text stringlengths 4 267 |
|---|
የሴዴቅያስንም ዓይን አሳወረ፤ ከዚያም ወደ ባቢሎን ለመውሰድ በመዳብ የእግር ብረት አሰረው። |
ከለዳውያንም የንጉሡን ቤትና የሕዝቡን ቤቶች አቃጠሉ፤ የኢየሩሳሌምንም ቅጥሮች አፈረሱ። |
የዘቦች አለቃ የሆነው ናቡዛራዳን በከተማዋ ውስጥ የቀሩትን በሕይወት የተረፉ ሰዎችና ከድተው ለእሱ እጃቸውን የሰጡትን ሰዎች እንዲሁም የቀሩትን ሁሉ በግዞት ወደ ባቢሎን ወሰዳቸው። |
ሆኖም የዘቦች አለቃ የሆነው ናቡዛራዳን ምንም ነገር ያልነበራቸውን አንዳንድ ያጡ የነጡ ድሆች በይሁዳ ምድር እንዲኖሩ ተዋቸው። ደግሞም በዚያ ቀን የወይን እርሻዎችና የሚያርሱት የእርሻ መሬት ሰጣቸው። |
በዚህ ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር ኤርምያስን አስመልክቶ የዘቦች አለቃ ለሆነው ለናቡዛራዳን እንዲህ የሚል መመሪያ ሰጠ፦ |
“ወስደህ የሚያስፈልገውን እንክብካቤ አድርግለት፤ ክፉ ነገር አታድርግበት፤ የሚጠይቅህንም ነገር ሁሉ አድርግለት።” |
በመሆኑም የዘቦች አለቃ የሆነው ናቡዛራዳን፣ ራብሳሪስ የሆነው ናቡሻዝባን፣ ራብማግ የሆነው ኔርጋልሻሬጸር እንዲሁም የባቢሎን ንጉሥ ሹማምንት ሁሉ ልከው |
ኤርምያስን ከክብር ዘቦቹ ግቢ አስወጡት፤ ደግሞም ወደ ቤቱ እንዲወስደው ለሳፋን ልጅ፣ ለአኪቃም ልጅ፣ ለጎዶልያስ ሰጡት። በመሆኑም ኤርምያስ በሕዝቡ መካከል ተቀመጠ። |
ኤርምያስ በክብር ዘቦቹ ግቢ ተዘግቶበት በነበረ ጊዜ የይሖዋ ቃል እንዲህ ሲል ወደ እሱ መጣ፦ |
“ሂድና ለኢትዮጵያዊው ለኤቤድሜሌክ እንዲህ በለው፦ ‘የእስራኤል አምላክ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “እነሆ፣ በዚህች ከተማ ላይ ለመልካም ሳይሆን ለጥፋት ቃሌን እፈጽማለሁ፤ በዚያም ቀን ይህ ሲፈጸም ታያለህ።”’ |
“‘አንተን ግን በዚያ ቀን እታደግሃለሁ’ ይላል ይሖዋ፤ ‘ለምትፈራቸውም ሰዎች አልፈህ አትሰጥም።’ |
“‘የምታመልጥበትን መንገድ አዘጋጅልሃለሁ፤ በሰይፍም አትወድቅም። በእኔ ስለታመንክ ሕይወትህ እንደ ምርኮ ትሆንልሃለች’ ይላል ይሖዋ።” |
በይሖዋ ቤት ዋና ሹም የነበረው የኢሜር ልጅ ካህኑ ጳስኮር፣ ኤርምያስ እነዚህን ነገሮች ሲተነብይ ሰማ። |
ጳስኮርም ነቢዩ ኤርምያስን መታው፤ ከዚያም በይሖዋ ቤት ባለው በላይኛው የቢንያም በር በእግር ግንድ ጠረቀው። |
ይሁንና በማግስቱ ጳስኮር ኤርምያስን ከእግር ግንዱ ውስጥ ፈታው፤ በዚህ ጊዜ ኤርምያስ እንዲህ አለው፦ “ይሖዋ፣ ማጎርሚሳቢብ ብሎ ይጠራሃል እንጂ ጳስኮር አይልህም። |
ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ ‘አንተም ሆንክ ወዳጆችህ እንድትሸበሩ አደርጋለሁ፤ እነሱም ዓይንህ እያየ በጠላቶቻቸው ሰይፍ ይወድቃሉ፤ ይሁዳንም ሁሉ ለባቢሎን ንጉሥ አሳልፌ እሰጣለሁ፤ እሱም በግዞት ወደ ባቢሎን ይወስዳቸዋል፤ በሰይፍም ይገድላቸዋል። |
የዚህችን ከተማ ሀብት ሁሉ፣ ጥሪቷን ሁሉ፣ ውድ የሆኑትን ነገሮች ሁሉ እንዲሁም የይሁዳን ነገሥታት ውድ ሀብት ሁሉ በጠላቶቻቸው እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ። እነሱም ይበዘብዟቸዋል፤ ወደ ባቢሎንም ያግዟቸዋል። |
ጳስኮር ሆይ፣ አንተና በቤትህ የሚኖሩ ሁሉ በግዞት ትወሰዳላችሁ። ወደ ባቢሎን ትሄዳለህ፤ በዚያም ትሞታለህ፤ ከወዳጆችህም ሁሉ ጋር በዚያ ትቀበራለህ፤ ምክንያቱም ለእነሱ የሐሰት ትንቢት ተናግረሃል።’” |
ይሖዋ ሆይ፣ አሞኘኸኝ፤ እኔም ተሞኘሁ። አንተ በእኔ ላይ በረታህ፤ አሸነፍክም። እኔም ቀኑን ሙሉ መሳለቂያ ሆንኩ፤ሁሉም ያፌዙብኛል። |
በተናገርኩ ቁጥር እጮኻለሁና፤“ዓመፅና ጥፋት!” ብዬ አውጃለሁ። የይሖዋ ቃል ቀኑን ሙሉ ስድብና ፌዝ አስከትሎብኛል። |
ስለዚህ “እሱን አላነሳም፤ከእንግዲህም በስሙ አልናገርም” አልኩ። ይሁንና ቃሉ በልቤ ውስጥ እንዳለ፣ በአጥንቶቼም ውስጥ እንደገባ የሚነድ እሳት ሆነብኝ፤አፍኜ መያዝ አቃተኝ፤ከዚህ በላይ መቋቋም አልቻልኩም። |
ብዙ መጥፎ ወሬ ሰምቻለሁና፤በዙሪያዬ ያለው ሁኔታ አሸብሮኛል። “አውግዙት፤ እናውግዘው!” ሰላም የሚመኝልኝ ሰው ሁሉ የእኔን ውድቀት ይጠባበቃል፦ “ምናልባት ይታለል ይሆናል፤እኛም እናሸንፈዋለን፤ ደግሞም እንበቀለዋለን።” |
ይሖዋ ግን እንደ አስፈሪ ተዋጊ ከእኔ ጋር ነበር። ከዚህም የተነሳ የሚያሳድዱኝ ሰዎች ይሰናከላሉ እንጂ አያሸንፉም። ስለማይሳካላቸውም ለከፍተኛ ኀፍረት ይዳረጋሉ። የሚደርስባቸው ዘላለማዊ ውርደት ፈጽሞ አይረሳም። |
የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን ጻድቁን ትመረምራለህ፤የውስጥ ሐሳብንና ልብን ታያለህ። በእነሱ ላይ የምትወስደውን የበቀል እርምጃ እንዳይ አድርገኝ፤ጉዳዬን ለአንተ አቅርቤአለሁና። |
ለይሖዋ ዘምሩ! ይሖዋን አወድሱ! እሱ ድሃውን ከክፉ አድራጊዎች እጅ ታድጓልና። |
የተወለድኩበት ቀን የተረገመ ይሁን! እናቴ እኔን የወለደችበት ቀን አይባረክ! |
ለአባቴ “ልጅ፣ አዎ ወንድ ልጅ ተወልዶልሃል!” የሚል ምሥራች አብስሮ እጅግ ደስ ያሰኘው ሰው የተረገመ ይሁን። |
ያ ሰው፣ ይሖዋ ያላንዳች ጸጸት እንደገለበጣቸው ከተሞች ይሁን። በማለዳ ዋይታ፣ በቀትርም የጦርነት ሁካታ ይስማ። |
እናቴ የመቃብሬ ቦታ እንድትሆን፣ማህፀኗም ዘወትር እርጉዝ እንደሆነ ይኖር ዘንድ፣ገና በማህፀን ሳለሁ ለምን አልገደለኝም? |
ችግርንና ሐዘንን እንዳይ፣ዕድሜዬም በኀፍረት እንዲያከትምለምን ከማህፀን ወጣሁ? |
ይሖዋ ሆይ፣ አቤቱታዬን ለአንተ ሳቀርብ፣ከፍትሕ ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ሳናግርህ እነሆ፣ አንተ ጻድቅ ነህ። ታዲያ የክፉዎች መንገድ ለምን ይሰምራል?ደግሞስ ከዳተኞች ሳይጨነቁ የሚኖሩት ለምንድን ነው? |
አንተ ተክለሃቸዋል፤ እነሱም ሥር ሰደዋል። አድገዋል፤ ፍሬም አፍርተዋል። ከከንፈራቸው አይለዩህም፤ የውስጥ ሐሳባቸው ግን ከአንተ የራቀ ነው። |
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን በሚገባ ታውቀኛለህ፤ ታየኛለህም፤ልቤን መረመርክ፤ ከአንተም ጋር የሚስማማ ሆኖ አገኘኸው። ለእርድ እንደተዘጋጁ በጎች ለያቸው፤ለሚገደሉበትም ቀን ለይተህ አቆያቸው። |
ምድሪቱ ተራቁታ፣የሜዳውም ተክል ሁሉ ደርቆ የሚቆየው እስከ መቼ ድረስ ነው? በምድሪቱ በሚኖሩት ሰዎች ክፋት የተነሳአራዊቱና ወፎቹ ተጠራርገው ጠፉ። እነሱ፣ “ወደፊት ምን እንደሚገጥመን አያውቅም” ብለዋልና። |
ከእግረኞች ጋር ሮጠህ ከደከምክ፣ከፈረሶች ጋር እንዴት ልትወዳደር ትችላለህ? በሰላም ምድር ተማምነህ ብትቀመጥ እንኳጥቅጥቅ ባለው የዮርዳኖስ ጥሻ ውስጥ እንዴት ልትሆን ነው? |
የገዛ ወንድሞችህ፣የገዛ አባትህ ቤተሰቦች እንኳ አታለውሃልና። እነሱ በአንተ ላይ ጮኸዋል። መልካም ነገር ቢናገሩህ እንኳፈጽሞ አትመናቸው። |
“ቤቴን ትቻለሁ፤ ርስቴን ጥዬ ሄጃለሁ። እጅግ የምወዳትን በጠላቶቿ እጅ አሳልፌ ሰጥቻታለሁ። |
ርስቴ በጫካ ውስጥ እንዳለ አንበሳ ሆነችብኝ። በእኔ ላይ ጮኻብኛለች። በዚህም የተነሳ ጠላኋት። |
ርስቴ ለእኔ ብዙ ቀለማት እንዳለው አዳኝ አሞራ ነች፤ሌሎች አዳኝ አሞሮች ይከቧታል፤ ደግሞም ያጠቋታል። እናንተ የዱር አራዊት ሁሉ ኑ፤ በአንድነት ተሰብሰቡ፤ትቀራመቷት ዘንድ ኑ። |
ብዙ እረኞች የወይን እርሻዬን አጥፍተውታል፤ይዞታዬንም ረግጠውታል። የተወደደውን ይዞታዬን ጠፍ ምድረ በዳ አድርገውታል። |
ባድማ ሆኗል። ደግሞም ተራቁቷል፤በፊቴ ወና ሆኗል። ምድሪቱ በሙሉ ባድማ ሆናለች፤ይሁንና ይህን ልብ ያለ አንድም ሰው የለም። |
በምድረ በዳ ባሉት፣ በተበላሹ መንገዶች ሁሉ አጥፊዎች መጥተዋል፤የይሖዋ ሰይፍ ከአንዱ ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ድረስ ምድሪቱን ትበላለችና። ማንም ሰው ሰላም የለውም። |
ስንዴ ዘሩ፤ ሆኖም እሾህን አጨዱ። እስኪዝሉ ድረስ ሠሩ፤ ነገር ግን ምንም ጥቅም አላገኙም። ከሚነደው የይሖዋ ቁጣ የተነሳበሚያገኙት ምርት ያፍራሉ።” |
ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ሕዝቤ እስራኤል እንዲወርሰው ያደረግኩትን ርስት የሚነኩ ክፉ ጎረቤቶቼን ሁሉ ከምድራቸው እነቅላቸዋለሁ፤ የይሁዳንም ቤት ከመካከላቸው እነቅላለሁ። |
ከነቀልኳቸው በኋላ ግን ዳግመኛ ምሕረት አደርግላቸዋለሁ፤ እያንዳንዳቸውን ወደየርስታቸው፣ እያንዳንዳቸውንም ወደየምድራቸው እመልሳቸዋለሁ።” |
“ሕዝቤን በባአል እንዲምሉ እንዳስተማሩ ሁሉ እነሱም የሕዝቤን መንገድ በእርግጥ ቢማሩና ‘ሕያው ይሖዋን!’ ብለው በስሜ ቢምሉ በሕዝቤ መካከል ጸንተው ይኖራሉ። |
ይሁንና ከእነዚህ ብሔራት መካከል የማይታዘዝ ቢኖር ያን ብሔር እነቅለዋለሁ፤ ነቅዬም አጠፋዋለሁ” ይላል ይሖዋ። |
የእስራኤል አምላክ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ስለ ሞዓብ እንዲህ ይላል፦ “ወዮ፣ ነቦ ጠፍታለችና! ቂርያታይም ኀፍረት ተከናንባለች፤ ደግሞም ተይዛለች። አስተማማኝ የሆነው መጠጊያ ተዋርዷል፤ ፈራርሷልም። |
ከእንግዲህ ሞዓብን አያወድሷትም። ለውድቀት ትዳረግ ዘንድ፣ ‘ኑ ብሔር መሆኗ እንዲያከትም እንደምስሳት’ ብለው በሃሽቦን ይዶልቱባታል። አንቺም ማድመን ሆይ፣ ዝም በይ፤ከኋላሽ ሰይፍ ይከተልሻልና። |
ከሆሮናይም የጩኸት ድምፅእንዲሁም የጥፋትና የታላቅ ውድቀት ድምፅ ይሰማል። |
ሞዓብ ጠፍታለች። ልጆቿ ይጮኻሉ። |
ወደ ሉሂት በሚወስደው አቀበት እያለቀሱ ይወጣሉ። በደረሰው ጥፋት የተነሳ፣ ከሆሮናይም ቁልቁል በሚወስደው መንገድ ሲወርዱም የጭንቅ ጩኸት ይሰማሉ። |
ሽሹ፤ ሕይወታችሁን አትርፉ! በምድረ በዳ እንዳለ የጥድ ዛፍ ሁኑ። |
ምክንያቱም አንቺ በሥራሽና ውድ በሆነ ሀብትሽ ትታመኛለሽ፤ደግሞም ትያዣለሽ። ከሞሽ ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋርበአንድነት በግዞት ይወሰዳል። |
አጥፊው በእያንዳንዱ ከተማ ላይ ይመጣል፤አንድም ከተማ አያመልጥም። ይሖዋ በተናገረው መሠረትሸለቆው ይጠፋል፤ ደልዳላውም መሬት እንዳልነበረ ይሆናል። |
ለሞዓብ ምልክት አቁሙ፤ስትፈራርስ ትሸሻለችና፤ከተሞቿም አስፈሪ ቦታ ይሆናሉ፤የሚቀመጥባቸውም ሰው አይኖርም። |
ይሖዋ የሰጠውን ተልእኮ በግድየለሽነት የሚያከናውን የተረገመ ነው! ሰይፉን ደም ከማፍሰስ የሚመልስ ሰው የተረገመ ነው! |
ሞዓባውያን ከልጅነታቸው ጀምሮበአምቡላው ላይ እንደረጋ ወይን ጠጅ ተረጋግተው ተቀምጠዋል። ከአንዱ ዕቃ ወደ ሌላው ዕቃ አልተገላበጡም፤በግዞትም ተወስደው አያውቁም። በዚህም ምክንያት ቃናቸው እንዳለ ነው፤መዓዛቸውም አልተለወጠም። |
“‘ስለዚህ፣ እነሆ እነሱን እንዲገለብጡ ሰዎችን የምልክበት ጊዜ ይመጣል’ ይላል ይሖዋ። ‘እነሱም ይገለብጧቸዋል፤ ዕቃዎቻቸውንም ባዶ ያስቀራሉ፤ ትላልቅ እንስራዎቻቸውንም ይሰባብራሉ። |
የእስራኤል ቤት ይተማመንበት በነበረው በቤቴል እንዳፈረ ሁሉ ሞዓባውያንም በከሞሽ ያፍራሉ። |
“እኛ ለውጊያ የተዘጋጀን ኃያላን ተዋጊዎች ነን” በማለት እንዴት በድፍረት ትናገራላችሁ?’ |
የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ተብሎ የሚጠራው ንጉሥ እንዲህ ይላል፦‘ሞዓብ ጠፍታለች፤ከተሞቿ ተወረዋል፤ ምርጥ የሆኑት ወጣቶቻቸውም ታርደዋል።’ |
በሞዓባውያን ላይ የሚደርሰው ጥፋት ቀርቧል፤ውድቀታቸውም በፍጥነት እየቀረበ ነው። |
በዙሪያቸው ያሉ ሁሉ፣ስማቸውን የሚያውቁ ሁሉ አብረዋቸው ያዝናሉ። ‘ኃያሉ በትር፣ የውበትም ዘንግ እንዴት ተሰበረ!’ በሏቸው። |
አንቺ በዲቦን የምትኖሪ ሴት ልጅ ሆይ፣ከክብርሽ ውረጂ፤ ተጠምተሽም ተቀመጪ፤የሞዓብ አጥፊ በአንቺ ላይ መጥቶብሻልና፤የተመሸጉ ቦታዎችሽንም ያፈራርሳል። |
አንቺ በአሮዔር የምትኖሪ፣ መንገዱ አጠገብ ቆመሽ ተመልከቺ። የሚሸሸውን ወንድና የምታመልጠውን ሴት ‘ምን ተፈጠረ?’ ብለሽ ጠይቂ። |
ሞዓብ ኀፍረት ተከናነበች፤ በሽብርም ተውጣለች። ዋይ ዋይ በሉ፤ እንዲሁም ጩኹ። ሞዓብ መጥፋቷን በአርኖን አውጁ። |
“ፍርድ ወደ ደልዳላው መሬት መጥቷል፤ በሆሎን፣ በያሃጽና በመፋአት፣ |
በዲቦን፣ በነቦና በቤትዲብላታይም፣ |
በቂርያታይም፣ በቤትጋሙልና በቤትምዖን፣ |
በቀሪዮትና በቦስራ እንዲሁም በሩቅና በቅርብ ባሉ የሞዓብ ከተሞች ሁሉ ላይ መጥቷል። |
‘የሞዓብ ብርታት ተቆርጧል፤ክንዱም ተሰብሯል’ ይላል ይሖዋ። |
‘በይሖዋ ላይ ስለ ታበየ አስክሩት። ሞዓብ በትፋቱ ላይ ይንከባለላል፤መሳለቂያም ሆኗል። |
እስራኤል የአንተ መሳለቂያ ሆኖ አልነበረም? ራስህን የምትነቀንቀውና እሱን የምትቃወመውእስራኤል ከሌቦች ጋር ተገኝቶ ነው? |
እናንተ የሞዓብ ነዋሪዎች፣ ከከተሞቹ ወጥታችሁ በቋጥኝ ላይ ኑሩ፤በገደል አፋፍ ጎጆዋን እንደምትሠራ ርግብም ሁኑ።’” |
“ስለ ሞዓብ ኩራት ሰምተናል፤ እሱ በጣም ትዕቢተኛ ነው፤ስለ እብሪቱ፣ ስለ ኩራቱ፣ ስለ ትዕቢቱና ስለ ልቡ ማበጥ ሰምተናል።” |
“‘ቁጣውን አውቃለሁ’ ይላል ይሖዋ፤‘ሆኖም ጉራው ከንቱ ይሆናል። አንዳች ነገር አያደርጉም። |
ከዚህ የተነሳ ለሞዓብ አለቅሳለሁ፤ለሞዓብ ምድር ሁሉ እጮኻለሁ፤ለቂርሄረስ ነዋሪዎችም እቃትታለሁ። |
የሲብማ ወይን ሆይ፣ ለያዜር ከተለቀሰው በበለጠለአንቺ አለቅሳለሁ። የተንዠረገጉት ቅርንጫፎችሽ ባሕሩን ተሻግረዋል። እስከ ባሕሩ፣ እስከ ያዜርም ደርሰዋል። አጥፊው በበጋ ፍሬሽናለመከር በደረሰው ወይንሽ ላይ መጥቷል። |
ከፍራፍሬ እርሻውና ከሞዓብ ምድርሐሴትና ደስታ ጠፍቷል። ከወይን መጭመቂያዎቹ ወይን መፍሰሱን እንዲያቆም አድርጌአለሁ። በእልልታ ወይን የሚረግጥ ሰው አይኖርም። ጩኸቱ ለየት ያለ ጩኸት ይሆናል።’” |
“‘በሃሽቦን የሚያስተጋባው ጩኸት እስከ ኤልዓሌ ድረስ ይሰማል። እስከ ያሃጽ ድረስ ድምፃቸውን ያሰማሉ፤በዞአር የሚያስተጋባው ጩኸት እስከ ሆሮናይምና እስከ ኤግላት ሸሊሺያ ድረስ ይሰማል። የኒምሪም ውኃዎች እንኳ ይደርቃሉ። |
ከፍ ባለ የማምለኪያ ቦታ ላይ መባ የሚያቀርበውንናለአምላኩ መሥዋዕት የሚያቀርበውን ሰውከሞዓብ አጠፋለሁ’ ይላል ይሖዋ። |
‘ስለዚህ ልቤ ለሞዓብ እንደ ዋሽንት በሐዘን ያንጎራጉራል፤ለቂርሄረስ ሰዎችም ልቤ እንደ ዋሽንት በሐዘን ያንጎራጉራል። ያከማቸው ሀብት ይጠፋልና። |
ራስ ሁሉ ተመልጧል፤ጢምም ሁሉ ተላጭቷል። እጅ ሁሉ ተሸንትሯል፤በወገባቸውም ላይ ማቅ ታጥቀዋል!’” |
“‘በሞዓብ ጣሪያዎች ሁሉናበአደባባዮቿ ሁሉ ላይከዋይታ ሌላ የሚሰማ ነገር የለም። ሞዓብን እንደተጣለ እንስራሰባብሬአታለሁና’ ይላል ይሖዋ። |
‘እጅግ ተሸብራለች! ዋይ ዋይ በሉ! ሞዓብ ኀፍረት ተከናንቦ ጀርባውን አዙሯል! ሞዓብ መሳለቂያ ሆኗል፤በዙሪያው ያሉት ሁሉ ከእሱ የተነሳ ይደነግጣሉ።’” |
“ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ ‘እነሆ፣ ተወንጭፎ እንደሚወርድ ንስር፣እሱም በሞዓብ ላይ ክንፎቹን ይዘረጋል። |
ከተሞቹ ይወረራሉ፤ምሽጎቿም ይያዛሉ። በዚያ ቀን የሞዓብ ተዋጊዎች ልብምጥ እንደያዛት ሴት ልብ ይሆናል።’” |
“‘ሞዓብም ሕዝብ መሆኑ ያከትማል፤በይሖዋ ላይ ታብዮአልና። |
የሞዓብ ነዋሪ ሆይ፣ሽብር፣ ጉድጓድና ወጥመድ ይጠብቅሃል’ ይላል ይሖዋ። |
‘ከሽብር የሚሸሽ ሁሉ ጉድጓዱ ውስጥ ይወድቃል፤ከጉድጓዱም የሚወጣ ሁሉ በወጥመዱ ይያዛል።’ ‘የሚቀጡበትን ዓመት በሞዓብ ላይ አመጣለሁና’ ይላል ይሖዋ። |
‘የሚሸሹት ሰዎች ኃይላቸው ተሟጦ በሃሽቦን ጥላ ሥር ይቆማሉ። ከሃሽቦን እሳት፣ከሲሖን መካከልም ነበልባል ይወጣልና። የሞዓብን ግንባርናየሁከት ልጆችን ራስ ቅል ይበላል።’ |
‘ሞዓብ ሆይ፣ ወዮልህ! የከሞሽ ሰዎች ጠፍተዋል። ወንዶች ልጆችህ ተማርከዋልና፤ሴቶች ልጆችህም በግዞት ተወስደዋል። |
በዘመኑ መጨረሻ ግን፣ ከሞዓብ የተማረኩትን እሰበስባለሁ’ ይላል ይሖዋ። ‘በሞዓብ ላይ የተላለፈው የፍርድ መልእክት እዚህ ላይ ይደመደማል።’” |
ከይሖዋ ወደ ኤርምያስ የመጣው ቃል ይህ ነው፦ |
“ተነሥተህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ውረድ፤ እኔም በዚያ ቃሌን አሰማሃለሁ።” |
ስለዚህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ወረድኩ፤ እሱም በሸክላ መዘውሮቹ ላይ እየሠራ ነበር። |
ሆኖም ሸክላ ሠሪው በጭቃ እየሠራ የነበረው ዕቃ እጁ ላይ ተበላሸ። በመሆኑም ሸክላ ሠሪው ተስማሚ ሆኖ ባገኘው መንገድ መልሶ ሌላ ዕቃ አድርጎ ሠራው። |
ከዚያም የይሖዋ ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፦ |
“‘የእስራኤል ቤት ሆይ፣ ይህ ሸክላ ሠሪ እንዳደረገው እኔም በእናንተ ላይ ማድረግ አልችልም?’ ይላል ይሖዋ። ‘የእስራኤል ቤት ሆይ፣ እነሆ፣ በሸክላ ሠሪ እጅ እንዳለ ጭቃ፣ እናንተም በእኔ እጅ እንዲሁ ናችሁ። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.