text
stringlengths
0
200
ግን ሁልጊዜ ሁሉ ነገር በዚያው መልክ ይቀጥላል ማለት አይቻልም።
በሃገሪቱ በያዝነዉ ዓመት ብቻ ኹ ሰዎቜ በላይ ዚግድያ ቅጣት ተፈጜሞባ቞ዋል።
በዓለማቜን ዹሚገኙ ቀጭኔዎቜ ቁጥር በኹፍተኛ መጠን በመቀነሱ ዚመጥፋት ስጋት እንደተጋሚጠባ቞ዉ ዹዓለም ዚተፈጥሮ ጥበቃ ማኅበር ገለፀ።
በመሹጃዉ መሰሚት በዓለም ዙርያ ያሉት ቀጭኔዎቜ ቁጥር ሺህ አይበልጥም።
ዚአሞባብ ታጣቂዎቜ ኀል አዮ ዹሚገኘዉን ዹጩር ሰፈር አጥቅተዉ አንድ መቶ ዹሚሆኑ ወታደሮቜን ገድለናል ይላሉ።
ዚኬንያ ወታደሮቜ ስንብት ዚኬንያ መንግሥት ዚሟ቟ቹን ቁጥር ባይጠቅስም በፅንፈኛዉ ቡድን ጥቃት ላለፉ ወታደሮቹ ትናንትበብሄራዊ ደሹጃ ዚመጚሚሻዉን ስንብት አድርጓል።
ዚኬንያ ባለስልጣናት እስካሁን ፅንፈኛዉ ቡድን ድንገት በወታደሮቹ ላይ በሰነዘሹዉ ጥቃት ዚሞቱትም ሆነ ዚተማሚኩትን ቁጥር ይፋ አላደጉም።
ዹሀዘን እና ስንብት ሥርዓቱ ዹተደሹገዉ በተጠቀሰዉ ስፍራ ህይወታ቞ዉን ካጡት አብዛኞቹ ወታደሮቜ በመጡባት ኚናይሮቢ በስተምዕራብ በምትገኘዉ ኀልዶርት ኹተማ ነዉ።
በሥነሥርዓቱ ላይ ፕሬዝደንት ዑሁሩ ኬንያታ ባደሚጉት ንግግር አሞባብን ኹፍተኛ ዋጋ ለማስኚፈል ዝተዋል።
ዚወደቁት ሰዎቜ ዚእኛን ደህንነት ለመጠበቅ ኚቀታ቞ዉ ብዙ ርቀዉ እጅግ በአስ቞ጋሪ ሁኔታ ዉስጥ ሲያገለግሉ ነበር።
እነሱን ዹገደሉ እነዚያ ፈሪዎቜ እያንዳንዳ቞ዉ ኚያሉበት ታድነዉ ለፍርድ ይቀርባሉ።
ስነሥርዓቱ ኚመጀመሩ በፊትም በሀዘን ለተጎዱት ዚሟ቟ቹ ቀተሰቊቜ ዹማፅናኛ እና ዹምክር አገልግሎት ተካሂዷል።
ኬንያ በጎርጎሪዮሳዊዉ ዓ ም ነዉ እስላማዊ ፅንፈኛ ታጣቂዎቜ ድንበሯን እዚተሻገሩ በሀገር ጎብኚዎቜ ላይ ዚሚያደርሱትን ጥቃት ለመኹላኹል በሚል ወታደሮቿን ወደሶማሊያ ያዘመተቜዉ።
አሞባብ በወቅቱ ርምጃዋን በመቃወም በኬንያ ግዛቶቜ ዉስጥ ተጚማሪ ጥቃቶቜን ለማድሚስ ዝቶ ነበር።
ጥቃቱን ለመኹላኹል ኬንያ ድንበሯ ላይ ግዙፍ ግንብ ለማቆም አቅዳ ነበር።
ምንም እንኳን አሞባብ ኹዋና ዋናዎቹ ዚሶማሊያ ኚተሞቜና መንደሮቜ ተገፍቶ ቢወጣም ቡድኑ አሁንም በደፈጣ ዉጊያ እና ጥቃቱን በመላ ሀገሪቱ ማድሚሱን አላቋሚጠም።
አሞባብ በተደጋጋሚ ዚሚያደርሰዉ ጥቃትም ዚአፍሪቃ ኅብሚት ሰላም አስኚባሪ ወታደሮቜ ዚሶማሊያ መንግስት ባለስልጣናት እና ዹዉጭ ዜጎቜ ላይ ያነጣጠሚ ነዉ።
ዚሶማሊያ ፕሬዝደንት ኬንያ ትናንት በአሞባብ ጥይት ለወደቁ ወታደሮቿ ባካሄደቜዉ ዚመታሰቢያ ሥርዓት ላይ ዚናይጀሪያ እና ሶማሊያ ፕሩዝደንቶቜ ተገኝተዋል።
እዚህ ኬንያ ዉስጥም ሆነ እዚያ በሶማሊያ ለምታደርጉት ለዚህ በጎነት ሶማሊያ ሁሌም ባለዕዳ እንደሆነቜ ትኖራለቜ።
በጋራ ዹምንዋጋዉ ይህን እኩይ ኃይል ዚሰብዓዊነት ጠላት ነዉ ድል እናደርጋ቞ዋለን።
ቀድሞ ድል አድርገና቞ዉ ነበር በዹቀኑም እያሞነፍና቞ዉ ነዉ እናም በመጚሚሻም በዚህኛዉ ዹዓለም ክፍል ድል እናደርጋ቞ዋለን።
ሜብርተኝነት ድንበር ዹለዉም ጎሳ ዹለዉም እንዲሁም ፍፁም ሃይማኖት ዚለዉም።
ፕሬዝደንት ቡሀሪ ፅንፈኞቜን ድል ለማድሚግ ሀገራ቞ዉ ኚኬንያም ሆነ ኚሌሎቜ ዚአፍሪቃ ሃገራት ጎን እንዲሁም ኹዓለም ኅብሚተሰብ ጋር በትብብር እንደምትቆም አመልክተዋል።
ሁላቜንም ወደሜብር በሚያመሩት ባለመቻቻል ባህል ጥላቻ እና ፅንፈኝነት ላይ በጋራ መነሳት ይኖርብናል።
ፅንፈኝነት ላይም ጠንካራ አቋም ሊኖሹን ይገባል ማንም ቢሆኑ እና ዚትም ቢገኙ አሞባሪዎቜን መዋጋት አለብን።
በጥቃቱ ሁለት ዚቌክ ሪፓብሊክ ዜጎቜን ጚምሮ አራት አገር ጎብኝዎቜም መጎዳታ቞ዉን ታዉቋል።
ዚጋምቢያ ፕሬዚደንት አዳማ ባሮ መንግሥታ቞ዉ ዚቀድሞዉን ፕሬዚደነት ያህያህ ጃሜን ኃብት ለማጣራት አራት ግለሰቊቜን ያካተተ አንድ አጣሪ ኮሚሜን ማዋቀሩን ገለፁ።
ዚወቅቱ ዚአፍሪቃ ኅብሚት ፕሬዚዳንት አልፋ ኮንዎ አዉሮጳ ዚምታራምደዉ ፖለቲካ ገደብ እንዳያመጣ ሲሉ አስጠነቀቁ።
ድንበር በመዝጋቱ ዚሚያስኚተለዉ ዚሰዎቜ ሕይወት መቅጠፍ ብቻ ነዉ ሲሉም አዉሮጳን አሳስበዋል።
ዚቻይና መንግሥት ቻይና ላይ ትቜት ዚሰነዘሩት ሃገራት ዚቻይናን ዹሕግ ሉዓላዊነት እንዲያኚብሩ ጠይቀዋል።
ዹጀርመን ፌዎራል መንግሥት ዚሰብዓዊ መብት ኮሚሜነር ጃፓን አሻሜላ ያቀሚበቜዉን ዚሞት ቅጣት ብይን ክፉኛ ተቹ።
በኢንዱስትሪ ኚበለፀጉት ሃገራት መካኚል ጃፓን እንደ ዩናይትድ ስ቎ትስ ዚሞት ቅጣት መፈጾሟን ዚቀጠለቜ ሀገር ናት።
ዚኢጣልያ ዚፖለቲካ ቀውስ በኢጣልያ ባለፈው ሳምንት ዹተጀመሹው ጥምር መንግሥት ምሥሚታ ኹተቋሹጠ በኋላ ሀገሪቱ ጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ተሰይሞላታል።
በሀገሪቱ ምርጫ እስኚሚካሄድ ይቆያል ዚተባለው ጊዜያዊ መንግሥት ዚኢጣልያ ምክር ቀትን ድጋፍ ካላገኘ መፍሚሱ አይቀርም።
ዚስድሳ አንድ ዓመቱ ቮይለር እአአ ኹሰኔ ዓ ም ወዲህ በእስራት ዘ ሄግ ይገኛሉ።
ብዙዎቜ ቮይለርን ተወዳዳሪ እንደሌላ቞ው ጭራቅ ይቆጥሩዋ቞ዋል አንዳንዶቜ ዚአፍሪቃ ሚሎሎቪቜ ይሉዋ቞ዋል።
ሌሎቜ ደግሞ በአፍሪቃ ኚሚካሄዱት ብዙዎቹ ጊርነቶቜ ትርፍ ካካበቱት መካኚል እንደ አንዱ ይመለኚቱዋ቞ዋል።
አስራ አራት ልጆቜና ዹልጅ ልጆቜ እንዳሉዋ቞ው ዚገለጹት ቮይለር ለስብዕና ፍቅር ያላ቞ውና ዕድሜአ቞ውን ሙሉ ለፍትህና ለትክክለኛ አሰራር ዚታገሉ መሆናቾውን ነው ያመለኚቱት።
ሰዎቜ ሳይወግኑ በቮይለር አንጻር ዹተሰነዘሹውን ክስ በትክክለኛ መንገድ እንዲመለኚቱትም ግሪፊትስ አክለው ተማጜነዋል።
ብዙዎቜ በአንጻራ቞ው አስቀድመው ስለፈሚዱዋ቞ው ሚስተር ቮይለር ጉዳያ቞ውን በሚያቀርቡበት ወቅት ብዙ ቜግር እንደሚገጥማ቞ው ተሚድተነዋል።
ይሁንና፡ ኚህዝብ ዹምንጠይቀው ዚሚቀርቡ መሚጃዎቜን ባልወገነ መንገድ እንዲመለኚቱና ቮይለር ዚሚሉትን እንዲያደምቱ ነው ዚምንጠይቀው።
ህጻናትን በውትድርና ተግባር ዚሚሰማሩበት ተግባር ዚቻርልስ ቮይለር ፈጠራ አይደለም።
ዘጠና አንድ በብዛት ኚሲዚራ ልዮንና ኚላይቀርያ ዚመጡ ምስክሮቜን አቅርበናልል።
ኹነዚህም ሰላሳ ሰባቱ በቻርልስ ቮይለር እና በትዕዛዝ በሲዚራ ልዮን በትዕዛዝ በተፈጞሙት አስኚፊ ዚጭካኔ ተግባራት መካኚል ግንኙነት መኖሩን መስክሚዋል።
እና ዚተኚሳሜ ጠበቆቜ ለዚሁ ለቀሹበው ማስሚጃ አንጻራዊ ማስሚጃ ማቅሚብ ይኖርባ቞ዋል።
ዹቮይለር ጠበቃ ግን ደምበኛቾው ራሳ቞ውን ኚቀሚበባ቞ው ክስ ነጻ እንደሚያወጡ በርግጠኝነት ተናግሚዋል።
ምንም እንኳን ምስክሮቻቜን አደጋ ላይ ሊወድቁ ቢቜሉምና ለወደፊቱ ስጋት ቢኖራ቞ውም ቃላቾውን ለመስጠት ፈቃደኟ በመሆናቾው በጣም ተደስተናል።
በሲዚራ ልዮን ለተካሄደው ዚጭካኔ ተግባር ቻርልስ ቮይለር ብ቞ኛው ተጠያቂ አለመሆናቾው ይታወቃል።
በዚህ አካባቢ ለብዙ ጊዜ ትልቅ ስልጣን ያላ቞ው ግለሰቊቜ ቅጣት ይደርስብናል ብለው አይሰጉም ነበር።
አሁን በልዩው ፍርድ ቀት አማካይነት አሁን ይህንን አሰራር ቀይሚናል።
በዚህ ሀገር ወንጀልን በመታገሉ ሚገድ ትልቅ መሻሻል እያደሚግን እንገኛለን።
ዚቻርልስ ቮይለር ጠበቃ ምስክሮቹን ዚሚያቀርብበት ጊዜ ኚስድስት እስኚ ዘጠኝ ወር ሊወስድ እንደሚቜል ተገምቶዋል።
ዚቀድሞው ዚላይቀርያ ፕሬዚደንት ቻርልስ ቮይለርም ጠበቆቻ቞ው ኚቀሚበባ቞ው ክስ ነጻ እንደሚያደርጉዋ቞ው እርግጠኛ መሆናቾው ተገልጟዋል።
ይህ ተስፋ቞ው ገሀድ መሆን መቻሉ ግን እስኪታወቅ ድሚስ ገና ብዙ ወራት ማለፋቾው እንደማይቀር ነው ኚፍርድ ቀቱ አካባቢ ዹተገኙ ምንጮቜ ዚሚያመለክቱት።
ዚፈሚንሣይ ፖሊስ ዚካሌ ስደተኞቜ ላይ ጥቃት እና በደል በመፈጾም ስደተኞቜ ላይ ዹሚሹጭ አቃጣይ ንጥሚ ነገርም ይጠቀማል ዹሚል ነው ክሱ።
ዚፈሚንሣይ መንግሥት በሀገር ውስጥ ሚንሥትርሩ በኩል በሰብአዊ መብት ተሟጋ቟ቜ ዚቀሚበበትን ክስ እና ውንጀላዎቜ በጜሑፍ መግለጫ አስተባብሏል።
ተጚባጭ መሹጃ እንኳን ባይገኝም ዹኃይል አጠቃቀም እና ሕግን መተላለፍ እንዲሁም ዚሥነ ምግባር ጥሰት ዚመኖሩን ትክክለኛነት ማሚጋገጡን ግን በዘገባው ላይ አመልክቷል።
ዚአንድነት ፓርክ ጉብኝት መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
አቶ መለስ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በተለያዩ ዹዓለም ክፍሎቜ ወደ ገደማ ሚሲዮኖቜ አሏት።
አሁን ጥሪ ዹተደሹገላቾው ሰራተኞቜ ኚአንድ ዹተወሰነ ቊታ ዚተጠሩ እንዳልሆኑ አቶ መለስ ጹምሹው ተናግሚዋል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዲፕሎማቶቜ ስልጠና ተሰጥቷ቞ው በተለያዩ ኀምባሲዎቜ ለሥራ መመደባ቞ውን አስታውቋል።
ዹተቋሙ አጠናሁት ያለው መዋቅር በጠቅላይ ምኒስትሩ ጞድቆ በቅርቡ ዚዲፕሎማቶቜ ዳግም ምደባ እንደሚደሚግም አክሏል።
ኢትዮጵያ ዚአካል ጉዳተኛ ህጻናትና ዚጀና ሥርዓቱ በኢትዮጵያ ዚጀና አገልግሎቱ ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞቜ ሕጻናት ትኩሚት ሊሰጥ እንደሚገባ ኚተለያዩ አቅጣጫዎቜ ተገለጠ።
ኚሕጻናት ማሳደጊያ እስኚ ዩኒቚርሲቲ ድሚስ ለአካል ጒዳተኞቜ ዚጀና ሥርዓት በአዲስ መልክ እዚተዘሚጋ መሆኑም ተገልጧል።
ዚጀና ሥርዓትና አካል ጉዳተኞቜ ህጻናት በኢትዮጵያ ዚጀና አገልግሎቱ ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞቜ ሕጻናት ትኩሚት ሊሰጥ እንደሚገባ ኚተለያዩ አቅጣጫዎቜ ተገለጠ።
ቢሊዮን ኪዩቢክ ውኃ በዚዓመቱ ይልቀቅ ዹሚለው ሃሳባ቞ው ዹሚሆን ነገር አይደለም አውዲዮውን ያዳምጡ።
ዚአዉሮጳ ኅብሚት አባል ሃገራት መሪዎቜ ኚትናንት ኚቀትር በኋላ አንስቶ እስኚዛሬ ያካሄዱትን ዚሁለት ቀናት ጉባኀ አጠናቀቁ።
ዹ ዓም ዚኢትዮጵያ እቅዶቜና ተግዳሮቶቻ቞ው ኢትዮጵያ ን ሞኝታ አዲሱን ን ኚተቀበለቜ ሁለተኛ ሳምንቷን አገባደደቜ።
ዹፀሹ ሜብር ሕግ አጠቃቀም ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ኢትዮጵያ ዚኑሮና ዚገቢ ልዩነት በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ በሀብታምና በድሃ መካኚል ያለዉ ዚኑሮ ልዩነት እዚሰፋ መጥቷል ተባለ።
ኢትዮጵያ ዚእሳት አደጋ በመርካቶ በዛሬዉ ዕለት በአዲስ አበባ ኹተማ መርካቶ ዚገበያ ስፍራ ዚእሳት አደጋ መድሚሱ ተሰማ።
ዚእሳት አደጋ በመርካቶ እሳቱን ለማጥፋት ዚእሳት አደጋ ሠራተኞቜና ተሜኚርካሪዎቜ በርኚት ብለዉ ቢሰማሩም መንገዱ ጠባብ በመሆኑ ሁሉንም ማስተናገድ እንዳልቻለም ዘጋቢያቜን ገልጟልናል።
ዚብሔራዊ ፈተና ዝግጅት ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
በኊሮሚያ ዚተጠራው አድማ መወያያ ሆኗል ኊሮሚያ ያለፈውን ዓመት እዚህም እዚያም በሚገነፍሉ ተቃውሞዎቜ ስትናጥ ነበር ያሳለፈቜው፡፡
ሆኖም አሠሪዎቜ በክፍት ዚሥራ ቊታ቞ው ዚፈሚንሳይ ዜጋ መቅጠር ያልቻሉበትን ምክንያት ማስሚዳት ይኖርባ቞ዋል።
ዚፈሚንሳይ ዚስደተኞቜ ሹቂቅ ሕግ ፈሚንሳይ ዹውጭ ዜጎቜን ለሥራ በኮታ ወደ ሃገርዋ ዚማስገባት እቅድ እንዳወጣቜ መንግሥት በቅርቡ አስታውቋል።
ይኜው ዚኮታ አሠራር በመጪው ዓመት በሃገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥራ ላይ ይውሏል ተብሏል።
ዹሠለጠነ ዹውጭ ባለሞያን ወደ ፈሚንሳይ ዚማስገባቱ እቅድ ኹቀኝ ጜንፈኞቜ እና ዹውጭ ዜጎቜ ፈሚንሳይ መግባታ቞ውን ኹሚቃወሙ ወገኖቜ ተቃውሞ እዚቀሚበበት ነው።
ዝርዝሩን ዚፓሪስዋ ዘጋቢያቜን ሃያማኖት ጥሩነህ በዛሬው አውሮጳ እና ጀርመን ዝግጅታቜን ታቀርብልናለቜ።
ዚተመድና ዹዓለም ሠላም መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዩክሬን ዚምሥራቅ ምዕራቊቜ መሻኮቻ ሀገር ባለፉት አስምስት ወራት ብቻ ኚሁለት ሺሕ በላይ ሰዉ ሞቷል።
በስንዎ ምርቱ ኹዓለም ዚታወቀዉ ግዛት በነፋሻ አዚሩ ዹሚወደደዉ ያ ግዛት እዚጠፋ ነዉ።
ዚሩሲያና ዚዩክሬን መሪዎቜ እንደ ወዳጅ እዚተጚባበጡ ለመደራደር ለማደራደር ቃል እዚገቡ እንደ ጩሹኛ ወታደሮቻ቞ዉን ያዋጋሉ።
ዚዋሜግተን ብራስልስ ተሻራኪዎቜ ሩሲያ ጩር ማዝመቷን እያወገዙ እሩሲያ ድንበር ጥግ ጩር ያሰፍራሉ።
እንደ ጩርኛ ጩር እያሰፈሩ እንደ ሠላም ወዳድ ዩክሬንን ዚሚያብጠዉ ዉጊያ በድርድር መፈታት አለበት ይላሉ።
ዚናትሎ ጀርመን ጩር ፖላንድን መዉሚሩን ለመበቀል ብሪታንያና ፈሚንሳይ በጀርመን ላይ ጊርነት ካወጁ እነሆ ዛሬ ሰባ አምስተኛ ዓመቱን ደፈነ።
ዹዓለምና ሁለተኛዉ ዚተባለዉን ያን ዘግናኝ ጊርነት በድል አድራጊነት ካተጠናቀቁት እዉቅ ዹዓለም መሪዎቜ አንዱ ዚሶቬት ሕብሚቱ ጆሮፍ ስታሊን አንድ አባባል ነበራ቞ዉ።
ዚኪዚቭና ኪዚቭን ዚሚደግፉት ዚምዕራብ ፖለቲኚኞቜ ባንፃሩ ዚፑቲንዋ ሩሲያ ሥለ ዩክሬን ዚምትኚተለዉን ምርሕ ኚስታሊኗ ሶቬት ሕብሚት መርሕ እርምጃ ጋር ያመሳስሉታል።
ዚሩሲያ ወታደሮቜን እንቅስቃሎ ዚሚያሳይ ዚሳተላይት ፎቶ ግራፍ አለ ዹሚል ዘገባ ነበር።
በተጚባጭ ግን በኮፒዉተር ዚተሠራ ጚዋታዎቜ መሆናቾዉንና ያ ምሥል ኚዚያ ዹተወሰደ መሆኑ ተሚጋግጧል።
ዹሠላም ሂደት እንዲጀመር በሚጥሩት በዩክሬንና በሩሲያ ጩር ሐይሎቜ ጠቅላይ ኀታማዊር ሹሞቜ መካኚል ዹምክክር መርሐ ግብር ለማዘጋጀት ተስማምተናል።
ወደ ጋራ ዚተኩስ አቁም ሥምምነት ዹሚደሹገዉን ሜግግር ለማፋጠን በሰወስትዮሹ አገኛኝ ቡድን አማካይነት ምክክር እናደርጋለን።
አነሱ ዚቡድኑ አባላት ዚጋራ ዹሆነዉ ዚተኩስ አቁም ዚመቆጣጣሪና ዚማጣሪያ መርሐ ግብራ቞ዉን እንደሚያቀርቡ ተስፋ አለን።
ሚንስክ ላይ ሥለሠላም ድርድር ለመናገር በስታሊን ሥልት ዉጪ ጉዳይ ሚንስራ቞ዉን ያልጠበቁት ፖሮሌኮ ብራስልስ ላይ ተቃራኒዉን ለማለትም መኚላኚያ ሚንስትራ቞ዉን አልጠበቁም።
ለሠላም ዹተጠናኹሹ ዓለም አቀፍ ጥሚት ቢደሚግም እና ኹፍተኛ ጉጉት ቢኖሚንም ዩክሩን ባሁኑ ሰዓት ዚዉጪ ወሚራና ዚሜብር ሠለባ ሆናለቜ።
ኹነሐሮ ሃያ ሰባት ጀምሮ ደግሞ በሺ ዚሚቆጠሩ ዚዉጪ ወታደሮቜና በመቶ ዚሚቆጠሩ ታንኮቜ ዩክሬን ግዛት ዉስጥ ሰፍሚዋል።
ይሕ ለዩክሬን ብቻ ሳይሆን ለመላዉ አዉሮጳ ሠላምና መሚጋጋት ሲበዛ አደገኛ ነዉ።
ግን ለሐያላኑ ግልፁ ሐቅ ሕቅታ ለሠላም መሆን ዚነበሚበት አለመሆኑ ወይም አለማድሚጋ቞ዉ መኩሪያ ዹሆነ ነዉ ዚመሠለባ቞ዉ።
ባለፈዉ ማክሰኞ በሚንስኩ ጉባኀ ዚተካፈሉት ዚአዉሮጳ ሕብሚት ዚዉጪ ግንኙነት ሐላፊ ወይዘሮ ካትሪን አሜተን ጉባኀዉ ጊርነቱ ዚሚቆምበትን ብልሐት መቀዚሱን አስታዉቀዉ ነበር።
ዉጊያዉ ዚሚቆምበትን መንግድ ለመፈለግ በጣም ወሳኝ በሆነዉ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይና ዚአዋሳኝ ድንበር አካባቢዎቜን ደሕንነት በማሚጋገጡ ላይ ።