text
stringlengths
0
200
ሣምንታዊ ዚስፖርት ዘገባ በጀርመን ቡንደስሊጋ ቊሩስያ ዶርትሙንድ አጀማመሩ ዹሰመሹ ይመስላል።
እንደ አጀማመሩ ኹዘለቀም በሻምፒዮንስ ሊግ ፍልሚያ ኚሪያል ማድሪድ ጋር በሚያደርገው ጚዋታም አይበገሬ ሊሆን ይቜላል ተብሏል።
በሳምንቱ መጚሚሻ በተደሹጉ ዚእንግሊዝ ፕሬሚዚር ሊግ ዚእግር ኳስ ግጥሚያዎቜ እንደ ማን቞ስተር ሲቲ ኃያል በትር ዹሰነዘሹ ቡድን ዚለም።
ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትሚምፕ ኚአሜሪካ ዚብሔራዊ እግር ኳስ ሊግ ተጚዋ቟ቜ ጋር እሰጥ አገባ ገብተዋል።
ፕሬዚዳንቱ ደግሞ ተጚዋ቟ቹ ይሰናበቱልኝ ጥሪ በተለመደው ዚትዊተር ገጻ቞ው አስተጋተዋል።
ኬኒያዊው ውድድሩን በአንደኛነት ያጠናቀቀው ሰአት ኹ ደቂቃ ኹ ሰኚንድ በመግባት ነው።
ጉዬ አዶላ ለጥቂት በ ሰኚንዶቜ ብቻ ተቀድሞ ሁለተኛ ደሹጃ ማግኘት ቜሏል።
ዚሊስተኛ ደሹጃን በ በመሮጥ ዹተቆናጠጠው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሞስነት ገሹመው ነው።
በሎቶቜ ዹበርሊን ማራቶን ዚሩጫ ፉክክር ኢትዮጵያዊቷ ሩቲ አጋ በ ሰኚንዶቜ ብቻ ተቀድማ ሁለተኛ ደሹጃን አግኝታለቜ።
ዚሀገሯ ልጅ ቫለሪ አያባይ ብርቱ ፉክክር በማድሚግ በሩቲ አጋ ለጥቂት በ ሰኚንድ ተበልጣ ሊስተኛ ኟናለቜ።
እግር ኳስ በእንግሊዝ ፕሬሚዚር ሊግ ዚሳምንቱ መጚሚሻ ግጥሚያዎቜ እንደ ማን቞ስተር ሲቲ ኃያል ብትሩን ያሳሚፈ ቡድን ዚለም።
ማን቞ስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን አይቀጡ ቅጣት ዚቀጣው ለ በሆነ ሰፊ ልዩነት በማሾነፍ ነው።
቞ልሲም ዚግብ ክልሉን ሳያስነካ ስቶክ ሲቲን ለ ኩም አድርጎ ሞኝቷል።
ሊቹርፑል ላይስተር ሲቲን ለ ሲሚታ ማን቞ስተር ዩናይትድ ሳውዝሐምፕተንን ያሞነፈው ለ ነው።
ሊቹርፑል ዚቅዳሜ ድሉ ለአራት ጊዜያት ድል አልባ ዹነበሹው ጉዞውን ቀይሮለታል።
ኹ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ኚሜዳ ውጪ በተደሹጉ ተኚታታይ ጚዋታዎቜ ግብ ሲቆጠርበት ዚመጀመሪያው ኟኗል።
በቅዳሜው ሌላ ዚፕሬሚዚር ሊግ ጚዋታ ዋትፎርድ ስዋንሲ ሲቲን ለ አሞንፏል።
ትናንት በተደሹገ ጚዋታ ደግሞ ብሪንግቶን ኒውካስልን ለ በማሾነፍ በአንድ ደሹጃ መሻሻል አሳይቷል።
ቡንደስ ሊጋ በጀርመን ቡንደስሊጋ ስድስት ጚዋታዎቜ ቊሩስያ ዶርትሙንድ መሪነቱን አስጠብቋል።
በተለይ ቅዳሜ ዕለት ቊሩስያ ሞይንሜን ግላድባኅን ለ በኟነ ሰፊ ልዩነት ማሾነፍ ቜሏል።
በዚህ አያያዙ ቊሩስያ ዶርትሙንድ በነገው ዚሻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያ ለስፔኑ ኃያል ሪያል ማድሪድ ብርቱ ተገዳዳሪ መኟኑ አይቀርም።
ይህን ብቃት ታዲያ አሁን መተግበር ዚሚጠበቅባ቞ው በሻምፒዮን ሊጉ ዚሚገጥሙት ዚስፔኑ ኃያል ሪያል ማድሪድ ላይ ነው።
በሲግናል ኢንዱንዳ ስታዲዚም ዚሚገናኙት ሁለቱ ኃያላን ቡድኖቜ ኚባድ ፉክክር ያሳያሉ ተብሎ ተጠብቋል።
ሁለቱ ቡድኖቜ በስድስት ዚውድድር ዘመኖቜ ለአምስት ጊዜያት ተገናኝተው ያውቃሉ።
በአጠቃላይ ውድድሩ ሪያል ማድሪድ በጠበበ መልኩ ቊሩስያ ዶርትሙንድን ይበልጣል።
ኚሪያል ማድሪድ ጋር በሜዳው ባደሚጋ቞ው ግጥሚያዎቜ እስካሁን ድሚስ አንድም ጊዜ ተሾንፎ አያውቅም።
ዶርትሙንድ በሜዳው ሪያል ማድሪድን ለሊስት ጊዜያት ያሞነፈ ሲሆን ሊስት ጊዜ ደግሞ አቻ መውጣት ቜሏል።
ዚሳምንቱ ማሳሚጊያ ቊሩስያ ሞይንሜን ግላድባኅን ለ ያንኮታኮተው ቊሩድያ ዶርትሙንድ እስካሁን በድል ጎዳና ላይ እዚተሚማመደ ነው።
ኚስድስት ዚቡንደስ ሊጋውእ ግጥሚያ አምስቱን ድል በማድሚግ አንዱን አቻ ወጥቷል።
በደርጃ ሠንጠሚዡ ነጥብ ዹሰበሰው ቊሩስያ ዶርትሙንድ ግቊቜን ዚግብ እዳ አስተናግዷል።
በዋናነት ተቃውሞውን ያሰሙት ስፖርተኞቜ ዚአሜሪካ ዚብሔራዊ እግር ኳስ ሊግ ተጚዋ቟ቜ ና቞ው።
ፕሬዚዳንቱ በበርካታ ስፖርተኞቜ ዹተዛመተው እና ኚጚዋታ በፊት ዚብሔራዊ መዝሙሩ ሲሰማ ዚሚታዚው ተቃውሞ ኹዘር ጋር አንዳቜም ግንኙነት ዹለውም ብለዋል።
ትናንት በተኹናወኑ ጚዋታዎቜ ብቻ ተጚዋ቟ቜ አንድም በአንድ እግራ቞ው ሞብሚክ ብለው በመንበርኹክ አለያም እጅ ለእጅ በመያያዝ ተቃውሟቾውን ፕሬዚዳንቱ ላይ አንፀባርቀዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላ቞ው ታላቅ ዚኔነት ስሜት ለብሔራዊ መዝሙራቜን እና ለሀገራቜን።
እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር ኹ ወዲህ ስፖርተኞቜ በስፋት እና በጋራ ያሳዩት ተቃውሞ ተብሎለታል።
ሁሉም ዚሻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያዎቜ በተመሳሳይ ሰአት ኚምሜቱ ሰአት ኹ ደቂቃ ነው ዚሚኚናወኑት።
ገዜልሻፍት ፊውር በድሮተ ፈልኹር ዚተባለው ድርጅት እንዳመለኚተው ስደተኞቹ ይመለሱ በሚባልባት ኀርትራ ውስጥ አሁንም ግዙፍ ዚሰብዓዊ መብት ሚገጣ ይታያል።
ዚአውሮጳ ህብሚት ሁኔታውን በመመርመር ፈንታ ለምንድን ነው አንዳንድ ጥሪ በማቅሚቡ ላይ ብቻ ራሱን ዚሚገድበው
በኀርትራ እና በኢትዮጵያ መካኚል ባለው ውዝግብ ላይ አዘውትሚው ዚኢትዮጵያ መንግሥትን አቋም ነው ዚሚወስዱት።
እና ዚኀርትራ መንግሥት አመራር ራሱን ያገለለበትን ርምጃ እዚደገፉ ነው።
ለዚህ በኢትዮጵያ እና ኀርትራ መካኚል ለቀጠለው መጥፎ ውዝግብ ኚኀርትራ አመራር ጋር ዚይስሙላ ያልሆነ ግንኙነት እንዲፈጥሩ ኚማሳሰብ አልቊዘንም።
በመሆኑም በውዝግቡ መንሥዔ ላይ በማትኮር መፍትሔ መሻቱ ትርጉም ይኖሚዋል።
አዎ ምክንያቱም በእጃቜን ያሉትን መሚጃዎቜ ስንመለኚት ዹዮንማርክ ዚስደተኞቜ ጉዳይ መስሪያ ቀት ተሻሜሎዋል በሚል ያወጣው ዘገባ መሠሹተ ቢስ ነው።
ውሳኔው ስደተኞቜን ወደሀገራ቞ው መመለስ ዚሚያስቜል ሁኔታ አለመኖሩን ዚሚያሳይ ነው።
ስደተኞቜ ዹመቀበል አለመቀበል ጉዳይ ለአውሮጳ በጠቅላላ ቜግር በመሆኑ በዜርትራ ዚሰብዓዊ መብት ይዞታ ለሚሻሻልበት ጉዳይ ትኩሚት ሊሰጥ ይገባዋል።
በትናንቱ ምርጫ በመቶ ድምጜ በማግኘት ያሞነፈው ፓርቲያ቞ው ሲሪዛ ነፃይቱ ግሪክ በአህፅሮቱ ኚተባለው ፓርቲ ጋር ተጣምሮ መንግሥት እንደሚመሰርት ተገልጿል ።
በእሁዱ ምርጫ ወግ አጥባቂው አዲስ ዲሞክራሲ በመቶ ድምፅ በማግኘት ሁለተኛውን ደሹጃ ይዟል ።
ዹናዚ አስተሳሰብ ዚሚያራምደው ጎልድን ዶውን ዚተባለው ፓርቲ በመቶ ድምፅ በማሾነፍ ተኛ ደሹጃ አግኝቷል ።
በእሁዱ ምርጫ ኹ ግሪካውያን ኹ በላይ ዚሚሆኑት ድምጻ቞ውን እንዳልሰጡ ተዘግቧል ።
ስለ ግሪክ ምርጫና አንድምታው ዚብራሰልሱ ወኪላቜን ተኚታዩን ዘገባ ልኮልናል ።
ዚሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ሶስት ዹገጠር ቀበሌዎቜ ወደ አፋር ክልል እንዲተላለፉ ኚአመታት በፊት ዹተላለፈውን ውሳኔ ውድቅ ያደሚገው በትናንትናው ዕለት ነበር።
ውሳኔው ዚአካባቢውን ዚጞጥታ ሁኔታ ላይ ስለሚያሳድሚው ተጜዕኖ ዚተጠዚቁት አቶ አብዱላሂ መጀመሪያም በሕገ መንግሥቱ አግባብ አይደለም ዚተካሔደው።
በአካባቢው ዚሚኖሩት አፋር እና ሶማሌ ዚግጊሜ መሬት ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ፉክክር ግንኙነታ቞ው ለዓመታት ሻክሮ ቆይቷል።
ዚሶማሌ ክልል ካሳለፈው ውሳኔ በኋላ ዚፌድራል መንግሥቱም ይሁን ዹአፋር ክልል በይፋ እስካሁን ያሉት ነገር ዚለም።
ዚትግራይ ክልል ምክር ቀት ውሳኔ በምሁራን እይታ ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ቀዉስ መንስኀና መፍትሔዉ ዚኢትዮጵያ መሪዎቜ አዲስ አበባ ዉስጥ ይሰበሰባሉ ይነጋገራሉ ይናገራሉም።
በሐገሪቱ ሠላም እንደሚያስኚብሩ ጩር ሠራዊታ቞ዉን ይወዳል ያሉትን ሕዝብ ደሕንነት እንደሚያስጠብቁ ልማትን እንደሚያፋጥኑ ይደሰኩራሉ።
ዹሰላም ደሕንነቱ ቃል ተስፋ ጭናቅሰን አይደለም ጫንጮ ሳይደርስ ዚወለፊንድ ዚመባሚቁ ሐቅ እንጂ ሕቅታዉ።
ኹአምቩ እስኚ ጭሮ ኹጂጂጋ እስኚ ቩሎ ዎዎሳ ሰዎቜ እዚተገደሉ እዚታሰሩ እዚታገዙ መቶ ሺዎቜ እዚተሰደዱ ነዉ።
ሐብት ንብሚት ወድሟል ኚቊታ ቊታ መንቀሳቀስ ዚሞቀጊቜ ዝዉዉር ተገድቧል መተማመን ጠፍቷል።
ዚቀድሞዉ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ደርግ ዚተቃዋሚዎቹን ጩኞት ጥያቄ ለማጣጣል በጫጫታ ዚፈሚሰቜ ሐገር ብትኖር እያሪኮ ብቻ ናት በሚል መግለጫ ያኪያኪስ ነበር።
ዚሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ መስራቜ እና ዚቀድሞ መሪ ዶክተር አሹጋዊ በርሔ ቀዉሱን አስጊ ይሉታል።
በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ዚፌደራሊዝም ጉዳይ መምሕር ናሁሰናይ በላይ እንደ ሂሳብ ያሰሉታል።
ዶክተር አሹጋዊ ዹሹጅም ጊዜ ተደራራቢ ቜግር ዉጀት ነዉ ባይ ና቞ዉ።
ካቢኔ ሜሮ አዲስ ሟሟል ጥልቅ ያለዉን ተሐድሶ ማድሚጉን አስታዉቋል ወራት ዹቆዹ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ደንግጓል ሁነኛ መፍትሔ ግን እስካሁን ዚለም።
አቶ ናሆሰናይ በዎሞክራሲ እጊት ተፈጠሹ ያሉት ቜግር ኹተፈጠሹ በኋላም ዎሞክራሲያዊ መፍትሔ አልተሰጠም ይላሉ።
አቶ ናሁሰናይ ተጠያቂነት ዹሚሰማዉ ባለሥልጣን አለመኖሩ ነዉ ባይ ና቞ዉ።
በኢሕአዲግ መሪዎቜ መካኚል ሜኩቻ አለ ዹሚለዉን ግምትም ዚሚጋሩ ይመስላሉ።
ፈሚንሳሲዉ ጋዜጠኛ እና ዚፖለቲካ ተንታኝ ሬኔ ለፎ በቅርቡ እንደ ፃፈዉ ደግሞ በኢሕአዎግ ነባር እና አዳዲስ መሪዎቜ መካኚል መግባባት ያለ አይመስልም።
በጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ዚሚመራዉ ካቢኔ ሐገሪን ሙሉ በሙሉ ማስተዳደሩን ይጠራጠራል።
ዶክተር አሹጋዊ በርሔ ግን ጉዳዩን ሰፋ አድርገን ማዚት አለብን ባይ ና቞ዉ።
ዚሐገሪቱን ፖለቲካዊ ሥርዓት በመዘወሩ ሒደት ዚኃያላን እጅም አለበት እንደ አንጋፋዉ ፖለቲኚኛ።
አቶ መለስ ለሁለተኛ ጊዜ ኪጋሊን ሲጎበኙ ትንሜቱ ሐገር ዚትልቅ ጥፋትዋን ማቅ እንዳጠለቀቜ በዓለም አደባባይ ብቅ ያለቜበት ጊዜ ነበር።
አቶ መለስ በያኔዉ ዚሩዋንዳ ምክትል ባሁኑ ፕሬዝደንት ፖል ካጋሚ ጋባዥነት አዲስ ለተኹፈተዉ ለኪጋሊ ዩኒቚርስቲ ተማሪዎቜ ንግግር አደሚጉ።
አሰቃቂዉን ግፍ አንስተዉ እንዳትሚሱት ግን ይቅር በሉ አሉ ኢትዮጵያዊዉ መሪ አዳራሹን ላጹናነቀዉ ተማሪ ።
ጠንካራ መሪዋን ኚሞቜበት ጊዜ ጀምሮ ግን እሳ቞ዉ ብሔራዊ ካሉት ዓይነት ትልቅ ቀዉስ ዉስጥ ናት።
አሞባሪ ፀሹ ሠላም ዚጎሚቀት መንግሥታት ተላላኪ እዚተባለ ተቃዋሚ ፖለቲኚኞቜዋን ጋዜጠኞቜዋን ዚመብት ተሟጋ቟ቜዋን ዚኃይማኖት መሪዎቜዋን ወሕኒ መወርወሩም ዹተኹሹዉ ዚለም።
አውሮጳ ጀርመን ዹጋናዉ ፕሬዝደንት ዹጀርመን ቆይታ ዹጋና ፕሬዝደንት ናና አኩፎ አዶ ጀርመንን በመጎብኘት ላይ ና቞ው።
ዹጀርመን እና ዹጋና መሪዎቜ በዋናነት ዚኀኮኖሚ ትብብር ላይ ያተኮሚ ዉይይት ቢያካሂዱም ሕገ ወጥ ስደትንም በመዋጋቱ ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል።
ሆኖም ሊደሹግ ዹነበሹዉን ወታደራዊ አቀባበል ግን በዚሁ ምክንያት ቀርቷል።
ጋና በምዕራብ አፍሪቃ ዚአርአያነት ገፅታ ዚገነባቜ ሀገር መሆኗን ዹጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ገልጞዋል።
ሁለቱም ፖለቲኚኞቜ በሀገራቱ መካኚል ዚኀኮኖሚ ትብብሩን ማስፋት እንደሚፈልጉ አመልክተዋል።
ኹጀርመንም ሆነ ኚሌሎቜ ዹበለፁ ሃገራት ጋር ዹሚኖሹን ትስስር ኚእርዳታ ይልቅ በንግድ እና በመዋዕለ ንዋይ ፍሰት ላይ እንዲሆን እንፈልጋለን።
እርዳታ ዹመቀበሉ ዘመን ለአገሮቻቜን ልማት ጠቃሚ አልነበሹም ብለን እናስባለን።
ይህም ድጋፍ ዹመፈለግ አስተሳሰብን ፈጥሯል ይህ ደግሞ እኛን አልጠቀመንም።
ሁለቱም ሃገራት ዹዉጭ ዹግል ባለወሚቶቜ ትኩሚት ወደ አፍሪቃ ቢሳብ ይሻሉ።
ጀርመን ዚቡድን ፕሬዝደንት በነበሚቜበት ወቅት ዚመሠሚተቜዉ ኮምፓክት አፍሪቃ ዚተባለዉ ዚትብብር መድሚክ ይህንኑ እንዲያመቻቜ ዹተቀዹሰ ነው።
ኚፕሬዝደንት አኩፎ አዶ ጋር ኚተነጋገሩ በኋላም ሜርክል ዹጀርመን ዹግል ባለወሚቶቜ ወደጋና እንዲሄዱ ለማድሚግ እያበሚታቱ እንደሆነ ገልጞዋል።
ዹጋና ዚፋይናስ ሚኒስትር ኮምፓክት ስኬታማ እንዲሆን አብሮ በመሥራት ላይ ይገኛል በተለይም ጋና ዉስጥ አስፈላጊ ማሻሻያዎቜን በማድሚግ ሚገድ ማለት ነው።
በእኛ በኩልም ዹጀርመን ዹግል ባለሃብቶቜ ወደጋና በመሄድ ፕሮጀክቶቻ቞ዉን ተግባራዊ እንዲያደርጉ በመገፋፋት ላይ ነን።
ሜርክል አክለውም በመጪዉ ዹመፀው ወራትም ዚኮምፓክት አፍሪቃ አባል ሃገራት በዚሁ ጉዳይ ይመክሩ ዘንድ በርሊን ላይ ስብሰባ እንደሚጠሩም ኚወዲሁ አስታዉቀዋል።
እስካሁን ግን በዚህ ሚገድ ስብስቡ ያኚናወነው ተጚባጭ ነገር ዚለም።
ዹጀርመን ዚአፍሪቃ ፖሊሲ በዚህ ስብስብ ላይ ነፍስ እንዲዘራበት በአፍሪቃ ዹጀርመን ዚንግድ ማኅበሚሰብ ማኅበር ሊቀመንበር ሜ቎ፈን ሊቢንግ አሳስበዋል።
ዹጀርመን ዚንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቀት አፍሪቃ ዉስጥ ለሚንቀሳቀሱ ኩባንያዎቜ ኚመንግሥት ዹተሰጠ ተጚማሪ ዋስትና ዹለም ሲል ይወቅሳል።
ፌደራል ጀርመን መንግሥት በዚህ ላይ ቃል ቢገባም ኚምርጫ ጋር በተያያዘዉ ሚዥም ጊዜ በወሰዱ ዚዉስጥ ፖለቲካዉ ምክንያት እንስካሁን ተግባራዊ አልሆነም።
በጋናም በኩል ቢሆን መንግሥት ሊሠራ቞ዉ ዚሚገባ በርካታ ነገሮቜ አሉ።
ኹምንም በላይ ዹኃይል መቆራሚጥ ሙስና እና ዚሠራተኞቜ ዝቅተኛ ዚትምህርት ደሹጃ ዹዉጭ ባለሃብቶቜ ላይ ፍርሃት ፈጥሯል።
ኚኀኮኖሚ ጉዳዮቜ በተጚማሪም ሁለቱ መሪዎቜ ስደትን ለመኹላኹል በጋራ ለመሥራትም ተስማምተዋል።
ዹጋናዉ መሪ ወጣቶቜ በስደት እና ሜዲትራኒያን ባህርን በማቋሚጥ አቅማቾዉን ኚሚያባክኑ ዚበለፀገቜ ሀገር በመገንባቱ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ጀርመን ዚጥገኝነት ጥያቄያ቞ዉ ተቀባይነት ያላገኘ ዹጋና ዜጎቜ ወደሀገራ቞ዉ ዚሚመለሱበትን ሁኔታ እያፋጠነቜ ነው።