text
stringlengths
4
267
ብዙ ብሔራትና ታላላቅ ነገሥታት ባሪያዎቜ ያደርጓ቞ዋልናፀ እኔም እንደ ድርጊታ቞ውና እንደ ገዛ እጃ቞ው ሥራ እኚፍላ቞ዋለሁ።’”
ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ብሎኛልናፊ “ዚቁጣ ወይን ጠጅ ያለበትን ይህን ጜዋ ኚእጄ ውሰድፀ እኔም ወደምልክህ ብሔራት ሁሉ ሄደህ አጠጣ቞ው።
እነሱም በመካኚላ቞ው ኹምሰደው ሰይፍ ዚተነሳ ይጠጣሉ፣ ይንገዳገዳሉ፣ እንደ አበደ ሰውም ይሆናሉ።”
ስለዚህ ኹይሖዋ እጅ ጜዋውን ወሰድኩፀ ይሖዋ ወደላኹኝም ብሔራት ሁሉ ሄጄ አጠጣኋ቞ውፊ
ዛሬ እንደሆነው ሁሉ ባድማ፣ መቀጣጫና ማፏጫ እንዲሆኑ እንዲሁም ለእርግማን እንዲዳሚጉ በመጀመሪያ ኢዚሩሳሌምንና ዚይሁዳን ኚተሞቜ፣ ነገሥታቷንና መኳንንቷን አጠጣኋ቞ውፀ
ኚዚያም ዚግብፅ ንጉሥ ፈርዖንና አገልጋዮቹ፣ መኳንንቱና ሕዝቡ ሁሉ፣
ድብልቅ ዹሆነው ሕዝባ቞ው ሁሉ፣ ዚዑጜ ምድር ነገሥታት ሁሉ፣ ዚፍልስጀማውያን ምድር ነገሥታት ሁሉ፣ አስቀሎን፣ ጋዛ፣ ኀቅሮንና ኚአሜዶድ ዚቀሩት ሰዎቜ፣
ኀዶም፣ ሞዓብና አሞናውያን፣
ዚጢሮስ ነገሥታት ሁሉ፣ ዚሲዶና ነገሥታት ሁሉና በባሕሩ ላይ ያለው ደሎት ነገሥታት፣
ዎዳን፣ ቎ማ፣ ቡዝና በሰሪሳራ቞ው ላይ ያለውን ፀጉር ዚሚላጩ ሁሉ፣
ዚዓሚብ ነገሥታት ሁሉና በምድሚ በዳ ዚሚኖሩት ድብልቅ ሕዝብ ነገሥታት ሁሉ፣
ዚዚምሪ ነገሥታት ሁሉ፣ ዚኀላም ነገሥታት ሁሉና ዚሜዶናውያን ነገሥታት ሁሉ፣
በቅርብም ሆነ በሩቅ ያሉ ዹሰሜን ነገሥታት ሁሉ አንድ በአንድ እንዲሁም በምድር ላይ ያሉ ሌሎቜ ዹዓለም መንግሥታት ሁሉ ጠጡፀ ኚእነሱም በኋላ ዚሌሻቅ ንጉሥ ይጠጣል።
“አንተም እንዲህ በላቾው፩ ‘ዚእስራኀል አምላክ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “በመካኚላቜሁ ኹምሰደው ሰይፍ ዚተነሳ ጠጡ፣ ስኚሩ፣ አስታውኩ፣ ዳግመኛም ላትነሱ ውደቁ።”’
ጜዋውን ኚእጅህ ወስደው ለመጠጣት ፈቃደኛ ባይሆኑ እንዲህ በላቾው፩ ‘ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “በግድ ትጠጣላቜሁ!
እነሆ፣ በመጀመሪያ ዹማጠፋው በስሜ ዚተጠራቜውን ኹተማ ኹሆነ እናንተስ ኚቅጣት ታመልጣላቜሁ?”’ “‘በምድር ነዋሪዎቜ ሁሉ ላይ ሰይፍን ስለምጠራ እናንተም ኚቅጣት አታመልጡም’ ይላል ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ።
“አንተም ይህን ቃል ሁሉ ትተነብይላ቞ዋለህፀ እንዲህም ትላ቞ዋለህፊ‘ይሖዋ ኹላይ ሆኖ ይጮኻልፀኚቅዱስ ማደሪያውም ድምፁን ያሰማል። በመኖሪያ ስፍራውም ላይ በኃይል ይጮኻል። ወይን መጭመቂያውን እንደሚሚግጡ ሰዎቜ፣በምድር ነዋሪዎቜ ሁሉ ላይ በድል አድራጊነት ይዘምራል።’
‘ታላቅ ጩኞት እስኚ ምድር ዳርቻ ድሚስ ያስተጋባልፀይሖዋ ኚብሔራት ጋር ሙግት አለውና። እሱ ራሱ በሰዎቜ ሁሉ ላይ ይፈርዳል። ክፉዎቜንም ለሰይፍ ይዳርጋል’ ይላል ይሖዋ።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘እነሆ፣ ጥፋት ብሔራትን አንድ በአንድ ያዳርሳልፀታላቅ አውሎ ነፋስም ኚምድር ዳርቻዎቜ ይነሳል።
“‘በዚያም ቀን፣ ይሖዋ ዹገደላቾው ኚምድር ዳር እስኚ ምድር ዳር ድሚስ ይሆናሉ። አይለቀስላ቞ውም፣ አይሰበሰቡም ወይም አይቀበሩም። በምድር ላይ እንደ ፍግ ይሆናሉ።’
እናንተ እሚኞቜ፣ ዋይ ዋይ በሉፀ ጩኹም! እናንተ በመንጋው መካኚል ያላቜሁ ታላላቆቜ፣ በአመድ ላይ ተንኚባለሉፀምክንያቱም ዚምትታሚዱበትና ዚምትበታተኑበት ጊዜ ደርሷልፀእንደ ውድ ዹሾክላ ዕቃ ትኚሰኚሳላቜሁ!
እሚኞቹ ዚሚሞሹበት ቊታ ዚለምፀበመንጋው መካኚል ያሉት ታላላቆቜም ማምለጫ ዚላ቞ውም።
አዳምጡ! ዚእሚኞቹ ጩኞትናበመንጋው መካኚል ያሉ ታላላቆቜ ዋይታ ይሰማልፀይሖዋ ማሰማሪያ቞ውን እያወደመ ነውና።
ኹሚነደው ዹይሖዋ ቁጣም ዚተነሳሰላማዊ ዚሆኑት ዚመኖሪያ ቊታዎቜ ሕይወት አልባ ሆነዋል።
እንደ ደቩል አንበሳ ኚጎሬው ወጥቷልፀኚጚካኙ ሰይፍናኹሚነደው ቁጣው ዚተነሳምድራ቞ው ዚሚያስፈራ ቊታ ሆኗልና።”
ይሖዋ እንዲህ አለኝ፩ “ሂድና ኚተልባ እግር ዚተሠራ ቀበቶ ግዛፀ በወገብህም ላይ ታጠቀውፀ ሆኖም ፈጜሞ ውኃ አታስነካው።”
ስለዚህ ይሖዋ ባዘዘኝ መሠሚት ቀበቶውን ገዝቌ ወገቀ ላይ ታጠቅኩት።
ዹይሖዋም ቃል ለሁለተኛ ጊዜ ወደ እኔ መጣፊ
“ዹገዛኾውንና ዚታጠቅኚውን ቀበቶ ይዘህ ተነስፀ ወደ ኀፍራጥስም ሄደህ በቋጥኝ ስንጥቅ ውስጥ ደብቀው።”
ስለዚህ ይሖዋ ባዘዘኝ መሠሚት ሄጄ በኀፍራጥስ አጠገብ ደበቅኩት።
ሆኖም ኚብዙ ቀናት በኋላ ይሖዋ “ተነስፀ ወደ ኀፍራጥስ ሄደህ፣ በዚያ እንድትደብቀው ያዘዝኩህን ቀበቶ አምጣ” አለኝ።
እኔም ወደ ኀፍራጥስ ሄጄ፣ ቀበቶውን ኚደበቅኩበት ቊታ ቆፍሬ አወጣሁፀ ቀበቶው ተበላሜቶና ሙሉ በሙሉ ኚጥቅም ውጭ ሆኖ አገኘሁት።
ኚዚያም ዹይሖዋ ቃል ወደ እኔ መጣፊ
“ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ዚይሁዳን ኩራትና ዚኢዚሩሳሌምን እብሪት ልክ እንደዚሁ አጠፋዋለሁ።
ቃሌን ለመታዘዝ አሻፈሚኝ ያለው፣ ግትር ሆኖ ዹገዛ ልቡን ዹሚኹተለው እንዲሁም ሌሎቜ አማልክትን ዚሚኚተለው፣ ዚሚያገለግለውና ለእነሱ ዹሚሰግደው ይህ ክፉ ሕዝብ ሙሉ በሙሉ ኚጥቅም ውጭ እንደሆነው እንደዚህ ቀበቶ ይሆናል።’
‘ቀበቶ በሰው ወገብ ላይ እንደሚጣበቅ፣ መላው ዚእስራኀል ቀትና መላው ዚይሁዳ ቀት ኚእኔ ጋር እንዲጣበቅ አደሚግኩ’ ይላል ይሖዋፀ ‘ይህም ሕዝቀ፣ ስሜ፣ ውዳሎዬና ውበቮ እንዲሆኑ ነው። እነሱ ግን አልታዘዙም።’
“አንተም ይህን መልእክት አክለህ ንገራ቞ውፊ ‘ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ “እያንዳንዱ ትልቅ እንስራ በወይን ጠጅ ይሞላል” ይላል።’ እነሱም ‘እያንዳንዱ ትልቅ እንስራ በወይን ጠጅ እንደሚሞላ እኛ መቜ ጠፋን?’ ብለው ይመልሱልሃል።
በዚህ ጊዜ እንዲህ በላቾው፩ ‘ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ዚምድሪቱን ነዋሪዎቜ በሙሉ፣ በዳዊት ዙፋን ላይ ዚሚቀመጡትን ነገሥታት፣ ካህናቱንና ነቢያቱን እንዲሁም ዚኢዚሩሳሌምን ነዋሪዎቜ በሙሉ በስካር እሞላ቞ዋለሁ።
እነሱንም እርስ በርሳ቞ው፣ አባቶቜንና ልጆቜንም አጋጫለሁ” ይላል ይሖዋ። “ምንም ዓይነት ርኅራኄም ሆነ ሐዘኔታ አላሳይምፀ ምሕሚትም አላደርግላ቞ውምፀ እነሱን ኚማጥፋት ምንም ነገር አያግደኝም።”’
ስሙፀ ልብ በሉ። ትዕቢተኞቜ አትሁኑፀ ይሖዋ ተናግሯልና።
ጹለማን ኚማምጣቱ በፊትናጚለምለም ባሉት ተራሮቜ ላይ እግሮቻቜሁ ኹመደናቀፋቾው በፊትለአምላካቜሁ ለይሖዋ ክብር ስጡ። እናንተ ብርሃንን ተስፋ ታደርጋላቜሁፀእሱ ግን ፅልማሞትን ያመጣልፀወደ ድቅድቅ ጹለማም ይለውጠዋል።
ለመስማት አሻፈሚን ካላቜሁ፣በኩራታቜሁ ዚተነሳ በስውር አለቅሳለሁ። ዹይሖዋ መንጋ በምርኮ ስለተወሰደእንባዬ እንደ ጎርፍ ይወርዳልፀ ዓይኔም በእንባ ይታጠባል።
ንጉሡንና ዚንጉሡን እናት እንዲህ በላቾው፩ ‘ዚሚያምሚው አክሊላቜሁ ኚራሳቜሁ ላይ ስለሚወድቅ፣ዝቅ ባለ ስፍራ ተቀመጡ።’
ዚደቡብ ኚተሞቜ ተዘግተዋልፀ ዚሚኚፍታ቞ውም ዚለም። መላው ይሁዳ በግዞት ተወስዷልፀ ሙሉ በሙሉም ተግዟል።
ዓይንሜን አንስተሜ ኹሰሜን ዚሚመጡትን ተመልኚቺ። ለአንቺ ዹተሰጠው መንጋ፣ ያማሩት በጎቜሜ ዚት አሉ?
ኚመጀመሪያው አንስቶ ዚተወዳጀሻ቞ው ዚቅርብ ጓደኞቜሜአንቺን ለመቅጣት ሲነሱ ምን ትዪ ይሆን? ልክ እንደምትወልድ ሎት ምጥ አይዝሜም?
በልብሜም ‘እነዚህ ነገሮቜ ዚደሚሱብኝ ለምንድን ነው?’ በምትይበት ጊዜ፣ ቀሚስሜን ዚተገፈፍሜውና ተሚኚዝሜ ለሥቃይ ዚተዳሚገው በፈጞምሜው ታላቅ በደል ዚተነሳ መሆኑን ልታውቂ ይገባል።
ኢትዮጵያዊ መልኩን፣ ነብርስ ዥጉርጉርነቱን መለወጥ ይቜላል? እንዲህ ማድሚግ ዚሚቜል ኚሆነ፣ክፉ ነገር መሥራት ዚለመዳቜሁት እናንተም መልካም ማድሚግ ትቜላላቜሁ ማለት ነው።
ስለዚህ ዹበሹሃ ነፋስ ይዞት እንደሚሄድ ገለባ እበትና቞ዋለሁ።
ይህ ዕጣሜ፣ ሰፍሬም ዚሰጠሁሜ ድርሻሜ ነው” ይላል ይሖዋፀ“ምክንያቱም እኔን ሚስተሜኛልፀ በሐሰትም ትታመኛለሜ።
በመሆኑም ቀሚስሜን እስኚ ፊትሜ እገልባለሁፀኀፍሚትሜም ይታያልፀ
ዚፈጞምሜው ምንዝር፣ በፍትወት ማሜካካትሜ፣ጞያፍ ዹሆነው ዝሙት አዳሪነትሜ ይገለጣል። አስጞያፊ ምግባርሜንበኮሚብቶቹና በሜዳው ላይ አይቌአለሁ። ኢዚሩሳሌም ሆይ፣ ወዮልሜ! ርኩስ ሆነሜ ዚምትኖሪው እስኚ መቌ ድሚስ ነው?”
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ በባቢሎንና በሌብቃማይ ነዋሪዎቜ ላይአጥፊ ነፋስ አስነሳለሁ።
እህል ዚሚያዘሩ ሰዎቜን ወደ ባቢሎን እሰዳለሁፀእነሱም ያዘሯታልፀ ምድሯንም ባዶ ያደርጋሉፀበጥፋት ቀን ኹሁሉም አቅጣጫ ይመጡባታል።
ቀስተኛው ደጋኑን አይወጥር። በተጚማሪም ማንም ሰው ጥሩሩን ለብሶ አይነሳ። ለወጣቶቿ ምንም ዓይነት ርኅራኄ አታሳዩ። ሠራዊቷን ሁሉ ፈጜማቜሁ አጥፉ።
እነሱም በኚለዳውያን ምድር ታርደው፣በጎዳናዎቿም ላይ ክፉኛ ቆስለው ይወድቃሉ።
እስራኀልና ይሁዳ ኚአምላካ቞ው፣ ኚሠራዊት ጌታ ኹይሖዋ ተለይተው መበለት አልሆኑም። ምድራ቞ው ግን በእስራኀል ቅዱስ ፊት በበደል ተሞልታለቜ።
ኚባቢሎን መካኚል ሞሜታቜሁ ውጡፀሕይወታቜሁን አድኑ። በእሷ በደል ዚተነሳ አትጥፉ። ይህ ዹይሖዋ ዹበቀል ጊዜ ነውና። ላደሚገቜው ነገር ዚእጇን ይኚፍላታል።
ባቢሎን በይሖዋ እጅ ያለቜ ዹወርቅ ጜዋ ነበሚቜፀምድርን ሁሉ አሰኚሚቜ። ብሔራት ወይን ጠጇን ጠጥተው ሰኚሩፀብሔራት ያበዱት ለዚህ ነው።
ባቢሎን በድንገት ወድቃ ተሰበሚቜ። ዋይ ዋይ በሉላት! ለሕመሟ ዹሚሆን በለሳን ውሰዱላትፀ ምናልባት ትፈወስ ይሆናል።”
“ባቢሎንን ለመፈወስ ሞክሹን ነበርፀ እሷ ግን ልትፈወስ አልቻለቜም። ትታቜኋት ሂዱፀ እያንዳንዳቜንም ወደ ገዛ ምድራቜን እንሂድ። ፍርዷ እስኚ ሰማያት ደርሷልናፀእስኚ ደመናት ድሚስ ኹፍ ብሏል።
ይሖዋ ፍትሕ አስፍኖልናል። ኑ፣ ዚአምላካቜንን ዹይሖዋን ሥራ በጜዮን እንናገር።”
“ፍላጻዎቻቜሁን አሹሉፀ ክብ ዚሆኑትን ጋሻዎቜ አንሱ። ይሖዋ ዚሜዶናውያንን ነገሥታት መንፈስ አነሳስቷልፀምክንያቱም ባቢሎንን ለማጥፋት አስቧል። ይህ ዹይሖዋ በቀል ይኾውም ስለ ቀተ መቅደሱ ዚሚወስደው ዹበቀል እርምጃ ነውና።
ዚባቢሎንን ቅጥሮቜ ለማጥቃት ምልክት አቁሙ። ጥበቃውን አጠናክሩፀ ጠባቂዎቜን አቁሙ። ሜምቅ ተዋጊዎቜን አዘጋጁ። ይሖዋ በባቢሎን ነዋሪዎቜ ላይ ዹጩር ስልት ነድፏልናፀበእነሱ ላይ ዹተናገሹውንም ቃል ይፈጜማል።”
“አንቺ በብዙ ውኃዎቜ ላይ ዚምትኖሪ፣በሀብትም ዚበለጞግሜ ሆይ፣መጚሚሻሜ ቀርቧልፀ አላግባብ ዚምታገኚው ትርፍ ገደቡ ላይ ደርሷል።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ሲል በራሱ ምሏልፊ‘እንደ አንበጣ ብዛት ባላ቞ው ሰዎቜ እሞላሻለሁፀእነሱም በአንቺ ላይ በድል አድራጊነት ይጮኻሉ።’
ምድርን በኃይሉ ዚሠራው፣ፍሬያማ ዚሆነቜውን መሬት በጥበቡ ዚመሠሚተውናሰማያትን በማስተዋሉ ዹዘሹጋው እሱ ነው።
ድምፁን ሲያሰማበሰማያት ያሉ ውኃዎቜ ይናወጣሉፀደመና ኚምድር ዳርቻዎቜ ወደ ላይ እንዲወጣ ያደርጋል። በዝናብ ጊዜ መብሚቅን ያበርቃልፀነፋሱንም ኹግምጃ ቀቱ ያወጣል።
እያንዳንዱ ሰው ማስተዋልና እውቀት ዹጎደለው ድርጊት ይፈጜማል። እያንዳንዱ አንጥሚኛ፣ በተቀሹጾው ምስል ዚተነሳ ኀፍሚት ይኚናነባልፀኚብሚት ዚተሠራው ምስሉ ሐሰት ነውናፀበውስጣ቞ውም መንፈስ ዚለም።
እነሱ ኚንቱና መሳለቂያ ና቞ው። ዚሚመሚመሩበት ቀን ሲመጣ ይጠፋሉ።
ዚያዕቆብ ድርሻ ግን እንደነዚህ ነገሮቜ አይደለምፀእሱ ዚርስቱን በትር ጚምሮዚሁሉ ነገር ሠሪ ነውና። ስሙ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ነው።”
“አንቺ ለእኔ እንደ ቆመጥ፣ እንደ ጩር መሣሪያም ነሜፀበአንቺ ብሔራትን አደቃለሁ። በአንቺ መንግሥታትን አወድማለሁ።
በአንቺ ፈሚሱንና ፈሹሰኛውን አደቃለሁ። በአንቺ ዹጩር ሠሹገላውንና ነጂውን አደቃለሁ።
በአንቺ ወንድንና ሎትን አደቃለሁ። በአንቺ ሜማግሌንና ልጅን አደቃለሁ። በአንቺ ወጣቱንና ወጣቷን አደቃለሁ።
በአንቺ እሚኛንና መንጋውን አደቃለሁ። በአንቺ ገበሬንና ጥማድ ኚብቶቹን አደቃለሁ። በአንቺ ገዢዎቜንና ዚበታቜ ገዢዎቜን አደቃለሁ።
ደግሞም በጜዮን፣ በፊታቜሁ ለሠሩት ክፋት ሁሉባቢሎንንና ዚኚለዳውያን ምድር ነዋሪዎቜን በሙሉ ዋጋቾውን እኚፍላ቞ዋለሁ” ይላል ይሖዋ።
“አንቺ ምድርን ሁሉ ያጠፋሜ፣አጥፊ ተራራ ሆይ፣ እነሆ እኔ በአንቺ ላይ ተነስቻለሁ” ይላል ይሖዋ። “በአንቺ ላይ እጄን እዘሚጋለሁፀ ኚቋጥኞቜም ላይ አንኚባልልሻለሁፀዚተቃጠለም ተራራ አደርግሻለሁ።”
“ሰዎቜ ዹማዕዘን ድንጋይም ሆነ ዚመሠሚት ድንጋይ ኚአንቺ አይወስዱምፀምክንያቱም አንቺ ለዘላለም ባድማ ትሆኛለሜ” ይላል ይሖዋ።
“በምድሪቱ ላይ ምልክት አቁሙ። በብሔራት መካኚል ቀንደ መለኚት ንፉ። በእሷ ላይ እንዲዘምቱ ብሔራትን መድቡ። ዚአራራት፣ ዹሚኒ እና ዚአሜኚናዝ መንግሥታት እሷን እንዲወጉ ሰብስቧ቞ው። በላይዋም ወታደሮቜን ዹሚመለምል መኮንን ሹሙባት። ፈሚሶቜንም እንደ ኩብኩባ ስደዱባት።
ብሔራትን፣ ዚሜዶንን ነገሥታት፣ ገዢዎቿን፣ ዚበታቜ ገዢዎቿን ሁሉናበእያንዳንዳ቞ው ግዛት ሥር ያለውን ምድር ሁሉበእሷ ላይ እንዲዘምቱ መድቧ቞ው።
ምድርም ትናወጣለቜፀ ትንቀጠቀጣለቜምፀይሖዋ ዚባቢሎንን ምድር አስፈሪ ቊታና ሰው አልባ ለማድሚግበባቢሎን ላይ ያሰበው ሐሳብ ይፈጞማልና።
ዚባቢሎን ተዋጊዎቜ መዋጋት አቁመዋል። በምሜጎቻ቞ው ውስጥ ይቀመጣሉ። ጉልበት ኚድቷ቞ዋል። እንደ ሎት ሆነዋል። መኖሪያዎቿ በእሳት ነደዋል። መቀርቀሪያዎቿ ተሰብሚዋል።
ኹተማው በዚአቅጣጫው እንደተያዘቜ ለባቢሎን ንጉሥ ለመንገርአንዱ መልእክተኛ ሲሮጥ ኹሌላው መልእክተኛ ጋር፣አንዱም ወሬ ነጋሪ ሲሮጥ ኹሌላው ወሬ ነጋሪ ጋር ይገናኛልፀ
መልካዎቹ እንደተያዙ፣ዚደንገል ጀልባዎቹ በእሳት እንደተቃጠሉናወታደሮቹ እንደተሞበሩ ሊነግሩት ይሯሯጣሉ።”
ዚእስራኀል አምላክ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላልና፩ “ዚባቢሎን ሎት ልጅ እንደ አውድማ ናት። ይህ በኃይል ዚምትሚገጥበት ጊዜ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ ዹመኹር ወቅት ይደርስባታል።”
“ዚባቢሎን ንጉሥ ናቡኚደነጟር ዋጠኝፀጚርሶ ግራ አጋባኝ። እንደ ባዶ ዕቃ አደሚገኝ። እንደ ትልቅ እባብ ዋጠኝፀዚእኔን መልካም ነገሮቜ በልቶ ሆዱን ሞላ። በውኃም ጠራርጎ አስወገደኝ።
ዚጜዮን ነዋሪ ‘በእኔና በአካሌ ላይ ዹተፈጾመው ግፍ በባቢሎን ላይ ይድሚስ!’ ትላለቜ። ኢዚሩሳሌም ‘ደሜም በኚለዳውያን ምድር ነዋሪዎቜ ላይ ይሁን!’ ትላለቜ።”
ስለዚህ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ እኔ እሟገትልሻለሁፀደግሞም እበቀልልሻለሁ። ባሕሯን አደርቃለሁፀ ዹውኃ ጉድጓዶቿንም ደሹቅ አደርጋለሁ።
ባቢሎንም ዚድንጋይ ቁልል፣ዚቀበሮዎቜ ጎሬ፣አስፈሪ ቊታና ማፏጫ ትሆናለቜፀዚሚኖርባትም አይገኝም።
ሁሉም በአንድነት እንደ ደቩል አንበሳ ያገሳሉ። እንደ አንበሳ ግልገሎቜ ያጉሚመርማሉ።”
“ፍላጎታ቞ው በኃይል ሲነሳሳ እጅግ ደስ እንዲሰኙድግሳ቞ውን አዘጋጅላ቞ዋለሁፀ እንዲሰክሩም አደርጋለሁፀኚዚያም ጚርሶ ላይነቁእስኚ ወዲያኛው ያንቀላፋሉ” ይላል ይሖዋ።
“እንደ ጠቊቶቜ፣እንደ አውራ በጎቜም ኚፍዚሎቜ ጋር ወደሚታሚዱበት ቊታ አወርዳ቞ዋለሁ።”
“ሌሻቅ እንዎት ተማሚኚቜ!ዚምድር ሁሉ ‘ውዳሎ’ እንዎት ተያዘቜ! ባቢሎን በብሔራት መካኚል ምንኛ አስፈሪ ቊታ ሆነቜ!
ባሕሩ ባቢሎንን አጥለቅልቋታል። በማዕበሉ ብዛት ተሞፍናለቜ።
ኚተሞቿ አስፈሪ ቊታ እንዲሁም ውኃ ዚሌለበት ምድርና በሹሃ ሆነዋል። ማንም ሰው ዚማይኖርበትና አንድም ሰው ዚማያልፍበት ምድር ሆነዋል።
ትኩሚ቎ን በባቢሎን በሚገኘው በቀል ላይ አደርጋለሁፀዚዋጠውንም ኹአፉ አስተፋዋለሁ። ብሔራት ኚእንግዲህ ወደ እሱ አይጎርፉምፀዚባቢሎንም ቅጥር ይፈርሳል።
ሕዝቀ ሆይ፣ ኚመካኚሏ ውጡ! ኹሚነደው ዹይሖዋ ቁጣ ሕይወታቜሁን ለማትሚፍ ሜሹ!
በምድሪቱ ላይ በሚሰማው ወሬ ልባቜሁ አይሞበርፀ በፍርሃትም አትዋጡ። በምድሪቱ ላይ ዓመፅ ስለመኖሩ፣ገዢም በገዢ ላይ ስለመነሳቱ፣ በአንደኛው ዓመት አንድ ወሬ ይሰማልፀበቀጣዩ ዓመት ደግሞ ሌላ ወሬ ይናፈሳል።
ስለዚህ፣ እነሆ ትኩሚ቎ንበባቢሎን ዚተቀሚጹ ምስሎቜ ላይ ዚማደርግበት ጊዜ ይመጣል። ምድሪቱ በሙሉ ኀፍሚት ትኚናነባለቜፀዚታሚዱባትም ሰዎቜ ሁሉ በመካኚሏ ይወድቃሉ።
ሰማያትና ምድር እንዲሁም በውስጣ቞ው ያሉት ሁሉበባቢሎን ዚተነሳ እልል ይላሉፀአጥፊዎቜ ኹሰሜን ይመጡባታልና” ይላል ይሖዋ።