text
stringlengths
4
267
እንዲህ በል፩ ‘ይሖዋ እንዲህ ሲል አውጇል፩ “ዚሰዎቜ አስኚሬን በምድር ላይ ልክ እንደ ፍግ ይወድቃልፀአጫጅ አጭዶ እንደተወውም እህል ይሆናልፀዚሚሰበስበው አይኖርም።”’”
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ጥበበኛው በጥበቡ አይኩራራፀኃያሉ በኃያልነቱ አይኩራራፀባለጞጋውም በሀብቱ አይኩራራ።”
“ኹዚህ ይልቅ ዚሚኩራራ በዚህ ነገር ይኩራራፊ ስለ እኔ ጥልቅ ማስተዋልና እውቀት ያለው በመሆኑእንዲሁም በምድር ላይ ታማኝ ፍቅር ዚማሳዚው፣ ደግሞም ፍትሕና ጜድቅ ዹማሰፍነው እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ በማወቁ ይኩራራፀበእነዚህ ነገሮቜ ደስ እሰኛለሁና” ይላል ይሖዋ።
“እነሆ፣ እንዲህ ዚሚሆንበት ቀን ይመጣል” ይላል ይሖዋ፣ “ዹተገሹዘ ቢሆንም እንኳ ያልተገሚዘውን ሁሉ ተጠያቂ አደርጋለሁፀ
ግብፅን፣ ይሁዳን፣ ኀዶምን፣ አሞናውያንን፣ ሞዓብንና በሰሪሳራ቞ው ላይ ያለውን ፀጉር ዚሚላጩትን በምድሚ በዳ ዚሚኖሩ ሰዎቜ ሁሉ ተጠያቂ አደርጋለሁፀ ብሔራት ሁሉ ያልተገሚዙ ና቞ውናፀ ዚእስራኀልም ቀት ሁሉ ልባ቞ው ያልተገሚዘ ነው።”
ዚማታን ልጅ ሰፋጥያህ፣ ዚጳስኮር ልጅ ጎዶልያስ፣ ዚሞሌምያህ ልጅ ዩካልና ዚማልኪያህ ልጅ ጳስኮር፣ ኀርምያስ ለሕዝቡ ሁሉ ዹተናገሹውን ዹሚኹተለውን ቃል ሰሙ፩
“ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘በዚህቜ ኹተማ ዹሚቀር በሰይፍ፣ በሚሃብና በቾነፈር ይሞታል። ለኚለዳውያን እጁን ዚሚሰጥ ግን ይተርፋልፀ ሕይወቱ እንደ ምርኮ ትሆንለታለቜፀ በሕይወትም ይኖራል።’
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ይህቜ ኹተማ ለባቢሎን ንጉሥ ሠራዊት መሰጠቷ አይቀርምፀ እሱም ይይዛታል።’”
መኳንንቱ ንጉሡን እንዲህ አሉትፊ “ይህ ሰው እንዲህ ያለ ቃል በመናገር በዚህቜ ኹተማ ውስጥ ዚቀሩትን ወታደሮቜና ዚሕዝቡን ሁሉ ወኔ እያዳኚመ ስለሆነ እባክህ አስገድለው። ይህ ሰው ለዚህ ሕዝብ ጥፋትን እንጂ ሰላምን አይመኝምና።”
ንጉሥ ሎዎቅያስም “እነሆ፣ እሱ በእጃቜሁ ነውፀ ንጉሡ እናንተን ለማስቆም ምንም ነገር ሊያደርግ አይቜልምና” ሲል መለሰላ቞ው።
እነሱም ኀርምያስን ወስደው በክብር ዘቊቹ ግቢ በሚገኘው በንጉሡ ልጅ በማልኪያህ ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ውስጥ ጣሉት። ኀርምያስን በገመድ ወደ ጉድጓዱ አወሚዱት። በጉድጓዱ ውስጥም ጭቃ ብቻ እንጂ ውኃ አልነበሚምፀ ኀርምያስም ጭቃው ውስጥ መስመጥ ጀመሚ።
በንጉሡ ቀት ዹነበሹው ኢትዮጵያዊው ጃንደሚባ ኀቀድሜሌክ ኀርምያስን በውኃ ማጠራቀሚያው ጉድጓድ ውስጥ እንደጣሉት ሰማ። በዚህ ጊዜ ንጉሡ በቢንያም በር ተቀምጩ ነበርፀ
በመሆኑም ኀቀድሜሌክ ኚንጉሡ ቀት ወጥቶ ንጉሡን እንዲህ አለው፩
“ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፣ እነዚህ ሰዎቜ በነቢዩ ኀርምያስ ላይ ክፉ ነገር ፈጜመዋል! በውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ውስጥ ጥለውታልፀ ኚሚሃቡም ዚተነሳ እዚያው ይሞታልፀ በኹተማዋ ውስጥ ዳቊ ዚሚባል ነገር ዚለምና።”
ኚዚያም ንጉሡ ኢትዮጵያዊውን ኀቀድሜሌክን እንዲህ ሲል አዘዘው፩ “ኹዚህ 30 ሰዎቜ ይዘህ ሂድፀ ነቢዩ ኀርምያስንም ኚመሞቱ በፊት ኹውኃ ማጠራቀሚያው ጉድጓድ ውስጥ ጎትተህ አውጣው።”
በመሆኑም ኀቀድሜሌክ ሰዎቹን ይዞ በንጉሡ ቀት ኹግምጃ ቀቱ ሥር ወዳለው ቊታ ሄደፀ ኚዚያም ዚተቊጫጚቀ ጹርቅና ያሚጀ ልብስ ኚዚያ ወስደው በውኃ ማጠራቀሚያው ጉድጓድ ውስጥ ላለው ለኀርምያስ በገመድ አወሚዱለት።
ኢትዮጵያዊው ኀቀድሜሌክ ኀርምያስን “ይህን ዚተቊጫጚቀ ጹርቅና ያሚጀ ልብስ በብብትህና በገመዱ መካኚል አድርገው” አለው። ኀርምያስም እንደተባለው አደሚገፀ
እነሱም ኀርምያስን በገመዱ ጎትተው ኹውኃ ማጠራቀሚያው ጉድጓድ ውስጥ አወጡት። ኀርምያስም በክብር ዘቊቹ ግቢ ተቀመጠ።
ንጉሥ ሎዎቅያስ ሰው ልኮ ነቢዩ ኀርምያስን እሱ ወዳለበት፣ በይሖዋ ቀት ወደሚገኘው ወደ ሊስተኛው መግቢያ አስመጣውፀ ንጉሡም ኀርምያስን “አንድ ነገር ልጠይቅህ እፈልጋለሁ። ምንም ነገር እንዳትደብቀኝ” አለው።
በዚህ ጊዜ ኀርምያስ ሎዎቅያስን “ብነግርህ ትገድለኛለህ። ብመክርህም አትሰማኝም” አለው።
ንጉሥ ሎዎቅያስም በሚስጥር ለኀርምያስ እንዲህ ሲል ማለለትፊ “ይህን ሕይወት በሰጠን ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ አልገድልህምፀ ሕይወትህን ለማጥፋት ለሚሹት ለእነዚህ ሰዎቜም አሳልፌ አልሰጥህም።”
ኚዚያም ኀርምያስ ሎዎቅያስን እንዲህ አለው፩ “ዚእስራኀል አምላክ፣ ዚሠራዊት አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ለባቢሎን ንጉሥ መኳንንት እጅህን ብትሰጥ ሕይወትህ ትተርፋለቜፀ ይህቜም ኹተማ በእሳት አትቃጠልምፀ አንተም ሆንክ ቀተሰብህ በሕይወት ትተርፋላቜሁ።
ለባቢሎን ንጉሥ መኳንንት እጅህን ዚማትሰጥ ኹሆነ ግን ይህቜ ኹተማ ለኚለዳውያን አልፋ ትሰጣለቜፀ እነሱም በእሳት ያቃጥሏታልፀ አንተም ኚእጃ቞ው አታመልጥም።’”
ኚዚያም ንጉሥ ሎዎቅያስ ኀርምያስን “ወደ ኚለዳውያን ዚኮበለሉትን አይሁዳውያን እፈራለሁፀ ለእነሱ አሳልፈው ዚሰጡኝ እንደሆነ ሊያሠቃዩኝ ይቜላሉ” አለው።
ኀርምያስ ግን እንዲህ አለው፩ “ለእነሱ አሳልፈው አይሰጡህም። እባክህ ዹምነግርህን ዹይሖዋን ቃል ታዘዝፀ መልካምም ይሆንልሃልፀ በሕይወትም ትኖራለህ።
እጅህን ለመስጠት ፈቃደኛ ካልሆንክ ግን ይሖዋ ዹገለጠልኝ ነገር ይህ ነው፩
እነሆ፣ በይሁዳ ንጉሥ ቀት ዚቀሩት ሎቶቜ ሁሉ ወደ ባቢሎን ንጉሥ መኳንንት ይወሰዳሉፀ እነሱም እንዲህ ይላሉፊ‘ተማምነህባ቞ው ዚነበሩት ሰዎቜ አታለውሃልፀ ደግሞም አሞንፈውሃል። እግርህ ጭቃ ውስጥ እንዲሰምጥ አድርገዋል። አሁን አፈግፍገው ተመልሰዋል።’
“ሚስቶቜህንና ወንዶቜ ልጆቜህን ሁሉ ለኚለዳውያን ይሰጣሉፀ አንተም ኚእጃ቞ው አታመልጥምፀ ይልቁንም ዚባቢሎን ንጉሥ ይይዝሃልፀ በአንተም ምክንያት ይህቜ ኹተማ በእሳት ትቃጠላለቜ።”
ኚዚያም ሎዎቅያስ ኀርምያስን እንዲህ አለው፩ “ስለዚህ ጉዳይ ማንም ሰው እንዳይሰማፀ አለዚያ ትሞታለህ።
መኳንንቱ ኹአንተ ጋር እንደተነጋገርኩ ሰምተው ወደ አንተ ቢመጡና ‘ለንጉሡ ዹነገርኹውን ነገር እስቲ ንገሚን። ምንም ነገር አትደብቀንፀ እኛም አንገድልህም። ንጉሡ ዹነገሹህ ምንድን ነው?’ ቢሉህ፣
‘በዚያ እንዳልሞት ንጉሡ ወደ ዚሆናታን ቀት መልሶ እንዳይልኚኝ ስለምነው ነበር’ በላ቞ው።”
በኋላም መኳንንቱ ሁሉ ወደ ኀርምያስ መጥተው ጠዚቁት። እሱም ንጉሡ እንዲናገር ያዘዘውን ቃል ሁሉ ነገራ቞ው። እነሱም ኚዚያ በኋላ ምንም አላሉትምፀ ያደሚጉትን ውይይት ዹሰማ ሰው አልነበሚምና።
ኀርምያስ ኢዚሩሳሌም እስኚተያዘቜበት ጊዜ ድሚስ በክብር ዘቊቹ ግቢ ተቀመጠፀ ኢዚሩሳሌም በተያዘቜበት ጊዜም እዚያው ነበር።
ይሖዋ በነቢዩ ኀርምያስ በኩል ስለ ባቢሎን ይኾውም ስለ ኚለዳውያን ምድር ዹተናገሹው ቃል ይህ ነው፩
“በብሔራት መካኚል ይህን ተናገሩፀ ደግሞም አውጁ። ምልክት አቁሙፀ ይህን አውጁ። ምንም ነገር አትደብቁ! እንዲህም በሉ፩ ‘ባቢሎን ተይዛለቜ። ቀል ኀፍሚት ተኚናንቧል። ሜሮዳክ በፍርሃት ርዷል። ምስሎቿ ተዋርደዋል። አስጞያፊ ዹሆኑ ጣዖቶቿ ተሞብሚዋል።’
ኹሰሜን አንድ ብሔር በእሷ ላይ ተነስቷልና። እሱም ምድሪቷን አስፈሪ ቊታ ያደርጋታልፀበእሷ ውስጥ ዹሚኖር ሰው ዚለም። ሰውም ሆነ እንስሳ ሞሜቷልፀአካባቢውን ለቀው ሄደዋል።”
“በእነዚያ ቀናትና በዚያ ጊዜ” ይላል ይሖዋ፣ “ዚእስራኀል ሕዝብም ሆነ ዚይሁዳ ሕዝብ በአንድነት ይመጣሉ። እያለቀሱ ይሄዳሉፀ በአንድነትም አምላካ቞ውን ይሖዋን ይፈልጋሉ።
ወደ ጜዮን ዚሚወስደውን መንገድ ይጠይቃሉፀ ፊታ቞ውንም ወደዚያ አቅጣጫ አዙሹው ‘ኑ፣ ኹይሖዋ ጋር ዚማይሚሳ ዘላለማዊ ቃል ኪዳን እንግባ’ ይላሉ።
ሕዝቀ ዹጠፉ በጎቜ መንጋ ሆኗል። ዹገዛ እሚኞቻ቞ው እንዲባዝኑ አድርገዋ቞ዋል። ወደ ተራሮቜ ነዷ቞ውፀ እነሱም በዚተራራውና በዚኮሚብታው ተቅበዘበዙ። ማሚፊያ ቊታ቞ውን ሚሱ።
ያገኟ቞ውም ሁሉ ዋጧ቞ውፀ ጠላቶቻ቞ውም ‘በይሖዋ ይኾውም ዚጜድቅ መኖሪያና ዚአባቶቻ቞ው ተስፋ በሆነው በይሖዋ ላይ ኃጢአት ስለሠሩ እኛ በደለኞቜ አይደለንም’ ብለዋል።”
“ኚባቢሎን መካኚል ወጥታቜሁ ሜሹፀኚኚለዳውያንም ምድር ውጡፀመንጋውንም እንደሚመሩ እንስሳት ሁኑ።
እነሆ፣ እኔ ኹሰሜን ምድር ዚታላላቅ ብሔራትን ጉባኀ አስነስቌበባቢሎን ላይ አመጣባታለሁና። እነሱም እሷን ለመውጋት ይሰለፋሉፀበዚያም በኩል ትያዛለቜ። ፍላጻዎቻ቞ው እንደ ተዋጊ ፍላጻዎቜ ና቞ውፀወላጆቜን ዚወላድ መሃን ያደርጋሉፀዓላማ቞ውን ሳይፈጜሙ አይመለሱም።
ዚኚለዳውያን ምድር ትበዘበዛለቜ። ዚሚበዘብዟትም ሁሉ እስኪበቃ቞ው ድሚስ ይመዘብሯታል” ይላል ይሖዋ።
“እናንተ እጅግ ደስ ብሏቜኋልናፀዚገዛ ርስ቎ን ስትመዘብሩ ሐሎት አድርጋቜኋል። በለምለም ሣር ላይ እንዳለቜ ጊደር ፈንጭታቜኋልናፀእንደ ድንጉላ ፈሚሶቜም አሜካክታቜኋል።
እናታቜሁ ለኀፍሚት ተዳርጋለቜ። ዚወለደቻቜሁም እጅግ አዝናለቜ። እነሆ፣ ኚብሔራት ሁሉ ያነሰቜ፣ውኃ ዚሌለባት ምድሚ በዳና በሹሃ ሆናለቜ።
ኹይሖዋ ቁጣ ዚተነሳ ሰው ዚማይኖርባት ምድር ትሆናለቜፀሙሉ በሙሉ ባድማ ትሆናለቜ። በባቢሎን በኩል ዚሚያልፍ ሁሉ በፍርሃት አፍጥጊ ይመለኚታታልፀኚደሚሱባትም መቅሰፍቶቜ ሁሉ ዚተነሳ ያፏጫል።
እናንተ ደጋን ዚምትወጥሩ ሁሉ፣ባቢሎንን ለመውጋት በዙሪያዋ ተሰለፉ። ፍላጻ ወርውሩባትፀ በይሖዋ ላይ ኃጢአት ስለሠራቜአንድም ፍላጻ አታስቀሩ።
በዙሪያዋ ሁሉ ቀሚርቶ አሰሙ። እጇን ሰጥታለቜ። ዓምዶቿ ወድቀዋልፀ ቅጥሮቿ ፈርሰዋልፀይህ ዹይሖዋ በቀል ነውና። እሷን ተበቀሏት። እንዳደሚገቜው አድርጉባት።
ዘር ዚሚዘራውንናበመኚር ወቅት ማጭድ ዹሚይዘውን ኚባቢሎን አስወግዱ። ኚጚካኙ ሰይፍ ዚተነሳ እያንዳንዱ ወደ ገዛ ሕዝቡ ይመለሳልፀእያንዳንዱም ወደ ገዛ ምድሩ ይሞሻል።
“ዚእስራኀል ሕዝብ ዚባዘነ በግ ነው። እንዲባዝን ያደሚጉት አንበሶቜ ና቞ው። በመጀመሪያ ዹአሩር ንጉሥ በላውፀ ኚዚያም ዚባቢሎን ንጉሥ ናቡኚደነጟር አጥንቱን ቆሚጣጠመው።
ስለዚህ ዚእስራኀል አምላክ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘እነሆ፣ በአሩር ንጉሥ ላይ እንዳደሚግኩት ሁሉ በባቢሎን ንጉሥና በምድሩ ላይ እንዲሁ አደርጋለሁ።
እስራኀልንም ወደ መሰማሪያው እመልሰዋለሁፀ እሱም በቀርሜሎስና በባሳን ይሰማራልፀ በኀፍሬምና በጊልያድ ተራሮቜም ላይ እስኪጠግብ ድሚስ ይመገባል።’”
“በእነዚያ ቀናትና በዚያ ጊዜ” ይላል ይሖዋ፣“ዚእስራኀል በደል ይፈለጋልፀሆኖም አይገኝምፀዚይሁዳም ኃጢአት አይገኝምፀእንዲተርፉ ያደሚግኳ቞ውን ይቅር እላ቞ዋለሁና።”
“በመሚታይም ምድር ላይ ውጣፀ በጰቆድ ነዋሪዎቜም ላይ ተነሳ። ነዋሪዎቹ ይጚፍጚፉፀ ሙሉ በሙሉም ይጥፉ” ይላል ይሖዋ። “ያዘዝኩህንም ሁሉ አድርግ።
በምድሪቱ ላይ ዚጊርነትናዚታላቅ ጥፋት ድምፅ ይሰማል።
ዚምድር ሁሉ መዶሻ እንዎት ተቆሹጠ! እንዎትስ ተሰበሹ! ባቢሎን በብሔራት መካኚል እንዎት መቀጣጫ ሆነቜ!
ባቢሎን ሆይ፣ በአንቺ ላይ ወጥመድ ዘርግቻለሁፀ ደግሞም ተይዘሻልፀአንቺ ግን አልታወቀሜም። ተገኘሜፀ እንዲሁም ተያዝሜፀዚተቃወምሜው ይሖዋን ነውና።
ይሖዋ ግምጃ ቀቱን ኚፍቷልፀዚቁጣ ዹጩር መሣሪያዎቹንም ያወጣል። ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት አምላክ ይሖዋበኚለዳውያን ምድር ዚሚሠራው ሥራ አለና።
ኚሩቅ ቊታ መጥታቜሁ በእሷ ላይ ውጡ። ጎተራዎቿን ክፈቱ። እንደ እህል ክምር ኚምሯት። ፈጜማቜሁ አጥፏት። አንድም ሰው አታስቀሩላት።
ወይፈኖቿን ሁሉ እሚዱፀወደ እርድ ቊታ ይውሚዱ። ቀናቾው ይኾውም ዚሚመሚመሩበት ጊዜስለደሚሰ ወዮላ቞ው!
ዚአምላካቜንን ዹይሖዋን በቀል፣ስለ ቀተ መቅደሱ ሲል ዹወሰደውን ዹበቀል እርምጃ በጜዮን ለማወጅኚባቢሎን ምድር ዚሚሞሹናአምልጠው ዚሚሄዱ ሰዎቜ ድምፅ ይሰማል።
ቀስተኞቜን፣ ደጋን ዚሚወጥሩትንም ሁሉበባቢሎን ላይ ጥሩ። በዙሪያዋም ስፈሩፀ አንድም ሰው እንዳያመልጥ። እንደ ሥራዋ መልሱላት። እሷ እንዳደሚገቜው ሁሉ እናንተም እንዲሁ አድርጉባት። በይሖዋ ላይ ይኾውም በእስራኀል ቅዱስ ላይዚእብሪት ድርጊት ፈጜማለቜና።
በመሆኑም ወጣቶቿ በአደባባዮቿ ይወድቃሉፀበዚያም ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይጠፋሉ” ይላል ይሖዋ።
“አንቺ ዓመፀኛ፣ እነሆ፣ እኔ በአንቺ ላይ ተነስቻለሁ” ይላል ሉዓላዊው ጌታ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋፀ“ቀንሜ ይኾውም አንቺን ተጠያቂ ዚማደርግበት ጊዜ ይመጣልና።
አንቺ ዓመፀኛ ተሰናክለሜ ትወድቂያለሜፀዚሚያነሳሜም አይኖርም። ኚተሞቜሜንም በእሳት አነዳለሁፀበዙሪያሜም ያለውን ሁሉ ይበላል።”
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ዚእስራኀል ሕዝብና ዚይሁዳ ሕዝብ ተጚቁነዋልፀማርኚው ዚወሰዷ቞ውም ሁሉ ጠፍሹው ይዘዋ቞ዋል። እነሱን ለመልቀቅ ፈቃደኞቜ አልሆኑም።
ይሁንና ዚሚቀዣ቞ው ብርቱ ነው። ስሙ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ነው። ለምድሪቱ እሚፍት ለመስጠትናዚባቢሎንን ነዋሪዎቜ ለማሞበርያላንዳቜ ጥርጥር ይሟገትላ቞ዋል።”
“በኚለዳውያን፣ በባቢሎን ነዋሪዎቜ፣ በመኳንንቷእንዲሁም በጥበበኞቿ ላይ ሰይፍ ተመዟል” ይላል ይሖዋ።
“ኚንቱ ነገር በሚናገሩ ሰዎቜ ላይ ሰይፍ ተመዟልፀ እነሱም ዚሞኝነት ድርጊት ይፈጜማሉ። በተዋጊዎቿ ላይ ሰይፍ ተመዟልፀ እነሱም በሜብር ይዋጣሉ።
በፈሚሶቻ቞ው፣ በጩር ሠሚገሎቻ቞ውናበመካኚሏ በሚኖሩ ድብልቅ ሕዝብ ሁሉ ላይ ሰይፍ ተመዟልፀእነሱም እንደ ሎቶቜ ይሆናሉ። ውድ በሆኑ ሀብቶቿ ላይ ሰይፍ ተመዟልፀ እነሱም ይዘሚፋሉ።
ውኃዎቿ ይበኚላሉፀ ይደርቃሉም። ዚተቀሚጹ ምስሎቜ ምድር ናትናፀአስፈሪ በሆኑት ራእዮቻ቞ው ዚተነሳ እንደ እብድ ያደርጋ቞ዋል።
ስለዚህ ዹበሹሃ ፍጥሚታት ኚሚያላዝኑ እንስሳት ጋር ይኖራሉፀበእሷም ውስጥ ሰጎኖቜ ይኖራሉ። ኹዚህ በኋላ ዚሚኖርባት አይገኝምፀኚትውልድ እስኚ ትውልድም ማንም አይቀመጥባትም።”
“አምላክ ሰዶምንና ገሞራን እንዲሁም በአካባቢያ቞ው ያሉትን ኚተሞቜ በደመሰሰ ጊዜ እንደሆነው ሁሉ” ይላል ይሖዋ፣ “በዚያ ማንም አይኖርምፀ አንድም ሰው በዚያ አይቀመጥም።
እነሆ፣ አንድ ሕዝብ ኹሰሜን ይመጣልፀአንድ ታላቅ ብሔርና ታላላቅ ነገሥታትኚምድር ዳርቻዎቜ ይነሳሉ።
ቀስትና ጩር ይይዛሉ። ጚካኝና ምሕሚት ዚለሜ ና቞ው። ፈሚሶቻ቞ውን እዚጋለቡ ሲመጡድምፃ቞ው እንደሚጮኜ ባሕር ነው። ዚባቢሎን ሎት ልጅ ሆይ፣ አንቺን ለመውጋት በአንድ ልብ ሆነው ይሰለፉብሻል።
ዚባቢሎን ንጉሥ ስለ እነሱ ወሬ ሰምቷልፀእጆቹም ይዝለፈለፋሉ። ጭንቀት ይይዘዋልፀልትወልድ እንደተቃሚበቜ ሎት ይሠቃያል።
“እነሆ፣ አንድ ሰው፣ እንደ አንበሳ በዮርዳኖስ ዳርቻ ኹሚገኙ ጥቅጥቅ ያሉ ጥሻዎቜ ወጥቶ አስተማማኝ በሆነው መሰማሪያ ላይ ይመጣልፀ እኔ ግን ወዲያውኑ ኚእሷ አባርራ቞ዋለሁ። ዹተመሹጠውን በእሷ ላይ እሟማለሁ። እንደ እኔ ያለ ማነው? ማንስ ሊሟገተኝ ይቜላል? በእኔ ፊት ሊቆም ዚሚቜል እሚኛ ዚትኛው ነው?
ስለዚህ እናንተ ሰዎቜ፣ ይሖዋ በባቢሎን ላይ ያስተላለፈውን ውሳኔና በኚለዳውያን ምድር ላይ ያሰበውን ሐሳብ ስሙ። ኹመንጋው መካኚል ትናንሜ ዚሆኑት ተጎትተው መወሰዳ቞ው አይቀርም። ኚእነሱ ዚተነሳ መሰማሪያ቞ውን ባድማ ያደርጋል።
ባቢሎን ስትያዝ ኹሚሰማው ድምፅ ዚተነሳ ምድር ትናወጣለቜፀኚብሔራትም መካኚል ጩኞት ይሰማል።”
ኚዚያም ይሖዋ በለስ ዚያዙ ሁለት ቅርጫቶቜን በይሖዋ ቀተ መቅደስ ፊት ለፊት ተቀምጠው አሳዚኝፀ ይህም ዹሆነው ዚባቢሎን ንጉሥ ናቡኚደነጟር ዚይሁዳን ንጉሥ ዚኢዮዓቄምን ልጅ ኢኮንያንን፣ ኚይሁዳ መኳንንት፣ ኚእጅ ጥበብ ባለሙያዎቹና ኚአንጥሚኞቹ ጋር ኚኢዚሩሳሌም ወደ ባቢሎን በግዞት ኚወሰዳ቞ው በኋላ ነው።
በአንደኛው ቅርጫት ውስጥ ያሉት በለሶቜ በመጀመሪያው ወቅት ላይ እንደሚደርሱ በለሶቜ ጥሩ ዓይነት ነበሩፀ በሌላኛው ቅርጫት ውስጥ ያሉት በለሶቜ ደግሞ መጥፎ ዓይነት ነበሩፀ በጣም መጥፎ ኹመሆናቾው ዚተነሳም ሊበሉ ዚሚቜሉ አልነበሩም።
ኚዚያም ይሖዋ “ኀርምያስ፣ ዚምታዚው ምንድን ነው?” ሲል ጠዚቀኝ። እኔም እንዲህ አልኩፊ “ዚበለስ ፍሬዎቜን አያለሁፀ ጥሩዎቹ በለሶቜ በጣም ጥሩ ዓይነት ና቞ውፀ መጥፎዎቹ ደግሞ በጣም መጥፎ ዓይነት ና቞ውፀ ኚመጥፎነታ቞ውም ዚተነሳ ሊበሉ አይቜሉም።”
ኚዚያም ዹይሖዋ ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣፊ
“ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ኹዚህ ስፍራ ወደ ኚለዳውያን ምድር ዚሰደድኳ቞ውን ዚይሁዳ ግዞተኞቜ እንደነዚህ ጥሩ ዓይነት በለሶቜ በጥሩ ዓይን እመለኚታ቞ዋለሁ።
መልካም ነገር አደርግላቾው ዘንድ ዓይኔን በእነሱ ላይ አኖራለሁፀ ወደዚህቜም ምድር እንዲመለሱ አደርጋለሁ። እገነባ቞ዋለሁ እንጂ አላፈርሳ቞ውምፀ እተክላ቞ዋለሁ እንጂ አልነቅላ቞ውም።
እኔ ይሖዋ መሆኔን እንዲያውቁም ልብ እሰጣ቞ዋለሁ። በሙሉ ልባ቞ው ወደ እኔ ስለሚመለሱ ሕዝቀ ይሆናሉፀ እኔም አምላካ቞ው እሆናለሁ።
“‘ይሁንና ኚመጥፎነታ቞ው ዚተነሳ ሊበሉ ዚማይቜሉትን መጥፎ በለሶቜ በተመለኹተ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ዚይሁዳን ንጉሥ ሎዎቅያስን፣ መኳንንቱን፣ በዚህቜ ምድር ላይ ዚሚቀሩትን ዚኢዚሩሳሌም ቀሪዎቜና በግብፅ ምድር ዚሚኖሩትን በዚሁ ዓይን እመለኚታ቞ዋለሁ።
ለምድር መንግሥታት ሁሉ መቀጣጫ እንዲሆኑ ጥፋት አመጣባ቞ዋለሁፀ በምበትና቞ው ቊታም ሁሉ ነቀፋ እንዲደርስባ቞ው፣ መተሚቻ እንዲሆኑ፣ እንዲፌዝባ቞ውና እንዲሚገሙ አደርጋለሁ።
ለእነሱና ለአባቶቻ቞ው ኚሰጠኋት ምድር ላይ እስኪጠፉ ድሚስ በእነሱ ላይ ሰይፍ፣ ሚሃብና ቾነፈር እሰዳለሁ።”’”
ፈርዖን ጋዛን ኚመውጋቱ በፊት ፍልስጀማውያንን በተመለኹተ ወደ ነቢዩ ኀርምያስ ዚመጣው ዹይሖዋ ቃል ይህ ነው።
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ ኹሰሜን ውኃ እዚመጣ ነው። ዚሚያጥለቀልቅም ወንዝ ይሆናል። ምድሪቱንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ፣ኚተማዋንና ነዋሪዎቿን ያጥለቀልቃል። ሰዎቹ ይጮኻሉፀበምድሪቱም ዚሚኖሩ ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ።
ኚድንጉላ ፈሚሶቹ ኃይለኛ ዚኮ቎ ድምፅ፣ኚሚንገጫገጩት ዹጩር ሠሚገሎቹ ድምፅናኚመንኮራኩሮቹ ዚማያባራ ድምፅ ዚተነሳአባቶቜ እጃ቞ው ስለሚዝልልጆቻ቞ውን ለመርዳት እንኳ ወደ ኋላ አይዞሩምፀ
ምክንያቱም ዚሚመጣው ቀን ፍልስጀማውያንን ሁሉ ያጠፋልፀበሕይወት ተርፈው ጢሮስንና ሲዶናን ዚሚሚዱትን ሁሉ ያስወግዳል። ይሖዋ ፍልስጀማውያንንይኞውም ኚካፍቶር ደሎት ዚመጡ ቀሪዎቜን ያጠፋልና።
ጋዛ ትመለጣለቜ። አስቀሎን ጞጥ ትላለቜ። ሾለቋሟ በሆነው ሜዳ቞ው ዚምትኖሩ ቀሪዎቜ ሆይ፣ሰውነታቜሁን ዚምትቆርጡት እስኚ መቌ ነው?
አንተ ዹይሖዋ ሰይፍ! ዚማታርፈው እስኚ መቌ ነው? ወደ ሰገባህ ግባ። እሚፍፀ ጞጥ ብለህም ተቀመጥ።
ይሖዋ ትእዛዝ ሰጥቶት እያለእንዎት አርፎ ሊቀመጥ ይቜላል? ትእዛዝ ዹተሰጠው በአስቀሎንና በባሕሩ ዳርቻ ላይ ነውፀበዚያ መድቊታል።”
በኢዮስያስ ልጅ፣ በይሁዳ ንጉሥ በኢዮዓቄም ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ይህ ዹይሖዋ ቃል ወደ ኀርምያስ መጣፊ
“ይሖዋ እንዲህ አለኝ፩ ‘ለራስህ ማሰሪያና ቀንበር ሠርተህ አንገትህ ላይ አድርገው።
ኚዚያም በኢዚሩሳሌም ወዳለው ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሎዎቅያስ በመጡት መልእክተኞቜ እጅ፣ ወደ ኀዶም ንጉሥ፣ ወደ ሞዓብ ንጉሥ፣ ወደ አሞናውያን ንጉሥ፣ ወደ ጢሮስ ንጉሥና ወደ ሲዶና ንጉሥ ላኚው።
ለጌቶቻ቞ው ይህን ትእዛዝ እንዲያስተላልፉ ንገራ቞ውፊ “‘“ዚእስራኀል አምላክ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ለጌቶቻቜሁ እንዲህ በሏቾው፩