text
stringlengths
0
200
በአሁኑ ጊዜም ኚአዉሮጳ ሀገራት በበለጠ ስደተኞቜን ዚምትቀበለዉ ጀርመን ናት።
ይሄ እንግዲህ በሀገራቜን በመላዉ ኢትዮጵያ በድምቀት ዹሚኹበር አንዱ በዓል ነዉ።
ይሄ ዹሁሉም ዚክርስትና ኃይማኖት ተኚታዮቜ በዓል ስለሆነ በጣም ደስ ዹሚል ነዉ።
በዚህ በተለይ በዉጭ በጀርመን ሃገር ሁሉ ተሰብስቊ እንዲህ ሲያኚብር ሳይ በጣም ነዉ ደስታ ዚተሰማኝ።
ለኔ ደግሞ በተለይ በጀርመን ሳኚብር ዚመጀመርያዬም ስለሆነ በጣም ተደስቻለሁ።
በዓለም ላይ ሀገራት ዚሚሰደዱ ሰዎቜን ተቀብሎ ማስተናገድ ዓለማቀፍ ሕግ ነዉ።
ደብሚ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስትያን ዘማሪ አስካለ ማርያም ደመራን በፍራንክፈርት ስታኚንር ይህ ለሊስተኛ ጊዜ ነዉ።
በድምቀት አክብሚናል ዚተለያዩ ኃይማኖታዊ ክንዉኖቜን በማድሚግ አሳለፍን ዹኹርሞ ሰዉ ይበለን።
በስደት ሀገር ላይ ሆነን እንደዚህ በዝማሪ በተለያዩ ባህላዊ ክንዉኖቜ ታጅበዉ ህዝቡም ዹሀገር ባህል ልብሱን ለብሶ ተዉቩ ነዉ ዚተገኘዉ።
እዚህ ዚተወለዱትንም ልጆቻቜንን ባህላ቞ዉንና ወጋቾዉን እንዲያዉቁ ዚባህል ልብስን አድርገዉ ነዉ ዚመጡት በጣም ደስ ይል ነበር።
ባቡር ዉስጥ ሆነዉ ፎቶ ሲያነሱም አይቻለሁ ጀርመናዊዉ ዮሎፍ ዩስት መስቀል በዓልን በፍራንክፈርት ሲያኚብሩ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነዉ።
በዚህ በባዕድ ሀገር ይህን ያህል ሰዉ ይገኛል ብዬ አልገምትም።
ምዕመናኑ ስላሉ ነዉ አባቶቜ ወደዚህ ዚመጡት ምዕመናኑ ስላሉ ነዉ ቀተ ክርስትያንዋ ወደዚህ ዚመጣቜዉ።
ይህ በዓል ብዙ እሎት ያለዉ ነዉ ለዚህ ሀገርም ቢሆን ጀርመን ዚክርስትያኖቜ ሀገር ነቜ እና ነዋሪዉ ይህን ሲያይ ይደሰታል።
መላኹ ስብሃት ተክሌ ሲራክ ጀርመን በርካታ ዹዉጭ ዜጋ መኖሩን ሀገሪትዋ ለስደተኞቜ በርዋን መክፈትዋ በተመለኹተ ዹጀርመን ታላቅነት ያሳያል ሲሉ ነዉ ዚገለፁት።
ይህ ጉዳይ ዚነሱ ጉዳይ ሆኖ ዚሚያስፈልገዉን ነገር አሟልተዉ ተቀብለዉ አስተናግደዉ ማስቀመጣ቞ዉ በጣም ዹሚደነቁ ህዝቊቜ ና቞ዉ።
ወ ሮ መብራት በፍራንክፈርት ደብሚ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስትያን ስትመሰሚት ጀምሮ ወደዚቜ ቀተ ክርስትያን እንደሚሄዱ ነዉ ዚነገሩን።
ይህቜ ቀተ ክርስትያን ስትመሰሚት ጀምሮ ወደዚህ ቀተ ክርስትያን እመጣለሁ።
ዚብሪታንያ መንግሥት በበኩሉ ዹዹመን መንግሥት አቶ አዳርጋ቞ዉን ለኢትዮጵያ አሳልፎ መስጠቱን ዚጄኔቫ ሥምምነትን ዚጣሰ ብሎታል።
በአቶ አንዳርጋ቞ዉ ላይ ግርፋት ወይም ሌላ በደል እንዳይፈፀምባ቞ዉ ኚኀምባሲና ኹሕግ ባለሙያዎቜ ጋር ዹመነጋገር መብታ቞ዉ እንዲጠበቅ ጠይቋል።
አዉሮጳ እና ሰሜን አሜሪካ ዹሚኖሹዉ ኢትዮጵያዊ በዹኹተማዉ ባደሚገዉ ዹተቃዉሞ ሠልፍ ዚአቶ አንዳርጋ቞ዉን መያዝና መጋዝ አዉግዟል።
ዚኢትዮጵያ መንግሥትን ባለሥልጣናትን ሥለ ጉዳዩ ለማነጋገር ቢቻል በዚሕ ዉይይት እንዲሳተፉ ለመጋበዝ ለተኚታታይ ቀናት ሞክሹን ነበር ያገኘና቞ዉ እስተያዚት ለመስጠት ፈቃደኛ አይደሉም።
ዚእርምጃዉ ሕጋዊ ሠብኣዊና ፖለቲካዊ እድምታ ዚዛሬ ዉይይታቜን ትኩሚት ነዉ።
ኹ ዓመት ገደማ በፊት ሚሊዮን ሰዎቜ ናቾው በልብ ድካም ወይም በስኳር በሻታ ሳቢያ ሕይወታ቞ውን ያጡት።
ኚእነዚህም መካኚል ኹሞላ ጎደል ገሚሱ ለምሳሌ ያህል ሚሊዮን ገደማ ዚሚሆኑት ዓመት ሳይደፍኑ ነው ለሕልፈተ ሕይወት ዚተዳሚጉት።
ዚሞቱትም በካንሠር በልብ ድካም በሰውነት ውስጥ ዹደም ዹዝውውር ሳንክ እና በስኳር በሜታ ነው።
ድርጅቱ እንደሚያስገነዝበው ኹሆነ ኹመደበኛ በሜታዎቜ ይልቅ ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው በቀላሉ ሊገቱ ዚሚቜሉት ናቾው ዚጀና ጠንቆቜ ዚሆኑት።
ትምባሆ ዚአልኮል መጠጥና አለመንቀሳቀስ ለተጠቀሰው ዚሥልጣኔ በሜታ ሰፊ ድርሻ አላ቞ው።
በምግብ ላይ ጹው ማብዛትና ዹደም ጋፊት ማዹልም ዕድሜን እንደሚያሳጥሩ ዚሚያጠራጥር አልሆነም።
እ ጎ አ እስኚ በዚሁ ዚሥልጣኔ በሜታና ፍጻሜው ሳቢያ በሚያድጉ አገሮቜ ዹ ቢሊዮን ዶላር ያህል ኪሣራ ማስኚተሉ ዹማይቀር ነው።
ታዲያ ተደጋጋሞ ዹሚሰጠው ምክርም ሆነ ማስጠንቀቂያ ቜላ ስለሚባል ሊሆን ይቜላል ዚሥነ ቎ክኒኩ ዓለም ተጚባጭ ያለውን ማስገንዘቢያ ይዞ ለመቅሚብ ዚተገደደው።
በዚያ ዚኀሌክትሮኒክስ ዐውደ ርእይ ላይ ኹ ያላነሱ በዋናነት ዚሚጠቀሱ ዹሹቂቅ ኀልክትሮኒክስ ውጀቶቜ መቅሚባ቞ውም ነው ዚተገለጠው።
በግዙፉ ማለትም ካሬሜትር ስፋት ባለው ዹዐውደ ርእይ ቊታ እጅግ ዘመናዊ ዹተሰኙ አውቶሞቢሎቜም ቀርበዋል።
ዹጀርመኑ ሜርሰደስ ቀንዝ በላስ ቬጋስ ጎዳና ያለ ዘዋሪ ዚሚሜኚሚኚር አውቶሞቢል አቅርቩ ነበር።
ሙሉ አውቶማቲክ ተሜኚርካሪ ያለአሜኚርካሪ ተንቀሳቅሶ በአውቶሞቢሎቜ ማቆሚያ ሥፍራ ቊታ ፈልጎ ያላንዳቜ ሳንክ መቆም እንደሚቜል አሳይቷል።
በተመሳሳይ ሁኔታ አውዲ አውቶሞቢልም ይህን ማድሚግ እንደሚቜል በዐውደ ርእዩ ላይ ለመታዘብ ተቜሏል።
እንዲሁም ዚደቡብ ኮሪያው ሂዩንዎይ ዚተለያዩ ዚአውቶሞቢል ክፍሎቜ በልዩ ዚእጅ ሰዓት ትእዛዝ ዚሚንቀሳቀሱበትን ሁኔታ አሳይቷል።
ኚብስክሌተኞቜ ቆብ ብርሃን ይንጞባሚቅና ፊት ለፊት ዚሚመጣ ቮልቮ ተሜኚርካሪ ካለ ስልኩ ዚመንቀጥቀጥም ሆነ ዚንዝሚት ምልክት ይሰጣል።
ሆኖም ገበያ ላይ ኹመዋሉ በፊት ቆቡ አሁንም ተጚማሪ ፍተሻ እንደሚያሻው ቮልቮ አስታውቋል።
በዚያው ዚተጠቃሚዎቜ ዚኀልክትሮኒክስ ዐውደ ርእይ ዚስፌት መኪናም በካሜራ ርዳታ ቅድን ጥለትን እንደ መራጩ ፍላጎት አሳምሮ ራሱ መስፋትም መጥለፍም እንደሚቜል ታይቷል።
ዹዓይን መንጜር ተንቀሳቃሜ ምስልና ዚመሳሰለው ዚሚታይበት ኢምንት ዚ቎ሌቭዥን ሣጥን ሆኖም ያገለግላል።
በባርሎሎና እስፓኝ ኚዚያም በሃኖፈር ጀርመን ዘንድሮ ምን ተጚማሪ አዳዲስ ዚኀልክትሮኒክስ ውጀቶቜ ይቀርቡ ይሆን ጊዜው ሲደርስ ዹምንመለኹተው ይሆናል።
ዚስፖርት ዘገባ መጋቢት ቀን ዓ ም በስፔን ላሊጋ ክሪያስቲያኖ ሮናልዶ በ ደቂቃ ሐትሪክ በመሥራት ለቡድኑ ግቊቜን አስቆጥሯል።
ዹውጭ ጉዳይ ሚንሥትር መግለጫ ዚኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮቜ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ዚኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮቜ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ኚድምፅ ሰጭዎቹ አብዛኛዎቹ እቅዱን ቢቃወሙም ድምጹን ለመስጠት ዚወጣው ህዝብ ቁጥር ኹ በመቶ በማነሱ ህዝበ ውሳኔው ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።
በስተሰሜን ስሎቫክያ በስተሰሜን ምዕራብ ኊስትሪያ በስተምዕራብ ስሎቬንያ በስተደቡብ ምዕራብ ክሮኀሜያ እና በስተደቡብ ሰርቢያ በስተምሥራቅ ሩሜንያ በስተሰሜን ምሥራቅ ደግሞ ዩክሬን።
ሀንጋሪ ዹአሁኑን ድንበርዋን ዚያዘቜው ኚግዛትዋ በመቶውን ኚህዝብዋ ደግሞ በመቶውን ካሳጣት ኹአንደኛው ዹዓለም ጊርነት በኋላ ነው።
ኚጊርነቱ በኋላ በኮሚንስቶቜ ጎራ ስር ዚወደቀቜው ሀንጋሪ ዚምሥራቁ ጎራ ሲፈሚካኚስ በጥቅምት ዎሞክራሲያዊ ምክርቀታዊ ሪፐብሊክ ሆነቜ።
በጎርጎሮሳዊው ዓ ም ዚአዉሮጳ ኅብሚት ዚሆነቜው ሀንጋሪ ወደ ሚሊዮን ዹሚጠጋ ህዝብ አላት ።
ድምፅ ለመስጠት ኚወጡት ሀንጋርያውያን በመቶው ወይም ሚሊዮኑ እቅዱን ተቃውመዋል ።
ይሁንና ድምጜ ዹሰጠው ህዝብ ቁጥር በመቶ ብቻ በመሆኑ ህዝበ ውሳኔው ውድቅ ተደርጓል ።
ያም ሆኖ ኊርባን ለፓርቲያ቞ው ለፊዎስዝ ደጋፊዎቜ ባሰሙት ንግግር ውጀቱን እጹብ ድንቅ ብለውታል ።
በንግግራ቞ው ዹህዝበ ውሳኔውን ተቀባይነት አለማግኘት ግን ፈጜሞ አላነሱም ።
ኹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ወዲህ ታይቶ ዚማይታወቅ ዚተባለ ስደተኛ በገባበት ባለፈው ዓመት ድንበሯን በመዝጋት ዚመጀመሪያዋ ዚምሥራቅ አውሮጳ ሀገር ናት ።
እርምጃው በአውሮጳ ኅብሚት ቢወገዝም ዚሀንጋሪ መንግሥት ኹዚህ አቋሙ አሁንም ፍንክቜ አላለም ።
ኚእሁዱ ህዝበ ውሳኔ በኋላም ኊርባን ግባ቞ውን ለማሳካት በመጪዎቹ ቀናት ህገ መንግሥታዊ ማሻሻያዎቜን ለማድሚግ ዚሚያስቜሉ ህጎቜን እንደሚያወጡ እና እንደሚሰሩም አስታውቀዋል ።
ኊርባን መንግሥታ቞ው አሁንም ዚህብሚቱን እቅድ መቃወሙን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል ።
ጥያቄው ብራሰልስ አሁን ዚብዙሃኑን ውሳኔ ይቀበላል አይቀበልም ነው ።
ዚኊርባንን ማስፈራሪያ እና አዝማሚያ቞ውን ዚብራሰልስ ባለሥልጣናት እንደ ዋዛ አላለፉትም ።
እጅግ ዝቅተኛው ዚምርጫ ተሳትፎ ዚሌሎቜን መብት ዹሚጋፉ ህዝበ ውሳኔዎቜ ዚአውሮጳ ፖለቲካ ዚሚካሄድበት መንገድ አለመሆኑን በድጋሚ ያሳያል ።
እዚህ ጥያቄው ህዝበ ውሳኔ ሳይሆን አንድ አምባገነን መሪ ለፀሹ ዹውጭ ዜጋ መርሁ ምኞት እና ፍላጎት ማሚጋጋጫ ማግኘት ነበር ።
ህብሚቱ እስኚ መጪው ዚጎርጎሮሳውያኑ ዓም መጚሚሻ ደግሞ ሺህ ያህሉን ለአባላቱ ለማኹፋፈል አቅዷል ።
ዚህብሚቱ አባል ሀገራት ዹሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሮቜ ባሳለፉት ውሳኔ መሠሚት ሀንጋሪ ስደተኞቜን መቀበል አለባት ።
ሀንጋሪ ግን ይህን በመቃወም አቀቱታዋን ለአዉሮጳ ዹበላይ ፍርድ ቀት አቅርባ ነበር ።
ኚዚያ በኋላ ደግሞ በእቅዱ ላይ ህዝበ ውሳኔ ጠራቜ ።
ሀንጋሪያዊው ዚፖለቲካ ሳይንቲስ ጋቩር ቶሮክ አሁን ሊተኮርበት ዚሚገባው ዋናው ጉዳይ ውጀቱ ነው ይላሉ ።
ውድቅ ኹሆነው ህዝበ ውሳኔ በኋላ ተቃዋሚዎቹ ዚግራ እና ዹቀኝ ፓርቲዎቜ ኊርባን ኚሥልጣን ይውሚዱ እያሉ ነው ።
ሀገሪቱ አንድ ላይ ናት ዋናው ነገር ብዙሀኑ ኮታውን እምቢ ሲል ድምጹን መስጠቱ ነው ።
በመቶ ዹሚሆነው ህዝብ ለህዝበ ውሳኔው ደንታ አልነበሹውም ወይም በጥያቄው አልተስማማም ።
እኚህ አስተያዚት ሰጭ ደግሞ ኊርባን እስካሁን ኚተናገሩት በላይ ዹህዝበ ውሳኔው ውጀት ሊያመጣ ዚሚቜለውን ነገር ያብራሩልን ሲሉ ጠይቀዋል ።
ቪክቶር ኊርባን ውጀቱ በብራሰልስ ምን እንደሚያስኚትል አንድ ዹተጹበጠ ነገር መናገር ኚቻሉ ዹበለጠ እናውቃለን ።
ማንም ምንም እስካልተናገሚ ድሚስ እኛ ዹምናውቀው ህዝበ ውሳኔው ተቀባይነት እንደሌለው ነው ።
ተቃዋሚዎቜ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶቜ እንዲሁም ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ህዝቡ ድምጹን ለመስጠት እንዳይወጣ ሲቀሰቅሱ ነበር ።
ኹተሰጠው ድምፅም ኹ ሺህ በላይ ዹሚሆነው ተቀባይነት አላገኘም ።
ኹህዝበ ውሳኔው በፊት መንግሥት ለቅስቀሳ ዚተጠቀመባ቞ው ዚ቎ሌቪዥን ማስታወቂያዎቜ ስደተኞቜን ኚአሞባሪነት እና ኹወንጀል ጋር ዚሚያያዙ ነበሩ ።
ሀንጋርያውያን አብዛኛው ህዝብ ስለ መጻኀ እድሉ አለመጹነቁ አሳስቧ቞ዋል ።
ኚአውሮጳ ኅብሚት ጋር በጀመሩት እሰጣ ገባ ዚቀጠሉት ኊርባን ግባ቞ውን ለማሳካት እወስዳለሁ ያሏ቞ው እርምጃዎቜ በርካታ ትቜቶቜ እዚተሰነዘሩባ቞ው ነው ።
ዚማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ ቅኝት ጠቅላይ ሚንሥትር አቢይ አህመድ ዹአምቩ ጉብኝት እና ዚኅብሚተሰቡ ዚለውጥ ተማጜኖን ይዳስሳል።
ጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁን እንዲያነሱ ዚለውጥ አቅጣጫ቞ውንም እንዲያመላክቱ ዚሚወተውቱ ጥያቄዎቜ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ እዚተነሱ ነው።
ኚተለያዩ ዚማኅበሚሰቡ አባላት ጋር ኚጀመሩት ንግግር ባሻገር ሌሎቜ ጉዳዮቜን ለመመልኚት ጊዜ ያስፈልጋ቞ዋል ሲሉ ዚሚሞግቱም አሉ።
ሹቂቁ በኢትዮጵያ ገዢው መንግሥት ሰብአዊ መብቶቜን እንዲያኚኚብር ብሎም ለመልካም አስተዳደር ትኩርት እንዲሰጥ ይጠይቃል።
በሳምንቱ ዚማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ መነጋገሪያ ኚኟኑ ጉዳዮቜ መካኚል ዹጠቅላይ ሚንሥትር አቢይ አህመድ በአንቩ ኹተማ ያደሚጉት ንግግር ይገኝበታል።
በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ነዋሪዎቜ ዹጠቅላይ ሚንሥትሩ ንግግርን በሥፍራው ተገኝተው ያደመጡ ሲኟን ይኜን መልእክት ዚያዘው ዚቪዲዮ ምስልም በትዊተር እና ፌስቡክ ተንሞራሜሯል።
በጠቅላይ ሚንሥትሩ ንግግር በመደመም አድናቆት ዚሰጡም ትቜት እና ተቃውሞ ዚሰነዘሩም ነበሩ።
በትዊተር እና በፌስቡክ ብሎም በዋትስአፕ ኚተሰጡት ዚድጋፍ እና ዚትቜት አስተያዚቶቜ ዚትዊተሮቹን እናስቀድም።
ዚቀድሞ ዚአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ አቢይ ተክለማርያም በትዊተር ገጹ ቀጣዩን መልእክት በእንግሊዝኛ አስፍሯል።
አቢይ ሰዎቜን ማነጋገር ይወዳል በማለት ይንደሚደራል አቢይ ጠቅላይ ሚንሥትር አቢይን ሲገልጣ቞ው።
ስትል ጜሑፏን ዚጀመሚቜው ሐና ጫላፊ ዚቀድሞው ሰርዐት ስትሉ ኚዶክተር አብይ በፊት ዹነበሹውን ኢህአዎግ ነው ዚምናስገባው ወይስ ደርግን ነው
እናመሰግናለን ክቡር ጠቅላይ ምኒስትር አሁን ኹሁሉም ነገር በላይ ዹሆነው አንድነትና ሰላም እዚሞተተን ነው በሞገስ ሀሚጎት ዹተሰጠ አስተያት ነው።
አብይ ዚበፊቱን በሚያወግዝ መልኩ ኹአሁን በኃላ በሚሉ ቃላቶቜ ዚታጚቀ ንግግር ነው ዚሚናገሚው።
በኹዚህ በፊቱም አመራር ላይ እኮ እሱም ነበሹ አሁን መቌስ አዲስ ጭንቅላት አላስገጠመ ብሏል።
ኀቜ አር ዚተባለው ዚውሳኔ ሐሳብ በዩናይትድ ስ቎ትስ ሕግ መምሪያ ምክር ቀት መጜደቁ በሣምንቱ ዋና ዚመነጋገሪያ ዹነበር ርእሰ ጉዳይ ነበር።
ውሳኔ ሐሳቡ በኢትዮጵያ ዹተፈጾሙ ግድያዎቜ እንዲጣሩ ዚታሰሩ እንዲፈቱ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ እና አፋኝ ዚተባሉ ሕግጋት እንዲሻሩ ይጠይቃል፡፡
ዚውሳኔ ሐሳቡ ኚመጜደቁ ቀደም ባሉት ጊዜያት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዎዎቜ ዹምክር ቀት አባላቱን ለማሳመን ኹፍተኛ ዘመቻ ተኚናውኗል።
ዚዘመቻው ተሳታፊዎቜ በዩናይትድ ስ቎ትስ ዹሚገኙ ዚኮንግሬስ አባላትን ዚትዊተር አድራሻ በማያያዝ ድጋፍ እንዲሰጡ በተደጋጋሚ ወትውተዋል።
ዚውሳኔ ሐሳቡ መጜደቁ ዚዘመቻው ተሳታፊዎቜን እና ሌሎቜ ዚውሳኔው ደጋፊዎቜን እጅግ አስደስቷል።
ማይክ ኮፍማንፊ በኮሎራዶ ግዛት ዚስድስት ዚምርጫ ወሚዳዎቜ ተወካይ ሲኟኑ ክሪስ ስሚዝ ዹኒው ጄርሲ አራተኛውን ዚምርጫ ወሚዳ ይወክላሉ።
እነዚህ ሁለት ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ዹሕግ መምሪያ ምክር ቀት አባላትን ኢትዮጵያውያን ውለታቜሁን መቌም አንሚሳም ሲሉ አወድሰዋል።
ፕራውድ ኢትዮጵያ በሚል ዚትዊተር አድራሻ ለማይክ ኮፍማን ዹቀሹበ መልእክት እንዲህ ይነበባል።