text
stringlengths
0
200
በትጋት ላደሚጉት በተጹቆነው ዚኢትዮጵያ ማኅበሚሰብ ስም እጅግ በጣም አመሠግናለሁ ማለት እፈልጋለሁ።
በሁለቱ ፖለቲኚኞቜ እና ዚውሳኔ ሐሳቡን ያጞደቁትን ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ኹፍተኛ ፖለቲኚኞቜ ያወገዙም አሉ።
ዚኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ ውሳኔው ወቅቱን ያልጠበቀ እና ያልተገባ ነው ሲል ተቜቷል።
አሁን ገና ዹሰላም አዹር መተንፈስ መጀመራቜንን እንደሰሙ አፀደቅን ምናምን እሚሉን
በውሳኔ ሐሳብ ዚተነሱትን ጥያቄዎቜ በተመለኹተም ጜሑፉን ሲቀጥልፊ ዹአሁኑ ጠ ሚ እንደሚያደርጋ቞ው ባለሙሉ ተስፋ ነን።
በዘር ተኹፋፍለን አንዱ በይ ሌላው ተመልካቜ ዹሚል አስተያዚት አስፍሯል።
ጉራቻ ጉማባሱ ዚተባለ አስተያዚት ሰጪፊ ለወያኔዎቹ ዚመጚሚሻዉ ዚራስ ምታትና ኮንትሮባንዳ቞ውን ዋጋ ያሳጣ ውሳኔ ስለሆነ ይወተውታሉ ግን ማምለጥ አይቜሉም ብሏል።
ዚኢትዮጵያ ቜግር በኢትዮጵያውያን እንጂ በአሜሪካውያን ሊፈታ አይቜልም ዹወርቁ ዋንታላ አስተያት ነው።
ወያኔዎቜ ምንም አይነት በደል ካልሰሩ ዹተሰኘውን ሕግ ለምን እንደዚ አጥብቀው ጠሉት
ማይክ ሐሹር፩ ዚኢትዮጵያ አለቃ አሜሪካ ሳትሆን ህዝቊቿ ናቾው ።
ሰብአዊ መብት ካወቁ በሶርያ ምንም በማያውቁት ህፃናት ላይ ቊምቊቜን ለምን ያዘንባሉ ሲል ዮሎፍ ደሳለኝፊ መግለጫ ብቻ ኹሆነ ለምን እንዳይፀድቅ ጣሩ
ለማስፈፀም ዚምሯሯጡት ዲያስፖራዎቜ ፀባ቞ው ኚኢህአዎግ ጋር ነዉ ወይስ ኚኢትዮጲያ እስቲ ይንገሩን።
ዓላማዉ ዚኢትዮጲያን መንግስት ስልጣንና ተግባር በመድፈቅ ሙሉ በሙሉ በምዕራባዉያን ሕግ ለመተካት ያለመ ተግባር ነዉ ብሏል፡፡
ክሪስቶፈር መኮንን ደግሞ፩ ኀቜ አር ሕግ እንዲኟን ደግሞ እንግፋ ዹሚል አስተያዚት ሰጥቷል።
ኚጥንቷ ዚሮማ ገዢዎቜ ዘር ዹሚወርሰዉ ያ ወጣት ዚቅዱስ ሮማ ሥርወ መንግሥት ኹተሰኘዉ ጎራ ተሠልፎ ሲዋጋ ቡድኑ ተሾንፎ ኚተማይቱ በጣሎቶቹ ተማሚኚቜ።
ዚጳጳሱ ታማኞቜ ይባሉ ዚነበሩት አሞናፊዎቹ ዳን቎ አምስት ሺሕ ፍሎሪን ዚፍሎሬንሶቜ ገንዘብ እንዲኚፍል አለያም በእሳት ተቃጥሎ እንዲገደል ፈሚዱበት።
ይሕ ዚሥነፅሁፍ በሚኚቱ ዳን቎ን በወገኖቹ ዘንድ ኢል ሶሞ ፖኀታ፥
ልዕለ ገጣሚ ሲያሰኘዉ በአለም አቀፍ ደሹጃ ደግሞ ፔትሬርክና ኚቊካሺዮ ጋር ተደምሮ ዚኢጣሊያ ሥነፅፍ ዘዉዶቜ ዹሚል አክብሮት አስቜሮታል።
ለዳን቎ ኢጣሊያ በተለይም ፍሎሬንስ ዉስጥ ዚተለያዩ መታሰቢያ ሐዉልቶቜ ቆመዉለታል።
እንደ አዉሮጳዉያኑ አቆጣጠር በ ዎቹ መጀመሪያ ዚተበዚነበት ፍርድ ዚተነሳለት ግን ባለፈዉ አመት ሰኔ ነበር።
ዳን቎ በሕወቱ ኮሞዲያ ያለዉን መፅሐፉን ዚመጀሪያዉ ዚሕወት ታሪክ ፀሐፊዉ ቊካሺዮ ዲቪና ያኚለበትን ቅኔ ዚሮማዉ ወኪላቜን ተኜለ እግዚ ገብሚዚሱስ ባጭሩ ያወጋን።
ኮሚሜኑ ሲቋቋም ጀምሮ ድጋፍ እና ተቃውሞ ገጥሞታል ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ቀጣዩ ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ፕሬዝደንት ሆነው ዚተመሚጡት ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ዘመቻ቞ዉ ወቅት እንዳሉት ዚሙቀት ልቀት መጠንን ለመቀነስ አምና ዚተደሚሰበትን ሥምምነት ያፈርሳሉ።
ዩናይትድ ስ቎ትስ ጃፓንን ጚምሮ ኚአስራ አንድ ዚፓሲፊክ አካባቢ ሐገራት ጋር ያደሚገቜዉን ዉል ን ይሰርዛሉ።
ዩናይትድ ስ቎ትስ ኚኩባ ጋር ዚነበራትን ዚግማሜ ምዕተ ዓመት ጠብ ለማርገብ ያደሚገቜዉ ስምምነት ኢራን ዹኑክሌር ጩር መሳሪያ እንዳታመርት ዚሚያግደዉን ዉሉ ይሰርዛሉ።
በተገን ጠያቂዎቜ መኖሪያዎቜ ላይ ዚተባባሰው ጥቃት ጀርመን ለስደት አዲስ ዚምትባል ሃገር አይደለቜም።
ጀርመናውያንም በተለያዩ ሃገራት ተሰደው ዚሚኖሩ ህዝቊቜ እንደመሆና቞ው ስደትን አያውቁትም ማለት አይቻልም ።
ሆኖም ለስደተኞቜም ሆነ ለስደት አዲስ ባልሆነቜው በጀርመን በውጭ ዜጎቜ ላይ በተለያዩ ጊዜያት ጥቃቶቜ ይፈፀማሉ ።
ኚቅርብ ወራት ወዲህ ጀርመን ውስጥ በተገን ጠያቂዎቜ ዚመኖሪያ ህንፃዎቜ ላይ ተኚታታይ ቃጠሎዎቜ ደርሰዋል።
ይህም በጎርጎሮሳውያኑ ዓመተ ምህሚት ኚተመዘገቡት ጥቃቶቜ በልጩ ነው ዹተገኘው ።
ጀርመን ውስጥ እነዚህን መሰል አደጋዎቜ ሲደርሱ ግን አዲስ አይደለም ።
በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በ ዎቹ በተለይ በምሥራቅ ጀርመን በውጭ ዜጎቜ ላይ ተመሳሳይ ጥቃቶቜ ደርሰዋል ።
ኚዚያን ወዲህም በተለያዩ አጋጣሚዎቜ ዚሚደርሱ እነዚህን ዚመሳሰሉ ዚዘሚኞቜ ጥቃቶቜ ሰለባ ዹሆኑ ዹውጭ ዜጎቜ ጥቂት ዚሚባሉ አይደሉም ።
በዶክተር ሜፈራው አስተያዚት ቀኝ አክራሪዎቜ ህብሚተሰቡ ተገን ጠያቂዎቜ ጀርመን መግባታ቞ውን እንዲቃወም ልዩ ልዩ ዘዎዎቜን ይጠቀማሉ ።
ጀርመን ዚምትቀበላ቞ው ተገን ጠያቂዎቜ ቁጥር ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚጚመሚ መሄድ እዚህ ሁሌም ዚሚያነጋግር ጉዳይ ነው ።
ዚስደተኞቜ ቁጥር ባደገ መጠን እነርሱን ለማስተናገድ ዚሚወጣው ገንዘብም ማኚራኚሩ አልቆመም ።
በጎርጎሮሳውያኑ ቱ ዹጀርመን ፌደራል ግዛቶቜ ለተገን ጠያቂዎቜ ጉዳይ ዹሚውል ተጚማሪ ቢሊዮን ዩሮ ያወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
ይህ ገንዘብም ሃገሪቱ በ ለዚሁ ለተገን ጠያቂዎቜ ኚመደበቜው በጀት በእጥፍ ዚሚበልጥ ነው ።
በዚህ ዓመት ጀርመን እንድትቀበላ቞ው ማመልኚቻ ያስገቡ ተገን ጠያቂዎቜ ቁጥር ኹ ሺህ ይበልጣል ።
ዚአመልካ቟ቹ ቁጥር በዚሁ ዓመት ኹ ሺህ በላይ ሊሆን እንደሚቜል ይገመታል ።
ጀርመን ይህን ያህል መጠን ያላ቞ውን ተገን ጠያቂዎቜ መቀበሏን ዹሚቃወሙ ወገኖቜና አንዳንድ ፖለቲኚኞቜ ሃገሪቱ ጫናው በዝቶባታል ሲሉ ይኚራኚራሉ ።
ኚጥቃቶቜ አብዛኛዎቹ ጀርመን ለጀርመናውያን ብቻ ዹሚል አስተሳሰብ በሚያራምዱ ቀኝ አክራሪዎቜ ና ደጋፊዎቻ቞ው ዹሚፈፀሙ መሆናቾው ይታመናል ።
ለምሳሌ ባለፉት ስድስት ወራት ኚደሚሱት አደጋዎቜ በመቶው በቀኝ አክራሪዎቜ ዹተፈፀሙ መሆናቾው ተነግሯል ።
አሁን አሁን ኹነዚህ ወገኖቜ ጋር ግንኙነት ዹሌላቾው ጀርመናውያንም ዹቀኝ አክራሪዎቹን አመለካኚት እንደያዙ ዶክተር መኮንን ያስሚዳሉ ።
ሆኖም በንፅፅር ዚተሻለ ሲባል በቆዹው በምዕራብ ጀርመንም በቀን አክራሪዎቜ ዹሚፈፀሙ ጥቃቶቜ እዚተባባሱ መሆኑ ነው ዹተነገሹው ።
በርሳ቞ው እምነት ይህን ለማስተካኚል ጥሚት እዚተደሚገ ቢሆንም ብዙ ይቀሹዋል ።
መጜሐፍትን በተንቀሳቃሜ ስልክ በስልክ ወይም በተመሳሳይ ዚኮምፒውተር መገልገያዎቜ ለንባብ ዚቀሚቡ መፅሀፍት ኢትዮጵያ ውስጥ መሞጥ እስካሁን ብዙም ዹተለመደ አይደለም።
በአንድ በኩል ይህንን አገልግሎት ዚሚሰጥ አፕሊኬሜን አለመኖሩ ሲሆን በሌላ ወገን ደግሞ ክፍያው በኩንላይን መፈፀም ስላለበት ነው።
ቮክኖሎጂውም እያደገ ሲሄድ ሰዎቜ መፅሀፉን በ ይገዙና እና ያነቡ ጀመር።
ዚኢትዮጵያ መጜሀፎቜን ለገበያ ያቀሚበው ሎሚ ቡክስ ወይም ሎሚ መፅሀፍት ኹነዚህ አንዱ ነው።
ሰዎቜ በቀላሉ ስልካ቞ውን ተጠቅመው መፅሀፍ ማንበብ እንዲቜሉ ነው ይላል ዹሎሚ መፅሀፍት መስራቜ ብሩክ ኃይሉ።
ለጊዜው ግን ዹዚህ ተጠቃሚ ዚሚሆኑት ዚአንድሮይድ ተገልጋዮቜ ብቻ ና቞ው።
ዚኢ ቡክ ወይም በዲጂታል መልክ ዚሚቀርብ መፅሀፍ ኚሚታተመው መፅሀፍ ጋር ሲነፃፀር ዋጋው መለስተኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ሌሎቜ አማራጮቜንም ይሰጣል።
አንባቢያን ዚማይቜሉት ነገር ቢኖር አንዮ ዚገዙትን መፅፋት ለሌላ ሰው መላክ ወይም ማጋራት ነው።
ሎሚ ቡክስ በአሁኑ ሰዓት ኹ መፅሀፎቜ ለገበያ እንዳቀሚበ ይናገራል።
ኹዚህም ሌላ ደራሲያኑ ምን ያህል መጜሀፋ቞ው እንደተሞጠ ራሳ቞ው ገብተው ዚሚቆጣጠሩበት መንገድ እንደተዘጋጀላ቞ው ዹሎሚ ቡክስ መስራቜ ይናገራል።
አንባብያኑም ኹዚህ ቀደም በቀላሉ ዚማያገኙትን አገልግሎት ይዘን ብቅ ስላልን ጥሩ አስተያዚት እዚሰጡን ነው ይላል ብሩክ።
ደራሲ ዮርዳኖስ አልማዝ ሰይፋ መንገደኛ ዹሚለው መፅሀፉን በሎሚ መፅሀፍት አማካኝነት በኩንላይን ኚሚሞጡ ደራስያን አንዱ ነው።
ደራሲው መፅሀፎቹን በአፕሊኬሜን መልክ ዚመሞጡ ጥያቄ ሲቀርብለት በደስታ ነው ዚተቀበለው።
ደራሲ አለማዹሁ ገላጋይም ቢሆን ሎሚ መጜሀፍት ሶስት መፅሀፎቹን ኩንላይን ላይ እንዲሞጥ ፈቅዷል።
ፍቃድ ጠይቀውት መፅሀፉ በኩንላይን ሲሞጥ ይህ ዚመጀመሪያ ጊዜው ነው።
ኹዚህ በፊት ግን ያለ ፍቃድ ስኬን እያደሚጉ መፅሀፎቌን በኩንላይን አሰራጭተዋል ይላል።
ዚፖለቲካ ፍጥጫ ያስኚተለው ስጋት እኛና እነሱ ዚፖለቲካ አሰላለፍ አገሪቱን ወደ አልሆነ አቅጣጫ እዚወሰዳት እንደሆነ ምሁራን አሳሰቡ።
ኚስልሳዎቹ አንስቶ ዚሚታዚው ዚተቃራኒ ፖለቲካ አካሄድ ዛሬም ሐገሪቱን እያሰጋ መሆኑን አመልክተዋል።
ዚሃሳብ ልዩነት መኖሩ መጥፎ እንዳልሆነ ዚጠቆሙት ምሁራኑ መነጋገርና መመካኚሩ ግን መፍትሄ ያመጣል ዹሚል እምነት እንዳላ቞ው ተናግሚዋል።
ይህን ተኚትሎም ዚውህደቱ ደጋፊዎቜና ዚውህደቱ ተቃዋሚዎቜ በዹፊናቾው እኛ እና እነሱ በሚል ዚፖለቲካ አሰላለፍ ገብተዋል።
ይህ ዚፖለቲካ አካሄድ አገሪቱን ወደ ባሰ ቜግር ውስጥ እንደሚወስዳት ምሁራን ስጋታ቞ውን ገልፀዋል።
ዚዲላ ዩኒቚርሲቲ መምህር ሚዳት ፕሮፌሰር ቎ዎድሮስ ተ ማርያምም ዚሁለቱን ምሁራን አስተያዚት ይጋራሉ።
አገሪቱና ህዝቊቿ አሁን ኚደሚሱበት አጣብቂኝ ውስጥ ለማውጣት ፖለቲኚኞቜ ዚሃሳብ ትግል አድርገው አሾናፊውን ሀሳብ መቀበል ተገቢ እንደሆነ ዶ ር ሲሳ ተናግሚዋል።
ዶ ር ገብሚ ኢዚሱስ እንደሚሉት ደግሞ ወደግጭት ኚሚመሩ ቃላትና ነገሮቜ መቆጠብና ኚራስ ስልጣን ይልቅ ዹአገርን ጥቅም ማስቀድም ይገባል።
ዹተቃውሞ ሰልፉን ዚጀመሚቜው አውስትራሊያ ስትኟን እንደ ተቃውሞ ሰልፉ አስተባባሪዎቜ ኚኟነ ቢያንስ ሰው በተቃውሞው ተሳታፊ ኟኗል።
በታይላንድ ሕንድ እና ደቡብ ኮሪያም ተማሪዎቜ እንዲሁም ዹሰልፉ ደጋፊዎቜ ተሳታፊ ኟነዋል።
በርሊን ኹተማ ውስጥ በተደሹገው ዚኚባቢ አዹር ጥበቃ ዹተቃውሞ ሰልፍ ሰዎቜ መሳተፋ቞ው ተገልጧል።
ቩን ዹሚገኘው ዚዶይ቞ ቬለ ሠራተኞቜም ዶይ቞ ቬለ ኚሚገኝበት ሕንጻ አቅራቢያ በሚገኘው ዚተባበሩት መንግሥታት መሥሪያ ቀት ፊት ለፊት ተኚናውኗል።
በመላው ዓለም ዙሪያ በዛሬው ዕለት ኹ በላይ ዹተቃውሞ ሰልፎቜ መኹናወናቾው ታውቋል።
ዚኢንተርኔት ጥሪ ቁለፋ መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
አፍሪቃ ዚካሜሩን ቀውስ እና ቀጣዩ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በካሜሩን ዚፊታቜን መስኚሚም ዓም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ይካሄዳል።
ዚሀገሪቱ ሕግ በሚፈቅደው መሰሚትም ዚምርጫው ዘመቻ በዛሬው ዕለት በይፋ ዘመቻ ተጀምሯል።
ዚካሜሩን ምርጫ ካሜሩንን ካለፉት ዓመት ወዲህ በሚመሩት ፕሬዚደንት ፖል ቢያ አንፃር ስምንት እጩዎቜ በተወዳዳሪነት ቀርበዋል።
ይሁንና ውዝግብ በቀጠለበት እንግሊዝኛ ቋንቋ ተናጋሪ በሆነው ዚሀገሪቱ አካባቢ ምርጫውን እና ዘመቻውን እንደታሰበው ማካሄድ መቻሉ አጠራጣሪ ሆኗል።
ይህንኑ አካባቢ ኹተቀሹው ካሜሩን ለመገንጠል ዚሚንቀሳቀሱት ታጣቂዎቜ እነርሱ ሀገር በሚሉት በዚሁ አካባቢ ዹውጭ ምርጫ እንዲካሄድ እንደማይፈቅዱ ዝተዋል።
ኹ ሚልዮኑ ዚካሜሩን ህዝብ መካኚል ፈሚንሳይኛ ቋንቋ ተናጋሪ ነው።
ይህን ተኚትሎ ታድያ ብዙ ሕዝብ በአካባቢው ተደጋግሞ በመታዚት ላይ ያለውን ግጭት መሞሹን መርጧል።
ዚግዛቱ ዋና አስተዳዳሪ ቀርናር ኊካሊያ ቢላይ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቎ሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ነዋሪዎቹ ወደዚመኖሪያ቞ው እንዲመለሱ ተማፅነዋል።
ዹጩር ኃይሉ በዚያ ያለው ህዝቡን እና ንብሚቱን ኚጥቃት ለመኹላኹል እና ጥቃቱን ለማስቆም ነው።
እንግሊዝኛ ተናጋሪዎቹ ዓማፅያን ናቾው ዹኃይል ተግባር እዚፈጞሙ ያሉት በሚል ዋና አስተዳዳሪ ቀርናር ኊካሊያ ቢላይ ያካባቢውን ህዝብ ለማሚጋጋት ሙኚራ቞ውን ቀጥለዋል።
ነዋሪዎቜ ኹለላ እንደሚደሚግላ቞ው በማስታወቅ በዚቀታ቞ው እንዲቆዩ ዚተማፀኑት ዋና አስተዳዳሪው ራሳ቞ው በሚኹ ላኹሏቾው ወታደሮቜ ታጅበው ነው ዚሚዘዋወሩት።
ባጠቃላይ ነዋሪዎቹ ውዝግቡ ባካባቢው እስካላበቃ ድሚስ ነፃና ትክክለና ምርጫ ማካሄድ ይቻላል ብለው አያምኑም።
በሰሜን ምዕራቡ እና በደቡብ ምዕራቡ ካሜሩን ግዛቶቜ ተዓማኒ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም።
እና በሁለቱ አካባቢዎቜ ነፃ እና ትክክለኛ ምርጫ ለማካሄድ ቢፈለግም ጊዜው በማለፉ በወቅቱ ምንም ሊደሹግ አይቜልም።
ብዙ እጩዎቜ ሰዎቜ ድምፃ቞ውን እንዲሰጡ ለማበሚታትት በመንቀሳቀስ ላይ ና቞ው።
ይሁንና እስካሁን ዹተቃዋሚው ዚካሜሩን ብሔራዊ ዜግነት ንቅናቄ ፓርቲ እጩ አፋኑዊ ብቻ ናቾው ውዝግብ ወደሚታይበት አካባቢ ዚሄዱት።
ዚህዝቡን ጥያቄ እና ፍላጎት ዚማያዳምጥ መንግሥት ስላለን ብቻ በውዝግብ ላይ ዚምትገ።
ሌላው ፕሬዚደንታዊ እጩ ጆሹዋ ኊሲህ ለቀውሱ ዚተሻለ መፍትሔ እንዳላ቞ው ነው ዚገለጹት።
ቜግሩ ወደ መገንጠል ጥያቄ ያመራው ህዝቡን ዹማግለሉ ድርጊት እና በህዝቡም ላይ እዚተፈጞመ ያለው ኢፍትሓዊ አሰራር ነው።
ጉዳዩን ዚሚሚዳ ፕሬዚደንት ካለ ቜግሩን ለማስወገድ በመጀመሪያ ህዝብ ለሚገለልበት አሰራር መፍትሄ መስጠት ነው።
እኔ ፕሬዚደንት ሆኜ ብመሚጥ ዚመጀመሪያው ውሳኔዬ ዹሚሆነው ጉዳዩ ዚፖለቲካ ቜግር መሆኑን አምኖ መቀበል ነው።
ዚካሜሩን አስመራጭ ቊርድ ሊቀ መንበር ኀኖው አብራምስ ምርጫው በሁሉም አካባቢዎቜ በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄድ ጥሚት በመደሹግ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።
ለምርጫ ዚሚያስፈልገው ቁሳቁስ ኹሞላ ጎደል ተዘጋጅቷል ዚድምፅ መስጫ ወሚቀቶቜን ዚመሳሰሉት ቁሳቁሶቜም ወዳካባቢው በመላክ ላይ ነው።
በካሜሩን ዚአውሮጳ ህብሚት ተጠሪ ሀንስ ፔተር ሻዎክ እንዳስታወቁት ህብሚቱ በምርጫው በታዛቢነት ባይሰማራም ዚምርጫውን ሂደት መኚታተሉ አይቀርም።