text
stringlengths
4
267
እነሱ ሲወድቁ ከሚሰማው ታላቅ ድምፅ የተነሳ ምድር ተናወጠች። ጩኸት ይሰማል! ድምፁም እስከ ቀይ ባሕር ድረስ አስተጋብቷል።
እነሆ፣ ልክ እንደ ንስር ወደ ላይ ይወጣና ተወንጭፎ ይወርዳል፤በቦስራም ላይ ክንፎቹን ይዘረጋል። በዚያ ቀን የኤዶም ተዋጊዎች ልብ፣ምጥ እንደያዛት ሴት ልብ ይሆናል።”
ስለ ደማስቆ የተነገረ መልእክት፦ “ሃማትና አርጳድክፉ ወሬ በመስማታቸው አፍረዋል። በፍርሃት ይቀልጣሉ። ባሕሩ ታውኳል፤ ጸጥ ሊል አይችልም።
ደማስቆ ወኔ ከዳት። ለመሸሽ ወደ ኋላ ዞረች፤ ይሁንና ብርክ ያዛት። ልትወልድ እንደተቃረበች ሴትጭንቅና ሥቃይ ያዛት።
የምትወደሰው ከተማ፣ በሐሴትም የተሞላችው መዲናእንዴት ሳትተው ቀረች?
ወጣቶቿ በአደባባዮቿ ይወድቃሉና፤በዚያም ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይጠፋሉ” ይላል የሠራዊት ጌታ ይሖዋ።
“የደማስቆን ቅጥር በእሳት አነዳለሁ፤እሳቱም የቤንሃዳድን የማይደፈሩ ማማዎች ይበላል።”
ይሖዋ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር ስለመታቸው ስለ ቄዳርና ስለ ሃጾር መንግሥታት እንዲህ ይላል፦ “ተነሱ፤ ወደ ቄዳር ውጡ፤የምሥራቅንም ሰዎች አጥፉ።
ድንኳኖቻቸውና መንጎቻቸው፣የድንኳን ሸራዎቻቸውና ዕቃዎቻቸው ሁሉ ይወሰዳሉ። ግመሎቻቸውን ይነጠቃሉ፤‘ሽብር በየቦታው ነግሦአል!’ ብለው ወደ እነሱ ይጮኻሉ።”
“እናንተ የሃጾር ነዋሪዎች፣ ሽሹ፤ ወደ ሩቅ ቦታም ተሰደዱ! ወደ ጥልቁ ወርዳችሁ ተደበቁ” ይላል ይሖዋ። “የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር በእናንተ ላይ የጦር ስልት ነድፏልና፤በእናንተም ላይ አንድ ዕቅድ አቅዷል።”
“በሰላም፣ ተረጋግቶ በተቀመጠው ብሔር ላይተነሱ፣ ውጡ!” ይላል ይሖዋ። “በሮችም ሆነ መቀርቀሪያዎች የሉትም፤ ብቻቸውንም ይኖራሉ።
ግመሎቻቸው ይበዘበዛሉ፤ብዛት ያላቸው ከብቶቻቸውም በምርኮ ይወሰዳሉ። በሰሪሳራቸው ላይ ያለውን ፀጉር የሚላጩትን ሰዎችነፋስ ወደሚነፍስበት አቅጣጫ ሁሉ እበትናቸዋለሁ፤ከሁሉም አቅጣጫ ጥፋት አመጣባቸዋለሁ” ይላል ይሖዋ።
“ሃጾርም የቀበሮዎች ጎሬ፣ለዘለቄታውም ባድማ ትሆናለች። በዚያ ማንም ሰው አይኖርም፤አንድም ሰው በእሷ ውስጥ አይቀመጥም።”
በይሁዳ ንጉሥ በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ኤላምን አስመልክቶ ወደ ነቢዩ ኤርምያስ የመጣው የይሖዋ ቃል ይህ ነው፦
“የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እነሆ፣ የብርታታቸው ምንጭ የሆነውን የኤላምን ቀስት እሰብራለሁ።
ከአራቱ የሰማያት ዳርቻዎች፣ አራቱን ነፋሳት በኤላም ላይ አመጣለሁ፤ እኔም እነዚህ ነፋሳት በሚነፍሱበት አቅጣጫ ሁሉ እበትናቸዋለሁ። ከኤላም የተበተኑት ሰዎችም የማይሄዱበት ብሔር አይኖርም።’”
“ኤላማውያንን በጠላቶቻቸውና ሕይወታቸውን ማጥፋት በሚሹ ሰዎች ፊት አሸብራለሁ፤ በእነሱም ላይ ጥፋትን ይኸውም የሚነድ ቁጣዬን አመጣለሁ” ይላል ይሖዋ። “ፈጽሞ እስካጠፋቸውም ድረስ ከኋላቸው ሰይፍ እሰዳለሁ።”
“እኔም ዙፋኔን በኤላም አደርጋለሁ፤ ከዚያም ስፍራ ንጉሡንና መኳንንቱን አስወግዳለሁ” ይላል ይሖዋ።
“በዘመኑ መጨረሻ ግን ከኤላም ተማርከው የተወሰዱትን እሰበስባለሁ” ይላል ይሖዋ።
የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ በነገሠ በ10ኛው ዓመት ይኸውም ናቡከደነጾር በነገሠ በ18ኛው ዓመት ወደ ኤርምያስ የመጣው የይሖዋ ቃል ይህ ነው።
በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ ሠራዊት ኢየሩሳሌምን ከቦ ነበር፤ ነቢዩ ኤርምያስም በይሁዳ ንጉሥ ቤት፣ በክብር ዘቦቹ ግቢ ታስሮ ነበር።
የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ እንዲህ በማለት አስሮት ነበርና፦ “እንዲህ ብለህ ትንቢት የምትናገረው ለምንድን ነው? አንተ እንዲህ ትላለህ፦ ‘ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ይህችን ከተማ በባቢሎን ንጉሥ እጅ አሳልፌ እሰጣታለሁ፤ እሱም ይይዛታል፤
የይሁዳም ንጉሥ ሴዴቅያስ ከከለዳውያን እጅ አያመልጥም፤ ያላንዳች ጥርጥር በባቢሎን ንጉሥ እጅ አልፎ ይሰጣል፤ ከንጉሡም ጋር ፊት ለፊት ይነጋገራል፤ በዓይኖቹም ያየዋል።”’
‘ሴዴቅያስን ወደ ባቢሎን ይወስደዋል፤ ትኩረቴን ወደ እሱ እስካዞር ድረስም በዚያ ይቆያል’ ይላል ይሖዋ። ‘ከከለዳውያን ጋር መዋጋታችሁን ብትቀጥሉም እንኳ አይሳካላችሁም።’”
ኤርምያስ እንዲህ አለ፦ “የይሖዋ ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፦
‘እነሆ፣ የአጎትህ የሻሉም ልጅ ሃናምኤል ወደ አንተ መጥቶ “የመቤዠት መብት ያለህ የመጀመሪያው ሰው አንተ ስለሆንክ በአናቶት የሚገኘውን መሬቴን ለራስህ ግዛው” ይልሃል።’”
ይሖዋ በተናገረው መሠረት የአጎቴ ልጅ ሃናምኤል እኔ ወዳለሁበት ወደ ክብር ዘቦቹ ግቢ መጥቶ እንዲህ አለኝ፦ “በቢንያም አገር፣ በአናቶት የሚገኘውን መሬቴን እባክህ ግዛኝ፤ የመውረስና የመቤዠት መብት ያለህ አንተ ነህና። ስለዚህ መሬቱን ለራስህ ግዛው።” ይህ የሆነው ይሖዋ በተናገረው ቃል መሠረት እንደሆነ ተረዳሁ።
በመሆኑም በአናቶት ያለውን መሬት ከአጎቴ ልጅ ከሃናምኤል ላይ ገዛሁ። እኔም ሰባት ሰቅልና አሥር የብር ሰቅል ገንዘብ መዝኜ ሰጠሁት።
ከዚያም የውል ሰነድ ካዘጋጀሁ በኋላ በማኅተም አሸግኩት፤ ምሥክሮችንም ጠርቼ ገንዘቡን በሚዛን መዘንኩ።
በመመሪያውና በሕጉ መሠረት የታሸገውን እንዲሁም ያልታሸገውን የግዢውን የውል ሰነድ ወሰድኩ፤
ከዚያም የግዢውን የውል ሰነድ በአጎቴ ልጅ በሃናምኤል፣ በግዢው ውል ላይ በፈረሙት ምሥክሮች እንዲሁም በክብር ዘቦቹ ግቢ ተቀምጠው በነበሩት አይሁዳውያን ሁሉ ፊት ለማህሴያህ ልጅ፣ ለነሪያህ ልጅ ለባሮክ ሰጠሁት።
ባሮክንም በእነሱ ፊት እንዲህ ብዬ አዘዝኩት፦
“የእስራኤል አምላክ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እነዚህን የውል ሰነዶች፣ የታሸገውንም ሆነ ያልታሸገውን የግዢ የውል ሰነድ ወስደህ ለረጅም ጊዜ እንዲቆዩ በሸክላ ዕቃ ውስጥ አስቀምጣቸው።’
የእስራኤል አምላክ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ ‘በዚህች ምድር፣ ቤቶችና የእርሻ ቦታዎች እንዲሁም የወይን እርሻዎች እንደገና ይገዛሉ።’”
የግዢውን የውል ሰነድ ለነሪያህ ልጅ ለባሮክ ከሰጠሁት በኋላ እንዲህ ብዬ ወደ ይሖዋ ጸለይኩ፦
“አቤቱ፣ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ! እነሆ፣ አንተ ሰማያትንና ምድርን በታላቅ ኃይልህና በተዘረጋች ክንድህ ሠርተሃል። አንተ ምንም የሚሳንህ ነገር የለም፤
ለሺዎች ታማኝ ፍቅር ታሳያለህ፤ ይሁንና የአባቶችን በደል ከእነሱ በኋላ በሚመጡት ልጆቻቸው ላይ ትመልሳለህ፤ አንተ እውነተኛ፣ ታላቅና ኃያል አምላክ ነህ፤ ስምህም የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ነው።
በምክር ታላቅ፣ በሥራም ኃያል ነህ፤ ለእያንዳንዱ እንደ መንገዱና እንደ ሥራው ለመክፈል ዓይኖችህ የሰው ልጆችን መንገዶች ሁሉ ያያሉ።
እስከ ዛሬ ድረስ የሚነገርላቸውን ምልክቶችና ተአምራት በግብፅ ምድር አደረግክ፤ በዚህም መንገድ አሁን እየሆነ እንዳለው ሁሉ በእስራኤልና በሰው ልጆች መካከል ለራስህ ስም አተረፍክ።
ሕዝብህን እስራኤልን በምልክቶች፣ በተአምራት፣ በኃያል እጅ፣ በተዘረጋች ክንድና አስፈሪ በሆኑ ክንውኖች ከግብፅ ምድር አወጣህ።
“ከጊዜ በኋላም ለአባቶቻቸው ለመስጠት የማልክላቸውን ወተትና ማር የምታፈሰውን ይህችን ምድር ሰጠሃቸው።
እነሱም ገብተው ምድሪቱን ወረሷት፤ ሆኖም ቃልህን አልታዘዙም ወይም በሕግህ አልተመላለሱም። እንዲያደርጉ ያዘዝካቸውን ነገር ሁሉ አላደረጉም፤ ከዚህም የተነሳ ይህን ሁሉ ጥፋት በላያቸው አመጣህ።
እነሆ፣ ከተማዋን ለመያዝ ሰዎች በዙሪያዋ የአፈር ቁልል ደልድለዋል፤ ከሰይፉ፣ ከረሃቡና ከቸነፈሩ የተነሳ ከተማዋ እየወጓት ባሉት ከለዳውያን እጅ መውደቋ አይቀርም፤ አሁን እንደምታየው አንተ ያልከው ሁሉ ተፈጽሟል።
ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን ከተማዋ በከለዳውያን እጅ መውደቋ የማይቀር ቢሆንም ‘መሬቱን ለራስህ በምሥክሮች ፊት በገንዘብ ግዛ’ አልከኝ።”
በዚህ ጊዜ የይሖዋ ቃል እንዲህ ሲል ወደ ኤርምያስ መጣ፦
“እነሆ፣ እኔ የሰው ዘር ሁሉ አምላክ፣ ይሖዋ ነኝ። ለመሆኑ እኔ የሚሳነኝ ነገር አለ?
ስለዚህ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እነሆ፣ ይህችን ከተማ ለከለዳውያንና ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነጾር እሰጣታለሁ፤ እሱም ይይዛታል።
ይህችን ከተማ የሚወጓት ከለዳውያንም ይገባሉ፤ በእሳትም ያቃጥሏታል፤ ደግሞም ከተማዋን እንዲሁም ሕዝቡ እኔን ለማስቆጣት ሲሉ በጣሪያዎቻቸው ላይ ለባአል መሥዋዕቶች ያቀረቡባቸውንና ለሌሎች አማልክት የመጠጥ መባ ያፈሰሱባቸውን ቤቶች በእሳት ያቃጥሏቸዋል።’
“‘የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ ከልጅነታቸው ጀምሮ በፊቴ ክፉ የሆነውን ነገር ብቻ አድርገዋልና፤ የእስራኤል ሕዝብ በእጃቸው ሥራ እኔን ማስቆጣታቸውን አልተዉም’ ይላል ይሖዋ።
‘ይህች ከተማ ከገነቧት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ ቁጣዬንና ንዴቴን ከማነሳሳት በስተቀር ምንም የፈየደችው ነገር የለም፤ በመሆኑም ከፊቴ አስወግዳታለሁ፤
ይህም የሆነው የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ ይኸውም እነሱ፣ ነገሥታታቸው፣ መኳንንታቸው፣ ካህናታቸው፣ ነቢያታቸው፣ የይሁዳ ሰዎችና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች እኔን ለማስቆጣት በሠሩት ክፉ ነገር ሁሉ የተነሳ ነው።
ለእኔ ፊታቸውን ሳይሆን ጀርባቸውን ሰጡ፤ ደግሜ ደጋግሜ ላስተምራቸው ብሞክርም፣ አንዳቸውም ተግሣጼን ለመቀበል ፈቃደኛ አይደሉም።
ስሜ የተጠራበትንም ቤት ለማርከስ አስጸያፊ ጣዖቶቻቸውን በዚያ አስቀመጡ።
በተጨማሪም ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን ለሞሎክ በእሳት አሳልፈው ለመስጠት በሂኖም ልጅ ሸለቆ ያሉትን የባአልን ከፍ ያሉ የማምለኪያ ቦታዎች ሠርተዋል፤ ይሁዳን ኃጢአት ለማሠራት ይህን አስጸያፊ ነገር እንዲፈጽሙ እኔ አላዘዝኩም፤ ፈጽሞም በልቤ አላሰብኩም።’
“ስለዚህ እናንተ በሰይፍ፣ በረሃብና በቸነፈር ለባቢሎን ንጉሥ አልፋ ትሰጣለች ስለምትሏት ስለዚህች ከተማ የእስራኤል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦
‘እነሆ፣ እነሱን በመዓቴና በታላቅ ቁጣዬ ከበተንኩባቸው አገሮች ሁሉ አንድ ላይ እሰበስባቸዋለሁ፤ ወደዚህም ቦታ መልሼ አመጣቸዋለሁ፤ ያለስጋት እንዲኖሩም አደርጋለሁ።
እነሱም ሕዝቤ ይሆናሉ፤ እኔም አምላካቸው እሆናለሁ።
ለእነሱም ሆነ ከእነሱ በኋላ ለሚመጡት ልጆቻቸው መልካም ይሆንላቸው ዘንድ ዘወትር እኔን እንዲፈሩ አንድ ልብና አንድ መንገድ እሰጣቸዋለሁ።
ደግሞም ለእነሱ መልካም ነገር ከማድረግ እንዳልቆጠብ ከእነሱ ጋር ዘላለማዊ ቃል ኪዳን እገባለሁ፤ ከእኔም እንዳይርቁ በልባቸው ውስጥ እኔን የመፍራት መንፈስ አሳድራለሁ።
ለእነሱ መልካም በማድረግ እጅግ ደስ እሰኛለሁ፤ በሙሉ ልቤና በሙሉ ነፍሴም በዚህች ምድር ላይ አጽንቼ እተክላቸዋለሁ።’”
“ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ ‘በዚህ ሕዝብ ላይ ይህን ሁሉ ታላቅ ጥፋት እንዳመጣሁ፣ ልክ እንዲሁ ቃል የገባሁላቸውን መልካም ነገር ሁሉ አመጣላቸዋለሁ።
እናንተ “ሰውም ሆነ እንስሳ የማይኖርባት ጠፍ መሬት ናት፤ ለከለዳውያንም ተሰጥታለች” ብትሉም በዚህች ምድር ላይ እንደገና መሬት ይገዛል።’
“‘ተማርከው የተወሰዱባቸውን ሰዎች መልሼ ስለማመጣቸው፣ በቢንያም አገር፣ በኢየሩሳሌም ዙሪያ ባሉ ቦታዎች፣ በይሁዳ ከተሞች፣ በተራራማው ምድር ባሉ ከተሞች፣ በዝቅተኛው ስፍራ ባሉ ከተሞችና በደቡብ በሚገኙ ከተሞች መሬት በገንዘብ ይገዛል፤ የግዢ ውል ተዘጋጅቶ በማኅተም ይታሸጋል፤ ምሥክሮችም ይጠራሉ’ ይላል ይሖዋ።”
“እስራኤል ሆይ፣ ብትመለስ” ይላል ይሖዋ፣“ወደ እኔ ብትመለስ፣አስጸያፊ ጣዖቶችህን ከፊቴ ብታስወግድተንከራታች አትሆንም።
‘በእውነት፣ በፍትሕና በጽድቅሕያው ይሖዋን!’ ብለህ ብትምል፣ብሔራት በእሱ አማካኝነት በረከት ያገኛሉ፤በእሱም ይኮራሉ።”
ይሖዋ ለይሁዳ ሰዎችና ለኢየሩሳሌም እንዲህ ይላልና፦ “ያልለማውን መሬት እረሱ፤በእሾህ መካከልም አትዝሩ።
እናንተ የይሁዳ ሰዎችና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች፣ለይሖዋ ተገረዙ፤የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ፤አለዚያ በክፉ ሥራችሁ የተነሳቁጣዬ እንደ እሳት ይነድዳል፤ማንም ሊያጠፋው አይችልም።”
ይህን በይሁዳ ተናገሩ፤ በኢየሩሳሌምም አውጁ። ጩኹ፤ በምድሪቱም ሁሉ ላይ ቀንደ መለከት ንፉ። ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ እንዲህ በሉ፦ “አንድ ላይ ተሰብሰቡ፤ወደተመሸጉት ከተሞችም እንሽሽ።
ወደ ጽዮን የሚጠቁም ምልክት አቁሙ። መጠለያ ፈልጉ፤ ዝም ብላችሁም አትቁሙ።” ከሰሜን ጥፋት ብሎም ታላቅ መዓት አመጣለሁና።
ጠላት እንደ አንበሳ ከጥሻው ውስጥ ወጥቷል፤ብሔራትንም የሚያጠፋው ተነስቷል። ምድርሽን አስፈሪ ቦታ ሊያደርግ ከቦታው ወጥቷል። ከተሞችሽ አንድም ሰው የማይኖርባቸው የፍርስራሽ ክምር ይሆናሉ።
ስለዚህ ማቅ ልበሱ፤እዘኑ፤ ዋይ ዋይም በሉ፤ምክንያቱም የሚነደው የይሖዋ ቁጣ ከእኛ አልተመለሰም።
“በዚያ ቀን” ይላል ይሖዋ፣ “የንጉሡ ልብናየመኳንንቱ ልብ ይቀልጣል፤ካህናቱም ይሸበራሉ፤ ነቢያቱም ይገረማሉ።”
ከዚያም እንዲህ አልኩ፦ “ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ ወዮ! ሰይፍ አንገታችን ላይ ተጋድሞ እያለ ‘ሰላም ታገኛላችሁ’ ብለህ ይህን ሕዝብና ኢየሩሳሌምን ፈጽሞ አታለሃል።”
በዚያን ጊዜ ለዚህ ሕዝብና ለኢየሩሳሌም እንዲህ ይባላል፦ “የሚለበልብ ነፋስ በበረሃ ከሚገኙ ጠፍ ኮረብቶች ተነስቶወደ ሕዝቤ ሴት ልጅ በፍጥነት ይነፍሳል፤ነፋሱ የሚነፍሰው እህል ለማዝራትም ሆነ ለማጥራት አይደለም።
በእኔ ትእዛዝ ኃይለኛው ነፋስ ከእነዚህ ስፍራዎች ይመጣል። አሁን በእነሱ ላይ ፍርድ አስተላልፋለሁ።
እነሆ፣ እሱ ዝናብ እንዳዘሉ ደመናት ይመጣል፤ሠረገሎቹም እንደ አውሎ ነፋስ ናቸው። ፈረሶቹ ከንስር ይበልጥ ፈጣኖች ናቸው። ጠፍተናልና ወዮልን!
ኢየሩሳሌም ሆይ፣ እንድትድኚ ልብሽን ከክፋት ሁሉ አጥሪ። እስከ መቼ በውስጥሽ ክፉ ሐሳብ ይዘሽ ትኖሪያለሽ?
አንድ ድምፅ ከዳን ዜናውን ይናገራልና፤ከኤፍሬም ተራሮችም ጥፋትን ያውጃል።
ይህን አሳውቁ፤ አዎ ለብሔራት ተናገሩ፤በኢየሩሳሌም ላይ አውጁ።” “ጠባቂዎች ከሩቅ አገር እየመጡ ነው፤በይሁዳ ከተሞችም ላይ ይጮኻሉ።
ማሳ እንደሚጠብቁ ሰዎች ከሁሉም አቅጣጫ ይመጡባታል፤ምክንያቱም እሷ በእኔ ላይ ዓምፃለች” ይላል ይሖዋ።
“ለተከተልሽው መንገድና ለፈጸምሽው ተግባር ዋጋሽን ትቀበያለሽ። የሚደርስብሽ ጥፋት ምንኛ መራራ ነው፤ወደ ልብሽ ዘልቆ ይገባልና!”
ወይ አበሳዬ! ወይ አበሳዬ! ልቤን ሥቃይ ቀስፎታል። ልቤ በውስጤ በኃይል ይመታል። ዝም ማለት አልችልም፤የቀንደ መለከት ድምፅ፣የጦርነት ማስጠንቀቂያ ድምፅ ሰምቻለሁና።
በጥፋት ላይ ጥፋት መድረሱ ተወርቷል፤ምድሪቱ በሙሉ ወድማለችና። የገዛ ድንኳኖቼ በድንገት፣የድንኳን ሸራዎቼም በቅጽበት ጠፍተዋል።
ምልክቱን የማየውናየቀንደ መለከቱን ድምፅ የምሰማው እስከ መቼ ድረስ ነው?
“ሕዝቤ ሞኝ ነውና፤እነሱ ለእኔ ትኩረት አይሰጡም። ማስተዋል የሌላቸው ቂል ልጆች ናቸው። ክፉ ነገር ለማድረግ ብልሃተኞች ናቸው፤መልካም ነገር ማድረግ ግን አያውቁም።”
ምድሪቱን አየሁ፤ እነሆም፣ ባዶና ወና ነበረች። ወደ ሰማያት ተመለከትኩ፤ ብርሃናቸው ጠፍቶ ነበር።
ተራሮቹን አየሁ፤ እነሆ፣ ይናወጡ ነበር፤ኮረብቶቹም ይንቀጠቀጡ ነበር።
እኔም ተመለከትኩ፤ እነሆ፣ በዚያ አንድም ሰው አልነበረም፤የሰማይ ወፎችም ሁሉ ሸሽተው ነበር።
እኔም አየሁ፤ እነሆ፣ የፍራፍሬ እርሻው ምድረ በዳ ሆኖ ነበር፤ከተሞቹም ሁሉ ፈራርሰው ነበር። ይህም የሆነው በይሖዋ፣በሚነደውም ቁጣው የተነሳ ነው።
ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ “ምድሪቱ በሙሉ ባድማ ትሆናለች፤ሆኖም ፈጽሜ አላጠፋትም።
ከዚህ የተነሳ ምድሪቱ ታዝናለች፤በላይ ያሉት ሰማያትም ይጨልማሉ። ምክንያቱም እኔ ተናግሬአለሁ፤ ደግሞም ወስኛለሁ፤ሐሳቤንም አለውጥም፤ ወደ ኋላም አልመለስም።
ከፈረሰኞቹና ከቀስተኞቹ ድምፅ የተነሳከተማዋ በሙሉ ትሸሻለች። ጥሻ ውስጥ ይገባሉ፤ዓለቶቹም ላይ ይወጣሉ። ከተሞቹ ሁሉ ተትተዋል፤የሚኖርባቸውም ሰው የለም።”
ለጥፋት ተዳርገሻል፤ ታዲያ ምን ታደርጊ ይሆን? ደማቅ ቀይ ልብስ ትጎናጸፊ፣በወርቅ ጌጣጌጦች ታጌጪናዓይኖችሽን ትኳዪ ነበር። ይሁንና ትዋቢ የነበረው እንዲያው በከንቱ ነው፤በፍትወት ስሜት ይከተሉሽ የነበሩት ትተውሻልና፤አሁን ሕይወትሽን ይሿታል።
እንደታመመች ሴት ድምፅ፣የመጀመሪያ ልጇንም ለመውለድ እንደምታምጥ ሴት ያለ የጭንቅ ድምፅ፣ደግሞም ትንፋሽ አጥሯት ቁና ቁና የምትተነፍሰውን የጽዮን ሴት ልጅ ድምፅ ሰምቻለሁና። እሷም እጆቿን ዘርግታ “ወዮልኝ! ከገዳዮች የተነሳ ዝያለሁና” ትላለች።
የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ በነገሠ በዘጠነኛው ዓመት፣ በአሥረኛው ወር፣ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾርና መላው ሠራዊቱ መጥተው ኢየሩሳሌምን ከበቧት።
በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት በ11ኛው ዓመት፣ በአራተኛው ወር፣ ከወሩም በዘጠነኛው ቀን የከተማዋን ቅጥር ነደሉ።
የባቢሎን ንጉሥ መኳንንት ሁሉ ይኸውም ሳምጋሩ ኔርጋልሻሬጸር፣ ራብሳሪስ የሆነው ነቦሳርሰኪም፣ ራብማግ የሆነው ኔርጋልሻሬጸርና የቀሩት የባቢሎን ንጉሥ መኳንንት ሁሉ ገብተው በመካከለኛው በር አጠገብ ተቀመጡ።
የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስና ወታደሮቹ ሁሉ ባዩአቸው ጊዜ፣ በንጉሡ የአትክልት ቦታ ባለው መንገድ፣ በሁለቱ ቅጥሮች መካከል በሚገኘው በር በኩል በሌሊት ከከተማዋ ወጥተው ሸሹ፤ ወደ አረባ የሚወስደውንም መንገድ ተከትለው ሄዱ።
የከለዳውያን ሠራዊት ግን አሳደዳቸው፤ ሴዴቅያስንም በኢያሪኮ በረሃማ ሜዳ ላይ ደረሱበት። ከያዙት በኋላ በሃማት ምድር በሪብላ ወደነበረው ወደ ባቢሎን ንጉሥ ወደ ናቡከደነጾር አመጡት፤ እሱም በዚያ ፈረደበት።
የባቢሎን ንጉሥ በሪብላ የሴዴቅያስን ወንዶች ልጆች ዓይኑ እያየ አሳረዳቸው፤ በተጨማሪም የባቢሎን ንጉሥ የይሁዳን ታላላቅ ሰዎች ሁሉ አሳረደ።