text stringlengths 140 24k | summary stringlengths 13 164 |
|---|---|
ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደው ኢትዮትሬል የተራራ ላይ ሩጫ በሚቀጥለው እሁድ ነሀሴ ሶስት ቀን ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት እንደሚካሄድ የውድድሩ አዘጋጆች ባለፈው ሀሙስ በጉለሌ የእፅዋት ማእከል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። ለሁለተኛ ጊዜ በሚካሄደው ሩጫ ለመካፈል ከሁለት መቶ ስድስት በላይ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ዜጎች ለመሳተፍ የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ አርባ በመቶ የሚሆኑ ከውጭ አገር ዜጎች መሆናቸውን ገልፀዋል። በዋነኛነት ከስፔን፣ ጣልያን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጃፓን፣ ብራዚልና ቬኑዝዌላ ተወጣጥተው ከሚሳተፉት የውጭ አገር ዜጎች ስላሳ ሰባት በመቶ ሴቶች መሆናቸውም ተገልጿል። የዘንድሮ ሩጫ በአለም አቀፍ ለማስተዋወቅና ኢትዮጵያ በተራራ ሯጮች እይታ ውስጥ እንድትገባ ለማድረግ የሁለት ሺህ አምስት የአውሮፓና የስፔን አልትራ ትሬል ከፍተኛ የትሬል ውድድር አሸናፊ የሆነችው ቼሪ አድሪያን ካሮ በክብር እንግድነትና ተሳታፊነት እንደምትገኝ ተገልጿል። የአብጃታ ሻላ የተራራ ላይ ሩጫ በዋናነት የአካባቢን ደሀንነት በመጠበቅና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገቢ ምንጭ ለማስገኘት ታስቦ በአብጃታና ሻላ ሀይቆች ብሄራዊ ፓርክ የሚካሄድ ሲሆን፣ ሩጫው ሶስት የተለያዩ ርቀቶችን ማለትም አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር፣ ሀያ አንድ ኪሎ ሜትርና ኪሎ ሜትር የሚያካልል ነው። ማንኛውም ሰው በመሮጥ ወይም በእግር በመጓዝ በግራር የተከበቡትን የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች የሚያደንቅበትና ደስታን የሚሽምትበት እንደሚሆን አዘጋጆቹ አትሌት ገብረ እግዚአብሄር ገብረ ማርያምና አቶ ቃለ አብ ጌታነህ በጋራ በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል። የሁለተኛው ውድድር ለየት ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣንና የኦሮሚያ ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ በውድድሩ ዝግጅት የራሳቸውን ሚና መጫወታቸው ሲሆን፣ ይህም በአደጋ ውስጥ የሚገኙትን የስምጥ ሸለቆ ሀይቆችንና የዱር እንስሶችን ለመታደግ የህዝብ ንቅናቄን እንደሚፈጥር የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳውድ ሙሜ ገልፀዋል። በዚህ ውድድር ለአንድ መቶ ሀምሳ የአገር ውስጥ ተሳታፊዎች ቦታ የተያዘ ሲሆን፣ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በአካል በመቅረብ የውድድሩ አዘጋጅ በሆነው ሪያ ኢትዮጵያ ቢሮ መመዝገብ እንደሚችልም ተገልጿል። | ሁለተኛው ኢትዮትሬል የተራራ ላይ ሩጫ ሳምንት ይካሄዳል |
ሰኔ ፲፯ አስራ ሰባት ቀን ፳፻፭ አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ፎሬን ፖሊሲ መፅሄት በእያመቱ በሚያወጣው የወደቁ አገራት ሪፖርት ወይም በእንግሊዝኛው አጠራር ፌልድ ስቴትስ ኢንዴክስ ኢትዮጵያ እንደ አለፉት አመታት ሁሉ ዘንድሮው የወደቁ ወይም በመውደቅ ላይ ካሉ ሀያ አገራት መካከል አንዷ ሆና ተመድባለች። የህዝብ ቁጥር ፣ የስደተኛ ቁጥር፣ የህዝብ ብሶት፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት፣ ያልተመጣጠነ እድገት፣ የመንግስት ህጋዊነት፣ ማህበራዊ አገልግሎት፣ የደህንነት ጥበቃ፣ የሊህቃን መከፋፈልና የውጭ ጣልቃ ገብነት የሚሉት መስፈርቶች ተገምግዋል። በዚህም መሰረት ከአንድ እስከ ሀያ ያሉት አገራት ህልውናቸው አስተማማኝ ያልሆነ ከፍተኛ ችግር ያለባቸው ተብለው ተመድበዋል። ሶማሊያ ቀዳሚ የወደቀች አገር ስትባል፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቻድ፣ የመን፣ አፍጋኒስታን፣ ሀይቲ ፣ ሴንትራል አፍሪካ ፣ ዝምባብዌ፣ ኢራቅ ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ፓኪስታን፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ኬንያ፣ ኒጀር፣ ኢትዮጵያና ቡሩንዲ ተከታታዮችን ደረጃዎች ይዘዋል። ከሀያዎቹ አገራት የተሻሉ ተብለው በሁለተኛው ምድብ ውስጥ ከሚገኙት መካከል ደግሞ ሶሪያ፣ ዩጋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ኤርትራ፣ ማይናማር፣ ካሜሩን፣ ስሪ ላንካ፣ ባንግሊያዲሽ፣ ኔፓል፣ ሞሪታኒያ፣ ኢስት ቲሞር፣ ሴራ ሊዮን፣ ግብፅ ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ኮንጎ፣ ኢራን፣ ማሊ፣ ርዋንዳ እና ማላዊ ተመድበዋል። የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያ በተሻለ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ጥንካሬ ላይ እንደምትገኝ በተደጋጋሚ ሲናገር ይሰማል። ይሁን እንጅ የፎሬን ፖሊስ መረጃ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ ባለፉት ተከታታይ አመታት ይህ ነው የሚባል የደረጃ መሻሻል አልታየባትም። በዚህ አመትም ኤርትራ በአንፃራዊ መልኩ ከኢትዮጵያ በተሻለ ደህንነት ላይ እንደምትገኝ ሪፖርቱ ሲያሳይ፣ ኬንያ፣ ናይጀሪያና ሱዳን ደግሞ ከኢትዮጵያ አንሰው ተገኝተዋል። | በሁለት ሺህ አምስት አም ኢትዮጵያ ከወደቁ አገራት ምድብ ተመደበች |
ኢሳት ጥር ሀያ ሁለት ፥ ሁለት ሺህ ዘጠኝ ባለፈው ስድስት ወራቶች ብቻ በአዲስ አበባ ከተማ ሺ የንግድ ተቋማት የንግድ ፈቃዳቸውን በተለያዩ ችግሮች እንደመለሱ ተገለፀ። እነዚሁ በተለያዩ የንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርተ የነበሩ ድርጅቶች ህገወጥ ንግድ መበራከት፣ በከተማዋ እየተካሄደ ያለው የልማት እንቅስቃሴ ደካማ የንግድ ስርአት አንዲሁም የቤት ዋጋ ንረት ከገበያ እንዲወጡ ጫና እንዳደረሰባቸው ማስታወቃቸውን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በከተማዋ እየተስተዋሉ ያሉ እነዚህን ችግሮች ተከትሎ በየእለቱ ሰባ የሚሆኑ የንግድ ተቋማት የንግድ ስራ ፈቃዳቸውን ለአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ እየመለሱ መሆናቸው ተመልክቷል። የንግድ ድርጅቶቹ ፈቃዳቸውን ለመመለስ በመንግስት የግብር ገቢና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ሊያሳድር እንደሚችል ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት አስረድተዋል። በተለያዩ አካላት ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ያልተቀረጡ ሸቀጣሸቀጦች በንግድ ስራቸው ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን አቶ ኤርሚያስ ሀይሌ የተባሉ በኮሞፒውተር ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ለጋዜጣው ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተወካይ የሆኑት ምትኬ እንግዳ በበኩላቸው ቢሮው ህገወጥ ንግዱን ለመቆጣጠር የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ ቢቆይም ችግሩ ሊቀንስ እንዳልቻለ ተናገረዋል። ባለፈው አመት በተመሳሳይ ችግሮች ሀያ ስድስትሺ ስምንት መቶ ስልሳ የንግድ ተቋማት ፈቃዳቸውን መልሰው የነበረ ሲሆን፣ አሁን ባለው ሂደት ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል ተመልክቷል። የንግድ ፈቃዳቸውን እየመለሱ ያሉ የንግድ ድርጅቶች መንግስት ለችግሮቹ መፍትሄን እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ሁለት መቶ ስልሳ አንድሺ አራት መቶ አንድ የንግድ ድርጅቶች በተለያዩ ስራዎች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ታውቋል። | በአዲስ አበባ ሺ የንግድ ተቋማት የንግድ ፈቃዳቸውን በተለያዩ ችግሮች መለሱ |
ከዚሁ ጋር ተያይዞም እቃ አቅራቢው ገቢው ከአምስት መቶ ሺ ብር በላይ ቢሆንም እንኳን ታክሱን የመክፈል ግዴታ የሌለበት ሲሆን የካፊቴሪያ ወይም የምግብ ቤት አገልግሎት የሚሰጠው ሰው ግን ገቢው ከአምስት መቶ ሺ ብር በላይ ከሆነ ለታክሱ የመመዝገብ ግዴታ እና ታክሱን የመክፈል ሀላፊነት ይኖርበታል። ከላይ የቀረበው ድንጋጌ የተወሰደው ተጨማሪ እሴት ታክስ በኢትዮጵያ በሚል ርእስ በሳሙኤል ታደሰ ተዘጋጅቶ በግንቦት ወር ሁለት ሺህ አራት አመተ ምህረት ለአንባቢያን ከቀረበው መፅሀፍ ነው። የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ በወጣ አስረኛ አመት ዋዜማ ታትሞ የቀረበው መፅሀፍ፤ ባለፉት አመታት ህብረተሰቡ ግር ለተሰኘባቸው ብዥታዎች ማጥሪያ ሊሆኑ የሚችሉ ሰፋ ያሉ መረጃዎችን ይዟል። ከቫት ነፃ የሆኑት ዳቦ፣ እንጀራና ወተት የቫት ሰለባ የሚሆኑበት ምክንያት ምን እንደሆነ የቀረበው አንዱ ማሳያ ነው።በሁለት መቶ ሰማኒያ ስምንት ገፆች የቀረበው መፅሀፍ፤ ግብርና ታክስ በአለም ላይ ምን ታሪክ እንዳላቸው በማመልከት ነው ወደ ተነሳበት ርእሰ ጉዳይ የሚዘልቀው። ግብርና ታክስን ክፈል፤ አልከፍልም ሙግትና ትግል ከክርስቶስ ልደት በፊት በእስራኤላዊያን ዘንድ ይታይ እንደነበርና ንጉስ ሰለሞን ግብርን ከህዝቡ አስገድዶ ይቀበል እንደነበር ተገልጿል።ግብርና ታክስ አንዱ ሌላውን መወንጀያ፣ ማሳደጃ፣ መውቀሸያ የመሆኑ ታሪክም እጅግ ጥንታዊ እንደነበር፤ ከሳሾቹ ከቄሳር ጋር ሊያጣሉት ሲሞክሩ የቄሳርን ለቄሳር፣ የእግዜአብሄርን ለእግዚአብሄር ስጡ ብሎ በብልሀት ያሸነፈው የኢየሱስ ክርስቶስ ታሪክም ተጠቅሷል።በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሀብት ያለው ለሌለው የሚያካፍልበት ዘካ በመባል የሚታወቀው ሀይማኖታዊ ግዴታ፣ በተለይም እስልምናን እንደ መንግስት ሀይማኖት ተቀብለው የሚከተሉ አገራት ህግ አውጥተው ዘካን እንደ ግብር በግዴታ እንደሚሰበስቡ ፓኪስታንን በምሳሌነት አቅርቧል መፅሀፉ።በጥንታዊ ግብፅ፣ ግሪክ፣ ሮም ግብርና ታክስ የመሰብሰብ ሂደት ምን ይመስል እንደነበር የሚያስቃኘው የሳሙኤል ታደሰ መፅሀፍ፤ እንግሊዝና ፈረንሳይን ጦር ያማዘዘው የግብርና ታክስ ታሪካቸው ምን ይመስል እንደነበርም ያስቃኛል።በግብፅ፣ በግሪክ፣ በሮም እንደታየው ሁሉ በጥንታዊው የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥም በነበረው የንግድ እንቅስቃሴ ቀረጥ ይሰበሰብ ነበር። በ ኛው ክፍለ ዘመን በእንግሊዝ የታክስና ግብር ስርአት እድገት እንዳሳየው ሁሉ በኢትዮጵያም ከአንድ ሺህ አራት መቶ እስከ አንድ ሺህ አራት መቶ ሀያ ዘጠኝ አመተ ምህረት በአፄ ይስሀቅ ዘመነ መንግስት ሰላሳ ዘጠኝ ግዛቶች ለማእከላዊ መንግስት ግብር ይከፈሉ እንደነበር ምንጭ ጠቅሶ ገልጿል።ግብርና ታክስን በተመለከተ ከጥንታዊያኑ ግብፅ፣ ግሪክና ከሮም ጋር ትመደብ የነበረችውና በመካከለኛውም ዘመን ከእንግሊዝና ፈረንሳይ እኩል ትታይ የነበረው አገራችን በብዙ ዘርፎች እንደሚታየው ተከታታይና ቀጣይነት ያለው እድገት ሳታስመዘግብ ቀረች። ሆኖም በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት አመተ ምህረት የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን በማውጣት ጥለዋት የሄዱት አገራት ላይ ለመድረስ የሚያፈጥናትን አቋራጭ መንገድ የተከተለች ይመስላል።ስለ ተጨማሪ እሴት ታክስ የጥናት ፅሁፎች መቅረብ የጀመሩት እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀምሳዎቹ ነው የሚለው የሳሙኤል ታደሰ መፅሀፍ፤ ታክሱን የግብር ስርአቷ አድርጋ በመንቀሳቀስ ጀማሪዋ ፈረንሳይ ነበረች አ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት።በመቀጠል ኮትዲቭዋር፣ ሴኔጋል ተግባራዊ አደረጉት። እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ እና በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባዎቹ ብዙ የአለም አገራት እንደ ተቀበሉት የሚጠቁመው መፅሀፍ፤ በሀያኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ አመታት በአለማችን የታክስ ስርአቶች ውስጥ ከታዩ እድገቶች መካከል የተጨማሪ እሴት ታክስ እድገት ዋነኛው ነው ይላል።መንግስታት የተጨማሪ እሴት ታክስ ስርአትን እንዲከተሉ ያተጋቸው የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። የምእራብ አውሮፓ አገሮችና የደቡብ አሜሪካ አገሮች የተጨማሪ እሴት ታክስ ስርአትን የሚጠቁሙበት ምክንያትን የሚጠቁመው መፅሀፉ፤ ታዳጊ አገሮች የግብር ስርአቱን እንዲከተሉ ያስገደዳቸው ዋነኛው ምክንያት ከቀጥታ ታክስ የሚያገኙት ገቢ የሚያወላዳ ባለመሆኑ እንደሆነ ገልፃ፤ በአገራችንም በዚህ ዋነኛ አላማ አዋጁ እንደወጣ ተጠቅሷል። ከአርባ አመት በፊት በአለማችን በጥቂት አካባቢዎች ብቻ ይታወቅ የነበረው የተጨማሪ እሴት ታክስ፤ በአሁኑ ወቅት አራት ቢሊዮን የሚያህል ህዝብ ወይም ከአለማችን ህዝብ ሰባ በመቶ ያህሉ በሚገኝባቸው አገሮች ተግባራዊ ሆኖ ይገኛል የሚሉት የመፅሀፉ ደራሲ፤ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስት አመተ ምህረት በፌደራል አገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን በነገረ ፈጅነት ተቀጥረው ሲገቡ ጀምሮ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር በተያያዘ ብዙ ችግሮች መኖራቸው እንደተረዱ ይገልፃሉ። የታክስ ህግ በአንፃራዊነት ሲታይ ከሌሎች የህግ አይነቶች ሁሉ በውስብስብነቱ የታወቀ ነው። የዚህም ዋና ምክንያት ሆኖ የሚነሳው ደግሞ ህጉ የሌሎች በርካታ የማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች ማለትም የህግ፣ የኢኮኖሚክስ፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና የአካውንቲንግ ድምር ውጤት ሲሆን ህጉን በቀላሉ ለመረዳት በርካታ ባለሞያዎች ብዙ መስራት ወይም መፃፍ እንዳለባቸው ይታመናል። በዚህ ምክንያትና አላማ ተጨማሪ እሴት ታክስን ርእሰ ጉዳይ ያደረገ መፅሀፍ ያዘጋጁት ደራሲው፤ ስለ ታክስ ምንነት፣ አተገባበሩ በተለያዩ አገራት ምን እንደሚመስልና በአገራችን በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት አመተ ምህረት የወጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ ህግ ዋና ዋና ድንጋጌዎች ምን እንደሚመስሉ ምሳሌና ማሳያ እያቀረቡ ለማስረዳት ታትረዋል።የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ አስር አመት ገደማ ቢሆነውም አሁንም ድረስ በምንበላውና በምንጠጣው ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ መጣሉ አግባብ አይደለም የሚል ቅሬታ በስፋት ይደመጣል። ምግብ የቫት ሰለባ ሊሆን የቻለበት ምክንያት ምን እንደሆነ ህጋዊ ትርጉሙን በሙያዊ ትንታኔ አቅርበዋል ደራሲው።ለረጅም አመታት ልማዳዊ በሆነ መልኩ ሲሰራበት የቆየውን የግብርና ታክስ ስርአትን ለማሻሻል ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ ምህረት በኋላ አገሪቱ የተከተለችውን የኢኮኖሚ ስርአት መሰረት አድርጐ የወጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ በስራ ላይ ሲውል የታዩት ክፍተቶች በዘርፉ ላይ ብዙ ስራ መሰራት እንዳለበት ያመላከተ ነበር የሚሉት ፀሀፊው፤ ደራሲ በተለያዩ ጊዜያት በወጡ ህጐች ውስጥ የተፈጠረ ልዩነት፣ የታክስ ሰብሳቢ መስሪያ ቤቶች ድክመትና የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተጠያቂነት አናሳ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለማሳየት ሞክረዋል።የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ለአገራችን አዲስ እንደመሆኑ ከፍተኛ የሆነ መደናገርና ብዥታ በአስፈፃሚውና በፈፃሚው ወገን ላይ ይታያል ያሉት ደራሲው፤ የታክስ ስርአቱ አሁንም ብዙ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን የሚያመለክቱ ምሳሌና ትንታኔዎችን አቅርበዋል በመፅሀፉ ማጠቃለያ።ህዳር አንድ ቀን አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስት አመተ ምህረት በፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን በህግ ባለሙያነት ሲቀጠሩ መስሪያ ቤቱ ስልሳኛ አመቱን ያከበረ ቢሆንም በህግ ባለሙያነት ስራዬ ተግባራዊ ስለማደርጋቸው ህጐች የተፃፈ አንድ መፅሀፍ እንኳን አለመኖሩ ስልሳ አመት ስንት ነው የሚለውን ጥያቄ እንዳነሳ አስገድዶኛል የሚሉት የመፅሀፉ ደራሲ ሳሙኤል ታደሰ፤ በፌደራል አገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣንና በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ለስምንት አመት ካገለገሉ በኋላ በተጨማሪ እሴት ታክስ ዙሪያ መፅሀፍ አዘጋጅተው ማሳተማቸው ተቋማትን ብቻ ሳይሆን ግለሰቦችንም ለተመሳሳይ ስራ የሚያነሳሳ አርአያነት ያለው ታላቅ ተግባር ነው። መፅሀፉ ሀምሌ ቀን ሁለት ሺህ አራት አመተ ምህረት በአዲስ ቪው ሆቴል በተመረቀበት ምሽት በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ ተፈራ ዋልዋ ጡረታ የወጣሁት እረፍት ፈልጌ የነበረ ቢሆንም ወጣቶች በየመድረኩ እየጋበዙኝ ንግግር ማድረጌን ቀጥያለሁ። በመፅሀፍ ምረቃ ላይ ስገኝ ሁለተኛ ጊዜዬ ነው። ዛሬ ወደዚህ መድረክ እንድመጣ ምክንያት ከሆነኝ አንዱ ሳሙኤል ታደሰ መፅሀፍ ባዘጋጀበት ርእሰ ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ ስራዎች እንዲሰሩ አልሞ መፅሀፉን ማሳተሙን በመስማቴ ነው ብለዋል።ሌሎች ባለሙያዎችም ለደራሲውና ለመፅሀፉ ያላቸውን አድናቆት በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ ተናግረዋል። | ታክስ፤ የህግ፣ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የአካውንቲንግ እውቀትን ይጠይቃል |
ነሀሴ አስራ ሰባት ቀን አመተ ምህረትኢሳት ዜናበኢትዮጵያ የፕትርክና ታሪክ አወዛጋቢ የሆኑት ብፁወ ቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የመንግስት ባለስልጣናት እና ሌሎች ዲፐሎማቶች በተገኙበት ዛሬ በቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን የቀብራቸው ስነስርአት ተፈፅሟል።ከሀምሌ ቀን አመተ ምህረት ጀምሮ ኛ አመት በአለ ሲመታቸውን ሲያከብሩ የነበሩት አቡነ ጳውሎስ በድንገት ማረፋቸው የብዙዎች መነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ ነው። በተለይም የእርሳቸውን ሞት ተከትሎ የአቶ መለስ ዜናዊ ዜና እረፍት ይፋ መሆን ኢትዮጵያውያን ነገሩን ከሀይማኖት ጋር እንዲያያዙት ግድ ብሎአቸዋል።አቡነ ጳውሎስ በልማቱ ዙሪያና ኤች አይ ቪ ኤድስን በመከላከል ረገድ አወንታዊ ተግባራትን መፈፀማቸው ቢነገርም ጥንታዊቷን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ከሁለት በመክፈልና በማዳከም የገዢው ፓርቲ መሳሪያ በመሆን እና ከህዝብ ጎን ባለመቆም እንዲሁም ለአለማዊ ቅንጦት ከፍተኛ ቦታ በመስጠታቸው ይወቀሳሉ። በተለይም በቅርቡ የብጿን አባቶች መደብደብ እና ሀውልታቸውን በቁማቸው ማሰራታቸው ለከፍተኛ ትችት ዳርጓቸው እንደነበር ይታወሳል። | የብፁእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የቀብር ስነ ስርአት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈፀመ |
ብዙውን ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮትም ሆነ በጋዜጦችና መፅሄቶች የሚተላለፉና የሚወጡ ትዝብቶች ወይም አስተያየቶች በአብዛኛው በታዋቂ ግለሰቦች በምሁራን አለያም በፖለቲከኞች ይጣበባሉ። እንደ እኔ ያለው ጭቁን የገጠር መምህር ግን እንዲህ ያለው እድል ብዙም አይገጥመውና እንዲሁ እድሌን ልሞክር ብዬ ነው ይህን ፅሁፍ መላኬ። ለሚዲያ ቢሆን ብዬ ስፅፍም የመጀመሪያ ጊዜዬ ነው። እድሜ ለአበበ ቢቂላ ይሁንና ከእሱ ጊዜ ጀምሮ አትሌቶቻችን በመላው አለም ታውቀው አሳውቀውናል። አበበ ቢቂላ በአለም የውድድር መድረክ አሸንፎ ከመጣ በኋላ ስታዲየሙን እየዞረ የኢትዮጵያን ባንዲራ እያውለበለበ ሲዞር፣ በወቅቱ በስፍራው የነበረ አፍሪካዊ ስደተኛ ራሱን ደፍቶ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ደስ አለው። ጀግኖች አትሌቶቻችን የታመመንም ያድናሉ። ለዚህ ሁሉ መንደርደሪያዬ ሙያዊ ብቃታቸው የትየለሌ መሆኑ ነው። አንድ ፌደሬሽንን ቀርቶ አለም አቀፍ ተቋምን መምራት እንደሚችሉ የሚያሳየን አትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትነት እንደተመረጠ ወዲያውኑ ድጋፋቸውን በተለያዩ ድረ ገፆች፣ አለም አቀፍ መፅሄቶችና ጋዜጦች ሲገልፁ ማየታችን ነው። በአለም ጋዜጦችና ታዋቂ ድረ ገፆች መነጋገሪያ መሆንና መሞካሸት ከሙያ ብቃት የመጣ ነው። አትሌት ሀይሌ አለም አቀፍ ድጋፍ ማግኘቱ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ዱሮ ታዳጊ ልጆች እያለን ነፍሳቸውን ይማርና ጋሽ ይድነቃቸው ተሰማም በተለያዩ የአለም መድረኮች አገራችንን ከፍ ከፍ አድርገውን እንደነበር ይታወሰኛል። የሀይሌን መመረጥ የደገፍኩት በተለይ ህዝቡን የማገልገል ውስጣዊ ፍላጎትና ብቃቱን ሳስብ ነው። በጀግንነት ባሸነፋቸው መድረኮች የራሱን ደስታ ብቻ አይደለም ያየነው፤ አገር ወዳድነቱን ጭምር እንጂ። ከፊቱ ከሚነበበው ስሜት፣ በቄንጠኛ ሁኔታ ባንዲራውን እያውለበለበ በርከክ ማለቱ ብቻም ሳይሆን፣ የአገሪቱ ብሄራዊ መዝሙር ሲዘመርና ባንዲራዋ ሲሰቀል እንባውን ማፍሰሱ ተቆርቋሪነቱንና ወገንተኝነቱን የሚያሳይ ነው። ወደፊት ፌዴሬሽኑን ሲመራም በሀቀኝነት ሁሉንም እያሳተፈ ውጤታማ መሪ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም። ያለአግባብ ለመጠቀም ብሎ እንደማይሰራ አምናለሁ። የዋህ ባህርይ የተባበሰ ሰው ነውና ቢሳሳትም ከአቅም ወይም ከአመራር ልምድ ማነስ እንደሚሆን ይሰማኛል። ህዝብንና አብረውት የሚሰሩ ባልደረቦቹን አክባሪ፣ ምክር ጠያቂም እንደሆነም አውቃለሁ። የስፖርት ጋዜጠኞች ሙያዊ አስተያየትም ትምህርት ሰጭ እንደሆነ የሚቀበል ሰብእና ያለው ስለመሆኑ እንዴት አወቅህ ብትሉኝ፣ በቴሌቪዥን የሚደረጉ ውይይቶችን ስለምከታተል ነው። የገጠር አካባቢ መምህር ብሆንም እንዷቅሚቲ በማገኛቸው መረጃዎች አማካይነት ነገሮችን ለመመዘን ስለሞክር፣ ወደ መፃህፍት ጎራም ስለማዘወትር ለማገናዘብ የምችልበት እድል ሰጥተውኛል። ወደ ርእሰ ጉዳዬ ልመለስና ላለፉት ስድስት ወራት የስፖርት ዜና አንባቢዎች የህዝብን ድምፅ እየተከታተሉና ከራሳቸውም ስፖርታዊና ሙያ መርሀ በመነሳት ለሚመለከታቸው የአትሌቲክስ ዘርፍ ሀላፊዎች ለምን ወደ ኋላ እየተጓዝን እንደሆነ፣ ውጤታችን ለምን ከዱሮው እንደቀነሰ ወዘተ እየጠቃቀሱ ሲያነጋግሩ፣ ሹሞቹ ሲሰጡ የነበሩትን ምላሽ ለህዝብ ድምፅ ጆሮ አለመስጠት ይታይባቸው እንደነበር አስታውሳለሁ። ስፖርት እንደሆነ ወዳጅን ብቻ ሳይሆን የሚያገናኘውና የሚያፈቅረው በክፉ የሚፈላለገውንም ጭምር ነው። የእስራኤልና የፍልስጤም ሁለት ወጣቶችን የዛሬ አምስት አመት አፋቅሮ ለጋብቻ ያበቃቸው ስፖርታዊ ትእይት ነበር። የፖለቲካ ታማኝነት ብቻውን የትም እንደማያደርስና እንደማያዋጣ መገንዘብ ይገባል። ጋዜጠኞች በአለም ኦሊምፒክ መድረክ አንድ ወርቅ ብቻ ማግኘታችን ውድቀትን አያሳይም ወይ ብለው ሲጠይቋቸው፣ በተቃራኒው ውጤታማ ነን በማለት ድርቅ ማለታቸው የሚያስተዛዝብ ነው። ይህ እንግዲህ ሙያዊ ብቃት አስፈላጊነቱ ምን ያህል እንደሆነ ያሳያል። ባለስልጣኖቹም ጥፋታቸውን ማመን ይገባቸዋል። የህዝቡን ውጤት አጣን ጥያቄ ማስተናገድ ይገባቸዋል። ጋዜጠኞች ውጤት ያጣንበትን ምክንያት በማውሳት እርምት እንዲደረግ ብዙ ታግለዋል። ሆኖም ሹሞቹ ግን ድንግጥም የሚሉ አይነት ሆነው አልተገኙም ነበር። እነሱ አይሰሙም እንጂ መንግስት የምሁራንን ሚና ተረድቶ በፕሮፌሰሮችና በዶክተሮች የተሞላ ካቢኔ አቋቁሟል። ሻለቃ ሀይሌ ገብረ ስላሴና አዲሱ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ የወደፊቱን አትሌቲክስ ስፖርት በድል ጎዳና እያራመዱ፣ የጠፋውን ውጤት እንደሚያስመልሱ በማመን መልካም የስራ ዘመን እላለሁ። አደፍርስ፣ ከወሎ ሀይቅ የህንፃዎችን የፓርኪንግ ክፍያ ተመን የሚቆጣጠር አካል አለን ለተለያዩ ጉዳዮች መኪኖች በህንፃዎች ማቆሚያ ቦታዎች ወይም የፓርኪንግ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ስፍራዎች ማቆም ሊያስፈልገን ይችል ይሆናል። ያስፈልጋልም። ምንም እንኳ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ህንፃዎች ተገቢውን የመኪና ማቆሚያ ቦታ በመገንባት ረገድ የሚወቀሱ ቢሆኑም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብቅ እያሉ ያሉት ህንፃዎች እንዲህ ያለውን አገልግሎት የሚሰጡ የፓርኪንግ ቦታዎችን ማዘጋጀት ጀምረዋል። እሰየው ያስብላል። ይሁንና ግን ችግር ያለባቸውም አሉ። አገልግሎቱን ቢሰጡም ለሚሰጡት አገልግሎት የሚጠይቁት ክፍያና የሚከተሉት የክፍያ አጠያየቅ ስርአት አስገራሚም፣ አሳፋሪም ሆኖ ያገኘናቸው ህንፃዎች አሉ። ከሰሞኑ የገጠመኝም ከዚሁ ከፓርኪንግ ክፍያ ጋር የሚገናኝ ነው። ቦሌ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ የሚገኝ ዘመናዊና አዲስ ህንፃ ነው። የተሟላ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ቢኖረውም፣ ህንፃው የሚከተለው የክፍያ ስርአት ግን አግባብነት የጎደለው ይመስለኛል። ለአንድ ሰአት ቆይታ የሚያስከፍለው ገንዘብ ስምንት ብር መሆኑ ግራ አጋብቶኛል። በየመንገዱ ለምናቆምበት የምንጠየቀው ሀምሳ ሳንቲም ሆኖ ሳለ በዚህ ህንፃ ውስጥ ለአንድ ሰአይ ቆይታ ስምንት ብር መጠየቅ ከምን መነሻ እንደሆነ ግልፅ አይደለም። የሂሳቡ መጋነን ሳያንስ ወደ ማቆሚያ ቦታ ለሚገባው አሽከርካሪ ሂሳቡ አይነገረውም። ይህ ደግሞ ፈፅሞ ስነ ምግባር የሌለው ድርጊት ነው። በጥቅሉ ግን እንዲህ ያሉ ቅጥ ያጡ አሰራሮች እየተለመዱ ከሄዱ የኋላ ኋላ ነገሮችን ለማስተካከል አስቸጋሪ ያደርጋቸዋልና የሚመለከተው አካል ካለ እርምት ያድርግበት። ቢሻው ቢልልኝ፣ ከአዲስ አበባ | ለአትሌቲክስ ውጤታማነት አዲሱን አመራር ተስፋ እናደርጋለን |
በእንግሊዝ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ በጋምቤላ ክልል በተከናወነ አስገዳጅ የሰፈራ ፕሮግራም፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ደርሶብኝ፣ ለስደት ተዳርጊያለሁ ያሉ አንድ ኢትዮጵያዊ ገበሬ፤ በአገሪቱ ላይ የመሰረቱትን ክስ ያዳመጠው የለንደን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች ለሚጥሱ ፕሮግራሞች መዋል አለመዋላቸው እንዲጣራ መወሰኑን የኢትዮጵያ መንግስት ተቃወመ። ብሉምበርግ ኒውስ ከትናንት በስቲያ እንደዘገበው፣ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በተመለከተ ለንደን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በላከው መግለጫ፤ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ማስተላለፉ አግባብነት እንደሌለው ገልፆ፣ ክሱ የተመሰረተው ያለምንም ተጨባጭ መረጃና የራሳቸውን ፖለቲካዊ ጥቅም ለማስከበር በሚፈልጉ ሀይሎች አነሳሽነት እንደሆነ ገልጿል። በክልሉ የተከናወኑ የሰፈራ ፕሮግራሞች በነዋሪዎች ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረቱና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በማሻሻል የተበታተነ አሰፋፈር ባለባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ማህበረሰቦችን ተጠቃሚ የማድረግ ግባቸውን በማሳካት ረገድም ውጤታማ እንደነበሩ መግለጫው አስታውሷል። መንግስት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያከናውነው በዚህ የሰፈራ ፕሮግራሞች ላይ መሰል ውንጀላዎችና የተዛቡ አመለካከቶች እንዲፈጠሩ ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ የሰፈራ ፕሮግራሙን አላማ በአግባቡ አለመረዳት ነው ብሏል። ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው አለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት በጋምቤላ ክልል የተከናወነው የሰፈራ ፕሮግራም፣ አስገዳጅና በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ ስቃይና የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የዳረገ ነው ማለቱን የዘገበው ብሉምበርግ ኒውስ፤ ፍርድ ቤቱ ይህን ውሳኔ ማስተላለፉ ይበል የሚያሰኝ ነው ሲል እንዳሞካሸውም ጠቁሟል። የእንግሊዝ አለምአቀፍ የልማት ተቋም በበኩሉ፣ በጋምቤላ ክልል ብዙ ዜጎችን ያለፍላጎታቸው ከቀያቸው አፈናቅሏል፣ ለእስራት፣ ለድብደባና ለስቃይ ዳርጓል ለተባለው የሰፈራ ፕሮግራም የገንዘብ እርዳታ እንዳልሰጠ መናገሩን ገልጿል። ከጋምቤላ ክልል ተፈናቅለው በኬኒያ በስደት የሚገኙ ስማቸው ያልተገለፀ ገበሬ፤ በእንግሊዝ መንግስት ላይ የመሰረቱትን ክስ የተቀበለው የለንደን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ የእንግሊዝ የእርዳታ ድርጅት ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ የአገሪቱን ዜጎች የሰብአዊ መብቶች በማይጥስ ሁኔታ ጥቅም ላይ ስለመዋሉ ይጣራ ሲል ከሁለት ሳምንታት በፊት መወሰኑን መዘገባችን ይታወሳል። ምንጭ፥ አዲስ አድማስ | መንግስት የእንግሊዝ እርዳታ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶችን ለመጣስ ስለመዋሉ መጣራቱን ተቃወመ |
በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት በጊዜያዊነት ወደ ጃንሜዳ ተዛውሮ የቆየው አትክልት ተራ በቋሚነት አገልግሎት እሚሰጥበት ወደ ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ መዛወሩንና በዛሬው እለት ታሀሳስ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት የማፅዳት ስራ እንደሚከናወን የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። ጃንሜዳ ለመጪው ለጥምቀት በአል እንዲደርስ፣ ስፖርታዊና ሌሎች ማሀበራዊ አገልግሎቶችን መስጠት እንዲችል በዛሬው እለት ከጠዋቱ ፡ ሰአት ጀምሮ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ወጣቶች፣ የፅዳት ባለሙያዎች ጨምሮ የማፅዳትና የማሳመር ስራ እንደሚሰሩ አስተዳደሩ ገልጿል። ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ እየተገነባ ያለው የገበያ ማእከል በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን የመንገድ፣ የመብራት፣ የመፀዳጃ ቤትና አስፈላጊ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ እየተጠናቀቀ መሆኑንም ተነግሯል። በመጠናቀቅ ላይ ያለው የገበያ ማእከሉ ከአንድ መቶ ሀያ በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚይዝ ሶስት ስድስት መቶ ካሬ ሜትር የመኪና ማቆሚያና ሶስት መቶ ሜትር በአርባ ሜትር ስፋት ያለው ከዋና መንገድ ጋር የሚያገናኝ መንገድ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አማካይነት በአንድ ቢሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ ያለው የአትክልት ገበያ ማእከል፣ ሰማኒያ ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያርፋል። በመጀመርያው ምእራፍ የሚገነቡት ሼጆች ናቸው። እያንዳንዱ ሼዶች ሰባ ሜትር በስድስት ነጥብ ስድስት ሜትር ስፋት አላቸው። አምስት መቶ ሰማኒያ ስምንት የሚሆኑ የመገበያያ ሱቆችም ይኖሩታል ተብሏል። | የጃንሜዳ ጊዜያዊ አትክልት ተራ ወደ ሀይሌ ጋርመንት የማዘዋወሩ ስራ ተጠናቀቀ |
ቻይና በሀገሪቱ ዋና ዋና ቦታዎች ላይ ብሄራዊ የሆኑ የሳይንስ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት እንቅሰቃሴ መጀመሯን አሰታውቃለች።በተለይም በመሰረተ ልማት ግንባታው ዘርፍ ከሀገሯ አልፋ በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር በትብብር በመሰራትም ላይ ትገኛለች ።በሳይንሰ እና ቴክኖሎጂው ዘርፍም ቢሆን የምታደርገው እንቅስቃሴ ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል። አሁን ደግሞ ሀገሪቱ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ቀመሰ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ቆርጣ መነሳቷን የሀገሪቷ መገናኛ ብዙሀን እየዘገቡይገኛሉ።የተራቀቁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ ሙከራ መግባቷም የተገለፀ ሲሆን ይህ ተጠናቆ ወደ ሰራ ሲገባ ሀገሪቷን በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአለም ላይ ተወዳዳሪ እድተሆን ያደርጋታል ተብሎ ይታመናል።ይህ ማለት ደግሞ ሀገሪቷ በተለያዩ ዘርፎች እያደረገችው ላለው ኢኮኖሚያው፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅሰቃሴም ሆነ ከሊሎች ሀገራት ጋር ላላት ግንኙነት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ታምኗል። ሀገሪቷ በአለም ላይ በዘርፉ ያላትን ተቀባነት እንደሚያሳድገው ተስፋ ተጥሏል።በሀገሪቷ የሚገባው የመጀመሪያው የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት የሚገነባው በሰሜናዊ ቤጅንግ የምትገኝው ኋሩ ከተማ ውሰጥ እደሆነ ታውቋል። ይቺ ከተማ ሁለት ነጥብ ስድስት ሰኩየር ኪሎሜትር የሚሰፍን ስፋት እንዳላት ይነገራል።በከተማዋ የሚገነባው ይህ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ተቋም የተለያዩ ቤተሙከራዎች እንደሚኖሩት እና ለአዳዲስ የፈጠራ ውጤቶችም ምቹ የሆነ ቦታ እንደሚሆን ተገልጿል።ከዚህ ውስጥ እንደ እቅድ የተያዘው እና በሙከራ ደረጃ ያለው የአለምን ሙቀት መቆጣጠር የሚያሰችል መሳሪያ ነው። የአለም የሙቀት መጨመር አሁን ላይ የያንዳንዱ ሀገር እራስ ምታት ከሆነ ሰነባብቷል።ለዚህም ሲባል የአለም ሀገራት የአለምን የሙቀት መጠን እንዳይጨምር ለመቆጣጠር እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በሁለት ሺህ በፈረንሳይዋ ዋና ከተማ ፓሪስ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም።ቻይና ለዚህ ሰምምነት ታማኝነቷን እያሳየች ያለች ሀገር ሰትሆን የአለምን የሙቀት መጠንም ለመቆጣጠር ቆርጣ መነሳቷን ያሳያል ሲሉ የኋሩ ከተማ የሳይንስ ቤተ ሙከራ ዋና ዳይሬክተር ፋንግ ቹንንግ ተናግረዋል።ከዚህም በተጨማሪ በርካታ አዳዲስ ፈጠራዎችን በመሰራት ላይ እንደሆኑ ሲያስታውቁ በቅርቡ በሰፋት መንቀሳቀሰ እንደሚጀምሩ እና የፈጠራ ውጤታቸውን ይፋ እንደሚያደርጉ አሰታውቀዋል ሲል የቻይናው አለም አቀፍ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲጅ ቲኤን ዘግቧል። | ቻይና ሳይንሳዊ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሯ ተገለፀ |
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂዮ ሜሎኒ በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ጉብኝት አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት ለጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂዮ ሜሎኒ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂዮ ሜሎኒ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በታላቁ ቤተ መንግስት የክብር የእራት ተጋብዘዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሯ ከጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ጋር የሶስትዮሽ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም ሀገራቱ ያላቸውን የሶስትዮሽና ባለብዙ ወገን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር መስማማታቸው ነው የተገለፀው። | የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ጉብኝት አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ |
አዲስ አበባ፣ መስከረም ሁለት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ፍርድ ቤቱ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ ምርመራ ማድረግ እንዲችል ለፖሊስ ቀናት ፈቀደ። የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮውን ለፖሊስ የፈቀደው የተሰሩና ቀሪ የምርመራ ስራዎችን እንዲሁም የተጠርጣሪዎችን የመከራከሪያ ነጥብ መርምሮ ነው። ተጠርጣሪዎቹ የፀሀይ ሪል ስቴት ጀነራል ማናጀር ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገር ዜጎች እና ሶስት ኢትዮጵያውያን ናቸው። የፌዴራል ፖሊስ መርማሪ ተጠርጣሪዎቹ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል መጠርጠራቸውን፣ በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅት የተለያዩ የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚታተምባቸው ማተሚያ ማሽኖች እና ለግብአት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች እንዲሁም በርካታ ዩሮ፣ የአሜሪካን ዶላርና የሌሎች ሀገራት ገንዘቦች መያዙን ተከትሎ የምርመራ ስራ መጀመሩን መግለፁ ይታወሳል። በዛሬው ቀጠሮ ደግሞ መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጡት የ ቀናት የምርመራ ጊዜ ውስጥ የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ለተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አስታውቋል። ቀሪ የምርመራ ስራዎችን ለማከናወንም ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠውም ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው የምርመራ ጊዜ ውስጥ የተጠርጣሪዎችን ተሳትፎ ለይቶ መቅረብ ሲገባው ለይቶ ባልቀረበበት ሁኔታ ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ መጠየቁ ተገቢነት እንደሌለው በመግለፅ የደንበኞቻቸው የዋስትና መብት እንዲፈቀድ በመጠየቅ ተከራክረዋል። የፀሀይ ሪል ስቴት ጀነራል ማናጀር ኪያ ዦንግን የተባሉት ተጠርጣሪ ባጋጠማቸው የጤና እክል በቂ ህክምና እንዲያገኙ እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። መርማሪ ፖሊስ በበኩሉ ተሳትፏቸውን በሚመለከት ከወንጀል ድርጊት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ብርበራዎች መቀጠላቸውን በመጥቀስ ቀሪ ምርመራውን አከናውኖ ተሳትፎ ደረጃን ለይቶ እንደሚያቀርብ ገልጿል። የወንጀል ድርጊቱ ሀገርን በከፍተኛ ሁኔታ የሚጎዳ ተግባር መሆኑን የጠቀሰው መርማሪ ፖሊስ የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና ጥያቄ በመቃወም ተከራክሯል። የግራ ቀኙን ክርክር የተከታተለው ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ከቀሪ ስራ አንፃር ተጨማሪ የማጣሪያ ምርመራ መደረግ እንዳለበት በማመን የዋስትና ጥያቄያቸውን ለጊዜው ውድቅ በማድረግ ፖሊስ የምርመራ ስራውን አከናውኖ እንዲቀርብ ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል። በታሪክ አዱኛ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ኢንስታግራም፦ ቲክቶክ፦ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን | የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያ በማስፋፋት በተጠረጠሩት ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ተፈቀደ |
አዲስ አበባ፣ ታሀሳስ ሶስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የቴክኒክና ሙያ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድን ቲንክ ታንክ ግሩፕ በአዲስ አበባ በይፋ ተመስርቷል። የስራና ክሀሎት ሚኒስትር ሙፈሪሀት ካሚል በምስረታው ላይ እንዳሉት፥ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለውጥ እንዲመጣ በእውቀት፣ በጥናትና ምርምር መደገፍ ያስፈልጋል። ለዚህም አዳዲስ አሰራሮች ቀጣይነት ባለው መልኩ የሚፈልቁበትን አሰራርና አደረጃጀት መፍጠር ይገባል ብለዋል። በዛሬው እለት የተመሰረተው የቴክኒክና ሙያ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድንም ጥሩ ጅምር መሆኑን ጠቅሰው፥ ሀገራዊ የልማት ተልእኮን ለማሳካት የላቀ ሚና እንደሚኖረው አመላክተዋል። በተጨማሪም የሪፎርም እሳቤዎችን ውጤታማ ለማድረግና ተወዳዳሪ ሀገራዊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የማይተካ ሚና አለው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር ዶክተር በበከሉላቸው፥ በዘርፉ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድን መመስረቱ የሀገሪቱን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራት ለማስጠበቅ ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል። የቡድኑ መመስረት በፖሊሲ አተገባበር ሂደት ውስጥ የካበተ ሀሳብ በመስጠት፣ ልምዶችን በማካፈል፣ የውይይት ባህል እንዲዳብርና በዘርፉ ተዋንያን መካከል ተቀራርቦ ለመስራት ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑንም ገልፀዋል። | የቴክኒክና ሙያ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድን ተመሰረተ |
አዲስ አበባ፣ ግንቦት ሀያ ዘጠኝ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የጃራ አባገዳ ትምህርት ቤት ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ህንፃዎች የግንባታ ስራ ለማስጀመር የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። ለተከታታይ ሶስት አመታት ሲጠየቅ የቆየውን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ የጃራ አባገዳ ትምህርት ቤት ውስጥ የተማሪዎች መማሪያ፣ የአስተዳደር ህንፃ፣ የላይብረሪና የላብራቶሪ አገልግሎት የሚውሉ ህንፃዎች ናቸው የሚገነቡት። ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የህዝብ ጥያቄ ከነበረባቸው አንዱ የሆነው ይህ ትምህርት ቤት፥ ግንባታው ሲጠናቀቅ የቅበላ አቅሙን ከአራት መቶ አምስት ወደ አንድ ሺህ አምስት መቶ በማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገልጿል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመሰረት ድንጋዩን ባስቀመጡበት ወቅት፥ የህዝብን አንገብጋቢ ችግሮች ቅድሚያ ሰጥተን በመፍታት ሂደት ላይ ነን ያሉ ሲሆን፤ ትምህርት ቤቱም የዚህ ማእቀፍ አንዱ አካል መሆኑን አስረድተዋል። ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር አለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኘና ህገ መንግስታዊም መብት ነው ያሉ ያሉት ከንቲባዋ ፥ በሌሎች የሀገራችን ክልሎችም በበርካታ ቋንቋዎች ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። አዲስ አበባ ውስጥም ተማሪዎች በአማርኛ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አለም አቀፍ ቋንቋዎች ማለትም በግሪክ፣ በፈረንሳይኛ፥ በአረብኛ፣ በቱርክና በመሳሰሉት እንደሚማሩ ጠቁመው፥ የአገራቸውን ባንዲራ ይሰቅላሉ፤ የአገራቸውንም መዝሙር ይዘምራሉ ፤ ከአገራቸው ቋንቋ አንዱ በሆነው በኦሮምኛም መማር ከጀመሩም ዋል አደር ብለዋል ነው ያሉት። ሆኖም ግን አንዳንዶች ይህንን እንደ ስህተት በመቁጠር የፖለቲካ አጀንዳ ሊያድረጉት መሞከራቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልፀው፥ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማርና መናገር ሙሉ መብት እንዳላቸው ገልፀው፥ ልጆች በመብታቸው እንዳይጠቀሙና እንዲሸማቀቁ የሚያደርጉ አካላት ከህገ ወጥ ድርጊታቸው እንዲታቀቡም አሳስበዋል። አዲስ አበባ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን እና ለአለም አቀፍ ተቋማት መልካም ቤት ሆናለች ያሉት ከንቲባ አዳነች ፥ የራስዋን ልጆች የምታሸማቅቅ እንድትሆን ለማድረግ የሚጥሩ አካላት መሰረታዊ ስህተት እየፈፀሙ ስለሆነ በፍጥነት መታረም አለባቸው ሲሉ በአፅንኦት ገልፀዋል። ዘላቂ ሰላምና ልማት የሚመጣው ህዝቡን አስተባብሮና አንድነቱን አጠናክሮ በመምራት እንጂ የጥላቻን አስተሳሰብ በመዝራት አይደለም ነው ያሉት ከንቲባዋ። የትምህርት ቤቱ ግንባታ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ መግለፃቸውንም ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን | ከንቲባ አዳነች አቤቤ የጃራ አባገዳ ትምህርት ቤት ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ህንፃዎች የግንባታ ስራ የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ |
የፌስ ቡክ ተከታዮቹ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሆነዋልቃና ቴሌቪዠን የተመልካቾቹን የመዝናኛ አማራጭ ለማጎልበት ሁለት አዳዲስ ዝግጅቶችን አንድ ወጥ እና አንድ በአማርኛ የተመለሰ ማቅረብ መጀመሩን ገለፀ። በአሁኑ ጊዜ ጣቢያው በየሳምንቱ የስላሳ ሰአት አዳዲስና ያልታዩ ዝግጅቶችን ለተመልካቹ እንደሚያቀርብ በላከው መግለጫ አስታውቋል።ሰሞኑን አምስትኛ ክፍሉ የተሰራጨው የ ምንድን ዝግጅት፣ የተለያዩ ወቅታዊ ማህበረሰብ ተኮር ርእሶችን እያነሳ ከተለያዩ ምልከታዎች አንፃር የሚያወያይ ሲሆን በዚህም የተመልካቾችን ተሳትፎና ጤናማ ውይይቶች ያበረታታል ተብሏል። አዲስ የተጀመረው ልጅቷ የተባለው የኮሎምቢያ ድራማ፤ በእውነተኛ ክስተቶች ላይ የተመረኮዘ ሲሆን የጦርነትን አስከፊ ገፅታ ያሳያል። ታሪኩ አንዲት ሴት በሽምቅ ተዋጊዎች ተመልምላ የጦርነትን አስከፊ ገፅታ በአፍላ እድሜዋ እንድትኖረው ስትገደድና ከብዙ አመት በኋላ አምልጣ አዲስ ኑሮ ለመጀመር ስትሞክር፣ ከህብረተሰብ ጋር ለመቀላቀል፣ ነፃነትዋን ለመልመድና ቤተሰብዋን ለመጋፈጥ የሚደርስባትን ውጣ ውረድ ያስቃኛል። ድራማው ከፍተኛ አድናቆትን ያገኘ ሲሆን በቅርቡ ኔትፍሊክስ በተባለው ታዋቂ የፊልም አቅራቢና አከፋፋይ ተገዝቶ፣ በብዙ አገሮች እየታየ ይገኛል ብሏል ቃና በመግለጫው።በተመልካቾች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈውን ጥቁር ፍቅር የተሰኘ ድራማ የሚተካ ቅጣት የተባለ ወደ አማርኛ የተመለሰ የቱርክ ድራማ በቅርቡ ማቅረብ እንደሚጀምር ጠቁሞ ቅጣት በይዘቱ ልክ እንደ ጥቁር ፍቅር በተለያዩ አገሮች ዝና እና ሽልማት ተቀዳጅቷል ተብሏል። ጣቢያው የተመልካቾቹን እይታ ለማበልፀግና ፍላጎታቸውን ለመገንዘብ፣ በየጊዜው የተለያዩ ጥናቶችና ዳሰሳዎች እንደሚያካሂድ ጠቁሞ ግኝቶችንም በሚያቀርባቸው ዝግጅቶች ላይ እንዲንፀባረቁ ይደረጋል ብሏል።በስርጭት ላይ በቆየበት የስድስት ወር ጊዜያት ውስጥ ጥሩ አቀባበል ማግኘቱን የጠቀሰው ቃና ፤ የፌስ ቡክ ተከታዮቹ ከአንድ ሚሊዮን በላይ መድረሳቸውን አስታውቋል። በቅርቡ በቤል ካሽ የተካሄደ በ አምስት ሺህ ሰዎች ላይ የተደረገ አገር አቀፍ የስልክ መጠይቅ፤ ከሶስት ተጠያቂዎች ውስጥ አንዱ የቃና ቴሌቪዥን ዝግጅቶችን ከሰኞ እስከ አርብ በየቀኑ እንደሚያዩ አመልክቷል። ቃና ቴሌቪዥን በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው አቀባበል አበረታችና ከጠበቅነው በላይ ነው። ወደፊትም የመዝናኛ አማራጭ የሆኑ አዝናኝና አሳታፊ ዝግጅቶችን ለማቅረብ የተመልካቾቻችንን ፍላጎት ማጥናት እንቀጥላለን ብለዋል፤ የቃና ቴሌቪዥን የኮሙኒኬሽን እና ማርኬቲንግ ዳይሬክተር። ቃና ቴሌቪዥንና የዝግጅት አጋሩ ቢ ሚዲያ በቅርቡ ይፋ የሚሆኑ ተጨማሪ ወጥ ስራዎችን እያዘጋጁ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል። | ቃና ሁለት አዲስ ዝግጅቶችን ማስተላለፍ ጀመረ |
ኢሳት ዲሲሚያዚያ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አል ሁሴን የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ መብትን በማክበር ለዜጎች ተስፋ እንዲሰጥ ጠየቁ።ኮሚሽነሩ በኢትዮጵያ ያካሄዱትን ጉብኝት ካጠናቀቁ በኋላ በሰጡት መግለጫ አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አመራር ለህዝቡ የሰጠውን ተስፋ በመተግበር የሰብአዊ መብቶች ሊጠበቁ ይገባል ብለዋል።በጉብኝታቸውም የፖለቲካ እስረኞች የነበሩ ሰዎችን የሀይማኖት አባቶችንና ባህላዊ መሪዎችን አነጋግረው ህዝቡ በአዲሱ አስተዳደር የተገቡ ተስፋዎች መክነው እንዳይቀሩ ስጋት እንዳላቸው መረዳታቸውን ኮሚሽነሩ ገልፀዋል።የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አልሁሴን የአገዛዙ ባለስልጣናትን ካነጋገሩ በኋላ በኦሮሚያና በአዲስ አበባ የፖለቲካ እስረኛ የነበሩትንና የሀይማኖት እንዲሁም ባህላዊ መሪዎችን አነጋግረዋል።በመጀመሪያው ጉብኝታቸው በኦሮሚያና አማራ ክልሎች ጉብኝት እንዲያደርጉ ተከልክለው የነበሩት ኮሚሽነሩ በአሁኑ ኛ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ገደቡ ተነስቶ ወደ ቢሾፍቱና መሰል አካባቢዎች ከነዋሪዎች ጋር መወያየታቸው አዎንታዊ ርምጃ መሆኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።በዚሁ ውይይታቸውም ዜጎች በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ንግግሮችና በሰጧቸው ቃል ኪዳኖች ተስፋ መሰነቃቸውን እንደተረዱ ነው የተናገሩት።ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ባካሄዱት ውይይትም ለግጭት ምክንያት የነበሩ የፍትህ እጦቶችን ለማስተካከል መንግስታቸው ቁርጠኛ መሆኑን እንደተገነዘቡም ገልፀዋል።መንግስትን በመቃወማቸውና በመተቸታቸው ታስረው የነበሩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች ከእስር መፈታታቸው አዎንታዊ ርምጃ እንደሆነም ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አልሁሴን በመግለጫቸው ተናግረዋል።እናም ከእስር የተለቀቁ ሰዎችንና ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ለማነጋገር መቻላቸውን ነው የገለፁት።በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ አባገዳዎችን ሲያናግሩም በሀገሪቱ ያለውን ችግር በግልፅ በማውራት በመንግስት የተፈፀሙ በደሎችን እንደዘረዘሩላቸው ተናግረዋል።ኮሚሽነሩ ከአባ ገዳዎች ጋር ሲወያዩ የክልል ባለስልጣናት የነበሩ ቢሆንም ሰዎቹ ግን ችግሩን ከመናገር አልተቆጠቡም።ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ በእሬቻው እልቂት ጉዳይ ላይ የፀጥታ ሀይሎች ሰው አልገደሉም የሚል ምስክርነት እንዲሰጡ ተገደው እምቢተኛ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።በተለይ ከሰብአዊ መብት ጠበቃ ከሆኑ ሁለት የአለም አቀፍ ተወካዮች ጋር በሮዝሜሪ የተካሄደው ውይይት በመንግስት ባለስልጣናት ትእዛዝ እንዲቋረጥ መደረጉ ተነግሯል። | የህወሀት አገዛዝ የሰብአዊ መብትን በማክበር ለዜጎች ተስፋ እንዲሰጥ ተጠየቀ |
ዜጐች ወደተለያዩ አገሮች ሄደው እንዲሰሩ የሚፈቅደው አዲሱ የግል ሰራተኞችና አሰሪ አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት ቢፀድቅም አዋጁ ማሟላት ያለባቸው ብዙ ነገሮች ስላሉ ጉዞው አሁኑኑ አይጀምርም ተባለ። ጉዞው መቼ እንደሚጀመር የተጠየቁት የሰራተኛና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሸለመ፣ አዋጁ ታኀሳስ ቀን ሁለት ሺህ ስምንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቢፀድቅም በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ስላልወጣ፣ የአዋጅ ማስፈፀሚያ፣ አደረጃጀት መመሪያና ደንብ መውጣት ስላለበትና ተጓዦች ስልጠና መውሰድ ስላለባቸው ጉዞው በዚህ ጊዜ ይጀመራል ማለት አይቻልም ብለዋል። ወደተለያዩ የአረብ አገሮች የሚሄዱ ዜጐቻችን የተለያዩ የመብት ጥሰቶች፣ እንግልት፣ የአካል ጉድለትና የሞት አደጋ ሲደርስባቸው ቆይቷል፤ መብታቸው፣ ደህንነታቸውና ክብራቸው ሳይጠበቅ እየተዋረዱ ይመለሱ ነበር ያሉት አቶ ግርማ፤ መንግስት፣ ዜጐቻችን እንደሌሎች አገሮች ዜጎች ለምንድነው መብታቸውና ደህንነታቸው የማይከበረው ኮንትራታቸውን ሲጨርሱ ለምንድነው በደሀና ወደ አገራቸው የማይመለሱት ችግሩ ምንድነው የአዋጁ ወይስ ውጭ ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ችግር ወይስ የዜጐቻችን ሳይሰለጥኑ መሄድ የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ችግሩን ለማወቅ ከሁለት አመት በፊት የውጭ አገር የጉዞ ስምሪት እንዲቆም መደረጉን አስታውሰዋል። በተደረገውም ጥናት የቀድሞው አዋጅ ክፍተቶች እንደነበሩት፣ ዜጐች ከሚሄዱባቸው አገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያለመኖር እንዲሁም ዜጐች ወደ ውጭ አገር ለስራ ሲሄዱ ያለምንም እውቀት እንደሚጓዙ ስለታወቀ አዲሱ አዋጅ በፊት የነበሩት ጉድለቶች ታርመው መዘጋጀቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በአዲሱ አዋጅ ወደተለያዩ አገራት የሚሄዱ ዜጐች የትምህርት ደረጃ ስምንትኛ ክፍልና ከዚያ በላይ መሆን እንዳለበት የተካተተ ሲሆን ተጓዦች በቤት አያያዝና በእንክብካቤ አጠባበቅ ቢያንስ የሶስት ወር ስልጠና የተወሰዱና የብቃት ማረጋገጫ ሲኦሲ ፈተና ተሰጥቷቸው ያለፉ መሆን እንዳለባቸው ተገልጿል። ስልጠናው የሚሰጠው በውጭ አገር እንዲሰሩበት ብቻ ሳይሆን ከመንግስት ብድር ወስደው፣ የመሸጫ ቦታ ተመቻችቶላቸውና የገበያ ትስስር ተፈጥሮላቸው በአገር ውስጥ እንዲሰሩም ጭምር ነው ብለዋል፤ አቶ ግርማ። የሙያ ስልጠናው የሚሰጠው በአራቱ ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች፡ በአማራ፣ በትግራይ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ብሄርና ብሄረሰቦች እንዲሁም በአዲስ አበባና በድሬዳዋ ከተሞች እንደሆነ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፣ ስልጠናው የሚሰጠው በክልሎቹና በከተሞቹ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት እንደሆነም ገልፀዋል። ከኩዌት፣ ከኳታርና ከጆርዳን ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተፈጥሮ ስምምነት ተፈራርመናል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ከሳኡዲ አረቢያና ከሌሎች አገሮች ጋር እየተወያዩ መሆኑንም ተናግረዋል። ህዝቡ ህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች፣ አሁን አዋጁ ፀድቋል በሚል ማታለያ ልጆቻቸውን እንዳያስኮበልሏቸውም ጥንቃቄ ያደርጉ ዘንድ አቶ ግርማ ሸለመ አሳስበዋል። | የውጭ አገር የስራ ስምሪት አዋጅ ቢፀድቅም አሁኑኑ ጉዞ አይጀመርም ተባለ |
አቶ አንዱአለም ተፈራ ከገዢው መደብ የምንለይበት በሚል ርእስ ባስነበቡን ፅሁፍ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግስት የሚለውን አጠራር ለምን እንደመረጡ ያስረዳሉ። መጠሪያው ለወያኔ የማይገባው በመሆኑና አቶ አንዱአለም መጠሪያውን ለመጠቀም ያአስቻለኝ ብለው ያቀረቡት ምክንያት በቂና ተገቢ ሆኖ ስላልተሰማኝ ይህችን አስተያየት ፃፍሁ። ትግሬ ስንል የኢትዮጵያ አንድ ክፍል በሆነው ትግራይ የተወለዱና ትግረኛ ቋንቋ የሚናገሩ ወይንም የወላጆቻቸው ስር ከዛ ሆኖ የትም ይሁን የት የተወለዱና ቋንቋውን ሊናገሩም ላይናገሩም የሚችሉትን ሁሉ የሚያጠቃልል ነው። ስለሆነም የትግሬ ነፃ አውጪ ስንል ወያኔ ትናንትም የታገለው ዛሬም ስልጣን ላይ ሆኖ የሚሰራው እነዚህን ነፃ ለማውጣት ነው፣ እነርሱም ነፃ አውጪነቱን አውቀውና አምነው የተቀበሉት ነው ወደሚል አንደምታ ይወስዳል። ይህ ደግሞ ወያኔ የሚፈልገው ነው። እሱ የሚለውን ተቀብሎ ትግሬና ወያኔን አንድ አድርጎ የመመልከቱ አደገኛነት የታያቸው ኢትዮጵያውያን ገና ከጅምሩ ወያኔንና ትግረኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ለይቶ ማየት እንደሚገባ፣ ሁለቱን መቀላቀል ትግሉን የሚጎዳና ወያኔን የሚጠቅም ብሎም በወደፊት የኢትዮጵያ አንድነት ላይ መጥፎ ደንቃራ የሚያስቀምጥ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፣ፅፈዋል። ይህም ሙሉ በሙሉ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ተቀባይነት በማግኘቱ ወያያኔ ባሰበውና በተመኘው መጠን ትግረኛ ተናጋሪውን ከቀሪው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ነጥሎ የርሱ ብቸኛ መከታ ማድረግ አልቻለም። ወያኔዎች ትናንትም ሆነ ዛሬ አላማ ፍላጎታቸው ስልጣን ነው። ትግል ሲጀምሩ መላ ኢትዮጵያን መያዝ አንችልም ብለው ስላመኑ ትግራይን ይዘው የስልጣን ፍልጎታቸውን ለማርካት ስማቸውን ተሀህት፣ማገብት ህውሀት እያሉ ለትግረኛ ተናጋሪው ወገን የሚታገሉ መስለው ተጓዙ እንጂ ከራስ ጥቅም ያለፈ አላማም አጀንዳም ያላቸው አይደሉም። ይህን ደግሞ በሀያ አራት አመታት አገዛዛቸው በሚገባ የተገነዘብን ይመስለኛል። በአላማም በግብርም የማይመስሉትን የቀዳማይ ወያኔን ስም የያዙትም በእምነት ሳይሆን ድጋፍ ለማግኘት ካልሆነም ተቃውሞን ለመቀነስ እንደሆነ የትግራይ አባቶችን ጠጋ ብሎ ጠይቆ መረዳት ይቻላል። በኢትዮጵያዊ እምነትና ስሜታቸው ጥያቄ የማይነሳባቸው ዶክተር ሀይሉ አርአያ በአንድ ፅሁፋቸው እነዚህ ሰዎች ከቀዳማይ ወያኔ ጋር በአላማም በተግባርም ስለማይመሳሰሉ ወያኔ ተብለው መጠራት የለባቸውም አስመሳይ ወያኔዎች ናቸው ማለታቸውን አስታውሳለሁ። ስለሆነም የትግሬ ነፃ አውጪ ማለት ለግብራቸው የማይመጥን ስም ነው፤ ይበዛባቸዋል። እንደውም ለእነርሱ ፍላጎት መሳካት የሚበጃቸው ነው። አቶ አንዱአለም በፅሁፋቸው እኔ ራሳቸውን እንዲጠሩበት በመረጡት ስም ነው የጠራኋቸው ይላሉ። ሰይጣን ለተንኮሉ ከመፅሀፍ ቅዱስ ይጠቅሳል እንዲሉ ወያኔ ትክክለኛ ማንነቱን የሚከልልለትንና ትግረኛ ተናጋሪውን ኢትዮጵያዊ ወገን ጋሻ ማድረግ ያስችለኛል ብሎ የመረጠውን ግብሩን የማይገልፅ ስም ለራሱ ስለሰጠ እኛ ተቀብለን ማስተጋባት የለብንም። ይህን አደረግን ማለት በተዘዋዋሪ የወያኔን ፍልጎት ማሳካት ነው የሚሆነው። የወያኔ ስብከትና ማስፈራራያ ያልበገራቸው በርካታ ትግረኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን በተቃውሞው ጎራ ጥንቃቄ የጎደለው ተግባር ያለፍላጎታቸው ወያኔን ለመደገፍ መገደዳቸው የአደባባይ ምስጢር ይመስለኛል። የሚወዱትን ሲያጡ እንደሚባለው ሆኖባቸው። አቶ አንዱአለም ትግሬዎችን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳ ግንባር፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ነኝ ሲል፤ ሌላ ምን ብዬ ልጠራው ይላሉ። ይህን አባባል ከላይ ለመግለፅ በሞከርኩት አስተሳሰብ ስናየው ሶስት ጉድለቶች አሉት የመጀመሪያው ትግሬዎችን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳ የሚለው ሲሆን ይህን ከላይ ለማሳየት ሞክሬአለሁ፤ ሁለተኛው ግንባር የሚለው ነው፡ከመጠሪያው ጋር ሊቀራረብ የሚችለው ህወሀት ነው እሱ ደግሞ ግንባር አይደለም፤ ግንባሩ ኢህአዴግ ነው። እሱን በጥቅሉ የትግሬ ነፃ አውጪ ለማለት ተፈልጎ ከሆነ ደግሞ ወያኔ ሀገራዊውን የፖለቲካ ትግል የጎሳ ትግል ለማድረግ ሌት ከቀን የሚማስንበትን ስራ እያሳካንለት ነው ማለት ነውና አደጋ አለው። ሶስተኛው ነኝ ሲል እኔ ምን ብዬ ልጥራው የሚለው ነው። እኛ መጠራት ያለብን እሱ ነኝ በሚለው ማንነቱን በማይገልፀው ሳይሆን ለማንነቱ በሚመጥነው ለግብሩ መገለጫ በሚሆን መጠሪያ መሆን አለበት። አሁን ልማታዊ መንግስት እያለ ራሱን እየጠራ ነው ታዲያ እኛ በዚህ እንጠራዋለን ነገርን ነገር ያነሳዋል አንዲሉ በዚህ ረገድ ሌሎች ስህተቶችም ስንፈፅም ኖረናል አሁንም እየፈፀምን ነው፤ ብሶት የወለደኝ ሲል ተቀብለን ብሶት የወለደው ብለናል፣ በረሀ የወረድነው አንባገነኑን የደርግ መንግስት ለማስወገድ ነው ሲሉ ሰምተን አሰምተናል ተቀብለን ተናግረናል። እንደሚነግሩን ጫካ የገቡት የካቲት አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ነው። በዚህ ወቅት ንጉሱን ከስልጣን | ወያኔን የትግሬ ነፃ አውጪ ማለት ያለ ግብሩ ስም መስጠት |
የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ባለፈው ረቡእ ለሶስት ሰአታት በፖሊስ ጣቢያ ታስረው መፈታታቸው ተገለፀ። ዶክተር ነጋሶ፤ ፓርቲው ነገ ያካሂዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ ካሰማራቸው አባላት ጋር በተያያዘ ታስረው እንደነበር ታውቋል። ባለፈው ረቡእ የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቅሳ ሲያደርጉ የነበሩ የፓርቲው አባላት የቅስቀሳ ፈቃድ የላችሁም ተብለው በፖሊስ መያዛቸውን የገለፀው ፓርቲው፤ የአንድነት ልሳን ጋዜጣ ፎቶግራፍ አንሺም በራሪ ወረቀት ሲቀበሉ የነበሩ ሰዎችን ያለፍላጐታቸው ፎቶግራፍ አንስቷል፤ ተሳድቧል በሚል ክስ እንደቀረበበት አስታውቋል። ዶክተር ነጋሶ የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ እንዲደረግ ለአባላቱ የስምሪት ደብዳቤ በመፈረማቸው፣ ድርጊቱ የተፈፀመው እሳቸው በሰጡት አመራር እንደሆነ በፖሊስ ተገልፆላቸው ጉዳዩ እስኪጣራ መታሰራቸውን ነው ፓርቲው የገለፀው። ከሶስት ሰአት እስር በኋላም ፎቶግራፈሩ በዋስ ሲለቀቅ ዶክተር ነጋሶ በነፃ እንደተለቀቁ ታውቋል። | ዶክተር ነጋሶ ለሶስት ሰአት ታስረው ተፈቱ |
ኢሳት ዜናጥቅምት በቅርቡ ስልጣን በለቀቁት በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢሳት ምንጮች ገለፁ።በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ ከተገነባው ደብል ትሪ ሆቴል ጋር በተያያዘ የተጀመረው ምርመራ ሙሉ በሙሉ የሆቴሉ ግንባታ የገንዘቡ ምንጭ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑን አረጋግጧል።ይህም የተፈፀመው በአቶ በረከት ስምኦን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ ሊቀመንበርነት ግዜ እንደሆነ መረጋገጡን ምንጮቹ ጨምረው ገልፀዋል።በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ መቀጠሉን ነው የኢሳት ምንጮች የገለፁት። በምርመራውም በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የደብል ትሪ ሆቴል የገንዘብ ምንጭም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑና አቶ በረከት የቦርድ ስብሳቢ በነበሩበት ጊዜ የተፈፀመ መሆኑንም አረጋግጧል።የደብል ትሪ ሆቴል ባለቤት ሆነው የተመዘገቡት አቶ ተካ አስፋውም የዳሽን ባንክ ቦርድ ሰብሳቢ ቢሆኑም ለዚህ ሆቴል ግንባታ በሚል ከዳሽን ባንክ ምንም አይነት ብድር እንዳልወሰዱም ታውቋል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር በዋናነት እንዲሰጥ የተቀመጠውን የመንግስት ፖሊሲ በመፃረር ብድሩ እንደተለቀቀም ለማወቅ ተችሏል።በዋናነት በአምራችነትና በወጭ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ብድር እንዲሰጥ በፖሊሲ ደረጃ አቅጣጫ የተቀመጠለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሆቴሉ ግንባታ የሚውለውን ወጪ መቶ በመቶ ማበደሩንም ምርመራው አረጋግጧል።በቅድሚያ ሁለት መቶ ሚሊየንበቀጣይ ደግሞ ሚሊየን ብር በአጠቃላይ ሚሊየን ብር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወጪ የሆነው በአቶ በረከት ስምኦን ትእዛዝና በባንኩ ፕሬዝዳንት በአቶ በቃሉ ዘለቀ አስፈፃሚነት እንደሆነም ለኢሳት የደረሰው ማስረጃ ያሳያል።ባንኩ ብድር ከመልቀቁ በፊት ተበዳሪው በመቶ መነሻ ማቅረብ እንዳለበት ተደንግጓል።በዚህ ሆቴል ግንባታ ግን ከተበዳሪው ወገን አንድም ሽራፊ ሳንቲም እንዳልቀረበና መቶ በመቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገንዘብ ሆቴሉ መገንባቱን ምርመራው አረጋግጧል።የኢሳት ምንጮች የምርመራ ቡድን አሁንም ስራውን መቀጠሉን አስታውቀዋል።መቀሌ የተጀመረው የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ስብሰባ ላይ እነ አቶ አባይ ወልዱ መልሰው የበላይነታቸውን ካላረጋገጡ በአቶ በረከት ላይ የተጀመረው ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በመገናኛ ብዙሀን ይፋ እንደሚደረግም ምንጮቹ ጨምረው ገልፀዋል።አንዳንድ ወገኖች እንደሚሉት በአቶ በረከት ስምኦን ላይ ከደብል ትሪ ሆቴል ጋር በተያያዘ በዚህ ወቅት ምርመራ የተጀመረው የሆቴሉ ባለንብረት ሆነው የተመዘገቡት አቶ ተካ አስፋው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትነት ስለሚወዳደሩ የህወሀት ሰዎች የእርሳቸውን ተቀናቃኝ የህወሀቱን ተክለወይኒ አሰፋን ለማስመረጥ የሚደረግ ማሸማቀቅ ሊሆን ሲሉ ስጋታቸውን ይገልፃሉ።ንብረትነቱ የአቶ በረከት ስምኦን በሚል ምርመራ የተጀመረበት በአለም አቀፍ ደረጃ የተገነባውና በአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የሚገኘው ደብል ትሪ ሆቴል በመጪው ሰኔ ስራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።ጠቅላላ ወጪው ሚሊየን ብር የፈጀው ደብል ትሪ ሆቴል ባለ ፎቅ ሲሆን መኝታ ክፍሎች እንዳሉትም ታውቋል። | በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ |
የአባዲ ሀዲስ እድሜ እያነጋገረ ነው በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ስላሳ አንድኛው ኦሊምፒያድ ከተጀመረ ስድስተኛ ቀን አስቆጥሯል። ከተለያዩ የአለም አገሮች የተሰባሰቡት ስፖርተኞች በተገኙበት የዘንድሮው የሪዮ ኦሊምፒክ ጨዋታ ሀምሌ ሀያ ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት በድምቀት ሲከፈት፣ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን በዋናተኛው አቤል ኪሮስ መሪነት ወደ ስታዲየም ሲገባ አቀባበል ተደርጎለታል። ኢትዮጵያ በወርቃማ ውጤቷ የምትታወቅበት የረዥም ርቀት ሩጫ ከነገ በስቲያ አርብ ነሀሴ ስድስት ቀን በሚካሄደው የሴቶች አስር ሜትር ፍፃሜ ውድድር የሚጀመር ሲሆን፣ አዲሷ ኮከብ አልማዝ አያና፣ ገለቴ ቡርቃ እና የሁለት ኦሊምፒኮች ባለድሏ ጥሩነሽ ዲባባ የአገሪቱን ድል እንደሚያስቀጥሉ ይጠበቃል። በመካከለኛ ርቀት በስምንት መቶ ሜትር መሀመድ አማን፣ በአንድ አምስት መቶ ሜትር ገንዘቤ ዲባባ፣ ዳዊት ስዩምና በሱ ሳዶ የመጀመርያ ማጣሪያ ውድድራቸውንም ያከናውናሉ። ቅዳሜ በሚካሄደው የአስር ሜትር ወንዶች ፍፃሜም ይገረም ደመላሽ፣ ታምራት ቶላ እና አባዲ ሀዲስ ሲፎካከሩ፣ በእሁዱ የሴቶች ማራቶን ፍፃሜ ትእግስት ቱፋ፣ ማሬ ዲባባና ትርፊ ፀጋዬ ይወዳደራሉ። የአርብ ተወዳዳሪ አትሌቶች ነሀሴ ሶስት ቀን ሪዮ የገቡ ሲሆን፣ የቅዳሜና እሁድ ተፎካካሪዎች ነሀሴ አራት ቀን ወደ ስፍራው እንደሚያቀኑ ብሄራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው አስታውቋል። አነጋጋሪው እድሜ የሪዮ ኦሊምፒክ ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያን በሚወክሉ አትሌቶች መረጣ ብዙ ማከራከሩ አይዘነጋም። በተለይ ኢትዮጵያ በረጅሙ ርቀት ካላት ታሪክ ጋር በተያያዘ ትክክለኛውን አትሌት ወደ ስፍራው ለመላክ ሽኩቻ መፍጠሩ ይታወሳል። ዛሬ ወደ ሪዮ ከሚጓዙት የአስር ሺህ ሜትር ርቀት ተወዳዳሪ አትሌቶች ውስጥ በግንቦት ወር ቻይና ሻንጋይ ላይ በተደረገ የዳይመንድ ሊግ አለም አቀፍ ውድድር የተሳተፈው ወጣቱ አባዲ ሀዲስ ተጠቃሽ ነው። አትሌቱ በዳይመንድ ሊግ ሲሳተፍ በ አመት እድሜ መወዳደሩ ይታወሳል። ባለፈው ግንቦት በሻንጋይ በተደረገው የአምስት ሺህ ሜትር ውድድር ላይ ደቂቃ ከሁለት ነጥብ አራትዘጠኝ ሰከንድ በመግባት አራተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል። በውድድሩ ላይ ያመጣው ሰአት ከቀድሞ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለና ኢብራሂም ጄላን የተሻለ ስለነበር ለሪዮ መመረጥ ችሏል። በእለተ ቅዳሜ ነሀሴ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት በሚደረገው የአስር ሜትር ፍፃሜ ውድድር ላይ ይግረም ደመላሽ፣ ታምራት ቶላና አባዲ ሀዲስ ቀዳሚ ተሰላፊዎች ተደርገው ተይዘዋል። በሻንጋይ አምስት ሜትር ውድድር አመት የሚታወቀው አባዲ አሁን የ አመት ወጣት ተደርጎ ኢትዮጵያን እንደሚወክላት እየተገለፀ ይገኛል። ግንቦት ወር ላይ በ አመት የተወዳደረው አባዲ እንዴት አሁን በ አመት ተደርጎ ተወስዶ ሊወዳደር ይችላል የሚለው የብዙዎቹ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል። አለም አቀፉ የአትሌቲክስ ማሀበር አይኤኤኤፍ እንደሚያስቀምጠው፣ የአስር ሜትር ደንብ ከሆነ በኦሊምፒክ አንድ አትሌት ከ አመት በታች ከሆነ ውድድር ላይ መሳተፍ እንደማይችል የተለያዩ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ለዚህም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጠባባቂ ባልያዘበት የአስር ሜትር ውድድር የእድሜ ማጣራት ተደርጎ አትሌትውን ከውድድሩ ውጪ ሊሆን ይችላል የሚለው ሀሳብ በብዙዎቹ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል። ፌዴሬሽኑ በበኩሉ በአትሌቱ ላይ የተነሳው የእድሜ ችግር ከአለም አቀፍ አትሌቲክስ ማሀበር ጋር በመነጋገር ተስተካክሏል ሲል በቅደም የሪዮ ዝግጅት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አብራርቷል። የብሄራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ስለሺ ብስራት ለሪፖርተር ከሪዮ በማሀበራዊ ድረ ገፅ እንደተናገሩት ከሆነ፣ አባዲ በ አመት እንደተመዘገበና መቶ በመቶ ውድድር ላይ እንደሚሳተፍ ከስፍራው አረጋግጠዋል። የረዥም ርቀት አሰልጣኝ ቶሌራ ዲንቃ አትሌቶቹ ለውድድሩ በቂ ዝግጅት እንዳደረጉ ተናግረው ስለ አባዲ የተነገረው የእድሜ ጉዳይ ፌዴሬሽኑ ከአይኤኤኤፍ ጋር ተነጋግሮ መፍትሄ ላይ እንደደረሰ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ካላት የረዥም ርቀት ውጤት አንፃር በዚህ ወቅት አንደዚህ ያልተጣሩና መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች በመነሳታቸው ብዙዎችን ቅር አሰኝቷል። በተለይ በአስር ሺህ ሜትር ኢትዮጵያ በእንግሊዛዊው ሞፋራህ የተወሰደባትን ብልጫ ስፖርት ቤተሰቡን እንዲሁም የቀድሞ አትሌቶችን ያስቆጨ ክስተት ነበር። በእንደዚህ አይነት ወቅት ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የሚከተለው መንገድ በተደጋጋሚ ችግር ሲስተዋልበት ይታያል። በተለያዩ አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በቡድን ውስጥ ልምድ ያላቸውን አትሌቶች እንዲሁም ተተኪ አትሌቶችን አጣጥሞ ለውድድር መዘጋጀት ዋነኛ ስራ እንደሆነ ባለሙያዎች በተለያየ አጋጣሚ ሲናገሩ ይደመጣል። ኢትዮጵያ በምታደርጋቸው አለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ከእድሜ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ችግርና መስተጓጎል ሲደርስ ይስተዋላል። በዚህም መሰረት ዘንድሮ ደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ ላይ በተደረገው የወጣቶች ሻምፒዮና ላይ ትክክለኛ እድሜ ያላቸውን አትሌቶች በቴክኒካል ባለሙያዎች ባለመስተካከሉ አትሌቶች ከኤምባሲ ሳይፈቀድላቸው ቀርቶ አራት አትሌቶች ብቻ ተስተካክሎላቸው ወደ ውድድሩ ማምራታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ቀሪዎቹ ተወዳዳሪዎች ግን በሌሎች ተተክተው ወደ ስፍራው ቢያመሩም፣ ዘጠኙ አትሌቶች ደርባን ላይ ባልተለመደ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ታሪክ በዚያው መቅረታቸው ይታወሳል። ለዚህም ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአግባቡ አትሌቶችን ለውድድር ያለመ ቅርብ ችግር እንደሆነ ይነገራል። በመጨረሻም ምንም እንኳ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የአባዲን ጉዳይ ከአለም አቀፍ የአትሌቲክስ ማሀበር ጋር ተነጋግሬያለሁ ቢልም ልምድ ያላቸው አትሌቶችን በተጠባባቂነት እንኳን ይዞ ባለመጓዝ ቅሬታ ያስነሳ ጉዳይ ሆኗል። | የሴቶችና የወንዶች አስር ሜትር አርብና ቅዳሜ ይካሄዳል |
አዲስ አበባ፣ ሰኔ ሁለት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳእና እና አዳማ ከተማ ሶስትለ ሶስት በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። ጥሩ ፉክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሶስት ለ እየመራ ቢቆይም ሀድያ ሆሳእና ነጥብ መጋራት ችሏል። በጨዋታው የአዳማ ከተማን ሁለት ግቦች ዳዋ ሆቴሳ ሲያስቆጥር ቀሪዋን አንድ ግብ አዲስ ተስፋዬ አስቆጥሯል። የሀድያ ሆሳእናን ሁለት ግቦች ደግሞ ባዬ ገዛኸኝ ያስቆጠረ ሲሆን ፥ አንዷን ግብ ሰመረ ሀፍተይ ማስቆጠር ችሏል። | የሀድያ ሆሳእና እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ |
አዲስ አበባ፣ ጥር ሀያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።ፕሬዚዳንቷ ለኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ባስተላለፉት መልእክት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።ዳንኤል አራፕ ሞይ ለኬንያ ነፃነት ያደረጉትን ተጋድሎ ያስታወሱት ፕሬዚዳንቷ፥ በኢጋድ ምስረታ ላይ ጉልህ ስፍራ እንደነበራቸውም አንስተዋል።ፕሬዚዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ ቢያልፉም ለህዝባቸው እና ለአፍሪካ ደህንነት ባደረጉት በጎ ተግባር ሁሌም ይታወሳሉ ብለዋል በመልእክታቸው።ለመላው ኬንያውያን፣ ለኬንያ መንግስት እና ለሟች ቤተሰቦችም መፅናናትን ተመኝተዋል።ዳንኤል አራፕ ሞይ በዘጠና አምስት ከዚህ አለም በሞት የተለዩ ሲሆን፥ ኬንያም ቀብራቸው እስከሚፈፀምበት እለት ድረስ ብሄራዊ የሀዘን ቀን አውጃለች።መረጃው በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነው፤ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ | ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ለኬንያውያን የሀዘን መግለጫ አስተላለፉ |
በአዲስ አበባ የዳቦ እጥረት ተከሰተ ዘሀበሻ በአዲስ አበባ ከተማ ዳቦ በበቂ ሁኔታ እየቀረበ እንዳልሆነ ተገለፀ። የከተማው ነዋሪዎች በየዳቦ ቤቱ ዳቦለመግዛት ሲሄዱ ዳቦ አለመኖሩ እየተነገራቸው በተደጋጋሚ እየተመለሱ መሆኑንና ችግሩም እስካሁን እንዳልተቀረፈሰንደቅ ጋዜጣ በጥቅምት ቀን አመተ ምህረት እትሙ ዘግቧል። እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ አንዳንድ ዳቦ መሸጫሱቅ የስራ ሀላፊዎችና ባለቤቶች በተገኘው መረጃ መሰረት በዳቦ መሸጫ መንግስት ከተመነው ዋጋ አንፃር ሲታይ አንድን ዳቦ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው የትርፍ መጠን አነስተኛ በመሆኑ ዘርፉ አበረታች አለመሆኑ ተገልፁአል።እጥረቱን በተመለከተ ጋዜጣው ያነጋገራቸው በንግድ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ሀላፊአቶ አብዱራህማን ሰይድ የዳቦ ዋጋ ትርፍን በተመለከተ መንግስት ተመኑን ሲያስቀምጥ ያሉትን ወጪዎች ታሳቢአድርጎ መሆኑን ገልፀዋል። የተፈጠረውንም የዳቦ እጥረት በተመለከተ ስንዴ በእህል ንግድ በኩል ተገዝቶሀገር ውስጥ ሲገባ መንገድ ላይበተፈጠረው መዘግየት የተፈጠረ መሆኑን ሀላፊው አመለክተዋል። ያም ሆኖ እህል ንግድ ከመጠባበቂያ ክምችቱበማውጣት ለአዲስ አበባም ሆነ ለክልል የዱቄት ፋብሪካዎች እንደተቀመጠላቸው ኮታ እንዲያከፋፍል መሆኑንም ጨምረውገልፀዋል። መንግስት በሀገሪቱ የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር በሚል በ አመተ ምህረት በበርካታ የፍጆታሸቀጦች ላይ የዋጋ ተመን ከጣለ በኋላ በስተመጨረሻ የሌሎች ተመን ሲነሳ የስኳር የዘይትና የስንዴ ምርቶችንየማከፋፈል ስራ ሙሉ ለሙሉ በመንግስት ቁጥጥር ስር ውሎ እስከ ዛሬም እንደቀጠለ ነው።ይሁን እስካሁን በስርጭቱረገድ በስኳር ላይ ተደጋጋሚ ችግር እየታየ ሲሆን አሁን ደግሞ በዳቦ ስንዴ ላይ ችግሩ እየተንፀባረቀ መሆኑንሰንደቅ ጋዜጣ ዘግቧል። የመጅሊስ እና የኡለማዎች ምክር ቤት የይፍረሱ ክስ ለሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ተገለፀ ዘሀበሻ የኢትዮጵያ እስልምና እና የኡለማዎች ምክር ቤት ይፍረሱ በሚል የቀረበው አቤቱታ ውድቅ ከተደረገ በኋላ በድጋሚለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ጥቅምት ቀን አመተ ምህረትባወጣው እትሙ አስነብቧል። የታሰሩት የኢትዮጵያ ሙስሊም ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠበቃ ተማም አባ ቡልጉ እንደተናገሩት የተጀመረውክስ ለመስከረም ቀን አመተ ምህረት ድጋሚ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለማየት እንደነበር ተናግረው ጉዳዩ ተብራርቶ በመቅረቡ ለማክሰኞ ጥቅምት ቀን አመተ ምህረት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚሰየም ጋዜጣውቢዘግብም የማክሰኞ ችሎት ውሎውን በመለከተ ግን ያለው ነገር የለም። እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ኡለማዎችምክር ቤት በራሱ በእስልምና ጠቅላይ ጉባኤዎች ስር ያለ በመሆኑ እና የነዚህ የበላይ ደግሞ መጅሊሱ በመሆኑኡለማዎች ምክር ቤት የማስመረጥ መብት የለውም የሚለው የክሱ አንዱ ጭብጥ መሆኑን ጠበቃ ተማም መናገራቸውተዘግቧል። እንደጠበቃ ተማም ገለፃ ኡለማዎች ምክር ቤት ምርጫ ያካሄደው የራሱ የሆነ ህጋዊ ሰውነት ሳይኖረው ነው።ምርጫውን የማካሄድ ስልጣን የኡለማዎች ምክር ቤት ሊሆን አይችልም። ምርጫው አስመራጭ በሌለበት ሁኔታ ሊደረግአይችልም። ለዚህም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የወጣውን ሁሉ በማስረጃነት አቅርበናል በማለት የክሳቸውን ዝርዝርጠቁመዋል። ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከቀረቡ የክስ ፋይሎች መካከል ጅሀዳዊ ሀረካትን በተመለከተ በኢቴቪ የቀረበው ዘጋቢ ፊልምፌደራል ፖሊስ ደህንነት ከፍተኛ ፍርድ ቤትን እና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ተከሰው የነበረ ቢሆንምፍርድ ቤቱ የዘጋቸው ፋይሎች በሰበር ችሎቱ በድጋሚ እንደሚቀርቡ ይጠበቃል ሲል ጋዜጣው ዘግቧል። ፖሊስ በቦምብ ፍንዳታ ህይወታቸው ያለፈው ሶማሊያውያን አሸባሪዎች ናቸው ሲል መናገሩ ተጠቆመ ዘሀበሻ ጥቅምት ቀን አመተ ምህረትበአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሯንዳ ማዞሪያና ቦሌ ሚካኤል መግቢያ አካባቢበቦንብ ፍንዳታ ህይወታቸው ያለፈው ሁለት ሶማሊያውያን ሽብርተኞች መሆናቸውን ማረጋገጡን የፌደራል ፖሊስ የፀረሽብር ግብረ ሀይል ማስታወቁን ሪፖርተር በጥቅምት ቀን አም እትሙ ዘግቧል። የአንድ ግለሰብ ሰርቪስ ቤት ተከራይተው ከነበሩት ሶማሊያውያን መካከል አንደኛው ከ ቀናት በላይ የቆየ ሲሆንሌላኛው ፍንዳታው ከመድረሱ በፊት ከሁለት ሰአታት በፊት የደረሰ መሆኑን ግብረሀይሉ ማረጋገጡን አስረድቷል።ሽርተኛ የተባሉት ሶማሊያውያን ካፈነዱት ቦምብ በተጨማሪ መጠናቸው ያልተገለፀ ቦምቦችና አንድ ሽጉጥ ከሁለት ካርታጥይት ጋር መገኘቱን የፈንጅ ማቀጣጠያና የአደጋ መከላከያ ጃኬቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድንማሊያና ቀበቶዎች መገኘታቸውም ተጠቁሟል። እንደሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ከሶማሊያውያኑ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችና የቤቷከራይ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑንም ግብረ ሀይሉ አስታውቋል። የአደጋውን መንስኤናአጠቃላይ ስለነበረው ሁኔታ ፖሊስ መረጃ እያሰባሰበ በመሆኑ ዝርዝ መረጃ ለመስጠት እንደማይችሉ የአዲስ አበባፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይህደጎ ስዩም ለሪፖርተር የገለፁ ቢሆንም የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ሀይልግለሰቦቹ ሽብርተኛ መሆናቸውን ማረጋገጡን አስታውቋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደጠቆሙት ከሆነ የፍንዳታው ቅንብር ኢህአዴግ ቀደም ሲል ልክጨዋታው ሲያልቅ በተለይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ካሸነፈ ስታዲየም አካባቢ በማፈንዳት የድርጊቱፈፃሚዎች የትጥቅ ትግል እያደረጉ ያሉ ተቃዋሚዎች እና የሀይማኖት አክራሪዎች ናቸው ለማለት አቅዶት የነበረውንሆን ብሎ ግቡ ሳይሳካ ሲቀር በበሌላ ቦታ ማፈንዳቱን የከዚህ ቀደም የኢህአዴግን ድርጊት እያመሳከሩ ያስታወሷልታጡም ። በተለይም በፍንዳታው አለም አቀፉ ማሀበረሰብ የታሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ላይ መንግስትየወሰደውን እርምጃ እንዲደግፉና እንዲፈጡ የሚጠይቀውን ጫና በመግታት እውቅና ለማግኘት ታቅዶ እንደነበርከኢህአዴግ ውስጥ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቁመዋል። | ዛሬ ከወጡ ጋዜጦች የተመረጡ ዜናዎች እነሆ። |
ኢትዮጵያና ሱዳን የአረብ ሊግን ውሳኔ ተቃውመዋል በህዳሴው ግድብ ጉዳይ ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በአምስት ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ተደራድረው መግባባት እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት ከድርድር ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌለ የኢትዮጵያ መንግስት አስታውቋል። እ ኤ አ በሁለት ሺህ በተፈረመው የመርሆ መግለጫ ስምምነት መሰረት፤ ከሰሞኑ አሜሪካና የአለም ባንክ ጣልቃ የገቡበት የድርድር ሂደት መጀመሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የህግ አማካሪ አምባሳደር ረታ አለሙ አስረድተዋል። በመርሆ ስምምነቱ አንቀፅ አምስት መሰረት፤ የግድቡ የውሀ ሙሌትን፣ የግድቡን አሰራር ሂደት ወይም የውሀ አለቃቀቅ በሚመለከት ከሁለቱ ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ እንደምትደርስ ተደንግጓል ያሉት አምባሳደር ረታ፤ በዚህ መሰረት ወደ ድርድር መገባቱን አውስተዋል። የተጀመረው ድርድርም የህዳሴውን ግድብ አሞላልና አለቃቀቅ የሚመለከት መሆኑን፣ በዚህም አምስት ስምምነት ላይ ሊደረስባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ተለይተው ወደ ድርድር መገባቱን አስረድተዋል አምባሳደሩ። እልባት ያላገኙትና በድርድር ሂደት ላይ የሚገኙት አምስቱ ጉዳዮችም የስምምነቱ የተፈፃሚነት ወሰን፣ የአፈፃፀምና የክትትል ስርአቱ እንዲሁም የአሞላልና የውሀ አለቃቀቅ ስርአትን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች፣ የመረጃ ልውውጥ ስርአት፣ ክርክር ቢነሳ መፍትሄ የሚሰጥበት አሰራር እንዲሁም አምስተኛው የማጠቃለያ ድንጋጌዎች ናቸው ተብሏል። የተፈፃሚነት ወሰንን በተመለከተ በኢትዮጵያ በኩል የቀረበው የድርድር ሀሳብም፡ አንደኛ ድርድሩ በህዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የታጠረ እንዲሆን፣ ሰነዱ የውሀ ክፍፍልን ወይም ድርሻን የማይመለከት መሆኑን እንዲሁም የቀድሞ የቅኝ ግዛት ስምምነቶችን የማይመለከት መሆኑ በግልፅ እንዲቀመጥ በድርድር ሀሳብነት መቅረቡን አምባሳደሩ አስረድተዋል። በውሀ አለቃቀቅና ሙሌት ጉዳይ እንደ ሁኔታው ተለዋዋጭ ሊሆን ስለሚችል በሰነዱ ላይ መጠንን የሚገልፁ ቁጥሮች እንዳይቀመጡ በመጠየቅ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን ሊያስጠብቅ የሚችል ሀሳብ ማቅረቧንና ጉዳዩም ገና በድርድር ሂደት ላይ መሆኑም ተጠቁሟል። የመረጃ ልውውጥን በተመለከተም ኢትዮጵያ የሰጥቶ መቀበል መርህን የመጠቀም ፍለጐት እንዳላት አቋሟን ማሳወቋን፣ ይህም ጉዳይ ገና በሶስቱ ሀገራት መግባባት ያልተደረሰበት መሆኑ ተመልክቷል። በሶስቱ ሀገሮች መካከል ክርክር ቢነሳ የሚፈታበትን መንገድ በተመለከተ ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲና ድርድር መንገድን መከተል የሚል ማቅረቧን በግብፅ በኩል ደግሞ የሽምግልና ስርአትና የግድ ውሳኔ የሚሰጥበት አሰራር እንዲኖር ሀሳብ መቅረቡንና ገና በድርድር ሂደት ላይ ያለ ጉዳይ መሆኑም ተገልጿል። በድርድር ላይ ያለው መመሪያዎችንና ደንቦችን የተመለከተው የስምምነት ሰነድ ከአስር አመት በላይ ሊያገለግል የማይችል መሆኑና በሂደት የሚከለስበት አማራጭ እንዲኖር ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሀሳብ ማቅረቧንም አምባሳደሩ አስረድተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገዱ አንዳርጋቸው በበኩላቸው፤ በቀጣይም በግድቡ ጉዳይ መግባባት ላይ ለመድረስ ብቸኛው አማራጭ ድርድር ብቻ መሆኑን ነገር ግን የሚካሄደው ድርድር የኢትዮጵያን ጥቅም እስካስከበረ ድረስ ብቻ ኢትዮጵያ ተሳትፎዋን እንደምትቀጥል አስታውቀዋል። በዚሁ ጉዳይ የተለያዩ ምሁራን የራሳቸውን ምልከታና ምክረ ሀሳብ እያቀረቡ ሲሆን የኢንሼቲቭ አፍሪካ መስራቹ አቶ ክቡር ገና በፌስ ቡክ ገፃቸው ባቀረቡት ምክረ ሀሳብ፤ ኢትዮጵያ በድርድሩ ውስጥ ለመቆየት የተቻላትን ጥረት ማድረግ እንዳለባትና ጉዳዩ የሶስቱንም ሀገር ጥቅም ባስከበረ መልኩ በመግባባት መቋጨት የሚችልበትን መንገድ መፈለግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በድርድሩ መቆየት የመጀመሪያው አማራጭ ሊሆን ይገባል የሚሉት ሌላው የአባይ ጉዳይ ተንታኙ አቶ ፈቄ አህመድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ሌሎች ተጨማሪ አሸማጋዮችን ወደ ድርድር ማእቀፉ በመሳብ የአሜሪካንና የአለም ባንክን ጫና መገደብ ይኖርባታል ሲሉ ምክረ ሀሳብ ያቀርባሉ። በተጨማሪም ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ከግድቡ ጐን በማሳለፍም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ እንደ አጋዥ መሳሪያ መጠቀም ያስፈልጋል፣ መንግስት በዚህ በኩል ጠንካራ የህዝብ ንቅናቄ መፈጠር አለበት ይላሉ አቶ ፈቄ። የፖለቲካ ተንታኙ አቶ ሙሼ ሰሙም ህዝብን ለአንድ አላማ በማሰለፍ ጉዳይ ይስማማሉ። ለሰላምና ለጋራ ጥቅም የሚደራደር ማንነት እንጂ ድፍረት የተሞላበትና ሏላዊነታችንን የሚፃረር ትእዛዝ ለመቀበል ዝግጁ የሆነ ኢትዮጵያዊነት እንደሌለብን በጋራ በመቆም ማስመስከር አለብን የሚሉት አቶ ሙሼ፤ኢትዮጵያም ግድቡን አጠናቃ ውሀ ከመሙላት የሚያግዳት ሀይል እንደሌለ ማሳየት ያስፈልጋል ብለዋል። አንዳንድ የአሜሪካ ባለስልጣናትም ከወዲሁ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ጣልቃ ገብነትንና ተፅእኖን መቃወም ጀምረዋል። የአሜሪካ ኮንግረስ አባሉ ስቴቪን ሆርስፎርድ እንዲሁም በኢትዮጵያና በቡርኪናፋሶ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ዴቪድ ሺን፤ የአሜሪካ መንግስት በድርድሩ ለግብፅ እያደላ ነው ሲሉ በግልፅ ወቅሰዋል። አሜሪካ ሶስቱን አገራት ለማደራደር ከፈለገች የገለልተኝነት መርህን እንድትከተል፤ ይህን ካደረገች ኢትዮጵያ ወደ ድርድሩ ለመመለስ እንደማትቸገር ኮንግረስማን ሆርስፎርድ ገልፀዋል። በተመሳሳይ አምባሳደር ሼንም አገራቸው በኢትዮጵያ ላይ የምታሳርፈው ጫና ሊታረም ይገባል ብለዋል። ግብፅ በበኩሏ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ጥቅም ለማስከበር ማንኛውንም አማራጭ እንደምትጠቀም፣ ለዚህም ከጎኗ በርካታ ደጋፊ አገራት እንዳሉ በመግለፅ፣ ኢትዮጵያ በአሜሪካ የቀረበውን የስምምነት ሰነድ እንድትፈርም አስጠንቅቃለች። አያይዞም የአገሪቱ መንግስት የአረብ ሊግ በአባይ ጉዳይ ከግብፅ አቋም ጎን እንዲሰለፍ ከትናንት በስቲያ ጥሪ ያቀረበች ሲሆን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሹክሮ ኢትዮጵያ ስምምነቱን እንድትፈርም የአረብ ሊግ ተፅእኖ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።ኢትዮጵያ በሁለት ሺህ የተፈረመውን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነትን በመጣስ የግድቡን ስራ በማከናወን ላይ ትገኛለች ስትልም ግብፅ ለአረብ ሊግ ባቀረበችው የድጋፍ ጥያቄ አመልክታለች። የአረብ ሊግም ግብፅ በአባይ ውሀ ላይ ያላትን መብት ኢትዮጵያ እያሳጣቻት ነው በማለት ኢትዮጵያን የሚኮንን ውሳኔ ማሳለፉ የተገለፀ ሲሆን የአረብ ሊግ አባል የሆነችው ሌላኛው አገር ሱዳን በበኩሏ፤ የውሳኔ ሀሳቡ ኢትዮጵያን የሚያስቀይም ከመሆኑም በላይ የአገሯን ብሄራዊ ጥቅም የሚጋፋ መሆኑን በማመልከት ሀሳቡን እንደማትቀበለው አስታውቃለች። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የአረብ ሊግ በግድቡ ዙሪያ እየተደረገ ያለውን ድርድር ቁልፍ እውነታዎች ሳያገናዝብ በውሳኔ ሀሳቡ የሰጠው ጭፍን ድጋፍ እንዳሳዘነው አመልክቶ ሱዳን ያሳየችውን አቋም አድንቋል። የሊጉ ውሳኔም ተቀባይነት የሌለው ነው ሲል መንግስት ውድቅ አድርጎታል። ይህ ሁሉ የግብፅ ማስጠንቀቂያ፣ ማሳሰቢያና አቤቱታ እያለ ግን የህዳሴው ግድብን አሁንም በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑን መንግስት ያስታወቀ ሲሆን ሰባ አንድ በመቶ የግንባታ አፈፃፀም ላይ መድረሱንም ለማወቅ ተችሏል። በቀጣይ ክረምትም አራት ነጥብ ዘጠኝ ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሀ እንደሚገደብ እንዲሁም በመጋቢት ሁለት ሺህ የመጀመሪያ የሙከራ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀመርም የውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ አስታውቀዋል። | ኢትዮጵያና ግብፅ አምስት ጉዳዮች ላይ ተደራድረው መግባባት ይጠበቅባቸዋል |
አዲስ አበባ፣ ግንቦት ሀያ ሶስት፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ባለፉት ሀያ አራት ሰአት ውስጥ ሶስት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በሀያ አራት ሰአት ውስጥ በተደረገው ሁለት ሺህ ስምንት መቶ ስላሳ ስድስት የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ዘጠኝ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በዚህም በአጠቃላይ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች አንድሺህ አንድ መቶ ሰባ ሁለት ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎችም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ ዘጠና ዘጠኝኙ ከአዲስ አበባ ፣ ሁለት ሰዎች ከትግራይ ክልል ፣ አምስት ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል እና ሶስት ሰዎች ከሀረሪ ክልል ናቸው። ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ሁለት መቶ ዘጠኝ ደርሷል። ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የሶስት ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል ፤ አንደኛዋ የሀያ ዘጠኝ አመት በትግራይ ክልል የሰቲት ሁመራ ነዋሪ፣ ሁለተኛ የሰባ አምስት አመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ እና ሶስተኛ የሀምሳ አምስት አመት በደቡብ ክልል የከፋ ዞን ነዋሪ በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ናቸው። በመሆኑም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ደርሷል። የመጀመሪያ ሁለቱ ግለሰቦች በሆስፒታል ውስጥ ህክምና ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ሶስተኛው ህይወቱ ያለፈና ለአስክሬን ምርመራ ወደ ሆስፒታል የመጣና በተደረገልት ምርምራ የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ነው። የዜና ሰአት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዘናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልእክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ብለው ይላኩ። | በኢትዮጵያ ባለፉት ሀያ አራት ሰአታት በኮሮና ቫይረስ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አንድ መቶ ዘጠኝ ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል |
የኢህአዴግ መስራች አባል የሆኑት ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ህወሀት እና የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ የተናጠል ግምገማቸውን ከዚህ ሳምንት ጀምሮ እስከቀጣዩ ሳምንት እንደሚያከናውኑ ተጠቆመ። በዚህ ሳምንት ግምገማውን የሚጀምረው የህወሀት ማእከላዊ ኮሚቴ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ደግሞ ኦህዴድ ግምገማውን እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል። ኢህአዴግን ከመሰረቱት ፓርቲዎች መካከል በቀዳሚነት የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን በማካሄድ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል እንዲሁም በፓርቲው ውስጥ ያሉ ችግሮችን የገመገመው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ደኢህዴን መሆኑ ይታወሳል። ከዚህ በመቀጠል የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት ግምገማውን በማካሄድ በሳምንቱ መጨረሻ ላይ መግለጫ ማውጣቱ አይዘነጋም። በአማራ ክልል በስፋት ለተነሳው ተቃውሞ መንስኤ ናቸው በማለት የክልሉ ገዥ ፓርቲ ካስቀመጣቸው ምክንያቶች መካከል የመንግስትን ስልጣን የህዝብ ጥቅም ማስከበሪያ መሳሪያ በማድረግ ከመንቀሳቀስ ይልቅ፣ የመንግስት ስልጣን የኑሮና የጥቅም መሰረት ሆኗል የሚለው ይገኝበታል። ሌላው ዋነኛ ምክንያት ለህዝብ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ያለመስጠት መሆኑ በብአዴን መግለጫ ተጠቅሷል። በእነዚህ ችግሮች የተነሳ ተዳክሞ የነበረው የጠባብነትና የትምክህተኝነት አስተሳሰብና ተግባር ቀስ በቀስ እየሰፋ ሄዶ፣ የአመራሩንና የአባላትን አስተሳሰብ ማዛባቱን መግለጫው ይጠቁማል። ይህ አይነቱ አስተሳሰብ ቀላል ባልሆነ ደረጃ በመስፋፋቱም ህዝባዊና አገራዊ አንድነትን የሚያዳክሙ የተሳሳቱ ተግባራት መከሰታቸውን መረጃዎች አመልክተዋል። ህወሀት በዚህ ሳምንት በሚጀምረው የማእከላዊ ኮሚቴው ግምገማ በትግራይ ክልል የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን የሚቃኝ ቢሆንም፣ በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች ፀረ ትግራይ አመለካከቶች የመታየታቸው መንስኤና መፍትሄውን በጥልቀት እንደሚወያይ መረጃዎች አመልክተዋል። የአማራ ክልል ተቃውሞ የተቀሰቀሰው ከወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጋር ተገናኝቶ በተነሳው የወሰን ለውጥ ጥያቄ ቢሆንም፣ ይህ ጥያቄ በፍጥነት ባለመመለሱ በአጠቃላይ የገዢው ፓርቲን አስተዳደር ሙሉ በሙሉ ወደ መቃወም ተለውጧል። በዚህ ተቃውሞም በአማራ ክልል ውስጥ ቦታዎች የትግራይ ተወላጆች ላይ ትኩረት ያደረገ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ እነዚህን ተቃውሞዎች አስመልክቶ የአማራና የትግራይ ክልል ርእሰ መስተዳደሮችና በየደረጃው ያሉ አመራሮች ተጠያቂ እንደሚሆኑ መግለፃቸው ይታወሳል። በቀጣዩ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ በሚጀምረው ግምገማ ማጠናቀቂያ ላይ፣ ከፍተኛ የሆነ የአመራር ለውጥ እንደሚጠበቅ ምንጮች ለሪፖርተር ገልፀዋል። የፓርቲዎቹ የተናጠል ግምገማ ገዢው ፓርቲ ኢህኢዴግ ለሚያዋቅረው አዲስ ማእከላዊ ኮሚቴና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የመጀመሪያው እርምጃ እንደሚሆንም ተጠቁሟል። ኢህአዴግ አዲሱን አመት በማስመልከት ባወጣው መግለጫ፣ ኢህአዴግ የህዝብ ሏላዊነትን ጠንቅቆ የሚረዳና ለዚህም የታገለና እየታገለ ያለ ህዝባዊ ድርጅት መሆኑን ገልፆ፣ በመሆኑም ለህዝብ ጥያቄዎች ሁነኛ ምላሽ መስጠት የሚያስችለውን ጥልቅ ተሀድሶ ለማድርግ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታውቋል። ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢ የሆነ ምላሽ በመስጠት እርካታውን ለማረጋገጥ በከፍተኛ የሀላፊነት መንፈስና ቁርጠኝነት እንደሚሰራ በአዲሱ አመት ቃሉን በማደስ መሆኑን ገልጿል። ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግና ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ህገ መንግስታዊ ዋስትና ባገኙባት አዲሲቷ ኢትዮጵያ ሰላማዊ ኑሮን በሚያውክ መልኩ ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ሳያስፈልግ፣ ማንኛውንም ጥያቄ በህጋዊ መንገድ ብቻ በማቅረብና ከዚህ ውጪ ለሚደረጉ ማናቸውም እንቅስቃሴዎች በፅናት በመታገል የአገራችንን ህዳሴ ለማረጋገጥ እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንረባረብ ኢህአዴግ ጥሪውን ያቀርባል፤ ሲል በመግለጫው አስታውቋል። | የህወሀትና የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴዎች የተናጠል ግምገማቸውን ሊጀምሩ ነው |
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ ሀያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በአፍሪካ ህብረት የሚመራውና ለጊዜው ተቋርጦ የነበረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዛሬ እንደሚቀጥል የውሀ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንደገለፀውም በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለ ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ከሁለት ሳምንታት በፊት የተቋረጠው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ከሳምንት በፊት ሊቀጥል የነበረ ቢሆንም በሱዳን በኩል በቀረበው ለአንድ ሳምንት የይዘግይልኝ ጥያቄ መሰረት ለአንድ ሳምንት ዘግይቷል። በመሆኑም ተቋርጦ የነበረው ድርድር ዛሬ ከሰአት ጀምሮ ለቀጣይ አንድ ሳምንት እንደሚቀጥል ተገልጿል። የዚህ ሳምንት ድርድር ቀደም ሲል ከተካሄደው የ ቀናቱ ድርድር በኋላ ለመሪዎች በቀረበው ሰነድ መሰረት መሪዎቹ ባስቀመጠጡት አቅጣጫ የሚቀጥል እንደሆነም ታውቋል። ሚኒስቴሩ ኢትዮጵያ እንደ ከዚህ ቀደሙ ፍትሀዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረገ ሁኔታ ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ድርድሩን ለመቋጨት ትሰራለች ብሏል። የዜና ሰአት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዘናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልእክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ብለው ይላኩ። | ተቋርጦ የነበረው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዛሬ ይቀጥላል |
አስናቀ ፀጋዬ አዲስ አበባ፡ በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሀገሪቱ የሚታየውን የሲሚንቶ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም አመለከተ። በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የብረታ ብረትና ኬሚካል ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ ዱጋሳ ዶንሳ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፣ሚኒስቴሩ ከስድስት ወር በፊት በምርትና በአቅርቦት በኩል የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት መንስኤ ለማጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ኮሚቴ አቋቁሞ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በሀገሪቱ ያሉ ፋብሪካዎች ለረጅም ጊዜ የሚቆሙ፣ ገሚሶቹም ያረጁና መለዋወጫ የሚፈልጉ፣ የገበያ ፍላጎታቸውም በሶስት ኢንዱስትሪዎች ላይ መሰረት ያደረጉ መሆናቸውንና አብዛኛዎቹ ግንባታዎችም በተመሳሳይ ወቅት መከናወናቸው ችግሩ እንዲጎላ ማድረጉን ለማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል። የሲሚንቶ ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ልዩነት እንደነበር መረጋገጡን አመልክተዋል። የሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት በኩል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተወሰነ ሲሚንቶ ከውጭ ሀገር እንዲገባ መፍቀዱን ጠቁመው ፣ ከዚህ በፊት ተይዞ የነበረው የሲሚንቶ ኢንቨስትመንትም እንዲለቀቅ መደረጉንም አስታውቀዋል። በአማራ ብሄራዊ ክልል ደጀን አካባቢ የሚገኘው አባይ የሲሚንቶ ፋብሪካ ግንባታ እንዲፋጠንም የሀያ ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ተፈቅዶለት ግንባታው እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል። ቀደም ሲል የነበረውን የሲሚንቶ የማምረት አቅም ለመጨመርም የመለዋወጫ እቃዎች ከውጭ ሀገር እንዲገቡ ሰማኒያ አምስት ሚሊዮን ብር መመደቡንም ጠቁመዋል። የክረምቱን ወቅት ተከትሎ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ ያጋጠሙ የተፈጥሮ አደጋዎችና በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች እጥረቶች እንዳሉ ሆነው እነዚህን ስራዎች በመስራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ በበጀት አመቱ የሀገሪቱን አጠቃላይ ሲሚንቶ የማምረት አቅም ለማሳደግ ከያዘው ሰማኒያ አምስት በመቶ እቅድ ውስጥ ሰባ ዘጠኝ ያህሉን ማሳካት እንደቻለም ገልፀዋል። በነሀሴ ወር መጨረሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሲሚንቶ የመሸጫ መቁረጫ ዋጋ መመሪያ አውጥቶ እንደነበርም አማካሪው አስታውሰው፤ ዋጋው እንደገበያው መሆን እንዳለበት ታምኖ መመሪያው እንዲነሳ መደረጉንም ጠቁመዋል። የዋጋ መመሪያው ከተነሳ በኋላም የሲሚንቶ ዋጋው እንዳልወረደ ነገር ግን መመሪያው እንዳያሻቅብ ማድረጉን የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩ አመልክተዋል። አምና የተመረተውን ስምንት ነጥብ አምስት ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ ወደ ሜትሪክ ቶን በማሳደግ በአቅርቦቱና በፍላጎቱ መካከል ያለውን ክፍተት ለመማጥብ እየተሰራ እንደሚገኝም አማካሪው አስታውቀው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባስቀመጠው እቅድ መሰረት ባደረገው ጥረት ከዚህ ቀደም በሀይል መቆራረጥ ምክንያት ሲቆም የነበረውን የሲሚንቶ የማምርት አቅም ችግር ሙሉ በሙሉ መፍታቱን አመልክተዋል። ፋብሪካዎች ከውጭ የሚያስገቧቸውን የድንጋይ ከሰል የመሰሉ የኢነርጂ ምንጮችን በሀገር ውስጥ እንዲጠቀሙ ከመአድን ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ጥረት መደረጉንም አማካሪው ጠቁመዋል። በዚህም የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካን ሳይጨምር በቀን በአማካይ ሁለት መቶ አርባ ሺ ኩንታል ማምረት እንደተቻለም ጠቁመዋል። ሆኖም ምርቱ ከወጣ በኋላ የአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ አስታውቀዋል | በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ ሚኒስቴሩ አስታወቀ |
ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው የሶማሌ ክልል ውስጥ በርካታ አሰቃቂ ድርጊቶች ሲፈፀምበት እንደቆየ የሚነገርለት የጄል ኦጋዴን እስር ቤት ሀላፊ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ። ሀሰን ኢስማኤል ኢብራሂም ሀሰን ዴሬ አብዲ ሞሀመድ ኡመር በቁጥጥር ስር ዋሉ የቀድሞው የእስር ቤቱ ሀላፊ ሀሰን ኢስማኤል ኢብራሂም በቅፅል ስሙ ሀሰን ዴሬ ሶማሊያ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሎ ለኢትዮጵያ ተላልፎ በመሰጠቱ ወደ ጅግጅጋ ተወስዷል። ግለሰቡ ክስ ወደ ተመሰረተበት አዲስ አበባ ሊወሰድ እንደሚችልም ተነግሯል። ምንጮች ለቢቢሲ እንደተናገሩት ግለሰቡ የተያዘው ሶማሊያን ከኢትዮጵያ ጋር በምታዋስነው ጎልደጎብ ተብላ በምትጠራው የድንበር ከተማ ውስጥ ነዋሪዎች ለፀጥታ ሀይሎች በሰጡት ጥቆማ አማካይነት ነው። ግለሰቡ በሶማሌ ክልል ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥ በተለይ ደግሞ ጄል ኦጋዴን ተብሎ በሚታወቀው እስር ቤት ውስጥ ተፈፅመዋል በሚባሉ ሰቆቃዎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ውስጥ ዋነኛ ሚና አለው ተብሎ ሲፈለግ ቆይቷል። አቶ ገዱም ሆነ ደመቀ እኛም ብንፈተሽ ግድፈት አለብን ማለታቸውን አስታውሳለሁ የአቶ ታደሰ ጥንቅሹ ባለቤት ሀሰን ኢስማኤል ሀሰን ዴሬ የቀድሞውን የክልሉን ፕሬዝዳንት አብዲ መሀመድ ኦማርን ጨምሮ በሶማሌ ክልል ውስጥ በተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ምክንያት ክስ ከተመሰረተባቸው አርባ ያህል ተጠርጣሪዎች መካከል አንዱ እንደሆነም ተነግሯል። ግለሰቡ በቀድሞው የሶማሌ ክልል መስተዳደር ውስጥ በከፍተኛ የደሀነትና የፀጥታ ሀላፊነቶች ላይ በተለያዩ ጊዜያት የሰራ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የሶማሌ ክልል የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ፣ የማረሚያ ቤቶች ሀላፊ፣ የጄል ኦጋዴን ሀላፊ እና በክልሉ ልዩ ፖሊስ ውስጥም በኮሎኔልነት አገልግሏል። በሶማሌ ክልል የሚገኙ እስር ቤቶች በተለይ ደግሞ ጄል ኦጋዴን ውስጥ ተይዘው የነበሩ እስረኞች ላይ አሰቃቂ ድርጊቶች ይፈፀሙባቸው እንደነበር የፌደራል መንግስቱና የክልሉ መንግስት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ በረከት አናግረውናል የአቶ በረከት ስምኦን ባለቤት በእስር ቤቱ ይገኙ በነበሩ በመቶች በሚቆጠሩ እስረኞች ላይ ይፈፀሙ ከነበሩት ድርጊቶች መካከል ከመሬት በታች ባሉ ጨለማ ጉድጓድ ውስጥ ማስቀመጥ፣ የተለያዩ አይነት ሰቆቃዎች፣ ከአደገኛ የዱር እንስሳት ጋር እስረኞችን ማስቀመጥ፣ አስገድዶ መድፈርና የመሳሰሉ ድርጊቶች እንደነበሩ ተገልጿል። | በሶማሌ ክልል የጄል ኦጋዴን እስር ቤት ሀላፊ ተይዞ ለኢትዮጵያ ተሰጠ |
የጣሊያን የፋይናንስ ተቋም የብድር ዋስትና ሰጠ የጣሊያን ግዙፉ ኩባንያ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን፣ ጊቤ አራት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክት እንዲሰጠው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር ሲያካሄድ የቆየው ድርድር ተጠናቀቀ። ሳሊኒ በቅርብ ቀናት ውስጥ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር ስምምነት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል። ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ያካሄደ በመሆኑ የቴክኒክ ጉዳይ አሳሳቢ እንዳልነበረ ያስታወሱት የሪፖርተር ምንጮች፣ የድርድሩ ማጠንጠኛ ሆኖ የቆየው የፋይናንስ ግኝት ጉዳይ እንደነበር አመልክተዋል። ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ለዚህ ፕሮጀክት የሚያስፈልገውን በጀት አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዩሮ የጣሊያን ብድር ዋስትና አገልግሎት ሰጪ ተቋም ዋስትና እንደሚሰጥ መተማመኛ በማቅረቡ፣ በጥር ወር ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀና የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የህግ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ዋሲሁን አባተ የተገኙበት ልኡካን ቡድን ጣሊያን ሮም በመጓዝ ውይይት አድርጎ ተመልሷል። ምንጮች እንደገለፁት፣ የልኡካን ቡድኑ ከጣሊያን ብድር ዋስትና አገልግሎት ሰጪ ተቋም ጋር ባደረገው ውይይት ለፕሮጀክቱ ፋይናንስ አቅራቢ ተቋም ዋስትና ለመስጠት ፈቃደኛ መሆኑን አረጋግጧል። በዚሁ ምክንያት የፋይናንስ ጉዳይ መቋጫ አግኝቷል ተብሏል። በዚህ ሳቢያ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ሚኒስትሩ ዶክተር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የኤሌክትሪክ ቦርድ በዚህ ሳምንት መጀመርያ ፕሮጀክቱን ያፀድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ማረጋገጫ ባይገኝም በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያን የሚጎበኙት የጣሊያኑ ፕሬዚዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ በተገኙበት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይልና በሳሊኒ ኮንስትራክሽን መካከል የግንባታ ውል እንደሚፈረም ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን የመንግስታቸውን የግማሽ አመት ሪፖርት ለህዝብ ተወዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ሰነድ፣ ሁለት ሁለት መቶ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ያለው ፕሮጀክት ግንባታ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት እንደተጠናቀቀ ገልፀዋል። ፕሮጀክቱ በጥቂት ወራት ውስጥ በይፋ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢገልፁም ፕሮጀክቱ የቱ እንደሆነ ግን ምንም ሳይሉ አልፈዋል። የሪፖርተር ምንጮች እንደገለፁት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት ጊቤ አራት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ፕሮጀክትን በሚመለከት ነው። ከማምረት አቅሙ ሲሶ ያህል አምስት መቶ አርባ ሜጋ ዋት ማምረት የጀመረው ጊቤ ሶስት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ ቀጣይ ክፍል የሆነው ጊቤ አራት፣ በደቡብ ክልል በቱርካና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው። ቀድሞ በተካሄደ ጥናት ይህ ፕሮጀክት አንድ አራት መቶ ሀምሳ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል ቢባልም፣ በተደረገው የዲዛይን ክለሳ የማምረት አቅሙ ወደ ሁለት ሁለት መቶ ሜጋ ዋት ከፍ ማለቱ ታውቋል። ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ በሀምሌ ወር ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ይኼንን ፕሮጀክት ለማጥናት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር የመግቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። ነገር ግን በዚሁ ስምምነት ብቻ የግንባታ ውል ሳይፈፀም የአፈር ቆረጣ ስራዎችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ መዘገባችን ይታወሳል። | የጊቤ አራት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግንባታ ድርድር ተጠናቀቀ |
አዲስ አበባ፣ የካቲት ሀያ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በጋምቤላ ክልል የእንቦጭ አረም በውሀ አካላት ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው ማሀበረሰብ አባላት በጋምቤላ ክልል ጎግ ወረዳ በሚገኘው የታታ ሀይቅ ላይ የእንቦጭ አረም የማስወገድ ዘመቻ አካሂዷል። የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ጋልዋክ ጋርኮት እንዳሉት በክልሉ በሚገኙ የውሀ አካላት ላይ የእንቦጭ አረም እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በጉልበትና በምርምር ለማገዝ ዩኒቨርሲቲው እየሰራ ነው። በሀይቆች፣ ወንዞች እና ኩሬዎች ላይ አረሙ የሚያደርሰውን ጉዳት በጥናት በመለየት ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚሰራም ነው ገልፀዋል። የዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ዳይሬክተር ዶክተር ቾል ኬት በበኩላቸው አረሙን ለማስወገድ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር ለማፍለቅ እንደሚሰራ ጠቁመው ከተያዘው በጀት አመት ጀምሮ የእንቦጭ አረም ላይ ምርምር ለማካሄድ ተግባራዊ ስራ ተጀምሯል ብለዋል። መምህራንን በማሳተፍ ጭምር እንቦጭ አረም ላይ በሚካሄደው ምርምር ተመራቂ ተማሪዎችም ጥናታቸውን በእንቦጭ ላይ እንዲሰሩ እየተደረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የጎግ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኡጁሉ ጎራ እንቦጭ አረም በታታ ሀይቅ ላይ ባደረሰው ጉዳት ምክንያት የሀይቁ መጠነ ስፋት ከአራት መቶ ሀምሳ ሰባት ሄክታር ወደ ሁለት መቶ ሀምሳ አንድ ሄክታር ዝቅ ማለቱን አብራርተዋል። ሀይቁን ከመጥፋት ለመታደግ የመከላከል ስራው ውጤታማ እንዲሆን የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብር ይጠይቃል ማለታቸውን ማለታቸውን ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን | ዩኒቨርሲቲው የእንቦጭ አረም እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል እየሰራ ነው |
ፀጋዬ አራርሳፀጋዬ አራርሳ በኢሊባቡር በተፈፀመው ዘግናኝ ዘር ተኮር ግድያ ጀርባ ያለውን እውነት እንድንመረምር ፍንጭ ሰጥቶናል።እንዲህም ብሏልኦነግ እኛ ከኦህዴድ ጋር ያደረግነውን የስልጣን ክፍፍል ስምምነት ኦነግ በቅናት አይን እየተመለከተው ነው። የተቃውሞ ሰልፉንም የጠራው የኦነግ ክንፍ የሆነው ነው ሲል ይፈርጃል።ጥቅምት በ ላይ እኦህዴድ ኦነግን ለመደምሰስ ከህወሀት ጋር ሰርቷል።በ ኦነግ ኦህዴድን ለማጥፋት ከህወሀት ጋር ወግኗል።ወዳጅ ጠላት ጠላትም ወዳጅ እየሆነ ነውይለናል።ጥቅምት ኦነግ የህወሀት አጋር ኦህዴድም የኦሮሞ አክቲቪስቶች ስልጣን ተጋሪና ተባባሪ ነው ከተባልን ጉዳዩ ወደ ኤሊባቡር ንፁሀን አማሮች ጭፍጨፋ ላይ የማን እጅ እንዳለበት ሁለት ምክንያታዊ ግምቶችን እንድናጤን ግድ ይለናል። ሰልፉን የጠራውና ያደራጀው ኦነግ ነው። ግድያው የተፈፀመው በዚህ ሰልፍ ባለበት አካባቢ ነው። ኦነግ ከህወሀት ጋር ወግኗልከተባልን ግድያውን ሊያቀነባብሩት የሚችሉት ኦነግና ህወሀት በጋራ ነው ማለት ነው። እነ ፀጋዬ አርአርሳና አክቲቪስቶች በኦነግ የተጠራውን ሰልፍ እንደማይደግፉት በመግለፅ ከኦህዴድ ጋር ያደረጉት የስልጣን ክፍፍል ስምምነት ካለ ኦነግና ህወሀት በአንድ ጎራ ኦህዴድና አክቲቪስቶቹ በሌላ ጎራ ሆነው የኦሮሞ ወገኖችን ድጋፍ ለማግኘት እየተናጩ ነው ማለት ነው።ስለዚህ የኤሊባቡር ንፁሀን አማሮች ጭፍጨፋ የተከናወነው በዚህ የስልጣን ሽኩቻ መሀል በመሆኑሀ አንድም ኦነግና ህወሀት ከእጃቸው የወጣውን ተቀባይነት ለመመለስ ሲሉ በጋራ ማለትም ከዚህ በፊት በአርባጉጉ አማሮች ላይ በጋራ እንዳደረጉት ጭፍጨፋወይምለ ኦህዴድና አክቲቪስቶቹ የኦነግና የህወሀትን ጥምረት ሚዛን ለማሳጣትና እቅዳቸውን ለማክሸፍ በሚስጥር እጃቸውን ከተዋል እርምጃውን ወስዷል ማለት ነው።ሁሉም ግምቶች ወደዚህ ያመራሉ። ለማንኛውም ሁሉም ክስተት እነዚህ አራት ተዋናይ ሀይሎች ያራግቡ የነበረውና እያራገቡም ያለው የጎሳ ፖለቲካና ጥላቻ መራር ውጤት ነው። በበደኖ ጉራፈርዳ ወዘተ የታየም ነው። ለዚህ ነው እነዚህ ሀይሎች አንድም አራትም ናቸው ማለት የምንደፍረው። | ከኤሊባቡር ንፁሀን አማሮች ጭፍጨፋ በስተጀርባ |
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ታላላቅ ሀይማኖታዊ በአላት መካከል አንዱ የሆነው የደመራ በአል በዛሬው እለት በመላ አገሪቱ ተከብሮአል። የደመራ በአል ንግስት ኢሌኒ እየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል ለመፈለግ የተጠቀመችበትን ደመራ እና የእጣን ጭስ ለመዘከር የሚደረግ ሀይማኖታዊ በአል ነው። የቤተክርስቲያኗ መፅሀፍት እንደሚያመለክቱት ግማደ መስቀሉ በአፄ ዳዊትና በልጃቸው ባአፄ ዘርአያቆብ በአስራ አምስተኛም ምእተ አመት መግቢያ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል። በአዲስ አበባ ዛሬ በተከበረው የደመራ በአል ላይ በርካታ ጎብኝዎች ስርአቱን ተከታትለውታል። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም በቀጥታ ስርጭቱ አንድ ጊዜ የአቶ መለስ ዜናዊን ፎቶ ግራፍ ሌላ ጊዜ የበአሉን ስነስርአት እያፈራረቀ ለህዝብ አቅርቧል። | የደመራ በአል በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ተከበረ |
አዲስ አበባ፣ መጋቢት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በማረሚያ ቤቶች ለመከላከል ይቻል ዘንድ አራት ሺህ የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንደሚለቀቁ አስታወቀ። የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በጉዳዩ ላይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እነዚህ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲለቀቁ የይቅርታ ቦርድ ለሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት አቅርቦ ማስፀደቁን አስታውቀዋል። የሚለቀቁት የህግ ታራሚዎች በቀላል ወንጀል እስከ ሶስት አመት ድረስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ፣ በማረሚያ ቤት ቆይተው የአመክሮ ጊዜያቸው እስከ አንድ አመት የሚቀረው፣ በግድያ ወንጀል ያልተሳተፉ የሚያጠቡ እናቶች፣ ነብሰ ጡሮች እና የውጭ ሀገር ዜጎች መካተታቸውን ነው ያመለከቱት። በይቅርታ የሚለቀቁ የውጭ ሀገራት ዜጎችም ወደየሀገራቸው እንደሚላኩ ገልፀዋል። በተጨማሪም የሚያጠቡ እናቶች ሆነው በእስር ላይ የሚገኙ ሰባት ሴቶች እና በሙስና ወንጀል በተባባሪነት የተሳተፉ ሴቶችም አሁን ካለው ችግር አንፃር ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን ጠቁመዋል። እነዚህ ዜጎች ከማረሚያ ቤት ሲወጡ ተገቢው ምርመራ እንደሚደረግላቸው፣ በቫይረሱ ተጠርጣሪዎች ካሉ ወደ ለይቶ ማቆያ እንደሚሄዱ፣ ከህብረተሰቡ ጋር ሲቀላቀሉም ከወንጀል እንዲጠበቁ ዝርዝራቸው በየአካባቢው ለፖሊስ እንደሚሰጥ እና ህግ ተላልፈው ከተገኙ ይቅርታቸው ተሰርዞ በህግ እንደሚጠየቁ ወይዘሮ አዳነች ተናግረዋል። በሀይለየሱስ መኮንን ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ | የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በማረሚያ ቤቶች ለመከላከል አራት ሺህ የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንደሚለቀቁ አስታወቀ |
ግንቦት ፲፬ አስራ አራት ቀን ፳፻፮ አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ከትናንት በስቲያ ከመደበኛ የስራ ሰአት ውጭ ከጧቱ አንድ ሰአት ተኩል ላይ ወደ ቢሮአቸው በመግባት ራሳቸውን ከሁለትኛ ፎቅ ወርውረው የገደሉት የስልሳ ሁለት አመቱ ዲፕሎማት አቶ ፍሰሀ ተስፉ ስለ አሟሟታቸው መንስኤ መንግስት እስካሁን ይፋዊ መግለጫ አልሰጠም። ክሮናካ ዲ ሮማ የተባለው የጣሊያን ጋዜጣ ዛሬ ይዞት በወጣው ሰፊ ዘገባ ዲፕሎማቱ ከመሞታቸው ከሁለት ቀናት በፊት ከስራ ተነስተው ወደ አገራቸው እንደሚመለሱ ተነግሮዋቸው እንደነበር አንዳንድ ጓደኞቻቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። ሌሎች የስራ ባልደረቦቻቸው ግን ዲፕሎማቱ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ስለመታዘዙ እንደማያውቁ ተናግረዋል። ጋዜጣው እንደዘገበው ዲፐሎማቱ ራሱን ያጥፋ ወይም ሌላ ሰው ይግደለው እንደማይታወቅ ገልፆ፣ ራሱን ካጠፋ ግን አንድ መልእክት ለማስተላለፍ አስቦ ያደረገው ሊሆን እንደሚችል የፖሊስ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። በዲፕሎማቱ ቢሮ ውስጥ ምንም አይነት ማስታወሻ አለመገኘቱን፣ የተዘበራረቀ ነገር አለመኖሩንም የገለፀው ጋዜጣው፣ የረጅም ጊዜ ዝግጅት የተደረገበት ነበር ብሎ ለመናገር እንደማይቻልም አትቷል። ፖሊስ ኢምባሲውን በመዝጋት ካለፉት ሁለት ቀናት ጀምሮ ምርመራ በሰራተኞች ላይ እያደረገ ይገኛል። ዲፕሎማቱን ያገኙት የኢምባሲው ሰራተኞች ሲሆኑ ከሞተ ከአንድ ሰአት በኋላ አምቡላንስ በቦታው ቢደርስም የዲፕሎማቱን ህይወት ለማትረፍ እንዳልተቻለ ታውቋል። አንዳንድ ጣሊያን ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ግለሰቡ ራሱን አጥፍቷል ብለው እንደማያምኑ እየተናገሩ ነው። አቶ ፍስሀ ወደ ኢጣሊያ ከመዛወራቸው በፊት በአውሮፓ ህብረት ዴስክ ኦፊሰር ሆነው ከሰሩ በኋላ፣ የአለማቀፍ ተቋማት ጊዜያዊ ዳይሬክተር እንዲሁም የዲያስፖራ ክፍል ዳይሬክተር ጄኔራል ሆነው ሰርተዋል። አቶ ፍስሀ የህወሀት አባል መሆናቸውን አንዳንድ ወገኖች ይገልፃሉ። | በጣሊያን ራሳቸውን እንዳጠፉ የተነገረላቸው ኢትዮጵያዊው ዲፕሎማት አሟሟት መንስኤ በውል አልታወቀም |
አማርኛ ተናጋሪዎችን የማመናመን የማደህየት የማራቆትና ክልላቸውን እያሳነሱ የማጥፋት እቅድ በህወሀት መርሀግብር ውስጥ የተካተተ ዋና ተግባር እንደሆነ ተገለፀ። አማርኛ ቋንቋንም ማሽመድመድ የዚሁ እቅድ አካል መሆኑ ተዘግቧል።አቶ ገመድህን አርአያ ከኢሳት ሬዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ በህወሀት ፕሮግራም ገፅ አካባቢ አማራ የትግራይና የኤርትራ ህዝብ ጠላት እንደሆነ ተመልክቷል ብለዋል። አያይዘውም አማራ ማጥፋት የቅስቀሳው ዋና መሳሪያ ቢሆንም የትግራይ ህዝብ አልተቀበለም ብለዋል። ቅስቀሳውን አንቀበልም ያሉ የትግራይ ሸዋ ተብለው መገደላቸውን ይፋ አድርገዋል።በተለይ የድርጊቱ ዋና አስተባባሪ በማለት የጠቀሷቸው አቶ መለስ ዜናዊ አቶ ስብሀት አቶ ስዩም መስፍን አቶ አባይ ፀሀዬን የጠቀሱት አቶ ገመድህን በ በሰሜን ጎንደር የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈፀሙን አጋልጠዋል። በወቅቱ የተካሄደው ጭፍጨፋ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሆነም አመልክተዋል። በሰላም እጃቸውን የሚሰጡ ወታደሮች እንኳ አማርኛ የሚናገሩ ከሆነ ይረሸኑ ነበር ሲሉ እነ መለስ ያለቸውን በዘር ላይ የተመሰረተ ቆሻሻ አመለካከት አጋልጠዋል።ኢትዮጵያ የምትበተነው አማራ ሲጠፋ ነው በሚለው የነመለስ ሀሳብ መተግበር የጀመረው ህወሀት አዲስ አበባ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑንን ያወሱት አቶ ገመድህን ህወሀት ያሰማራቸው ከሺህ በላይ ካድሬዎች ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ አማራዎች በተለያዩ ምክንያቶች እንዲጨፈጨፉ ማድረጋቸውን አመልክተዋል።ብአዴንን አማራን ለማጥፋት የተፈጠረ ፀረ አማራ ድርጀት ሲሉ የሰየሙት አቶ ገመድህን አመራሮቹ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች መሆናቸውን በርግጠኛነት ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የተወከለው በባንዳ ልጆችና የኤርትራ ተወላጆች ነው ሲሉም ህዝቡ አደጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱን የባሻ ወልዱ ልጅ ነው በማለት የትግራይ ህዝብ በባንዳ ኤርትራዊ ልጅ እንደሚመራ ያመለከቱት አቶ ገመድህን ብርሀነ ገብረክርስቶስ ቴድሮስ ሀጎስ ቴድሮስ አድሀኖም በማለት በመዘርዘር የባንዳ ልጆች መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል።አማራው የሚኖርበትን መሬት በመውሰድ መሬቱን ያጠቡበታል ከሌላው ክልል በማባረር የሚኖርበትን ክልል ያጠቡታል ያሉት አቶ ገመድህን ይህ የሚደረገው ከመጀመሪያው እንዲጠፋ የተወሰነበትን ህዝብ አጥብቦ በማፈን በችግር ለመግረፍና ለመቆጣጠር ተብሎ እንደሆነ ገልፀዋል።ዘር የማጥራት የህወሀት የቀደመ ድርጅታዊ መዋቅር እንደሆነ በማመልከት መለስን የጠቀሱት አቶ ገመድህን አማራውን ዝም ካልነው አያስቀምጠንም የሚለው የመለስ መፈክር አካል የሆነው የቤኒሻንጉል ክልል ርምጃ የህወሀት ቤት ስራ እንደሆነ አረጋግጠዋል። አማራውን ፋታ ማሳጣት ማንገላታት ስነልቦናውን መግፈፍ ህወሀት በፕሮግራም ደረጃ የያዘው እቅድ ስለሆነ ወደፊትም እንደሚቀጥል አቶ ገመድህን ተናግረዋል።ሞት መፍራት አያስፈልግም። የተቀደሰ ሞት መሞት ክብር ነው ሲሉ በቃለ ምልልሳቸው መጨረሻ የተናገሩት የቀድሞው የህወሀት የፋይናንስ ሀላፊ ህዝቡ ተባብሮ ህወሀትን ማስወገድ ካልቻለ ማፈናቀሉና መሰደዱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቀዋል።ማሳሰቢያ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገፅ ጋዜጣ ላይ የሚወጡት ፅሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገፅ ጋዜጣንብረት ናቸው። ይህንን ፅሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ፅሁፍ አስፈንጣሪ ወይም የድረገፃችንን አድራሻ አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሰራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን። | አማራንና አማርኛን ማጥፋት የህወሀት ፕሮግራም ነው |
የአገሪቱ ባለሙያዎችና ድርጅቶች እስከ ሀምሌ ይመዝገቡ ተባለበፌደራል ዋና ኦዲተር ጄነራል በብሄራዊ ባንክና በሌሎችም ተቋማት ለሂሳብ ባለሙያዎችና ለኦዲተሮች የሙያ ፈቃድ የብቃት ማረጋገጫና መሰል የእውቅና አሰጣጥ ስርአት በመሻር ለአዲሱ የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ የሰጠው አዋጅና እሱን ተከትሎ የወጣው ደንብ መተግበር ጀመረ። ለአዲሱ ቦርድ የቦርድ አባላትና የስራ ሀላፊዎች ተሹመውለታል።የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አለማየሁ ጉጆ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት ቦርዱ ለብቻው ተለይቶ በሂሳብ ሙያና በኦዲት አሰራር ላይ የበላይ አካል ሆኖ እንዲሰራ የተቋቋመው የህዝብ ጥቅም ባለባቸው በመንግስት የልማትና በግል ድርጅቶች ላይ ተፈፃሚነት ያለው አንድ ወጥ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ እንዲኖር ለማስቻል ነው። በመሆኑም በመላ አገሪቱ አንድ ወጥ የፋይናንስ ሪፖርት ስርአት የሚዘረጋ ሲሆን የፋይናንስ ስርአቱም አለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ደረጃዎችን እንዲከተል ለማድረግ ቦርዱ መመስረቱን አቶ አለማየሁ ገልፀዋል።መንግስታዊ የልማት ድርጅቶችና የግል እንዲሁም የውጭ ድርጅቶች ከዚህ ቀደም በተለያየ መለኪያ የሚለኩበት የሂሳብ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ስርአት ከእንግዲህ አይኖርም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በሌሎች አገሮችም እንደሚደረገው የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብን የሚመራ ራሱን የቻለ ተቋም መመስረት ወደፊት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የኢኮኖሚ ቀውሶችን ለመቀነስ እንዲቻልም የሚረዳ ነው ብለዋል።አዲሱ ቦርድ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ያሉት ሲሆን አባላቱ ከመንግስት መስሪያ ቤቶች ከግሉ ዘርፍ ከሂሳብና ኦዲት ባለሙያዎችና ለሙያው ቅርበት ካላቸው አካላት የተወጣጡ አባላት መሆናቸው ሲታወቅ የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድን በዋና ስራ አስፈፃሚነት የሚመራ ግለሰብ በዳይሬክተርነት ከመቅጠሩም ባሻገር ባለሙያዎችን እያካተተ እንደሚገኝ አቶ አለማየሁ ጠቅሰዋል።ከዚህ ቀደም በፌደራል ዋናው ኦዲተር ጄነራል ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረት ለሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች ፈቃድ የመስጠትና የማደስ ስልጣን ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን ቦርዱን ለማቋቋም በወጣው የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁጥር መሰረት መሻሩን አቶ አለማየሁ አብራርተዋል። ከዚህ ባሻገር በኢትዮጵያ ንግድ ህግ በመንግስት ልማት ድርጅቶች በምርት ገበያ ባለስልጣን ማቋቋሚያ አዋጅ በኤክሳይስ ታክስ አዋጅ በገቢ ግብር አዋጅ በባንክ ስራዎች አዋጅ በመንድን ስራ አዋጅ እንዲሁም በክፍያ ስርአት አዋጅ ውስጥ ስለ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት የተደነገጉ አንቀፆች መሻራቸው ታውቋል።የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅን የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድን አሰራርና አላማዎች ለማስረዳት መጋቢት ቀን አመተ ምህረት በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተጠራ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። የሚመለከታቸው የፌደራልና የክልል መስሪያ ቤቶች ተሳትፈዋል። ጥያቄዎችንም ለሚኒስትር ዴኤታውና ለባልደረቦቻቸው አቅርበዋል። ከተነሱት ጥያቄዎች መካከልም በአዋጁ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶችን አይመለከትም መባሉ በምን አግባብ እንደሆነ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል። ከዋናው ኦዲተር ጄነራል በመውሰድ የክልል ኦዲተር ጄነራሎች ለባለሙያዎች ፈቃድና እድሳት እየሰጡ እንደሚገኙ በመጥቀስ እጣ ፈንታቸው ምን እንደሚሆን ጠይቀዋል።አቶ አለማየሁ በምላሻቸው እንደገለፁት ቦርዱ በተማከለ አሰራር እየተንቀሳቀሰ በክልሎች ቅርንጫፎችን እንደሚከፍትና በመላው አገሪቱ ከአሁኑ በኋላ ከቦርዱ በስተቀር የሙያ ፈቃድ የመስጠትና የማደስ ስልጣን ሌሎች የክልል መስሪያ ቤቶች እንደማይኖራቸው አረጋግጠዋል። ቀደም ሲል ክልሎች በነበሯቸው ህጎች መሰረት ለኦዲተሮችና ለፋይናንስ ሪፖርት አቅራቢዎች ፈቃድ መስጠታቸውን ያቆማሉ። ህጎቻቸውንም ማሻሻል ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከዚህ ቀደም በነበራቸው የኦዲትና የሂሳብ አዘገጃጀትና አቀራረብ ስርአት መሰረት ይቀጥላሉ ስለመባሉ ምክንያትአዊነት ያስረዱት ሚኒስትር ዴኤታው ይህ የተደረገው ከሌሎች አገሮች ልምድ ተወስዶ ነው በማለት ምላሽ ሰጥተዋል።በመሆኑም የሚኒስትሮች ምክር ቤት አዲሱን ቦርድ ለማቋቋም ጥር ቀን አመተ ምህረት ባወጣው ደንብ ቁጥር መሰረት በስራ ላይ ያሉ የኦዲት ድርጅቶችና ኦዲተሮች የሂሳብ ባለሙያዎችና የፋይናንስ ሪፖርት አቅራቢዎች እስከ መጪው ሀምሌ ቀን አመተ ምህረት ማመልከቻቸውን ለቦርዱ በማቅረብ መመዝገብና ፈቃድ የማግኘት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማመልከቻ ያላቀረቡ ፈቃድ አያገኙም ተብሏል። ከዚህ ባሻገር አዲስ ፈቃድ መስጠት እንደቆመና ለነባር ባለሙያዎችና ድርጅቶች በትምህርትና ስልጠና ላይ ለሚገኙትም ጭምር በቦርዱ የሚቀመጡ መስፈርቶችን ማሟላት የማይችሉ ከሆነ ግን እስከ አምስት አመት የሚቆይ የእፎይታ ጊዜ መሰጠቱንና በዚያ ጊዜ ውስጥ የአገሪቱ የሂሳብ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መስፈርቶችን አሟልተው መገኘት እንደሚገባቸው ተመልክቷል። | የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮችን የሚቆጣጠር አዲስ ቦርድ ተቋቋመ |
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በስግብግቡ ጁንታ የህወሀት ሀይል ላይ የተደረገው የመጀመሪያው ዙር ዘመቻ በስኬት መጠናቀቁን አስታወቁ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ፤ የአየር ሀይል በወሰደው እርምጃ በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ማውደም መቻሉን ገልፀዋል።ሮኬቶቹ እስከ ሶስት መቶ ኪሎ ሜትር መወንጨፍ የሚችሉ በመሆናቸውና በወንጀለኛው ቡድን ሮኬቶቹን የመጠቀም ፍላጎት በመኖሩ በመቐለና አካባቢዋ በነበረው የከባድ መሳሪያ ማስቀመጫ ላይ የአየር ሀይሉ እርምጃ እንዲወስድ መደረጉ ተገልጿል።ከህወሀት ጋር ከእንግዲህ ድርድር እንደማይኖርና ጉዳዩ ፌደራል መንግስት በሚወስደው ህግን የማስከበር እርምጃ ብቻ ይፈታል የተባለ ሲሆን መከላከያ ሰራዊት ሰላማዊ ዜጐች በማይጐዱበት ሁኔታ ተልእኮውን በጥንቃቄ ይወጣል ተብሏል። በመከላከያ ሰራዊት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግልፅ፣ የተወሰነና ሊደረስበት የሚችል አላማ ያለው መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትርኒስትሩ ትናንት በትዊተር ገፃቸው ያመለከቱ ሲሆን እርምጃውም በሀገሪቱ ህግና ስርአትን ለማስፈን ያለመ ነው ብለዋል። መንግስት ወደ ሀይል እርምጃ ከመግባቱ በፊት ከህወሀት ጋር ያለውን ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለወራት ታግሶ ድርድርና ሽምግልና ሲያካሂድ መቆየቱን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትርኒስትሩ፤ ይሁን እንጂ መንግስት ያደረገው ጥረት በሙሉ በህወሀት እምቢተኝነት መክሸፉንም ገልፀዋል። የመንግስት ወቅታዊ አቋም ይፋ ያደረገው የመንግስት መግለጫ በበኩሉ ህወሀት ድብቅ ሴራ ሲያራምድ ቆይቷል፤ አሁንም እያደረገው ነው፤ ከአንድነት ይልቅ የብተና ፖለቲካ በማራመድ ህዝብን እርስ በእርስ በማጋጨት ለሞትና መፈናቀል ዳርጓል ይላል። ከለውጡ ማግስት ጀምሮም ይህን እኩይ አላማ ይዞ መንግስትን በተለያዩ ጉዳዮች ውጥረት ውስጥ በመክተት ወደ ኋላ ለመጐተት ያለማቋረጥ ትንኮሳ ሲፈፀም መቆየቱንም መግለጫው ያትታል። የፌደራል መንግስት በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ በሆደ ሰፊነት ነገሮችን ለማለፍ መሞከሩን፣ ለእርቅና ለሰላም ጥሪ ሲያቀርብ መቆየቱን፣ በተለያዩ አካላትም የሰላም ጥሪ በተደጋጋሚ መቅረቡን፤ ነገር ግን እነዚህን ሁሉ ህወሀት ሳይቀበላቸው መቅረቱም ተመልክቷል። ይባስ ብሎ በህገ ወጥ መንገድ ምርጫ ማካሄዱን፣ ከዚህም አልፎ የሀገሪቱ ኩራት የሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ተኩስ በመክፈት፣ የሀገር ሏላዊነትና ክብርን መዳፈሩን የጠቆመው መግለጫው፤ የህወሀት ቡድን በተለያዩ እኩይ ድርጊቶቹ ሀገሪቱን በግልፅ ለማፈራረስ መንቀሳቀሱን ያመለክታል። ከእንግዲህ በኋላ ግን ይህ ሀገርን የማፍረስ እንቅስቃሴ አይፈቀድለትም ያለው መንግስት፤ አስፈላጊው ሁሉ እርምጃ እስከመጨረሻው ተወስዶ የህግ የበላይነት እንደሚከበር ነው በአቋም መግለጫሙ ያስገነዘበው።በህወሀት ቡድን ላይ የሚደረገው የህግ የበላይነትን የማስከበር ተልእኮ ያለ ምንም ድርድር እንደሚከናወን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትርኒስትሩ በበኩላቸው፤ ሀሙስ እለት የተለያዩ የዲፕሎማቲክ አካላት ለድርድር እንዲቀመጡ ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸውንም ሲኤንኤን ዘግቧል።የህወሀት ቡድን በሰሜን እዝ ላይ የፈፀመው ክህደትና ወረራ በብቃት መመከቱን የገለፁት የመከላከያ ሰራዊት ምክትልኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ በበኩላቸው፤ ሀገራችን ያላሰበችው ጦርነት ውስጥ ገብታለች፣ ጦርነቱ አሳፋሪና አላማ የሌለው ነው ብለዋል። መከላከያ ሰራዊቱ ተልእኮውን ሰላማዊ ዜጐች በማይጐዱበት ሁኔታ በጥንቃቄ ያከናውናል ያሉት ጀነራል ብርሀኑ ጁላ፤ የትግራይ ወጣቶች በዚህ ጦርነት እንዳይሳተፉ ለሀገራቸው ኢትዮጵያ ዘብ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። የህወሀት ቡድን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ባደራጃቸው ቡድኖች ያልታሰቡ ጥቃቶችን ሊያደርስ ስለሚችልም ሁሉም ህብረተሰብ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ጀነራል ብርሀኑ ጁላ አሳስበዋል። የፌደራል ፖሊስ ትናንት በሰጠው መግለጫም፤ የህወሀት ፅንፈኛ ቡድን በትላልቅ ከተሞች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሀይል ማሰማራቱ መረጋገጡን አስታውቋል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንዳሻው ጣሰውና የኮማንድ ፖስቱ ፕሬስ ሴክሬቴሪያት ትናንት በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ቡድኑ የሽብር ሀይል ወደተለያዩ ትላልቅ ከተሞች ማሰማራቱንና ከእነዚህ ሀይሎችም የተወሰኑት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል። ህወሀትና ኦነግ ሸኔ ከሀገር ውስጥም ከውጭ በሚደረግላቸው የፋይናንስ ድጋፍ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች ባለፉት ሁለት አመታት ጥፋት ሲፈፀም ቆይተዋል ብለዋል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል። ጥቅምት ሀያ አራት ቀን ሁለት ሺህ በትግራይ ክልል ከሀያ ሁለት በላይ ተቋማት በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ሀይል ጥቃት ከመፈፀሙ በተጫማሪ ከፍተኛ የንብረት ዝርፊያ መፈፀሙ ነው ኮሚሽሩ በግለጫው ያመለከቱት።በአሁኑ ወቅት በህወሀት የተከፈተው ጦርነት ለመመከት የመከላከያ ሰራዊት ፌደራል ፖሊስ እና የክልል የፀጥታ ሀይሎች በተቀናጀ መልኩ እየወሰዱ ባለው እርምጃ አብዛኞቹ በቁጥጥር ስር መዋሉንና የተቀረውንም በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ኮሚሽነር ጀነራሉ አስገንዝበዋል። ውጥኑንም ሙሉ ለሙሉ ለማክሸፍ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ህብረተሰቡም ከፀጥታ ሀይሉ ጐን በመቆም ድጋፉን እንዲያሳይ ኮሚሽነሩ አሳስበዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መከላከያ ሰራዊት በተለያዩ አቅጣጫዎች ተልእኮ ተቀብሎ መሰማራቱንና ትናንትም ጠንካራ እርምጃዎች ሲወስድ መዋሉን ነው መንግስት ያስታወቀው። የመቀሌ አየር ማረፊያን ጨምሮ በትግራይ አየር ክልል ውስጥ ማንኛውም አውሮፕላን እንዳይበር የፌደራል ሲቪል አቪየሽን ትእዛዙንም አስተላልፏል። የሱዳን መንግስትም በከሰላ በኩል ያለውን ድንበሩን ሙሉ በሙሉ መዝጋቱን ሱዳን ፖስት አታውቋል። | በህወሀት ሀይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ዘመቻ በስኬት ተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትር |
አዲስ አበባ፣ሚያዚያ አስር፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢሲ በመዲናዋ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ የግለሰብን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ቆርጠው ሀይል አቋርጠዋል የተባሉ ሶስት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ። በክፍለ ከተማው ወረዳ ስድስት ልዩ ቦታው ጨው በረንዳ አካባቢ ተጠርጣሪዎቹ ወደ ግል ተበዳይ መኖሪያ ቤት በመምጣት ቆጣሪ ልናነብና ልንመረምር ነው ካሉ በኋላ የኤሌክትሪክ ቆጣሪውን አይተው ስላሳ ሶስት ሺህ ብር እንደቆጠረ ለግል ተበዳይ ነግረዋቸዋል ነው የተባለው። የግል ተበዳይም ያልተጠቀሙበትን ፍጆታ እንደቆጠረባቸውና ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ሲያስረዷቸው ከተፈቀደልህ በላይ ሀይል ጨምረህ ተጠቅመሀል በማለት የሁለት ቆጣሪዎች ሀይል እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር እሱባለው ጌትነት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ባለሙያዎቹ ሺህ ብር እጅ መንሻ ጉቦ ከሰጧቸው እንደሚያስተካክሉላቸው ለግል ተበዳይ ነግረው ገንዘብ መጠየቃቸውን የጠቀሱት ምክትል ኢንስፔክተሩ የግል ተበዳይም ይህን ያህል ገንዘብ እንደሌላቸው እና አስር ሺህ ብር እንዲያደርጉላቸው ተደራድረው ከጠየቋቸውም ገንዘብ ውስጥ አምስት ሺህ ብር ሲቀበሉ ቀደም ብለው ጉዳዩን ለፖሊስ አሳውቀው ስለነበር ከነ ገንዘቡ እጅ ከፍንጅ ሊያዙ መቻላቸውን አብራርተዋል። ህዝብ እና መንግስት የጣሉባቸውን ሀላፊነት ወደጎን በመተው ህብረተሰቡን የሚያማርሩ ግለሰቦችን ለህግ አጋልጦ በመስጠት ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ የሁላችንም ሀላፊነት ነው ሲሉ የግል ተበዳይ መናገራቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። | ሶስት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ፖሊስ ገለፀ |
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የምሁራን ሚና ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የበይነ መረብ ምክከር እየተካሄደ ነው። ውይይቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። በውይይቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ ፣የውሀ፣ መስኖ እና ኢነርጅ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሽ በቀለን ጨምሮ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ የስራ ኀላፊዎች እየተሳተፉ ነው። በዚህም የህዳሴ ግድብን ተከትሎ እየደረሰ የሚገኘውን ጫና ለመመከት የሚያስችል እና የዲጅታል ዲፕሎማሲውን ለማጠናከር ያለመ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማእከል ተቋቁሟል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማእከል ሁሉም ዜጋ ዲፕሎማት ነው የሚለውን ሀሳብ እንደሚያጠናክር ተናግረዋል። ሁሉም ኢትዮጵያውያን ህልማቸውን እውን ለማድረግ እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውን እና ሀብታቸውን አስተባበረው ግድቡን እውን ሊያደረጉ እየተጉ መሆኑንም አውስተዋል። ኢትዮጵያውያን የዚህን ፍሬ ለማየት ወደተራራው እየዘለቁ ባሉበት ወቅት የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ አካላት ከዚህ ለመመለስ የሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት። ግብፅ ኢትዮጵያውያን ፍሬያቸውን እንዳያዩ ያለ የሌለ አቅሟን እየተጠቀመች ትገኛለች ያሉት አቶ ደመቀ ይህ ማእከልም የግብፅ እና መሰሎቿን ሴራ ለመቋቋም ምሁራኖችን ከተማሪዎች ጋር ለማቀናጀት ጠቀሜታው ላቅ ያለ ነው ብለዋል። ማእከሉ የበሰሉ ኢትዮጵያዊ ዲፕሊማቶችን ለማፍራትም ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው መጠቆማቸውን ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ በበኩላቸው ምሁራን ለሀገራቸው የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ምሁራኑ ይህንን ሚና በማሳደግ ኢትዮጵያ እና አፍሪካን የማንቃት ሚናቸውን በተገቢው መንገድ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የውሀ፣ መስኖ እና ኢነርጅ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሽ በቀለም አሁን ላይ ዝናብ በአስተማማኝ እና ከመደበኛ በላይ እያገኘን በመሆኑ የግድቡ ሁለተኛ የውሀ ሙሌት ያለምንም ችግር እንደሚከናወን አረጋግጠዋል። | የዲጅታል ዲፕሎማሲውን ለማጠናከር ያለመ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማእከል ተቋቋመ |
ኢሳት ግንቦት ሀያ ሶስት ፥ ሁለት ሺህ ዘጠኝ በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ተጋልጠው የሚገኙ ከሰባት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከቀጣዩ ሰኔ ወር ጀምሮ የሚቀርብላቸው የምግብ ድጋፍ አቅርቦት ሊያልቅ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሳሰበ። የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣትና የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለእርዳታ ጥሪው የሰጠው ምላሽ አነስተኛ መሆን የእርዳታ አቅርቦቱ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩን ድርጅቱ የድርቁን ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው አዲስ ሪፖርት ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና መንግስት ባለፈው ወር ባወጡት አዲስ የተረጂዎች ቁጥር አምስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ሰባት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን መድረሱ የሚታወስ ነው። ይሁንና ድርቁን ለመከላከል እና ለተረጂዎች ድጋፍ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት የተጠበቀውን ያህል ውጤት ባለማምጣቱ ችግሩ እየተባባሰ ሊሄድ መቻሉ ታውቋል። የምግብ አቅርቦቱ እየተጠናቀቀ መምጣት ሰባት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን የሚሆኑ ተረጂዎች ከሰኔ ወር ጀምሮ የምግብ አቅርቦት ላይኖር እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና መንግስት የድርቁን አደጋ ለመታደግ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ከወራት በፊት ቢገልፁም እየተገኘ ያለው ድጋፍ ግን እጅግ አነስተኛ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። ችግሩን ለመቅረፍ የምግብ አቅርቦት ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በትንሹ ሶስት ወራትን የሚፈጅ ሲሆን፣ በቀጣዩ ወር ሊያልቅ ይችላል የተባለው የምግብ ክምችት በእርዳታ ተቋማት ዘንድ ስጋትን አሳድሯል። የአለም ምግብ ፕሮግራም በበኩሉ ከእርዳታ ድርጅቶች ጋር በመመካከር ምግብን ከገበያ ማግኘት ለሚችሉ ተረጂዎች ጥሬ ገንዘብ ለመስጠት አማራጭ መያዙም ታውቋል። በሶማሌ ክልል ያለው የምግብ አጥረት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያለው የምግብ እርዳታ ክምችት ወደ ማለቅ መሆኑ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል ሲል የተባበሩት መንግስታት የእርዳት ማስተባበሪያ ቢሮ በሪፖርቱ አክሎ ገልጿል። የኦሮሚያ፣ አፋር ደቡብና የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ስር የሚገኙ በርካታ ዞኖች የተከሰተው የድርቅ አደጋ ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑ ይገልፃል። ከአንድ አመት በፊት ለአስር ሚሊዮን ሰዎች የምግብ እጥረት ምክንያት የነበረው የድርቅ አደጋ ሙሉ ለሙሉ እልባት ሳያገኝ አዲስ የድርቅ አደጋ በአራቱ ክልሎች መከሰቱ በእርዳታ አቅርቦት ላይ ጫና ማሳደሩንም የእርዳታ ድርጅቶች አስታውቀዋል። በተለይ በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ያለው የድርቅ አደጋ ለአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ምክንያት የሆነ ሲሆን፣ ከሰባት መቶ በላይ ሰዎች መሞታቸውን የአለም ጤና ድርጅት በቅርቡ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው። ይሁንና፣ መንግስት በጉዳዩ ዙሪያ የሰጠው ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም። | ለተረጂዎች ሲሰጥ የነበረ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ከሰኔ ወር ጀምሮ ሊያልቅ እንደሚችል ተመድ አሳሰበ |
መጋቢት አስራ ዘጠኝ ቀን አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ላለፉት ሁለት አመታት ሲካሄድ የቆየው ከቅርብ ወራት ወዲህ ቀዝቀዝ ብሎ የነበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ዛሬ ቁጥሩ እጅግ ብዙ የሆነ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በአንዋር መስጊድ ተካሂዷል።ሙስሊም ኢትዮጵያዊያኑ አላህ ሰላምን እንዲያመጣ ሲማፀኑ አርፍዷል። የሰላም ሰዎች መሆናቸውን ነጭ ወረቀቶችን በማውለብለብ ያሳዩ ሲሆን ተቃውሞውም ያለምንም የፀጥታ ችግር ተጠናቋል።መንግስት እንቅስቃሴውን በሀይል እንደተቆጣጠረው ሲያውጅ ቢከርምም ዛሬ በአንዋር የተገኘው ህዝብ ብዛት ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ጥያቄዎቹ ካልተመለሱ ዝም የማይል መሆኑን አሳይቷል ሲል አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የፈለገ ወጣት ለዚጋቢያችን ተናግሯል።የዛሬው ተቃውሞ በግፍ እስር ላይ ለሚገኙት ለመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የስነልቦና ጥንካሬ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ የገለፀው አስተያየት ሰጪ በኮሚቴ አባላቱ ላይ የሚሰጠው የሀሰት የፍርድ ውሳኔም ተቃውሞውን ይበልጥ ያጎላዋል እንጅ አያደበዝዘውም ብሎአል።የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የፍርድ ሂደት ነፃና ገለልተኛ አይደለም በሚል በአለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ይተቻል። | ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ አሰሙ |
በሱዳን መንግስት እና አማፂያን መካከል የመጨረሻ የሰላም ስምምነት መስከረም ሀያ ሁለት በደቡብ ሱዳን መዲና ጁባ እንደሚፈረም የሰላም ድርድሩ ሀላፊ ገለፁ። የድርድር ቡድኑ ሀላፊ እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት የፀጥታ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑት ቱት ጋትሏክ ጥቅምት ሁለት በአውሮፓውያኑ በመንግስት እና በሰላም ድርድሩ ሂደት ውስጥ ባሉ ወገኖች መካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ፊርማ የሚደረግበት ቀን ነው ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ገልፀዋል። የሱዳን ባለስልጣናት እና የአማፂ ቡድኖች ጥምረት የሆነው የሱዳን አብዮታዊ ግንባር ኤስ አር ኤፍ ፣ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነውን በተለይም በምእራብ ዳርፉር የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም የታቀደ ታሪካዊ የሰላም ስምምነት በአውሮፓውያኑ ባለፈው ነሀሴ ስላሳ አንድ ጁባ ውስጥ ተፈራርመዋል። እ ኤ አ በ ሁለት ሺህ የተቋቋመው ኤስ አር ኤፍ በጦርነት ከተጎዳው የምእራብ ዳርፉር ክልል እና እንዲሁም ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የብሉ ናይል እና የደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች አማፂያንን ያሰባሰበ ነው። የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ በጁባ በተደረገው ድርድር ለመስማማት ፈቃደኛ ካልሆነው የሱዳን ህዝባዊ ነፃነት ንቅናቄ ሰሜን ኤስ ፒ ኤል ኤም አማፂ ቡድን ጋር በኢትዮጵያ ውስጥ የተለየ ስምምነት መፈራረማቸውን የሁለቱ ወገኖች ባለስልጣናት አስታውቀዋል። የሱዳን የረጅም ጊዜ መሪ ኦማር አልበሽር ፣ ለወራት የዘለቀውን ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ፣ እ አ ኤ ሚያዚያ ሁለት ሺህ ከስልጣን ሲወገዱ ወደ ሀላፊነት የመጣው የሱዳን የሽግግር መንግስት ከአማፂያን ቡድኖች ጋር የሰላም ስምምነት ላይ መድረስን ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። ስምምነቱ በዋነኝነት በፀጥታ ፣ በመሬት ባለቤትነት ፣ በሽግግር ፍትህ ፣ በስልጣን ማጋራት እና በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የተሰደዱ ሰዎችን መልሶ ማቋቋም ላይ ያተኮረ ነው። በተጨማሪም የአማፂ ሀይሎችን ማፍረስ እና ተዋጊዎቻቸውን ወደ ብሄራዊ ጦር ስለማቀላቀልም ይመለከታል። እ ኤ አ በ ሁለት ሺህ ሶስት አማፂያን መሳሪያ ካነሱ በኋላ በዳርፉር ብቻ በተካሄደው ውጊያ ሶስት መቶ ያህል ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል። ከጥቅምት ሁለት ሺህ እ ኤ አ ጀምሮ ደቡብ ሱዳን በሱዳን መንግስት እና በዳርፉር ፣ ደቡብ ኮርዶፋን እና ብሉ ናይል ግዛቶች በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች መካከል ሽምግልና ስታደርግ ቆይታለች። | የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ ከቀናት በፊት ከአንድ አማፂ ቡድን ጋር በአዲስ አበባ ተስማምተዋል |
አዲስ አበባ፣ የካቲት ሀያ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ወርሀ ፆሙ ለተፈናቀሉና በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የምናደርግበት ሊሆን ይባል ሲሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኩስም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሀይማኖት ተናገሩ። ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የአቢይ ፆም መግባትን አስመልክተው ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልእክታቸውም በግጭቱና በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ካለን በማካፈል የችግሮቻቸው ተካፋይ መሆን ይገባል ብለዋል። ህዝበ ክርስቲያኑ ወርሀ ፆሙን ራሱን ሀይል ሰጪ ከሆኑ ምግቦች በመከልከል ብቻ ሳይሆን ከፀብና ከጥላቻ በመራቅ ሊያሳልፈው እንደሚገባ ገልፀዋል። የፆሙ ወቅት ምእመኑ ንስሀ የሚገባበት፣ ጥላቻን ከህሊናው የሚያስወግድበት ፍቅርን በመሻት ወደ እግዚአብሄር የሚቀርብበት ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። በዚህ ፆም ህዝበ ክርስቲያኑ ስለሀገር እና ስለቤተክርስቲያን መፀለይ እንደሚገባውም በመልእክታቸው አንስተዋል። በቅድስት ብርሀኑ ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን | ወርሀ ፆሙ ለተፈናቀሉና በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የምናደርግበት ሊሆን ይገባል ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ |
አዲስ አበባ፣ጥር ዘጠኝ፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የከተራና የጥምቀት በአል ተሳታፊዎች በአሉን ሲያከብሩ ርቀታቸውን በመጠበቅ ፣ ከንክኪ በመቆጠብ ፣ በተደጋጋሚ እጃቸውን በማፅዳት እንዲሁም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ሳያወልቁ በመንቀሳቀስ ሊሆን እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አሳሰበ። ሚኒስቴሩ ለክርስትና እምነት ተከታዮች፥ ለከተራና ለጥምቀት በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል። ሚኒስቴሩ በመልእክቱ የከተራና የጥምቀት በአል በምእመናን በብዛት የሚታጀብና አካላዊ ንክኪው እና ጥግግቱ የጠነከረ በመሆኑ ሰዎች ስሜቶቻቸውን ስገልፁ በጥንቃቄ ሊሆን እንደሚገባ ነው ያሳሰበው። ይህ ሁኔታ በተለይ የኮቪድ ወረርሽኝን ከሰው ወደ ሰው በማስተላለፍ ረገድ ምቹ ሁኔታ ሊፈጥር ስለሚችል፥ በአሉን ለማክበር የሚሰባሰቡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብሏል። የበአሉ ተሳታፊ ምእመናንም በተቻለ መጠን ርቀታቸውን በመጠበቅ ከንክኪ በመቆጠብና በተደጋጋሚ እጃቸውን በማፅዳት እንዲሁም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ሳያወልቁ በመንቀሳቀስ በአሉን ማክበር እንዳለባቸው ሚኒስቴሩ አሳስቧል። ኢትዮጵያን፦ እናልማ፤ እንገንባ፤ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን | የከተራና የጥምቀት በአል ተሳታፊዎች በአሉን ሲያከብሩ ርቀታቸውን በመጠበቅና ከንክኪ በመቆጠብ ሊሆን እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጠ |
ሶስት መቶ ሰባ አምስት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የውሀና መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያለበትን ወቅታዊ የግንባታ ደረጃ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት የግድቡ ሲቪል ስሰራዎች በአሁኑ ወቅት የዋናው ግድብ የሲቪል ስራዎች ሰማኒያ በመቶ ተጠናቋል፤ የሀይል ማመንጫዎች የሲቪል ስራ በአማካይ ስልሳ ስድስት በመቶ ተጠናቋል፤ የጎርፍ ማስተንፈሻ የሲቪል ስራዎች ዘጠና ዘጠኝ በመቶ ተጠናቋል፤ የኮርቻው ግድብ ስራዎች ዘጠና ሶስት በመቶ ተጠናቋል የስዊችያርድ የሲቪል ስራዎች ስላሳ ሶስት በመቶ ተጠናቋል፤ በአጠቃላይ የሲቪል ስራዎች ሰማኒያ ሁለት በመቶ ተጠናቋል። የአሌክትሮመካኒካል ስራዎች ተርባይን እና ጄኔሬተር ምርትና ተከላን ያለበትነ ደረጃ በተመለከተም ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጀነር ስለሺ በቀለ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል። በዚህም መሰረት የዘጠኝ ተርባይን እና ጄኔሬተር በአብዛኛው የተከናወነ ሲሆን በፕሮጀክት የስራ ቦታ ጉባ እና አንዳነዶቹ በወደቦች ይገኛሉ። የተወሰኑት የተርባይንና ጄኔሬተር አካላት በሀገር ውስጥ ይመረታሉ ተብለው የታሰቡት አልተመረቱም፤ የመጀመሪያ ሁለት ዩኒቶች የተርባይን አካል የሆኑትውሀን ለተርባይኖች የሚያመራ ተከላ ሀያ ሶስት ነጥብ ሰባት በመቶ ተከናውኗል፤ የከፍተኛ ሀይል መቆጣጠሪያ እና ማስተላለፊያ ስዊችያርድ ተከላ የመጀመሪያ ሁለቱ ዩኒቶች ትርንስፎርመር ተመርተው ሳይት ደርሰዋል፤ የተከለ ስራ አልተጀመረም፤ የከፍተኛ ሀይል መቆጣጠሪያ እና የማስተላለፊያ ስዊችያርድ እቃዎች ተመርተው የደረሱ ሲሆን ተከላ በጅምር ላይ ነው። አጠቃላይ የኤሌክተሮ መካኒካል ስራዎች አፈፃፀም ሀያ አምስት በመቶ ሲሆን፤ የሀይድሮሊክስ ስቲል እስትራክቸር ስራዎች አፈፃፀም በመቶ ብቻ ነው። በብረታብረትና ኢንጅነሪንግ ብኢኮ የተሰራው ስራም ሀያ ሶስት በመቶ ብቻ ሲሆን ፕሮጀክቱ አሁን የደረሰበት የግንባታ ደረጃም ስልሳ አምስት በመቶ መሆኑን ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ አብራርተዋል። ሶስት መቶ ሰባ አምስት | ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሁን ያለበት ደረጃ ይፋ ሆነ |
ከግማሽ ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የጎንደር ከተማ ውሀ ፕሮጀክት በተመረቀ በጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት አቆመ።ኢሳት ዜና ሚያዝያ ቀን አመተ ምህረት ለዘመናት በከፍተኛ የውሀ እጥረት ችግር ተጠቂ ከሆኑት የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል አንዷ የሆነችው የጎንደር ከተማን የውሀ ችግር ከ በመቶ ወደ መቶ በመቶ ከፍ ያደርገዋል በዘላቂነትም የከተማዋን የውሀ ችግር ይፈታል የተባለለት የውሀ ፕሮጀክት በተመረቀ በጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት በማቆሙም ህዝቡ ለከፍተኛ ችግር መዳረጉ እና ከ ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ገንዘብ ባክኖ መቀረቱ ተዘግቧል።ፕሮጀክቱ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የውሀና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በተገኙበት ህዳር ቀን አመተ ምህረት በይፋ ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል።ከአለም ባንክ በተገኘ ብድርና በመስተዳደሩ ወጪ ከ ሚሊዮን ብር በላይ የፈሰሰበት የውሀ ፕሮጀክት ለሚቀጥሉት ሀያ አመታት ዋስትና አለው ተብሎ ታስቦ የተሰራ ነው ተብሎ ነበር። አዲሱ ፕሮጀክት ስምንት ጥልቅ ጉድጓዶች ሲኖሩት በሰከንድ እስከ ሊትር በቀን ደግሞ እስከ ሽህ ሜትር ኩብ ውሀ እንደሚያመነጭና ከአንገርብ የውሀ ማመንጫ ጋር ተዳምሮ በቀን እስከ ሽህ ሜትር ኩብ ውሀ ያቀርባል ተብሎ ዲዛይን ተደርጎ መሰራቱ ይታወቃል። ይሁንና ጉድጓዶቹ በተባለላቸው መጠን የተጠበቀውን ያህል ውሀ ማመንጨት ሳይችሉ አገልግሎት መስጠት በማቆማቸው የከተማዋ ነዋሪዎች በውሀ ማጣት ከመቸገራቸው በተጨማሪ ተጨማሪ ወጭዎችን ለማውጣት ተገዷል።ኢሳት ከወራት በፊት የውሀ ጉድጓዶች መድረቃቸውን መረጃ ደርሶ ሲከታተለው ቆይቷል። በግንባታው ላይ ከፍተኛ ሙስና መፈፀሙንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።ችግሩን አስመልክቶ የጎንደር ከተማ ውሀ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ሀላፊ ብዙ ገንዘብ ወጪ ወጥቶበት የተገነባው ፕሮጀክት የተጠበቀውን ያህል አገልግሎት መስጠት ባለመቻሉ በግንባታ ፕሮጀክቱ ላይ የተሳተፉ በሙሉ ተጠያቂዎች ናቸው ብለዋል።ታሪካዊቷን የጎንደር ከተማን ጨምሮ በመዲናዋ አዲስ አበባ አዳማ መቀሌ አሰላ በመሳሳሉት ታላላቅና አነስተኛ ከተሞች የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ በመባባሱ በነዋሪዎች ህይወት ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ ነው። | ከግማሽ ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የጎንደር ከተማ ውሀ ፕሮጀክት በተመረቀ በጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት አቆመ። |
Dataset Name
Amharic news dataset
Dataset Details
It is a non-normalized version of news dataset crawled from Amharic news websites and from researchers provided in their works.
Dataset Description
The dataset is collected from different news websites and from different researchers crawled Amharic news dataset from different NLP downstream tasks. News sites like FanaBC, EthiopianReporter, Zehabesha,Esat Amharic, BBC Amharic are the sources for these news data. Tasks like news classification and summarization are the related NLP applications where some of the data in this dataset are used from.
Uses
The dataset can be use in the area of NLP/AI/Data science to build models, improve or finetune previously built models.
Out-of-Scope Use
Please use this data only for research and educational purpose only.
Dataset Structure
The dataset has two fields namely "Text" and "Summary" which can also be "Article" and "Headline" or "Content" and "Title" as per your need of naming the fields. The dataset has three splits as "train", "test", and "eval" (validation) with as percentage split of 80:10:10 respectively.
Dataset Creation
Curation Rationale
The dataset is intended to be used in the task of news summarization and reverse summarization (News article generation).
Source Data
The data is prepared from Amharic news websites.
Data Collection and Processing
After the data is collected from different sources, different stages of processing are done on it. primarily the data gets integrated and filtered null rows, duplicates and removed none amharic scripts. so, in this dataset there are only Amharic/ge'ez scripts to make easy for the model on bias issues. the other processing tasks are abbreviation expansion, and Normalization. This data is the normalized version where all homophones and unliablized letters are as written on the news websites. the non-normalized version of this dataset is available at this Dataset
Recommendations
Users should be made aware of the risks, biases and limitations of the dataset.
- Downloads last month
- 14