text
stringlengths
707
989
### Text: አሳ ዛኝ ዜና️በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ወረዳ በጫነው አሸዋ ላይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ።የጃማ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የትራፊክ አደጋ መርማሪ እንደገለጹት ሲኖትራክ ተሽከርካሪው በቶ ከተባለ ስፍራ በጫነው አሽዋ ላይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ደጎሎ ከተማ በመጓዝ ላይ እያለ ነበር አደጋው ያጋጠመው።ተሽከርካሪው በዛሬው እለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት ገደማ 14 ቀበሌ ልዩ ቦታው ዝግባ ከሚባል ስፍራ ሲድርስ እስካሁን ባልታወቀ ምክንያት በግምት 60 ሜትር ከሚሆን ገደል ውስጥ በመግባቱ አደጋውም መከሰቱንም አስረድተዋል።በአደጋው የ7 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ13 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም በ11 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ዋና ሳጅን ተስፋው ነጋ አስታውቀዋል።ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው በጃማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 13 ሰዎች ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር መላካቸውን ዋና ሳጅን ገልጸዋል፡፡ዋና ሳጅን ተስፋው አሸዋና ድንጋይ ላይ ሰዎችን መጫን እየተለመደ እየመጣ በመሆኑ በቀጣይ ባለሀብቶችና ሹፌሮች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰባቸውን ከጃማ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።ምንጭ ### Response:
### Text: ዩኒቨርሲቲዎች የፌዴራል ተቋምነታቸው ሊረጋገጥ የአካዳሚክ ነጻነታቸውም ሊከበር ይገባል አሁን ባለው ሁኔታ ዩኒቨርሲቲዎች የሚስተዋለው እንደ ፌዴራል ሳይሆን እንደ አንድ አከባቢ ተቋም የመንቀሳቀስ አዝማሚያ ፈር ሊበጅለትና የፌዴራል ተቋምነታቸው ሊረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ የአካዳሚክ ነጻነታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል፡፡የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋምም ምልከታው ተገቢና ሊታረም እንደሚገባው በመጠቆም ዩኒቨርሲቲዎች የፌዴራል ተቋም ሆነው እንዲሰሩ እንደሚደረግና የአካዳሚክ ነጻነታቸው እንዲከበር የሚያስችሉ እርምጃዎችም እንደሚወሰድ አረግግጧል፡፡በ2012 የትምህርት ዘመን ወደትግበራ የሚገባውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ አስመልክቶ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴት አዘጋጅነት ዛሬ በሸራተን አዲስ በተካሄደው የባለድርሻዎች የውይይት መድረክ ላይ እንደተገለጸው ዩኒቨርሲቲዎች በአደረጃጀታቸውም ሆነ በአሰራራቸው የፌዴራል ሳይሆን የአከባቢ ተቋማት መስለዋል፡፡ ከተማሪዎች ምደባ እስከ መምህራንና አስተዳደር አካላት ያለው እውነትም ይሄንኑ ያሳያል፡፡ ይህ ደግሞ በዩኒቨርሲቲዎች ለሚስተዋለው አለመረጋጋት ጭምር ምክንያት ስለሚሆን ሊታረም ዩኒቨርሲቲዎችም የፌዴራል ተቋምነታቸው ሊረጋገጥ ይገባዋል ሲሉ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 08193 ### Response:
### Text: የአትክልትና ፍራፍሬ ዋጋ በጥቅምት መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል የጥቅምት ወር የአትክልትና ፍራፍሬ ዋጋ መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ገለፀ። የጥቅም ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 18 ነጥብ 6 በመቶ ሆኖ መመዝገቡንም አስታውቋል። ኤጀንሲው ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የዚህ ወር የአትክልትና ፍራፍሬ ዋጋ ካለፈው ወር ጋር ሲነፃፀር በዜሮ ነጥብ ሁለት ከመቶ ቅናሽ ታይቷል።በወሩ ቲማቲም፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ድንች፣ ጎመን፣ ካሮት፣ ምስር፣ ቅቤ፣ የምግብ ዘይት እና ወተት አይብና ዕንቁላል መጠነኛ ቅናሽ አሳይተዋል። ባለፉት ተከታታይ ወራት ምግብ ነክ በሆኑ ምርቶች ላይ የማያቋርጥ ጭማሪ መስተዋሉ ይታወቃል።በጥቅምት ወር ደግሞ ምግብ ነክ ባልሆኑ ምርቶች ላይ መጠነኛ ጭማሪ መስተዋሉን ኤጀንሲው አመልክቷል። በሌላ በኩል ዋና ዋና የእህል አይነቶች በተለይ ጤፍ፣ ገብስ፣ ማሽላ፣ በቆሎና የስንዴ ዱቄት እንዲሁም የበሬ ስጋ የተጋነነ ባይሆንም በተያዘውም ወር የዋጋ ጭማሪው እንደቀጠለ ነው።ምክንያቱ ደግሞ የልብስና መጫሚያ፣ የቤት ኪራይ፣ ማገዶና ከሰል፣ የቤት ዕቃዎችና ማስጌጫዎች፣ የቤት መስሪያ እቃዎች፣ ሕክምናና ትራንስፖርት ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ መሆኑን ኤጀንሲው ጠቅሷል።አጠቃላይ የጥቅምት ወር የዋጋ ግሽበት ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጻር ተመሳሳይ መሆኑን አስታውቋል። ### Response:
### Text: የሞት ፍርድ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት እና የሳውዲው ልዑል በሌሉበት የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው።በየመን የሑቲ ታጣቂዎች ፍርድ ቤት የአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕንና የሳኡዲውን ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማንን በሌሉበት ሞት ፈረደውባቸዋል።ፍርድ ቤቱ በነዶናልድ ትራምፕ መዝገብ ተከሰው የነበሩ ዘጠኝ ሰዎች ከትናንት በስቲያ በአደባባይ በሞት ቀጥቷቸዋል፡፡በሞት ከተቀጡት ዘጠኝ ሰዎች መሀል በሚያዝበት ወቅት አዳጊ የነበረ አንድ ልጅ ይገኝበታል፡፡በሰንዓ አደባባይ ላይ በመቺ ኃይል ከጀርባ እየተተኮሰባቸው እንዲገደሉ የተደረጉት ዘጠኝ የመናዊያን በ2018 አንድ ከፍተኛ የሑቲ አመራርን በሳኡዲ መራሹ ኃይል የአየር ጥቃት እንዲገደል መረጃ አቀብላችኋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው ናቸው፡፡7ኛው ተከሳሽ የሳኡዲው ልኡል መሐመድ ቢን ሰልማን እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሌሉበት ሞት ተፈርዶባቸዋል፡፡9ኙ ሰዎች የተገደሉት በሰንአ ታህሪር አደባባይ ሕዝብ በተሰበሰበበት ነበር፡፡ተመድ ይህን የአደባባይ ግድያ በጥብቅ ያወገዘ ሲሆን አሜሪካ ፣ ዩኬ ፣ እንዲሁም የአውሮጳ ኅብረት ድርጊቱን ኮንነዋል፡፡ተመድ የፍርድ ሂደቱ ዓለም አቀፍ ደረጃን የማያሟላ ነበር ሲል አሜሪካ ደግሞ የተፈፀመድን ድርጊት አሳፋሪ ብላዋለች የአውሮጳ ኅብረት በበኩሉ ቅጣቱ ኢሰብአዊና ነውረኛ ብሎታል፡፡ ### Response:
### Text: የፌዴራል ፖሊስ ለልጆቻችሁ ሙሉኃላፊነት ይወስዳል አስተማማኝ ጥበቃም ያደርግላቸዋል የጋምቤላ ትምህርት ቢሮከሰሞኑን በጋምቤላ ክልል የፀጥታ ችግር መከሰቱና የሰዎች ህይወት ማለፉ ፣ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ እንዲሁም በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ይታወቃል።ይህን ተከትሎም በክልሉ የሰዓት እላፊ ገደብ ታውጆ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እንዴት ሊሆን ነው የሚለው የብዙሃን ጥያቄ ነው።የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሰሞነኛው የክልሉ የፀጥታ ሁኔታ አንፃራዊ ሰላም እየታየበት በመሆኑ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፉ ብሔራዊ ፈተና ላይ እንዲሰጥ ተወስኗል ሲል አሳውቋል።ቢሮ ፈተናው በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እንደሚሰጥ አረጋግጧል።ተፈታኝ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲ በሚኖራቸው ቆይታ አስተማማኝ ጥበቃ ይደረግላቸዋልም ብሏል።የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ለማከናወን የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል ያለ ሲሆን በዚህም መሰረት ወላጆች ተፈታኝ ልጆቻቸውን በወረዳ ማዕከል በተዘጋጁ የትራንስፖርት አገልግሎት በመጠቀም ወደ መፈተኛ ዩኒቨርስቲ እንዲልኩ ጥሪ አቅርቧል።ቢሮው ተፈታኝ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲ በሚኖራቸው ቆይታ የፌዴራል ፖሊስ ሙሉ ኃላፊነት እንደሚወስድ እና አስተማማኝ ጥበቃ እንደሚደረግላቸው አሳውቋል። ### Response:
### Text: የሲዳማ እና ወላይታ እርቀ ሰላም️የሲዳማና ወላይታ የሀገር ሽማግሌዎች የእርቀ ሠላም ውይይት እያካሄዱ ነው።በሀዋሣና ሌሎችም አንዳንድ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረውን ግጭት በመፍታት በሲዳማና ወላይታ ሕዝቦች መካከል ዘላቂ እርቀ ሠላም ለማውረድና የሀገር ሽማግሌዎች እየተወያዩ ነው።የሁለቱን ህዝቦች የቆየ ታሪካዊና ሁለንተናዊ ትስስር እንዲሁም መልካም ጉርብትና ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።የሀገር ሽማግሌዎቹ በዚህ ዓመት ከታየው ጊዜያዊ ግጭት ይልቅ በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ለረጅም ዘመናት ጸንቶ የዘለቀው ታሪካዊ ትስስር፣ አንድነትና ወንድማማችነት ጎልቶ መውጣት የሚገባው ነው ብለዋል፡፡ግጭቱና ያስከተለው ዘርፈ ብዙ ጉዳት ሁሉንም ያሳዘነና ያሳፈረ ነው ያሉት ሽማግሌዎቹ ያም ሆኖ ግን ከጥንት ጀምሮ ያለ ምንም ቁርሾ ከዘለቀው የወላይታና የሲዳማ ጐረቤት ሕዝቦች መልካም ግንኙነት አንፃር ይቅር ተብሎ ሊታለፍ የሚገባው መሆኑን ገልጸዋል።የግጭቱ መንስኤዎችም ሆነ ድርጊቱ የጥቂቶች እንጂ አብዛኛውን የሲዳማም ሆነ የወላይታ ሕዝብ አይወክሉም ብለዋል።በዚህ አሳዛኝ ክስተት ሕይወት ጠፋቷል ንብረት ወድሟል፣ በርካታ ወገኖችም ተፈናቅለዋል፡፡ያለፈው አልፏል የወደፊቱን በማሰብ ሥር ነቀል እርቀ ሠላም መውረድ እንዳለበት መጠየቃቸውን የደቡብ ክልል መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዘግቧል።© ### Response:
### Text: ተስፋ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከምንም በላይ ለበርካታ ወራት የእናት አባቶቻቸውን የእህት ወንድሞቻቸውን ፣ የወዳጆቻቸውን ድምፅ ያልሰሙ እጅግ በርካቶች ስምምነቱ በፍጥነት ወደተግባር ገብቶ ያናፈቋቸውን ሁሉ ድምፃቸውን ሊሰሙ ጓግተዋል።ከዚህ ቀደም የባንክ አገልግሎት በመኖሩ እያገዟቸው የነበሩ መላ ቤተሰቦቻቸውን ዳግም አግኝተዋቸው የየትኛውም የእርዳታ ድርጅት እና ተቋም አካል ደጅ እንዳይጠኑ ለማድረግና ያለባቸውን ችግር ለመቅረፍ እየተጠባበቁ ነው።ቤተሰቦቻቸው በህይወት ይኑሩ አይኑሩ እርግጠኛ ያልሆኑ ሚሊዮኖች የሰላም ስምምነቱ እጅግ በፍጥነት ተተግብሮ ፣ መሰረታዊ አገልግሎት ጀምሮ ለማየት ተስፋን ሰንቀዋል።ከማንም ከምንም በላይ የጦርነቱ ቀጥተኛ ተጎጂዎች ህመማቸው ፣ ናፍቆታቸው ፣ ሀዘናቸው የከፋ ነውና ይህ የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን እና እፎይ እንዲሉ በተለይ በማህበራዊሚዲያ አፍራሽ ስራ የሚሰሩ ፣ የበለጠ ጥላቻን የሚዘሩ ሰላም በመሆኑ ጥቅማቸው የሚጎድልባቸው አካላት ከድርጊታቸው ቢታቀቡ መልካም ነው።የሰላም ስምምነት መፈረሙ የመጀመሪያው እርምጃ እንጂ የመጨረሻ አይደለምና በተለይ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ለስኬቱ የራሳቸውን በጎ ድርሻ መጫወት ይጠበቅባቸዋል። በሰላም ሁሉም አሸናፊ ነውና ከብሽሽቅ ፣ ከጥላቻ ከአጉል የአሸናፊነት ስሜት መራቅ ይገባል። ሰላም ### Response:
### Text: በአሜሪካ የሚደርስበትን ዘር ጥቃት በመሸሽ ኑሮውን አፍሪካ ያደረገው ግለሰብ በአሜሪካ የሚደርስበትን የዘር ጥቃት በመሸሽ ኑሮውን በአገረ ጋና መስርቶ እየኖረ መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል፡፡ ኦባዴል ካምቦን የተባለው ትውልደ አሜሪካዊው አሜሪካ እያለ መልኩ ጥቁር በመሆኑ በፖሊሶች ዘር ተኮር ጥቃት ሲደርስበት እንደቆየ ይናገራል፡፡በተለይ በአሜሪካ ቆይታው የህይወቱን ወሳኝ ምዕራፍ የቀየረው በአውሮፓዊያኑ 2007 ተገቢ ያልሆነ ክስ ተመስርቶበት ፍርድ ቤት ከቀረበ በኋላ መሆኑን ኦባዴል ካምቦን አስታውሷል፡፡ክሱም በግለሰቡ መኪና መቀመጫ ስር የተቀባበለ የጦር መሳሪያ መገኘቱና ይህም በተሸከርካሪው ላይ ሆኖ በሌሎች አካላት ላይ ተኩስ ለመክፈት የታሰበ እንደሆነ የሚል ነበር፡፡ይሁን እንጂ ግለሰቡ ያልተቀባበለ ህጋዊ መሳሪያ የያዘ በመሆኑና በኋላ ላይ ጉዳዮ ሲጣራ ከቀረበበት ክስ ነፃ ሊወጣ መቻሉን ነው የተነገረው፡፡ በወቅቱ በቀረበበት ክስ ክፉኛ የተደናገጠው ግለሰቡ በአሜሪካ በስራ ያጠራቀመውን 30 ሺህ ዶላር ይዞ እትብቱ የተቀበረበት አገር ዳግም ላይመለስ ከቤተሰቡ ጋር አክራ ጋና ለመኖር ወሰነ፡፡በአሁኑ ወቅትም በአገረ ጋና በአፍሪካ ጥናት ተቋም መምህር ሆኖ እያገለገለ ሲሆን ከባለቤቱና ከሶስት ልጆቹ ጋር በመሆን በአሜሪካ የተነፈገውን ነፃነት እያጣጣመ ስኬታማ ኑሮ እየኖረ መሆኑን ዘገባው ያትታል፡፡ ### Response:
### Text: የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን የተመለከተ ውይይት በባህርዳር ተካሄደ።የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልል ደረጃ ፈተናውን ውጤታማ ለማድረግ ከዞንና ወረዳ የፈተና ክፍል ሰራተኞች ጋር በባህር ዳር ከተማ ፈተናውን አስመልክቶ ውይይት አድርጓል፡፡የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምኃላፊ አቶ ሙላው አበበ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ባለው አጭር ጊዜ አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራ በመስራት በክልሉ ያለመንም ችግር በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።የፈተና ጊዜው አጭር በመሆኑ ከዛሬ ጀምሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት መስራትና ለትምህርት ቤቶችም ድጋፍ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።ከዚህ በፊት ለኦንላይን ፈተና የተመለመሉ ፈታኞች ቀጣዩን በወረቀት የሚሰጠውን ፈተና የሚፈትኑ ሲሆን በየደረጃው ያለው የትምህርት መዋቅር የፈተና ቁሳቁሶች እንዲሟሉ በትኩረት እንደሚሰራም ተነግሯል፡፡መምህራን እንዲሁም ወላጆች ተማሪዎችን በስነልቦና እንዲጠነክሩ እና ባላቸው ጊዜም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደረጉ የተለመደ ድጋፍ እንዲያደርጉ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል፡፡ከየካቲት29 እስከ መጋቢት 022013 ዓም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በአማራ ክልል ከ82 ሺህ በላይ ተማሪዎች በ249 የፈተና ጣቢያዎች እንደሚፈተኑ ይጠበቃል፡፡መረጃው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ነው። ### Response:
### Text: በሚዛን አማን 1 ኪሎ ስጋ ከ360 ብር በላይ መሸጥ ተከለከለ።የቤንች ሸኮ ዞን ንግድ እና ገበያ ልማት በልኳንዳ ቤቶች የስጋ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ አድርጓል።በስጋ ዋጋ ላይ እየታየ ያለዉ የዋጋ ጭማሪ የህብረተሰቡን የመግዛት አቅም የሚፈታተን እና ወጥነት የሌለዉ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት የቤንች ሸኮ ዞን ንግድ እና ገበያ ልማት መምሪያ በዞኑ ከሚገኙ የልኳንዳ ቤት ባለቤቶች ጋር ዉይይት አካሂዷል።ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር በተደረገዉ ዉይይት የስጋ ዋጋ ወጥነት እንዲኖረው መግባባት ላይ ተደርሷል። በዚህም መሠረት የ1 ኪሎ ስጋ የመሸጫ ዋጋ 360 ብር ሲሆን ፣ ግማሽ ኪሎ ግራም ስጋ 180 ብር እንዲሁም ሩብ ኪሎ ሰጋ በ90 ብር ወደ ውስጥ ሲሆን 85 ብር ደግሞ ወደውጭ እንዲሸጥ ተወስኗል። ከተገለፀዉ ዋጋ በላይ መሸጥ የተከለከለ መሆኑን መምሪያው ያሳሰበ ሲሆን የዋጋ ጭማሪ አድርገው የሚሸጡ የንግድ ድርጅቶችን ሲመለከት ማህበረሰቡ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ተጠይቋል።ይህንን ውሳኔ ተግባራዊ በማያደርጉት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ መምሪያው ማስታወቁን ከሚዛን አማን ፋና ኤፍ ኤም 925 የተገኘው መረጃ ያሳያል።ከዚህ ቀደም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በከተማው ውስጥ የሚገኙ ልካንዳ ቤቶች የስጋ መሸጫ ዋጋ እንደተመነላቸውና ከተላለፈው የዋጋ ተመን በላይ ጨምረው በሚሸጡት ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ማሳወቁ ይታወሳል። ### Response:
### Text: ዛሬ በመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እርስ በእርሳቸው ተጋጩ። ፓሊስም ወደግቢው በመግባት አስለቃሽ ጭስ በመጠቀም ሁኔታውን ለማረጋጋት ችሏል።የግጭቱ ምክንያት ዛሬ በግቢው በተደረገ ስብሰባ ላይ ተማሪዎች የሰነዘሩት ቃል አለመግባባትን እና ቁጣን በመፍጠሩ ነው። ስብሰባው በግቢው እየተስተጓጎለ የሚገኘውን የትምህርት ስርዓትን በሚመለከት ከተማሪዎች ጋር ወይይት ለማድረግ የታቀደ ነበር። በተፈጠረው ግጭት የተጎዱ ተማሪዎች እንዳሉ እና ብሄርን መሰረት ተደርጎም አንዳንድ ግለሰቦች በሰዎች ላይ ድብደባ መፈፀማቸውን ከአይን እማኞች ባገኘሁት መረጃ ለመረዳት ችያለሁ።በዩኒቨርሲቲው አቅራቢያም የትራስፖርት አገልግሎት ተስተጓጉሎ አምሽቷል።በሁኔታው የተደናገጡ ተማሪዎች አዳራቸውን በእምነት ተቋማት እና በተለያዩ ቦታዎች ለማድረግ መገደዳቸውንም ገልፀዋል። በግቢው የሚገኙ ተማሪዎችም ሁኔታው እጅግ እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። የሚመለከተው አካል ይህን ችግር እንዲፈታላቸውም ተማፅነዋል።በተጨማሪ በዩኒቨርሲቲው የሚማሩ የጋምቤላ ክልል ተማሪዎች ግቢው እንዲለቃቸው መጠየቃቸው ተሰምቷል። ነገር ግን ጥያቄያቸው ወድቅ መደረጉን እና የዩኒቨርሲቲው አስተዳደሮችም ሁኔታዎች ወደ ቀደመው መልኩ እንደሚመለሱ አስረድተዋቸዋል ተብሏል። በአሁን ሰዓት ግቢው ሰላማዊ ነው።ምንጭ የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ### Response:
### Text: በባቲ ከተማ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በመስጠት የተጠረጠረ ግለሰብ ተያዘ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባቲ ከተማ ሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በመስጠት የተጠረጠረ ግለሰብን እጅ ከፍንጅ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር መሃመድ አሊ እንደገለጹት ሀሰተኛ ማስረጃ በመስራት በህገ ወጥ መንገድ የመጠቀም 0ተግባር እየተስፋፋ መጥቷል። ሰሞኑን ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት ፖሊስ ባካሄደው ፍተሻ ከ170 በላይ የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ማግኘት መቻሉን አመልክተዋል። ከዚህም ውስጥ023 ተማሪዎች ከስምንተኛ ወደ ዘጠንኛ ክፍል አልፈዋል ተብሎ የተሰጣቸውና 115 የተለያዩ ኮሌጆች ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ይገኙበታል።ከጉዳዩ ጋር ከተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች መካከል 0አንደኛው ታህሳስ 22012 ዓም በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ከሰነድ መስሪያ ቁሳቁሶችና ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ጋር እጅ ከፍንጅ መያዙን ዋና ኢንስፔክተር መሃመድ አስታውቀዋል።የተያዘው ተጠርጣሪ 0ጉዳዩ በህግ እየተጣራ እንደሚገኝና ቀሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እየተደረገበት መሆኑን 0አመልክቷል። በከተማው በርካታ ህገ ወጥ ተግባራት በስውር እየተሰሩ ነው ያሉት ዋና ኢንስፔክተሩ እነዚህን ህገ ውጥ ተግባራት ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን አብራርተዋል፡፡ኢዜአ ### Response:
### Text: ቱርክ በየትኛዉም ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጎን ትቆማለች አምባሳደር ያፕራክ አልፕበኢትዮጵያ የቱርክ አምባሳደር ያፕራክ አልፕ የህዳሴዉ ግድብ ሶስትዮሽ ድርድር እና የኢትዮ ሱዳን የድንበር ዉዝግብ በሠላማዊ መንገድ ሊፈታ ይገባል አሉ።አምባሳደሩ ይህን ያሉት ለኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 በሰጡት ቃለምልልስ ነው።ቱርክ ከሱዳን እንዲሁም ከኢትዮጵያ ጋር መልካም ግንኙነት ያላት አገር መሆኗን የገለፁት አምባሳደሩ ጦርነት ለሁለቱም አገራት ስለማይበጅ ልዩነታቸዉን በዉይይት እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡አምባሳደር ያፕራክ አልፕ አገራቸዉ በየትኛዉም ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጎን እንደምትቆምም አስታዉቀዋል፡፡አገራቸዉ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድ ልዉዉጥ ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ እንደምትሰራም ገልፀዋል።ቱርክ እና ኢትዮጵያ በርካታ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት እንዳላቸዉ የገለፁት አምባሳደር ያፕረክ አልፕ አሁን ላይ የአገራቱ አመታዊ የንግድ ልዉዉጥ 6 መቶ ሚሊዮን ዶላር ደርሷል ብለዋል፡፡በሌላ መረጃ ኢትዮጵያና ቱርክ በትራንስፖርቱ ዘርፍ በቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን መግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወሮ ዳግማዊት ሞገስ ከቱርኩ የትራንስፖርት እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር አዲል ካራይስማይሎግሉ ጋር ስምምነቱን መፈራረማቸውን በትዊተር ገጻቸው አሳውቀዋል። ### Response:
### Text: የታላቁ ህዳሴ ግድብ 3ኛውን የውሃ ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ ነው ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ በትኩረት እየተሰራ ነው ሌጀኔራል ደስታ አብቼየመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ሌጀኔራል ደስታ አብቼ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው የምትገኘው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ያለምንም ፀጥታ ችግር እንዲከናወን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።ሌጀኔራል ደስታ ሠራዊቱ የተሠጠውን ተልኮ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት መፈፀም በመቻሉ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ ግብአቶች በሰላም ተጓጉዘው እንዲደርሱ እና ሰራተኞችም ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።የታላቁ ህዳሴ ግድብ 3ኛውንየውሃሙሌት ለማከናወን በ21 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ሌጀኔራሉ የግድቡ ግንባታ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።አክለውም የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ ዕድገታችንን ለማደናቀፍ ከሱዳን ሰርገው የሚገቡ ኃይሎችን እየተከታተለ ሴራቸውን እያከሽፈው ይገኛል በቀጣይም ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ሲቪል አመራሮች ጋር ተቀናጅቶ ግዳጁን በአስተማማኝ ለመወጣት ዝግጁነቱ የላቀ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ፎቶ ፋይል ### Response:
### Text: በአሁኑ ሰዓት የወልድያ ከተማ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ከተማሪዎች ጋር እየተወያዩ ነው ከግጭቱ ጋር በተያያዘ ተሳታፊና ተባባሪዎች ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 13 ተማሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው ወልዲያ ዩኒቨርሲቲየዩኒቨርሲቲያችንን ወቅታዊ መረጃ በተመለከተበቅድሚያ ከትናንት ወዲያ ጥቅምት 292012 ዓም ምሽት 500 ስዓት ላይ በወልድያ ዪኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ ግጭቱ የሁለት ተማሪዎቻችንን ህይወት የቀጠፈና በሌሎች 13 ተማሪዎችቻን ላይም ቀላል የሚባል ጉዳት መድረሱን የህክምና ምርመራ ውጤታቸው ላይ መረዳት ተችሏል፡፡ በመሆኑም ድርጊቱ መላውን የዩኒቨርሲቲያችንን ማህበረሰብ መምህራንን፣ ሰራተኞቻችንና ተማሪዎቻችንን ከዛም አልፎ የአካባቢውን ማህበረሰብ ያሳዘነ ድርጊት በመሆኑ ክስተቱን እያወገዝን በደረሰው ጉዳት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን አንገልፃለን።የሟቾቹን ነፍስ ፈጣሪ እንዲምር ጉዳት የደረሰባቸው የተማሪ ወላጆችና በተሰቦችም መፅናናቱን እንዲሠጣቸውና ህክምና በመከታተል ላይ ያሉ ተማሪዎችም በቶሎ እንዲያገግሙ እንመኛለን፡፡ በመቀጠል ከትናንት ወዲያም ሆነ ትናንት የነበረውንና አሁን ተቋሙ ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ መረጀዎችን ለመስጠት እንወዳለን ፡፡ 11112 ህዳር 1 2012 ዓምወልድያ ዩኒቨርሲቲ ### Response:
### Text: ደብረብርሃን ድጋፍ ይዘው መምጣት የሚፈልጉ ክልከላው አይመለከታቸውም ይህንን አውቀው ወደ ከተማው መምጣት ይችላሉ አቶ ደስታ አንዳርጌ በደብረ ብርሃን ከተማ የቀን እንቅስቃሴ ገደብ አስመልክቶ ተጨማሪ መልዕክት ከከተማው ከንቲባ ተላልፋል።የደብረ ብርሃን ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ደስታ አንዳርጌ የአሸባሪው ቡድን አባላት ከተፈናቃዮች ጋር ተመሳስለው ወደ ከተማው በመግባት የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በመንዛትም ሆነ በሌሎች መንገዶች የከተማውን ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዳያውኩ እንዲሁም ለተፈናቃዮችም ሆነ ለከተማው ህዝብ ደህንነት ሲባል ከህዳር 16 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ የቀን እንቅስቃሴ ማድረግ የሚችሉት የደብረብርሃን ከተማ መታወቂያ የያዙ ብቻ መሆን እንዳለባቸው የእንቅስቃሴ ገደብ ለመጣል ከተማ አስተዳደሩ ተገዷል ሲሉ አስታውሰዋል።ከንቲባው የእንቅስቃሴ ገደቡ ዓላማ ሰርጎ ገቦችን ለመቆጣጠር ታሳቢ ያደረገ ነው እንጂ ጤናማ እንቅስቃሴዎችን ለማገድ ታስቦ አለመሆኑን ሁሉም ሰው በውል እንዲረዳው ያስፈልጋል ብለዋል።በመሆኑም ከቀያቸው ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን ለመገኙ ወገኖች ከየትኛውም የሀገሪቱ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ድጋፍ ይዘው መምጣት የሚፈልጉ ሁሉ ክልከላው እንደማይመለከታቸው አውቀው ወደ ከተማው መምጣት እንደሚችሉ ከንቲባው አሳውቀዋል።መረጃው የደብርሃን ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ነው። ### Response:
### Text: ሰሞኑን በሲዳማ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እና ከተሞች በተከሰተው ግጭት ሀኪም ቤት ሳይደርሱ በየአካባቢው የተቀበሩትን ሳይጨምር 53 ሰዎች ሲሞቱ ሌሎች 54 ሰዎች ደግሞ መጎዳታቸውን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አረጋገጠ። በወቅቱ ከተከሰተው ግጭት ጋር በተያያዘም እስካሁን 935 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥራ ማዋሉን የሲዳማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።የመምሪያው ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር ዳኛው ደምሴ ዛሬ በተለይ ለጀርመን ራድዮ እንደገለፁት የግጭቱ መነሻ ሐምሌ 11 ቀን 2011ዓም በሐዋሳ ከተማ የሲዳማ ብሔር በክልል የመደራጀት ጥያቄን እናውጃለን የሚሉ ወጣቶች ከፀጥታ አካላት ጋር መጋጨታቸው ነው። በመቀጠልም ግጭቱ ሲዳማ ዞን ውስጥ ወደሚገኙት ሁላ፣ ይርጋዓለም፣ ማልጋ፣ ሞሮቾ እና አለታ ወንዶ ወረዳ እና ከተሞች መዛመቱን ተናግረዋል። በተጠቀሱት ከተሞች እና ወረዳዎች ከሞቱት እና ከቆሰሉት ወገኖች በጠጨማሪ የዱቄት ፋብሪካዎች እና የመዝናኛ ሎጆችን ጨምሮ በሚሊየን ብሮች የሚገመት ንብረት በቡድን ሲንቀሳቀሱ በነበሩት ወጣቶች መውደሙን እና መቃጠሉንም ዘርዝረዋል። በወጣቶቾ የተፈጸመው ድርጊት ከሲዳማ ባሕል እና ወግ ያፈነገጠ ብቻ ሳይሆን ከጥያቄው ጋር አይገናኝም ያሉት ምክትል ኮማንደሩ በአሁኑ ወቅትም ድርጊቱ በሲዳማ ማኅበረሰብ እና በየወረዳው በሚገኙ የሀገር ሽማግሌዎች እየተወገዘ እንደሚገኝም አመልክተዋል። ### Response:
### Text: በባሌ ሮቤ የሰላም ኮንፍረንስ በመካሄድ ላይ ነው በባሌ ሮቤ የአገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች፣ የሃይማኖት አባቶች የሮቤ ነዋሪዎች ከፌዴራልና ከክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ጋር የሰላም ኮንፍረንስ በማካሄድ ላይ ናቸው፡፡የገቢዎች ሚኒስቴር ወሮ አዳነች ሀቤቤ እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በምርዕሰ መስተዳዳር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ ዶር ግርማ አመንቴ መድረኩን የእየመሩ ነው፡፡ባሌ የምትታወቀው በሃይማኖትና በብሄር መቻቻል መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሯ ባሳለፍነው ሳምንት በሮቤ የተከሰተው ሁከት በፍፅም ይህንን ህዝብ የሚወክል ተግባር አይደለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡እንደዚህ አይነት ድርጊቶች ሰላማችንን እያወኩ በመሆናቸው አሰልችተውናል ያሉት ሚኒስትሯ መቼም ቢሆን የሃሳብ ልዩነት ሊፈጠር ይችላል ይሁንና ለችግሮች መፍትሄ የሚገኘው በመነጋገር እንጂ ልዩነትን በሃይል በማራመድ አይደለም ብለዋል።ሚኒስትሯ አክለውም የስልጣናችን ምንጭ የኦሮሞ ህዝብ እንደመሆኑ የዚህን ህዝብ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ነዋሪዎቹ የተለያዩ ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን አንስተው በመድረኩ ላይ ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑም ተገልጿል።ኮንፍረንሱ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት መጀመሩንም ከኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ### Response:
### Text: የሾፌሮችን እንቅስቃሴ ከስጋት ነጻ ለመድረግ ከኦሮሚያ ክልል ሃላፊዎች ጋር እየተነጋገርን ነው ኮማንደር ቢምረው አሰፋበአሽከርካሪዎች ላይ የሚደርሰውን ግድያ እና የንብረት ዘረፋ መንግስት ባለማስቆሙ ለስራቸው አስቸጋሪ እንደሆነባቸው በምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ከተማ የሚገኙ እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አሽከርካሪዎች ለወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ ተናግረዋል።በኦሮሚያ ክልል በተለይ ደግሞ አሊ ዶሮ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተደጋጋሚ በታጠቁ ሀይሎች በሾፌሮች ላይ ግድያና የንብረት ዘረፋ እየተፈጸመ መንግስት አልታደገንም ሲሉ ያለውን አስቸጋሪ ሁኔታ በምሬት አስረድተዋል።እነዚሁ ሾፌሮች እንደሚሉት መንግስት ባለበት ሀገር የስጋት ቦታዎችን ለይቶ መቆጣጠር ባለመቻሉ ከቀን ወደ ቀን በመንገዱ ለመንቀሳቀስ አሳሳቢ ሆኖብናል ብለዋል፡፡የደጀን ወረዳ ፖሊስ ጽቤት ሃላፊ ኮማንደር ቢምረው አሰፋ ስለጉዳዩ ተጠይቀው ምላብ ሰጥተዋል።ኮማንደሩ ችግሩ እንዳለ ገልጸው ዘላቂ መፍትሄ ለማጣትና የሾፌሮችን እንቅስቃሴ ከስጋት ነጻ ለመድረግ ከኦሮሚያ ክልል ሃላፊዎች ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ከተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበሩ አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች የመንገዱን የጸጥታ ስጋት በመፍራት ደጀን ከተማ ላይ እየተጉላሉ እንደሚገኙ የደጀን ወረዳ አሳውቋል። ### Response:
### Text: አሐዱ ባንክ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።ይህ አስመልክቶ ባንኩ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ 10 ሺህ በሚደርሱ ባለአክሲዮኖችንና በ564 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል እና በ702 ሚሊዮን በተፈረመ ካፒታል ተዋቅሯል ብለዋል።ሀላፊው እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓም የቅርንጫፎቹን ብዛት 50 እደሚያደርስም ተናግረዋል።ባንኩ ️ ከሚያቀርበው ብድር እስከ 15 በመቶ የሚሆውን ለስራ ፈጣሪዎች እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማቅረቡ ️ ከተለመደዉ በሰራተኛ ከታገዘ የቅርንጫፍ አገልግሎት በተጓዳኝ ደንበኞች በራሳቸዉ የዲጂታል አገልግሎት የሚያገኙበት የቅርንጫፍ ዉስጥ አገልግሎት አደረጃጀት ማመቻቸቱ ️ የገጠር የባንክ አገልግሎትን ለአርሶና አርብቶ አደሮች፣ የገበሬ ማህበራት ለማዳረስ መዘጋጅቱ ️ የውስጥ አሰራሩን ወረቀት አልባ ማድረጉ ️ ደንበኞች ካሉበትና ቦታ ሆነዉ ራሳቸዉን የባንኩ ደንበኛ ማድረግ የሚችሉበትን አሰራር ማምጣቱ ልዩ ያደርገዋል ተብሏል።ባንኩ ከሀምሌ 2 እስከ ሀምሌ 7 2014 የተለያዩ ማህበራዊ ግዴታዎች እንደሚያከናውን የገለፀ ሲሆን አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ በሚል ባንኩ በሚከፍታቸዉ ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍ እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸዉ ልጆች ዓመታዊ ወጪያቸዉን እንደሚሸፍን ገልጿል።ባንኩ በተጨማሪም አዲሱ መለያ ሎጎውንም በይፋ አስተዋውቋል። ### Response:
### Text: ምስራቅ ሀረርጌ️በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ቆላማ ወረዳዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች የተገዙት 318 የውሃ መሳቢያ ጀኔሬተር ፓምፖችን በመመዝበር ለግል ጥቅሙ ያዋለው ግለሰብ በ11 ዓመት ጽኑ እስራትና በ15 ሺህ ብር ተቀጣ ።የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የመንግሥት ኮሙኬሽን ጉዳዮች ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ስዩም ደገፋ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ግርማደረሰ ፍላቴ የተባለው ወንጀለኛ0 ቅጣቱ የተጣለው በድርቅ የተጎዱ አርሶ አደሮችን ለመታደግ0 በ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር የተገዙትን ፓምፖች ገቢ ባለማድረጉ ነው።የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰሞኑን በዋለው ችሎት0 ወንጀለኛው ድርጊቱን መፈጸሙ በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጡና ወንጀለኛው ባለመከላከሉ ቅጣቱም እንደወሰነበት ኃላፊው አስታውቀዋል።የኦሮሚያ ክልል ዋናው ኦዲተር መሥሪያ ቤት በዞኑ ግብርና ልማት ጽህፈት ቤት የንብረት ክፍል ሠራተኛ በነበረው ግለሰብ ባደረገው የሂሳብ ምርመራ ንብረቱ ለአርሶ አደሩ እንዳልደረሰ በምርመራ አረጋግጦበታል ብለዋል።ጉዳዩንም ለኦሮሚያ ክልልሥነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ማሳወቁን ገልጸዋል።ፓምፖቹ የኦሮሚያ ውሃ ቢሮ አርሶ አደሮቹ በመስኖ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆንባቸው የገዛቸው ነበሩ።ምሥራቅ ሐረርጌ በኦሮሚያም ሆነ በአገር ደረጃ የመስኖ ልማት በተሻለ ሁኔታ ከሚከናወንባቸው አካባቢዎች አንዱ ነው።ምንጭ ### Response:
### Text: የፍርድ ቤት ውሳኔ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ አቶጃዋር የክስ መዝገብ የተከሰሱ ሰዎች የሕክምና ጉዳይን በማስመልከት ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ይግባኝ ውድቅ በማድረግ ተከሳሾች በግል ሐኪም እንዲታከሙ ፈቀደ።ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት እነ አቶ ጃዋር መሐመድ በመረጡት የግል ሃኪም እና የግል ሕክምና ጣቢያ እንዲታከሙ መፍቀዱን በመቃወም ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ብሎ ነበር።ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቤቱታን ውድቅ አድርጓል።ነገር ግን ተከሳሾች በመረጡት ሃኪም የሕክምና አገልግሎት ማግኘት ያለባቸው በግል ሆስፒታል ሳይሆን ተከሳሾች ታስረው በሚገኙበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንዲሆን ትዕዛዝ መስጠቱን ከእነ አቶ ጃዋር ጠበቆች መካከል አቶ ሚኪያስ ቡልቻ ተናግረዋል።የዛሬው የጠፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ የላንድ ማርክ ሃኪሞች ተደራጅተው ተከሳሾች ባሉበት በመምጣት ሕክምና እንዲሰጣቸው ነው በማለት ጠበቃው አቶ ሚኪያስ ተናግረዋል።ጠበቃው እንደሚሉት ደንበኞቻቸው ሆስፒታል ተኝተው መታከም የሚያስፈልጋቸው ከሆነ፣ የሆስቲታል ማሸኖች ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ከሆነ እንዲሁም በጤና ባለሙያ የቅርብ ክትትል ቢያስፈልጋቸው በማረሚያ ቤት ሆነው መታከማቸው ይህን ስለማያሟላ አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤቱ መልሰው እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል። 0223 ### Response:
### Text: ከሰሞኑን የተለያዩ የውጭ ሀገራት ሚዲያዎች ተናበው ሚሰሩ በሚመስል መልኩ ኢትዮጵያን የተመለከተ በርካታ ዘገባዎችን አውጥተዋል።የሚዲያ ተቋማቱ ድርጊት ኢትዮጵያውያንን ክፉኛ አስቆጥቷል።ለአብነት በአራት ቀናት ብቻ ፣ ፣ አልጀዚራ ፣ ፍራንስ 24 ፣ አሶሼትድ ፕሬስ በድምሩ 72 ዜናዎችን በኢትዮጵያ ጉዳይ አውጥተዋል ይህን ቁጥራዊ መረጃ ያጋራው የቴክኖሎጂ ዘርፍ ላይ የሚሰራው ጋዜጠኛ ሰለሞን ካሳ ነውከ72ቱ ዜናዎች 21ዱን ፣ 13ቱን ፣ 11ዱን አልጀዚራ ፣ 19ኙን ፍራንስ 24 እና 8ቱን አሶሼትድ ፕሬስ ነው የሰሩት።አብዛኛዎቹ ዜናዎች ኢትዮጵያ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ለማሸበር የተሞከረበት ነው ከዚህ ባለፈም ኢትዮጵያን ለመበትን የሀሰት ትርክት እና የስነልቦና ጫናና አለመረጋጋት በህዝቡ ዘንድ ለመፍጠር ረጅም መንገድ የተሄደበት መሆኑ አመላካች እንደሆነ ያሳያል።የሚዲያዎቹ ድርጊት ከሙያዊ ስነምግባር ያፈነገጠና አድሏዊ የሆነ በሀገር ውስጥ ያለው ነዋሪ ምን መአት መጣ ብሎ እንዲጨነቅ እና እንዲሸበር ፣ አካባቢውን ቄየውን ለቆ እንዲሸሽ ለማድረግ የታለመበት ይመስል ነበር።የሚዲያዎቹ ድርጊት ያስቆጣቸው ነዋሪዎች ትላንት አዲስ አበባ ከተማ በነበረ ሰልፍ ላይ ሆን ተብሎ ህዝብ ለማሸበር እና ለማስደንገጥ የሚያደርጉትን ድርጊት እንዲያቆሙ እጃቸውን ከኢትዮጵያ ላይ እንዲሰበስቡ አሳስበዋል። ### Response:
### Text: አቶ ጌታቸው ከሀገር ወጡ️ይህ የአንጋፋው ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ዘገባ ነውሰበር ዜናከአዲስ አበባ ለአዋዜ የደረሰው ትኩስ ዜና። የቀድሞው ተፈሪ የብሄራዊ ስለላና ደህንነት ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ ከኢትዮጵያ ጠፍተው ሱዳን መግባታቸው በይፋ ተረጋገጠ ። አንድ ከፍተኛ ውስጥ አዋቂ ምንጭ ምሽቱን ለአዋዜ እንደተናገሩት ከሆነ ፌደራል መንግስቱ በህግ ይፈልጋቸው የነበሩ ባለስልጣን ናቸው ጌታቸው አሰፋ።ማዕከላዊ መንግስቱ በይፋ በህግ ሊጠይቃቸው እና ሊፋረዳቸው የሚፈልጋቸው ባለስልጣን ሆነው ሳሉ በትግራይ ፖሊስ ሽፋን ወደ ሱዳን እንዲወጡ አድርጓል ብለዋል ለአዋዜ። በዚህ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም።ጋዜጠኛ አለምነህ ጨምሮ እንደገለፀው ከሆነ እየተደረገ በሚገኘው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ አቶ ጌታቸው አሰፋ አልተገኙም። ይህም የሆነው ከሀገር በመውጣታቸው ነው ብሏል ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ።በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን እና ሬድዮ ከምንጮች አገኘሁት ባለው መረጃ እንዲህ ብሎ በሰበር ዜናው ዘግቧል️የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው የቀድሞ የደህንነት ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ ወደ ሱዳን መሸሻቸው ተነገረ።◾️ውድ የተከባራቹ የቻናላችን ቤተሰቦች ይህን ዜና እስካሁን ድረስ ከሌሎች የመንግስትም ሆነ የግል የሚዲያዎች ማረጋገጥ አልተቻለም። ### Response:
### Text: ማሳሰቢያውድ የአጠቃላይ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት የ10ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች ከግንቦት22242010 ዓም የኢትዮጵያ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት የ10ኛ ክፍል ፈተና ለ1200676 ተማሪዎች እንዲሁም ከግንቦት 27302010 ዓም የኢትዮጵያ ዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና የ12 ክፍል ፈተና 284312 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡የፈተናውን መሰጠት ተከትሎም ወደ እርማት ስራው በመግባት ከምንጊዜውም በፈጠነ መልኩ የ12ኛ ክፍል ውጤት በ24112010ዓም ይፋ የተደረገ ሲሆን አስከትሎም የ10ኛ ክፍልን ወደ ማረም ሂደት ውስጥ ተገብቷል፡፡እንደ 12ኛ ክፍሉ ሁሉ የ10ኛውም ፈተና ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ከጥቃቅን የዳታ ማጥራት ስራዎች በስተቀር በሰላም እየተጠናቀቀ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን፡፡ ከነሐሴ 25302010 ዓም ይለቀቃል ተብሎ ተደራሽ ተደርጎ የነበረውን መረጃ መሰረት በማድረግ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለያዩ አሉታዊ መረጃዎች በመሰራጨት ላይ መሆናቸውን በመረዳታችን ከላይ በተገለጸው አግባብ የፈተና እርማቱ በሰላም በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ እና በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ ውጤቱ ይፋ እንደሚሆን እየገለጽን በትዕግስት ትጠባበቁን ዘንድ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡የውጤቱን መለቀቅ አስመልክቶም ለተለያዩ ሚዲያዎች መግለጫ የምንሰጥ መሆኑን እናሳውቃለንመልካም ዕድል© ### Response:
### Text: ጎረቤታችን ሶማሊያ ነገ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ታካሂዳለች።ይህን ተከትሎ የሶማሊያ ፖሊስ ምርጫ እስኪጠናቀቅ በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ በጸጥታ ሥጋት ሳቢያ ከአስቸኳይ አገልግሎቶች ውጪ ሁሉንም ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች የሚያግድ የሰዓት ዕላፊ ተግባራዊ አድርጓል።የታወጀው ሰዓት እላፊ ከዛሬ ምሽት 3 ሰዓት እስከ ሰኞ ጧት ድረስ የሚቆይ ነው ተብሏል።ነገ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት የሚመርጠው የታችኛው እና የላይኛው ምክር ቤቶች በጋራ በሚሰጡት ድምጽ ነው። ጎሳን መሰረት ባደረገው በዚህ ለ6ኛ ጊዜ በሚካሄድ ቀጥተኛ ባልሆነ ምርጫ 39 እጩዎች ይወዳደራሉ። ስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ሞሐመድ አብዱላሂ መሐመድ ፍርማጆ ፣ የቀድሞዎቹን ፕሬዝዳንቶች ሸሪፍ ሼክ አህመድ እና ሀሰን ሼክ ሞሐመድን እንዲሁም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀሰን አሊ ኬህሬን ከእጩ ተወዳዳሪዎቹ መካከል ናቸው። የራስ ገዝዋ የፑንትላንድ ፕሬዝዳንት ሰዒድ አብዱላሂ ዳኒና የቀድሞ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፋውዛ ዩሱፍ አደንም ለፕሬዝዳንትነት ይወዳደራሉ። ፋውዛ ዩሱፍ አደን ብቸኛዋ ሴት ፕሬዝዳንታዊ እጩ ናቸው።የነገው ምርጫ ከአንድ ዓመት በላይ ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን በምርጫው አሸንፎ ስልጣን የሚይዘው ፕሬዝዳንት የሰርጎ ገቦች ጥቃትና ረሀብ ያስከትላል ተብሎ የሚያሰጋውን ድርቅ ጨምሮ በርካታ ፈተናዎች ተጋርጠውበታል።መረጃው የጀርመን ሬድዮ ጣቢያ ነው። ### Response:
### Text: አንድነት ፓርክ በየሳምንቱ ሰኞ ለጎብኝዎች ዝግ እንደሚሆን ተገለፀ በአንድነት ፓርክ ያሉ ቅርሶችንና፣ ንብረቶችን በተገቢው ሁኔታ ለመጠበቅ ሲባል ፓርኩ በሳምንት አንድ ቀን ሰኞ ለጎብኚዎች ዝግ እንደሚሆን ተገለፀ። በቤተ መንግስት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተሰራውን የአንድነትፓርክ ከመስከረም 2012 ዓም ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት መሆኑ ይታወሳል።ለአገልግሎት ክፍት ከሆነበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ከ20 እስከ 25 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎች ፓርኩን መጎብኘታቸውን ከአንድነት ፓርክ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። 40 ሄክታር ይዞታ ካለው የቤተመንግስት ቅጥር ግቢ ውስጥ 13 ሄክታር ላይ ያረፈው ፓርኩ ስድስት0የጎብኚ መዳረሻዎች አሉት።የተለያዩ አገር በቀል እጽዋትና እንስሳት፣ የነገስታቱ እልፍኞች ፣ ሙዚየምና ታሪክ ነጋሪ ክፍሎች ያሉት የአንድነት ፓርክ በሳምንት ለሰባት ቀናት ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት ወደ ስድስት ቀናት ዝቅ ማድረጉን ዛሬ አስታውቋል።የአንድነት ፓርክ ሥራ አስኪያጅ0ዶክተር ታምራት ኃይሌ ስለ ፓርኩ የስራ እንቅስቃሴና ያለበትን ደረጃ በሚመለከት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በፓርኩ ያሉ ቅርሶችንና፣ ንብረቶችን በተገቢው ሁኔታ ለመጠበቅ ሲባል ፓርኩ በሳምንት አንድ ጊዜ ሰኞ ለጎብኚዎች ዝግ ይሆናል። ፓርኩ ከማክሰኞ እስከ እሁድ ባሉ ቀናት ክፍት ሆኖ ጎብኚዎችን እንደሚያስተናግድ ተናግረዋል።ኢዜአ ### Response:
### Text: የታገቱት ተማሪዎች እስካሁን ድምጻቸው አልተሰማም ህዳር 2021 የታገቱበት ቀን። ህዳር 24 አምልጣ የወጣችው ተማሪ መታገታቸውን የተናገረችበት። ታህሳስ 27 የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በጋዜጣዊ መግለጫቸው የታገቱ ተማሪዎች እንዳሉ ቁጥራቸውም እስከ 4 እንደሚደርስ የገለፁበት ቀን። ጥር 2 የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬተርያት ኃላፊ ክቡር አቶ ንጉሱ ጥላሁን ስለታገቱት ተማሪዎች በሰጡት መግለጫ 21 ተማሪዎች መለቀቃቸውንና 6 ተማሪዎች ታግተው እንዳሉ የገለፁበት ቀን። ጥር 8 የኦሮሚያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ክቡር አቶ ጌታቸው ባልቻ ታግተው የተለቀቁት ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ተመልሰዋል ተማሪዎቹ ከእገታ ከተለቀቁ በኋላ ከወላጆቻቸው ጋር ያልተገናኙት በአካባቢው የስልክ ግንኙነት አገልግሎት ባለመኖሩ የተነሳ መሆኑን ገለጹበት ቀን።ይህ ሁሉ ሲሆን ተማሪዎቹ ከመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ውጪ ከቤተሰቦቻቸው ጋር አልተገናኙም ተለቀዋል ከተባለ በኃላም ምንም አይነት ማስረጃ ሊገኝ አልቻለም፡፡ ይህ ለምን እነደሚሆንና ቢያንስ የተማሪዎቹ መለቀቅ በግልፅ ታይቶ ነገሮችን ለማብረድ ምንም አልተሰራም፡፡ ይህ አስቸኳይ ፍትህ የሚፈልግ ጉዳይ ነው፡፡ ሁለት ወር ሊሞላቸው የተቃረቡት ለእኚህ ተማሪዎች ምንም አይነት ትኩረት ያለመሰጠቱ ጉዳይ አሳሳቢ ነው፡፡ ### Response:
### Text: ነሃሴ 242012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 783 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 53 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 4067 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 119 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 21 ከምዕራብ አርሲ 10 ከአሰላ ከተማ 10 ከቢሾፍቱ ከተማ 9 ከምዕራብ ሸዋ 8 ከጅማ ዞን 8 ከነቀምቴ ከተማ ይገኙበታል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 307 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 82 ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 35 ከጉባ ወረዳ 15 ከምዥጓከበሎ ጀጋንፎይ ወረዳ 9 ከማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ 9 ከባምቢስ ወረዳ 9 ከአሶሳ ወረዳ ይገኙበታል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 5641 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 91 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 33 ከሰወሎ ዞን 24 ከምስጎጃም ዞን 7 ከማዕጎንደር ዞን 6 ከደሴ ከተማ 5 ከሰሸዋ ዞን 4 ከጎንደር ከተማ ይገኙበታል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 164 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 17 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ሁሉም ከማህበረሰቡ ከተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው። በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 459 የላብራቶሪ ምርምራ የተደረገ ሲሆን 168 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ### Response:
### Text: የቀጠለየቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት 1 ትምህርት ቤት2 የህፃናት ማቆያ3 ክሊኒክ4 መኖሪያ ህንፃ ፓርኩ የሚያካትታቸው የኢንዱስትሪ ዓይነቶች ፓርኩ በዋናነት የሚያካትታቸው ኢንዱስትሪ አይነቶች የግብርና ምርትን በግብዓትነት የሚጠቀሙና የሚያቀነባብሩ፣ ምርታቸውን በጋራ ወይም በተናጠል ወደ ውጭ የሚልኩ፣ ለግብርናው ምርት መዘመን መሰረት የሚሆኑ፣ የተሻሻለ ቴክኖሎጅ የሚያስተዋውቁ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ አስተዋጽኦ ያላቸውና ሌሎችም ይገኙበታል። በፓርኩ እንዲለሙ የተፈቀዱ የኢንዱስትሪ ዓይነቶች1 የምግብ መጠጥና ፋርማሲቲዮካል፣2 የጥራጥሬና ቅባት እህል ውጤቶች ማቀነባባሪያ፣3 የአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበሪያ፣4 የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች በቡሬ ፓርክ የተገነቡ ዋና ዋና መሠረተ ልማቶች 1ደረጃውን የጠበቀ 13 ኪሜ ኮንክሪት አስፓልት መንገድ፣2 የውሃ መስመር፣ ዝርጋታ፣ ማከሚያና የውሃ ማከማቻ3 መካከለኛና አነስተኛ የመብራት መስመር ግንባታ4 የቴሌኮም መስመር5 የመረጃ ማዕከል6 የገበያ ማዕከል7 የስልጠና ማዕከል8 የእሳት አደጋ መከላከያ ማዕከል9 የፖሊስ ጣቢያ10 የጉምሩክና ጥበቃ ማዕከል11 4 ሞዴል የኢንዱስትሪ ሸዶች12 ሁለገብ የስፖርት ማዘውተሪያ ማዕከል እና ሌሎች ምንጭ የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ### Response:
### Text: ባቲ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በባቲ፣ ከሚሴና ሮቢት ከተሞች ብሔርን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው የትግራይ ተወላጆች ለቢቢሲ ተናግረዋል።ነዋሪዎች ብሄርን መሰረት ያደረገ ነው ባሉት ጥቃት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን እና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን አስታውቀዋል።ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ድጋፍ ሰልፍ ጋር ተያይዞ በደረሰው በዚህ ጥቃት ቤቶች መቃጠላቸውንንና ዝርፊያ መፈፀሙንም ጨምረው ገልፀዋል።ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች በደሴና በመቀሌ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን ሌሎች ወደ መቀሌ ከተማ እንደደሄዱ ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል።የአማራ ክልል መንግስት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በከተማዋ ውስጥ ግጭት መፈጠሩን ካረጋጋጡ በኋላ ፣የከተማዋን መረጋጋት ለመመለስ ብሎም የግጭቱን መንስኤ እና የጉዳት መጠን ለማጥናት በክልሉ የፀጥታ ቢሮ ሃላፊ የሚመራ ቡድን ወደ ከተማዋ ማምራቱን ተናግረዋል።በተጨማሪም በተጠቀሱት አካባቢዎች የደረሱትን ጥቃቶች ኮንነዋል።ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ግለሰብ ለቢቢሲ ጥቃቱ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የድጋፍ ሰልፍ ጋር ተያይዞ በትግራይ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ተናግሯል።የአካባቢው ማህበረሰብ ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን ገልፆ የጥቃቱን አድራሾች ማንነት እንደማያውቅ ጭምር ተናግሯል።© ### Response:
### Text: የህዳሴው ግድብ️በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የተለዩ ክፍተቶችን በማስተካከልበፈረንጆቹ 2022 እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ።በዛሬው ዕለት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ አስመልክቶ ውይይት እየተካሄደ ነው።ጥልቅ ጥናትና ምርምር ስራ ሳይከናወንለት ግንባታው በመጀመሩ ምክንያት ግንባታ ጊዜው ሊጓተት እንደቻለ የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።ታላቁ የኢትዮዽያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያስከተለው ጉዳት ሀገሪቷ በየዓመቱ 800 ሚሊየን ዶላር እንድታጣ አድርጓታል ተብሏል።የግንባታው ስራው በአሁን ወቅት የሚገኝበት ደራጀም በዛሬው ዕለት እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት ወቅት ይፋ ሆኗል።በዚህም በሳሊኒ ሲሰራ የነበረው የሲቪል ምህንድስናው ስራው 82 በመቶ ላይ የሚገኝ ሲሆን የኤሌክትሮ መካኒካል ስራው ደግሞ 25 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል በውይይቱ ወቅት።በአጠቃላይ የህዳሴ ግድብ ግንባታ 65 በመቶ መጠነቀቁ ተነግሯል። ከዚህ ባለፈ የግንባታው ፅህፈት ቤት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይልና ከውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስቴር የግንባታ ሂደቱን ለማፋጠን በትብብር እየሰሩ ይገኛሉ።የህዝባዊ ተሳትፎን ፣ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ባለው የሶስትዮሽ ግንኙነት እና የኃይል ሽያጭ ትስስር ላይ ትኩረት ባደረጉ አራት ጉዳዮች ላይ ውይይቱ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።ምንጭ ፋና ብሮድካስቲንግ ### Response:
### Text: በአዲሱ የትምህርት ሥርዓት የሚሰጡ ኮርሶች ተለዩ በአዲሱ ትምህርት ሥርዓት ይቀራልበአዲሱ የትምህርት ሥርዓት ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የመጀመሪያ ዓመት የሚሰጡ 18 የትምህርት ዓይነቶች ኮርሶች ተለዩ፡፡ በአዲሱ ትምህር ስርዓት ወይንም ኤፍ የሚባል ውጤት መፋቅ ይቀራል ተብሏል፡፡የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር ኤባ ሚጀና የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ፣ ኮርስ ካታሎግ፣ የምዘና ሥርዓትና የሙያ መስክ ፕሮግራም ድልደላ አስመልክቶ እስካሁን ያለውን ተሞክሮ እና ቀጣይ አቅጣጫ አስመልክቶ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ ሊተገበር በታሰበው የትምህር ሥርዓት ለሁሉም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሚሰጡ 18 ኮርሶች መለየታቸውን አስገንዝበዋል፡፡ቀደም ሲል በነበረው አካሄድ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያሰለጥኗቸው ተማሪዎችም ዓለም አፋዊ ሁኔታዎችን የመረዳት ነገሮችን በብቃት የመተንተንና የመተንበይ አቅም ውስነት በመኖሩ ከፍተኛ ትምህርት በተቋማት ምክረ ሃሳቦች ላይ ተመስርቶ ለመፍትሄ እየተሰራ መሆኑን አስንዝበዋል፡፡የሥርዓተ ትምህርት ጥራት ማጣት ለሥራ አጥነት መንገድ ከፍቷል ያሉት ዶክተር ኤባ ያለጥናት ትምህርት ክፍሎችን መክፈት፣ ተከታታይ ምዘና አለመኖር በተግባር የተደገፈ ትምህርት አለመኖር በዋናነት ለትምህርት ሥርዓቱ ውጤታማ አለመሆን የተጠቀሱ ዋነኛ ችግሮች ናቸው ተብሏል፡፡ ### Response:
### Text: በአፋር ክልል ፣ አብአላ ከተማ በሚሰነዘር የከባድ መሳሪያ ድብደባ የከተማው ነዋሪ ከቄዬው እየተሰደደ መሆኑን የከተማው ከንቲባ ተናገሩ።ከንቲባው ይህን የተገሩት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ነው።ከመቐለ ከተማ 40 ኪሜ ርቀት ላይ የምትገኘው የአፋር የንግድ ከተማ አብአላ ከንቲባ አቶ ጣሂር ሀሰን ህወሓት ተቆጣጥሯቸው ከነበሩት የአፋር እና አማራ ክልሎች እንዲወጣ ከተደረገ በኃላ አብአላ ላይ ተደጋጋሚ ጉዳት ደርሷል ብለዋል።የከተማው ከንቲባ አሁንም ድረስ አላቋረጠም ንፁሃን መደብደብ በከባድ መሳሪያ መደብደብ እንስካሁን አላቆመም። በእግረኛም ወረራ እየሞከረ ነው። መጀመሪያውንም እንደሚታወቀው በየአካባቢው የሚያደርገውን ወረራ እና የንፁሃን ጭፍጨፋ ሙከራ ነው ያደረገው ያኔም አልተሳካለትም እስካሁን አላቋረጠም። በከባድ መሳሪያ ንፁሃንን እየደበደበ ነው በእግረኛም እየሞከረ ነው ዘረፋ ለማድረግም እየሞከረ ነው ቢሆንም ግን አልተሳካለትም። ወደላይ ተመልሷል እስካሁን ግን የቆመ ነገር የለም ከከተማው ራቅ ብሎ ከባድ መሳሪያ እየተኮሰ ነው ብለዋል።እየተፈፀመ በሚገኘው ጥቃት ከንፁሃን በተጨማሪ የአምልኮ ቦታዎች ፣ የመንግስት እና የግል ባለሀብቶች ንብረት ላይ ጉዳት መደረሱ ተገልጿል።የደረሰውን ጉዳት በቁጥር ደረጃ ለመግለፅ ጥናት እየተደረገ መሆኑን የአብአላ ከንቲባ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል። ### Response:
### Text: የ12ኛ ክፍል ፈተና ወረቀት እስከ አርብ ድረስ ተጓጉዞ ይጠናቀቃል።የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ከየካቲት 29 ቀን 2013 ጀምሮ የሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወረቀት በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እስከ መጪዉ አርብ የካቲት 26 ቀን 2013 ዓም ድረስ ተጓጉዞ እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ።የፈተናዎች ኤጀንሲ ከኢትዮጲያ አየር መንገድ ጋር ባደረገዉ ስምምነት መሰረት ፈተናዎቹ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች እየተጓጓዙ መሆናቸዉን የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር ዶር ዲላሞ ቱሬ ተናግረዋል፡፡ በጥብቅ ቁጥጥር በሀገር መከላከያ ሰራዊት እና በፌደራል ፖሊስ አጃቢነት በተቀመጠዉ አቅጣጫ እና የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እየተጓጓዘ ነዉ ብለዋል፡፡አያይዘዉም ፈተናዎቹ ወደ ክልል ከተሞች ሲደርሱ የየክልሎቹ ፖሊስ እና ልዩ ሀይል ጥብቅ ቁጥጥር እና እጀባ አድርገዉ ወደ ዞኖች እንደሚያደርሱም ተናግረዋል፡፡እስካሁን እየተደረገ ያለዉ የማጓጓዝ ሂደትም ሰላማዊ ነዉ ምንም አይነት ችግር አልገጠመም ሲሉ ተናግረዋል፡፡የጸጥታ ስጋት አለባቸዉ የተባሉ ቦታዎች ላይም ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ በመከላካያ ሰራዊት እና በፌደራል ፖሊስ ታጅቦ እንደሚጓጓዝ ገልጸዋል፡፡ በመላዉ ሀገሪቱ ፈተናዉ እስከ መጪዉ አርብ የካቲት 26 ቀን 2013 ዓም ተጓጉዞ እንደሚጠናቀቅ ዶክትር ዲላሞ ማረጋገጣቸውን አሃዱ ሬድዮ ጣቢያ 943 ዘግቧል። ### Response:
### Text: ልዩ ሎተሪ ወጣበጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የልዩ ሎተሪ ህዳር 282011 ዓም በብሔራዊ ሎተሪ ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል።1ኛ 7000000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 12993262ኛ 3000000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር13866793ኛ 2000000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 05554544ኛ 1000000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 06915665ኛ 500000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 08701766ኛ 200000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 07481867ኛ 100000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 12799758ኛ 16 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር201209ኛ16 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር4577910ኛ150 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 400 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 029911ኛ 150 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 200 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር136312ኛ 1600 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 61613ኛ 1600 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 80 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር96514ኛ 16000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር2815ኛ 160000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 40 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 1አስተዳደሩ ለደረሳቸው ዕድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ እያለ ዜናውን ለጓደኞቻችሁ በማጋራት በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ አድርጉ፡፡ እናመሰግናለንየብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ### Response:
### Text: ዘጠኝ አመታትን ያስቆጠረው ካለፉት አመታት በተጠናከርረ ሁኔታ እንደገና ተመልሷል በትልልቅ የኢትዮጲያን በአል ላይ በአዲስ አመት፣በገና እና ፋሲካ የሚደረገው ወጣት በጎ ፍቃደኞችን በማስተባበር ከ 1000 በላይ ለሆኑ ጎዳና ተዳዳሪ ልጆች ፣ ወጣቶች እና አዛውንቶችን ተደራሽ ያደረገ ነውይሄ መልካም ተግባር በዋናነት የበአሉ እለት የምሳ ፕሮግራም በማድረግ በበአሉ ቀን ምንም ሳይሰማቸው ደስተኛ ሆነው እንደማንኛውም የኢትዮጲያ ህብረተሰብ በአሉን እያከበርን እንድንውል እና ከዛም በተጨማሪ የልብስ ድጋፍ ምናረግላቸው ይሆናል እኛም ይሄን ሃላፊነት ስንወስድ በጣም በደስታ በመሄኑ እናንተም በዚሁ መልካም ስራ ላይ እንድትሳተፉ ስንል በአክብሮት እንጠይቃለንእንዴት መርዳት እንችላለንያገለገሉ ፣ ያጠርዎት ወይም በዚህ ሰአት የማይለብሱት ልብስ ለነሱ በጣም ይጠቅማል እና እነዚህን ልብሶች ከ እርስዎ ፣ ከ ቤተሰብ፣ ከ ጓደኛዎት፣ ከ ጎረቤት ፣ ከስራ ቦታ እና ከመሳሰሉት በመሰብሰብ እና ለኛ በመስጠት በአሉን በጣም ደስተኛ ሆነው እንዲውሉ እናርጋቸው እናም እነዚህን ድጋፍ ለማድረግ ያሰበ ማንኛውንም ሰው ለመቀበል ደስተኛ ሆነን እየጠበቅንዎት ስለሆነ እና ሌላ ጥያቄ እና አስተያየቶች ካላቹ ከዚህ በታች ባሉት ስልቅ ቁጥሮች ይደውሉልን እና ያነጋግሩን ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን 251922175164 251923594536 251 92 453 9140 ### Response:
### Text: የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ዘውዱ እምሩ የተናገሩትሙሉ በሙሉ የታገዱት አራት ተማሪዎችን ጨምሮ ትምህርት እንዲስተጓጎል ያደረጉ 21 ተማሪዎች ከአንድ ዓመት እገዳ ጀምሮ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።ሌሎች ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን አካላትም በመለየትና በማጣራት በቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ይወሰዳል።የዩኒቨርስቲ ምሁራን ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን ተማሪዎችን በስነ ምግባር በማነጽ ችግር ፈቺ ሆነው እንዲወጡ ማድረግ ይገባቸዋል።ባለፉት ሳምንታት ተማሪዎች በሚያነሷቸው ጥያቄዎች ዙሪያ ተደጋጋሚ ውይይትና ምክክር ቢደረግም ምክንያታዊ ባልሆነ መንገድ በፖሊ ፣ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፣ ፔዳና ይባብ ካምፓሶች ትምህርት ተቋርጦ ነበር።ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ትምህርት ያልተቋረጠበት ነው ፋሽንና ዲዛይን እንዲሁም ግብርና ኮሌጅ በከፊል የተቋረጠባቸው ነበሩ።በውጫዊ ምክንያት ጊቢ ለቀው የወጡ ተማሪዎችም ከጥር 5 እስከ 72012 እንዲመዘገቡ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በወሰነው መሰረት ተመልሰው ወደ መማር ማስተማር ገብተዋል። ካለፈው ማከሰኞ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የማስተማር ስራው ቀጥሏል።ትምህርት ተቋርጦ በነበረበት ወቅት የባከነውን ጊዜ ለማካካስ መምህራን ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በትርፍ ሰዓታቸው እንዲያስተምሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ### Response:
### Text: ችሎት እነ አቶ ስብሃት ነጋ ጉዳያችን በትግራይ ክልል ፍርድ ቤት ይታይልን ሲሉ አቤቱታ አቀረቡ፡፡ይህን አቤቱታ ያቀረቡት ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት አራዳ ምድብ ችሎት ነው።የጠቅላይ አቃቤ ህግ ቡድን በበኩላቸው የፌዴራል መንግስትን ስልጣን ለመጣል በሚል የሽብር አዋጁን በመተላለፍ በመላው ሀገሪቱ የተፈጸመ ወንጀል መሆኑን በመጥቀስ ተጠርጣሪዎቹ መቀሌ ሆነው በሰጡት ትዕዛዝ ባህርዳር እና ጎንደርን በሮኬት ማስደብደባቸው አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።በተጨማሪም ተከሳሾቹ ስልጣን ተከፋፍለው በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸመ ወንጀል ነው ያለው0አቃቤ ህግ0ዶክተር አዲስ አለም0ባሌማ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ሆነው አዲስ አባባ ቁጭ ብለው ሲፈጽሙ የነበረው ወንጀል አንድ ቦታ አለመሆኑን ማመላከቻ ነው ብሏል በምላሹ።ይህ የሚያሳየው በሃገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች መፈጸማቸውን ስለሆነ በአካባቢ ስልጣን ሳይገደብ ጉዳያቸው መታየት ያለበት በፌዴራል ፍርድ ቤት ነው ሲል በጠበቆቻቸው ያነሱት መከራከሪያ ውድቅ እንዲደረግ ጠይቋል።ፍርድቤቱ ምርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለመጋቢት 17 ቀን 2013 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።ችሎቱ አቶ ስብሃት በግል ሃኪም እንዲታከሙ የታዘዘው ትዕዛዝ ተፈጻሚ እንዲሆን አዟል።አምባሳደር አባይ ወልዱ ለዐይናቸው ህመም በግል እንዲታከሙ ያቀረቡት አቤቱታን ተቀብሎ ትዕዛዝ ሰጥቷል። 0323 ### Response:
### Text: የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት በአፋር ክልል ውስጥ እየተስፋፋ የመጣውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በጋራ እንዲከላከል ጥሪ ቀረበ።የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በክልሉ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ለማሟላት በከፍተኛ የውጭ ማንዛሬ በማስገባት የማስፋፊያ የመልሶ ግንባታ እና አዳዲስ ከተሞች ላይ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ በማከናወን የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን በማስፋት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።ነገር ግን በአንዳድ የክልሉ ከተሞች በተለይም በአይሳኢታ እና ዱብቲ ከስኳር ፋብሪካው ጋር የተመሰረቱ መንደሮች እንዲሁም ለውሃ አግልግሎት የሚሰጡ ትራንስፈርመሮች እና የኤሌክትሪክ ሽቦና መለዋወጫ ላይ አሁን ባለው ዋጋ 39 ሚሊዮን ብር በላይ ስርቆት ተፈፅሟል።ተቋሙ ጉዳዩ በህግ ክትትል እየተደረገበት እንደሆነ የጠቆመ ሲሆን የችግሩን አሳሳቢነትም በመረዳት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚገዙና ከፍተኛ የህዝብ ሃብት የፈሰሰባቸው በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ እንደራሱ ንብርት ጥበቃ ሊያደርግላቸው ይገባል ብሏል።ህብረተሰቡ በየአካባቢው የኤሌክትሪክ የመሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ግለሰቦችን በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ አልያም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በስልክ ቁጥር 0913834455 ላይ ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል። ### Response:
### Text: ወለጋ ዩኒቨርሲቲ️የወለጋ ዩኒቨርሲቲ በፀጥታ ችግር የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ የእረፍት ቀናት ጨምሮ እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡በጸጥታ ችግር ምክንያት የባከነ የትምህርት ጊዜን በማካካስ የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት በስኬት ለማጠናቀቅ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራን ለኢዜአ ገልጸዋል።አሁን አንጻራዊ ሰላም በመስፈኑ ተቋሙ ያመቻቸላቸውን የትምህርት ማራዘሚያ ጊዜ በመጠቀም የባከነውን ጊዜ ለማካካስ ከመምህራን ጋር እየሰሩ እንደሚገኙ ተማሪዎች ገልጸዋል።የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ዘላለም አብዲሳ በበኩላቸው በምዕራቡ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው የጸጥታ ችግር ለተወሰነ ጊዜ የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ የሁለት ሳምንት ማራዘሚያ ተደርጓል።በእረፍት ቀናትም ጭምር የማካካሻ ትምህርቱ እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።በተለይ ለሴት ተማሪዎች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት መዘጋጀቱን የገለፁት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ስራን ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።በ1999 ዓም 851 ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የጀመረው የወለጋ ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት በመደበኛና ተከታታይ የትምህርት መርሀ ግብር በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ 38 ሺህ ተማሪዎች በማስተማር ላይ መሆኑ ታውቋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: የጥላቻንግግር የጀርመን ባለስልጣናት የማህበራዊ ትስስር ድረ ገጽ የሆነው ፌስቡክ የሀገሪቱን የጥላቻ ንግግር ህግ በመጣሱ በ2 ነጥብ 3 ሚሊየን የአሜሪካ እንዲቀጣ ውሳኔ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል።ባለስልጣናቱ በፌስቡክ ላይ ቅጣቱን በትናንትናው እለት ያሳለፉ ሲሆን ቅጣቱ የተላለፈውም ህጉን የጣሱ ይዘቶችን በፌስቡክ ገፅ ላይ ሲሰራጩ ምንም አይነት የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ ነው ተብሏል። የጀርመን የፌደራል ፍትህ ቢሮ ባወጣው መግለጫ ፌስቡክ የጥላቻ ንግግር ህግ የጣሱ ይዘቶች እና ህዝቡን የሚረብሹ ምስሎች ሲለቀቁ እርምጃ ባለመውሰዱ ውሳኔው እንደተላለፈበት አስታውቋል።ፌስቡክ ህገ ወጥ የተባሉ ይዘቶች ላይ የወሰደውን እርምጃም ግልጽ አድርጎ በሪፖርት እንዳላቀረበም ነው ቢሮው ያስታወቀው። በጀርመን ህግ መሰረት ፌስቡክን ጨምሮ ሁሉም የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፆች በበድረ ገፆቻቸው ላይ የሚያጋጥሙ ህገ ወጥ ይዘቶች ላይ የሚወስዷቸውን እርምጃዎች በየስድስት ወሩ በሪፖርት ማሳወቅ እንዳለባቸው ተደንግጓል።ፌስቡክን ለቅጣት ከዳረጉት ምክንያቶች ውስጥም አንዱ የተሟላ ሪፖርት አለማቅረቡ አንደሆነም ነው እየተነገረ ያለው። የፌስቡክ ኩባንያ ግን በተላለፈበት የቅጣት ውሳኔ ላይ እስካሁን ምላሽ እንዳልሰጠ እና የይግባኝም አንዳልጠየቀ ነው መረጃዎች የሚያመላክቱት።ምንጭ0 ቀን ሰኔ 262011 ዓም ### Response:
### Text: ነገ በኢትዮጵያአዲስ አበባ ምን አለ በነገው ዕለት ብሔራዊ ክብር በሕብር በሚል የውጭ ጣልቃ ገብነትን በመቃወም በያሉበት ሆነው ጽምጻቸውን የሚያሰሙበት መርሃግብር ይካሄዳል ተብሏል።ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ሃገራትን ጣልቃ ገብነት በመቃወም እጃችሁን ከኢትዮጵያ ላይ አንሱ በሚል መሪ ሐሳብ በያሉበት ሆነው ለአንድ ሰዓት መልዕክታቸውን የሚያስተላልፉበት መርሃግብር ነው።ማነው ያዘገጀው መርሃግብሩ ያዘጋጁት ከማህበረሰብ አንቂዎች፣ አርቲስቶች፣ ሲቪክ ማህበራትና ታዋቂ ግለሰቦች የተወጣጡ ናቸው ተብሏል።መርሀግብሩ ምን መልክ አለው ከቀኑ 10 እስከ 11 ሰዓት ድረስ የሚቆይ ከኢትዮጵያ እጃችሁን አንሱ በሚል መሪ ሐሳብ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በያሉበት ሆነው ድምጻቸውን ያሰማሉ ነው የተባለው።መርሃግብሩ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ሃገራትን ጣልቃ ገብነት በመቃወም አጋርነታቸውን ለማሳየት ተዘጋጅተዋል ተብሏል።ዜጎች የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመጠቀም እንዲሁም በአደባባይ በመውጣት መልዕክታቸውን ማስተላለፍ ይችላሉ ተብሏል።ነገ ማለዳ ከታዋቂ ግለሰቦች እና አርቲስቶች የተውጣጡ ግለሰቦች በአዲስ አበባ በሚገኙ ኤምባሲዎች በመሄድ የተዘጋጁ ደብዳቤዎችን እንደሚያስገቡ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: የዋጋ ንረቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ የኑሮ ውድነቱ ከፍ እያለ የሰዎችን ኑሮ በእጅግ እየተፈታተነው ነው።በተለይ ዝቅተኛ ደሞዝ የሚያገኘ ሰራተኞች ኑሮ ለመግፋት ፈተና እየሆነባቸው ነው በየዕለቱ ሚጨምረው የዋጋ ንረት የኑሮውን ጫና መቋቋም ከማይቻልበት ደረጃ እየደረሰ ነው።ቤት ኪራይ፣ ምግብ የልጆች ትቤት ክፍያ፣ የቀን ወጪ ሌሎችም ወጪዎች ሲጨምሩ እንጂ ሲቀንሱ አይታይም የሚገኘው ደሞዝ እዛው ነው።ከቅርብ ጊዜ በኃላ ደግሞ በኢትዮጵያ ሰሜናዊው ክፍል የተፈጠረውን ጦርነት እንደመልካም አጋጣሚ የተጠቀሙ ነጋዴዎች በተለላያዩ ምርቶች ላይ ያለአንዳች ምክንያት ዋጋ በመጨመር ዜጎችን ክፉኛ እያማረሩ ነው።በተለያዩ ከተሞች ዋጋን በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ በመንግስት እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ሪፖርት የሚደረግ ቢሆንም አሁንም የሚቀረው ስራ ብዙ ነው።በሀገሪቱ ውስጥ የሚሰሩ ኢኮሮሚያዊ አሻጥሮች ፣ ሆን ተብሎ ዜጎች እንዲማረሩ ለማድረግ የሚደረገው ሸር ነገ ሳይሆን ዛሬ አስሸኳይ መፍትሄ የሚፈልግ ነው።የዋጋ ንረት እየፈጠሩ የዜጎችን ኑሮ የሚፈታተኑ ለሀገር ህልውና አደገኛ የሆኑ አካላት ላይ እርምጃ መውሰድ ካልተቻለ መዘዙ ከባድ ነው። ዜጎችም ነገ ኑሯቸውን የሚያከዱ ህገወጦችን ፣ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ለሚመለከተው አካል በመጠቆም ዜግነታዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል። ### Response:
### Text: ሀዋሳ ከተማ️ሀዋሳ ከተማ በዛሬው ዕለት ባለፉት 2 ወራት የተገነቡ ህገ ወጥ ቤቶች ላይ መንግስት እርምጃ ወስዷል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ህዝቡን ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ ለመውሰድ አንዳንድ አካላት በማህበራዊ ሚዲያዎች በመጠቀም ትክክል ያልሆነ መረጃ እያሰራጩ እንደሚገኝ ተደርሶበታል። ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ቤቶች ፈርሰዋል ወደ ተባለበት ቦታ ደውዬ ከአካባቢውን ነዋሪ ጋር ቆይታ አድርጌ ነበር ነዋሪው በሰጠኝ መረጃ ዛሬ የተወሰደው እርምጃ ምንም አይነት ብሄርን መሰረት ያደረገ እንዳልሆነ አስረግጦ ነግሮኛል። በፌስቡክ የሚወሩ ወሬዎችም ህዝብን ለማጋጨት የታሰበባቸው በመሆኑ የከተማው ህዝብ በአንድነት ሊያወግዘው ይገባል ብሏል። ነዋሪው እንደገለፀልኝ እውነት ህጋዊ ቤቶች ፈርሰው ከሆነ ለአስተዳደሩ ያሉትን ማስረጃዎች አቅርቦ መፍትሄ ማግኘት እየተቻለ የከተማው ሰላም ለማደፍረስ እና በሰላም እየኖረ ያለውን ህዝብ ለማጋጨት የሚሰራው ስራ ሊቆም ይገባል ሲል ገልፆልኛል። ከቀናት በፊት ዶክተር አብይ አህመድ በሰጡት መግለጫ ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት እና ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ መንግስታቸው ቁርጠኛ እንደሆነ ማሳወቃቸው አይዘነጋም።© ህገ ወጥ ቤቶች ፈርሰዋል በተባለበት ቦታ ነው የሚኖረው ተጨማሪ ከራሱ አንደበት መስማትም የምትፈልጉ ካላችሁ ስልኩን ሰጣችኋለሁ። ### Response:
### Text: በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ፍሬህይወት ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት ዛሬ ኅዳር 172012 ጠዋት ላይ 25 ተማሪዎች እና 5 አስተማሪዎች ላይ በተፈጠረው የጤና ዕክል ምክንያት ወደ ጥቁር አንበሳ እና ዘውዲቱ ሆስፒታሎች የተወሰዱ ተማሪዎች ከሁለት ተማሪዎች በስተቀር ቀሪዎቹ ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለሳቸውን የትምህርት ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር ፍርህይወት አዳል ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ አስታውቀዋል። የ5እና የ7ኛ ክፍል የሚማሩ በተማሪዎቹ እና በአስተማሪዎቹ ላይ የማሳል፣ ማስመለስ፣ ብርድብርድ የማለት እንዲሁም እራሳቸውን የመሳት ምልክት መታየቱን ገልጸዋል። በትምህርት ቤቱ በሚሰጠው የምግብ አገልግሎት 700 ተማሪዎች የሚመገቡ ሲሆን ነገር ግን 25 ተማሪዎች ብቻ መታመማቸው ታውቋል። የጤና ዕክል ካጋጠማቸው አንዱ የሆነው ተማሪ ፉአድ ለአዲስ ማለዳ እንደገለፀው ጠዋት ለቁርስ የተመገቡት ዳቦ በማር ሲሆን ከተመገቡ በኋላ ሕመም እንደጀመራቸው አስታውቋል በቦታው የተገኙት አዲስ አበባ ጤና ቢሮ ባለሞያዎች ተማሪዎች ጠዋት የተመገቡት ምግብ ለምርመራ ናሙና መውሰዳቸውን የገለፁ ሲሆን ምርመራው እንደተጠናቀቀ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። በአሁን ሰዓት ከኹለት ተማሪዎች ውጭ ሁሉም ተማሪዎች በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ በመገኘታቸው ለቤተሰቦቻቸው መመለሳቸውን ፍርህይወት አዳል ገልጸዋል።አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ### Response:
### Text: ዶር ደብረፅዮን ገሚካኤልለሀገራችን እና ለራሳችን ስለማይጠቅመን ብዙ ተሸክመን ነው ያለነው። ነገሮቹ ይቀየሩና ይስተካከላሉ ይሆናል በሚል። እኛ በክልላችን ብቻ አይደለም ሃላፊነት ወስደን እየሰራን ያለነው በሀገር ደረጃ ጉዳት እንዳይደርስ በሚል ተጠንቅቀን እየሰራን ነው የምንገኘው።እንደ ትግራይ የታገልነው ለእኩልነት ነው እንጂ በሀገር ላይ የበላይነት ለማግኘት አይደለም ወደዛም አልሄድንም። አሁን ላይ ግን በእኩልነት ላይ የተመሰረተው አንድነት የሚያፈርስ እና ህብረ ብሄራዊ የፌደራሊዝም ስርዓቱን የሚበትን ሁኔታ ተፈጥሯል። ፌደራሊዝም ፌደራሊዝም ይባላል እንጂ በማንነት ላይ የተመሰረተ አይደለም። በጂዮግራፊያዊ አከላለ እንጂ ይህም ማንነትን ለማጥፋት ነው። እኛ ደግሞ ለማንነታችን ነው የታገልነው። እንደዚህ አይነት አካሄድ ደግሞ ልንቀበለው አንችልም።እስካሁንም በኢህአዴግ ውስጥ የቆየ ነው እራሳችን ገንብተን እራሳችን ከምናፈርስው በሚል ብዙ ተሸክመን አልፈናል። ትክክለኛ ትግል ለማካሄድ ብለን ነው። አሁን ግን ድርጅቱን በትነውታል። ኢህአዴግን በመበተንም ሌላ አዲስ ፓርቲና ፕሮግራም ነው የመሰረቱት። የህዝባችን አስተሳሰብ ሳንቀይር ሰላማችንን ጠብቀናል። ሌሎች ስራዎቻችንም እየሰራን ነው። ይህ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ጉዳይ ነው። 1229 ቲክቫህኢትዮጵያ ከትግራይ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደራጅ ኮሚቴ ከአካባቢው ተወላጅ አመራሮች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሀዋሳ ውይይት እያካሄደ ነውበመድረኩ የክልሉን የምስረታ አፈጻጸም አስመልክቶ የተከናወኑ ተግባራትን ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ምክክር እየተደረገ ይገኛልአዲሱን ክልል በታለመለት ጊዜ አደራጅቶ ወደ ስራ ለማስገባት ልዩ ልዩ ግብረ ሀይል መቋቋሙ በመድረኩ ተገልጿልአዲስ የሚመሰረተው ክልል ከነባሩ ክልል ያለውን ሀብት አስመልክቶ የሀብት ክፍፍል ግብረ ሀይል መቋቋሙ ይፋ ሆኗልየህገ መንግስት እና ህግ ነክ ጉዳዮችን የሚያዘጋጅ፣ የመሰረታውያን ግብረ ሀይል ደግሞ ሰንደቅ አላማ ፣ የክልሉን አርማ፣ የክልሉን መዝሙር እና ተያያዥ ጉዳዮችን ይመለከታልየልማት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅ ግብረ ሀይል ደግሞ የአዲሱን ክልል ጸጋዎች በመጠቀም እና በማልማት በቀጣዮቹ 10 አመታት የልማት ተጠቃሚነትን የሚያጎለብቱ ስራዎችን የሚያቅድ እና የሚያስተባብር ግብረ ሀይል ነውበሌላ በኩል በማህበራዊ ትስስር ገጾች የአዲሱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ማዕከል አስመልክቶ የሚሰራጨው መረጃ ተአማኒነት የሌለው ነው ተብሏልማዕከልን አስመልክቶም ከስድስቱም መዋቅር የተውጣጡ አመራሮች እና የሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የሚወሰን መሆኑ በውይይት መድረኩ ላይ ተገልጿልመረጃው የደቡብ ክልል ኮሚኒኬሽን ነው ### Response:
### Text: አምነስቲኢንተርናሽናል የፕሪቶሪያ የ ሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ የ ኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ወሲባዊ ባርነት ፣ ግድያዎችን እና ሌሎች ከባድ ጥሰቶች መፈጸማቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አዲስ ባወጣው ሪፖርት ይፋ አድርጓል።ሪፖርቱ ምን ይላል ከሰላም ስምምነቱ በኃላ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ምድር ወሲባዊ ባርነት፣ ግድያ፣ ከባድ ጥሰቶችን ፈፅመዋል። የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት መድፈር፣ ሴቶችን ለወራት ለወሲባዊ ባርነት መዳረግ፣ የዘፈቀደ ግድያ፣ ዘረፋዎችን እየፈጸሙም እንደሆነ ተገልጿል። የተፈፀሙት ጥሰቶች የጦር ወንጀሎች እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል ሊሆን ይችላል። ሸዊቶ በተሰኘች ወረዳ ቢያንስ 20 ነዋሪዎች በዋነኝነት ወንዶች ከጥቅምት15 ጥቅምት 22 ቀን 2015 ዓም ድረስ ባለው ወቅት በኤርትራ መከላከያ ኃይል መገደላቸውን ገልጿል። የፕሪቶሪያው0 ስምምነት ከተፈረመ በኃላ የኤርትራ መከላከያ ኃይል ወታደሮች 24 ሰላማዊ ነዋሪዎችን በኮኮብ ጽባህ ወረዳ መግደላቸውን ሪፖርት ተደርጓል። አምነስቲ በኮከብ ጽባህ የተደፈሩ እና ለወሲባዊ ባርነት ተዳርገው የነበሩ 11 ሴቶችን0 አነጋግሯል። ከ40 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎችም እንደተደፈሩ እና ለወሲባዊ ባርነት እንደተዳረጉ ለአካባቢው ለሚገኝ የሲቪል ማህበረሰብ መናገራቸውም ሪፖርቱ ላይ ሰፍሯል።ሙሉ ሪፖርቱ በዚህ ይገኛል 202309 ### Response:
### Text: በጋምቤላ ክልል 52 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች እና 10 ኪሎ ግራም ሐሺሽ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በተጨማሪም ከአንድ ሺህ በላይ የብሬን መትረየስና ክላሽንኮቭ ጥይቶች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር ተይዘዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር እንደገለጹት የጦር መሳሪያዎቹና ሐሺሹ በቁጥጥር ሥር የዋለው ከሕዝብ በደረሰ ጥቆማና በኬላዎች በተደረገ ፍተሻ ነው። የጦር መሣሪዎቹና ሐሺሹን ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ሥር የዋሉት ከሚያዚያ 6 እስከ 9፣ 2011 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ መሆኑን ተናግረዋል። የጦር መሣሪዎቹ የተያዙት በባጃጅ ተሽከርካሪዎችና አዘዋዋሪዎች በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ሐሺሹ ከአዲስ አበባ በሕዝብ ማመላለሻ በመኪና ጎማ ውስጥ ተጭኖ ወደ ጋምቤላ ከተማ በመግባት ላይ እንደነበረም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ የሚናገሩት። በቁጥጥር ስር የዋሉት ሁለት ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው በመጣራት ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ክልሉ ከደቡብ ሱዳን ጋር ሰፊ የድንበር ወሰን ያለው ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እየተስፋፋ ያለውን ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ለመግታት ከሕዝብና ከፌደራል የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል።ምንጭ፡ ኢ ዜ አ ### Response:
### Text: የአፋር ክልል ተፈናቃዮች ከ250 ሺህ በልጠዋል።የአፋር ክልል ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አህመድ ካሎይታ ህወሓት በሁለት ዙር ባካሄደው ወረራ የኢትዮጵያ የወጪ እና ገቢ ንግድ የሚሳለጥበትን ሚሌን ለመያዛ እና ለመዝጋት አስቦ ነበር ያ ግን ሳይሳካ ቀርቷል አሁን ደግሞ በሶስተኛ ዙር ወራር በሰርዶ በኩል ያሰበውን ለማሳካት ተነስቷል ብለዋል።አቶ አህመድ ክልሉ ከዚህ ቀደም ቡድኑ ባካሄደው ወረራ የተፈናቀለውን ህዝብ ለማቋቋም እየተሰራ ባለበት ሁኔታ ዳግም ለሶስተኛ ዙር ወረራ ተፈፅሞብናል ብለዋል።አክለውም አሻባሪው የህወሓት ቡድን 150 ኪሎ ሜትር ድረስ ወደ አፋር ክልል ዘልቆ በመግባት ከዚህ ቀደም በአፋር እና አማራ ክልል የፈፀመውን አይነት ጭካኔ እየፈፀመ ነው ሲሉ ገልፀዋል።ህወሓት ወደአፋር ክልል 150 ኪሎ ሜትር ዘልቆ በመግባት ኤሬብቲ ወረዳ፣ መጋሌ እና አብአላን መቆጣጠሩ ተሰምቷል።አዲስ በተከፈተው ጥቃት ከቀደሞው በተጨማሪ ለሶስተኛ ጊዜ ከ250 ሺህ በላይ ህዝብ ከገዛ ቄየው ተፈናቅሎ መጠለያ ካምፕ ውስጥ እንደሚገኝ የአፋር ክልል ሪፖርት አድርጓል።ከዚህ ቀደም ከ400 ሺህ በላይ ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን እነሱን መልሶ በማደራጀት እና በማቋቋም ሂደት ውስጥ በተገባበት ሰዓት ነው ድጋሚ 250 ሺህ ሰዎች የተፈናቀሉት።የአፋር ክልል ለደረሰው ጉዳት የሁሉንም እገዛ እና ትብብር እንደሚያስፈልገው አሳውቋል። ### Response:
### Text: ፍትሕን በገንዘብ ያልሸጣት ምስጉን ዳኛበምእራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ከተማ አስተዳደር 01 ቀበሌ ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓም ከምሽቱ 140 ሰዓት ላይ አንዲት ህፃንን አስገድዶ በመድፈሩ ምክንያት ተከሳሽ ተይዞ ጉዳዩ በህግ ይታያል።በዚህን ጊዜ የተከሳሽ ወንድምና ጓደኛ መዝገቡን የሚያየውን ዳኛ በከተማው በሚገኝ ፅናት ሆቴል ይቀጥሩታል። ኃሳባቸውም ለዳኛው 10 ሺህ ብር ጉቦ በመስጠት ተከሳሽ ነጻ እንዲወጣ ማድረግ ነበር።ዳኛውም ቀጠሮዎን አክብሮ ከቦታው ይደርሳል የተከሳሹ ተባባሪዎችም ገንዘቡን አውጥተው ለዳኛው ሊሰጡት ሲሉ ዳኛዉ አስቀድሞ ለፖሊስ አሳውቆ ነበርና እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸዉ እንደሚገኝ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ያገኘነው መረጃ ያሳል።አንዳንድ ፍትሕን በገንዘብ የሚሸጡ፣ ያስተማራቸውን ያሳደጋቸውን ማህበረሰብ እና ሀገርን በገንዘብ የሚለውጡ የፍትህ አካላት እንዳሉ ሁሉ ከላይ መረጃውን እንዳነበብነው አይነት ምስጉን የፍትህ አካላት አሉ። ማህበረሰቡን እና ሀገርን በታማኝነት የሚያገለግሉ አካላት ሊመሰገኑ ይገባል።በእርግጥ ሁላችንም ባለበት ቦታ ኃላፊነታችንን መወጣት ታማኝነታችንን ማሳየት ፣ ለማህበረሰባችን ፣ ለሀገራችን የገባነውን ቃል ማክበር ግዴታችን እና የሚጠበቅብን ቢሆንም እንዲህ ያሉ የሚያስመሰግኑ ተግባራትን ማበረታታና ማመስገን ይገባል። ### Response:
### Text: ተጠርጣሪዎቹ በዋስ እዲወጡ ተፈቀደ️ፍርድ ቤቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በፈጸሙ ተጠርጣሪዎች ላይ በምስክርነት የቀረቡ ግለሰቦችን ፎቶ በማንሳት በማህበራዊ ድረ ገጽ ሲለጥፉ በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች የጠየቁትን የዋስትና ጥያቄ ተቀበለ። ተጠርጣሪዎቹ ሃጎስ ግርማይ እና ተወልደ ውበት የተባሉ ግለሰቦች ሲሆኑ በፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ለሁለተኛ ጊዜ ቀርበዋል።መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በምርመራ ላይ በሚገኙ ግለሰቦች ላይ ምስክርነት በመስጠት ፍርድ ቤት ቅድመ ምርመራ ላይ እያሉ ፎቷቸውን በማንሳት በማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ በመለጠፍ መጠርጠራቸውን ተከትሎ ሲያደርግ የቆየውን ምርመራ ማጠናቀቁን እና የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ማስረከቡን ለችሎቱ ገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ፍርድ ቤቱ ዋስትና እንዲፈቅድላቸው አመልክተዋል። ፍርድ ቤቱም የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና ጥያቄ በመቀበል በሁለት ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ፈቅዷል። በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በምርመራ ላይ ከሚገኙትና ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ተጠርጣሪዎች ውጭ ከ16 በላይ መርማሪ ፖሊሶችና የማረሚያ ቤት አስተዳደር ሰራተኞች የመብትጥሰት ወንጀል ተጠርጣሪ ግለሰቦች ላይ ክስ መመስረቱ ይታወሳል። ### Response:
### Text: የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ላቀረባቸው ጥያቄዎች ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ ከኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድሮቸ ራሱን ማግለሉን አስታወቀ፡፡የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ኮሚቴ የቅዱስ ጊዮርጊስን የሜዳ ተጠቃሚነት ለማሳጣት ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር ሊያደርገው የነበረን ጨዋታ በዝግ ወይም አዳማ0ተጫወቱ በማለት ሁለት ጊዜ እንዲቋረጥ አድርጎል ብሏል፡፡ይህን ጨዋታ ከዚህ በፊት የተቋረጡ የሌሎች ክለቦች ጨዋታወችን ባስተናገደበት ሁኔታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን አላስተናገደም ሲል በፌዴሬሽኑ ላይ ቅሬታውን አቅርቧል፡፡እንዲሁም በ29ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ለፋሲል ከነማ የተሰጠው ፎርፌ አግባብነት የሌለውና አድሏዊ መሆኑንም ነው በመግለጫው ያመላከተው፡፡አዲስ ከመጡት የፌዴሬሽኑ አመራሮች ጋር በመተባበር፣ በመቻቻል እና በመተጋገዝ ለመስራት የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር የበኩሉን ድርሻ ሲወጣ ቆይቷልም ነው ያለው፡፡በመሆኑም ፌዴሬሽኑ የወሰናቸውን ኢ ፍትሃዊ እርምጃዎችን እንዲመረምር እና ያላአግባብ የተወሰነበትን ፎርፌ እንዲያነሳ የጠየቀ ሲሆን ያቀረባቸው ቅሬታዎች ምላሽ እስከሚያገኙ ከኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድሮች ራሱን ማግለሉን አስታውቋል፡፡ ቀን ሰኔ 282011 ዓም ### Response:
### Text: የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ህግ የማሻሻያ ስራ ተጠናቆ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ተመርቷል ከ50 ዓመት በላይ በስራ ላይ የቆየው የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ህግ የማስረጃ ጉዳዮችን እንዲያካትት እና በ1996 ዓም ከወጣው የወንጀል ህግ ጋር ስያሜው እንዲጣጣም ተደርጎ ሲሻሻል የነበረው ረቂቅ ተጠናቆ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን በኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የህግ ጥናት ማርቀቅና ማስረጽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በላይሁን ይርጋ ገልፀዋል፡፡አቶ በላይሁን አያይዘውም ረቂቁ «የወንጀል ሕግ ስነስርዓትና የማስረጃ ህግ» የሚል ስያሜ ተሰጥቶት በ444 አንቀጾች ተቀርጾና በርካታ ከዘመኑ ጋር የሚሄዱ አዳዲስ ጽንሰ ሃሳቦች ተካተውበት እንዲሁም የነበሩት ድንጋጌዎች አሁን ካለው የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርዓት ጋር አብረው እንዲሄዱ ተደርገው መሻሻላቸውን ተናግረዋል፡፡አሁን በስራ ላይ ያለው የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ህግ ከወጣ በኋላ በተለያዩ አዋጆች ላይ የወጡ የማስረጃ እና የስነስርዓት ድንጋጌዎች ተለቅመው አሁን በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ እንዲካተቱ የተደረገ ሲሆን ይህም የማስረጃና ወንጀል ህግ ስነስርዓት ድንጋጌዎች በአንድ ህግ ላይ ተሰባስበው እንዲገኙ የሚያስችል በመሆኑ ለአፈጻጸም ቀላል፣ ተደራሽና ምቹ እንደሚያደርገው ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ምንጭ፡ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ### Response:
### Text: ወፍሪ ሓርነትበመንግስት በኩል እንዲለቀቁ ከተወሰነላቸው 14 የትግራይ የፖለቲካ እስረኞች ውስጥ እስካሁን የተለቀቁት 11 ብቻ መሆናቸውን ወፍሪ ሀርነት አስታወቀ።ወፍሪ ሀርነት በፖለቲካ አመለካከታቸው የታሰሩ የትግራይ አስረኞችን መብት ለማስከበር የተቋቋመ ኮሚቴ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያ ዛሬ ረፋድ በአዲስ አበባ መግለጫ ሰጥቷል።የመግለጫው ዋና ዋና ነጥቦች መንግስት የካቲት 16 ቀን 2012 ምሽት ላይ እንዲፈቱ ውሳኔ የተላለፈላቸው 14 ሲሆኑ የተለቀቁት 11 ብቻ ናቸው። የተፈቱትም ቢሆን በተንጠባጠበ መልኩ የተለቀቁ ናቸው። ይህ ሂደት ግልፅኝነት የጎደለው እና የታሳሪ ቤተሰቦችን ያሳቀቀ ተግባር ነው። መንግስት በወቅቱ ያወጣቸው በነበሩ መረጃዎች 60 ትግራዋይ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱ የሚያመላክት የነበረ ቢሆንም እንዲፈቱ ትዕዛዝ የተላለፈላቸው ግን 14 ብቻ ናቸው። መንግስት እንዲፈቱ ትዕዛዝ ካሳለፈላቸው 61 እስረኞች ውስጥም 3 ያልታሰሩ የነበሩ እንዲሁም ሁለቱ ከዚህ በፊት ታስረው ከተፈቱ አንድ ዓመት ያለፋቸው፣ ሰባቱ ደግሞ ጥቅምት ታስረው አሁን የተፈቱ ናቸው። ለውጥ ላይ ነን እየተባለ አሁንም ድረስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ትግራይ የፖለቲካ እስረኞች በፌደራል፣ በክልሎች እና በሌሎች ድብቅ እስር ቤቶች ላለፉት ሁለት ዓመታት ታስረዋል መንግስት እነዚህን እስረኞች ሊፈታ ይገባል።ምንጭ ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ### Response:
### Text: ችሎትበፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የፀረ ሽብር እና ሕገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት እነ አቶ እስክንድር ነጋ በጠየቁት የዋስትና መብት እና የዐቃቤ ሕግ ምላሽ ላይ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለመስከረም 12 ተለዋጭ ቀጠሮ ያዘ።አቶ እስክንድርን ጨምሮ 7 ሰዎች የእርስ በርስ ግጭት መቀስቀስ እና በሽብር ወንጀል በዚህ ችሎት ክስ እንደተመሰረተባቸው ይታወሳል።ይህን ተከትሎም በአካል ካልተገኙት 6ኛ እና 7ኛ ተከሳሾች በስተቀር ሌሎቹ አምስቱ ተከሳሾች በአካል በችሎት ተገኝተው ክሱ ተነቦላቸዋል።የክስ መነበብን ተከትሎ በአራት ጠበቆች የተወከሉት አምስቱ ተከሳሾች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ለፈርድ ቤቱ ጥያቄ አቅርበዋል።ዓቃቤ ሕግ በተለይ አቶ እስክንድር ነጋ በሽብር ወንጀል ተሳትፈዋል በሚል የተከሰሰ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ እስከ 25 ዓመት የሚያስቀጣ በመሆኑ እና ድርጊቱም የሰው ህይወት የጠፋበትና ከ187 ሚሊዮን ብር በላይ የወደመበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሌሎቹም ተከሳሾች በተመሳሳይ መልክ የተከሰሱበት ጉዳይ ዋስት መብት የሚያስከለክል በመሆኑ ሕጉን በመጥቀስ ሕጉ የዋስትና መብትን ይከለክላል በማለት ተቃውሞ አቅርቧል። ችሎቱ በዋስትና መብት ላይ የተነሳውን ክርክር የግራ ቀኙን መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠትና የመጀመሪያ የክስ መቃወሚያ ለመቀበል ለመስከከረም 12፣ 2013 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። ኢቲቪ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አህመድ ለሱዳን ጠሚ ዶር አብደላ ሃምዶክ ጥሪ ምላሽ ሰጥተዋል ጠሚ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ለሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር አብደላ ሃምዶክ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ ለጻፉት ደብዳቤ ምላሽ ሰጥተዋል።ኢትዮጵያም የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር እና ለዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሴኬዲ ከግድቡ ጋር በተያያዘ ባሉ መጓተቶች ላይ ስብሰባ እንዲጠራ ሃሳብ አቅርባለች፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እስካሁን በግድቡ ዙሪያ የተካሄደው ውይይት እንዳልተሳካ መቁጠር አግባብ አለመሆኑን ጠቅሰው ለዚህም እንደ የመርሆዎች ስምምነት መፈረም እና የብሔራዊ ገለልተኛ የሳይንስ ምርምር ቡድን መመስረትን በመልካም ማሳያነት አንስተዋል፡፡በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች ህጋዊና ቴክኒካዊ ተግዳሮቶች ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርጉ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ እንቅፋት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡የአፍሪካ ህብረት ለዘጠኝ ጊዜያት ያህል መስተጓጎል የገጠመውን የሦስትዮሽ ድርድር ዕውን እንዲሆን ያደረገው ጥረት አድነቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚካሄደው የሦስትዮሹ ድርድር አሁንም ቢሆን በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ሆኖ እንዲቀጥል ጽኑ ፍላጎትት እንዳላት በደብዳቤያቸው ስለመግለፃቸው ኤፍ ቢ ሲ አስነብቧል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባዔ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የግንቦት 192013 ክንውን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በመግለጫቸው ተከታዮቹ ነጥቦች ተነስተዋል በትናንትናው ዕለት ውሳኔ የሰጠባቸውን 2 አጀንዳዎች ቃለ ጉባዔ ቀርቧል፡፡ በዚህም የቅዱስነታቸውን የመክፈቻ ንግግር ቅዱስ ሲኖዶስ አጽድቆታል ፡፡ ሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክቶ በሀገሪቱ በሚታዩት ወቅታዊ ችግሮች የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ስደትና መፈናቀል ዙርያ በሰፊው ተወያይቶ የመፍትሔ ሐሳብ የያዘ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ውሳኔው በዝርዝር በሚሰጠው መግለጫ ይገለፃል ብለዋል። የቤተክርስቲያን የአምልኮ ሥፍራ የሆኑት የመስቀል እና የጥምቀት ቦታዎች አስመልክቶ ሰፊ ውይይት በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ችግሩ የሚፈታበት ውሳኔ አሳልፏል የውሳኔው ዝርዝር በአጠቃላይ መግለጫው ይቀርባል ብለዋል። በሀገሪቱ በተለያዩ ጊዜያት እደረሱ ያሉ ችግሮችን አስመልክቶ ሦስት ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ለቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ መርጧል፡፡ በመላው ሀገሪቱ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ባሉት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት በሙሉ ስለ ሀገሪቱ ሰላም ጸሎተ ምኅላ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ተጨማሪ ያንብቡ 0527 ### Response:
### Text: ያለ አግባብ እንግልት እየደረሰብን ነው የትግራይ ተወላጆችበአዲስ አበባ ከተማ ጎፋ መብራት ሃይል አካባቢ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ያለ አግባብ እንግልት እየደረሰብን ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡በጎፋ መብራት ሃይል የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች እንደተናገሩት በአካባቢው በሚደረጉ ፍተሻዎች በማንነታችን የትግራይ ተወላጆች በመሆናችን እየታሰርን እና ቤቶቻችን እየታሸጉ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።ቅሬታ አቅራቢዎቹ እንዳሉት ለፍተሻ የሚመጡ የፀጥታ አካላት ምንም አይነት የመፈተሸ ፍቃድ ሳይዙ በተመረጡ የትግራይ ቤቶች ላይ ፍተሻ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።በትግራይ ተወላጆች እየቀረበ ስላለው ቅሬታ የተጠየቁት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን የህዝብ ግንኙነት እና የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ስለተፈጠረው ችግር ግን እውቀቱ የለኝም ብለዋል፡፡የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ጀላን አብዲ ጉዳዩን እንደማያውቁት ተናግረዋል፡፡በኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር የወንጀል ክትትል እና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ መንግስቱ አበራ ደግሞ እስካሁን አዲስ የወረደ የአሰራር አቅጣጫም ሆነ የቀረበ ቅሬታ የለም ሀገሪቱ ካለችበት ወቅታዊ ችግር አንፃር የተለመደ ሰላም የማሰጠበቅ ስራ እየተሰራ ነው ሲሉ ተናግረዋል።መረጃው የአሐዱ ኤፍ ኤም 943 ሬድዮ ጣቢያ ነው። ### Response:
### Text: የነዳጅ ማዕቀብ ውጤቱ እጅግ የከፋ ይሆናል ዳፋውም ለዓለም ይተርፋል የሩስያ ምክትል ጠሚ አሌክሳንደር ኖቫክ አሜሪካ በ ሩሲያነዳጅ ላይ ማዕቀብ የመጣል ውሳኔ ካሳለፈች ሩሲያ ለአውሮጳ የምታቀብለውን የተፈጥሮ ጋዝ አቅርቦቷን እንደምታቋርጥ ዝታለች።የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒትር አሌክሳንደር ኖቫክ የሞስኮን ነዳጅ ማቀብ ውጤቱ እጅግ የከፋ ይሆናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ዳፋውም ለዓለም ይተርፋል ብለዋል፡፡ሚኒስትሩ በዚህ ማስጠንቀቂያቸው ሩሲያ ነዳጅ ላይ ማዕቀብ ከተጣለ ምናልባትም የአንድ ድፍድፍ በርሜል የነዳጅ ዋጋ አስከ 300 ዶላር ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡አሜሪካ በሩሲያ ነዳጅ ላይ ማዕቀብ ለመጣል አማራጮችን እያየች ነው።ጀርመንና ኔዘርላንድስ ግን በሩሲያ የነዳጅ አቅርቦት ላይ ማዕቀብ መጣል እኛኑ መልሶ ይጎዳናልና ይቅርብን እያሉ ይገኛሉ።አውሮጳ ኅብረት ኃይል አቅርቦቱ በአመዛኙ የሚያሟላው ከሩሲያ ነው፡፡ በአማካይ ካየነው የአውሮጳ ኅብረት 40 የተፈጥሮ ጋዝ አቅርቦቱን እና 30 የነዳጅ አቅርቦቱን የሚያገኘው ከሩሲያ ነው፡፡የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኖቫክ የአውሮጳ ገበያ ሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ አቅርቦት ካቆመች ለከፍተኛ ችግር ይጋለጣል ብለዋል። ተተኪ የኃይል አቅርቦት ለማግኘት ዓመታት ሊወስድባቸውም ይችላል ከኛ ይልቅ እነሱ ይጎዳሉ ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ቢቢሲ አስነብቧል። ### Response:
### Text: የገቢዎች ሚኒስቴርበያዝነው ሳምንት በተለያዩ የመቆጣጠሪያ ጣቢዎች በድምሩ 4480305 ብር የሚገመት የኮንትሮባድ ዕቃ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ቡሌሆራ የመቆጣሪያ ጣቢያ ላይ 627100 ብር የሚገመት ተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ ቻርጀሮች እና ጀነሬተሮች የሚያካትት የኮንትሮባንድ ዕቃ መጋቢት 92011 ዓም በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ የኮንትሮባንድ ዕቃው በሰሌዳ ቁጥር ኮድ394467 አአ በሆነ ተሸከርካሪ ሲጓጓዝ በኦሮሚያ ፖሊስና በጉምሩክ ሰራተኞች ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ በምስራቅሀረርጌዞን ኮምቦልቻ ከተማ አካባቢ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ319171 አአ ተሸከርካሪ 697300 ብር ግምታዊ ዋጋው ኮንትሮባንድ የሆነ ኤሌክትሮኒክስ፣ መለዋወጫ እና ፌሮ ብረት በኦሮሚያ አድማ ብተና ፖሊስ፣ በመከላከያ ሰራዊት እና በጉምሩክ ሰራተኞች መጋቢት 92011 ዓም በቁጥጥር ስር ውሏል ግምታዊ ዋጋ 1200000 ብር የሆነ መድሃኒት፣ አልባሳት፣ የቤት ክዳን ቆርቆሮ ፣ ስኳር እና ሌሎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መጋቢት 10 ቀን 2011 ዓም ከምሽቱ 5፡00 ላይ የሰሌዳ ቁጥር 01526 ሱማ እና 02621 ሱማ በሆኑ ተሸከርካሪዎች ወደ ጅግጅጋ ለማስገባት ሲሞከር በአድማ ብተና አባላት እና በጉምሩክ ሰራተኞች ተይዟል፡፡በደቡብ ክልል ገደብ፣ ወናጎ እና አርባ ምንጭ ከተሞች 2026105 ብር የሚገመት መድሃኒት፣ አልባሳት እና ሌሎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ምንጭ ገቢዎች ሚኒስቴር ### Response:
### Text: አፈ ጉባኤዋ ይቅርታ ጠየቁ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዋናአፈጉባኤ የምክር ቤቱ አባላት ይቅርታ ያድርግልኝ ሲሉ በይፋ ጠየቁ። ዋና አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሄለን ደበበ ዛሬ ረፋድ ላይ የተጀመረውን የክልሉን አምስተኛ ዙር መደበኛ ጉባኤ በንግግር ሲከፍቱ ላለፉት አስራ አንድ ወራት የምክር ቤቱን መደበኛ ጉባኤዎች ባለመጥራቴ የተከበሩ የምክር ቤት አባላት ይቅርታ ያድርጉልኝ ሲሉ ተማፅነዋል።የህዝብ ውክልና ያለው ምክር ቤት በየጊዜው ማከናወን የነበረበትን ስብሰባ አለማድረጉ በየትኛውም መመዘኛ ትክክል አይደለም ያሉት ዋና አፈ ጉባኤዋ በቀጣይ ተመሳሳይ ስህተት እንደማይደገም በምክር ቤቱ ፊት ቃል እገባለሁ ብለዋል። በእርግጥ እንደምክንያት ማቅረብ ባይቻልም ምክር ቤቱ ማድረግ የነበረበትን መደበኛ ጉባኤዎች ሳያካሂድ የቀረው ክልሉ አጋጥሞት ከነበረው ነባራዊ ሁኔታ የተነሳ መሆኑን አፈ ጉባኤዋ ተናግረዋል።የደቡብ ክልል ምክር ቤት በዓመት አራት መደበኛ ጉባኤዎችን ማድረግ የሚገባው ቢሆንም ባለፈው የጥቅምት ወር የመጀመሪያውን ስብስባ ካደረገ ወዲህ ዳግም ሳይሰበሰብ ነው የበጀት ዓመቱ የተጠናቀቀው። በዚህም ምክንያት የክልሉ ዓመታዊ በጀት እስከአሁን ባለመፅደቁ የአስፈጻሚ ቢሮዎች ከሀምሌ 1 2012 ዓም ጀምሮ መደበኛ ስራዎቻቸውን በምክር ቤት ባልጸደቀ በጀት ሲያከናውኑ ቆይተዋል።ምንጭ የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በትግራይ ክልል 4ኛው የኮሮና ቫይረስ ሞት ተመዝግቧል ከዚህ በተጨማሪ ባለፉት 24 ሰዓት 60 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 101 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧልከነዚህ መካከል ከባሌ 18፣ ምስራቅ ሸዋ 16፣ ጅማ 6 ፣ ነቀምቴ 9 ሰዎች ይገኙበታል። በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 27 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል ሁሉም የጅግጅጋ ነዋሪዎች ናቸው። በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ሁለት 2 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዡ 294 ደርሰዋል። በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 115 የላብራቶሪ ምርመራ 9 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 41 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል ከነዚህ መካከል ሃያ አንዱ 21 ከሀኪም ወረዳ ናቸው። በድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 1 ሰው ሲሞት 3 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በከተማው የሟቾች ቁጥር 17 የደረሰ ሲሆን 521 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 184 የላብራቶሪ ምርመራ ስድስት 6 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 15 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል ከነዚህ መካከል 5 ከኦሮሞ ብሰብ ዞን ባቲ ከተማ ፣ 4 ከአዊ ብሰብ ዞን ይገኙበታል። ### Response:
### Text: ቀጣናውን ለመረበሽ የሚያልሙ ኃይሎች በንፁህ ዜጋ ላይ ተገቢ ያልሆነ ድርጊት እየፈፀሙ ነው አቶ ሰለሞን አልታዬመነሻውን ደብረብርሃን መድረሻውን አጣዬ አድርጎ ሲያሽከረክር የነበረ የታርጋ ቁጥሩ 3 71650 የሆነ የሲኖ ትራክ አሽከርካሪ በጥይት መመታቱን የኤፍራታና ግድም ወረዳ ሪፖርት አደረገ።ወረዳ በአሽከርካሪውን በጥይት ተኩሰው ጉዳት ያደረሱበት ፀረ ሰላም ሃይሎች ናቸው ብሏል።አሽከርካሪው ጉዳት የደረሰበት ወደ አጣዬ በመጓዝ ላይ እያለ በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ልዩ ስሙ ቆሮ ድልድይ አካባቢ ሲሆን ድርጊቱም የተፈፀመው ትናንት ከምሽቱ በግምት 3 ሰዓት ላይ ነው።ግለሰቡ ከተመታ በኋላ እያሽከረከረ ወደ አጣዬ ከተማ መግባቱን የኤፍራታና ግድም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን አልታዬ ተናግረዋል።በአሁን ሰዓት በአጣዬ ድስትሪክት ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑንም ገልፀዋል።አቶ ሰለሞን ቀጣናውን ለመረበሽ የሚያልሙ ኃይሎች በንፁህ ዜጋ ላይ ተገቢ ያልሆነ ድርጊት እየፈፀሙ ነው ብለዋል።በአሽከርካሪው ላይ የተፈፀመው እኩይ ተግባር የሚወገዝ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን የቀጣናውን ሰላም የማይፈልጉ አሸባሪ ኃይሎችን የአጣዬ ከተማ እና የወረዳው ህብረተሰቡ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን በንቃት መከታተል አለበት ብለዋል።መረጃው የኤፍራታና ግድም ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው። ### Response:
### Text: ትግራይ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የዛፍ አምበጣ መንጋ0የታየ ሲሆን ይኸው መንጋ በዛፍና በደረሱ እህሎች ጉዳት እያደረሰ መሆኑ የክልሉ እርሻና ገጠር ልማት ቢሮ አስታውቋል። የአምበጣ መንጋው ጉዳት ያደረሰባቸው የዞኑ ወረዳዎች ታሕታይ ኣድያቦ ፣ አስገደና ማእኸላይ ኣድያቦ የተባሉ ናቸው። የአንበጣ መንጋው ከመስከረም 22016 ዓም ጀምሮ መታየቱ የገለፀው ቢሮው በ471 ሄክታር መሬት በተካሄደው የኬሚካል መርጨት ስራ 17 በመቶ መከላከል መቻሉ በቢሮው የተባዮች መከላከል ከፍተኛ ባለሙያ አቶ መለስ ኣባዲ ገልፀዋል። አሁን በክልሉ ሰሜናዊ ምእራብ ዞን የተከሰተው የዛፍ አንበጣ መንጋ ወረራ ሙሉ በሙሉ ለመከላከል የሚያስችል የኬሚካል መርጫ መሳርያ እጥረት መኖሩንና አርሶ አደሩ በተቻለው ሁሉ በመጠቀም የመከላከል ስራው አጠናክሮ እንዲቀጥል ባለሙያው አሳስበዋል።በዞኑ ማእኸላይ አድያቦ ወረዳ ደግሞ በ8 ቀበሌ ገበሬ ማህበራት 1950 ሄክታር አዝርእት የሸፈነ የበቆሎ ተባይ መታየቱ ተገልፀዋል። በተያያዘ ዜና በትግራይ ደቡባዊ ዞን ራያ ዓዘቦ ወረዳ የአንበጣ መንጋ ወረራ በሁለት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት መታየቱንና በባለሙያዎችና በህዝቡ የተቀናጀ ተሳትፎ የመከላከለ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ከክልሉ የእርሻና ገጠር ልማት ቢሮ የተገኘ መረጃ ያስረዳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።0000000000000000000000000 ### Response:
### Text: የኤምሬትስ አየር መንገድ ከጋዜጠኞች ጋር ያደረገው ቆይታ ትላንት በራዲሰን ብሉ ሆቴል የኤምሬትስ አየር መንገድ ከጋዜጠኞች ጋር ባደገው የውይይት መድረክ ላይ አየር መንገዱ በአገልግሎት ዘርፉ በሚያካትታቸውና በቅርብ አገልግሎት መስጠት በጀመረባቸው ስራዎች ላይ በአትዮጲያ የኤምሬትስ ማናጀር በሆኑት አቶ ማኖጅ ናየር በኩል ገለጻ የተሰጠበት ሲሆን ከጋዜጠኞችም ጥያቄዎች ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡የኢምሬትስ አየር መንገድ በንጽጽር በአጭር ጊዜ ውስጥ አንጋፋ የሆነ አየር መንገድ መሆኑንና የመጀመሪያውን በረራ በኦክቶበር 25 1985 እኤአ ወደ ካራቺ ካደረገበት ጊዜ አንስቶ ባሉት 34 ዓመታት ውስጥ የአገልግሎቱን ስፋት ወደ 158 መዳረሻዎችና ወደ 85 ሀገራት በማሳደግ የበራራና የካርጎ አገልገሎት መስጠት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡አሁን ላይ አየር መንገዱ 586 ሚሊዮን ያክል ደንበኞችን በማስተናገድ ላይ ይገኛል፡፡ በአፍሪካም በ23 ሀገራት መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ኢትዮጲያም ከነዚህ መዳረሻዎች አንዷ መሆኗን በውይይቱ ወቅት ተገልጻል፡፡ ከዛም በተጨማሪ ወደ ሰሜን አሜሪካ 13 ወደ ደቡብ አሜሪካ 4 ወደ ኢሮፕ ሀገራት 41 ወደ ኤዢያ 60 ወደ መካከለኛው ምስራቅ 11ና ወደ አውስትራሊያ 7 ያክል በረራዎችን እየሰጠ ያለ አየር መንገድ ነው፡፡00 ተጨማሪ ያንብቡ የኤምሬትስአየርመንገድከጋዜጠኞችጋርያደረገውቆይታ0830 ### Response:
### Text: ይፋዊመግለጫ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ተደምስሷል የሶማሌ ክልል ፀጥታ ምቤትዛሬ ምሽት የሶማሌ ክልል ፀጥታ ምክር ቤት መግለጫ ሰጥቷል።በመግለጫው ከ4 ቀናት በፊት አቶ በሚባለው ቦታ ወደ ሶማሌ ክልል አፍዴር ዞን አልሸባብ የሽብር ቡድን ታጣቂ መግባቱን አመልክቷል።የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ሁልሁል በሚባል ንዑስ ቀበሌ ከተከበቡ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ተደምስሰዋል ሲል አሳውቋል።የፀጥታ ምቤቱ አልሸባብ በኤልከሬ ወረዳ አልፎ ወደ ኦሮሚያ ክልል በመግባት በኢትዮጵያ የህተምቤት አሸባሪ ተብሎ ከተፈረጀው ሸኔ ቡድን ጋር ለመገናኘት አልሞ እንደነበር ገልጿል።አልሸባብ ወዳሰበው ቦታ ሳይደርስ የያዛቸውን 13 ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል ያለው የክልሉ ፀጥታ ምቤት ይዞት የገባው ትጥቅ እና ስንቅ ተማርኳል ብሏል።ለ3 ቀናት ያህል በተካሄደው ኦፕሬሽን ከ100 በላይ የአሸባሪው አልሸባብ ቡድን አባላት መገደላቸውን የክልሉ ፀጥታ ምቤት አሳውቋል።ለኦፕሬሽኑ መሳካት የሶማሌ ክልል ህዝብ ለጀግናው የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል የተለያዩ ምግቦች፣ በርካታ የቁም እንስሳቶች፣ መጠጦች ፣አልሰባሳት እንዲሁም ደም በመለገስ ከልዩ ሀይሉ ጎን መቆማቸው የተገለፀ ሲሆን የክልሉ ህዝብ ላደረገው ድጋፍና እገዛ የፀጥታ ምክር ቤቱ ምስጋና ማቅረቡን ከክልሉ ኮሚኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ### Response:
### Text: አዲስ አበባ️ከአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን በመጡ ወጣቶችና ፒያሳ አካባቢ ባሉ ወጣቶች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት አካባቢው ተረብሾ ውሏል፡፡በተለያዩ አውቶብሶች ፒያሳ መሀል ላይ የተበተኑ ከኦሮሚያ ክልል የመጡ ወጣቶች ገጀራና ሚስማር የተመታበት እንጨት ይዘው እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን፣ የፒያሳ አካባቢ የማኅበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ፖሊስ ጣቢያን ለመዝረፍ እንቅስቃሴ መደረጉንና ፖሊሶችም በጥይት መበተናቸውን፣ ፖሊስ ለሪፖርተር ገልጿል፡፡የፒያሳ ማኅበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ተረኛ መኰንን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ 700 የሚሆኑ ወጣቶች ጭነው የመጡት መኪኖች በአካባቢው ወጣቶችና በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ሪፖርተርም ፖሊስ ጣቢያው ውስጥ ተገኝቶ፣ በአማርኛ መግባባት የማይችሉ ጉዳት የደረሰባቸው ወጣቶች የሕክምና ዕርዳታ ሲጠብቁ ለማስተዋል ችሏል፡፡በዳግማዊ በአፄ ምንልክ አደባባይ ሐውልትና አካባቢም በመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገለት የነበረ ሲሆን፣ የፌዴራል አድማ በታኝ ፖሊስም ወደ አመሻሹ አካባቢ ዓርማ የሌለው ሰንደቅ ዓላማ ይዘው ወደ ጎዳና የወጡ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ሲበትን ተስተውሏል፡፡በፒያሳ የሚገኙ ባንኮችና የንግድ መደብሮች ሙሉ በሙሉ ከመዘጋታቸውም በተጨማሪ፣ የትራንስፖርት አገልግሎትም በመቋረጡ ብዙዎች ሲቸገሩ ታይተዋል፡፡©ሪፓርተር ### Response:
### Text: ህዳር 30 የሚዘጉ መንገዶች️በአዲስ አበባ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ከትራፊክ ፍሰት ነፃ የሆነ ቀን ለማክበር ሚዘጉትመንገዶች ይፋ ሆኑ።ለትራፊክ ዝግ የሚሆኑ ሁለት መንገዶች የተለዩ ሲሆን አንደኛው ከጊዮርጊስ አደባባይ በቸርችል ጎዳናኢትዮ ኩባ ወዳጅነት ፓርክ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከጊዮርጊስ አደባባይበ6ኪሎበ5ኪሎ አድርጎ መድረሻውን ጊዮርጊስ አደባባይ ያደርጋል፡፡የአዲስ አበባ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከአዲስ አበባ ስፖርትና ወጣቶች ፌዴሬሽን ጋር በመሆን በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ የጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዶክተር ሳሙኤል ዘመንፈስ ቅዱስ የስኳር፣ የደም ግፊት እና የጡት ካንሰር ነጻ የምርመራ አገልግሎትም ይሰጣል ብለዋል፡፡በእለቱ የህብረተሰቡን የጤና ግንዛቤ ለማሳደግ የተለያዩ የጤና መልእክቶች ይተላለፋሉ፡፡በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስፖርት ውድድርና ተሳትፎ ባለሙያ አቶ እንግዳወርቅ ዳንኤል በበኩላቸው በእለቱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን የሚመሩ የአካል ብቃት ባለሙያዎችም እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡የፊታችን ህዳር 30 በሚካሄደው ከትራፊክ ፍሰት ነጻ ቀን የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ዲፕሎማቶች የሚሳተፉበት ሲሆን በዕለቱ ከ3ሺ እስከ 5ሺ ሰዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ፕሮግራሙ ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት የሚካሄድ መሆኑም ታውቋል፡፡ምንጭ አርትስ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ሀላባ ከተማ ይቅርታ ጠየቀባሳለፍነው እሁድ በ6ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ሀላባ ከተማ በሜዳው ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደበት ጨዋታ በ76ኛው ደቂቃ ላይ ከተመልካች በተወረወረ ድንጋይ የመሐል ዳኛው ኤፍሬምደበሌ ላይ ጉዳት በመድረሱ ምክንያት መቋረጡ የሚታወስ ነው። ይህንን አስመልክቶም የሀላባ ከተማ ክለብ ለፌዴሬሽኑ የይቅርታ ደብዳቤ አስገብቷል።የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ አንዋር ሲራጅ ስለ ጉዳዩ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት በተፈጠረው ስርዓት አልበኝነት በጣም እንዳዘኑ ገልፀው የሀላባ ከተማ በእግርኳስ ውድድሮች ባለፉት 10 ዓመታት ሲሳተፍ እንዲህ አይነት ድርጊት ታይቶ እንደማይታወቅ በማውሳት ከጨዋታው መቋረጥ በኋላ አመራሩ እንዲሁም የከተማው አስተዳደር ማምሻውን ስብስባ አድርጎ ወደ እርምጃ በመግባት ሁለት ተጠርጣሪዎችን ወዲያው በመያዝ በቀጣዩ ቀንም 9 ወጣቶችን በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ለፍርድ ለማቅረብ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል።0ፕሬዝዳንቱ የሀላባ እግር ኳስ ክለብ እና የከተማው አስተዳደር የተፈጠረውን ሁሉ አጥብቆ እንደሚቃወምና እንዲህ አይነት ድርጊት ዳግም እንዳይፈፀም አጥብቀው እንደሚሰሩ በመግለፅ የሚመለከታቸው አካላትን በክለቡ እና በሀላባ ህዝብና አስተዳደር ስም ይቅርታ መጠየቀቸውን ለሶከር ኢትዮጽያ ገልፀዋል።ምንጭ ሶከር ኢትዮጵያ ### Response:
### Text: የአንድ ዓመት ነጻ የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎት የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት 20 ለሚደርሱ ህሙማን የአንድ ዓመት ነጻ ዕጥበት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ነው ለህሙማኑ አገልገሎቱን መስጠት የጀመረው፡፡የኢትዮጵያ መድህን ድርጅትም ለህሙማኑ ለአንድ ዓመት ሙሉ የዕጥበት ክፍያ የሚውል የ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ሰጥቷል፡፡ የድርጅቱ የቢዝነስ ልማትና ሪስክ ማኔጅመንት ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ መንግስቱ መሃሩ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለማገዝ ሰፊ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው በማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ የሚያደርገውን ተሳትፎም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በሰጠው የገንዘብ ድጋፍ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የሚገኙ 20 የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ለአንድ ዓመት በነፃ እንዲጠቀሙ ተደርጓል ብለዋል፡፡የአገልግሎቱ ጠቃሚ ህሙማንም በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡ ሌሎች የመንግስትና የግል ድርጅቶችም እየጨመረ የመጣውን የኩላሊት ህመም ጉዳት ለመቀነስ እንዲረባረቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኤ ኤም ኤን ### Response:
### Text: የጅማ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ልገሳ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ኑ በጋራ የልጆቻችንን ተስፋ ብሩህ እናድርግ በሚል መሪህ ቃል ከነሃሴ 6 እስከ 102011 ዓም ባደረገዉ የልገሳ ሳምንት የተለገሰዉን የትምህርት ቁሳቁስ ለ13 ትምህርት ቤቶች በዛሬዉ እለት ጳጉሜ 12011 ዓም አስረክቧል፡፡በልገሳዉ ዝግጅት ላይ የዩኒቨርሲቲዉ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ የከተማ አስተዳደር አካላት፣ የከተማዉ ትምህርት ቢሮ፣ የ13 ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች፣ የወላጅ ኮሚቴ አባላት እና ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን ለ1014 ተማሪዎች ለእያንዳንዱ 1ደርዘን ደብተር እና 10 እስክሪፐቶ በትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች በኩል የተለገሰ ሲሆን ለ300 ተማሪዎች ደግሞ ዩኒፎርም ማሰፊያ ተበርክቷል፡፡ በዚህ የልገሳ ሳምንት ከዩኒቨርሲቲዉ፣ ከዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ በገንዘብ ሲተመን ግማሽ ሚሊዮን እንደሚደርስ በዝግጅቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡የልገሳ ዝግጅቱን የከፈቱት የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶር ጀማል አባፊጣ፣ የለገሱትን እና ያስተባበሩትን አካላት አመስግነዉ፣ በቀጣይ ዩኒቨርሲቲዉ የበጎ አድራጎት ማዕከል በመክፈት የበጎ አድራጎት ስራን በተሳለጠ መልኩ እንደሚያካሂድ ገልጸዋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ የታደሙት አባገዳዎች፣ የከተማዉ ትት ቢሮ እና የትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ለዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በላከልን ባለ 7 ነጥብ የቋም መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም የተቀሰቀሰው ጦርነት ቆሞ ሰላማዊ ድርድር እንዲቀጥል ጠይቋል።ምክር ቤቱ በሶስተኛ ወገን አማካኝነት ግጭቱን በድርድር ለመፍታት ሲደረግ የነበረውን ቅድመ ዝግጅት በቅርበት ሲከታተል እንደነበረ የገለፀ ሲሆን የድርድር ሂደቱ ተቋርጦ ግጭት መቀስቀሱ እጅጉን እንዳሳሰበው አመልክቷል።ዳግም ግጭት እንዲቀሰቀስ ምክንያት የሆነውን ጥቃት የጀመሩት የህዉሃት ኃይሎች መሆናቸው የገለፀው ምክር ቤቱ የህወሓት ኃይሎች የሠላም አማራጭ እንዳልተሟጠጠ አውቀው ቀደም ሲል በመንግስት የተወሰደውን የተኩስ አቁም እርምጃ በማክበር ወደ ሠላማዊ ውይይትና ድርድር እንዲገቡ ጠይቋል።የትግራይ ህዝብም ህዉሃት ጦርነትን አቁሞ ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲገባ ተፅዕኖ እንዲፈጥር ጥሪ አቅርቧል።ምክር ቤቱ በዚህ መግለጫው የውጪ ኃይሎች ከአገራችን የውስጥ ጉዳይ እጃቸውን እንዲሰበስቡና የሰላም መንገድን ብቻ አጥብቀው እንዲደግፉ የጋራ አጥብቆ እንደሚታገል አረጋግጧል።የአለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብም የችግሩን አሳሳቢነት ተገንዝቦ ጦርነቱ በሚቆምበትና ሰላማዊ ውይይትና ድርድር በሚጀምርበት ሁኔታ ላይ በፍትሐዊነትና በገለልተኝነት አጋርነቱን እንዲያሳይ አጥብቆ ጠይቋል።ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል ### Response:
### Text: እንኳን በጉራየሌለህን አለኝ ሳታውቅ አዋቂነኝ፣እንዳከብርህ ብቻ ውሸት አትንገረኝ።ከሌለህ ነውር አይደል ካለህ ለራስህ ነው፣እኔ የማከብርህ በሰውነትህ ነው።እንኳን በጉራ ደረት ተነፍቶ፣አልቻለውም ሰው አንገቱን ደፍቶ ።ዝቅ እያሉ ነው ተናንሶ ኑሮ፣ላካበደማ አይወን ዘንድሮ። 2ትልቅ ፈጣሪ ነው ትልቅ ለዘላለም፣የሰው ትልቅ የለምየእድሜ ሰረገላ የድሜ ሰረገላሄዶም መቶ አይሞላም 2እኔ ምን አውቃለው ካወክ አሰተምረኝ፣ ንቀቱን ተውና ይሄ ይሄ ነው በለኝ።ያን ያንን ሳታረገ ብትመፃድቅም ፣ሆዴን ልሙላ በዬ ብሞት ላንተ አልሰገድምወርቅ በሰው ልጅ የተወደደው፣እራሱን አቃሎ ጭቃ መሰሎ ነው።ከፍ ከፍ ያለው በባዶ ሜዳ፣አጅሬ ገለባ ወድቆ ተጎዳ።ወርቅ በሰው ልጅ የተወደደው፣እራሱን አቃሎ ጭቃ መሰሎ ነው።ከፍ ከፍ ያለው አጅሬ ገለባ እዩት ሲጎዳትልቅ ፈጣሪ ነው ትልቅ ለዘላለም፣አሃ አሃ የሰው ትልቅ የለምየእድሜ ሰረገላ የድሜ ሰረገላሄዶም መቶ አይሞላም።እንኳን በጉራ ደረት ተነፍቶአልቻለውም ሰው አንገቱን ደፍቶዝቅ እያሉ ነው ተናንሶ ኑሮላካበደማ አይሆን ዘድሮ። 2ትልቅ ፈጣሪ ነው ትልቅ ለዘላለም፣አሃ አሃ የሰው ትልቅ የለምየእድሜ ሰረገላ፣ሄዶም መቶ አይሞላ።የእደሜ ሰረገላ፣ሄዶም መቶ አይሞላ፣ትልቅ ፈጣሪ ነው ትልቅ ለዘላለምአሃ አሃ የሰው ትልቅ የለም።©ድምጻዊ አብዱ ኪያር ቲክቫህኢትዮጵያ ### Response:
### Text: ሰኔ 15 ቀን በክልልና በፌደራል ደረጃ በተፈጸመው ጥቃት ሳይደናገጡ፣ ክልላቸውንና ዞናቸውን ለማረጋጋትና ሠላም ለማስፈን በላቀ ዝግጁነት ላይ መሆናቸውን በሰሜን ወሎ ዞን የሚገኙ የመቅደላ ብርጌድ የልዩ ኃይል አባላት ተናገሩ።በእዙ ስር የሚገኙ ከ1 ሺ 300 በላይ ልዩ ኃይሉን የሚመሩት ከሻምበል አመራር በላይ የሆኑ መሪዎች ለሁለት ቀናት የሚቆይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ አባላቱ እርስ በእርሳቸው በመወያዬትና በመመካከር ችግሮችን በመፍታት በቀጣይ የአማራ ክልል ሕዝብን ካሉበት ውስጣዊ እና ውጫዊ የፀጥታ ስጋቶች ለመታደግ ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ገልጸዋል።ኅብረተሰቡ በተፈጠረው ድርጊት ሳይረበሽ እና ሳይደናገጥ ከፀጥታ መዋቅሩ ጎን በመሆን የፀጥታ ኃይሉ ሕግን ለማስከበር የሚያከናውነውን ሥራ እንዲያግዝም የልዩ ኃይል አባላቱ ጥሪ አቅርበዋል።በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲዎች ልዩ ኃይሉን አስመልክቶ የሚናፈሰው አሉቧልታ መሠረተ ቢስ መሆኑን መረዳት እንደሚገባ ያሳሰቡት አባላቱ በፀጥታ መዋቅሩ ልዩነት እና ክፍፍል አለመኖሩን አረጋግጠዋል።በውይይቱ እየተሳፉ የሚገኙት ከ1 ሺህ 300 በላይ የልዩ ኃይሉን የሚመሩት ከሻምበል አመራር በላይ የሆኑ መሪዎች ናቸው። እነዚህ መሪዎች ለአባሎቻቸው የውይይቱን ሐሳብ እንደሚያወርዱም ይጠበቃል። ቀን ሃምሌ 42011 ዓም ### Response:
### Text: 1 ሺ 442 ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በአደባባይ ይከበራልየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ በዓልን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ አብሮነቱን እንዲያሳይ ጥሪ አቅርበዋል።1 ሺህ 442 ኛው የኢድ በዓል በአደባባይ እንደሚከበር ተገልጿል። ባለፈው ዓመት በኮቪድ19 ምክንያት የኢድ አልፈጥር በዓል በመስጊድ እንዲከበር መደረጉን አስታውሰው ዘንድሮ መንግስት እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች በሰጡት መመሪያ መሰረት ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ከመስጊድ ውጭ በአደባባይ እንደሚከበር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ አሳውቀዋል።በዓሉን በመከባበርና በሰላም ማክበር እንደሚገባ የተናገሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር፣ ህዝበ ሙስሊሙ የተቸገሩ ወገኞችን በመደገፍ አብሮነቱን ሊያሳይ ይገባል ብለዋል። የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን በሰላም አክብረው መመለስ እና ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን ማሳየት እንዳለባቸውም ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪ መረጃ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር የዛሬው የአፍጥር ስነ ስርዓት በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር መወያየታቸውን ገልፀዋል።ስርዓቱን ያዘጋጁ ወገኖችና የመንግስት አካላት በሰላም እንዲጠናቀቅ ሊሰሩ እንደሚገባም መልዕክት ማስተላለፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል። ### Response:
### Text: ዛሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ሀገር መከላከያ ሰራዊት በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በመከላከያ በኩል ሌጄነራል ባጫ ደበሌ ናቸው መግለጫውን የሰጡት።ምን አሉ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከመቐለ ለቆ በመውጣቱን ገልፀዋል። እንደምንወጣ ከሳምንታት በፊት የነገርናቸው የውጭ ተቋማት ነበሩ ብለዋል። በሁሉም አቅጣጫ ማለትም በሱዳን ፣ ኤርትራ አፋር እና አማራ ወሰን ዝግ መሆኑን ገልፀዋል። የፌዴራል መንግስት ከዚህ በኋላ በትግራይ ክልል ዙሪያ ለሚኖር ችግር ተጠያቂ እንደማይሆን ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከዚህ በኋላ ዕርዳታ ደረሰ አልደረሰ ብለው የፌዴራል መንግስትን ሊጠይቁ እንደማይገባ ገልፀዋል የትግራይ ክልልን በተመለከተ ሙሉ ኃላፊነቱን አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው ህወሃት እንደሚወሰድ አሳውቀዋል። በትግራይ ክልል የተከሰተው ግጭት ኢትዮጵያን ለከፍተኛ ኪሳራ እንደዳረጋት ገልጸዋል በልማት ሂደቱ ላይም ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳሳደረ ተናግረዋል፡፡ ሕወሃት የሀገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ እንደጣለ ተናግረዋል ሱዳን የኢትዮጵያን ሉኣላዊ ድንበር ጥሳ እንድትገባ አጋልጦ እንደነበርም ገልፀዋል። 8 ወራት ብቻ የጦር ወጪን ሳይጨምር የፌደራሉ መንግሥት ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማደረጉን ገልጸዋል።ያንብቡ 0630 ### Response:
### Text: 262 የክርስትና እምነት ተከታዮችን በመስጊድ እና በቤቱ በመደበቅ ከገዳዮች ለታደጉት ናይጀሪያዊው ኢማም አሜሪካ እውቅና ሰጥታለች፡፡ የ83 አመቱ አዛውንት ኢማም አቡበከር አብዳላሂ የአለምአቀፍ የሃይማኖቶች ነፃነት ሽልማት ያገኙ ሲሆን ከቆጵሮስ፣ሱዳን፣ብራዚልና ኢራቅ የተለያዩ ሽልማቶች አግኝተዋል፡፡ኢማም አቡበከር አብዳላሂ በማዕከላዊ ናይጄሪያ ፕላትዮ ግዛት ልዩ ስሙ ባርኪን ላዲ በተባለው አካባቢ ከገዳዮች ሲሸሹ የነበሩትን ክርስትያኖች ህይወት መታደጋቸው ነው የተገለፀው፡፡ በወቅቱ ክርስቲያኖች ላይ ባነጣጠረው ጥቃት ሌሎች 80 ሰዎች መሞታቸውም ተገልጿል፡፡ኢማም አቡበከር አብዳላሂ 262 ክረስትያኖችን ባይታደጓቸው ኖሮ የሟቾች ቁጥር ከ80 በላይ ይሆን እንደነበር ተገልፅዋል፡፡ ኢማሙ ለዚህ በጎ ድርጊት ያነሳሳቸው ከ40 ዓመታት በፊት ክርስትያኖቹ በቦታው መስጊድ ለመስራት ስለፈቀዱላቸው ነው ተብሏል፡፡የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖንፕዮ ኢማም አቡበከር አብዳላሂ የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ በመጣል የሌላ እምነት ተከታዮች ህይወት ማትረፍ የቻሉ ራስ ወዳድ ያልሆኑ ሰው ናቸው ብለዋል፡፡ ያለሳቸው እርዳታ የሰዎቹን ህይወት ማትረፍ እንደማይቻልም አክለው ገልፀዋል፡፡ ኢማሙ ከዚህ ቀደምም ከናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ሙሃሙዱ ቡሃሪ እውቅና እንደተሰጣቸውም ተገልጿል፡፡ምንጭ ፡ቢቢሲ ### Response:
### Text: የእኛ ሰላምና እርቅ በየጊዜው እለት እለት ልንፈጽመው የሚገባን ተግባር መሆን አለበት 0ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በዛረው በበዓል ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በዛሬው ዕለት የምናከበው በዓለ መስቀል የእግዚአብሔር ሰላምና እርቅ ፍለጋ በብርቱ የተንቀሳቀሰችው ታላቋ ክርስቲያናዊት ንግሥት ዕሌኒ የፈጸመችውን የቅድስና ተግባር እና ያስገኘቸውን ሃይማኖታዊ ስኬት መነሻ አድርገን ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ ነው ብለዋል።0ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሲል በመስቀሉ ላይ ተሰቅሎ የሰውን ልጅ መርገመ ሃጢያት እንዲወገድ በማድረግ ሰው ወደቀደመ ቦታው ገነት እንዲገባ ምክንያት መሆኑን የገለጹት ቅዱስነታቸው በዚህም ምክንያት መስቀል ከሁሉም በላይ ነው ሊባል መቻሉን ገልጸዋል።የእኛ ሰላምና እርቅ በየጊዜው እለት እለት ልንፈጽመው የሚገባን ተግባር መሆን አለበት ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ አንገታችን ላይ ያለው መስቀል ጌጥ ሳይሆን በእግዚአብሄር እና በሰው፣ በእኛ እና በስነፍጥረት መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በመሆኑ ልንጠብቅበት ይገባል ካሉ በኋላ በዓለም ላይ ሰላም ፍቅር እና አንድነት እንዲሰፍን ጠንክረን እንስራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡0ያንብቡ 09262 ### Response:
### Text: በዛሬው ዕለት የተለያዩ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን አስመርቀዋል ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለ12ኛ ጊዜ በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸው 2 ሺህ 93 ተማሪዎችን አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከል ከ700 በላይ ሴቶች መሆናቸ ተገልጿል። 12 የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ4ኛ እና በ5ኛ ዙር በተለያዩ የህክምና ዘርፍ ያስተማራቸውን 127 ዶክተሮች አስመርቋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር አንበሳ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ 484 የሕክምና ባለሙያዎችን አስመርቋል። ከምሩቃኑ 209 በስፔሻሊስት፣ ሁለት በዶክትሬት እና 273 በ2ተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ የሕክምና ባለሙያዎች ናቸው። የመቱ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ ትምህርት ዘርፎ ያሰለጠናቸው 252 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ አስመርቋል። ከሰለጠኑባቸው የትምህርት መስኮች ውስጥ ነርሲንግ፣ ፋርማሲ፣ ህብረተሰብ ጤና እና አዋላጅ ነርሲንግ ይገኙበታል።ከመካከላቸው 93 ሴቶች ናቸው። የሆቴልና ቱሪዝም ስራ ማሰልጠኛ ማዕከል በተለያዩ የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 425 ተማሪዎችን አስመርቋል።በዘንድሮ መርሀ ግብር በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ በድግሪ 16 ተመራቂዎች ፣ በደረጃ 3 በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ 202 ተመራቂዎች ፣ በደረጃ 4 በሆቴል እና ቱሪዝም 157 ተመራቂዎች እንዲሁም በደረጃ 5 በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ 53 ተማሪዎች ነው የተመረቁት። ### Response:
### Text: በጀርመን ኤርትራዊ ወጣት ላይ በደረሰበት ጥቃት በርካቶች አደባባይ በመውጣት ተቃውሟቸውን ገለፁ። ከቆዳው ቀለም ጋር ተያይዞ በጥይት በተመታው ኤርትራዊ ምክንያት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በጀርመን ዋችተርስባች ከተማ ለተቃውሞ መውጣቸው ተገለፀ፡፡የጀርመን የአገር ውስጥ ሚድያ እንደገለፀው የ26 አመቱ ኤርትራዊ ወጣት በጥቃቱ ከፍተኛ ጉዳት ቢያጋጥመውም አሁን ላይ እየተሻለው መሆኑ ተገልፅዋል፡፡የፍራንክፈርት ግዛት አቃቤ ህግ ቃል አቀባይ አሌክሳንደር ባድል እንዳሉት የሃገሪቱ ባለስልጣናት ከውጪ ሃገር ዜጎች ጥላቻ የመነጨ ሊሆን ይችላል ያሉትን ጥቃት እየመረመሩ ይገኛሉ፡፡ቃል አቀባዩ ጨምረውም ጥቃት አድራሹ በዘፈቀደ እንደተኮሰ ገልጸው እራሱን ማጥፋቱን አመልክተዋል፡፡ ፖሊስ በበኩሉ ተጠርጣሪ ወንጀለኛው አጎራባች ከተማ መኪና ውስጥ ህይወት አልባ ሆኖ መገኘቱን ገልፆ በሆስፒታል መሞቱ ተረጋግጧል ብሏል፡፡የተጠርጣሪው ቤትና መኪና ሲፈተሸም ሁለት በከፊል አውቶማቲክ የሆኑ ህጋዊ ሽጉጦች መገኘታቸውንና ተጠርጣሪው የዘረኝነት ጥቃት የመፈፀም ዝንባሌ እንዳለው ተረጋግጧል መባሉን ዶቼ ዌሌ ፖሊስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡መርማሪዎች በበኩላቸው የ55 አመቱ ጥቃት አድራሽ ቀኝ አክራሪ ናሽናሊስት መሆኑን እስካሁን አላረጋገጥንም ብለው ምርመራው መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡ምንጭ፡አልጀዚራ ### Response:
### Text: የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ጽኑ ህሙማንን መቀበል የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ስራ እያጠናቀቀ መሆኑን አስታወቀ።ሆስፒታሉ የኮሮና ቫይረስ ድንገት ወደ ሀገር ውስጥ ቢገባ በቫይረሱ የተጠቁ ጽኑ ህሙማንን ተቀብሎ እንዲያስተናግድ በጤና ሚኒስቴር መመረጡ ይታወሳል።በዚህም የተሟላ የህክምና ማሽን እና አምስት የጽኑ ህሙማን ታካሚዎችን ማስተናገድ የሚችል የጽኑ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል ለይቶ ማዘጋጀቱን ዋና ስራ አስፈጻሚው ዶክተር ታምሩ አሰፋ ገልፀዋል።ከዚህ ባለፈም በጽኑ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከሉ ውስጥ ለሚሰሩ 40 ሰራተኞች በቫይረሱ ህክምና እንዲሁም የቅድመ ጥንቃቄና መከላከያ ስራዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።በቫይረሱ ዙሪያ ግንዛቤን ለመፍጠር እንዲያስችልም ብሮሸሮችና በራሪ ወረቀቶች በማተም በሆስፒታሉ ለመታከም ለሚመጡትም ሆነ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑም ነው የተገለፀው።በአዲስ አበባ ለሚገኙ 13 ሆስፒታሎችም በኢትዮጵያ አየር መንገድና በባቡር ጣቢያዎች ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች 5 ሺህ ለቅድመ መከላከያ የሚያገለግል የአልኮል እጅ ማጽጃ በሆስፒታሉ የፋርማሲ አገልግሎት ክፍል ተመርቶ መሰራጨቱን ከሆስፒታሉ የፌስ ቡክ ገፅ የተገኘነው መረጃ ያመላክታል።የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ### Response:
### Text: የዶናልድ ትራምፕ የስንብት ንግግር ቢቢሲ የቀረበከ12 ሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ተብለው የሚጠሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለደጋፊዎቻቸው የስንብት ንግግር አድረዋል።ይህ ንግግራቸው የተሰራጨው በዩትዩብ ነው።ለማድረግ ያሰብነውን አድርገናል፣ ከዚያም በላይ ነው ያሳካነው ብለዋል ትራምፕ በንግግራቸው።ከባዱን አውደ ውጊያ ላይ ነበር የተሳተፍኩት፣ ከባድ ፍልሚያ ነው ያደረኩት ምክንያቱም የመረጣችሁኝ ያን እንዳደርግ ስለነበረ ብለዋል ትራምፕ።ትራምፕ በዚህ ንግግራቸው በጆ ባይደን መሸነፋቸውን ሙሉ በሙሉ አልተቀበሉትም።ዶናልድ ትራምፕ በስንብት ንግግራቸው በአሜሪካ ታሪክ እጅግ አይበገሬውን ምጣኔ ሀብታዊ ስኬት አስመዝግበናል ይህም በዓለም አንደኛና ትልቁ ነው ብለዋል።ዶናልድ ትራምፕ ባደረጉት የስንብት ንግግር በሚቀጥለው ሕይወታቸው ምን እንደሚያደርጉ ፍንጭ አልሰጡም።ትራምፕ ደጋፊዎቼ ብዙ ናቸው እኔ ተወዳጁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነኝ ሲሉ በተደጋጋሚ ቢናገሩም በዚህ ወቅት በአሜሪካ ያላቸው ይሁንታና ተሰሚነት ምጣኔ አሽቆልቁሎ 34 ፐርሰንት መድረሱ ተዘግቧል።ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ረቡዕ ማምሻውን በምሥራቅ አፍሪካ አቆጣጠር፣ ቀትር ላይ በምሥራቃዊ አሜሪካ አቆጣጠር ከዋይት ሐውስ ይወጣሉ። ጆ ባይደን ቃለ መሐላ ይፈጽማሉ።በሥነ ሥርዓቱ ላይ ትራምፕ አይገኙም። ### Response:
### Text: ሳይፈቱ 24 ሰአት አለፈ ተመስገን ደሳለኝ፣እስክንድር ነጋ፣አንዷለም አራጌ፣ማህሌት ፋንታሁን፣በፍቃዱ ሀይሉ፣ወይንሸት ሞላ ፣ይድነቃቸው አዲሱ፣ ተፈራ ተስፋዬ፣ አዲሱ ጌታነህ፣ ሰንታየው ቸኮል፣ ዘላለም ወርቃገኘው የራስ ዋስትና ከተሰጣቸው በኃላ ሳይፈቱ 24 ሰአት አለፈ።ሰኞ መጋቢት 242010 ዓም አመሻሹ ላይ በፖሊስ መምሪያው ሀላፊ ተጠርተው የራስ ዋስትና ከተሰጣቸው በኃላ እስካሁን አለረተፈቱም። የራስ ዋስትና ማለት በተፈለጉ ግዜ ሊቀርቡ ካልቀረቡ ግን በሌሉበት ጉዳያቸው እንደሚታይ የሚገልፅ የዋስትና አሰጣጥ ነው። ይህን ያሞለ ሰው ህጉ ወዲያው መፈታት እንዳለበት ቢያስቀምጥም እነርሱ ግን ሳይፈቱ 24 ሰአት አልፏቸዋል።ያለ ክስ እስካሁን እስር ቤት ተቀምጠዋል፣ ኮማንድ ፖስቱን እንደታሰሩ አላቅም ካለ ሰንብቷል፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንም የኛ እስረኛ አይደሉም ብሏል በተጨማሪም ከ24 ሰአት በፊትም መጋቢት 242010 ዓም በፖሊስ መምሪያው በህጉ መሰረት የሚያስፈታቸውን የራስ ማስትና ተሰቷቸዋል ቢሆንም ግን አሁንም ድረስ አልተፈቱም።ተመስገን ደሳለኝ፣እስክንድር ነጋ፣አንዷለም አራጌ፣ማህሌት ፋንታሁን፣በፍቃዱ ሀይሉ፣ወይንሸት ሞላ ፣ይድነቃቸው አዲሱ፣ ተፈራ ተስፋዬ፣ አዲሱ ጌታነህ፣ ሰንታየው ቸኮል፣ ዘላለም ወርቃገኘው ዛሬ በፖሊስ መምሪያ ውስጥ እስር ላይ ናቸው።መጋቢት 262010ዓምምንጭ ### Response:
### Text: ነሃሴ 222012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 725 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 34 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል።አጠቃላይ በሱማሌ 1128 በቫይረሱ የተያዙ 23 ሞት 693 ያገገሙ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 3642 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 255 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 58 ከምዕራብ ሀረርጌ 54 ከምዕራብ አርሲ 23 ከሰሜን ሸዋ 17 ከለገጣፎ ከተማ 16 ከአዳማ ከተማ 15 ከሞጆ ከተማ 14 ከጉጂ ይገኙበታልአጠቃላይ በኦሮሚያ 5843 በቫይረሱ የተያዙ 42 ሞት 1762 ያገገሙ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 266 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 19 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት መካከል 1 ከቡለን ወረዳ 3 ከአሶሳ ከተማ 10 ከማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ 3 ከባንቢስ ወረዳ ይገኙበታል።አጠቃላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ 546 በቫይረሱ የተያዙ 274 ያገገሙ በሀረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 376 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 97 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 3972 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 143 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 42 ከሰወሎ ዞን 31 ከዋግ ኽምራ ብሰብ ዞን 19 ከጎንደር ከተማ 12 ከባህር ዳር ከተማ 9 ከደሴ ከተማ ይገኙበታል። ### Response:
### Text: በኦሮሚያ ሆሮ ጉድሩ ዞን 27 የጸጥታ ኃይሎች በታጣቂዎች ተገደሉ።የሆሮ ጉድሩ ዞን ጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዮት በቀለ 27 የጸጥታ ኃይሎች ትናንት ሐሙስ በታጣቂዎች መገደላቸውን ገለፁ።አስተዳዳሪው ከተገደሉት የጸጥታ ኃይሎች በተጨማሪ 10 የፌደራል ፖሊስ አባላት ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።ጸጥታ ኃይሎቹ ላይ ጥቃቱ የተነሰዘረው ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ገደማ ሲሆን ድርጊቱ የተፈጸመው በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉ የ ሸኔ ታጣቂዎችን በማሰስ ላይ ባሉበት ወቅት እንደነበር አቶ አብዮት አስረድተዋል።የጸጥታ ኃይሎቹ በሁለት ዙር ወደ አካባቢው መንቀሳቀሳቸውን የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው አቶ አብዮት ጥቃቱ የተሰዘረው በመጀመሪያው ዙር በተጓዙ 47 የፌደራል ፖሊስ እና ሁለት የሚሊሺያ አባላት ላይ ነው ብለዋል።ከስምንት አመታት በላይ ያገለገሉ እና ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ሁለት ሚሊሺያዎች ትናንት ሐሙስ ሰኔ 3 አካዩ ቀበሌ በተባለ ቦታ በተፈጸመው ጥቃት 24 የጸረ ሽብር ፖሊስ እና ሁለት የሚሊሺያ አባላት በድምሩ 26 የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ተናግረዋል።ጥቃቱ የተሰነዘረው ከንጋቱ 11 ሰዓት ገደማ ጀምሮ መሆኑ የሚገልጹት የሚሊሺያ አባላት በጥቃቱ ስምንት የጸጥታ ኃይሎች ቆስለው ወደ ሻምቡ አጠቃላይ ሆስፒታል ሪፈር መባላቸውን ለ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ደረገፅ ተናግረዋል።ምንጭ 20213536 ### Response:
### Text: እንዲህ ባማረ እና በደመቀ ሁኔታ በመቐለ ዩኒቨርስቲ ምትኩ ሀይሌ አዳራሽ ትላንት ቅዳሜ 17092011 ተመስርቷል፡፡ በቅንድል ዲጂታል መፅሔት ጠንሳሽነት ከሌሎች ተባባሪ አዘጋጆች ጋር በመሆን የተመሰረተ ነው፡፡በዚህ የምስረታ ዝግጅት ላይ ከ2300 በላይ ተማሪዎች፡ አስተማሪዎች እና የጊቢው የአስተዳደር አካላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የመቀሌ ነዋሪዎች ታድመዋል፡፡በዚህ ዝግጅት ላይ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ክንደያ ገሂወት ለታዳሚዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ምናልባት ዛሬ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት በመሆኔ ከኮራሁባቸው ጥቂት ቀናት መካከል አንዱ ነው በማለት ደስታቸውን በጥልቅ ገልፀዋል፡፡በዚህ ፕሮግራም ላይ ቅንድል ዲጂታል መፅሔት ከ ጋር በመሆን ግምታቸው ከ3000 ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን መፅሐፍት እና የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶች ለ ለማህበር ሕውነት ደቂስብ ማእከልየህፃናት ማሳደጊያ አበርክተዋል፡፡የእለቱ እንግዳ የነበረው እና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ዶር ምህረት ደበበ በሚል ርዕስ እጅግ ደስ የሚል ጣፋጭ ትምህርት አስተምረዋል፡፡በዚህ ፎረም ላይ በቋሚ አባልነት አብሮ ከ ጋር ለመስራት ለአባልነት በተበተነው ቅፅ ላይ ከ1100 በላይ ተማሪዎች አባል ለመሆን ቅፅ ሞልተዋል፡፡በቀጣይም ይህ መሰሉ መድረክ ተጠናክሮ በቋሚነት ይቀጥላል፡፡ ### Response:
### Text: ከኦሮሚያ ክልል በኩል ምን ተባለ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ታምሩ ባይሳ ለኢትዮጵያ ኢንሳይደር 20225900 የተናግሩት አባይ ድልድይ ከመደረሱ በፊት ባለው ኮቲቻ በሚባል አካባቢ ጥቃት የተሰነዘረው ትላንት ማክሰኞ የካቲት 1 ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ነው። ጥቃቱን የሰነዘሩት የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው።በጥቃቱ ኮንቲኔየር የጫነ ሎቤድ የጭነት መኪና አሽከርካሪ ተገድሏል።ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም አቅጣጫ በማሽከርከር ላይ በነበረው በዚሁ ግለሰብ ላይ የእሩምታ ተኩስ መከፈቱን ተከትሎ የወረዳው ፖሊሶች ምላሽ ሰጥተዋል። እነሱ ተኩስ እንደጀመሩ የእኛም ልጆች ተኩስ ጀመሩ። ከዚያ በኋላ ወደ ጫካቸው ተመለሱ። በአካባቢው ያለውን የጸጥታ ስጋት ለመቅረፍ በአቅማችን የምንችለውን እያደረግን ነው። ትላንት አመሻሽ ላይ ጥቃት በደረሰበት አካባቢም ተጨማሪ የጸጥታ ኃይሎች ተመድበዋል።ለአባይ ድልድይ ጥበቃ ከሚያደርጉት የፌደራል ፖሊስ አባላት በተጨማሪ የወረዳው ፖሊስ አባላት እና የአካባቢው ሚሊሺያዎች በአሁኑ ወቅት በቦታው ላይ ይገኛሉ።አሁንም አካባቢው ከስጋት ነጻ ባለመሆኑ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ ሊያሰርጉ ይገባል። ጠላት አድፍጦ ሰዓት ጠብቆ ሰለሚመጣ የትኛው ጋር ተደብቆ ጉዳት እንደሚያደርስ ስለማይታወቅ አሽከርካሪዎች ማታ ባይጓዙ የተመረጠ ይሆናል ### Response:
### Text: የሶማሊያው ፕሬዜዳንት በ3 ወር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ0 ወደ ኤርትራ አቅንተዋል።የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለ4 ቀን የስራ ጉብኝት ዛሬ ኤርትራ፣0 አስመራ መግባታቸው ታውቋል።የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አስመራ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው የሶማሊያ አቻቸውን ተቀብለዋቸዋል።ፕሬዝዳንት ሙሀሙድ ወደ ፕሬዜዳንትነት የስልጣን መንበር ከመጡ በኃላ ወደ ኤርትራ በስራ ጉብኝት ሲያቀኑ ይህ ሁለተኛቸው ነው። ከሶስት ወር በፊት ነበር ለስራ ጉብኝት ወደ ኤርትራ ሄደው የነበር።በወቅቱ በዛው በኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላትን ከፕሬዜዳንት ኢሳያስ ጋር እንደጎበኙ ፣ ከጉብኝቱ በኃላ ወታደሮቹን ወደ ሀገራቸው ሶማሊያ ለመመለስ በሚቻልበት መንገድ ላይ እየሰሩ መሆኑን በኤርትራ ከነበራቸው ቆይታ በኃላ ወደ አሜሪካ በሄዱበት ወቅትም በኤርትራ ያሉትን 5000 የሶማሊያ ጦር አባላትን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የአሜሪካን ድጋፍ እንደጠየቁ አይዘነጋም።ፕት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ የሶማሊያ ወታደሮች ከኤርትራ ያልተመለሱበት ምክንያት ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሀገሪቱ ውስጥ በሶማሊያ ባለው የፖለቲካ ልዩነት ምክንያት ሊመልሷቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው መሆኑን መግለፃቸው እና ኤርትራ የሶማሊያ ወታደሮችን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን እያስታጠቀችም እንደሆነ መግለፃቸው ይታወሳል። ### Response:
### Text: ለሚመለከተው ሁሉ️እኛ አመልካቾች በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 03 ቀበሌ 0607 በቤት ቁጥር 737 738 739 741 ልዩ ቦታው ቤላና ፈረንሳይ መገንጠያቀድሞ 11ቀበሌ የአሁኑ የፌዴራል ካምፕ ፌት ለፊት እስከ1983 ዓም ድረስ ስንጠቀምበት የነበረውን የጋራ መጠቀሚያ ሽንት ቤት እና ማዕድ ቤት እንዲሁም መተላለፊያችንን መንገድ በማጥበብ የሬሳ ማውጫ እንኳን በማሳጣት በቦታው የቀድሞ የቤቱ ባለቤቶች በላያችን ላይ ሌላ ቤት ሰርተው እየተጠቀሙበት ይገኛል። የሚገርመው እነዚህ ቤቶች በ ላይ እንደሌሉ እና የኛ የቀድሞው የጋራ መጠቀሚያንና ባዶ ቦታን ነው የሚያሳየው። ይህንን ችግራችንን ለረጅም አመታት ለወረዳ 03 እና ለየካክከ ብናመለክትም መጥተው ከማየትና ከንፈር ከመምጠጥ በስተቀር ምንም አይነት መፍትሔ አላገኘንም። ብሎም ቅሬታችንን ለከንቲባ ለህዝብ ቅሬታ አመልክተን በስልክ እና በደብዳቤ በ15 ቀን ውስጥ መፍትሔ ሰጥታቹ አሳውቁን ቢባሉም ይሄው አመታትን አስቆጠርን። በ21ኛው ክፍለ ዘመን መሀል ከተማ ተቀምጠን በፖፖ እየተጠቀሙ አስፓልት ዳር እየተደፋ ለአካባቢው ሰው እና ለሕፃናት ችግር እየፈጠረብን ይገኛል። እንዲሁም የአካባቢው ሕፃናት ለተለያዩ በሽታዎች እየተዳረጉ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖብናል። ስለዚህ የሚመለከተው አካል ቦታው መጥታቹ በማየት መፍትሔን እንድታሰጡን ስንል በትህትና እናመለክታለን። ### Response:
### Text: ፌደራል ፖሊስ️ባለፉት 6 ወራት በርካታ ሽጉጥ ክላሽ በርካታ ጥይቶችቦንብ እና የቡድን መሳሪያ መትረጊስ በአራቱም አቅጣጫዎች ማለትም በደቡብ ሞያሌ በምስራቅ ቶጎ ውጫሌ በምዕራብ ጋንቤላ ሱዳን አዋሳኝበሰሜን ከሱዳን መተማ እና በቤንሻጉል ጉምዝ አካባቢ ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገባና ቱርክ ሰራሽ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡ ይህ ህገ ወጥ መሳሪያም በፌደራል ፖለስ ኮሚሽን የሀገር መከላከያ ሚንስቴር የቢሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት እና ከጉምሩክ ኮሚሽን እንዲሁም ከሰፊው ሰላም ወዳድ ህዝብ ጋር በመቀናጀት ከበፊቱ ጋር ሲነጸጸር ቀንሷል፡፡ሌላው ሊቀንስ የቻለበት ምክንያት ደግሞ በማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎትና በተቋሙ ሚዲየሞች አማካኝነት ህብረተሰቡ ስለ ህገወጥ መሳሪያ ዝውውር አስከፊነት በፌደራልና በክልሎች ደረጃ በማስተማር የህዝቡን ተሳትፎ በማሳደግ መቀነስ ተችሏል፡፡ በፍተሻ ኬላዎቹም ጥብቅ ፍተሻ ቢደረግም ከዋናው መንገድ ውጭ ባሉ መንገዶች በጋማ ከብትና በሞተር እያጓጓዙ ወደ አራቱም አቅጣጫዎች እንደሚያስገቡ ተገጸል። ይህን የሃገር ሰላም የሚያናጋ ህገ ወጥ የመሳሪያ ዝውውር ግጭት እንዳይባባስ ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ ያለውን ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል ሰላም የሰፈነባትና የተረጋጋች ኢትዮጵያን መፍጠር ይኖርበታል፡፡ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ### Response:
### Text: ኢትዮጵያን ከኤርትራ የሚያገናኘው የየብስ መንገድ በአዲስ ዓመት ይመረቃል ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በየብስ የሚያገናኛትን ግዙፍ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አጠናቃ፣ በመጪው መስከረም 1 ቀን 2012 ዓም እንደምታስመርቅ ተገለጸ፡፡0ባለፈው አመት ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ የተጀመረው የ90 ኪሜትር የመንገድ ግንባታ በአሁኑ ወቅት 90 በመቶ መጠናቀቁን የዘገበው ኤርትሪያን ፕሬስ ቀሪው 10 በመቶ በቀጣይ ሁለት ሳምንታት0 ውስጥ ይጠናቀቃል ብሏል፡፡0ኤርትራን ከኢትዮጵያ በየብስ እንደሚያገናኝ የተነገረለት ይኼው መንገድ ቀደም ሲል በ6 ሜትር ስፋት የተሰራ ሲሆን አሁን በተደረገው ማሻሻያና ተጨማሪ ግንባታ፣ በእጥፍ ጨምሮ፣ ከ12 እስከ 20 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጓል 25 አዳዲስ ድልድዮችም ተገንብተዋል ተብሏል፡፡በሁለቱ አገራት ግንኙነት ላይ ወሳኝ ሚና እንዳለው በሚነገርለት በዚህ የመንገድ ግንባታ ላይ በርብርብ የተሳተፉት 5 የኤርትራ የመንገድ ኮንስትራክሽን ኩባንያዎችን ጨምሮ የአገሪቱ መከላከያ ሀይል መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡0የመንገዱ እድሳትና ግንባታ አንድ አመት የፈጀ ሲሆን ሙሉ ወጭው በኤርትራ መንግስት መሸፈኑ ታውቋል፡፡ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የመንገድ ግንባታው በአዲሱ ዓመት መስከረም 1 እንደሚመረቅና አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ኤርትሪያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡ምንጭ ኤርትሪያን ፕሬስ ### Response:
### Text: ኬንያና ሶማሊያን ሲያወዛግብ በቆየው የባሕር ላይ ይዞታ ይገባኛል ጉዳይ ላይ ኔዘርላንድስ ዘ ሔግ የተሰየመው ዓለም አቀፉ የፍትህ ፍቤት ብይን ሰጠ።በተፈጥሮ ሀብት የታደለ ነው የተባለውን አወዛጋቢ የውቅያኖስ ላይ ግዛትን ሁለቱ አገራት እንዲካፈሉት ጉዳዩን የተመለከቱት ፍርድ ቤት አስር ለአራት በሆነ ድምጽ ውሳኔ ሰጥቷል።የባሕር ላይ ይዞታውን በተመለከተ ኬንያ በትይዩ ያለውን ድንበር ከሶማሊያ ጋር ከስምምነት ላይ መድረሷን ያቀረበችውን መከራከሪያ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል።በተጨማሪም በውቅያኖስ ክልሉ ውስጥ ኬንያ የነዳጅ ፍለጋና ቁፋሮ ተግባርን በማከናወን ዓለም አቀፍ ሕጎችን ጥሳለች በማለት ሶማሊያ ያቀረበችውን ክስ ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ የካሳ ጥያቄዋን ሳይቀበለው ቀርቷል።በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስር የሚገኘው ይህ ፍርድ ቤት የባሕር ጠረፍ ውዝግቡን በተመለከተ የሰጠው ውሳኔ በአብዛኛው የሶማሊያን ፍላጎት የሚያሟላ መሆኑ ተገልጿል።ቀደም ሲል ኬንያ ዓለም አቀፉን ፍርድ ቤት በወገንተኝነት በመክሰስ የሚሰጠውን ውሳኔ እንደማትቀበለው አሳውቃ ነበር።ሁለቱ አገራት በይገባኛል የሚወዛገቡበት በሕንድ ውቅያኖስ ላይ ያለው 100000 ስኩዌር ኪሎ ሜትሮችን የሚሸፍን የውሃ አካል ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ ዘይትና የተፈጥሮ ጋዝ አለበት ተብሎ ይታሰባል።መረጃው የቢቢሲ ነው። ### Response:
### Text: የዳዋ ዞን ነዋሪዎች ያሉበት ሁኔታ በሶማሊ ክልል ዳዋ ዞን የቦረና አጎራባች በተከሰተው ድርቅ የሞቱት የቁም እንስሳት 47215 መድረሳቸውን ከአንድ ሪፖርት መመልከት ችለናል። ሪፖርቱ የተዘጋጀው ከጥቅምት 25 እስከ 29 ቀን 2021 ባለው ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ዳሰሳ ሲሆን ይህም የተመራው በዳዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ በዳዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽቤት፣ ከዞኑ የአደጋ ስጋት አስተዳደር እና የዞን መንግስት ቢሮ እና የሰብአዊ እርዳታ አጋሮች ፣ ፣ ፣ ፣ ፣ ፣ ፣ ፣ ፣ እና እንዲሁም የወረዳ መምሪያ ቢሮዎች ጋር በመሆን ነው።በሪፖርቱ ላይ በዚህ ወቅት ይዘንባል ተብሎ የሚጠበቀው ዝናብ በመላው ዞኑ አልጀመረም። በሙባረክ ወረዳ ብቻ በሰባት ንኡስ መንደሮች በ31 መንደሮች ትንሽ ዝናብ የዘነበ ሲሆን የቀሩት 3 ወረዳዎች ምንም ዝናብ አላገኙም። በዳዋ ዞን ከሁሉም ወረዳ 95 ቀበሌዎች አብዛኛው የውሃ ምንጭ በመድረቁ የውሃ ማጓጓዣ የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ በጥቅምት ወር መጨረሻ ይደርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። የእንስሳት ገበያ ዋጋ በእጅጉ ቀንሷል። በአጠቃላይ በዞኑ 47215 የእንስሳት ሞት ተመዝግቧል። ግመሎች 5666 ከብቶች 4241 ፍየሎች 37057 በዞኑ በተከሰተው አስከፊ ድርቅ 10 ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። 62960 አርብቶ አደሮች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ባለው ድርቅ ምክንያት እንስሳት ማርባት አልቻሉም። ### Response:
### Text: ሳዑዲአረቢያ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በሪያድ የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን እቃዎች ከሱቆች እና ከመደብሮች እየሰብሰበ ይገኛል።የሳዑዲ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ያስተዋውቃል በሚል የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን አሸንጉሊቶች፣ ቲሸርቶች፣ የጸጉር ማስያዣዎች፣ ኮፊያ፣ እና የእርሳስ መያዣወችን ከየመደብሩ እንዲሰበሰቡ እያደረገ ነው።የሀገሪቱ መንግስት ህፃናትን ለመጠበቅ ሲል መርዛማ መልዕክት የያዙ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን የሚያስተዋውቁ ቀለም ያላቸውን እቃዎችን ከሱቅ እና ከመደብር እየሰበሰበ መሆኑን ገልጿል።አንድ ከፍተኛ ባለስልጣን እቃዎቹ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነውን ማህበረሰብ ሞራልና እሴት የሚጻረሩ እንዲሁም አዲሱን ትውልድ ለተመሳሳይ የፆታ ግንኙነት የሚያበረታቱ ናቸው ብለዋል።የሳዑዲ ንግድ ሚኒሰቴር በትዊተር ገፁ እቃዎቹን የመሰብሰብ ዋና ትኩረት ለሳውዲ ህዝብ እሴቶች የማይመጥን ቀለም ያላቸው እቃዎች ማስወገድ ነው ብሏል። ሚኒስቴሩ መሰል እቃዎችን ሲሸጡ በሚገኙ ሱቆች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።ከዚህ ባለፈ ሳዑዲ አረቢያ በቅርቡ ሁለት የዲስኒ እና ማርቭል ፊልሞችን የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ያስተዋውቃሉ በሚል አግዳለች። በሳዑዲ አረቢያ ምድር የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ህገወጥ ሲሆን እስከሞት ድረስ ያስቀጣል።ቪድዮ ### Response:
### Text: ዛሬ ላይ ሁሉንም ነገር ማመን ነው ያቃተኝ ከትላንት በስቲያ ምሽት በአዲስ አበባ ሀዋሳ ፈጣን መንገድ ላይ መቂ አካባቢ በታጣቂዎች ተኩስ እህት እና ወንድም መገደላቸው እና ሌሎችም መቁሰላቸውን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ከሻሸመኔ ማሳወቃቸው ይታወቃል።ከደቂቃዎች በፊት አንድ የቤተሰባችን አባል ሟቾች አብሮ አደጎቹ እንደሆነ ገልጿል። አብሮ አደጎቼ ናቸው ዛሬ ላይ ሁሉንም ነገር ማመን ነው ያቃተኝ ያለው ይኸው ቤተሰባችን የዚህ አይነት አስደንጋጭ ድርጊቶች ዜጎች በሰላም እና ደህንነታቸው ላይ ማስተማመኛ እንዳይኖራቸው እንደሚያደርግ ገልጿል። መንግስት መቼ የዜጎችን ህይወት እንደሚታደግ አምላክ ይወቀው ሲልም ሀዘኑን እና በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የዜጎችን ህይወት መታደግ ባለመቻሉ እና ብዙ ተስፋ ያላቸውን ሰዎች እየነጠቁ ባሉ ጥቃቶች እየደረሰ ያለውን ጉዳት ማስቆም ባለመቻሉ ያደረበትን ቅሬታ ገልጿል።ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ታጣቂዎች በሚፈፅሙት ጥቃት የበርካታ ንፁሃን ሰዎች ህይወት መጥፋቱ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት የፀጥታ ችግር ባላባቸው ቀጠናዎች ንፁሃን እንዳይገደሉ ፣ ንብረት እንዳይዘረፍ ፣ ዜጎች ከቄያቸው እንዳይፈናቀሉ፣ ንብረት እንዳይወድም የደህንነት ስጋት በሆኑ ጉዳዮች ላይ ዘላቂ መፍትሄ እና እርምጃ እንዲወስድ ቤተሰቦቻችን ሲጠይቁ እንደነበር ይታወሳል። ### Response:
### Text: አዲሱ የብር ኖት መሰራጨት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ከ46 ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የግል ባንክ ቅርንጫፎች መሰራጨቱ ተገልጿል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብሔራዊ ባንክን በመወከል አዲሱን የብር ኖት ለግል ባንኮች ጭምር በማሰራጨት ላይ ነው። አዲሱን የብር ኖት ማሰራጨት ከተጀመረ ከመስከረም 62013 ዓ ም ጀምሮ አስካሁን ባለው ጊዜ ከ46 ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የግል ባንክ ቅርንጫፎች ተሰራጭቷል። ከዚህ ውስጥ 28 ቢሊዮን ብር ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ተሰራጭቷል። 22 ቢሊዮን አሮጌው የብር ኖት ወደ ማዕክል ገቢ ተደርጓል። 5 ሺ ብር እና ከዛ በላይ ይዘው ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብር ለመለወጥ የሚመጡ ደንበኞች የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በሚያዘው መሠረት በቁጥር 63 ሺ ደንበኞች አዲስ የባንክ አካውንት ከፍተዋል ከ 64 ቢሊዮን ብር በላይ ተቆጥቧል። በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጰያ ንግድ ባንክ 3700 ኤቲኤም ማሽኖች በሙሉ ማለት በሚያስችል ደረጃ አዲሱን የብር ኖት እንዲከፍሉ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል። ከመቶ ሽ ብር በላይ ብር ለሚቀይሩ ደንበኞች ዛሬ ጥቅምት 1 2013 ጨምሮ በቀሩት 5 ቀናት ውስጥ ሰንበትን ጨምሮ በመስራት ላይ ወዳሉት የኢትዮጰጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች በመምጣት በቀነ ገደቡ ሊጠቀሙ ይገባል። ### Response:
### Text: ፍቅር እስከ መቃብር️በአምቦ ከተማ ለ70 ዓመታት በትዳር ተሳስረው የቆዩት አጋሮች በአንድ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ዐርፈዋል ፡፡የአቶ ጉርሜሣኢሬንሶና ወይዘሮ ጉዲሴቂጣታ በአምቦ ከተማ ቀበሌ 03 ነዋሪዎች ነበሩ ለሰባት አሥርታት የዘለቀው ትዳራቸው ባለፈው ዓርብ እስኪያበቃ ድረስ፡፡ በዚህ በረጅም የትዳር ቆይታቸው 18 ልጆችን አፍርተዋል በርካታ የልጅ ልጆችንም አይተዋል፡፡አቶ ጉርሜሣ ኢሬንሶ የ101 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ ነበሩ። ባለቤታቸው ወይዘሮ ጉዲሴ ቂጣታ ደግሞ በዚህች ምድር የኖሩት ለ85 ዓመታት ነበር፡፡ባልና ሚስቱ በትዳር ያሳለፏቸው ዘመናት ፍቅር የተሞላባቸው እንደነበሩ ወዳጆቻቸውና ጎረቤቶቻቸው ይናገራሉ፡፡እነኚህ የዕድሜ ባለጸጋ ባልና ሚስት በእርጅና ምክንያት አልጋ ላይ ከዋሉ ጥቂት ወራት እንዳስቆጠሩ የቤተሰቡ አባል አቶ በፍቃዱ ማዴሳ ለኢ ዜ አ ሪፖርተር ገልጸውለታል፡፡የትዳር አጋሮቹ የካቲት 14 ቀን 2011 ዓመተ ምህረት በተመሳሳይ ሰዓት እኩለ ሌሊት ላይ ይህቺን ዓለም ተሰናብተዋል፡፡አቶ ጉርሜሳ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሲያርፉ፣ከግማሽ ሰዓት በኋላ ደግሞ በሌላው የመኖሪያ ክፍል አልጋ ይዘው የነበሩት ባለቤታቸው ተከትለዋቸዋል።የባልና ሚስቱ የቀብር ሥነሥርዓት ትናንት በአምቦ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ እውነተኛው ፍቅር እስከ መቃብር ይሄን ይመስላል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: የሲዳማ ክልል ምስረታና የስልጣን ርክክብ ቀን የሲዳማ ክልል ምስረታ እና የስልጣን ርክክብ ቀንን ምክንያት በማድረግ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በዓሉ በታላቅ ድምቀት ከሚከበርበት ከአዲሱ ኢንተርናሽናል ስታዲየም መነሻውን ያደረገ የስታዲየሙን ዙሪያ እንዲሁም የከተማ ማፅዳት ስራ መጀመሩን አቶ ዘሪሁን ሰለሞን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ገልፀዋል፡፡ የሲዳማ ብሔር እራሱን በራሱ ለማስተዳደር ህዝበ ውሳኔ በማካሄድ በነፃ ፍቃዱ ህገመንግስታዊ መብት መጎናፀፉን ተከትሎ የአዲሱ የሲዳማ ክልል ምስረታ እና የስልጣን ርክክብ ስራ በመከናወን ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ ዘሪሁን የስልጣን ርክክብ ስራው ሲጠናቀቅ ታላቅ ህዝባዊ የደስታ መግለጫ ፕሮግራም እንደሚኖርም አስታውሰዋል፡፡ለአዲሱ ክልል ምስረታ እና ለስልጣን ርክክብ ስራ ከተዋቀረው ኮሚቴ አንዱ በሆነው የቦታ መረጣ እና ዝግጅት አስተባባሪ ኮሚቴ አማካኝነት ዛሬ የተጀመረው የፅዳት ስራ ሀዋሳ ከተማ ወትሮም የምትታወቅበትን ውብ፣ፅዱ አረንጓዴ እና ምቹ ከተማነቷን በማስቀጠል በዓሉ በሚከበርበት ዕለት መላው የደስታው ባለቤት እና ተካፋይ ህዝብ እንዲሁም እንግዶችን ማራኪ በሆነ መንገድ ለማስተናገድ ከሚያስችሉ የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ውስጥ አንዱ መሆኑን ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ### Response: