text
stringlengths
4
267
ውኃዎቹ በሚፈስሱበት ቊታ ሁሉ ስፍር ቁጥር ዹሌላቾው ሕያዋን ፍጥሚታት በሕይወት መኖር ይቜላሉ። ይህ ውኃ ወደዚያ ስለሚፈስ በዚያ እጅግ ብዙ ዓሣዎቜ ይኖራሉ። ዚባሕሩ ውኃ ይፈወሳልፀ ጅሚቱ በሚፈስበት ቊታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል።
“ኚኀንገዲ እስኚ ኀንዔግላይም ድሚስ ዓሣ አጥማጆቜ በዳርቻው ይቆማሉፀ በዚያም መሚባ቞ውን ዚሚያሰጡበት ቊታ ይኖራል። በታላቁ ባሕር እንዳሉት ዓሣዎቜ በዚያም ስፍር ቁጥር ዹሌላቾው ብዙ ዓይነት ዓሣዎቜ ይኖራሉ።
“ሹግሹጋማ ዹሆኑና ውኃ ያቆሩ ቊታዎቜ ይኖሩታልፀ እነዚህ ቊታዎቜ አይፈወሱም። ጹዋማ እንደሆኑ ይቀራሉ።
“በወንዙ ዳርና ዳር ለመብል ዹሚሆኑ ብዙ ዓይነት ዛፎቜ ይበቅላሉ። ቅጠላቾው አይጠወልግምፀ ፍሬ ማፍራትም አያቆሙም። ኚመቅደሱ ዚሚወጣውን ውኃ ስለሚጠጡ በዚወሩ አዲስ ፍሬ ይሰጣሉ። ፍሬያ቞ው ለመብል፣ ቅጠላቾውም ለመድኃኒት ይሆናል።”
ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ለ12ቱ ዚእስራኀል ነገዶቜ ርስት አድርጋቜሁ ዚምታኚፋፍሏት ክልል ይህቜ ናትፀ ዮሎፍ ሁለት ድርሻ ይኖሚዋል።
እናንተ ትወርሷታላቜሁፀ እኩል ድርሻም ታገኛላቜሁ። ለአባቶቻቜሁ ይህቜን ምድር እንደምሰጣ቞ው ምዬላ቞ው ነበርፀ አሁንም ይህቜ ምድር ርስት ሆና ተሰጥታቜኋለቜ።
“በስተ ሰሜን በኩል ዚምድሪቱ ወሰን ይህ ነው፩ ኚታላቁ ባሕር ተነስቶ ወደ ሄትሎን በሚወስደው መንገድ በኩል እስኚ ጌዳድ ይደርሳልፀ
ኚዚያም እስኚ ሃማት፣ እስኚ ቀሮታ እንዲሁም በደማስቆ ክልልና በሃማት ክልል መካኚል እስካለው እስኚ ሲብራይም ብሎም በሃውራን ወሰን እስኚሚገኘው እስኚ ሃጞርሃቲኮን ይዘልቃል።
ስለዚህ ወሰኑ ኚባሕሩ በመነሳት በስተ ሰሜን በደማስቆ ድንበርና በሃማት ድንበር በኩል እስኚ ሃጻርኀናን ድሚስ ይዘልቃል። በሰሜን በኩል ወሰኑ ይህ ነው።
“በምሥራቅ በኩል ወሰኑ ኚሃውራን እስኚ ደማስቆ እንዲሁም በዮርዳኖስ አጠገብ ኚጊልያድ እስኚ እስራኀል ምድር ይዘልቃል። ኹወሰኑ አንስቶ እስኚ ምሥራቁ ባሕር ድሚስ ትለካላቜሁ። በምሥራቅ በኩል ወሰኑ ይህ ነው።
“በደቡብ በኩል ያለው ወሰን ኚትዕማር ተነስቶ እስኚ መሪባትቃዎስ ውኃዎቜ፣ ኚዚያም እስኚ ደሹቁ ወንዝና እስኚ ታላቁ ባሕር ይደርሳል። በደቡብ በኩል ወሰኑ ይህ ነው።
“በምዕራብ በኩል ታላቁ ባሕር ዹሚገኝ ሲሆን ይህም ኹወሰኑ አንስቶ ኚሌቊሃማት ትይዩ እስካለው ቊታ ድሚስ ይዘልቃል። በምዕራብ በኩል ወሰኑ ይህ ነው።”
“ይህቜን ምድር ለእናንተ ይኾውም ለ12ቱ ዚእስራኀል ነገዶቜ ታኚፋፍላላቜሁ።
ምድሪቱን ለእናንተ እንዲሁም በመካኚላቜሁ በመኖር ልጆቜ ለወለዱት፣ አብሚዋቜሁ ለሚኖሩት ዚባዕድ አገር ሰዎቜ ርስት አድርጋቜሁ አኚፋፍሉፀ እነሱም ዚአገሪቱ ተወላጆቜ እንደሆኑት እስራኀላውያን ይሆናሉ። እንደ እስራኀል ነገዶቜ ኚእናንተ ጋር ርስት ያገኛሉ።
ኚባዕድ አገር ለመጣው ሰው በሚኖርበት ነገድ ክልል ውስጥ ርስት ልትሰጡት ይገባል” ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።
ዹይሖዋ ቃል ዳግመኛ እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣፊ
“አንተም ዹሰው ልጅ ሆይ፣ በጢሮስ ላይ ሙሟ አውርድፀ
ጢሮስንም እንዲህ በላትፊ‘አንቺ በባሕሩ መግቢያዎቜ ላይ ዚምትኖሪናበብዙ ደሎቶቜ ላይ ኚሚኖሩ ሕዝቊቜ ጋር ዚንግድ ልውውጥ ዚምታደርጊ፣ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ጢሮስ ሆይ፣ አንቺ ራስሜ ‘ፍጹም ውብ ነኝ’ ብለሻል።
ግዛትሜ በባሕሩ መካኚል ነውፀዚገነቡሜ ሰዎቜም ውበትሜን ፍጹም አድርገውታል።
ሳንቃዎቜሜን ሁሉ ኹሰኒር በመጣ ዚጥድ እንጚት ሠሩፀለአንቺም ዚመርኚብ ምሰሶ ለመሥራት ኚሊባኖስ፣ አርዘ ሊባኖስ አመጡ።
በባሳን ዚባሉጥ ዛፎቜ መቅዘፊያዎቜሜን ሠሩፀዚፊተኛውን ክፍልሜንም ኚኪቲም ደሎቶቜ በመጣ በዝሆን ጥርስ በተለበጠ ዚጥድ እንጚት ሠሩ።
ኚግብፅ ዚመጣው ዚተለያዚ ቀለም ያለው በፍታ ዚመርኚብ ሞራሜን ለመሥራት አገልግሏልፀዚላይኛው መድሚክ መሞፈኛዎቜሜም ኚኀሊሻ ደሎቶቜ በመጣ ሰማያዊ ክርና ሐምራዊ ሱፍ ዚተሠሩ ና቞ው።
ቀዛፊዎቜሜ ዚሲዶና እና ዚአርዋድ ነዋሪዎቜ ነበሩ። ጢሮስ ሆይ፣ ዹገዛ ራስሜ ባለሙያዎቜ መርኚበኞቜሜ ነበሩ።
ልምድ ያካበቱት ዚጌባል ባለሙያዎቜ ስንጥቆቜሜን ይደፍናሉ። በባሕር ላይ ዹሚጓዙ መርኚቊቜና ባሕሚኞቻ቞ው ሁሉ ሞቀጣ ሞቀጊቜን ለመገበያዚት ወደ አንቺ ይመጡ ነበር።
ዚፋርስ፣ ዚሉድና ዚፑጥ ሰዎቜ ተዋጊዎቜ ሆነው በጩር ሠራዊትሜ ውስጥ ያገለግሉ ነበር። ጋሻ቞ውንና ዚራስ ቁራ቞ውን በአንቺ ውስጥ ሰቀሉፀ ደግሞም ግርማ ሞገስ አጎናጞፉሜ።
በሠራዊትሜ ውስጥ ያሉት ዚአርዋድ ሰዎቜ በቅጥሮቜሜ ላይ ዙሪያውን ቆመው ነበርፀጀግኖቜም በማማዎቜሜ ላይ ነበሩ። ክብ ዹሆኑ ጋሻዎቻ቞ውን በቅጥሮቜሜ ዙሪያ ሰቀሉፀውበትሜንም ፍጹም አደሚጉ።
“‘“ኚተትሚፈሚፈው ውድ ሀብትሜ ዚተነሳ ተርሎስ ኚአንቺ ጋር ዚንግድ ልውውጥ ታደርግ ነበር። ሞቀጣ ሞቀጊቜሜን በብር፣ በብሚት፣ በቆርቆሮና በእርሳስ ይለውጡ ነበር።
ያዋን፣ ቱባልና መሌቅ ኚአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበርፀ ሞቀጊቜሜን በባሪያዎቜና በመዳብ ዕቃዎቜ ይለውጡ ነበር።
ዚቶጋርማ ሰዎቜ ደግሞ ሞቀጊቜሜን በጭነት ፈሚሶቜ፣ በጩር ፈሚሶቜና በበቅሎዎቜ ይለውጡ ነበር።
ዚዎዳን ሰዎቜ ኚአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበርፀ በብዙ ደሎቶቜ ላይ ነጋዎዎቜ ቀጠርሜፀ ዹዝሆን ጥርስና ዞጲ በግብር መልክ ያመጡልሜ ነበር።
ኚምታመርቻ቞ው ዕቃዎቜ ብዛት ዚተነሳ ኀዶም ኚአንቺ ጋር ትነግድ ነበር። ሞቀጊቜሜን በበሉር፣ በሐምራዊ ሱፍ፣ ዚተለያዩ ቀለማት ባላ቞ው ጥልፎቜ፣ ጥራት ባለው ልብስ፣ በዛጎልና በሩቢ ይለውጡ ነበር።
“‘“ይሁዳና ዚእስራኀል ምድር ኚአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበርፀ ሞቀጊቜሜን በሚኒት ስንዎ፣ ምርጥ በሆኑ ምግቊቜ፣ በማር፣ በዘይትና በበለሳን ይለውጡ ነበር።
“‘“ደማስቆ ኚተትሚፈሚፈው ምርትሜና ኚሀብትሜ ዚተነሳ ኚአንቺ ጋር ትነግድ ነበርፀ ዹሄልቩን ዹወይን ጠጅና ዹዛሃር ሱፍ ጹርቅ ትሞጥልሜ ነበር።
በዑዛል አቅራቢያ ዚሚገኙት ዌዳንና ያዋን ሞቀጊቜሜን በሚተጣጠፍ ብሚት፣ በብርጉድና በጠጅ ሣር ይለውጡ ነበር።
ዎዳን፣ በኚብት ላይ ለመቀመጥ ዚሚያገለግል ግላስ በማቅሚብ ኚአንቺ ጋር ዚንግድ ልውውጥ ታደርግ ነበር።
ዚጠቊቶቜ፣ ዚአውራ በጎቜና ዚፍዚሎቜ ነጋዮ ዹሆኑ ዓሚቊቜንና ዚቄዳር አለቆቜን ሁሉ ቀጠርሜ።
ዚሳባና ዚራአማ ነጋዎዎቜ ኚአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበርፀ ሞቀጊቜሜን በሁሉም ዓይነት ምርጥ ዹሆኑ ሜቶዎቜ፣ ዚኚበሩ ድንጋዮቜና በወርቅ ይለውጡ ነበር።
ካራን፣ ካኔህና ኀደን እንዲሁም ዚሳባ፣ ዚአሹርና ዚኪልማድ ነጋዎዎቜ ኚአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበር።
በገበያ ቊታሜ ያማሩ ልብሶቜን፣ በሰማያዊ ጹርቅና ዚተለያዩ ቀለማት ባለው ጥልፍ ዚተሠራን ካባ እንዲሁም ብዙ ዓይነት ቀለም ያላ቞ውን ምንጣፎቜ ይነግዱ ዹነበሹ ሲሆን ሁሉም በገመድ በጥብቅ ዚታሰሩ ነበሩ።
ዚተርሎስ መርኚቊቜ ሞቀጊቜሜን ያጓጉዙልሜ ነበርፀበመሆኑም በባሕሩ መካኚል በሀብት ተሞልተሜና ጭነት በዝቶልሜ ነበር።
ቀዛፊዎቜሜ ወደ ታላቅ ባሕር አምጥተውሻልፀዚምሥራቁ ነፋስ በተንጣለለው ባሕር መካኚል ሰባብሮሻል።
ውድቀት በሚደርስብሜ ቀን ሀብትሜ፣ ሞቀጊቜሜ፣ ዚምትነግጃ቞ው ዕቃዎቜ፣ ባሕሚኞቜሜ፣ መርኚበኞቜሜ፣ስንጥቆቜሜን ዚሚደፍኑልሜ ሰዎቜ፣ ነጋዎዎቜሜና ተዋጊዎቜሜ ሁሉይኾውም በአንቺ ውስጥ ያለው ሕዝብ ሁሉበተንጣለለው ባሕር መካኚል ይሰምጣል።
መርኚበኞቜሜ ሲጮኹ ዚባሕሩ ጠሹፍ ይናወጣል።
ቀዛፊዎቹ፣ ባሕሚኞቹና መርኚበኞቹ ሁሉኚመርኚቊቻ቞ው ይወርዳሉፀ መሬት ላይም ይቆማሉ።
በአንቺ ዚተነሳ በራሳ቞ው ላይ አቧራ እዚነሰነሱና በአመድ ላይ እዚተንኚባለሉድምፃ቞ውን ኹፍ አድርገው ይጮኻሉፀ ምርር ብለውም ያለቅሳሉ።
በአንቺ ዚተነሳ ራሳ቞ውን ይላጫሉ፣ ማቅ ይለብሳሉእንዲሁም ዋይ ዋይ እያሉ አምርሹው ያለቅሳሉ።
ለአንቺም በሚያለቅሱበት ጊዜ ሙሟ ያወርዳሉፀ ዹሐዘን እንጉርጉሮም ያንጎራጉራሉፊ ‘በባሕር መካኚል ጞጥ እንዳለቜው እንደ ጢሮስ ያለ ማን ነው?
ሞቀጥሜ ኚተንጣለለው ባሕር በመጣ ጊዜ ብዙ ሕዝቊቜን አጥግበሻል። ዚተትሚፈሚፈው ሀብትሜና ሞቀጣ ሞቀጥሜ ዚምድርን ነገሥታት አበልጜጓል።
አሁን ግን በተንጣለለው ባሕር ላይ ተሰባብሚሜ ጥልቁ ውኃ ውስጥ ሰምጠሻልፀሞቀጥሜና ሕዝብሜ ሁሉ አብሚውሜ ሰምጠዋል።
ዚደሎቶቹም ነዋሪዎቜ ሁሉ በመገሹም አተኩሚው ይመለኚቱሻልፀነገሥታታ቞ውም በታላቅ ፍርሃት ይርዳሉፀ ፊታ቞ውም ይለዋወጣል።
በብሔራት መካኚል ያሉ ነጋዎዎቜ በአንቺ ላይ ኹደሹሰው ነገር ዚተነሳ ያፏጫሉ። ፍጻሜሜ ድንገተኛና አስኚፊ ይሆናልፀደግሞም ለዘላለም ኹሕልውና ውጭ ትሆኛለሜ።’”’”
ኚዚያም “ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ተነስተህ በእግርህ ቁምፀ እኔም አናግርሃለሁ” አለኝ።
እሱም ባናገሚኝ ጊዜ መንፈስ ወደ ውስጀ ገባፀ ዚሚያነጋግሚኝንም እሰማ ዘንድ በእግሬ አቆመኝ።
ኚዚያም እንዲህ አለኝ፩ “ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ወደ እስራኀል ሕዝብ፣ በእኔ ላይ ወዳመፁት ወደ ዓመፀኞቹ ብሔራት እልክሃለሁ። እነሱም ሆኑ አባቶቻ቞ው እስኚዚህቜ ቀን ድሚስ ሕጌን ተላልፈዋል።
ግትርና ልበ ደንዳና ወደሆኑ ልጆቜ እልክሃለሁፀ አንተም ‘ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል’ በላ቞ው።
እነሱ ዓመፀኛ ቀት ስለሆኑ ቢሰሙም ባይሰሙም በመካኚላ቞ው ነቢይ እንደነበሚ በእርግጥ ያውቃሉ።
“አንተ ግን ዹሰው ልጅ ሆይ፣ በአሜኬላና በእሟህ ዚተኚበብክ እንዲሁም በጊንጊቜ መካኚል ዚምትኖር ቢሆንም እነሱንም ሆነ ዚሚናገሩትን ቃል አትፍራ። እነሱ ዓመፀኛ ቀት ስለሆኑ ዚሚናገሩትን አትፍራፀ ኚፊታ቞ውም ዚተነሳ አትሞበር።
እነሱ ዓመፀኛ ስለሆኑ ቢሰሙም ባይሰሙም ቃሌን ንገራ቞ው።
“አንተ ግን ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ዹምነግርህን ስማ። እንደዚህ ዓመፀኛ ቀት፣ ዓመፀኛ አትሁን። አፍህን ክፈትፀ ዚምሰጥህንም ብላ።”
እኔም ባዚሁ ጊዜ ወደ እኔ ዹተዘሹጋ እጅ ተመለኚትኩፀ ደግሞም ዚተጻፈበት ጥቅልል አዚሁ።
እሱም በፊቮ ጥቅልሉን ሲተሚትሚው፣ ኚፊትና ኹኋላ ተጜፎበት ነበር። በላዩ ላይ ዚሙሟ፣ ዹሐዘንና ዚዋይታ ቃላት ተጜፈውበት ነበር።
ኚምሥራቅ ትይዩ ወደሆነው ወደ ውጹኛው ዚመቅደሱ በር ወደሚወስደው መንገድ መልሶ አመጣኝፀ በሩም ዝግ ነበር።
ኚዚያም ይሖዋ እንዲህ አለኝ፩ “ይህ በር እንደተዘጋ ይኖራል። መኚፈት ዚለበትምፀ ደግሞም ማንም ሰው አይገባበትምፀ ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ በዚያ በኩል ገብቷልናፀ ስለዚህ እንደተዘጋ ይኖራል።
አለቃው ግን አለቃ ስለሆነ በይሖዋ ፊት ምግብ ለመብላት በዚያ ይቀመጣል። በበሩ መተላለፊያ በሚንዳ በኩል ይገባልፀ በዚያም ይወጣል።”
ኚዚያም በስተ ሰሜን በሚገኘው በር በኩል ኚቀተ መቅደሱ ፊት ለፊት ወዳለው ቊታ አመጣኝ። እኔም ባዚሁ ጊዜ ዹይሖዋ ክብር፣ ዹይሖዋን ቀተ መቅደስ ሞልቶት ተመለኚትኩ። በዚህ ጊዜ በግንባሬ መሬት ላይ ተደፋሁ።
ይሖዋም እንዲህ አለኝ፩ “ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ስለ ይሖዋ ቀተ መቅደስ ደንቊቜና ሕጎቜ ዹምነግርህን ሁሉ በትኩሚት ተኚታተልፀ በዓይኖቜህም ተመልኚት እንዲሁም በጥሞና አዳምጥ። ዚቀተ መቅደሱን መግቢያና ዚመቅደሱን መውጫዎቜ ሁሉ ልብ በል።
ዓመፀኛ ለሆኑት ዚእስራኀል ቀት ሰዎቜ እንዲህ በላቾው፩ ‘ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ዚእስራኀል ቀት ሰዎቜ ሆይ፣ አስጞያፊ ልማድ መፈጞማቜሁ ኚእንግዲህ ይብቃ!
ልባ቞ውንና ሥጋ቞ውን ያልተገሚዙትን ዚባዕድ አገር ሰዎቜ ወደ መቅደሮ ስታመጧ቞ው ቀተ መቅደሮን ያሚክሳሉ። በምትፈጜሟ቞ው አስጞያፊ ልማዶቜ ሁሉ ዚተነሳ ቃል ኪዳኔ እዚፈሚሰ ሳለ እናንተ ግን ምግቀን ይኾውም ስቡንና ደሙን ታቀርባላቜሁ።
ቅዱስ ኚሆኑት ነገሮቌ ጋር በተያያዘ ያለባቜሁን ኃላፊነት አልተወጣቜሁም። ይልቁንም በመቅደሮ ውስጥ ያሉትን ሥራዎቜ እንዲያኚናውኑ ሌሎቜ ሰዎቜን መደባቜሁ።”’
“‘ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ልቡንና ሥጋውን ያልተገሚዘ በእስራኀል ዹሚኖር ማንኛውም ዚባዕድ አገር ሰው ወደ መቅደሮ አይግባ።”’
“‘ይሁንና እስራኀላውያን አስጞያፊ ዹሆኑ ጣዖቶቻ቞ውን ለመኹተል ሲሉ ኚእኔ በራቁ ጊዜ ኚእኔ ዚራቁት ሌዋውያን በደላቾው ዚሚያስኚትልባ቞ውን መዘዝ ይቀበላሉ።
ኚዚያም በመቅደሮ ዚቀተ መቅደሱን በሮቜ ዚሚቆጣጠሩ እንዲሁም በቀተ መቅደሱ ውስጥ ዚሚያገለግሉ አገልጋዮቜ ይሆናሉ። ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠለውን መባና መሥዋዕት ለሕዝቡ ያርዳሉፀ ደግሞም ሕዝቡን ለማገልገል በፊታ቞ው ይቆማሉ።
አስጞያፊ በሆኑት ጣዖቶቻ቞ው ፊት ስላገለገሏ቞ውና ዚእስራኀል ቀት ሰዎቜ ኃጢአት እንዲሠሩ ዚማሰናኚያ ድንጋይ ስለሆኑባ቞ው በመሐላ እጄን በእነሱ ላይ አንስቻለሁ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋፀ ‘እነሱም ዚሠሩት በደል ዚሚያስኚትልባ቞ውን መዘዝ ይሞኚማሉ።
ካህና቎ ሆነው ለማገልገል ወደ እኔ አይቀርቡምፀ ደግሞም ቅዱስ ወይም እጅግ ቅዱስ ወደሆኑት ነገሮቌ አይቀርቡምፀ በሠሯ቞ውም አስጞያፊ ነገሮቜ ዚተነሳ ዚሚደርስባ቞ውን ኀፍሚት ይሞኚማሉ።
ይሁንና በቀተ መቅደሱ ውስጥ በኃላፊነት እንዲሠሩ ይኾውም በውስጡ ዚሚካሄደውን አገልግሎትና መሠራት ያለበትን ሥራ ሁሉ እንዲያኚናውኑ አደርጋለሁ።’
“‘እስራኀላውያን ኚእኔ በራቁ ጊዜ ዹመቅደሮን አገልግሎት ያኚናውኑ ዚነበሩት ዚሳዶቅ ልጆቜ ዚሆኑት ሌዋውያን ካህናት ያገለግሉኝ ዘንድ ወደ እኔ ይቀርባሉፀ ለእኔም ስቡንና ደሙን ለማቅሚብ በፊቮ ይቆማሉ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።
‘ወደ መቅደሮ ዚሚገቡት እነሱ ና቞ውፀ እኔን ለማገልገልም ወደ ገበታዬ ይቀርባሉፀ በእኔ ፊት ያለባ቞ውንም ኃላፊነት ይወጣሉ።
“‘ወደ ውስጠኛው ግቢ በሚያስገቡት በሮቜ በሚገቡበት ጊዜ በፍታ መልበስ ይኖርባ቞ዋል። በውስጠኛው ግቢ በሮቜ ወይም በውስጥ ባሉት ቊታዎቜ ሲያገለግሉ ዚሱፍ ልብስ መልበስ ዚለባ቞ውም።
በራሳ቞ው ላይ ኚበፍታ ዚተሠራ ጥምጥም ያድርጉፀ በወገባ቞ውም ላይ ዚበፍታ ቁምጣ ይታጠቁ። እንዲያልባ቞ው ዚሚያደርግ ማንኛውም ዓይነት ልብስ መልበስ ዚለባ቞ውም።
ወደ ውጹኛው ግቢ ይኾውም ሕዝቡ ወዳለበት ግቢ ኚመውጣታ቞ው በፊት አገልግሎታ቞ውን ሲያኚናውኑ ለብሰውት ዹነበሹውን ልብስ አውልቀው ቅዱስ በሆኑት ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ውስጥ ማስቀመጥ አለባ቞ው። ኚዚያም ቅድስናን ወደ ሕዝቡ እንዳያስተላልፉ ሌላ ልብስ ይለብሳሉ።
ራሳ቞ውን አይላጩፀ ወይም ፀጉራ቞ውን አያስሚዝሙ። ይልቁንም ፀጉራ቞ውን ይኚርክሙ።
ካህናቱ ወደ ውስጠኛው ግቢ በሚገቡበት ጊዜ ዹወይን ጠጅ አይጠጡ።
መበለት ዚሆነቜ ወይም ኚባሏ ዚተፋታቜ ሎት አያግቡፀ ይሁንና ዚእስራኀል ዘር ዚሆነቜ ድንግል ወይም ዚካህን ሚስት ዚነበሚቜ መበለት ማግባት ይቜላሉ።’
“‘ቅዱስ በሆነና ተራ በሆነ ነገር መካኚል ያለውን ልዩነት ለሕዝቀ ያስተምሩፀ ንጹሕ ባልሆነውና ንጹሕ በሆነው ነገር መካኚል ያለውንም ልዩነት ያሳውቋ቞ው።
ፍርድ ነክ ጉዳዮቜን ይዳኙፀ በድንጋጌዎቌ መሠሚት ይፍሚዱ። ኹሁሉም በዓሎቌ ጋር ዚተያያዙትን ሕጎቌንና ደንቊቌን ይጠብቁፀ እንዲሁም ሰንበቶቌን ይቀድሱ።
ወደ ሞተ ሰው አይቅሚቡፀ አለዚያ ይሚክሳሉ። ሆኖም ለአባታ቞ው፣ ለእናታ቞ው፣ ለወንድ ወይም ለሎት ልጃ቞ው፣ ለወንድማ቞ው ወይም ላላገባቜ እህታ቞ው ሲሉ ራሳ቞ውን ሊያሚክሱ ይቜላሉ።
ደግሞም አንድ ካህን ኚነጻ በኋላ ለሰባት ቀን ሊያቆዩት ይገባል።
በተቀደሰው ስፍራ ለማገልገል፣ በውስጠኛው ግቢ ወደሚገኘው ቅዱስ ስፍራ በሚገባበት ቀን ዚኃጢአት መባውን ያቅርብ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።
“‘ዚእነሱም ውርሻ ይህ ይሆናል፩ ውርሻ቞ው እኔ ነኝ። በእስራኀል ምንም ዓይነት ርስት አትስጧ቞ውፀ ርስታ቞ው እኔ ነኝና።
ዚእህሉን መባ፣ ዚኃጢአቱን መባና ዹበደሉን መባ ይበላሉፀ በእስራኀል ምድር ቅዱስ ለሆነ ነገር ዹተለዹ ሁሉ ዚእነሱ ይሆናል።
መጀመሪያ ላይ ኚደሚሱት ፍሬዎቜ ሁሉና መዋጮ አድርጋቜሁ ኚምትሰጡት ነገር ሁሉ ምርጥ ዹሆነው ለካህናቱ ይሆናል። ዹተፈጹውንም ዚእህል በኩር ለካህኑ ስጡ። እንዲህ ዚምታደርጉ ኹሆነ ቀተሰቊቻቜሁ ይባሚካሉ።
ካህናቱ ሞቶ ዹተገኘውንም ሆነ በአራዊት ዹተዘነጠለውን ማንኛውም ወፍ ወይም እንስሳ መብላት ዚለባ቞ውም።’
እኔም እያዚሁ ሳለ ኚኪሩቊቹ ራስ በላይ ካለው ጠፈር በላይ እንደ ሰንፔር ድንጋይ ያለ ነገር ተገለጠፀ መልኩም ዙፋን ይመስል ነበር።
ኚዚያም አምላክ በፍታ ዹለበሰውን ሰው “በኪሩቊቹ ሥር ወደሚገኙት ዚሚሜኚሚኚሩ መንኮራኩሮቜ መሃል ግባና በኪሩቊቹ መካኚል ካለው ፍም በእጆቜህ ዘግነህ በኹተማዋ ላይ በትነው” አለው። እሱም እኔ እያዚሁት ገባ።
ሰውዹው ወደዚያ ሲገባ ኪሩቊቹ ኚቀተ መቅደሱ በስተ ቀኝ ቆመው ነበርፀ ደመናውም ዚውስጠኛውን ግቢ ሞላው።
ዹይሖዋም ክብር ኚኪሩቊቹ ላይ ተነስቶ ወደ ቀተ መቅደሱ በር ደጃፍ ሄደፀ ቀተ መቅደሱም ቀስ በቀስ በደመናው ተሞላፀ ግቢውም በይሖዋ ክብር ብርሃን ተሞላ።
ዚኪሩቊቹም ክንፎቜ ድምፅ ሁሉን ቻይ ዹሆነው አምላክ ሲናገር እንደሚሰማው ድምፅ እስኚ ውጹኛው ግቢ ድሚስ ይሰማ ነበር።
ኚዚያም አምላክ፣ በፍታ ዹለበሰውን ሰው “ኚሚሜኚሚኚሩት መንኮራኩሮቜ መካኚልና ኚኪሩቊቹ መሃል እሳት ውሰድ” ብሎ አዘዘውፀ ሰውዹውም ገብቶ ኚመንኮራኩሩ አጠገብ ቆመ።
ኚዚያም አንዱ ኪሩብ፣ በኪሩቊቹ መካኚል ወዳለው እሳት እጁን ዘሚጋ። ዹተወሰነ እሳት ወስዶ በፍታ በለበሰው ሰው እጆቜ ላይ አደሚገፀ እሱም እሳቱን ይዞ ወጣ።
ኪሩቊቹ ኚክንፎቻ቞ው ሥር ዹሰው እጅ ዚሚመስል ነገር ነበራ቞ው።