text
stringlengths
707
989
### Text: ሜጀር ጄኔራል መሀሪ ዘውዴሜጀር ጄኔራል መሀሪ ዘውዴ ገማሪያም የአብዬ ጊዚያዊ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጦርሀይልአዛዥ ሆነው መሾማቸውን የተባበሩት መንግስታት ሴክሬታሪ ጄኔራል አንቶኒ ጉቴሬዝ አስታወቁ፡፡ ሜጀር ጄኔራል መሀሪ እንደ እኤአ በሚያዝያ 23 2019 የስራ ጊዚያቸውን የሚያጠናቅቁትን ሜጀር ጄኔራል ገብሬ አድሃና ወልደዝጉን ተክተው ይሰራሉ ተብሏል፡፡ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ለተሰናባቹ ሜጀር ጄኔራል ገብሬ አድሃና ደከመኝ ሳይሉ ላደረጉት አገልግሎትና በተመድ ለነበራቸው ውጤታማ የአመራር ጊዜ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ጄኔራል ሴክሬቴሪያቱ በንግግራቸው ሜጄር ጄኔራል መሀሪ ዘውዴ ከኢትዮጵያ የታጠቁ ሀይሎች ጋር በመሆን ለ37 ዓመታት ማገልገላቸውን ገልጸው በቅርቡ የኢትዮጵያ የመከላከያ የሰው ሀይል ኃላፊ በመሆንና ለምድር ጦሩ እና ለአጠቃላይ የመከላከያ ሀይሉ የሰው ሀይልና የአስተዳደር ስራ በሀላፊነት መስራታቸውን አክለዋ፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የመከላከያ ሚኒስቴር የአማካሪ አባል በመሆን ከ2007 ጀምሮ ሰርተዋል፡፡ለኢትዮጵያ አየር ሀይል ከ20012007 ምክትል ኮማንደር፣ ለምስራቁ የአየር ሀይል ዕዝ በኮማንደርነት በ19891997 እና በሌሎች ተሳትፎዎችም ከኢትዮጵያ ታጣቂ ሀይሎች ጋር አገልግለዋል፡፡ሜጀር ጄኔራል መሀሪ ዘውዴ በብሪታንያ ከሚገኘው ግሪን ዊች ዩኒቨርስቲ በሳይንስ የማሰተርስ ድግሪ አግኝተዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: የገዛ ባሏን በመርዝ የገደለችው ተከሳሽ በ19 ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቷን የምሥራቅ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ አቶ ዋቁማ ጡሪ እንዳስታወቁት በነቀምቴ ከተማ አስተዳደር 03 ቀበሌ ውስጥ በምትኖረው ተከሳሽ ወይዘሮ እልፍነሽ በቀለ ጅራታ ላይውሳኔው የተላለፈው ባሏን አቶ አዳነ አሰፋውን በመርዝ መግደሏ በመረጋገጡ ነው።ሟች ከኦሮሚያ ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማህበር ከተበደሩት 86ሺህ ብር ውስጥ 10ሺህ ብር እንዲሰጣት ጠይቃ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ቂም ይዛ መርዝና አይብ በማደባለቅ መጋቢት 012011ዓም ከምሽቱ በግምት አራት ሰዓት አካባቢ እንዲመገብ አድርጋለች።ወደ መኝታ ክፍል እንደገባም በሩን በውጭ በኩል ዘግታ መሞቱን ካረጋገጠች በኋላ ራሱን በራሱ የገደለ ለማስመሰል ፀፀት ተብሎ የተፃፈና ሁለት ገጽ ያለው ወረቀት በደረቱ ላይ አስቀምጣ መኖሪያ ቤቱን በመዝጋት ንብረት ስታሸሽ መያዟን አመልክተዋል።የተከሳሿ ድርጊት በዞኑ ዓቃቤ ሕግየሕግ ምሥክሮች በመረጋገጡ፣ ራሷም የፈጸመችውን ድርጊት ማመኗንና የመከላከያ ማስረጃም የለኝም ማለቷን አቶ ዋቁማ አስረድተዋል፡፡በመሆኑም የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በግንቦት 212011 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሿ ሆን ብላ የሰውን ሕይወት ለማጥፋት ተዘጋጅታ የፈጸመችው ድርጊት በመሆኑ በ19 ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ ### Response:
### Text: የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ልዩ ስብሰባ ተጠናቀቀ==================================የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ባለፉት 10 ቀናት ከሰኔ 28 እስከ ሐምሌ 072011 ዓም በአገራዊና ክልላዊ ወቅታዊ የፖለቲካና የጸጥታ ሁኔታዎች እንዲሁም አዳዲስ ክልል ሆኖ የመደራጀት ጥያቄዎች ላይ ሲያካሄድ የነበረውን ስብስባው በስኬት አጠናቋል፡፡ ማእከላዊ ኮሚቴው አገራችን አሁን ያለችበትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ የተጀመረው አገራዊ ለውጥ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ መክሮ አቋም ወስዷል፡፡ ክልላዊ አደራጃጀቱን በተመለከተ ዝርዝር ሳይንሳዊ ጥናት ተደርጎ የቀረበ ሲሆን ጊዜ ወስዶ በሳል ውይይት ተካሂዶበታል የቀጣይ አቅጣጫም ተቀምጧል ፡፡ በማያያዝ የክልሉን ሰላምና ደህንነት አስተማማኝ ማድረግ፣ የህግ የበላይነትን ማስከበር ላይ ጥልቅ ውይይት ተካሂዶ ጠንካራ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ ስለሆነም የደኢህዴን ማእከላዊ ኮሚቴ ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን አጠናክሮ የማስቀጠል፣ የተጀመሩ የለውጥ እንቅስቃሴዎችንና ውጤታቸው ተጠናክረው እንዲሁም የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጽናትና በመርህ ላይ ቆሞ በመታገል ለላቀ ስኬት እንዲበቃ ማእከላዊ ኮሚቴው በሙሉ መግባባብት ላይ በመድረስ ለቀጣይ ተልእኮም በቁርጠኝነት መዘጋጀቱን አረጋግጧል፡፡ ዝርዝር መግለጫው እንደደረሰ ይቀርባል፡፡ ደኢህዴን ### Response:
### Text: ግብፅ️ግብፅ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ ያላቸው እና የሀገርደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥሉ ይዘቶችን የሚያሰራጩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲዘጉ የሚያስችል ህግ ይፋ አደረገች፡፡የግብፅ የመገናኛ ብዙሃንን የሚቆጣጠረው አካል ይፋ ያደረገው ይህ አሰራር በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ከፍተኛ የሆነ ገደብ እንዳላው ነው የተነገረው፡፡አዲሱ ህግ የሀገሪቱ ከፍተኛው የመገናኛ ብዙሃን ተቆጣጣሪ አካል ሀሰተኛ ዜናዎችን የሚያሰራጩ አካላትን ለማገድ እንደሚያሰችለውና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እስከ 14 ሺህ 400 ዶላር ቅጣት ለመጣል እንደሚያስችለው ተነግሯል፡፡ይህ አዲስ አሰራር በትናንትናው ዕለት ተግባራዊ መደረግ የጀመረ ሲሆን እርምጃው የኤል ሲ ሲ አስተዳደር ተቃዋሚዎችን ለመቆጣጠር እንደሚያስችለው ተጠቁሟል፡፡በቅርብ ዓመታት ውስጥ ግብፅ በመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች ላይ የወሰደቸው እርምጃ መነጋገሪያ ሆኖ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን በዚህም በርካታ ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡እርምጃው ኢ ህገ መንግስታዊ ነው ያሉት የግብፅ አንጋፋ ጋዜጠኞች የመገናኛ ብዙሃንን ነፃነት በመጋፋት የመንግስት ባለስልጣናት በመገናኛ ብዙሃንን ቁጥጥር እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡የሀገሪቱ ከፍተኛው የሚዲያ ተቆጣጣሪ አካል ሃላፊ ሙሃመድ አህመድ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ምንጭ፡ አልጀዚራ ### Response:
### Text: ህይወት ለማዳን ሲሉ ህይወታቸው ያለፈው የሩሲያ ሚኒስትር የሩሲያው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ሚኒስትር የሰውን ህይወት ለማዳን ሲሞክሩ ህይወታቸው አለፈ።የሩስያ አስቿኳይ ጊዜ ሁኔታ ሚኒስትር ህይወታቸው ያለፈው በኖርልስክ አርክቲክ ከተማ አቅራቢያ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በሚደረግበት ጊዜ ሕይወት የማዳን ኃላፊነታቸው ሲወጡ ነው ተብለዋል፡፡ሚኒስትሩ ኢቭጂኒ ዚኒቺቭ ህይወትን ለማዳን በቁፋሮ ስራ ላይ ሳሉ ለሞት የሚዳርግ አደጋ እንዳጋለጠቸውንም ነው የተገለጸው። መስርያ ቤታቸውም ዚኒቺቭ የአንድን ሰው ሕይወት ለማዳን ሲሞክሩ ህይወታቸውን በአሰቃቂ ሁኔታ ሊያልፍ ችለዋል ብለዋል፡፡በጉብኝታቸው ኖርልስክ ከተማ አዲስ የእሳት አደጋ ጣቢያ ሲመረምሩም ነበር ሚነሲትሩ።የአርቲ ዋና አዘጋጇ ማርጋሪታ ሲሞንያን በአደጋው ጊዜ ሚኒሰትሩ እና የካሜራ ባለሙያ ጠርዝ ላይ ቆመው ነበር ከዛም የካሜራ ባለሙያው ተንሸራቶ ወደ ውሃው ውስጥ ወደቀ። በርካታ ሰዎች በስፍራው የነበሩ ቢሆንም ፣ ዚንክቼቭ ወደ ውሃው እስኪወድቁና ኩፉኛ አስኪመቱ ድረስ ምን እየሆነ እንዳለ ለመገንዘብ አልቻሉም ነበር ስትል ሁኔታውን አስረድታለች። ማርጋሪታ ሲሞንያን እሱ እንደ አዳኝ ሞተ በሰላም እረፍም ስትል ኃሳቧን ገልጻለች። ማርጋሪታ የካሜራ ባለሙያው ህይወት ማለፉንም አስታውቃለች፡፡ አል ዓይን ሚኒስትሩ ከመሞታቸው ከሰዓታት በፊት የተቀረፀ ነው። ### Response:
### Text: ደቡብ ክልልበደቡብ ክልል እየተነሱ ያሉ የአደረጃጀት ጥያቄዎችን በተመለከተ ሳይንሳዊ ጥናት ለማድረግ ዝግጅት ማጠናቀቁን ጥናቱን የሚያከናውነው ፎረም አስታወቀ።ላለፉት ሶስት ወራት ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው ፎረሙ በቀጣዮቹ አስር ቀናት መረጃ ሰብሳቢዎች ወደ ስራ ይገባሉ ብሏል።ፎረሙ ጥናቱን ከአራት ወራት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለክልሉ መንግስት እንደሚያቀርብም ነው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ያስታወቀው።ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እና የሙያ መስኮች የተውጣጣ 20 አባላት ያለው የጥናት ቡድን የጥናቱን አካሄድ በተለመከተ ንድፈ ሀሳብ አዘጋጅቷል። አለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ለማየት መሞከሩንም አንስቷል።በዛሬው እለትም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተመለመሉ 22 የጥናቱ ሱፐርቫይዘሮች ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርጓል።በቀጣዩ ሳምንትም በሀዋሳ ከ150 የመረጃ ሰብሳቢዎች ጋር እንደሚመክር ነው በመግለጫው የተነሳው።የጥናቱ ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅም ከሰው ሀይል ባሻገር የሶፍትዌር ዝግጅት መደረጉን ፎረሙ የጥናትን መርህ እና አካሄድ ጠንቅቀው በሚያውቁ እስከ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ባላቸው የክልሉ ተወላጆች የሚደረገውን ጥናት ለክልሉ መንግስት እንደ ግብአት አቀርባለሁ ብሏል።የጥናቱ ውጤት ውሳኔ ሰጪ ሳይሆን እንደ ምክረ ሀሳብ የሚቀርብ መሆኑንም ፎረሙ በመግለጫው አንስቷል።ምንጭ ፋና ብሮድካስቲንግ ### Response:
### Text: ሀገር መከላከያ ሰራዊት እርምጃ የተወሰደባቸውን እና እጅ የሰጡ የህወሓት ቡድን አባላት ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል ኮሌኔል የማነ ገብረሚካኤልን ኮሎኔል አለም ገብረመድህን፣ ኮሎኔል ቢንያም ገብረመድህን፣ ኮሎኔል አምባዬ፣ ኮሎኔል ማሾ፣ ኮሎኔል ይርጋ ስዩም፣ ኮሎኔል ሃዱሽ፣ ኮሎኔል አጽብሃ፣ ኮሎኔል ተስፋዬ ገብረመድህን፣ ኮሎኔል ዮሃንስ ካልአዩ፣ ኮሎኔል ተክለእግዚአብሄር፣ ሌተናል ኮሎኔል ብርሃኔ ቶላ እና ሌሎች በስም ያልተገለጹ 4 ኮሎኔሎች እና ሁለት የዞን አመራሮች ይገኙበታል።እጅ የሰጡ የቀድሞ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሙሉ ገብረእግዚአብሔር ሃዱሽ ዘውገ ገዛኸኝ የክልሉ ኦዲት ሀላፊ የነበረ፣ ሰለሞን ህሉፍ ንጉሴ የክልሉ ልማት ስልጠና ሀላፊ የነበረ፣ ኪዳነማሪያም ገብረክርስቶስ ፋሲል የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ የነበረ፣ ባህታ ወልደሚካኤል የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ የነበረ፣ ሀጎስ ወልደኪዳን ገብረማሪያም የክልሉ ኢኮኖሚ ቢሮ የልማት እቅድ አስተባባሪ እጅ መስጠታቸውን መከላከያ አሳውቋል።በተጨማሪም በርካታ ቁጥር ያላቸው የሚሊሻ እና ልዩ ሀይል አባላት እጃቸውን መስጠታቸውን ሰራዊቱ ገልጿል። ከተማረኩት ውስጥ ዶክተር ዓለም ብርሃኔ፣ ኮሎኔል መብርሃቱ ገብረመድን፣ ኮሎኔል ሃዱሽ ሃጎስ፣ ኮሎኔል ህሉፍ ተመድህን፣ ሌተናል ኮሎኔል ተክለ ህይወት አሰፋ ይገኙበታል። ### Response:
### Text: ስቴም ፓወር ፣ ቪዛ እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ በመተባበር ባዘጋጁት የሥራ ፈጠራ ክህሎት እና መሰረታዊ የፋይናንስ ትምህርት ላይ የተሳተፉ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች የምርቃ መርኃግብር ተካሂዷል።ስልጠናውን ከተከታተሉ 200 ሰልጣኞች ውስጥ በአጠቃላይ 70 የሚሆኑ ፕሮጀክቶች የቀረቡ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ለመጨረሻው ዙር ከደረሱ 20 ፕሮጀክቶች በአራት ዘርፎች ለአራት አሸናፊዎች የ25000 ብር በድምሩ የ100000 ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።አሸናፊዎቹ በግብርና፣ በጤና፣ በኢንጂነሪንግና በአገልግሎት ዘርፍ የተመረጡ ሲሆን በጤናው ዘርፍ ኢሶፕ የተሰኘ የፈጠራ ሃሳብ በግብርናው ዘርፍ ደግሞ ፖሊተሪ ፋርሚንግ ላይ የቀረበ ፕሮጀክት አሸናፊ ሆኗል። በኢንጅነሪንግ ዘርፍ የፕላስቲክ ኮዳን ወደ ፋይበር ፕላስቲክ የሚለውጥ እንዲሁም በአገልግሎት ዘርፍ ደግሞ ሎሃ የተሰኘ የኦንላይን ትምህርት አገልግሎት አሸናፊዎች ሆነዋል።የስቴም ፓወር ሥራ አሥኪያጅና ቅድስት ገብረአምላክ አሸናፊዎቹ ከተበረከተላቸው ሽልማት በተጨማሪ ወደ አገልግሎት እስኪገቡ ድረስ በቀጣይ አንድ ዓመት ስቴም ፓወር ሙሉ የቴክኒክና የሞያ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።በሥራ ፈጠራ ክህሎት እና በመሰረታዊ የፋይናንስ ትምህርት ላይ ያተኮረው ሁለተኛው ዙር ስልጠና በቀጣይ ሳምንታት ይጀምራል። ቲክቫህ ኢትዮጵያም በቀጣይ የሚኖሩ ሁነቶችን ወደ እናንተ የሚያደርስ ይሆናል። ### Response:
### Text: ቁጥራዊ መረጃከ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሪፖርት ️ በ2021 በመላው ዓለም 591 ሚሊዮን ተፈናቃዮች ተመዝግበዋል ይህ ቁጥር በታሪክ ከፍተኛው ነው። ከ591 ሚሊዮኑ መካከል 532 ሚሊዮን በግጭት እና ሁከት 59 ሚሊዮን በተፈጥሯ አደጋዎች የተፈናቀሉ ናቸው። ኢትዮጵያ ️ በ2021 በኢትዮጵያ ግጭት እና ሁከት ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል። ይህ ቁጥር ከቀደመው ዓመት በ3 እጥፍ ይበልጣል። ️ በኢትዮጵያ የተመዘገበው የተፈናቃዮች ቁጥር በአንድ አገር ውስጥ ከዚህ ቀደም ከተመዘገበው ሁሉ የሚበልጥ ሲሆን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በአመቱ የአገሪቱን ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው በማፈናቀል ከፍተኛውን ቦታ ይዟል። በሌሎች ክልሎች የተከሰቱ የርስ በርስ ግጭቶችም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።በ ሪፖርት መሠረት በትግራይ ክልል 18 ሚሊዮን፣ በአማራ ክልል 17 ሚሊዮን፣ በኦሮሚያ ክልል 643 ሺ ተፈናቃዮች ተመዝግበዋል። ️ በ2021 መጨረሻ በመላው ኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን ዜጎች ሕይወታቸውን በተፈናቃይነት ለመግፋት ተገደዋል ከእነዚህ መካከል 17 ሚሊዮን የሚሆኑ ሕጻናት የትምህርት ዕድል የሌላለቸው ናቸው።️ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሀራ በርሀ በታች በሚገኙ አገራት የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ14 ሚሊዮን በላይ ደርሷል። ️ በተፈናቃዮች ቁጥር ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ያሉት ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና ቡርኪና ፋሶ ናቸው ከሰሀራ በታች።ሙሉ ሪፖርት 2022 ### Response:
### Text: የጅቡቲ ጦር የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሮ ጉዳት አድርሷል የሚባለው ወሬ ሐሰት ነው የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴርየጅቡቲ ጦር የኢትዮጵያን ድንበር አልፎ ወደ አፋር ክልል በመግባት ጉዳት አደረሰ በሚል የሚሰራጨው ወሬ ሐሰት ነው ሲል የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር ገለፀ።የጅቡቲ ጦር የኢትዮጵያን ድንብር ተሻግሮ በአፋር በኩል ዜጎች ላይ ጉዳት አደረሰ የሚለው ወሬ ሐሰት መሆኑን በመከላከያ ሚኒስቴር የምክትል ኤታማዥር ሹም ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኮሎኔል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ ተናግረዋል።በተለያዩ የማሕበራዊ ሚዲዎችና አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን በአፋር ድንበር በኩል የጅቡቲ ጦር ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ጉዳት አደረሰ በሚል የሚሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑም ተገልጿል።ጅቡቲም ኢትዮጵያን የመውረር ሐሳብ እንደማታራምድና የሁለቱ አገሮች ወዳጅነት እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ጥብቅ መሆኑንም ተናግረዋል። በሁለቱ አገሮች መካከል ለግጭት የሚዳርግ ምንም አይነት ተጨባጭ ምክንያት አለመኖሩን የገለጹት ኮሎኔል ተስፋዬ እየተሰራጨ ያለው መረጃም ትክክል አለመሆኑን አብራርተዋል።ይሁን እንጂ በአካባቢው አልፎ አልፎ በግጦሽ፣ ውሃና በሌሎች ምክንያቶች የሚከሰቱ ግጭቶች መኖራቸውን አስታውሰው በክልሉ በዜጎች ላይ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የመከላከያ ሰራዊት በስፍራው ተገኝቶ ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን ተናግረዋል። ### Response:
### Text: አዲስ ለሚገነባው የሀዲስ አለማየው ልዩ አዳሪ ትምህርት ዛሬ ላይ የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን እየተካሄደ ይገኛልበአንጋፋው ደራሲ ዶር0ሀዲስ ዓለማየሁ ተሰይሞ በትውልድ መንደራቸው በደብረማርቆስ ከተማ በ100000 ካሬ ሜትር ላይ ሊገነባ የታሰበውና 2000 የሚያህሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ያስተናግዳል ለተባለለት ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ማስገንቢያ አስመልክቶ ዛሬ በኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ዝግጅቱን በንግግር የከፈቱት የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴሩ አቶ መላኩ አለበል እንደተናገሩት ትምህርት ቤቱ በአንጋፋው ደራሲ በሀዲስ አለማየው መሰየሙ ስማቸው በራሱ ትምህርት ይሆናል ብለዋል፡፡ አክለውም ሀገር የሚለወጠው በሰው ነው ሰው የሚለወጠው በትምህርት ቤት ነው ሲሉ የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት አጉልተው ገልጸዋል፡፡በቀጣይም የትቤቱ የዲዛይን ገጽታ ለታዳሚው የቀረበ ሲሆን ከ100000 ካሬ ወደ 200000 ከፍ እንዲል ምክረ ኃሳብ የቀረበበት ሲሆን አሁን በተሰጠው በዩኒቨርሲቲው አቅራቢያ በሚገኝ ቦታ ላይ ይገነባል ተብሏል፡፡ዝግጅቱ በቀጥታ ስርጭት በአማራ ቴሌቭዢን እየተላለፈ ይገኛል፡፡ ከውጭ ሀገርና ከሀገር ውስጥ በዚህ ዝግጅት መሳተፍ ለሚፈልጉ ተከታዩን የስልክና የባንክ አድራሻዎች ተጠቅሰዋል፡ 0912005385 0913066163 0911814122 0911953473 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 100294537043አቢሲኒያ ባንክ፡ 16642134 ### Response:
### Text: የአየር ጥቃት ተፈፅሟል ኦነግ️ዕሁድ ጠዋት የሀገር መከላከያ በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ የኦነግ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች ላይ የአየር ጥቃት ሰንዝሯል የሚል መረጃ በስፋት ተሰራጭቶ ነበር።የምዕራብ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ገመቺስተመስገን በጉዳዩ ላይ የአማርኛው አገልግሎት አስተያየታቸውን ጠይቆ ይህ መረጃ እስካሁን አልደረሰኝም። በምዕራብ ኦሮሚያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ይንቀሳቀሳል። በተለያዩ አጋጣሚዎችም ከኦነግ ሠራዊት ጋር የተኩስ ልውውጥ አድርጓል። ዕሁድ ዕለት የአየር ጥቃት ተሰንዝሯል ወይም አልተሰነዘረም ማለት አልችልም ብለዋል።በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ የአየር ጥቃት የተፈጸመው በቤጊ እና ጊዳሚ ወረዳዎች አዋሳኝ ድንበር ላይ መሆኑ በስፋት ተነግሯል። ይሁን እንጂ ያነጋገራቸው የአከባቢው ነዋሪዎች የአየር ጥቃት ተፈጽሟል ሲባል ሰማን እንጂ ያየነው ነገር የለም ይላሉ።ነዋሪዎቹ እንደሚሉት የአየር ጥቃት ሲፈጸም ባይመለከቱም በአከባቢው የጦር ሄሊኮፕተሮች በብዛት ስለሚመላለሱ ከፍተኛ ስጋት ገብቷቸዋል። የኦነግሸኔ የሥራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ሚካኤልቦረና ግን መንግሥት በቤጊ እና ጊዳሚ ወረዳዎች ውስጥ የአየር ጥቃት እየሰነዘረ ነው ሕዝቡም እየተጎዳ ነው ብለዋል። አቶ ሚካኤል እንደሚናገሩት የኦነግ ጦር የነበረበትን ስፍራ ሳይለቅ እራስን የመከላከል እርምጃ እየወሰደ ነው።ምንጭ ### Response:
### Text: ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ በሰው እና በቤቶች ላይ ጉዳት ደረሰ።በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ፑኩሙ ቀበሌ ንፋስ ቀለቀቅሎ በጣለ ዝናብ በርካታ ቤቶችና ሰው ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ፡፡የፑኩሙ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ ጆን ኡጁዋቶ እንዳሉት በቀን 042013 ዓም ከምሽቱ 5 አካባቢ ንፋስ ቀላቀሎ በጣለው ዝናብ በቀበሌው ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡በደረሰው ጉዳትም 55 የቆርቆሮና 20 የሳር ቤቶች በድምሩ 75 መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም ትምህርት ቤትን ጨምሮ አራት የመንግስት ተቋማት ላይ ጉዳት መድረሱን ጠቁመው በ3 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል አደጋ መድረሱን አመልክተዋል፡፡በመሆኑም በደረሰው አደጋ መልሰው ለመቋቋም የወገንና የመንግስት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል፡፡ የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጋትቤል ሙን ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች መልሶ ለማቋቋም ኤጀንሲው ከሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ ይሰራል ብለዋል፡፡በአደጋው የደረሰ ተጨማሪ ጉዳት እንዳለ ለማጣራት እና እርዳታ ለማሰባሰብ ከተለያየ አካላት የተውጣጣ ቡድን ወደ ስፍራው እንደሚላክ አስረድተዋል፡፡ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ቦታው ላይ በመገኘት ምልከታ ማድረጋቸውን የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት መረጃ ያሳያል። ### Response:
### Text: የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ወቅት አማራ ክልል ፖሊስ ከሚሽን እንዳስታወቀው በኦፕሬሽን እና በሕዝብ ትብብር 218 የሚሆኑ የብርጋዲዬር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ጥቃት ተባባሪዎች ናቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች ውስጥ 113 ያህሉ በቀላል ደረጃ የተጠረጠሩ በመሆኑ በቅርቡ ውሳኔ እንደሚሰጣቸው የገለጹት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር አበረ አዳሙ ናቸው፡፡ቀሪዎቹ 105 ተጠርጣሪዎች ግን ተጨማሪ ማጣራት የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ የማጣራት ሥራው እየተከናወነ እንደሆነ ነው ኮሚሽነሩ ያስታወቁት፡፡ ጉዳያቸውን በዋናነት ይዞ እያጣራ የሚገኘው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን መሆኑንም አመላክተዋል፡፡እንደ ኮሚሽነር አዳሙ መግለጫ በአርሶ አደሮች በቁጥጥር ሥር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ከሌሎች ተጠርጣሪዎች ጋር ሳይቀላቀሉ ለብቻ በማረፊያ ቤት ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል በጥቃቱ የተጓደሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን ለማሟላት እየተሠራ መሆኑን የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አቶ አሰማኸኝ አስረስ ተናግረዋል፡፡ የሚሟሉት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር ጉዳይ በቅርቡ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆንም አስታውቀዋል፡፡ አብመድ ቀን ሰኔ 282011 ዓም ### Response:
### Text: ሼር የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች 19 በትኩሳት እና ደረቅ ሳል ይጀምራል። ከሳምንት በኋላ የመተንፈስ ችግር ያጋጥማል። በበሽታው የተያዘ ሰው እስከ 14 ቀናት ምንም አይነት ምልክት ላያሳይ ይችላል። አንዳንድ ሰዎች የበሽታ ምልክት ሳያሳዩ በሽታውን ሊያስተላልፉ ይችላሉ። ኮሮና ቫይረስ መድሃኒት አለው ቫይረሱን ከሰውነት ውስጥ የሚያስወግድ መድሃኒት የለም። ሃኪሞች በሽተኞችን እያከሙ የሚገኙት የታማሚዎችን የበሽታ የመከላከል አቅምን ከፍ በማድረግ ነው። ለመተንፈስ የሚረዱ ቁሶችም ጥቅም ላይ ይውላሉ። እራሴን ከቫይረሱ እንዴት ነው መጠበቅ የምችለው የዓለም ጤና ድርጅት የሚከትሉትን እንዲያደርጉ ይመክርዎታል እጅዎን ይታጠቡ ቫይረሱን ሊገድሉ በሚችሉ ሳሙናዎች በቫይረሱ የተበከሉ ነገሮችን ሊነኩ ስለሚችሉ በእጅዎ ዓይን፣ አፍ እና አፍንጫዎን ከመነካከት ይቆጠቡ። ወደ የሚያስነጥሱ፣ የሚያስሉ እና ትኩሳት ወዳለባቸው ሰዎች አይጠጉ። ቢያንስ የ1 ሜትር እርቀት ይፍጠሩ። ሲያስሉ እና ሲያስነጥሱ አፍ እና አፍንጫዎን ይሸፍኑ ከዚያም እጅዎን ይታጠቡ። ይህን ማድረግዎ በቫይረሱ ተይዘው ከሆነ የማሰራጨት ዕድልዎን ያጠባሉ።በቫይረሱ እርሶ ወይም ሌሎች መያዛቸውን ከተጠራጠሩ እራሰዎን ያግልሉ በቤትዎ ይቆዩ ሌሎችም ተመሳሳይ እንዲያደርጉ የበኩልዎን ይወጡ። 8335 ላይ በመደወል ለማሕብሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በፍጥነት ያሳውቁ።ምንጭ ### Response:
### Text: የየካቲት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 206 ሆኖ ተመዘገበ።የጥር ወር አጠቃላይ ግሽበት 192 ነበረ በየካቲት ወር የ4 በመቶ ጭማሪ አሳይቶ 206 በመቶ መድረሱን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ0ገልጿል።የየካቲት ወር ምግብ ዋጋ ግሽበት0 ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ228 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል ተብሏል።በእህሎች ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ በያዝነው ወርም የቀጠለ ሲሆን ለምግብ ዋጋ ግሽበት መጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ኤጀንሲው ገልጿል። በተጨማሪም አትክልትና ጥራጥሬ ዓይነቶች የዋጋ ጭማሪ አስመዝግበዋል ብሏል።በሌላ በኩል ስኳር፣ የምግብ ዘይት፣ ቅመማ ቅመም በርበሬ፣ ድንች እና ቡና የዋጋ ጭማሪ በዚህም ወር በመቀጠላቸው ለዋጋ ግሽበት ምጣኔ መጨመር አስተዋጽኦ አድርገዋል ተብሏል።በሌላ በኩል ምግብ ነክ ያልሆኑ0 የዋጋ ግሽበት የየካቲት ወር0ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ180 በመቶ ጭማሪ በማሳየት ፈጣን ዕድገት አሳይቷል ተብሏል።ከምግብ ነክ ያልሆኑ0ግሽበት ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር ከፍ እንዲል ካደረጉት ዋና ምክንያቶች ውስጥ በተለይም በአልኮልና ትምባሆ ትምባሆ ፣ ልብስና ጫማ፣ አነቃቂዎች ጫት፣ የቤት እንክብካቤ እና ኢነርጅ ማገዶና ከሰል ፣ የቤት መስሪያ እቃዎች ፣ ህክምና ፣ ትራንስፖርት ነዳጅ እና ጌጣጌጥ ወርቅ ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ ነው ተብሏል። ምንጭ ሸገር ኤፍ ኤም 1021 ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኢሰመኮ ሰኔ 23፣ 24 እና 25 ቀን 2013 ዓም በፌደራል የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው በእስር የሚገኙትን በቃሉ አላምረው፣ ያየሰው ሽመልስ፣ ፋኑኤል ክንፉ፣ አበበ ባዩ፣ መልካም ፍሬ ይማም፣ ፍቅርተ የኑስ፣ ዊንታና በርሄ እና ምህረት ገብረክርስቶስን ጨምሮ 21 የኢትዮፎረም እና የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኞችና ሰራተኞች አያያዝ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር በቅርበት ሲከታተል መቆየቱን ገልጿል።ከእነዚህ ታሳሪዎች መካከል ሦስቱን እና አንድ ሌላ ታሳሪን ጨምሮ አራት እስረኞች ማክሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2013 ዓም አመሻሽ ላይ መለቀቃቸውን ኢሰመኮ ገልጿል።ቀሪዎቹ ታሳሪዎች በወንጀል ስለተጠረጠሩ ለምርመራ ስራ በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ትዕዛዝ መሰጠቱን ፖሊስ እንደገለፀለት ኢሰመኮ አድረድቷል።ነገር ግን ኮሚሽኑ እስከ ሐምሌ 3 ቀን 2013 ዓም ምሽት ድረስ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ አለማየቱና ታሳሪዎቹን ለመጎብኘት አለመቻሉ እንዲሁም ታሳሪዎቹ ከቤተሰቦቻቸውም ሆነ ከጠበቆቻቸው ሳይገናኙ ከአንድ ሳምንት በላይ መቆየታቸው እጅግ የሚያሳስበው ጉዳይ እንደሆነ ገልጿል።በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮፎረም እና የአውሎ ጋዜጠኞችና ሰራተኞች አያያዝ ሕግን የተከተለ ሊሆን ይገባል ያለው ኢሰመኮ የፍርድ ቤት የእስር ትዕዛዝ ካልቀረበ በአፋጣኝ ሊለቀቁ እንደሚገባ አሳስቧል። ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: ጥንቃቄ ለቲክቫህ ቤተስብ አባላት የተለያዩ ገንዘብ የማግኛ ሀብት ማፍሪያ መንገዶች እየተባለ በዲጅታል ሚዲያው በኩል ከቀርብ ጊዜ ወዲህ በርካቶች እጅግ በስፋት እየተከሰቱ ነው።እነዚህ አካላት ፍቃድ ይኑራቸው አይኑራቸው የመስሪያ አድራሻቸው ይታወቅ አይታወቅ ፣ የሚመራቸው የሚያስተባብራቸው ግለሰብ ይኑር አይኑር የሚለውን በግልፅ ለማወቅ አዳጋች ነው።ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ከዚህ በፊትም እንዳልናችሁ ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችል እንቅስቃሴ ውስጥ ስትገቡ ኢንቨስት ስታደርጉ እነዚህ ጥያቄዎች እንድትጠይቁ አደራ እንላለን 1 ድርጅቱ ተቋሙ እውቅና ያለው ፣ ፍቃድ ያለው ነው የሚሰራበትን ፍቃድ በይፋ አሳውቋል 2 በትክክል የሚታወቅ አድራሻቸው የት ነው ቢሯቸው 3 ለሚደርስብኝ ማኛውም አይነት ነገር ማንን ተጠያቂ ማድረግ እችላለው 4 የሚሰራው ስራ ምን ያህል ቀጣይነት አለው ነገ እንደማይቆም ምን ማስተማመኛ አለ ይህንን ማንስተማመኛ ማን ይሰጠኛል የሚሉ ጥያቄዎችን መጠየቅ ያስፈልጋል።ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የማጭበርበር እና የማታለል ድርጊቶች እየሰፉ በመሆናቸው ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።ብዙሃንን ሊጠቅም ያሚችል ማንኛውም ህጋዊ ስራ በሚስጥር፣ በድብቅ ፈፅሞ ሊሰራ አይችልም እና ውድ ቤተሰቦቻችን ማኛውም እንቅስቃሴ ስትጀምሩ ከላይ የተዘረዘሩትን ጥያቄዎች በቅድሚያ መልስ እንዳያገኙ አድርጉ። ### Response:
### Text: ከሰሞኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተው የዜጎች ግድያ፣ የአካል ማጉደል ፣ መፈናቀል ብሎም የሃይማኖት ተቋማት ማውደምና የንብረት ማጋየት ወንጀል ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የተፈጸመበት መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አመለከተ። ተቋሙ አክሎም በአደባባይ የሕግ የበላይነትን የተገዳደረ ድርጊት መሆኑንም አስታውቋል።ድርጊቱ እጅግ አስደንጋጭ ፣ አሳዛኝና አስቆጭ እንደሆነበት ያመለከተው ኮሚሽኑ አጥፊዎች ገለልተኛ በሆነ መልኩ ጥናት ተደርጎ ለሕግ እንዲቀርቡም ጠይቋል። ይህ እንዲሳካም ኮሚሽኑ ስልታዊ ክትትል እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ በተለይ ከጀርመን ራድዮ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልፀዋል።በተፈጸመው ድርጊት ሪፓርት ያልተደረገውን ሳይጨምር እስካሁን በግምት ከ70 እስከ 80 ሰዎች የተወሰኑት በጥይት ተመትተው አብዛኞች ደግሞ በሚኖሩበት ቤትና አካባቢያቸው በሌሎች ሰዎች በድንጋይ ፣ ዱላ እና ስለት ተደብድበው መገደላቸውን ኮሚሽነሩ ዶክተር ዳንኤል በቀለ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ተናግረዋል። በምርመራው ወቅት ንፁሐን ያለ አግባብ እንዳይጠየቁና ጥቃት እንዳይደርስባቸው ያሳሰቡት ኃላፊው የማንነት እና የወሰን ጥያቄዎች ለከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ምክንያት እየሆኑ በመምጣታቸው መንግሥት ፖለቲካዊ ውሳኔ በማሳለፍ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።0 ### Response:
### Text: ቤቲንግ እንዲቆም ተወስኗል በሴቶች ህፃናት ወጣቶች ሚኒስቴር የወጣቶች ስብዕና ልማት ዳይሬክተር አቶ አለሙ ሰኢድ የስፖርት ውድድር ቤቲንግ እንዲቆም ተወስኗል። 26 አባላት ያቀፈ የፌደራል የአሉታዊ መጤ ልማዶችና አደንዛዥ ዕፆች ግብረ ኃይልና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ተሳተፊ የሆኑበት መድረክ በማዘጋጀት የስፖርት ውድድር በዜጎች ስነልቦና፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊና አጠቃላይ የሚያደርሰውን ችግር ተፈትሿል። በጥር ወር ውስጥ ለስፖርት ውድድር በሚል ይሰጥ የነበረው ፍቃድ የቆመ ሲሆን ስራ ላይ የሚገኙ አቋማሪ ድርጅቶች የውላቸው ጊዜ እስኪጠናቀቅ ብቻ ሊቆዩ ይችላሉ። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ገሚካኤል ሀጎስ በህጉ መሰረት እየሰሩ የሚገኙ አወራራጅ ድርጅቶች የውል ጊዜያቸው ሲያበቃ ውላቸውን ማደስ ይችላሉ። አሁን ላይ በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ፍቃድ ያላቸው 46 አወራራጅ ድርጅቶች አሉ። በአዲስ መልክ ፍቃድ መስጠት አቆምን እንጂ ፍቃድ ያለቸውን ድርጅቶች ስራቸው እንዲያቆሙ አልተወሰነም፡፡ ለአወራራጅ ድርጅቶቹ ፈቃድ የሚሰጠው እና በተቀመጠላቸው የአሰራር ህግ መሰረት መንቀሳቀሳቸውን የሚከታተለው ተቋም ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር እንጂ ሌላ ተቋም የለም። የተለያዩ ተቋማት በስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች ዙሪያ የሚሰጡት አስተያየት ትክክል አይደለም።አዲስ ዘመን ጋዜጣ ### Response:
### Text: ባለስልጣኑ ስልጣን ሊለቁ የፈለጉበት ምክንያት ምንድነው የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጠን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ በፍቃዳቸው ኃላፊነታቸውን እንደሚለቁ ገልፀዋል።ዋና ዳይሬክተሩ ከስልጣን ሊለቁ የፈለጉበት ምክንያት ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጀ ግን ሀሰት መሆኑን ኢብባ አሳውቋል።የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱአለም በቅርቡ ዶክተር ጌታቸው ድንቁ የተቋሙን ሰራተኞች ሰብስበው ተቋሙን እንደማይመሩና ኃላፊነታቸውን በፍቃዳቸውን ለመልቀቀ መወሰናቸውን አሳውቀዋል ሲሉ ገልፀዋል።ዶክተር ጌታቸው ኑሯቸውን በአሜሪካ አድርገው ለማስተማር እና ለመርምር ስራ ወደኢትዮጵያ መመለሳቸው የተገለፀ ሲሆን ምክትል ዳይሬክተሩ አቶ ወንድወሰን ዋና ዳይሬክተሩ ወደኃላፊነት ሲመጡ ለ2 ዓመት ብቻ ለመስራት እንደሆነ ተናግረዋል ብለዋል።በማስተማር እና በምርምር ስራ ጊዜያቸውን ማሳለፍ የበለጠ እንደሚወዱ የተናገሩት ዶር ጌታቸው ለሰራተኞችም ያሳወቁት ይህንኑ ነው ከዛ ውጭ የሚናፈሰው በሙሉ ሀሰተኛ መረጃ ነው ሲሉ አቶ ወንድወሰን አሳውቀዋል።የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ኢብቦ ተጠሪቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲሆን ጉዳዩ በቦርድ ውሳኔ እስከሚፀድቅ መልቀቂያቸው ተቀባይነት እስኪያገኝ ድረስ ኃላፊነታቸውን ለቀቁ ተብሎ መናገር እንደማይቻል ተገልጿል። 1021 ### Response:
### Text: በበይነመረብ እንዲያስተምሩ የተፈቀደላቸው የግል ተቋማት ቁጥር 5 መድረሱን ኤጀንሲው አሳወቀ።በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ በዋለው በበይነመረብ ትምህርት የእውቅና አሰጣጥ መመሪያ መሰረት ፈቃድ በበይነመረብ እንዲያስተምሩ የተፈቀደላቸው የግል ተቋማት ቁጥር 5 መድረሱን ኤጀንሲው አሳውቋል።ከዚህ ቀደም ኤጀንሲው ለ4 ተቋማት ፈቃድ የሰጠ ሲሆን አሁን ላይ ለሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ ኦፍ አድሚኒስትሬሽን የትምህርት መስክ በድህረምረቃ መርሃግብር በበይነመረብ የትምህርት አሰጣጥ ተማሪ ተቀብሎ እንዲያስተምር መፍቀዱን አሳውቋል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ በበይነመረብበኦንላይን ሞዳሊቲ የቅድመምረቃ እና ድህረምረቃ መርሃግብር እንዲያስተምሩ በኤጀንሲው የተፈቀደላቸው 5 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፡ 1 ሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ2 ኢቲ ኦንላይን ኮሌጅ 3 ኤስቲ አሜሪካን ኮሌጅ ኦፍ ቴክኖሎጂ4 ያርድስቲክ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ እና 5 ላይፍ ማፕ ኮሌጅ ናቸው፡፡ከተጠቀሱት 5 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብቻ ሲሆኑ ሌሎች በበይነመረብ በኦንላይን ትምህርት የእውቅና ፈቃድ ሳይኖራቸው ያላቸው በማስመሰል በተለያዩ የኢንተርኔት አውታሮች ራሳቸውን የሚያስተዋውቁ ህገወጥ አካላት መኖራቸው ታውቆ ተማሪዎች፣ ወላጆች እና ሁሉም ህብረተሰብ አካላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኤጀንሲው በጥብቅ ያሳስቧል፡፡ ### Response:
### Text: ሀገር አቀፍ የፆምና የፀሎት ምህላ አዋጅየኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አዲሱን አመት በሰላም ለመቀበል ያለመ ለ5 ቀናት የፀሎት መርሐግብር አወጀ።የፀሎት መርሐግብሩ ከጷግሜ 1 እሰከ 5 የሚቆይ መሆኑም ተገልጿል። ጉባኤው አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የሰላም ጥሪን በሚመለከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። አገሪቱ ያጋጠማት ወቅታዊ ችግር በይቅርታና በፍቅር እንዲፈታ የተለያዩ እምነት የሚከተሉ ዜጎች በየሐይማኖታቸው የልዩ ፀሎቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጉባኤው ጥሪ አቅርቧል።በሁለቱም ወገኖች ያሉና በትግል ውስጥ ያሉ አካላት ለእርቅ ዝግጁ ሆነው አገሪቷን ማሻገር ይጠበቅባቸዋል ተብሏል። የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ኢትዮጵያ አሁን ወዳለችበት ጦርነት እንዳትገባ ምዕመናንን ስለሰላም ከማስተማር ባለፈ ፖለቲከኞች ህዝቡን ወደ ጦርነት እንዳያስገቡ ሲሸመግል መቆየቱንም አስታውሷል።አሁንም ምዕመናን እና የፖለቲካ አመራሮች ለሰላም መቼም ቢሆን ረፍዶ አያውቅም እና ሁሉም ወገን ወደ ሰላም እንዲመለሱ አሳስቧል።የሀይማኖት አባቶችም ምዕመናኑን ስለ ሰላም ማስተማራቸውን እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርቧል።ጉባኤው ጦርነት ውስጥ ያሉ ሁሉ ንጹሀንን፣ የማምለኪያ ስፍራዎችን በጦርነቱ እንዳይጎዱ አዲያደርጉ ብሏል ያለንበት ጦርነት ወደ አዲሱ 2014 ዓመት እንዳይተላለፍ ሁላችንም የሚጠበቅብንን እናድርግ ሲልም ጥሪ አቅርቧል። ### Response:
### Text: ድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን️ኮማንደር አለሙመግራ የድሬ ዳዋ ከተማ 0አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ።ኮማንደር አለሙ መግራ 0ከዚህ በፊት የከተማ አስተዳድሩ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር 0የነበሩትን አቶ ጌታቸው አስረስን በመተካት መሾማቸውን የድሬዳዋ ፖሊስ 0ኮሚሽን አስታውቋል።ኮማንደር አለሙ መግራ ለ26 አመታት በፖሊስ ሙያ በተለያየ ሃላፊነት የሰሩና ያገለገሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ በአዳማ ፣ቢሾፍቱ ፣በሻሸመኔ ከተሞችና በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች ፖሊስ አዛዥ በመሆን አገልግለዋል።በተጨማሪም 0የኦሮሚያ ትራፊክ ፖሊስ ሃላፊ በመሆንና 0ላለፉት 5 ወራት በሐረሪ ክልል መንግስት የክልሉ ምክትል ኮሚሽነር በመሆን ሰርተዋል።ኮሚሽነሩ ሹመታቸውን 0አስመልክቶ ባስተላለፉት 0መልዕክት ህዝብን በባለቤትነት በማሳተፍ ለህግ የበላይነት መረጋገጥና ለዘላቂ ሰላም መስፈን ቅድሚያ ሰተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።በቀጣይም ከህብረተሰቡና እና ከፖሊስ ሰራዊቱ ጋር ሰፊ የውይይት መድረኮች የሚካሄድ መሆኑን ጠቁመዋል።ኮሚሽነሩ አያይዘውም መላው የአስተዳደሩ ነዋሪ እስካሁን ለሰላም መስፈን ሲያበረክት የቆየውን 0ትብብርና እገዛ 0አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አቅርበዋል።ኮማንደር አለሙ መግራ በማኔጅመንትና በህግ የመጀመሪያ ድግሪና በሙያው የረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸው መሆኑ ተገልጿል።ምንጭ ድሬ ፖሊስ ### Response:
### Text: በምስራቅ ጎጃም ዞን ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ሞጣ ከተማ አስተዳደር ዛሬ አመሻሽ ላይ ከምሽቱ 130 ጀምሮ በከተማዋ በሚገኘው የታላቁ ጀሚዑል ኸይራት መስጂድና ሌሎች ሁለት መስጅዶች ላይ የማቃጠል ተግባር መፈፀሙ ተሰምቷል። ይህ አስደንጋጭ ድርጊት ከመፈፀሙ ቀደም ብሎ ፈፃሚዎቹ እና ምክንያቱ በግልፅ ባይታወቅም በጥንታዊው ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያነጣጠረ የጥቃት ሙከራም ነበር ተብሏል። በአሁን ሰዓት በከተማይቱ ውስጥ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማም ነው ከአካባቢው እየወጡ የሚገኙ መረጃዎች የሚጠቁሙት። የሱቆች ዝርፊያ እየተካሄደ እንደሆነና በሰዎች ላይም አደጋ መድረሱ እየተገለፀ ነው። የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ሁኔታው ከዚህ የከፋ አደጋ ከማድረሱ በፊት ሊያስቆሙና አጥፊዎችንም በመለየት ለህግ ሊያቀርቡ ይገባል። ሞጣ ከተማ ማህበረሰቡ ለእልፍ አመታት ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ፣ በሃይማኖት መቻቻል፣ በመከባበር፣ በመዋደድ የሚኖርባት ከተማ እንደሆነች ነው የሚነገርላት። መንግስት አጥፊዎች በአፋጣኝ ለፍርድ ማቅረብ እና ለህዝብ ማሳወቅ አለበት። አፋጣኝ የእርቅ መርሃ ግብርም ሊዘጋጅ፣ የተጎዱም ሊካሱ፣ የተቃጠሉ መስጊዶችም በአስቸኳይ ሊገነቡ ይገባል። ነዋሪዎችን የማያባራ ግጭት ውስጥ ለመክተት እየተደረጉ ያሉ አደገኛ እንቅስቃሴዎች በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል።ከኡስታዝ አቡበክር አህመድ 1221 ### Response:
### Text: የ2005 የ2080 ባለ3 መኝታ ተመዝቢዎች በ14ኛው ዙር የዕጣ አወጣጥ የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች በቴክኖሎጂ ሆነ በማኑዋል ዕጣ የማውጣት ሂደቶች በሚፈጠሩ ችግሮች ሊወጣለት ከሚገባው ባለእድለኛ ወጪ ለሌላ ለማይመለከተው አካል እንዳይተላለፉ የሄደበትን ርቀት እናደንቃለን፡፡ ነገር ግን ይህ ቁርጠኝነት በባለ3 መኝታ 2005 ዓም የ2080 ተመዝቢዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲገለጽ እንፈልጋለን፡፡ በቅርቡ የተሰረዘውን የ14ኛው ዙር የዕጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓትን አስመልክቶ በዋዜማውና ከዛ በኋላ በተሰጡ መግለጫዎች ባለ3 መኝታ የኮንዶሚኒየም ቤት ዕጣ ውስጥ እንደማይገባ የተሰጠው መግለጫ ግልጽነት የጎደለውና ማብራሪያ የሚሻ ሆኖ አግኝተነዋል።ይህ ሁኔታ የ2005 የ2080 ባለ3 መኝታ ተመዝቢዎችን በእጅጉ ያሳዘነ፣ ያስደነገጠና ግራ ያጋባ ሆኗል፡፡ ይህን አስመልክቶ በከተማ አሰተዳደሩ የተለያየ የስራ ኃላፊዎች በቅርብ ጊዜያት በተለያዩ ሚዲያዎች በሚሰጡት መግለጫዎችና ማብራሪያዎች ላይ የ2080 ባለ3 መኝታ የ2005 ተመዝቢዎችን አቤቱታና ቅሬታዎችን በግልጽ ከመመለስ ይልቅ ሆን ተብሎ በሚመስል መልኩ ቸል በማለትና በማድበሰበሰ እየታለፈ በመሆኑ በመንግሥት ላይ ያለንን እምነት እየሸረሸረ ይገኛል። የ2005 የ2080 ባለሶስት መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች አሉን ያሏቸውን ጥያቄዎች በዝርዝር በመፃፍ ትኩረት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።ሙሉ ጥያቄያቸው በዝርዝር ተገልጿል ### Response:
### Text: የኦሮሚያ አባ ገዳዎች ህብረት የ2012 የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ የእርቅ ሳምንት አውጇል የኦሮሚያ አባ ገዳዎች ህብረት የ2012 የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ የእርቅ ሳምንት አወጀ። የእርቅ ሳምንቱ ከመስከረም 9 እስከ መስከረም 22 2012 ዓም ድረስ የሚቆይ መሆኑንም የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።የእርቅ ሳምንቱ የታወጀው በ2012 ዓም መስከረም 24 እና 25 በተከታታይ በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እና በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዴ የሚከበሩ የኢሬቻ በዓላትን ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተገልጿል። አባ ገዳ ጎበና ሆላ እንዳስታወቁት የእርቅ ሳምንቱ የታወጀው ሰማይና ምድሩን በማስታረቅ በሰላምና በፍቅር የኢሬቻ በዓልን ለማክበር ነው። የ2012 አዲስ ዓመትም የሰላምና አደስታ እንዲሆንም የኦሮሞ አባ ገዳዎች ምኞታቸውን ገልፀዋል። የኦሮሞ ህዝብ የምስጋና ቀን የሆነው ኢሬቻ በዓል በተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች በዓመት ሁለት ጊዜ ይከበራል። የመጀመሪያው የክረምት መውጣትን ተከትሎ በውሃማ አካባቢዎች የሚከበር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በበልግ ወቅት በተራራማ አካባቢዎች ይከበራል። ተቋርጦ የነበረውን የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልንም በአዲስ አበባ ለማክበር አስፈላጊው ቅደመ ዝግጅት መጠናቀቁን የኦሮሚያ አባ ገዳዎች ህብረትና የኦሮሚያ ቱሪዝም ቢሮ በጋራ በሰጡት መግለጫ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ምንጭ፡ ### Response:
### Text: የኮቪድ19 ስርጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ ትላንት በዓለም አቀፍ ደረጃ 649149 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ሲረጋገጥ 10206 ሰዎች ሞተዋል። ህንድ ውስጥ ትላንት 366499 ሰዎች በኮቪድ19 ሲያዙ 3748 ሰዎች ሞተዋል። ብራዚል ትላንት 34162 ዜጎቿ ለበሽታው ተጋላጭ መሆናቸውን እና 934 ሰዎች ደግሞ መሞታቸውን ሪፖርት አድርጋለች። ትላንት ከፍተኛ ሞት የተመዘገበባቸው ሀገራት ስንመለከተ ኮሎምቢያ 495 አርጀንቲና 283 ሩሲያ 334 ቱርክ 283 ይገኙበታል። የአፍሪካ አቀፍ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ትላንት 7320 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 220 ሰዎች ሞተዋል። ደቡብ አፍሪካ 1596595፣ሞሮኮ 513864 ፣ቱኒዝያ 320813፣ ኢትዮጵያ 262702 ታማሚዎችን ሪፖርት በማድረግ የቀዳሚዎችን ቦታ ይዘዋል።ክትባት የዓለም ጤና ድርጅት ለ ሲኖፋርም በቻይና ኩባንያ የተዘጋጀ የኮቪድ19 መከላከያ ክትባት ለአስቸኳይ ጊዜ ሥራ ላይ እንዲውል ፈቃድ ሰጥቶታል።ይኸ ሲኖፋርም የተባለው ኩባንያ በቤጂንግ ባዮሎጂካል ኢንስቲትዩት ያዘጋጀው ክትባት በዓለም ጤና ድርጅት ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የቻይና ክትባት ነው። የዓለም ጤና ድርጅት ይኸን ውሳኔ ከማስተላለፉ በፊት በበርካታ አገሮች ሥራ ላይ የዋለው ክትባት በሁለት ዙር የሚሰጥ ነው። ከዚህ ቀደም ፋይዘርባዮንቴክ፣ ሞዴርና፣ ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን እንዲሁም አስትራዜኔካ በተባሉ ኩባንያዎች የተሰሩ ክትባቶች በአስቸኳይ ጊዜ ሥራ ላይ እንዲውሉ ፈቃድ ሰጥቶ ነበር። ### Response:
### Text: አብይ ነጥቦች ዶር አብይ በህተምቤት ካቀረቡት ንግግር ውስጥ ወቅቱ ከስህተታችን ተምረን ህዝባችንን የምንክስበት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ማህፀነ ለምለም ናት ችግሮቻችን ተለያይተን ቀርቶ ተባብረን ለመፍታት ዘመናትን ይወስዱብናል፡፡ ኢትዮጵያዊነት ያስተማረን ችግሮቻችንን ወደተሻለ ዕድል መለወጥን ነው፡፡ ማንነታችን እንዳይለያይ ሆኖ የተሰናሰለ እንዳይነጣጠል ሆኖ የተገመደ የተዋደደ እና የተዋሃደ ነዉ፡፡ አንድነት የማይፈታው ችግር የለም አንድነት ማለት ግን አንድ አይነትነት ማለት አይደለም፡፡ ነፃነት ከመንግስት ለህዝብ የሚበረከት ስጦታ አይደለም፡፡ ሀሳብን የመግለፅ ፣ የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ሊከበሩ ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ የጋራችን የሁላችን መሆኗን ማወቅ ህዝባችን የሚፈልገው የህግ የበላይነትን ብቻ ሳይሆን ፍትሐዊነትንም ጭምር ነው፡፡ ከኤርትራ መንግስት ጋር ልዩነቶቻችንንለመፍታት ዝግጁነን፡፡ ሙስናን ፀረ ሙስና ተቋምን በመመስረት ብቻ መታገል አይቻልም፡፡ በጀመርነው አዲስ ምዕራፍ ሙስናን ሌት ተቀን ለመዋጋት እንሰራለን፡፡ ኢትዮጵያ የሁላችን አገር የሁላችን ቤት ናት መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍትህ እና የሠላም ነው የ7 ዓመት ልጅ እያለሁ እዚህ ፊታችሁ እንደምቆም የታያት እናቴን ማመሰገን እፈልጋለሁ የእናቴን ራዕይ ተረክባየእናቴ ምትክ የሆነች ባለቤቴን ማመስገን እፈልጋለሁ፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: የትግራይ ዲያስፖራ ፌስቲቫል2ኛው ዓለምቀፍ የትግራይ ዲያስፓራ ፌስተቫል ለመካሄድ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስታውቋል፡፡ፌስቲቫሉ በተለያዩ የዓለም ሃገራት የሚገኙ የትግራይ ዲያስፓራ ማህበረሰብ በክልሉ ብሎም በሃገራቱ እየተከናወኑ ባሉት የሰላም የዴሞክራሲና የልማት ስራዎች ተሳታፊ ለማድረግ ያለው ነው ተብሏል፡፡በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማትና ንግድ ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶር አብርሃምተከስተ ዝግጅቱን አስመልክቶ በሠጡት መግለጫ ፌስቲቫሉ የትግራይ ዲያስፓራ ስለሃገራቸውና ስለ ክልላቸው ተጨባጭ ሁኔታ ተገንዝበው ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት በተደራጀ መልኩ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ለማድረግ ነው፡፡ፌስቲቫሉ ዲያስፓራውን በክልሉ በሚካሄደው የንግድ የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴዎች ተሳታፊ ለማድረግ ነው ያሉት ዶክተር አብርሃም የፐብሊክ ዲኘሎማሲውን በማጠናከር በኢትዮ ኤርትራ የተጀመረውን የሰላም ግንኙነት ተጠናክሮ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ነው፡፡ዋናው ፌስቲባል ከሃምሌ 24 ሃምሌ 3ዐ 2ዐ11 ዓም ድረስ የሚካሄድ ሲሆን የህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ ህወሓት የተመሰረተበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ከየካቲት 112ዐ11 ዓም ጀምሮ በተለያዩ ስነስርዓቶች እንደሚካሄደ ተገልጿል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጅማአባጅፋር የእግር ኳስ ክለብን ከማንኛውም ፌዴሬሽኑ ከሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ማገዱን አስታወቀ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለ እንዳስታወቀው ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብ ከየካቲት 29 2011 ጀምሮ ፌዴሬሽኑ ከሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ላይ ታግዷል። እንደ ፌዴሬሽኑ ገለጻ ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብ የታገደው አብዱልፈታህ ከማል ለተባለው ተጫዋቹ ተገቢውን ክፍያ ባለመፈፀሙ ነው። አብዱልፈታህ ከማል የተባለው የእግር ኳስ ተጫዋች ከክለቡ ጋር ውል እያለው ከመስከረም ወር 2010 ዓም ጀምሮ ወሉ በክለቡ በመቋረጡ ለፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን ኮሚቴ አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን ኮሚቴውም የተጫዋቹን አቤቱታ በመመልከት ለአመልካች ያልተከፈለው ደመወዝ ታስቦ በአምስት ቀናት ውስጥ እንዲከፈለው የካቲት 12 2010 ዓም ለክለቡ በተፃፈ ደብዳቤ ማሳወቁን ገልጿል። ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብም ይህንን ተግባራዊ ሳያደርግ በመቆየቱ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ሚያዝያ 12 2010 ዓም በፃፈው ደብዳቤ በክለቡ ላይ ቀጣይ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀ ቢሆንም ክለቡ ግን ለተጫዋቹ ክፍያውን ሳይከፍል ቆይቷል ብሏል። በመሆኑም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብ ከየካቲት 29 2011 ዓም ጀምሮ ፌዴሬሽኑ ከሚያዘጋጃቸው የእግር ኳስ ውድድሮች የታገደ መሆኑን አስታውቋል። ### Response:
### Text: ትናንት ቅዳሜ ምሽት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ቢያንስ ሁለት ተማሪዎች መሞታቸው ተነገረ። ያነገውራቸው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እና መምህር የብሄር መልክ በያዘው ግጭት የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን እና በርካቶች መቁሰላቸውን አረጋግጠዋል።በዩኒቨርሲቲው መምህር የሆኑት የቢቢሲ ምንጭ ትናንት ምሽት በተፈጠረው ግጭት ሁለት ተማሪዎች መሞታቸውን ወደ ዩኒቨርሲቲው ደውለው መስማታቸውን ተናግረዋል።የሆስፒታል ምንጮች እንደጠቆሙት ደግሞ ወደ ወልዲያ ጄኔራል ሆስፒታል 14 ተማሪዎች ተጎድተው መጥተዋል።ስማቸወን መግለጽ ያልፈለጉ የወልዲያ ጀነራል ሆስፒታል ባልደረባ ለቢቢሲ እኔ የገባሁት ዛሬ እሁድ ጠዋት 2፡30 ላይ ነው። ተማሪዎቹ ጉዳት ደርሶባቸው ሲመጡ አልተመለከትኩም። ግን አሁን ከ1415 የሚሆኑ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሆስፒታሉ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው ሲሉ ተናግረዋል።እኚሁ የሆስፒታል ባልደረባ በተማሪዎች ላይ የደረሰው ጉዳት ከቀላል እስከ ከባድ መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን ጉዳቱ ያጋጠመው በድብደባ መሆኑንም ጠቁመዋል።ከዚህ በተጫማሪ ትናንት ምሽት የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በተፈጠረባቸው የደህንነት ስጋት ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ለመውጣት የሞከሩ ተማሪዎች ከግቢው እንዳይወጡ መከልከላቸውን ያነጋገራቸው ተማሪዎች ተናግረዋል። 1110 አማርኛው አገልግሎት ### Response:
### Text: የትምህርት ሚኒስትር ፕር ብርሃኑ ነጋ ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች ጋር ምክክር አደረጉበምክክር መድረኩ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትርፍ ባለፈ ማህበረሰቡን ማገልገል እንዳለባቸው ተገልጿልየትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በትምህርት ዘርፉ ላይ ካሉ የግል ተቋማት ጋር ግልፅ መናበብ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።ሚኒስትሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመንግስት ላይ የሚያነሱትን ቅሬታዎችን እንዲሁም ህብረተሰቡ በተቋማቱ ላይ የሚያነሳቸውን ቅሬታዎች እና ጥያቄዎች አንስተው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።ፕሮፌሰር ብርሀኑ በቀጣይ የትምህርት ዘርፉ የሚሄድበትን አቅጣጫ እና ለውጦችም ለተሳታፊዎች ገልፀዋል።በዚህም በመንግስት እና በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እኩል ቁጥጥር እንደሚደረግ እና በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የመውጫ ፈተናዎች በግል ከፍተኛ ተቋማትም እንደሚሰጡ ተናግረዋል።የግል ኮሌጆች የማስተማሪያ ፍቃድ አሰጣጥ ላይም ከፍተኛ ቁጥጥር እንደሚደረግም ገልፀዋል።በመድረኩ የግል ከፍተኛ ተቋማት አመራሮችም ለተቋማቱ አፈፃፀም እንቅፋት ናቸው ያሏቸውን ሀሳቦች ለሚኒስትሩ አቅርበዋል።ከዚህም ውስጥ የትምህርት አዋጁ ፣የመምህራን እጥረት፣ የመንግስት ድጋፍ አናሳ መሆን የተቋማቱ ተግዳሮቶች መሆናቸውን ነው የተናገሩት።ምንጭ ትምህርት ሚኒስቴር ### Response:
### Text: የዋጋ ጭማሪ የቢራ ፋብሪካዎች የዋጋ ጭማሪ ሊያደርጉ እንደሆነ ታወቀ፡፡ ቢጂአይ ኢትዮጵያ በምርቶቹ ላይ የዋጋ ጭማሪ አድርጎ ማከፋፈል መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡በአገሪቱ ውስጥ ቢራ ፋብሪካዎች ከዚህ ሳምንት ጀምሮ በማከፋፈያ ዋጋቸው ላይ የዋጋ ጭማሪ ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ መሆኑን የሪፖርተር ምንጮች የገለጹ ሲሆን፣ ቢጂአይ ግን ይህንን የዋጋ ጭማሪ ከትላንት ጀምሮ ተግባራዊ አድርጓል፡፡በትላንትናው ዕለት ቢጂአይ የዋጋ ለውጡን ተግባራዊ መሆኑን የሚያረጋግጠው፣ በማከፋፈያ ዋጋ የሚረከቡ ሆቴሎች 214 ብር ያወርዱ የነበረውን አንድ ሳጥን ቢራ በ251 ብር መግዛታቸው ነው፡፡ በተመሳሳይ 590 ብር የሚያወርዱትን አንድ በርሚል ድራፍት በ700 ብር እንዲረከቡ መደረጋቸውን የተለያዩ ሆቴሎች ገልጸዋል፡፡የቢራ ፋብሪካዎቹ ከሦስት ወራት በፊት የዋጋ ጭማሪ ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በወቅቱ ለጭማሪያቸው ምክንያት አድርገው የነበረው የውጭ ምንዛሪ ለውጥን ነበር፡፡ ሆኖም የፌዴራል የሸማቾች ጥበቃና የንግድ ውድድር ባለሥልጣን ጭማሪው ምክንያታዊ አይደለም በማለቱ ዋጋው ወደነበረበት እንዲመለስ ተደርጎ ነበር፡፡ፋብሪካዎቹ አሁን የዋጋ ጭማሪ ለማድረግ ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል የተባለው፣ ከአዲሱ የምንዛሪ ለውጥ ወዲህ ጥሬ ዕቃ ማስገባት በመጀመራቸውና በተለይ የብቅል ዋጋ ጭማሪ በመደረጉ እንደሆነ ታውቋል፡፡ምንጭ ሪፖርተር ### Response:
### Text: መንገዱ ተከፍቷል️በጸጥታ ችግር ምክንያት ከሁለት ቀን በላይ ተዘግቶ የበረው ከሐረር ጅግጅጋ የሚወስደው የመኪና መንገድ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።የመንገዱ መከፈትን አስመልክቶ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እንዳለው ከባቢሌ ወረዳው ስድስት ቀበሌ ገበሬ ማህበር የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ባስነሱት የጸጥታ ችግር ምክንያት መንገዱ ከሁለት ቀን በላይ ተዘግቶ ቆይቷል።00የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ ቦንሲቱ ኢብራሂም ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት መንገዱ የተከፈተው ያለምንም ግጭት የአካባቢውን ህብረተሰብ በሰላማዊ ሁኔታ በማወያየትና የጋራ ስምምነት ላይ በመድረሱ ነው።ተፈናቃዮቹ የአዋሳኝ ድንበር ሁኔታ መፈታት አለበት፣ በአካባቢው የዜጎች መፈናቀልና ሞት ሊቆም ይገባል እንዲሁም ተፈናቅለው በባቢሌ ከተማ የሚገኙ ዜጎች በዘላቂነት መቋቋምና ወደ ቀያቸው መመለስ አለባቸው በሚል ባቀረቧቸው ሐሳቦች ላይ በጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።ከእዚህ በተጨማሪ ተፈናቃዮች የወደመባቸው ቤትንብረት እንዲተካላቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን ወይዘሮ ቦንስቱ አመልክተዋል።በውይይቱ የሀገር መከላከያ፣ የዞኑ የጸጥታና የአመራር አካላት፣ የሀገር ሽማግሌዎችና0 የህብረተሰቡ ተወካዮች የተሳተፉ ሲሆን የተደረሰውን የጋራ ስምምነት ተከትሎም መንገዱ ከዛሬጠዋት ጀምሮ መከፈቱን ገልጸዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ህጋዊሰነድ እና ማስረጃ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር 116 ደረሷልህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር 116 መድረሱን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አሳወቀ።እስከ ባለፈው ሳምንት ድረስ ህጋዊ ሰነድ እና ማስረጃዎችን ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ፣ ያላመሟሉ እና ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ በሚል የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ማሳወቁ ይታወሳል ኤጀንሲው አያይዞም የተጠየቁትን ያላቀረቡ ተቋማትን በሚመለከት እስካላቀረቡ ድረስ የያዙትን ተማሪ ከማስጨረስ በቀር አዲስ ተማሪ መመዝገብ እንደማይችሉ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።እስከ ባለፈው ሳምንት ህጋዊ ሰነድ እና ማስረጃ ሳያመሟሉ እና ምንም ሳያቀርቡ ቀርተው የነበሩት የተቋማት ቁጥር 74 እንደነበሩ ይፋ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 18 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ የተጠየቁትን ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ማቅረባቸውን ኤጀንሲው ገልጿል። ይህም ሙሉ ለሙሉ ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር ወደ 116 ደርሷል።የቀሩት 58 ተቋማት ህጋዊ ሰነዶቹንና ማስረጃዎቹን እስቃላቀረቡ ድረስ አዲስ ተማሪ መመዝገብ እንደማይችሉ የተላለፈው ውሳን እንተጠበቀ መሆኑን እየገለጽን ያላቀረቡትን ለይተን ዝርዝራቸውን የምናሳውቅ ይሆናል።የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ### Response:
### Text: ከወደ ካናዳ የዳቦ ዋጋ ሲጨምር የነበረው ዳቦ አምራች 50 ሚሊዮን የካናዳ ዶላር በፍርድ ቤት ተቀጣ።ካናዳ ውስጥ ሆን ብሎ የዳቦ ዋጋ የጨመረ እንዲንር ያደረገ የዳቦ አምራች የ50 ሚሊዮን የካናዳ ዶላር ቅጣት መቀጣቱን ቢቢሲ ፅፏል።ድርጅቱ ካናዳ ብሬድ የሚባል ሲሆን ለዓመታት የዳቦ ዋጋ ሲጨምር እንደነበር አምኗል ተብሏል።የካናዳ የገበያ ውድድር ቢሮ ዳቦ ቤቱን ጠርጥሮ ለበርካታ ዓመታት ምርመራ ሲያደርግበት መቆየቱ የተነገር ሲሆን ቢሮው ዳቦ ቤቱ ላይ የተጣለው ቅጣት ሲያንስ እንጂ የሚበዛ አይደለም ብሏል።የቢሮው ሠራተኛ ማቲው ቦስዌል ናች የዳቦ ዋጋን ሆነ ብሎ መጨመር ሊያውም የካናዳዊያን የለተ ዕለት ማዕድ የሆነውን ዳቦ ይህ ትልቅ ወንጀል ነው 0 ሲሉ ተናግረዋል። ዋጋ የሚጨምሩ ሌሎች ሰዎችንም እያሳደድን ለሕግ እናቀርባለን ሲሉ አስጠንቅቀዋል።የገበያ ውድድር ቢሮ ሌሎች ዋጋ የጨመሩ ዳቦ ቤቶች ካሉ የእጃቸውን እንዲያገኙ እናደርጋለን ያለ ሲሆን የአንድ ዳቦ ዋጋ ማንም ሳያስተውለው በ16 ዓመታት ውስጥ የ1 ዶላር ከሐምሳ ዋጋ ጭማሪ ማምጣቱን ደርሼበታለሁ ብሏል።በካናዳ በርካታ ቸርቻሪዎች የዳቦ ዋጋ ጨምራችኋል ተብለው በቢሮው ዓይን ውስጥ የገቡ ሲሆን አንዳቸውም ግን ጥፋታቸውን አላመኑም ተብሏል።ቢሮው በቅርቡ ደግሞ የትኛው ሱፐርማርኬት የሸቀጥ ዋጋ እንደጨመረ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።መረጃው የቢቢሲ ነው። ### Response:
### Text: የድሬ ነዋሪዎች ለዶር አብይ ያስተላለፉትይህ መልእክት ለክቡር ለጠቅላይ ሚንስትራችን አብይ አህመድ ነው። እባኮትን ድሬ እያነባች ነው መጥተው ችግራችንን ያዳምጡ። ድሬ ከነልጆችዋ አልቅሳ እየለመነች ነው። እናመሰግናቸዋለን። ጥያቄዎቻችን ድሬድዋችን ብቃትና አቅም ባላቸው ልጆቿ ትመራ ነው ። በልማት ወደ ኋላ የቀረችው ፣ ፕሮጀክቶች በጊዜ ማለቅ ያልቻሉት ፣ በራሳችሁ ሪፖርቶች መሰረት አፈፃፀማችሁ ከ50 ፐርሰንት በታች የሆነው እናንተ አቅም ስለሌላችሁ ነው 40፣ 40፣ 20 ማንንም አልጠቀመም ሁሉም የሚጠቀመው ሁሉንም የሚጠቅም ስርአት ሲኖር ነው እንጅ በከፋፍለህ ግዛ አይደለም የህግ የበላይነት ይኑር ። ሁሉም ሰው በሰውነቱ በህግ ፊት እኩል ይሁን ። ባለስልጣናት እንዳሻቸው አይሁኑ ከተማዋን ያራቆቱ ሌቦችና ሙሰኞች ለህግ ይቅረቡ የመንግስት መኪኖችንና ንብረቶች እንዲሁም ገንዘብ ለግል ጥቅማችሁ አታውሉ ሰሞኑን በመንግስት ገንዘብ የተደገሰውን ድግስ ልብ ይሏል መልካም አስተዳደር ይስፈን ። ባለስልጣናት ቢሮ ይግቡ ፣ የህዝቡን ሮሮ አድምጠው መልስ ይስጡ ፣ አድሎና መድሎ ይቅር ናቸው ። ከዚህ ውጭ የሚያስተዳድረው ግለሰብ በብቃትና በፍትሃዊነት እስከመራ ድረስ ብሄሩ ጉዳያችን አይደለምየድሬ ልጆች ድሞ እባካችሁ ሼር እድርጉት ድምጻችን እንዲሰማ ተባብረው ያደረጉት ሁሌ ያሽንፋል አመሰግናለሁ ። አትከፋፈሉ እንድ ነን። ### Response:
### Text: በእነ አቶ ጃዋር ላይ ክስ ሳይመሰረት ቀረአቃቤ ሕግ በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባ ላይ ክስ የሚመሰርትበት ቀን ዛሬ የመጨረሻው የነበረ ቢሆንም በተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ ይመሰረታል ተብሎ ሲጠበቅ ተጠርጣሪዎቹ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።በዚህም አካልን ነጻ የማውጣት አቤቱታ ለፍርድ ቤት እንደሚያቀርቡ የእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጠበቃ አቶ ቱሊ ባይሳ ተናግረዋል።ጠበቃ ቱሊ ባይሳ ለ ከተናገሩት አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በ11 ሰዎች ላይ አቃቤ ሕግ ክስ ለመመስረት ለዛሬ ቀጠሮ ቢሰጥም እነአቶ ጃዋር ፍርድ ቤት አልቀረቡም። በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ ላይ 15 ሰዎች አሉ አቶ ጃዋርን ጨምሮ 11 ሰዎች ላይ ፍርድ ቤቱ ክስ ለመመስረት ቀጠሮ የሰጠው እስከ ዛሬ ድረስ ነበር። አራት ተጠርጣሪዎች ላይ ደግሞ እስከ ጳጉሜ 42012 ዓም ድረስ ክስ ይመሰረታል ተብሎ ነበር ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በመቅረታቸው ከጳጉሜ 5 ጀምሮ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በሕገወጥ መንገድ ታስረው ይገኛሉ። እነ አቶ ጃዋር ከዛሬ አርብ መስከረም 8 11፡30 ጀምሮ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ እውቅናና ፍቃድ ከሕግና ሥርዓት ውጭ ታስረው ነው ያሉት። ከዚህ በኋላ አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ ለፍርድ ቤቱ ይቀርባል።አቶ ጀዋር መሃመድ የድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ የተፈጠረ አለመረጋጋትን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ ሁለት ወራት አልፏቸዋል። ### Response:
### Text: መቐለ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከመቐለ ከተማና አካባቢው እንዲሁም ከትግራይ የክልል የተለያዩ ዞኖች ከተውጣጡ ተሳታፊዎች ጋር ተወያዩ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይት መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያን ያለ ትግራይ ትግራይንም ያለ ኢትዮጵያ ማሰብ አይቻልም ብለዋል።የትግራይ ተወላጆች የሃገር መውደድና ፍቅር የቆየ ታሪክ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትግራውያን ኢትዮጵያን ለመውረር የመጡ ሃይሎችን በመመከት ድንበራቸውን ማስጠበቃቸውን ጠቅሰዋል።በየትኛውም ጊዜ ቢሆን ኢትዮጵያዊነትን ለድርድር አለማቅረባቸውን ጠቅሰው ለዜጎች የነጻነትና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርም የትግራይ ተወላጆች መስዋዕትነት ከፍለዋል ነው ያሉት።ከዚህ ባለፈም የትግራይ ክልል የስልጣኔ፣ የዜማና ቅኔ መነሻ መሆኗንም ጠቅሰዋል ትግራውያን ለኢትዮጵያ አነድነትና መጠንከር ሲታገሉ እንደነበር በማውሳት።በሃገሪቱ የተደረገው የነጻነትና የዴሞክራሲ ትግል ከዳር እንዲደርስም ከፍተኛ ሚና መጫታቸውንም ጠቅላይሚኒስትሩ አንስተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው መጭው ጊዜ የሰላምና የልማት ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው መላው ህዝብ ፊቱን ለሰላምና ልማት ሊያዞር እንደሚገባም አስረድተዋል።የትግራይ ህዝብ ያለውን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት ተባብረን እንሰራለንም ብለዋል በንግግራቸው።ምንጭ ### Response:
### Text: እግር ኳስ ለሰላም እጦት ምክንያት ሊሆን አይገባም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝዳንትእግር ኳስ ለፍቅርና ለአንድነት እንጂ ለሰላም እጦት ምክንያት ሊሆን አይገባም ሲሉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴረሽን ፕረዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ገለጹ።ከሰባት ወራት በፊት በአዲስ አበባ ስታዲዮም የኢትዮጵያ ቡናና መቀሌ 70 እንደርታ እግር ኳስ ክለቦች ሲጫወቱ ደጋፊዎች በፈጠሩት ችግር ለደረሰው ጥፋት ትላንት በመቀለ ከተማ የይቅርታ ስነስርዓት ተኳሄዷል፡፡በስነስርዓቱ ወቅት የተገኙት አቶ ኢሳያስ ጅራ ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ህዝብ በስነ ምግባሩ የታነፀ ኢትዮጵያዊነት የሚያስተምር ስፖርተኛ ይፈልጋልብለዋል።የስፖርትን ልማት ለማጠናከር ሁሉም አመራር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅበት አመልክተው እግር ኳስ ለፍቅርና ለአንድነት እንጂ ለሰላም እጦት ምክንያት ሊሆን አይገባም ሲሉ ገልጸዋል።የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ስራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ0 በቀለ እና የመቀሌ 70 እንደርታ ክለብ ስራ አስኪያጅ0 አቶ ሽፈራው ተክለኃይማኖት በወቅቱ በተፈጠረው ችግር ይቅርታ በመባባል0 መልካም ግንኙነታቸውን ለማጠናከር የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡ጥር 14 ቀን በትግራይ ዘመናዊ ስታዲዮም የኢትዮጵያ ቡና ከመቀሌ 70 እንደርታ ጋር0 የፕሪሜር ሊግ0 ውድድራቸውን የሚካሄዱ መሆናቸውን በዚሁ ስነስርዓት ወቅት ተገልጿል፡፡0ምንጭ ### Response:
### Text: ቦርደዴ አካባቢ በተፈጠረ ግጭት 7 ሰው ሞተ ከሀረር ወደ ኢዲስ አበባ በሚወስደው መንገድ ልዩ ስሙ ቦርደዴ አካባቢ በተፈጠረ ግጭት ሰባት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ። በአካባቢው በተፈጠረ ግጭት መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ምንም ዓይነት መኪና እንዳያልፍ ተዘግቷል፡፡ከሀረር ወደ አዲስ አበባ ፣አዳማ እንዲሁም ሌሎች አካቢዎች ለመሄድ የተሳፈሩ ተጓዦች ከማለዳው 2 ሰዓት ጀምሮ መንገዱ መዘጋቱን እና በረሀ ላይ መሆናቸውን መንቀሳቀስም እንዳልቻሉ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡ጥቆማውን የሰጡ ግለሰቦች እንዳሉት ከቦርደዴ አዋሽ መግቢያ ድረስ መኪኖች መንቀሳቀስ ባለመቻለቸው ተሰልፈው መቆማቸውን እና ይህ ነው ብሎ የተፈጠረውን ችግር ያስረዳቸውም ሆነ መፍትሄ የነገራቸው አካል እንደሌለ ጠቁመዋል፡፡ መንገዱ የተዘጋውም በግጭት ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ ወደ አሰብ አስክሬን ጭኖ የሚያልፍ መኪና ማየታቸውንም አክለዋል፡፡የሚመለከተው አካል ጉዳዩን አጣርቶ መፍትሄ እንዲሰጣቸውና የተፈጠረውን ችግር እንዲያስረዳቸውም ጠይቀዋል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎችም ቢሆኑ ግጭት መፈጠሩን ያረጋገጡልን ሲሆን ተፈጠረ ባሉት ግጭትም 7 ሰዎች ሞተዋል 3 ሰዎች ደግሞ በህይወት እና በሞት መካከል ናቸው ብለዉናል፡፡ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ጉዳዩን እያጣራ እንደሚገኝ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ገልጿል።ምንጭ ኢትዮ ኤፍ ኤም ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኤፍ ቢ ሲ የተናገሩትየሀይል መቋረጡ ከጊቤ 2 የሀይል ማመንጫ ከሚነሳው የሀይል ማስተላለፊያ መስመር ጋር የተያያዘ ነው። ከጊቤ 2 የሀይል ማመንጫ የሚነሳው እና ወደ ሰበታ እና ወደ ሶኮሮ የሚሄደው 400 ኪሎ ቮልት ሀይል ተሸካሚ ከፍተኛ መስመር በአካባቢው በነበረ ንፋስ በቀላቀለ ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት ችግር ገጥሞት ነበር። በዚህ ምክንያት በዚህ መስመር የሚያልፈው ሀይል ከጊቤ 3 ተነስቶ ከወላይታ ሶዶ ወደ ገላን ወደሚገባው መስመር ሀይሉን ልኳል። በዚህ ወቅት ከጊቤ 3 የሚነሳው እና ብዙሃኑን የሀገሪቱን የሀይል ፍላጎት የሚያሟላው መስመር ይህ ሀይል ሲመጣበት ራሱን በራሱ አቋርጣል። ሰዓቱ ከፍተኛ ሀይል ጥቅም ላይ የሚውልበት በመሆኑም ከቀሩት የሀይል ማመንጫዎች የሚገኘው ሀይል ፍላጎቱን ማሟላት እንዳልቻለ እና አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል አቅርቦቱ ተቋርጧል። የችግሩ ምንጭ በመታወቁ እና ማስተካከያ በመደረጉም እስከ ንጋቱ 11 ሰዓት ድረስ ሀይል ተቋርጦባቸው ከነበሩ አካባቢዎች መካከል አብዛኛዎቹ አገልግሎቱ ተመልሶላቸዋል። ችግሩ ሙሉ በሙሉ ቢቀረፍም የአዳንድ መስመሮችን ደህንነት የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ በመሆኑ በተወሰኑ አካባቢዎች አሁንም ሀይል እንዳልመጣ እና ደህንነት የማረጋገጡ ስራ እንደተጠናቀቀ አገልግሎቱን ያገኛሉ። ### Response:
### Text: ጳጉሜ 12012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 769 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 7 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 542 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 22 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 5 ከአሶሳ ከተማ መናኸሪያ 7 ከጾሬ ስደተኛ መጠለያ 1 ከማኦ ኮሞ ጉራስምቦላ ስደተኛ መጠለያ 6 ከደቡስ ኬላ 3 ከሸርቆሌ ስድተኛ መጠለያ በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 7802 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 84 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ከባህር ዳርበቫይረሱ ከተያዙት መካከል 23 ከሰሸዋ ዞን 21 ከሰወሎ ዞን 13 ከጎንደር ከተማ 9 ከባህር ዳር ከተማ 6 ከምዕጎንደር ዞን 6 ከደጎንደር ዞን ይገኙበታል። በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1957 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 41 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 31 ሰዎች ከማህበረሰቡ የተገኙ ናቸው። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 4022 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 506 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 269 ከምስራቅ ሸዋ 51 ከዱከም ከተማ 46 ደምዕሸዋ 28 ከፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን 25 ከሰሜን ሸዋ 20 ከሰበታ ከተማ 13 ከሞጆ ከተማ 10 ከምስራቅ ሀረርጌ 8 ከአምቦ ከተማ 8 ከቢሾፍቱ ከተማ ይገኙበታል። ### Response:
### Text: የ4ቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጉዳይ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የሚገኙ አራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ላይ ሲያካሂድ የነበረውን የወንጀል ምርመራ ማቋረጡን አስታወቀ፡፡ምርመራቸው እንዲቋጥ የተደረጉት የጦር መኮንኖች1 ሜጀ መሀመድ ኢሻ ዘይኑ ትኩእ2 ብጀ ሙሉጌታ በርሄ ይልማ3 ኮል ገእግዚአብሔር ገሚካኤል እና4 ኮል ገዋህድ ኃይሉ መሸሻ ናቸው፡፡በጥቅምት 242013 በሰሜን ዕዝ ላይ በተሰነዘረው ጥቃት ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩት መኮንኖቹ የመከላከያ ሰራዊት ባደረገው ክትትል ተይዘው ለምርመራ ቡድኑ ተላልፈው የተሰጡ መሆናቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡በዚሁ መሠረትም ተጠርጣሪዎቹ ፈጸሙ በተባሉበት ወንጀል ምርመራ ሲካሄድባቸው የቆዮ ቢሆኑም የምርመራ ቡድኑ ባደረገው ማጣራት የወንጀል ተሳትፎአቸው ዝቅተኛ መሆኑን በመገንዘብ ምርመራው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ መደረጉን ፌደራል ፖሊስ አሳውቋል ሲል ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።በሌላ በኩል ደግሞ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመጀራ ቡድን ሃላፊ ኮማንደር አበራ የጦር መኮንኖቹ ጊዜ ቀጠሮ ነው የተቋረጠው እንጅ ተጠርጣሪዎቹ ነፃ ናቸው አለመባሉን እና ከእስር ያልተፈቱ መሆናቸውን በመጠቆም ጉዳያቸው ወደ መከላከያ ጦር ፍርድ ቤት መዞሩን ጠቁመዋል ብሏል። ### Response:
### Text: ቀይ መስቀል አአ ቅርንጫፍ ተለዋጭ ቦታ ተሰጠው።በአዲስ አበባ ከተማ ከ1973 ዓም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ያለው የቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽቤት ተለዋጭ ቦታ ማግኘቱንና ከኅዳር 9 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ ወደ አዲሱ ሕንፃ ተዘዋውሮ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ፡፡የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሰብዓዊ፣ የዲፕሎማሲና የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ሰለሞን ዓሊ ዶር የአዲስ አበባ ከተማ የቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ይገለገልበት የነበረውን ቦታ ለልማት በመፈለጉ ምክንያት የቦታ ይዞታውን እንዲለቅ ተደርጓል ብለዋል።በዚህ መሠረት የከተማ አስተዳደሩ በምትኩ ሰእሊተ ምሕረት አካባቢ ከሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ፊት ለፊት የሚገኘውን የቀድሞ የማምረቻዎች ልማት ኤጀንሲ ጽሕፈት ቤት የነበረውን ጂ4 ሕንፃ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አገልግሎት እንዲውል በስጦታ መልክ ማበርከቱን ኃላፊው ገልፀዋል።አዲሱ ጽሕፈት ቤት ከ15 በላይ አምቡላንሶችን የመያዝ አቅም እንዳለው የሚናገሩት ዶር ሰለሞን፣ ከዚህ ቀደም አገልግሎት ይሰጡበት ከነበረው ሕንፃ የተሻለ፣ እንዲሁም እጅግ ዘመናዊ የሆነ ነው ሲሉ ተናግረዋል።ቀይ መስቀል አአ ቅርንጫፍ ከዚህ ቀደም የነበረበት ሕንፃ መፍረሱን ተከት ቅሬታ ማስነሳቱ በተለይም ደግሞ ለተቋሙ የሚሆን ተለዋጭ ቦታ አለመሰጠቱ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም። ሪፖርተር ### Response:
### Text: አዲስአበባ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ይፋ እስኪደረግ ድርስ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ አካላት በነባሩክፍያታሪፍ በሙሉ አቅም ሊሰሩ ይገባል ተብሏል።የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም ተቋማት፣ የታክሲና ሀይገር ባለንብረቶች ማህበራትና ግለሰቦች አዲስ የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ እስኪደረግ ድረስ በነባሩ የክፍያ ታሪፍ መሰረት አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ ገልጿል።ከነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ ጋር ተያይዞ አገልግሎቱን በተገቢው መንገድ የማይሰጡና ህብረተሰቡን ለተለያዩ እንግልቶችና አላስፈላጊ ወጪዎች የሚዳርጉ ማንኛውም የህዝብ ትራንስፖርት ሰጪ አካላት ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ወደ ስራ እንዲገቡ በማይገቡትም ላይ ቢሮው አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።ቢሮው ያለምንም ቅድመ ሁኔታና በህጋዊ መንገድ ለተቋሙ ሳያሳውቁ ከስራ ገበታቸው የወጡት የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶቡስ አገልግሎት ሰጪ ማህበራት በገቡት ውል መሰረት መብታቸውን እየጠየቁ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው አሳስቧል።የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶብሶች ስራቸውን ካቆሙ ቀናት የተቆጠረ ሲሆን ባለንብረቶች በሰጡት ቃል ስራ ያቆሙት ከሁለትና ሶስት ወር በላይ ውል ስላልታደሰለቸው እና ተገቢ ክፍያ እየተከፈላቸው ስላልሆነ መሆኑን መግለፃቸው ይታወሳል። 70126 ### Response:
### Text: አማራ ከፊታችን ያሉት ሃማኖታዊ በዓላት በአደባባይ እንዲከበሩ ተፈቀደ።የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ በአማራ ክልል ለመውሊድ ፣ ደመራ እና መስቀል በዓላት መሰባሰብን ፈቀደ።ዕዙ መስከረም 16 እና 17 2016 የሚከበሩት የመውሊድ፣ የደመራና የመስቀል በዓላት በአማራ ክልል የሃይማኖቶቹ ሥርዓት በሚፈቅዱት መንገድ እንዲከበሩ እየሰራሁ ነው ብሏል።ምንም እንኳን የሕዝብ ስብሰባዎች በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ ቢከለከሉም መስከረም 16 እና 17 የሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት የአደባባይ በዓላት በመሆናቸው ለበዓላቱ ሥነ ሥርዓት ሲባል የአደባባይ መሰባሰብን መፍቀዱን ገልጿል።ዕዙ እነዚህ መሰባሰቦች ለሃይማኖታዊ የበዓል አከባበር ሥነ ሥርዓት ብቻ0 የሚውሉ እንደሆነ አሳውቋል። የአደባባይ መሰባሰቦች የበዓላቱ አከባበር ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ብቻ የሚከናወኑ ገልጿል።በእነዚህ አከባበሮች ወቅት ለሕዝብ ደኅንነት ሲባል ከጸጥታ አካላት ጋር መተባበር ግዴታ እንደተጣለ አሳውቋል።በአማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ከክልሉ አስተዳደር አቅም በላይ በመሆኑ ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት ባቀረበው ጥሪ መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል።በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተቀመጡ ክልከላዎች አንዱ ደግሞ መሰባሰብ ነው። ከቀናት በኃላ በሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት ላይ ስነሥርዓቶቹ ተከናውነው እስኪያልቁ መሰባሰብ መፈቀዱ ይፋ ተደርጓል። ### Response:
### Text: የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት በሐገሪቱ ዉስጥ ለሚሰሩ የዉጪ ሐገር ባለሙያዎችና ባለወረቶች ቋሚ የመኖሪያ ፍቃድ ሒቃማ ሊሰጥ ነዉ። እስካሁን ድረስ ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ የሚሰራ የዉጪ ሐገር ባለሙያም ሆነ ባለሐብት መኖሪያ ፍቃድ የሚያገኘዉ የሳዑዲ አረቢያ ዜጋ ከሆነ ቀጣሪዉ ወይም የሐብት ተሻራኪዉ ግለሰብ ወይም ኩባንያ ነዉ። የሳዑዲ አረቢያ ምክር ቤት ሹራ ባለፈዉ ሳምንት ባፀደቀዉ ደንብ መሠረት ለዉጪ ሐገር ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ የሚሰጠዉ የሐገሪቱ መንግስት ነዉ።ዩናይትድ ስቴትስ «ግሪን ካርድ» በምትለዉ የመኖሪያ ፈቃድ አምሳያ ይዘጋጃል የተባለዉ ፈቃድ «ጎልደን ካርድ» የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ፈቃዱ በተለይ በተለያዩ ሙያዎች የሰለጠኑ የዉጪ ሐገር ሠራተኞችና ባለሐብቶች ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ እንዲሠሩና እንዲወርቱ ለማማለል ያለመ ነዉ። ፍቃዱን ለማግኘት ግን ባለሙያዉ ቀጣሪ ባለሐብቱ ደግሞ የሚሰራበት የሥራ መስክ ማግኘት ይኖርባቸዋል። በንጉሳዊቱ አረባዊት ሐገር አሰራር መሰረት የሐገሪቱ ምክር ቤት ያፀደቀዉ ረቂቅ የሚፀናዉ የሐገሪቱን ንጉስ ይሁንታና ፅዲቂያ ሲያገኝ ነዉ። የሳዑዲ አረቢያ ነገስታት ባለፉት ሰወስት ዓመታት «ሕገወጥ» ያሏቸዉን የዉጪ ሐገር ዜጎች በጅምላ ሲያባርሩ ነበር። ሕጋዊ መኖሪያ ፈቃድ ያላቸዉ የዉጪ ሐገር ተወላጆች ደግሞ ለራሳቸዉና ለየቤተሰቦቻቸዉ አባላት በነብስ ወከፍ ግብር ተጥሎባቸዋል። ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና️በሕንድ በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ 19 ተማሪዎች መሞታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታወቁ።በትምህርት ቤቱ የተነሳው ቃጠሎ ተፋፍሞ ጥቁር ጭስ በመስኮቶቹ መውጣት እንደጀመረ፣ ተማሪዎች ነፍሳቸውን ለማትረፍ በመስኮት ሲዘሉ መታየታቸው ተዘግቧል።በእሳቱ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎቹ አብዛኛዎቹ ታዳጊዎች ናቸው የተባለ ሲሆን በትምህርት ቤቱ የማጠናከሪያ ትምህርት እየወሰዱ ነበር።እሳቱ የተነሳበት ምክንያት ባይታወቅም ተማሪዎች በብዛት ወደሚገኙበት ክፍል የተዛመተው ተቀጣጣይ በሆነው ኮርኒስ ሰበብ ነው ተብሏል።20 ተጨማሪ ተማሪዎች ከፍተኛ ጉዳት ያጋጠማቸው ሲሆን በጉጅራት በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ሕክምና እያገኙ ነው።ለፈረንሳዩ የዜና ወኪል ተማሪዎቹ ሕይወታቸውን ያጡት በእሳቱ ምክንያትና ከእሳቱ ለማምለጥ በመስኮት በሚዘሉበት ወቅት ነው ያሉት የአካባቢው ባለስልጣን የሆኑት ዲፓክ ሳፕታሌ ናቸው።ሮይተርስ እንደዘገበው ሟቾቹ በአጠቃላይ እድሜያቸው ከ20 በታች ሲሆን እሳቱ መወጣጫ ደረጃ አካባቢ በመከሰቱ መንቀሳቀስ ባለመቻላቸው ሕይወታቸውን አጥተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በትዊተር ገፃቸው ሐዘናቸውን ገልጠው የአካባቢው ባለስልጣናት አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። የአደጋው መንስኤ ተጣርቶ በሦስት ቀን ውስጥ ውጤቱ ይፋ አንዲደረግ ታዟል። ### Response:
### Text: ኢቦላ ኢትዮጵያ የኢቦላ ወረርሽኝን ቀድሞ ለመከላከል የህክምና ባለሙያዎች በመላ ሃገሪቱ መሰማራታቸውን የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ለቅድመ መከላከል ስራውም ከ290 በላይ የህክምና ባለሙያዎች በመላ ሃገሪቱ መሰማራታቸውን ነው ኢንስቲቲዩቱ የገለፀው።የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር በየነ ሞገስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ወረርሽኙ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ የቅድመ መከላከል እና የቁጥጥር ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።በዚህም በቦሌ፣ ድሬዳዋ፣ መቀሌ እና ባህር ዳር አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች የተጓዦችን የሰውነት ሙቀት በመለካት የልየታ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በየብስ ትራንስፖርት ወደ አገር ወስጥ በሚገቡ መንገደኞች ላይ ደግሞ በ21 የፍተሻ መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ክትትል በመደረግ ላይ መሆኑንም ገልፀዋል።በተለይም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚመጡ መንገደኞች ነጻ መሆናቸውን ለማረጋገጥ እስከ 21 ቀን ድረስ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። እስካሁንም ከ17 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ልየታ የተደረገባቸው መንገደኞች የ21 ቀን ክትትል ተደርጎላቸው ነጻ መሆናቸው ታውቋል።በአጠቃላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ኬላዎች የልየታ ማዕከል ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑንም የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል። ### Response:
### Text: ለታማኙ የፓሊስ አባል የማዕረግ እድገትና የገንዘብ ሽልማት ተበረከተለት በአፋር ክልል ኤሊደአር ወረዳ በህገወጥ መንገድ ወደ መሀል ሀገር ሊገባ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ላዋለ የፖሊስ አባል የማእረግ እደገትና የገንዘብ ሽልማት ተበረከተለት። የወረዳው ፖሊስ አባል የሆነው ሲራጅ አብደላ የዋና ሳጅነት ማዕረግና የ50 ሺህ ብር ሽልማት ከክልሉ ርዕሰመስተዳድር አቶ አወል አርባ እጅ ተቀብሏል።ዋና ሳጅን ሲራጅ አብደላ የማእረግና የገንዘብ ሽልማቱ የተበረከተለት መስከረም 6 ቀን 2012 አም ወደመሃል ሀገር ሊገባ የነበረ 29 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ በመያዙ ነው። ዋና ሳጅን ሲራጅ በወቅቱ መሳሪያው ወደ መሀል ሀገር እንዲያልፍ ከህገወጥ ነጋዴዎች ሊሰጠው የነበረውን 40 ሺህ ብር የመደለያ ገንዘብ አልቀበልም በማለት መሳሪያው እንዲያዝ አድርጓል።የአፋር ክልል ርእስ መስተዳደር አቶ አወል አርባ የማእረግ አድገቱን በሰጡበት ወቅት አንደተናገሩት የፖሊስ አባሉ የፈጸመው ተግባር የክልሉን ህዝብና መንግሰት ብቻ ሳይሆን ሀገርንም ያኮራ ነው። ከግል ጥቅሙ ይልቅ ሀገር ወዳድነትና የህዝብ አገልጋይነት የሆነውን ፖሊሳዊ ተግባር በተጨባጭ አሳይቷልብለዋል። ዋና ሳጂን ሲራጅ አብደላ በበኩሉ የተሰጠው የማረግ እድገትና የገንዘብ ሽልማት ለእሱ ብቻ ሳይሆን ለሌችም ኃላፊነታቸውን ለተወጡ የፖሊስ አባለት ማበረታቻ መሆኑን ገልጻል። ### Response:
### Text: የዘንድሮ የሐጅ አድራጊ ክፍያ 315000 ብር እንዲሆን ተወስኗል።የ14442015 የሁጃጆች ምዝገባ በ16 የምዝገባ ጣቢያዎች እንደሚካሄድ የተገለፀ ሲሆን የአንድ ሐጅ አድራጊ ክፍያ ብር 315000 ሶስት መቶ አስራ አምስት ሺህ እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል።ይህ የተሰማው በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ14442015 ዓል የሐጅ ምዝገባ በተመለከተ እየሰጠ በሚገኘው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።በመግለጫው የሐጅ ተጓዥ ለምዝገባ በአካል መቅረብ ይኖርበታል የተባለ ሲሆን ማንኛዉም ተመዝጋቢ የሚከተሉትንን መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል 1 የታደስ የነዋሪነት መታወቂያ መንጃ ፈቃድ2 የጉዞ ሰነድ ፖስፖርት የመጠቀሚያ ጊዜው ለመጠናቀቅ ከ9 ወራት በላይ የቀረው መሆን ይኖርበታል፡፡3 አንድ ጉርድ ፍቶ ግራፍ4 የኮቪድ ክትባት የወሠደበት ማስረጃ እንዲሁም የቢጫ ወባ ክትባት ካርድ ቢጫ ካርድ ማቅረብ ይጠበቅበታል።5 እራሳቸዉን ችለው የሐጅ ስርዓቱን መፈፀም የሚችሉ ወይም አስፈላጊውን መስፈርት አሟልተዉና ክፍያ ከፍለው ሊያግዛቸው የሚችል ሰው ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።ከእስልምና መሰረቶች ውስጥ አንዱ የሆነዉና አቅሙ ለፈቀደት ሙስሊም ወንድም ሆነ ሴት በዕድሜ ዘመኑ ቢያንስ አንድ ጊዜ ሐጅ የማድረግ ግዴታ እንዳለበት መሆኑ ይታወቃል።ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟልምንጭ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ### Response:
### Text: የባለስልጣኑ እስር የኦሮሚያ ክልል ፍትህ ቢሮ ቃል አቀባዩ አቶ ታዬ ዳንዳአ ከመታሰራቸው በፊት በራሳቸው የፌስቡክ ገፅ ላይ ከዚህ በታች ያለውን ፅሁፍ ለጥፈው ነበር። ፅሁፉ ቅዳሜ ሞያሌ ውስጥ በስህተት ነው ስለተባለው የዜጎች ግድያ የሚመለከት ነውየምን ስህተት ሊሆን አይችልም ትላንት ሞያሌ ላይ ከአስር ያላነሱ ንፁሃን ዜጎች ሲገደሉ ከደርዘን በላይ ቆስሏል። ወንጀሉን የፈፀመዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ናቸዉ። ኮማንድ ፖስት ደግሞ ጭፍጨፋዉ የተፈፀመዉ በስህተት ነዉ ይላል። ይህ በንፁሃን ደም መቀለድ ነዉ ከፍ ሲል ደግሞ የኦሮሞን ህዝብ መሳደብ ምንም አይነት የተለየ እንቅስቃሴ ባልነበረበት ከተማ ላይ በጠራራ ፀሃይ ያን ያህል ህዝብ መፍጀት ፈፅሞ በስህተት ሊሆን አይችልም። በኮማንድ ፖስቱ የበላይ ሀላፊዎች ታቅዶ የተፈፀመ የጅምላ ጭፍጨፋ ስለመሆኑ ጥርጥር የለዉም። ከመነሻዉ አዋጁን አጭበርብረዉ ያሳለፉት ለዝሁ ነበር። ተጠያቂነት ካለ የላይኞቹን ማየት ነዉ በነገራችን ላይ በኮማንድ ፖስት የላይኛዉ ኮሚቴ ዉስጥ አንድም ኦሮሞ አልተካተተም። ይህ ለምን ሆነ በቂ ምክንያት ይኖሯልአንዳንድ ምንጮች አቶ ታዬ የታሰሩት በፌስቡክ ላይ በፃፉት ፅሁፍ እና ከ እንዲሁም ከ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ላይ በተናገሯቸው ንግግሮች እንደሆነ ይገምታሉ።በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መረጃዎች የሚወጡ ከሆነ ተከታትዬ አደርሳችኃለሁ ### Response:
### Text: ያየነውን እንመሰክራለንባለፉት ዓመታ በኢትዮጵያ የእግር ኳስ ሜዳዋች ሲፈጠሩ የነበሩትን ክስተቶች ሁላችንም የምናውቀው ነው። በየጊዜው ተስፋ ሲያስቆርጡን፣ በሀዘን ውስጥ ሲከቱን የነበሩ ክስተቶች ነበሩ። እዚህ መዘርዘር አያስፈልግም። ዘንድሮ ግን በእግር ኳስ ሜዳዎቻችን ላይ ያየነው ለውጥ እጅግ ድንቅና ሊበረታታ የሚገባው ነው። ይህ ነው የሚባል ችግር ሳንሰማ ዛሬም በአስደማሚ የሜዳ ላይ ትዕይንቶች እየተገረምን ፣ ተስፋችን እየለመለመ ነው እውነትም እግር ኳስ የፍቅር እና የሰላም ፣ የህዝብ አቀራራቢ መሆኑን የመሰከርንበት ነው።ማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ዘውትር የሚጠመዱት ግጭትን በማያባብሱ ጉዳዮች፣ በስድብ፣ በጥላቻ፣ በክፋት በመሆኑ ሁሉም ነገር ጨለማ ሆኖ እንዲታየን ያደርጉታል። በሀገራችን መልካም ስራዎች እንደ ክፉና መጥፎ ድርጊቶች ጎልተው አይደመጡም ሽፋን አያገኙም። ግጭቶች ፣ አለመግባባቶች ግን ሰፊ ሽፋን ይሰጣቸዋል። እኛ የቲክቫህ ቤተሰቦችን ያየነውን እንመሰክራለን። ዘንድሮ በእግር ኳስ ሜዳዎች፣ በደጋፊዎች ፣ በተጫዋቾች ያየነው ለውጥ ልባችንን በተስፋ ሞልቶታል በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም የእግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ፣ ተጫዋቾች ፣ አሰልጣቾች ፣ የፀጥታ አስከባሪዎች ፣ የስፖርት አመራሮች ላሳያችሁን መልካም ስራ ፣ ለሰጣችሁን ትልቅ ተስፋ እናመሰግናለን።መልዕክቶቻችሁን ትግራይ ስታድየም ### Response:
### Text: ነገ የሚዘጉ መንገዶች የኢትዮጵያዊነት ቀንነገ ሰኞ ጳጉሜ 1 ለኢትዮጵያ ክብር እቆማለሁ እዘምራለሁ በሚል መሪ ቃል በመስቀል አደባባይ ዝግጅት ይኖራል።ይህን ዝግጅት አስመልክቶ ከጠዋቱ 1130 ጀምሮ መርሃ ግብሩ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል። ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ኡራኤል ቤክ ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ኦሎምፒያ ከሸራተን ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ ሀራምቤ ትራፊክ መብራት ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ለገሃር ትራፊክ መብራት ላይ ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ብሄራዊ ቤተ መንግስት ከተክለሀይማኖት ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ብሔራዊ ቲያትር ከቼርቸል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ጥላሁን አደባባይ ዝግ የሚሆን ሲሆን ለከባድ ተሽከርካሪ ከጎተራ ወደ መስቀልአደባባይ ለሚመጡ መንገዱ አጎና ሲኒማ ላይ የሚዘጋ ይሆናል።ከዚህም በተጨማሪ በነዚህ መንገዶች ላይ ተሽከርካሪን ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት አቁሞ መሄድ ተከልክሏል።አሽከርካሪዎች ከላይ የተዘረዘሩት መንገዶች ዝግ መሆናቸውን አውቀው አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል። ### Response:
### Text: ዛሬ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ አውጥቶ ነበር።በዚህም መግለጫው ላይ ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይቀርብ እንቅፋት ሆኖ መቀጠሉን አስገንዝቧል።የመንግስት ኮሚኒኬሽን እንደ ዓለም ጤና ድርጅት አይነት ለሁሉም ሰው በእኩል ቆመናል የሚሉ አለምአቀፍ ተቋማት ግን አሸባሪው ቡድን የአማራና አፋር ክልሎችን በወረረበት ወቅት ሀስፒታሎችንና የጤና ጣቢያዎችን ሲዘርፍና ሲያወድም ንፁሃንን ሲደፍርና ሲገድል የሽብር ቡድኑን ድርጊት ሲያወግዙ አልተደመጡም ብሏል። ይልቁንም መንግስት ወደ ትግራይ ክልል እርዳታ እንዳይገባ እያደረገ ነው በሚል የአሸባሪው ቡድን የሚያሰማውን ፕሮፖጋንዳ ተቀብለው እያስተጋቡት ይገኛል። ይህ በመንግስት ዘንድ ፍፁም ተቀባይነት የለውም ሲል አሳውቋል።የመንግስት ኮሚኒኬሽን አሁንም ለአንድ ወገን ባጋደለው አቋማቸው በመጽናት የሽብር ቡድኑ ወደ ትግራይ የሰብአዊ እርዳታ እንዳይገባ እንቅፋት መሆኑን በግልጽ አለማንሳታቸው በተዛባ አመለካከታቸው መጽናታቸውንና ውግንናቸው ለህዝብ ጥቅም ሳይሆን ለፖለቲካ አጀንዳ መሆኑን ያመለክታል ሲል ገልጿል።የኢትዮጵያ መንግሥት ለትግራይ ክልል ህዝብ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ያለ ምንም መስተጓጎል እንዲቀርብ ለማስቻል በየጊዜው ከአጋር አካላት ጋር ምክክሮችን በማድረግ እየሠራ ይገኛል ሲል አሳውቋል። ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: የወላይታ ብሄር ተወላጆች ውይይት አደረጉየማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማችንን በማዘመን ሚዲያ ለህዝቦች ትስስርና ለሀገር ግንባታ አዎንታዊ ሚና እንዲጫወት ከማድረግ ባሻገር በህዝቦች ዘንድ ግጭት የሚቀሰቅሱ መረጃዎችን ባለማሰራጨት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት።የወላይታ ብሔር ተወላጆች ከሌሎች ህዝቦች ጋር ቀድሞ የነበረውን ፍቅር፣ ሰላም፣ አንድነት እና የመቻቻል እሴታቸውን በማጠናከር ለሰላምና ለሀገር ግንባታ የበኩላቸውን ድርሻ ማበርከት አለባቸው፡፡በወላይታ እና በሲዳማ ህዝቦች መካከል የተፈጠረውን የሰላም፣ የአብሮነትና የመቻቻል እሴቶችን ለማስቀጠል ተከታታይ ያለው ህዝብን የማወያየት ሥራ ይሰራል።የወላይታ እና የሲዳማ ህዝቦች ትስስር በጊዜያዊ ግጭቶች የሚሸረሸር ሳይሆን ትናንትም የነበረ ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ ስለሆነም ሰላም በዋጋ የማይተመን ትልቅ ሀብት ስለሆነ እጅ ለእጅ ተያይዘን ድህነትን ለማሸነፍ ልንሠራ ይገባል ብለዋል፡፡የወላይታ እና ሲዳማ ህዝቦች የግጭት ታሪክ የሌላቸው ከመሆናቸውም ባሻገር በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ ህዝቦች ናቸው፡፡ሰላም ለአንድ ሀገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ የወላይታ ብሔር ተወላጆች በሚኖሩበት አከባቢ ለሀገር ሰላም የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።ሀዋሳ ጥር 04052011 የወላይታብሔርተወላጆች0112 ### Response:
### Text: አረንጓዴአሻራ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና በሚኒስቴሩ ስር የሚገኙ 15 ተጠሪ ተቋማት በቦሌ ለሚና በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሐምሌ 152011 የችግኝ ተከላ አካሄዱ፡፡ከ3800 በላይ ሠራተኞች በተሳተፉበት በዚህ የችግኝ ተከላ ከ22000 በላይ ችግኞችን በቦሌ ለሚና በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለመትከል ተችሏል፡፡ በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ በነበረው የቸችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተሳተፉት የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተካ ገብረየሱስ እንደገለፁት ይህ የችግኝ ተከላ መርሃግብር በዋናነት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ አቅም መፍጠሪያና በሐምሌ 222011 የሚካሄደው ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ ቀን መንደርደሪያ ነው ብለዋል፡፡ ሐምሌ 22 ለሚካሄደው ሀገራዊ የችግኝ ተከላ ሁሉንም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞችን ማሳተፍ እንዲቻል የቅድመዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አውስተው በእለቱም በኦሮሚያ ክልል በፍቼ ከተማ አካባቢ 80000 ችግኞች እንደሚተከሉ ገልፀዋል፡፡በችግኝ ተከላው የተሳተፉ ሠራተኞች እንደገለፁት በዚህ ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ ቀን ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ በመቻላቸው የተሠማቸውን ደስታ ገልፀው በሀገራዊው የሠላም፣ የዴሞክራሲና የልማት እንቅስቃሴም ውስት ሁሉም በላፊነት የየግሉት አስተዋፅኦ በማድረግ የተጀመረውን ሀገራዊ መግባባት ማሳደግ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ ### Response:
### Text: የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን የሚያስችል ሳይንሳዊ ጥናት ተጀመረአብያተ ክርስቲያናቱ ታሪካዊ ይዘታቸውን እንደጠበቁ ለመጠገን የስነምድርና የአርኪዮሎጂ ጥናት መጀመሩን የኢትዮፈረንሳይ የጥናት ቡድን ገልጿል። የአብያተ ክርስቲያናቱ የሙከራ ጥገና በመውጭው የአውሮፓዊያኑ አዲስ ዓመት ይጀምራል ተብሏል።በ1970 ዓም በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡት ቤተክርስቲያናቱ የመፍረስ አደጋ ተጋርጦባቸዋል። ከ10 ዓመት በፊት በአምስት ዓመት ጊዜ ይነሳል ተብሎ በ11 ሚሊዮን ዩሮ የተሰራው መጠለያ ተጨማሪ አደጋ በመሆን የቅርሱን ህልውና እየተፈታተነ ይገኛል።በመሆኑም በቅርሱ ላይ የደረሰውን የመሰንጠቅ አደጋ ለመጠገንና መጠለያውን ለማንሳት ዘርፈ ብዙ ሳይንሳዊ ጥናት እንደሚያስፈልግ አጥኝዎቹ ይናገራሉ። ስንጥቁን ለመጠገንና መጠለያውን ለማንሳት የአርኪዮሎጂ፣ የስነ ምድር፣ የቅርጽ ጥናት በማድረግ ላይ መሆናቸውን አጥኚዎቹ ገልጸዋል።በቅርሱ ላይ መረጃ ለመሰብሰብ የሚገጠሙ 3ዲ ካሜራዎች በተጨማሪ በየሁለት ሰዓቱ መረጃ የሚያደርሱ የሌዘር ስካን መሳሪያዎች ጥቅም ላይ ይውላሉ ብለዋል። የጉዳት መጠናቸው ጊዜ የማይሰጥ ቅርሶች እየታዩ ጥገና እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ከጥቂት ወራት በኋላ ከቤተክርስቲያናቱ አንዱ በሆነው ቤተጎለጎታ ላይ የሙከራ መጠለያ ይሰራለታል ተብሏል።ምንጭአሐዱ ቴሌቭዥን ### Response:
### Text: የኤክሳይዝ ታክሱ በድጋሚ ይታይልኝ ኢትዮ ቴሌኮም ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌኮምኒኬሽን አገልግሎቶች ላይ 5 በመቶ የኤክሳይዝ ታክስ መጣሉ ተገቢ ስላልሆነ በድጋሜ ይታይልኝ ብሏል፡፡ የኢንተርኔት ፣ የድምፅ እና የፅሑፍ መልክት ላይ በኤክሳይስ ታክስ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የቴሌኮምኒኬሽን አገልግሎቶች ላይ 5 በመቶ የኤክሳይስ ታክስ መጣሉ በድጋሜ ቢታይ ጥሩ ነው ብሏል፡፡ኢትዮጵያ ኋላቀር የቴሌኮም አጠቃቀም ያላት ሀገር ናት በመሆኑም መንግስት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ፣ አሁን አዲስ የተጣለው ታክስ በቴሌኮም ኢንድስትሪው ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ አለው ተብሏል፡፡ የስማርት ስልኮችና ታብሌቶች ታክስ ዋጋ ቢቀነስባቸው ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ይሆናል ፣ ጎረቤታችን ኬኒያ የሞባይል ግብይት ላይ ከፈተኛ ደረጃ ላይ ደርሳለች ፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቷ መማር እንዳለባት ተነግሯል፡፡አዲሱ የኤክሳይስ ታክስ ማሻሻያ አዋጅ አብዛኛው ትኩረቱ በምርቶች ላይ በአገልግሎት ዘርፍ ግን ኢትዮ ቴሎኮም ትኩረት አድርጓል፣ ትኩረቱ መሆን ያለበት ዲጂታል ኢኮኖሚ መፍጠር ላይ ነው ተብሏል፡፡ በገንዘብ ሚኒስቴር የታክስ አማካሪ የሆኑት አቶ ዋሲሁን አባት በበኩላቸው የኢንተርኔት ፣ የድምፅ እና የፅሑፍ መልዕክት ላይ 5 መቶ ኤክሳይዝ ታክስ እንዲጣል የተደረገው ገቢ ለመሰብሰብ ነው ፣ የብዙ ሀገሮች ተሞክሮም የሚያሳየው ይሄንን ነው ብለዋል፡፡ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ### Response:
### Text: በጊዜ ገደቡ ምላሽ ካልሰጠ ወደ ክሥ እናመራለን የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ ቤቶቻቸው ለፈረሱባቸው ሰዎች አቤቱታዎች፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ምላሽ እንዲሰጥ መጠየቁን ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።ተቋሙ፣ ከሸገር ከተማ አስተዳደር የቤቶች ፈረሳ ጋራ ተያይዞ፣ ከ100 ሺሕ በላይ አቤቱታዎችን እንደተቀበለ፣ ከዚኽ ቀደም ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽቤት የምርመራ ዲሬክተር አቶ ቶሌራ በላይ፣ የከተማ አስተዳደሩ ለአቤቱታዎቹ ምላሽ እንዲሰጥ በደብዳቤ እንደተጠየቀ ገልጸዋል።የሸገር ከተማ አስተዳደር፣ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ፣ ጉዳዩ ወደ ክሥ እንደሚያመራ፣ የምርመራ ዲሬክተሩ አቶ ቶሌራ በላይ አመልክተዋል፡፡ጉዳዩን በተመለከተ የሸገር ከተማ አስተዳደር ያለው ነገር የለም።ከዚህ ቀደም ግን በሰጠው ለእንባ ጠባቂ ተቋም 100 ሺሕ አቤቱታዎች መቅረባቸውን አላውቅም ብሎ ነበር።የኢትዮጵያ የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ በሸገር ከተማ፣ ሕገ ወጥ ግንባታ በሚል እየተካሔደ ካለው የቤቶች ፈረሳ ጋራ የተያያዙ፣ 100 ሺሕ አቤቱታዎችን እንደተቀበለ ማሳወቁ አይዘነጋም።አሁን ደግሞ፣ እንባ ጠባቂ ተቋሙ የሸገር ከተማ አስተዳደር ለአቤቱታ አቅራቢዎቹ ምላሽ እንዲሰጥ፣ የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ እንደጠየቀው ማስታወቁን ሬድዮ ጣቢያው አመልክቷል። ### Response:
### Text: የመብራት መቆራረጥ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የሃይል ስርጭት መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል አስታውቋል።የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተትአቶ ምስክር ነጋሽ ለ እንዳሉት በጊቤ 3 የሃይል ማመንጫ ጣቢያ የሚገኘውብሬከር በመከፈቱ ምክንያት በተለያዩ አካባቢዎች የሃይል መቋረጥ ተከስቷል።አቶ ምስክር ከምሽቱ ጋር ባደረጉት ቆይታ በብሬከሩ መከፈት ሳቢያ ወደ ሌሎች የሃይል ማሰራጫ ጣቢያዎች የሚሄዱ መስመሮች ጠፍተዋል። በዚህ ሳቢያም በርካታ የሃገሪቱ ከተሞች የሃይል አቅርቦት ተቋርጦባቸዋል ነው ያሉት።አሁን ላይም የሃይል ስርጭት መቋረጡን ችግር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ደረጃ በደረጃ በመፍታት የሃይል ስርጭቱ ወደነበረበት ይመለሳል ብለዋል።የሃይል መቋረጡን ለመፍታት ሌሎች የሃይል ማመንጫዎችን ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ምስክር እስካሁንም ጣና በለስና ፊንጫ አመርቲነሼየሃይል ማመንጫዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።በቀጣይም ችግሩ እስከሚቀረፍ ብሬከሩ ላይ የተከሰተውን ችግር በመለየት መፍትሄ የመስጠትና መሰል አማራጮችን የመውሰዱ ስራ እንደሚቀጥል አንስተዋል።ደንበኞችም የተፈጠረውን ችግር ተረድተው ችግሩ እስከሚቀረፍ ድረስ በትዕግስት እንዲጠባበቁም ጠይቀዋል።ምንጭ ፋናእንደወረደ ### Response:
### Text: ደቡብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል የሚታዩ የክልል እንሁን ጥያቄዎችን በጥናት ለመፍታት የክልሉ ገዥ ፓርቲ ደኢህዴን ሲያስጠና ቆየው ጥናት ውጤት ዛሬ ይፋ ሆነ።የጥናት ቡድኑ ምክትል ሰብሳቢ ዶር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንዳሉት 20 አባላት ያሉት የጥናት ቡድን ተዋቅሮ ላለፉት ሰባት ወራት ሰፊ ጥናት ሲያካሂድ ቆየቷል። በዚህም መሰረት ሶስት አማራጮችን አስቀምጧል ብለዋል ምክትል ሰብሳቢዋ።በጥናቱ የተለየው የመጀመሪያው አማራጭ አብዛኛው የክልሉ ህዝብ አሁን ያለው የክልሉ አደረጃጀት ቢቀጥል የህዝቦችን አብሮነትና ያጠናክራል ጠነካራ የደቡብ ህዝቦች ክልልንና የኢትዮጵያን አንድነት ያጠናክራል የሚል ነው።በጥናቱ የተለየው መጀመሪያ አማራጭ አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሮ ተቀባይነት የሚያጣ ከሆነ በጥናቱ በሁለተኝነት የተለየው አማራጭ ደግሞ ክልሉን በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በመክፈል ከዚህ በፊት ይነሱ የነበሩ የፍተሃዊነት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ማድረግ ነው።በጥናቱ በሶስተኝነት የተቀመጠው ሃሳብ ደግሞ ሁለቱ አማራጮች ተግባራዊ የማይሆኑ ከሆነና ሁኔታው ከክልል አልፎ በአገሪቱ ሰላምና አንድነት ላይ ጫና የሚፈጥር ከሆነ ጉዳዩ ለጊዜው ቢቆይና በእርጋታ ቢታይ የሚል ነው። እንደጥናት ቡድኑ ምክትል ሰብሳቢ ከ17 ሺህ በላይ ሰዎች በላይ ለጥናቱ በመረጃ ሰጪነት ተሳትፈዋል።ምንጭ ኢፕድ ### Response:
### Text: ተጨማሪ ጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ለህክምና 98 ተማሪዎች የመጡ ሲሆን ምርመራ ከተደረገላቸዉ ሴት 47 እና 51 ወንድ በአጠቃላይ 98 ተማሪዎች የመደንገጥና ከመጠነኛ ማስታወክ ስሜት ዉጭ የከፋ ኬዝ አለመኖሩን ነገር ግን ሁለት ተማሪዎች ብቻ መጠነኛ ህመም እንዳጋጠማቸው ሆስፒታሉ አሳውቋል።ሆስፒታሉ ይህን ያሳወቀው ለኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ሬድዮ ነው።የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ዶክተር ሳምሶን ጉታ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል የዛሬው ክስተት ለከፋ ጉዳት የሚዳርግ አለመሆኑን እና የሞተ ተማሪ አለመኖሩን ገልፀዋል።ዶር ሳምሶን ወደ ሆስፒታሉ የገቡ ተማሪዎች ምርመራ እየተደረገላቸዉ መሆኑን ሁሉም ተማሪዎች ጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።በምግቡ ላይ የተከሰተዉን ሁኔታ በባለሙያ ጥናት ተደርጎ ይረጋገጣል ለህብረተሰቡም ይፋ ይደረጋል ያሉ ሲሆን ወላጆች እንዲረጋጉ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።በሌላ በኩል ዶር ሙልጌታ እንዳለ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ 714 ተማሪዎች ወደ ህክምና ማዕከላት ሄደው በተደረገላቸው ምርመራ 7 ተማሪዎች ላይ ከታየ የማስመለስ ምልክት በስተቀር በሌሎቹ ላይ ምንም አይነት ከምግብ መመረዝ ጋር የተገናኘ ችግር አላጋጠመም ብለዋል። የሰባቱ ተማሪዎች የድምና ሰገራ ናሙና ተወስዶ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑንና ውጤቱም እንደታወቀ ለህብረተሰቡ ይገለፃል ሲሉ አሳውቀዋል። ### Response:
### Text: በጎረቤታችን ሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ትላንት በተፈፀመው የሽብር ጥቃት በትንሹ 100 ሰዎች ሲሞቱ 300 ሰዎች ተጎድተዋል።በሁለት መኪና በተፈፀመውን የቦንብ ጥቃት ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ ሲቪሎች ተገድለዋል።የሶማሊያ ፕት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ የትላንቱን የሽብር ጥቃት ጭካኔ የተሞላበት እና የፈሪዎች ጥቃት ሲሉ ገልፀው ድርጊቱን የፈፀመው ሽብርተኛው አልሸባብ መሆኑን አመልክተዋል።በጥቃቱ ሲቪሎች መሞታቸውን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ የአልሻባብ የሽብር ቡድን ድርጊት ተስፋ ሊያስቆርጠን አይችልም ይልቅ ለአንዴና ለመጨረሻ ጌዜ ለማሸነፍ አልሸባብን ያለንን ቁርጠኝነት ያጠናክራል ሲሉ ገልፀዋል።ፕት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ዛሬ የሽብር ጥቃቱ የተፈፀመበትን ቦታ በአካል የተመለከቱ ሲሆን በጥቃቱ በትንሹ 100 ሰዎች መገደላቸውን እና 300 የሚደርሱ ሰዎች መጎዳታቸውን ገልጸዋል።የተጎዱትን ለማከም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የህክምና ዶክተሮች እና የህክምና ቁሳቁሶችን እንዲልክ ተማፅነዋል።ህዝቡም ወደ ሆስፒታል እየሄደ ደም እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።በትላንቱ እንዲሁም በሌሎች የአልሸባብ የሽብር ጥቃት ሰለባ ለሆኑ ህፃናት ነፃ የትምህርት ዕድል እንደሚመቻች ፕሬዜዳንቱ ቃል ገብተዋል።የትላንቱ የመኪና የቦምብ ጥቃት በመዲናዋ ሰው ከሚበዛባቸው መገናኛዎች ውስጥ በሚገኘው የትምህርትሚኒስቴር ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ተነግሯል። ### Response:
### Text: ብዝሃነትን መሰረት ያደረገ ፌዴራሊዝምን ለማጠናከርና በህዝቦች መካከል አንድነትና እኩልነት እንዲኖር ይሰራል ጋድሰ ሆገንሰ ኦሮሞበጋድሰ ሆገንሰ ኦሮሞ ስር የተደራጁ የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ብዝሃነትን መሰረት ያደረገ ፌዴራሊዝምን ለማጠናከርና በህዝቦች መካከል አንድነት፣ እኩልነትና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲኖር ይሰራሉ፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች አሁን የምንወስዳቸው እርምጃዎች ለቀጣይ የኦሮሞና የአገሪቱ ህዝቦች ዕጣ ፋንታ ወሳኝ ናቸው ብለዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በአጠቃላይ በኦሮሚያ ክልል እየታዩ ባሉ የጸጥታ ችግሮችና ሰሞኑን በክልሉ በተከሰተው የጸጥታ ችግር መሰረታዊ መንስኤዎች ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት የስራ ክፍፍል ማድረጋቸውም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡በአገሪቱ የሚደረገው ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞራሲያዊ እና ፍትሓዊ እንዲሆን መደረግ በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ጥናት ከተደረገ በኋላ ጥልቀት ያለው ውይይት ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥም ፓርቲዎቹ ወስነዋል፡፡ፓርቲዎቹ በመካከላቸው ያሉትን ልዩነቶች በውይይት ለመፍታት ተስማምተዋል፡፡ በአገሪቱ የመጣው ለውጥ አስተማማኝ መሰረት እንዲኖረው ለማድረግ በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ድርሻ ካላቸው ሁሉም አካላት ጋር ቀጣይነት ያለው ውይይት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑም ተገልጿል፡፡ምንጭ ኢቢሲ ### Response:
### Text: ጳጉሜ 32012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 2 በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 1528 የላብራቶሪ ምርመራ ስልሳ አንድ 61 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ከቤንች ሸኮ ዞን የ32 ዓመት ወንድበቫይረሱ የተያዙት፡ ከከምባታ ጠምባሮ ዞን 17 9 ከሺንሺቾ፣ 3 ከዱራሜ ከተማ፣ 2 ከደምቦያ፣ 1 ከቃጫቢራ፣ 1 ከጠምባሮ እና 1 ከዶዮ ገና ከጌዴኦ ዞን 12 8 ከዲላ ከተማ፣ 2 ከረጲ፣ 1 ከዲላ ዙሪያ እና 1 ከይርጋጨፌ፣ ከወላይታ ዞን 8 4 ከአባላ አባያ፣ 2 ከቦዲቲ ከተማ፣ 1 ከሶዶ ከተማ እና 1 ከኪንዶ ኮይሻ፣ ፣ ከደቡብ ኦሞ ዞን 5 3 ከማሌ እና 2 ከሰሜን አሪ፣ ከሃዲያ ዞን 5 3 ከሾኔ ከተማ እና 2 ከሆሳዕና ከተማ፣ ከቤንች ሸኮ ዞን 4 2 ከሚዛን ከተማ እና 2 ከጉራፈርዳ፣ ከካፋ ዞን 3 3ቱም ከዴቻ፣ ከጉራጌ ዞን 2 2ቱም ከሶዶ፣ ከስልጤ ዞን 2 2ቱም ከአሊቾ ወሪሮ፣ ከባስኬቶ ልዩ ወረዳ 1፣ ከኮንሶ ዞን 1 ኬና፣ እንዲሁም 1 ከኦሮሚያ ክልል የመጣ። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 244 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 49 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 23 ከሀዋሳ ከተማ 4 ከሀዌላ 3 ከሸበዲኖ 3 ከወንዶ ገነት 2 ከአርቤጎና ይገኙበታል።አጠቃላይ በሲዳማ ክልል ውስጥ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 1703 የደረሰ ሲሆን ከነዚህ መካከል የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል 1008 ሰዎች ደግሞ አገግመዋል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ የበረራ ቁጥር ኢቲ 3905 አውሮፕላን ናይጄሪያ ሌጎስ ደርሶ ካረፈ በኋላ ወደ መቆሚያ ስፍራው እየሄደ ሳለ ከመንገዱ ወጥቶ እንደነበር ተገለጸ።የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳደረጋገጠው ወደ ካርጎ የተቀየረው የመንገደኞች ቦይንግ 777300 ግዙፍ አውሮፕላን ካጋጠመው ከስተት በኋላ ወደ ሥራ ተመልሷል።አውሮፕላኑ ከአዲስ አበባ ወደ ናይጄሪያ ሌጎስ ከተማ ጭነት ይዞ ከበረረ በኋላ በሌጎስ ኤርፖርት አርፎ ወደ መቆሚያው እየሄደ ሳለ የአውሮፕላኑ በስተግራ በኩል ያለው ጎማ ከአስፓልቱ መውጣቱን አየር መንገዱ አስታውቋል።በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተለቀቀ ተንቀሳቃሽ ምስል የአውሮፕላኑ በስተግራ በኩል ያለው ጎማ ጭቃ ውስጥ ገብቶ አሳይቷል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ክስተቱን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ምንም አይነት ጉዳት ሳያጋጥመው በመብረር ወደ አዲስ አበባ መመለሱን አስታውቋል። አየር መንደጉ የሌጎስ ኤርፖርት ሠራተኞች ላደረጉት ድጋፍ ምስጋናውን አቀርቧል።አውሮፕላኑ ከአስፓልቱ እንዲወጣ ያደረገው ምክንያት ምን እንደሆነ በአየር መንገዱ መግለጫ ላይ አልተመለከተም።ፍላይትግሎባል ድረገጽ ክስተቱ ባጋጠመበት ወቅት በአውሮፕላን ማረፊያው የነበረው የሜትሮሎጂ መረጃ ምንም አይነት አስቸጋሪ የአየር ጠባይ መኖሩን አላሳየም ማለቱን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።ምንጭ ቢቢሲ ### Response:
### Text: የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በጽኑ እስራት ተቀጣ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግተከሳሽ መሀዲ መሀመድ ሳድቅ የወንጀል ህግ አንቀጽ 6271 ላይ የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው ዳትሰን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አስር አመት በሆናት ህጻን ላይ በፈጸመው የግብረ ስጋ ድፍረት በደል ማድረስ ወንጀል ተከሶ ፍቤት ቀርቧል፡፡ተከሳሹ በ2010ዓም መጋቢት ወር መጀመሪያ ሳምንት ባሉት ቀናት በግምት ከቀኑ 5፡00 ስዓት ሲሆን ታዳጊ የሆነችዋን ህጻን ግብረ ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት በመሆኑ በፈጸመው የግብረ ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ዐቃቢ ህግ ክስ መስርቶበታል፡፡ዐቃቢ ህግ በቅጣት አስተያየቱ እንደገለጸው ተከሳሽ በዚህ እድሜው ይህን አይነት ድርጊት መፈጸሙ መጥፎ አመል እንዳለው የሚያሳይ ስለሆነ በወህቁ841ሀ መሰረት እንደ ቅጣት ማክበጃ ተይዞ ተከሳሹን ያስተምራል የሚል ቅጣት እንዲወስንለት ፍቤቱን ጠይቋል፡፡ክሱን የተከታተለው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ልደታ ምድብ 7ኛ ወንጀል ችሎት ዐቃቢ ህግ ያቀረበውን የሰውና የህክምና ማስረጃዎች አድምጦና መርምሮ እንዲሁም ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ በመቀበል ተከሳሽ ከአሁን በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን እንደ አንድ የቅጣት ማቅለያነት ይዞለት ጥቅምት 112012ዓም በዋለው ችሎት በ14 ዓመት ጽኑ እስራት ይቀጣ ሲል ወስኗል፡፡ ### Response:
### Text: አሜሪካ ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላም እያበረከተች ያለውን በጎ ሚና አደነቀች የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ ከአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር በዋሽንግተን ዲሲ የተወያዩ ሲሆን፣ በውይይቱ ላይ የአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስቴር ኃላፊዎች ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም የሚታበረክተው በጎ ሚና እና በመከላከያ ዘርፍ የምታካሄደውን ማሻሻያ አድንቀዋል፡፡ የሁለቱ አገራት 9ኛው የሁለትዮሽ የመከላከያ ኮሚቴ ዓመታዊ ስብሰባ በዋሽንግተን ከተማ ተካሂዷል።በስብሰባው ሁለቱ አገራት በቀጣናው የጸጥታና ደህንነት፣ የመረጃ፣ ሰላም ማስከበር እና መከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ ገምቢ ምክክር ያደረጉ ሲሆን፣ ይህም የአገራቱን በጸጥታና ደህንነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር የበለጠ እንደሚያጎለብት ተገልጿል፡፡አገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የበለጠ እንዲጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት የገለጹ ሲሆን፣ ባለፉት 18 ወራት በጸጥታው ዘርፍ እያደገ የመጣው ትብብርም ለዚህ ማሳያ እንደሆነ ነው የተገለጸው። የሁለትዮሽ የመከላከያ ኮሚቴ ስብሰባው ኢትዮጵያና አሜሪካ ያላቸውን ጠንካራ ግንኙነት በማበልጸግ በጸረ ሽብር፣ በደህንነት መረጃ እና ሌሎች የትብብር ዘርፎችን በመለየት በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ እንደሚያስችላቸው ከአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ኢቢሲ ### Response:
### Text: ህዳር 24 ቀን 2013 ሮይተርስ ዜና ወኪል በትግራይ ክልል 4 ለውጭ ድርጅቶች የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን ገልፆ እንደ ነበር የምታስታውሱት ነው።በወቅቱ ሮይተርስ ሰራተኞቹ ስለሚሰሩበት ድርጅቶቹ እንዲሁም በማን እና እንዴት እንደተገደሉ ምንም ያለው ነገር አልነበረም። በዛሬው ዕለት ባወጣው መረጃ ሰራተኞቻቸው የተገደሉባቸው ድርጅቶች ዳኒሽ ሪፊውጂ ካውንስል እና ኢንተርናሽናል ሬስኪው ኮሚቴ መሆናቸው ታውቋል።ዳኒሽ ሪፊውጂ ካውንስል ባሳለፍነው ወር 3 የሰብዓዊ እርዳታ ሠራተኞቹ መገደላቸውን ሲያስታውቅ ኢንተርናሽናል ሬስኪው ኮሚቴ በሽረ ከተማ ህጻጽ የሰደተኞች መጠለያ ካምፕ ይሰራ የነበረ ባልደረባው መገደሉን አስታውቋል።ዳኒሽ ሪፊውጂ ካውንስል የተገደሉት በትግራይ ካሉት ፕሮጀክት ጣቢያዎች በአንደኛው ቦታ በጥበቃ ሥራ የተሰማሩት ናቸው ብሏል። ዳኒሽ ሪፊውጂ ካውንስል በአከባቢው ላይ የቴሌኮም አገልግሎት ባለመኖሩ እንዲሁም ወደ ስፍራው ለመጓዝ የደኅንነት ስጋት በመኖሩ የሟች ቤተሰቦችን ማግኘት እና ድጋፍ ማድረግ አለመቻሉን አስታውቋል። በሠራተኛው መገደል የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን የገለጸ ሲሆን የተገደለው ሠራተኛ ማንነትን ግን ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል። በአከባቢው የቴሌኮም አገልግሎት በመቋረጡ የሠራተኛውን የአሟሟቱን ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝር ሁኔታ ማጣራት ለማድረግ አለመቻሉን አስታውቋል። ### Response:
### Text: አጫጭር የምርጫ 2013 መረጃዎች ነገ መጋቢት 162013 ዓም የ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ይጀምራል። የመራጮች ምዝገባ ነገ ጀምሮ የሚጠናቀቀው ሚያዚያ 15 ቀን 2013 ዓም ነው። እንደምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከትላንት ጀምሮ ለምርጫ ክልሎች ማሰራጨት ጀምሯል፡፡ ቦርዱ ለአንድ ወር ለሚቆየው የመራጮች ምዝገባ ለ673 የምርጫ ክልሎችና 50 ሺህ የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች የሚሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶችን ነው ማጓጓዝ የጀመረው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓም ለመራጮች ምዝገባ ያለውን የቁሳቁስ ዝግጅት ለብዙኃን መገናኛ አካላት አስጎብኝቷል በጉብኝቱ ወቅት የኮሚኒኬሽን ኃላፊዋ ወሪት ሶሊያ ሽመልስ እንዲሁም የቦርዱ የሎጂስቲክ ድልድልና ሥርጭት ባለሙያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በአፋር ክልል 8 ቀበሌዎች ሊከፈቱ የነበሩ 30 የምርጫ ጣቢያዎች እንዳይቋቋሙ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ውሳኔ አሳልፏል። በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎች በአቅራቢያቸው ባለ ሌላ ቀበሌ መመዝገብ እና ድምጻቸውን መስጠት የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል። በጋላእቶአዳይሌ በአዳይቱአዳይቱ በቴውኦአላሌ በጉርሙዳሊዳንሌሄላይ በኡንዳፎኦኡንዱፎ በጋዳማይቱጋርባኢሴ በአፍዓሶአፉአሴ በባላእቲ ጎናመደኒ ቀበሌዎች ነው ሊከፈቱ የነበሩትን 30 የምርጫ ጣቢያዎች በአካባቢው እንዳይቋቋሙ የተወሰነው። ### Response:
### Text: ጊዳሚ ከተማ ሁለት ሰዎች በጥይት ተመትተው ተገደሉ ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ከምሽቱ 1 ሰዓት ገደማ በቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ከተማ ሁለት ሰዎች በጥይት ተመትተው መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል። በምዕራብ ኦሮሚያ ይህን መሰሉ ግድያ ነዋሪ የዕለት ተዕለት ሰቆቃ ከሆነ ሰነባብቷል።ቅዳሜ ምሽት ተኩስ ነበር። በዚያ ተኩስ ሳቢያ ነው ሁለቱ ነዋሪዎች የተገደሉት። እነሱን የገደለው አካል የቱ እንደሆነ ደግሞ መለየት አልቻልንም በማለት ለደህንነታቸው ሲባል ስማቸውን የማንጠቅስ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ተናግረዋል።ከተገደሉት ሁለቱ ግለሰቦች አንዱ የጊዳሚ ከተማ ቀበሌ 01 ነዋሪ የነበሩት አቶ ነጋሽ ፉፋ ሲሆኑ ሌላኛው ሟች ደግሞ ከቄለም ገጠራማ ስፍራ የመጡ ናቸው ማንነታቸውን አለየንም በማለት የከተማዋ ነዋሪ ተናግረዋል።የጊዳሚ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ደሳለኝቱጁባ በበኩላቸው ሟቾቹ አቶ ነጋሽ ፉፋ እና አቶ ያዕቆብ ቶላ እንደሚባሉ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋሽ ፉፋ ቤት አቅራቢያ በቅኝት ሥራ ላይ በነበሩ የልዩ ፖሊስ እና የሃገር መከላከያ አባላት ላይ ቦንብ ተወረወረ ተኩስም ተከፈተ የሚሉት የወረዳው አስተዳዳሪ ቦንምቡን የወረወረው እና ተኩስ የከፈተው አካል አሁን ድረስ እንደማይታወቅ ጠቅሰው ድንገተኛ ጥቃቱ የተሰነዘረው ግን በመንግሥት ኃይሎች ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ቢቢሲ ተጨማሪ ያንብቡ 09165 ### Response:
### Text: የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ በፓስፖርት አቅርቦት ዕጥረት እየተስተዋለ ያለበትን የኪራይ ሰብሳቢነት ድርጊት ለመታገል የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አውጥቶ በጥብቅ ዲስፕሊን እንዲተገብር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።የኤጀንሲውን የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ጥቅምት 24 ቀን 2012 ዓም በገመገመበት ወቅት ኤጀንሲው በበቂ መጠን ፓስፖርት ባለማሳተሙ በተፈጠረበት የፓስፖርት ዕጥረት አስቸኳይ ጉዳዮችን ከማስተናገድ ባለፈ አብዛኛው የአገልግሎቱ ጠያቂ የህብረተሰብ ክፍሎች በወረፋ በመመዝገብ በረጅም ቀጠሮ እንዲስተናገዱ እየተደረገ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሙጂብ ጀማል ያስረዳሉ፡፡ለአስቸኳይ አገልግሎት መስፈርት የማያሟሉ ተገልጋዮች በአቋራጭ አገልግሎቱን ለማግኘት በኤጀንሲው አካባቢ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲከሰት ማድረጋቸውን ዋና ዳይሬክተሩ የጠቆሙ ሲሆን በተቋሙ እጅ ይገኝ ከነበረው 200000 ፓስፖርት ላይ ተጨማሪ 1 ሚሊዮን እንዲታተም ከፈረንሳዩ ኦቨር ቱር ካምፓኒ ጋር ውል ተገብቶ 100000 መረከባቸውን አብራርተዋል፡፡በቅርብ ጊዜ ቀሪውን 900000 እንደሚረከቡም የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ ሌላ 1 ሚሊዮን ፓስፖርት እንደሚታተምም በማስረዳት ለተፈጠረው ችግር በቂ ፓስፖርት ማቅረብ መፍትሔ እንደሚሆን ነው አቶ ሙጂብ ጀማል ያስረዱት፡፡ኢፕድ ### Response:
### Text: 19 ከአዲስ አበባ ከተማ ቀጥሎ ከፍተኛው የ24 ሰዓት ኬዝ የተመዘገበው በሐረሪ ነው። 100 የላብራቶሪ ምርመራ 7 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል። 6 ወንዶች እና 1 ሴት ሲሆኑ ሁለቱ በለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበሩ አምስቱ ለህክምና ወደ ሐረር መጥተው ናሙና የተወሰደላቸውና ነዋሪነታቸው 1 ሰው ሱማሌ ክልልና 6 ሰዎች ምስራቅ ሐረርጌ ዞን የሆኑ ናቸው። 19 በትግራይ ክልል ከኮሮና ቫይረስ ኮቪድ19 ያገገሙ ሰዎች 96 ደርሰዋል። ባለፉት 24 ሰዓት ተጨማሪ 19 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል የጤና ሚኒስቴር ሪፖርት ላይ አልተገለፀም።በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 195 የላብራቶሪ ምርመራ 3 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል 2 ሰዎች የውጭ ጉዞ ታሪክ ያላቸውና 1 ሰው ንክኪ ያለው ነው በአጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 209 ደርሰዋል። 19 ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 215 የላብራቶሪ ምርመራ 3 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ከተገኝቶባቸዋል። የ24 ዓመት እድሜ ያለው የምሥራቅ ሐረርጌ ነዋሪ ከማህበረሰቡ የተገኘ ፣ የ55 ዓመት እድሜ ያላቸው የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ነዋሪ ከማህበረሰቡ የተገኙ እንዲሁም 20 ዓመት ሴት ከምዕራብ ሐረርጌ ናት። 19 ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 451 የላብራቶሪ ምርመራ 1 ሰው ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል። ቫይረሱ የተገኘበት የ23 ዓመት ወጣት ሲሆን በወረይሉ አውቶብስ መናኸሪያ በተወሰደ የናሙና ምርመራ ነው ቫይረሱ ሊገኝበት የቻለው። ### Response:
### Text: በሊባኖስ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉየኢትዮጵያ ቆንስላ ጄፅቤት ቤይሩት ሊባኖስበቤይሩት ወደብ ዛሬ የተከሰተው ፍንዳታ ጋር ተያይዞ እስከ አሁን ወደ 10 የሚጠጉ ሰዎች መሞታቸው የተዘገበ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደግሞ እንደቆሰሉ ሪፖርት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ፍንዳታው በተከሰተበት አካባቢ መንገዶች እና ህንጻዎች የፈራረሱ ሲሆን ከፍንዳታው እስከ በ10 ኪሎሜትር ርቀት ደግሞ ብዙ ህንጻዎች መስኮቶች ተሰባብረዋል፡፡ በመሆኑም ሁኔታዎች እስኪረጋጉ ዜጎች በተቻለ መጠን በቤታችሁ እንድትቆዩ ይመከራል ከቤት መውጣት የግድ ከሆነም ከቤት ከመውጣታችሁ በፊት መረጃዎችን እንድታጣሩና ጥንቃቄ እንድታደርጉ እንዲሁም በሚከተሉት መልኩ ራሳችሁን እንድትጠብቁ ቆንስላ ጽቤቱ ያሳስባል ፡1 ፍንዳታው ከተከሰተበት አካባቢ ራሳችሁን እንድትጠብቁና እንድትርቁ፣2 የአገሪቱን የዜና አውታሮች እንድትከታተሉ፣ መረጃዎችን እንድትለዋወጡ3 ከሊባኖስ መንግስት የሚሰጡ መግለጫዎችን እንድትከታተሉና እንድትተገብሩ4 በተቻለ መጠን ከመኖሪያ ቤታችሁ አካባቢ እንድትቆዩ ወይም ብዙ እንዳትርቁ5 ከቤት ስትወጡ የሞባይል ስልኮቻችሁን ቻርጅ እንድታደርጉ ይመክራልከዚህ ጋር ለተያያዙ ለድንገተኛ እና አስቸኳይ ጉዳዮች ብቻ በስልክ ቁጥሮች 71463074 ወይም 70696193 ወይም 81952182 ይደውሉ፡፡ፈጣሪ ከሁላችን ጋር ይሁን፣ ይጠብቃችሁም ሼር ### Response:
### Text: አጠቃላይ የምርጫ ውጤት ፓርላማ 1 አዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና 22 መቀመጫዎችን አሸንፏል አንዷን መቀመጫ አንድ የግል ዕጩ ተወዳዳሪ አሸንፈዋል2 አፋር ክልል 8 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት ሰኔ 14 ምርጫ የተካሄደባቸው 6 መቀመጫዎችን በሙሉ ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል 3 አማራ ክልል ምርጫ ከተካሄደባቸው 125 የፓርላማ መቀመጫዎች ውስጥ ብልጽግና በ114ቱ አሸንፏል አብን 5 መቀመጫዎችን አሸንፏል4 ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 9 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት በሶስት የፓርላማ መቀመጫዎች ሰኔ 14 ምርጫ ተከናውኗል ሶስቱንም መቀመጫዎች ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል5 ድሬዳዋ 2 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት ብልጽግና ፓርቲ አንዱን መቀመጫ አሸንፏል6 ጋምቤላ ክልል 3 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት ሶስቱንም ምርጫ ክልሎች ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል7 ኦሮሚያ ክልል 178 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት ምርጫ ከተካሄደባቸው 170 መቀመጫዎች ውስጥ ብልጽግና 167ቱን መቀመጫ አሸንፏል ቀሪ 3 መቀመጫዎችን 3 የግል ዕጩዎች አሸንፈዋል8 ሲዳማ ክልል 19 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት 19ኙንም መቀመጫዎች ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል9 ደቡብ ክልል 104 የፓርላማ መቀመጫዎች አሉት ምርጫ ከተከናወነባቸው 85 የፓርላማ መቀመጫዎች ውስጥ በ75ቱ ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል ኢዜማ 4 መቀመጫዎችን አሸንፏል የጌድዮ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 2 መቀመጫዎችን አሸንፏልፅሁፍ ዝግጅት ኢትዮጵያ ኢንሳይደር።ፎቶ ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር የሚያገናኟትን መንገዶች ግንባታ እና ጥገና ማጠናቀቋን አስታወቀች ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 እንዳስታወቀዉ ኢትዮጵያን እና ኤርትራን የሚያገናኙት መንገዶች ጥገናቸዉ ተጠናቋል ብሏል፡፡ የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ወንድሙ ቡሬ አሰብ ራማ መረብ እና አዲግራት ዛላምበሳ መንገዶች ጥገናቸዉ በመጠናቀቁ የትራንስፖርቱ አገልግሎቱ ካለ መንገዶቹ ዝግጁ ናቸዉ ባለስልጣኑም የሚጠበቅበትን ሃላፊነት ተወጥቷል ነዉ ያሉት፡፡በነዚህ ድንበሮች አማካኝነት የሁለቱ አገራት ዜጎች እንዲገናኙ ከተደረገ በኋላ ድንበሮቹ መዘጋታቸዉ የሚታወስ ሲሆን የአየር በረራዉ ግን አሁንም እንቀጠለ ይገኛል፡፡ አገሪቱ ከኤርትራ ጋር ዕርቀ ሰላም ማዉረዷን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ20 አመታተ በኋላ ወደ አስመራ በረራ መጀመሯ የሚታወስ ነዉ፡፡ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ድንበሮቹ ለምን ተዘጉ መቼስ ይከፈታሉ ሲል የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የጠየቀ ሲሆን የሁለቱን አገራት የንግድ እንቅስቃሴ ህጋዊ ማእቀፍ እንዲኖረዉ እየተሰራ ነዉ እሱ እንዳለቀ ድንበሮቹ እንደሚከፈቱ አስታዉቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በኢኮኖሚ እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ግንኙነት እንዲኖራት በትኩረት እንደምትሰራ በተደጋጋሚ አታስታዉቃለች፡፡ምንጭ ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ### Response:
### Text: ነሃሴ 202012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 555 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 14 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 3869 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 383 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። የ1 ሰው ህይወት አልፏል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 39 ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ 38 ከምስራቅ ሸዋ 34 ከቢሾፍቱ ከተማ 33 ከምዕራብ አርሲ 28 ከምዕራብ ወለጋ 24 ከሻሸመኔ ከተማ 23 ከምስራቅ ሀረርጌ 22 ከሞጆ ከተማ ይገኙበታል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 565 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 13 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 12 ከሆምሻ ወረዳ 1 ከፓዌ ወረዳ በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 2502 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 48 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 12 ከሰሸዋ ዞን 10 ከደሴ ከተማ 8 ከባህር ዳር ከተማ 5 ከምስጎጃም ዞን 3 ከምዕጎንደር ዞን ከአዊ ብሄረሰብ ዞን 2 ፣ ከጎንደር ከተማ 2 ፣ ከደጎንደር ዞን 2 ፣ ከኦሮሞ ብሰብ ዞን 2፣ ከሰወሎ ዞን 2 ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 144 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 9 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል።አጠቃላይ በድሬዳዋ 877 በቫይረሱ የተያዙ 20 ሞት 701 ያገገሙ በሀረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 825 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 13 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ### Response:
### Text: ጎረቤት ሀገር ኬንያ እንደአዲስ የተቀሰቀሰውን የኮቪድ 19 ስርጭት ለመቆጣጠር በ5 ግዛቶች ናይሮቢ ፣ ካጂያዶ ፣ ኪያምቡ፣ ማቻኮስ እና ናኩሩ ጥብቅ ክልከላዎችን ጣለች። ጥብቅ ክልከለዎቹ ምንድናቸው በግዛቶቹ እና ከግዛቶቹ ውጪ የሚደረጉ ማናቸው አይነት ጉዞዎች ታግደዋል። ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ እንዲዘጉ ተወስኗል። በምግብ ቤቶች ውስጥ ተቀምጦ መመገብ ተከልክሏል። መጠጥ ቤቶች አልኮል መሸጥ አይችሉም ተብሏል። ከዚህ ቀደም ከምሽቱ አራት ሰዓት ይጀምር የነበረው ሰዓት እላፊ በማሻሻል ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ንጋት 10 ሰዓት የሚዘልቅ እንዲሆን ታውጇል። የአገሪቱን ፓርላማም ላልተወሰነ ጊዜ በእረፍት ላይ እንዲቆይ ተጠይቋል። በሐይማኖት ተቋማት ሰዎች በጋራ ተሰብሰበው መጸለይ ወይም ማምለክ እንዳይችሉ ታውጇል። የግል እና የመንግሥት ተቋማት ሠራተኞች ከቤት ሆነው እንዲሰሩ ተጠይቋል በቀብር ሥነሥርዓት ላይ ከ50 ያልበለጡ በሠርግ እና መሰል ሥነሥርዓቶች ላይ ደግሞ ከ30 ያልበለጡ ሰዎች ብቻ እንዲገኙ ታዟል።በመላው ኬንያ ደግሞ ሁሉም ስፖርታዊ ውድድሮች ላልተወሰነ ጊዜ ታግደዋል።በተጨማሪ መረጃ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ማርጋሬት ኬንያታ በዛሬው ዕለት የወረርሽኙን መከላከያ ክትባት በቀጥታ በቴሌቪዥን እየታዩ ወስደዋል።ምንጭ ቢቢሲ እና ሲትዝን ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ከ ልብ የሚነካ መልዕክትበፀሎታችሁ አትርሱን እያሉ ነው ተማሪዎቹእንዴት አደርክ ጸግሽ እኔ የ ተማሪ ነኝ ግን የ አአ ልጅ ነኝ ወደ ቤት እንዳንመለስ መኪናም ተከልክለናል። ትላንት ሙሉ ቀን ከቁርስ በስተቀር በረሀብ ተገርፈን ነው የዋልነው እቺንም ሽሮ ከለከሉን ወላሂ ነው ምልህ በታም ተስፋ እየቆረጥን ነው ያለነው ለሊት ግማሹ መስጊድ ግማሹ ቤተ ክርስቲያን የቀረው ደሞ ጎረቤት ምናምን ለምነው እያደሩ ነው ዛሬ ደሞ ከ ቁርስ ጀምሮ እንደሚቀጡን ነው ሚወራው።21ኛው ክዘመን ላይ አይደል እንዴ ያለነው የሰው ልጅ እንዴት በረሀብ ይቀጣ የፈለገ ቢያረክ እኮ እህል አይከለልም አይደል እንዴ ደሞ እኛ ምንም አላረግንም ውሳኔውን ተቃወምን እንጂ በአሁን ሰዓት ጸግሽ እኛ የ ተማሪዎች እጅግ ከፍተኛ የሚባል እንግልት እየደረሰብን ነው። ምግብ ተከልክለናል ዶርም ተከልክለናል በፌደራል እየተደበደብን ነው ትራንስፖርት ተከልክለናል ተማሪው ለብርድ እና ለጸሀይ ተዳርጉዋል ትምርት ሙሉ በሙሉ ተቊርጧልእኔ እዚ የማውቀው ሰውም ዘመድም የለኝም ምን እንደምሆን አስበው ጅማ ውስጥ ያለው እየመሰለኝ አደልም። በትረፋ ጸግሽ አንተን በጣም አደንቅሀለው ጎብዝልኝ እባካቹ ህዥብ እንዲያውቀው ምትችሉትን ያክል ጣሩልን። በጸሎታቹ አትርሱን መልካም ቀን ተመኘውቃጅማ ኢትዮጵያበጅማ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተማሪ ህዳር 19032010 ዓም ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር ከ45000 በልጧል። በአንድ ቀን ብቻ ከ2700 በላይ ሰው ሞቷል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ824000 በልጧል። በዩናይትድ ኪንግደም ባለፉት 24 ሰዓት 759 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተድርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 18100 ደርሷል። በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት ተጨማሪ 1194 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ 94 ሰዎች ሞተዋል። በስፔን የሟቾች ቁጥር መጨመር እያሳየ ነው። ባለፉት 24 ሰዓት 435 ሰዎች ሞተዋል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 21717 ደርሷል። ከዚህ በተጨማሪ በአንድ ቀን 4211 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 204178 ደርሷል። በደቡብ ኮሪያ 11 ተጨማሪ ኬዞች ሪፖርት ተደርገዋል። ከአስራ አንዱ መካከል ስድስቱ 6 ከውጭ የገቡ ናቸው። ሲንጋፖር የኮሮና ቫይረስ ኮቪድ19 ስርጭትን ለመግታት ያወጣቻቸውን ገደቦች እስከ 1 አራዝማለች። በኳታር ባለፉት 24 ሰዓት ተጨማሪ 608 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቻይና ተጨማሪ 30 ኬዝ ተመዝግቧል። ሀያ ሶስቱ 23 ከውጭ የገቡ ናቸው። በማዳጋስካር ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት አዲስ ኬዝ እንዳልተመዘገበ ተሰምቷል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 121 ሲሆኑ 52 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል። በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 2586639 ደርሷል። 179942 ሰዎች ሞተዋል። 705814 ሰዎች አገግመው ከሆስፒታል ወጥተዋል። ### Response:
### Text: ሴት ሰራተኞች አርፋችሁ ቤት ተቀመጡ የካቡል ከንቲባየታሊባን አዲሱ የካቡል ከንቲባ ስማቸው ሐምዱላህ ኖማኒ በካቡል የሚገኙ የማዘጋጃ ቤት ሴት ሠራተኞችን አርፋችሁ ቤት ተቀመጡ ሲሉ ተናገሩ።ከንቲባው ይህን ያሉት ታሊባን ለጊዜው ሴቶች ሥራ እንዳይሠሩ ማዘዙን በመጥቀስ ነው።ክፍት የሥራ መደቦች በወንዶች የማይሞሉ ከሆነ ብቻ ለሥራ ልትመጡ ትችላላችሁ አለበለዚያ ግን አርፋችሁ ቤት ተቀመጡ ብለዋል ከንቲባው።የካቡል አዲሱ ከንቲባ እንዳሉት በከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ሠራተኞች ውስጥ አንድ ሦስተኛው ሴቶች ነበሩ። ቤት እንዲቀመጡ የተነገራቸውም በቁጥር ወደ አንድ ሺህ ይጠጋሉ። ታሊባኖች ሥልጣን ከያዙበት ዕለት ጀምሮ ሥራ የነበራቸው ሴቶች በሙሉ የአገሪቱ የደኅንነት ሁኔታ እስኪሻሻል ድረስ ቤት እንዲቀመጡ አዟል።ሕጉን በመቃወ ሰልፍ በወጡ ሴቶች ላይም ድብደባ ፈጽሟል።ታሊባን የሴቶች ጉዳይ ሚኒስትርን ያፈረሰ ሲሆን በምትኩ ሐይማኖታዊ ደንቦች መከበራቸውን የሚቆጣጠር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት አቋቁሟል።በዚህ ሳምንት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተከፈቱ ቢሆንም ወንድ ተማሪዎች እና ወንድ አስተማሪዎች ብቻ ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ነው የተነገራቸው። ሴት ተማሪዎቸና አስተማሪዎች ግን ለጊዜው ቤት እንዲቆዩ ተደርጓል።ታሊባን ለሴቶች የተለየ ትምህርት ቤቶችን እያዘጋጀሁ ነው ብሏል።መረጃው ከቢቢሲ ነው የተገኘው። ### Response:
### Text: ይቅርታ ባቀድነው ልክ ውጤታማ ባለመሆናችን የ ኢትዮጵያ ህዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁንየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአፍሪካ ዋንጫው ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠየቀ።ዛሬ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን የኢትዮጵያን የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ቆይታ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።የፌዴሬሽኑ ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ባቀድነው ልክ ውጤታማ ባለመሆናችን የ ኢትዮጵያ ህዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ ብለዋል።አክለውም የአሰልጣኙን ኮንትራት እናከብራለን ፣ እስከ ኮንትራቱ መጨረሻ አብሮን ይቀጥላል ብለን እናምናለን ሲሉ ተናግረዋል ።አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በበኩላቸው ስንሄድም ስንመጣም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው አልተደበቅንም ፣ ብሄራዊ ቡድኑ ኩራት ነው ፣ በ ማህበራዊ ገፆች እንደተመለከትነው ድንጋይ ይዞ የተቀበለን ሰው የለም ብለዋል። እስከ መስከረም 302015 ከ ፌዴሬሽኑ ጋር ኮንትራት አለኝ ያሉት አሰልጣኙ እስከዛው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ነኝ ሲሉ ተናግረዋል።ብሄራዊ ቡድኑ ከ8 ዓመታት በኃላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ቢመለስም ምድቡን ማለፍ ሳይችል በመቅረቱ የመጀመሪያ ተሰናባች ሆኖ ከቀናት በፊት ወደ ሀገሩ መመለሱ ይታወቃል። ### Response:
### Text: ዕድሜ አጭበርብረዋል የተባሉት አትሌቶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ።ከጥር 23 282015 ዓም በአሰላ አረንጓዴው ስቴድዮም ከ ሃያ 20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና እየተካሄደ ይገኛል።በዚሁ ውድድር ላይ ከእድሜ ተገቢነት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ መነጋገሪያ ጉዳዮች ተፈጥረዋል በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወሩ የነበሩ ፎቶዎችም በርካቶችን እንዴት እኚህን የሚያክሉ አትሌቶች ከ20 ዓመት በታች ይወዳደራሉ በሚል አስገርመዋል።ይህን በተመለከተ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከደቂቃዎች በፊት ባሰራጨው መልዕክት ከእድሜ በላይ ሆነው የተገኙ አትሌቶችን በሠነድ እና በአካላዊ ምርመራ ከውድድር ውጭ መሆናቸውን ይፋ አድርጓል። ፌዴሬሽኑ ቁጥራቸው ከ80 የሚልቁ አትሌቶችም ስማቸውን ይፋ አድርጓል።ተግባሩን በፈፀሙ ቡድኖች አሰልጣኞች ላይም እርምጃ እንዲወሰድ ለየክልላቸው፣ ከተማ አስተዳደራቸው፣ ክለባቸውና ተቋሞቻቸው ፌዴሬሽኑ ማስጠንቀቂያ አዘል ደብዳቤ እንደሚልክ አሳውቋል።ማጣራቱ እስከ ውድድሩ ማብቂያ ድረስ የሚቀጥል እንደሆነ የገለፀው አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከዚህ ሲያልፍ ከሳምንትም ሆነ ከወር በኋላም ቢሆን ተጨማሪ መረጃ ከተገኘ አትሌቱ የተሸለመው ሜዳልያም ሆነ የገንዘብ ሽልማት ተመላሽ እንደሚደረግ በጥብቅ አሳስቧል።የእድሜ ተገቢነት ችግር ውስጥ የተገኙ አትሌቶችን ዝርዝር ከሥር ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: ባህር ዳርበኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክል ላይነር በባሕር ዳር ጉብኝት እያደረጉ ነው፡፡በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክል ላይነር በባሕር ዳር ጉብኝት እያደረጉ ነው፡፡አምባሳደሩ ከባሕር ዳር ከንቲባ ከሙሉቀን አየሁ ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይታቸውም ሶስት አበይት ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡የወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ፣በጣና ላይ የተጋረጠው እንቦጭ እና በግንባታው ዘርፍ ባለሀብቶች ወደ ከተማዋ እንዲመጡ ምን መደረግ እንዳለበት ተወያይተዋል፡፡አምባሳደር ማይክል የወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ፣በክልሉ መስህቦች ላይ በተጋረጡ ጉዳዮች እና ባለሀብቶች ወደ ከተማዋ እንዲመጡ ከአቻ አሜሪካ ከተሞች ጋር በጋራ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ ቅርሶች ላይ አሜሪካ እየሰራች ነው፡፡ በቀጣይም እቅዷን ይፋ እንደምታደርግም ገልጸዋል፡፡አምባሳደር ማይክል ራይነር ዛሬ ከሰዓተ በኋላ ደግሞ በባሕር ዳር የሚገኘውን የገነሜ ቤተመጽሀፍትን ይጎበኛሉ፡፡ቤተመጽሀፍቱም በኢምባሲው ወጪ እድሳት ይደረግለታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡አምባሳደር ማይክል ራይነር ዛሬ ከአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገዱ አንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ማይክል ራይነር አምባሳደር ሆነው ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያ ጉብኝት ያደረጉት ባሕር ዳር መሆኑ ይታወሳል፡፡ምንጭ አብመድ ### Response:
### Text: ልዩ 2 ሎተሪ ወጣ ሼር በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የልዩ ሎተሪ ግንቦት 192011 ዓም በብሔራዊ ሎተሪ ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል1ኛ 7000000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 00562402ኛ 3000000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር07443953ኛ 1000000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 10596644ኛ 400000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 07881295ኛ 100000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 11120776ኛ 50000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 05195017ኛ 30000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 00410378ኛ 12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር318899ኛ 12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር9116310ኛ12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 400 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 2966111ኛ 120 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር612512ኛ 120 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 099013ኛ 1200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 80 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር51914ኛ 1200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር9616ኛ120000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 40የማስተዛዘኛ ዕጣ ቁጥር 5አስተዳደሩ ለደረሳቸው ዕድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ እያለ ዜናውን ለጓደኞቻችሁ በማጋራት በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ አድርጉ ይላል፡፡ እናመሰግናለንየብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ### Response:
### Text: አስቸኳይ ግዜ አዋጅ️ቡርኪናፋሶ አስቸኳይ የግዜ አዋጅ አወጀች። ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ቡርኪናፋሶ ከማሊ በሚያዋስናት ሰሜናዊ ግዛቷ ነው አስቸኳይ ግዜ አዋጅ ያወጀችው፡፡አገሪቱ በአካባቢው አስቸኳይ ግዜ አዋጅ ያወጀችው እስላማዊ ቡድኑ የሚሰነዝራቸው ጥቃቶች አጠናክሮ በመቀጠሉ እንደሆነ የአገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ ተናግረዋል፡፡የምዕራብ አፍሪካ አገራት ጄ ኒም የተሰኘ ጅሃዲስት ቡድን በሚያደርስባቸው ጥቃት ደህንነታቸው ከግዜ ወደ ግዜ አደጋ ላይ እየወደቀ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡የቡርኪናፋሶ ባለስልጣናት ድንበር ተሻጋሪ በሆነው የሽብር ስጋት አደጋ ላይ መውደቃቸውን ቃል አቀባዩ ሬሚ ፉልጋንሴ ዳንጂኑ ተናግረዋል፡፡ባለፈው ሳምንት አገሪቱ ከማሊ በሚያዋስናት ድንር ላይ አሥር ወታደሮች በተበላው በአልቃይዳ ስር በሳህራ አከባቢ በሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ቡድን እንደተገደሉ ነው የተገለጸው፡፡ታጣቂ ቡድኑ ባለፈው መጋቢት ወር በዋና ከተማዋ ኡጋዱጉ ለስምንስት ሰዎች ሞት እና በርካቶች መቁሰል ምክንያት የሆነውን ጥቃት ጨምሮ ሌሎች በአከባቢው ለሚፈጠሩ ጥቃቶች ሃላፊነቱ ወስደዋል፡፡በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ታጣቂዎች በሚሰነዝሩት ጥቃት እና የመንግስት የፅጥታ ሃይሎች በሚወስዱት የአፀፋ እርምጃ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን የሰብዓዊ መብት ድርጅት መግለፁ ይታወሳል፡፡ምንጭ ሲጂቲኤን ### Response:
### Text: ካዎ ኮይሻ ወረዳ በደረሰ ድንገተኛ አደጋ የ1 ሰው ህይወት አለፈ በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት በተፈጠረ የመኖሪያ ቤት የመደርመስ አደጋ የአባወራው ህይወት ማለፉንና በልጃቸው ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ።አደጋው የደረሰው ትናንት እኩለ ቀን አካባቢ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲጥል የቆየው ከባድ ዝናብ ተከትሎ የተከሰተ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት የአንድ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት በመደርመሱ ነው፡፡ በወረዳው ኦፋ ሂራ የገጠር ቀበሌ እኩለ ቀን አካባቢ አደጋው ድንገት በመድረሱ በመኖሪያ ቤታቸው ከልጃቸውጋር የነበሩ አባወራ ህይወት ሊያልፍ ችሏል።በአከባቢው ማህበረሰብ ጥረት ሊድን የቻለው 14 ዓመት ዕድሜ ያለው ወንድ ልጃቸው ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶበት በወረዳው ላሾ ጤና 0ጣቢያ የህምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን የካዎ ኮይሻ ወረዳ ወንጀል መርማሪ ሻምበል ምትኩ ዘውዴ ለኢዜአ ገልጸዋል።ሟች በአከባቢዉ ሞዴል አርሶ አደር እንደነበሩ አመልክተው ለአከባቢዉ አርሶ አደሮች የሚያቀርቡት ምርጥ ዘር የተከማቸ እህልና ሌሎች ንብረቶች ጨምሮ ከ100 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙን አስረድተዋል፡፡ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስራት ሴታ በበኩላቸው ጉዳቱ የደረሰበትን ቤተሰብ በዘላቂነት ለማቋቋም አስተዳደሩ የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል ብለዋል፡፡ምንጭኢዜአ ### Response:
### Text: 5 በባለቤቶቻቸው እውቅና የሌላቸው ገፆች ️ ቴሌግራም 1 አማርኛ ይህ የቴሌግራም ቻናል የቢቢሲ አይደለም። ቢቢሲ አማርኛ በፌስቡክና በትዊተር ላይ ካለው የመገናኛ አማራጭ ውጪ በቴሌግራም ምንም አይነት ገፅ የለውም2 የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ምንም አይነት ይፋዊ የሆነ የቴሌግራም ገፅ የለውም። 3 የ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃዋር መሃመድ በቴልግራም መልዕክት የሚያሰራጭበት ምንም ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል የለውም። እንዲሁም በፌስቡክ ላይ ያለው የግል ገፁ በ የተደረገው ብቻ ነው። ፌስቡክ 1 ዲያቆን ዳንኤል ክብረት19359 ያለው የፌስቡክ ገፅ የዲያቆን ዳንኤል ክብረት አይደለም። በዚህ ገፅ የመሰራጩ መረጃዎችም የዲያቆን ዳንኤል አይደሉም።2 ጉለሌ ፖስት 87 ሺህ ያለው ጉለሌ ፖስት በሚል የተከፈተው ገፅ ሀሰተኛ ነው። የዋናው የጉለሌ ፖስት ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ 47 ሺ ያለው ነው። ይገርማልትክክለኛውን የሚከተለው እና ሀሰተኛውን ገፅ የሚከተለውን የሰው ቁጥር መልስ ብላችሁ ተመልከቱ ሌላው ከሰሞኑን በወዳጃች እና እጅግ በምናከብረው አለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ስም ብዙ ሀሰተኛ መረጃዎች እየተሰራጩ እንደሆነ ተመልክተናል ጥንቄቄ ይደረግ ያልተናገረውን ተናግሯል ያላለውንም ብሏል በሚል አንዳንድ ገፆች ሀሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው። በየዕለቱ 5 ሀሰተኛና በባለቤቶቻቸው እውቅና የሌላቸውን ገፆች እናቀርባለን ### Response:
### Text: በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን ኮልሜ ክላስተር እና ኧሌ ልዩ ወረዳ አዋሳኝ አካባቢዎች መጋቢት 1 ቀን 2014 ዓም ደግም ያገረሸው ግጭት በመኃል ለቀናት ጋብ እያለ የመጣ ቢሆንም ከመጋቢት 15 ወዲህ ግን ለተከታታይ 4 ቀናት ያለመቋረጥ በቀጠለ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱን የቲክቫህ ቤተሰቦች ገልጸዋል።በኮንሶ ዞን ኮልሜ ክላስተር በኩል ዲማያ የሚባል አካባቢ ወደ 6 ሰው እንደሞተና በርካታ መኖሪያ ቤቶች እንደተቃጠሉ እንዲሁም በኧለ ልዩ ወረዳ በኩል ዳታኔ በሚባል አካባቢ ቤቶች እንደተቃጠሉ ና ወደ 10 ሰው እንደሞተ ነው መረጃ የሰጡን ቤተሰቦቻችን የገለጹት። በአጠቃላይ በሁለቱም በኩል ከ50 በላይ የሚሆኑ ቤቶች መቃጠላቸው ተጠቅሷል።ይህን ክስተት አስመልክቶ ለቲክቫህ ቤተሰቦች መረጃ የሰጡት የኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰራዊት ቲቶ በሁለቱ ማኅበረሰብ መካከል በተፈጠረው ግጭት የሰው ህይወት ጠፍቷል ከፍተኛና ቀላል የአካል ጉዳት ተመዝግቧል እንደዚሁም የቤት ንብረት ቃጠሎዎች አሉ። ሲሉ አረጋግጠዋል።ምን ያህል ለሚለው ጥያቄ ግን የጸጥታ ችግር ሲባል ቀላል ነገር አንደለም ራስህ በአካል ሄደህ ካላጣራህና ካልመዘገብክ በቁጥር የደረሰውን ጉዳት እንዲህ ነው ማለት ይከብዳል። አንዳንድ ቀጠናዎችም በጸጥታ ምክንያት ገብቶ ማረጋገጥ አልተቻለም ሲሉ ነው የመለሱት። ### Response:
### Text: የአሜሪካው ልዩ መልዕክተኛ አዲስ አበባ ይገኛሉ።የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባ ይገኛሉ።አምባሳደር ሐመር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምሥጋኑ አርጋ የመከሩ ሲሆን ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋርም ተገናኘተው መምክራቸው ታውቋል።የአሜሪካው ልዩ መልዕክተኛ ከአምባሳደር ምስጋኑ ጋር በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያና የአሜሪካ የሁለትዮሽ ጉዳዮች እንዲሁም ቀጣናዊ፣ አኅጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል ተብሏል።ከትግራይ ጊዜዊ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በነበራቸው ቆይታ የጋራ ጉዳዮችን በማንሳት የመከሩ ሲሆን የፕሪቶሪያው ስምምነትን ሙሉ ተግባራዊነትን በተመለከተ ተነጋግረዋል።አቶ ጌታቸው ውይይቱን በተመለከተ ባሰራጩት መልዕክት የጋራ ጉዳዮችን አንስተን ተወያይተናል በተለይም የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም ደግሞ በኢትዮጵያ እና በቀጠናው መረጋጋት ላይ በጋራ ለመስራት ያለንን ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ብለዋል።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መቤት ሐመር በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ቆይታ፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች በድርድር እንዲቋጩ እና ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ እና ከለላ እንዲያገኙ ግፊት እንደሚያደርጉ ማሳወቁ ይታወሳል። ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪኤድስ ወረርሽኝ ሊባል በሚችል ደረጃእየተስፋፋ መምጣቱ ተገለፀ።በዓመት ከ27 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ ይይዛሉ የተባለ ሲሆን ከ19 ሺህ በላይ የሰዎች ደግሞ በቫይረሱ አማካኝነት ይሞታሉ ነው የተባለው።በዚህ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና በፌዴራል የኤች አይ ቪኤድስ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ፅህፈት ቤት አዘጋጅነት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።በመድረኩ እንደተገለፀው ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የስርጭት ምጣኔው ከ2 ነጥብ 5 እስከ 25 በመቶ ደርሷል።በትልልቅ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶች፣ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ የአበባ ልማትና መሰል ሰፋፊ የልማት አካባቢዎች የኤች አይ ቪ አጋላጭ ባህሪያት መስፋት ለቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ ስጋት ሆኗል።የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር ከበደ ወርቁየቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር በተደረገው ጥረት የተመዘገበው ለውጥ መዘናጋት መፍጠሩን አንስተዋል።ከአምስት እና ስድስት ዓመት በፊት የነበረውን ኤች አይ ቪን የመግታት ስራ ለመድገም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል።ምንጭ ለፋና ብሮድካስቲንግ ትዕግስት አብርሀምእባካችሁ ራሳችሁን ጠብቁ በተለይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና በትልልቅ ፕሮጀክቶች አካባቢ የምትሰሩም የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን። ### Response:
### Text: ሆሳዕናየሆሳዕና ከተማ የመብራት ጉዳይ አሰልቺ ደረጃ ላይ ደርሷል። የመብራት ሀይል ዝርክርክ አሰራሮች ህዝብን ምሬት ውስጥ ከቶታል የሆሳዕና ከተማ የመብራት ጉዳይ አሁንስ ቅጥ አጣ። ሀይ የሚላቸው አካል የለም ወይ 3 እና አራት ቀን እያጠፉ በስለት ብልጭ ቢል ለደቂቃ እንኳ ሳይቆይ ህልም እያለ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። እንዲህ አይነት ዝርክርክ አሰራር በጣም ያበሽቃል። ሆቴሎችንና የተለያዩ ፍሪጅ የሚጠቀሙ ጁስ ቤቶችና ወተት ቤቶች ለኪሳራ እየተዳረጉ ነው ያሉት። ከምንም በላይ ሆስፒታሎች እና ጤና አጣቢያዎችም በአገልግሎት አሰጣጣቸው ላይ ከፍተኛ እንቅፋት እየፈጠረ ይገኛል።ፍሪጅ ውስጥ የተለያዩ የክትባት ቫክሲኖችና የላቦራቶሪ ሪኤጀንቶች ይቀመጣሉ ታዲያ እነዚህ የህክምና መገልገያዎች በመብራት እጦት ምክኒያት ለብልሽት መዳረጋቸው አይቀሬ ጉዳይ ነው። ለብልሽት የተዳረገን የላቦራቶሪ ሪኤጀንት ለምርመራ መጠቀም ደግሞ የተሳሳተ ውጤት እንዲኖር ያደርጋል።በቅዝቃዜ እጦት ምክኒያት የሞተን ቫክሲን ደግሞ ለተገልጋይ ማድረስ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያይላል ታዲያ ለዚህ ሁሉ ችግር ተጠያቂው መብራት ሃይልና መብራት ሃይል ብቻ ነው። ዝርክርክ አሰራራችሁን ወዲያ በሉና ለህዝብ አገልግሎትን አድርሱ አቦ አሁንስ በዛ ኦድ ጨዊና ቦያ ሰለሜ ይኖሞ ሀዲይ መኢሲኖሞ ፎራም መን ቤሄሄ ዬኮኪም ጣሌ ጎቲች ገጊን ጣሌ። ፀጋ ናዝሬት ### Response:
### Text: ትምህርት ሚኒስቴር በ2012 ዓም የትምህርት ዘመን ወደ 11ኛ ክፍል መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነበ2011ዓም የአጠቃላይ ትምህርት 10ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ወደ 11ኛ ክፍል መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ መሆኑን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ በዚህም መሰረት፡ 08 የመደበኛ፣የማታና የግል ተፈታኝ ተማሪዎች ለወንድ 200 እና በላይ ለሴት 186 እና በላይ ሆኖ የማታና የግል ተፈታኝ ተማሪዎች በማታው ፕሮግራም ይቀጥላሉ።08 ለአካል ጉዳተኞች መስማት የተሳናቸው ለወንድ 186 እና በላይ ለሴት 171 እና በላይ እንዲሁም ለዓይነ ስውራን ለወንድ 171 ለሴት 161 እንዲሆን ተወስኗል።08 ልዩ ድጋፍ የሚሹ ክልሎች፣አርብቶ አደር አካባቢዎች እና የፀጥታ ችግር የታየባቸው አካባቢዎች ደግሞ ለወንድ 186 ለሴት 171 እንዲሆን መወሰኑን ኤጀንሲው አስታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ 08 ሁሉም ወደ 11ኛ ክፍል የሚገቡ ተማሪዎች የሚመርጡት የትምህርት መስክ በትምህርትና ሥልጠና ፍኖተካርታው በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በምርጫ ተፈጥሮ ሳይንስና ማህበራዊ ሳይንስ ብቻ ይሆናል፡፡08 ከዚህ በፊት የአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት 10ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 200 ነጥብ እና ከዚያ በላይ ያመጡ በማታው ፕሮግራም የ11ኛ ክፍል ትምህርታቸውን መቀጠል የሚችሉ መሆኑን ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡ምንጭ ትምህርት ሚኒስቴር ### Response:
### Text: ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በዓለም ተፅዕኖ ከፈጠሩ 50 ግለሰቦች አንዱ ሆኑጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዓቢይ አህመድ በፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ከፈረንጆቹ 20102019 በነበሩት 10 ዓመታት በዓለም ላይ ለውጥ በማምጣት ከተጠቀሱት 50 ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ዝርዝር ተካትተዋል። 1ኛ በፖለቲካው መስክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ቱኒዚያዊው ሞሃመድ ቡአዚዝ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜሪከል የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይናው መሪ ዢ ዥንፒንግ እና ሌሎችም ተካትተዋል። 2ኛ በምጣኔ ሀብት፣ በቢዝነስና በቴክኖሎጂ የአማዞን ኩባንያ ባለቤት ጄፍ ቤዞስ የአፕል ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቲም ኩክ ቢል እና ሚሊንዳ ጌትስ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ ፕሬዚዳንት ክርስቲን ላጋርድ ቻይናዊው ስራ ፈጣሪ ባለሃብት ጃክ ማ የፌስቡክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ እና ሌሎችም ተካትተዋል። 3ኛ በባህል፣ በሚዲያ፣ በስፖርት እና በሳይንስ ዘርፍ ሊዮኔል ሜሲ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ አሜሪካዊቷ ሙዚቀኛ ቴይለር ስዊፍት የሜዳ ቴኒስ ንግስቷ ሴሬና ዊሊያምስ እና ሌሎችም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተካትተዋል።ምንጭ፡ ኢፕድ ### Response:
### Text: ሀርጌሳ ሀገራችንን አልሸጥንም ሙሴ ባሂ አብዲባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ የነበሩት የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት ዛሬ ሐሙስ ዕለት ወደ ሀርጌሳ ተመልሰዋል።ፕሬዚዳንቱ ሀርጌሳ ሲገቡ ህዝቡ ወደ አደባባይ ወጥቶ ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።አደባባይ ወጥቶ ለተቀበላቸው ህዝብ ባሰሙት ንግግር ከጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ ጋር የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ትልቅ ዋጋ ያለው መሆኑ ገልጸዋል።ፕሬዜዳንቱ ሀገራችንን አልሸጥንም ያሉ ሲሆን ኢትዮጵያ የባህር ሃይል ጦር ሰፈር በሊዝ ነው የምትከራየው ብለዋል። ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ እውቅና ለመስጠትም ተስማምታለች ሲሉ ተናግረዋል።ፕሬዜዳንቱ መቼ እንደሆነ ቀኑን በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በቅርቡ ለሶማሌላንድ እውቅና እንደሚሰጥ በድጋሚ ለህዝባቸው ገልጸዋል። ይህ የሶማሌላንድ ህዝብ ላለፉት ሶስት አስርት አመታት የደረሰበት ትልቅ ስኬት ነው ሲሉም ገልጸዋል።ስምምነቱ በሁለቱም ወገን በኩል ፍላጎትና ጥቅማቸውን መሰረት ያደረገ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።በሌላ በኩል ሶማሌላንድን እንደ ራሷ አንድ ግዛት የምትቆጥራትና የተፈረመው ስምምነት ሉዓላዊነቴን ጥሷል በሚል የተቃወመችው ሶማሊያ ውስጥ ዛሬ የተቃውሞ የአደባባይ ሰልፎች ሲደረጉ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።ፎቶ ቪድዮ ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ዛሬ ታህሳስ 25 ቀን 206 ዓም ### Response:
### Text: ጊፋታ2013 የዘንድሮው የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በተለያዩ ፕሮግራሞች ይከበራ ተብሎ ይጠበቃል።በዓሉን በዩነስኮ ለማስመዝገብ የሚያደርገውን ጥረት የዞኑ አስተዳደር መላ የዞኑን ህዝብና አጋር አካላትን በማስተባበር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።ኮቪድ19 በፈጠረው ችግር ምክንያት የዘንድሮውን የወላይታ ህዝብ ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ከዚህ በፊት በተለመደው ሁኔታ ህዝቡ በብዛት በተሰበሰበት ቦታ ለማክበር የማይቻል ቢሆንም ህዝቡ ቫይረሱን እየተከላከለ በተለያዩ ሁነቶች ማክበር እንዲቻል ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።በዓሉን ይዘቱ በጠበቀ መልኩ ህዝቡ በያለበት አካባቢ ሆኖ በአጫጭር ፓነል ውይይቶች ፣ በማስታወቂያ እንዲሁም በፕሮሞሽን የጊፋታ በዓል እንዲያከብር ጥሪ ቀርቧል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲሰራጩ የነበሩ መረጀዎች ሀሰተኛ መሆናቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ ዶክተር እንድሪያስ ጌታ አሳውቀዋል 1 የወላይታ ህዝብ ህገመንግስታዊ በክልል የመደራጀት ጥያቄን በተመለከተ በዘንድሮዉ የጊፋታ በዓል ቀን የህዝቡ ክልል መዋቅር በይፋ ይታወጃል በማለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቀው መረጃ የተሳሳተ ነው።2 የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገብተዋል በማለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ መረጃዎች የተሳሳቱ ናቸው።ምንጭ የወዞመኮጉ ### Response:
### Text: 350 ሺ ሰዎች ለረሃብ ተጋልጠዋል ሮይተርስ ተመልከቱት ያለው የተመድ የውስጥ ሪፖርት ኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ ተከስቷል ለማለት የተቀመጡ መስፈርቶች አሉ አሁን በትግራይ ባለው ሁኔታ ከ90 በላይ የክልሉ ነዋሪ ሰብዓዊ ድጋፍ አግኝቷል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርበሮይተርስ የተመለከትኩኝ ባለው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ሰነድ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ወደ 350000 ያህል ሰዎች በረሃብ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ተገምቷል።በሰነዱ ላይ ትንታኔ የሰጡት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኤጀንሲዎች እና የእርዳታ ቡድኖች ናቸው።ይህ ነው የሮይተርስ ዘገባ 35000020210609=401 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ሳምንታዊ ሰጥተው ነበር።በዚህ መግለጫቸው ላይ በትግራይ ክልል 350 ሺህ ሰዎች ለረሃብ ተጋልጠዋል በሚል በተመድ የውስጥ ሰነድ ላይ ቀረበ የተባለውን ለህዝብ ይፋ ያልሆነ ሰነድ ምንጭ ተደርጎ የወጣውን መረጃ ትክክል እንዳልሆነ አሳውቀዋል።አምባሳደር ዲና ኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ ተከስቷል ለማለት የተቀመጡ መስፈርቶች አሉ አሁን በትግራይ ባለው ሁኔታ ከ90 በመቶ በላይ የክልሉ ነዋሪ ሰብዓዊ ድጋፍ አግኝቷል ሲሉ አስረድተዋል።አክለውም በቀጣይ የእርሻ ስራም 70 በመቶ ለግብርና ስራ የሚውል መሬት ለእርሻ ስራ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰው በዚህ ሁኔታ ረሃብ ይከሰታል የሚለው ትክክል እንዳልሆነ ተናግረዋል። ### Response: