text
stringlengths
4
267
በመንገድ ዚሚያልፉ ሁሉ በማሟፍ እጃ቞ውን ያጚበጭቡብሻል። “‘ፍጹም ውበት ዚተላበሰቜና ዚምድር ሁሉ ደስታ’ በማለት ይጠሯት ዚነበሚቜው ኹተማ ይህቜ ናት?” እያሉ በመገሹም በኢዚሩሳሌም ሎት ልጅ ላይ ያፏጫሉፀ ራሳ቞ውንም ይነቀንቃሉ።
ጠላቶቜሜ ሁሉ በአንቺ ላይ አፋቾውን ኚፍተዋል። እነሱ ያፏጫሉፀ ጥርሳ቞ውንም ያፋጫሉፀ ደግሞም “ዋጥናት። ስንጠብቀው ዹነበሹው ቀን ይህ ነው! ጊዜው ደርሶ ለማዚት በቃን!” ይላሉ።
ይሖዋ ያሰበውን አድርጓልፀዚተናገሚውን፣ ኚጥንትም ጀምሮ ያዘዘውን ፈጜሟል። ያላንዳቜ ርኅራኄ አፍርሷል። ጠላት በአንቺ ላይ በደሹሰው ነገር ደስ እንዲሰኝ፣ ዚባላጋራዎቜሜም ብርታት ኹፍ ኹፍ እንዲል አድርጓል።
ዚጜዮን ሎት ልጅ ቅጥር ሆይ፣ ልባ቞ው ወደ ይሖዋ ይጮኻል። እንባሜ እንደ ጅሚት ቀን ኚሌት ይፍሰስ። ለራስሜ ፋታ አትስጪፀ ዓይንሜ እንባ ማፍሰሱን አያቋርጥ።
ተነሺ! ሌሊት፣ ክፍለ ሌሊቶቹ ሲጀምሩ ጩኺ። በይሖዋ ፊት ልብሜን እንደ ውኃ አፍስሺ። በሚሃብ ምክንያት በዚመንገዱ ማዕዘን ተዝለፍልፈው ለወደቁት ልጆቜሜ ሕይወት ስትዪ፣እጆቜሜን ወደ እሱ ዘርጊ።
ይሖዋ ሆይ፣ ክፉኛ ዚቀጣኞውን እይፀ ደግሞም ተመልኚት። ሎቶቜ ዚሆዳ቞ውን ፍሬ፣ ዹገዛ ራሳ቞ውን ልጆቜ ይብሉ?ደግሞስ ካህናቱና ነቢያቱ በይሖዋ መቅደስ ውስጥ ይገደሉ?
ወንድ ልጅና ሜማግሌ ሞተው በዚመንገዱ ተዘርሚዋል። ደናግሌና ወጣት ወንዶቌ በሰይፍ ወድቀዋል። በቁጣህ ቀን ገደልክፀ ያላንዳቜ ርኅራኄ አሚድክ።
በበዓል ቀን እንደሚደሚገው ሁሉ ሜብርን ኚዚአቅጣጫው ጠራህ። በይሖዋ ዚቁጣ ቀን ያመለጠም ሆነ በሕይወት ዹተሹፈ ዚለምፀዚወለድኳ቞ውንና ያሳደግኳ቞ውን ልጆቜ ጠላቮ ፈጃ቞ው።
ይሖዋ ሆይ፣ ዚደሚሰብንን ነገር አስታውስ። ውርደታቜንን እይፀ ደግሞም ተመልኚት።
ርስታቜን ለእንግዶቜ፣ ቀቶቻቜን ለባዕድ አገር ሰዎቜ ተሰጡ።
አባት እንደሌላ቞ው ወላጅ አልባ ልጆቜ ሆንንፀ እናቶቻቜን እንደ መበለቶቜ ሆኑ።
ዹገዛ ራሳቜንን ውኃ ለመጠጣት መክፈል ነበሚብንፀ ዹገዛ እንጚታቜንን ዹምናገኘውም በግዢ ነበር።
አሳዳጆቻቜን አንገታቜንን ሊይዙ ተቃሚቡፀዝለናልፀ እሚፍት ዚሚባል ነገርም አላገኘንም።
በቂ ምግብ ለማግኘት ወደ ግብፅና ወደ አሩር እጃቜንን ዘሚጋን።
ኃጢአት ዚሠሩት አባቶቻቜን አሁን በሕይወት ዚሉምፀ እኛ ግን ዚእነሱን በደል ለመሾኹም ተገደድን።
አሁን አገልጋዮቜ ይገዙናልፀ ኚእጃ቞ው ዚሚያስጥለን ማንም ዚለም።
በምድሚ በዳ ካለው ሰይፍ ዚተነሳ ምግባቜንን ዚምናመጣው በሕይወታቜን ቆርጠን ነው።
ኚኚባድ ሚሃብ ዚተነሳ ቆዳቜን እንደ ምድጃ ጋለ።
በጜዮን ያሉ ሚስቶቜና በይሁዳ ኚተሞቜ ያሉ ደናግል ተዋሚዱ።
መኳንንቱ በእጃ቞ው ተንጠለጠሉፀ ሜማግሌዎቜም አልተኚበሩም።
ወጣቶቜ ወፍጮውን ይሞኚማሉፀ ልጆቜም ኚባድ እንጚት ሲሞኚሙ ይደናቀፋሉ።
ሜማግሌዎቜ ኹኹተማዋ በር ሄደዋልፀ ወጣቶቜም ሙዚቃቾውን መጫወት አቁመዋል።
ደስታ ኚልባቜን ራቀፀ ጭፈራቜን በሐዘን ተተካ።
ራሳቜን ላይ ያለው አክሊል ወድቋል። ኃጢአት ስለሠራን ወዮልን!
ኹዚህ ዚተነሳ ልባቜን ታመመፀኚእነዚህም ነገሮቜ ዚተነሳ ዓይኖቻቜን ፈዘዙፀ
ባድማ ዚሆነቜው ዚጜዮን ተራራ አሁን ዚቀበሮዎቜ መፈንጫ ሆናለቜና።
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን ለዘላለም በዙፋንህ ላይ ትቀመጣለህ። ዙፋንህ ኚትውልድ እስኚ ትውልድ ነው።
ለዘላለም ዚሚሳኞንና ለሹጅም ዘመን ዹተውኹን ለምንድን ነው?
ይሖዋ ሆይ፣ ወደ አንተ መልሰንፀ እኛም በፈቃደኝነት እንመለሳለን። ዘመናቜንን እንደቀድሞው አድስልን።
አንተ ግን ፈጜሞ ጥለኞናል። አሁንም በእኛ ላይ እጅግ እንደተቆጣህ ነህ።
ያንጞባርቅ ዹነበሹው ጥሩው ወርቅ፣ ምንኛ ደበዘዘ! ዚተቀደሱት ድንጋዮቜ በዚመንገዱ ማዕዘኖቜ ላይ እንዎት ተበተኑ!
በጠራ ወርቅ ዚተመዘኑት ዚጜዮን ውድ ልጆቜ፣ዚሞክላ ሠሪ እጅ እንደሠራውዚሞክላ ዕቃ እንዎት ተቆጠሩ!
ቀበሮዎቜ እንኳ ግልገሎቻ቞ውን ለማጥባት ጡታ቞ውን ይሰጣሉፀዚሕዝቀ ሎት ልጅ ግን በምድሚ በዳ እንዳሉ ሰጎኖቜ ጚካኝ ሆነቜ።
ኹውኃ ጥም ዚተነሳ፣ ዚሚጠባው ሕፃን ምላስ ኹላንቃው ጋር ይጣበቃል። ልጆቜ ምግብ ይለምናሉፀ አንዳቜ ነገር ዚሚሰጣ቞ው ግን ዚለም።
ምርጥ ምግብ ይበሉ ዚነበሩ ሰዎቜ በዚጎዳናው ላይ ጠኔ ይዟቾው ይተኛሉ። ውድ ልብስ ለብሰው ያደጉም ዚአመድ ቁልል ያቅፋሉ።
ዚሕዝቀ ሎት ልጅ ዚደሚሰባት ቅጣት፣ዚማንም እጅ ሳይሚዳት በድንገት ዚተገለበጠቜው ሰዶም፣ በሠራቜው ኃጢአት ዚተነሳ ኚደሚሰባት ቅጣት ይበልጥ ታላቅ ነው።
ናዝራውያኗ ኚበሚዶ ይልቅ ዚጠሩ፣ ኚወተትም ይልቅ ዚነጡ ነበሩ። ኹዛጎል ይበልጥ ዹቀሉ ነበሩፀ እንደተወለወለም ሰንፔር ነበሩ።
መልካ቞ው ኚጥላሞት ይልቅ ጠቁሯልፀበጎዳና ላይ ማንነታ቞ውን መለዚት ዚቻለ ዚለም። ቆዳ቞ው ተሞብሜቊ አጥንታ቞ው ላይ ተጣብቋልፀ እንደደሚቀ እንጚት ሆኗል።
በሰይፍ ዚሚወድቁት በሚሃብ ኚሚያልቁት ይሻላሉፀእነዚህ ዚምድርን ፍሬ በማጣታ቞ው መንምነው ያልቃሉ።
ሩኅሩኅ ዹሆኑ ሎቶቜ በገዛ እጃ቞ው ልጆቻ቞ውን ቀቅለዋል። ዚሕዝቀ ሎት ልጅ ጥፋት በደሚሰባት ጊዜ እንደ እዝን እንጀራ ሆነውላ቞ዋል።
ይሖዋ ቁጣውን ገልጿልፀዚሚነድ ቁጣውንም አፍስሷል። በጜዮን መሠሚቶቿን ዹሚበላ እሳት አንድዷል።
ዚምድር ነገሥታትና ዚምድር ነዋሪዎቜ ሁሉባላጋራም ሆነ ጠላት በኢዚሩሳሌም በሮቜ ይገባል ዹሚል እምነት አልነበራ቞ውም።
ይህ ዹደሹሰው ነቢያቷ በሠሩት ኃጢአትና ካህናቷ በፈጞሙት በደል ዚተነሳ ነውፀእነሱ በመካኚሏ ዚነበሩትን ጻድቃን ደም አፍስሰዋል።
ታውሚው በዚጎዳናው ተቅበዘበዙ። በደም ስለተበኚሉማንም ልብሳ቞ውን ለመንካት አይደፍርም።
“እናንተ ርኩሳን! ሂዱ!” ይሏ቞ዋል። “ሂዱ! ሂዱ! አትንኩን!” ብለው ይጮኹባ቞ዋል። መኖሪያ አጥተው ይቅበዘበዛሉና። በብሔራት መካኚል ያሉ ሰዎቜ እንዲህ ብለዋልፊ “ኚእንግዲህ ኚእኛ ጋር እዚህ መኖር አይቜሉም።
ይሖዋ ራሱ በታትኗ቞ዋልፀዳግመኛም በሞገስ ዓይን አይመለኚታ቞ውም። ሰዎቜ ለካህናቱ አክብሮት አይኖራ቞ውምፀ ለሜማግሌዎቹም ሞገስ አያሳዩም።”
አሁንም እንኳ እርዳታ እናገኛለን ብለን በኚንቱ ስንጠባበቅ ዓይኖቻቜን ደኚሙ። ሊያድነን ኚማይቜል ብሔር እርዳታ ለማግኘት ስንጠባበቅ ቆዚን።
እግር በእግር ተኚታተሉንፀ በመሆኑም በአደባባዮቻቜን መንቀሳቀስ አልቻልንም። መጚሚሻቜን ቀርቧልፀ ዚሕይወት ዘመናቜን አብቅቷልፀ ፍጻሜያቜን ደርሷልና።
አሳዳጆቻቜን በሰማይ ኚሚበርሩ ንስሮቜ ይልቅ ፈጣኖቜ ነበሩ። በተራሮቜ ላይ አጥብቀው አሳደዱንፀ በምድሚ በዳ አድፍጠው አጠቁን።
በይሖዋ ዚተቀባው፣ ዚሕይወታቜን እስትንፋስ፣ ጥልቅ ጉድጓዳ቞ው ውስጥ ገብቶ ተያዘፀ“በእሱ ጥላ ሥር በብሔራት መካኚል እንኖራለን” ብለን ነበር።
በዑጜ ምድር ዚምትኖሪ ዚኀዶም ሎት ልጅ ሆይ፣ ሐሎት አድርጊፀ ደስም ይበልሜ። ይሁንና ጜዋው ለአንቺም ይደርስሻልፀ ትሰክሪያለሜፀ እርቃንሜንም ትገልጫለሜ።
ዚጜዮን ሎት ልጅ ሆይ፣ በበደልሜ ምክንያት ዚደሚሰብሜ ቅጣት አብቅቷል። ኚእንግዲህ ወዲህ ወደ ግዞት አይወስድሜም። ይሁንና ዚኀዶም ሎት ልጅ ሆይ፣ ትኩሚቱን በሠራሜው በደል ላይ ያደርጋል። ኃጢአትሜን ይገልጣል።
ኚዚያም ኚምሥራቅ ትይዩ ወደሆነው በር ወሰደኝ።
በዚያም ዚእስራኀል አምላክ ክብር ኚምሥራቅ ሲመጣ አዚሁፀ ድምፁም እንደሚጎርፍ ውኃ ድምፅ ነበርፀ ኚክብሩም ዚተነሳ ምድር አበራቜ።
ያዚሁት ነገር ኹተማዋን ለማጥፋት በመጣሁ ጊዜ ያዚሁትን ራእይ ይመስል ነበርፀ ደግሞም በኬባር ወንዝ አቅራቢያ አይቌው ኹነበሹው ነገር ጋር ይመሳሰል ነበርፀ እኔም መሬት ላይ በግንባሬ ተደፋሁ።
ኚዚያም ዹይሖዋ ክብር ኚምሥራቅ ትይዩ በሆነው በር በኩል ወደ ቀተ መቅደሱ ገባ።
መንፈስም አንስቶ ወደ ውስጠኛው ግቢ አመጣኝፀ እኔም ቀተ መቅደሱ በይሖዋ ክብር ተሞልቶ አዚሁ።
ኚዚያም አንድ ሰው ኚቀተ መቅደሱ ውስጥ ሲያናግሚኝ ሰማሁፀ ሰውዹውም መጥቶ አጠገቀ ቆመ።
አምላክም እንዲህ አለኝ፩ “ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ይህ ዹዙፋኔ መቀመጫ፣ ዚእግሬ ማሳሚፊያና በእስራኀል ልጆቜ መካኚል ለዘላለም ዚምኖርበት ስፍራ ነው። ዚእስራኀል ቀት ሰዎቜ፣ እነሱም ሆኑ ንጉሊቻ቞ው በሚፈጜሙት መንፈሳዊ ምንዝርና በሞቱት ንጉሊቻ቞ው ሬሳ ኚእንግዲህ ቅዱስ ስሜን አያሚክሱም።
በእኔና በእነሱ መካኚል ግንቡ ብቻ ሲቀር፣ ደፋቾውን ኚቀ቎ ደፍ አጠገብ፣ መቃናቾውንም ኚቀ቎ መቃን አጠገብ በማድሚግ በሠሯ቞ው አስጞያፊ ነገሮቜ ቅዱስ ስሜን አርክሰዋልፀ ስለዚህ በቁጣዬ አጠፋኋ቞ው።
ኚእንግዲህ ዚሚፈጜሙትን መንፈሳዊ ምንዝር ያስወግዱፀ ዚንጉሊቻ቞ውንም ሬሳ ኚእኔ ያርቁፀ እኔም በመካኚላ቞ው ለዘላለም እኖራለሁ።
“አንተም ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ኚሠሩት በደል ዚተነሳ ኀፍሚት እንዲሰማ቞ው ለእስራኀል ቀት ሰዎቜ ስለ ቀተ መቅደሱ ግለጜላ቞ውፀ ንድፉንም ያጥኑ።
በሠሩት ነገር ሁሉ ኀፍሚት ኹተሰማቾው ዚቀተ መቅደሱን ንድፍ፣ አቀማመጡን፣ መውጫዎቹንና መግቢያዎቹን አሳውቃ቞ው። አጠቃላይ ንድፉንና ደንቊቹን፣ ንድፉንና ሕጎቹን አሳያ቞ውፀ ደግሞም እነሱ እያዩ ጻፋ቞ውፀ ይህን ዚምታደርገው አጠቃላይ ንድፉንና ደንቊቹን አስተውለው በተግባር እንዲያውሉ ነው።
ዚቀተ መቅደሱ ሕግ ይህ ነው። በተራራው አናት ዙሪያ ያለው ቊታ ሁሉ እጅግ ቅዱስ ነው። እነሆ፣ ዚቀተ መቅደሱ ሕግ ይህ ነው።
“ዚመሠዊያው ልክ በክንድ ሲለካ መጠኑ ይህ ነውፀ እያንዳንዱ ክንድ አንድ ጋት ተጚምሮበት ነበር። ዚመሠዊያው መሠሚት አንድ ክንድ ነውፀ ወርዱም አንድ ክንድ ነው። በጠርዙ ዙሪያ፣ ወርዱ አንድ ስንዝር ዹሆነ ክፈፍ አለው። ይህ ዚመሠዊያው መሠሚት ነው።
መሬት ላይ ካሚፈው መሠሚት አንስቶ በዙሪያው እስካለው ዚታቜኛው እርኚን ድሚስ ሁለት ክንድ ሲሆን ወርዱ ደግሞ አንድ ክንድ ነው። በዙሪያው ካለው ኚትንሹ እርኚን እስኚ ትልቁ እርኚን ድሚስ አራት ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ አንድ ክንድ ነው።
ዚመሠዊያው ምድጃ ኚፍታ አራት ክንድ ሲሆን ኚምድጃው በላይ ወጣ ወጣ ያሉ አራት ቀንዶቜ አሉ።
ዚመሠዊያው ምድጃ አራት ማዕዘን ሲሆን ርዝመቱ 12 ክንድ፣ ወርዱም 12 ክንድ ነው።
በዙሪያው ያለው እርኚን አራቱም ጎኖቜ ርዝመታ቞ው 14 ክንድ፣ ወርዳ቞ውም 14 ክንድ ነውፀ በዙሪያውም ያለው ክፈፍ ግማሜ ክንድ ሲሆን መሠሚቱም በሁሉም ጎኖቜ አንድ ክንድ ነው። “ደሚጃዎቹም ኚምሥራቅ ትይዩ ነበሩ።”
ኚዚያም እንዲህ አለኝ፩ “ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘በመሠዊያው ላይ ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ እንዲቀርብና በላዩ ላይ ደም እንዲሚጭበት፣ መሠዊያው ሲሠራ ሊኹተሏቾው ዚሚገቡት መመሪያዎቜ እነዚህ ና቞ው።’
“‘እኔን ለማገልገል በፊቮ ለሚቀርቡት ዚሳዶቅ ዘር ለሆኑት ሌዋውያን ካህናት፣ ኹመንጋው መካኚል ለኃጢአት መባ ዹሚሆን አንድ ወይፈን ትሰጣ቞ዋለህ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።
‘ኹደሙ ጥቂት ወስደህ በመሠዊያው አራት ቀንዶቜ፣ በዙሪያው ባለው እርኚን አራት ጎኖቜና በዙሪያው ባለው ጠርዝ ላይ አድርግፀ ይህን ዚምታደርገው መሠዊያውን ኚኃጢአት ለማንጻትና ለመሠዊያው ማስተሰሚያ ለማቅሚብ ነው።
ኚዚያም ኚመቅደሱ ውጭ፣ በቀተ መቅደሱ ውስጥ ለዚህ ተብሎ በተመደበው ቊታ ታቃጥለው ዘንድ ዚኃጢአት መባ ዹሆነውን ወይፈን ውሰድ።
በሁለተኛው ቀን ዚኃጢአት መባ ዹሚሆን እንኚን ዚሌለበት ተባዕት ፍዹል ታቀርባለህፀ እነሱም በወይፈኑ መሠዊያውን ኚኃጢአት እንዳነጹት ሁሉ በዚህም መሠዊያውን ኚኃጢአት ያነጹታል።’
“‘መሠዊያውን ኚኃጢአት ካነጻህ በኋላ ኚኚብቶቹ መካኚል እንኚን ዚሌለበት አንድ ወይፈንና ኹመንጋው መካኚል እንኚን ዚሌለበት አንድ አውራ በግ ታቀርባለህ።
ለይሖዋ ታቀርባ቞ዋለህፀ ካህናቱም ጹው ኚነሰነሱባ቞ው በኋላ ለይሖዋ ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ አድርገው ያቀርቧ቞ዋል።
በዚዕለቱ፣ ለሰባት ቀናት አንድ አውራ ፍዹል ዚኃጢአት መባ አድርገህ ታቀርባለህፀ እንዲሁም ኚኚብቶቹ መካኚል አንድ ወይፈንና ኹመንጋው መካኚል አንድ አውራ በግ ታቀርባለህፀ ዚምታቀርባ቞ው እንስሳት እንኚን ዚሌለባ቞ው ይሁኑ።
ለሰባት ቀናት ለመሠዊያው ማስተሰሚያ ያቀርባሉፀ መሠዊያውንም ያነጹታል እንዲሁም ለአገልግሎት ያዘጋጁታል።
እነዚህ ቀናት ኹተፈጾሙ በኋላ ኚስምንተኛው ቀን አንስቶ ካህናቱ ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባቜሁንና ዚኅብሚት መሥዋዕቶቻቜሁን በመሠዊያው ላይ ያቀርባሉፀ እኔም በእናንተ ደስ እሰኛለሁ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።”
ኚዚያም በስተ ሰሜን ወዳለው ወደ ውጹኛው ግቢ ወሰደኝ። ደግሞም በአቅራቢያው ኹሚገኘው ሕንፃ በስተ ሰሜን፣ ክፍት ኹሆነው ስፍራ አጠገብ ወዳሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ያሏ቞ው ሕንፃዎቜ አመጣኝ።
ሕንፃዎቹ በሰሜኑ መግቢያ በኩል ርዝመታ቞ው 100 ክንድ ነበርፀ ወርዳ቞ው ደግሞ 50 ክንድ ነበር።
ሕንፃዎቹ ዚሚገኙት ወርዱ 20 ክንድ በሆነው በውስጠኛው ግቢና በውጚኛው ግቢ መመላለሻ መንገድ መካኚል ነበር። ሕንፃዎቹ ባለ ሁለት ፎቅ ሲሆኑ ትይዩ ሆነው ዚተሠሩ ሰገነቶቜ ነበሯ቞ው።
በመመገቢያ ክፍሎቹ ፊት ወርዱ 10 ክንድ፣ ርዝመቱ ደግሞ 100 ክንድ ዹሆነ መተላለፊያ በውስጥ በኩል ነበርፀ ዚክፍሎቹም መግቢያዎቜ ዚሚገኙት በስተ ሰሜን በኩል ነበር።
ኹላይ ያሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ኚታቜ ካሉትና መካኚል ላይ ካሉት ዹሕንፃው ክፍሎቜ ይልቅ ጠበብ ያሉ ነበሩፀ ምክንያቱም ሰገነቶቹ ሰፋ ያለ ቊታ ይዘውባ቞ው ነበር።
ዚመመገቢያ ክፍሎቹ ባለ ሁለት ፎቅ ነበሩፀ ይሁንና በግቢው ውስጥ እንዳሉት ዓይነት ዓምዶቜ አልነበሯ቞ውም። ኚታቜ ካሉትና መካኚል ላይ ካሉት ይበልጥ ኹላይኛው ፎቅ ክፍሎቜ ሰፊ ቊታ ዹተወሰደው ለዚህ ነው።
ኚሌሎቹ ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ጋር ትይዩ ኚሆኑትና በውጹኛው ግቢ በኩል ካሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ አጠገብ ዹሚገኘው ዹውጹኛው ዚድንጋይ ቅጥር ርዝመት 50 ክንድ ነበር።
በውጹኛው ግቢ በኩል ያሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ርዝመት 50 ክንድ ሲሆን ኚመቅደሱ ትይዩ ያሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ርዝመት ግን 100 ክንድ ነበር።
ዚመመገቢያ ክፍሎቹ በስተ ምሥራቅ በኩል፣ ኹውጹኛው ግቢ ወደ ክፍሎቹ ዚሚወስድ መግቢያ ነበራ቞ው።
በደቡብም በኩል ክፍት በሆነው ስፍራና በሕንፃው አቅራቢያ፣ በስተ ምሥራቅ ባለው ዚግቢው ዚድንጋይ ቅጥር ውስጥ ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ነበሩ።
በስተ ሰሜን እንዳሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ሁሉ በእነዚህ ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ፊትም መተላለፊያ ነበር። ክፍሎቹ ተመሳሳይ ርዝመትና ወርድ ነበራ቞ውፀ መውጫዎቻ቞ውም ሆኑ ንድፎቻ቞ው ተመሳሳይ ነበሩ። መግቢያዎቻ቞ው
በደቡብ በኩል ኚሚገኙት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ መግቢያዎቜ ጋር ተመሳሳይ ነበሩ። በስተ ምሥራቅ በኩል በአቅራቢያው ካለው ዚድንጋይ ቅጥር ፊት፣ በመተላለፊያው መንገድ መነሻ ላይ ሰው ሊገባበት ዚሚቜል መግቢያ ነበር።
ኚዚያም እንዲህ አለኝ፩ “ክፍት ኹሆነው ስፍራ አጠገብ ዚሚገኙት በስተ ሰሜን ያሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜና በስተ ደቡብ ያሉት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ፣ ወደ ይሖዋ ዚሚቀርቡት ካህናት እጅግ ቅዱስ ዚሆኑትን መባዎቜ ዚሚበሉባ቞ው ዚተቀደሱ መመገቢያ ክፍሎቜ ና቞ው። በዚያም እጅግ ቅዱስ ዚሆኑትን መባዎቜ፣ ዚእህል መባ፣ ዚኃጢአት መባና ዹበደል መባ ያስቀምጣሉፀ ምክንያቱም ቊታው ቅዱስ ነው።
ካህናቱ በሚገቡበት ጊዜ፣ ሲያገለግሉ ዚሚለብሱትን ልብስ ሳያወልቁ ኚቅዱሱ ስፍራ ወደ ውጹኛው አደባባይ መውጣት አይቜሉምፀ ልብሶቹ ቅዱስ ና቞ውና። ለሕዝቡ ወደተፈቀዱት ቊታዎቜ ኚመሄዳ቞ው በፊት ልብሳ቞ውን ይቀይሩ ነበር።”
ዚቀተ መቅደሱን ዚውስጠኛውን ስፍራ ለክቶ ሲጚርስ ኚምሥራቅ ትይዩ ወደሆነው በር በሚወስደው መተላለፊያ በኩል ይዞኝ ወጣፀ ኚዚያም ስፍራውን በጠቅላላ ለካ።
በስተ ምሥራቅ በኩል ያለውን በመለኪያ ዘንግ ለካ። በመለኪያ ዘንጉ ኚአንዱ ጎን እስኚ ሌላው ጎን ርዝመቱ 500 ዘንግ ሆነ።
በስተ ሰሜን በኩል ያለውን ለካፀ በመለኪያ ዘንጉም ርዝመቱ 500 ዘንግ ሆነ።
በስተ ደቡብ በኩል ያለውን ለካፀ በመለኪያ ዘንጉም ርዝመቱ 500 ዘንግ ሆነ።
ኚዚያም ወደ ምዕራብ ዞሚ። በመለኪያ ዘንጉ ሲለካ ርዝመቱ 500 ዘንግ ሆነ።
ስፍራውን በአራቱም ጎን ለካ። ቅዱስ ዹሆነውንና ቅዱስ ያልሆነውን ስፍራ ለመለዚት ዚሚያገለግል ርዝመቱ 500 ዘንግ፣ ወርዱም 500 ዘንግ ዹሆነ ቅጥር በዙሪያው ነበር።
ኚዚያም ወደ ውጹኛው መቅደስ አስገባኝፀ በጎንና በጎን ያሉትንም ዓምዶቜ ለካፀ ዚዓምዶቹ ወርድ በአንደኛው ጎን ስድስት ክንድ፣ በሌላኛውም ጎን ስድስት ክንድ ሆነ።