text
stringlengths
707
989
### Text: የጥቆማ መስጫ ስልክ መስመሮችየአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽቤት በከተማው የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ቅሬታዎች፣ በህገወጥ መንገድ ታጥሮ የተቀመጡ መሬቶች ፣ ህገወጥ የቀበሌ ቤቶች እና የኮንደሚኒየሞች እንዲሁም በአገልግሎት መስጫ ተቋማት እና የመንግስት መስሪያ ቤት ኃላፊዎች ወይም ሰራተኞች በአጠቃላይ በከተማው ውስጥ የሚከናወኑ ማንኛውንም ህግን ያልተከተሉ ሥራዎች ላይ ህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲያደርግ ይፈልጋል፡፡ ወሪት ፌቨን ተሾመየከንቲባ ፅቤት የፕሬስ ሴክሬታሪ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ህብረተሰቡ በከተማው የሚስተዋለውን ደካማ አሰራር እና በብልሹ አሰራር የተዘፈቁ አመራሮችን እና ባለሙያዎችን እንዲጠቁሙ እና ለውጡን በመደገፍ የድርሻቸውን እንዲወጡ ለከተማዋ ነዋሪ ጥሪ አቅርበዋል፡፡በጥቆማው ላይ ሊካተቱ ከሚገባቸው መረጃዎች ውስጥ 1የድርጊቱ አይነት፣ 2የኃላፊው ሙሉ ስም3የሰራተኛው ሙሉ ስም4የአገልግሎት ዘርፍየጥቆማ መስጫ የስልክ መስመሮችየካ 251 118548252 ንፋስስልክ 251 118548067 ልደታ 251 118547907 ኮልፌ 251 118547896 ጨርቆስ 251 118548753 አዲስከተማ 251 118548423 አራዳ 251 118548397 አቃቂ 251 118548257 ቦሌ 251 118548415 ጉለሌ 251 118548638 በመጠቀም ጥቆማ በማድረስ ለውጡን እንዲደግፉ የከንቲባ ፅቤት ጥሪውን አቅርቧል።ምንጭ የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን ### Response:
### Text: ወሎ ዩኒቨርሲቲደሴ ካምፓስ የተቋረጠውን ትምህርት ለማስቀጠል ዛሬ ከተማሪ ተወካዮች ጋር ውይይት እንደሚደረግ ተነግሮናል። አብዛኛው ተማሪ ትምህርት ፈላጊ ነው ዛሬ ውይይት ከተደረገ በኃላ ነገ ትምህርት ይጀምራል የሚል ተስፋ አድሮብናል ብሎናል አንድ የወሎ ዩኒቨርሲቲ የተማሪ ተወካይ። በሌላ በኩል አሁንም ስጋታቸው ሙሉ በሙሉ እንዳተቀረፈ ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለስ እንደሚፈልጉ መልዕክቶቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ ተማሪዎች ገልፀዋል።በተመሳሳይ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒስቨርሲቲ ዛሬ ተማሪዎቹ ተመልሰው ትምህርታቸው እንዲማሩ ድጋሜ ማስታወቂያ ቢያወጣም በማህበራዊ ሚዲያዎች ውስጥ ለውስጥ የሚሰራስጩ የማስፈራሪያ መልዕክቶች ስጋት አጭረውብናል ብለዋል የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች። ዩኒቨርሲቲው እንዲህ ያሉ ነገሮችን እንዲቆጣጠር አሳስበዋል። በሌላ በኩል ባለፈው ሳምንት ትምህርት የተቋረጠባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ እየሰሩ እንደሆነ እየገለፁልን ይገኛሉ። በአንፃሩ ችግር ላይ ነን የሚሉ ተማሪዎች ድምፃችን ይሰማ ወደቤተሰቦቻችን፣ ወደ እናትና አባታችን በሰላም መልሱን እያሉ ይገኛሉ።የዩኒቨርሲቲ ሁኔታዎች07032012 1117 አዳዲስ ጉዳዮች ሲኖሩ እናሳውቃለን ### Response:
### Text: በትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈበትግራይ ደቡባዊ ዞን ራያ አዘቦ ወረዳ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ አራት ሰዎች ወድያውኑ ሲሞቱ በስድስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።በመምሪያው የትራፊክ አደጋ ደህንነትና አጣሪ ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር አብርሃ ወረደ እንደተናገሩት አደጋው የደረሰው ዛሬ ከንጋቱ 11ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ በወረዳው ኮርማ በሚባል አከባቢ ነው።የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 ትግ 08801 የሆነ የደረቅ ጭነት አይሱዝ ተሽከርካሪ ከአፋር ክልል 16 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ጨርጨር በመጓዝ ላይ እያለ ተገልብጦ አደጋው ሊደርስ መቻሉን ኮማንደሩ ተናግረዋል።በአደጋው ምክንያት ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በማይጨው ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ደግሞ በእንዳመኾኒ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።በአደጋው የሞቱት በሙሉ ሴቶች ሲሆኑ አስከሬናቸው ለቤተሰቦቻቸው መሰጠቱን ፖሊስ አያይዞ ገልጿል።አሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ውሎ በአጠቃላይ የአደጋ መንስኤውና የጭነት ተሽከርካሪ ሆኖ ሰው የጫነበትን ምክንያት ጨምሮ የተጠናከረ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡ኢዜአ ### Response:
### Text: አሜሪካ የ2025 አመልካቾችን መቀበል ጀመረች።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመታዊውን የዲይቨርሲቲ ቪዛ ዲቪ ፕሮግራም ግሪን ካርድ ሎተሪ በመባል የሚታወቀውን በአሜሪካ ለመኖር እና ለመስራት ለሚፈልጉ አመልካቾች ዛሬ ክፍት አድርጓል።እንደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ መግለጫ መርሃ ግብሩ ዛሬ ሩቡዕ ጥቅምት 4 ተጀምሮ ማክሰኞ ህዳር 7 ቀን 2023 ይጠናቀቃል።አሜሪካ አሁን ባለው ፕሮግራም 55000 ለሚደርሱ የውጭ ዜጎች የግሪን ካርድ እድል ትሰጣለች።የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዲቪ ፕሮግራም ለመመዝገብ ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ እንደሌለው አሳውቋል።ነገር ግን ወደፊት ለቃለ መጠይቅ ቀጠሮ የተያዙ ተመራጮች መደበኛ የቪዛ ማመልከቻ ከማቅረባቸው በፊት የቪዛ ማመልከቻ ክፍያ እንዲከፍሉ ይገደዳሉ። እነዚህ ተመራጮች በቆንስላ ኦፊሰር አማካኝነት ለቪዛ ብቁ መሆን አለመሆናቸውን የሚወሰንላቸው ናቸው።በአጠቃላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዲቪ ለመሙላት ብቁ ከሆኑ በርካታ ሀገራት 55000 አመልካቾች በዘፈቀደ በውስጥ ስርዓት ይመረጣሉ።አስፈላጊ መመሪያዎችን ፣ መስፈርቶችን እንዲሁም ለማመልከት ይህን ትክክለኛ ድረገፅ ይከተሉ አመልካቾች ዲቪ ለማመልከት ክፍያየማያስፈልግ ስለሆነ ከአጨባርባሪዎች እንዲጠነቀቁ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳስቧል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ መንግስት ህዝቡን ይቅርታ ጠየቅማምሻውን ለሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ጠሚር ሀይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ በተከሰተው የስኳር እጥረት ምክንያት ለተፈጠረው መጉላላት መንግስት ህዝብን ይቅርታ ይጠይቃል አሉ። እጥረቱ ስኳር በሚመረትባቸው አካባቢዎች ያልተጠበቀ ዝናብ በመጣሉ፣ ወደ ስራ ይግባሉ ተብለው የተጠበቁት አዲስ የስኳር ፋብሪካዎች ወደ ስራ ባለመግባታቸው እና ነባሮቹም በሚፈለገው ደረጃ ባለማምረታቸው የመጣ ነው ብለዋል። አሁን ላይ ስኳር ከውጭ በግዢ የገባ በመሆኑ የተፈጠረው እጥረት እየተቃለለ እንደሚሄድ ገልፀዋል።በተጨማሪም ጠሚር ሀይለማርያም ደሳለኝ ሳዑዲ አረቢያ ከሙስና ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ካዋለቻቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው ቢሊየነርየሼክ መሀመድ ሁሴን አሊ አል አሙዲንን በተመለከተ መንግስት በዲፕሎማሲያዊ መልኩ ጉዳዩን አስመልክቶ መረጃን እየተከታተለ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህን ተከትሎ በኢትዮጵያ ባለው የእሳቸው ኢንቨስትመንት ላይ እክል ይፈጠራል ብሎ መንግስት እንደማያምንም ነው የገለፁት።ከዚህ ውጭ ግን ሳዑዲ አረቢያ ሉዓላዊ ሀገር እንደመሆኗ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ሌላ ሊሰራ የሚችል ነገር እንደሌለ አስታውቀዋል።ምንጭ ፋና ብሮድካስቲንግ ### Response:
### Text: ስምምነት ሊፈራረሙ ነውየአማራና ትግራይ ክልሎች ርዕሳ መስተዳድሮች ስምምነት ሊፈራረሙ ነው፡፡ የአማራና ትግራይ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች በሁለቱ ክልሎች መካከል እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ስምምነት ዛሬ በሂልተን ሆቴል ከደቂቃዎች በኋላ ይፈራማሉ ፡፡ሕዝቡ ችግሩ የአማራና ትግራይ ክልሎች መንግሥታት ነው ማለቱንና በሁለቱ ክልል ሕዝቦች መካከል ችግሮች አለመኖራቸውን የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል፡፡የሁለቱን ክልል መንግሥታት መሪዎች ችግሮች መፍትሔ ለመፈለግ ለስድስት ወራት ሕዝቡንና በየደረጃው ያሉ አመራሮችን ያወያዩት የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች አሁን ሁለቱም ርዕሰ መስተዳድሮች ችግሩን ለመፍታት ጫፍ መድረሳቸውን አስታውቀዋል፡፡የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ናቸው ስምምነቱን ይፈራረማሉ፡፡የማስማማት ሂደቱን የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በራሳቸው ተነሳሽነት እንደጀመሩት ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የሀገር ሺማግሌዎች ከስድስት ወራት በፊት በፈቃዳቸው ተገናኝተው ወደ ማሸማገል ሂደት መግባታቸውን ነው ያስረዱት፡፡ምንጭ አብመድ ### Response:
### Text: ክብ ውስተ ደመናበደሴ እና በአንዳንድ የወሎ አካባቢዎች በፀሐይ አካባቢ የታየው ክስተት ግርዶሽ አይደለም ተብሏል፡፡ ክስተቱ የፀሐይ ግርዶሽ ሳይሆን የክብ ቀስተ ደመና መፈጠር ነው ተብሏል፡፡በወሎ ዩኒቨርስቲ የፊዚክስ መምህርና በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የህዋ ሳይንስ የዶክትሬት ተማሪ መምህር ሰይዴ መብሬ ስለክስተቱ ማብራሪያ ሰጥተውበታል፡፡ እንደ መምህሩ ገለጻ ዛሬ ግንቦት 292011 ዓም በደሴና በአንዳንድ የወሎ አካባቢዎች የተፈጠረው ትዕይንት የፀሐይ ግርዶሽ ሳይሆን ክብ ቀስተ ደመና ነው፡፡እንደ መምህሩ ገለፃ ብርሃን ከአንዱ ውሳጭ ወደ ሌላ ውሳጭ ሲሸጋገር ስብረት ያካሂዳል፡፡ በዚህ ወቅት የብርሃን 7ቱ ቀለማት ይበተናሉይህም ቀስተ ደመና ይፈጠራል፡፡ በመሆኑም ዛሬ በደሴና በአንዳንድ የወሎ አካባቢዎች የተፈጠረው የፀሐይ ትዕይንት የፀሀይ ግርዶሽ ሳይሆን ክብ ቀስተ ደመና ነው ብለዋል፡፡ቀስተ ደመናው ክብ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ፀሐይ በአናት ላይ ስለሆነች እና ደመናውም ቀስተ ደመና ለመፍጠር ጥሩ ሁኔታ ላይ ስለነበር ነው ብለዋል መምህሩ፡፡ ክስተቱ የተፈጠረው በታችኛው የከባቢ አየር ንጣፍ ነው ያሉት የህዋ ሳይንስ የዶክትሬት ተማሪው ይህም ማለት ከመሬት እስከ 10 ኪሜ ከፍታ የተፈጠረ ክስተት እንደሆነ ነው ያስረዱት፡፡ አብመድ ### Response:
### Text: አዲስአበባ በአዲስ አበባ የነበረው የኢሬቻ በአል አከባበር ባማረ መልኩና በሰላም ተጠናቋል። ይህን አስመልክቶም የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለከተማዋ ነዋሪዎችና ለበአሉ አከባበር አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ የምስጋና መልእክት አስተላልፈዋል።ኢንጂነር ታከለ በሁሉም የከተማዋ ጫፎች የሚገኙ የከተማዋ ነዋሪዎች ያሳዩት ትብብር የሚደነቅና የሚከበር ነው ብለዋል። በአሉን ለማክበር ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡትን በልዩ ፍቅርና ያላቸውን በማቅረብም ጭምር አክብሮታቸውን ስላሳዩም ለከተማዋ ነዋሪዎች ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።የከተማዋ ባለሀብቶችም የበአሉን አከባበር በመደገፍ በአሉ እውን እንዲሆን ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋናን አቅርበዋል። በበአሉ ላይ አንድም የጸጥታ ችግር እንዳይፈጠር በበቂ ዝግጅትና በሀላፊነት ስሜት በብቃት ለሰሩ የጸጥታ አካላትም ምስጋናን አቅርበዋል።ለጸጥታው መከበር ወጣቶች ያሳዩትንም ተሳትፎና ትብብርም የሚደነቅ ነው ብለዋል ኢር ታከለ ኡማ። ኢንጂነር ታከለ ኡማ በአጠቃላይም አዲስ አበባ ህብረብሄራዊነቷን በጠበቀና ባማረ መልኩ የኢሬቻ በአል በመዲናዋ እንዲከበር ድጋፍ ላደረጉና በጨዋነት ለተባበሩ በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናቸውን መግለፃቸውን የከንቲባ ፅሀፈት ቤት አስታውቋል። ### Response:
### Text: በኮቪድ19 የተያዙ ሰዎች ከ5000 አለፉባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 4034 የላብራቶሪ ምርመራ 186 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5034 ደርሷል።ቫይረሱ የተገኘባቸው 73 ወንድ እና 113 ሴት ሲሆኑ የእድሜ ክልላቸው ከ6 ወር 75 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 181 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 5 የውጭ ዜጋ ናቸው።147 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 16 ሰዎች ከሱማሌ ክልል ፣ 10 ሰዎች ከአፋር ክልል፣ 8 ሰዎች ከድሬዳዋ ከተማ፣ 4 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል እና 1 ሰው ከደቡብ ክልል ናቸው።ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 35 15 ከጤና ተቋም እና 20 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን ሁለት ናሙናዎች ከጤና ተቋም የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበቸዋል። በተጨማሪ አንድ 1 በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበር ሰው ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰባ ስምንት 78 ደርሷል፡፡ በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ሰባ አራት 74 ሰዎች 63 ከአዲስ አበባ፣ 6 ከትግራይ ክልል፣ 2 ከሶማሊ ክልል፣ 2 ከደብብሕ ክልል፣ እና 1 ሐረሪ ክልል ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1486 ደርሰዋል። ### Response:
### Text: በ13 ከተሞች አዲስ የወባ በሽታ ተህዋስ አስተላላፊ ትንኝ መሰራጨቱ ተገለፀ በኢትዮጵያ 13 ከተሞች አዲስ የወባ በሽታ ተህዋስ አስተላላፊ ትንኝ መሠራጨቱን አርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ ከዚህ ቀደም ከነበሩት ትንኞች የሚለየው ለመራባት የሚመርጠው አካባቢ ከተሞችን መሰረት ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ኢንስትትዩቱ ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት መሰረት አዲስ የወባ በሽታ ተህዋስ አስተላላፊ ትንኝ በሶማሌ፣ አፋር፣ አማራና ምሥራቅ ኦሮሚያ ክልሎች መስፋፋቱን አመላክቷል፡፡አዲስ የወባ በሽታ ተህዋስ አስተላላፊ ትንኝ ከተሰራጨባቸው ከተሞች ሰመራ፣ ገዋኔ፣ አዋሽ፣ ኤረር፣ ጅግጅጋ፣ ቀብሪደሃር፣ ጎዴ፣ ደጋሃቦር፣ ደሬደዋና መታሃራ እንዲሁም ባቱ ፣ መቂ እና ሞጆ ተጠቅሰዋል፡፡የተጣሉ ጎማዎች፣ የፕላስቲክ ዕቃዎች፣ የተለያየ ስሪት ያላቸው የውሃ ማጠራቀሚያዎች ለመራባት የሚመርጣቸው ቦታዎች መሆናቸው በእስካሁኑ ጥናት ተደርሶበታል፡፡ አዲሱ የወባ በሽታ አስተላላፊ ትንኝ ዝርያ በኢትዮጵያ በ2008 ዓም የታየ ሲሆን ከዚያ ቀደም ባሉት ጊዚያት በምሥራቅ አረብ ፔንሱላ እና አፍሪካ ቀንድ አካባቢዎች ይታይ እንደነበር ነው የተገለጸው፡፡በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ለመጀመሪያ ጊዜም በ2004 ዓም በጅቡቲ ተገኝቶ እንደነበር ተነግሯል፡፡ ### Response:
### Text: ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረገ ይገኛልትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግና ኮሮናን በመከላከል ትምህርት መጀመር የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እያጠና ይገኛል።በተደረጉ የዳሰሳ ጥናቶች ተማሪዎች የትምህርት መጀመርን በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን ለመረዳት እንደተቻለ ሚኒስቴሩ ገልጿል። በሌላ በኩል ወላጆች የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ባለበት በአሁኑ ወቅት ልጆቻቸው ትምህርት ቤት ሲሄዱ ለኮሮና ቫይረስ ሊጋለጡ ይችላሉ የሚለው ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡እነዚህን ተቃራኒ ሃሳቦች ከግምት ውስጥ በማስገባት ትምህርት ሚኒስቴር እንደ አካባቢዎቹ ወቅታዊ የኮሮና ስርጭት ሁኔታ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ በደረጃ መክፈት የሚያስችሉ መንገዶችን እየገመገመ ይገኛል። ትምህርት ሚኒስቴር እያካሄደ ባለው ጥናት ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት በአንድ ክፍል ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ማስተማር ፣ የንፅህና መጠበቂያ ለትምህርት ቤቶች ማቅረብ፣ ተጨማሪ ትምህርት ቤቶችን መገንባት የሚሉ አማራጮች ቀርበዋል። ሚኒስቴሩ ጥናቱ ሲጠናቀቅ በሚቀርበው ተጨማሪ ምክረ ሃሳብ መሰረት አስፈላጊው ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ትምህርት ለመጀመር ጥረት ይደረጋል ብሏል። ### Response:
### Text: ወላጆች ልጆቻችሁን ጠብቁ ትላንት በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ዋና እንዋኛለን ብለው ወንዝ ውስጥ ከገቡ 2 ልጆች የአንዱ ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።ህይወቱ ያለፈው የ12 ዓመት ታዳጊ መሆኑ ተነግሯል።የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ ንጋቱ ማሞ ወረዳ አንድ ለቡ አርሴማ አካባቢ ነው በአንድ ወንዝ ውስጥ እድሜያቸው የ8 እና የ12 ዓመት ታዳጊዎች ዋና ለመዋኘት በሚል ነው ወንዝ ውስጥ ገብተው ዋና ሲዋኙ የ12 ዓመት ታዳጊው ህይወቱ አልፏል። የ8 ዓመቱ ታዳጊ በአካባቢው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተረባርበው እሱን ከነህይወቱ አውጥተውታል። ጥሪው ለኛ ቢመጣም እኛ ከመድረሳችን በፊት ህይወቱ የተረፈውን የ8 ዓመት ታዳጊ እና የሞተውን ልጅ የአካባቢው ህብረተሰብ አውጥተውታል ሲሉ ሁኔታውን አስረድተዋል።በዚህ ወር ብቻ ዋና ለመዋኘት በሚል ወንዝ ከገቡት 3 ልጆች ህይወታቸው አልፏል።የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ወላጆች አሁን ትምህርት ቤት የሚዘጋበት ወቅት በመሆኑ ታዳጊዎች ወደ ወንዝ እንዳይሄዱ ማድረግ በከተማው ያሉ ገደላማ እና ውሃ የሚያቁሩ ቦታዎችን መከለያ በማበጀት ልጆችን ከአደጋ መጠበቅ ይገባል ሲል ማሳሰቡን ሸገር ኤፍ ኤም 1021 ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል። ### Response:
### Text: ለግል መገልገያ ከቀረጥ እና ታክስ ነፃ ሆነው የሚገቡ ዕቃዎች የትኞቹ ናቸው ሲጋራ መለኪያ ግራም 0 የሚፈቀደው መጠን 200 ሲጋር መለኪያ በቁጥር 0 የሚፈቀደው መጠን 20 ብትን ትንባሆ መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 250 የአልኮል መጠጥ መለኪያ ሊትር የሚፈቀደው መጠን 2 ለስላሳ ሽቶ መለኪያ ሚሊ ሊትር የሚፈቀደው መጠን 500 ሽቶ መለኪያ ሚሊ ሊትር የሚፈቀደው መጠን 500 ሞባይል መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 2 ሁለት ላፕቶፕ መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 1 አንድ የፎቶግራፍካሜራ መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 1 ዊልቸር መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 1 የእጅሰዓት መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 1 የፂም ወይም የፀጉር መላጫ መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 1 የፀጉር ማድረቂያ መለኪያ በቁጥር 0 የሚፈቀደው መጠን 1 የፀጉር መተኮሻ መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን 1 መንገደኛው የሚጠቀምባቸው መድሃኒቶች እና የህክምና በቁጥር መገልገያዎች መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን ለአንድ ሰው በሚያስፈልግ መመጠን በጉዞ ወቅት ጥቅም ላይ የሚውሉ እና ለቤተሰብ የሚያገለግሉ ፣ ልብሦች፣ ጫማዎች፣ እና የፅዳት እቃዎች መለኪያ በቁጥር የሚፈቀደው መጠን ለአንድ ቤተሰብ ከሚያስፈልገው ያልበለጠየተሻሻለው የግል መገልገያ እቃዎች የጉምሩክ መመሪያ 73728 ### Response:
### Text: በአስቸኳይ መስጂዶችን ማፍረስ አቁሙ የፈረሱትንም በፍጥነት መልሳችሁ አሰሩ ህዝበ ሙስሊሙንም በይፋ ይቅርታ ጠይቁ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትየኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዲሱ በሸገር ከተማ መስጂዶች እየፈረሱ መሆኑን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም አሳሰበ።ምክር ቤቱ ለኦሮምያው ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በፃፈው ደብዳቤ ነው ይህንን ማሳሰቢያ ያስተላለፈው።ጠቅላይ ምክር ቤቱ በደብዳቤው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እየፈረሱ ያሉ መስጂዶች በአስቸኳይ እንዲያስቆም ብሏል።ከዚህ ባለፈም የፈረሱ መስጂዶች በሸገር ከተማ አስተዳደር በፍጥነት እንዲሰሩና ሕዝበ ሙስሊሙን አስተዳደሩ በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ አሳስቧል።የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ለጠቅላይ ምክር ቤቱ በተፃፈው ደብዳቤ 1 በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ ዉንዴሳ ወረዳ ልዩ ስፍራ ቀርሳ በቀን 1407152 በሸገር ከተማ ሰበታ ክፍለ ከተማ መጉላ ቶውፊቅ መስጂድ 1908153 በሸገር ከተማ መልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ ወረዳ ልዩ ስሙ አን ኢ ሳይት ሰላም መስጂድ በቀን 2408254 በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ አሸዋ ሜዳ በቀን 250815 መፍረሳቸውና ጉዳዩ ከአቅሙ በላይ መሆኑን አሳውቋል። ### Response:
### Text: የኦነግ መግለጫበኢትዮጵያ መንግስት እየተፈጸመ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በነፃ እና ገለልተኛ አካል ምርመራ ልደረግበት ይገባል ከምዕራብ ኦሮሚያ የወለጋ ዞኖች ቴሌፎንና ኢንተርኔትን የመሳሰሉት የመገናኛ አገልግሎቶች በመንግስት ከተቋረጡ 1 ወር ኣለፈ። ከዚህም የተነሳ የዕለት ተዕለት ክስተቶችን በጊዜዉ ከነበቂ መረጃ ጋር ማግኘት አዳጋች ብሆንም እንኳ የመንግስት ወታደሮችና ታጣቂዎች በሰላማዊ ትጥቅኣልባ ዜጎች ላይ እያካሄዱ ባሉት ግድያ የሰዎች ህይወት እንደቅጠል እየረገፈ መሆኑ መተለያየ መንገድ እየተሰማ ነዉ። በተለይም በሁለት ዞኖች ምዕራብ ወለጋ እና ቄሌም ወለጋ ዉስጥ የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች በሕዝቡ ላይ እየፈጸሙ ያሉትን ግድያና ጭፍጨፋ በቃላት መግለጽ እንኳን ይከብዳል። የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚሉት ቃላቶችም በትክክልና በበቂ ሁኔታ ልገልጹት ኣይችሉም። በደቡብ ኦሮሚያ በጉጂ ዞኖች ያለዉ ሁኔታም እምብዛም ከዚህ የተለየ አይደለም። በዚህ መልኩ ከአንድ ዓመት በላይ በወታደራዊ አስተዳደር ኮማንድ ፖስት ሥር በሕዝቡ ላይ እየደረሰ ያለዉን እሮሮና ስቃይ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸን መፍትሄ እንድፈለግለት ብንወተዉትም እስካሁን የሕዝባችን ኡኡታና ችግሩ ተገቢዉን ተሰሚነት ሊያገኝ አልቻለም። 0202 ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት 123 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል ከመጋቢት 10 በኃላ የተመዘገበ ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ነው። በዩናይትድ ኪንግደም ከመጋቢት 17 በኃላ ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ተመዝግቧል ባለፉት 24 ሰዓት 210 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 32000 ደርሷል። ኮቪድ19 በቻይና ዳግም እንዳያገረሽ ተፈርቷል ባለፉት 24 ሰዓት 17 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል አምስቱ 5 ከውሃን ከተማ ናቸው። በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር 80807 ደርሷል 1369157 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ 246345 ሰዎች አገግመዋል። በደቡብ ኮሪያ የኮቪድ19 ወረርሽኝ እንዳያገረሽ ተፈርቷል ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 35 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በሩሲያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከጣልያን እንዲሁም ከፈረንሳይ በልጧል። ባለፉት 24 ሰዓት 11656 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 221344 ደርሷል። በሳዑዲያ አረቢያ በአንድ ቀን 1966 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል እስካሁን በአንድ ቀን ከተመዘገበው ከፍተኛው ነው አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 41014 ደርሷል። በመላው ዓለም ከኮሮና ቫይረስ ኮቪድ19 ያገገሙ ሰዎች ከ1500000 በልጧል እንዲሁም በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ 4215497 ሰዎች መካከል 284680 ሰዎች ሞተዋል። ### Response:
### Text: ከሰኔ 302011ዓም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ እንዳይደረግ ተከለከለ፡፡ኢር ታከለ ኡማ በከተማዋ አጠቃላይ የፀጥታ ሁኔታ እና የክረምት የበጎ ፈቃድ ስራ ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የአለምአቀፍ ተቋማት መቀመጫ፣ የአገራችን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበበ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተደራጀ መልኩ በሞተር ሳይክል በመታገዝ የቅሚያ እና የዝርፊያ ድርጊቶች ተበራክተዋል፡፡የከተማዋን ፀጥታ አስተማማኝ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ ፣ ከፌደራል ፖሊስ ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ እና ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመሆን ለአንድ ሳምንት በዚሁ ዙሪያ ጥናት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡በዚህም ለሞተር ሳይክል ባለቤቶች ለ15 ቀን የሚቆይ የልምምድ ጊዜ እንዲሰጥ እና ከሰኔ 302011ዓም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከተፈቀደላቸው ውጪ ሞተር ሳይክሎች እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ተደርጓል፡፡በተጨማሪም በከተማዋ ያለውን የትራፈክ መጨናነቅ ለመቅረፍ በትራፊክ ፍሰቱ ላይ መስተጓጎል እየፈጠሩ ያሉ የጭነት መኪኖችም በቀን እንዳይንቀሳቀሱ እገደ ተደርጓል፡፡በዚህም ማንኛውም የጭነት መኪና ከማለዳ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እንዳይንቀሳቀስ ክልከላ ተደርጓል፡፡ ### Response:
### Text: ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት ዓመት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ የመስሪያ ቤቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ስራ አፈፃጸም በተመለከተ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።ወይዘሪት ፍሬ ህይወት በመግለጫቸው ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት ላይ የተለያዩ የአሰራር ማሻሻያዎች ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ተቋሙ በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያው ሩብ ዓመት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቀዋል።በዚህም የእቅዱን 98 በመቶ ማሳካት መቻሉን የገለጹት ወይዘሪት ፍሬህይወት ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 56 በመቶው ከድምጽ አገልግሎት 29 በመቶው ደግሞ ከሞባይል ዳታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል። እንዲሁም ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 41 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላሩ ከአለም አቀፋ አገልግሎቶች የተገኘ መሆኑን ነው ተናገሩት።የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ተመሳሳይ ሩብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 21 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በሩብ ዓመቱ የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 44 ነጥብ 4 ሚሊየን የደረሰ ሲሆን የደንበኞች ቁጥርም 10 በመቶ መጨመሩ ተመላክቷል። ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ ወንበሩን ባዶ በማድረግ ስብሰባውን ማለፏ በበሳል ዲፕሎማሲ የተደረገ ውሳኔ ነው አምባሳደር ዲና ሙፍቲየኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሩሲያ ዩክሬን ቀውስ ላይ በመከረው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ወንበሯን ባዶ በማድረግ ስብሰባውን ማለፏ በበሳል የዲፕሎማሲ ውሳኔ የተደረገ ነው አለ።ኢትዮጵያ በዩክሬን እና ሩስያ ጦርነት ዙሪያ በተመድ ጠቅላላይ ጉባኤ ላይ ሩስያን በማውገዝ ወታደሮቿንም እንድታስወጣ በሚል በቀረበው የውሣኔ ሃሳብ ላይ ሙሉ በሙሉ ድምፅ ሳትሰጥ መውጣቷ ይታወሳል።በዚሁ ጉዳይ ዛሬ ሳምንታዊ መግለጫ የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ማብራሪያ ሰጥተዋል።አምባሳደር ዲና የሩሲያ ዩክሬን ግጭት ከሌላው የሚለየው ከግጭቱ ጀርባ ያሉ ሃይሎች ማንነት ነው ያሉ ሲሆን በግጭት ውስጥ ያሉት አካላት ኒውክሌር የታጠቁ ናቸው ብለዋል። በዚህ ጦርነት አሸናፊ የሚሆን የለም ያሉት ቃል አቀባዩ ሁለቱም አካላት ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ኢትዮጵያ መጠየቋን አስታውሰዋል።አምባሳደር ዲና በሁለቱ ወገኖች ቀውስ ላይ በመከረው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ወንበሩን ባዶ በማድረግ ስብሰባውን ማለፏ በበሳል ዲፕሎማሲ የተደረገ ውሳኔ ነው ሲሉ መግለፃቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። ### Response:
### Text: በአውሮፓ የሙቀት መጠን በድጋሜ ከፍተኛ ሪከርድ ሊያስመዘገብ እንደሚችል ተጠቆመ። በአብዛኛው የምዕራብ አውሮፓ ሃገራት በአንድ ወር ውስጥ ክብረ ወሰን ይሰብራል በተባለለት የሙቀት ወጀብ እንደሚመቱ ቢቢሲ ዘገቧል፡፡ፖሪስ ውስጥ ያለው የትንበያ ተቋም በሰሜናዊ ፈረንሳይ 41 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ የሚለካ ሙቀት ሊኖር እንደሚችል መተንበዩን ዘገባው አመልክቷል፡፡እንግሊዝ ደግሞ 39 ዲግሪ ሴንቲ ግሬት የሚለካ ሙቀትን የምታስተናግድ ሲሆን የባቡር እንቅስቃሴዎችም ሙቀቱን ለመቋቋም በሚያስችል ፍጥነት በዝግታ እንዲጓዙ ታዘዋል ነው የተባለው።በቤልጂየም፣ ጀርመንና ደች የሚስተዋለው የሙቀት መጠን ለሁለተኛ ጊዜ በሁለት ቀናት ውስጥ ክበረ ወሰን ይሰብራል መባሉንም ዘገባው አስፍሯል፡፡የእንግሊዝ ብሄራዊ የአየር ንብረት አገልግሎት እንዳስታወቀው የአየር ንብረት ለውጡና የሙቀት ሁኔታው በመላው አውሮፓ ከባድነቱ እየጨመረ መጥቷል ሲልም ጠቁሟል፡፡ትላንት ቤልጅየም፣ ጀርመንና ኔዘርላንድስ በቅደም ተከተል 399 ፣ 405 እና 393 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በሆነ ከፍተኛ ሙቀት ማስመዝገባቸውን ነው ቢቢሲ የዘገበው።የተለያዩ ቅሪተ አካላት እና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች የፕላኔቷን የአየር ንብረት ፈተና ውስጥ ከቶታል ሲሉ የዘርፉ ምሁራን አመልክተዋል፡፡ ### Response:
### Text: ትራምፕ ጀግና ለተባለው 0ውሻ ሜዳሊያ እንደሰጡ የሚያሳይ ሀሰተኛ ፎቶ መልቀቃቸው እያነጋገረ ነው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አል ባግዳዲን ለመግደል በተካሄደው ዘመቻ ተሳትፎ ለነበረው ውሻ ሜዳሊያ ሲሰጡ የሚሳይ የተቀነባረ ፎቶ በመልቀቃቸው ተቃውሞ እየቀረበባቸው ነው።ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ የለቀቁት ፎቶ በአይ ኤስ መሪ አል ባግዳዲ ግድያ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለነበረው ጀግና ውሻ0 በአንገቱ ላይ ሜዳሊያ ሲያጠልቁለት ያሳያል፡፡ ነገር ግን ይህ ፎቶ በተግባር ያልተደረገ እና አሶሴትድ ፕሬስ በ2017 ጄሜስ ማክክሎከን የክብር ሜዳሊያ ሲበረከትላቸው የሚያሳየውን ፎቶ በማቀነባበር የተዘጋጀ ነው ተብሏል፡፡አል ባግዳዲ በተገደለበት ዘመቻ ላይ ተሳትፎ የነበረው ይህ ውሻ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት እንዳልገባ እና ጉዳት አጋጥሞት የነበረ ቢሆንም 0ወደ ሌላኛው ሃላፊነት መሰማራቱ ነው የተነገረው፡፡ይህ የፕሬዚዳንት ተግባርም በአሁን ወቅት ከፍተኛ ችግር የሆነው የሀሰተኛ ዜናዎች መገለጫ ነው በማለት ክስ አቅርበዋል፡፡ ጄሜስ ማክክሎከን ም ፎቶዋቸውን ተቀነባብሮ ጥቅም ላይ በማወሉ ምን አይነት ምላሽ እንዳልሰጡና0 በተግባሩ እንደተስማሙ ይመስላል የሚል ግምት እየተሰጠ ነው፡፡ምንጭ፡ ሃፊንግተንፓስትኤፍ ቢ ሲ ### Response:
### Text: ኤርትራዊው ሙዚቀኛ በአዲስ አበባ ጥቃት ደረሰበትወዲ ማማ በሚል የቅጽል ስም የሚታወቀው ኤርትራዊ ሙዚቀኛ፣ ተክለ ነጋሲ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በማይታወቁ ሰዎች ጥቃት እንደተፈጸመበት ተነገረ።ድምጻዊው ባለፈው እሁድ ከሰዓት በኋላ ገርጂ በሚገኘው አንበሳ ጋራዥ አካባቢ በእግሩ በሚጓዝበት ወቅት ማንነታቸውን በማያውቃቸው አምስት ሰዎች ጥቃቱ እንደተፈጸመበት ተክለ ለቢቢሲ ተናግሯል። ጨምሮም ጥቃቱን ከፈጸሙበት ሰዎች ጋር ምንም አይነት ንግግር እንዳልነበረና አላማቸው ጉዳት ማድረስ እንደነበረ ገልጿል። ምንም አይነት ንግግር አልተናገሩኝም በቀጥታ ወደ ድብደባ ነበር የገቡት ሲል ተናግሯል።ድምጻዊው ተክለ ነጋሲ ሱዳን ውስጥ በነበረበት ጊዜ በደረሰበት የመኪና አደጋ እግሩ ተሰብሮ እንደነበር ጠቅሶ እግሩ ላይ ብረት እንዳለውና ጥቃት ያደረሱበት ሰዎች በተደጋጋሚ በአደጋው ጉዳት የደረሰበት እግሩን ይመቱት እንደነበር ተናግሯል።ከዚህም በመነሳት ከባድ አደጋን ለማድረስ ዕቅድ እንደነበራቸውና ጥቃቱ የታቀደና በደንብ የሚያውቁኝ መሆን አለባቸው በማለት ግምቱን አስቀምጧል። ድማጻዊ ወዲ ማማ በደረሰበት ድብደባ ሳቢያ በቀኝ እጁ፣ በአፍንጫው፣ በጭንቅላቱና የግራ ኩላሊቱ ላይ ከባድ ጉዳት እንደደረሰበትም ለቢቢሲ ተናግሯል። 1203 ### Response:
### Text: የጤና ሙያ ብቃት ምዘና ለወሰዱ ከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ማሳሰቢያ አሰራጭቷል።ከሰሞኑን ከጤና ጥበቃ ወደ ኤጀንሲው ዝርዝራቸው የተላከላቸው የሙያ ብቃት ምዘና የተፈተኑ የጤና ሳይንስ ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት እየተሰጣቸው ነው።ነገር ግን የተገልግላዮች ቁጥር እየተበራከተ በመምጣቱ በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ማሻሻይ የሚያደርግ መሆኑን ኤጀንሲው አሳውቋል።በዚህ መሰረት ከግንቦት 23 ከጥዋት 230 ሰዓት ጀምሮ በስልክ ቁጥር 0111236127 ወይም በኤጀንሲው ቅጥር ግቢ በአካል በመገኘት የሙያ ብቃት ምዘና ከወሰዱት ውስጥ በምዘናው የተሳካላቸው እንዲሁም ያልተሳካላቸው ውጤታቸውን ቀድመው ማወቅ ይችላሉ ተብሏል። የሙያ ብቃት ምዘና ውጤት ያልተሳካላቸው ምሩቃኖች ከሚጉላሉ ውጤታቸውን አውቀው ወደመጡበት ስፍራ እንዲመለሲ ለማድረግ ነው ነገር ግን የትምህርት ማስረጃቸውን ህጋዊነት ማረጋገጥ ግዴታ በመሆኑ በሌላ ጊዜ ተገኝተው ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል ሆኖም የምዘና ውጤቱ ባይሳካም የትምህርት ማስረጃቸውን አሁኑኑ ማረጋገጥ ከፈለጉ ይችላሉ የሙያ ብቃት ምዘና ውጤት የተሳካላቸው ውጤታቸውን እንደሰሙ በዚያው የትምህርት ማስረጃቸውን ህጋዊነት የማረጋገጥ ግዴታቸውን ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል። ### Response:
### Text: የብሄራዊ ኩላሊት ንቅለ ተከላ ማዕከል በዚህ አመት ለ50 ህሙማን የኩላሊት ንቅለ ተከላ ለማከናወን ማቀዱን አስታወቀ። ይህ የተገለፀው ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ህክምና መስጫ መከፈቱንና የኩላሊት ንቅለ ተከላ የተጀመረበት ሁለተኛ ዓመትንአስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።የማዕከሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ሞሚና መሃመድ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ከሰሐራ በታች ካሉ ሀገራት ውጤታማ የሆነ የኩላሊት ንቅለ ተከላበማካሄድ ከቀዳሚዎች ተርታ መሰለፏን ተናግረዋል።ባለፉት ሁለት ዓመታት 50 የኩላሊት ንቅለ ተከላዎችን ሲያከናውን ያከናወነው ማዕከሉ የአርባ ዘጠኙ ኩላሊት በሙሉ ጤንነት መስራት እንደቻለ ነው የገለፁት ተናግረዋል።በኩላሊት ንቅለ ተከላ ህክምናው አራት ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሰልጥነው የህክምናውን 90 በመቶ እያከናወኑ ይገኛሉ።በውጭ ሀገር ህክምናውን ለማከናወን ከ400 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የሚፈጅ ሲሆን ማዕከሉ ከድህረ ንቅለ ተከላ ጀምሮ የንቅለ ተከላውን ህክምና እና የሁለት ወር መድሃኒት በነጻ እየሰጠ ይገኛል።በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ህግ የሚፈቅደውና እየተሰራበት ባለው መመሪያ መሰረት ኩላሊት መለገስ የሚቻለው የደም ወይም የጋብቻ ዝምድና ባላቸው ሰዎች መካከል ብቻ ነው።ምንጭ ፋና ብሮድካስቲንግ ### Response:
### Text: ስፖርት የ2018ቱ የሩሲያ ዓለም ዋንጫ ምድብ ድልድል ይፋ ሆኗል። ሩሲያ በምታዘጋጀው የ2018ቱ የዓለም ዋንጫ ምድብ ድልድል በሩሲያ ሞስኮ ከተማ ይፋ ተደርጓል፡፡በዚሁ መሰረት፡ምድብ 1፡ ሩሲያ ሳኡዲ አራቢያ ግብጽ ኡራጋይምድብ 2፡ ፖቹጋል እስፔን ሞሮኮ ኢራንበምድብ 3፡ ፈረንሳይ አውስትራሊያ ፔሩ ዴንማርክበምድብ 4፡ አርጄንቲናአይስላንድ ክሮሺያ ናይጄሪያምድብ 5፡ ብራዚል ስዊዘርላንድ ኮስታሪካ ሰርቢያምድብ 6፡ ጀርመን ሜክሲኮ ስዊድን ደቡብ ኮሪያምድብ 7፡ ቤልጂየም ፓናማ ቱኒዚያ እንግሊዝምድብ 8፡ ፖላንድ ሴኔጋል ኮሎምቢያ ጃፓን ሆነውተደልድለዋል፡፡ከተደለደሉት ምድቦች መካከል በጠንካራ ቡድኖች ስብስባቸውም ደረጃ ወጥቶላቸዋል፡፡በዚሁ መሰረት፡ምድብ 6፡ ጀርመን ሜክሲኮ ስዊድን ደቡብ ኮሪያ በጠንካረነቱ የመጀመሪያውን ደረጃ ሲይዝ2ኛ በምድብ 3፡ ፈረንሳይ አውስትራሊያ ፔሩ ዴንማርክ3ኛ ምድብ 2፡ ፖቹጋል እስፔን ሞሮኮ ኢራን4ኛ በምድብ 4፡ አርጄንቲናአይስላንድ ክሮሺያ ናይጄሪያ5ኛ ምድብ 7፡ ቤልጂየም ፓናማ ቱኒዚያ እንግሊዝ6ኛ ምድብ 8፡ ፖላንድ ሴኔጋል ኮሎምቢያ ጃፓን7ኛ ምድብ 5፡ ብራዚል ስዊዘርላንድ ኮስታሪካ ሰርቢያእንዲሁም የመጨረሻው 8ኛ ቀላል ምድብ ድልድል ምድብ 8፡ ፖላንድ ሴኔጋል ኮሎምቢያ ጃፓን ናቸው ተብሏል፡፡ምንጭ ኢቢሲ ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በፈረንሳይ የሟቾች ቁጥር መቀነስ አሳይቷል። ባለፉት 24 ሰዓት 389 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 22245 ደርሷል። በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር ከ51000 በልጧል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ905000 በልጧል። የዓለማችን ግዙፍ ጸረተህዋሲያን የንጽህና መጠበቂያ ምርቶች አቅራቢው ምርቶቼ ለመድሃኒትነት አይውሉም ሲል አስጠንቅቋል። ፕሬዝደንት ትራምፕ ከኮቪድ19 ለመዳን ሰዎች ለምን ጸረተህዋሲያን አይወጉም ሲሉ አስተያየት መስጠታቸው ይታወሳል ዋይት ሃውስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የኮቪድ 19 ህክምና አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ከአውድ ውጭ ተወስዷል ብሏል። የዋይት ሃውስ ፕሬስ ሴክሬተሪ ካይሌህ ማክኢናንይ ፕሬዚደንት ትራምፕ በተደጋጋሚ የኮሮና ቫይረስ ህክምናን በተመለከተ አሜሪካ የህክምና ባለሙያዎችን ማማከር እንደሚገባ ተናግረዋል ይህ ንግግራቸውንም በሌላ መግለጫቸው ላይም ደግመውታል። ነገሩን የፕሬዚደንቱን ንግግር ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ከአውድ ውጭ ለወሰዱና በአሉታዊ አርዕስት ላሰራጩ ሚዲያዎች ተውት ብለዋል በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 2804455 ደርሷል። 195585 ሰዎች ሞተዋል። 776310 ሰዎች አገግመው ከሆስፒታል ወጥተዋል። ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ አሁን ያለው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት የአኗኗር ሁኔታችንን እንድንቀይር ያስገዳል ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶር ሊያ ታደሰ ገልፀዋል። ዶር ሊያ ዛሬ በሱጡት መግለጫ እንዳሉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጉዞ ታሪክ የሌላቸው በርካታ ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እየተገኘባቸው ነው። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ ሳይኖራቸው ቫይረሱ የሚገኝባቸውም ሰዎች ቁጥር ጨምሯል ሲሉ ተናግረዋል።የኮቪድ19 ስርጭት ጎረቤት አገራት ጋር በማይዋሰኑ አካባቢዎችም ጭምር እየሰፋ መጥቷል ያሉት ዶክተር ሊያ ይህም አደጋው ወደ እያንዳንዳችን ቤት እየመጣ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።የኮሮና ቫይረስ ኮቪድ19 ሲከሰት በቀላሉ እየጨመረ የሚሄድ የስርጭት ባህሪ እንዳለው ጠቁመው ስርጭቱ ምን ያህል ይጨምራል የሚለው ጥያቄ ግን በእያንዳንዳችን ጥንቃቄ ይወሰናል ብለዋል። በኢትዮጵያ ያለፈው ሳምንት የቫይረሱ ስርጭት ሁኔታ ይህን በግልጽ ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም ከመደናገጥ ወጥተን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በሚጠይቀው ልክ የአኗኗር ባህሪያችንን መቀየር አለብን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።መራራቅ ፣ መታጠብ ፣ መቆየት ፣ መሸፈን የሚሉ አራቱ የኮቪድ19 መ ህጎችን መተግበር ደግሞ ከእያንዳንዱ ዜጋ የሚጠበቅ የጥንቃቄ አማራጭ መሆኑ ዶር ሊያ ገልፀዋል ### Response:
### Text: አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ️ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎላላ እና ጣራ ወረዳ ዛሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ 15 ሰዎች ህይወት አለፈ።አደጋው የደረሰው ከቀኑ 6 ሰአት ከ30 ሲሆን ከደብረ ብርሀን የሚመጣ ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሀን ሲጓዝ ከነበረ ኮድ የህዝብ ማመለሻ አይሱዙ ቅጥቅጥ ጋር በመጋጨታቸው መሆኑን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ምክትል ኮማንደር ወርቅአገኘሁ ሸዋ ለ ተናግረዋል።የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን የተናገሩት ምክትል ኮማንደሩ አደጋው እንደደረሰም የሁለቱን ተሽከርካሪዎች ሾፌሮች ጨምሮ የ12 ሰዎች ህይዎት ወዲያውኑ ሲያልፍ የ 3 ሰዎች ህይዎት ደግም በደብረ ብርሀን ሪፈራል ሆስፒታል ከደረሱ በኋላ ህይዎታቸው ሊያልፍ ችሏል።በ4 ሰዎች ላይ ከባድ በ5 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን እና ተጎጂዎቹም ደብረ ብርሀን ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን መክትል ኮማንደር ወርቃገኘሁ ሸዋ ተናግረዋል።ህይዎታቸው ያለፉት ሰዎችም አብዛኞቹ መታወቂያ ያልያዙ በመሆናቸው አድራሻቸውን ማወቅ አለመቻሉን የተናገሩት ኮማንደሩ ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረብርሀን ለመጓዝ የወጡ ቤተሰቦች ያሏቸው ሰዎችም ካሉ መረጃው እንዲደርሳቸው አሳስበዋል።© ### Response:
### Text: መግለፂ ሓዘን ብሄራዊ ክልላዊ መንግስቲ ትግራይሎሚ ዕለት 18082011 ዓም አባላት ጋንታ ዋልታ ፖሊስ ትግራይ ኣብ ማእኸል ሃገር ዝነበሮም ፀወታ ዛዚሞም ናብ ትግራይ እናተመለሱ ኣብ ዝነበረሉ እዋን ኣብ ዓፋር ክልል ፍሉይ ቦታ ጉዋኔ ዝተብሃለ ከባቢ ዛጊድ መንነቶም ብዘይተፈለጡ ዑጡቓት ብዝተፈነወ መጥቃዕቲ ንሕልፈተ ህይወት ሓደ ሰብን ኣብ ልዕሊ ካልኦት ሓሙሽተ ኣባላት እታ ጋንታ ድማ ናይ ኣካል ጉድኣት ከም ዝበፀሐ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስቲ ትግራይ ኣረጋጊፁ እዩ፡፡ብሄራዊ ክልላዊ መንግስቲ ትግራይ እዚ ኣብ ልዕሊ ወገናትና ዝተፈፀመ መሕዘኒ ፍፃመ ብፅኑዕ ከምዝኹንኖ እናገለፀ ነዚ ተግባር ዝፈፀሙ ኣካላት ምስ ሓይልታት ፀጥታ መንግስቲ ክልል ዓፋርን ፌደራል ፖሊስን ብምዃን እቶም ገበነኛታት ናብ ሕጊ ክቐርቡ ኣብ ምፅራይ ይርከብ፡፡ጉድኣት ዝበፅሖም ወገናት ድማ ብሄልኮፕተር ናብ ደብረዘይት ከይዶም ኣድላይ ክትትልን ሕክምናን ይግበረሎም ከምዘሎ እናሓበርና፡፡ብሄራዊ ክልላዊ መንግስቲ ትግራይ ብምኽንያት እቲ ሓደጋ ህይወቱ ንዝሰኣነ ወገና ብስም ህዝብን መንግስቲ ትግራይን ዝተሰምዖ መሪር ሓዘን ብምግላፅ ንስድራ ግዳይ እቲ ሓደጋን ንመላእ ህዝቢ ትግራይን ፅንዓት ይምነ።ቢሮ ርክብ ህዝብን መንግስትን ክልል ትግራይመቐለ 18 ሚያዝያ 2011 ዓም ### Response:
### Text: በተሽከርካሪ የጦር መሳሪያ ሲያዘዋውር የተያዘው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ ተከሳሽ አብዱራህማን ዩኑስ ከሚመከለተው የመንግስት ፈቃድ ውጪ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ገደብ የተደረገባቸው የጦር መሳሪያዎችን በተሸከርካሪ ደብቆ ወደ ሀገር ሊያስገባ ሲል ተይዞ ዐቃቤ ሕግ በመሰረተው ክስ በእስራት ተቀጥቷል፡፡ተከሳሽ 53 ቱርክ ስሪት ሽጉጦችንና 35 ሺህ 766 ጥይቶችን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 350931 አአ በሆነ ላንድክሩዘር መኪና ደብቆ ወደ ሀገር ሊያስገባ ሲሞከር በተደረገው ክትትል በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ክልል ልዩ ቦታው ጣፎ አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተሸከርካሪው ላይ በተደረገ ፍተሻ ተይዟል፡፡ተከሳሽ ክሱ በችሎት ተነቦለት እንዲረዳ ከተደረገ በኃላ ድርጊቱን ክዶ በመከራከሩ ዐቃቤ ሕግ እንደ ክሱ አቀራረብ ምስክሮች አሰምቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም መዝገቡን መርምሮ ተከሳሽ ሽጉጥና ጥይት በመኪና ደብቆ በፍተሻ ስለመያዙ በመረጋገጡና መከላከልም ባለመቻሉ በተከሰሰበት ድንጋጌ ጥፋተኛ መሆኑን በይኗል፡፡የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 8ኛ ወንጀል ችሎት መዝገቡን መርምሮ የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት በመመልከት ተከሳሽ በ2 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ5 ሺህ ብር መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል፡፡ምንጭ፡ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ### Response:
### Text: ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5414 የላብራቶሪ ምርመራ 250 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5425 ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው 158 ወንድ እና 92 ሴት ሲሆኑ የእድሜ ክልላቸው ከ3 ወር 90 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 240 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 10 የውጭ ዜጋ ናቸው።177 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 21 ሰዎች ከትግራይ ክልል ፣ 20 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 18 ሰዎች ከጋምቤላ ክልል፣ 8 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 4 ሰዎች ከሱማሌ ክልል፣ 1 ሰው ከድራዴዋ ከተማ እና 1 ሰው ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ናቸው።ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 32 11 ከጤና ተቋም እና 21 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን 6 ናሙናዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። ከዚህ ባለፈ ሁለት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 89 ደርሷል፡፡ በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት 144 ሰዎች 123 ከአዲስ አበባ፣ 7 ከአማራ ክልል፣ 7 ከትግራይ ክልል፣ 5 ከሶማሊ ክልል፣ እና 2 ከኦሮሚያ ክልል ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1688 ነው። ### Response:
### Text: ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች ላይ የተከፈተው መዝገብ ላይ ለመበየን ቀጠሮ ሰጠበዋስትና እንዲፈቱ ከተወሰነላቸው በኋላ ሲቪል በለበሱ ግለሰቦች በድጋሜ ታስረው ከሀጫሉ ግድያ በኋላ አመፅ አስነስተዋል በሚል ሌላ የምርመራ መዝገብ የተከፈተባቸው በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ለመስከረም 72013 ዓም ለብይን ተቀጠሩ።የአሥራት ጋዜጠኞች በድጋሜ የተከፈተባቸውን መዝገብ ከቀደመው ጉዳይ የተለየ አይደለም ብለው በመከራከራቸው ፍርድ ቤቱ የፖሊስና የፍርድ ቤቱን መዝገብ መርምሮ በድጋሜ የተከፈተባቸው መዝገብ ከቀደመው የተለየ ስለመሆን አለመሆኑ ለመበየን ለዛሬ ቀጠሮ ይዞ ነበር። የቀደሙት የፖሊስና የፍርድ ቤት መዝገቦች ከቀጠሮው ቀደም ብለው በድጋሜ ከተከፈተባቸው መዝገብ ጋር እንዲያያዙ አራዳ መጀመርያ አንደኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ትዕዛዝ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ፖሊስ መዝገቦቹን ያያያዘው ዛሬ ጠዋት መሆኑን ተናግሯል። በዚህም ምክንያት ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት እንዳልቻለ ተገልፆአል። ፍርድ ቤቱ የአሥራት ጋዜጠኞች ሌላ መዝገብ የተከፈተባቸው ባለፈው ዋስትና ባገኙበት ተመሳሳይ ጉዳይ ነው ወይንስ አይደለም የሚለውን ለመበየን ለመስከረም 72013 ዓም ከሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል።ምንጭ አስራት ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: በአአ ከተማ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ ተደረገ።በአአ አስተዳደር የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ መደረጉ በዛሬው ዕለት መደረጉ ታውቋል።ለታሪፍ ማሻሻያው እንደምክንያትነት የተቀመጠውም ወቅታዊው የነዳጅ ጭማሪ መሆኑ ተገልጿል።ቢሮው ባለፉት 2 ወራት በነዳጅ ላይ የ5 ነጥብ 90 ብር ጭማሪ መኖሩን ከግምት በማስገባት የነዋሪውን የኑሮ ሁኔታ ከግምት በማስገባት በሚኒ ባስ፣ ሃይገርና መካከለኛ አውቶብሶች ላይ የታሪፍ ማሻሻያ ማድረጉን አስታውቋል።በሚድ ባስ ወይም የሃይገር እና መካከለኛ አውቶብሶች ላይ የተሻሻለው ታሪፍ እስከ 8 ኪሎሜትር 3 ብር የነበረው ባለበት ይቀጥላል ከ8 ኪሜትር በላይ ያሉት ታሪፎች ላይ የ1 ብር ጭማሪ ተደርጓል። በሚኒ ባስ ኮድ 13ን በተመለከት እስከ 25 ኪሜ 2 ብር የነበረው ባለበት ይቀጥላል። ከ 26 እስከ 5 ኪሜ 4 በር የነበረው 450 ብር ከ51 እስከ 75 ኪሜ 6ብር የነበረው 650 ብር ከ76 10 ኪሜ0 8 ብር የነበረው 9 ብር0 ከ101 125 ኪሜ 10 ብር የነበረው 11 ብር ከ126 15 ኪሜ 12 ብር የነበረው 13 ብር ከ151 175 ኪሜ 13 ብር የነበረው 1550 እንዲሁም ከ176 20 ኪሜ 15 1750 ብር ሆኗል።በሸገር አንበሳ እና ድጋፍ ሰጪ የብዙሃን ትራንስፖርቶች ላይ የከተማ አስተዳደሩ በአመት 15 ቢሊየን ብር ድጎማ በማድረግ በነበሩበት ዋጋ እንዲቀጥሉ ተደርጓል። ኤፍ ቢ ሲአዲስ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ፋይዘር የመጀመሪያውን በታብሌት መልክ የሚወሰድ የኮቪድ 19 መድሃኒት እየሞከረ ነው ፋይዘር የመድሃኒት አምራች ተቋም በታብሌት መልክ የሚወሰድ የኮቪድ 19 መድሃኒት ለመስራት ሙከራዎችን እያደረገ እንደሆነ ተነግሯል።አሁን ላይ ባለው ህክምና በጽኑ ህሙምነት ላሉ ሰዎች የሚደረገው የህክምና እርዳታ ኦክስጅን እንዲያገኙ በማድረግ ሰውነታቸው በራሱ የበሽታ መከላከል ብቃቱን በማሳደግ እስኪያገግሙ መጠበቅ ነው፡፡ ይህ ግን ሁል ጊዜ አዋጭ አይሆንም ለዚህም ነው ብዙዎች ኦክስጅን እንኳን እያገኙ እንደ ቅጠል እየረገፉ ያሉት፡፡ ተቋሙ ይህን የህሙማንን ስቃይ ሊያቀልና ከበሽታቸው እንዲያገግሙ የሚያግዛቸውን መድሃኒት ነው እየሞከረ ያለው፡፡ መድሃኒቱ አሁን ላይ በቤልጀም ብራሰልስ የመጀመሪያ ደረጃ ክሊኒካዊ ሙከራ እየተደረገበት ሲሆን መድሃኒቱም ቫይረሱ በሰውነታችን ውስጥ ለመራባት የሚጠቀምበትን ኢንዛይም በመለየት የሚያጠቃ ነው፡፡ እንደ ፋይዘር መረጃ ከሆነ ይህ 07321332 የተሰኘ ክኒን ታብሌት በሽታው በሰውነታችን እንደገባ ወይም እንደያዘን ወዲያው የሚወሰድ ነው፡፡ታማሚዎች የመጀመሪያው የህመም ስሜት እንደተሰማቸው ወደ ተጨማሪ ህክምና ሳይሔዱ መድሃኒቱን ሊወስዱት እንዲችሉ ታስቦም የተሰራ መሆኑን ድርጅቱ ተናግሯል፡፡ ምንጭ 2 ### Response:
### Text: የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ድጋፍ ጉዳዮች ኃላፊ ማርክ ሎውኮክ ትግራይ ክልል ውስጥ የኤርትራ ኃይሎች የትግራይ ህዝብ ለረሃብ እንዲጋለጥ እያደረጉ ነው ሲሉ ከሰዋል።ሎውኮክ ይህን ያሉት ከሮይተርስ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ ወቅት ነው።ኃላፊው የኤርትራ ወታደሮች እና የአከባቢው ተዋጊዎች ሆን ብለው ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ ባሉ አካባቢዎች ለሚገኙ ከ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሰብዓዊ አቅርቦት እንዳይደርስ እያገዱ ነው ብለዋል።በእርግጠኝነት ምግብ እንደ ጦር መሳሪያነት እያገለገለ ነው ሲሉም ተናግረዋል።የኢትዮጵያ መንግስት ፣ የተባበሩት መንግስታት እና የእርዳታ ድርጅቶች ከመጋቢት ወር ጀምሮ ለ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ለሚጠጉ የትግራይ ነዋሪዎች ምግብና ሌሎች ድጋፎችን ማድረሳቸውን ገልጿል ነገር ግን አብዛኛው እርዳታ በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች የሚከናወን ነው ሲሉ ሎኮክ ተናግረዋል።የተመድ ሰብዓዊ ጉዳዮች ኃላፊ በሆኑት ማርክ ሎውኮክ ለቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት አሁናዊ ምላሽ ባይሰጥም ከዚህ ቀደም የኤርትራ ጦር ትግራይ ውስጥ ሰብዓዊ ድጋፎችን ይዘርፋል ያግዳል መባሉን በተመለከተ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገመስቀል የፈጠራ ወሬ ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተው ነበር። የሮይተርስ ሙሉ ዘገባ 20210611 ### Response:
### Text: ላሊበላ የገባው የህወሓት ሽብር ቡድን አሁን ላይ በመከላከያ ሰራዊት እና በክልሉ ልዩ ሃይል እየተመከተ ነው አቶ ግዛቸው ሙሉነህበትላትናው ዕለት የህወሓት ታጣቂዎች አማራ ክልል ወደምትገኘው ላሊበላ ከተማ መግባታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የከተማይቱ ምክትል ከንቲባ አቶ ማንደፍሮ ታደሰ ማረጋገጣቸው ይታወቃል።የቡድኑ ታጣቂዎች በሶስት ትምህርት ቤቶች ውስጥም ካንፕ ሰርተው መቀመጣቸውን ነዋሪዎች እንደገለፁ አይዘነጋም።ላሊበላ ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ በዛሬው ዕለት የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ተናግረዋል።ላሊበላ የገባው የህወሓት ቡድን አሁን ላይ በመከላከያ ሰራዊትና በክልሉ ልዩ ሃይል እየተመከተ ነው ብለዋል አቶ ግዛቸው ሙሉነህ።ህብረተሰቡ በቡድኑ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ አካባቢውን ለቆ መውጣት እንደሌለበት የገለፁት አቶ ግዛቸው ህብረተሰቡ ሳይሸበር ራሱን ሊከላከልና0 አካባቢውን በንቃት ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል።ህወሓት አሁን ላይ በክልሉ 3 ግንባሮች ውጊያ መክፈቱን አቶ ግዛቸው የገለፁ ሲሆን አሁን ላይ በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ሃይል ፣ በፋኖ እየተደመሰሰ እና እየተመታ ነው ብለዋል።ዳይሬክተሩ በርካታ የቡድኑ አባላት መማረካቸውን መጥቀሳቸውን ኤፍ ቢ ሲ በድረገፁ አስነብቧል ### Response:
### Text: ደንበኞች በሚበዙበት አካባቢ የፖስ ማሽን የሙከራ አገልግሎት እየተሰጠ ነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች በሚበዛባቸው አካባቢዎች የሚስተዋለውን መጨናነቅ ለመቀነስ የሚያስችል የፖስ ማሽን የሙከራ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል።የፖስ ማሽን የሙከራ አገልግሎቱ በስራ ላይ የዋለው በአዲስ አባባ በአራቱም ዲስትሪክቶች በሚገኙና ደንበኛ በሚበዛባቸው የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ነው፡፡በሙከራ ደረጃ አገልግሎት መስጠት የጀመሩት ፖስ ማሽኖች ብዛት 15 ሲሆኑ በቀጣይም አዋጭነታቸው እየታየ ደንበኛ በሚበዛባቸው ማዕከላትና በተመረጡ የንግድ ድርጅቶች፣ ሱፐር ማረኬቶች እንዲሁም ተደራሽ በሆኑ አካባቢዎች አገልግሎቱ የሚሰጥ ይሆናል ብሏል ተቋሙ።ተጨማሪ ፖስ ማሽኖችን በስራ ላይ ለማዋል ከአቅራቢ ድርጅቶች ጋር የኮንትራት ውል ስምምነት ፈርሞ ማሽኖችን ለማስገባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝም ገልጿል። በሌላ በኩል ተቋሙ የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞችን ድካምና እንግልት ለማስቀርትና ካርድ ለማስሞላት የሚያጠፉትን ጊዜ ለማስቀረት በእጅ ስልካቸው አፕልኬሽን በመጫን ኤሌክሪክ ሃይል መሙላት የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ አሳውቋል። ### Response:
### Text: 4 ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ በንብረት ግምጃ ቤት ውስጥ የተቀመጡ ከ 1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ህዳር 8 ቀን 2014 ዓም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ በህዝብ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ብርበራ ከ1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።በቤተ ክህነቱ ግቢ በሚገኝ የንብረት ግምጃ ቤት በሚገኝ የፅህፈት እና የፅዳት እቃዎች ማስቀመጫ ውስጥ በተደረገው ብርበራ የተገኙት 1ሺህ 363 የብሬን እና 493 የሽጉጥ ጥይቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም 2 የጥይት ማስቀመጫ ሳጥኖች እና 1 የክላሽንኮቭ ጠብመንጃ ካዝና ተይዟል፡፡ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 1 ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ሲሆን ህብረተሰቡ በስልክ፣ በአካል እና ሌሎች የመገናኛ አማራጮችን በመጠቀም እየሰጠ የሚገኘው ጥቆማ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።የአዲስ አበባ ፖሊስ አሸባሪው የህወሃት ቡድን ለሽብር ተግባሩ የሚጠቀምባቸውን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሲያከማች እና በኃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ግለሰቦችን በተላላኪነት እያሰማራ በበርካታ ንፁሃን ላይ አሰቃቂ እልቂት ሲፈፅም እንደቆየ ይታወሳል ብሏል። ### Response:
### Text: ጥቆማ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ሰልጣኝ አብራሪፓይለት ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ ሰልጣኝ የመንገደኛ አገልግሎት ኢጀንት አመልካቾች ለምዝገባ ሊያሟሉ የሚገባቸው የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውንና ኮፒው፣ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ፣ የልደት ካርድ፣ የታደሰ የቀበሌ የነዋሪነት ማረጋገጫ ካርድ እና አንድ ጉርድ ፎቶግራፍአመልካቾች ከተዘረዘሩት የሥራ መደቦች ውስጥ ማመልከት የሚችሉት በአንዱ ብቻ ነው። የምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 15 እስከ 192015 ዓም የምዝገባ ቦታ፡ አዲስ አበባ በኦንላይን፣ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ማርቆስኦኒቨርሲቲ፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ ሚዛንቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ ቲቺንግ ኮሌጅ፣ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲዕድሜ ፣ ቁመት እና ሌሎች ተያያዥ መረጀዎችን ከላይ በተያያዘው የተቋሙ ማስታወቂያ ይመልከቱ ### Response:
### Text: ጋምቢያ ፕሬዚዳንት አዳም ባሮ ላይ በ2017 ከተቃጣ የመፈንቅለ መንግስት ሴራ የተጠረጠሩ በርካታ የቀድሞ ወታደሮችን በቁጥጥር ስር አውላለች፡፡የሀገሪቱ ወታደራዊ ፍርድ ቤት በመፈንቅለ መንግስት ተሳትፈዋል ተብለው ከቀረቡለት ውስጥ በሰባቱ ላይ 9 አመት እስራት ሲወስን በቀሪዎቹ ላይ 3 አመት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡የምእራብ አፍሪካዊቷን ሀገር ለ22 አመታት መርተው እአአ 2016 በተደረገ ምርጫ ተሸንፈው ከሀላፊነት አለቅም ቢሉም በግፊት ከወረዱት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ያህያ ጃሜህ ለመፈንቅለ መንግስቱን ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡የቀድሞዎቹ ወታደሮች የሀገር መክዳትና የጃሜህ መንግስት የመመለስ የወንጀል ክስ አግባብነት የሌለውና የፖለቲካ ሴራ ነው ብለውታል ለፍርድ ቤት በሰጡት የክስ መልስ፡፡ወታደራዊ ፍርድ ቤቱም የመፈንቅለ መንግስት ሴረኞች ከቀድሞው ፕሬዚዳንት ታማኝ ወታደሮች ጋር ጥቃት ለመፈጸም በማህበራዊ ሚዲያ የዋትስ አፕ የመልእክት ልውውጥ ማድረጋቸውን በማስረጃ መገኘቱን አስረድቷል፡፡የሰብአዊ መብት ተሞጋቾች የአሁኑ የባሮ መንግስት ባለፉት 22 አመታት የጃሜ የሠብአዊ መብት ጥሰትና ማጭበርበር የተሞላበት ነው ቢሉም ጃሜ ይህን ክስ አጥብቀው ይክዳሉ፡፡ የወታደሮቹ ቤተሰቦች ይህን ውሳኔ ይግባኝ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ ### Response:
### Text: የቲክቫህ አባላት ከ1 ሚሊዮን አልፈዋልበኢትዮጵያ እና በውጭ የሚገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ከ1000000 አልፈዋል። የቲክቫህ ቤተሰብ አባላቶች እድገት ላደረጋችሁር ትልቅ ስራ ምስጋና ይገባችኃል እንኳን ደስ አለን ሁላችንም እንኳን ደስ አላችሁ እያላችሁን ያላችሁ አባላት መልዕክታችሁ እንኳን ደስ አለን በሚል ይቀየርልን እኛ ምን አቅም አለን 1 ሚሊዮን ሰው በአንድ ቦታ የማሰባሰብ ይህ ሁሉ የናተው ተግባር ነውዛሬ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ዙሪያ ጥያቄ መጠየቅ ትችላላችሁ የምንችለውን ምላሽ ለመስጠት እንሞክራለን ማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት ላይ አስቀምጡልን።ከምን በላይ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ጨዋነታችሁን ፣ ለሰው ያላችሁን አክብሮት ፣ እርጋታችሁና ትዕግስታችሁን ለመመስከር እንፈልጋለን ከ2 ዓመት በላይ አብረን በዚህ ቤት ስንቆይ ከአፋችሁ ክፉ ቃል ሳይወጣ፣ ሳትሳደቡ፣ የሰዎችን ክብር ሳትነኩ፣ በሀሳብ እየሞገታችሁ፣ ስህተቱን ስህተት ነው እያላችሁ በመቆየታችሁ ትልቅ ክብር አለን። ከ1000000 በላይ የቤተሰቡ አባላት በ2 ዓመት ውስጥ ብንቆጥራቸው 50 ሰዎች እንኳን እይሞሉን የጥላቻ ፣ ስድብ እና ሰዎችን የማንቋሸሽ መልዕክት የላኩት። ይህ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ካየነው ሁሉ ልዩ ነገር ነው ረጅምን እድሜና ጤና እንመኝላችኃለን ### Response:
### Text: ከኃላፊነታቸው ተነሱ በምስራቅ ወለጋ ዞን መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በየደረጃው በተካሄደው የጥልቅ ተሃድሶ ግምገማ 195 አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የዞኑ የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡በዞኑ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ በሪሶ ተመስገን እንደገለጹት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ከዞን ጀምሮ በተዋረድ በየደረጃው ባሉ የስልጣን እርከኖች የተነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በተካሄደው ጥልቅ የተሃድሶ ግምገማ 195 ነባር አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነስተው በአዲስ እንዲተኩ ተደርጓል።የዞንና የወረዳ አመራሮች ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የተደረገው በህዝቡ እንዲተቹ ተደርጎ የአመራርና የአቅም ማነስ የተስተዋለባቸውና ከጥልቅ ተሃድሶው ጋር ራሳቸውን አቀናጅተው መራመድ ያልቻሉ መሆናቸው በመረጋገጡ ነው።በተነሱት ምትክ ወደ ኃላፊነት የመጡ አዲስ አመራሮች ከምሁራን፣ ከሴቶችና ከህብረተሰቡ የተወጣጡ ሲሆኑ ህዝቡን በሀቀኝነትና በቁርጠኝነት በማገልገል የመልካም አስተዳደር ችግሮቹን ለመፍታት የተዘጋጁና ብቃት አላቸው ናቸው ተብሎ የታመነባቸው ናቸው።ወደ አመራር ከመጡት 195 አዳዲስ አመራሮች መካከል 35ቱ ሴቶች መሆናቸውን አቶ በሪሶ አክለው ተናግረዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ከኢህአዴግህወሓት ቁጥጥር ኮሚሽን አባላት የተሰጠ መግለጫከተቋማዊና ሕጋዊ አሰራር እንዲሁም ከመርህ ውጭ የሚገነባ ድርጅት እና ሀገር የለምከኢኮኖሚ ኮንትሮባንድ ይልቅ የፖለቲካ ኮንትሮባንድ ሀገርን በባሰ ሁኔታ ይንዳልህዳር 152012 ዓምየኢህአዴግ ምክር ቤት ፅሕፈት ቤት ሰሞኑን ባካሄዳባቸው ተከታታይ መድረኮች ግንባሩ ወደ አንድ ወጥ ፓርቲያደረገውን የውህደት ውሳኔ አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ በመገናኛ ብዙኃን ተከታትለናል፡፡ በመግለጫው የኢህአዴግ ቁጥጥር ኮሚሽን ድጋፉን ሰጥተዋል የሚልምሰምተናል፡፡ ይህንን የተሳሳተ መረጃ እና አደገኛ አካሄድ የኢህአዴግ ቁጥጥር ኮሚሽን አመራር አቋም ወስዶ ማስተባበያ ይሰጣልበሚል እምነት የተነሳ ተቃወሞ ሳናሰማ በትእግስት ጠብቀናል፡፡ይሁን እንጂ የቁጥጥር ኮሚሽኑ አመራር የመግለጫው ታሪካዊ ስህተት አካል ለመሆን ስለመረጠ እስካሁን ድረስ አንዳች ነገር ሊተነፍስ አልቻለም፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ ሆን ተብሎ ለማደናገር የተሰጠ መግለጫ በመሆኑ መላው የኢህአዴግ አባላትና ካድሬዎች እንዲሁም የኢትዮጲያ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ትክክለኛ መረጃ ሊያገኙ ስለሚገባና መብታቸውም ስለሆነ እኛ የኢህአዴግህወሓት ቁጥጥርኮሚሽን አባላት የሚከተለውን መግለጫ እንድናወጣ ተገደናል፡፡ 1127 ### Response:
### Text: 2012 የምርጫው የጊዜ ሰሌዳ በቅርቡ ይፋ ይደረጋልወሪት ሶሊያና ሽመልስየምርጫው የጊዜ ሰሌዳ እስካሁን ድረስ ይፋ ያልሆነው ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስፈልጉ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ በመሆናቸው ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከመንግስት ለምርጫው ማስፈጸሚያ ከጠየቀው አራት ቢሊዮን ብር ገደማ በጀት ውስጥ እስካሁን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈቀደው 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም 40 ሚሊዮን ዶላር ከልማት አጋሮች እያሳባሰበ ይገኛል። የአውሮፓ ህብረት፣ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ኤጀንሲ ዩኤስአይዲ እና ሌሎች አጋር አካላት ለምርጫው ማስፈፀሚያ ድጋፎችን ያደርጋሉ። ምርጫ ቦርድ ከዚህ በፊት ከነበረው ደካማ ተቋማዊ አቅም አንጻር ባለፈው አንድ ዓመት ምርጫውን ለማስፈጸም የሚያስችለውን ጠንካራ አቅም የመገንባት ስራ ሲያከናውን ቆይቷል። በቦርዱ በኩል ነጻ፣ ፍትሐዊና ሰላማዊ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኛ እንደሆነና ይህንንም ለማድረግ የሚያስችል ተግባር እያከናወነ ነው የሚገኘው። የቦርዱ መጠናከር ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና አጠቃላይ ማህበረሰቡ ለምርጫው ውጤታማነት የራሳቸውን ሃላፊነት በአግባቡ መወጣት አለባቸው። ### Response:
### Text: የአገር ነፃነት በገንዘብ አይለወጥም አምባሳደር ዲና ሙፍቲየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው አሜሪካ ስላሳለፈችው እገዳ አንስተዋል።የአሜሪካ እገዳ የ2ቱን አገራት ግንኙነት ቢጎዳም ቀዩ መስመር ግን የኢትዮጵያ ነፃነት በገንዘብ ሊቀየር የሚችል አለመሆኑ ነው ሲሉ ተናግረዋል።አክለውም የአገር ነፃነት በገንዘብ አይለወጥም ብለዋል። አምባሳደር ዲና ወቅታዊዉ የአሜሪካ ውሳኔ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ቢያደርስም ፣ ነገር ግን ለገንዘብ ተብሎ ኢትዮጵያ ነፃነቷን አሳልፋ አትሰጥም ይሄ ቀይ መስመር ነው ብለዋል።መንግስት ከአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ለሚያገኘው ገንዘብ ብሎ ልደራደር ቢል እንኳን የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነቱን በገንዘብ የሚቀይር አይደለም ሲሉ ተደምጠዋል። የአሜሪካ እገዳ የ2ቱን አገራት ግንኙነት የሚጎዳ ብቻ ሳይሆን፣ ቀጠናውና ሌሎች አገራት ላይም ተፅዕኖ የሚያሳድር በመሆኑ አሜሪካ ውሳኔዋን ደግማ ልታስብበት ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል። የአሜሪካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ላይ የኢኮኖሚ ተፅዕኖ ቢኖረውም የኢትዮጵያ ሉአላዊነት ግን ለሚደራደር የሚቀርብ አይሆንም ሲሉ አምባሳደር ዲና ተናግረዋል።መረጃው የኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ሬድዮ ጣቢያ ነው። ### Response:
### Text: የጠሚ ጽቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢልለኔ ስዩም ምን አሉ መንግስት የሰሜኑ ጦርነት በሰላም ለመቋጨት በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር ለሚደረገው ሂደት ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል። የሰላም ሂደቱ ውስብስብ እና ረጅም መሆኑን ገልፀዋል። የትኛውም የሰላም ሂደት ረጅም ነው። ቀላል አይደለም። ውስብስብና የተደራረቡ ሁነቶችን የያዘ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት አደራዳሪ ለሆኑት ኦባሳንጆ ትልቅ ቦታ እንዳላት ተናግረዋል። ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ 2 ነጥብ 1 ቢሊየን ጥሬ ብር፣ 87 ሺ ሜትሪክ ቶን ምግብ እና ከ783 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ፣ 217 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የህክምና መድሃኒቶች እንዲሁም የመጠለያ ግብዓቶች ጨምሮ 130 ሺህ ኪሎ ግራም ምግብ ነክ ያልሆኑ የሰብዓዊ ድጋፎች ወደ ትግራይ ክልል ተልኳል ብለዋል። ህወሓት ቀጣይ የዝናብ ወቅት እየመጣ ባለበት በዚህ ወቅት ለሌላ ጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑን ያሉ ሲሆን ህዝቡን በሃይል ለጦርነት እየመለመለ ነው ብለዋል። ድርጊቱ ቀጣዩን የእርሻ ስራ እንደሚያደናቅፍና በክልሉ ያለውን የሰብዓዊ ቀውስ እንደሚያባብስ ያደርጋል ብለዋል። በአፋር ክልል በግጭቱ ጉዳት ለደረሳበቸው ዜጎች 19 ሺ ሜትሪክ ቶን ምግብ ለአማራ ክልል ተፈናቃዮችም 244 ሺህ ሜትሪክ ቶን ምግብ መሰራጨቱን ገልፀዋል። ቢቢሲ ኤፍቢሲ ### Response:
### Text: ዶክተር ነገሪ ስለ ደምቢ ዶሎ️በኦሮሚያ ክልል ደምቢ ዶሎ ከተማ በአንድ ነፍሰጡር እና በሌሎች አራት ሰዎች ላይ ጥቃት የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩንኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ አስታወቁ።ትናንት ማምሻውን ደምቢዶሎ ከተማ በአንድ በለሶስት እግር ተሽከርካሪ አንድ ነፍሰጡር እናት ይዞ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ ያለ ቤተሰብ ላይ ጥቃት ደርሶ ነበር።በጥቃቱም ነፍሰጡሯ እናት ህይወቷ ሲያልፍ በቀሪዎቹ አራት ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።ጥቃቱ ማንም ፈጸመ ማን የተወገዘና አሳፋሪ ድርጊት ነው ያሉት ዶክተር ነገሪ ለቤተሰቦቻቸው የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል።ይህን አስነዋሪ ድርጊት በመቃወምም የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ በከተማዋ ሰላማዊ ሰልፍ ያካሄዱ ሲሆን ሰልፈኞቹም በሰላም ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ገልጸዋል።ወደ ፊትም መሰል ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶች ሲከሰቱ ህዝቡ በተመሳሳይ ከመንግስት ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።እንደ ዶክተር ነገሪ ገለጻ በጥቃቱ የተጠረጠሩ ሶስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው።ጥቃቱን በፈጸሙ አካላት ላይ የተጀመረው ምርመራ ሲጠናቀቅም ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ዶክተር ነገሪ ተናግረዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ያለ አግባብ ዲግሪያችንን ተከልክለናል የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችትምህርቱን ቢያጠናቅቁም የመግቢያ መስፈርቱን ላላሟሉ ዲግሪ አንሰጥም ዩኒቨርሲቲውበኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በቡራዩ ቅርንጫፍ ለአራት ዓመታት ስማር ቆይቻለሁ። የተማርኩት ለማወቅ ብቻ ሳይሆን ዲግሪ አግኝቼ በሥራዬ ዕድገት ለማግኘትና ለመሻሻል ነበር የሚሉት አቶ ገመቹ ዳባ ትምህርቱን ሲያጠናቅቁ ያልገመቱትን ዲግሪ አይሰጥህም የሚል ምላሽ ማግኘታቸውን ይናገራሉ።እንደ አቶ ገመቹ ገለፃ ትምህርቱን ለአራት ዓመታት ሲከታተሉ ዲግሪ ከተሰጣቸው ጓደኞቻቸው የተሻለ ውጤት ሲያስመዘግቡ ቆይተዋል። ሆኖም ትምህርቱን ሲያጠናቅቁ ጓደኞቻቸው ዲግሪ ሲሰጣቸው ለእርሳቸው እና ለተወሰኑ ሰዎች ቀድሞ ስትመዘገቡ መስፈርቱን አታሟሉም ነበር በሚል ሰበብ ዲግሪ አይሰጣችሁም ተብለዋል።ምንም እንኳን የአስራሁለተኛን ክፍል ብሔራዊ ፈተና አልፈው ዩኒቨርሲቲ ባይገቡም በቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ በመማር የደረጃ ሦስትን የትምህርት ብቃት ምዘና ሲኦሲወስደው አልፈዋል። ዩኒቨርሲቲውም በዲግሪ መርሐ ግብር መማር ትችላለህ ብሎ የመዘገባቸው ይህንን መስፈርት እንደመግቢያ በመውሰድ እና ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀውንተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በማለፋቸው ነበር።ተጨማሪ ያንብቡ 0816 ### Response:
### Text: መፍትሄ ባልተበጀለት ግጭት እየተበጠበጠች ያለችዉ ድሬደዋ ከተማገንደ ገራዳ በተባለው የከተማይቱ አካባቢ ትናንት የተቀሰቀሰ ግጭት ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ አንድ የህክምና ባለሞያ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ እንደገለፁት ትናንት እና ዛሬ ብቻ በከተማው አካባቢዎች እየተፈጠረ ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ ወደ ድል ጮራ ሪፈራል ሆስፒታል ከመጡ ተጎጂዎች የሁለቱ ሕይወት አልፏል። ከዚህም ሌላ የህክምና ባለሞያው «በዛሬው ዕለት ተጎድተው የመጡ ሰዎች ቢኖሩም እንኳን ወደ ሆስፒታሉ አይገቡም የሚሉ ሰዎች እንደነበሩ ሀኪሞችም ላይ አደጋ ሊያደርሱ እንደነበር ገልጸዋል። ድሬደዋን ጨምሮ አጎራባች ለሆኑ አካባቢዎች የሪፈራል ህክምና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የድል ጮራ ሪፈራል ሆስፒታል ሠራተኛ በራሱ ለሁለት ተከፍሏል ያሉት አስተያየት ሰጭው አስተዳደሩ ራሱ ሥራ ላይ መቸገሩንና ሆስፒታሉ ባለቤት አልባ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል። የተቋሙ የጥበቃ ስርዓት ልል መሆኑንም ጠቁመዋል። በሌላ በኩል ከፖሊስ ወይም የሚመለከተው አካል ስለድረጊቱም ሆነ ምክንያቱ ማረጋገጫ ማግኘት ባይቻልም በከተማው ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ ትናንት አንድ የባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ በእሳት መቃጠሉ ታውቋል። የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ### Response:
### Text: የአቶ እስክንድር ነጋ የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ የወንጀል ችሎት አቶ እስክንድር ነጋን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።መርማሪ ፖሊስ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ያገኘውን የምርመራ ሥራ ለፍርድ ቤቱ አብራርቶ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎችም የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።ጠበቆችም አቶ እስክድር ነጋ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ የጠየቁ ሲሆን ፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።ምክንያቱ መርማሪ ቡድኑ አቶ እስክንድር ነጋ የጠረጠረበት ወንጀል ሞት ያስከተለ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከ15 ዓመት በላይ ሊያስቀጣቸው ስለሚችል ነው ብሏል።በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአቶ እስክንድር ነጋ ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል እንዲከፈት የወሰንኩ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ይስጠኝ በማለት አመልክቷል።ችሎቱ በሰጠ ትዕዛዝ ዐቃቤ ሕግ ለቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚያቀርበው አቤቱታ እስከነምስክሮች ዝርዝር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓም ዐቃቤ ሕግ በሚያቀርበው አቤቱታ የጠበቆች መቃወሚያ ካለም እሰማለሁ ብሏል። ይህ እስከሚሆን ድረስ ግን ተጠርጣሪው አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ አዝዟል። ### Response:
### Text: በአፋርና ኢሳ ጎሳ መካከል ተከስቶ የነበረውን ግጭት ለመፍታት የሚያስችል የሰላም ኮንፈረንስ ተካሄደ በአፋርና ኢሳ ጎሳ መካከል ተከስቶ በነበረው ለመፍታት የሁለቱ ጎሳ አባላት እና የአካባቢው ነዋሪዎች የተሳተፉበት የሰላም ኮንፈረንስ በሚሌ ወረዳ አዳይቱ ቀበሌ ተካሂዷል፡፡በኮንፈረንሱ ላይ የተሳተፉ የሁለቱ ጎሳ አባላት በአፋር እና በኢሳ መካከል ችግር እንደሌለ ገልፀው በአካባቢው ባለፉት 11 ወራት የተከሰተው ግጭት ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ወጣቶች ወዳልተገባ ግጭት እንዲገቡ በመደረጉ ነው ብለዋል፡፡የሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት ሁለቱ ጎሳዎች ግጭት ውስጥ እንዲገቡ ያስቻለ መሆኑን ያስታወሱት የጎሳ አባላቱ በቀጣይ ሰላምን በማስጠበቅ ወደ ልማት ፊታቸውን እንደሚያዞሩ በውይይቱ ወቀት አንስተዋል፡፡ሁለቱንም ጎሳዎች በመሰረተ ልማት ለማስተሳሳር በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ የአፍር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ በዚህ ወቅት ገልፀዋል፡፡ የአርብቶ አደሩን ልጆች በትምህርት ተጠቃሚ የሚያደርግ አዳሪ ትምህርት ቤት ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ በዚሁ ወቅት ተቀምጧል። የክልሎቹ የስራ ኃላፊዎችም ችግሩን ከመሰረቱ በመፍታት በቀጣይ የልማት ስራዎች ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል፡፡ምንጭ ዋልታ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: የሚዲያው ሚና ሃሳቦችን ለማቀራረብ እንደ ዶክተር ሙላቱ አለማየሁ ገለጻ የሚዲያው ዘርፍ በሀገራችን ከተጀመረበት 1992 እኤአ ጀምሮ ብዙ ውጣወርረዶችን ማለፉን ይጠቅሳሉ፡፡ አንድ ጊዜ የህዝብን ድምጽ ሌላ ጊዜ ደግሞ የመንግስትን ድምጽ በማሰማት አልፎ አልፎ ገለልተኛ ሆነውም ለመዘገብ ሲሞክሩ ዘመናትን አልፈዋል፡፡ መንግስትም ለዘርፉ እድገት እንዲሁም ለሞያው ክብር ማነቆ የሆኑ ህጎችን ሲቀርጽ አንዳንዴም ከዛ በተቃራኒው ህጎችን ሲያሻሽል ቆይቷል፡፡ የሚዲያዎችን ጉዳይ የመቆጣጠር ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ የብሮድ ካስት ባለስልጣንም እስካሁን በተሰጠው ስልጣን ለመጠቀም ሲሞክር ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ ግን የሚዲያ ነጻነትን ማስከበር በመንግስት ብቻ ሳይሆን እስከ ህዝቡ ዘልቆ የሚገባ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ጋዜጠኛ መብቱ ሳይረገጥ የመዘገብ መብቱ እንደተጠበቀ ሆኖ የህብረተሰቡንም ትክክለኛ መረጃ የማግኘት መብት መጣስ የለበትም፡፡ ሀገራችንን ወደፊት ሊያሻግሯት ከሚችሉ ጠንካራ ተቋማት መካከል አንዱ ሚዲያ ለመሆኑ ክርክር የለውም ይህንን የምንመራበት መንገድ ግን ሞያዊ ስነምግባሩን በጠበቀ ትክክለኛ፣ ታማኝ፣፡ሚዛናዊ፣ ፍትሐዊ፣ ምሳሌያዊ መርሆዎችን ተጠቅሞ እንዲራመድ ካልስቻልነው ጉዳቱ የዛኑ ያህል የከፋ ይሆናል፡፡ 1216 ### Response:
### Text: የቀዳማዊ ኃይለስላሴ መታሰቢያ ኀውልት️ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ የተገነባው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ መታሰቢያ ኀውልት የካቲት 3 ቀን 2011 የሚመረቅ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ።ለቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት መመስረት በነበራቸው ታላቅ የመሪነት ሚና የመታሰቢያ ኀውልት እንዲቆምላቸው መወሰኑ ይታወቃል።የኀውልቱ ግንባታ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ ፈለገ ሰላመ የስነ ጥበብ ባለሙያዎች መከናወኑን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች በተገኙበት በ32ኛው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ላይ ይመረቃል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብያት ጌታቸው እንደገለፁት የኀውልቱ መቆም ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት መመስረት ላመረከቱት ጉልህ አስተዋፆ መታሰቢያነት ነው።አፍሪካውያን አንድ ሆነው በመቆም ለነፃነታቸው እንዲታገሉ ህብረቱ እንዲመሰረት በማድረግ ላደረጉት ትግል እውቅና ለመስጠት የተሰራም ነው ብለዋል።በአዲስ አበባ በሚካሄደው 32ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በርከት ያሉ የተለያዩ አገራት መሪዎችና ድፕሎማቶች እንደሚገኙ ይጠበቃል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: 2019 «አሸናፊ መሆኔ የሚገርም ነገር ነዉ። ብቻ እንደ ግለሰብ በጣም ያኮራል። ትልቁ ግን ግን ሃገርን ማስጠራት ማለት ኩራት ነዉ። ለአፍሪቃም ኩራት ነዉ። ስለዚህ ይህን ጉዳይ ጉዳያችን ብለን ለዓለም ሕዝብ ለመጀመርያ ጊዜ ለመላዉ ዓለም ያሳወቅንበት ነዉ። ጥሩ ስራ ተሰርቶአል እስካሁን ድረስ ግን ብዙ ስራ እንደሚጠብቀን ነዉ የሚያሳየን። ሆኖም ግን ብቻችንን የምንሰራዉ ስራ ስላልሆነ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ድምፅ ሰጥቶ እዚህ ደረጃ ላይ አድርሶናል። ዘንድሮ ለዉድድር ከኔጋ የቀረቡት አስሩም ጀግኖች በጣም ጥሩ ስራን ሰርተዉ ነዉ የቀረቡት። ሆኖም ግን የኛ በለጥ ብሎ የታየበት ምክንያት ሁሉንም ማኅበረሰብና ዜጋ የሚነካ ጉዳይ በመሆኑ ነዉ። የሴቶች ጉዳይ ደግሞ ለዘመናት የቆየ ጮክ ብለን የማንናገርለት ችግራችን ነበር። አሁን ግን እዚህ ላይ የደረስነዉ የችግሩን መፍቺያና የግንዛቢ ማስጨበጫ በመስራታችን ነዉ። እናም ለሃገር በተለይ ጥሩ ጥሩ መፍትሄ ነዉ የሚሆነዉ። እንደ አፍሪቃዉያንም በጣም ትልቅ ኩራት ነዉ። አንድ የ «» ጀግና ከአፍሪቃ ሲገኝ ይህ ለመጀመርያ ጊዜ ነዉ። ለ «» ኖች ስለሸለሙኝ ምስጋናዬን ገልጬላቸዉ ነበር። ነገር ግን « ድምፅ የሰጠሽን ህዝብሽን አመስግኝ» ነዉ ያሉኝ መላዉ ኢትዮጵያዉያንን አመሰግናለሁ» ፍሬወይኒ መብርሃቱ ### Response:
### Text: የሴቶችና ህፃናት ጥቃትበኢትዮጵያ ሦስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት እንደተፈጸመባቸው አንድ ጥናት አመለከተ።የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት መከላከልና ጥቃቱ ሲፈጸም ምን አይነት ምላሽ መስጠት ይገባል በሚሉ ጉዳዮች ላይ በሴቶች ጉዳይ ከሚሰሩ ሲቪክ ማህበራትና ፌዴሬሽኖች ጋር ዛሬ እየተወያየ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።በውይይቱ ላይ ከመጋቢት 1 ቀን 2012 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2012 ዓም ባሉት ጊዜያት በሴቶችና ህፃናት ላይ የደረሰውን ጥቃት የሚያብራራ ጥናት ቀርቧል።ጥናቱ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና የአዲስ አበባ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በጋራ ያስጠኑት ጥናት ነው።በጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ በሁለት ወር ከሃያ ቀን ብቻ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል ከነዚህ ውስጥ 273ቱ ሴቶች ሲሆኑ ሰባቱ 7 ወንዶች ናቸው ተብሏል።ጥቃት ከደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናት መካከል 215ቱ በአዲስ አበባ በሚገኙ አስሩ ክፍለ ከተሞች ነዋሪ ሲሆኑ ቀሪዎቹ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚኖሩ መሆናቸውን ጥናቱ አመላክቷል።በሴቶች እና ህፃናት ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች አስገድዶ መድፈር ፣ ግብረሰዶም ና ያለዕድሜ ጋብቻ መሆናቸውን በጥናቱ ተገልጿል። ### Response:
### Text: ከ864 ሺህ በላይ ተከታይ ያለው የዋልታ የፌስቡክ ገፅ መጠለፉን ለመመልከት ተችሏል።የፌስቡክ ገፁ በክሪፕቶ ከረንሲ ጠላፊዎች እጅ እንደገባ የሚፃፉት ኮዶች እንደሚያመላክቱ የዘርፉን ባለሞያ ዋቢ አድርጎ ኢትዮጵያ ቼክ አስነብቧል።የአክስዮን እና ክሪፕቶ ከረንሲ የሚገበያይ ነጋዴ የሆነው አብነት ተፈራ እየጠየቁ ያሉት የክሪፕቶ ከረንሲ ቲተር ነው። ቴተር ማለት ወደ አሜሪካ ዶላር የሚመነዘር እና የሚተመን መጠን ያለው ሲሆን ስሌቱም 1 5000 = 5000 ነው። ብሏል።አክሎም በስተመጨረሻ የሚታየው ረጅም ቁጥር ደግሞ ኤተሪየም ዋሌት አድራሻ ነው፣ በህግ አስከባሪዎች እንዳይታወቁ ደግሞ አድራሻውን እየቁያየሩት ይገኛል ሲል ለ ኢትዮጵያ ቼክ 1074 አስረድቷል።ገፁን በቁጥጥር ስር ያዋሉት ጠላፊዎች የገፁን አድራሻ የቀየሩት ሲሆን የተለያዩ መልዕክቶችንም እያስተላለፉ ይገኛሉ። የገፁ ፕሮፋይል ፒክቸርም ተነስቷል።ዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት በበኩሉ ሕጋዊ የፌስቡክ ገጹ የቴክኒክ ችግር እንደገጠመው ገልጿል።ድርጅቱ በፌስቡክ ገፁ ላይ የገጠመውን የቴክኒክ ችግር ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን በመግለፅ ችግሩ መፈታቱን አስከሚያስታውቅ ድረስ በፌስቡክ ገፁ የሚለጠፉ ማናቸውም መልዕክቶች ከተቋሙ ዕውቅና ውጭ መሆናቸውን አሳውቋል። ### Response:
### Text: ከድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ ከትላንት ህዳር 8ቀን 2011አም ከሰአት በሃላ እና ህዳር 9ቀን እረፋድ ላይ በቀበሌ 09 ፖሊስ መሬትና መጋላጨብጡ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ፖሊስ አሁን ላይ መነሻ ምክንያቱን እያጣራው ያለው ግጭትና ሁከት የተፈጠረ ሲሆን በዚህም ግጭት በህክምና ጭምር የተረጋገጠ በስለት ጉዳት ጉዳት ደርሶበት የ1ሰው ህይወት ሲያልፍ በ2 ቤቶች ላይ ቀጠሎ እንዲሁም በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።ፖሊስ ከፌደራል ፖሊስና ከመከላኪያ ጋር በመሆን ግጭቱ ወደ 01 ቀበሌ መልካ ጀብዱ የመስፋፋት አዝማሚያ መታየቱን ተከትሎ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ለመቆጣጠርም ችሏል።በአሁን ወቅት ችግሩ በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ተገቢው ፀጥታን የማረጋገጥና ሰላምን የማስፈን ስራ እየተሰራ ሲሆን ተፈጥሮ የነበረውንግጭትና ሁከትም አሁን ላይ ለማስቆምና ለመቆጣጠር ተችሏል።በመሆኑም መላው ህብረተሰብ ወደ ግጭት ሁከትና መረበሽ ሰዎችን እንዲያመሩ ከሚያደርጉ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችናያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሱን በመጠበቅ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመሆን የማረጋገጥ ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጨምሮ ጥሪውን ያቀርባል።ህዳር 92011 አም ### Response:
### Text: ጀዋር መሀመድ እና እክንድር ነጋ በ የአዲስ አበባ የባለቤትነት ዉዝግብ«እኛ የምንለዉ ሕጉ የሚለዉን ነዉ። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ሕግ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ ነች ይላል። የፌደራሉ ሕገ መንግሥትም ኦሮሚያ ከአዲስ አበባ ልዩ ጥቅም እንዳለዉ ያስቀምጣል»የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅና የመብት አቀንቃኝ ጀዋርመሐመድ «የአዲስ አበባ ጉዳይ የዜግነት ጥያቄ ነዉሕገ መንግስቱ ከየት መጣ ማን አወጣዉ ምንስ አላማ ነበረዉ» ጋዜጠኛና የመብት አቀንቃኝ እስክንድርነጋ ።«እንዴ ምነዉ እባክሕ እስክንድር ነጋ እኮ የመብት ታጋይ ነዉልንቃወመዉ፣ ልንተቸዉ እንችላለን፣ ከዚያ ባለፈ ግን ዛሬ እስክንድርን ያስፈራሩ ነገ ጀዋርን ያስፈራራሉ እስክንድር ብቻዉን ሳይሆን ሁላችንም አብረነዉ ተሰልፈን እንታገላለን»ጀዋር መሐመድጀዋር ያለዉን «የምጠራጠርበት ምንም ምንም ምክንያት የለኝም። አመሰግነዋለሁ ።»እስክንድር ነጋ።«በግሌ ከጠይቀከኝ ከእስክንዳር ጋር አይደለም ከማንም ጋር በማንኛዉም ሰዓት በዚሕ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ብቻ ሳይሆን በሌላም ጉዳይ ላይ ለመወያየት ዝግጁ ነን»ጀዋር መሐመድ«ለመወያየት መቶ በመቶ ዝግጁ ነኝ። እምንፈታዉም በድርድርና ዉይይት ነዉ።ብስለቱም አለን» እስክንድር ነጋ። የጀርመን ድምፅ ራድዮ ### Response:
### Text: የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በትናንትናው እለት ሁለት የፖሊስ አባላቱ በቄራ ጎፋ ማዞሪያ አካባቢ የፈፀሙትን ድርጊት እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ትናንት ረፋድ ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ቄራ ጎፋ ማዞሪያ አካባቢ በድለላ ስራ ላይ በተሰማሩ ሁለት ቡድኖች መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበር አስታውሷል።ይህን ተከትሎም የተፈጠረውን አለመግባባት ለመዳኘት ወደ ስፍራው ያቀኑ ሁለት የፖሊስ አባላት አለመግባባት የፈጠሩት የቡድን አባላት ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንዲሄዱ በጠየቁበት ወቅት አለመግባባቱ ተካሮ የፖሊስ አባላቱ በግለሰቦች ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን እና ጥይት መተኮሱን ጠቅሷል። የፖሊስ አባላቱ አዲስ እና በቅርቡ ሰራዊቱን የተቀላቀሉ መሆናቸውን ያስታወሰው ኮሚሽኑ የፈፀሙት ድርጊት ግን ተገቢነትም ሆነ ተቀባይነት የሌለው መሆኑንም ገልጿል። አሁን ላይም ጉዳያቸው በወንጀልና በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት እየተጣራ መሆኑን ጠቅሶ ጉዳዩን አጣርቶ የደረሰበትን ውጤት ለህዝብ አሳውቃለሁ ብሏል። ህብረተሰቡም መሰል ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በየደረጃው ለሚገኙ የስራ ኃላፊዎች የማሳወቅ ልምዱን አጠናክሮ እንዲቀጥል መጠየቁን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ### Response:
### Text: ዛሬ ማምሻውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት ለመሸፈን ጩኸቱን ቀጥሎበታል ብሏል። በአማራ ክልል እና በአፋር ክልል የተለያዩ ጥቃቶችን በመፈጸም በዜጎች ላይ ከፍተኛ አካላዊና ቁሳዊ ጉዳት እያደረሰ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል።ቡድኑ በውጫሌና ጭፍራ አካባቢዎች ላይ በፈጸመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ከ30 በላይ ንጹሃን ዜጎች በግፍ መግደሉን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል። እያደረሰ ያለው ጭፍጨፋና ግድያ እንዳይታወቅበት ለመሸፋፈን የተለመደውን የተኩላ ጩኸት ቀጥሎበታል ሲል ገልጿል።ሚኒስቴሩ የህወሓት ቡድን በወረራ ከያዛቸው አካባቢዎች የተፈናቀሉና የሰብዓዊ እርዳታ የሚሹ ዜጎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን አመላክቷል።ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በ የሐሰት መረጃ ሳይወናበድ በሰሜን ወሎ፣ በጎንደር በዋግ ህምራ እና በአፋር ክልሎች የዜጎችን ጉዳት ሊመለከት እንደሚገባ መንግስት ጥሪ ያቀርባል ብሏል።የኢትዮጵያ መንግስት አሜሪካንና አጋሮቿ በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ሚዛናዊ ያልሆነ አቋም ዳግም እንዲመለከቱት መጠየቁን እንዲሁም የአውሮፓ ፓርላማ ያወጣው መግለጫ ከእውነታው የራቀ መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አስፍሯል። ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: ተማሪዎቹ በድጋሚ እንዲፈተኑ ተወስኗል በኮንሶ ዞን በፀጥታ ችግር የ2013 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ተፈትነው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች በድጋሜ እንዲፈተኑ መወሰኑን የኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታውቋል።መምሪያው ይህን ያሳወቀው የክልሉን ትምህርት ቢሮ ዋቢ በማድረግ ነው። ተማሪዎቹ ድጋሜ እንዲፈተኑ ውሳኔ የተላለፈው ለኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር በቀረበ ቅሬታ ሲሆን ተፈታኝ ተማሪዎች ከወዲሁ ለፈተናው እንዲዘጋጁ ጥሪ ቀርቧል።በኮንሶ ዞን አከባቢ ከ2011 ዓም ጀምሮ በፀጥታ ችግር ምክንያት ተማሪዎች በሙሉ ቀልባቸው አልተማሩም።የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተፈተኑ 824 ተማሪዎች መካከል 51 ተማሪዎች ብቻ ዩኒቨርሲቲ የገቡ ሲሆን 773ቱ ወደ ዩኒቨርሲቲ ማለፍ አልቻሉም። እኚሁ 773 ተማሪዎች ናቸው በድጋሜ የ12ኛ ክፍል ፈተና እንዲወስዱ ዕድል የተመቻቸላቸው።ከዚህ ቀደም ትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ ክልሎች በፀጥታ ችግር ውስጥ ሆነው ፈተና ተፈትነው ውጤት ያልመጣላቸው ተማሪዎች ከ2014 ተፈታኞች ጋር በድጋሜ እንዲፈቱን ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 202015 ዓም በኃላ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።መረጃውን ከኮንሶ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉመምሪያ ነው ያገኘነው። ### Response:
### Text: ፈተናውን 986 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል በትግራይ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 986 ከመቶ0ወደ ቀጣዩ ክፍል ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።ኮሮና ተከትሎ በትግራይ በተካሄደው ጦርነት ተቋርጦ የነበረው የመማርና የማስተማር ሂደት ከሚያዝያ 2015 ዓም ጀምሮ በተሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በመውሰድ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤታቸዉ ይፋ ሆኗል።በትግራይ ትምህርት ቢሮ0የትምህርት ጥራትና ምዘና ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዳይሬክቶሬት አቶ ክንፈ ፍስሃ0 ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ከተፈታኞቹ 986 በመቶ ወደ ቀጣይ ክፍል ተሸጋገረዋል።00የነበረውን ክፍተት ለሞምላት የተሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በቂ ባለመሆኑ በ2016 ዓም ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች በሚሰጠው ትምህርት ሁሉም መምህራንና የሚመለከታቸው አካላት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተማሪዎቹ ለማብቃት ጥረት ማድረግ አለባቸው ብለዋል ዳይሬክተሩ።0በተያያዘ በክልሉ ትምህርት ቢሮና የፌደራል መንግስት ቅንጅት ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑንና አገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 22016 ዓም እንደሚወስዱ ከትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።መረጃውን የመቐለ ቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው ያደረሰን።0 ### Response:
### Text: የገቢዎች ሚኒስቴር️ግምታዊ ዋጋቸው 1 ሚሊየን 300 ሺህ ብር በላይ የሚሆኑ የኮንትሮባንድ ዕቃች በተለያዩ የጉምሩክ የፍተሻ ጣቢያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።ባዛሬው ዕለት በተለያዩ የጉምሩክ የፍተሻ ጣቢያዎች ላይ በተደረገ ክትትል ግምታዊ ዋጋቸው 1 ሚሊየን 315 ሺህ 310 ብር የሚሆኑ የተለያዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።በዚህ መሰረትም በወልዲያ የጉምሩክ ፍተሻ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ ጊዜው ያለፈበት የፋፋ ዱቄት እና ግምታዊ ዋጋቸው 385 ሺህ 50 ብር የሆኑ 369 ሞባይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ነው የተገለፀው።በተመሳሳይ በድሬዳዋ ከተማ ውስጥ ዋጋቸው 76 ሺህ 500 ብር የሚገመቱ የመኪና ጎማዎችና የተለያዩ መድሃኒቶች በግለሰቦች ቤት ውስጥ በፌዴራል ፖሊስ፣ ጉሙሩክ ሠራተኞች እና ህብረተሰቡ ባደረገው ትብብር በቁጥጥር ስር ውለዋል።ከዚህ ባለፈም በህገ ወጥ መንገድ ከመተማ ወደ መሀል ሀገር ሊገቡ የነበሩ ግምታዊ ዋጋቸው 167 ሺህ 760 ብር የሆኑ 1 ሺህ 997 የብሬን ጥይቶችና 100 የክላሽ ጥይቶች በሠራባ ኬላ ላይ በጉምሩክ ሰራተኞች በቁጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን ሲያንቀሳቅሱ የነበሩ ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።ምንጭ ### Response:
### Text: በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግለጫበከተማችን ሀዋሳ ከየካቲት 28 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ ውይይት እንድቋረጥ ተደርጓል።ውይይቱ የተቋረጠበት ዋናው ምክንያት ለውይይቱ በቀረበው ሰነድ ውስጥ የተካተቱ አንዳንድ ነጥቦች የሲዳማን ብሄር ህገ መንግስታዊ መብቶችን የምጻረሩ እንደሆኑ በመረዳት የብሄሩ ተወላጅ የሆኑ አመራር በሙሉ የቀረበው ሰነድ ለውይይት የማይጋብዝ እንደሆነ አቋም በመያዝ ከስብሰባው ራሳቸውን ካገለሉ በኋላ በ29062011 ዓም አጠቃላይ ክልላዊ መድረኩን ለማስኬድ ምቹ ሁኔታ ስላልነበረ መድረኩ ሊቋረጥ ችሏል።ከዚህ ጋር ተያይዞ በዕለቱ በከተማው የሚገኙ የሲዳማ ብሄር ወጣቶች በዲርጊቱ ላይ ስሜታቸውን ከገለጹ በኋላ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደየቤታቸው ተመልሷል።በአሁኑ ሰአትም በከተማው የሚገኝ ህብረተሰብ ያለምንም የጸጥታ ስጋት የዘወትር ተግባር በአግባቡ በማከናወን ላይ ይገኛል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ህብረተሰቡን እንዳይረጋጋ ለማድረግ አቅደው የሚሰሩ አንዳንድ ሚድያዎች እና በግለሰብ ደረጃ በማህበራዊ ገጾች ላይ አፍራሽ መልዕክቶች እየተለቀቁ ስለሚገኙ ህብረተሰቡ በዚህ ሳይሸበር የዘወትር ተግባሩን እንዲያከናውን ከተማ አስተዳደሩ ጥርውን ያቀርባል።ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመኮሙ ### Response:
### Text: በመስቀል ደመራ በዓል አከባበር 55 ሰዎች መታሰራቸውን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት አስታወቀ በዛሬው የመስቀል ደመራ በአል አከባበር ላይ 55 የበዓሉ ታዳሚዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ህዝብ ግንኙነት እና ጉዳይ አስፈፃሚ መላከ ሕይወት አባ ወልደየሱስ ሰይፉ ለቢቢሲ ገለፁ። መላከ ህይወት አባ ወልደየሱስ እንደገለፁት 33ቱ ምእመናን በቁጥጥር ስር የዋሉት ቤተክርስትያኗ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት እንዲቆም የሚያወግዝ ፅሁፍ ያለበት ቲሸርት ለብሰው በመገኘታቸው ነበር።ምእመናኑ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት የሆኑት ቲሸርቶች የቤተክርስትያን ጉዳይ ያገባኛል፣ የቤተክርስትያን መቃጠልና ጥቃት ይቁም የሚሉ ፅሁፎች ያለባቸው እንደነበሩ አባ ወልደየሱስ አስረድተዋል። አራቱ ደግሞ የሌላ ሰው ባጅ አድርገው በመገኘታቸው በቁጥጥር ሲውሉ ቀሪዎቹ 12 የሚሆኑት ደግሞ ስለት ይዘው ተገኝተዋል በሚል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ያስረዳሉ። በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች የተወሰዱት ካዛንችዝ ከሚገኘው ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደነበርና በኋላ እሳቸው ወደ ፖሊስ ጣቢያው ሄደው ሃላፊዎች ከነጋገሩ በኋላ 37 በዋስ መለቀቃቸውን መላከሕይወት አባ ወልደየሱስ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: በትራፊክ አደጋ የ1 ሰው ህይወት ሲያልፍ 13 ሰዎች ተጎድተዋልበወላይታ ዞን ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ በተሽከርካሪ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በ13 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ፖሊስ አስታወቀ። አደጋው የደረሰው ዛሬ ረፋዱ ላይ 0በወረዳው አመያ 0በተባለው መንደር ነው።ከዳውሮ ዞን ዋና ማዕከል ተርጫ ከተማ 56 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ሀዋሳ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 301926 ኢት የሆነ ሀገር አቋራጭ አውቶብስ በመገልበጡ አደጋው መድረሱን የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር አርጋው ፈለቀ ተናግረዋል።አውቶቡሱ በግልገል ጊቤ ሶስት ፍተሻ ጣቢያ 0ከቆመበት ቦታ ወደ ኋላ ተንሸራቶ 200 ሜትር ጥልቀት ካለው ጉድጓድ ውስጥ በመግባቱ አደጋው ደርሷል0ብለዋል።በአደጋው ህይወቱ ያለፈ ግለሰብ አስከሬን ወደ ቤተሰቦቹ መላኩን ጠቁመው 0ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው አምስት ሰዎች በወላይታ ሶዶ ክርስትያን ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተሩ አመልክተዋል።ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ስምንት ሰዎች ደግሞ 0በአቅራቢያው በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እያገኙ ነው። የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ምክትል ኢንስቴክተሩ ገልፀዋል።ኢዜአ ### Response:
### Text: የፖሊስ የዘፈቀደ እስር በአስቸኳይ ሊቆም እና የታሰሩትም ሊለቀቁ ይገባልየኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንበዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ የተገኙ ሰዎች በፖሊስ እየታሰሩ ከመሆናቸው ጋር በተያያዘ በሚዲያዎች የወጡ ዘገባዎችንና ለኮሚሽኑ የቀረቡ አቤቱታዎችን ተከትሎ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሚከተለውን ብለዋል የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል አስፈላጊ የጤና መመርያ ሲሆን ሕብረተሰቡም ሊከተለው የሚገባ ነው፡፡ በእርግጥም የአስቸኳይ ጊዜ ደንቡ ማንኛውም ሰው እንደ ገበያ ቦታዎች ሱቆች ፣ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ባሉ የሕዝብ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች እና በሌሎች ህዝብ በሚበዛባቸውና የአካል መራራቅን መጠበቅ በማይቻልባቸው አካባቢዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ውጪ ግን በየትኛውም ቦታ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ የተገኙ ሰዎች ላይ ሁሉ የሚደረግ የዘፈቀደ እስር ከህግ ውጭ ከመሆኑም በላይ ለነገሩ ሁኔታ ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ እና የታለመለትን አላማ የሚቃረን በመሆኑ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል፣ በዚህ ሁኔታ የታሰሩ ሰዎችም በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል። ### Response:
### Text: የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ወደ ትግል ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል።ከንቲባው ዛሬ አመሻሹን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት ከእኛ ይጠበቃልና እኔም ከሌሎች ወንድሞቼ ጋር ወደ ትግሉ ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ። በግንባር ተገኝተን ያዘጋጀነውን ስንቅ እናቀብላለን ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ጀግናው ሠራዊታችንን በወኔ እናበረታታለን ብለዋል።የአስተዳደሩ የፀጥታ ኃይሎችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ከመቼውም ጊዜ በላይ የድሬዳዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ የልማትና አስተዳደራዊ ሥራዎችን በሙሉ አቅማቸው ለማከናወን ተዘጋጅተዋል ሲሉም አሳውቀዋል።አቶ ከድር ጁሀር መላው ነዋሪዎች አካባቢያችሁን በመጠበቅ ሠራዊቱን በመደገፍና ወደ ግንባር በመዝመት እንዲሁም በፀሎት ከጎናችን እንድትሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ። ያለጥርጥር ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ሲሉ ነው በተረጋገጠ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት።የኢትዮጵያ ጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ ወደግንባር ዘምተው ሰራዊቱን እንደሚመሩ ካሳወቁ በኃላ የተለያዩ ባለስልጣናት ፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ታዋቂ የስፖርት ሰዎች ጨምሮ ሌሎችም ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ እገለፁ መሆናቸው ይታወቃል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጾመ ነነዌን በማስመልከት ያወጀው ጾምና ጸሎት ዛሬ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓም ያበቃል።ቅዱስ ሲኖዶስ ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁርልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ሲል ባስተላለፈው ጥሪ መሰረት ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት ምዕመኑን ይህንኑ ተግባራዊ ሲያደርግ ነበር።ቤተክርስቲያኗ ጥቁር ልብስ0 የምንለብሰው በመከራ መጽናት ለመግለጽ ነው ማለቷ ይታወሳል።በሌላ በኩል ቅዱስ ሲኖዶስ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ በጸሎትና በምሕላ ጊዜያት የደነደኑ ልቦች ወደ ልቦናቸው ተመልሰው የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥሪ ሰምተው የማይፈጽሙ ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።ቅዱስ ሲኖዶስ ሰልፍ ይደረጋል ያለው በየካቲት 52015 ዓም ሲሆን በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን ድምፃቸውን የሚያሰሙበት ቤተክርስቲያኗ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል እንዲሁም እየተፈፀመ ያለው ህገወጥ ድርጊት ለዓለም ህዝብ የሚገለፅበት እንደሆነ ማስረዳቱ አይዘነጋም። ### Response:
### Text: ከሾኔ️ሀይ ፀጊሽ ነኝ ከሾኔ የሾኔ ወጣቶች በትላንትናው እለት ከቀኑ 800 ሰዓት ጀምሮ በሾኔ ሁለገብ አዳራሽ ታላቅ የሀሳብ ምልልስ በሰላማዊ መንገድ በጣም በርካታ ወጣቶች በተገኙበት ስብሰባ ተደርጓል። የስብሰባው መነሻም ሾኔ የዛሬ 107 ዓመት ነው የተቆረቆረችው ነገር ግን የዕድሜዋን ያክል ልታድግ አለመቻሏ የከተማዋ ባለስልጣናት ስልጣን ላይ ሲመጡ የራሳቸውን ጥቅም ብቻ የማስቀደም ስራ እየሰሩ ተተኪውም በእነርሱ አርአያነት እየተከተለ እንዲሄድ አድርገዋል በማለት እጅግ በጣም ኪራይ ሰብሳቢነት እንደተንሰራፋ በመግለፅ ወጣቶች ስለ ሾኔ ችግር ሊያውቅ የሚችል የከተማው ተወላጆች በየሙያቸው በመቀጠር የከተማዋን እድገት ማፋጠን ያስችል ዘንድ የቀድሞው አመራሮች ቶሎ ስልጣን ይልቀቁ ፡ ሌቦችም ለፍርድ ይቅረቡ በመለት ለሀዲያ ዞን ምአስተዳደር ለአቶ ሀብታሙ ታረቀኝ ያሳሰቡ ሲሆን ወጣቶች በቂ ማስረጃዎች እንዳሉዋቸውም ገልፀዋል፡፡ በከተማዋ የተስተዋለው ግልፅ ችግር የመሬት አስተዳደር፣ የማዘጋጃ ቤት፣ የኮንስትራክሽን፣ የመብራት፣ የሆስፒታል፣ የስቴድዬም ችግሮች እንዲሁም የፋይናንስ ወዘተ የተገለፁ ትችቶች ውስጥ ተካተዋል። ከቻልክ የሾኔ ወጣቶች ሀሳባቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለፃቸውን እነድታበረታታ እፈልጋለሁ፡፡ ### Response:
### Text: ባህርዳር ትናንት እሁድ ባህር ዳር ከተማ ውስጥ አባይ ማዶ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በአካባቢው ሚሊሻዎችና ሲፈለግ በነበረ በአንድ ግለሰብ መካከል በተደረገ የተኩስ ለውውጥ የሦስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የባህር ዳር ፖሊስ አባል ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም ተፈጸሞ ከቆየ ሌላ የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጥሮ ሲፈለግ የቆየ ነው የተባለን ግለሰብ ሊይዙ ሲከታተሉት የነበሩ የአካባቢው ሚሊሻዎች ላይ ተኩስ በመክፈቱ ነው ጉዳት የደረሰው።ሸፍቶ ነበር የተባለውን ግለሰብ ሲከታተሉ የቆዩት ሁለት የሚሊሻ አባላት እሁድ ምሳ ሰዓት አካባቢ ተጠርጣሪው አለበት ወደተባለው ቤት በሄዱበት ጊዜ ተተኩሶባቸው ህይወታቸው ሲያልፍ ተጠርጣሪው በሌሎች የጸጥታ አባላት እንደተተኮሰበት ለማወቅ ተችሏል።በተኩስ ለውውጡ የተመቱት ሁለቱ ሚሊሻዎች ወዲያው ህይወታቸው ሲያልፍ ተፈላጊው ግለሰብ ግን ከቆሰለ በኋላ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ነው ህይወቱ ያለፈው ተብሏል።ከሳምንታት በፊት መንግሥት የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ነው ካለው ግድያ ጋር በተያያዘ ከገባችበት ድንጋጤ በማገገም ላይ በምትገኘው የባህር ዳር ከተማ ውስጥ እሁድ ዕለት ያጋጠመው የተኩስ ልውውጥ በነዋሪዎች ላይ ስጋትን ፈጥሮ ነበር። ### Response:
### Text: የሶማሊያ መከላከያ ሶስት የአልሻባብ ታጣቂዎችን ገደለ። ሶስት የአልሻባብ ታጣቂዎች የተገደሉት በደቡባዊ ሶማሊያ አርብ ምሽት በተካሄደ ኦፕሬሽን ሲሆን የሶማሊያ ሃይል በአውድኒል ከተማ ባካሄደው ስምሪት ነው ተብሏል፡፡የከተማዋ አስተዳዳሪ ኢብራሂም መሃመድ ኑር ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት የሶማሊያ ሃይል እርምጃውን የወሰደው የከተማዋ ነዋሪዎች ጽንፈኛው አልሻባብ አስገዳጅ ግብር እንድንከፍል አድርጎናል በሚል በሰጡት ጥቆማ ነው፡፡በተካሄደው ኦፕሬሽን ሶስት የአልሻባብ ታጣቂዎች ሲገደሉ አንዱ ከነህይወቱ በቁጥጥር ስር ውሏል የጦር መሳሪያዎችና ጥይቶችንም መያዝ ተችሏል ያሉት አስተዳዳሪው የተያዘው ታጣቂም በመንግስት ቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል፡፡የአካባቢው ነዋሪ ለዥንዋ በስልክ በሰጠው ቃለ መጠይቅ እንደተናገረው በከተማዋ በሶማሊያ መንግስት ኃይልና በአልሻባብ ታጣቂዎች መካከል አርብ ምሽቱን የተኩስ ልውውጥ እነደነበር ተናግሯል፡፡የሶማሊያ ኃይል አሁን ከወሰደው እርምጃ በፊት በዋንሎዌይን ከተማ በሎወር ሸበሌ ክልል 15 የአልሻባብ ታጣቂዎቸን ገድሏል፡፡ የሶማሊያ ኃይል በማእከላዊና በደቡብ ሶማሊያ መጠነ ሰፊ ኦፕሬሽኖች በማካሄድ የአልሻባብ ጽንፈኞች አካባቢውን እንዲለቁ እየሰራ ነው፡፡ምንጭ፡ ኢዜአ ### Response:
### Text: ባለፉት ሶስት ቀናት ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በቀን 28112011 በሁለት መኪና ተጭኖ ወደ ድሬዳዋ ሊገባ የነበረ ግምቱ 1785140 ብር የሚያወጣ የምግብ ዘይት ሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ በፀጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር ውሎ ድሬዳዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽቤት ገቢ ተደርጓል። በተመሳሳይ ቀን ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ ይሄድ የነበረ የመንገደኞች ባቡር ሞተሩ ባለበት ክፍል ውስጥ በጥርጣሬ በተደረገ ፍተሻ 4955 የሞባይል ፍላሾች፣ 1195 የሞባይል ከቨር እንዲሁም 14 ዎኪቶኪ የሬድዬ መገናኛ በአጠቃላይ ግምታቸው 12 ሚሊዬን ብር በላይ የሚያወጡ ዕቃዎች በጉምሩክ ፈታሾችና የፌደራል ፓሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ዉለዋል፡፡በቀን 29112011 ዓም በቱሪስት ስም ገብቶ ታርጋ የቀየረ 4 መኪና በአዳማ ከተማ ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ከአዲሰ አበባ ወደ ጅማ ከተማ ሲገባ የነበረ ግምታዊ ዋጋ 480000 ብር የሆነ ዘይትም እንደተያዘ ተነግሯል፡፡ በቀን 3011 2011 ዓም በሞያሌ ቅርንጫፍ ፅቤት ግምታዊ ዋጋው 1142 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ 2855 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ የተያዘ ሲሆን በወንጀሉ የተጠረጠሩ 2 ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብሏል፡፡ምንጭ የገቢዎች ሚኒስቴር ### Response:
### Text: ለአዲስ አበባ መምህራን ታብሌት ሊሰጥ ነው በአዲስ አበባ ለሚገኙ መምህራን የትምህርት ዝግጅትና ቁጥጥር የሚያደርጉበት እንዲሁም የትምህርት እቅድ የሚያወጡበት ታብሌት ሊሰጥ ነው። የከተማ አስተዳደሩ በአዲስ አበባ ያለውን የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ በከፍተኛ ደረጃ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል፡፡በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን በከተማዋ ለሚገኙ የመንግስት ትቤት መምህራን የትምህርት ዝግጅት እና የትምህርት እቅድ የሚያወጡበት ታብሌት ለመስጠት የከተማ አስተዳደሩ ዝግጅቱን አጠናቅቋል፡፡ ለዚህ የሚረዱ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑም ይገኛሉ።ታብሌቶቹ በሳተላይት የሚገናኙ ሲሆን መረጃዎችን ወደ ማእከል የሚልኩበት መተግበሪያዎችን ያካተተም ይሆናል። ከታብሌቶቹ በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ ዓርማ ያረፈበት ቦርሳ እና ደረጃውን የጠበቀ ገዋን ለመምህራን የሚያቀርብ ይሆናል።በመምህራን የሚነሱ የተለያዩ ጥያቄዎችን ለመመለስም የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራም ይገኛል። በቀጣይ አመት ለመምህራን ቁሳቁሶች የማሟላቱ ተግባር የከተማ አስተዳደሩ በአዲሱ አመት በከተማዋ ለሚገኙ 600ሺ የመንግስት ትቤት ተማሪዎች ዩኒፎርምና የመማሪያ ቁሳቁሶች የማቅረብ ፕሮጀክት አካል ነው። ### Response:
### Text: 2013 በምርጫ 2013 ክልሎች የሚኖራቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፓርላማ የውክልና መቀመጫ የሲዳማ0ክልል0በሕዝብ0ተወካዮች0ምክር0ቤት0የሚኖረው0መቀመጫ0190 የደቡብ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውክልና 104 0ደቡብ ክልል ላለፉት 26 ዓመታት ገደማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነበረው ውክልና ወይም መቀመጫ 123 ነበር ሲዳማ ከደቡብ ክልል ወጥቶ ራሱን ከቻለ በኃላ ፣ ደቡብ የሚኖረው መቀመጫ ብዛት 104 ሆኗል። ኦሮሚያ0ክልል0በነበረበት 178፣0 አማራ0ክልል0በነበረበት 138፣ ሶማሌ0ክልል0በነበረበት 23፣0 አዲስ0አበባ0ከተማ0በነበረበት 23፣ ቤንሻንጉል0ጉምዝ0ክልል0በነበረበት 9፣0 አፋር0ክልል በነበረበት08፣0 ጋምቤላ0ክልል0በነበረበት 3፣ ሐረሪ0ክልል0በነበረበት 20እንዲሁም ድሬዳዋ0ከተማ0በነበረበት 20ሆነው ይቀጥላሉ።6ኛው0አጠቃላይ0ምርጫ0በትግራይ0ክልል0እንደማይከናወን0ምርጫ0ቦርድ0ቀድሞ0ያስታወቀ0ሲሆን፣ ከሰሞኑ0ምርጫ ቦርድ0ይፋ0ባደረገው0የክልሎች0የፓርላማ0ውክልና0ድርሻ0ውስጥም0የትግራይ0ክልል0አልተገለጸም።0ይሁን0እንጂ0ላለፉት0አሥርት0ዓመታት0የትግራይ0ክልል0የፓርላማ0ውክልና0380እንደሆነ0ይታወቃል።ይህንን0ከግምት0በማስገባት0ሥሌት ሲደረግ0የሕዝብ0ተወካዮች0ምክር0ቤት0አጠቃላይ0መቀመጫ0ብዛት0ከነበረበት05470አልተለወጠም።ከሪፖርተር ጋዜጣ ### Response:
### Text: የብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶር እና የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓም በመንበረ ጸባኦት ቅደስት ሥላሴ ካተድራል እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶር መግለፃቸውን የኢኦተቤ ቴሌቪዥን ዘግቧል።ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶር ለረጅም ጊዜ በሀገር ውስጥ እና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ትላንት ከዚህ ዓለም በሞተ ስጋ መለየታቸው መገለፁ ይታወቃል።ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓም ምሽት ነበር ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት።ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ከ፲፯ ዓመታት በፊት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእረ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አንብሮተ ዕድ የተሾሙ ነበሩ።ብፁዕነታቸው አስኬማ መላእክት ከሚለበስበት የኤጲስ ቆጶስነት ሹመት በፊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች ሲያገለግሉ እንደነበር ታሪካቸው ያስረዳል።ብፁዕነታቸው በሰሜን አሜሪካ በኒውዮርክ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በመንበረ ጵጵስና ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ከአገልጋይነት እስከ የበላይ ጠባቂነት በአባትነት አገልግለዋል።ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም ነበሩ። ### Response:
### Text: ቆም ብለን እናስብ️ ሰውን እንደሰው የሚያከብር ማህበረሰብ ካልተፈጠረ የኢትዮጵያ ችግር መቆሚያ ያለው አይመስለኝም። ዛሬ ለምንሰማቸው አሳዛኝ ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ብዙ የሚጠየቁ አካላት ቢኖሩም ዛሬ ያለነው በተለይም ፊደል ቆጥረናል የምንል ሰዎች ስለሰውነት ብዙ መጮኸ አለብን በምንችለው ቋንቋ ሁሉ ሰው ክቡር መሆኑን ላገኘነው ሰው ሁሉ እንናገር።የኢትዮጵያ ችግር ዴሞክራሲ እና ነፃነት ብቻ አይመስለኝም። ሌሎች መሰረታዊ ችግሮች አሉብን እውነተኛ ዴሞክራሲ እንኳን ቢመጣ እንጠቀምበት ይሆን የሚለውም ነገር ያሳስበኛል።የሀይማኖት አባቶች፣ መምህራን፣ አርቲስቶች፣ጋዜጠኞች፣ በተለይ በሀገር ውስጥም በውጭም ያላችሁ አክቲቪስት ነን የምትሉ ሰዎች ሌት ተቀን ለሰው መከበር ልትሰሩ ይገባል ሌላው ቀስ ብሎ ይደርሳል። ሰው እንደሰውነቱ ባልተከበረበት ሀገር ስለምንም ነገር ማውራት አይቻልምና።ለሰው ክብር የሌለው ግለሰብ፣ ቤተሰብ እንዲሁም ማህበረሰብ የሚፈጠር ከሆነ የዚህች ሀገር እጣፋንታ መጥፎ ሊሆን ይችላል።የ ቤተሰቦቻ አሁን ባለነበት ቦታ ሆነን የሰው ፍጡር ምን ያህል ክብር እንዳለው እንነጋገር፣ እንወያይ። በየሀይማኖቶቻችን እና ባለንም እውቀት ለትንንሽ እህት ወንድሞቻችን ስለሰውነት እናስተምራቸው።ሰው ይከበር ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ አየር መንገድ የወደብአየር የጭነት አገልግሎት ጀምሯል።የጅቡቲ ዓለም አቀፍ ነጻ የንግድ ቀጠና አካል በሆነው የጅቡቲ ወደብ የሚተላለፍና የኤሌክትሮኒክስና የቤት ውስጥ መገልገያ እቃዎችን የያዘው 17 ቶን የሚመዝን የመጀመሪያ የወደብአየር ጭነት አገልግሎት ጥቅምት 18 ቀን 2014 ዓም የኢትዮጵያና ጅቡቲ ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል። ጭነቱ ከሸንዘን ቻይና በመነሳት በጅቡቲ ወደብ አልፎ ሌጎስና ካኑ ይራገፋል ተብሎ ይጠበቃል።የወደብአየር የጭነት አገልግሎቱን ስራ ያስጀመሩት የጅቡቲ ወደቦችና ነጻ የንግድ ቀጠና ሊቀመንበር፣ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ዲፕሎማት አቶ አቦበክር ኡመር፣ አቶ ቢኒያም ኤፍሬም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጅቡቲ ቅርንጫፍ ቢሮ ሀላፊ፣ እንዲሁም በአቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ናቸው። በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው የጭነት አገልግሎት አቅራቢ የኢትዮጵያ አየር መንገድና ጅቡቲ በጋራ የሚተገብሩት ይህ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር የአየር መንገዱን የጭነት አገልግሎት አቅም በሁለት እጥፍ የሚያሳድግ ሲሆን፣ ጅቡቲን የወደብአየር ጭነት አገልግሎት ሎጂስቲክስ ማእከል ያደርጋታል ተብሎ ይጠበቃል። መረጃው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው። ### Response:
### Text: ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር በተያያዘ በርካታ ጉዳዮች እየተነሱ እንደሆነ ይታወቃል።የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትም ጉዳዩ በዛው ዕለት አልያም በቀጣዩ ቀን የሚመለከታቸው አካላት በመነጋገር በፍጥነትይፈቱታል በሚል በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ቀናት አልፎ አሁን ላይ ምዕመኑ ሰልፍ እስኪወጣ አስገድዶታል።ዛሬ ምዕመኑ በአንዳንድ መስጂዶች በሰልፍ ድምፁን አሰምቷል።የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሆን ተብሎ በሚመስልና በዘመቻ መልኩ የረመዳን ፆም ወቅትን ጠብቆና አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ፈተና በሚፈተኑበት ጊዜ ጭምር ትምህርት ቤት ውስጥም አትሰግዱም ወጥታችሁም ከግቢ አትሰግዱም ብለዋቸዋል ሲል ይገልጻል።አንዳንድ የትምህርት ቤት አስተዳደሮችም ተማሪዎቹን ኢህገመንግስታዊ የሆነ ተንኳሽ ንግግር ተናግረዋቸዋል ብሏል።የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምንም እንኳን ስለጉዳዩ በግልፅ ያለው ነገር ባይኖርም ትምህርት ከማንኛውም ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴ ነጻ በሆነ ሁኔታ መካሄድ አለበት ሲል አሳውቋል።ዛሬ የነበረውን የተቃውሞ ሰልፍ እንዲሁም አጠቃላይ ከሰሞኑ የነበሩትን ሁኔታዎች በሚመለከት ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በዝርዝር ቀርቧል ያንብቡ 0408 ### Response:
### Text: አቃቤ ሕግ የቀድሞ የሜቴክ የስራ ሀላፊዎች በነበሩት ሻለቃ ክንደያግርማይና ሌተናል ኮሎኔል አሰፋዮሐንስ ላይ ክስ መሰረተ። በዚሁ መዝገብ ስር0 በዋና ወንጀል አድራጊነት ተጠርጥረው የተከሰሱት ብርጋዴል ጄነራል ጠና ቁርንዲ፣ሻለቃ ክንደያ ግርማይና ሌተናል ኮሎኔል አሰፋ ዮሐንስ ናቸው። በወንጀሉ ተባባሪነት ክስ የተመሰረተበት ቻይናዊ ሚስተር ዩሀን ዮን ደግሞ እስካሁን አልተያዘም። ተከሳሾቹ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘትና ለማስገኘት የኮርፖሬሽኑን የግዥ አፈፃፀምን ወደ ጎን በመተው ከጨረታ ውጭ ሌሎች የግዥ ዘዴዎችን በመጠቀም ግዥ በመፈፀም ነው። በዚህም ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ያለአግባብ ወጪ እንዲሆን ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተመልክቷል። ሌተናል ኮሎኔል አሰፋ ዮሐንስ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክ የፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ሃላፊ፣ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁርንዲ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የማርኬቲንግ ኃላፊና ሻለቃ ክንደያ ግርማይ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ ኃላፊ ነበሩ። የግራ ቀኝ ክርክሩን0 ያደመጠው ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች መቃወሚያቸውን ለጥር 29 ቀን 2011 ዓም አንዲያቀርቡ ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: የ2 ወር ደሞዝ አልተከፈላቸውም የአፍሪሄልዝ ቴሌቪዥን ሰራተኞች የ2 ወር ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ተናገሩ። አፍሪሄልዝ ቴሌቪዥን ትኩረቱን በጤና ነክ ጉዳዮች ላይ በማድረግ ነበር በቅርቡ ወደ ተመልካቾች መድረስ የጀመረው።ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት የዚህ ቴሌቪዥን ጣቢያው ሰራተኞች ለኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 እንደተናገሩት ድርጅቱ በወቅቱ የሰሩበትን ደመወዝ እየከፈላቸው እንዳልሆነ ገልጸዋል። ሰራተኞቹ እንዳሉትም በድርጅቱ ከተቀጠሩበት ወቅት አንስቶ ደመወዛቸው በወቅቱ ተከፍሏቸው አያውቅም።እንደ ሰራተኞቹ ገለጻ ከሆነ ለመጨረሻ ጊዜ ደመወዝ ከተከፈላቸውም 2 ወር አልፏቸዋል፣ ለድርጅቱ የበላይ ሃላፊዎች ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው ሲጠይቁ በቂና ተገቢ መልስ ካለመሰጠቱም በላይ ጥያቄውን የሚያነሱ ሰራተኞች ከስራ ይሰናበታሉ፣ካለፍላጎታቸው የዓመት እረፍት እንዲወጡ ይደረጋሉ። የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሜሎን ሰራተኞቹ ያነሱት ቅሬታ ትክክል አለመሆኑንና ድርጅታቸው ለሰራተኞቹ የሰሩበትን ደመወዝ በወቅቱ እየከፈለ መሆኑን ተናግረዋል። በድርጅቱ ሰራተኞች ላይ የተፈጸመ የህግ ስህተት የለም የሰሩበት ክፍያም ተፈጽሟል ዝቅተኛ የስራ አፈጻጸም ያሳዩ ሰራተኞችን ብቻ ከስራ አሰናብተናል ሲሉ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ### Response:
### Text: «የሽብርተኞቹን ጭንቅላት ማፍረሳችንን እንቀጥላለን» የቱርክ ፕሬዝዳንት ረቺብ ጣይብ ኤርዶኻን የኩርድ ታጣቂዎች በአሜሪካ አሸማጋይነት ተግባራዊ የሆነው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ከማብቃቱ በፊት ከሰሜን ምሥራቅ የሶርያ ክፍል ለቀው ካልወጡ «ጭንቅላታቸውን እንደሚያፈርሱ» ዛቱ። ፕሬዝዳንቱ በማዕከላዊ ቱርክ በምትገኘው የካይሴሪ ከተማ ለደጋፊዎቻቸው ባደረጉት ንግግር ለ120 ሰዓታት የሚዘልቀው የተኩስ አቁም ስምምነት ተጨባጭ ለውጥ ካላመጣ አገራቸው የሶርያ ዘመቻዋን ትቀጥላለች ብለዋል። ከደጋፊዎቻቸው ፊት ቆመው ወታደራዊ ሰላምታ ሲሰጡ የታዩት ኤርዶኻን የተኩስ አቁም ስምምነቱ ካልዘለቀ «የሽብርተኞቹን ጭንቅላት ማፍረሳችንን እንቀጥላለን» ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንቱ እንዲህ አይነት ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ የዛሬው ሁለተኛቸው ነው። ለአምስት ቀናት በሚዘልቀው የተኩስ አቁም ስምምነት የኩርድ ታጣቂዎች ከተወሰኑ አካባቢዎች ለቀው እንዲወጡ ቱርክ ትሻለች። ይሁንና በዛሬው ዕለት ሁለቱም ወገኖች የተኩስ አቁሙ ተጥሷል ሲሉ ተወነጃጅለዋል። ቱርክ በኩርዶች የሚመራው እና የሶርያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ተብሎ የሚጠራው ኃይል አገሪቱ ከሶርያ ከምትዋሰንበት 444 ኪሎ ሜትር የድንበር አካባቢ 32 ኪሎ ሜትር እንዲርቁ ትሻለች። ### Response:
### Text: የተመድ ፀጥታው ምቤት ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በህዳሴ ግድብ ላይ ሶስቱ አገራት ወደ ውይይት እንዲመለሱ ከማድረግ ውጪ ሌላ መፍትሔ እንደሌለ ገልጿል።በሐምሌ ወር የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት በተባበሩት መንግሥታት የፈረንሳይ አምባሳደር የሆኑት ኖኮላስ ደ ሪቪዬር ትላንት ለጋዜጠኞች ገለፃ አድርገዋል።በመንግስታቱ ድርጅት የፈረንሳይ አምባሳደር የሆኑት ኒኮላስ ደ ሪቬሪ በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን በህዳሴ ግድቡ ላይ የገጠማቸውን አለመግባባት በውይይት እንዲፈቱ ከማድረግ ውጪ ሌላ መፍትሄ እንደሌለ ገልጸዋል።አምባሳደሩ አክለው ምክር ቤቱ ሶስቱ አገራት ልዩነቶቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ ከማግባባት ባለፈ ሌላ የሚያደርገው ነገር አለ ብዬ አላስብም ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።የፀጥታው ምክር ቤት በግድብ ዙሪያ በሚቀጥለው ሳምንት ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።ምክር ቤቱ በግድቡ ዙሪያ ጣልቃ እንዲገባ ሱዳን ፣ ግብጽ እና የአረብ ሊግ መጠየቃቸው ይታወሳል።ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በሶስቱ አገራት ዘንድ ያለው ልዩነት አፍሪካ ህብረት መር በሆነ ውይይት ብቻ ነው የሚፈታው ስትል ደጋግማ ማስታወቋ የሚታወስ ነው፡።መረጃው የሮይተርስአልዓይን ነው።የተስተካከለ ### Response:
### Text: በርካቶችን ያስቆጣው ድርጊት ከትላንት ምሽት ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አንዲት ሴት በፖሊስ ስትመታ የሚያሳይ ቪድዮ በስፋት እየተሰራጨ ነው።ድርጊቱ የተፈፀመው አዲስ አበባ ከተማ ጀሞ አካባቢ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርብ ነን ያሉ ግለሰቦች ያሳወቁ ሲሆን ድብደባው የተፈፀመው ከህፃን ልጅ ፊት ለፊት መሆኑም አስረድተዋል።የትኛውም የህግ አካል አንድ ዜጋ ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ እንኳን በተገቢው ስነስርዓት ወደህግ ማቅረብ እንጂ ከልካይ የለኝም ብሎ በአደባባይ እንዲህ ያለውን ድርጊት ሲፈፅም መመልከት እጅግ አደገኛና አሳዛኝ መሆኑንና እንዲህ የሚያደርጉ አካላትን ለሌላው አስተማሪ በሆነ መንገድ ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባ ድርጊቱን አጥብቀው የኮነኑ የቲክቫህ አባላት ገልፀዋል።ከዚህ ቀደምም እንዲህ ያለው ተመሳሳይ ድርጊት ተፈፅሞ እጅግ ከፍተኛ መነጋገሪያ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። ድርጊቱ ሁለት የፖሊስ አባላት አንድን ወጣት መሬት ላይ አስተኝተው ድብደባ ሲፈፅሙበት የሚያሳይ ነበር።ማንኛውም ሰው ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ በአግባቡ በህግ መዳኘትና ወደህግ ፊት ማቅረብ እየተቻለ ሰዎች ላይ በአደባባይ ድብደባ መፈፀም እጅግ የሚወገዝ ድርጊት ነው።ትላንት ስለተሰራጨው ቪድዮ እስካሁን ከፖሊስ በኩል የተሰጠ ማብራሪያ የለም። ### Response:
### Text: ዛሬ በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር የጣና ፎረም መካሄድ ጀምሯል።10ኛው የ ጣና ፎረም ጉባኤ በአፍሪካ የሰላም ፣ ጸጥታ እና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ የሚመክር ሲሆን እስከ ጥምቅት 6 ቀን 2015 ዓም ድረስ ይቆያል።በባህር ዳር እየተካሄደ ባለው የጣና ፎረም ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ እና ምክትል ጠሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ፣ የሶማሊያ ጠሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ ፣ የሱዳን የሉዓላዊ ምቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን እና ሌሎችም እየተካፈሉ ይገኛሉ።ጠሚ ዶክተር ዐቢይ የጣና ፎረም አፍሪካውያን መሪዎችን እና ባለ ድርሻ አካላትን በአሕጉራዊ የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ በማወያየት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለመቀየስ አልሞ ሚካሄድ ውይይት መሆኑን ገልፀው 10ኛው የጣና ፎረም በአፍሪካውያን ለአፍሪካውያን የሚጠቅሙ መፍትሔዎች የሚወጡበት ውጤታማ የውይይት ጊዜ እንደሚሆንልን እምነቴ ነው ብለዋል።በሌላ በኩል ጠሚ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን የሽግግር መንግስት ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ከሆኑት ሌተናል ጀነራል አል ቡርሃን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል ከዚህ በተጨማሪ ዓባይ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ያለውን ግዙፍ የድልድይ0ግንባታ ስራ ጎብኝተዋል።ፎቶ የጠሚ ፅቤት ### Response:
### Text: ሻሸመኔ️በሻሸመኔ ከተማ ተፈፅሟል የተባለው ድርጊት ከወር በፊት በእርቅ የተፈታ ጉዳይ ነው፡ የከተማ አስተዳደሩበኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ ከተማ የተፈፀመ ድርጊት በሚል የተለቀቀው አሰቃቂ ቪዲዮ ብዙዎችን በማህብራዊ ሚዲያ እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ሆኗል፡፡ኢቢሲ ወደ ሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ደውሎ በማህበራዊ የትስስር ገፆች ላይ ስለተለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል ለማጣራት እንደሞከረው፣ ድርጊቱ የተፈፀመው በከተማዋ ይሁን እንጂ ከአንድ ወር ከ11 ቀን በፊት የተፈፀመ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ኮሙዪኒኬሽን ኃላፊው አቶ ሀሮን ከድር ለኢቢሲ እንደገለፁት ጉዳዩ ህዳር 6፣2011 በእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል የተፈመ ፀብ ነበር፡፡ፀቡን ተከትሎም ጉዳት በደረሰባቸው እና ድርጊቱን በፈፀሙት ወገኖች መካከል የፀጥታ አካላት፣የከተማው ከንቲባና የአገር ሽማግሌዎች በተገኙበት እርቀ ሰላም ከተፈፀመ ውሎ ማደሩንና ጉዳዩ አሁን ላይ በቪዲዮ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ መለቀቁ የከተማዋን ገፅታ ሆን ብሎ ለማጠልሸት የታለመ መሆኑን አቶ ሀሮን ተናግረዋል፡፡በሻሸመኔ ከተማ አሁን ላይ ምንም አይነት የተፈጠረ ችግር የለም ከተማዋም የተረጋጋ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እየተከናወነባት መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: ታሪካዊቷ የላሊበላ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ፋኖ በቁጥጥር ስር መዋሏን የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አሳውቋል።የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት የጋሸናን ግንባር ምሽጎችን በመሰባበር የአሸባሪውን አከርካሪ የሰበሩት የመከላከያ ሠራዊት ፣ የአማራ ልዩ ኃይል ፣ የአማራ ሚሊሻና ፋኖ ታሪካዊቷን የላስታ ላሊበላ ከተማንና የላሊበላ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ተቆጣጥረዋል ብሏል።በአሁን ሰዓት የመከላከያ ሠራዊት ፣ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ፣ ሚሊሻ እና ፋኖ የላስታ ላሊበላን አካባቢ በማጽዳት የሰቆጣ ከተማን ለመቆጣጠር ወደፊት እየገሠገሡ ነው ሲልም አሳውቋል።ዛሬ ጥዋት የመንግስት ኮሚኒኬሽን በሰጠው መግለጫ በጋሸና ግንባር ጋሸና ፣አርቢት፣ አቀት እና ዳቦ በወረኢሉ ግንባር ጃማ ደጎሎ ፣ ወረኢሉ፣ ገነቴ፣ ፍንጮፍቱ እና አቀስታ በሸዋ ግንባር መዘዞ ፣ ሞላሌ ፣ሸዋሮቢትና አካባቢው፣ ራሳና አካባቢው የኢትዮጵያ ጦር መቆጣጠሩን ማሳወቁ ይታወሳል።እንዲሁም በምስራቅ ግንባር በኩል ነፃ በሆኑ አካባቢዎች የአካባቢው አስተዳደር ወደ ቦታው መመለሱ መገለፁ አይዘነጋም። የአካባቢው አስተዳዳሪዎች የተመለሱባቸው ካሳጊታ ቡርቃ ዋኢማ ጭፍራ ጪፍቱ ድሬሮቃ አለሌ ሱሉላ ናቸው። ### Response:
### Text: ከአርባ ምንጭ️ጋሞ ባይራኮጋሞይ ጊታኮዛሬ በተካሄደው የጋሞ ህዝብና የኦሮሞ ህዝብ ምክክርና ይፋ የምስጋና ፕሮግራም ላይ በርካታ የጋሞ ናቶዎችና በርካታ የኦሮሞ ቄሮዎች ተገኝተዋል።ከዛ ባሻገርም የጋሞ ወጋ አባቶች የኦሮሞ አባገዳዎች እርስ በእርስ ለእርቅ ድርድር ምቹ መንገድ ፈጥረዋል።በዛሬው ቀን ከተነሱ ሃሳቦች ውስጥ በቡራዩ በተነሳው እልቂት ቄሮ እጁ እንደሌለበት እናውቃለን ነገር ግን ቄሮ ይህንን የወንብዴ ግሩፕ ለማስቆም እንዴት ተሳነው የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል።በተጨማሪም በቀጣይ ቄሮና የኦሮሚያ መንግስት ለዚህ ጨዋ እና ይቅር ባይ ህዝብ ምን ዋስትና ይሰጣል የሚል ጥያቄም ተነስቶ ነበር። ቡራዩ የሚገኙት የጋሞ ተወላጆች ከዚህ ቡኋላ አስተማማኝ ጥበቃ እንዲደረግላቸውም ተጠይቋል።ከአመስጋኞቹ በኩልም ቄሮን በመወከል ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን ከዚህ ቡኋላም የጋሞን ህዝብ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ በኦሮሚያ የሚገኙ የሌሎች ብሄረሰብ ህዝቦችን የመጠበቅ ግዴታ የኛ የቄሮና የክልሉ መሆኑን አስረድተዋል። ናቶንና የጋሞ ሽማግሌዎችንም አመስግነዋል። በመጨረሻም ከሁለቱም ወገን የሰላም ፎረም የተቋቋመ ሲሆን ከኦሮሞና ከጋሞ ወጣቶች አራት አራት ወጣች በሰላም ፎረሙ ላይ እንዲካተቱ ተደርጓል። ©ፋሪስ ንጉሴ ከአርባምንጭ ### Response:
### Text: ትግራይ ክልል️የቱርክ ባለሀብቶች በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን አደ ጉደም ከተማ በ750 ሚሊየን ዩሮ የኢንዱስትሪ ፓርክ ሊገነቡ ነው፡፡ባለሀብቶቹ የሚገነባውን ኢንዱስትሪ ፓርክ በተመለከተ ከከተማ አስተዳደርና የህብረተሰብ0 ክፍሎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ኢንዱስትሪ ፓርኩ በ500 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ወደ ስራ ሲገባ በዓለም ተወዳዳሪና አዲስ ቴክኖሎጂ ይጠቀማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡የሕንጣሎ ወጀራት ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ከለሌ ሓጋዜ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት እንዲችል የመሬት ርክክብና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ለሟሟላት መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡በውይይቱ የትግራይ ህዝብ እንግዳ ተቀባይና ስራ ወዳድ መሆኑ ባለሀብቶቹ0 አካባቢውን ለመምረጥ ምክንያት እንደሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ባለሀብቶቹ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለፀ ሲሆን አካባቢው ከፍተኛ የእርሻ መሬትና0 የሰው ሀይል ያለው መሆኑን ገለፀዋል፡፡ከዚህ ባለፈ ከተማዋ ለመቀለ ከተማ0 ያላት ቅርበት ባለሀብቶች0 ማዕዋለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ተመራጭ እንዳደረጋት ተነግሯል፡፡የኢንዱስትሪ ፓርኩ ግንባታ በመጪው መጋቢት ወር የሚጀመር ሲሆን በሁለት ዓመታት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: ከደምቢዶሎ ከጠፉት 17 ተማሪዎች፡ታግተዋል ከተባሉት ውስጥ 14ቱ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መሆናቸው 2 ተማሪዎች በግቢው ውስጥ መኖራቸው 2 ተማሪዎች ጎንደር እና ጎጃም ቤተሰቦቻቸው ጋር መመለሳቸው 10 ተማሪዎች በፍለጋ ላይ መሆናቸው የተቀሩት ስማቸው እየተጠቀሱ ያሉት ተማሪዎች ግን የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች አይደሉም ተብሏል፡፡ በግቢው ዉስጥ አሉ የተባሉት ሁለት ተማሪዎች ግን መኖራቸው የተረጋገጠው የመመገቢያ ካርዳቸው ባለፉት ቀናት በጥቅም ላይ መዋሉ ታይቶ ስለሆነ ተጨባጭ መሆኑ አጠያያቂ ነው የማጣራቱ ስራ ሂደት ላይ ቢሆንም፡፡ በወሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና በአቶ ንጉሱ ጥላሁን የተመራ የልዑካን ቡድን ከደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋር በስፍራው ውይይት እያካሄደ ነው፡፡ በስፍራው የሚገነኘው የኢቢሲ ሪፖርተር የመንግስት ቃል አቀባዩን አቶ ንጉሱ ጥላሁንን እና የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዝዳንት አነጋግሯቸዋል፡፡ አቶ ንጉሱ ከዚህ ቀደም ሌሎች 21 ሰዎች ታግተው መለቀቃቸውን በድጋሚ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡ ከተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት እየተሰጡ ያሉ የተዛቡ መረጃዎችንም በሂደት እያጠራን እንሄዳለን ብለዋል፡፡ የፍለጋውን ሂደት ዝርዝር መረጃዎች ግን ለተማሪዎቹ ደህንነት ሲባል ለጊዜው አንናገርም ብሏል መንግስት፡፡ኢቢሲ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ መቐለ ቅርንጫፍ በትግራይ ክልል ለሚገኙ 47 ጤና ተቋማት 18 ሚሊየን ብር የሚያወጣ0 የመደበኛ እና የጤና ፕሮግራም መድሀኒትና00 የህክምና ግብዓቶችን በቀጥታ በማድረስ ማሰራጨቱ ገለፀ።ቅርንጫፉ ለ21 ሆስፒታሎችና 26 ጤና ጣቢያዎች በቀጥታ ያሰራጨ ሲሆን ከእነዚህም መቐለ የሚገኙ 4 ሆስፒታሎች እና ሁሉም ጤና ጣቢያዎች፣ ለውቅሮ፣ ሀውዜን፣ ዓዲግራት፣ አክሱም ቅድስተ ማርያም፣ ኮረም፣ መኾኒና ሌሎች ሆስፒታሎች ይገኙበታል ።በሌላ በኩል በሰሜን እና በምዕራብ እንዲሁም በማዕከል ከሚገኙ በኤጀንሲው ቅርንጫፎች የመደበኛ እና የጤና ፕሮግራም መድሀኒት የህክምና ግብዓቶች ለሑመራ፣ አላማጣ እና ለሌሎች ጤና ተቋሟት እየተሰራጨ እንደሚገኝ ኤጀንሲው በፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።የመቐለ ቅርንጫፍ በአሁኑ ወቅት ከማዕከላዊ መጋዝን ከተላከው 71 ሚሊየን ብር ግምት ካላቸው መድሀኒትና የህክምና ግብዓቶችን ጨምሮ 350 ሚሊየን የሚሆን0 የመደበኛ እና የጤና ፕሮግራም መድሀኒትና የህክምና ግብዓቶች ክምችት አለው ብሏል።በቅርንጫፉ ከሚገኙ መድሀኒትና የህክምና ግብዓቶቹ ውስጥ ለእናቶች እና ህፃናት ጤና፣ ለስኳርና ደም ግፊት ህመምተኛች፣ ለፀረ ወባ፣ ለሳንባ ነቀርሳ እና ኤች አይቪ ኤድስን ለማከም የሚውሉ ናቸው። ### Response:
### Text: የይስማዕከ ባለቤት ነኝ ያለች ሴት በአዲስ አድማስ ቀርባ የተናገረችው ነገር አስደንጋጭ ሆኖብኛል።ከዳነ በኋላ አብሬው ኖሬያለሁ በደንብ ያወራል እንደሚናገር በጣም ሠላም እንደሆነ አብረውት ያሉ የእርዳታ አስተባባሪ ኮሚቴ ነን የሚሉት ታዋቂ አርቲስቶች እና ጓደኞቹ በደንብ ያውቃሉ አካውንቱ ውስት 400 ሺ ብር መግባቱን አረጋግጫለሁ ህዝቡ እየትጨበረበረ ነው።አራት ኪሎ ባሻ ወልዴ ነበር። ከእነቤት እቃው የኔንም የልጆቼንም ልብስ፣ የልጆች መኝታና መጫወቻ ሁሉ ሳይቀር የለም። ከዚያም እኔም የምሰራበት የምንተዳደርበት ማተሚያ ቤት ስሄድ ማሽኖቹን የት እንዳደረሳቸው አላውቅም። የማተሚያ ማሽኖቹ 13 እና 14 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጡ ባለሞያዎች ነግረውኛል። እንዲህ ከሆነ አሁን ሶስት ወር ሊሆነን ነው ለልጆቹ ቀለብ የለ፣ አይጠይቃቸው፣ የት እንዳለ አይታወቅ፣ ራሱን ሰውሯል። ነገር ግን በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በሰይፉ ሾው ቀርቦ መናገር አልችልም ሲል ስሰማ ማመን ነው ያቃተኝ።ሙሉውን ቃለመጠይቅ በቀጣይ ይዤ እመለሳለሁ። ለጊዜው ይህ ጉዳይ ከስር መሰረቱ ማጣራት ስላለብኝ እና ሀላፊነቴም ስለሆነ 4 ኪሎ ባሻ ወልዴ ችሎት የምትኖሩ እባካችሁ ብዚህ ስልክ ደውሉልኝ 0919 74 36 30 ወይም በተለመደው የቴሌግራም አድራሻዬ መልዕክት አኑሩልኝ። ### Response:
### Text: አብዲ ኢሌ️የሶማሌ ክልል አዲሱ ፕሬዚዳንት አህመድ አብዲ መሀመድ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሀመድ ኦማር ስልጣን እንዳስረከቡና ሽግግሩም በሰላም እንደተጠናቀቀ ለቢቢሲ ሶማልኛ ተናግረዋል።የክልሉ አዲሱ ፕሬዚዳንት እንደተናገሩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ስልጣን ለመልቀቅ በመጠያቃቸው የስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አዲሱን የክልሉ ፕሬዚዳንት እንደመረጠም ገልፀዋል።ሰሞኑን ለብዙ ሰዎች መሞት፣ አብያተ ክርስትያናት መቃጠልና ንብረት መውደም ጋር ተያይዞም በክልሉ የመከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን በክልሉ በነበረው አለመረጋጋትና ተቃውሞዎች ጋር ተያይዞም በማዕከላዊ መንግሥት ግፊት ምክንያት እንደወረዱ ብዙዎች አስተያታቸውን ቢሰጡም አዲሱ ፕሬዚዳንት ሲንከባለል የነበረ ጥያቄ እንደሆነ ያስረዳሉ።ስልጣን ለመልቀቅ ባለፈው አራት ዓመት ጥያቄ ቢያቀርቡም በፓርቲያቸው ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም ነበር። ብለዋል። በትናንትናው ዕለት ይህ ጥያቄ ተቀባይነት እንዳገኘም ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጂግጂጋ በሚገኘው ቤታቸው በሰላምና በጤና ቤታቸው ውስጥ እንደሚገኙ ተናግረው ምንም እንኳን የስራ አስፈፃሚነትን ስልጣን ቢያስረክቡም የፓርቲያቸው ሶህዴፖ ኃላፊ ሆነው ይቆያሉ ብለዋል።© ### Response:
### Text: ወንጀል ነክ መረጃ️ስልክ በመንጠቅ ሊያመልጥ የሞከረዉ ወንጀለኛ በእስራት ተቀጣ። ተከሳሽ ዛኪር ቢላል በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 665 1 ላይ የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፉ ስርቆት በመፈፀሙ ክስ ተመሰረቶበታል።ተከሳሹ መጋቢት 12 ቀን 2011 ዓም በግምት ከምሽቱ 12፡30 ሰዓት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው 05 ቀበሌ እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ የግል ንብረትነቱ የተበዳይ ባህርያ ፈይድ የሆነ የዋጋ ግምቱ 1500 የሚያወጣ ሳምሰንግ ሞባይል ከተሳፈረችብት ታክሲ ውስጥ እሷ ከታክሲ ወርዳ እስከምትይዘኝ በሩጫ አመልጣለሁ በሚል እሳቤ በመኪና መስኮት እጁን በማስገባት እና በመንጠቅ ሊያመልጥ ሲሞክር በአካባቢው በነበሩ ሰዎች የተያዘ በመሆኑ በዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል።የፌደራሉ መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት ተከሳሽ የተመሰረተበትን ክስ እንዲከላከል ጥያቄ ያቀረበለት ሲሆን ተከሳሽ በተመሰረተብኝ ክስ ጥፋተኛ ነኝ ድርጊቱን ፈጽሜያለሁ በማለት የእምነት ክህደት ቃሉን የሰጠ በመሆኑ ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ህግን ዝርዝር ማስረጃዎች በመስማትና ተከሳሹ በሰጠው የእምነት ክህደት ቃል መሠረት ተከሳሽ ጥፋተኛ ሆኖ በማገኘቱ በ1 ዓመት ከ8 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ### Response:
### Text: ሞጆ ጥቅምት 172012 ዓም ዛሬ ጠዋት በሞጆ ከተማ በተከሰተ ሁከት ሁለት ሰዎች በጥይት ተመተዋል። በከተማዋ ዛሬ ጠዋት የታሰሩ ሰዎች ከእስር ይለቀቁ በማለት ሰልፍ የወጡ ሰዎች ከመንግሥት ጸጥታ አስከባሪዎች ጋር ተጋጭተው በሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የከተማው ከንቲባ ወሮ መሰረት አሰፋ ለቢቢሲ ተናግረዋል።ቅዳሜ ሌሊት ላይም በከተማዋ በምሽት ሰልፍ ተካሂዶ እንደነበር ከንቲባዋ ተናግረዋል። ቅዳሜ ሌሊት ቤተክርስቲያን ተቃጥለ የሚል ወሬ ተናፍሶ ሌሊቱን ሁከት ተፈጥሮ ነበር። በንብረት ላይ ጉዳት ደርሶ ነበር ብለዋል።ከንቲባዋ ጨምረው እንደተናገሩት ቅዳሜ ሌሊት ቤተክርስቲያን ተቃጥሏል እየተባለ የተናፈሰው ወሬ ሃሰት መሆኑን እና ይህ የተደረገው በከተማው ሆን ተብሎ ረብሻ ለመፍጠር ታስቦ መሆኑን ተናግረዋል።በተመሳሳይ መልኩ ዛሬም የታሰሩ ሰዎች ከእስር ይለቀቁ በማለት አደባባይ እንደወጡ እና ከጸጥታ አካላት ጋር እንደተጋጩ እንዲሁም በተከፈተው ተኩስ ሁለት ሰዎች መጎዳታቸውን አስረድተዋል። እስካሁን የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ የሞከሩ 9 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የተናገሩት ከንቲባዋ ዛሬ ተከስቶ የነበረው ሁከት በቁጥጥር ሥር ውሎ በከተማዋ አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን ጨምረው ተናግረዋል።ምንጭ አማርኛው አገልግሎት ### Response:
### Text: የቻይና ጤና ባለሙያዎች በሰሜን ምሥራቅ የአገሪቷ ክፍል የተገኘው የኮቪድ19 ታማሚ ወረርሽኙ በዉሃን ሲጀምር ከታየው በተለየ መልኩ የበሽታ ምልክትና ምልክቱ ለመታየት ረዘም ያለ ጊዜ መውሰዱን መታዘባቸውን ተናገሩ።በቻይና ብሔራዊ ጤና ኮሚሽን የህክምና ቡድን ከሚገኙ የጽኑ ህሙማን ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት ዶክተር ኪው ሃይቦ ለብሔራዊው ቴሌቪዥን ቡድኑ ስለታዘበው አዲስ ነገር ተናግረዋል።ዶር ኪው ቡድናቸው በሰሜን ምሥራቅ ሄሎንግጂያንግና ጂሊን ግዛት በኮቪድ19 ታማሚዎች ላይ ያልተለመደ ምልክት ማየታቸውንና ምልክቱን ለማየትም ረዥም ጊዜ መውሰዱን ተመልክተዋል።ታማሚዎቹ ትኩሳት የላቸውም ነገር ግን የጉሮሮ መከርከር ህመም አሊያም በድካም ይሰቃያሉ። አንዳንዶቹ እንዲያውም ምንም ዓይነት የበሽታው ምልክት የላቸውም ብለዋል ዶር ኪው። አክለውም ታማሚዎቹ ቫይረሱን ረዘም ላለ ጊዜ ተሸክመው እንደቆዩ አስረድተዋል።ግሎባል ታይምስ ጋዜጣ በዉሃን አንድ ታማሚ የበሽታውን ምልክቶች ካሳየ በኋላ በሳምንት ግፋ ሲልም በሁለት ሳምንት ከቫይረሱ ነጻ ይሆናል።ይሁን እንጂ አዲሱ ምልከታ ምንም እንኳን ኮሮና ቫይረስ የሚድን በሽታ ቢሆንም ሰዎች ቫይረሱን ተሸክመው ለረዥም ጊዜ ሊቆዩ እንደሚችሉ የሚያሳይ ነው ተብሏል። ### Response:
### Text: 6 ፓርቲዎች ወደሀገር ውስጥ ገቡ️ስድስት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወደ ሀገር ውስጥ ገቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አህመድ ለተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረጉት በሰላማዊ መንገድ የመታገል ጥሪ መሰረት ስድስት የተፎካካሪ ፓርቲ ወደ ሃገር ውስጥ ገብተዋል፡፡ ከውጭ ሃገር ከሰሜን አሜሪካና ከእንግሊዝ ስድስት ድርጅቶች በዛሬው ዕለት ወደ ሃገር ውስጥ ተጠቃለው መግባታቸው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ ተናግረዋል፡፡ አክለውም ከውጭ ሃገር ከሰሜን አሜሪካና ከእንግሊዝ ስድስት ድርጅቶች በመሆን እንዲሁም ከሃገር ውስጥ አንድ ሃገር አቀፍና አንድ ክልል አቀፍ ፓርቲዎች በመሆን እስከ ውህደት የሚደርስ አብሮ ተባብሮ ለመስራት የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ህዳር 15 ቀን 2011 ዓም መፈራረማቸውን ገልጸዋል፡፡ውህደት ለመፈጸም የተፈራረሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚከተሉት ቀርበዋል፡፡መድህን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ፣ ቱሳ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ፣ኢትዮጵያ ህዝባዊ ንቅናቄ ፣ብሩህ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፣ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤት እና ደቡብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኮኮብ ቅንጅት ወደ ሃገር ውስጥ መግባታቸውን አስተባባሪው አቶ ተሻለ ሰብሮ ገልጸዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴርሪፖርተር ጋዜጣ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በአሁኑ ወቅት ህክምና የመስጠት አቅሙ የመጨረሻ ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑ የቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሪፌራል ሆስፒታል በኮሮና ቫይረስ ለተያዙ ሰዎች ብቻ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ በመወሰኑ ሆስፒታሉ ነባር ታካሚዎችን ወደ ሌሎች የህክምና ማዕከላት ለማዛዋወር ዝግጁ ሆኗል ብሎ ያወጣው ዘገባ ሀሰት ነው። በአሁኑ ሰዓት በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ለኮሮና ቫይረስ ታማሚዎች ተብሎ የተዘጋጀው አልጋ ጋዜጣው እንዳለው 109 ሳይሆን 600 ነው። በሌላ በኩል በአሁኑ ሰአት በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው የምገኙት ህሙማን 69 ብቻ ናቸው። ይህ ደግሞ በአጠቃላይ ከተዘጋጀው 600 አልጋ ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት ከሚችለው 115 ብቻ ነው። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ምንም እንኳን በተወሰነ መልኩ ለዚሁ አገልግሎት አመቺነቱ ታይቶ በተለየ ህንጻ ላይ የኮቭድ 19 ህሙማንን ለመቀባል ዝግጅት እያደረገ ቢሆንም ሆስፒታሉ መደበኛ የህክምና አገልግሎትን በነበረበት አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። በዚሁ መሰረት የሪፖርተር ጋዜጣ ያወጣውን የተሳሳተ ዘገባ እንድያስተካክል የተነገረው ስሆን በረቡዕ እትሙ አስተካክሎ እንደሚያወጣ ቃል ገብተዋል።የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ### Response:
### Text: የዜጎች መረጃን የማግኘት መብት እስከምን ድረስ ነው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት ረፕሮፌሰር ዶር ሙላቱ አለማየሁ ለሀገራዊ ደኅንነት ከሚያሰጉና በልዩነት ከሚቀመጡት ውጪ ያለ ማንኛውም መረጃ የህዝብ መረጃ ነው ተብሎ ይታሰባል። ይህ ሕግ ከላይ ከተጠቀሱት ውስን ገደቦች ውጭ ማንኛውም ሰው መረጃ ጠይቆ የማግኘት መብትን ያጎናጽፋል። ለምሳሌ አንድ ግለሰብ የህተምክር ቤት የተወያዩበትን ቃለ ጉባዔ አሳዩኝ ብሎ የመጠየቅ መብት ጭምር አለው። ይህ በግለሰብ ደረጃ መተግበር የሚገባው ሕግ ለሚዲያዎች እንኳን ተፈጻሚ አይሆንም። ◾️ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ የመረጃ መዛባት አንደኛው መንስዔ የመረጃ እጦት ነው።መረጃ አሰጣጡ ተቋማዊ ቅርጽ አለመያዙና በግለሰቦችና በኃላፊዎች ፈቃድ መወሰኑ የመረጃ ነጻነትን የሚጋፋ ጉዳይ ሆኗል። ለዚህም መረጃ በመስጠት የሚሞገስ መረጃ ባለመስጠት የሚወቀስበት ዘመን መምጣት አለበት።መረጃ ከልካዮች ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚያደርጉት ይመስላቸዋል። የመንግሥት ተቋማት የህዝብ ሀብትን መሰረት አድርገው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው ይህንን በግልጽና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ ለህብረተሰቡ ማቅረብ በሕግ ይገደዳሉ ያንብቡ 0506 ### Response:
### Text: የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምቤት በአሸባሪነት የሰየመውን ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሕወሓት የሽብርተኝነት ስያሜ ይነሳ አይነሳ በሚለው ጉዳይ ላይ ዛሬ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።በምክር ቤቱ ውስጥ የብልፅና አባላት ሕወሓትን ከአሸባሪነት ለመሰረዝ ያለመ ዝግ ስብሰባ ትናንት መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓም የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔን ጨምሮ፣ የፍትህ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ዶር፣ እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በተገኙበት ሲያካሂድ እንደዋለና በውይይቱም በርካታ መግባባት ያላስቻሉ ጠንካራ ሐሳቦች መሰንዘራቸውን ጋዜጣው ከምንጮቼ0 ሰምቻለሁ ብሏል።ይሁን እንጂ በፓርላማው የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲን የ2014 በጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት ላይ ለመምከር ለመጋቢት 13 ቀን 2015 ዓም ለጠዋት ጠርቶት የነበረውን ስብሰባ ወደ ከሰዓት በማጠፍ፣ በዚሁ ቀን ጠዋት አስቸኳይ ስብሰባ ለፓርላማ አባለቱ መላኩ ተገልጿል፡፡ፓርላማው ሕወሓትንና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ድርጅት ወይም በመንግሥት ሸኔ 0 ተብሎ የሚጠራውን ታጣቂ ቡድን በአሸባሪነት የፈረጀው በሚያዚያ በ2013 ዓም ነበር፡፡ ሪፖርተርጋዜጣ ### Response: