text
stringlengths
0
200
እኛ አዉሮጳ ሕብሚት ዉስጥ ያለነዉ ኚሩሲያ ጋር መጋጚቱን አንፈልገዉም።
ሩሲያም ኚአዉሮጳ ሕብሚት ጋር ዚመጋጚቱ ፍላጎት ሊኖራት አይገባም ብዬ አምናለሁ።
ይሕ ቢቀር ዚአዳዲሶቹ ዚኪዚቭ መሪዎቜ ርምጃ ሩሲያን አዉሮጳ ዉስጥ ዚነበራትን ተሠሚነትና ዚምታሳርፈዉን ተፅዕኖ ኹፍፃሜዉ ዚሚያደርስ ነዉ ኹሚል ሥጋት ባልዶላት ነበር።
ተገንጣዮቹ በሩሲያ ዹሠለጠኑ በሩሲያ ዚታጠቁ በሩሲያ ገንዘብ ዹሚደገፉ ና቞ዉ።
ሩሲያ ሆን ብላ እና በተደጋጋሚ ዚዩክሬንን ሉዓላዊነትና ዚግዛት አንድነት ጥሳለቜ።
ዚሩሲያ ወታደሮቜ ዩክሬን ዉስጥ መግባታ቞ዉን ዚሚያሳዚዉ አዲሱ ምሥል ደግሞ ዓለም ሁሉንም በግልፅ እንዲያዉቀዉ ያደርጋል።
ዓለም አዉቆ ዚሚያደርገዉ ወይም ለማድሚግ ዚሚቜለዉ ካለ ዚሚያዉቀዉ ሁሉንም ነዉ።
ተሰናባቹ ዚአዉሮጳ ሕብሚት ኮሚሜን ፕሬዝዳንት ሆሮ ማኑኀል ባሮሶ እንዳሉት ምዕራባዉያንም ሩሲያም ቀጥታ ግጭት ጊርነቱን አይፈልጉት ይሆናል።
ባለፉት አስምስት ወራት ብቻ ኚሁለት ሺሕ በላይ ሰዉ ሞቷል።
ዚአሜተን ዲፕሎማሲ ዚባሮሶ ዚድርድር ሐሳብ ኹዘገዹ ዚፑቲንም ዚድርድር መልዕክት በርግጥ አርፍዷል።
ለሠላም ካሰቡ ግን ዚዉይይት ድርድሩ መፍትሔ ዘገዹ እንጂ ጚርሶ አልቀሚም።
ኮምፒውተር ሳይንስ ለሁለተኛ ደሹጃ ተማሪዎቜ ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ቃዛፊ ኹተገደሉ በኋላ ሊቢያ ዹጩር አበጋዞቜ ዚዚጎጥ ሚሊሺያ መፈንጪያ ዚአሞባሪዎቜ መደራጂያ ዚስደተኞቜ መገደያ መሞጪያ መደፈሪያ መታገቻ ሆናለቜ።
ዚሊቢያ መዘዝ ለሳሕሎቜ ተርፎ ኹማሊ እስኚ ለኒዠር ኚቡርኪና ፋሶ እስኚ ቻድ ሺዎቜ ተገድለዋል።
ሞስኮ ላይ ድርድር በርሊን ላይ ጉባኀ ብራስልስ ላይ ዉይይት እያለ ይራወጥ ያዘ።
በሊቢያ እና በሶሪያ ጊርነት ተቃራኒ ኃይላትን ዚሚሚዱት ዚቱርክ ዚፈሚንሳይ ዚሩሲያ እና ዚግብፅ መሪዎቜ እንደ እንደ ፖለቲካ ዲፕሎማሲዉ ወግ ተነጋግሚዋል።
ዚአንዲት ሊቢያ ዚአንድ ዘመን ትዉልዶቜ ግን ዹተፋላሚ ኃይላት መሪዎቜ ስለገዛ ሐገራ቞ዉ መነጋገር ዓይደለም አንድ አዳራሜ ዉስጥ አብሮ መቀመጥም አልፈለጉም።
ምክንያቱም ልዩነታ቞ዉ ስር ዹሰደደ ስለሆነ ይላሉ ዚጉባኀዉ አስተናጋጅ ዹጀርመኗ መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል።
በሁለቱ ወገኖቜ መካኚል ያለዉ ልዩነት በጣም ሰፊ በመሆኑ አይነጋገሩም።
ይሁንና እዚሁ በቅርብ ነበሩ አንድ ክፍል ዉስጥ ግን አልነበሩም።
ዹዓለም ኃያላን በርሊን ላይ ሥለ ሊቢያ ዉድመት ሲነጋገሩ ዚሐፍጣር ጩር ዚነዳጅ ማምሚቻና ማኚማቻ ተቋማት ነዳጅ ዘይት እንዳሞጡ አግዷል።
ሐፍጣር እንደ ጩር አበጋዝ ወታደራዊ እርምጃ ሲወስዱ አል ፈራጅ እንደ ሲቢል መሪ ዹተሹፋቾዉን አማራጭ ቀሰቀሱ።
ምክንያቱም ተኩስ አቁሙን ወንጀለኛዉ ሐፍጣር ትሪፖሊን ለመቆጣጠር እና ተጚማሪ ደም ለማፍሰስ ጩር መሳሪያ ለማኚማቜትና ወታደሮቹን ለማደራጀት ይጠቀምበታልና።
ተቃዉሟቜን ለምዕራባዉያን ለፀጥታዉ ምክር ቀትና ለአዉሮጳ ሕብሚት መልዕክት ለማስተላለፍ ነዉ።
ቱርክ ዚኔቶ አባል ብትሆንም ዚቱርኩ ፕሬዝደንት አጋጣሚዉን በመጠቀም ጊራ቞ዉን ወደሊቢያ ለማዝመት ይፈልጋሉ።
በ ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምሕርቱን ለመኚታተል ኹሰሜን ምስራቃዊቱ ዚትዉልድ መንደሩ አጅዳቢያ ሻል ወዳለቜዉ ኹተማ ደርና ገባ።
በዚያዉ ዓመት ኚጥንቷ ጣራቊሊስ ቅኝ ገዢ ኚቱርክ ደም ዚሚወርሱት ዚንጉስ ኢድሪስ ሐብታም ሚንስትር መሐመድ አል ሳራጅ ዚወንድልጅ አባት ሆኑ።
ፋይዝ እንደ ሐብታም ሚንስትር ኚቱጃሮቹ ትምሕርት ቀት ፊደል ሲቆጥር ወጣቱ ኾሊፋ ጩር ትምሕርት ቀት ገባ።
በ ሻለቃ ሙዓመር ቃጣፊ በመሩት መፈንቅለ መንግሥት ዚንጉስ ኢድሪስን ዘዉዳዊ አገዛዝ ሲያስወግዱ ወጣቱ ዹጩር መኮንን ኹቃዛፊ ቀኝ እጆቜ አንዱ ነበር።
ኾሊፋ እንደ ወታደር ምሜግ ገብቶ እንደ ፖለቲኚኛ ቀተንግስትን ዚሚያማትሚዉን ዚናስር አስተምሕሮን ሲያቀነቅኑ ፋይዝ ትምሕርት ቀት እያማሚጡ ዩኒቚርስቲ ለመግባት ይዘጋጁ ነበር።
በዉልደት ክልስ ባመለካኚት ቅይጥ ዚሆኑት ዚመስመር መኮንን ሶቭዬት ሕብሚት ሔደዉ ዚአብዮታዊ ዹጩር መኮንንነትን ተምሹዉ ተመለሱ።
በ አሚቊቜ እና እስራኀል ሲዋጉ ሲና በሹሐ ዹነበሹዉን ዚእስራኀል ጩር ምሜግ ሰብሮ ዚገባዉ ዚአሚብ ጩር አባል በመሆናቾዉ ተሾልመዉ ተሟሙ።
በ ቻድን ዹሚወጋዉን ጩር እንዲያዙ ሲሟሙ ፈይዝ አልሰራጅ በሥነ ሕንፃ አርክቮቾር ትምሕርት ኚዩኒቚርስቲ ተመሚቁ።
ዚአሜሪካዉ ማዕኹላዊ ዚስለላ ድርጅት መሹጃ አቀባይ ሰላይ መሆናቾዉ በሰፊዉ መነገር ዹጀመሹዉም ያኔ ነዉ።
ዚሥነ ሕንፃዉ ባለሙያ ፋይዝ አልሰራጅ ግን በዚህ ሁሉ መሐል ዚሊቢያ ዚቀቶቜ ጉዳይ ሚንስ቎ር ባልደሚባ ሆነዉ ይሰሩ ነበር።
ኹ ጀምሮ አልሰራጅ ዚፖለቲካ ኃይልና ተጣማሪ እዚቀያዚሩ ዚትሪፖሊን ፖለቲካ ሲዘዉሩ ሐፍጣር ኚቀንጋዚ ተቀናቃኞቻ቞ዉን ተራ በተራ እያጠፉ ኃይላቾዉን ያጠናኚሩ ነበር።
ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሊቢያ ተዋጊዎቜ ላይ ዹጩር መሳሪያ ሜያጭ ማዕቀብ ጥሏል።
በ ዚተባበሩት መንግሥታት ዚፀጥታ ጥበቃ ምክር ቀትን ዉሳኔን በመጣስ ሊቢያ በቊምብ እድትደበደብ ሲወሰን ኢጣሊያ ዚትነበሚቜ።
ዚያኔዎቹን ጀብደኞቹን መሪዎቜ ማንነት ሁሉም ስለሚያወቀዉ እኔ መጥቀስ ያለብኝ አይመሰለኝም።
ላቭሮቭ ጀብደኛ ያሏ቞ዉ ዹ ዶቹ ወራሪዎቜ ሳርኮዚ ካሜሩን እና ኊባማ ነበሩ።
ዚአንካራና ዚሞስኮ መሪዎቜ ዚሊቢያ ተፋላሚ ኃይላትን ተኩስ እንዲያቆሙ ማስገደዳ቞ዉ ንቅናቄዉ ለሰላም ወዳዶቜ ሳይደግስ አይጣላም ዓይነት ሆኖ ነበር።
ይሁንና ባለፈዉ ሳምንት ተኩስ አቁሙን በፊርማ ለማፀደቅ ሞስኮ ላይ ዚተጠራዉን ድርድር ዹጩር አበጋዝ ኾሊፋ ሐፍጣር ማቋሚጣ቞ዉ ተስፋ በተስፋ ያስቀሚዉ መስሏል።
ትናት በርሊን ዹተደሹገዉ ዓለም አቀፍ ጉባኀ ደግሞ ዚሞስኮዉን ጅምር ዚሚያጠናክር ዚተኩስ አቁሙን ዚሚያፀና መሆኑ በሰፊዉ ተነግሯል።
ዹጀርመኑ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሐይኮ ማስ ኹሚነገሹዉም አለፍ ብለዉ ለሊቢያ ሰላም ዚሚወርድበት ቁልፍ አግኝተናል ይላሉ።
ዚገንባንበት ጉባኀን ዓላማ ዛሬ ኚግቡ ካደሚስን በኋላ ዚሊቢያን ጊርነት ዚምንፈታበትን ቁልፉ አግኝተናል ማለት እቜላለሁ።
እስካሁን በሊቢያዉ ቀዉስ በቀጥታ እጃ቞ዉን ካላስገቡ ትላልቅ ዚአዉሮጳ ሐገራት አንዷ ጀርመን ናት።
ጀርመን ዚጚበጠቜዉ በማስ አገላለጥ ዚመትሔ ቁልፍ ዚአዉሮጳ ሕብሚት እንዲሆን ዚሕብሚቱ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮቜ እዚመኚሩ ነዉ።
ዚቱርክ ዹሹጅም ጊዜ ጠላት ግሪክ ግን ዚሕብሚቱን ዚጋራ አቋም ለመሻር ትፎክራለቜ።
ግብር ኚፋዮቜ በሐሚሪ ክልል ቅሬታ እያሰሙ ነው ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚሰማያዊ ፓርቲ ውዝግብ በነኢንጅንዚር ይልቃል ጌትነት ዚሚመራው ዚሰማያዊ ፓርቲ ክንፍ ፓርቲውን ወደ ቀድሞው ህጋዊ ዚአመራር ጥንካሬው ለመመለስ እዚተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታወቀ።
ይኾው ዚፓርቲው ክንፍ ትናንት በአዲስ አበባ ባካሄደው ስብሰባ ይህን ዚፓርቲውን እቅድ ዚሚያስፈጜም አንድ ዚስራ አስኪያጅ ኮሚ቎ም ማቋቋሙንም ገልጿል።
ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ዚተኅዋሲዉን ስርጭት ለመቀነስ ይህን ያህል ሚና ይጫወታል ብለን መዘርዘር ባንቜልም አደጋዉን ለመቀነስ ሚና እንዳለዉ እሙን ነዉ።
በኀቜ አይቪ ላይ ዚሰራነዉ ስህተት ዚኮሮና ላይ ልንደግም አይገባም።
ሁሉም በጥምሚት በጋራ ዚሚሰራበት ጊዜ ነዉ ተወያዮቜ ያነስዋ቞ዉ ነጥቊቜ ና቞ዉ።
ያም ሆኖ ለተኅዋሲዉ ማርኚሻ ዹሚሆን መድሐኒትም ይሁን መኚላኚያ ክትባት አልተገኘም።
ዚኮሮና ተኅዋሲ ስርጭትን ለመግታት ዹዓለም ሃገራት መንግሥታት በዚሃገሮቻ቞ዉ ዚተለያዩ ዚጥንቃቄ ድንጋጌዎቜን እያሳለፉ ነዉ።
ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዚኮሮና ሥርጭትን ለመግታት ለአምስት ወራት ዹሚዘልቅ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን አስታዉቋል።
በኢትዮጵያ ኅብሚተሰቡ በተኅዋሲዉ እንዳይያዝ ነባሩን ማኅበራዊ ትስስር እንዲገታ ለማድሚግ ዹሚደሹገዉ ሙኚራም ኚባድ ሲሆን ታይቶአል።
ዚኮሮና ስርጭትን ለመግታት ኢትዮጵያ ኚሌሎቜ ሃገሮቜ ምን ልምድን ትዉሰድ
በሃገሪቱ ዉኃ በወሹፋ ዚሚታደልበት አሰራር በመኖሩ ዚንጜሕና መጠበቅያ ዉኃ እጥሚት ቢኖር እንኳ ንክኪን መቀነስ አካላዊ ቅርቀትን መጠበቅ ያስፈልጋል።
ዚኮሮና ተኅዋሲ አደገኝነነት ለጥቁር አልያም ለአፍሪቃ አደጋ ዹለዉም በሚል በተሳሳተ መሹጃ ቜላ ተብሎ ነበር።
ነገር ግን ሃገሪቱ ላይ ዚመጀመርያዉ ዚኮሮና ተኅዋሲ ታማሚ ኹተገኘ በኋላ ጉዳዩ አጜኖት ተሰጥቶት ጥንቃቄ ለማድሚግ እዚተሞኚተሚ ነዉ።
ዚኮሮና ተኅዋሲ በመጀመርያ በኢትዮጵያ ሳይሆን በሌሎቜ ሃገሮቜ ተዛምቶ መሹጃዉ እኛ ጋር ቢደርስም በቅድምያ ጥንቃቄ ለማድሚግ እድሉን አልተጠቀምንም።
ለዚህ ምክንያቱ ዚኅብሚተሰቡ አንድ ላይ ዹመኖር ባህላዊ ሁኔታ ሊሆን ይቜላል።
ወይም ኅብሚተሰቡ ላይ ያለዉን ዚባህሪ ለዉጥ ለማምጣት አስ቞ጋሪ ይሆናል።
ኮሮና ኹሁለተኛዉ ዹዓለም ጊርነት ወዲህ ዹተኹሰተ ኚባድ ቀዉስ ነዉ።
እንዲህ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ሕዝብን ዚሚያፈናቀል እንዲህ ፍርሃት ዉስጥ ዚሚኚት ሁኔታ ታይቶ አይታወቅም።
ማኅበራዊ ትስስር በጎላበት በኢትዮጵያ ኮሮናን ለመኹላኹል ዹሚደሹገዉ ጥሚት ኚባድ አድርጎታል።
ለምሳሌ ኚአዲስ አበባ ም ኚንቲባ ጀምሮ ዚተለያዩ ሚኒስትሮቜ ኅብሚተሰቡን ስለኮሮና ጥንቃቄ ንቃትና ትምህርት ለማድሚግ ሲጥሩ ይታያል።
ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ዚተኅዋሲዉን ስርጭት ለመቀነስ ይህን ያህል ሚና ይጫወታል ብለን መዘርዘር ባንቜልም አደጋዉን ለመቀነስ ግን ሚና እንዳለዉ እሙን ነዉ።
በአፍሪቃ ዚኮሮና ተኅዋሲ መዛመት ታሪክ ሲታይ አብዛኛዉን ዚሚታዚዉ በኚተሞቜ ላይ ነዉ።
ይህ ዹሆነዉ በአፍሪቃ ዋና ኚተሞቜ ኚአዉሮጳ አልያም ኹሌላ ክፍለዓለማት ኚተኅዋሲዉ ጋር ንኪኪ ያላ቞ዉ ተጓዊቜ ስለሚገቡ ነዉ።
ኢትዮጵያ ላይ ያለዉን ሁኔታ ስንወስድ አዲስ አበባ ላይ ይህ ይታያል።
በሌላ በኩል ኹተማ ዉስጥ ዹሚኖሹዉ ሕዝብ ቁጥር በጣም ኹፍተኛ እና ተጠጋግቶ ዹሚኖር በመሆኑ ነዉ።
ዚተኅዋሲዉን መዛመት ስናጀን አዲስ አበባ ኚሌሎቜ ኚተሞቜ ጋር ያ ለዉን መስተጋብርም ማጀን ይኖርብናል።
ግን አሁንም ይህ ጉዳይ ሊጀን ይገባል ወደ አዲስ አበባ እንደልብ መዉጣት መግባት ይቻላል።
ስንት ሰዉ ተመርምሮ ስንት ሰዉ ተገኘበት ብሎን ልንጠይቅ ይገባል።
በሃገሪቱ ዉስጥ ኮሮናን ለመርመር ያለዉ አቅም እጅግ ጥቂት ነዉ።
ስለዚህም መሹጃ ስንሰጥ ኹዚህ ሰዉ መካኚል ይህን ያህል ተመርምሮ ይህን ያህል በተህዋሲዉ ተይዞ ተገኘ ብለን ግልፅ ልናደርግ ይገባል።
በመሹጃዉ ላይ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል ተብሎ በአጜሕኖት ሊነገር ይገባል።
በዚህ ወቅት ምንም አይነት ዚፖለቲካ ልዩነት ዚሚታይበት መድሚክ ሊኖር አይገባም።
ዚኮሚና ተኅዋሲ ወሚርሺኝ ዹዓለምን ዚጀና ፖሊስ ዚጀና መርህ ያጋለጠበትም አጋጣሚ ነዉ።
ዚሃገራት ፖለቲኚኞቜም ሆኑ ዚጀና ባለሞያዎቜ በጀና ፖሊስያቜን እንዎት እናስተካክል በተለይ ዚወሚርሜኝ ሕክምናን እንዎት እናቃል ብለዉ ዳግም መርሃቾዉን ዚሚፈትሹበት ይሆናል።
በሌላ በኩል በተለይ በአፍሪቃ ዚኮሮና መፈወሻ መድሃኒት ናቾዉ ተብሎ እዚተራገፉ ናቾዉና ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል።
ተኅዋሲዉን ማርኚሻም ሆነ መኚላኚያ መድሃኒትም ሆነ ክትባት እስካሁን አልተገኘም።
በዉይይቱ ዚተሰታፉትን በማመስገን ሙሉ ዉይይቱን ዚድምፅ ማድመቻ ማይቀፉን በመጫን እንዲኚታተሉ እንጋብዛለን
ኚመቶ ዓመታት በላይ ዘልቋል ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ውጀቶቜ በዚጣቢያዎቜ ይፋ ተደርገዋል መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚመንግሥት ባለስልጣናት መታሠር በዛሬዉ ዕለትም ዚኊሮሚያ ፍትህ ቢሮ ዚኮሙኒኬሌን ጉዳዮቜ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ መታሰራ቞ዉ ተሰምቷል።
ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኀርትራ ላይ ዚጣለዉ ማዕቀብ እንዲነሳ ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ኹዚሕ ቀደም ያቀሚቡት ጥያቄ ድጋፍም ተቃዉሞ ገጥሞታል።
ይህ ዕልቂት በሰዉ ልጆቜ ላይ ዹተፈፀመ ወንጀል ነዉ ሲልም ድርጅቱ ገልጿል።
ዚድርጅቱ ዚሰብዓዊ መብት ኮሚሜን ሀላፊ ሚሾል ባቜሌት እንደገለፁት ግጭቱ ኚተቀሰቀሰባ቞ዉ አራት ቊታዎቜ ዉስጥ በሶስቱ ድርጅቱ ማጣራት አድርጓል።
በዩንምቢ ኹተማ ዉስጥ ቩንጌንዮ እና እንኮሎ መንደሮቜ ቢያንስ ወንዶቜ ሎቶቜና ህፃናት መገደላቾውን እና ሌሎቜ ሰዎቜ ደግሞ መጎዳታ቞ውን ማሚጋገጥ ቜለናል።
ዹተወሰኑ አስኚሬኖቜ ወደ ኮንጎ ወንዝ በመወርወራ቞ው ዚሟ቟ቜ ቁጥር ኹዚህ በላይ ሊጹምር ይቜላል ተብሎ ይታመናል።
ዚድርጅቱ ዚምርመራ ቡድን ናባናዚ በተባለዉ ቊታ ማጣራት ያላደሚገ በመሆኑ ዚሟ቟ቜና ዹጠፉ ሰዎቜ ቁጥር ሊያሻቅብ ይቜላል ዹሚል ግምት መኖሩንም ሃላፊዋ አመልክተዋል።
እንደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዘገባ ማጣራቱ በተደሚገባ቞ዉ ቊታዎቜ ዹጅምላ መቃብሮቜ ተገኝተዋል።
ግድያዉ ለማምለጥ ጊዜ በማይሰጥ ሁኔታ በፍጥነት ዚተካሄደና ዘግንኝ እንደነበርም በሪፖርቱ በዝርዝር መቀመጡን ሃላፊዋ ገልፀዋል።
በአንዳንድ ኹኔታዎቜ ዹዐይን እማኞቜ ዚኮንጎን ወንዝ ለማቋሚጥ ሲሞክሩ በርካቶቜ መገደላቾውን ሌሎቜ ኹነ ሕይወታ቞ው መቃጠላቾውን ገልጞዋል።
ኹቃጠሎዉ በህይወት ዚተሚፉትም ኹፍተኛ ዚአካል ጉዳት ደርሶባ቞ዋል በጎሳዎቹ መካኚል ዕርቅ ለማዉሚድ በድርጊቱ ዹሚጠዹቅ አካል መኖር አለበት ብለዋል።
ግጭቱ በተቀሰቀሰበት አካባቢ ዹሚገኙ ዚመንግስት ባለስልጣናትም ህዝቡን ኹአደጋ መኹላኹል ባለመቻላ቞ዉ ተወቃሟቜ መሆናቾውን ተናግሚዋል።