text
stringlengths
707
989
### Text: ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ዛሬ በአዳማ ከተማ የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። በኮንፈረንሱ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳና ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡በተመሳሳይም በደቡብ ምዕራብ ኦሮሚያ ካሉ ዞኖችና ከተሞች የተውጣጡ ነዋሪዎች ተሳታፊ የሆኑበት የሰላም ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በሰላም ኮንፈረንሱ ላይ ከጅማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር ዞን፣ ባሌ ሮቤ እና ከጅማ ከተማ የተውጣጡ ከ1 ሺህ 600 የሚልቁ ነዋሪዎች ከክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመምከር ላይ ናቸው። በውይይቱ ላይ የኦዲፒ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እንዳሉት በጥፋት ድርጊቶች ውስጥ የተሳተፉ0አካላትን ለህግ በማቅረብ የህግ የበላይነት ይረጋገጣል።ባሌ ሮቤ ላይ በተደረገው ውይይት የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው ሰሞኑን የተፈጸመው ድርጊት ህብረተሰቡን እንደማይወክል ተናግረዋል። አያይዘውም እንደዚህ አይነት ዋጋ መክፈል እንደማያስፈልግ ጠቅሰው ችግሮች ሲከሰቱ መመካከርና መደማመጥ አስፈላጊ ነው ብለዋል። ውይይቱ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የታየውን የሰላም እጦት ችግር ከመሰረቱ ይፈታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ### Response:
### Text: አቶ አብዲ መሃመድ ኡመርን ጨምሮ በ47 ተከሳሾች ላይ የዓቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ትዕዛዝ ተሰጠፍርድ ቤቱ የሶማሌ ክልል የቀድሞ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሃመድ ኡመርን ጨምሮ በ47 ተከሳሾች ላይ የዓቃቤ ህግን ምስክሮችን ለመስማት ትዕዛዝ ሰጠ።የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት የሶማሌ ክልል የቀድሞ ርዕሰ መስተዳድር አብዲ መሃመድ ኡመርን ጨምሮ የ47 ተከሳሾች ጉዳይ ተመልክቷል። በዚህም ፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የአቃቤ ህግን የመጀመሪያ ዙር የምስክር ቃል ለመስማት ከጥር 14 እስከ 22 ቀን 2012ዓም ቀጠሮ ሰጥቷል።በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ከዚህ በፊት በዋለው ችሎት እስከ አሁን ያልተያዙ 10 ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲሁም 3 ተከሳሾች በፖሊስ ተይዘው ባዛሬው ችሎት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር።ይሁን እንጂ በጋዜጣ ጥሪ የተደረገላቸው 10ሩም ሆኑ ሶስቱ ተከሳሾች በዛሬው ችሎት አለመቅረባቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ከተባሉት 3 ተከሳሾች ውስጥ ሁለቱ ከሀገር ውጭ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን አንደኛው ተከሳሽ ግን በቁጥጥር ስር ውሎ ለፌዴራል ፖሊስ መሰጠቱ ተገልጿል። ፍርድ ቤቱ ከሀገር ውጭ ናቸው የተባሉት ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲቀርቡና ለፌዴራል ፖሊስ ተላልፎ የተሰጠው ተከሳሽም በቀጣይ ችሎት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ### Response:
### Text: ቅዱስ ሲኖዶሱ በዛሬው አስቸኳይ ጉባኤው በሶስት ጉዳዮች ላይ ይወያያል ተብላል በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በሦሰት ዐበይት ጉዳዮች ጥልቀት ያለው ውይይት አድርጎ የመፍትሄ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ለዋዜማ ሬዲዮ ገልጸዋል፡፡በመጀመሪያ የሚያየው አጀንዳ ሕዝቡንና ቤተ ክርስቲያናን የመጠበቅ ሓላፊነት ስላለበት ቅዱስ ሲኖዶስ የኦሮሚያ ቤተ ክህነትን ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይመለከተዋል ብለዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እንዳሉት መግለጫውን የሰጡት አካላት ጉዳዩ የማይመለከታቸው ናቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም አይወክልም፡፡ ምክንያቱም መግለጫ ሰጭዎች የራሳቸውን አሳብ ይዘው ነው የተነሡት፡፡ አሳቡ በራሱ የቤተ ክርስቲያኗን መዋቅር የሚጻረር ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ቤተ ክርስቲያን እስከወዲያኛው እንደማትደግፋቸው አበክረው ተናግረዋል፡፡ሁለተኛው አጀንዳ ቤተ ክርስቲያኗ በቀጣይ ከመንግሥት ጋር እንዴት መቀጠል እንዳለባት ቅዱስ ሲኖዶስ ይወያያል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የቤተ ክርስቲያን ጥያቄዎች መንግሥት በቀጣይ በምን አግባብ መመለስ እንዳለበት እንዲሁም በቤተ ክርስቲያን በኩል ደግሞ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ካሉ ቅዱስ ሲኖዶስ እንደሚወያይባቸው ተገልጿል፡፡ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ አያይዘውም መንግሥት በልዩ ልዩ ችግሮች የተወጠረ እንደሆነ ቤተ ክርስቲያን ትረዳለች ብለዋል፡፡ተጨማሪ የንብቡ 0905 ### Response:
### Text: ከትላንት የቀጠለ ወይዘሪት ብርትኳንሚደቅሳ የምርጫ ኦፕሬሽንን አስመልክተው ትላንት በሰጡት ማብራሪያ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና እገዛ ላይ ከፍተኛ ተግባራት አየተከናወነ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ ሁሉም ፓርቲዎች በእኩል የመወዳደሪያ መድረክ ላይ እንዲገኙ ለማስቻል ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ቢሆንም እስካሁን ፓርቲዎች ሟሟላት የሚገባቸውን ነገር ቶሎ ባለመሟላታቸው ፍጥነታችንን ቀንሶታል ብለዋል፡፡ እንደ ሰብሳቢዋ ገለጻ የምርጫ ኦፕሬሽን ዋናው ተግባር የመራጮች ምዝገባ ሲሆን ይህም የምርጫ ታአማኒነት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡የምርጫ ክልል አደረጃጀትና የምርጫ ጣቢያ ልየታ ከሞላ ጎደል የተጠናቀቀ ሲሆን ለዚህ የሚመጥን የሰው ኃይል ሟሟላት በጣም ከባዱ ሥራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በዘንድሮ ምርጫ ብቻ 250 000 ምርጫ አስፈጻሚዎች የሚያስፈልጉ ሲሆን ለእነዚህ ሥራ አስፈጻሚዎች በሙሉ ሥልጠና የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የምርጫ ቆጠራን በተመለከተ ልዩ ልዩ ጥናቶች የተጠንቶ በዘንድሮው አመት በምርጫ ምዝገባውም ሆነ ቆጠራው ላይ የቴክኖሎጂ ማሻሻያ እንደማይደረግ ነገር ግን የውጤት አገላለፅ ፍጥነትን ለመጨመር ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም እንደታሰበ ጠቁመዋል፡፡ ይህም ቴክኖሎጂው በራሱ 80 ሚሊየን ዶላር የሚጠይቅ በመሆኑና አዲስ ቴክኖሎጂን ስንጠቀም ከሚያስፈልጉት የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት አንጻር እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ ### Response:
### Text: በእንሳሮ ወረዳ በ22 ቢሊዮን ዶላር ኢንዱስትሪ ሊገነባ ነው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እሳሮ ወረዳ ዲረሙ ቀበሌ ሰሊላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በ22 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የብሄራዊ ሲሚንቶ አክሲዎን ማህበር ለሚ የግንባታ ቁሳቁስ ኢንዱስትሪ ሊገነባ መሆኑ ተሰማ።ዛሬ ለዚህ ግዙፍ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ይጣላል ተብሎ እየተጠበቀ ነው።አጭር መረጃ ስለ እንሳሮ እንሳሮ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ ካሉት 23 ወረዳዎች እና 4 ከተማ አስተዳደሮች መካከል አንደኛ ዋ ወረዳ ስትሆን ለሚ የወረዳዋ ዋና ከተማ ናት፡፡ ከአዲስ አበባ 130 ከሜ፣ ከባህር ዳር 513 ኪሜ ከደብረ ብርሃን ደግሞ 83 ኪሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች። እንሳሮን ከምስራቅ የሲያደብርና ዋዩ ወረዳ፣ ከሰሜን የሞረትና ጅሩ እንዲሁም የመርሃቤቴ ወረዳ፣ ከምዕራብ ኦሮሚያ ክልል ግራር ጃርሶ ወረዳ፣ ከደቡብ ኦሮሚያ ክልል ውጫሌ ወረዳ ያዋስናታል፡፡ ወረዳዋ በ13 የገጠር ቀበሌዎችና በ1 የከተማ ቀበሌ አስተዳደር የተከፋፈለች ናት፡፡ ከ75 ሺህ በላይ ህዝብ የሚኖርባት እንሳሮ 41 ሺህ 27 ሄክታር ያህል የቆዳ ስፍት አላት፡፡ አየር ንብረቷ 46 በመቶ ቆላ፣ 33 በመቶ ወይና ደጋ እንዲሁም 21 በመቶ ደጋ የሚሸፍን ሲሆን ለኑሮ እጅግ ተስማሚ የሆነ አየር ያላት ናት፡፡ የህዝቦቿ ዋነኛ መተዳደሪያ ግብርና ነው፡ ከአጠቃላይ የቆዳ ስፋቷ 21465 ሄክታር መሬት ያህሉ ለእርሻ የዋለ ነው፡፡ምንጭ እንሳሮ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ### Response:
### Text: ካቡል በካቡል ኤርፖርት መግቢያዎች ድጋሚ ጥቃት ሊፈፀም እንደሚችል አሜሪካ አስጠንቅቃለች።አሜሪካ ዛሬ ባወጣቸው የደህንነት ማስጠንቀቂያ በካቡል ኤርፖርት አቅራቢያ ጥቃት ሊደርስ እንደሚችል የሚጠቁም የተለየ እና ተዓማኒነት ያለው ስጋት አለኝ ብላለች። 31 አሜሪካ ኃይሎቿን ሙሉ በሙሉ አስወጥታ የምታጠናቅቅበት የመጨረሻው ቀን ነው።በካቡል የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የመግቢያ በሮቹን ጨምሮ በካቡል አየር ማረፊያ የተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ጥቃት እንደሚደርስ አስጠንቅቋል። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለሪፖርተሮች በሰጡት ቃል ደግሞ አዛዦቻቸው ሌላኛው ጥቃት ምናልባትም በቀጣይ 2436 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈፀም ነግረዋቸዋል። ባለፈው ሀሙስ ካቡል ኤርፖርት አቅራቢያ በ የቦንብ ጥቃት 13 የአሜሪካ ወታደሮችን ጨምሮ በርካታ የአፍጋኒስታን ሲቪል ዜጎች መገደላቸው ይታወሳል።ከጥቃቱ በኃላ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ምህረት አይኖረንም አንረሳውምም የገባችሁበት ገብተን እናድናችኋለን ዋጋ እንድትከፍሉም እናደርጋለን ሲሉ ዝተው ነበር።ከፕሬዜዳንቱ መግለጫ በኃላ የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል በካቡል አውሮፕላን ማረፊያ ከደረሰውን ፍንዳታ ጀርባ ባለው ቡድን ውስጥ ዕቅድ የሚያወጣ ነው የተባለ ግለሰብ በሰው አልባ አውሮፕላን ድሮን አማካይነት እንደገደለ ማስታወቁ አይዘነጋም።ፎቶ ባለፈው ሀሙስ በተፈፀመው ጥቃት የተገደሉት የአሜሪካ ወታደሮች ### Response:
### Text: የደቡብ ክልል የ2012 በጀት አለመጽደቅ ውዝግብ አስነሳ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ላለፉት ስምንት ወራት መሰብሰብ ባለመቻሉ የክልሉን በጀት ያላፀደቀ ሲሆን የ2011 በጀት ላይ በመመስረት የአንድ ወር በጀት ብቻ ታስቦ መለቀቁ የዋጋ ግሽበትን ያላማከለ እና የዞን አመራሮችን ጫና ውስጥ የከከተ ነው ተባለ።የተለቀቀው አንድ አስራ ሁለተኛ በጀት ያለፈው አመት ቀመር ላይ በመመስረቱ መደበኛ ስራዎችን ለማከናወንም ሆነ ለአስቸኳይ ወጪዎች በቂ አይሆንም፡፡ በተጨማሪም ገንዘቡ የግብር ከፋዩ ገንዘብ እንደመሆኑ ይህንን መከልከል አግባብነት የለውም ሲሉ የወላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ ወብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ተከተል ላቤና ገለፀዋል።የክልሉ ፕሬስ ሴክሪታሪያት ኀላፊ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው የመንግስት ሰራተኞችን ደመወዝ ለመክፈል፣ መደበኛ ስራዎችን ለማስኬድ እንዲሁም አስቸኳይ ስራዎችን ለማከናወን ጊዜያዊ በጀቱ በቂ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አክለውም ክልሉ የገቢ ግብር ማሰባሰብ ስራውን በማካሄድ ላይ መሆኑን ገልጸው የገንዘብ እጥረት አይኖርም ብለዋል፡፡ምክር ቤቱ በየትኛውም አይነት ሁኔታ ተሰብስቦ መደበኛ ስራውን መስራት በአዋጅ የተሰጠው ተግባሩ ነው ያሉት የወብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ይህንን ስራውን በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ ማከናወን አለመቻሉም አግባብ አይደለም ሲሉ ይተቻሉ፡፡ አዲስማለዳ ተጨማሪ ያንብቡ 08192 ### Response:
### Text: ትናንት ሌሊት በደንቢዶሎ ዩኒቨርስቲ አንድ ተማሪ መገደሉን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል። በሌሎች ከፍተኛ ተቋማትም ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች ይታያሉ። ተማሪዎችም ከግቢ መውጣታቸው እና በየቤተክርስትያናት ተጠልለው እንደሚገኙ ተሰምቷል። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጉሩሙ ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ እንደተናገሩት ተማሪዎችን የማረጋጋት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከአብመድበደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተማሪዎች በስጋት ውስጥ መሆናቸውኖ ተናገሩ። በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ትናንት ሕዳር 1 ቀን 2012 ዓም በግምት ምሽት 2፡00 አካባቢ በተፈጠረ ግጭት የአንድ ተማሪ ሕይወት እንዳለፈ ተማሪዎች ተናግረዋል በግጭቱ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ተማሪዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰም ተሰምቷል፡፡ ለአብመድ አስተያዬታቸውን የሰጡ ተማሪዎች እንደገለፁት ሦስት ተማሪዎች ተጠልፈው ተወስደው የደረሱበት አልታወቀም፡፡ ሕይወቱ ያለፈው ተማሪ ምንም ዓይነት የሕክምና እርዳታ ሳያገኝ በግቢው ውስጥ ሕይወቱ ማለፉንም ተናግረዋል፡፡ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎችም በተማሪዎች ክሊኒክ ውስጥ ሕክምና ቢያገኙም ለተሻለ ሕክምና ወደ ሆስፒታል አልተወሰዱም ብለዋል፡፡ አሁንም አፋጣኝ የሕክምና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች መኖራቸውን ነው አስተያዬት የሰጡን ተማሪዎች ያመለከቱት፡፡ 1113 ### Response:
### Text: ኢንጂነር ስመኘው️ኢንጂነር ስመኘው በቀለ በሰው በደረሰባቸው ጉዳት ህይወታቸው እንዳላለፈና ራሳቸውን እንዳጠፉ የምርመራ ውጤቱ እንደሚያመላክት ፖሊስ ገለፀ።ፖሊስ የኢንጂነር ስመኘውን አሟሟት በተመለከተ በሰጠው መግለጫ ኢንጅነር ስመኘው ራሳቸውን ማጥፋታቸውን የተደረገው የምርመራ ውጤት ያመላክታል ብሏል።ፖሊስ በመግለጫው ሞተው የተገኙበት መኪና ውስጥ የተገኘው ሽጉጥም በእርሳቸው ስም ተመዝግቦ የሚገኝ መሆኑን ገልጿል።በፎረንሲክ ምርመራ በተገኘው ውጤት መሰረትም የሽጉጡ ቀልሃና የተገኘው እርሳስም የዚሁ ሽጉጥ መሆኑን ፖሊስ እንዳረጋገጠ አስታውቋል።ኢንጅነር ስመኘው ከመሞታቸው ቀደም ብሎ ባለው ቀን ከትልቁ ልጃቸው ጋር የስንብት የሚመስል መልዕክት መለዋወጣቸውንም ነው ፖሊስ በመግለጫው ያነሳው።ኢንጅነሩ ባደረጉት የስልክ ልውውጥም በአብዛኛው የስንብት ይዘት ያለው መልዕክትን ከልጃቸውና ፀሃፊያቸው ጋር ተለዋውጠዋልም ነው ፖሊስ።ከዚህ ጋር ተያይዞም ለፀሃፊያቸው ልጀን አደራ የሚል መልክዕክት ማስተላለፋቸውን የፌደራል ፖሊስ ጀኔራል ኮሚሽነር ዘይኑጀማል ተናግረዋል።በሞቱበት ዕለት ማለዳ ላይም ለአንደኛው ሾፌራቸው ፖስታ በመስጠት ለማን እንደሚያደርስላቸው እነግርሃለው ማለታቸውን እና ለሌላኛው ሾፌር ደግሞ ፖስታ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እንዲያደርስላቸው መስጠታቸውም በመግለጫው ተነስቷል።© ### Response:
### Text: ሰበር መረጃአዲስ አበባ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ነገ፣ መስከረም 92018 ዓም ዝግ እንደሚሆን አስታውቋል።ኤምባሲው ለነገ አገልግሎቱን የሚያቋርጠው በከተማዪቱ ውስጥ በሚካሄደው ግዙፍ ሊሆን ይችላል ባለው ሰልፍ ምክንያት የተጠናከረ ጥንቃቄ ለመውሰድ ሲባል መሆኑን ገልጿል።ቀደም ሲል ተይዘው የነበሩ የቪዛ ቀጠሮዎችና ኤምባሲው ለአሜሪካዊያን ዜጎች ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች ለነገ መስከረም 92018 ዓም 19 2018 ተቀጥረው የነበሩ ጉዳዮች በሙሉ የተሠረዙ መሆናቸውን አስታውቋል።አሜሪካዊያን በኤምባሲው ዌብሳይት አማካይነት አዲስ ቀጠሮ እንዲይዙ መክሯል።ከኢሚግራንት ቪዛ ጠያቂዎች ጋር ተለዋጭ ቀጠሮ ለማድረግ ኤምባሲው በቅርቡ የሚያገኛቸው መሆኑንና ነንኢሚግራንት ቪዛ ለማግኘት ያመለከቱ ደግሞ በኤምባሲው ዌብሳይት ላይ አዲስ ቀጠሮ እንዲጠይቁ አሳስቧል።አጣዳፊ አገልግሎት የሚፈልጉ አሜሪካዊያን ዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ዌብሳይት ላይ ያለውን የአድራሻየመገናኛ መረጃ እንዲያዩ መክሯል።ከኤምባሲው መደበኛ አገልግሎቶች በተጨማሪ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የአሜሪካ ማዕከል እና ዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ውስጥ የሚገኘው ሳችሞ ማዕከልም ነገ ዝግ ሆነው እንደሚውሉ አስታውቋል።በሰልፉ ላይ የሚሣተፉ ሁሉ ሃሣቦቻቸውንና ፍላጎቶቻቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለፃቸውን እንደሚያበረታታም ኤምባሲው ገልጿል።© 24የአማርኛው አገልግሎት ### Response:
### Text: ከፍተኛ የስራ ሀላፊ ከሀገር መኮብልለዋል ለ11 ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የመገናኛ ብዙሃን ፈቃድና ምዝገባ ዳይሮክተሬት0 ዳይሬክተር የነበሩት 0አቶ ሙሉጌታ ሲሳይ መንገሻ 0ካናዳ ቶሮንቶ ጥገኝነት መጠየቃቸው ተሰምቷል።በባለስልጣ መስሪያ ቤቱ የመገናኛ ብዙሃን ፈቃድና ምዝገባ ስራ ላይ ለመሰማራት ለሚፈልጉ ወገኖች ፈቃድ የሚሰጠው እሳቸው የሚመሩት ዳይሮክተሬት እንደሆነ የሚናገሩት ዳይሬክተሩ በተለይ የመንግስት ባለስልጣት ተፅእኖ ይደረግ እንደነበር ገልጠው በተለይም ለፖለቲካው ቅርበት ላላቸው ወገኖች ከህጉ ውጭ ፈቃድ እንዲሰጣቸው ግፊት ይደረግ እንደነበር ባለፈው ሳምንት በካናዳ ቶሮንቶ እየተዘጋጀ በ143 ሀገራት በኢንተርኔት በሚደመጠው ከራዲዮ መገናኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልስ ገልፀዋል፡፡ እንደ ዋልታ ያሉ ለመንግስትና ለገዢው ፖርቲ ቅርበት ያላቸው ሚዲያዎች ህጉ ከሚያዘው ውጭ በፍጥነት ፍቃድ እንዲሰጣቸው ግፊት ከመደረጉም በላይ ዋልታ ፈቃድ ሳይሰጠው የቴሌቪዥን ስርጭት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በህግ ከተሰጠው ሃላፊነት አልፎ በህትመት ስራዎች የይዘት ቁጥጥር ውስጥ ይገባ እንደነበር የጠቀሱት አቶ ሙሉጌታ መንግስትን ይተቻሉ ተብለው በተፈረጁ የህትመት ውጠቶች ላይ የህትመት ትንተና እየሰራ ለመንግስት ያቀርብ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 10302 ምንጭ ቁምነገር መፅሄት ### Response:
### Text: በደሴ 10 በሚሆኑ ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ሳጥኖች ተሞልተው ተገኙ ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን ወሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አሳውቀዋል።በ10ሩ የምርጫ ጣቢያዎች የተፈጠረውን ጉዳይም ዛሬ በነበራቸው መግለጫ አስረድተዋል።በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የውጤት አገላለፅ እንዲሁም የውጤት አመዘጋገብ በትክክለኛው መንገድ ስለመፈፁ የሚረጋገጥበት የራሱ ደረጃ አለው ይህም በስልጣና ላይ ተሰጥቷል ብለዋል።ከእንዚህ ደረጃዎችሂደቶች መካከል የመጀመሪያው በዚያ ጣቢያ ስንት ሰው ነው የሚመዘገበው በዕለቱ መጥቶ መዝገብ ላይ ፈርሞ ድምፅ የሰጡ ብዛት ስንት ናቸው ፊርማቸው ተቆጥሮ መመዝገብ አለበት። የመጡት ሰዎች ተመዝግበዋል ከተባሉት ሰዎች ቁጥራቸው መበላለጥ ስለሌለበት ይህም ይረጋገጣል። የደረሰው የድምፅ መስጫ ወረቀት ብዛት ስንት ነው ሳጥን ውስጥ የተገኘው ምን ያህል ነው የተበላሸ የድምፅ መስጫ ወረቀት ስንት ነው የሚሉት ይገኙበታል።ደሴ የተገኙት 10 ምርጫ ጣቢያዎች ትክክለኛነቱን የሚያረጋግጡ አካሄዶችን ሳይፈፅሙ ፣ ሂሳቡንም በትክክል ሳይሰሩ በመላካቸው በምርጫ ክልል ደረጃ እንደገና መታየት ስላለበት ድምፅ ቆጠራው መደገም ስላለበት የምርጫ ክልሉ ለጊዜው ኳራንታይን አድርጎ አስቀምጦታል።ይህ ሁኔታ ነው የማይሆን ትርጉም ተሰጥቶት ሀሰተኛመረጃ እንዲሰራጭ ምክንያት የሆነው ሲሉ ወሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ገልፀዋል። ### Response:
### Text: ️ጥንቃቄ አዘል መረጃ ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ️ከሰሞኑን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ካምፓስ በር አካባቢ የሞተር ላይ ዝርፊያ ተባብሷል።ጆዬ የተባለ ተማሪ የላከልኝን አንብቡትከሁለት ቀን በፊት እኔ እና ጓደኛዬ ወደ ግቢ ልንገባ ወደ በሩ ለመድረስ 100 ሜትር ሲቀረን ከጓደኛዬ እጅ ላይ አዲስ ቅርብ ጊዜ የተገዛ ላፕቶፕ በሞተር ላይ የነበሩ ሰዎች ነጠቁት ወዲያውም ተሰውሩብን ሰውም ሊተባበረን አልቻለም። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክቴን አስተላልፍልኝ። እኛ 4ኛ አመት ሆነን ነው የተዘረፍነው ለአዲስ ተማሪዎች ደግሞ ይከብዳል። አምና በከተማው የሞተር ላይ ስርቆት ከፍተኛ የማህበረሰቡ ችግር የነበር እና ለጥቂት ጊዜም ቢሆን የሚዲያዎች ጩኸት የነበር ጉዳይ ነው። ባለፈው አመት የከተማው ፖሊስ በዚህ ጉዳይ ከፍተኛ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን አውቃለሁ። አሁንም የከተማው ፖሊስ እነዚህ ዘራፊዎች አጣርቶ በመያዝ ህግ ፊት ሊያቀርባቸው ይገባል። እንዲሁም ንብረታቸው ለተዘረፉ ተማሪዎች ንብረታቸውን የሚያገኙበት አግባብ ቢፈጠር መልካም ነው። ይህን መሰሉ መጥፎ ተግባር የከተማውን ስም ከማጥፋት ባሻገር ሰዎች በነፃነት እንዳይንቀሳቀሱ ያደርጋል። ሌላው የተዘረፋችሁ ሰዎች ደግሞ ወዲያው ተስፋ ከመቁረጥ ለፖሊስ ማመልከትም ያስፈልጋል።ይህን መልዕክት የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ለከተማው ፖሊስ መምሪያ አድርሱ። ### Response:
### Text: ከፍተኛጥንቃቄእያደረጋችሁ ጎንደር ኮሚኒኬሽንበጎንደር ከተማ ውስጥ ከ31000 ብር በላይ ሃሰተኛ የብር ኖት በቁጥጥር ስር መዋሉ የ3ኛ ዋና ፖሊስ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።ሃሰተኛ የብር ኖቶች የተያዙት በከተማ አስተዳደሩ በማራኪ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ኮሌጅ ማዞሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ነው።ሃሰተኛ የብር ኖቶች በፀጥታ ሃይል በተደረገ ክትትል ትላንት ጥቅምት 9 ቀን 2013 ከጧቱ 2 ስዓት ላይ መያዙ ተገልጿል።የድርጊቱ አስፈፃሚዎች እንዲሁም ተባባሪዎቻቸው ፖሊስ እየተከታተላቸው መሆኑ በማወቃቸው በመታተም ላይ የነበረ 27 ሺህ ብር አዲሱ ባለ 200 የብር ኖት 4 ሺህ 600 ብር ነባሩ ባለ 100 የብር ኖቶችን በባጃጅ በመጫን ከወሰዱ በኃላ ውሃ ቦይ ላይ ጥለው አምልጠዋል። የድርጊቱ አስፈፃሚዎችና ተባባሪዎቻቸውም በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።ሃሰተኛ የብር ኖቶች የሞባል ካርድ በመግዛት ፣ ምግብ ቤት በመጠቀም እንዲሁም የሱቅ ሸቀጣሸቀጦችን በመግዛት እያዘረዘሩ በመሆኑ ህብረተሰቡ ሃሰተኛ የብር ኖት ሲያጋጥም ተጠያቂ ከመሆን በፊት ለፓሊስ ሊጠቁም እንደሚገባ ፖሊስ አሳስቧል።በህገ ወጥ መንገድ እየተመረተ ያለው ሃሰተኛ የብር ኖቶች ከአዲሱ የብር ኖቶች ጋር ተመሳሳይ በመሆናቸው እና በሁሉም የብር ኖቶች ዓይነቶች ሃሰተኛ የብር ኖቶች እየተሰሩ ወደ ገበያ ውስጥ እየገቡ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይታለል መልዕክት ተላልፏል። ### Response:
### Text: ሀገርን ማክበር የሚለው ሀሳብ የሚጀምረው የሀገርን ህግ ከማክበር ነው ወሮ ሰላማዊት ካሳየአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ያወጣውን ክልከላ የሚተላለፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የኢትዮጵያ መንግስት አሳሰበ።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ከቀናት በፊት ማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን፣ የጦር ሜዳ ውሎዎችን እና ውጤቶችን በተመለከተ፣ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ሥልጣን ከተሰጠው አካል ውጪ፣ በየትኛውም የመገናኛ አውታር መስጠትና ማሰራጨት ክልክል ነው።በየግንባሩ የሚገኙ የሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ከተሰጣቸው ሥምሪትና ተልእኮ ውጭ ማንኛውንም ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን፣ የጦር ሜዳ ውሎዎችን እንዲሁም ውጤቶችን የሚመለከቱ መግለጫዎች መስጠት የተከለከለ ነው። የጸጥታ አካላትም ይሄን ተላልለፈው በሚገኙት ላይ አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስዱ ታዟል። የሚል ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወሳል።በዛሬው ዕለት መግለጫ የሰጡት የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ወሮ ሰላማዊት ካሳ የተላለፈውን ክልከላ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በመተላለፍ ላይ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግስት ያሳስባል ብለዋል።ሚኒስትር ዴኤታዋ ሀገርን ማክበር የሚለው ሀሳብ የሚጀምረው የሀገርን ህግ ከማክበር በመሆኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ያወጣውን ክልከላ የሚተላለፉ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። ### Response:
### Text: አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ግጭትን በመሸሽ ወይም በማምለጥ ከቶውንም ለውጥ አናመጣም። የተሻለ አገርና ቤትም አንገነባም። ብዙ ጊዜ ግጭትና ግፊት የሚመጣው አለቅጥ ምቾት ከመፈለግና በተቃራኒው በጎረቤታችን ያለው ልዩ ምቾት በሚፈጥርብን ቅንዓት ነው። ግጭት ለምን ተነሳ አይባልም ። ጉርብትና በራሱ፣ አብሮ መኖር በራሱ፣ የሚያማዝዘው ቅራኔ አይጠፋምና። ግጭት እንዴት ሊነሳ ቻለ ብሎ መፍትሔውን መፈለግና እንዴትነቱን ማጤን ከአስተዋይ ልብ ይጠበቃል። አሁን ከእኛ የሚፈለገው ይህ ነው። የሰው ልጅ በራሱ ከራሱ ጋርም ይጋጫል። ሰው በህይወቱ የሚያጋጥመውን ነገር፣ በሥርዓት ማየት ሲያቅተው ከራሱ ጋር ይጋጫል። በአንድ ጊዜ ሁለት ሶስት ነገሮች ተደራርበው ሲገጥሙት ወይም አንዱን ችግር ተጋፍጦ ሳያበቃ ሌላኛው ሲጨመርበትና ለውሳኔ ሲቸገር ከመፍትሔው ይልቅ ችግሩ ላይ ሲያፈጥ በግለ ግጭት ውስጥ ገብቶ ይወጠራል። አንደኛው በተፈጠረብን ምቾት ሳቢያ የበለጠና የተሻለ ምቾት ፍለጋ የጎረቤት ድንበር እንገፋለን የጎረቤት ሰው እንጋፋለን ግጭትም ይፈጠራል። በሌላ ወገን ደግሞ፣ ለፍቶ ጥሮ ግሮ ያገኘው ሃብት ዓይኖቻችንን ሲያቀላብን የሌላውን መልካም ቤት ፣ መኪና፣ ሰው እንደፍራለን፣ እናንጓጥጣለን። በሁሉም ረገድ ግን ግጭታችን የፍላጎቶቻችን እስረኞች ከመሆን የሚመነጭ የሰብዕና ግድፈት የሚመነጭ ዋልጌነት ነው። አዲስዘመን ተጨማሪ ያንብቡ 09032 ### Response:
### Text: ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር ተያይዞ አሁንም በቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች በአፋጣኝ ይለቀቁ ኢሰመኮየኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኢሰመኮ የኢፌዲሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ከጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ ተግባራዊ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ ለሕዝብ ተወካዮች ምቤት ያቀረበው የውሳኔ ሃሳብ አበረታች እርምጃ መሆኑን ገልጿል።ኮሚሽኑ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት የነበረው ሁኔታ በመሻሻሉና የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ ከግምት በማስገባት የአዋጁ አስፈላጊነት እየተገመገመ0ተገቢው ማሻሻያ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቦ0የነበረ መሆኑ አስታውሷል።የሕዝብ ተወካዮች ም ቤት በመንግስት የቀረበለትን ውሳኔ ሃሳብ በአፋጣኝ እንደሚያጸድቀው ኢሰመኮ ተስፋውን የገለፀ ሲሆን የመንግስት ስራ አስፈጻሚ አካላት ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር ተያይዞ አሁንም በቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲለቀቁ ጥሪውን አቅርቧል።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታው አዋጅ የተነሳ መሆኑን ከሚያጸድቅበት ቀን ጀምሮ ከእስር ያልተለቀቁ ሰዎች የሚኖሩ ቢሆን ከ48 ሰዓታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ወደ ፍርድ ቤት አለመቅረብ እስሩ ከሕግ ውጭ የሚያደርገው በመሆኑ የሁሉም የሕግ አስከባሪ አካላት የሕግ ማስከበር ተግባራት የሰብአዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በመደበኛው ሥርዓት እንዲከናወኑ አሳስቧል። ### Response:
### Text: የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላማዊመንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ።በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ።ዶር ጌዲዮን ፓርቲው ሰላማዊ ውይይት ለማድረግ ዉሳኔ አሳልፏል ብለዋል። ሚኒስትሩ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተካሄደው ጦርነት መንግሥት ተገዶ የገባበት መሆኑን ገልፀው መንግሥት ይህንን ለመፍታት እየሠራ ስለመሆኑም አስረድተዋል ። ፓርቲዉ ተጨማሪ ደም መፋሰስ እንዳይኖር ታሳቢ በማድረግ ለሰላምቅድሚያይሰጣል ነው ያሉት። ዶክተር ጌዲዮን እንዳሉት ፓርቲዉ ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የሰላም አማራጩ፡ 1 ሕገ መንግሥታዊ እና ሕጋዊነትን የሚያስከብር መሆን አለበት፡፡ 2 የሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ መሆን አለበት፡፡ 3 በሀገር ዉስጥ መፍታት ካልተቻለ በአፍሪካሕብረት ጉዳዩ መታየት እንዳለበት በሥራ አስፈጻሚ እና በማእከላዊ ኮሚቴ ዉይይት ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። በተጨማሪም ትንኮሳዎች ካሉ ሕግ አስከባሪዉ አካል እርምጃ እንዲወሰድ ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። ሕዝቡም ለዚህ ተሳታፊ እንዲሆንም ጥሪ ማስተላለፋቸውን ከአሚኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ### Response:
### Text: በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የደቡብ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ሙዘይ መኮነን እንደተናገሩት በባሌ ሮቤ፣ ዶዶላ፣ አዳማ እና ሌሎችም አካባቢዎች ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎች፣ ከሃይማኖት አባቶችና ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር በቅንጅት እየሠሩ በመሆናቸው አንጻራዊ ሠላም እየታዬ ነው፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች ከጥቅምት 162012 ዓም ጀምሮ አዲስ ግጭት እንዳልተከሰተም ነው ጄኔራል ሙዘይ ያስረዱት፡፡ሠራዊቱ እያደረገ ባለው ጥረትም በዶዶላ ከተማ በሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተጠልለው ያሉትን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የሚገኙ የኅብረሰብ ክፍሎች ሕጋዊ ከለላ እንዲገኙ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ይህንኑ ሐሳብ በችግሩ ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችም ለአብመድ አረጋግጠዋል፡፡ ስጋት ይታይባቸዋል በሚባሉ አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት እንዳይከሰትም የቅድመ መከላከል ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል ጄኔራሉ፡፡የምሥራቅ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዘውዱ በላይ ደግሞ በሀረር፣ ድሬዳዋ እና አሰበ ተፈሪ ከተሞች ኅብረተሰቡን እያረጋጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአካባቢው ሠላማዊ እንቅስቃሴዎች እየታዩ እንደሆነም ነው የተናገሩት፡፡ አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ችግሮችንም ከኅብረተሰቡ ጋር በውይይት ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል ጄኔራል ዘውዱ፡፡ እየታዬ ያለው አንፃራዊ ሠላም እንዲደናቀፍ የሚሠሩ ግለሰቦች እንዳሉ ማረጋገጣቸውንም ለአብመድ ጠቁመዋል፡፡ 10293 አብመድ ### Response:
### Text: ማንኛውም ዜጋ የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ከቀበሌ መታወቂያ በተጨማሪ የልደት ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለበት የልደት ምስክር ወረቀት ከየት ይወጣል ለህፃናት የልደት ምስክር ወረቀት ለማውጣት ከወላጆች አንዱ በነዋሪነት የተመዘገበቡበት ቀበሌ ሁለቱም ወላጆች ህፃኑኗን ይዘው በመቅረብ ማውጣት ይችላሉ፡፡ ከ18 አመት በላይ የሆነ ሰው ለተለያዩ አገልግሎቶች የልደት ምስክር ወረቀት በሚፈልግበት ጊዜ በነዋሪነት ወደተመዘገበበት እና መታወቂያ ወደተሰጠበት ቀበሌ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ፅቤት በመሄድ ተመዝግቦ የልደት ምስክር ወረቀት ማግኘት ይችላል፡፡ የልደት ምስክር ወረቀት መቼ ማውጣት ይቻላል ለለህፃናት ከተወለዱበት ቀን ጀምሮ እስከ 90 ቀናት ድረስ በመደበኛ የምዝገባ ጊዜ ውስጥ ተመዝግበው ቢያወጡ እንደሃገር ለሚሰበሰበው መረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታን ይሰጣል፡፡ አዋቂዎች በማንኛውም ጊዜ በቀበሌ የስራ ቀን እና ሰአት በመሄድ ማውጣት ይቻላል በገጠሪቱ የሃገሪቱ ክፍል የልደት ምስክር ወረቀት እንዴት ይገኛል ከላይ እንደተገለፀው በማንኛውም የሃገሪቱ ክፍል ባሉ ቀበሌዎች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራ በማከናወን ላይ ስለሚገኙ በነዋሪነት ወደተመዘገቡበት ቀበሌ በመሄድ የልደት ምስክር ወረቀት ማግኘት ይቻላል፡፡ ማስታወሻ፡ ማንኛውም ዜጋ ፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ከቀበሌ መታወቂያ በተጨማሪ የልደት ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለበት ### Response:
### Text: በመንግስት ጥሪ እየተደረገ ሰዎች የሚሰበሰቡባቸው ዝግጅቶች መላ ቢፈለግላቸው መልካም ነው እንላለን።ፎቶው ዛሬ ጠዋት ሐና አካባቢ የነበረ የፅዳት ዘመቻ ለማድረግ የተሰባሰቡ ሰዎችን የሚያሳይ ነው። ማስክ ያላደረጉ አንዳንድ ሰዎችም ጭምር ነበሩበት።ከቅርብ ጊዜ ወደህ እያየን ያለነው አንዳንድ እንቅስቃሴ መንግስት ራሱ ለወረርሽኙ እየሰጠ ያለው ትኩረት ከጊዜ ወደጊዜ እየቀነሰ እየመጣ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።ዝግጅቶች መቅረት የለባቸውም ከተባለ በጤና ባለሞያዎች የሚሰጡ ምክሮችን ሳያጓድሉ መፈፀም ይገባል።የጤና ባለሞያዎችን ምክር መፈፀም የማይቻል ከሆነ ግን ይህ ሁኔታ ሀገርን አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ቢቀር የተሻለ ነው።የጤና ሚኒስቴር፣ ጤና ቢሮዎች እንዲሁም የጤና ባለሞያዎች አሁን ላይ በአንዳንድ ቦታዎች እየታየ ያለው ማስክ ማድረግ ብቻ ሙሉ በሙሉ በሽታውን ይከላከላል የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት በተቻለ አቅም በእቸኳይ እንዲታረም ርብርብ ማድረግ ይገባል።ዛሬ ጥዋት በቲክቫህ ኢትዮጵያ የተጋራውን የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ሪፖርት ከነሃሴ 1 እስከ 30 አንብባችሁታል። ከሪፖርቱ ምን ያህል ይህ ወረርሽኝ በአደገኛ ሁኔታ በፍጥነት እየተዛመተ የሰዎችንም ህይወት እየቀጠፈ እንደሆነ ተመልክታችኃል ስለዚህ መዘናጋቱ በቃ ሊባል ይገባዋልነገን በህይወት ለመኖር ዛሬን እንጠንቀቅየቲክቫህ አባላት አዲስ አበባጳጉሜ 32012 ዓም ### Response:
### Text: የአሜሪካ ጦር ከሱማሊያ እንዲወጣ ታዘዘ።የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ሁሉም የአሜሪካ የጦር ኃይል አባላት በ2021 መጀመሪያ ወር ላይ ሶማሊያን ለቅቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጡ።0700 የሚሆኑ የአሜሪካ ሠራዊት አባላት እንዲወጡ የታዘዘው ተመራጭፕሬዚደት ጆ ባይደን ቃለ መሃላ ከመፈጸማቸው አምስት ቀናት ቀደም ብሎ ጃኑዋሪ 15 ነው።ይህ በሶማሊያ ይሰጥ የነበረውን ስልጠናና ይካሄድ የነበረውን ፀረሽብር ተልዕኮ ፋይዳ አስመልክቶ ባልበረደው ክርክር ላይ ግለትን ጨምሯል።በሶማሊያ የአሜሪካ ጦር ተልዕኮ ደጋፊዎችና የተወሰኑ ብርቱ የትራምፕ ደጋፊዎች ዘንድ የሠራዊቱ መኖር አል ሻባብ በሪጂኑ ኃይሉን አጠናክሮ እንዳይስፋፋ የገታ መሆኑንና የጦሩ ሶማሊያን ለቅቆ መውጣትም ለሶማሊያ የጸጥታ ኃይላት የሚሰጡትን ስልጠናዎች የሚያቋርጥ መሆኑ ጉዳት እንዳለው በማንሳት ድምጻቸውን አሰምተዋል።ሆኖም የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ባለስልጣናት ዓርብ ዕለት እንዳስታወቁት ገሚሱ ጦር ወደ ጎረቤት አገር ኬንያ በመዛወር እዚያ ሆኖ የድሮን አየር ጥቃት ሊፈጽም እንደሚችል ጠቅሰዋል።የአሜሪካ ጦር ሶማሊያን ለቅቆ የሚወጣው አገሪቱ የፓርላማ ምርጫ ለማድረግ ስድስት ወራት እና ፕሬዚደንታዊ ምርጫም ፌብሪዋሪ 2021 ለማከናወን በዝግጅት ላይ ባለችበትና የኢትዮጵያ ጦርም በአገር ውስጥ ወታደራዊ ግዳጆች ተጠምዶ ባለበት ወቅት መሆኑን ኤስ ቢ ኤስ አስነብቧል። ### Response:
### Text: የፊቼ እሴቶች በሀገሪቱ ያሉ መቃቃሮችን በመፍታት የነገይቱን ኢትዮጵያ ብሩህ ለማድረግ ጥቅም ላይ መዋል እንዳሉባቸው ተነገረ።የፊቼ የመጀመሪያው ቀን የሆነው ፊጣሪ በተለያዩ ስርዓቶች ሲከበር ውሏል፡፡ የተለያዩ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችና ግለሰቦችም የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባደረጉት ንግግር እንደጠቀሱት የፊቼ ጨምበላላ እሴት የሆነውን ይቅር መባባልን በመጠቀም በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ ያሉ መቃቃሮችን ይቅር በመባባል የነጋይቱን ህይወታችንና የነገይቱን ኢትዮጵያ ብሩህ ለማድረግ እጅ ለእጅ ተያይዞ ቀን ከሌሊት መስራት ያስፈልጋል፡፡በዓሉ በውስጡ የሰላም፣ የመቻቻልና የአቃፊነት እሴት የያዘ ከመሆኑም ባሻገር ከሰው አልፎ እንስሳትና እፅዋት ጭመር እንክብካቤ የሚደረግበት መሆኑ በዓሉ የሰው ልጅ ስልጣኔ ጫፍ ነው ብለዋል፡፡የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ፕሬዝደንት አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በበኩላቸው ፍቼ የዘመን መለወጫ ብቻም ሳይሆን በውስጡ ሰላምን፣ አብሮነትንና እርቅን ያቀፈ ነው ብለዋል፡፡ይህ ትል ቅርስ ነው፡፡በዓሉ ልዩነቶችን በማክበር እውነተኛ የፌዴራል ስርዓት እንዲጠናከር ግብዓት የሚሆን ነው ብለዋል፡፡ መቻቻልን ሰላምንና ፍቅርን በመስበክ ሀገሪቱ ለያዘቺውየብልፅግና ጉዞ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ብለዋል ፎቶ ### Response:
### Text: በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ጸብ ሕይወት አጠፋበሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ጸብ የአንድ ተማሪ ሕይወት ማለፉን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ። ትናንት ምሽት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በተከሰተው ጸብ የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሕይወት ማለፉን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ገልጸዋል።የተማሪው አስክሬን በአዲስ አበባ ምንሊክ ሆስፒታል ምርመራ ከተደረገለት በኋላ ወደ ትውልድ ስፍራው ወልዲያ መላኩንም የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ተናግረዋል። የነገሩ መነሻ የሁለት ተማሪዎች ጸብ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አየለ ከጀርባው ሌላ ተልኮ ይኑረው ወይንም አይኑረው እየተጣራ ይገኛል ብለዋል። አክለውም «በአሁኑ ወቅት ከግድያው ጋር በተያያዘም 44 ተማሪዎች በቁጥጥር ሰር ውለው በፖሊስ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል።» ብለዋል። «የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብም በተፈጠረው ሁኔታ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ቢገኝም የመማር ማስተማሩ ሂደት ግን ሳይቋረጥ ቀጥሏል» ሲሉም አክለዋል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ሰላማዊ ድባብ ከሚስተዋልባቸው ጥቂት የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ በመሆን ይታወቃል። አሁን የተባለው ጸብ የተነሳውና የሰው ሕይወትም ያለፈው ተማሪዎቹ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የአንደኛ ወሰነ ትምህርት ፈተና ለመውሰድ በዝግጅት ላይ ባሉበት ውቅ ነው።የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ### Response:
### Text: የሱዳን እና ግብፅ ነገር የግብፅ ጦር አዛዥ ካርቱም የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካይሮ ናቸው።ካርቱም ላይ ሰኞ ወደ ካርቱም ያመሩት የግብፅ ጦር አዛዥ ሌጀ ሞሀመድ ፋሪድ ከሱዳን አቻቸው ሌጀ ሞሀመድ አል ሁሴን ጋር የተለያዩ ወታደራዊ ስምምነቶችን ፈፅመዋል።የግብፁ ጦር አዛዥ ማምሻውን በሰጡት መግለጫ ግብፅ እና ሱዳን ተመሳሳይ ብሄራዊ የደህንነት ስጋት ተደቅኖባቸዋል በጋራ መስራት የሚገባን ጊዜ አሁን ነው ብለዋል። እንዲሁም ሱዳን ለምታቀርብልን ወታደራዊ ነክ ጥያቄዎች ሁሉ ምላሽ ለመስጠት ግብፅ ዝግጁ ናት ሲሉ ተናግረዋል ።የሰዳኑ አቻቸው እንዳሉት ደግሞ ሃገራቱ የጋራ አደጋ የተደቀነባቸው በመሆኑ በወታደራዊ መስክ ትብብራቸው ጠንክሯል ብለዋል።ካይሮ ላይ የሱዳን ውጉሚኒስትር ማርየም አል ሳዲቅ ግብፅ በማቅናት በዋናነት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ከግብፅ መንግስት ሃላፊዎች ጋር ሲመክሩ ዉለዋል።የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትን እንዳይካሄድ ለማድረግ ያስችላል ያሉትን ምክክር አድርገዋል። የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርየም አል ሳዲቅ ኢትዮጵያ ለብቻዋን የምታደርገውን ነገር እንድታቆም እንነግራታለን አካሄዷ ወደአላስፈላጊ አቅጣጫ ይዞን ሊሄድ ይችላልም ሲሉ ማስፈራሪያ አዘል ንግግር ሲያደርጉ ተደምጠዋል።የግብፅ እና ሱዳን ሚኒስትሮች በጋራ በሰጡት መግለጫ አለም አቀፍ አሸማጋዮች በድርድሩ እንዲገቡ ግፊት ለማድረግ ተስማምተዋል። ### Response:
### Text: በውጤት እና መቁረጫ ነጥቡ ዙሪያ አስፈላጊው ማብራሪያ እንዲሰጥ ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ ጥያቄ አቅርቤ ምላሽ እየጠበኩ ነው የአበክመ ትቢሮየአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2013 ዓም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የፈተና በውጤት እና መቁረጫ ነጥቡ ዙሪያ አስፈላጊው ማብራሪያ እንዲሰጥ ለሚኒስቴር መቤቱ ጥያቄ አቅርቤ ሚኒስቴር መቤቱ ዛሬ ተገቢው ማብራሪያ እንደሚሰጥ ገልጾልኛል ሲል አስታውቋል።ቢሮው ብሔራዊ ፈተና በሁለቱም ዙር በሰላማዊ መንገድ እንዲሰጥ የሚፈለግብንን ሁሉ አድርገናል። ከ12ኛ ክፍል ፈተና አኳያ የክልሉ ድርሻም ይሄው ነው። ሲል ነው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ያሰፈረው።የአንደኛው ዙር ፈተና እንደተጠናቀቀ በሚቀጥለው ቀን ለሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት በወቅቱ ፈተና ተሰርቋል እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ ሲስራጭ በነበረው የተለያየ መረጃ ምክንያት የፈተና ውጤት ትንተናው በጥንቃቄ እንዲታይ በፅሁፍ ጥያቄ አቅርበናል። ሌሎች ጠቃሚ ሀሳቦችንም በወቅቱ አቅርበናል። ሲል ገልጿል።አክሎም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኩል አስፈላጊው ማብራሪያ ከተሰጠ በኋላ በትምህርት ቢሮው በኩል የሚፈለጉ መረጃዎች ካሉ መረጃዎችን ሳልደብቅ ገልጻለሁ ብሏል።የተማሪዎች ውጤት ለዞኖች፣ ወረዳዎች እና ትምህርት ቤቶች በግልፅ የተላለፈ ስለሆነ ለመሸፋፈን የሚፈልግ አካልም የለም መሸፋፈንም አይቻልም። ማለቱን ከቢሮው ገጽ ተመልክተናል። ### Response:
### Text: ከ15 ሺ በላይ ጥይቶች ተያዙ ከመተማ ወደ ጎንደር ከተማ በድብቅ ሊገቡ የነበሩ 21 ሽጉጦችና ከ15 ሺህ በላይ ጥይት መያዙን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የጎንደር ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ አስታወቀ።በጎንደር ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ የሰራባ ኬላ አስተባባሪ ኮሎኔል ብርሃነ መብራት ለእንደተናገሩት የጦር መሳሪያና ጥይቶቹ የተያዙት ከጭልጋ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው ሰራባ በተባለው የመቆጣጠሪያ ኬላ ነው።የጦር መሳሪያዎቹንና የክላሽ ጥይቶቹን በድብቅ ጭኖ የተገኘው የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 212155 አዲስ አበባ የሆነ ፒካፕ ተሸከርካሪ ሲሆን በመኪናው ውስጥ የነበሩ አራት ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።ከትናንት በስቲያ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በተደረገው ጥብቅ ቁጥጥርና ፍተሻ የተያዙት የጦር መሳሪያዎችና ጥይቶች በመኪናው አካል ላይ በረቀቀ መንገድ ተበይደው በተዘጋጁ ስውር ቦታዎች ተቀምጠው የተገኙ ናቸው።ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር በአካባቢው እየተስፋፋ መጥቷል ያሉት የኬላው አስተባባሪ፣ በዚህ ተግባር ላይ የሚሳተፉ ወንጀለኞችን በማጋለጥና ጥቆማ በመስጠት ሕብረተሰቡ የጀመረውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።ከታህሳስ እስከ የካቲት ወር 2010 ዓም ባሉት ሦስት ወራት ብቻ በሰራባ ኬላ 7 ሺህ ጥይቶች፣ 25 ሽጉጦችና ሁለት ክላሽን ኮቭ ጠብመንጃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮሎኔል ብርሃነ ተናግረዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት️የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በያሬድ ዘሪሁን፣ በተስፋዬ ኡርጌና ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ላይ ፓሊስ የጠየቀውን 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቀደ።ተጠርጣሪዎቹ በዛሬው እለት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት ነው የቀረቡት።ፍርድ ቤቱ በያሬድ ዘሪሁን ላይ ከህዳር 26 2011 ጀምሮ ታሳቢ የሚሆን የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።እንዲሁም በተስፋዬኡርጌ ላይ ፍርድ ቤቱ ከህዳር 24 2011 ጀምሮ ታሳቢ የሚሆን የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።ፖሊስ ቀድሞ በተሰጠው ጊዜ ከተጠርጣሪዎች ጋር ተያያዥ የሆነ ማስረጃ እየሰበሰበ በመሆኑና የሚቀረው ስራ በመኖሩ በዋስ ቢወጡ ማስረጃ እንደሚያጠፉ ስለታመነበት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜው ፍርድ ቤቱ ፈቅዷል ተብሏል።የሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘውን ጉዳይ የተመለከተው ፍርድ ቤት ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ ለታህሳስ 10 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በተመሳሳይ የሜጀር ጄኔራል ክንፈ ወንድም አቶ ኢሳያስ ዳኘውን ጉዳይ የተመለከተው ፍድር ቤት ለተጨማሪ ምርመራና ለቀሪ ስራ ማጠናቀቂያ ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን ፈቅዷል።ይህም ከህዳር 24 ጀምሮ የሚቆጠር ሲሆን ለታህሳስ 4 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በዛሬው የችሎት ውሎ የሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ጠበቆች በመገናኛ ብዙሃን ዘገባ ላይ ሃሳብ እናቀርባለን ብለው የነበረ ቢሆንም ሳያቀርቡ ቀርተዋል።ምንጭ ### Response:
### Text: በመቂ ከተማ መትረየስን ጨምሮ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ተያዙ በምስራቅ ሸዋ ዞን ዱግዳ ወረዳ መቂ ከተማ መትረየስን ጨምሮ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችና ጥይቶችን መያዙን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር አስቻለው አለሙ እንደገለጹት የጦር መሳሪያዎቹ የተያዙት በዱግዳ ወረዳ መቂ ከተማ ቀበሌ 03 ውስጥ ነው።ኮማንደር አስቻለው እንዳሉት የጦር መሳሪያዎቹ የተያዙት የወረዳው ፖሊስ ከፍርድ ቤት የፍትሻ ትዕዛዝ በማውጣት በሁለት ግለሰቦች መኖሪያ ቤት ባደረገው ብርበራ ነው።በእዚህም አንድ ኤስኬኤስ መተረየስ፣ ሦስት ሹጉጦች፣ 17 የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ለመጠገን የሚያስችሉ መለዋወጫዎችን ጨምሮ የተለያዩ ጥይቶች መያዛቸውን ገልጸዋል።በተደረገው ፍተሻም 164 የሹጉጥ ፣ 61 የብሬን መተረየስ፣ 31 የክላሽ እንኮብና የኋላቀር መሳሪያዎች ጥይቶች ከግለሰቦቹ መኖሪያ ቤት መገኘታቸውን አመልክተዋል።በተጨማሪም 12 የተለያዩ የክላሽንኮብ፣ የኡዝና የስታር ማካሮፍ ጥይት መያዣ ካርታዎችና 121 አርቴፊሻል ጥይት በግለሰቦቹ ቤት መያዙን አመልክተዋል።ትላንት መስከረም 20 ቀን 2012 ዓም እኩለ ቀን ላይ በተካሄደው ፍተሻ ከነዚህ ግለሰቦች ቤት የዝሆን ጥርስ አብሮ መያዙን የተናገሩት ኮማንደር አስቻለው፣ ግለሰቦቹ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን አስረድተዋል። ### Response:
### Text: ጠሚር አብይ የኖርዌይ እና የአለም አቀፍ ሚድያ ጋዜጠኞችን ቢያገኙ ምኞቴ ነበር የኖቤል ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር የኖቤል ሽልማት ፕሮግራም ረዥምሰፋ ያለ ነው። ለአንድ የሀገር መሪ ሁሉም ፕሮግራሞች ላይ መካፈል አስቸጋሪ ነው፣ በተለይ ሀገር ውስጥ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ባሉበት ወቅት የጠሚሩ ፕረስ ሰክረታሪ ቢለኔ ስዩምየኖርዌይ የኖቤል ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ኦላቭ ጆልስታድ ጠሚር አብይ ከአምስት ቀን በሁዋላ ሽልማታቸውን በሚቀበሉበት ወቅት ጥያቄዎች የሚጠየቁበት ፕሮግራም ላይ እንደማይገኙ ገልፀው ይህ በጣም ችግር ነው። ጠሚር አብይ የኖርዌይ እና የአለም አቀፍ ሚድያ ጋዜጠኞችን ቢያገኙ ምኞቴ ነበር ብለው ለአሶሼትድ ፕረስ ተናግረዋል። ዛሬ የጠሚሩ ፕረስ ሰክረታሪ ቢለኔ ስዩም ለ ጋዜጠኛው ኤልያስ መሰረት በሰጡት መረጃ የኖቤል ሽልማት ፕሮግራም ረዥምሰፋ ያለ ነው። ለአንድ የሀገር መሪ ሁሉም ፕሮግራሞች ላይ መካፈል አስቸጋሪ ነው፣ በተለይ ሀገር ውስጥ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ባሉበት ወቅት። ስለዚህ ጠሚሩ በተመረጡ እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፕሮግራሞች ላይ ከኖቤል ኢንስቲትዩት ጋር በመነጋገር ይካፈላሉ ብለዋል። ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ባሰራጨው መረጃ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በ2009 የኖቤል የሰላም ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት የሚድያ ፕሮግራሙ ላይ ሳይሳተፉ ቀርተው እንደነበር አስውሷል።ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ### Response:
### Text: የህወሓት መግለጫ እና የተፎካካሪ ፓርቲዎች አስተያየትትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የአረና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አምዶም ገብረስላሴ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ህወሓት ለመጀመሪያ ጊዜ ያካሄደውን አስቸኳይ ጉባኤ ሲያጠናቅቅ ባወጣው የአቋም መግለጫ ውህደቱን አልቀበልም፣ ከኢህአዴግ የጋራ ሀብት እካፈላለሁ ማለቱንና በውስጥ እንቅስቃሴዎች እርምጃ እወስዳለሁ ማለቱን ሰምቻለሁ ሁኔታው ወደግጭት የሚያስገባ ይመስላል። በአጠቃላይ የህወሓት መሪዎች ኢህአዴግ በመፍረሱ ከፍተኛ ቁጭት እንደተሰማቸው ያሳያል፡፡ ያስተላለፉት መልዕክትም የመገለል እና ባዕድ ስሜት እንደተሰማቸው የሚገልጽ ነው፡፡ ይህም ወደ ግጭት ሊያድግ እንደሚችልና እነርሱም ለጦርነት እንደተዘጋጁ የሚያመለክት አንድምታ አዝሏል። መልእክቱ ለትግራይ ህዝብ ጥሩ ዜና አይደለም፡፡ ህብረተሰቡ ከችግሩ መውጣት አለበት፣ ካለበት ችግርም የሚያወጣው ይፈልጋል፡፡ ድርጅቱ የጦርነት ፕሮፖጋንዳ መንዛቱም ለህብረተሰቡ ጥሩ ነገር እንደሌለው ያመለክታል። ሁልጊዜም ምክንያትና ሰበብ የሚያደርጉት እኛን ነው፡፡ ዛቻ ይደርስብናል፣ ጉዳትም እያደረሱብን ይገኛሉ ሰላማዊ ታጋዮች በመሆናችንም ይጎዱናል ይህ ግን ጥሩ አይደለም። ህግም ህገ መንግስቱም መከበር አለበት። አረና ዘንድሮ ለሚደረገው ምርጫ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል የህወሓት አቋምም መስተካከል አለበት። ### Response:
### Text: አፋጣኝ ፍትሕ ስጡን እና ከእስር ቤት ወጥተን ለምርጫው አስተዋፅኦ ማድረግ እንፈልጋለን አቶ እስክንድር ነጋየባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ባልደራስ አመራሮች እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል ፣ አስቴር ስዩም እና አስካለ ደምሌ ትላንት የከፍተኛ ፍርድ ቤት ችሎት ቀርበው ነበር።ፍርድ ቤቱ ብይን መስጠት የሚችለው የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ ካወቀ በኋላ እንደሆነ በመጥቀስ ለሚያዝያ 11 ቀን 2013 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። አቶ እስክንድር ነጋ አሁንም እድሎች ሙሉ በሙሉ አላለፉም አፋጣኝ ፍትሕ ስጡን እና ከእስር ቤት ወጥተን ለምርጫው አስተዋፅኦ ማድረግ እንፈልጋለን ሲሉ ጠይቀዋል። የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዳኞች በበኩላቸው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ አፋጣኝ ምላሽ ከሰጠ እነርሱም ፈጣን ብይን እንደሚሰጡ ገልፀዋል። አቶ ስንታየሁ ቸኮል ወቅቱ ዐብይ ፆም የሚጾምበት መሆኑን ጠቅሰው የምልኮ ስፍራ ወዳለበት የእስር ቤቱ ክፍል ዞን አራቱንም የህሊና እስረኞች እስር ቤቱ እንዲያዘዋውራቸው ጠይቀዋል። ይህ ካልሆነ በያሉበት የአምልኮ ስፍራ እንዲሰጣቸው ፍርድ ቤቱ ወህኒ ቤቱን ያዝዝ ዘንድ አሳስበዋል። ወይዘሮ አስቴር ስዩም በበኩላቸው የመደመር መንገድ የተባለው የጠቅላይ ሚንስትሩ መፅሐፍ እስር ቤት ውስጥ እየገባ ነውሀገር ስታምጥ የተሰኘውን የእኔን መፅሐፍ ግን ማስገባት አልቻልኩም። ተከልክያለሁ። ለምን ሲሉ ጠይቀዋል።ተጨማሪ ያንብቡ 0325 ### Response:
### Text: የብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ባለቤት ወሮ መነን ኃይሌ ምን አሉ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ በአዲስ አበባ ከቤታቸው እንደወጡ እስካሁን አልተመለሱም።ይህን ተከትሎ ባለቤታቸው ወሮ መነን ኃይሌ ለቢቢሲ አማርኛው ክፍል በሰጠቱ ቃል የሚከተለውን ብለዋል ትናንት ሰኞ ግንቦት 082014 ዓም ከቤታቸው 5፡15 አካባቢ የወጣው ከጓደኛው አቶ ዮሐንስ ቧያለው ጋር ቀጠሮ እንደነበረው ገልጾ ነው።ከዚያ በኋላ ግን ወደ ቤት አልተመለሰም ደጋግመን ወደ ተንቀሳቃሽ ስልኩ ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም። ከጄኔራል ተፈራ ጋር የተገናኙት ሰዎች በዕለቱ አስከ 10 ሰዓት ድረስ አብረው መቆየታቸውን እና ከዚያ በኋላ እንደተለያዩ ነግረውናል።ከዚያ በኋላ ግን የደረሰበትን ማወቅ አልቻልንም።ወደ ፌደራል ወንጀል ምርመራ እንዲሁም አዲስ አበባ ፖሊስ በመሄድ ብንጠይቅም በቁጥጥራቸው ስር እንደማይገኝ ገልፀውልናል።በአሁኑ ሰዓት ሊኖርበት ይችላል ወደተባሉ የተለያዩ የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት በመሄድ ፍለጋ ቀጥለናል።ባለቤቴ የስኳር ሕመምተኛ ነው የታዘዘለትን መድኃኒት እየወሰደ ነበር መድኃኒቱን ካልወሰደ ይታመማል ይህም ስጋት ውስጥ ከቶናል።ከሚኖርበት ባሕርዳር ወደ አዲስ አበባ የመጣው በእግሩ ውስጥ የሚገኙትን ጥይቶች በተመለከተ የሕክምና ክትትል ለማድረግ ነበር።እስሩን ለምዶታል ያለፈበትም ነው የሚያሳስበን የጤናው ሁኔታ ነው። ብርጋዴርጄነራልተፈራማሞ ### Response:
### Text: ኦሮሚያ ፖሊስ️በሻሸመኔ ከተማ ዛሬ በተጠራ የድጋፍ ስልፍ በተከሰተ ግርግር እና መጨናነቅ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ በግርግሩ በሰው አካልና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱንም ገልጿል።ኮሚሽኑ በህዝቡ አስተባባሪነት ለድጋፍ ሰልፍ በውጡ ዜጎች ላይ በተከሰተ አለመረጋጋት በተፈጠረው መገፋፋትና መጨናነቅ የሰው ህይወት ማለፉንና ንብረትነቱ የሻሸመኔ አስተዳደርና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት የሆነ አንድ መኪና መቃጠሉን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል አለማየሁ እጅጉ ለኢቲቪ ዜና ተናግረዋል።በተለያዩ ማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎችና ድረ ገጾች እየተዘዋወሩ ያሉት መረጃዎች እውነተኛነታቸው ሳይረጋገጥ ወደ ተሳሳተ ድምዳሜ ስለሚያደርሱ ጥንቃቄ ያስፈልጋልም ብለዋል።እስከ አሁን ፖሊስ የግርግሩ መነሻ ምክንያት ለማጣራት በምርመራ ላይ መሆኑን ገልጸው በድጋፍ ሰልፉ ከሻሸመኔና ዙሪያዋ ከፍተኛ ቁጥርያለው ህዝብ መገኘቱን ገልጸዋል።ኮሚሽነር ጄኔራል አለማየሁ እጅጉ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት ሻሸመኔ ከተማ እና በዙሪያዋ የነበረው ግርግር ተረጋግቶ መደበኛ እንቀቃሴዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።ፖሊስም በቀጣይ ቀናት ምርመራውን በማጠናቀቅ ተጠርጣሪዎችን ለሕግ ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል።ሕብረተሰቡም በመረጋጋት ትክክለኛመረጃዎችን ከፖሊስ እና የጸጥታ ሀይሉ ማግኘት እንደሚገባው አሳስበዋል።© ### Response:
### Text: ነሃሴ 262012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 2 በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2215 የላብራቶሪ ምርመራ 108 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ቤንች ሸኮ ዞንበቫይረሱ ከተያዙት መካከል፡ ከጋሞ 31 24 ከአርባምንጭ ከተማ ፣ 3 ከአርባምንጭ ዙሪያ፣ 2 ከላንቴ፣ 1 ከሼሌ እና 1 ቻኖ ሚሌ ፣ ከወላይታ 16 8 ከቦሎሶ ሶሬ ፣ 2 ከሶዶ ከተማ፣ 2 ከኪንዶ ኮይሻ፣ 2 ከዳሞት ዎይዴ፣ 1 ከዳሞት ጋሌ እና 1 ከሶዶ ዙሪያ፣ ከጎፋ 13 13ቱም ከኦይዳ ፣ ከደራሼ 11፣ ከአሌ 7፣ ከካፋ 6 6ቱም ከቦንጋ፣ ከቤንች ሸኮ 53 ከደቡብ ቤንች፣ 1 ከሚዛን እና 1 ከጉራፈርዳ፣ ከኮንታ 2 ይገኙበታል። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 974 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 12 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 6 ከሀዋሳ ከተማ 2 ከዳራ ወረዳ 1 ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ 1 ከወንዶ ገነት ወረዳ 1 ብላቴ ዙሪያ ወረዳ ይገኙበታል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 364 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 30 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል የአንድ ሰው ህይወት አልፏል። በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 542 የላብራቶሪ ምርምራ የተደረገ ሲሆን 110 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የነሃሴ 25 ሪፖርት ከ698 የላብራቶሪ ምርመራ 89 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል 62 ሰዎች አገግመዋልአጠቃላይ በትግራይ 3867 በቫይረሱ የተያዙ 21 ሞት 2483 ያገገሙ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተከርስቲያን የማህበራዊና ልማት ኮሚሽን የሴቶችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል በርካታ ስራዎችን ታከናውናለች፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ ሀገረስብከት የልማት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂ ሴቶች የስራ ተወዳዳሪነትን ማሻሻል ለተሻለ የስራ እድል ተጠቃሚነት በሚል መነሻ ሃሳብ ጥናታዊ ፕሮጅክት ለማካሄድ በሀገር አቀፍ ደረጃ ማቀዷን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቃለች።የጥናቱ ዋነኛው ዓላማ ምሩቃን ሴቶችን በስራ ዝግጁነት ስልጠና በማሰልጠን የስራ እድል መረጃዎችን በማቅረብ እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በመስጠት እና በማብቃት የስራ ተወዳዳሪነታቸውን መጨመር መሆኑ ተገልጿል።ሂደቱ ለሴቶች ተቃሚነት ያለውን ሚና በጥናት በማስረዳት ለፖሊሲ ግብዓት በመሆን ያገለግላል ተብሏል። ጥናቱ ከሚካሄድባቸው ስፍራዎቸ የአዲስ አበባ ከተማ አንዱና ዋነኛው መሆኑ ተገልጿልጥናታዊ ፕሮጀክቱ በአአ ከ2009 ጅምሮ እስከ 2013 ዓም ባለው የትምህርት ዘመን ከታወቀ ዩኒቨርስቲዎች ተመርቀው መደበኛ የሥራ ዕድል ያላገኙ 662 ሴት የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ያሳትፋል፡፡ በመቀጠልም ይህ ፕሮጀክት ለ 441 ሴት ምሩቃን በግልጽ ሂደት ተመርጠው የስልጠናዎች እና የሥራ እድል መረጃ በመስጠት ተጨማሪ ድጋፎች ያደርጋል፡፡ ዝርዝር መስፈርቶች ፣ የመመዝገቢያ ቦታ እና ተጨማሪ መረጃዎች ከላይ ተያይዟል ### Response:
### Text: የትግራይና የአማራ አጎራባች ወረዳዎች የአሸንዳና አሸንድዬ በዓልን በጋራ ሊያከብሩ ነው የትግራይና የአማራ ክልል ዘጠኝ አጎራባች ወረዳዎች የአሸንዳአሸንድዬ በዓልን በጋራ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው። የበዓሉ ዋናው ባለቤት የሆኑት ልጃገረዶች፣ የሚመለከታቸው አካላትና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በሰጡት አስተያየት በዓሉን በጋራ ማክበራቸው በሁለቱም ክልል ሀዝቦች ለዘመናት የቆየውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከር ለማድረግ ነው።የትግራይ ማእከላዊ ዞን የቆላ ተምቤን ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሰ አብርሃ እንደገለፁት ከትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን አራት ወረዳዎችና ከአማራ ክልል ዋግኽምራ አምስት ወረዳዎች የተወጣጡ ልጃገረዶችና ወጣት ሴቶች በጋራ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ተዘጋጅተዋል።በተምቤን ዓብይዓዲ ከተማ በጋራ የሚከበረው የአሸንዳአሸንድዬ በዓል በሁለቱም ክልሎች አጎራባች ወረዳዎች የሚገኙ ህዝቦች የበዓሉን ቱሩፋቶች ተጠቅመው በመካከላቸው የቆየውን ግንኙነት ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ ነው። በአማራ ክልል የዋግኸምራ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ተወካይ አቶ ምስገናው መስፍን ለኢዜአ በስልክ በሰጡት አስተያየት የልጃገረዶች የነጻነት መገለጫ ተደርገው የሚታሰቡ የአሸንድዬናአሸንዳ በዓላት በጋራ ለማክበር መነሳሳት መፈጠሩ ተገቢነት አለው ብለዋል።ተጨማሪ ያንብቡ 0814 ### Response:
### Text: አዲስ ተገኘ የተባለው የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ለዓለም ሀገራት ስጋት እየሆነ ነው።ከ40 በላይ አገራት ከ ወደ አገራቸው የሚደረጉ በረራዎችን አግደዋል።የአውሮፓ ሕብረት አባል አገራት በዚህ ዙሪያ የጋራ ፖሊሲ ለማውጣት እየተወያዩ ነው።ዴንማርክ ውስጥ አዲሱ የቫይረስ ዝርያ በመታየቱ ስዊድን ወደ ዴንማርክ የሚደረግ ጉዞ አግዳለች።ዝርያው በከፍተኛ ሁኔታ የሚሰራጭ ነው። በከፍተኛ ደረጃ ጎጂ ስለመሆኑ ግን እስካሁን የተገኘ መረጃ የለም።የዓለም ጤና ድርጅቱ ማይክ ራየን አዲሱ የቫይረስ ዝርያ በወረርሽኙ ዝግመተ ለውጥ ሂደት የሚጠበቅ ነው ብለዋል።የ የጤና ሚንስትር ጸሐፊ ማት ሀንኮክ አዲሱ ዝርያ ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል ቢሉም ማይክ ራይን አዲሱ ዝርያ ከቁጥጥር አልወጣም ብለዋል። ከተገኘው የቫይረስ ዝርያ የተለየ አዲስ ዝርያ በደቡብ አፍሪካም ተገኝቷል። የደቡብ አፍሪካ ተጓዦች ላይ እገዳ እየተጣለም ነው።እስካሁን የአዲሱ ቫይረስ ዝርያ በዴንማርክ፣ አውስትራሊያ፣ ጣልያን እና ኔዘርላንድስም ተገኝቷል።አንዳንድ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ የቫይረሱ ዝርያ ከተገኘባቸው ቦታዎች ውጪ ተሰራጭቶ ሊሆን ይችላል። የዘረ መል ቅንጣት ላይ ጥናት በማድረጓ አዲሱን የቫይረስ ዝርያ እንደደረሰችበት አስረድተዋል።በቤልጄም የሚሠሩት የቫይረስ አጥኚ ማርክ ቫን በቀጣይ ቀናት አዲሱ የቫይረሱ ዝርያ በብዙ አገሮች ይገኛል ብለን እንጠብቃለን ብለዋል። ### Response:
### Text: ቅሬታ️በአማራ ክልል ዞኖች ውስጥ የምንገኘው በውሃ መስኖና ኢነርጅ መምሪያ የመስኖ ቡድን ሰራተኞች መዋቅሩ ይስተካከላል እየተባልን ከ3 ዓመታት በላይ ያለስራ በነፃ ደሞዝ እየተከፈለን ቆይተናል። በተደጋጋሚ ለአማራ ውሃ መስኖና ኢነርጅ ልማት ቢሮ ብናመለክትም ምላሽ የሚሰጠን አላገኘንም፡ በሰራተኞችም ሆነ በመምሪያ ሃላፊዎች የመስኖ ቡድንን ወይ መዋቅሩን አስተካክሉት ካለበለዚያ ቡድኑን አጥፉት የሚል ጥያቄ በየመድረኩ ቢነሳም ይሄ ከእኛ አቅም በላይ ነው የሚል ምላሽ ነው የሚሰጠው፡፡ ይህ የመስኖ ቡድን በውሃ መስኖና ኢነርጅ ቢሮ በኩል እስከ ዞን ብቻ የተዘረጋ ሲሆን በግብርና በኩል ግን የሰው ሃይሉን በዛ አድርጎ እስከ ወረዳ ድረስ መዋቅር ተሰርቶለታል፡፡ እንደዚህ አይነት መዋቅር በአማራ ክልል ብቻ የሚገኝ ሰራተኞችን እንደ ጡረተኛ በባዶው ደሞዝ ከመክፈሉ በተጨማሪ የእኛን የሰራተኞቹን ስን ልቦና እየጎዳን ይገኛል፡፡ ይሄን ጉዳይ ርዕሰ መስተዳድሩ የሚያቁት ቢሆንም እስከ አሁን የተሰጠን ምላሽ የለም። እናም መስራት የሚችልን ጉልበት እና ጭንቅላት ተጠቀሙት፡ አትቀልዱበት። እባካችሁ፡ እባካችሁ የሚመለከታችሁ የፈደራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት መፍትሄ ስጡን እያልን እንገኛለን በየዞኑ የምንገኝ በውሃ መስኖና ኢነርጂ መምሪያ ውስጥ የምንገኝ የመስኖ ቡድን ባለሙያዎች ነኝ ከአዊ ዞን ውሃ መስኖና ኢነርጅ መምሪያ፡ እንጅባራ ### Response:
### Text: ከወልዲያ ዩኒቨርሲቲሰላም ጽግሽ ከወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ነው ምጽፍልህ። ትላንት ግቢው የለቀቀው ማስታወቂያ ያለው ችግር በጣም ቀላል እንደሆነ ሰለሚያስረዳ ነው ይህን ልጽፍልህ የተገደድኩት። በግቢው ለ11 ቀን ያህል ውሀ ጠፍቶ ነበር። እናም እኛ መጀመሪያ በሰላማዊ መንገድ ነበር ሰልፍ ወጥተን የጠየቅናቸው ከዛ በላያችን ላይ ልዩ ሃይል እና መከላከያ ላኩብን። ኑ ብሎ በአደራ የተቀበለህ አስተዳደር ባንተ ላይ እንዲህ ሳደርጉብህ ማየት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ አልነግርህም። ደሞ ልዩ ሀይሎች ዶርም እየሰበሩ ገብተው ሲደብድቡን ነበር። የሚገርምህ ወንድ ልጅ ቢደበደብ እኮ ብዙም ላይከብደው ይችህላል ግን ሴት እህቶቻችን ዶርም እየገቡ ሴቶቹን መደብደብ ምን ያህል መወረድ ነው እና ይኸው ዛሬም ሁለት ሰኣት ተኩል አካባቢ በድጋሚ ተነስቶ ነበር። እና ግን መከላከያዎች ተኩስ ከፈቱብን። እንዴትም ብለን ከግቢ ወጥተን በባጃጅ ስንሄድ ደግሞ ከባጃጅ እያስወረዱ ይመልሱናል። እሺ ከተማ መቀመጥ ከልክለውን ዶርም ስንቀመጥ ከደበደቡን እሺ የት እንሂድ እኛ ትላንት ደሞ ለ11 ቀን ሙሉ የጠፋ ውሃ እረብሻ ሲነሳ መለቀቁስ ጥያቈ ውስጥ አይከትም እሺ የፓምፕ ብልሽት ከሆነ 11 ቀን ሙሉ ያልተሰራ ፓምፕ እንዴት በዛች ሰኣት ውስጥ ሊሰራ ይችላል ብቻ በጣም እየተበደልን ነው ጸግሻ ስሜን እንዳትጠቅስከዩኒቨርሲቲው በኩል የማገኘው ምላሽ ካለ ወደእናተ አደርሳለሁ ### Response:
### Text: ኡስታዝ አቡበከር አህመድ በምርጫ ለመሳተፍ እጩ ሆኖ ለመቅረብ የያዙትን ሃሳብ እንደሰረዙ ገለፁኡስታዝ አቡበከር አህመድ በዛሬው ዕለት በይፋዊ የማዕበራዊ ሚዲያ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት በምርጫ 2013 እጩ ሆኖ ለመቅረብለመመዝገብ የያዙት ሃሳብ መተዋቸውን አስታውቀዋል።በምርጫ 2013 ሂደት በግል ተነሳሽነት እና በቀረቡላቸው ጥያቄዎች መሰረት በምርጫ ተሳታፊ ለመሆን ሲያሰቡብት መቆየታቸውን ገልፀዋል። ለምን ምርጫ የመወዳደር ሃሳባቸውን ተዉት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እንደገለፁት ከሆነ ከትግል ወንድሞቻቸውና ከሌሎች ጋር በመሆን ለማህበረሰቡ እና ለአገሪቱ ይጠቅማል በሚል ወደፊት ለመስራት የተስማሙባቸው እንቅስቃሴዎች እና ፕሮጀክቶች ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ጥረት የጊዜ ጥበትን እንዲሁም አመቺነትን ታሳቢ ለማድረግ በመገደዳቸው ነው ለጊዜው ለምርጫ በእጩነት የመመዝገቡን ሀሳብ ለመተው የወሰኑት።ከውሳኔው ላይ በመድረሱ ሂደት የወንድሞቻቸው ምክር እና አስተያየት ዋናውን ድርሻ የያዘ እንደነበረም ገልፀዋል።በሌላ በኩል ኡስታዝ አቡበከር ዛሬ ባሰራጩት የፅሁፍ መልዕክት ኡስታዝ አህመዲን ጀበል እና ኡስታዝ ካሚል ሸምሱን ጨምሮ ሌሎችም ወንድም እና እህቶቻቸው ለአገራዊ ምርጫ በእጩነት መመዝገባቸው ገልፀው ስኬታማ እንዲሆኑ ከመመኘት ባለፈ በአስፈላጊው መስክ ሁሉ ድጋፍ በመስጠት ከጎናቸው እንደሚሆኑ አረጋግጠዋል። ### Response:
### Text: ስራ ዝግ ሆኖ ይውላል ነገ መስከረም 20 የሚካሄደው ምርጫን እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ ተከትሎ ስራ ዝግ ሆኖ እንደሚውል ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አሳውቋል።ስራ ዝግ ሆኖ የሚውለው በሐረሪ ክልል፣ በሶማሌ ክልል፣ በደብብህ ክልል በምእራብ ኦሞ ዞን፣ በደቡብ ኦሞ ዞን፣ በቤንች ሸኮ ዞን፣ በሸካ ዞን፣ በጌዲዮ ዞን፣ በሃድያ ዞን፣ በጉራጌ ዞን፣ በጋሞ ዞን፣ በካፋ ዞን፣ በወላይታ ዞን ፣ በዳውሮ ዞን፣ በባስኬቶ ልዩ ወረዳ እና በኮንታ ልዩ ወረዳ ነው። ምርጫ ቦርድ ዜጎች እለቱን ለድምጽ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ ከላይ በተጠቀሱት ክልሎች እና ዞኖች የሚገኙ የፌዴራል እና የክልል መንግስታዊ ተቋማት መስከረም 20 ቀን 2014 ዓም ስራ ዝግ እንዲያደርጉ አሳውቋል።ቦርዱ የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የእለት ተእለት አገልግሎት ሰጪዎች ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት ወዘተ በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ ማከናወን እንደሚችሉ ገልጾ እነዚህ ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አይጠበቅባቸውም ብሏል።የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም በተጠቀሱት ክልሎች እና ዞኖች ዜጎች ድምጽ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና እቅዶችን እንዳይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምጽ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉም ቦርዱ አበረታቷል። ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ በሀገራችን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ለ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ እና ከተማ አቀፍ ፈተና ይቀመጣሉ።ፈተናው በክልሎች እንዲሁም በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ሰኔ 26 እና ሰኔ 27 2015 ዓም እንደሚሰጥ ከየክልሉ ትምህርት ቢሮዎች ያገኘነው መረጃ ያሳያል።በዘንድሮው ዓመት በሚሊዮን ሚቆጠሩ ተማሪዎች ፈተናው ላይ የሚቀመጡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ግዙፎቹ የኢትዮጵያ ክልሎች ኦሮሚያ እና አማራ በድምሩ ከ830 ሺህ በናይ አማራ 347666 ኦሮሚያ 484994 ተማሪዎችን ፈተና ላይ ያስቀምጣሉ።በደቡብ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ፣ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ75 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተና ላይ የሚቀመጡ ሲሆን በሌሎች ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ በርካታ ሺዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።እንደ ክልል ትምህርት ቢሮዎች መረጃ በአጠቃላይ በመላው ሀገሪቱ ፈተናውን የሚወስዱት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ናቸው።ነገ መሰጠት የሚጀምረው ፈተና ሙሉ ቀን ጠዋት እና ከሰዓት እንደሚሰጥ የታወቀ ሲሆን ተፈታኞች እርሳስ፣ ላጲስ እና ማስመሪያ ብቻ ወደ ፈተና ማዕከላት ይዘው መሔድ ይችላሉ።ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ዲጂታል ሰዓት እንዲሁም ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን ይዞ በፈተና ማዕከላት መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ወላጆችም ልጆቻችሁ የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ይዘው ወደ መፈተኛ ጣቢያ እንዳይሄዱ ክትትል አድርጉ። ### Response:
### Text: ዶር አብይ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲው መምህር ላነሱት ጥያቄዎች የሰጠው ምላሽ️1 ጥያቄ እነ ለምን ገቡ ሉአላዊነታችን ተደፈረ◾️መልስ ደሃ ሀገር ምን ሉአላዊነት አላት ሉአላዊነት የምድር ብቻ አይደለም። የአየር ክልላችን ላይ የሚፈነጭ ብዙ ነው። የሳይበር ሴኩሪት አለ እኔ የማደርገውን ጎርጉረው ያገኛሉ። የኔን ውሎ የማያውቅ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። የዚህ ሀገር ምርመራ ከወገንተኝነት የፀዳ አይደለም። አግዞናልግን ውስጣችንን አላሳየነውም። በ የሚነጫነጩትንም እስቲ ለምን ብለህ ጠይቃቸው።2 ጥያቄ 2 ሰው ያለማስረጃ ይታሰራል◾️መልስ እንኳን ያለ ማስረጃ ልናስርተጨባጭ ማስረጃ የተገኘባቸውን 1001 ሰዎች አላሰርንም። እነርሱን አስረን ከትግራይ ህዝብ ጋር ከምንቀያየምየትግራይ ህዝብ ራሱ ስራቸውን ሲረዳ ይትፋቸው ብለን ዝም አልን አዕምሮህን ስለምፈልገው ሙሉ ማስረጃ ልሰጥህ እችላለሁ። 20 አመት የሰራበትን መስሪያ ቤት ንብረት ሳያስረክብ ሄዶ መቀሌ የተደበቀ አለ። የእሮብ ሚሊሻ ያለ ምንም ክፍያ 15 አመት ድንበር ሲጠብቅ የርሱ አይነቱ እዚህ አዲስ አበባ ሲንደላቀቁ ነበር። ዛሬ መቀሌ እነርሱ ወዳረፉበት ሆቴል የሚመላለሱ የሴቶች ብዛትን ሲታይ ማንነታቸውን ትገነዘባለህ።ለትግራይ ህዝብ ተጨንቀው አያውቁም። ኢሳያስን መቀሌ መጋበዝ ነበር እቅዴ እነዚህ ተንኮለኞች ያልሆነ ስራ ሰርተው ሁለቱን ወንድማማች ህዝብ እንዳያቀያይሙ ሰግቼ ተውኩት© © ### Response:
### Text: በኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ልዩ መረጃ ላይ የቀረበው መረጃ የተሳሳተ ስለሆነ ሊታርም ይገባል ሲሉ የአፋር የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ሊቀመንበር አቶ ጋአስ አህመድ ለ ተናግረዋል። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ጋአስ አህመድ ለ በላኩት የድምፅ መልዕክት ተከታዩን ብለዋል በሬድዮ ጣቢያው የተሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም ሶስቱ ከተማ የሚባሉት በሱማሌ ክልል ቁጥጥር ስር የነበሩ አልነበሩም የ ዞኖች ሲመሰረቱ አመሰራረታቸው ከኮብትሮባንድ ጋር የተያያዘ ስልነበር በሁለቱም በኩል እንዳይተዳደሩና ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በራሱ የኮንትሮባንድ ከተማ ሆኖ የቆየ ነው። በኃላ ውሳኔ ሲሰጥ ወደአፋር የተካለሉ እንጂ በሱማሌ ክልል ስር ሆኖ ሲተዳደሩ ነበሩ አይደሉም። ሌላው ደግሞ የአፋር ኃይሎች የሱማሌ ክልልን ዘልቀው በመግባት ጥቃት ፈፅመዋል የሚለውም ከእውነት የራቀ ነው። ግጭቱ ያለበት አካባቢ እራሱ አፋር አካባቢ ነው ቦታውም ከሱማሌ ክልል ወደ 300 ኪሎሜትር ወደአፋር ውስጥ ገብቶ ነው። ስለዚህ መረጃው የአንድ ወገን ብቻ በመሆኑ ሊታረም ይገባዋል። የአንድ ወገንን ድምፅ ብቻ ይዞ እንዲህ ያለ ፕሮፖጋንድ መስጠት ተገቢ አይደለም። ይሄ ለሁለቱም ህዝቦች መፍትሄ ሊሆን አይችልም።አቶ ጋአስ አህመድ ለ ጨምረው እንደገለፁት በአፋር ክልል በሚገኙ አርብቶ አደሮች ላይ ጥቃት እየተፈፀመ ያለው ከተለያዩ አካላት ስለመሆኑ የቪድዮ መረጃ ጭምር አለን ብለዋል። ### Response:
### Text: በእኔ ደረጃ በአደባባይ የሚሰደብ ጠሚ የለም ዶር አብይ ከሰሞኑን በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ከህዝብ ጋር ውይይት ያደርጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር አብይ አህመድ ተከታዩን ሲናገሩ ተደምጠዋልአሁን ወጥቶ ሚሳደበውን ወጥቶ ሚራገመውን ሁሉ ሰድበን፣ ሁሉ አስረን እንችለዋለን በኢትዮጵያ ውስጥ እንደምታውቁት በኔ ደረጃ በአደባባይ ሚሰደብ ጠቅላይ ሚኒስትር የለም።ድሮ ተሳድባችሁ ሳይሆን ልትሳደቡ አስባችኃል ተብላችሁ ትታሰሩ ነበር። አስባችኃል ያልኩት ቀልድ አይደለም ድምፃችን ይሰማ እኮ እንዲህ አስባችኃል ተብለው የታሰሩ ናቸው። ህገ መንግስት ይከበር፣ የሃይማኖት እኩልነት ይከበር፣ ድምፃችን ይሰማ ሲሉ አይ ይሄን አይደለም ያላችሁት ያሰባችሁት ሌላ ነገር አለ ተብለው ነው የታሰሩት። እንጂማ ህገ መንግስት ይከብር እንዴት ሰው ያሳስራል።አሁን ደግሞ ህገ መንግስት ይከበር፣ ሙስሊም እውቅና ያግኝ፣ እስላሚክ ባንክ ይኑር፣ መጅሊሱ ተቋም ይሁን ተቋም ይሁን ማለት ምን እንደሆነ አይገባችሁም ለምሳሌ ሳዑዲ በህግ እውቅና ካልሰጠን በስተቀር እስላሚክ ሴንተር መፈራረም አይችልም ከመጅሊስ ጋር አሁን እውቅና አግኝተን ወር ሳይሞላ 80 እና 90 ሚሊዮን ዶላር እያመጣን ነው እኮ።ይሄን የሚየውቁ ሰዎች እኛን መልሰው የሙስሊም ጠላይ ይላሉ። ሚናገር ሰው ሚያጥላላ ሰው ካለ ትክክል አይደለም። እንኳን መስጅድ የአንድ ሰው ደሳሳ ጎጆ መቃጠል የለበትም። ### Response:
### Text: ሰላም ሚኒቴር️በምንጃር ሸንኮራ እና ፈንታሌ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በቁጥጥር ስር መዋሉን የሰላም ሚኒስቴር ገለፀ፡፡በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ መካከል አሞራ ቤት በምትባል ቀበሌ እንስሳትን ውሃ በማጠጣት ሂደት የተፈጠረው ግጭት በዛሬው ዕለት በቁጥጥር መዋሉን በሚኒስቴሩ የግጭት አፈታት ዳይሬክተሩ አቶ ኃይለአብ ጌታቸው ለ ተናግረዋል፡፡ዳይሬክተሩ እንዳስታወቁት በአዋሳኝ አካባቢዎቹ መጋቢት 8 ፣2011 የተፈጠረው ግጭት እንሰሳትን ውሃ ለማጠጣት በሚል ምክንያት ተጀምሮ ለሁለት ሰው ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡በግጭቱ በሁለቱም ወገን ከሞቱት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ በሰባት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡የመከላከያ ሠራዊትም ግጭት በተፈጠረበት አካባቢ ገብቶ የማረጋጋት ስራ እየሰራ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡የሁለቱ ዞን አስተዳዳሪዎች ግጭት በተፈጠረበት አካባቢ ዛሬ በመሄድ ህዝቡን በማወያየት ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረጉ መሆኑንም አቶ ኃይለአብ አመልክተዋል።በእንሰሳት ግጦሽ እና የመጠጥ ውሃ የተፈጠረው አለመግባባት ከዚህ በፊትም እንደሚከሰትና በሁለቱም ወገን በኩል ያሉ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ እንደከዚህ ቀደም ባሉ ውይይቶች ችግሩን እንደሚፈቱት ዳይሬክተሩ አስረድተዋል። ### Response:
### Text: 7ኛው የበጎ ሰው ተሸላሚ እጩዎች ታወቁለ7ኛው የበጎ ሰው ሽልማት 291 ሰዎች ተጠቁመው 27 እጩዎች ለዳኞች ውሳኔ ቀርበዋል ከእነዚህም መካከል በመምህርነት ዘርፍ 1ኛ ፕሮፌሰር ሽታዬ አለሙ2ኛ ወሮ ህይወት ወልደመስቀል3ኛ ዶር መስከረም ለቺሳ በሳይንስ ህክምና፣ቴክኖሎጂ፣ፊዚክስ፣ምህንድስና፣ኬሚስትሪ፣አርክቴክቸር፣ወዘተ 1ፕሮፌሰር ለገሰ ነጋሽ2ኛ ፕሮፌሰርሰብስቤ ደምሴ3ኛ ዶክተር ታደለች አቶምሳ በኪነ ጥበብሥነ ጥበብ፣በፎቶ ግራፍ ዘርፍ 1ኛ አቶ ሚካኤል ፀጋዬ2ኛ አቶ በዛብህ አብተው3ኛ አቶ ዳኜ አበራ በበጎ አድራጎትርዳታና ሰብአዊ አገልግሎት 1ኛ ዶር ጀምበር ተረፈ2ኛ አብድላዚዝ አህመድ3ኛ ላሌ ለቡኮ በንግድና ስራ ፈጠራ ዘርፍ 1 ዳንኤል መብራቱ2ኛ አቶ ክቡር ገና3ኛ ነጋ ቦንገር በመንግስታዊ የስራ ተቋማት ሀላፊነት 1ኛ አቶ በትሩ አድማሴ2ኛ ዶር አሚር አማን3ኛ አቶ ግርማ ወንዳፍራሽ በቅርስና ባህል ዘርፍ 1ኛ አብዱልፈታህ አብደላ2ኛ አድማሴ መላኩ3ኛ ሳሙኤል መኮነን ከጎንደር በሚዲያና ጋዜጠኝነት 1ኛ አቶ በልሁ ተረፈ2ኛ አቶ አማረ አረጋዊ3ኛ ወሮ አንድነት አማረ በኢትዮጵያ እድገት አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች 1ኛ አቶ ኦባንግ ኡሜቶ2ኛ አርቲስት ታማኝ በየነ3ኛ ፕሮፌሰር ፀጋዬ ታደሰበመሆን የታጩ ሲሆን ከእያንዳንዳቸው ዘርፎች 1ኛ አንደኛ የሚወጡት ደግሞ ነሀሴ 262011 ዓም ከቀኑ 800 በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል አሸናፊዎች ተለይተው ይሸለማሉ፡፡ ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች ሳዑዲ አረቢያ ባለፉት 24 ሰዓት 1132 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ሪፖርት አድርጋለች። እስካሁን በአንድ ቀን ከተመዘገቡት ኬዞች ከፍተኛው ነው። በሳዑዲ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 8274 ናቸው። በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት 1374 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል በ26 ቀን የተመዘገበ ዝቅተኛው ኬዝ ነው። እንዲሁም 73 ሰዎች በአንድ ቀን ሞተዋል በ38 ቀናት የተመዘገበ ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ነው። በስፔን የእንቅስቃሴ ገደብ እስከ 9 ተራዝሟል። በፈረንሳይ ባለፉት 24 ሰዓት የ642 ሰዎች ሞት ተምዝግቧል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 19323 ደርሷል። በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር ከ38000 በላይ ሆኗል። በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ728000 በላይ ሆኖ ተመዝግቧል። በሩዋንዳ ባለፉት 24 ሰዓት 712 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ አንድ 1 ሰው በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 144 ደርሰዋል። በሌላ በኩል ተጨማሪ 4 ሰዎች በማገገማቸው አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 69 ደርሰዋል። ባለፉት 24 ሰዓት በሱማሊያ 25 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 19 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 135 ደርሰዋል። በተጨማሪ ሁለት 2 ሰዎች ባለፉት 24 ሰዓት ሞተዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በኮሮና ቫይረስ ኮቪድ19 የተያዙ ሰዎች 2313897 ደርሷል። ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ከ590000 በላይ ሆኖ ተመዝግቧል። ከ159000 በላይ ሰዎች ደግሞ ሞተዋል። ### Response:
### Text: ነሃሴ 182012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 602 የላብራቶሪ ምርምራ የተደረገ ሲሆን 19 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።አጠቃላይ በአፋር 825 በቫይረሱ የተያዙ 231 ያገገሙ በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 630 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 18 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 3514 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 236 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 70 ከቢሾፍቱ ከተማ 42 ከምዕራብ ወለጋ 18 ከቄለም ወለጋ 13 ከነቀምቴ ከተማ 11 ከምስራቅ ሸዋ 10 ከአዳማ ከተማ ይገኙበታል።አጠቃላይ በኦሮሚያ 4860 በቫይረሱ የተያዙ 41 ሞት 1480 ያገገሙ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 769 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።3 ከምዥጋ በሎጂጋንፎይ ወረዳ1 ከሸርቆሌ ወረዳ1 ከሆሞሻ ወረዳ በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 2499 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 103 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ከቦሩ ሜዳ ህክምና ማዕከልበቫይረሱ ከተያዙት መካከል 24 ከደሴ ከተማ 23 ከሰወሎ ዞን 12 ከምስጎጃም ዞን 11 ከሰሸዋ ዞን 11 ከኦሮሞ ብሰብ ዞን 10 ከጎንደር ከተማ 9 ከባህር ዳር ከተማ ይገኙበታል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 361 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 49 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ### Response:
### Text: ስለሱዳን እና ግብፅ ወታደራዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ምን ትላለች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ሰሞኑ ሱዳን እና ግብጽ ሰሞኑን ባደረጉት ወታደራዊ ስምምነት ዙሪየ ተጠይቀው ለኢፕድ ምላሽ ሰጥተዋል።ሱዳንም ሆነ ግብጽ ልአላዊ አገር ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የፈለጉትን አይነት ስምምነት የማድረግ መብት እንዳላቸው እና ኢትዮጵያም እንደማይመለከታት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለፀዋል።አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ልአላዊ አገራት የሚያደርጉት ስምምነት እኛ ምንም አይመለከተንም። የሱዳን እና የግብጽ ስምምንት ኢትዮጵያ ላይ ጉዳት የሚያስከትል ከሆነ ግን ለሁለቱም አገራት የሚጠቅም አይሆንም ሲሉ አስታውቀዋል።በሌላ በኩል በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር በኩል ያለው ግጭት ምንም ለውጥ እንዳላሳየ የገለፁ ሲሆን ሱዳን ቀድሞ ወደነበረችበት ስፍራ ስትመለስ ኢትዮጵያ ወደ ድርድር ለመመለስ ዝግጁ መሆኗን ዳግም አረጋግጠዋል።በህዳሴው ግድብ ጉዳይ በተመለከተ የአዲሷ አደራዳሪ አገር ኮንጎ ሪፐብሊክ ልኡካን በካርቱም፣ ካይሮ እና አዲስ አበባ ላይ የየአገራቱን ስሜት ለመረዳት እና መረጃ ለማሰባበስ ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው ብለዋል።በቀጣይ ሳምንታት የተቋረጠው የሦስትዮሽ የህዳሴ ግድብ ድርድር ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባን በተመለከተም ተጠየቀው ምላሽ ሰጥተዋል 0306 ### Response:
### Text: የኢትዮጽያ የሚድያ ህግ ከሴቶችና ህጻናት መብቶች አንጻር በሚል ርዕስ ከሚድያ አካላት እና ከኪነጥበብ ባለሙያዎች ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል።በአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ህጻናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ የኢትዮጵያ የሚድያ አዋጅና ድንጋጌዎቻቸው ከሴቶች እና ህጻናት ጥበቃ አንጻር የተቀመጡት ድንጋጌዎች የቀረቡ ሲሆን ቢሮው የሰራቸውንና በመስራት ላይ ያለው ስራ ቀርቧል።ቢሮው ለዓመታት ስትደፈር ስለቆየች ሴት በአባታቸው ስለተደፈሩ ልጆች ተገለው በመንገድ ስለተጣሉ ልጆች እና0 ሌሎችም በመዲናዋ አዲስ አበባ የተከሰቱ ዘግናኝ ኬዞችን እየተከታተለ እንዳለ አሳውቋል። አንዳንድ ሀኪሞች፣ መምህራን፣ መንገደኞች ፣ ሚድያዎች እና ሌሎችም በሴቶችና ህጻናት ላይ ጥቃት ከሚያደርሱ መካከል እንደሚመደቡም ተነግሯል።በመድረኩ በሀገሪቱ የሚሰሩ ፊልሞችና ማስታወቂያዎች ለአብነትም የዳይፐር፣ የሳሙና፣ የማድ ቤት እቃዎችና ሌሎች ማስታወቂያዎች ላይ የሚሰሩት ሴቶች መሆናቸውን በመጠቆም የማስታወቂያዎቹ አሰራርም የሴቶችን አቅም የሚያዳክምና መሰል ኃላፊነቶች የእነሱ ብቻ መሆናቸውን አመልካች በመሆኑ ሊስተካከል እንደሚገባ ተገልጿል።በመጨረሻም የኪነጥበብ ስራዎች የሴቶችና ህጻናትን መብቶች የሚያከብሩ እና ክብራቸውን የሚጠብቁ ሊሆኑ እንደሚገባና ሚድያውም የራሱን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል። ### Response:
### Text: ስለ ሀገሬ ምን ያህል አውቃለሁ ፊቼ ጨምባላላ የሲዳማ ሕዝብ የጨረቃና ከዋክብትን አቀማመጥ በማጥናት አዲስ ዓመት ያከብራል ይኸው በዓል ፊቼ ጨምበላላ ነው የሚባለው። እንደ ሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች ፊቼ ጫምባላላ መከበር ከጀመረ ከ1800 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል።በዓሉ የሲዳማ ሕዝብ ማንነቱን ከተረዳበት ጊዜ አንስቶ በድምቀት ሲከበር ቆይቷል አሁንም እየተከበረ ይገኛል።ፊቼ ጨምበላላ በዓል የሚከበርበት ቋሚ ቀን የለውም። በዓሉ የሚከበርበት ቀን በአያንቱዎች ጥቆማ መሰረት ነው የሚቃረጠው።የፊቼ ጨምበላላ ዋነኛ ትርጉም ሰላም ነው አንድነትና ፍቅር የበዓሉ መለያ ነው። በዚህ በላይ የተጣሉ ሰዎች ይታረቃሉ። ሃዘን ላይ የነበሩ ሰዎችም የሃዘን ልብሳቸውን ይቀይራሉ።በዚህ በዓል ከቀዬው ርቆ የነበረ ሰው ወደቀዬው ይመለሳል ለዚህ በዓል ተብሎ እርድ አይፈጸምም ስጋም አይበላም። ክብቶችን መምታትም ክልክል ነው። ላሞች ሳር የበዛበት መስክ ላይ ይሰማራሉ።ሌላው በሲዳማ ሕዝብ ዘንድ በፊቼ ጨምበላላ በዓል ወቅት ማረስ ነውር ነው ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮም ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው። ፊቼ የአዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ ሲሆን ጨምበላላ ደግሞ የአዲስ ዓመት መጀመሪያው ቀን ሲሆን የሲዳማ ሕዝብ አዲስ ዓመትን ሲቀበል ዓመቱ የብልጽግና እንዲሆንላቸው ፊቼ ጄጂ ይላሉ።ፊቼ ጄጂ ኢትዮጵያ ሲዳማ ### Response:
### Text: መስከረም 12013 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በሀረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 918 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 7 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 181 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 142 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 44 ከማንዱራ 17 ከአሶሳ 18 ከብልዲግሉ 28 ከካማሽ 13 ከባምቢስ ስደተኛ መጠለያ ይገኙበታል። በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 649 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 77 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 2925 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 48 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ከኬሚሴ ህክምና ማዕከልበቫይረሱ ከተያዙት መካከል 19 ከደወሎ ዞን 12 ከሰወሎ ዞን 5 ከደጎንደር ዞን 5 ከምዕጎጃም ዞን ይገኙበታል። በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 897 የላብራቶሪ ምርመራ 48 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።ቫይረሱ የተያዙት መካከል ከወላይታ ዞን 19 7 ከሶዶ፣ 7 ቢኮይሻ፣ 4 ቦሎሶ ሶሬ እና 1 ጉኑኖ ከተማ ከዳውሮ ዞን 8 7 ከተርጫ ከተማ እና 1 ወረዳ ያልተገለጸ ከጎፋ ዞን 8 6 ቡልቂ ከተማ፣ 1 ከኦይዳ እና 1 ከኡባ ደብረጸሐይ ይገኙበታል። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 91 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 23 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 21 ከሀዋሳ ከተማ 2 ከሁላ ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ 3ኛው ዙር የኮቪድ19 3 ወረርሽኝ እየጀመረ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ነው።በተለያዩ የዓለም ሀገራት መረጃዎች እና ጥናቶች እንደሚያሳዩት 3ኛው ዙር 3 የኮቪድ19 ወረርሽኝ መከሰቱ ታውቋል። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ የኮቪድ19 ዴልታ ቫይረስ ነው። በሀገራችን የኮቪድ19 የዴልታ ቫይረስ መኖሩ ባይረጋገጥም የሶስተኛ ዙር 3 ወረርሽኝ መከሰቱን የሚያሳዩ ምልክቶች መታየት ጀምሯል።በአማካኝ በቀን በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እንዲሁም ወደፅኑ ህሙማን ክፍል የሚገቡ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።ሁለተኛው ዙር 2 ካበቃ በኋላ በተወሰነ መልኩ በማህበረሰቡ የታዩ መዘናጋቶች እንዲሁም የኮቪድ19 መከላከያ መንገዶች በአግባቡ ባለመተግበራቸው ሶስተኛ ዙር 3 ሊከሰት የሚችልበት ምልክቶች እየታዩ ስለሆነ እያንዳንዱ ግለሰብ ፣ ቤተሰብ ፣ ሁሉም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ የሐይማኖት ተቋማት ፣ ሲቪክ ማህበራት ፣ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፣ የጤና ባለሙያዎች ፣ መምህራንና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመከላከል ማስክ ማድረግ ፣ የእጅን ንፅህና በአግባቡ መጠበቅ እና ርቀትን በመጠበቅ በተጨማሪም የኮቪድ19 ክትባት በመከተብ የኮቪድ19 መከላከከል እና መቆጣጠር ተግባር ላይ በባለቤትነትና በኃላፊነት ስሜት አጠናክረው እንዲሠሩ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ማሳሰቢያ አስተላልፏል። ### Response:
### Text: የሊቀመንበሬ እስር በፓርቲው ባላቸው ኃላፊነት አይደለም ኢዜማየኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ኢዜማ የፖርቲው ሊቀመንበር ዶር ጫኔ ከበደ በቁጥጥር ስር የዋሉት በፓርቲው ባላቸው ኃላፊነት ሳይሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በኮማንድ ፖስቱ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉ መሆኑን ገልጿል።ከሊቀመንበሩ እስር በኋላ የብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚው ኮሚቴው መስከረም 19 ቀን 2016 ዓም አስቸኳይ ስብሰባ ማድረጉን የጠቀሰው መግለጫው ከድርጅቱ ዓላማ እና የትግል መስመር ባፈነገጠ መንገድ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ የፀና አቋም ይይዛል። ሲል አስታውቋል።ኢዜማ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጪ በዘውጌ ብሔርተኝነትም ሆነ አፈሙዝ በታከለበት የትግል መንገድ መንቀሳቀስን ድርጅቱ የቆመበትን መርኅ መቃረን አድርጎ ያየዋል። ማንኛውም የኢዜማ አባል ብሎም ከወረዳ እስከ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ድረስ የሚሳተፍ አመራር ከዚህ የድርጅቱ ፅኑ ዕምነት ውጭ የተንቀሳቀሰ እንደሆነ ድርጅቱን ለማፍረስ እንደሚሰራ ተደርጎ እንደሚቆጠር መታወቅ አለበት። ሲል መግለጫው ይጠቅሳል።የፖርቲው ሊቀመንበር ዶር ጫኔ ከበደ ከሰላማዊ ትግል እና ከዜግነት ፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውጭ ያለን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከመደገፍ፣ በሀሳብም ሆነ የተግባር ተሳትፎም ሆነ ትብብር ማድረግ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁሟል።ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል ### Response:
### Text: አሜን በሉህይወት አስቸጋሪ ብትሆንና የሰራኸው ሁሉ ባይሳካ እንኳን አሜን በል ምክንያቱም የተሻለ ቀንና አዲስ የሂወት ምእራፍ ዛሬ ስለተሰጠህ ያልተሳካልህና አስቸጋሪ የሆነብህን ሁሉ በዛሬው አዲስ ቀን መቀየርና ማስተካከል ትችላለህና።ፍቅረኛሽ ጥሎሽ ቢሄድና እሱን መመለስ ወይም መታረቅ የማይቻልበት ሁኔታ ቢፈጠርም አሜን በይ ምክንያቱ እሱ ያንቺ አይደለም ማለት ነው። አንቺ የአቅምሽን ጥረሻልሁኔታዎች ግን ሊመለስ እንደማይችል ነገሩሽ።ዋው ዛሬ ደሞ እንዴት ደስ የሚል አዲስ ቀን በሂወትሽ ላይ ተጨመረልሽ ምናልባትኮ ዛሬ ውስጥሽ በደስታ ከተሞላና ከውስጥሽ ያሉትን የቅሬታ ስሜቶች ሁሉ ካባረርሻቸው የተባረከና ያንቺ የሆነውን የሂወት አጋርሽን የምታገኚበት ቀን ይሆንልሻል። ታዲያ ይሄ አሜን አያስብልምከስራ ብትባረርም አሜን በል። ዛሬ ለአንተ አዲስ አማራጭንና ምናልባትም ትናንት ተቀጥረህ ትሰራበት ከነበረው ስራ የተሻለ ዛሬ ታገኛለህና አሜን በል። ይህኛው ስራህም ከባለፈው የበለጠና ከራስህ አልፈህ ሌሎችንም የምትቀጥርበት ሊሆን ይችላል።ለዶክተሮችበጣም ያስቸገረና የማይድን የመሰላቸው ህመም ቢያሰቃይሽም አንቺ ግን እያመመሽ እንኳን ህመሙንረስተሽ አሜን በይ ያኔ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ ሁሉን ቻይ አምላክ ለዶክተሮቹ የከበዳቸውን ሁሉ ይቀይረዋል አይቻልም ያሉትን ሁሉ ይለውጠዋል። ህይወትሽም አዲስ ይሆናል።️መልካም ቀን️ ### Response:
### Text: በ187 የአለም ሀገራት የሚገኙ ትልልቅ ከተሞች ለ1 ሰዓት ጨለማ ሆኑየአየር ንብረት ለውጥ ጉዳቶችን ለማስገንዘብ የዓለም ከተሞች ለአንድ ሰዓት ያህል ጨለማ ሆኑ። የአየር ንብረት ለውጥ በከባቢ ላይ በሚያመጣው ከፍተኛ ጉዳት ላይ ህብረተሰቡ ግንዝቤ እንዲኖረው ለማስቻል በ187 የዓለም ሃገራት የሚገኙ ትላልቅ ከተሞች ለአንድ ሰዓት ያህል ጨለማ ውስጥ ቆይተዋል፡፡ ይህ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሂደት በየዓመቱ የሚከናወን ሲሆን የብዝሃ ህይወትን ከመጥፋት ለመታደግ ሁሉም የድርሻውን እንዲጠዋ ተጠይቋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በኒዮርክ የሚገኘውን ዋና መስሪያ ቤትና በሌሎች የዓለም ክፍሎች የሚገኙትን ቢሮዎች ብርሃንን በማጥፋት በጨለማ ውጥ ለአንድ ሰዓት እንዲቆዩ አድርጓል፡፡ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአለም ህብረተሰብ ለሰው ልጅ ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአንድነት እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ ከታሰበው በላይ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱንና የምድሪቱ ሃብትና ብዝሃ ህይወት አደጋ ላይ መውደቁን ተናግረዋል፡፡ አካባቢን መታደግ ህይወትን መታደግ በመሆኑ ማንም ችላ ሊለው የማይገባ ጉዳይ መሆኑንገልጸዋል፡፡ የዓለም ሙቀት እየጨመረ በመሄዱ በሺዎች የሚቆጠሩ የእንስሳትና የእጽዋት ዝርያዎች ከምድረ ገጽ የመጥፋት አደጋ እንደተደቀነባቸውም አብራርተዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና️በምሰራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ መርመርሳ በተባለው አካባቢ ዛሬ ጠዋት0 ባጋጠመው የተሽከርካሪዎች ግጭት የአስር ሰዎች ህይወት ማለፉን0 ፖሊስ አስታወቀ።የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር አስቻለውዓለሙ እንደገለፁት ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ተኩል አከባቢ አደጋው የደረሰው ከአዋሽ ሰባት0 ኪሎ ከተማ016 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ አዳማ ሲጓዝ የነበረ ሃይሩፍ የህዝብ ማመለለሻ ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ ይጓዝ0 ከነበረ ዋልያ አገር አቋራጭ የህዝበ ማመላለሻ አውቶቡስ ጋር መርመርሳ በተባለው አካባቢ በመጋጨታቸው ነው።በአደጋው በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ኢት 01289 ሃይሩፍ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ውስጥ የነበሩ ሾፌሩን ጨምሮ 9 ሰዎች ወዲያውኑ ህይወታቸውን አልፏል።በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ኢት 97486 ዋልያ አገር አቋራጭ አውቶቡስ ውስጥ ከነበሩ ተሳታፊዎች መካከል የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን ኮማንደሩ ተናግረዋል።በአደጋው ህይወታቸው ካለፈው ሌላ በአራት ሰዎች ላይ ከባድ በሶስት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን አመልክተው ተጎጂዎቹ በአዳማ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል።የአደጋው መንስኤ አለአግባብ ደርቦ ለማለፍ መሞከርና ቅድሚያ አለመስጠት ነው ያሉት ኮማንደር አስቻለው0 የአውቶቡሱ ሾፌር ለጊዜው ባለመገኘቱ ፖሊስ ክትትል በማድረግ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።ምንጭ ### Response:
### Text: ጠቁሙ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓም ባካሄደው 2ኛ ልዩ ስብሰባው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265 2014 ማጽደቁ ይታወሳል፡፡በአዋጁ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 1 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የዕጩ ኮሚሽን አባላትን ከህዝብ፣ ከፖለቲካ ድርጅቶች ና ከሲቪል ማህበራት እንደሚቀበል ተደንግጓል፡፡ በዚህም መሰረት የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቀበያ ጽቤት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቋቁሟል፡፡በአዋጁ አንቀጽ 13 መሰረት ለኮሚሽነርነት የሚያበቁ መሥፈርቶችም፡1 ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ 2 ሁሉንም ሃይማኖቶች፣ የተለያዩ ብሔሮችን፣ ብሔረሰቦችን እና ሕዝቦችን በእኩል ዓይን የሚያይ3 የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ4 ለአገራዊ መግባባት ጉልህ አስተዋፅዖ ሊያበረክት የሚችል 5 መልካም ሥነምግባርና ስብዕና ያለው6 በሕዝብ ዘንድ ዓመኔታ ያለው፣7 በከባድ ወንጀል ተከሶ የጥፋተኝነት ውሳኔ ያልተላለፈበት 8 የኮሚሽኑን ሥራ በአግባቡ ለመሥራት የሚያስችል የተሟላ ብቃት ያለው 9 ሙሉ ጊዜውን ለኮሚሽኑ ስራ ለማዋል ፍቃደኛ የሆነ።የሚሉ ናቸው፡፡የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ ፡ በቀጥታ ስልክ 0111300340 ወይም 9988 በፋክስ ቁጥር 0111233007 በኢሜል ወይም በ ወይም በአካል በምቤቱ መረጃ ማአከል መስጠት ይቻላል።በቀጣይ ሶስት ቀናት ውስጥ ጠቆማ የሚሰጥበትን ቅጽ እንደሚጭን የህተምክር ቤት አሳውቋል። ### Response:
### Text: ስራ ፈጣሪዎችን ከባለሀብቶች ጋር የሚያገናኝ መተግበሪያ ስሙኒ ምንድነው እንዴትስ ላግኘው ትላንት ስሙኒ የተሰኘ ኩባንያ ከኮካ ኮላ ቢቭሬጅስ አፍሪካኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ስራ ፈጣሪዎችን ከባለሀብቶች ጋር የሚያገናኝ በመተግበሪያ እንዲሁም በድህረገጽ በይፋ አስጀምረዋል።ስሙኒ የሥራ ፈጠራ ባለቤቶችንና ባለሃብቶች ማገናኛ በስራ ፈጠራ ስነምህዳር ውስጥ ያሉ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚገናኙበት እና የሚተሳሰሩበት የኦንላይን መድረክ ነው።መድረኩ የውጭ ኢንቨስተሮች በሀገር ቤት ስታርታአፖች ላይ መዋለ ንዋይ እንዲያፈሱ በማስቻል ምንዛሪ በማስገኘት እንዲሁም የውጭ ኢንቨስትመንት በመሳብ ለኢትዮጵያ የምጣኔ ሀብት እድገት ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ታምኗል።በተጨማሪም በባለድርሻ አካላት መካከል የኢኮኖሚ ትስስርና ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ለሀገሪቱ ዕድገት አስተዋፅዖ ያደርጋል።ኮካ ኮላ ቤቭሬጅስ በስሙኒ መገናኛ መተግበሪያ በኩል በዚህ ዓመት ለ10 ስታርታፖች ለእያንዳንዳቸው 100000 ብር ስራ ማስጀመሪያ ይሰጣል፡፡በተጨማሪም 10000 የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን፣ ወጣት ስራ ፈጣሪዎችን እና አነስተኛ የንግድ ባለቤቶችን አቅም ለመገንባት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የክህሎትና የዕውቀት ድጋፍ በማድረግ ከሌሎች ኢንቨስተሮችን የማገናኘት ስራ ይሰራል፡፡መተግበሪያውን እና ድረገፁን እንዴት ላግኘው ድረገፁ 1395995164 መተግበሪያው = ### Response:
### Text: በሰበብ አስባብ ግጭት አያስፈልግም፣ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ለውጥ ውስጥ ላለ አገር አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ነገር ነው ታስሮ የተፈታውም ድጋሜ ይገባል አይገባም ድንጋይ ወርውሮ ይሞክራል፣ ዴሞክራሲ ዝም ብሎ የተከፈተ ስለሚመስል ሰው ራሱን ለመግራት ይቸገራል፡፡ ነገር ግን ይህ ጉዳይ ወደ ሁለት ነገር ነው የሚያመራው፡፡ አንደኛው በብስለት መብትን መጠየቅና ግዴታን መወጣት ድንበር እንዳለው አውቀን ወደተሻለ ዴሞክራሲ የሚያሸጋግረን ይሆናል፣ ወይም ደግሞ የለየለት አምባገነን መንግስት እንዲፈጠር ይሆናል። አምባገነን መንግስታት የሚፈጠሩት በህዝባቸው ምላሽ ነው የሚባለው ለዚህ ነው፡፡ ውሃ ቀጠነ እያልን መኪና የምንሰባብር ከሆነ መንግስት ፖሊስ ስላለው የተለመደውን ነገር ማድረጉ አይቀርም፡፡ መንግስት ወደዚያ እንዳይገባ ህዝብ፣ ማህበረሰብ በበሰለ መንገድ እያንዳንዱን እንቅስቃሴ መፈተሽ ያስፈልጋል፡፡ ክፍት ነው ብለው ሕግን ሕገ መንግስትን እየጣሱ መሄድ ተገቢ አይደለም፡፡ ሕገ መንግስቱ ችግር ያለው እንደሆነ በውይይት፣ በምክክር፣ የህዝቡን ፍላጎት ታሳቢ አድርጎ ማሻሻል ይቻላል፡፡ ሕጉ እያለ ያንን የሚተላለፍ ነገር ማድረግ ይጎዳናል፡፡ ጥያቄ ያለው ማንኛውም ኃይል ሌላውን ሰው ሳያውክ ጥያቄውን ማቅረብ ይችላል፡፡ እኔ ስረብሽ ሁላችሁም ቁሙ ከሆነ ግን ጸረ ዴሞክራሲ ነው፡፡▪️▪️ ጠሚ ዶር አብይ አህመድ▪️▪️ ### Response:
### Text: ኢዜማ ያለምንም ህጋዊ መሰረት ንብረቶቻችንን እየተጠቀመ ስለሆነ ሊመልስልን ይገባል ኢዴፓ በህገወጥ መንገድ የያዝሁት ምንም ንብረት የለም ኢዜማየኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ ከኢዴፓ አፈንግጠው በወጡ አራት አባላት የተሰጠውን የፓርቲው ንብረቶች ያለምንም ህጋዊ መሰረት እየተጠቀመ ስለሆነ ሊመልስልን ይገባል ሲል ኢዴፓ ጥሪ አቅርቧል ኢዜማ በበኩሉ በህገወጥ መንገድ የያዝሁት ምንም ንብረት የለም ብሏል፡፡ከኢዴፓ አፈንግጠው የወጡ አራት ግለሰቦች በምርጫ ቦርድ ፍፁም ህገወጥ የሆነ ትብብር የፓርቲውን ፅህፈት ቤቶች፣ በባንክ የተቀመጠ ገንዘብ፣ መዛግብትና ማህተም ያለአግባብ በህገወጥ መንገድ እንዲረከቡ ተደርጓል ያለው ኢዴፓ ግለሰቦቹ ኢዴፓ ከግንቦት 7 ጋር እንዲዋሀድ የኢዴፓ ጠቅላላ ጉባኤ ተሰብስቦ እንደወሰነ አድርገው የሀሰት መረጃ በማቅረብ ንብረቶቹን በፓርቲዎች ውህደት ሳይሆን በግለሰቦች ስብስብ ለተቋቋመው ኢዜማ ማስረከባቸውን የኢዴፓ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከትናንት በስቲያ በሰጠው መግለጫ ጠቅሷል፡፡ ኢዜማም ያለምንም ህጋዊ መሰረት እነዚህን የኢዴፓ ንብረቶች እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝ የጠቀሰው ማእከላዊ ኮሚቴው በዚህ የተነሳ የእለት ከእለት ስራዎችን በአግባቡ ለማከናወን መቸገሩን ገልፆ ኢዜማ ግለሰቦቹ የፈፀሙትን የማጭበርበር ወንጀል ተረድቶ ንብረቶችን እንዲመልስ ጠይቋል፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 0823 ### Response:
### Text: የብር የምንዛሬ ለውጥ ሊደረግ ነው የሚናፈሰው ወሬ ሁሉ ሀሰት ነው አቶ ማሞ ምህረቱበኢትዮጵያ የገንዘብ ምንዛሬ ተመን ማስተካከያ ሊደረግ ነው በሚል የሚናፈሰው ወሬ ሀሰት ነው ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳውቋል።የባንኩ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ እስከዛሬ ድረስ እስካሁን ድረስ በአንድ ጊዜ የሚደረግ የብር የምንዛሬ ተመን ለውጥ ለማድረግ የተደረገ ውይይትም፣ የተወሰነ ውሳኔ ፈፅሞ የለም ብለዋል።የብር የምንዛሬ ለውጥን በተመለከተ የተደረገ ውይይት ወይም የተወሰነ ውሳኔ የለም ያሉት አቶ ማሞ ዜጎች በተረጋጋ ሁኔታ በገበያ ስርዓቱ እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።አቶ ማሞ ምህረቱ በማህበረሰቡ ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ መንግሥት የብር የውጭ ምንዛሬን ለውጥ በማድረግ ሊያደርግ ነው የሚል ብዙ ወሬ አለ ይሄን ተከትሎ ገበያ ውስጥ ስካር በሚባል ሁኔታ ሰዎች አንዳንዴ እቃ ይይዛሉ አንደንዴ ደግሞ መሰረታዊ በሚባሉት እቃዎች ላይ አላስፈላጊ የሆነ ዋጋ ይጨምራሉ ከዛም አልፎ የኢኮኖሚ ጥቅም በሌለው ጉዳይ ላይ ያላቸውን ገንዘብ ኢንቨስት ያደርጋሉ ይሄ ፈፅሞ ትክልል ያልሆነና ሊስተካከል የሚገባው ጉዳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።ከሰሞኑን በተለይ በመዲናዋ መንግሥት የብር የውጭ ምንዛሬን ለውጥ በማድረግ ሊያደርግ ነው በዚህም መሰረታዊ እና ሌሎች ቁሶች ዋጋ ሊጨምር ይችላል የሚል ወሬ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ### Response:
### Text: ጦላይ️በጦላይ ስልጠና ላይ ባሉ የኦነግ አባላት ላይ ምንም አይነት የከፋ ጉዳት አለመድረሱን የኦሮሚያ ክልል አስታወቀ። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ስልጠና ላይ ያሉ የኦነግ አባላት የገጠማቸውን የጤና እክል መነሻ ምን እንደሆነ ፖሊስና የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ እያደረጉ ነው። ውጤቱ ሲታወቅም ለህዝብ ይፋ ይደረጋል ብለዋል ።ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ከሰሞኑ በአባላቱ ላይ የምግብ መመረዝ አጋጥሟል በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑንም አቶ አድማሱ ገልፀዋል።የጤና እክል የገጠማቸው 136 የሚሆኑ የሰራዊቱ አባላት በወሊሶ ሉቃስ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን ምንም አይነት የከፋ የጤና ችግር እንደሌለባቸውም ተረጋግጧል ብለዋል። መንግስት በስልጠናው ላይ የምግብ የመኝታና የጤና እንዲሁም ሌሎች አቅርቦቶችን ማሟላቱንም የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊው ገልፀዋል።በማህበራዊ ሚዲያ በሰራዊቱ አባላት ላይ የምግብ መመረዝ ደርሶባቸዋል ሰራዊቱ ላይም ይህ ነገር እንዲደርስ ተደርጓል በሚል አየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች ውሸት መሆናቸውን ሀብረተሰቡ ተገንዝቦ ትክክለኛውን መረጃ ከመንግስት ሊያገኝ እንደሚገባ ተናግረዋል። በጦላይ ወታደራዊ ካምፕ በስልጠና ላይ የሚገኙ የኦነግ ሰራዊት አባላት ከ1ሺህ በላይ እንደሆኑ ተገልጿል። ### Response:
### Text: በየወሩ እስከ 18 ሺህ ብር እያወጡ የኩላሊት እጥበት ወይንም ዲያሊስስ ህክምና ሲወስዱ የቆዩ 29 ህሙማን ህክምናቸው በነፃ ሊሆንላቸው ነው፡፡በዘውዲቱ ሆስፒታል የኩላሊት እጥበት ህክምና ሲያገኙ የነበሩ 20 ታካሚዎችና በየመንገዱ እርዳታ እየለመኑ በግል የሕክምና ተቋማት ሲታከሙ የቆዩ 9 የኩላሊት ህመምተኞች ህክምናቸውን ከነገ ጀምሮ በነፃ ያገኛሉ ተብሏል፡፡ ይህን ያለው የኩላሊት ህመመተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ነው፡፡29ኙ ህሙማን በዘውዲቱ ሆስፒታል በነፃ የኩላሊት እጥበት ህክምናውን እንዲያገኙ የተደረገው የተለያዩ 5 ባንኮች በሰጡት የገንዘብ ድጋፍ ነው ብለዋል ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ሰለሞን አሰፋ፡፡ባንኮቹ ከበጎ ፈቃደኛ ሰራተኞቻቸውና ከደንበኞቻቸው በሚሰበስቡት ገንዘብ ህሙማኑ የሚታከሙበትን በአመት ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ይከፍላሉ ብለዋል አቶ ሰለሞን፡፡ዋና ስራ አስኪያጁ ለሸገር እንደተናገሩት ማህበሩ ህሙማኑ የዲያሊስስ ህክምና እንዲያገኙ በወር እስከ 4 ሺህ ብር ወጭ ያደርጋል፡፡ህክምናው በመንግስት በወር 4 ሺህ ብር በግል የህክምና ተቋማት ደግሞ እስከ 18 ሺህ ብር ይጠይቃል ብለዋል፡፡በግላቸው የሚታከሙት በህክምናው ውድነት ምክንያት ጥሪታቸውን አሟጥጠው በሕይወት ለመቆየት በየመንገዱ የሚለምኑም እንደነበሩ አስታውሰው አሁን ሁሉም ጎዳና ላይ ሲለምኑ የነበሩ 9 ሰዎች በነፃ ሊታከሙ ቃል ገብቷል ብለዋል፡፡ ### Response:
### Text: ሁላችን ከተባበርን የማንፈታው ችግር የለም ዶር ደብረጽዮን ገሚካኤልሁሉም ሕብረተሰብ በሚችለው ከተባበረ የማንፈታው ችግር እንደማይኖር የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ።ዶር ደብረጽዮን ገሚካኤል በሰሓርቲ ሳምረ ወረዳ የበሪ ሜዳ ሆስቴልና የሴት ተማሪዎች ትምህርት ማዕከል ምርቃት ስነ ስርዓት ላይ እንደተናገሩት የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ባለሃብቶችና የአካባቢው ሕብረተሰብ ይህንን የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ችግር የሚፈታ ህንፃ ገንብቶ ለአገልግሎት ማብቃቱ የሚመሰገን ነው።ዶክተር ደብረጽዮን አያይዘውም በተመሳሳይ መልክ የህዝብን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ ሌሎች የልማት ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።በተለይ ትምህርት ላይ የሚደረግ ልማት ለሁሉሞ ቁልፍ ሲሆን የሴት ተማሪዎችን በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ችግር መፍታትና ማስተማር ደግሞ ሁሉንም ሕብረተሰብ ማስተማር በመሆኑ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።ዋናው ነገር ከዚህ ሆስቴልና የትምህርት ማዕከል መገንባት በስተጀርባ ያለው የእንችላለን አስተሳብ መሆኑን የጠቆሙት ዶር ደብረጽዮን ሌሎች በጎ አድራጊ ድርጅቶችና ባለሃብቶች ህብረተሰቡን በማስተባበር የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱ ስራዎችን እንዲያከናውኑ አደራ ብለዋል።ማዕከሉ የተሰራው በበጎ አድራጊዎች ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚማሩ 160 ሴት ተማሪዎችን ተጠቃሚ ሆነዋል። ### Response:
### Text: በጉሊሶ ወረዳ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ሰዎች ተገደሉ ትላንት ጥቅምት 22 በኦሮሚያ ክልል ግንቢ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቃናቱ በተባለ ቀበሌ እስካሁን ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በታጣቂዎች መገደላቸውን የቲክቫህ አባላት ገልፀዋል።ጥቃት የፈፀሙት ታጣቂዎች በቁጥር ከሃምሳ 50 እስከ ስልሳ 60 የሚደርሱ መሆናቸውን ከሞት የተረፉ ሰዎች ተናግረዋል።ላለፉት 3 ወራት ሰፍሮ የቆየው የመከላከያ ሰራዊት ከረፋዱ 6 ሰዓት አካባቢው ለቆ እንደወጣም ነዋሪዎች ገልፀዋል።መከላከያው ከወጣ በኃላ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የመከላከያ ካምፕን በመቆጣጠር ከፍተኛ ጥይት ሲተኩሱ መዋላቸውን ነዋሪዎች አሳውቀዋል።በሌላ በኩል በፅሁፍ መልዕክታቸውን ያስቀመጡ የቲክቫህ አባላት እንደገለፁት ጥቃቱ በከባድ መሳሪያዎች ጭምር የተፈፀመ ነው።የኦሮሚያ ክልል መንግስት ይህን ጭካኔ የተሞላበት ጥቃት የፈፀመው ኦነግ ሸኔ ነው ብሏል የገቡብት ገብተን እርምጃ እንወስዳለን ሲል ዝቷል።ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአካባቢውን አባላትና ከጥቃቱ የተረፉትን ሰዎች እያነጋገረ ነው ተጨማሪ መረጃ ይዘን እንመሳለን።በተጨማሪ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ሰዎች ለተለያዩ ሚዲያዎች የሰጧቸው አስተያየቶች እያሰባሰብን ነው አደራጅተን እናሳውቃለን።በርካቶች እየተደጋገመ የመጣውን ጥቃት እና የንፁሀን ሞት በከፍተኛ ሁኔታ እያወገዙ ይገኛሉ ቁጣቸውንም እየገለፁ ይገኛሉ። ### Response:
### Text: በአዲስ አበባ የመሬት ስም ዝውውርና የኮንዶሚኒየም ሽያጭ ስም ዝውውር የታገዱ ሰፈሮችን የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ይፋ አድርጓል።በተለዩት ሰፈሮች የሚገኙ ይዞታዎች የኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶችንና ሌሎችንም ጨምሮ የስም ዝውውርና ሌላውም እስከ ጳጉሜ መታገዱ ተገልጿል።ከእነዚህ ሰፈሮች ውስጥ በአራዳ ክከተማ ሐግቤስ አካባቢ ፣ ጅንአድ ራስ እምሩና አግአዚ ሰፈር የካ ክፍለ ከተማ ኪዳነ ምህረት ሰፈር ዞን 03 ፣ ሲግናል ሲግናል አፓርትመንት እና ቡና ቦርድ ኮልፌ ክከተማ አርሴማ ሰፈር ፣ አየር ጤና ለማ ነጋገዎ ሰፈር ፣ እፎይታ አየር ጤና መሰናዶ አካባቢ ፣ ሞቢልና መሳለሚያና ሌሎችም በቦሌ ክፍለ ከተማ ጅማ ህንፃ ፣ 24 ቀበሌ ውሃ ልማት ወይም ቅርቦትና ሌሎችንም ሰፈሮች በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቀጠና 2 ላይ ሰፈረ ሰላም ጭማድ ፣ ሰላሌ ሰልጤ ማርያም፣ መኮድ ጃቴ ኪዳነ ምህረትና ሌሎችም በልደታ ክፍለ ከተማ ማዕድን ሚኒስቴር ድል ገበያ ሰባራ ድልድይ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቃጤ ሰፈር ድላችን ኮንዶሚኒየም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክከተማ ላፍቶ ኢንዱስትሪ ሰፈር ፣ ላፍቶ መድሃኒያለም አካባቢ ፣ 54 ማዞሪያ አካባቢ ፣ ላፍቶ 1 ኮንዶሚኒየም በሙሉ የመሬት ሽያጭና ስም ማዛወር እስከ ጳጉሜ አምስት ድረስ ለ5 ወር ታግዶ ይቆያል።ምንጭ ሸገር ኤፍ ኤም 1021 ሬድዮ የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ### Response:
### Text: የመጨረሻ የሰላም ጥሪ️የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአንዳንድ አካባቢዎች ግጭቶችን ለሚፈጥሩ አካላት ወደ ሰላም እንዲገቡ የመጨረሻ የሰላም ጥሪ አቀረቡ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ዛሬም በሚያሳፍር ሁኔታ ሰዎች ይሞታሉ በማለት ንግግር ያሰሙ ሲሆን ይህ እንዲያበቃም እባካችሁ ወደ ሰላም ግቡ ይህየመጨረሻ የሰላም ጥሪዬ ነው ብለዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ እና በአስመራ መካከል ያለው የጥላቻ ግንብ መንዳቱን አንስተው በአንዳንድ ክልል ያለው የሳር ቀጤማ ግንቦች ይፍረሱ በማለት ጥሪ አቅርበዋል፡፡የዛሬው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ይዘው የመጡት ፍቅር በ50 ቢሊየን ብር የማይገዛ ውድ ነው ብለዋል፡፡እንዲሁም ዛሬ የተቀደደው ጥቁር መጋረጃ ነው የሚበጀን ፍቅርና ሰላም ብቻ ነው ሲሉ ንግግር አድርገዋል፡፡በተጨማሪም የሰላም ዋጋው ያልገባቸው አካላት በአንዳንድ አካባቢዎች ግጭቶች እንደሚያስነሱ ጠቅሰው ዛሬ እንኳ ስለ ሰላም ተማሩ በማለት ጥሪአቅርበውላቸዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወስጥ የሰዎች ሞት ማብቃት አለበት ያሉ ሲሆን የሰላም ጥሪያቸውን አጽንዖት በመስጠት አስተላልፈዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመጨረሻም አልፎ አልፎ የምታውኩን ሰዎች ፍቅራችንን ባታበላሹት መልካም ነው ነግርግን ግጭቶች በዚህ የሚቀጥሉ ከሆነ ሰውነንና ወዳልተፈለገ ነገር እንዳታስገቡን አደራ እላለው ብለዋል፡፡© ### Response:
### Text: ኮቪድ19 በህንድ ዛሬ 368147 አዲስ የኮሮና ቫይረስ ተያዦች ተመዝግበዋል። በየቀኑ ከ300000 በላይ አዲስ የቫይረሱ ተያዥች ሲገኙ ዛሬ 12ኛ ቀን ነው። ከዓለም የሚበዛው የኮቪድ19 ክትባት የሚያመርተው ዘ ሴረም ኢኒስትቲዩት የተባለው የመድሃኒት አምራች ተቋም የሚገኘው ህንድ ውስጥ ሆኖ ሳለ ከ1 ነጥብ ሦስት ቢሊዮኑ ህዝቧ የተከተበው ሁለት ከመቶው ብቻ መሆኑ ታውቋል። የአሜሪካ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ጽህፈት ቤት ሹም ሮን ክሌይን ለሲቢኤስ ቴሌቭዥን በሰጡት ቃል ለህንድ በጥድፊያ እርዳታ በመላክ ላይ ነን ብለዋል። አሜሪካ ያን እያደረገች ቫይረሱ እንዳይስፋፋ ለመከላከል ርምጃዎች በመውሰድ ላይ ናት ብለዋል። አሜሪካ ከነገ ማክሰኞ ጀምሮ ከህንድ በረራዎች አታስገባም። አውስትራሊያ ከህንድ በረራ እንዳይገባ ከልክላለች። ወደህንድ ተጉዞ ሲመለሱ የሚገኙ አውስትሬሊያውያን በገንዘብ እና በእስራት ሊቀጡ ይችላሉ።በሌላ የኮቪድ19 መረጃ ኢንዶኔዥያ ሁለት የተቀየሩ የኮሮናቫይረስ ዝርያዎች ሃገርዋ መግባታቸውን አስታውቃለች። አንደኛው ከደቡብ አፍሪካ ሌላው ከህንድ መሆኑን ነው የገለጸችው። ይህንኑ ተከትሎ የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል ሲዲ ተጓዥች ወደኢንዶኔዥያ ከመሄድ እንዲቆጠቡ መክሯል። የኮቪድ መከላከያ ክትባት የወሰዱ ሰዎችም ቢሆኑ በልውጦቹ ቫይረሶች ሊያዙ እና ሊያዛምቱ እንደሚችሉ ነው ሲዲሲ ያሳሰበው።ምንጭ ቪኦኤ ### Response:
### Text: 5 እኔምየዕርቅሀሳብአለኝ ዘወልድ የራያ ቆቦ ማህበረሰብ ባህላዊ የእርቅ ስርዓት)አዘጋጅ ዮሐንስ ቢሰጥእንደ አሁኑ ዘመናዊ የፍትህ ስርዓት ባልሰፈነበት ጊዜ በራያ አካባቢ የሚኖሩ ማህበረሰቦች የአካባቢያቸውን ባህል መሰረት በማድረግ ህግ አውጥተው ይተዳደሩና በመረጧቸው ሽማግሌዎች ይዳኙ ነበር ፡፡ የዘወልድ ሽማግሌዎች የዕርቅ ሥነስርዓት ከጠፋው የሰው ልጅ ህይወት ተጨማሪ የአካልና የህይወት እንዲሁም የንብረት ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል ስራ ይሰራሉ፡፡ የሽምግልና ሂደቱን የሚመሩት አባቶች የሚመረጡት በአካባቢው ማሕበረሰብ ሲሆን መስፈርቱም አርቆ አሳቢነት፣ ታማኝና ሐቀኛ የሆኑ፣ የችግር ቋጠሮ የመፍታት እይታቸው ላቅ ያለ አባቶችን በመመልመል ይሰይማል፡፡ ከዕርቅ ሽማግሌዎች አፈንግጦ የሚወጣ ተበዳይ የአካባቢውን ማህበረሰብ በመሰብሰብ እንበደዲ በማለት ይወስናሉ፡፡ እንበደዲ ማለትም ይህን ግለሰብ ተበዳይ ከማንኛውም የማህበራዊ ህይወት ማግለል ማለት ነው፡፡ ከወንድ ሽማግሌዎች ባልተናነሰ ሁኔታ በአካባቢው መጠሪያ የዱበርቲዎች ወይንም የሴቶች ሚና የሟች ቤተሰብ የበቀልና የቁጭት ስሜት እንዳያሳዩ ልብ የሚያራራ የምልጃና የልመና ዜማ ለሟች ቤተሰቦች ያቀርባሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በዕርቁ ዕለት ምግቡን በማቀራረብና ሟችና ገዳይ አብረው እንዲበሉ በማድረግ ይቅር ባይነትን ያስተምራሉ።ሙሉውን ከላይ በ ያንብቡ ### Response:
### Text: ሞያሌ️በሞያሌ ከተማ በተከሰተ ግጭት 21 ሰዎች መሞታቸውንና 61 ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱን የሶማሌ ክልል0 መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ0 ገለጸ።በሞያሌ ከተማና አከባቢዋ የሚከሰቱ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ውይይት እየተደረገ ነው።የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሱረውመሐመድ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት በዜጎች ላይ ጉዳቱ የደረሰው ባለፉት ሁለት ቀናት በደረሱ ግጭቶች ነው።በግጭቱ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ወገኖችን ለመርዳት ሁለት ቡድኖች ወደ አካባቢው ተልከው ሕክምና መስጠት መጀመራቸውን ገልጸዋል።በግጭቱ ከተፈናቀሉት ወገኖች የተወሰኑት ወደ ኬንያ መሰደዳቸውንም አቶ መሐመድ ተናግረዋል።በመከላከያ ሠራዊት ካምፕ ለተጠለሉ ተፈናቃዮች ደግሞ የክልሉ መንግሥት እርዳታ ለማቅረብ እንቅስቃሴ ጀምሯል ብለዋል።በሞያሌ ከተማና አከባቢዋ የሚከሰቱ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የፌዴራል፣የሶማሌና የኦሮሚያ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮችና ባህላዊ መሪዎች እየተወያዩ መሆናቸውን ገልጸዋል።የክልሉ መንግሥት በሞያሌ ከተማና አካባቢውና የሚታዩ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን ምክትል ኃላፊው አስታውቀዋል።ሕዝቡ የሁለቱ ክልሎችን ሕዝብ ወደ አላስፈላጊ ግጭት ውስጥ ለማስገባት የሚንቀሳቀሱ አካላትን እንቅስቃሴ ለማክሸፍ እንዲረባረብ አቶ መሐመድ ጠይቀዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ህብረተሰቡ ለእኛ ያለው አመለካከት ሊሻሻል ይገባል የቀድሞ የኢትዮጵያ የሰራዊት አባላት️ህብረተሰቡ ለእኛ ያለው አመለካከት ሊሻሻል ይገባል ሲል በቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት የተቋቋመው የድጋፍና የልማት ማህበር ጥሪ አቀረበ፡፡ማህበሩ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሰራዊቱ ህብረተሰቡ ለእኛ ያለው አመለካከት ሊቀየር ይገባል ልክ እንደ ጨፍጫፊ ነው የሚመለከተን ይህ አመለካከት ሊቀር ይገባል ብሏል፡፡ማህበሩ ለቀድሞ የኢትዮጵ ሰራዊት አባላትንና ቤተሰቦቻቸው የድጋፍና እገዛ ስራዎችን ለመስራት ታልሞ የተቋቋመ ማህበር መሆኑን በመግለፅ የማህበሩ ዋና አላማ ማህበረሰቡ ለሰራዊቱ ያለውን መጥፎ አመለካከትን ማስቀየርና የተጎዱ የሰራዊቱን አባላት በመርዳት እንደሆነ መቶ አለቃ ሰለሞን ገልፀዋል፡፡ማህበሩ ስራውን በሁለት አባላት የጀመረ ሲሆን አሁን ላይ 1 ሺህ 200 ደርሷል ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ሶስት ወርሀዊ ጉባኤዎችን አካሂዷል ተብሏል፡፡የቀድሞ የኢትዮጵያ የሰራዊት የድጋፍና የልማት ማህበር በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ እየተፈጠረ ያለውን የኢትዮጵያዊነትንና የአንድነትን ስሜት እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ ሰፋፊ ስራዎችን ለማከናወን አቅዶ ወደ ስራ መግባቱን መቶ አለቃ ሰለሞን ተናግረዋል፡፡የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት የድጋፍና የልማት ማህበር ባሳለፍነው ጥቅምት ወር መመስረቱ ይታወሳል፡፡ምንጭ ኢፕድ ### Response:
### Text: 1 ሺህ 323 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ ተመሰረተ በ2011 በጀት አመት በተለያዩ ክልሎች በተፈጠሩ ግጭቶች ተሳትፈዋል በተባሉ 1 ሺህ 323 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ፡፡በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ 1 ሺህ 229 ሰዎች ህይዎት ያለፈ ሲሆን በ1 ሺህ 393 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ19 ሰዎች ላይ የግድያ ሙከራ መደረጉን በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁ ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ ገልፀዋል፡፡በግጭቶቹ ከ22 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዜጎች ንብረት የወደመ ሲሆን 12 ሚሊዮን ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸውና ከአካባቢያቸው ተፈናቅለዋል። ከተከሳሾቹ መካከል 645 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ሲሆን 667 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎች ደግሞ በቁጥጥር ስር አልዋሉም፡፡ የ10 ተጠርጣሪዎች ክስም በምህረት መነሳቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡በመጨረሻም አቶ ፍቃዱ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረግ እንቅስቃሴ ዙሪያ የሚስተዋለው ክፍተት አስመልክቶ መፍትሔ ያሉትን ሀሳብ ሲጠቁሙ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከፍትህ አካላት ጎን በመቆምና ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ በመስጠት በኩል በጉዳዩ ላይ በባለቤትነት ስሜት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽእኖት ሰጥተው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ 09246 ምንጭ የፌደራል ጠቃቤ ህግ ### Response:
### Text: ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተከናወነው የላብራቶሪ ምርመራ 519 ሲሆን ከእነዚህ መካከል ነው ዘጠኝ 9 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው። የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ታማሚ 1 የ60 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸው በለይቶ ማቆያ የሚገኙ።ታማሚ 2 የ10 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም በለይቶ ማቆያ የምትገኝ።ታማሚ 3 የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም በለይቶ ማቆያ የምትገኝ።ታማሚ 4 የ12 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም በለይቶ ማቆያ የምትገኝ።ታማሚ 5 የ42 ዓመት ኢትዮጵያዊ የሰንዳፋ ቤኬ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የለውም በለይቶ ማቆያ የሚገኝ።ታማሚ 6 የ3 ዓመት ህፃን ኢትዮጵያዊ የጉጂ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የለውም በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያለው።ታማሚ 7 የ14 ዓመት ኢትዮጵያዊት የጉጂ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላት።ታማሚ 8 የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ የምዕራብ ወለጋ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የለውም ከማህበረሰቡ የተገኘ።ታማሚ 9 የ48 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ነዋሪ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው ድንበር ተሻጋሪ መኪና አሽከርካሪ ምርመራው የተደረገው ነቀምቴ ላብራቶሪ ነው ### Response:
### Text: የሂዩማን ራይትስ ዎች ሪፖርት እና የመንግስት ምላሽ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ትላንት ረቡዕ ባወጣው ሪፖርት ከሳዑዲ አረቢያ የተመለሱ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ የመብት ጥሰት መፈጸሙን ገልጿል።ተቋሙ በሪፖርቱ ከስደት ተመላሾቹ ላይ የዘፈቀደ እስር እና እንግልት ደርሶባቸዋል ደብዛቸውም ጠፍቷል ብሏል።የሂዩማን ራይትስ ዎች የስደተኞች እና የስደተኛ መብት ተመራማሪ ናዲያ ሃርድማን በሳዑዲ እስር ቤት አሰቃቂ በደል የደረሰባቸው የትግራይ ተወላጆች ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ በማቆያ እስር ቤቶች እየተቆለፉ ይገኛሉ ብለዋል።ሙሉ ሪፖርቱ 20220105 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለሱ የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ ሂዩማን ራይትስ ዎች በትላንትናው ዕለት ያወጣው ሪፖርት ድርሰት ነው ሲሉ አጣጥለውታል።አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የተቋሙ ሪፖርት በኢትዮጵያ ላይ እየተደረጉ ያሉ ጫናዎች አካል ነው ብለዋል።በሰፈር፣ በማንነት የተለየ እና የተጎዳ ሰው አልነበረም። እንደዚያ አይነት አሰራርም አልነበረም ያሉት አምባሳደር ዲና ሂዩማን ራይትስ ዎች ኢትዮጵያን በሚመለከት መዓት ድርሰቶች አሉት ይሄም ከድርሰቶቹ አንዱ ነው ብለውታል።በጉዳዩ ላይ ከዚህ በላይ ማብራሪያ የሚሰጠበት እንዳልሆነም ተናግረዋል።ምንጭ ኢትዮጵየ ኢንሳይደር ### Response:
### Text: ከውሸት ዜናዎች ተጠንቀቁ።በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ባባ በህይወት በነበረበት ሰዓት የዓይን ብሌኑን ለመለገስ ቃል በገባው መሰረት የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ የአርቲስቱን ቃል ተፈፃሚ ማድረጉ አይዘነጋም።ነገር ግን ከአርቲስት ታሪኩ ጋር በተያያዘ በዩትዩብ እና በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ሀሰተኛ ዜናዎች እና መልዕክቶች እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ አሳውቋል።የዓይን ባንኩ የታዋቂው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ዓይን ለመጋቢ ሃድስ እሸቱ አለማየሁ ተሠጠ ተብሎ በዩትዩብ የሚተላለፈው ዜና የወሸት ዜና መሆኑን ገልጿል።በተጨማሪ የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ተደርጎላቸው ኪድ ኢትዮጵያ በተሰኘ ዩትዩብ ላይ ቀርበው ቃለመጠይቅ ያደረጉ ታሪኩ ሁሴን እና ሜላት ተሰማ የተባሉ ታካሚዎች ጣቢያው ላይ ካደረጉት ቃለ መጠይቅ አውድ ውጭ በመውሰድ የአርቲስት ታሪኩ የዓይን ብሌን የተሰጣቸው እያሉ የተለያዩ ዩቱበሮች እና የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚወች ቻናሉ ላይ ያልተላለፈውን መልእክት እያሰራጩ መሆኑን የዓይን ባንክ ገልጿል።ወጣቶቹ ከተሰራላቸው ከአንድ አመት በላይ0 እንደሆናቸው የገለፀው ባንኩ እነሱም የሱ የተሰራልን ነን ብለው ምንም አይነት መልዕክት አላስተላለፉም ብሏል።0 የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ የተለገሱ የዓይን ብሌኖች የሚነሱት በኮድ ስለሆነ የማን ለማን እንደተሰራ አይታወቅም ሲልም አሳውቋል። ### Response:
### Text: በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ሁከት ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ሰላምና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘው ተሻገር ተናገሩ በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ትናንት በተከሰተው ችግር ዙሪያ የአማራ ክልል ሰላምና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘው ተሻገር እየተካሄደ በሚገኘው 5ኛ ዙር 5ኛ አመት 14 መደበኛ ጉባኤ ላይ ወቅታዊ የክልሉ የጸጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ለክልሉ ምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ትናንት ምሽት ላይ ተማሪዎች እግር ኳስ እየተመለከቱ እያለ በደጋፊዎች መካከል ግጭት ተከስቶ ነበር፡፡ግጭቱን የሚፈልጉት ሀይሎች ስለነበሩ ግጭቱን ወዲያውኑ የብሔር ግጭት አደረጉት በዚህም ተማሪዎች ተጎድተዋል ብለዋል፡፡በአሁኑ ሰአት የተፈጠረውን ግጭት አረጋግተነዋል በዚህ ወንጀል ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩትንም በቁጥጥር ስር አውለናል በማለት አቶ አገኘሁ ተናግረዋል፡፡በአማራ ክልል በሚገኙ አስሩም ዩኒቨርሲቲዎች ሰላም እንዲደፈርስ አቅደውና አልመው የሚሰሩ ሀይሎችን ለይተን እርምጃ ለመውሰድ እየተንቀሳቀስን ነው ሲሉም ለምክር ቤቱ ገልጸዋል፡፡በዚህም በግለሰቦች መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶችን ወደ ብሔር ግጭት ለመውሰድ የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን ለመታገል የምክር ቤት አባላት እና መላው የክልሉ ህዝብ ከጸጥታ ሀይሉ ጎን በመሆን እንዲተባባር ቢሮ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ### Response:
### Text: ዶር ደብረፅዮን ገሚካኤል የካቲት 11ን አስመልክተው ከመቓልሕ ትግራይ መፅሄት ጋር ባደረጉት ቆይታ የተናገሩትብሄራዊ ጭቆና ነበር ሲያጣላን የነበረው እሱን የሚፈታ በህገ መንግስት ደረጃ መጣ ስለዚህ የትግል ውጤት ነው። እሱም አንድነትን አምጥቷል። ሁሉም የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች እኩል ናቸው። ስለዚህ ትልቅ ትንሽ የሚባል ነገር ፈረሰ ማለት ነው። ትልቅ ድል ደግሞ ህገ መንግስት ነው።ክልሎችም እራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩበት ዕድልም ተፈጥሯል። አንዱ ቋንቋ፣ ባህል ከሌላው ቋንቋና ባህል ይጣጣል ነበር እሱም ተወግዷል። በአጠቃላይ በመረጥነው እንድንተዳደር ተደርጓል። ማንም ተነስቶ ነበር የሚያስተዳድረው አሁን ግን ማስተዳደር የሚችል ብቃት ያለው ሰው ይመረጣል። በአጠቃላይ ስርዓቱ ተቀይሯል። በመታገላችንና መስዋዕት በመክፈላችን የደርግን ስርዓት አፈረስን ቀበርን ብቻ ሳይሆን ቀልጣፋ የሆነ እድገት ማሳየት የጀመርንበት ጭምር ነው። ከድህነት መውጣት ጀመርን ስለዚህ የትጥቅ ትግሉ ውጤት አንደኛ ደርግን ማፍረስ ነው ሌላውና ዋናው ግን ወደ ልማት ገብተን የነበረውን አስከፊውን ድህነት ለማጥፋት ስራ መጀመራችን ነው። በመታገላችንም ትልቅ ድል አስመዝግበናል። በጤናም ይሃን በትምህርት ያስመዘገብነው አውታር ጥሩ የሚባል ነው። ከድህነትም ጨርሰን ባንወጣም የመኖር እድላችን እየተራዘመ ነው።ትግራይ ቴሌቪዥን፣ ### Response:
### Text: ሽያጭ የናፈቃቸው የመኪና ነጋዴዎችበአዲስ ዘመን ጋዜጣበተለምዶ እንቁላል ፋብሪካ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ በመኪና ገበያነት ይታወቃል። ሰሞኑን ግን ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው እንዲሉ የአካባቢው የመኪና ነጋዴዎች አዲሱ የኤክሳይዝ አዋጅ ረቂቅ ለተወካዮች ምክር ቤት ከቀረበ ጀምሮ ባልተረጋገጠ እሳቤ ምክንያት ሽያጭ ከቆመ ወራት አስቆጥረናል ይላሉ።ከመሸጫዎቹ በአንዱ የአንዲት ቶዮታ ቪትስ የኋላ በር ተከፍቶ በዕቃ ማስቀመጫው ውሃ ተቀምጦበታል። አራት ወጣቶች እና ሁለት ጎልማሶች ክፍት ከተተወው የኋላ በር ፊት ለፊት ከብበው ተቀምጠው የያዙትን ውሃ እየተጎነጩ ያወራሉ። ስለገበያው ሁኔታ ሲጠየቁ ቀደም ሲል በሃዘን ስሜት ሲነጋገሩ የነበሩት ሁሉም አንድ ላይ በቁጣ ይናገራሉ ገበያው ሞቷል በፊት አንድ መኪና ይሸጥ ከነበረበት በ40 እና በ50 ሺህ ብር ቅናሽ ለመሸጥ ብንሞክርም እንኳን ደፍሮ የሚገዛ የለም ይላሉ።የመኪና አስመጪው አቶ መሃመድ አወል እንደሚናገሩት መኪና ሻጭ ብዙ ቢሆንም መኪና ገዢ ጠፍቷል። ቀድሞ የመኪና ማስገቢያ ግብር ጨመረ ተብሎ ሲወራ እነርሱም በመኪና ዋጋ ላይ ጨምረው ነበር። አሁን ደግሞ አዲስ ያልተነዳ መኪና የማስገቢያ ቀረጥ ቀንሷል መባሉ ገበያውን አበላሽቶታል። በተጨማሪ ገዢው ህዝብም ሆነ የመኪና ነጋዴው ግብሩ በምን ያህል ቀነሰ ወይም ጨመረ የሚለው በትክክል አልገባውም በዚህ ሳቢያ ገበያው ተበላሽቷል። 0224 ### Response:
### Text: በነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት አስረባባሪነት ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ በተመረጡ 11 ጎዳናዎች ላይ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ይካሄዳል።«ኑ አብረን በጋራ እናፍጥር» በሚል የሚካሄደው ይህ የኢፍጣር መርሃ ግብር 35 ኪሎ ሜትር ገደማ ይሸፍናል።የሚያካትታቸው 11 ጎዳናዎች ዝርዝር 1 ከኮካ ቢላል መስጂድ ተክለሃይማኖት 2 ከእህል በረንዳ ቢላል መስጂድ3 ከቢላል መስጂድ እፎይታ 4 ከኮልፌ ቀብር ሎሚ ሜዳ5 ከአስኮ አዲስ ሰፈር በድር መስጂድ6 ከመንዲዳ ኢማሙ አሕመድ መስጂድ7 ከአየር ጤና ግራር8 ከግራር ስልጤ ሰፈር9 ከጀሞ 2 አደባባይ ኖክ10 ከረጲ ትምቤት አጃምባ ማዞሪያ11 ከአየር ጤና እስከ አለም ባንክአቅሙ ያለው ሰው በዕለቱ ኢፍጣር በሚካሄድባቸው ጎፋናዎች ሲያቀና እንደ ውሃና ቴምር ያሉ ቀለል ያሉ ማስፈጠሪያቸውን ለሌሎች ቢይዝ መልካም ነው ተብሏል።ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ባለፈ አመት በ6 ጎዳናዎች ላይ ደማቅ የኢፍጣር ፕሮግራም ማካሄዱ ይታወሳል። ተቋሙ በዚህም አመት ረመዷን ከገባ ጀምሮ በየቀኑ 250 ሰዎችን በቋሚነት እያስፈጠረ ሲሆን በክልል ከተሞች በሚገኙ ቅርንጫፎቹ ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በትጋት እየሠራ እንደሚገኝ ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።ዛሬ በሚካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም አጋር መሆን የሚፈልጉና አቅመ ደካሞችን ማስፈጠር ለሚፈልጉ 0972747474 ላይ መደወል ይችላሉ ተብሏል።ፎቶ ፋይል ### Response:
### Text: ሹመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር አብይ አህመድ ለፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ለአዳዲስ 5 አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል።አስተዳደሩ ላይ የአሰራር ውስንነቶችና ክፍተቶች በመኖራቸው የአሰራር ማሻሻያ ለማድረግ መንግስት መገደዱንም የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ገልጿል።በተለይም አስተዳደሩ ከተቋቋመበት ዓላማ አንፃር ለአሰራር ክፍተቶች የተጋለጠ መሆኑ፣ የአሰራር ግድፈት፣ ሙስና ፣የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የተጠያቂነት እጦት ፣ሙያን የተላበሰ የጥበቃ ስርዓት አለመኖርና ያለ አግባብ የታራሚዎችን ሰብዓዊ መብት የሚገድቡ አሰራሮች በመተግበራቸው ተቋማዊ ማሻሻያ ለማድረግ መገደዱን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታውቋል፡፡በዚህም የቀድሞ አመራሮችን በመተካት ለፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዳዲስ አመራር መሾማቸው ተመልክቷል፡፡በዚህም1 ጀማል አባሶ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር2 ረዳት ኮሚሽነር ያረጋል አደመ ምክትል ዋና ዳሬክተር የፋይናንስና የሰው ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ3 ኮማንደር ደስታ አስመላሽ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የተሃድሶ ልማት ዘርፍ ኃላፊ4 ኮማንደር ሙላት አለሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የጥበቃና የደህንነት ዘርፍ ኃላፊ5 ኮማንደር ወንድሙ ጫማ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የመሰረታዊ ፍላጎት ዘርፍ ኃላፊ ሆነው እንዲመሩ ከሰኔ 25 ፣2010 ጀምሮ ተሹመዋል፡፡© ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ክትባት ሙከራ ለሁለት በጎ ፍቃደኞች በዛሬው ዕለት ተሰጥቷል። በፈረንሳይ ተጨማሪ 516 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 21856 ደርሷል። በጣልያን የሟቾች ቁጥር ጨምሯል። ባለፉት 24 ሰዓት 464 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። ተጨማሪ 2646 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በዩናይትድ ኪንግደም ባለፉት 24 ሰዓት 638 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተድርጓል። ቁጥሩ ባለፉት 2 ቀናት ከተመዘገበው ዝቅተኛ ነው። በሀገሪቱ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 18738 ደርሷል። በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር ከ48000 በልጧል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ865000 በልጧል። በደቡብ አፍሪካ ባለፉት 24 ሰዓት 9796 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ ተጨማሪ 318 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 3953 ደርሷል። በሴኔጋል ባለፉት 24 ሰዓት 387 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 37 ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 479 ደርሰዋል። 257 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል። በሩዋንዳ 1343 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ አንድ 1 ሰው በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 154 ደርሰዋል። በሌላ በኩል ተጨማሪ 3 ሰዎች ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 87 ደርሰዋል። ### Response:
### Text: ይህ አድማ ምን ያክል እንደመረረን የሚያሳይ ነው ሳንጃይ ባንዳሪየእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ፣ እንግሊሽ ፉትቦል ሊግ እንዲሁም የሴቶች ሱፐር ሊግ ክለቦች ለአራት ቀናት ከማሕበራዊ ሚዲያዎች ራሳቸውን አግልለዋል።አድማውን የጀመሩት ትላንት ሚያዚያ 22 ጀምሮ ሲሆን ለአምስት ቀናት ይቆያል።ክለቦች ከዚህ ውሳኔ የደረሱት ማሕበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚታዩ ብዘበዛዎችና ማግለሎችን በመቃወም ነው።የእግር ኳስ ማሕበር፣ እንዲሁም ሌሎች ይመለከተናል የሚሉ መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ ኪክ ኢት ኦፍ የተባለው ፀረማግለል ድርጅት በዚህ አድማ ላይ እየተሳተፉ ነው።አድማው ከመጀመሩ ከቀናት በፊግ የኪክ ኢት ኦፍ ሊቀመንበር ሳንጃይ ባንዳሪ በሰጡት አስተያየት ይህ አድማ ምን ያክል እንደመረረን የሚያሳይ ነው ማሕበራዊ ሚዲያ አሁን አሁን በጣም መርዛማ ለሆኑ ብዝበዛዎች የተጋለጠ ሆኗል ብለዋል።አክለውም እኛ አንድ ላይ ሆነን ይህን አድማ የምንመታው ሥልጣኑ ላላቸው መልዕክት ለማስተላለፍ ነው እርምጃ እንድትወስዱ እንፈልጋለን። ለውጥ እንድታመጡ እንሻለን ሲሉ ተናግረዋል።ከትላንት ጀምሮ ክለቦች፣ አስተዳዳሪ አካላት እና የእግር ኳስ ዳኞች ማሕበር ከትዊተር፣ ፌስቡክና ኢንስታግራም ራሳቸውን አግልለዋል።አድማ መቺዎች ዋነኛ ዓላማቸው የማሕበራዊ ሚዲያዎች ጥላቻን እንዲያስወግዱና ትምህርትም እንዲሰጡ መሆኑን ከቢቢሲ ያገኘነው መረጃ ይገልጻል። ### Response:
### Text: የፀጥታው ምክር ቤት በአንድ ድምፅ እንዳይናገር እንቅፋት ሆናለች ተብላ በቻይና የተተቸችው ሀገረ አሜሪካ እስራኤል እና ፍልስጤም ተኩስ አቁሙ ስትል ጥሪ ማቅረቧ ተሰምቷል።ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን በእስራኤልና ፍልስጤም የተኩስ አቁም እንዲደረስ ጥሪ አቅርበዋል።ለእስራኤል ጠሚ ቤንያሚን ኔታንያሁ አሜሪካ የተኩስ አቁም እንዲደረስ ግብጽን ጨምሮ ከተለያዩ ሃገራት ጋር መስራቷን ገልጸዋል ተብሏል።እስራኤል የንጹሃንን ደህንነት ከግምት ውስጥ ማስገባት አለባት ያሉት ፕሬዚዳንቱ አሜሪካም ይህን ታበረታታለች ብለዋል።ነገር ግን ባይደን በፀጥታው ምክር ቤት የቀረበውን እና እስራኤል የምትወስደውን ወታደራዊ እርምጃ እንድታቆም የሚጠይቀውን ሃሳብ ውድቅ አድርገዋል፡፡ከዛ ይልቅ ነገሮችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ መፍታት ይሻላል የሚል አቋማቸውን ስለመግለፃቸው ቢቢሲ አስነብቧል።ተባብሶ በቀጠለው የእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት የሟቾች ቁጥር ጨምሯል።ጋዛ ውስጥ የሞቱ ፍልስጤማውያን ቁጥር 213 የደረሱ ሲሆን ከነዚህ መካከል 61ዱ ህፃናት ናቸው ወደ 1500 ሰዎች ተጎድተዋል።እስራኤል በምትፈፅመው የአየር ጥቃት 58000 ፍርልስጤማውያን መፈናቀላቸውን የ ሪፖርት ያሳያል።በእስራኤል በኩል ዛሬ በተፈፀመ የሀማስ ሮኬት ጥቃት 2 የታይ ሰራተኞች መሞታቸውን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር ወደ 12 ከፍ ብሏል 2ቱ ህፃናት ናቸው 300 ሰዎች ተጎድተዋል። ### Response:
### Text: ሰላም እና መረጋጋት እየታየ ነውበአማራ ክልል የፀጥታ ችግር ተፈጥሮባቸው የነበሩ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች መረጋጋትና ሰላማዊ ሁኔታ እንደሚታይ ተገለፀ።የአማራ ክልል ሰላም እና ደህንነት ግንባታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አለበል አማረ እንደተናገሩት የፀጥታ ችግሩ ተከስቶባቸው በነበሩ በሁሉም አካባቢዎች መረጋጋት እና ሰላማዊ ሁኔታ ታይቶባቸዋል።የአካባቢውን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት ለመመለስ የፀጥታ አካላት ከህብረተሰቡ ጋር እየሠሩ እንደሚገኙ የገለፁት ኮሎኔል አለበል አጥፊዎችን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል።አሁንም ቢሆን ግጭቱን ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማዛመት እና ችግሩን ለማባባስ የተለያዩ ያልተጣሩ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦች በመኖራቸው ህዝቡ ከወዲሁ መጠንቀቅ እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።ግጭቶቹ የተከሰቱባቸው አካባቢ ነዋሪዎች በበኩላቸው ችግር ተፈጥሮባቸው የነበሩ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች የተሻለ መረጋጋት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።እንደ አስተያት ሰጭዎቹ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት ተደናግጠው አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ፈረዶ ውኃ እና መሀል ሜዳ ሸሽተው የነበሩ የአጣየ ከተማ ቀበሌ 01፣ 02 እና 03 ነዋሪዎች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነው፡፡በማጀቴም ከትናንት የተሻለ ሰላማዊ ሁኔታ እንደሚታይ ተጠቁሟል።ምንጭ አብመድ ### Response:
### Text: መመሪያ ቁጥር 9402015የሲሚንቶ ግብይት እና ስርጭትን ለመቆጣጠር የወጣው መመሪያ ቁጥር 9082014 ተሽሮ መመሪያ ቁጥር 9402015 መፅደቁ ታውቋል።አዲሱ መመሪያ ምን ይላል በኬላዎች አከባቢ ሲሚንቶ ምርት ላይ የሚደረግ ማንኛውም ቁጥጥር ተነስቷል። ቸርቻሪዎችን እና አከፋፋዮችን መምረጥ የፋብሪካዎች ሃላፊነት እንዲሆን ተደርጓል። ያለደረሰኝ ምንም አይነት ግብይት እንዳይካሄድ ተደርጓል። ከፋብሪካዎች የሚወጣ ማንኛውም የሲሚንቶ ምርት በቂ ሰነድ ሊኖረው ይገባል።ይኸው መመሪያ የሲሚንቶ ጅምላ እና ቸርቻሪ ነጋዴዎች ግዴታ እንዳለባቸው የሚደነገግ ሲሆን ግዴታዎቹም የሲሚንቶ ጅምላ ነጋዴ ሲሚንቶ የሚገዛውን ቸርቻሪ ድርጅት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በመመዝገብ በህጋዊ የረሰኝ ሽያጭ የማከናወን ግዴታ አለበት። በግዥ የተረከበውን ሲሚንቶ በተቀመጠው የዋጋ ጣሪያ መሠረት ለማንኛውም ተጠቃሚ የመሸጥ ግዴታ አለበት። ሲሚንቶን ከህጋዊ መስመር ውጭ አላግባብ አከማችቶ መያዝና ከተተመነው የዋጋ ጣሪያ በላይ ያለመሸጥ ግዴታ አለበት። የሲሚንቶ ቸርቻሪ ነጋዴ የያዘውን የሲሚንቶ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በንግድ0 መደብሩ በግልፅ በሚታይ ቦታ ላይ የመለጠፍ ግዴታ አለበት። ማንኛውም ሲሚንቶ ገዢና ሻጭ የንግድ እንቅስቃሴውን መረጃ በአግባቡ የመያዝ እና0 በተቆጣጣሪ አካላት ሲጠየቅም የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡ምንጭ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ### Response:
### Text: የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዛሬ በሰጠው መግለጫ የግል ትምህርት ቤቶች ከመደበኛው የትምህርት ክፍያ ውጭ ማንኛውንም ወጭ ከተማሪ ወላጆች መጠየቅ እንደማይችሉ አስታውቋል።በከተማዋ ለቀጣይ የትምህርት ዘመን የዋጋ ጭማሪ ለማድረግ 1 ሺህ 253 የግል ትቤቶች ጥያቄ ማቅረባቸውን ባለስልጣን መቤቱ ገልጿል።የግል ትምህርት ቤቶች ዋጋ የሚጨምሩባቸው ምክንያቶች ግብዓቶችን ለማሟላት፣ ለአስተዳደራዊ ወጭዎች እና የትምህርት ጥራትን አስጠብቆ ለማስቀጠል ታሳቢ ያደረጉ ናቸው ሲል አመልክቷል።የዋጋ ጭማሪው ተግባራዊ የሚሆነው ግን ወላጆች እና ትምህርት ቤቶች ተወያይተው ሲስማሙ መሆኑንም ባለስልጣኑ አስታውቋል። ትምህርት ቤቶች የወላጆችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ክፍያ እንዲያቀርቡ እና ወላጆችም ሁኔታውን አይተው ተግባብተው ሰላማዊና ስኬታማ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲቀጥል ባለስልጣን መቤቱ ጥሪ አቅርቧል።በሌላ በኩል አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች በዓይነትም በገንዘብም ግብዓቶችን ለማሟላትና ለተለያዩ ጉዳዮች ተጨማሪ እንደሚጠይቁ ነገር ግን ከዚህ በኋላ ከመደበኛው የትምህርት ክፍያ ውጭ ምንም አይነት ተጨማሪ ጥያቄ ማቅረብ እንደማይቻል ማሳሰቢያ ተላልፏል።የተማሪዎች የምዝገባ ጊዜም የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በሚያወጣው ጊዜ ከሐምሌ ወር በኋላ መሆኑን ማመልከቱን ኢብኮ ዘግቧል። ### Response:
### Text: የ17 ዓመቷን ወጣት የደፈረው ግለሰብ በ8 ዓመት እስራት ተቀጣ።አዛኝና ተባባሪ መስሎ በመቅረብ የ17 ዓመቷን ወጣት የተከራየው ቤት ወስዶ የደፈረው ግለሰብ በ8 ዓመት ጽኑ እስራት መቅጣቱን የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡የ18 ዓመቱ ወጣት ተከሳሽ ዳንኤል ጥር 28 ቀን 2013 ከምሽቱ 10፡00 ሰዓት ላይ ወጣት ብርትኳን ሀሰንን በወቅቱ በሚዛን ከተማ የደቡብ ክልል የባህል ስፖርት ውድድር በሚካሄድበት ወቅት አብዛኛው የከተማዋ መኝታ ቤቶች በስፖርተኞች መያዙን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም ወንጀሉን መፈፀሙ ተገልጿል።ተከሳሹ የ17 ዓመቷን ወጣት ብርትኳን ለስራ ከሄደችበት ቤሮ ወረዳ ለዕረፍት ወደ ቤሰቦቿ ጂማ ለመጓዝ ሚዛን ስትደርስ አልጋ ያለበት ቦታ ላሳይሽ በሚል ከተግባባ በኋላ ወዲያው ሀሳቡን በመቀየር ወደእኔ ቤት ሂደን ከእህቴ ጋር ትተኚያለሽ በማለት አታሎ በኪራይ ወደሚኖርበት ቤት ከወሰደ በኋላ በሀይል በማስገደድና ግለሰቧ ራሷን መከላከል በማትችልበት ሁኔታ ከደፈረና ደጋግሞ ግብረስጋ ግንኙነት ከፈጸመ በኋላ አውጥቶ ጎዳና ላይ መጣሉን በቀረበበት ክስ ተመላክቷል፡፡ተከሳሽ ዳንኤል በዐቃቤ ህግ የተመሰረተበትን ክስ በችሎቱ ካዳመጠ በኋላ ወንጀሉን መፈጸሙን በማመኑ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ ማስረጃና መረጃ ሳያቀርብ በ8 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንደሰጠበት የቤንች ሸኮ ኮሚኒኬሽን ገልጿል። ### Response:
### Text: 2014 ኢሬቻ መስከረም 22 እና መስከረም 23 ቀን 2014 ዓም ይከበራል።የኦሮሞ አባገዳዎች ህብረት የኦሮሞ ህዝብ የአንድነትና የሰላም ተምሳሌት የሆነውን የኢሬቻን በዓል ያለ ምንም እንከን ለማክበር ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል።ህብረቱ ይህን ያሳወቀው መስከረም 22 እና 23 ቀን 2014 ዓም የሚከበረውን የዘንድሮውን ኢሬቻ በዓል በማስመልከት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።የአባገዳዎች ህብረት ምክር ቤት ሰብሳቢ አባገዳ ጂሎ ማኖ በኢሬቻ ውስጥ ፖለቲካ የለም፣ ሰላምና ምስጋና ነው ያሉ ሲሆን ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ የአንድነትና የሰላም ተምሳሌት ነው በዓሉን ያለምንም እንከን ለማክበር ተዘጋጅተናል ነው ብለዋል።ዕለቱ የኦሮሞ ህዝብ በአንድነት ለፈጣሪው ምስጋና የሚያቀርብበት በመሆኑ በዓሉ ያለምንም ችግር በሰላም እንዲከበር ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።የህብረቱ ፀሐፊና የቱለማ አባገዳ ጎበና ሆላ ደግሞ በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ ባህልና ትውፊቱን፣ ማንነቱ፣ የሰላም እና የአንድነት ተምሳሌት መሆኑን የሚያሳይበት ነው ያሉ ሲሆን የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ በዓሉን ሲያከብር ከኮሮና ወረርሽኝ ራሱን በመጠበቅ መሆን ይገባዋል ብለዋል።በዓሉ የፖለቲካ ትርፍ ይገኝበታል ብለው ለሚያስቡ ሃይሎች መጠቀሚያ እንዳያደርጉት የኦሮሞ ቄሮዎች፣ ቀሬዎችና ፎሌዎች በየደረጃው ከሚገኙ የፀጥታ ሃይሎች ጋር በትብብር መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ### Response:
### Text: ሃሰተኛ የነዋሪነት መታወቂያ እያዘጋጁ ሲሸጡ የነበሩ 3 ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ መታወቂያዎቹን ለማዘጋጀት የሚጠቀሙባቸው ማህተሞችና ወረቀቶችም በብርበራ ተይዘዋል፡፡ እንደ ፖሊስ መረጃ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው አውቶብስ ተራ አካባቢ ነው።ተጠርጣሪዎቹ ለዚሁ ህገወጥ ተግባር ማስፈፀሚያ የሚውሉ በአዲስ አበባ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር ጽቤት እና0 በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ የቀበሌ 01 አስተዳደር ጽቤት የሚሉ ሃሰተኛ ክብ ማህተሞችን እንዲሁም የግለሰብ የስም ቲተር በማስቀርፅ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርማ ያረፈበትን የመታወቂያ ወረቀት አመሳስለው በማሳተም ወንጀሉን ሲፈፅሙ እንደነበር ተገልጿል።ማህተሞቹንና ወረቀቶቹን በአንድ የሸቀጣሸቀጥ መሸጫ ሱቅ ውስጥ ደብቀው በማስቀመጥ የነዋሪነት መታወቂያ ለሚፈልጉ ሰዎች ሃሰተኛ መታወቂያዎችን እያዘጋጁ እንደሚሸጡ ከህብረተሰቡ በተገኘ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ክትትል 3 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ ነው።ግለሰቦቹ ሃሰተኛ መታወቂያውን ለማዘጋጀት የሚጠቀሙባቸው ወረቀቶችና ማህተሞች ከተደበቁበት በብርበራ እንደተገኙም ፖሊስ አስታውቋል። 1229 አዲስ አበባ ፖሊስ ### Response:
### Text: የአዲስአበባ ግብር ከፋይ የሆኑ እና ጉዳያቸው በፖሊስ እና በአቃቤ ህግ ተይዞ የነበሩ 1077 ነጋዴዎች ክሳቸው እንዲቋረጥ ተወሰነ። የከተማ አስተዳደሩ የአዲስ አበባ ግብር ከፋይ የሆኑ ክሳቸው እንዲቋረጥና ፍርድ የተሰጠባቸው በምህረት እንዲለቀቁ ለጠቅላይ አቃቤ ህግ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት 1077 መዝገቦች እጅግ አነስተኛ የገንዘብ መጠን የያዙ ሆነው ያለ ደረሰኝ እና ከዋጋ በታች ግብይት የተከናወነባቸው፣ ደረሰኝ ሳይዙ ዲኪላራይሶን ሳይኖራቸው የተለያዩ ዕቃዎች በንግድ ሱቃቸው የተገኘባቸው፣ የባለስልጣኑን ስራ በማሰናከል እና ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳርያ አድራሻ ጋር የተፈፀሙ ጥፋቶች በመሆናቸው እነዚህ ወንጀሎች ከአፈፃፀማቸው ፣ ከያዙት የገንዘብ መጠን አነስተኛ መሆን እንዲሁም ከተያዘው የታክስ ሪፎርም እና ከግለሰቦቹ የኢኮኖሚ አቅም አንፃር በምርመራ እና በፍቤት ደረጃ ያሉ በሙሉ እንዲቋረጡ ቢደረጉ በመንግስት እና በህዝብ ጥቅም ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ዝቅተኛ በመሆኑ ክሳቸው ተቋርጦ ወደ ስራ ቢገቡ የሚያበረክቱትን አስተዋፅዖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ክሳቸው እንዲቋረጥ ተወስኗል፡፡ ከመርካቶየታክስሪፎርም አስተባባሪዎች ጋር ውይይት ያደረጉት ኢር ታከለ ኡማ መንግስት የንግዱን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት የሚሄደውን ርቀት ያህል ግብር ከፋይ ነጋዴውም ግብሩን በወቅቱ በመክፈል ኃላፊነቱ እንዲወጣም አሳስበዋል፡፡ ### Response:
### Text: ጊዜያችንን ትርጎም በሌላቸው ውይይቶች አናጠፋም። ሁሉም አማራጮች ጠረጴዛው ላይ አሉ፡፡ ምርጫችን ግን ድርድር እና ፖለቲካዊ መፍትሄ ነው አንድ የግብጽ ባለስልጣን ከአሶሺየትድ ፕሬስ ጋር ባደረጉት ቆይታ ግብፅ አነስተኛ ግዛት አይደለችም ሁሉም ዲፕሎማሲያዊ እና ህጋዊ አማራጮች ከከሸፉ ወታደራዊ ጣልቃገብነት አስገዳጅ ሊሆን ይችላል። ለዕለታዊ ጋዜጣ ኤልሾሮክ ታዋቂው አምድ አዘጋጅ የሆኑት አብደላ ኤልሴናው ሲናን ለመልቀቅ ከታገልን ውሃውን ነፃ ለማውጣት መዋጋት ምክንያታዊ ነው የአልማሳሪ አልዮየም ጋዜጣ የቀድሞው አምደኛ አንዋር ኤል ሃውሪርግብጽ እና ኢትዮጲያ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የጀመሩት ድርድር ካልተሳካ ወታደራዊ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ የግብጽ መገናኛ ብዙሃን ግፊት ማድረጋቸወን ቀጥለዋል።አምስት ቢሊየን ዶላር እንደሚፈጅ በተነገረለት እና ሰባ በመቶም ግንባታው በተጠናቀቀው ግድብ ዙሪያ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የተደረገው ውይይት ያለስኬት ተጠናቋል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ለአንድ መቶ ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ሃይል ፍላጎት እንደሚያሟላ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ከኢትዮጲያ ተቃራራቢ የሕዝብ ብዛት ያላት ግብፅ የግድቡን የውሃ ማጠራቀሚ የመሙላት ሂደት የግብጽን የውሃ ድርሻ ይቀንሰዋል የሚል ስጋት አላት፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 10226 ምንጭ ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078ጋዜጠኛ ያይንአበባ ሻምበል ### Response:
### Text: የፀጥታው ምክር ቤት መግለጫ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምቤት በኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ፣ በክልሉ ላለው ቀውስ እልባት ለመስጠት የኢትዮጵያ መንግስት እያከናወነ ያለውን ተግባር አድንቋል፡፡መግለጫው እንደሚገልፀው ፣ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ መንግስት ሰብዓዊ ዕርዳታን ለማቅረብ እና ሰብዓዊ ተደራሽነትን ከፍ ለማድረግ እያደረገ ላለው ጥረት እውቅና ሰጥተዋል፡፡ ነገር ግን የምክር ቤቱ አባላት የሰብዓዊ ችግሮች አሁንም መኖራቸውን እንደሚገነዘቡ እና በክልሉ ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ እንደሚያሳስባቸውም ነው መግለጫው ያመለከተው፡፡ከምግብ ዋስትና ጋር በተያያዘ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት እና ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ ለሁሉም የተቸገሩ ወገኖች ተደራሽ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ አስቸኳይ እርዳታ መርሆዎች ጋር በሚጣጣም መልኩ ሰብዓዊነትን ፣ ገለልተኛነትን እና ነፃነትን መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶች እንዲቀጥሉ የፀጥታው ም ቤት አባላት ጥሪ አቅርበዋል።በትግራይ የተፈጠረው ፀጥታ ችግር ለቀጣይ የሰብአዊ አገልግሎቶች እንቅፋት መሆኑን በመግለጽ መደበኛ ሁኔታው እንዲመለስም አባላቱ መጠየቃቸው በመግለጫው ተካቷል ፡፡ያንብቡ 0423 ምንጭ አል ዓይን ### Response:
### Text: የዓለም አትሌቲክስ የአመቱ ምርጥ ሴት አትሌት ዘርፍ የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ተደርገው ድምፅ እየተሰጠ ይገኛል።ሁለት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከምርጥ አስራ አንድ እጩዎች ውስጥ ይገኙበታል።እጩዎቹም በቅርቡ የአለም የማራቶን ሪከርድን መስበር የቻለችው ኢትዮጵያዊት አትሌት ትዕግስት አሰፋ እንዲሁም የ5000ሜ የዓለም ክብረወሰን የሰበረችው ጉዳፍ ፀጋይ ናቸው።አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በዚህ አመት የ5000 ሜትር የአለም ክብረወሰን ከመስበሯም በተጨማሪ የ10000ሜ የዓለም ሻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል።ምርጫው እንዴት ይካሄዳል የዓለም አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የአሸናፊዎች ምርጫ ለዓለም አትሌቲክስ ኮሚቴ እና ለዓለም አትሌቲክስ ቤተሰቦች ድምፅ በኢሜል መስጠት እንደሚቻል ተገልጿል።ደጋፊዎች እንዴት መምረጥ ይችላሉ ሁሉም የአትሌቲክስ ደጋፊዎች የሚመርጧቸውን አትሌቶች ፎቶ በአለም አትሌቲክስ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በመፈለግ በፌስቡክ ፣ ዩቲዩብ እና ኢንስታግራም ላይክ በማድረግ እንዲሁም በ ሪፖስት በማድረግ መምረጥ ይችላሉ። ጉዳፍ ፀጋይን ላይክ ሪትዊት ለማድረግ ፌስቡክ 10006439142138606826124314563= የቀድሞ ትዊተር ላይ ሪትዊት ለማድረግ 1712082175250563508=04=19 ኢንስታግራም 97=2== ትዕግስት አሰፋን ላይክ ሪትዊት ለማድረግ ፌስቡክ 100064391421386019472517937= የቀድሞ ትዊተር ሪትዊት ለማድረግ 1712082042391802157=056=19 ኢንስታግራም 8=2== ሼር ያድርጉ ### Response:
### Text: ሊፈቱ ነው አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በልዩ ሁኔታ በይቅርታ ከእስር እንዲፈቱ መወሰኑን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ አስታውቋል።የፌዴራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው የነበሩ 576 ግለሰቦች በልዩ ሁኔታ ይቅርታ ተደርጎላቸው እንዲፈቱ መወሰኑን አስታውቋል።በልዩ ሁኔታ በይቅርታ ከእስር እንዲፈቱ ከተወሰነላቸው መካከል 18ቱ ሴቶች መሆናቸውም ተገልጿል።እንዲፈቱ ከተወሰነላቸው መካከል ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኝና ክሳቸው እንዲቋረጥ የተደረገ እንዲሁም ጉዳያቸው በይቅርታ ቦርድ ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ቀርቦ በልዩ ሁኔታ በይቅርታ እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ናቸው።ግለሰቦቹ ስነ ምግባራቸውና መፀፀታቸው ታይቶና ከእስር ቢፈቱ ለህብረተሰቡ ስጋት የማይሆኑና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ መሆኑንም የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ገልጿል።በአጠቃላይ ለ745 ታራሚዎች እና ተከሳሾች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ መወሰኑንም ነው ጠቅላይ አቃቢ ህግ ያስታወቀው።ከእነዚህ ውስጥ 576ቱ በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰውና ተፈርዶባቸው የነበሩና በልዩ ሁኔታ ይቅርታ የተደረገላቸው ናቸው።137ቱ ደግሞ በሽብር ወንጀል ተከሰው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የበነበረና ክሳቸው የተቋረጠ ነው።31 ግለሰቦችና ተቋማት ደግሞ በሙስና ወንጀል ተከሰው የነበሩና ክሳቸው የተቋረጠላቸው ናቸው።© ### Response:
### Text: በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አካባቢዎች በተቀሰቀሰ ግጭት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ️በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አካባቢዎች የተቀሰቀሰው ግጭት አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል።ግጭቱ ትናንት ከቀኑ 930 ጀምሮ በአጣዬ በማጀቴና በካራ ቆሬ አካባቢዎች መባባሱም ተሰምቷል።ስለ ጉዳዩ የጠየቅናቸው የአጣዬ ከተማ ከንቲባ አቶ ጌታቸው በቀለ ግጭቱ በአካባቢው ነዋሪና በታጠቁት ኃይሎች መካከል መፈጠሩን ነግረውናል።ምክንያቱ በውል እንደማያውቁ የገለፁልን አቶ ጌታቸው የታጠቀው ኃይል ከትናንት ቅዳሜ ጀምሮ በፈፀመው ጥቃት 9 ሰዎች መገደላቸውንና በርካቶች መቁሰላቸውን ገልፀውልናል።ግጭቱ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል ያሉት ከንቲባው ቤት ለቤት ዘረፋ መጀመሩንና 3 ሰዎች ታፍነው መወሰዳቸውንም ነግረውናል።በአካባቢው የነበረው የክልሉ ልዩ ኃይል ጥቃቱ ከአቅሙ በላይ በመሆኑ መከላከያ ኃይል መግባቱንም ከንቲባው አያይዘው ተናግረዋል።የኤፍራታና ግድም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሰው መሸሻ በበኩላቸው ተደራጅቶ ዘመናዊና የቡድን መሳሪያዎችን የታጠቀው ቡድን በከፈተው ጦርነት ብዙዎች ተገድለዋል ብለዋል።በአካቢው ያሉ የእምነት ተቋማት ጭምር ጥቃት እንደደረሰባቸው ነው አስተዳዳሪው የገለፁት።ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ወደ አካባቢው የገባው የመከላከያ ኃይል ሁኔታውን ማረጋጋት እንዳልቻለ ገልፀዋል። ### Response:
### Text: ተማሪዎች ሚዲያዎችን ወቀሱ ችግር ባለባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች ያለንበትን ሁኔታ ሚዲያዎች እየደበቁ ነው ዩኒቨርሲቲዎችም ተገቢ መረጃ እየሰጡ አይደለም ሲሉ ወቅሰዋል። ለተከታታይ ቀናት ከግቢ ውስጥ እንዳንወጣ በር ተዘግቶብናል፣ ግቢ ውስጥ በየዶርሙ በሚፈጠሩት ችግሮች ስጋት አድሮብናል፣ በየደቂቃው ምን ሊፈጠር ነው በሚል ተጨንቀናል፣ በዚህ መልኩ ተማሪዎችን ማስቀመጥ እና ድምፃቸውን ማፈን ተገቢ አይደለም መንግስት በሰላም ወደቤተሰቦቻችን ይሸኘን ብለዋል። በፌዴራል እና በመከላከያ እየተጠበቅን በየመማሪያ ክፍል ውስጥ እንዲሁም ሜዳ ላይ ፍራሽ ዘርግተን የምናድር ተማሪዎች ቁጥርም ቀላላ አይደለንም ያለንበትን ሁኔታ ግን ሚዲያዎች አንድ ወገን በመያዝ ብቻ ነው እያቀረቡ ያሉት ሲሉ ወቅሰዋል። አንደኛው ክልል ያለው ሚዲያ የሌላኛውን ችግር አንዱም የሌላኛውን ችግር እንጂ እዛው ክልላቸው ውስጥ ያለውን ችግር በአግባቡ እየዘገቡ አይደለም ይህ አሳፋሪ ተግባር ነው ብለዋል። ሚዲያዎች የተማሪዎችን ችግር በአግባቡ ያለ አድሎ አሰምተው መፍትሄ እንዲመጣ ከመጣር ይልቅ በተማሪ ህይወት ላይ እየቀለዱ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል። የሚዲያዎቹ እንቅስቃሴ ሀገሪቱን እልቂት ውስጥ የሚያስገባ በመሆኑ የሚሰማ መንግስት ካለ ሃይ ይበላቸው ሲሉ ተማሪዎቹ አሳሳበዋል። ### Response:
### Text: 1ኛ አባ ሳዊሮስ2ኛ አባ ኤዎስጣቴዎስ3ኛ አባ ዜና ማርቆስ ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ መነሳቱ ተገልጿል። ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ መወሰኑን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳውቋል።በቤተ ክርስቲያኗ መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን እንደለያቸው አሳውቋል።የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አውግዞ በለያቸው ግለሰቦች ይመሯቸው በነበሩ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ አገልግሎት በማከናወን ሀገረ ስብከቱን የሚመሩ ብፁዐን አባቶችን ለደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ለኬንያኡጋንዳታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ሀገረ ስብከት ለኢሉ አባቦራ እና በኖ በደሌ ሀገረ ስብከት በሰሜን አሜሪካ ለሜኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ለጉጂምዕራብ ጉጂ እና ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም በአባትነት የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደቡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ወስኗል፡፡ቅዱስ ሲኖዶስ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽተው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው ይሆናል ብሏል።ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል ### Response: