በባለ 2 መኝታ = 572773 በባለ 3 መኝታ = 56138በጠቅላላ 125114 ተመዝጋቢዎች በ4060 የቤት ልማት ፕሮግራም እየቆጠቡ ይገኛሉ።ሐ ለ2ኛው ዙር የ4060 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውስጥ ለመግባት የሚያስፈልገው ዝቅተኛው የቁጠባ መጠን ለሁሉም የመኝታ ዓይነት በምዝገባው ወቅት ከነበረው ጠቅላላ ዋጋ ውስጥ 40 እና ከዚያ በላይ የቆጠቡ ለዕጣው ተወዳዳሪ ይሆናሉ1 ለባለ 1 መኝታ = 16264504 = 65058 ብር2 ለባለ 2 መኝታ =25000004 = 100000 ብር3 ለባለ 3 መኝታ = 38640004 = 154560 ብርመ ለ2ኛው ዙር የ4060 የዕጣ ፕሮግራም ብቁ ዝቅተኛ የቁጠባ መጠንን ያሟሉ ሆነው ለዕጣው ተወዳዳሪ የሚሆኑ የተመዝጋቢዎች ብዛት በቁጥር1 በባለ 1 መኝታ = 55022 በባለ 2 መኝታ = 256343 በባለ 3 መኝታ = 26126በጠቅላላ 57262 ብቁ ተመዝጋቢዎች ለ18576 የ4060 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለዕጣው ተወዳዳሪ ይሆናሉ። ### Response:
### Text: 19በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።የኢንስቲትዩቱ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ አያሌው ከተናገሩት የኮሮና ቫይረስ ወደ ክልሉ እንዳይገባ ቀድሞ መከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው። የመከላከል ተግባሩን በውጤታማነት ለመምራትም ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ክልላዊ ግብረሃይልና የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። ከተደረጉት ዝግጅቶች መካከል በባህርዳር፣ ጎንደር፣ ላሊበላና ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያዎች የምርመራና ልኬታ ስራዎችን ለማካሄድ የሚያስችል ስራ ተከናውኗል። በኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጨምሮ በ39 የልማት ፕሮጀክቶች አጠራጣሪ ምልክት የሚታይባቸውን ሰዎች ተለይተው የሚቆይባቸውን ካምፖች ተዘጋጅተው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል። የምርምራ ስራውን የሚያካሄዱ ባለሙያዎችን በመመልመል የማሰልጠን ፣ ቁሳቀስ የማቅረብና የማቆያ ቦታዎችን የመለየት ስራ እየተካሄደ ይገኛል። በኢንስቲትዩቱ ስር የሚገኘው የወረርሽኝ ማስተባበሪያ ማዕከል አስፈላጊውን ግብዓት ተሟልቶለት ስራውን እንዲጀምር ተደርጓል። ### Response:
### Text: የኢንተርኔት ሶሳይቲ በኢትዮጵያ ቻፕተር መስርቷልበአለም ሀገራት ወደ 114 የሚጠጉ ቻፕተሮች እንዳሉት የተገለጸው ኢንተርኔት ሶሳይቲ የተባለው ለትርፍ ያልተቋቋመ ማህበር በኢትዮጵያም ቻፕተሩን መስርቷል፡፡ ከዚህ ቀደም 35 በሚሆኑ የአፍራካ ሀገራት ቻፕተሩን መመስረቱ ነው የተነገረው፡፡ እስካሁን በነበሩት የህግ ገደቦች ምክንያት በኢትዮጵያ እንዳልተቋቋመና አሁን ላይ ህጉ ላይ ማሻሻያ በመደረጉ ቻፕተሩ ሊመሰረት እንደቻለ ተነግሯል፡፡የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡት አቶ አዱኛ ነቾ ስለ ማህበሩ አላማ እንደነገሩን ከሆነ ማህበሩ በሀገሪቱ የኢንተርኔት አስተዳደር ዙሪያ አውደ ጥናቶችን፣ ስልጠናዎችንና ሴሚናሮችን የሚያዘጋጅ ሲሆን ክፍት፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና አስተማማኝ የኢንተርኔት ተደራሽነት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የሚደረጉ የልማት ማስፋፋት ስራዎችን ይደግፋል ብለዋል፡፡ማህበሩ ላይ ለመሳተፍ ሙያ እንደማይጠይቅ የተናገሩት የኢንተርኔት ሶሳሳይቲ የአፍሪካ አስተባባሪ ዶክተር ዳዊት በቀለ በትላልቅ ከተሞችም ሆነ በገጠራማ ቦታዎች የኢንተርኔት ተደራሽነትን ለማስፋትና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚደረጉ ጥናቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ### Response:
### Text: ከስልጤ ዞን ዳሎቻ ወረዳ️እባክህን ፀጊሽ ይህን ነገር የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ ይወቅልን በራሳችን ፖሊሶች አማካኝነት በሕፃንትና ወጣቶች ተኩስ ተከፍቶብናል። በአቢይ እንደመር ዘመን ቀንሰውናል። ምክንያቱ አመራሩ ያስፈልገዋል ብሎ ህዝቡ በጫዋ መንገድ ሰልፍ ሳይወጣ የዞኑ ሃላፊ የወረዳው አስተዳዳር በተገኘበት በስብሰባ ጥያቄውን አቅርቦ በትንሽ ግዜ ዉስጥ እናስተካክላን ብለውት 3 ሳምንት ያህል በትዕግስት ቢጠብቅም ምንም አይነት ምላሽ ስላላገኘ ቀጣይ ወዴት አቤት ማለት አለብን በሚለው ጉዳይ ወጣቱና ነጋዲው ስብሰባ አድርጎ ወደ ላይ አካል አቤት ለማለት ኮሚቴ መርጦ በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ ወስኖ ከተበተነ በኋላ የተወሰኑ ልጆች ኣስተዳደሩ ጥያቅያቸውን ችላ ማለቱ ንቀት ስለመሰላቸው ስሜታዊ ሆነው አመራሩን ስም አየጠራ ሌባ አያለ መሄድ ሲጀምር የካባቢው ፖሊስ እላያቸው ላይ ተኩስ ሲከፍት እቤቱ የነበረው ሰው በጠቅላላ ግልብጥ ብሎ ወጣ ፖሊሶች ወደላይም አደለም ቀጥታ መተኮስ ጀመሩ ከ6 በላይ ሰው በጥይት ተመቷል። በኋላ ልዪ ሃይል መጥቶ ለምን ተኮሳችሁ ብሏቸው አረጋግቶ ከወጣ በኋላ እየዞሩ ወጣቱን እያሰሩ ነው። ብዙ ሰው ታስሯል እስካሁን አሁንም በየቤቱ እያሰሱ ነው። ነ ከዳሎቻ ወረዳ ### Response:
### Text: ኮሎኔል አሰፋ ዮሃንስ️የቀድሞው የመከላከያ ፓዎር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ስራ አስኪያጅ ኮሎኔል አሰፋዮሃንስ ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ የህዝብ ሀብት በማባከን መጠርጠራቸውን ፓሊስ አስታወቀ፡፡ፖሊስ እንዳለው ተጠርጣሪው የበለስ ቁጥር 1 የስኳር ፕሮጀክት ከአንድ የቻይና ኩባንያ ጋር ፈርሞት የነበረው ኮንትራት ያለጨረታ በ5 ሚሊዮን 720 ሺህ ዶላር እንዲሻሻል አስደርገዋል፡፡ኩባንያውም ገንዘቡን ተቀብሎ ምንም ሳይሰራ ከሀገር እንዲሸሽ በማድረግ ራሳቸውንና ኩባንያውን ብቻ አላግባብ ተጠቃሚ አድርገዋል፡፡በዚህም የህዝብና የመንግስት ሀብት መዝብረው አስመዝብረዋል በሚል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረዋል፡፡ኮሎኔል አሰፋ የ6 ሚሊዮን 400 ሺህ ዶላር ሌላ የፕሮጀክት ኮንትራት ፈርሞ የነበረ ሌላ ኩባንያም ከዚህ ውስጥ 1 ሚሊዮን 920 ሺህ ዶላር በቅድሚያ ተቀብሎ ግዴታውን ሳይፈፅም እንዲጠፋ አስደርገዋል በሚል ተጨማሪ የሙስና ወንጀልም ተጠርጥረዋል ብሏል ፖሊስ፡፡ተጠርጣሪው የተከላካይ ጠበቃ ለመቅጠር አቅም እንደሌላቸው በመግለፅ መንግስት እንዲመድብላቸው ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ግራ ቀኙን አዳምጦ ውሳኔ ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ጥሏል፡፡ምንጭ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ሰበር ዜና️በጅግጅጋና አካባቢው ብሔርን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ወንጀል ዙሪያ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳደር በተጨማሪ ሌሎች በቁጥጥር ስር የሚውሉ አካለትም መኖራቸው ታውቋል።ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና የፌዴራል ፖሊስ ከሀምሌ 28 እሰከ 30 በሶማሌ ክልል በጅግጅግናና ሌሎች ዞኖች ላይ ብሔርን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ወንጀል ዙሪያ በጋራ ሲያደርጉት የቆዩትን የምርመራ ስራ አጠናቀዋል።ከተቋሙ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከሀምሌ 28 እስከ 30 ቀን 2010 ዓም ድረስ ባሉት ቀናት በጅግጅጋና ሌሎች ዞኖች ላይ ብሄርን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ከባድ የወንጀል ድርጊቶች ዙሪያ የድርጊቱ ተሳታፊ የነበሩ በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።በዚሁ የምርመራ ውጤት መሰረት ተጨማሪ ትልልቅ ወንጀሎች እንደተገኙ የታወቀ ሲሆን ይህንን ተከትሎም በቁጥጥር ስር የሚውሉ ተጨማሪ ግለሰቦች መኖራቸውም ታውቋል።የምርመራው ውጤት በመጠናቀቁም በቁጥጥር ስር ያሉትን የክልሉን የቀድሞ ርዕሰ መስተዳደር ጨምሮ ሌሎች አካላት ላይ ክስ መመስረቱ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።የምርመራ ሂደትንና ውጤቱን በተመለከተም አርብ ጥር 17 ቀን 2011 ዓም በጠቅላይ ቃቤ ህግ ለጋዜጠኞች መግለጫ ተሰምቷል።ምንጭ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ### Response:
### Text: የቀድሞው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ከአዲሱ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል።ዛሬ አዲሱ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቀድሞ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶር ሳሙኤል ኦርቃቶ የስራ ርክክብ ማድረጋቸው ተገልጿል።በርክክቡ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት ንዑስ ዘርፍ ልማት ፣ የከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ፣ የ10 ዓመት ዕቅድ እና ሌሎች በሳይንስ ና እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እየተከናወኑ ያሉ ሌሎች ሥራዎች ገለፃ ተደርጓል።በተጨማሪም ከሳይንስ ንዑስ ዘርፍ ልማት የሳይንስ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ፣ የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ እና እንደ ብሔራዊ የምርምር ስትራቴጂ ፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ንዑስ ዘርፍ ልማትየቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ፣ የ10 ዓመት ዕቅድ ፣ የምሥራቅ አፍሪካ 7 የልህቀት ማዕከል ግንባታ ዙሪያ ማብራሪያ ተሠጥቷል።እንዲሁም የተቋማዊ የአቅም ግንባታ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ልየታ፣ የከፍተኛ ትምህርት መረጃ ዲጂታል ሲስተም ፣ የአካዳሚክ አመራር ፣ የከፍተኛ ትምህርት እና የሥልጠና ዕውቅና ስትራቴጂ ዙሪያም የተሠሩ ስራዎች ማብራሪያ መሰጠቱን ለማወቅ ተችሏል። ### Response:
### Text: ብፕላዛ ፕሪሚየም ግሩፕ እና ኤንኤችዋይ የሽርክና አጋርነት ስምምነት አደረጉ፡፡ስምምነቱ በአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ዋና መዳረሻ በሆነው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ያለውን የተጓዦች አቀባበል እና የላውንጅ አገልግሎት ደረጃን እንደሚያሳድግ እምነት የተጣለበት ነው።ፕላዛ ፕሪሚየም ላውንጅ ኢትዮጵያ በያዝነው አመት መጋቢት ወር በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተርሚናል 2 የሚከፈት ይሆናል፡፡ በአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ቀዳሚ መዳረሻ የሆነው አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ በየአመቱ ከ12 ሚሊዮን በላይ ተሳፋሪዎችን ያስተናገዳል፡፡ ይህ አዲስ የተመሰረተ የሽርክና አጋርነት የፕላዛ ፕሪሚየም ግሩፕን የ24 ዓመታት የላቀ ልምድ እና የኤንኤችዋይን የሀገር ውስጥ የእንግዳ መስተንግዶ ልምድ በማዋሃድ በአየር ማረፊያ ውስጥ ያለውን የመንገደኞች አቀባበል እና የላውንጅ አገልግሎት ደረጃን የበለጠ ለማዘመን ያለመ ነው፡፡በ1000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው ፕላዛ ፕሪሚየም ላውንጅ ኢትዮጵያ በአንድ ጊዜ ለ325 እንግዶች አለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ መስተንግዶ ለመስጠት እንዲያስችል ታልሞ የተደራጀ ነው። ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: ትላንት በኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተመረጡት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባላት በጉባኤው ፊት ቃለመሃላ ፈፅመዋል።በሌላ በኩል የፓርቲው የኦዲት እና ኢንስፔክሽን አባል የሆነው የተመረጡ አባላትም ቃለመሃላ ፈፅመዋል።ትላንትና በነበረው የመጀመሪያው ቀን የኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ፕር መረራ ጉዲና ሊቀመበር ፣ አቶ በቀለ ገርባ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ፣ አቶ ጃዋር መሃመድ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው እና የፓርቲው የስራ አስፈፃሚ አባላት መመረጣቸው ይታወሳል።አቶ ጃዋር ምንም እንኳን ለሊቀመንበርነት እና ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበርትነ በጉባኤተኛው ተጠቁመው ውድቅ ቢያደርጉም ጉባኤው የፓርቲው ም ሊቀመንበር አድርጎ መርጧቸዋል።የኦፌኮ ም ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ለረጅም ዓመታት በውጭ ሀገር ሆነው የ ኢህአዴግ መራሹን መንግስት ተገዶ ወደ ለውጥ እንዲገባ በማስገደድ በሚዲያው እና በአክቲቪዝሙ መስክ ጉልህ ድርሻ የተጫወቱ ሲሆኑ በኃላም ወደ ሀገራቸው በመግባት ምርጫቸውን ኦፌኮ በማድረግ ሙሉ በሙሉ የፖለቲካውን ዓለም ሊቀላቀሉ ችለዋል።አቶ ጃዋር መሀመድ ለአንድ አመት ከመንፈቅም ታስረው ከወራት በፊት ታህሳስ 292014 ዓም መፈታታቸው አይዘነጋም። ### Response:
### Text: እምቦጭ ከጣና አልፎ ዓባይን እየወረረ ነውየአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅትበዚህ ዓመት እምቦጭ ከጣና አልፎ አባይ ወንዝ ዳርቻዎች በሚገኝ 200 ሄክታር መሬት ላይ ተንሠራፍቷል። ባለፈው ዓመት በ34 ሄክታር መሬት ላይ የተከሰተው የአባይ እምቦጭ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 166 ሄክታር ጨምሮ ወደ 200 ሄክታር መስፋፋቱ የአደጋውን አሳሳቢነት ቁልጭ አድርጐ የሚያሳይ ነው። ይሁንና ሀገሪቱን በበላይነት የሚያስተዳድረው የፌዴራል መንግስት፣ ጣና በለስን ጨምሮ በጢስ አባይ ቁጥር አንድ እና ቁጥር ሁለት የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫዎች ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሀይል የሚሰበስበው የኢትዮጵያ ውሀ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር እና ህይወታችን የተመሠረተው በአባይ ወንዝ ላይ ነው የሚሉት ግብጽ እና ሱዳን ሀይቁን ለመታደግ ምንም አይነት ጥረት አለማድረጋቸው እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው የባህር ዳርና አካባቢዋ ነዋሪዎች ይናገራሉ።እንደ ነዋሪዎቹ ገለፃ እምቦጭ ከተከሰተበት ዓመት ጀምሮ በመከላከል ተግባር ደፋ ቀና የሚሉት የሰሜንና ደቡብ ጐንደር አርሶ አደሮች፣ የክልሉ መንግስት፣ የአካባቢው ተቆርቋሪ ግለሰቦችና ሀገር ወዳድ የበጐ አድራጐት ማህበራት ብቻ ናቸው።የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት 1202 ሼርያድርጉት ### Response:
### Text: ህጻናት በ19 እንዳይጠቁ ምን አይነት ጥንቃቄ እናድርግ በዶክተር ኃይለልዑል መኮንንህጻናት በተፈጥሮ ፈጣኖች እና ሁሉን ነገር ለማወቅ ብሎም ያገኙትን ነገር ለመንካት ቅርብ ናቸው። ይሄ ባህርይ ደሞ ለዚህ አስከፊ በሽታ 19 ተጋላጭ ሊያደርጋቸዉ ይችላል።ስለዚህ ህጻናት በቤት ውስጥ ካሉ የሚከተሉትን ምክሮች ተግባራዊ እናድርግ 1 ህጻናት እጆቻቸውን አዘውትረው እንዲታጠቡ ማድረግ ፣2 በተቻለ መጠን ወደ ውጪ እንዳይወጡ መከልከል ፣3 ለስራ እንዲሁም ለተለያዩ ጉዳዮች ከቤት ወጥተው ከሆነ ውጭ የዋሉበትን አልባሳት ቀይረው ወደ ቤት ይግቡ፣4 ህጻናት የሚጫወቱበትን ቦታ መወሰን ፣5 ልጆችን በተቻለ መጠን አለማቀፍ ፣ አለመሳም አንዲሁም አላስፈላጊ ጨዋታ እና ግንኙነቶችን መቀነስ ፣6 ልጆችን ለብቻቸው ጥሎ አለመሄድ ብዙ ነገሮችን ስለሚነካኩ ተጋላጭ ያደርጋቸዋል ፣7 ስለ 19 በቂ እና አስፈላጊ መረጃዎችን ብቻ መንገር ፣8 ልጆች ብዙ ጊዜ ጉንፋን ስለሚያጠቃቸው የተለየ ምልክት ሲመለከቱ የህክምና ባለሙያ ማማከር ፣9 አዘዉትረው የሚነኩ ቦታዋች እና ቁሶችን0 ማጽዳት ፣10 ከጤና ባለሙያዎች የሚሠጡትን ምክሮች በመተግበር እራሳችንን እና ልጆቻችንን ከኮሮና ቫይረስ እንከላከል የምንሰማውን ወደ ተግባር እንለውጥ ### Response:
### Text: የካቲት12 የካቲት12 ቀን ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት በጀነራል ግራዚያኒ ትዕዛዝ የተጨፈጨፉ ኢትዮጵያዉያን የሚታሰቡበት ነዉ። የዛሬ 85 ዓመት ግራዚያኒ የተባለዉ የጣሊያን ጀነራል ከሀገሩ ኢጣሊያ ንጉሳዊያን ቤተሰቦች ዘንድ አንድ ልዑል መወለዱን አስመልክቶ ደስታዉን ለማክበር የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በአሁኑ 6 ኪሎ ዩንቨርሲቲ በቀድሞዉ ገነተ ልሎል ቤተመንግሥት ሰበሰበ። በዚህ ወቅት የፋሽሽት ኢጣሊያ ወረራ ያስቆጫቸዉ ሞገስ አስገዶም እና አብርሃ ደቦጭ የተባሉ ሁለት ወጣቶች ከተሰበሰበዉ ሕዝብ መሀል ወጥተዉ ወደ ግራዚያኒ ቦንብ ወረወሩ። በዚህም ግራዚያን እና በርካታ ባለስልጣናቱ ቆሰሉ። ይህ ያበሳጨዉ የፋሽስት ኢጣሊያ ጀነራል ግራዚያኒ ያለርህራሄ ኢትዮጵያዉያን እንዲጨፈጨፉ አዘዘ።ኢትዮጵያውያኑ ሰማዕታት በፋሽሽት ኢጣሊያ የተጨረጨፉት በ1929 ዓም የካቲት 12 ቀን ልክ የዛሬ 85 ዓመት ነበር። ወጣት አብርሃ ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶምን ጨምሮ በሦስት ቀናት ብቻ 30 ሺህ ኢትዮጵያዉያን በዕለቱ ተሰውተዋል። የሰማዕታቱ መታሰቢያ ሀውልት በአዲስ አበባ ከተማ በስድስት ኪሎ አደባባይ ላይ ቆሟል። በሀውልቱ ሥር በየዓመቱ የአበባ ጉንጉን በማስቀመጥ የመታሰቢያ ስነስርዓት ይካሄዳል። ### Response:
### Text: በአርባምንጭ ከተማ በዝርፊያ፣ በህገወጥ መሳሪያና ኮንትሮባንድ ንግድ የተሰማሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የከተማው ሠላምና ጸጥታ ጽቤት አስታወቀ፡፡የክልሉን ሠላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ ኮማንድ ፖስት ማወጁን መነሻ በማድረግ ከመከላከያና ልዩ ሃይል ጋር በቅንጅት በመስራት የቡድን ዘረፋን ጨምሮ ህገወጥ መሳሪያና የተለያዩ ኮንትሮባንድ ንግዶችን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደቻለ የአርምንጭ ከተማ ሠላምና ፀጥታ ጽቤት ኃላፊ ሻምበል መስፍን አንዳርጌ ገልፀዋል፡፡የነዋሪውን ደህንነት ለማስጠበቅ የከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንዳለ ያሳውቁት ኃላፊው በከተማው በውህ ምንጭ ቀበሌ በተለምዶ ቆንጥር ሰፈር በሚባልበት አከባቢ ለበርካታ ጊዜያት በመመሸግ የተለያዩ ዝርፍያዎችን ሲፈፅሙ የቆዩና የነዋሪውን የቤት እንስሳ ሰርቀው በማረድ ለሆቴሎች በሽያጭ ሲያከፋፍሉ የነበሩ 12 ግለሰቦች ለእኩይ ተግባራቸው ማስፈፀሚያ የሚጠቀሙበትን ገጀራና ሰንጢዎች አደንዛዥ እፆች እንዲሁም ስልክና የተለያዩ ክህብረተሰቡ የዘረፏቸው ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በኤግዝብትነት መያዛቸውን አሳውቀዋል፡፡ምንጭ የከተማ አስተዳደሩ ኮሚኒኬሽን ### Response:
### Text: ከ850 በላይ ተማሪዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል።ዛሬ መቐለ ዩኒቨርሲቲ የዓዲግራት ተማሪዎችን ሲቀበል ውሏል።የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ2012 ተመራቂዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ መልዕክት መተላለፉ ይታወቃል።ዛሬ እና ነገ ተማሪዎች የሚገቡ ሲሆን ጥር 2 ቀን 2013 ትምህርት ይጀመራል።እስካሁን ድረስ ከ850 በላይ ተማሪ ግቢ ገብቷል።ለተማሪዎች ትራንስፖርት መኪና ለመመደብ እንቅስቃሴ እንደነበር ቢገለፅም ምንም የተመደበ መኪና የለም።ወደ ግቢ የገቡ ተማሪዎች እንደገለፁት ከአዲስ አበባ በባስ 850 ብር ትኬት ቆርጠው ነው መቐለ የደረሱት።ከአዲስ አበባ ውጭ ከመቐለ በቅርብ ርቀት ያሉ ከተሞች ወልዲያ፣ ደሴ የሚገኙ ተማሪዎች ደግሞ ኮንትራት መኪና በራሳቸው ይዘው መቐለ እንደገቡ ተሰምቷል።የትራንስፖርት ክፍያው ውድነት እንዲሁም ትራንስፖርት አጥተው የተቸገሩ የቲክቫህ አባላት ተማሪዎች ቅሬታቸውን አቅርበዋል።ገንዘቡ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑና የትራንስፖርት እጥረት በመኖሩ ጉዟቸውን ፈታኝ እንዳደረገው አሳውቀዋል።ምንም እንኴን እጥረት ቢኖርም ከአዲስ አበባ መቐለ ትራንስፖርት አለ መንገድ ላይም ምንም አይነት ችግር እንደሌለ ዛሬ መቐለ የገቡ ተማሪዎች ገልፀዋል። ### Response:
### Text: አሜሪካ አይመን አልዛዋሂሪን ገደልኩኝ አለች።አሜሪካ የአልቃይዳውን መሪ አይማን አልዛዋሂሪን በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል ባካሄደችው የድሮን ጥቃት መግደሏን ነው በፕሬዝዳንቷ ጆ ባይደን በኩል ያሳወቀችው።የአሜሪካ የደህንነት መስሪያ ቤት ሲአይኤ ባሳለፍነው ዕሁድ ካቡል ውስጥ ባካሄደው የፀረሽብር ዘመቻ ዛዋሂሪን መግደል መቻሉን ባይደን ገልፀዋል።ፕሬዘዳንት ባይደን ዛዋሂሪ በአሜሪካ ዜጎች ላይ ግድያ እና ጥቃትን የቀረጸ ሰው ነው ብለዋል።አክለው አሁን ፍትህ ተሰጥቷል ይህ የአሸባሪ ቡድን መሪ ከዚህ በኋላ በሕይወት የለም ሲሉም ተናግረዋል።የአሜሪካ ባለስልጣናት ዛዋሂሪ በአንድ በጥብቅ በሚጠበቅ ቤት በረንዳ ላይ ተቀምጦ ባለበት ነው የአሜሪካ ድሮን 2 ሚሳኤሎችን ተኩሶ የገደለው።በቤቱ ውስጥ የነበሩ ሌሎች የቤተሰብ አባላት ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው ዛዋሂሪ ብቻ ተነጥሎ መገደሉንም ተናግረዋል።አሜሪካ ዛዋሃሪ ከቀድሞው የአልቃይዳ መሪ ኦሳማ ቢን ላደን ጋር በመሆን የ 911 ጥቃትን እንደመራ ትገልፃለች። በዚህም ለረጅም አመታት ስታፈላልገው ቆይታለች።አልዛዋሃሪ 71 ዓመቱ ሲሆን የኦሳማ ቢንላደን ህልፈትን ተከትሎ አልቃይዳን ሲመራ እንደነበርም ተገልጿል።መረጃው የቢቢሲ ነው። ### Response:
### Text: ለባለቤቷ ለቅሶ የተቀመጠችው በዚሁ አደጋ ወላጅ እናቷንም አጥታለች የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንትላንት በአዲስ አበባ ሸጎሌ አካባቢ አንድ የከተማ አውቶብስ ለለቅሶ የተጣለ ድንኳን ጥሶ በመግባት ባደረሰው ጉዳት የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ።አደጋው ከምሽቱ 1 ሰዓት የደረሰ ሲሆን በአደጋውን እስከ ትናንት ምሽት ድረስ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ከ20 በላይ ሰዎች ላይም ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።በአደጋው ጉዳት0 ከደረሰባቸው ተጎጂዎች መካከል የተወሰኑትን የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቅድመ ሆስፒታልና አምቡላንስ አገልግሎት ባለሞያዎች ሕክምና እያደረጉላቸው ወደሆስፒታል አድርሰዋቸዋል።የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በድንኳን ውስጥ ለባለቤቷ ለቅሶ የተቀመጠችው በዚሁ አደጋ ወላጅ እናቷንም አጥታለች ሲል ገልጿል።ህይወታቸውን ያጡትና ጉዳት የደረሰባቸውም ሀዘንተኛዋን ለማጽናናት በድንኳን ውስጥ የተቀመጡ ናቸው ብሏል።ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል በአስጊ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ያሉ ሲሆን ተጎጂዎቹ በአቤትና በራስ ደስታ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል፡፡መረጃው የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ነው። ### Response:
### Text: የትብብር የትምህርት ፕሮግራም እንዳይሰጡ የታገዱት ዩኒቨርሲቲዎች ኦዲት እንዲደረጉ ተጠየቀ ከግል ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጧቸውን የትምህርት ፕሮግራሞች እንዲያቋርጡ ማሳሰቢያ የተሰጣቸው የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ኦዲት መደረግ እንዳለባቸው የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ከግል ተቋማት ጋር በመተባበር ከዋና ካምፓሳቸው ውጪ በአዲስ አበባና በሌሎች አካባቢዎች ተማሪዎችን ተቀብለው ሲያስተምሩ የነበሩት ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲና ጅማ ዩኒቨርሲቲ የአገርን ሀብት የሚያባክን አሠራር የሚከተሉ በመሆናቸው የግድ ኦዲት መደረግ እንዳለባቸው የገለጹት፣ የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምራት ሞታ ናቸው፡፡ኤቢኤች ከተባለ አማካሪ ተቋም ጋር በትብብር በአዲስ አበባ ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያስተምረውን የጅማ ዩኒቨርሲቲ አሠራር በምሳሌነት ያቀረቡት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፣ በኤቢኤች ካምፓስ የሚማሩ ተማሪዎች በተርም 75 ሺሕ ብር እንደሚከፍሉና ከዚህም ውስጥ 52 በመቶ የሚሆነው ለኤቢኤች፣ ቀሪው ደግሞ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ገቢ የሚደረግበት አሠራር መኖሩን ገልጸዋል፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 08252 ### Response:
### Text: 71 ፓርቲዎች በአራት ኪሎ አደባባይ የረሃብ አድማ ያደርጋሉጤና ሚኒስቴር ሃኪሞች እንዲመድብ ተጠይቋል አዲስ የወጣውን የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጅን የሚቃወሙ 71 የፖለቲካ ድርጅቶች በጥቅምት መጨረሻ በአራት ኪሎ የድል ሃውልት አደባባይ ላይ ተሰባስበው ለሁለት ቀናት የረሃብ አድማ ለማድረግ መዘጋጀታቸው አስታወቁ፡፡አዋጅን በመቃወም በተደጋጋሚ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለምርጫ ቦርድ፣ ለህዝብ ተወካዮች ምቤት ደብዳቤ ቢጽፉም እስካሁን ምላሽ አለማግኘታቸውን የገለፁት 71ዱ የፖለቲካ ድርጅቶች በቀጣይ በአዋጁ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለጽ ተከታታይ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለማድረግ መሰወናቸውን አስታውቀዋል፡፡ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ካወጧቸው እቅዶች መካከል የረሃብ አድማ ዋነኛው ሲሆን ይህን አድማ ጥቅምት 5 እና 6 ለማድረግ አቅደው የነበረውን ወደ ጥቅምት 25 እና 26 ማሸጋገራቸውን አስታውቀዋል፡፡የረሃብ አድማውን ወደ ጥቅምት መጨረሻ ለማሸጋገር የወሰኑትም በጥቅምት መጀመሪያ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በተፈጠሩ አለመረጋጋትና ሁከት ምክንያት በየክልሉ ያሉ የክልል ፓርቲዎች በተያዘለት ቀን ወደ አዲስ አበባ ለመግባት መንገዶች ዝግ በመሆናቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ 1020 ### Response:
### Text: ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም አመራሩ ብሔሩን እየለየ የሚያገለግል ከሆነ አስቸጋሪ ነው። በእያንዳንዱ ክልል የተለያየ ብሔር ብሔረሰብ አለ። መንግሥት እኩል ካላገለገለ አድሎ ከተፈፀመ በአግባቡ አልተገለገልኩም የሚል ጥያቄ ያቀርባል። አንዱ ከአንዱ ጋር የሚገፋፋ ከሆነ አንድነት አይመጣም። ሰው ሲሞት ለምን ሞተ ከማለት ይልቅ የየትኛው ብሔር ተወላጅ ብዙ ሞተ እየተባለ ነው። ይህ ቀድሞ መሠራት የነበረበት ሥራ ባለመሥራቱ የመጣ ነው። ማንኛውም ሰው የራሱን ማንነት እንዲከበርለት የሚፈልግ ከሆነ የሌላውንም እኩል ማክበር አለበት። እዚህ ላይ ትልቅ ክፍተት ነበር። ስለብሔር ማሰብ ላይ ብቻ መተኮር የለበትም። አንዲት ትልቅ አገር መኖሯንም መዘንጋት የለበትም። አገርን ከመገንባት ለሌሎች ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች እኩል ክብር እና እውቅና መስጠት ያስፈልጋል። ብሔራዊ ማንነት ቢኖረንም ከአገራዊ ማንነት ውጭ መሆን አንችልም። እርስ በእርሳችን እንከባበር የምንለው አገራችንን ለመገንባት ነው። ትልቁ ችግር አገራዊ እና ብሔራዊ ማንነት ሚዛናቸውን ጠብቆ አለመሄዳቸው ነው። ለራስ ብሔር ብቻ ማሰብ ትርጉም የለውም። 1210 ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤአዲስ ዘመን ጋዜጣ ### Response:
### Text: የምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መከላከል ድርጅት የመረጃ አሰባሰብና ትንበያ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ፈለገ ኤልያስ የተናገሩትከሁለቱ አገራት ሊገባ የሚችል የአንበጣ መንጋ ለኢትዮጵያ ስጋት ነው። የመንና ሶማሊያ በጸጥታ ችግር ሳቢያ መንጋውን በአግባቡ መከላከል ስለማይችሉ ለአጎራባች አገራት በተለይም ለኢትዮጵያ አስጊ ይሆናል። የአንበጣ መንጋው የመራቢያ ጊዚውን ሳይጨርስ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ በተለይ በደቡብ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚያደርሰው ጉዳት የበረታ ሊሆን ይችላል።ኢትዮጵያ ከድርጅቱ ጋር በመተባበር ከአሁን በፊት ወደ አገር ውስጥ የገባውን የአንበጣ መንጋ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መከላከል ችላለች። የአገራት ትብብር ዝቅተኛ መሆንና የመከላከል አቅም ማነስ ለአካባቢው አገራት ስጋት ነው።0 አንበጣው0ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኬንያ በምግብ እህል ራሳቸውን ለመቻል በሚያደርጉት ጥረት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል።ባለፉት አራት ወራት በኢትዮጵያ የተከሰተውን የአንበጣ መንጋ ለመከላከል ሁለት አውሮፕላን በማሰማራት የመከላከል ስራ ተስርቷል። በቀጣይም0በምስራቅ አፍሪካ ባሉ አጋራት የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ አስቀድሞ የመከላከል ስራው0ተጠናክሮ0ይቀጥላል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: በእኔ እይታ ዩክሬን በአሜሪካ የተቀነባበረ ቀውስ ሰለባ ነች አያቶላህ አሊ ካሜኒ የኢራን ሐይማኖታዊ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ በዩክሬን ያለው ጦርነት መቆም እንዳለበት ገለፁ።ካሜኒ ማፍያ መሰል መንግስት ብለው የጠሯት አሜሪካን የዩክሬንን ቀውስ እየፈጠረች ያለችው እሷ ናት ሲሉ ከሰዋል። የዩክሬን ግጭት ሊቆም ይገባዋል ነገር ግን የግጭቱ ስር መሰረት እውቅና ሊሰጠው የግድ ነው የግጭቱ ስር መሰረት ደግሞ ምዕራባውያን እና የአሜሪካ ፖሊሲ ነው ብለዋል። ዩክሬንን እዚህ ያደረሰቻት አሜሪካ ናት አሜሪካ በአገሮች የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ትገባለች በመንግስት ላይ ተቃውሞዎችን ታመቻቻለችሁሉም እንደዚህ ያበቃል ሲሉ ተደምጠዋል። ካሜኒ አሜሪካ በችግር ውስጥ የምትኖር አገዛዝ ነች ያሉ ሲሆን በእኔ እይታ ዩክሬን በአሜሪካ የተቀነባበረ ቀውስ ሰለባ ነች ሲሉ ተናግረዋል።ካሜኒ አክለው እዚህ ላይ ሁለት ትምህርቶችን መውሰድ አለብን። በአሜሪካ እና በምዕራባውያን ኃያላን ድጋፍ ላይ የተመሰረቱ መንግስታት እንደነዚህ ያሉትን ሀገሮች ማመን እንደማይችሉ ማወቅ አለባቸው። ዋናው ጉዳይ የህዝቡ ነው ዩክሬናውያን መንግሥታቸውን ቢደግፉ ኖሮ ሁኔታው 200200አሁን ላይ ካለው ቀውስ የተለየ ይሆን ነበር ብለዋል። ### Response:
### Text: በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ አስቀማጮች ዋስትና ለመስጠት የተቋቋመው የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ እስከ 200 ሺሕ ብር ተቀማጭ ገንዘብ ላላቸው ዋስትና እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡ባንኮች እና የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ከተቀማጭ ገንዘባቸው 02 በመቶ ለፈንዱ ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተከታዩን ብለዋል በየባንኩ ለእያንዳንዱ አስቀማጭ እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆን ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋን ይሰጣል፡፡የመድን ሽፋኑ መጠን እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆነው ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋኑ እንዲሰጥ የተወሰነው፣ 96 በመቶ ያህል አስቀማጮች የተቀማጭ ገንዘባቸው መጠን የተጠቀሰውን ያህል ስለሆነ ነው። በዚህ መሠረት የመድን ሽፋኑ ይሰጣል። ይህ ውሳኔ አብዛኞቹን አስቀማጮች የሚሸፍን ነው።ባንኮች ለዚህ ዋስትና ሽፋን ተቀማጭ የሚያደርጉት በየዓመቱ ከጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘባቸው 02 በመቶ የሚሆነውን በማስላት ለፈንዱ ገቢ በማድረግ ተፈጻሚ ይሆናል። የተቀማጭ ገንዘብ ዋስትና ፈንድ አገልግሎት ሲጀመር ባንኮቹ የሚከፍሉት ክፍያ ይኖራል። የገንዘቡ መጠን ግን ገና አልተወሰነም ። 0507 ሪፖርተር ### Response:
### Text: የብድር ስርዓት ብሔራዊባንክ ባንኮች ብድር ለመስጠት መያዣ የሚጠይቁበት አሰራር እንዳለ ይታወቃል።ከዚህ ቀደም ዜጎች ቋሚ የሆነ ማስያዣ ሳያቀርቡ ከባንክ እንዲበደሩ ለማስቻል ስራዎች ተጀምረው እንደነበር መነገሩ ይታወሳል።አሁን ላይ ይህ ስራ ከምን ደረሰ የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ ለሸገርኤፍኤም 1021 ሬድዮ የሰጡት ቃል ተንቀሳቃሽ ዋስትና ሲስተም ዘርግተናል።ብዙ ነገሮች ከዚህ በፊት ተቀባይነት የሌላቸው የቁም እንስሳት እህል በግምጃ ቤት ውስጥ እህል እናስቀምጥና ርሲት እንይዛለን የመሬት አጠቃቀም የምንለው አለ ሶፋ ፍሪጅ ቴሌቪዥን ሌሎችም አሉ አስይዘን የምንበደርበት ሁኔታ ተፈጥሯል።ከዚህም ባለፈ ጭምር ሃሳብ ፋይናንስ የሚደረግበት ስርዓት ነው ይሄ ስለዚህ ሃሳቡን ወይም የሆነ ነገር ይዞ ከመጣ ያንን ያሳያል እንደ ከዚያ በኃላ ብድር ይሰጡታል ባንኮች ማለት ነው። ያን ሂደት አሁን ተጀምሮ ወደ 70 ሺህ በ ላይ ተመዝግቧል። ተንቀሳቃሽ ዋስትና አስይዘው ወደ 70 ተበዳሪ ተበድሯል። ከእውቀት ጋር ፣ ከ ጋር ተያይዞ የሚሰራ ስራ አለ፣ ለግብርና ወዘተ ከ5 ያላነሰ ብድር እንዲሰጥ መመሪያ አውጥተን እሱንም ተግባራዊ እያደረግን እንገኛለን። አሁን ባለን መረጃ ከ5 በላይ ሄዷል። ### Response:
### Text: እኔ ሰውን አከብራለሁ ነገር ግን እንዲህ መብቴን የሚጥስ ነገር ሲገጥመኝ ከማንም ፈቃድ አልጠይቅም ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳታዋቂው የኦሮምኛ ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ አዲስ አበባ ውስጥ በአንድ ጎዳና ላይ በመኪና እየተከተሉ ሲሰድቡኝ ነበር ካላቸው ሰዎች ጋር አለመግባባት ውስጥ ገብቶ እንደነበር ተናገረ።ሃጫሉ ማንነታቸው ካልታወቁ ሰዎች ጋር ሲነጋገርና ሌሎች ሰዎች ደግሞ ለመገላገል ሲጥሩ የሚያሳይ ቪዲዮ በማሕበራዊ መገናኛ መድረኮች ላይ በስፋት ሲዘዋወር ቆይቷል። ነገሩ የተከሰተው ሜክሲኮ አካባቢ በተለምዶው ኮሜርስ የተባለው ስፍራ ላይ እንደሆነ በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ይታያል።አንዳንዶች ድምጻዊው ጥቃት እንደተፈጸመበት ቢናገሩም በቪዲዮው ላይ እንደሚታየውና እርሱም እንደሚናገረው ስሜታዊ ከሚያደርጉ የቃላት ልውውጥ በስተቀር ጉዳት የሚያስከትል ጸብ አልነበረም።ክስተቱን በሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ ድምጻዊው ከመኪናው ወርዶ በሚናገርበት ጊዜ ሌሎች ሰዎች ለመገላገል ሲሞክሩና ሌሎች ሰዎችም በስፍራው ሲሰበሰቡ ይታያል። በተጨማሪም መኪናው የቆመው ሌሎች ተሽከርካሪዎች በሚያልፉበት ቦታ ላይ በመሆኑ መንገድ የተዘጋባቸው መኪኖች የጡሩምባ ድምጽ ይሰማል።ተጨማሪ ያንብቡ 10102 ### Response:
### Text: እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ሀገር ብንበተን እንኳን ሩጠን የምንሸሽበት ጤናማ ጎረቤት ሀገር የለንምየጋሞ የሀገር ሽማግሌአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የተቀበላቸውን ከ5ሺህ በላይ አዳዲስ ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት እንኳን ደህና መጣቹልኝ ብሏል። በሥነስርዓቱም ላይ የጋሞ አባቶች በሥፍራው ተገኝተው ለተማሪዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል እንዲሁም ምክርም ለግሰዋል።በመድረኩ ላይ የጋሞ አባቶችን በመወከል ንግግር ያሰሙት ጋሽ ሳዲቃ ስሜ እንደተናገሩት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች የነገዋ ኢትዮጵያ ተረካቢዎች በመሆናቹ የዘረኝነት እና ጎሰኝነት ሐኪሞች መሆን ከናንተ ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል።እኛ ኢትዮጵያውያን ማስተዋል ያለብን እንደ ሀገር ብንበተን እንኳን ሩጠን ለመሸሽ ጤናማ ጎረቤት ሀገርም የለንም ያሉት እኚው የሀገር ሽማግሌ ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ቆይታቸው ጋሞ በሚታወቅበት ፍጹም ኢትዮጵያዊ እሴት ውስጥ እንዲያልፉ ጥሪ አቅርበዋል።በዚህ የእንኳን ደህና መጣችሁ ዝግጅት ላይ ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ሙዚቃ ተጫዋቹ ድምጻዊ ሮፍናን ተገኝቶ ለተማሪዎች የህይወት ልምዱን አካፍሏል። ድምጻዊው ጋሞ ደሬ በተሰኘው ሥራው አካባቢውን በማስተዋወቁ ዕውቅና ተሰቶታል። ### Response: