text
stringlengths
707
989
### Text: ምን ነካውየሲዳማ ህዝበ ውሳኔ የድምጽ አሰጣጥን አስመልክቶ የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ አሉ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ እርሳቸው ያላሉት ነውበሀዋሳ ከተማ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገበዉ መራጭ ዉስጥ ከ90 በመቶ በላይ ድምጽ ሰጥቷል ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነትናትና በተካሄደዉ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ የድምጽ አሰጣጥ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የነበረዉ ሂደት በሰላም መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገለጹ፡፡በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ሁሉም ክፍለ ከተሞች ድምጽ ለመስጠት በመራጭነት ከተመዘገበዉ ህዝብ ከ90 በመቶ በላይ ድምጽ መስጠቱን በየምርጫ ጣቢያዎች እየወጣ ያለው ውጤት እንደሚያሳይም ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል፡፡በድምፅ መስጫው ቀን እንዲቋረጡ ተደርገዉ የነበሩ መንግስታዊ አገልግሎቶችና የንግድ እንቅስቃሴዎች ወደ መደበኛ ተግባራቸዉ መመለሳቸዉንም ተናግረዋል፡፡የሲዳማ ህዝበ ዉሳኔ በሀገሪቱ ለታየዉ የዴሞክራሲ ሂደት ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ቀድሞ የነበረውን አንድነታችንን በማጠናከር ከድህነት ለመዉጣት መተባበር ይኖርብናል ብለዋል ምክትል ከንቲባው፡፡ትክክለኛው መረጃ የፋና ብሮድካስቲንግ እና የ ነው ### Response:
### Text: ጅማ ዩኒቨርሲቲየጅማ ዩኒቨርስቲ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ያደረገባቸውን ተቋማት የፊታችን ቅዳሜ ሊያስመርቅ ነው።ተቋማቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸውንና ሙሉ ወጪያቸውን በመንግስት በጀት የተሸፈነ መሆኑን የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬለሜሳ ተናግረዋል፡፡በእለቱ ከሚመረቁት ውስጥ 30 ሺ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የጅማ የህክምና ማዕከል አንዱ ነው፡፡የህክምና ማዕከሉ ለጎረቤት አገራት ጭምር አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ የተገነባ ሲሆን ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚችል ሰምተናል፡፡75 ሺ 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈውና 40 ሺህ የእግር ኳስ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ስቴዲየምና የስፖርት አካዳሚ በእለቱ ይመረቃል ተብሏል፡፡አካዳሚው የኢትዮጵያ ስፖርት ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚረዳም ተነግሮለታል፡፡ዘመናዊ የኮንፍረንስና የሲቪክ ማዕከሎች እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች የሰለጠኑ ተማሪዎችም እንደሚመረቁ ታውቋል፡፡ተቋማቱ ትምህርት እንዲስፋፋ በማስቻል ምርምር እንዲካሄድና የማህበረሰብ አገልግሎት በማበርከት ዩኒቨርስቲው አገራዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ የሚያግዙ ናቸው ተብሏል፡፡ምንጭ ሸገር 1021 ፎቶ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ### Response:
### Text: አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከምርጥ 10 የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሆነ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ ውስጥ ካሉ ምርጥ 10 ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑን የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ አውጪ ተቋም ጥናት አመልክቷል። ተቋሙ ዓለማችን ላይ ያሉ ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎችን በ13 መስፈርቶች አወዳድሮ ደረጃ ያወጣል።ከመስፈርቶቹም መካከል ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ጥናት የማድረግ ብቃት፣ የቀጠና ደረጃን የጠበቀ ጥናት የማድረግ ብቃት፣ የማሳተም ብቃት፣ የመጽሐፍ አቅርቦት፣ ኮንፈረንሶችን የማካሄድ እና የዩኒቨርሲቲው ሳይት የመደረግ ብቃት ይገኙበታል።እያንዳንዱ ተቋም የተመዘነው ጥናት በማድረግ ብቃቱ እና በቀጠናው እና በዓለም ዙሪያ ያሉ የአካዳሚክ ማኅበረሰቦች በሰጡት ነጥብ እንደሆነ ተገልጿል።በደረጃው መሰረት ከ1ኛ እስከ 5ኛ የተቀመጡት የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ሲሆኑ የግብፁ ካይሮ ዩኒቨርሲቲ በ6ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጧል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ከደቡብ አፍሪካ፣ ግብፅ፣ ሞሮኮና ኡጋንዳ ዩኒቨርሲቲዎች ቀጥሎ በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና ዩኒቨርሲቲው ላስመዘገበው ውጤት ለዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ### Response:
### Text: በጊምቢ ወረዳ በተሽከርካሪ አደጋ የ13 ሰዎች ህይወት አለፈበምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ዛሬ ከረፋዱ አምስት ሰዓት አካባቢ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።በወረዳው ጆብር ቀበሌ ልዩ ስሙ 0ቡሉል በተባለ ስፍራ የደረሰው ይሄው አደጋ የታርጋ ቁጥር ኮድ 3 42548 ኦሮ ዶልፊን የህዝብ ማመላለሻ ከነቀምቴ ወደ ጊምቢ ከሚጓዝ የታርጋ ቁጥር ኮድ 3 58995 ኢት 0ከሆነ ተሳቢ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።በዞኑ ፖሊስ 0የትራፊክ ዲቭዥን ኃላፊ 0ሳጅን ጋጃሳ አሰፋ እንዳሉት በአደጋው 012 ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ አንድ ሰው ደግሞ ጊምቢ ከተማ አድቬንቲስት ሆስፒታል ለህክምና ከደረሰ በኋላ ህይወቱ አልፏል።ህይወታቸው ካለፈው መካከል አስር ወንዶችና ቀሪዎቹ ሴቶች ሲሆኑ ከነዚህም የዶልፊኑ አሽከርካሪና 0ረዳቱም ይገኙበታል። የጭነት ተሽከርካሪው ሾፌር 0እጁን ለፖሊስ መስጠቱን ሳጅን ጋጃሳ አመልክተዋል።የጊምቢ ከተማ አድቨንትስት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍራፍያድ ጉደታ እንደተናገሩት በአደጋው ህይወታቸው ካለፈው ሌላ ስምንት ሰዎች ከበድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከእነዚህም ሶስት ሰዎች በአስጊ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ### Response:
### Text: በቦሌ ኤርፖርት 12064000 ብር የሚያወጣ አደገኛ አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር ዋለመነሻውን ከብራዚል ሳኦፖሎ ያደረገ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር 507 በቀን 07032012 ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በዓለም አቀፍ መንገኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በጉምሩክ ኢንተሊጀንስ ሰራተኞችና በኢንተር ፖል አባል እንዲሁም በሰዓቱ ከነበረ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኛ ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል።በሰዓቱም አደንዛዥ ዕፁን ሲያዘዋውር የነበረው ግለሰብ ባራቱንደ ሞጆድ የፓስፖርት ቁጥሩ 505538358 የሆነ አሜሪካዊ ቀጣይ የጉሾ መዳረሻውም ህንድ የነበረ ግለሰብ በሻንጣው ውስጥ ሻግ በመስራት 52 ኪሎ ግራም በገንዘብ 12064000 ብር የሚገመት ኮኬይን እንደያዘ በቁጥጥር ስር ውሏል።አደንዛዥ ፅፁና አዘዋዋሪው መንገደኛምም በቁጥጥር ስር የዋለው በደረሰ መረጃና በተደረገ ክትትል ነው።ህገ ወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ ስራ የአገርን ሉዓላዊነት ለአደጋ የሚያጋልጥ የማህበረሰቡን ማህበራዊ ህይወት የሚያቃዉስና የተረጋጋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዳይኖር የሚያደርግ በመሆኑ ህዝቡ እንደዚህ አይነት ህገ ወጦች ሲያጋጥሙ የሚደርገዉን ጥቆማ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት የገቢዎች ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡የገቢዎች ሚኒስቴር ### Response:
### Text: አዲስ የታተሙት የብር ኖቶች አይነት፣ የደህንነት መጠበቂያ ምልክቶች እና ምስሎች ተከታታይ ቁጥሮች የገንዘቡ ቁጥሮች በሚያጎላ ማሽን ሲታዩ ከጥቁር ወደ አረንጓዴ ፍሎረሰንት ቀለም ይለወጣሉ።ማየት ለተሳናቸው እውቅና ምልክት የብሩን ዋጋ የሚገልፅ ማየት የተሳናቸው በእጅ ዳሰሳ ማወቅ የሚችሉበት የደህንነት መጠበቂያ ምልክት አለው።ጎርባጣ መስመሮች የባንክ ኖቱ ሲዳሰስ የመጎርበጥ ስሜት እንዲሁም የኖቱ ዋጋ ይታያል።ደማቅ አንፀባራቂ ምልክት ገንዘቡ ወደ ላይ ወይም ወደታች ሲዞር የሚንቀሳቀስ ደማቅ የቀለም ፍንጣቂ የደህንነት መጠበቂያ ምልክት።የደህንነት መጠበቂያ ክር የሚሽከረከር ደማቅ ቀለም ኮከብ አዲስ የደህንነት መጠበቂያ ክር በክሩ ውስጥ ፣ ኢብባ እና የገንዘቦቹ አይነት ተፅፎ ይገኛል።የውሃ ምልክት ገንዘቡ ወደ ብርሃን አቅጣጫ ተደርጎ ሲታይ በላዩ ላይ ከሚገኘው ምስል ፊት ለፊት ተመሳሳይ ደብዛዛ የውሃ መልክ ያለው ምልክት ይታያል።ትይዩ ምልክት የብር ኖቶች ከብርሃን አቅጣጫ ሲታዩ ኳስ መሳይ ምልክት ከገንዘብ በስተኃላው ካለው ተመሳሳይ ጋር በፍፁም ትይዩ ሆነው በአንድ ቦታ ላይ ያርፋሉ።ፈሎረሰንስ ምልክት አንበሳው ምስል ራስ ላይ አልትራቫዮሌት ጨረር ሲበራበት ወደ ቢጫነት የሚለወጥ ፍሎረሰንት ምልክት። ### Response:
### Text: ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶር ሙሉ ነጋ ለተማሪዎች ሊሰጥ ስለታሰበው የተከታታይ ምዘና ተከታዩን መረጃ አግኝቷል ተማሪዎች ከሚማሩበት ተቋም የሚላክላቸውን የኮርስ ማቴሪያሎች በማንበብ ለቀጣይ ስራ ዝግጁ እንዲሆኑ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይቷል ይህ ስራ በምዘና መደገፍ ስላለበት ነው ውሳኔው የተላለፈው። ተማሪዎች በቤታቸው ሆነው የሚላክላቸውን የኮርስ ማቴሪየሎችን ይበልጥ እንዲየነቡ ለማድረግ ፣ ያነበቡትንም ለመመዘን እስከ 30 ተከታታይ ምዘና ይሰጣቸዋል። ከ30 የሚያዘው ምዘና ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲዎች ተከፍተው እስኪመለሱ ድረስ ከትምህርታቸው እንዳይርቁ ለማነሳሳትም ጭምር ነው። ተማሪዎች የሚያነቡትን ማቴሪያል ከ30 ቤት ውስጥ ሆነው በሚሰሩት አሳይመንት ይመዘናሉ ይህ ማለት ተማሪዎች የሚወስዱትን ኮርስ 30 በቤታቸው ሆነው ይጨርሳሉ ምዘናው እንደየዩኒቨርሲቲው ሊለያይ ይችላል ከ5 ፣ 10 እያደረጉ መጨረስ ይችላሉ የተቀረው 70 ደግሞ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመለሱ የሚወስዱት ምዘና ይሆናል። ተማሪዎች ትምህርት የሚያስፈልጋቸው ለራሳቸው መሆኑን አውቀው የሚላክላቸውን ማቴሪያሎች ተግተው እንዲያነቡት መልዕክት ተላልፏል።ሁሉንም የመንግስት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ይመለከታል ### Response:
### Text: አፋር ክልል የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።የአፋር ክልል አደጋ ስጋት ጽቤት በክልሉ ውስጥ የተፈናቃይ ተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን አስታውቋል።ጦርነቱ ተስፋፍቶ በቀጠለባቸው ባለፉት 3 ሳምንታት በአፋር የተፈናቃዮች ቁጥር ወደ 300 ሺህ ማሻቀቡን ፅቤቱ ለዶቼቨለ ሬድዮ በሰጠው ቃል ገልጿል።የአፋር ክልል አደጋ ስጋት ጽቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ጦርነት ቀጠና ውስጥ የዞን 2 በርሃሌ አለ እንዲሁም ከዞን 2 ጀምሮ ያለው እዋ አውራ እንዲሁም ጭፍራ ዞን አንድ ደግሞ ሐዳር እያለ ወደ ዞን አምስትም ይሻገራል። ስለዚህ በአጠቃላይ አሁን ያለን የተፈናቃይ ቁጥር ከ300000 በላይ ይደርሳል ብለዋል።በዚሁ ጦርነት የተፈናቀሉትን የተሻለ ደህንነት ወዳለበት አከባቢዎች እንዲጠጉ እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።ጭፍራ አከባቢ የነበሩት 60 ሺ ገደማ ተፈናቃዮች ወደ ሚሌ አቅጣጫ 50 ኪሜ ያህል ርቀት ላይ በተገነባ መጠለያ እየተረዱ መሆናቸውን ፅቤቱ አሳውቋል።ለተፈናቃዮቹ ለመድረስ መንግሥት እና የርዳታ ተቋማት ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም በቂ እንዳልሆነ ተገልጿል።እስከ ከሚሴ አዋሳኝ ወረዳዎች ከ13 ሚሊየን የማያንስ ሕዝብ የጦርነ ገፈት ቀማሽ መሆኑንም የአፋር ክልል አደጋ ስጋት ጽቤት ለሬድዮ ጣቢያው አሳውቋል። ### Response:
### Text: ፍሬወይኒ መብራቶም የ2019 ምርጥ አስር ውስጥ ገብታለች፡፡ ለዚህም የበቃችው የሚታጠብና መልሶ ጥቅም ላይ መዋል የሚችል የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ ሞዲየስ በመስራቷና ሴቶች ተማሪዎች ተፈጥሯዊ በሆነው የወር አበባ ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ በምትሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዋ ነው፡፡ እንደ ዩኒሴፍ ጥናት በኢትዮጵያ ከ10 ሴቶች አንዷ በዚህ ምክንያት ትምህርቷን ታቋርጣለች፡፡ ፍሬወይኒ ይህንን ውድድር ካሸነፈች 100000 የአሜሪካን ዶላር አሸናፊ ትሆናለች፡፡ምረጧት 10 የድምጽ አሰጣጥ ሂደት1 ሊንኩን ማስፈንጠሪያውን መጫን። ከተጫን ነው ቡሃላ ውደድ የ የአመቱ 10 ጀግኖች ዝርዝር እንግርባለን ከዛ የፍሬወይን መብራቶም ስምችና ፎቶዋ ዜግነት የሚል ፈልገን እንጫናለኝ።2 የሷን ፎቶ ከተጫንን ቡሃላ ዝቅ ብለን ከሷ ፎቶ በታች 1 0 ቁጥር ይኖራል ከሚለው በላይ ከሚለው በታች የለቸውን መሳቢያ ወደቀኝ በመሳብ 10 ድምጽ መስጠት ይችላሉ።3 የሚለውን ከተጫንን ቡሃላ ያለን ብቻ ነው የምን መርጠው ከላይ አንብባቿል ዲስኮርሱን የሚል ሲመጣ ማንበብ ወይም አንቢብያለሁ ማለት ከዛ ይጠይቀናል እናስገባና ማረጋገጫውን እንጫን ከዛ አበቃ።ማሳሰቢያ ሁሉም ሰው በየቀኑ 10 ድምጽ መስጠት ይችላል። ማብቂያው ህዳር 21 ነው፡፡ ቲክቫህኢትዮጵያ ### Response:
### Text: የስልክ ስክሪን ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው ፈሳሽ ዕውቅና የለውም ተባለበየመንገዱ የስልክ ስክሪን ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ስላለው ፈሳሽ የሚያውቀው ነገር አለመኖሩን የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለሥልጣን አስታወቀ።ናኖ ቴክኖሎጂ ማለት ዘረፈ ብዙ ቴክኖሎጂዎችን በውስጡ የሚይዝ መሆኑም ተገልጿል። የሞባይል ስልክ ስክሪን ማጠንከሪያ ተብሎ ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው ፈሳሽ መፈተሽ እንዳለበት የባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አወቀ ሺፈራው ተናግረዋል።በፍተሻውም ወቅት በስልክ ገጽ ላይ የሚቀባው ፈሳሽ ጨረራ አለው ወይስ የለውም የጨረራ ይዘቱ ምን ያህል ነው የሚለው ፍተሻ እንደሚደረግበት ገልጸዋል።በፍተሻው ውጤት መሠረት ጨረራ አመንጪ ከሆነ ደግሞ መጠኑ ከዚህ በላይ ከሆነ ጉዳት አለው፣ ከዚህ በታች ከሆነ ደግሞ ጉዳት የለውም የሚለውን በሳይንሳዊ ትንታኔ መሠረት መናገር ይቻላል ይህ ባልታወቀበት ሁኔታ ግን ይህ ነው ብለን መናገር አንችልም በማለት አብራርተዋል። አያይዘውም፣ በተቋማችን አሠራር አንድ ጨረር አመንጪ ቁስ አካል ወደ አገር ውስጥ ሲገባ አስመጨዎቹ ያመጡትን ነገር ወደ ተቋማችን አምጥተው የማሳወቅ ግዴታ እንዳለባቸው ሕጉ ያስገድዳል። 12102 ኢቲቪ ### Response:
### Text: የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓም ባካሄደው 6ኛ ዙር፣ 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ አስቸኳይ ስብሰባ አስቸካይ ጥሪ ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡ውሳኔዎቹ ከላይ የተዘረዘሩ ሲሆን ከውሳኔዎቹ መካከል የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጡ ከተፈቀደላቸው ተቋማት ውጭ በሁሉም ከተሞች ከምሽቱ 2፡00 በኋላ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም ተብሏል።ከሚሰጡት አገልግሎት አስፈላጊነት አኳያ እየተመዘነ የሚወሰን መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ማንኛውም የመንግስት ተቋም መደበኛ አገልግሎቱን አቋርጦ በጀቱን ጨምሮ ሁሉንም ነገር የገጠመንን የህልውና ዘመቻ ለመቀልበስ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲረባረብ ተወስኗል።ሁሉም የመንግስት ተሸከርካሪ ወደ አንድ ማዕከል በማሰባሰብ ለሕልውናው ዘመቻ አገልግሎት እንዲውል እንዲደረግ ተብሏል።የግል ተሸከርካሪ ባለቤቶች ለሕልውና ዘመቻው ስኬት ሲባል በተፈለገ ጊዜ ሁሉ ተሸከርካሪዎቻቸውን በመስጠት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ተወስኗል።በየደረጃው የሚገኝ አመራርም የሕልውና ዘመቻውን ተቀብሎ የሚሰለፈውን ሕዝብ አደራጅቶ ከፊት ሆኖ እየመራ ወደ ግንባር እንዲዘምት ይህን በማያደርጉ አመራሮች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተወስኗል። ሙሉ ውሳኔዎችን ከላይ ያንብቡ ### Response:
### Text: ሼር ሆስፒታሉ ነጻ ቀዶ ህክምና ሊሰጥ ነው የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፊት እና የአፍ ውስጥ የቀዶ ህክምና ተደራሽ ለማድረግ በማሰብ ከጥቅምት 3142012 ዓም ከካናዳ ቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ በሚመጡ የፊት እና የአፍ ውስጥ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስቶች ከአአ ዩኒቨርሲቲ የፊት እና የአፍ ዉስጥ የቀዶ ህክምና ትክፍል ጋር በመተባበር የነጻ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ስለሚሰጥ የሚከተሉትን የህክምና አይነቶች ችግር ያለባችሁ ታካሚዎች እንድትመዘገቡ እና የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳውቃለን፡፡መመዝገብ የሚችለው የህመም አይነቶች የመንጋጋ መገጣጠሚያ እና የአፍ አለመከፈት ችግር የፊት አካባቢ የነርቭ ህመም የፊት አካባቢ እና የአፍ ውስጥ እባጮች ካንሰርን ጨምሮ የምራቅ አመንጪ እጢዎች ህመሞች የፊት እና የመንጋጋ አጥንት ስብራት የፊት አጥንቶች እድገት አለመመጣጠን እና የፊት መጣመም ችግር የፊት እና የመንጋጋ አጥንቶች በተፈጥሮዊና በጉዳት የሚከሰቱ የገጽታ ችግሮች መመዝገቢያ ቦታዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻሊዝድ ሆስፒታል ኦፒዲ ቁ14 0913572592 ዶር ግዛቸውበአአ ዩኒቨርሲቲ የጥርስ ህክምና ትቤት 0913838118 ዶር ህይወት 0912855802 ዶር ገላነ ይህንን እድል የሚጠብቁ ብዙዎች አሉና ሼር ያስድርጉ ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ በ15 ቀናት 139 ዜጎቿን በኮቪድ19 አጥታለች ሀገራችን ኢትዮጵያ ከመስከረም 122013 እስከ ዛሬ መስከረም 272013 ዓም ባሉት ቀናት 139 የውድ ዜጎቿን ህይወት በኮሮና ቫይረስ አጥታለች።ከ15 ቀናቱ ውስጥ ከፍተኛው ሞት የተመዘገበው በመስከረም 122013 19 ሰዎች ሲሆን ሁለተኛው ከፍተኛ ሞት ደግሞ ዛሬ መስከረም 272013 ዓም 17 ሰዎች ተመዝግቧል።የሰው ልጅ ህይወት ዳግም አይተካም በየዕለቱ ሰዎች ሲሞቱ መቁጠር ለኛ ቀላል ሊመስል ይችላል ነገር ከነዚህ ውድ ከሆኑ የሰው ልጆች ጀርባ ስንት ቤተሰብ፣ ተስፋ ፣ እቅድ ፣ ዓላማ፣ ጓደኛ ፣ ወዳጅ ፣ ዘመድ ይኖራል መዘናጋታችን ፣ መሰላቸታችን ሀዘን ቤታችን ስላልገባ ይሁን በየዕለቱ ከሚሞቱ ሰዎች ጀርባ ስንት ቤተሰብ ይሁን የተበተነው ስንት እናት አባት ይሁኑ ተስፋቸውን ልጆቻቸውን ተነጥቀው በመሪር ሀዘን ውስጥ የሚገኙት ስንት ሰው ይሁን የሚወደውንና የሚሳሳለትን ወዳጁን ከጎኑ ያጣው ለአንድ ደቂቃ እንኳን እራሳችንን በሌሎች ወገኖቻችን ቦታ አድርገን እንመልከት ያን ማድረግ ካልቻልን ህመሙ ፣ ሀዘኑ ፣ ጉዳቱ ፈፅሞ አይሰማንም።ለሰዎች ሞትና ስቃይ ምክንያት አንሁን እራሳችንን በተቻለን አቅም ሳንሰላች፣ ሳንዘናጋ እንጠብቅ። ዛሬም ኮቪድ19 ገዳይ ነውነፍስ ይማርቲክቫህ ኢትዮጵያ መስከረም 272013 ዓም ### Response:
### Text: አሜሪካውያኑ የኅብረተሰቡን የፖለቲካ አደረጃጀት ጨምሮ የራሳቸውን ፍላጎት ለመጫን ሞክረዋል ግን አልተሳካላቸውም ቭላድሚር ፑቲንየሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የአፍጋኒስታን የ20 ዓመት ዘመቻ በአሳዛኝ ሁኔታ አብቅቷል ዋሽንግተን ምንም አላገኘችም ሲሉ ተችተዋል፡፡የአሜሪካ ጦር በአፍጋኒስታን ውስጥ የነበረው ቆይታ ከንቱ ነበር ሲሉም ተችተዋል።ፑቲን ከወጣቶች ጋር ባደረጎት ስብሰባ እንደተናገሩት የአሜሪካ ወታደሮች በአፍጋኒስታን ለ 20 ዓመታት ኖረዋልና በእነዚህ 20 ዓመታት ውስጥ የአካባቢውን ህዝብ ሥልጣኔ ለማሳደግ ሳይሆን የኅብረተሰቡን የፖለቲካ አደረጃጀት ጨምሮ የራሳቸውን ፍላጎት ለመጫን ሞክረዋል ግን በእውነቱ አልተሳካላቸውም ብለዋል።ፑቲን የትኛውንም ህብረተሰብ ላይ ቢሆን ከውጭ ማንኛውንም ነገር መጫን አይቻልም ነው ሲሉ ገልፀዋል።የሩሲያው መሪ ምዕራባውያን አገሮችን እሴቶቻቸውን በምዕራባዊ ባልሆኑ ሀገሮች ላይ ለመጫን በመሞከራቸው ትልቅ ውድቀት ገጥሟዋል ሲሉ አጣጥለዋቸዋል፡፡ያንን ለሚያደርጉት አሜሪካ እና በአፍጋኒስታን ለሚኖሩ ሰዎች የበለጠ ውጤቱ እጅግ አሳዛኝ ፣ ከባድ ኪሳራ፣ ድምር ውጤቱም ዜሮ ነው ብለዋል ፑቲን።መረጃውን አልጀዚራን ዋቢ አድርጎ ያሰራጨው ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ነው። ### Response:
### Text: የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት️ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓም ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይአህመድ ድጋፍ ለመስጠት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በተዘጋጀ ሰልፍ ላይ ቦምብ በማፈንዳት የተጠረጠሩት ግለሰቦች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ፍርድ ቤት ቀረቡት አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ፣ሁለተኛ ብርሀኑ ጃፋር፣ ሶስተኛ ጥላሁን ጌታቸው ፣ አራተኛ ባህሩ ቶላ እና አምስተኛ ደሳለኝ ተስፋየ ናቸው፡፡ከአንደኛ እሰከ አራተኛ ያሉት ተከሳሾች በፀረ ሽበር አዋጅ 6522001 አንቀጽ 31 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን በማደራጀት ክስ የመሰረተባቸው መሆኑ የታወሳል፡፡ሆኖም ግን ጥቅምት 14 2011 ዓም በነበረ ቀጠሮ ክሱ ላይ ወንጀል የተፈፀመበት ጊዜና ቦታ ግልፅ አለመሆኑ፣ ወንጅሉን አለመፈፀማቸውን እና መንግስት ያመጣውን ለውጥ ተቀባይ እንጅ ተቃዋሚ አለመሆናቸውን በመቃውሚያ ሀሳብ ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተከሳሾች ላቀረቡት የክስ መቃወሚያ ሀሳብ መልስ ለመስጠት ዛሬ ችሎት የተገኘ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ለህዳር 7 ቀን 2011 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ አስታውቋል፡፡ምንጭ ፋና ብሮድካስት ### Response:
### Text: በፌደራሊዝም ስርዓትና በኢፌዴሪ ህገ መንግስት ዙሪያ የሚያተኩር የምሁራን የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። መቐለ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ምሁራን ተሳትፈዋል።የውይይት መድረኩ ነፃ ሃሳብ የሚንፀባረቅበትና በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውይይት የሚደረግበት መሆኑን የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ተናግረዋል።ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም መሰል መድረኮችን ማዘጋጀቱን የገለጹት ፕሮፌሰር ክንደያ በዚህም ሀገሪቱ የምትከተለውን የፌደራል ስርዓትን የሚያጠናክሩ ሃሳቦች መገኘታቸውን አስታውሰዋል።በውይይት መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የፖለቲካ ምሁርና ተንታኝ ፕሮፌሰር ህዝቄል ገቢሳ የፌዴራል ስርዓት የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ጥያቄ የመለሰ ስርዓት መሆኑን ተናግረዋል።ከዚህ ስርዓት በተፃራሪ መሄድ ሀገሪቱን ወደ አልተፈለገ ሁከትና ብጥብጥ ሊያመራት ይችላል የሚል ሀሳብ አስቀምጠዋል።ህግ መንግስቱ እንዲሻሻል ጥያቄ የሚያቀርቡ አካላት መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ህዝቄል የሚነሱ ጥያቄችን ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ መመለስ እንደሚቻል አብራርተዋል። ቀን ሃምሌ 42011 ዓም ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምቤት አፈጉባዔ ለቦርዱ ያቀረበው የሕዝበ ውሣኔ ማደራጀት ጥያቄ ላይ ውሣኔ አሳለፈ ነሐሴ 122014 የፌዴሬሽን ም ቤት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከ6 ዞኖችን እና 5 ልዩ ወረዳዎችን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በ3 ወር ህዝበ ውሳኔ በማድረጃት ውጤቱን ለምክርቤቱ እንዲያሳውቅ ብሎ ነበር።ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለምክር ቤቱ ምላሹን ሰጥቷል። ምላሹ የህግ አግባብን ተከትሎ የተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።ለህዝበ ወሳኔ የሚወስደውን ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ የመወሰን ፣ የመርሀ ግብር ሰሌዳ የማዘጋጀት የማፅደቅ እንደ አስፈላጊነቱ የማሻሻል እና የማስፈፀም ስርልጣን የተቋሙ ብቻ መሆኑን ምርጫ ቦርድ አስገንዝቧል።ከቦርዱ ምላሽ ቦርዱ ለዚህ ጉዳይ አፈፃፀም የሎጂስቲክስ ዝግጅት ለማድረግ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላ እና ምደባ ለመተግበር፣ የምርጫ ፀጥታ ጉዳይን ለመገምገም፣ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ ጣቢያዎች ለማደራጀት፣ ለታዛቢ ሲቪል ማህበራት ፈቃድ ለመስጠት እና በጉዳዩ ላይ የሚያገባቸውን ባለድርሻ አካላት ለማወያየት የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ ለምክር ቤቱ እንደሚገልፅ ከአክብሮት ጋር እናሳውቃለን። ቦርዱ ያሳለፈው ውሳኔ ከላይ ተያይዟል ### Response:
### Text: ጭልጋ ችግሩ የተፈጠረው ቅማንት ኮሚቴውን መያዝ መቻል አለብን ወንጀለኛ ነው ብሎ ነው እያሰማራ ያለው ይሄን ፋኖ ወደ 8 9 ሰው ሞቶብናል 78 ሰው ቁስለኛ አለ።ፋኖ የሚባለው እራሱን የቻለ ልብስ ነው ያለው። ፋኖ ነው የሚለው የቅማንት ማህበረሰብ አባል ፋኖ የሚባል ጦር የለም እውነታው ይሄ ነው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ በክልሉ ውስጥ በህዝቦች መካከል ግጭት እንዲነሳ ለማድረግ አጀንዳ ይዞ የሚሰራ ኃይል አለ። ይሄ ኃይል አሁን ፅንፈኛ የቅማንት ኮሚቴ አባላት ክልሉን ማተራመስ እንዲችሉ ማስታጠቅ ነው አንደኛው ባለፉት አመታት እኔም ወደዚህ ቢሮ ከመምጣቴ በፊት ጄነራል አሳምነው በነበረ ጊዜም ከዚያም በፊት ሌሎች ቢሮ ኃላፊዎች በነበሩ ጊዜ ግጭት ነበር። ስለዚህ እዚህ ቢሮ ያለ ሰው በሙሉ ለቅማንት ፅንፈኛ ኮሚቴ ጠላት ነው። ጄነራል አሳምነው ነበር ጠላት ነው ከዚያ በፊት አቶ ደሴ አሰሜ ነበር ጠላት ነው ከዚያ በፊት አቶ እዘዝ ዋሴ ነበር ጠላት ነው አሁን ደግሞ እኔ መጣሁ ጠላት ነኝ ስለዚህ አጀንዳ መቅርፅ ነው። እዚህ ቢሮ ላይ የምንመደብ ሰዎች ህግና ስርዓት ለማስከበር በምናደርገው እንቅስቃሴ ስም ማጥፋት ነው ስም ማብጠልጠል ነው። የአማራ ክልል ሰላምና ግንባታ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘው ተሻገር ### Response:
### Text: ዋልታ ሰራተኞቹን ከስራ አሰናበተበዋልታ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ኮርፖሬት የፌስ ቡክ ገጽ ታህሳስ 3 ቀን 2012 ዓም ከትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፂዮን ገሚካኤል ጋር በተያያዘ ከተቋሙ እውቅና ውጭ በተላለፈ መረጃ ተቋሙ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባላቸው ሶስት ሰራተኞች ላይ ከሥራ ከታገዱበት ቀን ጀምሮ የሥራ ስንበት ውሳኔ አስተላልፏል። ተቋሙ ከሥራ አግዷቸው ከነበሩት አራት ሰራተኞች መካከል ከባድ የሙያ ላይ ቸልተኝነት በማሳየት ስህተቱ እንዲፈጸም ሚና የነበራቸው ሰራተኞች ላይ በተቋሙ መመሪያ እና ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል፡፡በዚህ መረትም፡ 1 የአይቲ፣ ዲጅታል ሳይኔጅ እና ስቱዲዮ ኦፕሬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የነበሩት፣ 2 የድረገጽ አርታኢ የነበሩት እና3 የድረገጽ ረዳት አዘጋጅ የነበሩት ሰራተኞች ከሥራ ተሰናብተዋል።በተጨማሪም አንድ አመራርም ከኃላፊነታቸው እንዲነሱና ዝቅ ብለው እንዲሰሩ ተወስኗል ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ ተወስኗል፡፡ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ መሆኑንና ከዚህ ጋር በተያያዘ ፖሊስ በምርመራ ሂደት በቁጥጥር ስር አውሎ ሲመረምራቸዉ የነበሩት ሰባት ተጠርጣሪዎች በአራት ሺህ ብር ዋስ ከሁለት ቀን በፊት መለቀቃችው ይታወሳል። ### Response:
### Text: ከወራት በፊት የጀመረው ምርመራ ተጠናቋል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ኢሰመኮ ምርመራ ቡድን በትግራይ ያካሄዱትን የመስክ ስራ አጠናቀዋል።ሁለቱ ተቋማት የመስክ ምልከታ አድርገው መረጃዎችን ቃለመጠይቆችን እና ሌሎች አስፈላጊ ማስረጃዎችን የመሰብሰብ ስራዎችን ማጠናቀቃቸውን ተገልጿጻ።የመስክ ምርመራ ስራው የተካሄደው በመቐለ ውቅሮ ሳምረ አላማጣ ቦራ ማይጨው ዳንሻ ማይካድራ ሁመራ ጎንደር ባህርዳር እና አዲስ አበባ ከተሞች ነው።ተቋማቱ የጋራ ምርመራቸውን ያካሄዱት ከፈረንጆቹ ግንቦት 16 አስከ ነሀሴ 20 ቀን 2021 ድረስ ሲሆን ከ200 በላይ ሰዎችን ቃለመጠይቅ አድርገዋል።በሁለቱ የጋራ ተቋማት የመስክ መርማሪዎች በአደጋው የተጎዱ ሰዎችን የአይን ምሰክሮች የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ሰራተኞችን የክልል እና የፌደራል ተቃማት ሰራተኞችን እና አመራሮችን የህክምና ባለሙያዎችን የፍትህ አካላትን እና ሌሎች ስለ ጉዳዩ ያውቃሉ የተባሉ አካላትን እና ተቋማትን ሁሉ ቃለመጠይቅ አድርገዋል።ከዚህ በተጨማሪም የምስል እና የዶክመንት ማስረጃዎችን ቪዲዮዎችን እና ሌሎች ለምርመራ ይጠቅማሉ የተባሉ መረጃዎችን ሁሉ አሰባስበዋል።በአካባቢዎቹ የደህንነት ችግር መኖሩ ለምርመራ ስራው እንቅፋት እንደሆነባቸው ገልፀዋል። ### Response:
### Text: በጎንደር ከተማ ዙሪያና አጎራባች ወረዳዎች ተከስቶ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የእለት እርዳታ ስርጭት መጀመሩን የማእካዊ ጎንደር አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ መንበሩ አውደው እንደተናገሩት አስቸኳይ የእለት እርዳታው ከትናንት በስቲያ ጀምሮ አርባባ ግንድ መጣያና አምቦ በር በተባሉ መጠለያዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች እየተሰራጨ ነው፡፡ የእለት እርዳታ ስርጭቱም በመጠለያዎቹ ለሚገኙ 3ሺ 187 አባወሯዎችና ቤተሰቦቻቸው 500 ኩንታል የሚጠጋ የምግብ እህል መከፋፈሉን ገልፀዋል።በቀጣዮቹ ቀናትም ለ2ሺ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የእለት እርዳታ ማሰራጨት እንዲቻል በመጋዘን የሚገኘውን የአደጋ ጊዜ የመጠባበቂያ እህል ክምችት ወደ መጠለያ ጣቢዎቹ የማጓጓዝ ስራ እየተካሄደ ነው፡፡በተጨማሪም በመጠለያዎቹ ለሚገኙ ህጻናት፣ አጥቢ እናቶችና ነብሰ ጡር እናቶች አልሚ ምግብን ጨምሮ የምግብ ዘይት ፣ ፓስታና ማኮሮኒ እንደሚቀርብ ሃላፊው ተናግረዋል፡፡በተለይም አርባባ በተባለው መጠለያ ጣቢያ ባለፈው አመት ለተፈናቃዮች ተዘጋጅተው የነበሩትን የንጹህ መጠጥ ውሃና መጸዳጃ ቤቶችን በተሟላ መንገድ ወደ አገልግሎት ለማስገባት የሚያስችሉ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ ### Response:
### Text: ተፈፀመ የተወዳጁ ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ።የድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ በመንበረ ጸባኦት ቅድሥተ ሥላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል።ከሥርዓተ ቀብሩ ቀደም ብሎ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ ዘመድ ወዳጆች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና አድናቂዎቹ በተገኙበት በመኖሪያ ቤቱ እና በወዳጅነት ዐደባባይ የአስከሬን ሽኝት ተካሂዷል፡፡በመንበረ ጸባኦት ቅድሥተ ሥላሴ ካቴድራል በነበረው የቀብር ስነሥርዓት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ፣ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ፣ የድምፃዊው ቤተሰቦች የስራ ባልደረቦች ፣ ጓደኞች ፣ ወዳጆች ፣ አድናቂዎች ተገኝተው ነበር።መስከረም 17 ቀን 2015 ዓም ህመም ተሰምቶት ወደ አንድ ክሊኒክ ከሄደ በኃላ ህይወቱ ያለፈው ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ የአንዲት የ17 ዓመት ሴት ልጅ አባት ነበር። ከድምፃዊ ማዲንጎ አፈወትቅ ህልፈት ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የገለፀው ፖሊስ ምርመራው እንደተጠናቀቀ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ መግለፁ አይዘነጋም። ### Response:
### Text: ስለ ነገው የአዲስ አበባ ሰልፍ ከመምህር ስዩም ተሾመበነገው እለት በመስቀል አደባባይ በሚካሄደው ታላቅ ህዝብዊ ሰልፍ ላይ ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር መፈጠር የለበትም፡፡ ትላንት ማታ ከፌደራል ፖሊስ፣ አዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች፣ እንዲሁም ከደህንነት መስሪያ ቤት ተወካይ ጋር ውይይት አድርገናል፡፡እውነት ለመናገር ወደ ስብሰባ አዳራሹ የገባሁት በጥፍሬ እየተራመድኩ ሲሆን ስወጣ ደግሞ እንደ አይጥ ላሽ ብዬ ነው፡፡ ሆሆ ሃሳባቸውን ቢቀይሩስ ሃሃሃ ለማንኛውም የተጠቀሱት የፀጥታ ሃላፊዎች የአስተባባሪ ኮሚቴውን ምን እንርዳችሁ እንዴት እንደግፋችሁ ያሉን ሲሆን እኛም በሰልፉ ላይ ምንም አይነት የፀጥታ ችግር እንዳይከሰት ድጋፍ ያደርጉልን ዘንድ ጠይቀናል፡፡ በእርግጥ 9999 የሚሆነው ተሳታፊ በሰላማዊ መንገድ ሃሳብና አስተያየቱን በነፃነት ለመግለፅ ነው፡፡ ሆኖም ግን፣ ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው ግጭትና ሁከት ለማስነሳት ጥረት የሚያደርጉ ግለሰቦች አይጠፉም፡፡ ስለዚህ ማህብረሰቡ እንዲህ ያለ እኩል ወይኧረ እኩይ ነው ዓላማ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ወዲያውኑ በአከባቢው ለሚገኙ ፖሊሶች ወይም የዝግጅቱ አስተባባሪዎች መጠቆም በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ የአስተባባሪ ኮሚቴ ### Response:
### Text: ኢሰመኮ ሃምሌ 3 እና 4 2013 ዓም መተከል ዞን ቡለን ወረዳ በምትገኘው ኢማንጅ ቀበሌ በተከሰተ ግጭት ቢያንስ 16 ሰዎች መገደላቸውን መረጃ እንደደረሰው አሳውቋል።ኮሚሽኑ መረጃው ከደረሰው ጀምሮ ክትትል ሲያደርግና ከአካባቢ የፀጥታ እና አስተዳደር ኃላፊዎች ጋር ሲነጋገር መቆየቱን ገልጿል።ሃምሌ 4 ከአንድ ቀን አስቀድሞ በታጠቁ ኃይሎች ስለመገደላቸው በሚነገር አንድ የኢማንጅ ቀበሌ ነዋሪ የቀብር ስነስርኣት ወቅት በተከሰተና የአፀፋ ስለመሆኑ በሚነገር ጥቃት 15 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።በተጨማሪም ከማሽ ዞን በምንጅጋ ወረዳ ሃምሌ 8 በደምቤ ቀበሌ ሌሎች 8 ነዋሪዎች በታጠቁ ኃይሎች ከተገደሉ በኃላ ስጋት ያደረባቸው ከ4 ሺህ ያላነሱ የቀበሌው ነዋሪዎች ተፈናቅለው ምጅንጋ በሎይጂንጋፎይ ወረዳ ተጠልለው እንደሚገኙ ኢሰመኮ ገልጿል።ኢሰመኮ መግለጫውን እስካወጣበት ሰዓት ድረስ የመሳሪያ ድምፅ ይሰማ እንደነበርና የፀጥታ ኃይሎችም ወደቦታው እንዳልደረሱ አሳውቋል በምጅንጋ ተጠልለው ለሚገኙ ነዋሪዎች ጥበቃ እንዲደረግ አሳስቧል።ኮሚሽኑ የክልሉ ሰላም እንዲሁም ደህንነት በዘላቂነት ለመመለስ አጥፊዎችን በአፋጣኝ ለህግ ማቅረብ ፣ የነዋሪዎችን ሰላም እና ደህንነት በተሟላ መልኩ ማረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆነም አሳስቧል። ### Response:
### Text: በሽብርተኛነት የተፈረጀው ህወሀት ከያሎ እና ጎሊና ወረዳዎች ተፈናቅለው ጋሊኮማ ጤና ጣቢያ እና ትምህርት ቤት ተጠልለው በነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች ላይ ጥቃት ፈፀመ ሲል የክልሉ መንግስት ገለፀ።ቡድኑ በአፋር ክልል በፈንቲ ረሱዞን በኩል ጥቃት በመክፈቱ ምክንያት ከያሎ እና ጎሊና ወረዳዎች ከቤት ንብረታቸው በመፈናቀል በጎሊና ወረዳ ጋሊኮማ የምትባል ቀበሌ በጤና ጣቢያ እና ት ቤት ጊዚያዊ መጠለያ ውስጥ ተጠልለው የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደር ማህበረሰብ ላይ በከባድ መሳሪያ በመድፍ፣ በሞርታር እንዲሁም በታንክ የታገዘ ድንገተኛ ጥቃት በመክፈት እጅግ ዘግናኝ የሆነ ጭፍጨፋ ፈፅሟል ብሏል።ተፈናቃዮቹ በጊዚያዊነት ተጠልለውበት የነበረውን ጤና ጣቢያ እና ትምህርት ቤት በማቃጠል በንፁሀን ህዝብ ላይ አረመኔያዊ ጥቃት በመፈፀም አስከፊ እልቂት አስከትለዋል ሲልም የክልሉ መንግስት ሁኔታውን ገልጿል።ከዚህ በተጨማሪ ህወሓት ለተፈናቃዮች በጋሊኮማ የሚገኘውን የምግብ መጋዘን በከባድ መሳሪያ አጋይቶታል። በጥቃቱ መጋዘኑ ውስጥ የነበረ ከ30000 በላይ ለሚሆኑ ስደተኞች የቀረበ አስቸኳይ የምግብና አልባሳት እርዳታ ሙሉ በሙሉ ወድሟል ሲል የክልሉ መንግስት አሳውቋል።ቪድዮ የአፋር ክልል ኮሚኒኬሽን ### Response:
### Text: ዛሬ በአማራ ክልል፣ ሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ እየተካሄደ ባለ የመልሶ ግንባታ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ስዩም መኮንን የተናገሩት በጦርነቱ ከደረሰው ሰብአዊ ጉዳት ባሻገር 291 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ቁሳዊ ውድመት መድረሱ በጥናት መረጋገጡን ተናግረዋል። በክልሉ የደረሰውን ውድመት መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት የመልሶ ማቋቋምና ግንባታ ፈንድ ፅ ቤት አቋቁሞ እየሰራ መሆኑ ገልፀዋል። ዛሬ የመልሶ ግንባታ የማስጀመሪያ መርሀግብር እየተካሄደ በሚገኝበት ራያ ቆቦ ወረዳ ብቻ ወደ 9 ቢሊዮን ብር የሚገመት ውድመት መድረሱም ጠቁመዋል። በዚህ አመት ብቻ 12 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ የመልሶ ግንባታ ለማከናወን የታቀደ ሲሆን የክልሉ መንግስት ለዚሁ ስራ 1 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አሳውቀዋል። ሶስት ሺህ 3000 የግለሰብ መኖሪያ ቤቶች፣ 21 ትምህርት ቤቶች፣ 10 ጤና ጣቢያዎች፣ 1 ሆስፒታል፣ 31 የንፁህ መጠጥ ውሀ ተቋማትና ሌሎችም ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡ ገልጸዋል። ድጋፍ የሚያደርጉ አካላት ለመልሶ0 ግንባታው የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ካሰራጨው ዘገባ የተወሰደ።በጦርነት የወደመው ህንፃ ፎቶ ፋይል ### Response:
### Text: ቪዲዮ ከላይ የምትመለከቱት በአሜሪካ ሀገር ፣ ፊላደልፊያ በአንድ የ አይፎን ስቶር ላይ ከቀናት በፊት የተፈፀመ ዘረፋ ነው።ነገሩ እንዲህ ነው በርካታ ጭምብል የለበሱ እና ያለበሱ ሰዎች የአፕል ስትሮን በኃይል ሰብረው ይገባሉ።በኃላ ውስጥ የነበሩ ለእይታ የቀረቡ ሁሉንም አዳዲሶቹን የ አይፎን 15 ምርቶች እና ሌሎች የአፕል ቴክኖሎጂ ውጤቶችን እያሉ እየጮሁ ይወስዳሉ።ከአፕል ስቶር ስልኮቹን ይዘው ከወጡ በኃላ አንድ ድምፅ ይሰማሉ ስልኩ አገልግሎት እንደማይሰጥ እንዲሁም ስልኩን የያዘው ሰው ላይ ክትትል እንደሚደረግ ስልኩ ላይ በተመለኩት ፅሁፍ ይረዳሉ።በየአፕል ስቶር ውስጥ ለማሳያ የሚቀመጡት አይፎን ስልኮች ለሽያጭ ከሚቀርቡት አይፎኖች ላይ ከሚጫነው ሶፍትዌር በተለየ ልዩ ሶፍትዌር የሚጫንባቸው ናቸው።ይህን ሲገነዘቡ አይፎን 15 ስልኮቹን ጥቅም እንዳይሰጡ አድርገው ወደ መሬት እየጣሉ ይሰባብራሉ ። የውሃ መውረጃ ትቦ ውስጥም ይጨምራሉ።ፖሊስ ደርሶ በዘረፋው ላይ የተሳተፉትን በቁጥጥር እንዳዋለ ተነግሯል። በርካታ ሰዎች መታሰራቸውን ፖሊስ አሳውቋል።ድርጊቱ ብዙ የአሜሪካ ዜጎችን በማህበራዊ ሚዲያ እያናጋገረ እና እያወያየ ሲሆን አንዳንዶች በዘረፋ ድርጊት ፈፃሚዎች ላይ ላልቷል ያሉትን ህግ ሲተቹ ታይተዋል። ### Response:
### Text: የሲዳማ ክልል የመሆን ጥያቄ️ የሲዳማ ዞን ምክር ቤት ሐምሌ 11 ቀን 2010 ዓም ተሰብስቦ ሲዳማ 10ኛው የኢትዮጵያ ክልል ሆኖ እንዲዋቀር የሚጠይቅ የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል። የሲዳማ ዞን የባሕል፣ ቱሪዝም እና የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ውሳኔው 161 ገደማ ከሚሆኑት የምክር ቤቱ አባላት አንድም ተቃውሞ አሊያም ድምፀ ተዓቅቦ ሳይገጥመው በሙሉ ድምፅ ጸድቋል። በወጣቱ አዋቂው ውስጥ ያለ ጥያቄ በመሆኑ ሰፊ ውይይት ነው የተደረገበት። ከዚህ አንፃር ሕገመንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት በሲዳማ ሕዝብ ውስጥ በምሁራኑ፣ በወጣቶቹ እስከ አርሶ አደር ድረስ ማለት ይቻላል ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ የሲዳማ ሕዝብ በክልል መደራጀት አለብኝ በሚል ያቀረበው ጥያቄ ሕጋዊ እና ሕገመንግሥታዊ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ የሲዳማ ዞን ምክር ቤት ትናትና ባካሔደው አራተኛ ዙር ሁለተኛ አስቸኳይ ጉባኤ ላይ ይኸን ውሳኔ በሙሉ ድምፅ አፅድቆታልበሕገመንግሥት ባለሙያው አቶ ውብሸት ሙላት ማብራሪያ መሠረት የሲዳማ ዞን ምክር ቤት የውሳኔ ሐሳቡን ሲያጸድቅ ክልል ለመሆን ከሚያስፈልገው ሒደት ግማሽ ያክሉን አጠናቋል ማለት ነው ብለዋልተጨማሪውን️ 188218318891018918818818218951818518181888188844753442 ### Response:
### Text: የተመድ ማስጠንቀቂያ️የአለም ሀገራት የምድራችን ሙቀት እንዳይጨምር አስፈላጊውን እርምጃ ካልወሰዱ እስከ አውሮፓዊያኑ 2030 ባለው ጊዜ የከፋ የአየር ንብረት ለውጥ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል የተባበሩት መንግስታቱ ድርጅትተመድ አስጠነቀቀ ፡፡ድርጅቱ ይሄን ያስታወቀው ከአውሮፓዊያኑ 2030 ወዲህ የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ከተነበየ በኋላ ነው ተብሏል፡፡ይሄም ሁኔታ እውን ከሆነ በአለም በሚሊዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የከፋ ድርቅ፣ ሰደድ እሳት፣ ጎርፍ እና የምግብ እጥረት እንደሚከሰት የመንግስታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ፓናል ገልጿል፡፡ድርጅቱ እዚህ መደምደሜያ ላይ የደረሰው ለአለም ሙቀት መጨመር ምክንያት የሆነው የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት አሁን ያለበትን ደረጃ ጥናት በማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡አሁን ላይ የአለም ሙቀት በ1 ዲግሪ ሴልሺየስ እየጨመረ ሲሆን ይህን ሁኔታ እንዳይባባስ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት የአለም መንግስታት አስፈላጊውን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ድግሪ ሴልሺየስ የዘለለ እንዳይሆን እስከ 2030 ባለው ጊዜ ውስጥ የአለም የካርቦን ዳይ ኦክሳይድ ልቀት በ45 በመቶ ሊቀንስ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡ምንጭ ሲኤንኤን ### Response:
### Text: ግምታዊ ዋጋቸው ከ 11 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ህገወጥ ገንዘብና እና ሌሎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። በዛሬው የካቲት 222011 ዓም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት አካባቢ አንድ ግለሰብ 23 ሺህ 150 የአሜሪካን ዶላር በጫማው ውስጥ ደብቆ ከሀገር ሊያስወጣ ሲል በቶጎጫሌ መቆጣጠሪያ ኬላ በጉምሩክ ሰራተኞች አማካኝነት በቁጥጥር ስር ውሏል። ተጠርጣሪውም ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት እንዳለ ለማወቅ ተችሏል።በሌላ በኩል ትላንት የካቲት 21062011 ዓም ሌሊት 6፡00 ሰዓት ላይ የሰሌዳ ቁጥራቸው 44741 ኦሮ እና 61734 ኦሮ በሆኑ አይሱዙ ተሸከርካሪዎች ግምታዊ ዋጋቸው 350 ሺህ ብር የሚሆኑ የተለያዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ወደ ሀረር መስመር ሲጓዙ ቦምባስ በተባለ ቦታ በአድማ ብተናና በጉምሩክ አባላት የተቀናጀ ስራ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ሶስት ተጠርጣሪዎችም መያዛቸውም ታወቋል፡፡በተመሳሳይ በትላንትናው ዕለት ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ሰሌዳ ቁጥራቸው 04663 ሱማ እና 04320 ሱማ የሆኑ የጭነት ተሸከርካሪዎች ግምታዊ ዋጋቸው 200 ሺህ ብር የሆኑ 200 ከረጢት ስኳር፣ 150 ከርጢት ሩዝ እና 50 ከረጢት ዱቄት ከቀብሪ በያ ወደ ጅግጅጋ በሚወስደው መንገድ አጋማሽ ላይ በፌደራል ፖሊስ እና በጉምሩክ አባላት የጋራ ክትትል ሊያዝ ችሏል፡፡ምንጭ የገቢዎች ሚኒስቴር ### Response:
### Text: የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋጋ ጭማሪ ቅሬታ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ይፋ ያደረገው የአገልግሎት ዋጋ ተመን ማሻሻያ የሕብረተሰቡን የኑሮ ደረጃና አቅም ያገናዘበ አይደለም ሲሉ ተጠቃሚዎች ቅሬታ አቀረቡ። መንግሥት በኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመን ላይ ለአራት አመት የሚቆይ የታሪፍ ማሻሻያን በ2011 ይፋ ማድረጉና በየዓመቱ እየጨመረ የሚሔድ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል፡፡ይህን ተከትሎም በአገልግሎቱ ቅሬታ የሚበዛበት ተቋሙ ሁለተኛው ዙር የዋጋ ጭማሪን ከታኅሣሥ 2012 ጀምሮ እንደሚተገብር መናገሩ አይዘነጋም፡፡ይሁንና ከአገልግሎቱ መቆራረጥ ባሻገር የኑሮ ውድነቱ ጫና ውስጥ ያስገባቸው የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ ደንበኞች ጭማሪው የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃና አቅም ያገናዘበ አይደለም ሲሉ ቅሬታቸው ያሰማሉ።የዋጋ ተመን ማሻሻያው ቀደም ሲል ይከፍሉት ከነበረው ታሪፍ እስከ ሶስት እጥፍ እንዲከፍሉ ማድረጉንም ይጠቅሳሉ፡፡የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ አገራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎትና የደንበኞች ብዛት እንዲሁም ካለው ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍላጎት አንጻር ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠትና ለማስፋፋት የሚያስችል ገቢ ማግኝት ባለመቻሉ የታሪፍ ጭማሪው ማስፈለጉን ያስረዳል፡፡ምንጭ አሐዱ ቴቪ ### Response:
### Text: የመጀመሪያ ደረጃ ምርመራ የመመረዝ ምልክት አይተናል ዶር ደሳለኝ አበበየጊምቢ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርበኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኘው የኢናንጎ ከተማ ባለ መሰናዶ ትምህርት ቤት የሚማሩ ተማሪዎች ሳይመረዙ እንዳልቀረ የህክምና ባለሙያዎች አስታወቁ። የጊምቢ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶር ደሳለኝ አበበ የመሰናዶው ትምህርት ቤት 23 ተማሪዎች ለህክምና ወደ ሆስፒታሉ መግባታቸውን ለጀርመን ሬድዮ ጣቢያ ተናግረዋል።ተማሪዎቹ ወደ ጊምቢ አጠቃላይ ሆስፒታል የመጡት ከጠዋቱ አራት ሰዓት ገደማ እንደነበር የተናገሩት ሜዲካል ዳይሬክተሩ በተደረገላቸው የመጀመሪያ ደረጃ ምርመራ የመመረዝ ምልክት አይተናል ብለዋል። ህክምናቸውን እየተከታተሉ ከሚገኙት ተማሪዎች ውስጥ ስድስቱ በጠና መታመማቸውንም ገልጸዋል።ተማሪዎቹን ለመመረዝ አጋልጧል የተባለ ዱቄት መሰል ንጥረ ነገር በመማሪያ ክፍላቸው ውስጥ እንደተገኘ መስማታቸውን ዶር ደሳለኝ አስረድተዋል። የጊምቢ ሆስፒታል በተማሪዎቹ ላይ መመረዝ አስከትሏል ስለተባለው ንጥረ ነገር ተጨማሪ ምርመራ እንዲካሄድ ናሙናዎችን ወደ ኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በነገው ዕለት እንደሚልክም ጠቁመዋል።ምንጭ የጀርመን ሬድዮ ጣቢያ ### Response:
### Text: የግብፅ ሚዲያዎች እንዲሁም ፣ አልጀዚራ ፣ ሮይተርስ ሮይተርስን ዋቢ አድርገው ደግሞ ሌሎች በርካታ የውጭ ሚዲያዎች በሰበር ዜናቸው ኢትዮጵያ የታላቁ የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ስምምነት ላይ እስኪደረስ ድረስ አራዝማለች ከስምምነት በፊት የውሃ ሙሌት ላለመጀመር ተስማምታለች እንዲሁም የኢትዮጵያ ፣ የሱዳን እና ግብፅ መሪዎች በሁለት 2 ሳምንት ውስጥ ከስምምነት ላይ ሳይደርስ የውሃ ሙሌቱ እንዳይጀመር ተስማምተዋል የሚሉ ዘገባዎችን አውጥተዋል።ይህ ፅሁፍ የተፃፈው ከለሊቱ 840 በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ነው መረጃዎች መሰራጨት የጀመሩት ከለሊት 6 ሰዓት በኃላ ቢሆንም በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ምንም አልተባለም። ማብራሪያም አልተሰጠምበርካታ የሀገራችን ዜጎችን በጉዳዩ ላይ ምላሽ ለማግኘት፣ እውነቱን ለማወቅ ፣ በግብፅ ሚዲያዎች የሚነገረውን ለማረጋገጥ በዚህ ለሊት ማህበራዊ ሚዲያውን እያተራመሱት ነው።በጉዳዩ ላይ ስጋት ያደረባቸው ፣ ያሳሰባቸው በርካታ የቤተሰባችን አባላት የደወሉልን ሲሆን ለጉዳዩ ቅርበት አላቸው ብለን ወዳሰብናቸው ሰዎች ስልክ ብንሞክርም ልናገኛቸው አልቻልንም።ውድ የቲክቫህ አባላት ነገ በጉዳዩ ላይ በመንግስት በኩል የሚሰጠውን ማብራሪያ ተከታትለን እናሳውቃለን በድጋሚ ሰላም እደሩ ### Response:
### Text: ሀገር መከላከያ ሰራዊት በማይካድራ ጭፍጨፋ ላይ ተሳትፎ አድርገዋል ያላቸውን ኃይሎች መደምሰሱን ገለፀ።መከላከያው ደመደስኩኝ ያለው ከሱዳን በመነሳት በማይካድራ አድርጎ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ የነበረ 320 የህወሓት ሀይል ነው።በዛሬው ዕለት መግለጫ የሰጡት የሀገር መከላከየ ህብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ ሀላፊ ተወካይ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ቡድኑ በማይካድራ ጭፍጨፋ አድርሶ ወደ ሱዳን በመሸሽ ተደራጅቶ የተለያዩ የመገናኛ መሳሪያዎችንና መድሀኒቶችን በመያዝ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ ሙከራ ስለማድረጉ እና ሰራዊቱ በወሰደው እርምጃ መደምሰሱን ገልጸዋል።ሀገራዊ ሀላፊነት ተሰጥቷቸው በአሜሪካ ይገኙ የነበሩና ሀገርን በመካድ ሱዳን ካርቱም ከሚገኙ የህወሓት አመራሮች ጋር ወደ ሀገር ውስጥ የመገናኛ መሳሪያዎችና መድሀኒቶችን ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ ነበር ብለዋል። በሱዳን መንገድ ላይ በውሀ ጥም የተንጠባጠቡ የህወሓት አባላቶችና እጃቸውን ለመስጠት ፍቃደኛ ያልሆኑት ሙሉ በሙሉ ሰራዊቱ እርምጃ ወስዶ ደምስሷቸዋል ሲሉም ተደምጠዋል።ከዚህም በተጨማሪ ብዛት ያለው የሬድዮ መገናኛ ፣ ሳተላይት ስልኮችና መድሀኒት በቁጥጥር ስር መዋሉን ሀላፊው ስለመግለፃቸው ከሀገር መከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያሳያል። ### Response:
### Text: ጥቆማ እና ከ ጋር በመሆን የሚያዘጋጁት የሥራ ፈጠራ እና መሰረታዊ የፋይናንስ ክህሎት ስልጠና ላለፉት 2 ዓመት ከ 11 ወር ሲካሄድ ቆይቷል። በእነዚህም ጊዜያት 9 ዙር ስልጠናዎች ተካሂደው ወደ 2400 የስራ ፈጠራ ፍላጎት ያላቸው እና በተለያየ የስራ ዘርፍ ሰልጣኞች የሰለጠኑ ሲሆን ከነዚህም ዉስጥ ከ50 በላይ የሚሆኑ ስራ ፈጣሪ እንዲመሰረቱ እና እንዲጠነክሩ እገዛ ተደርጎላቸዋል። አሁን የ 10ተኛ ዙር ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን፣ እርሶም ከታች የተያያዘውን ማስፈንጠርያ በመጫን እና በመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩትን አገልግሎቶች በነጻ ከሚያገኙ 300 ሰልጣኞች አንዱ መሆን ይችላሉ።ስልጠናው የሚያካትተው የ6 ቀን መሰረታዊ የገንዘብ አያያዝ ትምህርት እና የስራ ፈጠራ ክህሎት ስልጠና በተጨማሪ የ3 ወር የንግድ ማማከር እና ድጋፍ 9 ወር የማማከር ድጋፎች፣ የኔትዎርኪንግ እና የተለያዩ ክትትሎች በተጨማሪም ቢዝነ ፕሮቶታይፕ የሚያስፈልገው ከሆነ ፕሮቶታይፕ መስሪያ ጥሬ ዕቃዎችን ጨምሮ ነጻ የማምረቻ ላብራቶሪ አገልግሎት መስጠት ሴት የሥራ ፈጣሪዎች እንዲመዘገቡ እናበረታታለን።በሥልጠናው መሳተፍ የምትፈልጉ እና የፈጠራ ሀሳብ ያላቹህ እስከ አርብ ሐምሌ 16 2015 ብቻ ተመዝግባችሁ ስልጠናውን በነጻ መውሰድ ትችላላችሁ።መመዝገቢያ ሊንክ 88 ### Response:
### Text: የተያዙ ተጠርጣሪዎች 62 ደረሱበቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በማምቡክና አካባቢው ግጭት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች ቁጥር 62 መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ፡፡የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መሃመድ ሀምደኒል ለኢዜአ እንዳሉት ማምቡክና አካባቢው ከጸጥታ ችግር ወጥተው በአሁኑ ወቅት ወደ ቀደመ መረጋጋት ተመልሰዋል፡፡በግጭቱ ምክንያት ተቋርጦ እና ተስተጓጉሎ የነበረው የአሶሳ ግልገል በለስ፣ የግለገል በለስ ማምቡክ፣ የግልገል በለስፓዌጃዊማንኩሽና እና ሌሎችም ከተሞች የህዝብ ትራንስፖርት ትናንት እንደገና ተጀምሯል ብለዋል፡፡በፌዴራል እና በክልል ፖሊስ የተደራጀው ግጭቱን የሚመረምረው ቡድን ስራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ኮሚሽነር መሃመድ ጠቅሰዋል፡፡እስከ አሁን በማምቡክና አካባቢው ግጭት ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 50 ሲደርስ በጃዊ ግጭት ደግሞ ሌሎች 12 ሰዎች መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡በተጠርጣሪዎች ላይ ማስረጃ የማሰባሰብ ሥራው መቀጠሉንም አስታውቀዋል፡፡ በቅርቡ የምርመራ ቡድኑ 200 የሚጠጉ የቀስት ደጋን ከነመወርወሪያው፣ ገጀራ እና መጥረቢያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ኮሚሽነሩ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ በማምቡክና አካባቢው ግጭት የ21 ሰዎች ህይወት እንዳለፈ መገለጹ ይታወሳል፡፡ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: የኢፌዲሪ የከተማ ልማትና ኮንስራክሽን ሚኒስትር ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በባሊ ኢንዶኔዢያ በመካሄድ ላይ ባለው የኢንዶኔዢያ አፍሪካ የመሰረተ ልማት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡በጉባዔው ላይ በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ ማብራሪያ የሰጡት ክበርት ኢንጂነር አይሻ ባለፉት አስርተ ዓመታት ኢትዮጵያ ጠንካራ የኤከኖሚ ዕድገት ማሰመዝገቧን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በመሰረተ ልማት ልማት ላይ ያላትን ተሳትፎ ይበልጥ ውጤታማና ተወዳዳሪ ለማድረግ እየሰራች መሆኗንም ገልፀዋል፡፡በመንገድ መሰረተ ልማት ፣ በባቡር ሐዲድ ፣ በብሔራዊ ሎጅስቲክስ ልማት ፣ በትራንስፖርት ዘርፍ እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፎች የተመዘገቡት ውጤቶች አስደናቂ መሆናቸውን ለጉባኤው ተሳታፊዎች ያብራሩት ክብርት ሚኒስትሯ የባቡር ሐዲድ ኮርፖሬሽን መዘርጋቱንና ዘመናዊ የሆነ ክልላዊና አገራ አቀፋዊ የባቡር ኔትወርክን በመገንባት ላይ መሆኗንም ተናግረዋል፡፡ የባቡር ኮርፖሬሽኑ ዋና ከተማዋን ከጂቡቲ ወደብ ጋር የሚያገናኝ የ 656 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር መዘርጋቱንና ይህም ወደጅቡቲ ወደብ ለመድረስ ይፈጅ የነበረውን የ 84 ሰዓታት ቆይታ ጊዜ ወደ 10 ሰዓታት ድረስ ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 0822 ### Response:
### Text: በመጠለያው ውስጥ የሚገኙት ወገኖች እንኳን ለራሳቸው ለሌላው የሚተርፉ አርሶ አድሮች ነበሩ አቶ መላኩ አለበልዛሬ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማቱ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማንዱራ ወረዳ እና አካባቢው ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ ለሚገኙ ወገኖች በቦታው በመገኘት ድጋፍ አደረጉ።የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በቻግኒ ከተማ ተጠልለው ለሚገኙ ከ40 ሺህ በላይ ለሆኑ ተፈናቃዮች የሚውል 2800 ኩንታል ስንዴ አስረክበዋል። አቶ መለኩ አለበል በመጠለያው ውስጥ የሚገኙት ወገኖች እንኳን ለራሳቸው ለሌላው የሚተርፉ የነበሩ አርሶ አድሮች ናቸው ነገር ግን የነሱ ባልሆነ ጅንዳ የተለያየ ፍላጎት ባላቸው ሃይሎች የተሳሳተ ስሌት ለችግር ተጋልጠዋል ብለዋል።መንግስት ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስ የተጠናከረ ሥራ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በመጠለያው ውስጥ ለሚገኙት ዜጎች ከተለያዩ ወገኖች የሚመጣውን ርዳታ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ፍትሃዊ በሆነ መልኩ በፍጥነት እንዲያከፋፍሉ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።አቶ መላኩ አለበል በመጠለያ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ተዟዙረው ተመልክተዋል አሉብን ያሏቸውን ችግሮችም ጠይቀው መረዳታቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በድረገፁ አስነብባል። ### Response:
### Text: ተጨማሪ የመንግስት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ጥቅምት 14 ቀን 2014 ዓም፣ ዐድዋ አካባቢ የሚገኝ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር ወታደራዊ ትጥቅ እና ወታደራዊ አልባሳትን አመሳስሎ የሚያመርትበት ማዕከል በአየር ድብደባ ከጥቅም ውጭ ሆኗል ሲል አሳውቋል።ከዚሁ ከአየር ጥቃት ጋር በተያያዘ በሽብርተኛ ድርጅትነት የተፈረጀው የትግራይ ነፃ አውጪ ቃል አቃባይ አቶ ጌታቸው ረዳ የጥቃቱን መፈፀሙን ለሮይተርስ አረጋግጠዋል። የመጀመረው ጥቃት በአንድ የገጠር ሆስፒታል አቅራቢያ ተፈጽሟል ነው ያሉት።በዐድዋ በተፈጸመው ጥቃት ቀደም ሲል በኢትዮጵያ እና የኤርትራ ወታደሮች ውድመት ደርሶበት የነበረው እና ጥቂት ተርፎ የነበረው የአልሜዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ መመታቱን ለሮይተርስ ተናግረዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያን ስደተኞች የሚገኙባቸው የማይ አኒ እና አዲ ሃሩሽ የመጠለያ ጣብያዎች በማይጠምሪ አቅራቢያ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን ሚንስትር ዶር ለገሰ ቱሉ የመጠለያ ጣብያዎቹ ለአየር ጥቃቱ ተጋላጭ እንዳልነበሩ ገልጸዋል።የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ እየፈፀመ የሚገኘው የአየር ጥቃት ከንፁሃን በራቀ ሁኔታ በሽብረተኛ ድርጅትነት የተፈረጀውን ኢላማ ያደረገ እንደሆነ በተደጋጋሚ ገልጿል።ፎቶ ፋይል ### Response:
### Text: ይህ የቆየን ዜና ያለምክንያት አይደለም ዛሬ ላይ የለጠፍኩት አሁን ነገሩ ተባብሷልእጅግ በጣም አስፈሪ ጊዜ ነውወንዶች እየተደፈሩ ነው ይህ ደግሞ እየሆነ ያለው በአፍሪቃዋ መዲና አዲስ አበባይህ ከዓመታት በፊት የአሜሪካ ድምፅ የሰራው ዜና ነውነገር ግን ዛሬም የሚሰሙ እጅግ አስደንጋጭ መረጃዎች አሉበአዲስ አበባ ከተማ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አባዲና እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በአንድ መንደር ውስጥ የሚኖሩ ከሰባት በላይ የአዳጊ ወንድ ልጆች ወላጆች የመደፈር አደጋ ለደረሰባቸው ልጆቻችን የሕክምናና የሥነ ልቦና አገልግሎት የሚሰጠን አጣን ልጆቻችንንም የምናደርስበት ግራ ገባን ሲሉ ተናገሩ። በልብስ አጠባና በጽዳት ሥራ የተሰማሩና እጅግ በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ መሆኑን የተናገሩት እናቶች በዚህ ኑሮ ላይ ይህ ሁኔታ እንዴት እንደምንቋቋም ግራ ተጋብተናል ብለዋል።ሕፃንቱን በመድፈር የተጠረጠረው ወጣት በእስር ላይ እንደሚገኝና መዝገቡ ውሳኔ ሳያገኝ አንድ ዓመት መቆጠሩን ገልፀዋል። በወረዳው በሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚሰሩ ወጣቶች ሕፃናቱ በደረሰባቸው አደጋ መጎዳታቸውን ማየታቸውን ገልፀው አምስት ሕፃናት መደፈራቸውን የሚያረጋግጥ የሕክምና ማስረጃ አይተናል እሱም ለፍርድ ቤት ተያይዟል ብለዋል። ### Response:
### Text: ፌስቡክ️የማይናማር ግጭትን ለማባባስ ፌስቡክ ጥቅም ላይ መዋሉን ሪፖርት ጠቆመ።ፌስቡክ በማይናማር ከ18 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት። ፌስቡክ ለበርካቶች ዋነኛው ወይም ብቸኛው የመረጃና የዜና ምንጭ ነው።የፌስቡክ አስተዳደሮች በማይናማር እየገጠመን ያለውን ችግር ለመቅረፍ እየሠራን ነው። ሆኖም ብዙ ይቀረናል ብለዋል።ባለፈው ዓመት የሮሂንጋ ታጣቂዎች ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ የሃገሪቱ ጦር ራክሂን በምትባለው ግዛት ላይመጠነ ሰፊ ጥቃት ሰንዝሮ ነበር።በሺዎች የሚቆጠሩ ህይወታቸውን ሲያጡ ከ700 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ ወደ ጎረቤት ሃገር ባንግላዲሽ ተሰደዋል። በሮሂንጋውያን ላይ የአስገድዶ መድፈር፣ የእርሻ መሬትን መቃጠልና መሰል በደሎች ሮሂንጋውያን በማይናማር በርማ ተብላ ትጠራ በነበረው ሃገር ውስጥ እንደ ስደተኛ ይቆጠራሉ። በመንግሥት እና በተቀረው ሕዝብለበርካታ አስረት ዓመታት ተገልለዋል።ቢዝነስ ፎር ሶሻል ሪስፖንሲቢሊቲ ያቀረበው ባለ 62 ገጽ ገለልተኛ ሪፖርት በማይናማር ግጭትና ጥላቻን ማባባስ ለሚፈልጉ ቡድኖች ፌስቡክ መጠቀሚያ ሆኗል ይላል።ሪፖርቱ ፌስቡክ የጥላቻንግግርን በተመለከተ ያለውን ፖሊሲ እንደገና ሊከልሰው ይገባል ሲልም አክሏል።ምንጭ ቫይስ ኒውስበጌጡ ### Response:
### Text: የህዝብና ቤት ቆጠራ ኮሚሽን ትላንት መጋቢት 9 ቀን 2011 ባካሄደው ስብሰባ አራተኛዉን የህዝብና ቤት ቆጠራ ለማካሄድ የተደረገዉን ዝግጅት በመገምገም የዉሳኔ ሃሳቦች ኣሳልፏልበዚህም መሠረት የሕዝብና ቤት ቆጠራው እንዲቀጥል በቴክኒክ ደረጃ በቂ ዝጅግት የተደረገ መሆኑንና ኮሚሽኑና ማእከላዊ እስታትስቲክስ ኤጀንሲ ሰፊ ስራ የሰሩ መሆኑን የካርታ እና ተያያዥ ስራዎች እየተገባደዱ መሆኑን ሌሎች ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆኑን ግንዛቤ ወስዶ የቆጠራውን አላማና ግብ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት የተሟሉ ባለመሆናቸው ማለትም በየአካባቢው ለስራው መሳካት በተገቢው ሁኔታ መጠናቀቅ የሚገባቸው ተግባራት ባለመጠናቀቃቸው እና ተጨማሪ ግዜ የሚያስፈልግ በመሆኑ ምንም አንኳን ለቆጠራ የቀሩን ቀናት ጥቂት ቢሆንም በተለያዩ ገጭቶች ምክንያት የትፈናቀሉ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወገኖች ወደነበሩበት ቀዬ የመመለሱ ስራ በበቂ ሁኔታ ባለመሰራቱ አሁንም በርካታ ዜጎች በጊዜያዊ መጠለያ የሚገኙ በመሆኑ እነዚህ ወገኖች ትርጉም ባለው ደረጃ ወደ ነበሩበት ቦታ እስኪመለሱ ድረስ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ቆጠራው እንዲራዘም የውሳኔ ሃሳቡን ለተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች እንዲቀርብ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል። ### Response:
### Text: በወላይታ ዞን ሁለት ሕጻናት በጅብ ተበሉበወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ ሁለት ህጻናት በጅብ መበላታቸውን የወረዳው ፖሊስ አስታወቀ። የወረደው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ደስታ ዳና ዛሬ እንደገለጹት በትናንትናው ዕለት ህጻናቱ በጅብ ተበልተው ህይወታቸው ያለፈው በወረዳው ቃናፋ ጎደራ በሚባል የገጠር ቀበሌ ነው።ከምሽቱ 1፡00 አካባቢ ከዱር ድንገት በመጣ ጅብ የተበሉት ህጻናት የ8 እና የ11 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህጻናት ናቸው። እንደ ኢኒስፔክተር ደስታ ገለጻ የስምንት ዓመቷ ህጻን ከቤቷ ደጃፍ ላይ እንዳለች በጅቡ ድንገት የተወሰደች ሲሆን የ11 ዓመቱ ህጻንም ኳስ ተጫውቶ ወደ ቤቱ ሲመለስ በጅብ ተበልቶ ሕይወቱ አልፏል። ጅብ በቀጣይም ወደአካባቢው መጥቶ ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ ከቀበሌው በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኙ የጅብ ጉድጓዶችን የመድፈን ስራ ህብረተሰቡን በማስተባበር መሰራቱን ኢኒስፔክተር ደስታ አስታውቀዋል። በወረዳው በጅብ የሚደርስ ጉዳት ብዙም አለመለመዱን ገልጸው በአሁኑ ወቅት የአካባቢው ማህበረሰብ ከጸጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ጅብ ይኖርባቸዋል በተባሉ አካባቢዎች የማሰስ ሥራ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ከአንድ ወር በፊት ሦስት ህጻናት በጅብ መበላታቸው ይታወሳል። ### Response:
### Text: ለተማሪዎቻችን ደህንነት እንጨነቃለን የሚቀርቡ የጤና እክል ማስረጃዎችን ሚኒስቴሩ ይመለከታል የ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አመለወርቅ ህዝቄልአዲስ የተመደቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያላቸውን ቅሬታ በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው በድረ ገጽ፣ በኢሜይል እና በስልክ ማቅረብ እንደሚችሉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።ይሁን እንጂ ከጤና እክል ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ቅሬታዎች ያሏቸው ተማሪዎች በአካል ሊስተናገዱ የሚችሉበት እድል መኖሩን ሚኒስቴሩ ገልጿል።ተማሪዎች ከመንግስት የሕክምና ተቋም የሀኪሞች ቦርድ የተፈረመ ትክክለኛ ማስረጃ ይዘው መቅረብ እንደሚችሉ የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አመለወርቅ ህዝቄል ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገፅ ተናግረዋል። ለተማሪዎቻችን ደህንነት እንጨነቃለን ያሉት ኃላፊዋ የሚቀርቡ የጤና እክል ማስረጃዎችን ሚኒስቴሩ እንደሚመለከት ገልፀዋል። የ2013 አዲስ ዩኒቨርስቲ ገቢ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምደባ በዩኒቨርስቲዎች ልየታ መሰረት ተማሪዎቹ ምርጫቸውን ካስተካከሉ በኋላ የተፈፀመ መሆኑን ኃላፊዋ አስታውሰዋል። በቀጣይ ዩኒቨርስቲዎች በራሳቸው ፕሮግራም መሠረት ተማሪዎችን መጥራት እንደሚጀምሩ ኃላፊዋ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልፀዋል።ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ 42 ### Response:
### Text: ገንዘቤ ዲባባ ወርቅ በርሚንግሃም የሚካሄደው 17ኛው የዓለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በትናንትናው እለት ተጀምሯል።በትናንትናው እለት ምሽትም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉበት የሴቶች የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ የሩጫ ውድድር ተካሂዷል።በውድድሩንም አትሌት ገንዘቤ ዲባባ 8 ደቂቃ፣ ከ45 ሰከንድ ከ05 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩም ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች።ገንዘቤን በመከተለም ኔዘርላንዳዊቷ ሲፋን ሀሳን 8 ደቂቃ 45 ሰከንድ 68 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ስትሆን እንግሊዛዊቷ ላውራ ሙሪ 8 ደቂቃ 45 ሰከንድ 78 ማይክሮ ሰከንድ ሶስተኛ ሆና በመግባት ውድድሩን አጠናቃለች።በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ ፋንቱ ወርቁ በ8 ደቂቃ ከ50 ሰከንድ 54 ማይክሮ ሰከንድ ስድስተኛ ሆና በመግባት ውደድሩን አጠናቃለች።በአለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው እለትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን ከቀኑ 9 ሰዓት 50 ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉበት የወንዶች 3 ሺህ ሜትር ውድድር ይካሄዳል።በውድድሩ ላይም አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና አትሌት ሐጎስ ገብረህይወትና ኢትዮጵያን በመወከል ይሳተፋሉምንጭ ፋና ### Response:
### Text: መቱ ዩኒቨርሲቲ እርምጃ ወሰደመቱ ዩኒቨርሲቲ የተስተጓጎለዉን የመማር ማስተማር ሥራ ወደ መደበኛ ቦታዉ ለመመለስ ዩኒቨርሲቲው ያላሰለሰ ጥረት ቢያደርግም ችግሩን የሚፈጥሩ አካላት ከድርጊታቸው ባለመቆጠባቸዉ ትምህርት ለማስቀጠል የተደረገ ጥረት እስከ ዛሬ ድረስ ሳይሳካ ቆይቷል ሲል አስታውቋል።በመሆኑም የዩኒቨርሲቲዉ ሴኔት በ 06052012 ዓም ባደረገዉ አስቸኳይ ስብሰባ በድርጊቱ እየተሳተፉ ናቸዉ ባላቸው 26 ሃያ ስድስት ተማሪዎች ላይ ከአንድ ዓመት እስከ ሙሉበሙሉ ከትምህርት ገበታ የማገድ ቅጣት ጥሏል።በዚሁ መሰረት በድርጊቱ የተሳተፉ፡ ስድስት 6 ተማሪዎች ለአንድ ዓመት አስራ ሁለት 12 ተማሪዎች ለሁለት ዓመት ስምንት 8 ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ ከትምህርት ገበታቸዉ እንድታገዱ መወሰኑን አስታውቋል፡፡በቀጣይም እጃቸዉ ያለበትን ሌሎች ተጠርጣሪ ተማሪዎች መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞችንም አጣርቶ ተመሳሳይ የእርምት እርምጃ እንደሚወስድ ሴኔቱ ወስኗል። ይህን ተከትሎም ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ያሳሰበ ሲሆን በየትምህርት ክፍለ ጊዜው በሚሰበሰበዉ አቴንዳንስ መሰረት በትምህርት ገበታዉ ላይ በማይገኝ ተማሪ ላይ በዩኒቨርሲቲዉ ህግ መሰረት ያደረገ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡ ### Response:
### Text: ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ስለብሄራዊ ቡድኑ ምን አሉ የጊኒ ብሄራዊ ቡድን በካሜሮን የ2021 አፍሪካ ዋንጫ በጊዜ ከተሰናበቱት ሀገራት መካከል እንደምትገኝበት ይታወቃል።ቡድኑ ወደ ካሜሮን በተሸኘበት ምሽት አሁን ጊኒን እያስተዳደር ያለው የጁንታ መሪ ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ለቡድኑ አባላት ያስተላለፉት መልዕክት መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር የሁላችንም ትውስታ ነው።ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ የሀገሪቱን ባንዲራ ለቡድኑ ካስረከቡ በኃላ ባስተላለፉት መልዕክት የቡድኑ አባላት ዋንጫውን ይዘው እንዲመጡ ካልሆነ ግን በእነሱ ላይ ኢንቨስት የተደረገውን እያንዳንዱን ገንዘብ እንዲመልሱ እንዲተኩ ነበር ያሉት።ቡድኑም በአፍሪካ ዋንጫው ሳይሳካለት ቀርቶ በጊዜ ተሰናብቷል ይህን ተከትሎ የጁንታውን መሪ ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ አስተያየት ብዙዎች ሲጠብቁት ነበር።ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያም ዝም አላሉም። ኮሌኔሉ ብሄራዊ ቡድኑን ይቅር እንዳሉ ገልፀው በወቅቱ ያን ንግግር የተናገሩት ቡድኑን ለማበረታታ ብቻ መሆኑ አሳውቀዋል። የቡድን ግንባታ ጊዜ እንደሚወስድ እገነዘባለሁም ብለዋል።ነገር ግን ለቡድኑ የተሰጠው ገንዘብ ሩብ ፍፃሜ ፣ ግማሽ ፍፃሜ እና የፍፃሜ ጨዋታዎችን የሚሸፍን ሲሆን ያ ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና ይመለሳል ተብሏል። ### Response:
### Text: የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ማክሰኞ በ29012016 ዓም ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ ብሏል።ተፈታኞች የሚከተሉትን 3 አማራጭ አድራሻዎችን ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ ሲል ገልጿል። 0000 በዌብ ሳይት፡ በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡ 6284 ቴሌግራም አድራሻ፡ አገልግሎቱ ከላይ ከተገለጹት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌላ የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን አሳውቋል። ተማሪዎች በማመሳሰል ውጤት እንገልጻለን ከሚሉ ከማንኛውም አጭበርባሪዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት ተላልፏል።በተጨማሪ ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ምንም ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑን አስገንዝቧል። እንዴት ውጤት ልመልከት በዌብ ሳይት ለማየት 1 ብለው ብሮውዘር ላይ ይጻፉ2 በመቀጠልም በሚመጣው ገጽ ላይ የአድሚሽን ቁጥር ሬጅስትሬሽን ቁጥር እና የመጀመሪያ ስም ይጻፉ3 የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማግኘት ይችላሉ። በአጭር የጽሁፍ መልዕክት 1 6284 የአድሚሽን ቁጥር ሬጅስትሬሽን ቁጥር ብቻ ጽፎ አንዴ ብቻ በመላክ መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ። በቴሌግራም ቦት 1 ይፈልጉ2 የሚመጡ አማራጮችን በመከተል የአድሚሽን ቁጥር ሬጅስትሬሽን ቁጥር ያስገቡ በመቀጠልም መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ፡፡ ### Response:
### Text: ዛሬ የተሰሙ የሀገር ውስጥ ስፓርት ዜናዎች1⃣የቀድሞው የሻሸመኔ ከተማ አሰልጣኝ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ።2⃣የእግር ኳስ ደረጃ ኢትዮጵያ ባለፈው ወር ከነበረችበት በአምስት ደረጃዎች ዝቅ ብላለች 151 ላይ ተቀምጣለች።3⃣ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት መሀበር ለኢእፌ ጅማ ላይ በድጋፊውና በክለቡ ላይ ለደረሰው በደል የቅሬታ ደብዳቤ ላከ።4⃣ዲሲፕሊን ኮሚቴ የጊዮርጊስና መከላከያ ተጨዋቾችን ቀጣመከላከያ ከቅጊዮርጊስ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ላይ እርስ በርስ የተደባደቡት የመከላከያው አዲስና የጊዮርጊሱ አዳነ እንዲሁም በጨዋታ እንቅስቃሴ ላይየተጋጣሚን ተጨዋች ላይ ጉዳት ያደረሰው የመከላከያው ዳዊት እስጢፋኖስ እያንዳንዳቸው ላይየ 4 ጨዋታ እገዳ ተላልፎባቸዋል። ከቀሪ 5 ጨዋታ አራቱ ላይ ሁለቱን ወሳኝ ተጨዋቾቹን የሚያጣው መከላከያ ይግባኝ መጠየቁታውቋል። ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴም በቀናት ውስጥ ይግባኙን ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል።5⃣በጋና አስተናጋጅነት በ2018 ለሚካሄደው የቶታል አፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ለማለፍ የመጨረሻው የማጣርያ ዙር ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከአልጄርያ ጋር ያደረገውን የመጀመርያ ጨዋታ 31 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።ከመረጃዋቹ ጋር ፍቅር አሰፋ ነበርኩ ለስፓርት መረጃ ### Response:
### Text: አህመድ አብዲ ኤልካስ️የቀድሞውን የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሐመድ ኦማርን የተኩት አህመድ አብዲ ሼክ ሞሃመድ ኤልካስ️◾️በፊቅ ዞን ገርቦ በተባለ ስፍራ ተወለዱ።◾️የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ከተማ በጊዜው በልማት ወደኋላ ለቀሩ ታዳጊ ክልሎች አገልጋሎት እንዲሰጥ በተቋቋመው ዕድገት አዳሪ ትምህርት ቤት ተምረዋል።◾️በ2001 ዓም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላ ወደ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመግባት በ2004 ዓም በቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ትምህርት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀዋል።◾️ከምረቃ በኋላ በሶማሌ ክልል ጎዴ እና ጂግጂጋ ከተሞች የገቢዎች መስሪያ ቤት ባልደረባ ሆነው በመስራት የሥራ ዓለምን ተቀላቅለዋል ።◾️በ2006 ዓም የቀብሪ ደሃር ከተማ ከንቲባ ሆነው የተሾሙ ሲሆን በቀጣይ ዓመት ደግሞ የክልሉ ምክትል የፋይናንስ ሃላፊ ሆነው ለመስራት ችለዋል።◾️ከ2008 ዓም ጀምሮ የክልሉ የፋይናንስ ቢሮ ዋና ሃላፊነትን ተረክበው የሰሩ ሲሆን ከሦስት ወራት ወዲህ የክልሉ የውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ሃላፊ ሆነው እየሰሩ ነበር።◾️በ2009 ዓም ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በዲዛስተር ማኔጂመንት ተመርቀዋል።◾️በ30ዎቹ ዕድሜ መጀመሪያ የሚገኙት አቶ አህመድ ሼክ ሞሐመድ ባለትዳር እና የ7 ልጆች አባት ናቸው።© ### Response:
### Text: የድርሻውንእየተወጣያለውየኔድርሻበጎአድራጎትማኅበር የኔ ድርሻ በጎ አድራጎት ማኅበር የተሰኘ ግብረ ሰናይ የወጣቶች በጎ ፈቃደኞች ማኅበር በዱራሜ ከተማ ለሚገኙ የድሃ ደሃ ሰዎች የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓል ዳቦ ዘይት እና የኪስ ገንዘብ ድጋፍ አደረገላቸው።በዱራሜ ከተማ ወጣቶች ከአራት ወራት በፊት የተቋቋመው የኔ ድርሻ በጎ አድራጎት ማኅበር የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በማኅበረሰብ ውስጥ ማስረፅ የሚል ዓላማ ይዞ የተቋቋመ የበጎ አድራጎት ማኅበር ሲሆን በዘንድሮው የትንሳዔ በዓል በዱራሜ ከተማ ለሚገኙ በዓሉን ማክበር ለማይችሉ ስድስት ሰዎች ዳቦ ዘይት እና ከ300400 ብር ድረስ የኪስ ገንዘብ ማበርከቱን የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ተባረክ ተክሉ ገልጿል።የበጎ አድራጎት ማኅበሩ ከዚህ ቀደምም ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ተግባር በዱራሜ ከተማ ነዋሪ ለሆኑ አሥር ቤተሰቦች የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ዓመታዊ ክፍያ እንደሸፈነ የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ተባረክ ገልፆልናል።የኔ ድርሻ በጎ አድራጎት ማኅበር በከምባታ ጠምባሮ ዞን ፍትሕ መምሪያ ሲቪክ ማኅበራት ምዝገባ እና ፈቃድ እድሳት ዋና የሥራ ሂደት በፈቃድ ቁጥር 212011 በቀን 17052011 የተመዘገበ እና 20 ቋሚ አባላት ያሉት ሕጋዊ በጎ አድራጎት ማኅበር ነው። ### Response:
### Text: በመጠንቀቅ ያተረፈ እንጂ የተጎዳ የለምበዶክተር ኃይለልዑል መኮንንየዛሬ ሁለት እና ሶስት ሳምንት አካባቢ የፋሲካው ግርግር ምን ሊያስከትል እንደሚችል በተለያዩ ሚድያዎች ስንሰማ ቆይተናል።ነገር ግን ጆሮ ዳባ ልበስ ብለን ሰምተን እንዳልሰማን ሆነን ኮሮና እኛን አይነካም በሚል የባለሙያዎችን ትእዛዝ ሳንተገብር ቆየን።ይባስ ብሎ ደግሞ ቁጥሩ በጣት የሚቆጠር ሲሆን አይ ፈጣሪ ይጠብቀናል ችግር የለም እያልን ከኛ የሚጠበቀውን ጥንቃቄ ረስተን ብዙ ተዘናጋን።የዛሬ ሶስት ሳምንት ገደማ ለመጠንቀቅ የሞት ዜና አንጠብቅ ብዬ ከፋሲካ ዋዜማ በስትያ የታዘብኩትን እና ሊመጣ ስላለው ከባድ ጊዜ አያይዤ ፅፌ ነበር። ይኸው ጊዜ ደጉ አሁን ላይ አየነው አሁንም አረፈደብንም ለመጠንቀቅ ጊዜው አለን። እባካችሁ በቁጥር ከፍ እና ዝቅ ማለት ጥንቃቄያችን እና ስሜታች ከፍ ዝቅ አይበል።ከፍ ሲልበቃ አለቀልን ዝቅ ሲል ደግሞ የት አባቱ ኮሮናን ድባቅ መታነው እያልን ቁጥር ላይ መሰረት አናድርግ።አሁን ከምን ግዜውም በላይ የምንጠነቀቅበት ሰዓት ላይ ነን የትላንቱን ስህተት አንድገመዉ።እባካችሁን እንጠንቀቅየዛሬዋ የሴኮንድ ስህተት ዘመን ተሻግሮ ጠባሳ እንዳያሳርፍብን እንጠንቀቅ ይሄን ከባድ ጊዜ አሳልፈን ነገን በደስታ እንየው። ### Response:
### Text: ዛሬ ለሠዓታት ተቋርጠው የነበሩት ዓለም አቀፍ የዜና አውታር ተቋማት ድረገፆች የብሉምበርግ ኒውስ ፣ የፋይናንሻል ታይምስ ፣ የኒውዮርክ ታይምስ መስራት ጀምረዋል።ከዓለም ዜና አውታር ድረገፆች በተጨማሪ የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት ድረገፅ ፣ አማዞን መገበያያ፣ ሬዲት ተመሳሳይ ችግር ገጥሟቸው ነበር።ችግሩ እጅግ በበርካታ የዓለም ክፍል የታየ ቢሆንም በርሊን ውስጥ ድረገፆቹ ሳይቋረጡ ሲሰሩ ነበር ብሏል ዘጋርዲያን።አሁን ላይ ለሰዓታት ያህል ተቋርጠው የነበሩት ድረገፆች መስራት የጀመሩ ሲሆን ለችግሩ መፈጠር ምክንያቱ ፋስትሊ የተሰኘው የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት ነው ሲል ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል። ፋስትሊ ኩባንያ ድረ ገጾችን ከጥቃቶች የመከላከል አግልግሎት በመስጠት እንዲሁም በድረ ገጾች ላይ የጎብኚዎች ቁጥር ሲበዛ የድረ ገጹ ፍጥነት እንዳይቀንስ በመሥራት ይታወቃል።የአንድ ኩባንያ ችግር የበርካታ ድረ ገጾች አገልግሎት እንዲቋረጥ ማድረጉ መነጋገሪያ ሆኗል።ኢሴት በተሰኘ ኩባንያ ውስጥ የሳይበር ደህንነት ባለሙያ የሆኑት ጄክ ሞር በርካታ መሠረት ልማት ፈሰስ የተደረገባቸው ድረ ገጾች በአንድ ኩባንያ እጅ ላይ እንዲወድቁ ማድረግ አግባብ አይደለም ሲሉ ስለመናገራቸው ቢቢሲ ዘግቧል። ### Response:
### Text: አርባ ምንጭ ከነማ ወረደ️አርባምንጭ ከተማ ከፕሪምየር ሊጉ ወልድያ ከተማን ተከትሎ ወርዷል።በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ወሳኝ የ30ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሲካሄዱ ሁለተኛው ወራጅ ቡድን የተለየበት ውጤቶች ተመዝግበዋል።ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎቸ ወላይታ ድቻ ወልዲያን 30 በማሸነፍ መቆየቱን ሲያረጋግጥ ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡናን 21 ቢያሸንፍም ወልዋሎ እና ድሬዳዋ ሲያደርጉት የነበረው ጨዋታ በሁለተኛው አጋማሽ በመቋረጡ እጣ ፈንታውን ለመወሰን ጨዋታው እስኪያልቅ ይጠብቃል።ድሬዳዋ የተቋረጠው ጨዋታ ነገ ርፋድ ሲቀጥል ካሸነፈ የሚተርፍ ሲሆን ከተሸነፈ እና አቻ ከተለያየ ኤሌክትሪክ የሚተርፍ ይሆናል።አርባምንጭ ላይ ፋሲል ከተማን የገጠመው አርባምንጭ ከተማ 10 ቢያሸንፍም ኤሌክትሪክ እና ወላይታ ድቻ በማሸነፋቸው ምክንያት ወደ ታችኛው ሊግ ለመውረድ ተገዷል።በ2004 ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ያደገው አርባምንጭ ከተማ እስከ 2007 ድረስ የተረጋጉ የውድድር ዘመናትን አሳልፉል።ከዛ ወዲህ ባሉት ጊዝያት በተደጋጋሚ አሰልጣኞችን በመቀያየር እና ወሳኝ ተጫዋቾቹን ማቆየት ባለመቻሉ ላለመውረድ ሲጫወት ቆይቷል ያለው ሶከር ኢትዮጵያ ነው።ዘንድሮም በ33 ነጥቦች ከወልዲያ ቀጥሎ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረደ ቡድን መሆኑ አረጋግጧል።ምንጭ ### Response:
### Text: «መንግሥት ስለ ቫይረሱ አስገንዝቦ ተስፋ ያለዉ ትዉልድን ካላነፀ ማንን ሊመራ ነዉ» ቫይረሱን ለመከላከል የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች እና ግለሰቦችአሳሳቢዉ የኤድስ ስርጭትበኢትዮጵያ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ዓለም አቀፍ ፀረስርጭት ቀንን መጠበቅ የለብንም ሲሉ ቫይረሱን ለመከላከል የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ገለፁ። «የኤድስ ስርጭትን ለመከላከል በየዓመቱ የፀረ ኤድስ ቀን በሚታሰብባት በኢትዮጵያ ትኩረቱ ከርዳታ ድርጅቶች በሚገኘው ገንዘብ ላይ እንጂ የኤድስን ስርጭት ለመግታት እና ግንዛቤ ማስጨበጡ ላይ አይደለም» ሲሉ አንድ ከኤድስ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ተናግረዋል። «ወጣቱን ትዉልድ መድሃኒት የሚዉጥ ተስፋ አልባ ትዉልድ ለማድረግ እየታሰበ ነዉ» ሲሉም ቅሬታቸውን ገልጸዋል። ከስድስት ሰባት ዓመታት በፊት የኤድስ ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ግንዛቤ ለመፍጠር እና በቫይረሱ የተያዙትን ለመርዳት በመላ ኢትዮጵያ 430 ማኅበራት እንደነበሩ ያስታወሱት ግለሰቡ በአሁኑ ወቅት ግን ግማሹ ያህል እንኳ መኖራቸዉ እጠራጠራለሁ ብለዋል። «መንግሥት ስለ ቫይረሱ አስገንዝቦ ተስፋ ያለዉ ትዉልድን ካላነፀ ማንን ሊመራ ነዉ» ሲሉም ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥበት ጠይቀዋል።የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ### Response:
### Text: እንቁጣጣሽ ሎተሪ ወጣ እንቁጣጣሽ ሎተሪ ዛሬ አርብ ጷጉሜን 5 ቀን 2013 ዓም በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል፡፡ 1ኛ 20000000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 05808562ኛ 10000000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0470508 3ኛ 5000000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 1973063 4ኛ 3000000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 0612715 5ኛ 1500000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 08160016ኛ 750000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 19639137ኛ 300000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 0716025 8ኛ 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 20000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 375109ኛ 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 7959310ኛ 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 2766311ኛ 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 832612ኛ 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 2843 13ኛ 2000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 022 14ኛ 20000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 42 15ኛ 200000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር የማስተዛዘኛ ዕጣ ደግሞ 2 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡ ### Response:
### Text: ኮሚሽነር ተኮላ አይፎክሩ የስራ መልቀቂያ አላስገቡም በመደበኛ የስራ ገበታቸው ላይ ናቸው አማራ ፖሊስየአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተኮላ አይፎክሩ የስራ መልቀቂያ እንዳላስገቡ ሰሞኑን እሳቸውን በተመለከተ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ መሆኑን አስገነዘበ።ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተኮላ አይፎክሩን በሚመለከት ሀሰተኛ መረጃዎች እየተሰራጩ መመልከቱን ኮሚሽኑ ዛሬ ገልጿል። በእርግጥ ስለ ተቋማችንም ሆነ ከፍተኛ አመራሮቻችን በተመለከተ በተደጋጋሚ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲፈበረኩ ይህ አዲስ ባይሆንም አወናባጆቹ የተቋሙን የዓላማ አንድነት ለማናጋት የሚፈጥሩትን ብዥታ ለማጥራት ትክክለኛውን ማሳወቅ ያስፈልጋል ብሏል።አክሎም ኮሚሽነሩ ተቋሙ በአደረጃጀት፣ በሰው ሀይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ በአጠቃላይ ዘመኑን የዋጀ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ የሚችል አደረጃጀት እንዲኖረው ከባልደረቦቻቸው ጋር በትጋት የለውጥሪፎርም ስራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ ሲል ገልጿል።የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ሀሰተኞች ህዝቡን ለማደናገር እንደሚሉት ኮሚሽነሩ የስራ መልቀቂያ አላስገቡም በመደበኛ የስራ ገበታቸው ላይ ናቸው ሲል አሳውቋል። ### Response:
### Text: የመከላከያ ቀንየካቲት 7️ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታወቀ፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓም እንደሚከበር ተገልጿል፡፡ዳይሬክተሩ ሜጀር ጄኔራል መሐመድተሰማ እንዳስታወቁት፣ በዓሉ ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነታችንና ሕዝባዊ ባህርያችንን ጠብቀን የተጀመረውን ለውጥ እናስቀጥላለን በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ ዓላማው ሠራዊታችን በሕገ መንግሥቱ የተሰጡትን ተልዕኮዎች መፈጸም የሚያስችል አቅም ዝግጁነት እንዳለው፣ በጎ ገጽታውን በማሳየት ከሕዝቡ ጋር ያለውን ጠንካራ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ደኅንነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉ የሠራዊት አባላትን ለማሰብና የጀግንነት ክብር እንዲያገኙ ማድረግ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡በበዓሉ ምክንያትም በተለያዩ ደረጃዎች የሚካሄዱ የፓናል ውይይቶች፣ ስፖርታዊ ዝግጅቶች፣ የበጎ ተግባር ሥራዎችና ወታደራዊ ትርዒቶች እንደሚኖሩ ታውቋል፡፡የዘንድሮውን በዓል ለየት የሚያደርገው አገሪቱ በለውጥ ሒደት ውስጥ መሆኗ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ምንጭ ሪፖርተር ### Response:
### Text: አስቸኳይ መረጃ️ሼር ይደረግከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው በምዕራብ ወለጋ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ከ70 ሺህ የማያንሱ ዜጎቻችንን አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር ባደረግነው ውይይት መሰረት ለኦሮሚያ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ቢሮ በአፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታዎች ለማድረስ ተስማምተናል።በዚህም መሰረት በአዲስ አበባና በአካባቢው የምትኖሩ ለሰብዓዊ እርዳታ ገር ልብ ያላችሁ ጽኑ ኢትዮጵያዊያን የተለመደው ርብርባችሁ ይጠበቃል። የማይበላሹምግቦች መኮረኒሩዝፉርኖ ዱቄትዘይትሴሪፋም ፋፋብስኩት ጋቤጣ የንጽህናቁሳቁሶች ሳሙናኦሞሳኒታይዘርየሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ሞዴስ አልባሳት ብርድ ልብስነጠላ ጫማ የተለያዩ አልባሳት ያገለገሉም ቢሆንእነዚህን ቁሳቁሶች ብቻ ለግዜው የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ እኛ በምናዘጋጀው ግዜያዊ መረከቢያ ቦታ ታደርሱልን ዘንድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።ቦታው የሀገርፍቅርቴአትር ቅጥር ግቢ ሰኞና ማክሰኞ መስከረም 28 እና 29 ብቻ ጫካ ያደሩ ህፃናትና እናቶች አረጋውያንና ደካሞች ከምንም በላይ የኢትዮጵያዊያን ያለህ እያሉ ነው። ሰብዓዊነትይቅደም ከአንድ ግዜ በላይ ሼር በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነትዎን ይወጡከያሬድ ሹመቴ ### Response:
### Text: ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው️የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቡድን የቀድሞው የብረታብረት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ላይ ያቀረበው የአቤቱታ መዝገብ ዋና ዋና ጭብጦች ሜቴክ ባሉት 10 ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ እንዲሰሩ የተያዙ ፕሮጀክቶችን ማጓተት ያዩ ማደበርያ የስኳር ፋብሪካዎች ታላቁ የህዳሴ ግድብ በዚህ ሳቢያም የህዝብና የመንግስት ንብረት እንዲባክን ማድረግ የጨረታ ህግን በመጣስ ጨረታ ስራ ያጓትታል በሚል ያለ ጨረታ ህገወጥ ግዢ መፈፀም ከኢትዮጵያ ባህር ትራንዚት አገልግሎት 28 ዓመት በማገልገላቸው ለሜቴክ ብረታቸው ቀልጦ ለግብአትነት እንዲውሉ የተሰጡ መርከቦችን የስራ ኃላፊው ያለሙያቸው በመግባት ከ29 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በማድረግ ተጠግነው በህገወጥ መልኩ ለንግድአገልግሎት ስራ ላይ እንዲውሉ አድርገዋል በኋላም መርከቦቹን በ2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር እንዲሸጡ አድርገዋል ለጥገና ወጪ ቢያስወጡም ስራ ላይ ሲሰማሩም ሆነ በመጨረሻ ሲሸጡ መርከቦቹ ለሀገሪቱ አንድም ሳንቲም ገቢ አላስገቡም በዚህም በሀገር ሀብት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ለያዩ ማዳበሪያ ከተያዘው 11 ቢሊዮን ብር 25 በመቶውን 25 ቢሊዮን ብር ሜቴክ ቢወስድም ምንም ስራ አልሰራምምንጭ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ታራሚዎች አመለጡ በጋምቤላ ከተማ ማረሚያ ቤት ትላንት በተቀሰቀሰ ብጥብጥ 90 ታራሚዎች ማምለጣቸውን የከተማዋ ከንቲባ አቶ ኮት ሜንታፕ ለጀርመን ራድዮ ተናገሩ። ታራሚዎቹ ያመለጡት በአጥር ዘልለው ነው ብለዋል። በጋምቤላ ማረሚያ ቤት ብጥብጡ የተነሳው ትላንት ረፋድ ላይ በሁለት ታራሚዎች መካከል በተፈጠረ የግል ጠብ ምክንያት መሆኑን ከንቲባ ኮት ሜንታፕ ገልጸዋል። ሁለቱ ታራሚዎች ውኃ በጀሪካን ሲቀዱ መጋጨታቸውን የሚናገሩት አቶ ኮት ጠቡ የብሔር መልክ ከያዘ በኋላ ወደ ብጥብጥ ተቀይሯል ብለዋል። ግጭቱ በተነሳበት ወቅት ከተማው ላይ ተኩስ ይሰማ እንደነበር አንድ የከተማዋ ነዋሪ ለጀርመን ራድዮ ተናግሯል። ማረሚያ ቤቱን እንደሚያውቀው የገለጸው ይሄው ነዋሪ አመለጡ የተባሉት 90 ሰዎች ከጠቅላላው የማረሚያ ቤቱ ታራሚዎች አንጻር ቁጥሩ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁሟል።ያመለጡትን ታራሚዎች ለማስመለስ እና በቁጥጥር ስር ለማዋል የጸጥታ አካላት የተቀናጀ ዘመቻ መጀመራቸውን የጋምቤላ ከንቲባ አስታውቀዋል። አቶ ኮት ካመለጡት አንዳንዶቹ ወደ ማረሚያ ቤቱ መመለሳቸውን ቢገልጹም ትክክለኛ ቁጥራቸውን ከመግለጽ ተቆጥበዋል። ከንቲባው በትላንትናው የጋምቤላ ማረሚያ ቤት ብጥብጥ «የተጎዳ ሰው የለም» ብለዋል። የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: የፖላንድ አውሮፕላን ድንገተኛ የሞተር ብልሽት ገጥሞት በአዲስ አበባ ለማረፍ ተገደደ።ንብረትነቱ የኢንተር አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን በሞተር ላይ በገጠመው ድንገተኛ ብልሽት ምክንያት በኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ለማረፍ መገደዱን የፖላንድ መንግስት አስታውቋል።አውሮፕላኑ ከኬንያ ሞምባሳ 167 ሰዎችን አሳፍሮ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት በአንደኛው የሞተር ክፍሉ ላይ የተሳሳተ መረጃ በመነበቡ ምክንያት አዲስ አበባ እንዲያርፍ ተገዷል ብለዋል።በአውሮፕላኑ ሞተር ላይ በገጠመ ብልሽት ምክንያት የተሳፈሩ ሰዎች ለእንግልት እንዳይዳረጉ ተተኪ አውሮፕላን ከፖላንድ መላካቸውን የሀገሪቱ ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ፒዮትር ዋውርዚይክ ተናግረዋል።ምክትል ሚኒስትሩ ተተኪው አውሮፕላን ዛሬ አአ ከተማ እንደሚደርስ ጠቁመው እስከዛው ተጓዦቹ በሆቴል መቆየት የሚያስችላቸውን የኢትዮጵያ ቪዛ እንዲያገኙ በአዲስ አበባ የሚገኙ የፖላንድ ጉዳይ አስፈጻሚዎች እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል።አውሮፕላኑ ተሳፋሪዎቹን ጭኖ ስለመነሳቱ በቂ መረጃ ሰጥቶን ነበር ያሉት የፖላንድ አየር መንገድ ሃላፊ የሞተሩ ቴክኒካዊ ብልሽት ምክንያት ምን እንደሆነ እየተመረመረ መሆኑንም ተናግረዋል። ### Response:
### Text: በምርጫ ጉዳይ አሜሪካ ሶማሊያን አስጠነቀቀች።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሶማሊያ መሪዎች የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን እንዲያከብሩና ተጨማሪ መዘግየት እንዳይኖር ማስጠነቀቁን ቢቢሲ ዘግቧል።ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምርጫው የሚዘገይ ከሆነ የቪዛ ገደቦችን ጨምሮ ባለስልጣናት ላይ ያነጣጠሩ ማዕቀቦችን እንደሚጥል አስታውቋል።አገሪቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልታደርገው ባቀደችው አዲሱን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ የካቲት 18፣ 2014 ዓም ምርጫ መጠናቀቅ እንደሚኖርበት አሜሪካ አስታውቃለች።ሶማሊያ አዲሱ የምርጫ ቀን የወሰነችው በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የክልል አስተዳደር መሪዎች መካከል ለተወሰኑ ቀናት በሞቃዲሾ ሲደረጉ የነበሩ ስብሰባዎችን ተከትሎ ነው።ለህዝብ ተወካዮች የሚደረገው ምርጫ መካሄድ የነበረበት በህዳር ወር ተጀምሮ እስከ ታህሳስ አጋማሽ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም በነበሩ እሰጣገባዎች ምክንያት ዘግይቷል።በሌላ ከሶማሊያ ጋር በሚገናኝ መረጃ ዛሬ በሞቃዲሾ ከኤርፖርቱ ብዙም በማይርቅ ቦታ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን የነፍስ አድን ሠራተኞች ማስታወቃቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በጥቃቱ ቢያንስ 9 ሰዎች ተገድለዋል። የጥቃቱ ፈፃሚው ደግሞ አሸባሪው አልሸባብ ነው ተብሏል። ### Response:
### Text: የትምህርት ሚኒስትሩ ፕር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ በ2014 የትምህርት ዘመን ለፈተና የተመዘገቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጠቅላላ 985 ሺህ 354 ተማሪዎች ሲሆኑ ለፈተና የቀረቡት 92 ነጥብ 2 908 ሺህ 256 ተማሪዎቹ ሲሆኑ 77 ሺህ 98 ተማሪዎች ፈተና አልወሰዱም። በደንብ ጥሰት ፣ለመኮራረጅ በመፈለግ እና በሌሎች ምክንያቶች 50 ሺህ 170 ተማሪዎች ሳይፈተኑ ቀርተዋል። በ2014 የትምህርት ዘመን 899 ሺህ 520 ተማሪዎች ተፈትነዋል ። በፆታ ማዕከልነት የአማካይ ውጤት በወንዶች 30 ነጥብ 2 እንዲሁም ሴቶች 28 ነጥብ 09 አማካይ ውጤት አስመዝግበዋል። በትምህርት ዘርፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ በተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን የተፈጥሮ ሳይንስ 31 ነጥብ 63 ከመቶ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ 27 ነጥብ 79 ከመቶ በአማካኝ አስመዝግበዋል። በክልል ደረጃ ይህየ ነው የሚባል የውጤት ልዩነት የሌለ ሲሆን አዲስ አበባ ፣ ሐረሪ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የተሻለ ውጤት አስመዝግበዋል። ከተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወንድ ከ 700 666 ያስመዘገበ ሲሆን 650 ሴት ተማሪ አስመዝግባለች ። በማህበራዊ ሳይንስ ከ600 ወንድ 524 አስመዝግቧል። ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር እውቅና እና ሽልማት ይሰጣቸዋል። ### Response:
### Text: ዶክተር አብይ አህመድ️የጠቅላይ ሚኒስተር ዶር ዐብይ አህመድ ከአሜሪካ ቆይታ ሲመለሱ የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ዋና ዋና ሃሳቦች ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎችን ወደ ሀገር ቤት ሲመጡ በፍቅር ተቀብለን እንድንሸኛቸው አደራ፡፡ የሚፈልጉትን ሁሉ በመስጠት በክብር ተቀብለን አክብረን በሃገራቸው ኮርተው እንዲሄዱ ሁሉም ሃገር ውስጥ ያለ ዜጋ ርብርብ ያድርግ፡፡ ዋና ተቃዋሚ በመሆን የሚታወቁት ጀዋር ሙሃመድ እና ታማኝ በየነ ጋር በጋራ መክረናል ወደ ሃገራቸው በመምጣት ከህዝባቸው ጋር ለመገናኘት በቅርቡ እንደሚመጡ ተግባብተናል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያሉበትን ችግሮች መፍታቷ ሁሉንም ሊያስደስት ይገባል፡፡ ሙስሊሙ፣ ዋቄ ፈታ፣ ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንቶች እና ሌሎች እምነቶች በዚህ ላይ ደስተኛ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ያሉባቸውን ችግሮች ፈተው በሰላም ለመፎካከር ወስነዋል በዚያ ያለ ሁሉ የኛ ያልሆነ የለም፡፡ የነበረን ጉዞ ስኬታማ ነበር፡፡ አንዱ አንዱን ቁስል እያሻረ አብሮ እንዲቀጥል አደራ ለሚቀጥለው ትውልድ ፍቅርን አንድነትን ማውረስ ስለሚገባ ከምናወጣው ቃላት ጀምሮ ጥንቃቄ እናድርግ። የኢትዮጵያ መጭው ጊዜ ብሩህ ነው ሁላችንም ተደምረን አብረን እንስራ፡፡© ### Response:
### Text: በባሌ ዞን የተከሰተ ረሃብ የለም የኦሮሚያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንየኦሮሚያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ዛሬ በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ረሃብ ተከስቷል ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ መሰረት ቢስ መሆኑን ገልጿል፡፡ በባሌ ዞን እንደ ሌሎች ዞኖች ድጋፍ ለሚሹና ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ ድጋፍ የሚፈልጉ ዜጎችን ለማቋቋም በቅንጅት እየተሰረ መሆኑንም አስታውቋል፡፡ለተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ አባላት አስፈላጊው ድጋፍ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የኦሮሚያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ገረመው ኦሊቃ ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች በክልሉ 500 በሚሆኑት የድጋፍ መስጫ ጣቢያዎች ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑም በመግለጫው ተመልክቷል፡፡ በፌዴራል መንግስት ከሚደረገው ድጋፍ በተጨማሪ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የምግብ እጥረት ችግር ለሚታይባቸው አከባቢዎች በ65 ሚሊዮን ብር ለመጠባበቂያ የሚሆን እህል ገዝቶ ችግር ወደተከሰተባቸው አከባቢዎች መጫኑን ኮሚሽኑ በመግለጫው አስታውቋል፡፡ምንጭ የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ### Response:
### Text: ለሕክምና ከሄዱበት ሕንድ መመለስ ያልቻሉ ኢትዮጵያዊያን ችግር ላይ ነን ብለዋልበአሁኑ ሰዓት አገሪቱ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኘን ለመከላከል ከአንድ ነጥብ ሦስት ቢሊየን በላይ ሕዝቧ ከቤት እንዳይወጣ እና ማንኛውም እንቅስቃሴ እንዳይደርግ አግዳለች።ይህን ተከትሎም ለህክምና ወደ አገሪቱ የሄዱ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራቸው መመለስ ባለመቻላቸው ከባድ ችግር ላይ እንደሚገኙ ለቢቢሲ ገልፀዋል።ዘውዲቱ ንጉሴ የመቅኔ ንቅለ ተከላ ወይም ቦንማሮ ትራንስፕላንት የሚባል ህክምና ለማግኘት ነበር ለሁለት ሳምንታት ወደ ሕንዷ ዋና ከተማ ኒው ደልሂ ያቀናችው።ዘውዲቱ የደርሶ መልስ የአውሮፕላን ትኬት ብትቆርጥም በሕንድ እንቅስቃሴ እንዳይኖር በመታወጁ ካሰበችው በላይ ለተጨማሪ ቀናት እንድትቆይ ተገዳለች።የተወሰነ ገንዘብ ብቻ ነበር ይዤ የመጣሁት ግን የእንቅስቃሴ ገደቡ ከታወጀ በኋላ መንቀሳቀስ ስላልተቻለ ካሰብኩት ጊዜ በላይ በቀን 1000 ሩፒ እየከፈልኩኝ እንድቆይ ተደርጌለሁ እጄ ላይ ያለው ገንዘብ አልቋል። አላስፈላጊ ወጪ እና እንግልት እየደረሰብኝ ነው ትላለች።አጋጣሚ ሆኖ ለትምህርት የመጡ የማውቃቸው ሰዎች በመኖራቸው አገር ቤት ስሄድ የምከፍላቸው ገንዘብ ሰጥተውኛል በማለት ስላለችበት ሁኔታ ታስረዳለች። 2 ### Response:
### Text: የወጣቶች ተሳትፎ ለብሄራዊ መግባባት እና ለመጪው ምርጫ በሚል እዕስ ነገ ቅዳሜ ጥዋት 3 ሰዓት በብሄራዊ ትአትር መዘጋጀቱ አዘጋጆቹ ገልፀውልናል።የመግቢያ ካርዱ በከተማዋ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ መደብሮች ማግኘት እንደሚቻል የተነገረ ሲሆን በመድረኩ ዶር ብርሃኑ ሌንጂሶ ፣ ዶር መስከረም ገስጥ፣ ፓስተር ፃድቁ አብዶ ፣ ዶር ወዳጄነህ መሃረነ፣ ኡስታዝ አቡበክር አህመድ፣ መጋቢ ሀዲስ እሸቱ አለማየሁ ይገኛሉ።ይህን መድረክ ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ ማነቃቃት አገልግሎት ነው።በሌላ መረጃ አፍሪካን ሞዛይክ ኤዲት የተሰኘ ትኩረቱን በፋሽን ላይ ያደረገ መጽሔት ታትሞ ለንባብ ሊበቃ መሆኑን አዘጋጆቹ በላኩልን መልዕክት ገልጸውልናል። መጽሔቱ ለብዙዎች ተደራሽ እንዲሆን በእንግሊዝኛ እና አማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ የሚበቃ ነውም ተብሏል።76 የገጽ ብዛት ያሉት መጽሔቱ በአመት ሁለት ጊዜ በሦስት ሺ ቅጂ 1500 አማርኛ 1500 እንግሊዝኛ ታትሞ ለገቢያ እንደሚቀርብ ከአዘጋጆቹ ሰምተናል።ላለፉት 2 አመት ዝግጅት የተደረገበት መጽሔቱ የፊታችን ቅዳሜ የሚመረቅ ሲሆን የመጽሔቱን ምርቃት ተከትሎ እሁድ ለገጣፎ በሚገኘው የአፍሪካ ሞዛይክ ግቢ ውስጥ የተለያዩ ዝግጅቶች ተሰናድተዋል።ለበለጠ መረጃ 0970231639 ላይ ማግኘት ይችላሉ። ### Response:
### Text: አጭር ማስታወሻ 1ኛ በአዲስ አበባ በጊዜያዊነት ታግዶ የነበረው መሬት ነክ አገልግሎት አሁን ላይ እግዱ ተነስቶ አገልግሎቱ በየክፍለ ከተማው እየተሰጠ ነው። ታግደው ከነበሩ አገልግሎቶች መካከል ጊዜያዊ እግድ የተነሳላቸው አገልግሎቶች ዝርዝር በዚህ ይመልከቱ 66990 2ኛ ተቋርጦ የቆየው የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የማስተላለፍ ውል ከሰኞ ጥር 23 2014 ዓም ጀምሮ ይጀምራል። አገልግሎቱን ለማግኘትና የጉዳይ መከታተያ ቁጥር በኦንላን ለማግኘት ይጠቀሙ።3ኛ ዩኤኢ ኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ላይ ጥላው የነበረው የጉዞ እገዳ ከዛሬ ቅዳሜ ጀምሮ ተነስቷል። በተያያዘ ማስታወሻ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ የዱባይ በረራውን ይቀጥላል።4ኛ በወሰን ማስከበር ምክንያት ሳይጠናቀቅ የቆየው የገርጂ ሮባ ዳቦ መብራት ኃይል አዲስ አበባ አስፓልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል።5ኛ በአዲስ አበባ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ማስክ ያላደረጉ አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ከተገኙ ብር 1 ሺህ ይቀጣሉ ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪ በሚጭኑበት ወቅት ደግሞ በአንድ ሰው 500 ብር ይቀጣሉ።6ኛ የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ የመታሰቢያ ሀዉልት ነገ እሁድ በሆሳዕና ከተማ ይመረቃል። ### Response:
### Text: ምርጫ2013 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 3 ቀን 2013 ዓም ባደረገው ስብሰባ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች አስመልክቶ ትላንት መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። ዛሬ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል።በዚህም በተለያዩ ምክንያቶች ሰኔ 14 ድምጽ መስጠት የማይቻልባቸው አካባቢዎችን ገልጿል። በእነዚህ አከባቢዎች ምርጫው ጳጉሜ 1 የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።እነዚህም ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል፣ ሺናሻ ልዩ፣ ካማሽ እና ዳለቲ በኦሮሚያ ክልል ቤጊ፣ ሰኞ ገበያ፣ አያና፣ገሊላ፣አሊቦ፣ጊዳሚ፣ ኮምቦልቻ አማራ ክልልማጀቴ ማኮይ፣ አርጎባ ልዩ፣ ሸዋሮቢት፣ ኤፌሶን፣ ጭልጋ 1፣ ጭልጋ 2፣ ላይ አርማጭ፣ አንኮበር ደብብህ ክልል ሱርማ ልዩ ፣ ዲዚ ልዩ፣ ቀይ አፈር መደበኛ፣ ማጀት መደበኛ፣ ሸኮ ልዩ፣ ቴፒ ሐረሪ ክልል ጀጎል ልዩ ፣ ጀጎል መደበኛ ናቸው። በተጨማሪም የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን አስመልክቶ በፍጥነት ህትመት ሊከናወንባቸው የሚችልባቸውን መንገዶችን በመፈለግ ትላንት አስታውቆት የነበረውን 32 የምርጫ ክልሎች ወደ 27 ዝቅ ማለቱን ገልጿል። በዚህም መሰረት በነዚህ 27 የክልል እና የተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ድምጽ የሚሰጠው ከላይ በተጠቀሰው ጷግሜ 01 ቀን 2013 ዓም ይሆናል። ### Response:
### Text: ሼር ለጠቅላላ ሀኪሞች የወጣ የኮንትራት ቅጥር የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በዞን ጤና መምሪያ እና በልዩ ወረዳ ጤና ፅቤት ክፍት የስራ መደብ ላይ ተፈላጊውን ችሎታ የሚያሟሉ ሀኪሞችን በኮንትራት ቅጥር አወዳድሮ መመደብ እንደሚፈልግ አሳውቋል። የስራው መደቡ መጠሪያ ጠቅላላ ሀኪም የሙያ መስመር ተፈላጊ ችሎታ በጠቅላላ ህክምና በዲግሪ የተመረቀች የስራ ልምድ ዜሮዓመት ብዛት 379 ሶስትመቶሰባዘጠኝ ደመወዝ 9056 የስራ ቦታ በእጣ ነው የሚለየውማሳሰቢያ 1ኛ በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በሚመደብበት በማንኛውም ዞን ልዩ ወረዳ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ የሆነች።2ኛ በዕጣ ከጤና ቢሮ ለዞንልዩ ወረዳ ሲመደቡ ዞንልዩ ወረዳ በሚሰጠው በማንኛውም ጤና ተቋማ ምደባ ቦታ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነየሆነች።3ኛ በማንኛውም የመንግስት ተቋም ውስጥ ያልተቀጠረ ያልተቀጠረችየመመዝግቢያ ጊዜ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት። ከተሰጠው ቀን ውጭ የሚመጣ አይስተናገድምየመመዝገቢያ ቦታ ፡ በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ሲሆን ኦርጂናል የትምህርት እና የሙያ ፍቃድ ማስረጃ ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር መያዝ እንዳትዘነጉ።የፈተናው ቀን በቀጣይ ይገለፃል። ### Response:
### Text: በአዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ፓሊስ በመምሰል የአንድን ግለሰብ ቤት ለመዝረፍ የሞከሩ ግለሰቦች ሙከራቸው በህብረተሰቡ እና በፀጥታ ኃይሎች ትብብር መክሸፉን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።ድርጊቱ የተፈፀመው በልደታ ክከተማ ወረዳ 08 ልዩ ቦታው ቀጠና አንድ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን 4 የፌዴራል ፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሱና 2 ሲቪሎች ሆኖው በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት በመግባትና ሀሰተኛ የፌዴራል ፖሊስ መታወቂያ በማሳየት በር እንዲከፈትላቸው ካደረጉ በኃላ ሰራተኛዋን አግተው ዝርፊያ ሊፈፅሙ ሲሉ በአካባቢው በነበሩ የፀጥታ ሀይሎች እና ህዝባዊ ሰራዊቶች የዝርፊያ ሙከራቸው0መክሸፉን አስተሳደሩ ገልጿል።የፀጥታ ሀይሎች ቀድሞም በነበራቸው0 ጥርጥሬ ዘራፊዎቹን ሲከታተሏቸው እንደነበረ የተገለፀ ሲሆን ዘራፊዎች ከውጭ ባስቀመጧቸው ግብር አበሮቻቸው ቀድሞ አዘጋጅተውት በነበረው ኮድ 3 ኦሮ በሆነ ተሽከርካሪ ሊያመልጡ ችለዋል።ተጠርጣሪዎቹ ቢያመልጡም በአካባቢው0 የደህንነት ካሜራ ስለነበረ ጉዳዩን ፖሊስ ይዞት ክትትል እያደረገበት ይገኛል ተብሏል።ማህበረሰቡ እራሱን ከመሰል አጭበርባሪዎች ሊጠብቅ ይገባል አጠራጣሪ ነገሮችንም ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኙ የፀጥታ ሀይሎች ሊያሳውቅ ይገባል ተብሏል። ### Response:
### Text: የዝነኛው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ባለቤት ወይዘሮ ፋንቱ ደምሴ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ በሰጡት ቃል ድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ ህይወቱ ከማለፉ በፊት ሰርቶ ያጠናቀቀው ሙሉ አልበም በሚቀጥለው ሳምንት ይለቀቃል ብለዋል።ወሮ ፋንቱ ደምሴ የፊታችን ሰኞ ድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ በ34 ዓመቱ ከተገደለ 1 ዓመት እንደሚሆነው አስታውሰዋል።አክለውም ህዝቡ ለእሱ ያለውን ስሜት አውቃለሁ ድምፁን መስማት ያፅናናቸዋል ብዬ አስባለሁ ብለዋል።ወሮ ፋንቱ የድምፃዊ ሃጫሉ አዲሱ 3ኛው አልበም ከመሞቱ ብዙም ሳይቆይ በፊት የተቀዱ ስራዎች እንዳሉት ተናገረዋል።አዲሱ አልበም የሚሰኝ ሲሆን የአማርኛ ትርጉሙ መፍትሄው ምንድነው የሚል ነው።በነገራችን ላይ አልበሙ በቀጣይ ሳምንት ለገበያ የሚቀርብ ቢሆንም ዛሬ ማምሻውን ጀምሮ በ ላይ ቀርቧል እዛ ላይ በመግዛት ማዳመጥ ይቻላል።ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ አልበሙ በ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ለገበያ ይቀርባል።ውድ የቲክቫህ አባላት አልበሙን ህጋዊ በሆነ መንገድ ብቻ በመግዛት እንድታዳምጡ እናበረታታለን በማህበራዊ ሚዳያዎች ላይ በህገወጥ መንገድ እንዳይሰራጭ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ አድርጉ።ድምፃዊ ሃጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓም ምሽት በሰው እጅ በጥይት ተመቶ መገደሉ ይታወሳል። ### Response:
### Text: ከትላንቱ የአውሮፕላን አደጋ ትረፊ ያላት ነብስበመዘግየቱ ምክንያት ከኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ሞት ያመለጠው ግርካዊ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ግሪካዊ አንቶኒስ ማቭሮፖሎስ በትላንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በሚበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመሳፈር ትኬቶን ቆርጦ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ደርሶ ነበር፡፡ነገር ግን ለ2 ደቂቃ ያህል በመዘግየቱና መጓዝ አትችልም ተብሎ መከልከሉ አበሳጭቶት ነበር፡፡ከ6 ደቂቃ በራረ በኃላ በቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ ግን በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ 157 ሰዎችን ለወሬ ለነጋሪ ሳያስቀር ቅርጥፍ ማድረጉ ለማመን የሚከበድ ክስተት እንዲሆን አድርጎታል፡፡ግሪካዊዩ ተጓዥ አርፍደሃል ስባል በጣም ተናድጄ ነበር፣ሊተባበረኝ የነበረ አካል አልነበረም ብሏል በወቅቱ፡፡ኋላ ላይ ግን በአወሮፕላኑ ለመጓዝ ትኬት ከቆረጡት መሃል በመዘግየቴ የተረፍኩ ብቸኛው ሰው መሆኔ ሲነገረኝ ለማመን ከባዶኛል ሲል ትኬቱን ጭምር በፌስ ቡክ ገፁ አያይዞታል፡፡የአንድ አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ኃላፊ የነበረው አንቶኒስ ማቭሮፖሎስ ናይሮቢ ላይ በአካባቢ ጥበቃ ላይ ባተኮረው ጉባኤ ለመካፈል ነበር ወደ ኬንያ ሊያመራ የነበረው፡፡ምንጭ፡ቻነልኒውስ ኤስያ ### Response:
### Text: ከጅዳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሳዑዲ አየር መንገድ አውሮፕላን በአንዲት መንገደኛ ድንገተኛ ምጥ ምክንያት በኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ አረፈ። ጀነቲ ሑሴን ከጅዳ ወደ አዲስ አበባ ስትጓዝ የስምንት ወር እርጉዝ እንደነበረች በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል። ጀነቲ ባለፈው ቅዳሜ በጉዞ ላይ ሳለች ከጠዋቱ 1 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ምጥ ሲጀምራት ከአዲስ አበባ በመብረር ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኤርትራ የአየር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመነጋገር አስመራ ማረፉን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል። ኤምባሲው አውሮፕላኑ እንዳረፈ የኤርትራ ጤና ጥበቃ አምቡላንስ በምጥ ስትሰቃይ የነበረችው ጀነቲ ሁሴንን በፍጥነት በአስመራ ከተማ ትልቁ ወደሆነው ኦሮታ ሪፈራል ሆስፒታል ወስደዋት በኤርትራውያን አዋላጅ ሀኪሞች እርዳታ ሁለት ሴት መንታ ልጆችን በሰላም ተገላገለች ሲል ኹኔታውን አብራርቷል። ጊዜያቸው ሳይደርስ የተወለዱ የጀነቲ ልጆች በአስመራ ከተማ በሚገኘው የኦሮታ ሪፈራል ሆስፒታል ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሕክምና ባለሙያዎች አገኘሁ ባለው መረጃ መሰረት መንታዎቹ ልጆች እስከ መጪው ሐሙስ ክትትል እየተደረገላቸው ይቆያሉ።ምንጭ የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: በግለሰቦች መካከል በተፈጠረ ግጭት የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ በባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ትናንት በገበያ ስፍራ በግለሰቦች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡በመምሪያው የኮሚኒኬሽን ዲቪዥን ባለሙያ ኮማንደር ናስር ኡመር እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ትናንት መስከረም 18 ቀን 2012 ከቀኑ 9፡00 ሰዓት አካባቢ0ሀረዋ ከተማ በሁለት ሰዎች መካከል በተከሰተ አለመግባባት ነው፡፡አለመግባባቱ ወደ ከፍተኛ ግጭት በማምራቱ አምስት ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ግለሰቦችም በጊኒር አጠቃላይ ሆስፒታል የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ኮማንደር ናስር አስረድተዋል፡፡በአሁኑ ወቅት አካባቢው መረጋጋቱን የጠቀሱት ኮማንደሩ ከግጭቱ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በአሁኑ ወቅት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረጋባቸው መሆኑን ገልጸዋል።በሰዎች መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በየደረጃው ወደሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች በመቅረብ በህጋዊ መልኩ መዳኛት አስፈላጊ መሆኑንም አመልክተዋል። ህብረተሰቡ አለመግባባት ሲፈጠር ከህገወጥ ተግባራት ራሱን ሊያርቅ እንደሚገባም ኮማንደር ናስር አስገንዝበዋል። ### Response:
### Text: የ2ተኛው ቀን የ12ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ ተሰጥቷል።የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ትላንት የካቲት 29 ቀን 2013 ዓም መጀመሩ ይታወቃል።በዛሬው ዕለት የ2ኛው ቀን ፈተና በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ ውሏል።ከፈተናው ሂደት ጋር በተያያዘ የተለያዩ አስተያየቶች ከተማሪዎች እና ከተማሪ ወላጆች እያደረሱን ይገኛሉ። አንዳንድ ተማሪዎች ስልክ ይዞ የመገኘትም ነገር እንደነበረ ተፈታኞች ለቲክቫህ እያሳወቁ ነው።በተለያዩ የቴሌግራም ግሩፖች ላይ ሞባይል ስልክ ይዘው የሚገቡ ተማሪዎች ፈተናውን በማንሳት እያሰረጩ እንደሆነና ይህንንም የሚገልፅ በቂ ማስረጃ እንዳላቸው የተማሪ ወላጆች እንዲሁም ተፈታኞች እየገለፁ ነው።እኛም ጉዳዩ ለትምህርት ሚኒስቴር አካላት ለማሳወቅ ጥረት አድርገናል።በቀጣይ ቀናት ፈተናዎች በሞባይል ስልክ ዙሪያ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግ እያሳሰቡ ነው።ባደረግነው ማጣራት ፈተና ይሰራጭባቸዋል ከተባሉት እንዲሁም ቴሌግራም ላይ ካየናቸው ግሩፖች አንደኛው ሙሉ በሙሉ ሲጠፋ ፣ አንደኛው ግሩፕ ስሙ ተቀይሯል ሌላኛው ደግሞ በውስጡ የነበሩት መልዕክቶች ጠፍተዋል።ተማሪዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ስለሁለቱ ቀናት ስለነበረው የፈተና ሂደት በተመለከተ በአስተያየት መስጫው ላይ መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። ### Response:
### Text: የ አበበች ጎበና ህፃናት ክብካቤ እና ልማት ማህበር ከሰዓታት በፊት ባሰራጨው መልዕክት ክብርት ዶር አበበች ጎበና እዳዬ አሁንም በጳውሎስ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል ሕክምና እያገኙ መሆኑን አሳውቋል።ዶክተሮቻችው ለቤተሰብ እንደገለፁት ጤናቸው በጣም መሻሻል አሳይተዋል፡፡ የልብ፣ የኩላሊት፣ የጉበት፣ የደም ግፊትና የመሳሰሉት ምርመራ ተደርጎላቸው ጥሩ የሚባል ሁኔታ ላይ መሆናቸው ዶክተሮች ገልፀዋል ብሏል ማህበሩ ባሰራጨው መልዕክት።ማህበሩ የጳውሎስ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች ደከመኝ ሰለጨኝ ሳይሉ 24 ሰዓታት የእዳዬን ጤና ለመመለስ የህምና እርዳታ ላደረጉላቸው ከልብ የመነጨ ምስጋና እናቀርለን ሲል አመስግኗል።ወዳጆቻቸው፣ ልጆቻችው እና ሎሎችም ከኢትዮጵያ ና ከተለያዩ ሀገራት በእንዳዬ መታመም ተጨንቀው ስልክ በመደወልና መልዕክት በመላክ የጠየቁትን በአጠቃለይ በፀሎትም አብረው ለሆኑ ሁሉም ማህበሩ አመስግኗል።በመጨረሻም የሺዎች እናት የሆኑት ክብርት ዶር አበበች ጎበና ፈጣሪ ጨርሶ ይምራቸው ዘንድ ሁላችንም እንፀልይላቸው ሲል የአበበች ጎበና ህፃናት ክብካቤ እና ልማት ማህበር መልዕክት አስተላልፏል።ክብርት ዶር አበበች ጎበና በኮቪድ19 ተይዘው ለህክምና ሆስፒታል መግባታቸው ይታወሳል። ### Response:
### Text: ኢትዮ ሶማሌ ክልል️◾️በሶማሌ ክልል የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደሚፈፀሙ በነዋሪዎች ሲነሳ ቆይቷል።◾️በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች በታየው የፍቅርና የመደመር ሂደት ውስጥ እኛም እንካተት በሚል ጥያቄ ያነሱ የህዝብ ተወካዮች እና የሀገር ሽማግሌዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ በክልሉ መንግስት ጥቂት አመራሮች ሲደርስ ቆይቷል።◾️ስልጣን ልቀቅ ተብያለሁ ስልጣኔን ከምለቅ ብሞት ይሻለኛል በሚል ሰፊ ቅስቀሳ ሲደረግ ነበረ።◾️ያለ ክልሉ ነዋሪዎች ፈቃድና ይሁንታ ክልሉን አስገነጥላለሁ በማለት ከፍተኛ ውዥንብር በመፍጠር ኢህገመንግስታዊ እና አስነዋሪ ድርጊት ሲፈፀም ቆይቷል።◾️የሀገር ሉዓላዊነትን አደጋ ላይ ለመጣል እንዲሁም አካባቢው እንዳይረጋጋ የተለያዩ ፕሮፖጋንዳዎችን የማሰራጨት ተግባር ሲፈፀም ነበር።◾️ስልጣኔን እነጠቃለሁ በሚል የክልሉ ልዩ ሀይልን ላልተቋቋመለት ዓላማ በማዋል መንገዶች ሲዘጉ ነበር በማለት ለአብነትም ከሀረር ጅግጅጋ እና ወደ ጅቡቲ የሚወስዱት መንገዶች ተዘግተው ቆይተዋል።◾️በሶማሌ ክልል በተለይም በጅግጅጋ በተፈጠሩ የፀጥታ ችግሮች የሰው ህይወት፣ የሀይማኖትና የፋይናንስ ተቋማት ላይ ጉዳት ደርሷል።©አቶ አህመድ ሽዴየመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሚኒስትር ### Response:
### Text: 1627ኛ መደበኛ ሎተሪ ወጣ ሼር 1627ኛው መደበኛ ሎተሪ ሐሙስ ሐምሌ 18 2011 ዓም በብሔራዊ ሎተሪ ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል1ኛ 600000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1444522ኛ 300000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0129903ኛ 150000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0638484ኛ 60000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1038435ኛ 30000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 2268876ኛ 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1200 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 011469፣159001 እና 1362967ኛ 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 600 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 225384፣ 063624 እና 0338868ኛ 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 150 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 85649ኛ 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 984710ኛ 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 90 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 542911ኛ 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 23912ኛ 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 45 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 31713ኛ 3400 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 30 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 0014ኛ 34000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 15 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር የማስተዛዘኛ ዕጣ ደግሞ 9 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡ የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ሼር ### Response:
### Text: አተዳዳሪዎች ዛሬ የስራ ቀን አይደለም ወደቤት ግቡከምርጫ ጣቢያዎች ውጪ በተለይም በፖለቲካ ፓርቲ እጩ ወኪሎች ላይ በስፋት የሚደረጉ ህገወጥ ተግባራት በውጤቱ ላይ ትልቅ ተፅእኖ አላቸው።ምርጫ ቦርድ የምርጫውን ውጤት በሚመረምርበት ሁኔታ እና በሚያፀቅድበት ጊዜም ይህንን ታሳቢ አድርጎ ነው። ይሄን የመንግስት አካላት ማወቅ አለባቸው።የመንግሥት አካላት ሰራተኞቻቸውን ፣ አስተዳዳሪዎቻቸውን ወደቤቶቻቸው እንዲገቡ ማድረግ አለባቸው። ዛሬ የስራ ቀን አይደለም ከህግ አስፈፃሚዎች ውጪ፣ ከምርጫ ቦርድ ውጪ ፣ ከመሰረታዊ አገልግሎት ሰጪዎች ውጪ ደጅ ላይ የሚሰራ ማንኛውም አካል የለም።ለሎጅስቲክስ እገዛ በሚያስገልግበት ጊዜ መገኘት አለባቸው ነገር ግን ምርጫ ጣቢያ አካባቢ ተገኝተው ፣ ወይም የምርጫ ክልል ፅቤት ተገኝተው ሌላ ቦታ ተገኝተው የእጩዎችን ወይም የወኪሎቻቸውን ተግባር የሚያሰናክሉበት ምንም ምክንያት አይኖርም ተቀባይነትም የለውም ህገወጥ ነው።በአማራ እና በደቡብ ክልል በጣም አሳሳቢ በሚባል ደረጃ፣ በአፋር ክልል ደግሞ በመለስተኛ ደረጃ በፓርቲ እጩ ወኪሎች ላይ ህገወጥ ተግባር የመፈፀም ሁኔታ መታየቱን ምርጫ ቦርድ አሳውቋል።ከምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወሪት ብርቱካን መግለጫ ላይ የወሰድነው። ### Response:
### Text: 4 የፖለቲካ አመራሮች እና አንድ የፖሊስ አመራር ላይ እርምጃ ተወስዷል አቶ ጀማል ሀሰን ከጥቂት ቀናት በፊት በሰሜን ሸዋ ዞን እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አዋሳኝ ቦታዎች ተከስቶ የነበረውን ግጭት ማብረድ የተቻለ ሲሆን ችግሩን መከላከል አልቻሉም በተባሉ ላይ እርንጃ እየተወሰደ ነው።የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር የህዝብን ሰላም፣ ደህንነት አላረጋገጡም ባላቸው አመራሮች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አሳውቋል።የብሄረሰብ አስተዳደሩ ኮሚኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጀማል ሀሰን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል አምስት አመራሮች ላይ እምርጃ ተወስዷል። አራቱ የፖለቲካ አመራሮች ናቸው አንድ የፖሊስ አመራር ደግሞ በህግ ተጠያቂ እንዲሆን በቁጥጥር ስር አውለናል ብለዋል።ፖሊሶች አስፈላጊውን እርምጃ ወስደው ጉዳዩን ማብረድ ይችሉ ነበር ከስምሪት እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ተገምግሞ በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ተሰርቷል ሲሉ ገልፀዋል።እየተወሰደ ያለው እምርጃ እስከ ታች ቀበሌ እንደሚደርስም ገልፀዋል።የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትላቸው እንዲሁም ሁለት የወረዳው የድርጅት አመራሮች የፖለቲካ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገልፀው ከስልጣናቸው እንዲነሱ ተደርገዋል ብለዋል።ያንብቡ 0719 ### Response:
### Text: የዩኒቨርሲቲ ምደባን በተመለከተ️የዩኒቨርሲቲ ትምህርት በጥቅምት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ይጀመራል የትምህርት ሚኒስቴር የ2011 ትምህርት ዘመን በጥቅምት የመጀመሪያ ሳምንት እንደሚጀመር አስታወቀ።በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ማዘጋጃ ጥናት ላይ ሰፊ ውይይት ለማካሄድ፣ በመስከረም ወር ያሉትን ብሄራዊና የሀይማኖታዊ በአላትን እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎትን ከግምት በማስገባት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርት መስጠት የሚጀመረው ከጥቅምትወር የመጀመሪያው ሳምንት ጀምሮ ይሆናል።የአዲስ ተማሪዎች ምደባም በቀናት ውስጥ ይፋ የሚደረግ ይሆናል ያሉት ዶር ሳሙኤል ይህን ተከትሎ ዩኒቨርስቲዎች በሚያወጡት ፕሮግራም መሰረት ነባርና አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲገቡ የሚደረግ ይሆናል።ዩኒቨርስቲዎችም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀዋል።የ10ኛ ክፍል ወይም የመሰናዶ መግቢያ ሀገር አቀፍ ፈተና ያልቀረ መሆኑንና በነበረበት የሚቀጥል መሆኑንም አስታውቀዋል።© አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2011 የኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት ### Response:
### Text: እንኳን ደስ አለንኢትዮጵያዊቷ ድምጻዊት ብሩክዊትጌታሁን ቤቲ ጂ ለአምስተኛ ጊዜ በተካሄደው በመላው አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት አፍሪማ ላይ በሦስትዘርፍ አሸናፊ ሆነች።ድምጻዊት ቤቲ ጂ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ አልበም፣ የምስራቅ አፍሪካ በምርጥ ሴት አርቲስት እና የአፍሪካ ተስፋ የተጣለበት ዘርፍ ነው ሽልማትዋን የተቀበለችው።ድምጻዊት ቤቲ የዓመቱን ምርጥ አልበም ሽልማትዋን ያሸነፈችው ወገግታ በሚለው አልበሟ ነው።እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ሴት አርቲስት ሽልማትን መንገደኛ በሚለው የሙዚቃ ስራዋ ስታሸንፍ ተስፋ የተጣለባቸው በሚለው ዘርፍ ደግሞ ኧረ ማነው በሚለው የሙዚቃ ስራዋ ነው ያሸነፈችው።ቤቲ ጂ ሽልማቶቹን ከተቀበለች በኋላ በፌስቡክ ገጿ ላይ ድምፅ በመስጠት ላገዛችሁኝ አድናቂዎቼ በሙሉ ምስጋናዬ የላቀ ነው ብላለች፡፡ኢትዮጵያን ወክዬ ስቆም አኮራችሁኝ እናንተ ከጐኔ ነበራችሁ አንድ ላይ ሆነን የአገራችንን ስም እናስጠራለን በማለት ከጎኗ ለነበሩ ሁሉ ምስጋናዋን አቅርባለች፡፡ እንዲሁም ይህ መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደለም በማለት መልዕክቷን አስተላልፋለች።አፍሪማ በአውሮፓውያኑ 2014 የተጀመረ የሙዚቃ ውድድር ሲሆን የዘንድሮው ዝግጅት በጋናዋ መዲና አክራ ነው የተካሄደው፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ ️ ኢትዮጵያ በሴቶች 5000 ሜትር ውድድር ባስመዘገበችው ወርቅና ነሀስ ከፍተኛውን የቡድን ስራ የሰራችው ለተሰንበት ግደይ ከድሉ በኃላ ተከታዩን ብላለች የገባሁት ለቡድን ስራ ነው። ተሳክቶልኛል በ1500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያመጣችው በ5000 ሜትር ለሀገሯ ወርቅ ያስገኘችው ጉዳፍ ፀጋይ ተከታዩን ብላለች ውድድሩን ለማሽነፍ ነበር የገባሁት። እግዚአብሔር ረድቶኛል በጣም ደስ ብሎኛል። ወደ ሀገራችን ወርቁን አምጥተነዋል ደስ ብሎኛል።ወርቅ ነው የምፈልገው ወርቅ በማምጣታችን ደስ ብሎኛል። ለቡድን ስራው ተነጋግረን ነው የገባነው። ከ6 ዙር በኃላ ለመፍጠን ነበር እያደረግን ነበር በመቀያየር ዳዊትንም እኛ ብናግዛት የተሻለ ሶስታችን እንወጣለን ከ13 ብለን ነበር።ከአንድ እስከ ሶስት ባንወጣም ወርቁን ለህዝባችን አምጥተናል። ደስተኛ ነኝ። በ1500 ያላሳካሁትን በ5000 አሳክቼዋለሁ ደስ ብሎኛል። ከህመም መጥቼ ወርቅ በማምጣቴ ለእኔ ልዩ ቀን ነው።መታሰቢያነቱ ለውዷ እናቴ ይሁንልኝ ውዷ እናቴ ️ በጣም ጠንካራዋ እንዲሁም ለባለቤቴ ይሁንልኝ። ለኢትዮጵያ ነሃስ ያስገኘችው ዳዊት ስዩም ተከታዩን ብላለች ለእኔ ይህ ውድድር ልዩ ነው ከ5 አመት ጉዳት በኋላ ያመጣሁት ውጤት ነው። መታሰቢያነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ ይሁንልኝ። ### Response:
### Text: አዲስ አበባ️በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በተለምዶ ዘይት መጭመቂያ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ጤፍን ከባዕድ ነገሮች ጋር በመቀላቀል እንጀራ በሚሸጡ ግለሰቦች ላይ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥርስር ውሏል፡፡ወሪት ወርቄና ትዕግስት አዳነ እንጀራ በመጋገር ለአንድ ወር ሰርተዋል፡፡በቆይታቸውም 45 ኪሎ ግራም ጤፍን 100 ኪሎግራም ጀሶ ጋር በመቀላቀል ለባለሱቆች ያከፋፍላሉ፡፡የማይሸጥና የተበላሸ እንጀራን ጀሶ ከተቀላቀለበት ጤፍ ጋር እንደገናበመቀላቀል ለጥቅም እንደሚውል የታዘቡትን ያስረዳሉ፡፡በህብረተሰቡ ላይ ብዠታ የሚፈጥሩ ነገሮችን ለፖሊስና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ጥቆማ መስጠት እንደሚገባ ለዳት ሳጅን ተክሌ በቀለ ጠቁመዋል፡፡የቦሌ ክፍለ ከተማ የምግብና መድሀኒትና ጤና እንክብካቤ አስተዳደር ቁጥጥር ጽቤት ሀላፊ አቶ በሐይሉ ዘለቀ በተገኘው ጥቆማ መሰረት ወደ ቦታው ከባለድርሻ አካላት ጋር ወደ ቦታው በመሄድ እንጀራ ጋጋሪዎች የንግድ ፍቃድና የብቃት ማረጋገጫ የሌላቸው መሆኑን ጠቅሰው ለእንጀራ የሚውል ሶስት ኩንታል ባዕድ ነገር ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ጤፍን ከባዕድ ነገር ጋር ቀላቅለው በሚሸጡ ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቀዋል፡፡ምንጭ የክከተማውን ኮምኒኬሽን ቢሮ ### Response:
### Text: የእሳት አደጋ️በኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ መግቢያ ላይ የሚገኘው ኢንተማ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሻማ ፋብሪካ ላይ በደረሰበት የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገለፀ።በዚህ የእሳት አደጋ ከፋብሪካው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት የንግድ ሱቆችና አንድ መኖሪያ ህንፃ ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን አስታውቋል።የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ በአጠቃላይ 11 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ተናግረዋል።ከንግድ ሱቆች 500 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን ከመኖሪያ ህንፃውና ከሱቆቹ 7 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማትረፍ መቻሉንም ገልፀዋል።ባለስልጣኑ የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠርም ከአመስት ቅርንጫፎቹ የተውጣቱ 80 የአደጋ ተቆጣጣሪ ባለሙያዎች፣217 ሺህ 500 ሊትር ውሃ፣ 5 ሺህ 975 ኬሚካል ፎም እና 13 ከባድ ተሸከርካሪዎችን መጠቀሙን አንስተዋል።አደጋውን ለመቆጣጠር በነበረው ሂደትም አንድ የባለስልጣኑ ሰራተኛ ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የገለፁት ባለሙያው የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል።ምንጭ ### Response:
### Text: የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በተፈጸሙ ወንጀሎች ዙሪያ በኦሮሚያ ክልል ሲካሄድ የነበረው ምርመራ መጠናቀቁን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዛሬ አስታውቋል።የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ እና ኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጉዳዩን አስመልክተው በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።ምአቃቤ ህጉ አቶ ፍቃዱ ጸጋ በመግለጫው ተከታዩን ብለዋል በ488 የክስ መዝገብ 5 ሺህ 728 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመስርቶባችዋል። 3 ሺህ 377 ተከሳሾች በፌደራል መንግስት ስልጣን ስር የሚወድቅ ወንጀል በመፈጸማቸው ተጠያቂነታቸው በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሲሆን 2 ሺህ 351 ተከሳሾች ደግሞ በኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ስር ይሆናል። በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ተከሳሾች በ114 የክስ መዛግብት ክሳቸው ተደራጅቷል። በኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ደግሞ በ374 የክስ መዛግብት ክሳቸው ተደራጅቷል። የክስ መዝገብ ከተከፈተባቸው መካከል 63 ግለሰቦች በሀረር በፈረሱ ሃውልቶች ምክንያት በሽብር ህጉ መሰረት ተጠያቂ የሚሆኑ ናቸው። በኦሮሚያ ክልል ከአርቲስ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኃላ በተከሰተው ሁከት 167 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል ፣ 360 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ፣ ከ4 ቢሊየን 673 መቶ ሚሊየን ብር በላይ የንብረት ጉዳት ማድረሱ በምርመራ ተጣርቷል። ኤፍ ቢ ሲ ### Response:
### Text: ጥቅምት 42013 ዓምየኢትዮጵያ ኮቪድ19 መረጃዎች በሶማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 146 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰው አልተገኘም። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 85 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 765 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 76 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰው ህይወት አልፏል 1 ከእንጅባራ ህክምና ማዕከል፣ 1 ከሃይቅ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 579 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 102 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል። በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 142 የላብራቶሪ ምርመራ 54 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 94 የላብራቶሪ ምርመራ 13 ሰዎች በቫረረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 1304 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 55 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በአአ ባለፉት 24 ሰዓት 3246 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 308 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል። ያልተካከቱ የክልል ሪፖርቶችን ቆይት ብላችሁ ይህንኑ ፖስት ተመልከቱ ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ ለአራተኛ ጊዜ የሚካሄደው የህዝብና ቤት ቆጠራ መጋቢት 19 ቀን 2011 ዓም በመላው አገሪቷ ይጀመራል። በየአስር ዓመቱ ለሚካሄደው ለዚህ ስራ 152 ሺህ የቆጠራ ቦታዎች፣ 182 ሺህ ቆጣሪዎችና 38 ሺህ ተቆጣጣሪዎች እንደዚሁም ለቆጠራው የሚያመቹ የቆጠራ ቦታ ካርታዎች መዘገጀታቻዉን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎች ዘግቧል፡፡ ህዝቡ ትክክለኛውን መረጃ በመስጠት ለስኬቱ የበኩሉን ሚና መጫወት እንዳለበት ነው በኤጀንሲው የኦሮሚያ የህዝብና ቤት ቆጠራ ኮሚሽን ፀሃፊ አቶ ሼኮ ጉሩ አሳስበዋል። የቆጠራው በትክክልና በጥራት መካሄድ የአገሪቱን ሁለንተናዊ ተጨባጭ ሁኔታ በማመላከት ከአገር ባሻገር ዓለም አቀፍ ፋይዳም ያለው በመሆኑ መረጃው በትክከል መሰብሰብ እንዳለበት ፀሃፊው ገልጸዋል። በጎዳና ላይ የሚኖሩና ተፈናቅለው ወደየቄያቸው ያልተመለሱ የህብረተሰብ ክፍሎችን በያሉበት ለመቁጠር የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘጋጀቱንም አስታውቀዋል። አራተኛው የህዝብና ቤት ቆጠራ የሚካሄደው በዲጂታልሳተላይት ስርዓት በመታገዝ ነው ያሉት አቶ ሼኮ የአፋር ስምጥ ሸለቆን ጨምሮ ለዲጂታል ስርዓቱ አመቺ ባልሆኑ አንዳንድ የአገሪቱ ክፍሎች ቆጠራው የሚካሄደው ከዚህ በፊት በነበረው አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።ምንጭ፡ ኢፕድ ### Response:
### Text: 1 የመጀመሪያው የገዳ ፌስቲቫል ከፊታችን መስከረም 20 2012 ዓም ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለፀ።በዘንድሮ ዓመት በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እና በቢሾፍቶ ሆራ ሀርሰዴ የሚከበሩ የኢሬቻ በዓላት መስከረም 24 እና 25 2012 እንደሚበሩ ይታወቃል።የመጀመሪያው የገዳ ፌስቲቫል እና ታላቁ የኢሬቻ ሩጫ የዚሁ በዓል አካል መሆናቸው ተገልጿል። በዚሁ መሰረት መጀመሪያው የገዳ ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማእከል እንደሚካሄድ የፌስቲቫሉ አዘጋጅ ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።በኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስተባባሪነት የሚዘጋጀው የገዳ ፌስቲቫል ከፊታችን መስከረም 20 ጀምሮ እስከ መስከረም 30 2012 ዓም ድረስ ይካሄዳልም ተብሏል።በፌስቲቫሉ ላይ በኢሬቻ በዓል እንዲሁም የገዳ ስርዓት በአንድነት፣ በኢኮኖሚያዊ እና በማህበራዊ ዝርፍ ያለው ፋይዳ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀርቡ ተገልጿል። እንዲሁም የሙዚቃ ኮንሰርት እና የኦሮሞ ባህል አውደ ርዕዮችም የፌስቲቫሉ አካል እንደሆኑም ነው አዘጋጅ ኮሚቴው በመግለጫው ያስታወቀው።ታላቁ የኢሬቻ ሩጫም የፊታችን መስከረም 11 2012 ዓም እንደሚካሄድ እና በሩጫው ላይም ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሚካፈሉ ይጠበቃል መባሉ ይታወሳል። ### Response:
### Text: ከ38 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት በበጎፈቃድ መሰብሰብ ተችሏል በትምህርት ሚኒስቴር አነሳሽነት የተጀመረው የእኛ ለእኛ የበጎ ፈቃደኞች መርኃግብር ላይ ላለፉት 3 ወራት ለተሳተፉ በጎፈቃደኛ ወጣቶች ዛሬ በትምህርት ሚኒስቴር ቅጥር ግቢ ሚኒስትር ዴኤታዋ ወሮ ጽዮን ተክሉ በተገኙበት የሰርተፍኬት አሰጣጥ መርኃግር ተከናውኗል፡፡ በአጠቃላይ የበጎ ፈቃድ ዘመቻው ከ350 በላይ በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ለሚገኙት በጎፈቃደኞች ይህ መርኃግብር ተዘጋጅቷል፡፡ በሦስት ወር የበጎ ፈቃድ ስራ በትምህርት ቁሳቁስ ከ3 ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ሺ በላይ የተሰበሰበ ሲሆን በአልባሳትና በሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ከገቢዎች ሚኒስቴር የተገኘውን ድጋፍ ጨምሮ 30 ሚሊየን የሚቆጠር ድጋፍ ማሰባሰብ ተቻለ ሲሆን በአጠቃላይ ግን በዚህ መርኃግብር 38 ሚሊየን ሀብት መሰብሰብ ተችሏል፡፡ በዚህም በበርካታ ቦታዎች የሚገኙ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ጉዳት ትምህርታቸውን መከታተል ላልቻሉና ችግር ለደረሰባቸው አከባቢዎች ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡ በቀጣይ የትምህርት ሚኒስቴር በእኛ ለእኛ የበጎፈቃድ አገልግሎት ስር የተማረ ያስተምር የተሰኘ መርኃግብር የሚጀመር ሲሆን በዚህም በርካታ በጎፈቃደኞች ይሳተፉበታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ### Response:
### Text: ማሳሰቢያ በሌሊት አካባቢያቸውን የሚጠብቁ ሁሉ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት ማክበር አለባቸው የደብረብርሃን ሰላምና ህዝብ ደህንነት ጽ ቤት የደብረብርሃን ሰላምና ህዝብ ደህንነት ጽ ቤት በሌሊት አካባቢያቸውን የሚጠብቁ ሁሉ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት ማክበር እንዳለባቸው አሳስቧል።ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ በወቅታዊ ሀገራዊ ችግር ምክንያት ነዋሪዎች ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተቀናጅተው አካባቢያቸውን እየጠበቁ እንደሚገኙ አስታውሰዋል፡፡ይሁን እንጂ ህብረተሰቡ አካባቢውን በተራ በመጠበቅ ሰላሙን ማረጋገጥ መቻሉ መልካም እና በቀጣይ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር ቢሆንም አንዳንድ የሌሊት የጥበቃ ተረኞች የዜጎችን ሰብኣዊ መብት የጣሱ መኖራቸው መልካሙን ስራ አጉድፎታል ብለዋል፡፡መስከረም 12 ቀን 2014 ዓም በቀበሌ 07 ሌሊት አካባቢያቸውን ሲጠብቁ ከነበሩት ውስጥ አንድ ሰው በጥይት መምታቱን ጠቅሰው ድርጊቱን የፈጸመው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው እየተደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።በቀጣይም ከህግ ጋር የሚጻረር ተግባር ሲፈጽሙ የሚገኙ ሲያጋጥሙ ለሚመለከተው አካል ማስረከብ ይገባል ያሉት ኃላፊው ህብረተሰቡ ለወጣው ህግ ተገዢ በመሆን ከምሽቱ 4 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ እንዲያቆም አሳስበዋል፡፡ ### Response:
### Text: ኤርትራ ሩስያ የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ።የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው ባወጡት ቃል ፕሬዚደንት ኢሳይያስ እና ፕሬዚደንት ፑቲን ዛሬ ረቡዕ ከቀትር በኋላ ባደረጉት ቆይታ የአገሮቻቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ዐለም አቀፍ ጉዳዮች እንዲሁም በጋራ ትኩረት በሚሰጧቸው ሁኔታዎች ዙሪያ በስፋት መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡አያያዘውም የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ በሩሲያ ፌዴሬሽን ያደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝት ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ፕሬዚደንት ፑቲን አስምረውበታል ብለዋል፡፡የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ርምጃ ሙሉ በሙሉ አመርቂ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ፑቲን መናገራቸው አክለው በመጪው ሐምሌ ወር ሞስኮ በምታስተናግደው ሁለተኛው የሩሲያ እና የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንዲገኙ ጋብዘዋቸዋል ብለዋል፡፡የኤርትራ ፕሬዚደንት በበኩላቸው ጉብኝታቸው የሁለቱን ሀገሮች ከፍተኛ የአጋርነት እና የምክክር ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን መናገራቸውን የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረ መስቀል አመልክተዋል፡፡ ቪኦኤ ፎቶ የማነ ገመስቀል ### Response:
### Text: በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የነን ካፌ ተማሪዎች መመገቢያ ወይም በግቢው ተማሪዎች ክፍያ ከፍለው የሚጠቀሙባቸው ካፌዎች የጥራት ጉድለት እንዳለባቸው ተማሪዎች ገለፁ። ተማሪዎች እንደሚሉት ካፌዎቹ ጨረታ የሚያሸንፉት በከፍተኛ ገንዘብ በመሆኑ ትርፍ ለማግኘት ሲሉ ደረጃውን ያልጠበቀ እና የወረደ ምግብ እያቀረቡ እንደሆነ ገልፀዋል። ተገልጋይ ተማሪዎች ጉዳዩን ለተማሪዎች ህብረት በተደጋጋሚ ቢናገሩም እስካሁን ድረስ ምንም ለውጥ ሊመጣ አልቻለም። የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እንደሚሉት ከሆነ ውጭ ወጥቶ ለመመገብ እሩቅ ስለሆነ ሳይፈልጉ በግድ ጥራት የሌለው ምግብ ለመመገብ ተገደዋል። ኦባማ ዋይትሀውስ ኢሳኮር የድሮው ኦባማ ከላይ የተጠቀሱት በግቢው አገልግሎት የሚሰጡ ካፌዎች እጅጉን ተማሪዎችን እንዳስመረሩ እና ተማሪዎች ገንዘብ ከፍለው እንኳን ጥሩ ምግብ ሊያቀርቡ እንዳልቻሉም መረጃውን የላኩት ተማሪዎች ገልፀዋል። የተማሪዎች ተወካይ ነን የሚለው የተማሪዎች ህብረት በዚህ ጉዳይ መፍትሄ ባለማምጣቱ እጅግ እንዳዘኑ ተማሪዎቹ ጨምረው ገልፀዋል። የሚሰማ የመንግስት አካል እና የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካለ ይህ መልክት እንዲተላለፍ ልከዋል። እኔም ይኸው ወደናተ አድርሻለሁምንጭ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ### Response:
### Text: ሜቴክ️ሰሞኑን ከታሰሩት የሜቴክ እና ደኅንነት አመራሮች እና አባላት መካከል የተወሰኑት ሥም ዝርዝር ይፋ ወጥቷል፡፡ ከእነዚህም መካከልየሰሜን ጎንደር ደኅንነት ሃላፊ አቶ አሸናፊተስፋሁን ፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የአማራ ክልል ደኅንነት ሃላፊ የነበረው አቶ ነጋኑሩ ፣በሱማሌ ክልል የደኅንነት ሥራዎችን ሲያስተባብር የነበረው አቶ ቢኒያምማሙሸት ፣ በደኅንነቱ ሥር የግንቦት 7 ክትትል ዴስክ ሃላፊ የነበረው አቶ ሸዊትበላይ ፣የሐረሬ ክልል ደኅንነት ሃላፊ የነበረው አቶ ተከተል የአባት ሥም አልተጠቀሰም፣ የክትትል መምሪያ ሃላፊ እና የአፋኝ ቡድን ቁልፍ አባል የነበረው አቶ አጽብሃግደይ እና የጸረስለላ መምሪያ ሃላፊ የነበረው አቶ ሳሙዔል የአባት ሥም አልተጠቀሰም ይገኙበታል፡፡በተያያዘ ዜናበሙስና ተከሰው የታሰሩት የሜቴክ እና ደኅንነትና መረጃ አመራሮች ዛሬ ከሰዓት በኋላ ፍርድ ቤት ቀርበዋል ። ተጠርጣሪዎቹ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ልደታ ምድብ 10ኛ ወንጀል ችሎት ነው የቀረቡት፡፡ ፍርድ ቤት ከቀረቡት ውስጥ 36ቱ በሰብዓዊ መብት ጥሰት የተጠረጠሩ ሲሆኑ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት ደሞ 27 ናቸው፡፡ አቃቤ ሕግ በሁለቱም ምድብ ተጠርጣሪዎች ላይ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ምንጭ ዋዜማ ራድዮ ### Response:
### Text: የኦሮሞ እና የአማራ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ምሁራን በዜጎች ደህንነት ላይ ልዩነትን በማጥበብ የጋራ ጉዳዮችን ይዞ መሄድ በሚል ሀሳብ ላይ ምክክር ማድረጋቸው ተገለጸ፡፡ምክክሩ የተደረገው የሁለቱ ብሄር ፖለቲከኞችና ምሁራን በሁለቱ ህዝቦች የጋራ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የጋራ ሀሳብ መያዛቸው አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው ተብሏል።የሁለተኛው የጋራ መድረክ ባለ አምስት 5 ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫ ኢትዮጵያ የብዙ ብሄሮችና ብሔረሰቦች፣ ሃይማኖቶችና የፖለቲካ አመለካከቶች ሀገር መሆኗን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያለባት እንድትሆን ተስማምተናል ሁለቱ ህዝቦች ሰፊ የሆነ የጋራ መስተጋብርና ማህበራዊ ትስስር ያላቸው መሆኑን ተገንዝበናል የሁለቱን ህዝቦች አሰፋፈር እና የጋራ አኗኗር ከግንዛቤ በማስገባት ሰላምና መረጋጋትን እንዲሁም መሰረታዊ መብቶችን ማረጋገጥ የሁላችንም ኃላፊነት መሆኑን ተረድተናል ዝርዝር ታሪካዊ ጉዳዮችን ለአጥኚዎች በመተው በሚያግባቡን ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ተግባባተናል ይህን በፖለቲካ ፓርቲዎችና ልሂቃን የተጀመረውን ውይይት ደረጃ በደረጃ እያዳበርን ለመሄድ በውይይታችን ተስማምተናል፡፡ ኢዜአ ### Response:
### Text: ቲክቫህ ኢትዮጲያ ከ ጋር በመተባበር ከአፋር፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች 14 ወረዳዎች0 ለተዉጣጡ 56 ወጣቶች በዲጂታል ሰላም ግንባታና መሰረታዊ የሚዲያ ክህሎት ላይ በየክልሉ የ4 ቀን የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጥተዋል፡፡ ስልጠናው ቴክኖሎጂ በተለይ ማህበራዊ ሚዲያ እንዴት የግጭት መንስዔ ሊሆን እንደሚችልና ግጭቶችን እንደሚያባብስ፣ እንዴት የሰላም ግንባታ ጥረቶችን ሊደግፍ አንደሚችል እንዲሁም በዲጂታል ሰላም ግንባታ ላይ የወጣቶች ሚና ምን እንደሆነ፣ የወጣቶችን እምቅ አቅም እንዴት ለዲጂታል ሰላም ግንባታ መጠቀም እንደሚቻል ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡ በስልጠናው ላይ ወጣቶቹ በየአከባቢያቸው ለግጭት መንስዔ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት፣0 በመተንተንና ማህበራዊ ሚዲያው ግጭቶችን በማባባስ ረገድ ያለውን አስተዋጽኦ በመለየት የመፍትሄ ሃሳቦችን አስቀምጠዋል፡፡ ስልጠናውን የተከታተሉ 56 ወጣቶች ወደ የክልሎቻቸው በመውረድ በ14ቱም ወረዳ ለሚገኙ 280 ሌሎች አቻ ወጣቶቻቸውና ማኅበረሰቦቻቸው በቀጥታ መድረስ ተችሏል፡፡ስልጠናውን ተከትሎ የአፋር ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ሌሎች ወጣቶችና ማህበረሰቦች ስልጠናውን ለሰጡና ላመቻቹ ወጣቶች የታብሌትና ፓወር ባንክ የማበረታቻ ሽልማት ሰጥቷል፡፡ ### Response:
### Text: እጅግ አሳዛኝ ዜና ታላቁ የጥበብ ሰው ጋሽ ፍቃዱ ተክለማርያም ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጭ ሆኑ የወገኖቹንም ድጋፍ ጠይቋል፡፡በሀገራችን ስማቸው ቀድሞ ከሚነሱ የመድረክ ፈርጦች አንዱ የሆነው ጋሽ ፍቃዱ ተክለማርያም ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጭ በመሆናቸው በከፋ ህምም ላይ እንዳለ እና የህዝቡ ድጋፍእንደሚያስፈልገው ተገለጿል፡፡ላለፈው አንድ ወር በቤተሰብ እና ወዳጅ እገዛ ህመሙን ለመቆጣጠር መሞከሩን የገለጹልን የድጋፍ ኮሚቴ አስተባባሪዎቹ በቤተሰብ በኩል አስፈላጊውን የህክምና ክትትል እና ኩላሊት ለመለገስ ጭምር የተሞከረ ቢሆንም ለአርቲስቱ የሚያስፈልገው የኩላሊት እና የደም ሁኔታ ከፍቃደኞቹ ጋር ሊገጥም ባለመቻሉ ሙከራው እንዳልተሳካም ነው ለሸገር ታይምስ የተናገሩት፡፡ከህክምናው አቅም ጠያቂነት እና ከተፈላጊው ኩላሊት ካለመገኘት አንፃር በቤተሰብ ብቻ ተይዞ የነበረውን ይህን ጉዳይ አማራጭ በማጣት ለህዝብ ይፋ ያደረጉት አርቲስቱ እና ቤተሰቦቹ በአስተባባሪዎች በኩል በነገው እለት ከረፋዱ 4፡00 ጅምሮ በአፍሮዳይት ሆቴል ለመገናኛ ብዙሃን አካላት መግለጫ እንደሚሰጡም ነው ለሸገር ታይምስ የጠቆሙት፡፡ እባክዎት ይህን ሼር በማድረግ በርካቶች ጋር አንዲደረስ በማድረግ ይተባበሩንምንጭ ### Response:
### Text: የአድዋ ድል በአልን ምክንያት በማድረግ በ 6 የሚዘጋጅ የ 3ቀናት ዘመቻበጫማ ጠረጋ ሊስትሮ የሚደረግ የገቢ ማሰባሰቢያ ገቢው የሚሰበሰበው በተመረጡ የከተማችን አካባቢወች ሲሆን ከ ሰበታ አጃምባ ተፈናቅለው ዓለም ባንክ ለሚገኙ ተጎጂዎች የሚደረግ በጎ ፈቃደኞች የሚከናወን ለ3 ቀናት የሚቆይ የጫማ ጠረጋ ሊስትሮ ዘመቻ ነው፡፡ መጽሐፍ ማሰባሰብ ይህም ዘመቻ በደቡብ ክልል በወራቤ ከተማ ለሚገኘው ወራቤ 1ኛ ደረጃ ትቤት ቤተ መጽሐፍት ሁሉም ሰው ለ 3 ቀናት አድዋን በማሰብና የተለያዩ መጽሐፍትን በበጎ ፈቃደኝነት በማበርከት የእንቅስቃሴው አካል የሚሆንበት ነው፡፡ ዘረኝነትን የመቃወም ዘመቻዘመቻው ዘረኝነት ፣ ጥላቻ የሚሉ ፅሁፎችን በተመረጡ የከተማችን አካባቢዎች በሚቀመጡ የቆሻሻ ቅርጫቶች ውስጥ በመጣል ሁሉም የሚሳተፍበት ትዕይንት ነው፡፡ማሳሰቢያ1 በጫማ ጠረጋው ላይ ለመሳተፍና ተጎጂዎችን መርዳት የምትፈልጉ በውስጥ መስመር አነጋግሩን፡፡2 መፅሐፍት በመለገስ መሳተፍ የምትፈልጉ ፒያሳ አራዳ ህንፃ ዋው በርገርሜክሲኮ ጃዕፋር የመፅሐፍት መደብርአራት ኪሎ ሮሚና እንዲሁም በአካል ለአስተባባሪዎቹ መስጠት ትችላላችሁ፡፡መቀላቀል የምትፈልጉ 0983007703 0938077868 0918511580 ደውሉልን፡፡ ዕውቀትነፃያወጣል አዘጋጆቹ ### Response: