text
stringlengths
707
989
### Text: የግል ትምህርት ቤቶች ምንም አይነት ተጨማሪ ክፍያ ማድረግ እንደማይችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀየ2013 ዓም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ከነሃሴ 20 ጀምሮ እንዲከናወን ትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁን ተከትሎ ከተማሪዎች ምዝገባ እና ከትምህርት ክፍያ ጋር ተያይዞ ወላጆች ቅሬታን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ይህንን ተከትሎ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የትምህርት ቤት ምዝገባ ክፍያ መመሪያን ተላልፈው ምዝገባ እያከናወኑ ያሉ ትምህርት ቤቶች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ከመመሪያ ውጪ የሰበሰቡትን ገንዘብ ለወላጆች ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡ ሚኒስተር ዴኤታዋ አክለውም የ2013 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ላይም ምንም አይነት የክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደማይቻል እና እንደሚያስጠይቅም ተናግረዋል፡፡ትምህርት ቤቶች ምዝገባ ሲያከናውኑ ከዚህ በፊት ይጠቀሙበት የነበረውን የክፍያ አቀባበል ዘዴ መቀየር የማይችሉ መሆኑን እና ከዚህ በፊት በነበረው የክፍያ ስርዓት መቀጠል እንዳለባቸውም ተገልጿል።፡ከዚህም በተጨማሪ ትምህርት ቤቶች ከመደበኛ የትምህርት ክፍያ እና ከመመዝገቢያ ክፍያ ውጪ ሌሎች ተጨማሪ ክፍያ ማስከፈል ማይቻል መሆኑም ተነግሯል፡፡ምንጭ ትምህርት ሚኒስቴር ### Response:
### Text: ይበቃል ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ያሉ ዜጎቻችን ፍትህን እንዲያገኙ የሚጠይቅ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተካሄደ ነው።ዘመቻው ሳዑዲ ያሉ ዜጎቻችን እምነበረድ ላይ ለብሰው የሚተኙትን ጥቁር ፌስታል በመልበስ አጋርነት የሚገለፅበት ነው።ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በርካታ ዜጎቻችን እጅግ አስከፊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ይታወቃል።የሳኡዲ አረቢያ መንግስት መሰረታዊ የእስረኛ አያያዝ ህግን እንዲተገብር፣ ፍትሃዊ የሆነ ምላሽም እንዲሰጥ የሚጠየቅበት የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ነው እየተካሄደ ያለው።ዘመቻው ከተጀመረ ሳምንታት ተቆጥረዋል። በሳዑዲ አረቢያ ስላሉት ወገኖች የሰማነው ተስፋ ሰጪ ዜና እስካሁን የውሀ ሽታ እንደሆነ ነው።የማህበራዊ ሚዲያው ዘመቻው በሳዑዲ አረቢያ ላሉት ወገኖች ድምፅ የሚኮንበት፣ ዜጎቻችን ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ድምፅ የሚኮንበት ፣ በሳዑዲ መንግስት ላይ ጫና ለማሳደር መሰረታዊ የሆነው የእስረኞች አያያዝን ተግባራዊ እንዲያደርግም ግፊት የሚደረግበት ነው።የአረብኛ ቋንቋ ተናጋሪ የሆናችሁ ውድ የኢትዮጵያ ልጆች በይበልጥ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የሳዑዲ አረቢያ ባለልስጣናት እና የዓለም መንግስታት የዜጎቻችንን ስቃይ እንዲያውቁ መልዕክቶችን በማጋራት ድምፅ ሁኑ። ይበቃል ጥቁርፌስታል الحريةللسجناءالاثيوبيين العدالةللسجناءالاثيوبيين ፎቶ ሶሻል ሚዲያ ### Response:
### Text: የዶር ጥላዬ ጌቴ ማብራሪያ አፕቲትዩድን በሚመለከት የሁለቱ ቡክሌቴች የመልስ መፍቻ ችግር እንዳለበት ዛሬ ተረጋግጧል። በተሻሻለውና በተስተካከለው የመልስ ቁልፍ እርማቱ እየተካሄደ ነው።329000 ተማሪዎች ተፈትነዋል ከነሱ ውስጥ ከ100 እስከ 150 ሺህ ተማሪዎች ውጤት ለውጥ ያመጣል ብለን እንገምታለን። ለውጥ ብቻ ሳይሆን በተለይም በጣም ጎበዝ ተማሪዎች ከ600 በላይ የሚያመጡ ሊኖሩ ይችላሉ። ተማሪዎችና ወላጆች በተፈጠረው ችግር ይቅርታ እየጠየቅን በትዕግስት እንዲጠብቁን እንጠይቃለን በተወሰኑ ቀናት ውስጥ ታርሞ ትክክለኛው ውጤት ለተማሪዎቹ ይገለፃል ከአፕቲትዩድ ውጪ የሌሎችን ችግሮች በተመለከተ ዛሬ ባለን መረጃ ከኤጀንሲው 3 ሺ የሚሆኑ ተማሪዎች ኦንላይን ቅሬታቸውን አቅርበዋል 6 ሺ የሚሆኑ በአካል በፅሁፍ አቅርበዋል። በአጠቃላይ ወደ 9 ሺ ተማሪዎች ቅሬታቸውን አቅርበዋል የነሱም በደንብ ይታያል።ተማሪዎችና ወላጆች እዚህ ከሚመጡ ኦንላይ በተዘረጋው ስርዓት ቅሬታቸውን ቢያቀርቡ በእርግጠኝነት መልስ ይሰጣቸዋል። የታገደባቸውን ተማሪዎች በሚመለከት በአጠቃላይ ፈተናው ምን ላይ ነው ችግሩ ከፈተናው ነው ከተማሪዎች ነው ከአፈታተኑ ነው ምን ላይ ነው ችግሩ የሚለውን ለማጥናት አንድ ሀገራዊ ግብረ ኃይል አቋቁመን እያጣራው ይገኛል በቅርቡ የሚገለፅ ይሆናል። ### Response:
### Text: ኅብረተሰቡ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ከግምት በማስገባት አሁንም የሚያደርገውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ዶክተር ሊያ ታደሰ አሳሰቡ።ባለፉት 24 ሠዓታት ብቻ 17 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ያሳዘናቸው የጤና ሚኒስትር ዶር ሊያ በዚህም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር አስመዝግባለች ብለዋል።እስከሁን የተመዘገቡትና የተገለጹት ቁጥሮች ትክክለኛ አሃዝ እንደማያሳይ ገልጸው የምናውቀው የመረመርነውን ብቻ ነው፣ የመረመርነው ደግሞ ትንሽ ነው ሲሉ ተናግረዋል።ስለዚህ ወረርሽኙን መርሳትና መዘናጋት እንደማይገባ እና ኅብረተሰቡም ቁጥሩ ያነሰው በሽታው እኛ ጋር ስላልመጣ ወይንም ስለማይመጣ እንዳልሆነ ሊገነዘብ እንደሚገባ አሳስበዋል።በኬንያ እና በሱዳን በመጀመሪያዎቹ ቀናት ትንሽ ቁጥር ማስመዝገባቸውን ተከትሎ መዘነጋት መታየቱን አስታውሰው ዋጋ አስከፍሏቸዋል ብለዋል።ሕዝቡም ከጎረቤት አገሮች መዘናጋት ትልቅ ችግር ሊያመጣ እንደሚችል በመማር የሚደረጉትን ጥንቃቄዎች ማጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል።ትክክልኛ ትምህርትና እርምጃ ለመውሰድ ፣ በብዙ ቁጥር መያዝ ፣ በብዙ ቁጥር መሞት የለብንም ያሉት ሚኒስትሯ ያለው ብቸኛ አማራጭ መጠንቀቅ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ደቡብ ጎንደር️በደቡብ ጎንደር ዞን ትናንት ምሽት አንድ መስጂድ ላይ የእሳትአደጋ ደረሰ። በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ጃራ ገዶ አካባቢ አደጋው የደረሰው ትላንት ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ነው፡፡የአማራ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩአላምረው እንደተናገሩት የቃጠሎ አደጋው በጨለማ መፈፀሙ ከድርጊቱ ጀርባ የተደራጀ ቡድን መኖሩን ያመላክታል፡፡ ይህም የዳር አገሩን ግጭት ወደ መሃል አገር ለማምጣት ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ክልሉ መገንዘቡን አቶ መላኩ ተናግረዋል፡፡ክልሉ የአደጋውን ሁኔታ የሚከታተል አጣሪ ቡድን ወደ ስፍራው መላኩንም አመልክቷል፡፡ ቃጠሎ የደረሰበትን መስጂድ ለማጥፋት የአካባቢው ህብረተሰብ ርብርብ ማድረጉንና መስጅዱን መልሶ ለመገንባት ገንዘብ በማሰባሰብ ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘ በደቡብ ጎንደር እስቴ ላይ በሁለት መስጅዶች ቃጠሎ ጋር በተያያዘ እጃቸው አለበት የተባሉ 6 ተጠርጣሪዎችን የክልሉ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መላኩ ገልጸዋል፡፡ከመስጊድ ቃጠሎው ጀርባ በአካባቢው የሚንቀሳቅስ ህቡዕ ቡድን መኖሩ እንደተደረሰበትና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ክልሉ እየሰራ መሆኑን ምክትል ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: የህግጉዳይ ከክልል ፍርድ ቤቶች እስከ ፌዴሬሽን ደርሶ ወደ ከፍተኛ የተመለሰው የንብረት ክርክር መጨረሻ ምን ይሆን በሪፖርተር ጋዜጣ አሳዬ ቀፀላከ10 ዓመታት በፊት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓም0በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነበር ክርክሩ የተጀመረው።የክርክሩ መነሻ፣ በኦሮሚያ ክልል በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ጌትእሸት ዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሽያጭ ነው፡፡ ድርጅቱ የእነ ጌታቸው እሸቱ ኢንጂነር አራት ሰዎች ሲሆን፣ ጠቅላላ የቦታው ስፋት 11305 ካሬ ሜትር ነው፡፡የዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ፋብሪካው ያረፈው በ3015 ካሬ ሜትር ላይ ሲሆን፣ ስመ ሀብቱ የተመዘገበው በጌታቸው እሸቴ ኢንጂነር ስም ነው፡፡ ቀሪው 8290 ካሬ ሜትር ደግሞ ጅምር ግንባታ ያለበት ሆኖ፣ ስመ ሀብቱ ካርታው የተመዘገበው በጌትእሸት ዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስም ነው፡፡ ፋብሪካውንና ጅምር ግንባታ ያረፈበትን በሁለት የተለያዩ ስሞች የተመዘገቡ ይዞታዎች ሁለት ይዞታዎች እነ ጌታቸው ኢንጂነር አራት ሰዎች ለእነ ዶር በዕውቀቱ ታደሰ ከአሥር ዓመታት በፊት ኅዳር 18 ቀን 2005 ዓም በ22500000 ብር ሸጠውላቸዋል፡፡ የሽያጭና የግዥ ውሎች የኢትዮጵያ ፍትሐ ብሔር ሕጎችን ሒደት በጠበቀ ሁኔታ ተፈጽመዋል፡፡ ያንብቡ 0806 ### Response:
### Text: የአፕል የገበያ ድርሻ ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ በ200 ቢሊዮን ዶላር ቀነሰ።ከሰሞኑን የቻይና መንግሥት የአፕል ምርት የሆነውን አይፎንን ማገዱ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ተዘግቧል።እገዳው ምናልባት ከደህንነት ጋር ሊያይዝ ይችላል ተብሏል።ይህን እገዳ ተከትሎ የአፕል የገበያ ድርሻ ለ2 ተከታታይ ቀናት ቅናሽ ማሳየቱ ተነግሯል።የድርጅቱ የድርሻ ገበያ ከ6 በመቶ በላይ የቀነሰ ሲሆን ይህም ማለት በ200 ቢሊዮን ዶላር ባለፉት ሁለት ቀናት ቀንሷል።ቻይና የአፕል ምርቶች ሦስተኛዋ ትልቁ ገበያ ስትሆን ከዓመታዊ ገቢው 18 የሚገኘውም ከቻይና ገበያ ነው።ግዙፉ የአፕል ምርቶች አምራች የሆነው ፎክስኮን በርካታ የአፕል ምርቶችን የሚሠራው በቻይና ነው።ዋል ስትሪት ጆርናል እንደዘገበው የማዕከላዊ ቻይና መንግሥት ሠራተኞች አይፎን ለሥራ እንዳይጠቀሙና መቤት ይዘውም እንዳይሄዱ ታግደዋል።ብሉምበርግ እንደዘገበው ዕገዳው በመንግሥት የሚተዳደሩ ተቋሞችን እንዲሁም መንግሥት የሚደግፋቸውን ተቋሞችም ይጨምራል።ስለዘገባዎቹ ከቻይና መንግሥት የተሰጠ ምላሽ የለም። ይህ በቻይና መንግሥት ይፋ የተደረገው ዕገዳ የተጣለው አይፎን 15 ከመውጣቱ ከ5 ቀናት በፊት ነው።አፕል የዓለም ትልቁ የስቶክ ገበያ ያለው ሲሆን፣ ገበያው ወደ 28 ትሪሊዮን ዶላር ይደርሳል።መረጃው የቢቢሲ ነው። ### Response:
### Text: ዓለም አቀፍ ለጋሾች ያቆሙት የምግብ ርዳታ ይቀጥል ዘንድ በጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ እና በአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን መካከል የስልክ ውይይት ተደረገ።የሚኒስቴር መቤቱ ቃል አቀባይ ማት ሚለር እንዳሳወቁት ብሊንከን ከጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ ጋር የስልክ ውይይት አድርገዋል።በዚህ ውይይት ወቅትም ዓለም አቀፍ ለጋሾች ያቆሙት የምግብ ርዳታ ይቀጥል ዘንድ ፣ የሰብአዊ ሁኔታ ቁጥጥር ተሻሽሎ ስለሚቀጥልበት አሠራር ላይ ተወያይተዋል።በተጨማሪ አንተኒ ብሊንከን፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ አሳስቦኛል 0 ሲሉ ተናግረዋል።በሁለቱ ክልሎቹ ያሉትን ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት፣ የፖለቲካ ውይይትንና የሰብአዊ መብቶች መከበር አስፈላጊነትን አጽንዖት ሰጥተውበታል።እውነተኛ ፣ ታማኝ እና ሁሉን አካታች የሽግግር ፍትሕ ሒደትን ለመፍጠር እየተከናወነ ያለውን ሥራ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመልካም እንደተቀበሉት ተጠቁሟል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከንና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አሕመድ፣ በአፍሪካ ቀንድ ስለሚታየው የጸጥታ ተግዳሮት፣ እንዲሁም አንዲት፣ ሰላማዊት እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት ያላቸውን የጋራ ግብ አስመልክቶም እንደተወያዩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መቤትን ዋቢ በማድረግ ቪኦኤ ዘግቧል። ### Response:
### Text: ለጉምሩክ ሰራተኞች ጉቦ ሰጥቼ መኪኖችህን አስለቅቃለሁ በሚል 1 ሚሊዮን ብር ቼክ ሲቀበል የነበረ ትራንዚተር እጅ ከፍንጅ ተይዟል ፌዴራል ፖሊስ ጉቦ ሰጥቼ መኪኖችህን አስለቅቅልሃለሁ ብሎ ከባለ ጉዳይ የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበል የነበረ አንድ ትራንዚተር እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ጉቦ ሰጥቼ መኪኖችህን አስለቅቅልሃለሁ ብሎ ከባለ ጉዳይ የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበል የነበረ አንድ አስተላላፊ ትራንዚተር ህዳር 30 ቀን 2016 ዓም ከነኤግዚቢቱ በአዲስ አበበ ከተማ አቃቂ ቃልቲ ክፍለ ከተማ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ተገልጿል።ትራንዚተሩ የተያዘው ለጉምሩከሠራተኞች ጉቦ ሰጥቼ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተያዙ መኪኖችህን አስለቅቅልሃለሁ በማለት ጉቦ እንደሚሰጥ አስመስሎና አታሎ ከባለጉዳይ የ1 ሚልየን ብር ቼክ ሲቀበል የኢትዮጵያ ፌዳራል ፓሊስ ወንጃል ምርመራ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አባላት ጋር በመሆን ባደረጉት ክትትል እጅ ከፈንጅ ከነቼኩ ተይዘው በቁጥጥር ሥር ሊውሉ ችለዋል።ኅብረተሰቡ በመሠል ግለሰቦች እንዳይታለል ጥንቃቄ እንዲያደርግና በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ቡድኖችንም ሲያገኝ ጥቆማ እንዲሰጥ የኢትዮጽያ ፌደራል ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል። ### Response:
### Text: በጎረቤት ሀገር ደቡብ ሱዳን ምን ተፈጠረ ደቡብ ሱዳን ውስጥ የተጠራውን የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ ዛሬ የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጧል ጎዳናዎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች ሲዘዋወሩ ውለዋል።ፕሬዚደንት ሳልቫ ኪርን ለመቃወም ተቃውሞ ሰልፉ ጥሪ ተከትሎ ነዋሪዎች በየቤታቸው በመከተታቸው ጎዳናዎች ከወትሮው ጭር ብለው ነው የዋሉት።መንግሥትን ለመቃወም ዛሬ በተጠራው ሰልፍ ላይ ሰዎች እንዳይገኙ የሀገሪቱ ፖሊስ አሥጠንቅቆ ነበር።ባለፈው ሐምሌ ወር በሀገሪቱ ለውጥ እንዲመጣ የሚጠይቅ ዘመቻ ሲመራ የቆየው፣ ራሱን ቅንጅት ለህዝባዊ እርምጃ ብሎ የሚጠራው ቡድን የተቃውሞ ሰልፉን የጠራው በፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር የሚመራው ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ ዜጎች ለገጠሟቸው በርካታ ችግሮች ተገቢውን ምላሽ አልሰጠም በማለት ነው።ቡድኑ ስለተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ለፖሊስ በደብዳቤ ማሳወቁን ቢገልፅም የፖሊስ ቃል አቀባይ ሜጀር ጀነራል ዳንኤል ጀስቲን የተቃውሞ ሰልፉ በህዝቡ ዘንድ አለመረጋጋት ስለሚፈጥር ባለስጣናቱ በቸልታ የሚያልፉት አይሆንም ሲሉ መከልከሉን አስታውቀዋል።ፕሬዚደንቱ በሃገሪቱ ፓርላማ መከፈቻ ንግግር እንደሚያደርጉ የተገለጸ ሲሆን የተቃውሞ ሰልፉ አደራጆች ሰልፉን በማካሃድ አቋማቸው እንደጸኑ ትናንት በድጋሚ አሳውቀው እንደነበር ቪኦኤ አስነብቧል። ### Response:
### Text: መስከረም 30 ቀን 2015 መሰጠት የሚጀምረው የ2014 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ ወጥቷል በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆነን0 የትምህርት ምዘናና0ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።የአገልግሎተ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከፈተና ስርቆት ጋር በተያያዘ እተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል።በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የዘንድሮ ነው ተብሎ የሚሰራጨው ፈተና በ201314 2021 ዓም የተሰጠ እንደሆነ አስረድተዋል። እየተሰራጩ ያሉት ፈተናዎች ዓመቱ ኤዲት ተደርጎ መሆኑንም አመልክተዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ መሰል መረጃዎችን ከማመናቸው በፊት የአሰራጩን ታማኝነት እንዲያጣሩና ትክክለኛነቱን እንዲመረምሩ መልዕክታቸውን አስተላፈዋል።የአገር አቀፍ ፈተናን የተመለከቱ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ፖለቲካን ከታዳጊዎች ህይዎት ቢለዩ መልካም ነው ሲሉ ለ ኢትዮጵያ ቼክ መረጃ አጣሪ ድረገፅ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።የ2014 ዓም የሀገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 302015 ዓም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሁለት ዙር የሚሰጥ ይሆናል።ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንደሰማነው ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ይገኛል ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ተብሏል። ### Response:
### Text: ፈተናው የምርጫ ጥያቄዎችን የያዘ ነው ትምህርት ሚኒስቴርትምህርት ሚኒስቴር ከመስከረም 28 እስከ 30 2016 ዓም በሀገር ደረጃ የሚሰጠው የድህረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና ወጥ በሆነ መንገድ በአንድ የፈተና መተግበሪያ የሚከወን መሆኑን ገልጿል።ፈተናው ምርጫጥያቄዎችን የያዘ ነው ብሏል።ለፈተናው 53 የፈተና ማእከላት እና 84 የፈተና ጣቢዎች የተዘጋጁ ሲሆን በግማሽ ቀን ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል ተብሎ ታቅዷል።አይነስውራን ተፈታኞች የቃል እና ምክንያታዊ አስተሣሠብ ክህሎቶቻቸው ላይ ያተኮሩ ፈተናዎችን ይወስዳሉ ያለው ሚኒስቴሩ በወሠዱትም ፈተና ከ100 ይመዘናሉ ብሏል።ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ጥያቄዎች አመልካቾች መርጠው በሚያመለክቱበት የትምህርት መስክ ላይ ትኩረት ያደረገ እንዳልሆነ ትምህርት ሚኒስቴትር ገልጿል።ትምህርት ሚኒስቴር የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ዓላማ በግል እና በመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው የድህረ ምረቃ ትምህርት በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ገብቶ ትምህርት ለመከታተል ፍላጎት ያላቸውን አመልካቾች ብቃት ለመመዘን ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች የሚገቡ ተማሪዎች ሂሣባዊ ትንተና ፣ ምክናያታዊ አስተሳሠብ ፣ የቃልና የጹህፍ ከህሎት ለመመዘን ነው ሲል አስታውሷል። ### Response:
### Text: ዶክተር አብይስዊዘርላንድየኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ስዊዘርላንድ ዳቮስ ገቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስዊዘርላንድ ዳቮስ በሚካሄደው የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ላይ ለመሳተፍ ነው ወደ ስፍራው ያቀኑት።በፎረሙ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዓለም ሃገራት መሪዎች በተገኙበት ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።በንግግራቸውም በኢትዮጵያ ባለፉት 10 ወራት ስለተደረጉ ማሻሻያዎችና ለውጦች ያነሳሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው።የተለያዩ ሃገራት እና ቢዝነስ መሪዎች በስዊዘርላንዷ ዳቮስ ከተማ በየአመቱ በመገናኘት በወደፊቱ የዓለም ኢኮኖሚ ሁኔታ ላይ ይመክራሉ።ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከትናንት በስቲያ ወደ ጣሊያን በማምራት በሮም የሁለት ቀናት ቆይታ ማድረጋቸው ይታወሳል።በጣሊያን በነበራቸው ቆይታም ከጣሊያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ጁሴፔ ኮንቴ ጋር ስኬታማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።ከዚህ ባለፈም ካጣሊያኑ ፕሬዚዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።በተጨማሪም ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች ጋር እንዲሁም ከሮማው ሊቀጳጳስ አቡነ ፍራንሲስ ጋር በመወያየት የጣሊያን ቆይታቸውን አጠናቀው ዛሬ ዳቮስ ገብተዋል።ምንጭ ኢፕድ ### Response:
### Text: ህዳር14 ኮሞሮስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሞሮሱ አደጋህዳር 141989 ዓም ልክ በዛሬዋ ቀን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 767260 አውሮፕላን በዋና ካፒቴን ልዑል አባተና በረዳት አብራሪው ዮናስ መኩሪያ እየተመራ 175 ተጓዦችንና የበረራ ቡድን አባላትን በመያዝ ወደ ናይሮቢ ለመጓዝ ነበር ከአዲሰ አበባ ተነሳ፡፡በጉዞው መሃል ሦስት ኢትዮጵያዊያን ሰዎች አውሮፕላኑን በመጥለፍ አውስትራሊያ አድርሱን ካልሆነ ይህን ቦምብ እናፈነዳዋለን አሏቸው፡፡ ነገር ግን አውሮፕላኑ ናይሮቢ የሚያደርሰውን ነዳጅ ብቻ ሞልቶ ነበር የተነሳው፡፡ ታዲያ ወደ መጀመሪያ መዳረሻው ናይሮቢ የሁለት ሰዓት ተኩል ጉዞ ለማድረግ የተነሳው አውሮፕላን ከአራት ሰዓት በላይ አየር ላይ በመቆየቱ ነዳጁን ጨረሰ በመጨረሻም በህንድ ውቅያኖስ በኮሞሮስ ደሴት ውሃ ላይ ተከሰከሰ፡፡ በአደጋው 125 ሰዎች ሲሞቱ ሁለቱን አብራሪዎችን ጨምሮ 50 ሰዎች ተርፈዋል፡፡ ሶስቱ ኢትዮጵያውያን ጠላፊዎችም ከሞቱት መካከል ናቸው።በጊዜው የጠላፊዎቹን ከፍተኛ የአካልና የአዕምሮ ጥቃት ተቋቁመው ውሃ ላይ ማሳረፍ በመቻላቸው ካፒቴን ልዑል አባተና ረዳት አብራሪው ዮናስ መኩሪያ ከፍተኛ አድናቆት አግኝተው ነበር፡፡ እሁድን 23 ዓመታት ወደኋላ ተመልሶ ያስቃኘንን የአማርኛ ክፍል ዝግጅት አመሰገንን፡፡ ### Response:
### Text: በቲክቫህ ቤተሰቦች ስምበፍሬወይኒ መብርቶም የክብር አቀባበል ላይ ተገኝተን በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በተለይም የቤተሰባችን አባላት በሆኑ ወጣቶች ስም በገንዘብ ሲተመን 5000 ብር የሚያወጣ ሞዴስ እገዛ አድርገናል። እገዛችን በጣም ትንሽ እንደሆነች ብናውቅም ለሌሎች ወጣቶች መነሳሳትን ለመፍጠር ያህል ነው። የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በተለያዩ በጎ ስራዎች ላይ ስንሳተፍ ለበርካቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለመልካም ስራም መጠቀም እንደምንችል ለማስታወስ ያህል ነው በያላችሁበት ከግንዛቤ ጀምሮ እስከ ቁሳቁስ የምታበረክቱት አስተዋጽኦ የብዙዎችን ህይወት ይለውጣል ብለን እናምናለን፡፡ በመላው ቤተሰቦቻችን ስም ለ2019 የ ጀግና ፍሬወይኒ መብርሃቱ በድጋሚ እንኳን ደስ አለሽ እንኳን ደስ አለን ለማለት እንወዳለንበነገራችን ላይ ዩኔስኮ ባጠናው ጥናት መሰረት በሀገራችን 75 የሚሆኑ ሴቶች በቂ ንጽህና መጠበቂያ አያገኙም 50 የሚሆኑ ተማሪዎች በዚሁ የተነሳ ከትምህርት ገበታቸው ይስተጓጎላሉ፡፡ ስለ ሴቶች የወር አበባ አሁንም ድረስ ማህበረሰባችን ካለው አመለካከት ላይ የኢኮኖሚ ጫናው ተደምሮ ለበርካታ ሴት እህቶቻችን ከትምህርት መስተጓጎል እስከማቋረጥ ምክንያት ሆኗል፡፡ እናተም በየክፍለ ከተማው በመገኘት አግዙእያንዳንዳችን ለውጥ ማምጣት እንችላለን ### Response:
### Text: በጉራ ፈርዳ ወረዳ 12 ሰዎች ተገደሉ ጥቅምት 82013 ምሽት 300 ገደማ ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ማንነታቸው ያልታወቀ የተደራጁ ወንጀለኞች ባደረሱት ጉዳት የ12 ሰዎች ህይወት መጥፋቱ እና በ5 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን ደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነብዩ ኢሳያስ አሳውቀዋል።ኮሚሽነር ነብዩ የአካባቢውን ሰላም ወደ ነበረበት ለመመለስ ተጨማሪ የፀጥታ አካላት ወደ አካባቢው መግባቱን ገልጸው ጉዳት የደረሰባቸው ወደ ህክምና መወሰዳቸውን ለደቡብ ኤፍ ኤም 1009 ተናግረዋል፡፡ ህብረተሰቡ ለፀጥታ ሀይሎች መረጃዎች በመስጠት ትብብር በማድረግ ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ የሚሰረውን ስራ እንዲያግዝ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል፡፡ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቲችንግ ሆስፒታል የሚሰራ የቲክቫህ አባል ሀኪም 12 ሰዎች መገደላቸው መረጃ እንዳለው በላከልን የፅሁፍ መልዕክት አረጋግጧል።ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታላቸው ከአንድ ቀን በኋላ የሄዱም እንዳሉ አሳውቋል ስለሁኔታውስለጥቃቱ መነሻ አለኝ ባለው መረጃ አንድ ሰው ተገድሎ መንገድ ላይ ተጥሎ መገኘቱ ነው ብሏል።የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ማንነታቸው ያልታወቁ የተደራጁ ወንጀለኞች ባደረሱት ጉዳት የ12 ሰዎች ህይወት ጠፋ ብሎ ከመግለፅ በዘለለ መነሻውምክንያቱ ምን እንደሆነ የሚገልፅ መረጃ አልሰጠም። ### Response:
### Text: የአአ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ሕዳር 202014 ዓም በአንደኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ስብሰባው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ሆፕ ፎር ችልድረን ኦርጋናይዜሽ አውስትራሊያ ሊምትድ የተባለው ግብረሰናይ ድርጅት በአአ በየካ ክከተማ ወረዳ 010ክልል ውስጥ በ600 ሚልየን ብር የመሬት አጠቃቀሙ ባለ ብዙ አገልግሎት የሆነ ቦታ ላይ ወላጅ አልባና ደጋፊ ለሌላቸው ሕጻናት የልህቀት ማእከል ለመገንባት በመሬት ልማትና አስተዳደር የቀረበውን የውሳኔ መነሻ ተቋሙ ስራውን አጠናቆ ወደ ተግባር ሲገባ የሚሰጠውን አገራዊ ፋይዳ ከግምት በማስገባት የተዘጋጀው ቦታ ከዚህቀደም መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት በሚስተናገዱበት መሰረት እንዲስተናገዱ ውሳኔ አሳልፏል። በሱማሌ ክልል እና ኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በዝናብ እጥረት ምክንያት በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች እየደረሰ ያለውን ጉዳት መነሻ በማድረግ የ100 ሚሊዮን ብር0የአይነት ድጋፍ ውሳኔ0አሳልፏል 50 ሚሊዮን ለሱማሌ ክልል እና 50 ሚሊዮን ለኦሮሚያ ክልል ካቢኔው ለሸማቾች ህብረት ሥራ ዩኒየኖች የግብርና ምርቶች የሚያቀርቡበት ብድር ማቅረብ አስፈላጊ በመሆኑ ለጤፍና ለስንዴ ግዢየ ሚውል 500 ሚሊዮን ብር ለሪቮልቪንግ ፈንድ የፈቀደ ሲሆን የግዢ ሂደቱ የሸማቾች ሕብረት ስራ ማኀበራት ግዢውን በቀጥታ ከአምራች መሰረታዊ ማኀበራት እንዲፈጸም ተወስኗል። ### Response:
### Text: የትምህርት ሚኒስቴርና የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች ከብሄራዊ ፈተና አስተዳደር ጋር በተያያዘ ባለፉት አመታት የታዩ ችግሮች ለመቅረፍ ከፈተና ዝግጅት ጀምሮ እስከ ውጤት ማሳወቅ ያሉትን ተግባራት በጥቃቄ እንዲከናወኑ 1ኛ ፈተናዎችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደግፎ መስጠት የሚቻልበትን ሁኔታ ለማረጋገጥ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይህ እውን እስኪሆን ድረስ የሚሰጡ ፈተናዎች በየክልል ትምህርት ቤቶች መሆኑ ቀርቶ የፈተና ጣቢያዎች በፌዴራን ተቋማት ውስጥ ብቻ ሊሆኑ የሚችሉበትን መንገድ ከአሁኑ እንዲመቻች2ኛ ማህበረሰቡ ለረጅም ጊዜያት ሲጠይቅ የነበረውን እና መንግስት ግልፅ አቋም የያዘበትን የትምህርት ስርዓቱን የጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ማሳኪያ መሳሪያ አድርጎ መጠቀም፣ ማንንም የማይጠቅም በተለይ የልጆቻችን ትምህርት የሚጎዳ መሆኑ ታውቆ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ከእንዲህ አይነት ጎጂ አሉታዊ እንቅስቃሴ እራሱን እንዲያቅብ3ኛ በየደረጃው ያለው የፖለቲካ እና ከመንግስት አመራር የትምህርት ባለድርሻ አካላት መላው ህብረተሰብን ጨምሮ በጉዳዩ ዙሪያ ማነጋገርና ለመፍትሄው በከፍተኛ ደረጃ ተሳትፎ እንዲደረግ ለማስቻል ርብርብ እንዲደረግ ከወዲሁ ስምምነት ላይ ተደርሷል።ተጨማሪ ከላይ ያንብቡ ትምህርትሚኒስቴር ### Response:
### Text: መከላከያም ፣ ፀረ ሽምቅም ፣ ሚሊሺያም ወደ ቦታው ልከናል አሁን ተረጋግቷል አቶ ፋንታሁን ኪሮስ የመተማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሱዳን ታጣቂዎች ዛሬ በምዕራብ ጎንደር ዞን መንዶካ ልዩ ስሙ እንዲብሎ በተባለ ቦታ ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ እስከ ጠዋት 4 ሰዓት ተኩስ ከፍተው የግብርና ባለሀብቶችን ካምፕ ማቃጠላቸውን አንድ የአካባቢው ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።የሱዳን ኃይሎች ከርቀት ከፍተኛ ድምፅ ያለው መሳሪያ ሲተኩሱ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ መንዶካ ከሱዳን ደንበር 70 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ የአካባቢ ሚሊሺያና ሌሎችም የፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት የአፃፋ እርምጃ የሱዳን ኃይሎች መመለሳቸውንም ነዋሪዎች ገልፀዋል።የመተማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ፋንታሁን ኪሮስ መከላከያም ፣ ፀረ ሽምቅም ፣ ሚሊሺያም ወደ ቦታው ልከናል አሁን ተረጋግቷል ሲሉ ተናግረዋል። ከጥቅምት መጨረሻ ጀምሮ በአንድንድ የምዕራብ አማራ ወረዳዎች ዘልቀው በመግባት የባለሀብቶችን ንብረት የሚያወድሙት የሚዘርፉትና የሚያቃጥሉት የሱዳን ታጣቂዎች አሁንም ድረስ ከኢትዮጵያ ግዛት እንዳልወጡ የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ ማስታወቁን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ በዘገባው አስታውሷል። ### Response:
### Text: አዲስ ስታንዳርድ️የሱማሌ ክልል ፕረዜዳንት አብዲ ኢሌ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር መሆኑ እርግጥ ነው። በትላንትናው ዕለት አብዲ ኢሌ ከፌደራሉ መንግስት እና የፀጥታና ደህንነት ኃላፊዎች ጋር በክልሉ እየተባባሰ ስላለው የፀጥታ ችግር ለመነጋገር ስብሰባ ተጠርቶ ነበር። አብዲ ኢሌ ግን ከፌደራሉ መንግስት የቀረበለትን ጥያቄ ወደ ጎን በመተው የክልሉን ፓርላማ እና ካቢኔ ስብሰባ ይጠራል። የዚህ ስብሰባ ዋና ዓላማ የሕገመንግስቱን አንቀፅ 39 በመጠቀም የሱማሌ ክልልን ለመገንጠል ውሳኔ ለማሳለፍ እንደሆነ ታውቋል። በዚህ መሰረት ዛሬ ጠዋት አብዲ ኢሌ ከክልሉን ምክር ቤት እና ካቢኔ አባላት ጋር ስብሰባ ላይ እንዳለ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ቁጥጥር ስር ውሏል። ከሰዓት በኋላ በክልሉ ቴሌቪዥን ቀርቦ የክልሉ ሕዝብ እንዲረጋጋ ጥሪ አቅርቧል። ማታ ላይ ደግሞ ስለ ጉዳዩ ዝርዝር ማብራሪያ የሚሰጥ ይሆናል። ሆኖም ግን አብዲ ኢሌ አንቀፅ 39 መሰረት የሲማሌ ክልልን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል ጥረት ማድረጉ የተረጋገጠ ሀቅ ነው። ፍፁም ባልተጠበቀ መልኩ ሀገር ለመገንጠል ውሳኔ ከማሳለፉ በፊት ግን በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ውሏል። በቀጣይ ምን ሊሆን እንደሚችል አብረን የምናየው ይሆናል። ለበለጠ ማብራሪያ ይህን የአዲስ ስታንዳርድ ዘገባ መመልከት ይቻላል። ### Response:
### Text: ሳውዲ በየመን ድሮኖች ላይ ጥቃት መፈፀሟን ገለጸች፡፡ የየመን 3 የስለላ ድሮኖች ጅዛን እና አብሃ በተባሉ የየመን አዋሳኝ ወደ ሳውዲ ከተሞች ከመንቀሳቀሳቸው በፊት በሳውዲ አየር ሀይል መደምሰሳቸውን ወታደራዊ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡በመንግስት የሚመራው ሳውዲ ፕረስ ኤጀንሲ እንደዘገበው ቦምብ ተሸካሚ ድሮኖቹ በየመን በሚንቀሳቀሱት የሀውቲ አማፅያን የሚመሩ ቢሆንም ድርጊቱን በዋናነት የምታቀነባብረው ኢራን መሆኗን ነው የገለፀው። ሳውዲ በየመን ላይ በምትወስዳቸው ጥቃቶች የተነሳ ንፁሀን ዜጎች ምን ያህል እየተሰቃዩ መሆኑን አንድ የየመን ሰብዓዊ መብት ቡድን ገልጿል፡፡ቡድኑ እንዳለው የሳውዲ የአየር ጥቃት ትምህርት ቤቶችንና ሆስፒታሎችን ኢላሚ ያደረገ በመሆኑ ብዙ ጥፋቶችን በየመን አስከትለዋል ብሏል፡፡ እስካሁን በተደረጉ የአየር ላይ ጥቃቶች ቢያንስ ወደ 175 ንፁሀን እንዲሁም 165 ህፃናትን ጨምሮ መገደላቸው ተገልጿል፡፡በአደጋው ከ427 በላይ የቆሰሉ ንፁሀን ሲኖሩ ይህም 172 ህፃናትን ያካትታል ነው ያለው፡፡ ይህም ቁጥር ለ 150 ጊዜ በተደረጉት የአየር ላይ ትቃት ብቻ መሆኑ ነው የተነገረው፡፡የየመኑ የሰብዓዊ መብት ቡድኑ ይህንን ሪፖርት ያወጣው ከ2 ሺህ በላይ የመናውያንን በማነጋገር መሆኑን የአሜሪካው ዜና አውታር ኤፒ ዘግቧል፡፡ ኢትዮኤፍኤም ### Response:
### Text: ከ140 በላይ ኢትዮጵያውያ ከእስር ተለቀቁ ባለፈው ሳምንት በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ጂፒ በተሰኘው የንግድ አካባቢ ፖሊስ ባደረገው ብርበራ ታስረው ከነበሩ 150 ኢትዮጵያውያን ከ140 በላይ የሚሆኑት እስከ ትናንት ምሽት ድረስ መለቀቃቸው ተነገረ።በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ዶክተር ሽፈራው ተክለ ማርያም ለቢቢሲ ሲናገሩ ታስረው የነበሩት ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ፍቃድ እንዳላቸው ከተረጋገጠ በኋላ እንደተፈቱ ተናግረዋል።ቀሪዎቹ 450 የሚሆኑት እስረኞች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን ባላቸው መረጃ ፍርድ ቤት ከቀረቡት መካከል ኢትዮጵያዊያን እንዳልነበሩ አምባሳደሩ ገልፀዋል።አምባሳደሩ ጨምረው እንደተናገሩት አሁን በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውንን በተመለከተ ኤምባሲው አስፈላጊውን ማጣራት እና ከሚመለከታቸው የሃገሪቱ ሃላፊዎች ጋር ንግግር እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ፖሊስ ኢትዮጵያዊያኑን ያሰራቸው ተመሳሳይ ተደርገው የተሰሩ ሃሰተኛ ምርቶችን ይሸጣሉ በሚል ጥርጣሬ ነበር። ተመሳሳይ ያልሆኑና በፖሊስ የተወሰዱ የኢትዮጵያዊያኑን እቃዎች ለማስመለስ ኢትዮጵያዊያኑ ጠበቃ ቀጥረው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱትና ኤምባሲውም ለዚህ ድጋፍ እንደሚያደርግ አምባሳደሩ አመልክተዋል። አማርኛ ### Response:
### Text: ሌላው አሳሳቢ ጉዳይየአማራ ክልል የምዕራብ ጎንደር ዞን ማህበራዊ ልማት መምሪያ በድንበር አካባቢ የሚደረገው የሠዎች ዝውውር አፋጣኝ መፍትሄ ካልተሰጠው በስተቀር የኮሮና ቫይረስ በክልሉ ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ ከፍተኛ ህሙማን ሊመዘገብ እንደሚችል አስታውቋል።የአማራ ክልል ባለስልጣናት እንዳሉት በአማካይ በቀን ከ100 እስከ 150 ሰዎች ድንበር አቋርጠው ወደ ክልሉ ይገባሉ።ለይቶ ማቆያ ውስጥ እንዲገቡ ከሚደረጉት ከነዚሁ ሰዎች መካከል በምርመራ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ቁጥር ጥቂት የሚባል አይደለም።የመምሪያ ኃላፊዋ ወሮ ክሽን ወልዴ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ እንደገለፁት ዞኑ ከጎረቤት ሱዳን 400 ኪሎ ሜትር ይዋሰናል።በዚህም በየቀኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰው ድንበር እያቋረጠ ወደ ዞኑ እንደሚገባ ገልፀዋል።ችግሩ ከአቅም በላይ እየሆነ መምጣቱን የጠቆሙት ወሮ ክሽን ዞኑን፣ ክልሉንና አገሪቱን ከሚመጣው አስከፊ ቀውስ ለመታደግ በየደርጃው ያለው አካል አፋጣኝ ትኩረትና ምላሽ እንዲሰጥ አሳስበዋል።የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እንዳሉት0ከሱዳንና ከጅቡቲ አካባቢዎች ድንበር አቋርጠው ከሚገቡ ሰዎች ጋር በተያያዘ ያለውን ችግር ከፌደራል መንግስት ጋር በጋራ የምንፈታው ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል።ምንጭ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ### Response:
### Text: ዶር ፍሳሃየ አለምሰገድ በ1970 ዓም በትግራይ ክልል ዓድዋ ወረዳ ልዩ ስሙ ይሓ በተባለ ቦታ ነው የተወለዱት። ዶክተር ፍሳሃየ በጠቅላላ ሓኪም እና በሕብረተሰብ ጤና የኢፒዶሞሎጂ የማስተርስ ትምህርታቸውን አጠናቅቀዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በመምህርነት፣ በተማራማሪነትና በሙያ እማካሪነት ከ1994 ዓም እስከ 2011 ዓም አገልግለዋል። ከመስከረም 2012 ዓም ጀምሮ ወደ በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የህብረተሰብ ጤና ትምህርት ክፍል ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በእናቶች እና ህፃናት ህክምና፣ ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች፣ በስነምግብ ፣ በወባ ፣ በኤች አይቪ ኤድስ እና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን ጨምሮ በሌሎች የሕብረተሰብ ጤና ዘርፎች ከ50 በላይ ችግር ፈቺ ጥናቶችን በታዋቂ ጆርናሎች በማሳተም አዳዲስ እውቀቶች በማፍለቅ ለዓለም አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኮሮና ወረርሺኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ ፈጣን ግብረ መልስ ቡድን መሪ በመሆን ህዝባቸውን ከቫይረሱ ለመታደግ ሌተቀን ሲሰሩ ቆይተዋል። የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ባደረገላቸው ጥሪ በኮሮና ቫይረስ መረጃ ትንተና እና ትንበያ ክፍል በመስራት ላይ እያሉ በኮሮና ቫይረስ ተይዘው ህክምና ሲደረግላቸው ቆይቶ ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።አክሱም ዩኒቨርሲቲነፍስ ይማር ### Response:
### Text: ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓም ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኃላ ለ3ተኛ ጊዜ የተካሄደውን የ1997ቱ ሀገር አቀፋዊ ምርጫ ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ ሳቢያ ሰኔ 11997 በመንግስት የተገደሉ ዜጎች ዛሬ 16ኛ ዓመት መታሰቢያቸው ነው።በወቅቱ ኢህአዴግ ይህን መሰሉ አንባገነናዊ ተገባር የፈፀመው ስልጣኑን ለማስጠበቅ ፣ ስልጣኑን የሚያስጠብቀውም በመሳሪያ ኃይል እንጂ በህዝብ ድምፅ እንዳልሆነ የተቀናቃኝ ፖለቲካ ኃይሎች በተለያየ ጊዚያት ተናግረዋል።ሰኔ 1 ቀን 1997 በግፍ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ዜጎች ለነፃነት፣ ለዴሞክራሲ፣ ለፍትህ፣ ለሀገራዊ አንድነት ዋጋ የከፈሉ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል በየዓመቱም በዚህ ቀን ይታሰባሉ።ፖለቲከኞች ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾ ይህን የሰኔ 1 ቀን 1997 ዓም ክስተት ለሁሉም ትምህርት የሚሰጥ እና መቼም ቢሆን ሊደገም የማገባው ብዙ ትምህርትም ሰጥቶ ያለፈ እንደሆነ ይናግራሉ።በወቅቱ ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓም በግፍ የተገደሉ ፣ የቆሰሉ፣ ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ዜጎች ኢትዮጵያን ያስተዳደር በነበረው ኢህአዴግ በሚባለው ፓርቲ ወቅት ሲሆን ፓርቲው ከዓመት በፊት በኢትዮጵያ ምድር ህልውና እንዳይኖረው ተደርጎ፣ ከስሟል።በውስጡ የነበሩ ድርጅቶችም ከአንዱ ህወሓት በቀር አንድ ላይ ተዋህደው ውህድ ፓርቲ ፈጥረው ኢትዮጵያን እያስተዳደሩ ነው። ### Response:
### Text: የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሰኔ 3 ቀን 2013 በመስቀል አደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚደረግ እየተላላፈ ያለው መረጃ የተዛባ ነው ብሏል።ኮሚሽኑ ህገወጥ ስብሰባ ለማድረግ እንቅስቃሴ የሚደረግ ከሆነ በህግ አግባብ እርምጃ ለመውሰድ እገደዳለሁ ሲል አስጠንቅቋል።የሰላም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳውያን ለወጣቶችና ጎልማሶች ማህበራት ሕብረት በቁጥር ዘ11 804 መ113 10 ሰኔ 1 ቀን 2013 ዓም በፃፈው ደብዳቤ የኮቪድ ፕሮቶኮልን በጠበቀ መልኩ በአዳራሽ ስብስባ እንዲደረግ እንደፈቀደ ነገር ግን በማይመለከታቸውና እና ውክልና ባልተሰጣቸው አካለት በስህተት በመስቀል አደባባይ ስብሰባው እንዲደረግ የተሰጠው ፈቃድ አግባብ አለመሆኑን ለኮሚሽኑ በግልባጭ አሳውቋል።በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎችና በከተማው በተለጠፉ ማስታወቂያዎች ሰኔ 3 ቀን 2013 ዓም ሀይማኖታዊ ይዘት ያለው ህዝባዊ ስብሰባ በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ የሚገልፅ መረጃ እየተሰራጨ ቢሆንም የሰላም ሚር ስብሰባውን በመስቀል አደባባይ ማደረግ የማይቻልበትን ዝርዝር ሁኔታ ለጥያቄ አቅራቢዎቹ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ኮሚሽኑ በተጠቀሰው እለት በመሰቀል አደባባይ ይካሄዳል የተባለው ስብሰባው በከተማ አስተዳደሩም ይሁን በፖሊስ ኮሚሽኑ እውቅና የሌለው ነው ብሏል። ### Response:
### Text: በጃዊ ወረዳ የ3 ሰው ህይወት አለፈ️በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ጃዊ ወረዳ ፈንድቃ ከተማ በመብራት መቆራረጥ ምክንያት በተከሰተ አለመግባባት የሰው ህይወት ማለፉን የወረዳው የሰራ ኃላፊዎች እና ነዋሪዎች አረጋግጠዋል፡፡የችግሩ መነሻ ትላንት የኢንጂነር ስመኝው በቀለን ስርዓተ ቀብር እንዳንከታተል መብራት ሆን ተብሎ ጠፍቶብናል በሚል በተቀሰቀሰ ቁጣ ነው፡፡ ይህንንም የወረዳው መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ንብረት አረጋግጠዋል፡፡ ከሁለት ቀናት በፊትምበተከተማዋ መብራት ጠፍቶ ነበር በተደጋጋሚም ይቆራረጣል ነው ያሉት አቶ ብርሐኑ፡፡ከፈንድቃ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ስለጉዳዩ ስለጉዳዩ የገልፁት የአቶ ተሰራ ቄሴ ሃሳብም ከአቶ ብርሐኑ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ስርዓተ ቀብሩን እየተከታተሉ እያሉ መብራት እንደተቋረጠባቸው የተናገሩት አቶ ተሰራ ከነበሩበት ቤት ሲወጡ ግጭት ተፈጥሮ መመልከታቸውን ነው የነገሩን፡፡ በወቅቱም ጉዳት የደረሰበትን አንድ ግለሰብ ይበልጥ እንዳይጎዳ በማለት ለጸጥታ ኃይሎች ማስረከባቸውን ተናግረዋል፡፡በግጭቱ የሶስት ሰዎች ህይዎት ማለፉንም አቶ ብርሐኑ እና የዓይን እማኞች አረጋግጠውልናል፡፡ በኃይማኖት አባቶች፣ በህብረተሰቡ እና በጸጥታ ኃይሎች ጥረት ግጭቱ መረጋጋቱንም ነው የተሰማው።© ### Response:
### Text: ለሞጣ ከተማ ሙስሊም ወገኖች የሙስሊም ተቋማትና መሳጆድ ላይ ባለፈዉ ታሕሳስ በተፈፀመዉ ጥቃት ሐብት ንብረታቸዉ ለጠፋባቸዉ ሙስሊሞች መርጃ በብዙ ሚሊዮን የሚገመት ብር ተዋጥቷል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሰየመዉ ኮሚቴ እንዳስታወቀዉ ኮሚቴዉ በዘጠኝ ባንኮች ከከፈታቸዉ ቁጥሮች በአንዱ ብቻ ዛሬ ቀትር ድረስ ከ 24 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሆኗል። አዲስ አበባ ዉስጥ ብቻ የተሰበሰበዉ ገንዘብ፣ ቁሳቁስና ወርቅ ኮሚቴዉ በፊት ካሰበዉና ከተገመተዉ በላይ ነዉ። የሕዝቡ ተሳትፎ «ስሜት የሚነካ» ነበር ተብሏል አካል ጉዳተኛዉ መጓዧ ምርኩዙን ወይም ክራንቹን፣ ገንዘብ የሌለዉ የጥርሱን ወርቅ ነቅሎ፣ ሌሎቹ ወርቅ፣ ጌጥ እና ተንቀሳቃሽ ስልካቸዉን ጭምር ሰጥተዋል።በአማራ መስተዳድር ባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ከሚሴ እና ኮምቦልቻን በመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞችና በሌሎችም አነስተኛ ከተሞች ገንዘብ ሲዋጣ ነዉ የዋለዉ። የባሕርዳር ከተማ የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴ አስተባባሪ ዶክተር አደም ጫኔ እንዳሉት ባሕርዳር ዉስጥ ከ50 ብር እስከ 50ሺሕ ብር ድረስ የሰጡ ለጋሶች አሉ።እስከ ማምሻዉ ድረስ የተሰበሰበዉ ገንዘብ መጠን በትክክል ባይታወቅም ከባሕርዳር ከተማ ብቻ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ይሰበሰባል ተብሎ ይታመናል።የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ### Response:
### Text: የ2012 ዓም የ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተናን ከግማሽ በላይ ተማሪዎች ከ350 በላይ ማምጣታቸው ተገለፀ።የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን በተመለከተ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል።የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶር ዲላሞ ኦተሪ የ2012 ዓም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተመዝጋቢ ፣ በተፈታኝም እንዲሁም በውጤትም ደረጃ ከፍተኛ መሆኑ ገልፀዋል።ፈተናውን ከወሰዱ አጠቃላይ ተፈታኞች ውስጥ 557 ፐርሰንቱ ከ 350 በላይ አምጥተዋል።በመግለጫው የፈተና ውጤት ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም ከ600 በላይ ያመጡ ተማሪዎች 702 መሆናቸው ተገልጿል።የዓመቱ ከፍተኛ ውጤትም 669 ሆኖ መመዝገቡን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።ተማሪዎችም ውጤታቸውን በፈተናዎች ኤጀንሲ ድረገፅ እንዲሁም በአጭር የፁሁፍ መልዕክት 8181 የፈተና መለያ ቁጥራቸውን በማስገባት ከነገ ጀምሮ ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ተገልጿል።ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜን እና ማለፊያ ነጥብን በተመለከተ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ በመግለጫው ማስታወቃቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ይገልጻል። ### Response:
### Text: የዳሰሳ ጥናት በአማራ ክልል ዶቼ በለየአማራ ክልል ፕላን ኮሚሽን ህወሓት በክልሉ ላይ በከፈተው ጦርነት እና ወረራ በንብረት ላይ ስለደረሰው ጉዳት የዳሰሳ ጥናት አድርጓል።በዚህም ህወሓት በወረራ በያዛቸው እና ነፃ በንብረት ብቻ 280 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት ማውደሙንና መዘረፉን ኮሚሽኑ አሳውቋል።አብዛኛው ዝርፊያና ውድመት በግብርናው ዘርፍ የተፈፀመ ነው።ጥናቱ የተካሄደው ወረራ በተካሄደባቸው 45 ወረዳዎች ሲሆን የደሴና ኮምቦልቻ አካባቢዎችን አላካተተም።የደሴንና የኮምቦልቻ አካባቢ ውድመት በጥናት ሲረጋገጥ የውድመቱና የዘረፋው ሁኔታ የከፋና ግዙፍ እንደሚሆን ተገልጿል።በዳሰሳ ጥናቱ በከፊልና በሙሉ ተቋማትን የዳሰሰ ሲሆን የግብርናው ዘርፉ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል።የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ደግሞ የወደመውንና የተዘረፈውን የግብርና ምርት ለማካካስ 100ሺህ ማሳ በመስኖ በማልማት 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ለማልማት አውጃለሁ ብሏል።በጦርነቱ ምክንያት በተለይ በምስራቅ አማራ ዞኖች ከፍተኛ የምርት ቅናሽ ይኖራል። የማካካሻ ሥራ እንደሚሰራ ተገልጿል።በጥናቱ መሰረት በአማራ ክልል በጦርነት ቀጠና ውስጥ ከ6 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለከፋ የኑሮ ጉስቁልና መዳረጉና ከ1 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ናቸው፡፡ ### Response:
### Text: ነዳጅ የነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ ለረጅም ጊዜ ሊቆይ ይችላል ሲሉ የነዳጅ ላኪዎች ህብረት መሪ አስጠነቀቁ።የ23 ነዳጅ ላኪ ሀገራት ህብረት የሆነው ኦፔክ ዋና ፀሀፊ ሄይታም አል ጋይስ ለሃይል አቅርቦት ያለው ፍላጎት በመጨመሩ የነደጅ ዋጋ እንዳሻቀበ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።ዋና ጸሃፊው በቀን የነዳጅ ፍላጎት ወደ 24 ሚሊዮን በርሜል ሲያድግ እየተመለከትን ነው ብለዋል።ሁለቱ ዋነኛ የነዳጅ አምራችና ኦፔክ አባል የሆኑት ሳዑዲና ሩሲያ የወሰኑት ውሳኔ በዚህ ዓመት መጨረሻ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያስከትላል ሲል ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ አስታውቋል። ይህ ሁለት ሉአላዊ ሀገራት ሳዑዲ አረቢያ እና ሩስያ በፍቃደኝነት የወሰኑት ነው። ይህ ውሳኔ እርግጠኛ ልንሆንበት በማንችልበት ሁኔታ ምክንያት የተደረገ ጥንቃቄ ወይም ቅድመ ዝግጅት ብለን ልንገልጸው እንችላል ሲሉ የኦፔክ ዋና ጸሃፊ ተናግረዋል።ሰሞኑን በምርት እጥረት ምክንያት የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 95 ዶላርን አልፎ የነበረ ሲሆን ዋጋው 100 ዶላርን ሊያልፍ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።ይህ የዋጋ ለውጥ በሚቀጥሉት 10 ወራት ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ሊያሻቅብ እንደሚችልና በወሳኝ የኢኮኖሚ መስኮች ያለው የዋጋ ግሽበት ለረዥም ጊዜ እንዲቀጥል ምክንያት ይሆናል የሚል ስጋትን ማጫሩን ቢቢሲ ዘግቧል። ### Response:
### Text: የ32 ዓመቷ ወጣት በፖሊስ ጥይት ከጀርባዋ ተመታ ህይወቷ ያለፈ ሲሆን ፖሊስ የድርጊቱ ፈፃሚ በቁጥጥር ስር ይገኛል ብሏል።በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ነዋሪ የሆነች የ32 አመት ወጣት ከፖሊስ አባል በተተኮሰ ጥይት ተመታ ህይወቷ አልፏል።በፖሊስ አባል ጥቃት የደረሰባት ኢየሩሳሌም አስራት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ስትሆን ጥቃቱ ካጋጠማት በኋላ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና እና ሕክምና ክትትል ሲደረግላት የነበረ ቢሆንም ህይወቷ ሊተርፍ አልቻለም።በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ቀበሌ 25 ህዳር 13 ቀን 2016 ዓም ከምሽቱ 5 ሰአት አካባቢ በወጣቷ ጓደኞች እና በሌሎች ሰዎች መካከል በተፈጠረ0አለመግባባት0 በቦታዉ የደረሰዉ የፖሊስ አባል በተተኮሰ0 ጥይት0ህይወቷ እንዳለፈ ተገልጿል።እየሩሳሌም አስራት ከጀርባዋ በመመታቷ ነው ህይወቷ ያለፈው።ጉዳዩን በተመለከተ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር0 ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደስ ወንጀሉን የፈፀመዉ የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ዉሎ ለምን እና በምን ሁኔታ ዉስጥ ሊተኩስ ቻለ የሚለዉ ጉዳይ እየተጣራ ነው ብለዋል።ወደፊትም እንደ አስፈላጊነቱ የፍርድ ሂደቱ በመከታተል ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአሐዱ ሬድዮ ኤፍ ኤም 943 ነው። ### Response:
### Text: ገንዘቡ ገቢ አልተደረገምለተፈናቃዮች ማቋቋሚያ ቃል የገቡ አካላት በቃላቸው መሠረት ገንዘቡን ገቢ እንዲያደርጉ የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትና ፕሮግራም እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጠየቀ፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ዜጎችን ለማቋቋም ቃል የተገባው ገንዘብ በተባለው መሠረት ገቢ አልተደረገም፡፡በአማራ ክልል የሚገኙ ከ107 ሺህ በላይ ተፈናቀዮችን በመንግሥት አቅም ብቻ ማቋቋም እና በዘላቂነት ወደ ቀደመ ሕይወታቸው መመለስ አልተቻለም፡፡ በመሆኑም ኮሚቴ ተዋቅሮ መጋቢት 2011 ዓም የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል መዘጋጀቱ ይታወሳል፡፡ መርሀ ግብሩ በአማራ አቀፍ ልማት ማኅበር አልማ ከተዘጋጀ በኋላም ከአዲስ አበባ ውጭም በተለያዩ ቦታዎች ቀጥሏል፡፡በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ባለሀብቶች እና የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች 720 ሚሊዮን ብር ለመርዳት ቃል ገብተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ቃል ከተገባው ውስጥ በአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትና ፕሮግራም እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን የባንክ ሒሳብ ቁጥር ገቢ የተደረገው 384 ሚሊዮን 151 ሺህ 812 ብር ብቻ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነር እታገኘሁ አደመ ተናረዋል። ### Response:
### Text: የመጀመሪያው አገር አቀፍ የፍቅርና የሰላም ጉዞ ሊካሄድ ነው በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የፍቅርና የሰላም ጉዞ የፊታችን ጳጉሜ 32011 ጉዞ በአዲስ አመት ለሰላምና ለአንድነት በሚል መሪ ቃል ከአዲስ አበባ እስከ ደብረ ዘይት ይካሄዳል፡፡የሰላም ተጓዥ አገልግሎት ድርጅት በሀገራችን ዘላቂ ሰላምና ፍቅርን ለመፍጠር እና ለማስፈን የተለያዩ የፍቅርና የሰላም ጉዞዎችን ለማካሄድ ማቀዱንና ይህንንም የፊታችን ጳጉሜ 32011 በሚያካሄደው የጉዞና የጉብኝት ፕሮግራም እንደሚጀምር የድርጅቱ መስራች አቶ ቸርነት ጥላሁን ተናግረዋል፡፡አቶ ቸርነት በሰጡት መግለጫ የሰላም ተጓዥ አገልግሎት ድርጅት ወደ ፊት በሀገር ውስጥ በሚፈጠሩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ሳቢያ በሀገሪቱ የተከሰቱ ግጭቶችን ለመፍታትና ለማረጋጋት ከሃይማኖት አባቶችና ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመሆን ለመስራት ማቀዱን አስታውቀዋል፡፡የሰላም ተጓዥ አገልግሎት ድርጅት ከሰላም ሚኒስቴር ተለይተው በተሠጡት አካባቢዎች ላይ የተለያዩ የሰላምና የእርቅ ስራዎችን በመስራት የሀገሪቱን የቱሪስት መስብነት ለማስተዋወቅና በ2014 ኢትዮጵያ የህዝቦቿ ሰላም ተመልሶ በቱሪዝም መዳረሻነትና በሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከአፍሪካ 5 ሀገራት አንዷ እንድትሆን እንደሚሰራ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ ### Response:
### Text: ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠ ማሳሰቢያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2011 ዓም ያስመዘገባቸው ስኬቶች፣ በቀጣይ ዓመት ሊሰራ ያቀዳቸውንና ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች መገናኛ ብዙሃን ጠርቶ በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ጥቂት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ስም ተጠቅመው አፈፃፀሙን በተመለከተ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሀበራዊ ትሰስር ገፆች እያስተላለፉ ይገኛሉ። ይኸውም የባንኩ ትክክለኛ ገፅ እንደሆነ በማስመሰል የባንኩን ያለፈው ዓመት ክንውን አስመስለው የለቀቁትን ሃሰተኛ መረጃ ላነበበና መረጃውን ለሌሎች ሰላሳ ሰዎች እስከ መስከረም 20 ላጋራሸር ላደረገ፣ ባንኩ የገንዘብ ሽልማት እንደሚሰጥ የሚያትት ሃሰተኛ መረጃ ነው፡፡ በመሆኑም የተለቀቀው መረጃ ባንኩን በምንም ሁኔታ እንደማይመለከት እየገለፅን፣ ካሁን በፊት እንዳሳወቅነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በተመለከተ ትክክለኛ መረጃዎች የሚለቀቁት በባንካችን የሬዮና ቴሌቪዠን እንዲሁም በማህበራዊ የትስስር ገፆቻችን ብቻ መሆኑን በድጋሚ እያሰወቅን፣ ህሰቡ ከመሰል ሃሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ እናሳስባለን፡፡ በቀጣይ ባንኩን በተመለከተ መሰል ሃሰተኛ መረጃ የሚለቁ ግልሰቦችን ለፍትህ አካል ለማቅረብ ባንኩ እየሰራ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ### Response:
### Text: ሀዋሳ ከሀምሌ 11 ጋር ተያይዞ ስጋት ውስጥ የሚጥሉ ነገሮች የሉም አቶ ሚሊዮንማቲዮስ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንትየሲዳማ የክልልነት ጥያቄን አስመልክቶ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን ስጋት ላይ የሚጥሉ ጉዳዮች እንደሌሉ ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን በቅርበት እየተከታተሉ እንደሆነ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ ተናገሩ። ከሀምሌ 11 ጋር በተያያዘም ዜጎችን ስጋት ላይ የሚጥል ምንም ነገር የለም ብለዋል።ክቡር ፕሬዘዳንቱ የተናገሩትን ቃል በቃል ከዚህ በታች እንድታነቡት ፅፌላችኃለሁየሀዋሳ ከተማን ነዋሪ ወደስጋት ሊጥሉ የሚችሉ ጉዳዮችን በቅርበት እየተከታተልን ከህዝቡ ጋር በመሆን ምላሽ ለመስጠት ሰፊ ስራዎችን ስንሰራ ነው የቆየነው። አሁንም ቢሆን በዚህ ጉዳይ ላይ በተለይም ከሲዳማ አንፃር የተነሳውን ጥያቄ ተንተርሶ ስጋት ውስጥ የሚያስገቡት ነገሮች እንዳሉ ሚደመጡ ነገሮች አሉ ግን ደግሞ የሲዳማ ህዝብ ጥያቄውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ሲያቀርብ ነው የቆየው ይሄ በተለያየ ሂደት አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰ በመሆኑ አሁን ባለንበት ሁኔታ የከተማችንን ፀጥታ የሚያውክ ነገር ይፈጠራል ብለን የምንጠብቀው ነገር የለም። ከሀምሌ 11 ጋር ተያይዞ ስጋት ውስጥ የሚጥሉ ነገሮች የሉም የሚል ነገር ነው እየገለፅኩ ያለሁት። ### Response:
### Text: የምርጫ ማስታወቂያ የቀደደ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።በአርባ ምንጭ ዙርያ ወረዳ የ ጋንታ መይጨ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው የ44 ዓመቱ ተከሳሽ ደርጉ እማኔ ግንቦት 12 ከቀኑ 11፡00 ሰዓት አካባቢ ንብረትነቱ የብልፅግና ፓርቲ የሆነውን የምርጫ ምልክት አምፖል ፖስተር ከተሰቀለበት ቦታ ቀዶ በመጣሉ የኢትዮጵያ የምርጫ ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ 11622013 ስር አንቀፅ 158 የምርጫ ማስታወቂያ ማጥፋት የተደነገገውን ክልከላ በመተላለፍ ተከሷል ። ተከሳሹ ድርጊቱን ስለመፈጸሙ ሶስት የዐቃቤ ሕግ የሰው ማስረጃዎች በመመስከራቸው ተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ፍ ቤት ልዩ የምርጫ ችሎት ግንቦት 17 ባስቻለው ችሎት ተከሳሽ ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌለበት በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠቡ ያስተምራል ተከሳሹን ያርማል ያለውን የ2 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡ የአርባንጭ ዙሪያ ወረዳ ዐቃቤ ህግ ጽቤት ማንኛውም ሰው እጩ ተወዳዳሪ ፣ አባል እና ደጋፊ ፖስተር ወይም የምርጫ ማስታወቂያ ያበላሸ ፣ ያስወገደ የቀደደ እንደሆነ የወንጀል ተጠያቂነት ይከተለዋል ህብረተሰቡም ከመሰል ድርጊቶች ሊቆጠብ ይገባል ብሏል።መረጃው የጋሞ ዞን ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው። ### Response:
### Text: ወደ ሙቱ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባው መንገድ ጭቃማ በመሆኑ ተማሪዎች መቸገራቸውን ገለፁ። ቦታው የአንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሚገኝበት በመሆኑ መንግስት በአካባቢው የመንግድ መሰረተ ልማት ሊያሟላ ይገባል ብለዋል።ሌላውበመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርት እየተማሩ እንዳልሆኑም ከግቢው ተማሪዎች የተላከው መረጃ ያሳያል። ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያም ተማሪዎች በአግባቡ ወደ ክፍል ገብተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ጠይቋል። በአግባቡ ትምህርታቸውን በማይከታተሉ ተማሪዎች ላይ ዩኒቨርሲቲው የራሱ እርምጃ ይወስዳል ብሏል።ያነጋገርናቸው ተማሪዎች እንደገለፁልን በግቢው ሁኔታ ስጋት ስላላቸው ከግቢው ውጪ ወጥተው ለማደር መገደዳቸውን ገልፀዋል። ከቅርብ ከተሞች የመጡ ተማሪዎችም ወደየቤታቸው እየተመለሱ መሆኑን የአይን እማኞች የላኩልን መረጃ ይጠቁማል። ዛሬም ተማሪዎች ግቢውን ለቀው በመውጣት ላይ ይገኛሉ። ተማሪዎቹም ማደሪያቸውን በቤተክርስቲያን እና በተለያዩ ቦታዎች ለማድረግ እንዳሰቡ ገልፀውልናል።ምንጭ መቱ ዩኒቨርሲቲበተያያዘ መንግስት በየዩኒቨርሲቲዎቹ ለተነሱት ጥያቄዎችን መፍትሄ በመስጠቱ ለሳምንታት ትምህርት ተቋርጦ በነበረባቸው የጅማ እና የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ተጀምሯል። ### Response:
### Text: ጋምቤላ️ወደ ጋምቤላ ክልል አቦቦ ወረዳ ሄደው የነበሩ ስምንት ጋዜጠኞች በመንግሥት ባለሥልጣናት ተደበደብን፣ ተዋከብን፣ ታገትን፣ ያለአግባብ በቁጥጥር ሥር ዋልን ሲሉ አቤቱታ አሰምተዋል። የወረዳው አስተዳደር አስተባብሏል።በሌላ በኩል ደግሞ በክልሉ ውስጥ ነዋይ እያፈሰስንና የልማት ሥራ ላይ ተሠማርተን ሳለን ወከባ፣ ሙስናና እንግልት ይደርስብናል ሲሉ ቁጥራቸው በርከት ያለ ባለሃብቶች ቅሬታቸውን እየገለፁ ናቸው።ባለሃብቶቹ አቤቱታና በጋዜጠኞች ላይ የደረሰውን ወከባና ጥቃት አስመልክቶ የወረዳው አስተደዳሪ ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ የጋዜጠኞቹን ክሥ ሙሉ በሙሉ አስተባብለው ከአንድ ባለሃብት ላይ ያለአግባብ ተሰጥቶ ነበር ያሉትን የከሰል ምርት ፍቃድ ወረዳው ከማንሣቱ በስተቀር ለባለሃብቶች ጥበቃ እንደሚደረግ ተናግረዋል።ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን አቤቱታ ቃላቸውን ተቀብሎና ከወረዳው ባለሥልጣናትም ጋር እየተፃፃፈ መሆኑን የገለፁው የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ጉዳዩን እየመረመረ መሆኑን ገልጿል።ፌደራሉ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በዚህ የጋዜጠኞቹ አቤቱታና በሌሎችም ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አሠራርና የሕግ ጉዳዮች ጋር በተያያዙ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ከቪኦኤ የቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለው ቀጠሮ ሰጥተዋል።ምንጭ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ ### Response:
### Text: ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ግጭት️በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭት የሟቾች ቁጥር 24 መድረሱ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ በ167 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው አስተዳደር ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭት የሟቾች ቁጥር 24 መድረሱ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ በ167 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው አስተዳደር ዛሬ ለ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የጸጥታ አካላት ወደ ሥፍራው መግባታቸውን ተከትሎ ግጭቱ እየተረጋጋ መምጣቱን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች መካከል ባለፈው ረቡዕ ግጭቱ የተቀሰቀሰው በመሬት ይገባኛል በተፈጠረ አለመግባባት ነበር። ግጭቱ የተከሰተበት ቦታ በጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ሰሜን ዲዳ እና ባቶ ፎቶ በተባሉ ሁለት ቀበሌዎች የነበረ ሲሆን በዚህም ምክንያት0በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችም መፈናቀላቸውን የዓይን እማኞች ለ ተናግረዋል።0በደቡብ ክልል መስቃን ወረዳ መሰል ግጭት ሲከሰት የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ባለፈው መስከረም በደረሰው ግጭት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን እና ንብረት መውደሙ ይታወሳል።ምንጭ አማርኛው አገልግሎት ### Response:
### Text: ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶር ይናገር ደሴ ከሰጡት መግለጫ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች የብር ለውጡን ተከትሎ ህገ ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር ዝግጅት ተደርጓል። በተለያዩ ጎረቤት አገራት የኢትዮጵያ የብር ኖቶች ክምችት አለ ለብር ለውጡ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ቁጥጥር ይደረጋል። ለዚህም ከጸጥታና የደህንነት አካላት ጋር በመነጋገር የመቆጣጠርና የማምከን ተግባራት ይከናወናል። በድንበር አካባቢ የሚገኙ ባንኮች በብር ለውጡ ለህገ ወጥ ድርጊቶች እንዳይጋለጡ ጥብቅ ክትትል ይደረጋል። የብር ቅያሬውን ለማከናወን ማንኛውም ግለሰብ የብር ኖቶቹን ራሱ በባንክ መቀየር ሲገባው በሌላ ግለሰብ በውክልና መቀየር አይችልም። በ3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን የብር ኖት ታትሟል የመጠባበቂያ ክምችት እንዲኖር ተጨማሪ የብር ኖቶች እየታተሙ ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት አዳዲሶቹን የብር ኖቶች ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የማጓጓዝ ስራ ተሰርቷል። አሮጌውን ገንዘብ መቀየር የሚያስችል በቂ ክምችት አለ። አዳዲሶቹ የብር ኖቶች እንዳይበላሹ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ይሄም ኢትዮጵያ የተበላሸ ገንዘብ ለመተካት የምታወጣውን ብዙ ወጪ ያስቀራል። ህገ ወጥ ተግባራት የሚፈጽሙ ባንኮች እንደ ጥፋታቸው መጠን እና ልክ ቅጣት ይጣልባቸዋል። ### Response:
### Text: የባህር ዳር ጉዳይ እንደዘገብው ዩኒቨርሲቲው እና ተማሪዎቹ በመስማማታቸው ወደ ቅጥርግቢው እንዲመለሱ ተደርጓል።በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የ4ኛ ዓመት የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ተቋም ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው ለብቃት ምዘና ፈተና ዝግጅት በቂ ጊዜ አልሰጠንምየምዘና ስርዓቱም አዲስ እና አግባብነት የሌለው ነው በማለት ፈተናውን አንወስድም በማለታቸው ከቅጥር ግቢ እንዲወጡ መደረጉ ይታወሳል።ዩኒቨርሲቲው በበኩሉ የምዘና ስርዓቱ የነበረ ነው በማለት የምግብ እና የመኝታ አገልግሎት አቋርጦ ካሳለፍነው ሰኞ ጀምሮ ተማሪዎቹ በፖሊስ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አድርጎ ነበር።አብዛኛው ተማሪም አዳሩን በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ አድርጎ የነበረ ሲሆን በምግብ በኩል የከተማው ነዋሪዎች ባሰባሰቡት መዋጮ ፈቃደኛ ግለሰቦች ሲያበሰሉላቸው ነበር።ትላንት ወደ ተማሪዎቹ እና ወደ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩትሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶር ንጉስ ጋቢዬ ደውሎ ማረጋገጥ እንደቻልነው ለፈተና ዝግጅት ከ2 ያላነሰ እና ከ3 ሳምንት ያልበለጠ ጊዜ እንዲሰጣቸው በመስማማት ወደ ግቢው ተመልሰዋል። በስልክ ያነጋገርናቸው ተማሪዎች እንደነገሩን አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ወደ ቅጥር ግቢ እየተመለሱ እንደሆነና የምግብ አገልግሎት እንደተጀመረተናግረዋል። ### Response:
### Text: ድብቅ እስር ቤቶቹ️በአዲስ አበባ የተገኙት 7ቱ ድብቅ እስር ቤቶች ንብረትነታቸው የቤቶች ኮርፖሬሽን መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለሸገር ራድዮ ተናገረ፡፡ዜጎች የተለያየ ስቃይ እና እንግልትን አሳልፈውባቸዋል የተባሉት እነዚህ ድብቅ እስር ቤቶች በቀድሞው የኪራይ ቤቶች ወይም የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ በአሁኑ የቤቶች ኮርፖሬሽን ሲተዳደሩ እንደቆዩ ተረጋግጧል ተብሏል፡፡በፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ ዝናቡቱኑ እንደነገሩን ከ7ቱ ድብቅ እስር ቤቶች መካከል የሚደረግባቸውምርመራ ተጠናቆ የተወሰኑት ለቤቶች ኮርፖሬሽን ተመልሰዋል፡፡ የቀሩት ግን የሚካሄደው ምርመራ ስላላለቀ ታሽገው እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡በድብቅ እስር ቤትነት ሲያገለግሉ የቆዩት ቤቶች በየትኛው ክፍለ ከተማና ወረዳ የሚገኙ እንደሆኑ ግን አቶ ዝናቡ በግልፅ ለመናገር አልፈቀዱም ፡፡ የቤቶችኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ የሚያስተዳድራቸውን በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶቹን ገሚሱን ለመንግስት ሹማምንት በመስጠት የተረፉትንም ለተለያዩ ግለሰቦች በዝቅተኛ ዋጋ በማከራየት ያስተዳድራል፡፡ድብቅ እስር ቤት ሆነው ቆይተዋል የተባሉት ቤቶች ኮርፖሬሽኑ ለባለስልጣናት ከሰጣቸው መኖሪያዎች መካከል ይሁኑ ወይንም ሌላ እስካሁን አልታወቀም፡፡ምንጭ ሸገር 1021 ### Response:
### Text: ህወሓት አይዋሀድም ይሄ ምንም ይቅርታ አያስፈልገዉም፡፡ ሊቀመንበሩ እንደሚሉት የግድ አደርጋለሁ ካሉ እና ከተሳካላቸዉ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላቸዉ አቶ ጌታቸው ረዳ አቶ ጌታቸው ረዳ ለትግራይ ሚድያ ሃውስ ኢህአዴግ የግድ ለውጥ ማድረግ ነበረበት። ቀድመን የተነጋገርንበት ነበር።ለዉጡ ወደኋላ ተመልሷል ብቻ ሳይሆን መንገዱን ስቶ ለሀገሪቱም አደጋ ጋርጧል።ትግራዋይነት እንርሳ። አማራነት እንርሳ። ኦሮሞነት እንርሳ። ኢትዮጵያውነት ብቻ ነው የምያዋጣን ብለው የምያምኑ የዋሃን ናቸው።ህወሓት አይዋሀድም ይሄ ምንም ይቅርታ አያስፈልገዉም፡፡ ሊቀመንበሩ እንደሚሉት የግድ አደርጋለሁ ካሉ እና ከተሳካላቸዉ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላቸዉ።ትግራይን ለማስተዳደር የሚፈልጉ እና ለመላክ የተዘጋጁ አዲስ አበባ የሚኖሩ ሰዎች አሉ።ኢትዮጵያ ለዉጭ ጨረታ የቀረበች ሀገር መስላለች።የትግራይ ህዝብ ጥቅም በእንደዚህ አይነት ሰርከስ መመለስ አይችልም።ኢትዮጵያን ማዳን ካለብን እዉነት እናዉራ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ የምር ለዉጥ ይፈልጋል፡ የመበለቶች ተረት በማዉራት የኢትዮጵያ ችግር ሊፈታ አይችልም።ሌብነት ኢንስቲቱሽናላይዝ እስከሚመስል ድረስ ከፍተኛ ምዝበራ የሚካሄድበት በደም የተጨማለቁ ሰዎች እንደፈለጉ የሚፈነጩበት ሀገር ነዉ የሆነዉ። አማርኛ ### Response:
### Text: 5 ሚሊዮን ብር ለሥራ ጀማሪዎች ማጠናከሪያ ከኩዱ ቬንቸር በተገኘው የ5000000 ብር አምስት ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ሥራ ላይ ያሉ እና ምርትና አገልግሎታቸውን ማሳደግ ለሚፈልጉ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ላይ ለተሰማሩ ሰባት ድርጅቶች የአቅም ማበልጸግ ፣ የገበያ ትስስር መፍጠር እና በትንሹ 250000 ብር ከፍ ካለ እንደ ፕሮጀክቱ ታይቶ የሚጨመር ድጋፍ ለመስጠት ጀምሯል።የፕሮጀክቱ ማናጀር የሆኑት አቶ ህሩይ ፀጋዬ እንደገለጹት ሥራ ጀማሪዎቹ ከፕሮግራሙ ጋር በሚኖራቸው ቆይታ ማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ፕላናቸውን ይበልጥ እንዲያሻሽሉ የሚደረግ ይሆናል።ከ7ቱ ፕሮጀክቶች መካከል 5ቱን በመውሰድ 10 ቀን የሚቆይ የውጭ ሀገር ልምድ ልውውጥ እና የሚያስፈልጋቸው የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ገበያው እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል፡፡ይህንን መሰሉን ሥራ ስንሰራ በዋናነት ማወቅ የምንፈልገው የቴክኖሎጂው ዘርፍ በኢትዮጵያ ምን አይነት ደረጃ ላይ ደርሷል የሚለውን ነው ያሉት አቶ ህሩይ የወጣቱን አቅም ማጎልበትና ትርፋማ ማድረግም ሌላው ትኩረት የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ስራ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ፣ የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራ እና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲና ጥቃቅ እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በአጋርነት ይሰራሉ ተብሏል፡፡ ቲክቫህኢትዮጵያ ### Response:
### Text: ግብፅ 2ኛው ዙር የሕዳሴ ግድብ ሙሌት ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ ለመጋፈጥ ዝግጁ ናት ኢንጂነር ሞሐመድ ጋኔምአል ዓይን ኒውስየግብፅ ባለሥልጣናት በመጪው የክረምት ወቅት ሊሞላ ለታቀደው ሁለተኛ ዙር የሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ሀገሪቱ በመዘጋጀት ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡የግብፅ መስኖ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢንጂነር ሞሐመድ ጋኔም ትላንት ለ አልአረቢያ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ግብፅ ሁለተኛው ዙር የሕዳሴ ግድብ ሙሌት ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡ ቃል አቀባዩ የግድቡን 2ኛ ዙር የውሃ ሙሌት ተጽዕኖ ለመቀነስ በመስኖ መስክ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ወደ ትግበራ መግባታቸውን አንስተዋል፡፡ ይሁን እና በዓባይ ውሃ ላይ ያለንን ታሪካዊ መብት እንዳልተውን እናረጋግጣለን በማለት በውሃ ክፍፍል ረገድ ግብፅ ያላት አቋም የጸና መሆኑን ገልጸዋል፡፡ቃል አቀባዩ አክለውም በሕዳሴ ግድብ ጉዳይ የሁሉም ወገኖች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የምንጥር በመሆኑ ኢትዮጵያ ከግብፅና ከሱዳን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ የተወሰነ የአቋም ለውጥ ማሳየት አለባት ብለዋል፡፡መረጃ ከመለዋወጥ በፊት በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ላይ መድረስ እንፈልጋለን ሲሉም ነው ኢንጂነር ሞሐመድ የሀገራቸውን አቋም የገለጹት፡፡ ### Response:
### Text: ለኩ ከዛሬ ሁለት ቀን በፊት የለኩ ወዳጆቼንጉዳዩን በቅርበት ሲከታተሉ የነበሩ የተዘረፉ ንብረቶች በአንዳንድ አመራሮች ቤት ተገኝተዋል የሚል ነገር ሰማሁ ምን ያህል እውነት ነው ብዬ ጠይቄያቸውን ይህ ነበር የመለሱልኝእንዴት ዋልክ ፀጊሽ እውነት ነው ዛሬ ጠዋት ጀምሮ ትናንትናም ልዩ አይል በደረገው ብርበራ ንብረቶች እየተገኙ ነው። ፀጊሽ እውነት ነው ከንቲባው መታሰሩንም ነግሬክ ነበር። ዛሬ ከነጋም ብኋላ ንብረት ሲያሸሹ እየተያዙ ነው ፖሊሶች ቤት እናም አንዳንድ አመራሮች ቤት ንብረት ተገኝቶአል። እውነት ነው ፀጊሽ ወደ ገጠር ድረስ ገብተው አጋዜ ልዩ አይል ንብረት እያስመለሰ ነው ፀጊሽ ዛሬ ከነጋ አንድ መኪና ተጨማሪ ሀይል ገብቶ አሰሳው ተጠናክሮ ቀጥሉአል። ትናንትና አንድ ፖሊስ የዘረፈው ፍራሽ ላይ ቁጭ ብሎ የዘረፈውን መጠጥ ቁጭ ብሎ ሲጠጣ ተደርሶበት በልዩ አይሎች ተደርሶበታል እይልኝ እንግዲ ፀጊሽ የዚህ አይነቱ ነው ህዝቡንና አገሪቱን እንዲ እንድትሆን ትልቁን ሚና የተጫወቱት እንደዚህ አይነት ሆዳሞች ናቸው እግዚሃብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይጠብቅ።አዎ የተያዘው ንብረትማ ከከተማው ጥግ ጥግ ካሉት ቤቶች በበርካታ መኪኖች እየተመለሱ ነው ወደ 3 የሚጠጉ የፖሊስ አባላት ቤት ውስጥም ተገኝቷል እነሱም በመከላከያ ሰራውት እየተለቀሙ ነው ### Response:
### Text: ኢምፔርያል ሆቴል አካባቢ እየተገነባ ያለው የመሻገሪያ ድልድይ ፕሮጀክት ፕሮጀክቱ የጀመረው የካቲት ወር 2013 ዓም የተጀመረ ነው። ግንባታው በቻይና ዓለም አቀፍ ኩባንያ ነው የሚካሄደው። በ791 ሚሊዮን ብር በጀት ነው እየተገነባ ያለው። 18 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። ይህ ፕሮጀክት በከተማው ውስጥ ከሚገነቡት 7 የማሳለጫ ፣ ዋሻ እና የመሬት ስር መተላለፊያዎች መካከል አንዱ ነው። ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ የተያዘው ጊዜ 1 ዓመት ከ8 ወር ሲሆን ቀደም ብሎ ለማጠናቀቅ እና መንገዱን ለተሽከርካሪ ክፍት ለማድረግ በቀን እና በማታ ከመደበኛ ስራ ሰዓት ውጪ ፣ በዝናብ ወቅትም እየተሰራ ነው። ተሻጋሪ ድልድዩ 14 ሜትር ስፋት አለው በአንድ ጊዜ በአንድ በኩል ሁለት መኪኖችን በአጠቃላይ 4 መኪኖችን ማስተላለፍ ይችላል። የመገናኛውን አቅም ለማሳደግ የግራ ታጣፊዎችን በመከልከል በመገናኛ እና በቦሌ አቅጣጫ በኩል ሉፖች ይኖሩታል። በአንድ ጊዜ ሁለት መኪና ብቻ በሁለት አቅጣጫ መልቀቅ እንዲቻል በማድረግ በሚገነባው ሉፕ በኩል የግራ ታጣፊዎች መስተናገድ እንዲችሉ አካባቢው ላይ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ የሚቀንስ ነው ተብሏል። በኢምፔሪያል አካባቢ በቀን ውስጥ እስከ 70 ሺህ ተሽከርካሪዎች ይስተናገዳሉ። ኢር ሞገስ ጥበቡ የአአ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ### Response:
### Text: የህፃኑ አገዳደል የሁላችንም ስሜት የነካ ቢሆንም ህብረተሰቡ የተፈጠረውን ችግር በሰከነ መልኩ ሊያየው ይገባል የጎንደር ከተማ ፖሊስየጎንደር ከተማ ፓሊስ መምሪያ የእገታ ወንጀልን ለመከላከል ህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቀረበ።የመምሪያው ኃላፊ ኮማንደር አየልኝ ታክሎ መስከረም 3 ቀን 2014 ዓም በከተማዋ የ13 ዓመት ህፃን የእገታ ወንጀል መፈፀሙን አመልክተዋል።ለመምሪያው የእገታ ወንጀሉ ጥቆማ መስከረም 5 ቀን 2014 ዓም እንደደረሰው የገለፁ ሲሆን ጥቆማው ከደረሰ ጀምሮ የክትትል ስራዎችን ሲያከናውኑ መቆየቱን አስታውሰዋል።በኃላም በከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ አካላትና የላይ አርማጭሆ ወረዳ የፀጥታ አካላት ስራ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ገልፀዋል።ይሁን እንጅ የታገተውን የ13 ዓመት ህፃን ለማስለቅ የተደረገው ጥረት ህፃኑን በህይወት ለመታደግ እንዳልተቻለ አመልክተዋል።ኮማንደር አየልኝ በድርጊቱም እንደ ፓሊስ መምሪያ ስሜታችን ክፉኛ ተጎድቷል ብለዋል።በተፈፀመው ድርጊትም ማዘናቸውን ገልፀዋል።በድርጊቱ የተሳትፈዋል የተባሉ 2 ግለሰቦችን ፓሊስ በህግ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን በድርጊቱ የተሳተፉና ተባባሪ ግለሰቦች ሊኖሩ ይችላሉ በሚል ጥርጣሬ ምርመራው መቀጠሉን አሳውቀዋል።ያንብቡ 0924 ### Response:
### Text: በቀጣይ ተመሳሳይ አድማዎች እንዳይደረጉ ኮማንድ ፖስቱ እቅዶችን ነድፎ እየሰራ ነውየአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ ወዲህ አንዳንድ ችግሮች ቢከሰቱም የአገሪቱን ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ከማረጋጋጥ አንጻር አይነተኛ ሚና አየተጨዋተ መሆኑን የኮማንድ ፖስቱ ዋና ሴክሬታርያት ሲራጅ ፈጌሳ አስታወቁ፡፡ አዋጁ ከታወጀ ወዲህ ዜጎች የደህንነት ስሜት ቢሰማቸውም በአንዳንድ ኦሮሚያ አከባቢዎች አድማዎች መደረጋቸውንና የህዝብ አገልግሎት መስጫ ትራንስፖርቶች መስተጓገላቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ግን ከአንዳንድ ረጃጅምመስመሮች በስተቀር ሰላምና መረጋጋት እየተመለሰ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ዜጎች ማንኛውም ችግር ቢገጥማችው በአከባቢያቸው ለሚገኝ ኮማንድ ፖስት በመጠቆም ሰላማቸውን ነቅተው እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እውነታኛ የህዝብ ጥያቄ ቢኖርም ያንንየህዝብ ጥያቄ መሰረት በማድረግ የጥፋት ሀይሎች አጀንዳውን ጠልፈው ለራሳቸው ጥቅም በማዋል ህብረተሰቡን እያሳሳቱት ይገኛሉ ብለዋል አቶ ሲራጅ፡፡የጥፋት ኃይሎች መንግስት የደከመ ቢመስላቸውም መንግስት አሁንም ጠንካራ መሆኑን ሊያውቁ ይገባል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ተመሳሳይ አድማዎች እንዳይደረጉ ኮማንድ ፖስቱ ዝርዝር ዕቅዶችን አውጥቶ እየሰራ መሆኑን አስውቀዋል፡፡ምንጭ ኢቢሲ ### Response:
### Text: ጠሚ ዶር አብይ ወጣቶችን በአመራርነት ለማብቃት መንግስት አመቺ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ገለፁጠቅላይ ሚንስትር አብይ ዶር ይህን የገለፁት የነገዋ ኢትዮጵያ መሪዎችን ማነቃቃት በሚል በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በተካሄደ መድረክ ላይ ነውጠቅላይ ሚኒስትር አብይ እንዳሉት ወጣቶች የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ትራንስፎርሜሽን እውን ለማድረግ ሚናቸው ትልቅ ነው፣ በመሆኑም የሀሪቱን ቀጣይ እድገት ለማረጋገጥ በየመስኩ የመሪነቱን ሚና ሊወስዱ ይገባል ብለዋልለወጣቱ አርዓያ የሚሆኑ በተለያዩ ዘርፎች የአመራር ኃላፊነታቸውን በስኬት እየተወጡ የሚገኙ ግለሰቦችን የማስተዋወቅ ስራም እንደሚሰራም ገልፀዋልበመድረኩ የተገኙት የቀድሞው የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚንስትር ቶኒ ብሌር ኢትዮጵያ ባለፉት አስርት አመታት በኢኮኖሚም ሆነ ማህበራዊ ጉዳዮች ላመጣችው ለውጥ እውቅና ሰጥተዋል በዚህ ለውጥም የወጣቱ ሚና የጎላ እንደነበርም ተናግርዋል አሁንም የኢትዮጵያን የከፈተኛ እድገት ራዕይን ለማሳከት የወጣቶችን እምቅ አቅም መጠቀም አስፈላጊ ነው ብለዋልለዚህም ድርጅታቸው ቶኒ ብለር ኢንስቲቲዩት ፎር ግሎባል ቼንጅ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋልምንጭ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ### Response:
### Text: አቶ ተስፋዬ እና አቶ ማርክስ️የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ የወንጀል ችሎት በቀድሞዎቹ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባልደረቦች አቶ ተስፋዬ ኡርጌ እና አቶ ማርክስ ፀሃዬ ላይ ፖሊስ የጠየቀውን የጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ።ማርክስ ፀሃዬን በተመለከተ መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው ጊዜ ተገቢውን ስራ መስራቱን ገልጾ ቀሪ ስራዎችን ለመስራት የ14 ቀን ጊዜ ጠይቆ ችሎቱ በከፊል ተቀብሎታል።ከሰኔ 16ቱ ጥቃት ጋር በተያያዘ የቀረበባቸው አዲስ የወንጀል ተሳትፎን በተመለከተ ማቅረብ አይገባም የሚል የህግ ክልከላ አለመኖሩን በመጥቀስም መርማሪ ፖሊስ ይቀረኛል ያለውን ስራ አጠናቆ እንዲመጣ ከታህሳስ 8 ቀን ጀምሮ የሚታሰብ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።በከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ጋር በተያያዘም ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ችሎቱ ፈቅዷል።ተጠርጣሪው በእስር ቦታ ላይ ሰብዓዊ መብቴ እየተጣሰ ነው በሚል ያቀረቡትን አቤቱታ ፖሊስ አጣርቶ እንዲያቀርብ ችሎቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።ከዚህ ባለፈም ግለሰቡ ደመወዛቸው በፍርድ ቤት ሳይታገድ እየተከፈላቸው አለመሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል።ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ ጉዳዩ እንዲፈታ እንዲያግዛቸው ትዕዛዝ አስተላልፏል።ምንጭ ፋና ብሮድካስቲንግ ### Response:
### Text: በጋምቤላ ፈቃድ የሌላቸው 11 የውጭ ኮሌጆች ተገኙ ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ እንደተደረሰባቸው፣ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ኤጀንሲው ከተለያዩ ግለሰቦች በደረሰው ጥቆማ መሠረት ወደ ክልሉ ተንቀሳቅሶ የለያቸው እነዚህ 11 ተቋማት በድኅረ ምረቃና በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች0ተማሪዎችን እየተቀበሉ እንደሚያስተምሩ ለሪፖርተር የገለጹት፣ የኤጀንሲው የኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ገረሱ ናቸው፡፡ከኤጀንሲው ፈቃድ ሳያገኙ ሊያስተምሩ የተገኙት 11 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በአገር ውስጥ የማይታወቁና እንግዳ መጠሪያ ያላቸውና ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡በተደጋጋሚ በደረሰን ጥቆማ መሠረት ለማጣራት ወደ ክልሉ ስናመራ የጠበቅነው አንድ ተቋም ብቻ ነበር፡፡ ስንደርስ ግን 11 ሆነው አገኘናቸው፡፡ በወቅቱ ምንም ማድረግ ስላልቻልን ለክልሉ መንግሥት ስለሁኔታው በማስረዳት የክልሉን ነዋሪዎች ከሕገወጦች እንዲጠብቅ ደብዳቤ ጻፍን የሚሉት አቶ ታረቀኝ፣ ለክልሉ ደብዳቤ ከተጻፈ ስድስት ወራት የተቆጠረ ቢሆንም ምንም ዓይነት ምላሽ ለኤጀንሲው አለመድረሱን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ሪፖርተርጋዜጣ ተጨማሪ የንብቡ 08283 ### Response:
### Text: 5 በባለቤቶቻቸው እውቅና የሌላቸው ገፆች️ ቴሌግራም 1 በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ስም የተከፈተው እና 5770 ያሉት የቴሌግራም ቻናል የ አይደለም። በይፋ ይህ ነው የኔ ቻናሌ ብሎ ያሳወቀው የቴሌግራም ቻናል የለም። ፌስቡክ 1 ይህ 149000 ያለው የፌስቡክ ገፅ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ትክክለኛ ገፅ አይደለም። ይህ ብዙ ተከታይ ይለው ገፅ በርካቶችን ያደናግራል ተጠንቀቁ። የኤጀንሲው ትክክለኛው ገፅ 119000 ያለው ነው። ኤጀንሲው ገፁን በፌስቡክ ቢያስደርገው መልካም ነው።2 ይህ 7740 ሺህ ያለው ገፅ ሀሰተኛ ነው። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ሊቀ መንበር ዶር ደሳለኝ ጫኔ በፌስቡክ ላይ የላቸውም። ጥንቃቄ ይደረግ3 አማርኛ ይህ ከ 4 ሺህ በላይ ያለው የፌስቡክ ገፅ ሀሰተኛ ነው። ትክክለኛው የ አማርኛ የፌስቡክ ገፅ የተደረገና ከ300 ሺህ በላይ ያለው ነው።4 ይገርማል ይህ ከ286000 በላይ ህዝብ የሚከተለው ገፅ ሀሰተኛ ነው። ብዙ የሀሰት መረጃዎች የሚሰራጩበት በመሆኑ ጥንቃቄ ይደረግ። ትክክለኛው የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ዳይሬክተር አቶ ጃዋር መሃመድ የፌስቡክ ገፅ የተደረገ ነው። ልብ በሉ አይደለም ትግርኛድምፂ ወያነ የትግርኛው አገልግሎት የፌስቡክ ገፅ ከ163 ሺህ በላይ ሰዎች የሚከተሉት ነው። የአማርኛው አገልግሎት ገፅ ደግሞ ከ46 ሺህ በላይ ያለው ነው። ቲክቫህ ### Response:
### Text: ነሃሴ 282012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 2 በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2802 የላብራቶሪ ምርመራ 86 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ከከምባታ ጠምባሮ ዞንበቫይረሱ የተያዙት ከደቡብ ኦሞ 34 11 ከጂንካ ከተማ፣ 9 ከማሌ፣ 5 ከባካዳውላ፣ 3 ከሐመር፣ 2 ከበናፀማይ፣ 2 ከኡባአሪ፣ 1 ደቡብ አሪ እና 1 ከኛጋቶም፣ ከጋሞ 13 8 ከአርባምንጭ ዙሪያ፣ 3 ከቁጫ አልፋ እና 2 ከአርባምንጭ ከተማ ፣ ከቤንች ሸኮ 12 11 ከሚዛን ከተማ እና 1 ከደቡብ ቤንች ከጉራጌ 11 11ዱም ከቡኢ፣ ከወላይታ 6 4 ከሶዶ ከተማ፣ 1 ከቦሎሶ ቦንቤ እና 1 ከዱጉና ፋንጎ ፣ ከጌዴኦ 5 2 ከጮርሶ፣ 2 ከረጲ እና 1 ከኮቾሬ ፣ ከጎፋ 4 4ቱም ከመለኮዛ ፣ ከካፋ 1 ቦንጋ ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች ናቸው። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 377 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 64 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 438 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 10 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 187 የላብራቶሪ ምርምራ የተደረገ ሲሆን 11 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1108 ላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 91 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል። ### Response:
### Text: የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ኃይል አዲስ አበባ ውስጥ ተከታታይ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ላካሂድ ነው አለ።ግብረ ኃይሉ በላከው መግለጫ በተለያዩ ጊዜያት የአዲስ አበባ ከተማን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ሲያካሄድ ቆይቷል ብሏል።አሁን ላይ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የፀጥታ ችግሮችን ለመፍጠር የተዘጋጁ ኃይሎች እንዳሉ ደርሼባቸዋለሁ ያለ ሲሆን ይህንን ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማ ተከታታይ የተቀናጀ ኦፕሬሽን አካሂዳለሁ ሲል አሳውቋል።ኅብረተሰቡ ይህን አውቆ ትብብር እንዲያደርግ በአካባቢው ላይ ፀጉረ ልውጦች ን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥ እና አካባቢውን እንዲጠብቅ አሳስቧል። ኅብረተሰቡ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች እንዲሁም በስልክ ቁጥር 251111110111 ፣ 251115526303 ፣ 251115524077 ፣ 251115543678 0 251115543681 ፣ 251115543684 ፣ 251115543804 ፣ 251115312208 ፣ 251115312223 ፣ 251115312247 ፣ 251115312220 ፣ 251115312063 ፣ 251115312033 ፣ 251115312131 ፣ 251115312221 ፣ 251115312042 ፣ 251115312005 ጥቆማዎችን በፍጥነት በመስጠት ወይም በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች መረጃውን በአካል በማድረስ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ሲል ጥሪውን አቅርቧል። የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ በቀጣይ የሚደርስበትን ውጤት ለሕዝብ እየገለፅኩኝ እሄዳለሁ ብሏል። ### Response:
### Text: ትላንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለ የምትሰጠውን ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታቅብ ተናገረዋል። የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪድ19 የዓለም አቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን በጊዜ አልተናገረም ብለዋል ፕሬዘዳንቱ። ድርጅቱ ይህን ያደርገው በሽታው ለተጀመረባት ቻይና ሲል ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምት አዘል አነጋገር ተናግረዋል። በጣም ቻይና ተኮር ይመስላሉ ፣ ይህን ማጤን ይኖርብናል ሲሉ ተደምጠዋል ዶናልድ ትራምፕ። በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ባለበት በዚህ አይነት ሁኔታ ለጤናው ድርጅት የሚዋጣ ገንዘብ መከልከ ተገቢ ነው ወይ ተብለው ከጋዜጠኛ የተጠየቁት ትራምፕ እኔ አንሰጥም አላልኩም፣ እናጤነዋለን ነው ያለኩት ሲሉ መልሰዋል።ከፍተኛ ዘመቻ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶር ቴድሮስ አድሃኖም ዛሬ በሰጡት ዕለታዊ መግለጫቸው ላይ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው እሳቸው ግን ግድ እንዳልሰጣቸው ተናግረዋል። በማን ይህ ሊደረግ እንደቻለ ግን አልተናገሩም።ከሁለት 2 እና ከሦስት 3 ወር በላይ ዘረኛ ጥቃቶች ተሰንዝረውብኛል ያሉት የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተሩ ዶር ቴድሮስ ጥቁር ተብያለሁ። እውነቱን ለመናገር እኔ በጥቁርነቴ እኮራለሁ። የሚባለው ነገርም ግድ አይሰጠኝም ሲሉም ተደምጠዋል።ምንጭ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ ### Response:
### Text: ቪድዮ በጀርመን ስቱትጋርት ከተማ ቅዳሜ የኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎች ከፖሊስ ጋር ተጋጭተው በመቶዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያን በቁጥጥር ሥር ውለዋል።ሁከቱ የተፈጠረው የኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች በከተማዋ የባሕል ፌስቲቫል ማዘጋጀታቸውን ተከትሎ ተቃዋሚዎች ሥነስርዓቱን ለማወክ ሁከት ከፈጠሩ በኋላ ነው።ተቃዋሚዎቹ በጀርመን ፖሊስ አባላት ላይ ጥቃት አድርሰው በአጠቃላይ 26 የፖሊስ አባላት የተጎዱ ሲሆን ከ6 የማያንሱ አባላት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።የስቱትጋርት ከተማ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ወደ ስፍራው የተሰማራው ፖሊስ በሁለቱ ቡድኖች መካከል ያልጠበቀው ከባድ አመጽ አጋጥሞታል ብለዋል።ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ተቃዋሚዎቹ በዱላ፣ በሚስማር፣ በብረት፣ በጠርሙስ እና በድንጋይ የጀርመን ፖሊስ አባላት ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።ሁከቱን ተከትሎ 228 ኤርትራውያን በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተገለጸ ሲሆን በሁከቱ ምን ያክል ኤርትራውያን ጉዳት እንደደረሰባቸው እስካሁን የተባለ ነገር የለም።ከጥቂት ሳምንታት በፊት በእስራኤል መዲና ቴል አቪቭ መሰል ሁከት ተከስቶ የአገሪቱን መንግሥት ማስቆጣቱና ጠ ሚንስትር ኔታኒያሁ አፍሪካውያን ስደተኞች በሙሉ በአስቸኳይ ከእስራኤል ምድር ለማባረር የሚያስችል እቅድ እንዲወጣ ትዕዛዝ መስጠታቸው ይታወሳል። ### Response:
### Text: አዳዲስ መኪኖች ላይ የቀረጥ ቅናሽ ተደረገ ዓለም ዐቀፉ የጉምሩክ ድርጅት በየአምስት ዓመቱ የሚያሻሽለውን የታሪፍ መጽሐፍ መሰረት በማድረግ ከሁለት ዓመት በፊት ተከልሶ መጠናቀቅ ይገባው የነበረውን የታሪፍ መፅሐፍ በማዘጋጀት ያፀደቀው የገንዘብ ሚኒስቴር አዳዲስ መኪኖች ላይ የአምስት በመቶ የቀረጥ ቅናሽ አደረገ።የታሪፍ መጽሐፉ ለተሽከርካሪ ምርቶች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እና ከዚህ ቀደም ከሦስት ገፅ ባልበለጠ የተዘረዘረውን ሰንጠረዥ ከ 34 ገፅ በላይ ከፍ በማድረግ አሻሽሏል። የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የትራንስፖርት ባለሥልጣን በጋራ በመሆን ከአንድ ዓመት በላይ በፈጀ ጊዜ ባካሔዱት ጥናት መሰረት የታሪፍ መጽሐፉ ዝርዝር መዘጋጀቱን ለማወቅ ተችሏል።በተሸከርካሪ ላይ ከተደረጉት ማስተካከያዎች መካከል አንዱ ከአስር ዓመት በላይ እና በታች በመለየት በመጽሐፉ ላይ ለሁለት መከፈሉ ሲሆን፣ ከአንድ ዓመት እስከ አስር ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችም በየዓመቱ የተከፋፈሉበት ነው። ምንም እንኳን ከአንድ ዓመት በላይ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ላይ ተመሳሳይ 35 በመቶ ቀረጥ ቢጣልባቸውም ወደፊት በሚወጡ ሕጎች መሰረት በዓመት በተከፋፈሉት ተሽከርካሪዎች ላይ ሕግ አውጪው የተለያዩ ቅጣቶችን ሊጥል እንደሚችልም ተጠቁሟል። 1021 ### Response:
### Text: ጉዳዩ ማስታወቂያዎች ለጥቂት ቀናት ማቆማችንን ስለማሳወቅለድርጅት ባለቤቶች ለሆናችሁ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትበእንዲህ ያለ ወቅት በተለይም የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት እየተፈጠሩ ባሉ ክስተቶች ዙሪያ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲያገኙ ፣ በተለያዩ ሚዲያዎችም የሚሰራጩ መረጃዎች በፍጥነት ይደርሳቸው ዘንድ እንደምንሰራ ይታወቃል። እንዲህ ያለሁ ክስተቶች ሲፈጠሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመልካች ቁጥር በሰዓታት ውስጥ በመቶ ሺህ የሚቆጠር እንደሆነም ይታወቃል ይህን መሰል ወቅት ወቅታዊ ጉዳዮች አሳስቧቸው መረጃ በሚከታተሉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ስልኮች ላይ ምንም አይነት የድርጅት ማስታወቂያ አናሰራጭም። ይህ አሁን የጀመርነው እንዳልሆ እና ከዚህ ቀደምም ለበርካታ ጊዜያት ስናደርግ የቆየነው እንደሆነም ለማስታወስ እንወዳለን። ረጅም ጊዜ ከቲክቫህ ጋር አብራችሁ የቆያችሁ ድርጅቶችም አሰራራችን እና የምንከተለውን መንገድም እንደምታውቁት ተስፋ እናደርጋለን። የቲክቫህ አባል የሆናችሁ የድርጅት ባለቤቶች ማስታወቂያ የማስነገር ሙሉ መብት እንዳላችሁ ብናውቅም በእንዲህ ያሉ ወቅቶች ግን የድርጅቶቻችሁን ማስታወቂያ ማስተናገድ አንችልም ለዚህም ይቅርታ እንጠይቃለን።ከጥቂት ቀናት በኃላ ማስታወቂያዎች ይቀጥላሉ 0919743630 ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ ተጨማሪ 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧልባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 1047 ላቦራቶሪ ምርመራ አምስት 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር መቶ አርባ አምስት 145 ደርሷል።የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ታማሚ 1 የ75 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የሌላቸው በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት በመጣራት ላይ ያለ በጤና ተቋም ተኝተው ከሚታከሙ ህሙማን ከተወሰደ ናሙና የተገኘታማሚ 2 የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ የመኖሪያ ቦታ አፋር ከጅቡቲ የተመለሰና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።ታማሚ 3 የ22 ዓመት ኢትዮጵያዊ የመኖሪያ ቦታ አፋር ከጅቡቲ የተመለሰና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።ታማሚ 4 የ8 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የላትም በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላት ።ታማሚ 5 የ19 ዓመት ኢትዮጵያዊት የመኖሪያ ቦታ ኦሮሚያ ባቱ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላት ።ተጨማሪ መረጃ በትላንትናው ዕለት 16 ሰዎች 15 ከአዲስ አበባ እና 1 ከአማራ ክልል ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ዘጠና አንድ 91 ደርሷል። ### Response:
### Text: የፍርድ ቤት ውሎ️በሃገር ኢኮኖሚ ላይ አሻጥር በመስራት እና በኢኮኖሚ ላይ ጫና ማሣደር ወንጀል ተሣትፈዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የነበሩ 9 የሲቪል አቪዬሽን የአየር ትራፊክ ቁጥጥር ሰራተኞች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ቡድን በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት በአቀረበው የምርመራ መዝገብ ተጠርጣሪዎች በቡድን በመደራጀት መንግሥትና ህዝብን ለማለያየት ተንቀሣቅሰዋል የሚለውን ጠቅሷል፡፡ወርሀዊ ደሞዛቸው በአስር እጥፍ እንዲያድግና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች አልተከበሩልንም በማለት ከነሐሴ 21 ጀምሮ የሥራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውንም ፖሊስ ጠቅሷል፡፡ለዚህም እንዲረዳቸው የሌሎች ሰራተኞችን ፊርማ በማስመሰል መፈረም እና ስራ እንዲያቆሙ አነሣስተዋል በሚል ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር እንዲውሉ ካደረጓቸው ምክንያቶች ይጠቀሣል የሚለውንም የምርመራ ቡድኑ በመዝገቡ አካቷል፡፡ቡድኑ ሌሎች የምርመራ ስራዎችን ለማከናወን 14 ቀን ጠይቋል። ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው የመብት ጥያቄዎችን ማንሣታቸውን በመጥቀስ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸው እንዲያከብርላቸው አመልክተዋል፡፡ግራቀኙን የተመለከተው ችሎት ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀን 8 ቀን በመፍቀድ ለመስከረም 2 2ዐ11 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡© ### Response:
### Text: ፌደራል ፖሊስ️በአዲስ አበባ ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውለው በጦላይ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ ወጣቶች በያዝነው ሳምንት እንደሚለቀቁ ተገለፀ።ወጣቶቹ ከመስከረም 2 እስከ መስከረም 8 2011 ዓም በአዲስ አበባ ከተማ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት።የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል ለ እንደተናገሩት በመንግስት በኩል በቁጥጥር ስር ለዋሉት ወጣቶቹ እስካሁን የተለያዩ ስልጠናዎችን ሲወስዱ ቆይተዋል።በጦላይ ለአንድ ወር እራስን ከወንጀል ስለማራቅ እና ተያያዠ ስልጠናዎችን ለመስጠት የተያዘው የጊዜ ሰሌዳም የፊታችን ሀሙስ ይጠናቀቃል ብለዋል ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል።አስፈላጊው ሎጀስቲክስ ሚሟላ ከሆነ ወጣቶቹ የፊታችን ሀሙስ ካልሆነ ደግሞ እስከ መጪው ቅዳሜ ድረስ የሚለቀቁ መሆኑን ገልጸዋል።አቶ ዘይኑ ወጣቶችን አስተምሮ ከመልቀቅ ባለፈ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመነጋገር ስራ አጥ የሆኑትን በጥቃቅንና አነስተኛ አደራጅቶ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።በከተማዋ በነበረው የጸጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ውለው ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ 1 ሺ 204 ወጣቶች ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ በወንጀል የተጠረጠሩት 83 ወጣቶች በህግ የሚጠየቁ ናቸው ብለዋል።ምንጭ ### Response:
### Text: ሹመት️የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ወሮ መዓዛ አሸናፊን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾመ፡፡የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይአህመድ ናቸው ተሿሚዋን ተሰናባቹን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዳኜ መላኩ ተክተው እንዲሰሩ በእጩነት ያቀረቧቸው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አህመድ ወሮ መዓዛ ባላቸው የዳበረ ልምድ ምክንያት የአገሪቱን የፍትህ ስርዓቱ ወፊት ያራምዱታል በሚል በእጩነት እንዳቀረቧቸው ለምክር ቤቱ ተናግረዋል፡፡በዚህም መሰረት ወሮ መዓዛ አሸናፊ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ይሁንታውን ሰጥቷቸዋል፡፡ወሮ መዓዛ አሸናፊ በህግ የዳበረ ልምድ ያላቸው ፣ በተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ከፍተኛ ተቋማት ውስጥ በማገልገል አንቱታን አትረፈዋል፡፡ከህገ መንግስት አርቃቂ ከሚሽን አባልነት በግላቸው ለሴቶች ከለላ የሚሆን ድርጅት እስከማቋቋምም ደረሰዋል፡፡በመሆኑም በዛሬው ዕለት የተሰጣቸው የጠቅላይ ፍርድቤት ፕሬዝዳንትነት ሹመት በፍርድ ቤቱ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት ያደርጋቸዋል፡፡ወሮ መዓዛ አሸናፊም ቃለ መሃላ ፈፅመው በህዝብና በመንግስት የተጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ቃል ገብተዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: ከሰሞኑን በሀገሪቱ ከነበረው ግጭት ጋር ተያይዞ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እየዋሉ እንደሚገኙ ተገልጿል የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስቴር ሰሞኑን በሀገሪቱ በተከሰቱ ግጭቶች ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በየደረጃው ካሉ የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆኑን አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ከሃይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአባ ገዳዎች፣ ከወጣቶች፣ ከሴቶች እና ችግሩ ከተፈጠረባቸው አካባቢ አመራሮች ጋር በመሆን ግጭቱ የብሔር መልክ እና የሃይማኖት መልክ ይዞ እንዳይስፋፋ ማድረጉን ገልጿል።ከብሔራዊ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን እና ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተውጣጡ ግብረ ኃይሎች ለተጎጂዎች እርዳታ እያቀረቡ ነው ብሏል። በዚህም 878 ኩንታል የምግብ፣ 712 ካርቶን ብስኩት፣ እንዲሁም ምግብ ነክ ያልሆኑ 10 ሺህ 280 የቤት ቁሳቁሶች ተደራሽ መሆናቸውን ነው የተጠቀሰው።የሰላም ሚኒስቴር በህዝቦች መካከል መተማመን እንዲኖር መጣር፣ የሀሳብ ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያና በህግ ስር መፍታት አስፍላጊ መሆኑን ተናግሯል። ሚኒስቴሩ ሰሞኑን የተከሰተው ግጭት እንዳይባባስ የድርሻቸውን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ያበረከቱትን በማመስገን ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። ### Response:
### Text: ከኮቪድ19 ጀርባበዶክተር መክብብ ካሳየአስራ ስምንት 18 አመቷ እንግሊዛዊት ሜሪየም ዘመር ከዚህ በፊት ሆስፒታል የሚያስተኛ ህመም ገጥሟት አያውቅም፡፡ከሆስፒታል ስልክ የተደወለላቸው አባቷ ልጃቸው ከባድ የሆነ የትንፋሽ ማጠርና የደረት ህመም እንዳጋጠማትና በአምቡላንስ ሆስፒታል መወሰዷ ይነገራቸዋል፡፡ከሰዓታት በኃላ ችግሩ እየተባባሰ ሄዶ ፅኑ ህሙማን ክፍል መግባት እንዳለባት ይነገራቸዋልከባድ ድንጋጤ ውስጥ ገባሁእግሮቼ የራሴ አልመስል አሉኝ ይላሉ አባት፡፡ከሰዓታት በኃላ አያትና እናቷ ቫይረሱ ባስከተለባቸው ህመም ምክንያት ተከታትለው በአምቡላንስ መጡ አያቷ በጠና ታመው ነበር፡፡ ቀናት አለፉ ሜሪየም ከህመሟ አገግማ ቤት እንደተመለሰች የአያቷ ህልፈት ተነገራትበህይወቷ ከባዱን ጊዜ አሳለፈች፡፡ይህ የብዙዎች ታሪክ እየሆነ ነው እኛም ሀገር ተመሳሳይ ታሪኮች እንዳይገጥሙን አሁንም እንጠንቀቅ፡፡ በተለይ ወጣቶች ህመሙ እኛም ላይ ሊበረታ እንደሚችል ማሳያ ነው ስለዚህ አንዘናጋ፡፡ማስታወሻ ጭንብሎችን ስንጠቀም አፍንጫና አፋችንን በትክክል መሸፈኑን እናረጋግጥ፣ የእጅ ንፅህና መጠበቅ አሁንም አስፈላጊ መሆኑን አንርሳ፣ ርቀታችንን እንጠብቅ፡፡ከተሳሰብን ካልተሰላቸን ከፈጣሪ እርዳታ ጋር ይህን ከባድ ጊዜ በቀላሉ እናልፈዋለን ### Response:
### Text: የአሜሪካ ምክር ቤቶች የጆ ባይደንን የምርጫ ውጤት አረጋገጡ።የሁለቱ ምክር ቤት እንደራሴዎች የተሰጡትን የውክልና ድምጾች ኤሌክቶራል ቮት በመቁጠር ጆ ባይደን ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውን አረጋግጧል።ኮንግረስ ጆ ባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሀሪስን የቀጣዮቹ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት በማድረግ ያገኙትን ድምጽ አጽድቋል ።የተሰጡት የውክልና ድምጾች የጸደቁት የሁለቱ ምክር ቤት ተወካዮች በፔንሰልቫንያ እና አሪዞና ግዛቶች የቀረበውን ተቃውሞ ውድቅ ካደረጉ በኋላ ነው።የአገሪቱ ሕዝብ እንደራሴዎች ተሰብስበው ቀጣዩ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የምርጫ ውጤት ዙሪያ በመነጋገር ላይ ሳሉ በድንገት በሺህ የሚቆጠሩ የዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች ምክር ቤቱን ሰብረው ገብተው ነበር።በዚህ የተነሳ ተቋርጦ የነበረው የምክር ቤቶቹ የጋራ ስብሰባ ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ቀጥሏል።ዋሺንግተን ውስጥ የተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች የአገሪቱን ምክር ቤት ጥሰው መግባታቸውን ተከትሎ በተፈጠረ ፍጥጫ 4 ሰዎች ሞተዋል።በተቀሰቀሰው ግርግር ሳቢያ የዋሺንግተን ከንቲባ በከተማዋ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ ጥለዋል። የካፒቶል ሂል አካባቢም ሙሉ በሙሉ ዝግ እንዲሆን ተደርጓል። ### Response:
### Text: የፖሊስ መልዕክት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ምንም በማያውቁት ጉዳይ በህጻናቱ ላይ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ወንጀል ሁሉንም በእጅጉ አሳዝኗል።ወላጆች የሚቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችን ማንነት ጠንቅቀው ማወቅ ይገባቸዋል።እንደ ቤተሰብ ሆነው የሚኖሩ የቤት ሠራተኞች እንዳሉ ሁሉ እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ወንጀል የሚፈጽሙም ስላሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። ተጨማሪመረጃ በአንድ ቀን በአሰቃቂ ሁኔታ ሁለት ታዳጊ ልጆቻቸውን ያጡት ወላጆች በከባድ ሐዘን ውስጥ ይገኛሉ። ወንጀሉ በተፈጸመበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም በእጅጉ ተረብሸው ነው የሚገኙት። ፖሊስ በወንጀሉ ዙሪያ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ ነው። ተጠርጣሪዋ ህጻናቱን አንቃ እና ስለት ተጠቅማ በአስቃቂ ሁኔታ መግድሏ የሚያመላክቱ መላምቶች አሉ። ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ለማወቅ ምርመራዎች እየተካሄዱ ነው። በወንጀሉ የተጠርጠረችው ግለሰብ በቤት ሠራተኛነት ግድያው ለተፈጸመበት ቤተሰብ ስታገለግል ቆይታለች። ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን የፈጸመችው ወላጆች የሌሉበትን ሰዓት ጠብቃ ነው።መረጃው ምኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የአማርኛ አገልግሎት ከሰጡት ቃል የተወሰደ ነው። ### Response:
### Text: ቦንጋ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሥነሥርዓት አዳዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ሥራ ጀምሯል።ከአዳዲስ አሥራ አንዱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ የሆነው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 262010 ዓም የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት ደማቅ የሥራ ማስጀመሪያ ምረቃና የተማሪዎች ቅበላ ሥነሥርዓት አካሄዷል፡፡ዩኒቨርሲቲው አዲስ ተማሪዎችን የተቀበለው ለሌሎችም መሰል ዩኒቨርሲቲዎች አርኣያ በሚሆን ሁኔታ እስከ ጅማ ከተማ በመምጣት በራሱ ባዘጋጀው የትራንስፖርት አገልግሎት ሲሆን መንገዱ አቋርጦዋቸው የሚያልፍባቸው የዞኑ የወረዳዎችና ጣቢያቸው ከተሞች ነዋሪ ህዝቦች ከጎጀብ ከተማ እስከ ቦንጋ ድረስ በነቂስ ወጥተው ለተማሪዎች ፍቅር የተሞላበት አቀባበል አድርገዋል።በተደረገላቸው የአቀባበል ሥነሥርዓትና መስተንግዶ ደስተኛ መሆናቸውንም ተማሪዎች ገልጸዋል።በተማሪዎች ቅበላና የዩኒቨርሲቲው የሥራ ማስጀመሪያ ምረቃ ሥነሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶር ጥላዬ ጌቴ ተገኝተው ነበር።በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንትን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በስነ ስርአቱ ላይ ተሳታፊ ነበሩ።ምንጭ የትምህርት ሚንስቴር ### Response:
### Text: በትግራይ ክልል የዓዲግራት እና የአክሱም ከተሞችን የሚያገናኘው መንገድ ላለፉት 12 ቀናት በመዘጋቱ የነፍስ አድን የህክምና ስራዎቹ መስተጓጎላቸውን ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አስታውቋል።ድርጅቱ በአክሱም ድጋፍ ለሚያቀርብላቸው የሕክምና ተቋማት ቁልፍ አቅርቦቶች ለመላክ መቸገሩን ገልጿል።የድርጅቱ የምሥራቅ አፍሪካ ቢሮ በሚደግፋቸው ሆስፒታሎች 27 ህሙማን የኦክስጅን ሕክምና ይፈልጋሉ። እነዚሁ ሆስፒታሎች በየዕለቱ ኦክስጅን የሚያስፈልጋቸው ሰባት የቀዶ ሕክምና ያካሂዳሉ።አቅርቦቶቻችን እየተጠናቀቁ ነው። ምንም ነገር ካልተለወጠ በ3 ቀናት እንጨርሳለን ያለው ድርጅቱ በአክሱም በመድኃኒቶች እጦት ሳቢያ ከቀዶ ህክምና በኋላ የሕመም ማስታገሻ መስጠት አልቻልንም ብሏል።ድርጅቱ በርካታ የተጎዱ ሰዎች በሚኖሩበትና የድንገተኛ እርዳታ በሚፈለግበት ጊዜ ሆስፒታሉ ህሙማንን በቅጡ ለማከም ይቸገራል። አክሱም እና ዓዲግራትን የሚያገናኘው 135 ኪሜ ርዝመት ያለው አውራ ጎዳና ከ1 ሳምንት በላይ ተዘግቶ መቆየቱ የህክምና ተቋማት ስራዎች ላይ ይበልጡኑ ጋሬጣ ደቅኗል ብሏል። በመንገዱ መዘጋት ምክንያት ከአክሱም ውጪ ባሉ ገጠራማ አካባቢዎች ግልጋሎት የሚሰጡ ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች ስራ ተስተጓጉሏል። የክትባት መርሐ ግብሮች ተቋርጠዋል ብሏል። 0421 ### Response:
### Text: በጥምረት የተካሄደውን ምርመራ እውቅና መንፈግ ነው ኢሰመኮየኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ለተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምቤት ፕሬዚዳንት ናዛት ካን፣ ለሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት ፣ ለተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባቼሌት ግልጽ ደብዳቤ ፅፏል።ኢሰመኮ በጻፈው ደብዳቤ በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል እስከ ፈረንጆቹ ሕዳር 3 ቀን 2021 ድረስ የተፈጸሙትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በሌላ አካል በድጋሚ እንዲጣራ ማድረግ በተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት እና በኢትጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በጥምረት የተካሄደውን ምርመራ እውቅና መንፈግ ነው ብሏል፡፡ኮሚሽኑ ምርመራ ተደርጎ በሪፖርት የቀረበውን ጉዳት በሌላ አካል ከማስደገምና ሂደቱን ከማጓተት፣ ቀደም ብሎ በወጣው የምርመራ ሪፖርት መሰረት ተጎጂዎች እንዲያገግሙ፣ ወደ ተፈናቀሉበት ቦታ እንዲመለሱ እንዲሁም እንዲካሱ ብሎም ወንጀል የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ መሠራት ነበረበት ብሏል።ኮሚሽኑ ሰብዓዊ መብት ጥሰቱ እንደገና ይጣራ ከተባለ አጥፊዎቹ አካላት የፈጸሙትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለመካድና እና ኮሚሽኑ የሰራውን ምርመራ ለማጣጣል ብሎም የኮሚሽኑን ተግባር ዝቅ የሚያደርግ ይሆናል ሲል ስጋቱን ገልጿል።ሙሉ ደብዳቤው በዚህ ተያይዟል ### Response:
### Text: የበዓል መልዕክቶች ኪሩቤል ከሀረር ለምወዳቸው የካምፓስ ጓደኞቼ በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም እና በፍቅር አደረሳችሁ መልካም በዓል እመኝላችኃለሁ አቤል ከሀረር ጅማ ለሚገኙት እናት እና አባቴ መልካም በዓል ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እመኝላችኃለሁ በሀይሉ ለፍፁም እና ለጌታእንዳለ መልካም በዓል ሀብታሙ ለቤተሰቦቼ፣ ለፊዩቸር ታለንት ተማሪዎች፣ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሁም ለ ቤተሰቦች መልካም በዓል እንዲሆን እመ ኛለሁ ጆ ከአለም ባንክ ለሰማራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሁም ለኔ እንኳን አደረሰህ ብሎኛል አመሰግናለሁ ጫላ ቦረና ከሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም በዓል ሆሮ ጉዱሩ፣ ሻምቡወለጋ ለሚገኙት ቤተሰቦቼ እንኳን አደረሳችሁ መልካም በዓል እመኛለሁ ሄኖክ ታደለ ከደብረ ዘይት ለቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ በተለይም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሚማሩትደጁ፣ ጌች፣ ጵንኤል፣ ታፌ፣ ታዴ እንኳን ለትንሳኤው በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሳምሶን ገመድህን ከአዲ አበባ ለቱሚ፣ ሳንቼዝ፣ የአብስራ፣ ትንቢት፣ ጄሪ፣ አቤል እንኳን አደረሳችሁ መልካም በዓል ይዲዲያ ከመቀሌ ሀረር ለሚገኘው ባለቤቴ ጃራ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም እና በፍቅር አደረሰህእንኳን አደረሳችሁ መልካም የትንሳኤ በዓልይቀጥላል ### Response:
### Text: ክቡር አቶ ለማ መገርሳ የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፡ የኢንዱስትሪ ልማት የአገራችንን ጎስቋላ ገፅታ የሚለውጥ ነው ግብርና እንዲዘምንና በሂደትም ለኢንዱስትሪ መሪነቱን እንዲለቅ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው መንግስት ለኢንዱስት ልማት ትኩረት ሰጥቷል በዘርፉ ተጨባጥና ፍሬያማ ስራዎች እየተሰሩ ነው የተመቻቸ የኢንዱስትሪ ፓርክ ባለሀብቶች በአጭር ጊዜ ስራ እንዲጀምሩ ያስችላል የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ፋና ወጊ ከሆኑት መካከል ነው በጠርቃጨርቅና አልባሳት ስፔሺያላይዝ ያደረገ ፓርክ ነው ለባቡር፣ አየር፣ የብስ ትራንስፖርተ ቅርበት ያለው ከተማ ነው አዳማ ከውጭ የሚመጡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት የሚያስችል፣ የአርሶ አደሩን ገቢም የሚያሻሽል ፓርክ ነው በሙሉ አቅሙ መንቀሳቀስ ሲጀምር ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራል የቴክኖሎጂ ሽግግርኽ የጥናትና ምርምር ማዕከል ይሆናል ፓርኩ የላቀ የብቃት ማዕከል እንዲሆን እንሰራለን ወጣቶች በአነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት ተደራጅተው ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ግብዓት እንዲያቀርቡ ይመቻችላቸዋል የክልሉ መንግስት ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል።ምንጭ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ከከሰልና እንጨት ጋር አብረን እንድንጓዝ ተገደናል፡፡ ነዋሪዎችበኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ከከሚሴ በደዌ ሃረዋ በሚወስደዉ መንገድ ነዋሪዎች በትራንስፖርት ችግር እንግልት እየደረሰባቸዉ ነዉ፡፡ የሚመደቡ የህዝብ ማመላለሻ አዉቶብሶች በቂ ባለመሆናቸዉ በአንድ አዉቶብስ ከ100 እስከ 120 ሰዎች እንደሚጓጓዙ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተናግረዋል።የአካባቢዉ ህብረተሰብ እንደ አማራጭ የጭነት መኪኖችን ለመጓጓዣነት እየተጠቀመባቸዉ ነዉ፡፡ የአካባቢዉ የትራንስፖርት ችግር ነዋሪዎችን በአይሱዙ መኪኖች ከከሰልና እንጨት ጋር አብረዉ እንዲጓዙ አስገድዷቸዋል፡፡ ለትራፊክ አደጋ እያጋለጣቸዉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡ለአብነት በቅርቡ በደረሰ የትራፊክአደጋ የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተሰምቷል፡፡ የደዌ ሃረዋ ትራፊከ ፖሊስ ምክትል ሳጅን መሃመድ ጀማል ህብረተሰቡ የሚያስፈልገዉን የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኘ አለመሆኑ ይታወቃል በተደጋጋሚ ትርፍ የሚጭኑትን አሽከርካሪዎች እየቀጣን ነዉ፣ ሆኖም መፍትሄ አልመጣም ብለዋል፡፡ የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሃሰን በብሄረሰብ አስተዳደሩ የሚታየዉን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡ምንጭ አብመድ ### Response:
### Text: በነገው ዕለት በሚካሄደው የኢህአዴግ ምክርቤት ስብሰባ ላይ ህወሓት እንዳይማይሳተፍ ውሳኔ አሳለፈ የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ አባላት ነገ በሚጀመረው የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እንደማይሳተፉ የህወሓት ፅሕፈት ቤት ገለፀ፡፡ ህወሓት በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ በኩል ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው የኢህአዴግ ውህደት በግንባሩ ሥራ አስፈፃሚ ደረጃ ይሁን ምክር ቤት ስብሰባ ሊወሰን የማይችል መሆኑ ጠቅሶ አባላቱ ነገ በሚጀምረው የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እንደማይሳተፉ ዐስታውቋል፡፡አራቱ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች እያንዳንዳቸው 45 ተወካዮች የሚያሳትፉበት የኢህአዴግ ምክር ቤት ከነገ ጀምሮ ስብሰባ እንደሚያካሂድ ግንባሩ በዛሬው ዕለት ገልፅዋል፡፡ «የህወሓት እጣ ፈንታ ሊወሰን የሚችለው በየደጃው ውይይት ከተደረገበት በኋላ በህወሓት ጉባኤ ብቻ በመሆኑ በአሁኑ ሰአትስብሰባ ላይ ለመሳተፍ የማንችል መኾኑን እናሳውቃለን» ይላል የህወሓት መግለጫ። ከኢሕአዴግ ምክር ቤት 180 አባላት መካከል 45ቱ የህውሓት አባላት ናቸው፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በግንባሩ ውህደት ዙርያ የቀረበው የጥናት ውጤት በአብላጫ ድምፅ ማፅደቁ ይታወሳል፡፡ ጉዳዩ በግንባሩ ምክር ቤት ደረጃ እንደሚታይም ተገልፆ ነበር፡፡ ### Response:
### Text: ነሃሴ 102012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 5877 የላብራቶሪ ምርመራ 93 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ከጎንደር ከተማበቫይረሱ ከተያዙት መካከል 18 ከኦሮሞ ብሰብ ዞን 14 ከደወሎ ዞን 13 ከሰሸዋ ዞን 11 ከባህር ዳር ከተማ 9 ከአዊ ብሰብ ዞን 7 ከሰወሎ ዞን ይገኙበታል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 547 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 4 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 1 ከኩርሙክ ወረዳ 3 ከካማሽ ወረዳ በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 415 የላብራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 85 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።አጠቃላይ በአፋር 415 በቫይረሱ የተያዙ ያገገሙ 191 ባለፉት 24 ሰዓት የተደረገው ምርመራ 3537 ሲሆን 185 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የስምንት 8 ሰዎች ህይወት አልፏል። አጠቃላይ በኦሮሚያ 2953 በቫይረሱ የተያዙ 35 ሞት 939 ያገገሙ በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1145 ላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 82 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል ከመቐለ የኮቪድ19 ህክምና ማዕከል አጠቃላይ በትግራይ 1770 በቫይረሱ የተያዙ 13 ሞት 809 ያገገሙ በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 260 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 9 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል። 9 ጅግጅጋ ### Response:
### Text: የዩኒቨርሲቲዎች ዝግጅት ምን ይመስለል ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ ከንክኪ ዉጪ የሆነ የእጅ መታጠቢያ ተማሪዎች በብዛት በሚገኙበት አከባቢ ለማኖር ተዘጋጅቷል። የንፅህና መጠበቂያ ሳኒታይዝር ፣ ሳሙና እና ዉኃ ተደራሽ የማድረግ ሥራም ይሰራል። የካፌ ዝግጅትን በተመለከተ ሁለቱም የተማሪዎች መመግቢያ አዳራሾች ጥገና እና በዘመናዊ ማሽን እየተተካ ነዉ፡፡ ዶርምን በተመለከተ ካራኒታይን የሆኑ መኝታ ቤቶች የዲስ ኢንፌክት ስራ ከዛሬ ጅምሮ ይካሄዳል፡፡ የዶርምና አከባቢም ፅዳት በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡ ከኮሮና ጋር በተያያዘ ጥግግትን ከመቀነስ አንፃር በአንድ ዶርም 3 ተማሪ የመመደብ ስራ ለመስራት ዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ አካዳሚክ ጉዳዮችን በተመለከተ ሁሉም መምህራን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአካዳሚክ ዘርፉም ልዩ ትኩርት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። አምቦ ዩኒቨርሲቲው ካለው 4 ካምፓሶች አሁን ላይ የሀጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ አዋሮ በካሯንቲን ማዕከልነት እያገለገለ ይገኛል፡፡ አምቦ ዩኒቨርሲቲ ዝግጅት ከጀመረ የቆየ ሲሆን ግቢዎችን ዲስኢንፌክት የማድረግ ሥራም ይሰራል ተብሏል፡፡ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ቅድመ ዝግጅት በየጊዜው እየጠየቀ እና እየተከታተለ ለተማሪዎች እንዲሁም ለተማሪ ወላጆች ያሳውቃል ### Response:
### Text: ሱዳናውያን ሴቶች አደባባይ ወጡ ሱዳናዊያን ሴቶች በሽግግር መንግስቱ ምስረታ የሴቶች ተሳትፎ አልተረጋገጠም ሲሉ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥተዋል፡፡ ሱዳንን ለሦስት አስርት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት የመሩት ዑመር ሃሰን አልበሽር በሕዝባዊ ተቃውሞ ባለፈው ሚያዝያ ላይ ከስልጣን ከተወገዱ በኋላም ሱዳን ሰላም አልነበራትም፡፡ከበርካታ ግጭቶች እና ተቃውሞዎች በኋላ ከሦስት ቀናት በፊት ለሚቀጥሉት 21 ወራት ሀገሪቱን የሚመሩ የሽግግር መንግስት አባላት ተሰይመዋል፡፡ የሽግግር መንግስቱ ከተቋቋመ እና ቃለ መሃላ ከፈፀመ በኋላ ትናንት ሰኞ በሱዳን ኦምዱርማን ሴቶች በሽግግር መንግስቱ መስረታ በውሳኔ ሰጪነት ቦታ ላይ የሴቶች ተሳትፎ የለም በሚል ለተቃውሞ ጎዳና ወጥተዋል፡፡በኡማ ፓርቲ መቀመጫ ኦምዱርማን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ሰልፈኞቹ ትግላችን ለሴቶች እኩልነት፣ ፍትሃዊነት እና የሴቶችን ነፃነት እስኪረጋገጥ ድረስ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ሴቶች እንደማንኛውም የተፎካካሪ ፓርቲ ተደራጅተን ለመብታችን እንከራከራለን ወይም ደግሞ በሽግግር መንግስቱ አባላት ውስጥ ሴቶች በውክልና ሳይሆን 50 በመቶ የሚሆነውን ቦታ ሊሸፍኑ ይገባል ብለዋል፡፡ የውክልና መብታቸው እስኪረጋገጥ ድረስም ተቃውሞው እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ምንጭ፡ አፍሪካ ኒውስ ### Response:
### Text: ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በባልደራስ ዋና ፅቤት በመገኘት ታህሳስ 292014 ዓም ከእስር ለተፈቱት አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወሮ ቀለብ ስዮም እና ወሮ አስካለ ደምሌ እንኳን ደስ ያላችሁ እንኳን ለቤታችሁ አበቃችሁ በማለት መልካም ምኞቷን ገልፃለች።አትሌቷ ከእስር ለተፈቱት አመራሮች መጭው ጊዜአቸው የተቃና እንዲሆን እና ኢትዮጵያም ሰላሟ፣ አንድነቷ እና ክብሯ እንዲመለስ ያላትን ምኞት ገልፃለች።የባልደራስ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ በበኩላቸው ኮማንሰር አትሎህ ደራርቱ የፓርቲው ፅቤት ድረስ ቃሏን አክብራ በመልካም መንፈስ በመገኘት ይህንን እውቅና በመስጠቷ ከልብ አመስግነዋል።በተጨማሪም በቀጣይ በኢትዮጰያ ሰላምና ልማት ይሁን። ሲል መልካም ምኞቱን ገልፀዋል።ሌሎች ከእስር የተፈቱ የፓርቲው አመራሮች አትሌቷ ቃሏን አክብራ በባልደራስ ዋና ፅቤት በመገኘት የእንኳን ደስ ያላችሁመልዕክት በማስተላለፏ የተሰማቸውን ደስታ መግለፃቸውን ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።በሌላ በኩል ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር አቶ በቀለ ገርባን እንኳን ለቤትዎት አበቃዎት በማለት መልካም ምኞቷን ገልፃለች። ### Response:
### Text: የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በመላ ሀገሪቱ ለ6 ወራት የጸና ይሆናል፡የመከላከያ ሚኒስትርና የብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሰብሳቢ ሲራጅ ፈጌሳ የአዋጁ መታወጅ ምክንያት በአንዳንድ አካባቢዎች ህገመንስታዊ ስርዓቱን የሚፈታተኑ ጉዳዮች በማጋጠማቸው እና የሰዎች መፈናቀል እና ህይወት ማለፍ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚከለክላቸው ወይም ገደቦች 18 ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ ጽሁፍ ማሳተም ትዕይንት ማድረግ ሰላማዊ ሰልፍ በቡድን መንቀሳቀስ የጦር መሳሪያና ስለታማ ነገሮችን ይዞ መጓዝ አይቻልም፡፡ ያለፍርድ ቤት መበርበር ለፀጥታው መረጋጋት አስጊ መስሎ ከተገኘ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማንኛውም አይነት የመገናኛ ዘዴዎች ሊቋረጡ ይችላሉ ።የአስቸኳይ ጊዜ ኮማንድ ፖስትና የአፈፃጸም መምሪያ ቦርድ ተቋቁሟል ። እንደሁኔታው ታይቶ የሰዓት ዕላፊ ገደብ ማስቀመጥና ሌሎች ድንጋጌዎች አሉት ብለዋል ሚኒስትሩከ15 ቀናት በኋላም ለተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል፡፡የመከላከያ ሚኒስትርና የብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሰብሳቢ ሲራጅ ፈጌሳ አሁን ላይ ስለ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አተገባበር በሰጡት መግለጫ አሳውቀዋል፡፡ሚኒስትሩ አክለውም አዋጁ የታወጀው በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 93 መሰረትን አድርጎ ነው፡፡ምንጭ፡ አመብድ ### Response:
### Text: አሳቴዩ️የመማር ማስተማሩ ሂደት ተቋርጦ የነበረው የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ተማሪዎች ተመልሰው ትምህርት እንዲጀምሩ በሴኔት መወሰኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ።የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ለሚጉታ ለ እንደተናገሩት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር እና መምህራን ትናንት ከተማሪ ወላጆች ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ ሴኔቱ ተማሪዎች ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ወስኗል ብለዋል።ከተማሪ ወላጆች ጋር በተደረገ ውይይትም ወላጆች ተማሪዎች ጥያቄ ቢኖራቸውም ትምህርት ማቋረጣቸው ተቀባይነት የሌለው መሆኑንና የተፈጠረው ችግርም እንዳሳዘናቸው መናገራቸውን አንስተዋል።ወላጆች ለተማሪዎቹ ድርጊት ይቅርታ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ተከትሎም ሴኔቱ ያስተላለፈውን የአንድ ሴሚስተር ቅጣት ማንሳቱን ገልጿል።በዚህ መሰረትም ከፊታችን ሰኞ የካቲት አራት ጀምሮ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ የሚገቡ መሆኑ ነው የተገለፀው።የተቋሙን የመማር ማስተማር ሂደት ሆነ ብለው ሲያውኩ የነበሩ ተማሪዎች ግን የስነ ምግባር ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርት ማቆማቸውን ተከትሎ 0ከጥር 12 ቀን 0እስከ 14 ቀን 2011 ዓም 0ጊቢውን ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸው ይታወሳል ።ምንጭ ### Response:
### Text: በባንግላዴሽ ኑስራት ጃሃን የተባለች ተማሪ ርዕሰ መምህር ፆታዊ ትንኮሳ ሪፖርት ማድረጓን ተከትሎ በነጭ ጋዝ አርከፍከው አቃጥለው ገድለዋታል የተባሉ 16 ተጠርጣሪዎች ታስረዋል።ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር፣የአካባቢው ፖለቲከኞችና ተማሪዎች ይገኙበታል።ርዕሰ መምህሩ ግድያውንም መናዘዙንም ፖሊስ አስታውቋል። ብዙዎቹም በተጠርጣሪዎቹ ላይ የሞት ፍርድ ተግባራዊ እንዲሆንም እየጠየቁ ነው።በትንሽ መንደር የተወለደችው የአስራ ዘጠኝ አመቷ ኑስራት ማዳራሳ ወይም የእስልምና ትምህርትን ትከታተል ነበር።የደረሰባትን ትንኮሳ በመናገሯ ድፍረቷን ብዙዎች ቢያደንቁትም ከቀናት በኋላ ግን ሰቅጣጭ የሆነው አገዳደሏ ብዙዎችን አስደንግጧል።ከመሞቷ በፊት ኑስራት በሰጠችው መግለጫ አንዲት ሴት ተማሪ አንድ ጓደኛዋ እንደተጎዳ ነግራት ጣራው ላይ ወሰደቻት። ጣራው ላይ ስትደርስ ግን አምስት ተማሪዎች እንደከበቧትና በርዕሰ መምህሩ ላይ ያቀረበችውን ክስ እንድትተው ጫና ሊያደርጉባት ሞክረዋል። እምቢ ስትልም በእሳት እንደለኮሷት ተናግራለች።የወንጀል መርማሪ ፖሊስ ኩማር ማጁምደር እንደገለፀው ገዳዮቿ ራሷን ያጠፋች ለማስመሰል ቢሞከሩም እቅዳቸው ሳይሳካም ለጥቂት ቀናትም ቢሆን በህይወት ተርፋ መግለጫ መስጠት ችላለች። ### Response:
### Text: በአዲስ አበባ ከተማ ያለ ደረሰኝ ግብይት ባከናወኑ፣ የዳቦ ግራም በቀነሱና የምርት ጥራት ጉድለት አስከትለዋል የተባሉ 40 የንግድ ቤቶች ታሸጉ፡፡የማሸግ እርምጃው የተወሰደው በ27 ወፍጮ ቤቶች፣ 7 ዳቦ ቤቶች፣ 2 አትክልት ቤቶች እና በሌሎች የንግድ ቤቶች ላይ መሆኑ ተገልጿል፡፡እርምጃውን የወሰደው የጉለሌ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽቤት 60 ለሚሆኑ የንግድ ተቋማትም የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታውቋል፡፡በከተማው ንግድና ኢንዱስትሪ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ ከተማ አቀፍ የቁጥጥርና የክትትል ስራዎችን እየተሰራ መሆኑን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽቤት ሀላፊ አቶ ቴዎድሮስ ዓለሙ ተናግረዋል፡፡በነጋዴዎች ላይ እርምጃ ከመወሰዱ በፊት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች የተሰጠ መሆኑንም አቶ ቴዎድሮስ ጨምረው ገልጸዋል፡፡የቁጥጥር ስራ ብቻውን በቂ እንዳልሆነና በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ሱቆች መሰረታዊ የሚባሉ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት ወደ ገበያ እንዲያስገቡ ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር ውይይት መደረጉም ተገልጿል፡፡የፀረኮንትሮባንድ ስራዎችንም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በአዲስ አበባ መውጫና መግቢያ ላይ ከፍተኛ የቁጥጥር ስራ እንደሚከናወን ሀላፊውን ጠቁመዋል፡፡ የክፍለከተማው ኮሙኒኬሽን ጽቤት ቀን 13102011 ዓም ### Response:
### Text: የድሬዳዋ ሪፈራል ሆስፒታል በ2002 ዓም ግንባታው ተጀምሮ ዛሬም ድረስ ያልተጠናቀቀው የድሬዳዋ ሪፈራል ሆስፒታል ለድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ተሰጠ። ሆስፒታሉ ዛሬ በተካሄደ ስነ ስርዓት ወደ ዩኒቨርስቲው እንዲተላለፍ የተደረገው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በወሰነው መሰረት ነው።የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የሆስፒታሉን ቀሪ የግንባታ ስራዎችን አጠናቅቆ የህክምና ማስተማርያና እና ምርምር ማዕከል እንደሚያደርገው በዛሬው የርክክብ ስነ ስርዓት ተገልጿል። የርክክብ ሰነዱን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አህመድ መሀመድ ቡህ እና የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶር ያሬድ ማሞ ተፈራርመዋል። ዶር ያሬድ ዩኒቨርስቲው የሆስፒታሉን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ብር በጀት መመደቡን ተናግረዋል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የግንባታ ስራውን እንደሚያጠናቅቅም ገልጸዋል።በ324 ሚልዮን ብር በጀት ግንባታው ሲከናወን መቆየቱ የተገለጸው የድሬዳዋ ሪፈራል ሆስፒታል ሲጠናቀቅ ከሶስት መቶ በላይ አልጋዎች እና የተለያዩ የህክምና ማዕከላት ይኖሩታል። ሆስፒታሉ ወደ ዩኒቨርስቲው እንዲዛወር መደረጉ ለከተማይቱ እና አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችል ተቋም ያደርገዋል ተብሏል።ምንጭ የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: የሲዳማ ህዝብ ከዓመታት በፊት ያቀረበዉ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ዘግይቶም ቢሆን ምላሽ ማግኘት በመጀመሩ መላው የሲዳማ ብሔር እንዲረጋጋ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ሲአን ጠየቀ። የንቅናቄው ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ደስላኝ ሜሳ፣ «ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ ተቀብሎ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ መዘጋጀቱን አረጋግጧል።» ብለዋል። በዚሕም ምክንያት የሲዳማ ሕዝብ የህዝበ ውሳኔውን ሂደት እንዲጠባበቅ ንቅናቄው ጥሪ ማስተላለፉን አቶ ደሳላኝ ለጀርመን ራድዬም በሰጡት ቃለ መጠይቅ አመልከተዋል። ይሁንና አቶ ደሳለኝ እንደሚሉት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝበ ዉሳኔዉ ሊደረግ ከሚገባዉን ቀን አዘግይቷል ብሎ ንቅንቄያቸዉ እንደሚያምን ጠቅሰዉ ለዚሕም ቦርዱ፣ ሕዝቡን ይቅርታ መጠየቅ ይገባዋል ብለዋል። በሲዳማ ዞን የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ሲአን ፣ የሲዳማ ሀድቾ ዴሞክራሲያዊ ደርጅት ሲሀዴድ እና የሲዳማ ብሄራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሲብዴፓ ፣ የሲዳማ ህዝብ በክልል ለመደራጀት የሚያስችለው የህዝበ ውሳኔ የሚደረግበትን ቀን መንግሥት በአምስት ቀናት ዉስጥ ይፋ እንዲያድርግ ባለፈዉ ሳምንት መጀመሪያ ጠይቀዉ ነበር። የተቀሩት ሁለቱ ፓርቲዎች አስከአሁን ሥለ ጉዳዩ በይፋ ያሉት ነገር የለም። የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 9 ሺህ 750 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው፡፡ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው 9 ሺህ 750 ተማሪዎችን በተለያዩ መርሀ ገብሮች እያስመረቀ ነው፡፡ በፕሬዝዳንቱ እንደተገለጸው ከተመራቂዎች መካከል 6 ሺህ 520 ያህሉ በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 3 ሺህ 167 በሁለተኛ ዲግሪና 63 በሦስተኛ ዲግሪ የሚመረቁ ናቸው፡፡የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በምሥራቅ አፍሪካ ብቸኛ በሆነበት በማሪታይም አካዳሚ ጭምር በርካቶችን እያስመረቀ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ፍሬውተገኝ በትምህርት ጥራት ተወዳዳሪነቱ በየጊዜው እያደገ መምጣቱን አብራርተዋል። በሕግ ትምህርት ቤት በሀገር አቀፍ ደረጃ 1ኛ እና 3ኛ ደረጃ የያዙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሆናቸውንም በአብነት አንስተዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለሕይወት ዘመን የሚበጁ ዕውቀቶችን እንዳስታጠቃቸው በመግለጽ በምክንያታዊነት የሚያምኑ ሀገር የሚገነቡ ዜጎች እንዲሆኑም ተመራቂዎቹን አሳስበዋል፡፡ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ336 ፕሮግራሞች እያስተማረ እንደሚገኝ ያመለከቱት ፕሬዝዳንቱ ተመራቂዎችን የሕይወት ዘመን ተማሪዎች እንዲሆኑም አሳስበዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የድህረ ዶክትሬት ዲግሪ ትምህርት ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት ማድረጉንም አስታውቀዋል፡፡ ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ ️ሀገራችን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ድል ያስመዘገበችበት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቋል። ከዓለም ከአሜሪካ ቀጥላ ሁለተኛ እንዲሁም ከአፍሪካ ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ ነው ያጠናቀቀችው።በዓለም ሻምፒዮናው 4 ወርቆችን ያገኘን ሲሆን የዘንድሮው ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሆኗል።ከተገኙት አራት ወርቆች መካከል ታምራት ቶላ በማራቶን ያገኘው ወርቅ በዓለም ሻምፒዮናው በወንዶች የተገኘው ብቸኛው ወርቅ ነው።ለሀገራቸው ሜዳሊያ ያስገኙ አትሌቶቻችን እነማን ናቸው ወርቅ ለተሰንበት ግደይ ጉዳፍ ፀጋይ ጎተይቶም ገስላሴ ታምራት ቶላ ብር ወርቅውሀ ጌታቸው ሞስነት ገረመው ለሜቻ ግርማ ጉዳፍ ፀጋይነሐስ ዳዊት ስዩም መቅደስ አበበአጠቃላይ ከተገኘው 10 ሜዳሊያ ሰባቱ በሴቶች የተገኘ ነው የቀረው 3 ሜዳሊያ ደግሞ በወንዶች ውድድር የተገኘ ነው።የዓለም ሻምፒዮናው ምንም እንኳን ከፍተኛው ድል የተመዘገበበት ቢሆንም በወንዶች ውድድሮች ላይ የተሻለ መስራት እንደሚጠይቅ የሚጠቁም ነው።የአትሌቲክስ ቡድናችን ወደ ሀገሩ ሲመለስ የጀግና ፣ የክብር አቀባበል እንደሚደረግለት ይጠበቃል።ውድ አትሌቶቻችን ላደረጋችሁት ከፍተኛ ተጋድሎ ላስመዘገባችሁት ድል ፣ የሀገራችሁን ህዝብ ክብር ከፍ ስላደረጋችሁ ምስጋና ይገባችኃል።እንኳን ደስ አለን ️ ### Response:
### Text: አምቡላንስ ተሽከርካሪያችን በኃይል ተወስዷል ቀይ መስቀልየኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አምቡላንስ ተሽከርካሪው በኃይል እንደተወሰደበት አሳወቀ።ማኅበሩ የምዕራብ ጎጃም ዞን ቅርንጫፍ ጽቤት ንብረት የሆነ ማኅበሩ ለሰብዓዊ አገልግሎት የሚጠቀምበት ታርጋ ቁጥሩ 0501107 አምቡላንስ ተሸከርካሪ መስከረም 08 ቀን 2016 ዓም ማንነታቸው ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች እንደተወሰደ ገልጿል። አምቡላንስ ተሸከርካሪው የተወሰደው በፍኖተ ሰላም ከተማ ከሚገኘው የቅርንጫፉ ጽቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲሆን የተወሰደውም በአስገዳጅ ሁኔታ ነው ብሏል።ይህ ድርጊት ኢትዮጵያ የፈረመችውን ዓለም አቀፍ የጄኔቫ ሥምምነቶችን የሚፃረርና ከማህበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ገልጿል።ድርጊቱን የፈፀሙት አካላት አምቡላንሱን ለማህበሩ በመመለስ ለማኅበረሰቡ የተለመደውን ሰብዓዊ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል እንዲያሰርጉ ጠይቋል።በመላው ሀገሪቱ በሰብዓዊ አገልግሎት የተሰማሩ የቀይ መስቀል ሠራተኞችና በጎፈቃደኞች እንዲሁም አምቡላንሶችና ሌሎች ተሽከርካሪዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው መስራት እንዲችሉ፣ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ፣ ታጣቂ ኃይሎች ከእንደዚህ አይነት ድርጊት እንዲቆጠቡና ማኅበረሰቡም መሰል ድርጊቶችን እንዲያወግዝ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጠይቋል። ### Response:
### Text: በጎንደር ከተማ በሚገኘው የአፄ ቴዎድሮስ ሐውልት ላይ ጉዳት ያደረሰችው ግለሰብ በአምስት ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቷን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው የወንጀል ዐቃቤ ሕግ አቶ ድረስ ዘለለው ለኢዜአ እንደተናገሩት ቅጣቱ የተላለፈባት ነዋሪነቷ በጎንደር ከተማ በሆነው በወይዘሮ መንደሬ እያዩ አባተ ላይ ነው፡፡ ግሰሰቧ የካቲት 5 ቀን 2011 ከምሽቱ 5 ሰዓት ከ30 ሲሆን፣ ፒያሳ አደባባይ ላይ የቆመውን ሐውልት ቀኝ እጅ ጎራዴ ላይ ጉዳት ማድረሷ በሦስት ምስክሮች በመረጋገጡ ነው፡፡ ግለሰቧ በወንጀል ሕግ ቁጥር 690 ንዑስ ቁጥር ሁለት የሕዝቦች የጋራ ሐውልት በሆኑ ታሪካዊ ቅርሶች ላይ ጉዳት በማድረስ የተደነገገውን አንቀጽ ተላልፋ መገኘቷንም አመልክቷል፡፡ ተከሳሿ በቀረበባት ክስ በፍርድ ቤት ወንጀሉን አልፈጸምኩም በሚል ክዳ ብትከራከርም ዐቃቤ ሕግ ያቀረበባትን ማስረጃን ባለማስተባበሏ ቅጣቱ ተወስኖባታል፡፡ የጎንደር ከተማ ፍርድ ቤት ግለሰቧ የቤተሰብ አስተዳዳሪና ከዚህ ቀደም የወንጀል ሪከርድ የሌለባት መሆኑን በቅጣት ማቅለያነት ተይዞላታል፡፡ ግለሰቧ የፈጸመችው ወንጀል እስከ 15 ዓመት በሚደርስ እስራት የሚያስቀጣ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ማስረጃዎቹን በቅጣት ማቅለያነት እንደያዘላት ዐቃቢ ሕጉ አስረድተዋል፡፡ ### Response:
### Text: 19 ኮሮና ቫይረስ ሀገረ አቀፍ መረጃ ከሁሉም ክልሎች ለተወጣጡ ባለሞያዎች ስልጠና ተሰጥቷል ከሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በሐዋሳ ከተማ ለይቶ ማቆያ ተመርጦ የተዘጋጀ ሲሆን በጂንካ እና አርባ ምንጭ ለማዘጋጀት ስራ ተጀምሯል፡፡ በጋምቤላ በጎግ ዲማ ላሬ ዋንታዎ እና ጂካዎ በድንበር ኬላዎች ከሚደረግ የልየታ ስራ በተጨማሪ ከሆስፒታሎች ጋር በመተባበር የለይቶ ማቆያ እና የህክምና መስጫ ተዘጋጅቷል፡፡ በአማራ ክልል በመተማ ድንበር እና ባህርዳር ዓለም አቀፍ አየር መንገድ የልየታ ስራ የተጀመረ ሲሆን በተመሳሳይ በላሊበላ ጎንደር እና ኮምቦልቻ የልየታ ስራ ለመጀመር እና በእነዚህ ቦታዎች የለይቶ ማቆያ እና ህክምና መስጫ ለማቋቋም እየተሰራ ይገኛል፡፡ በድሬደዋ ከተማ ካለው በዳወሌ ድንበር በባቡር እና በዓለም አቀፍ አየር መንገድ የተጠናከረ የልየታ ስራ በተጨማሪ ከመከላከያ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የለይቶ ማቆያ ተቋቁሟል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ለከተሞች ለዞን እና ለሆስፖታሎች ስለ ኮቪድ 19 ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በቢሾፍቱ እና በጅማ ለይቶ ማቆያ ተቋቁሟል፡፡ እንዲሁም በሐረማያ በአዳማ ሻሸመኔ ያቤሎ እን ነቀምቴ ተመሳሳይ የለይቶ ማቆያ ለማቋቋም ስራ ተጀምሯል፡፡የኮሮና ቫይረስ በሽታ የኮቪድ19 አስመልክቶ የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ 190302 ### Response:
### Text: ሀገራችን ኢትዮጵያ በቅርቡ በተደረገው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ሩስያ ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ም ቤት እንድትታገድ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ለምን የተቃውሞ ድምፅ ሰጠች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ሲመልሱ እኛ ሀገሮችን በማግለል እንደ ካሉት ዓለም አቀፍ ተቋም በማስወጣት ጥቅም አይመጣም ሰላምም በእንዲህ አይነት አይመጣም ከሚል የመነጨ ነው በዋናነት።አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር በሰላም እንዲዘጋ እንደምንፈልግ ገልፀናል። በሰላማዊ መንገድ በሰላማዊ ሂደት ይሄ ነገር እንዲቆም ነው እንጂ አንድንወገንለይቶበማግለል ሊመጣ የሚችል ሰላም የለም ከሚል የመነጨ አቋም ነው።ከተባለው ሀገር ሩስያ ጋርም ያለን ግንኙነት በጣም ጠንካራ ስለሆነ ነው። እንደሚታወቀው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት መድረክ የሰጡን ድጋፍ የሚታወስ ነው። ብለዋል።ከጥቂት ቀናት በፊት 193 አባል ሀገራት ላሉት የተመድ ጠቅላለ ጉባኤ የቀረበው ሩስያን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምቤት የማገድ የውሳኔ ሀሳብ በአብላጫ ድምፅ መፅደቁ ሩስያም ከምቤቱ መታገዷ ይታወሳል።በወቅቱ የውሳኔ ሃሳቡን ከ193 አባልት 93 ሀገራት የደገፉት ሲሆን 58 ሀገራት ድምጸ ተአቅቦ አድርገዋል 24 ሀገራት ደግሞ ተቃውመዋል ከተቃወሙት 24 ሀገራት አንዷ ሀገራችን ኢትዮጵያ ናት። ### Response:
### Text: ዛሬ በዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ፍቅር ያሸንፋል የሲቪክ ማህበር ከኃይማኖት አባቶች፣ ከአባገዳዎችና ከፓለቲካ ፖርቲ ተወካዮች ጋር ስለ ማህበሩ እንቅስቃሴና በቀጣይ የካቲት 15 በሚደረገው ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ የጎዳና ሩጫ አስመልክቶ ባሰናዳው መድረክ የድርጅቱ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሚፍታ ከድር የተናገሩት፡በእስር ቤት በቆየንበት ወቅት እኛ ላይ ግፍ ሲፈጽሙ የነቀሩት የሁሉም ብሔረሰቦች አባላት ነበሩበት ግን እነሱ የስርዓቱ ሎሌዎች ነበሩ ስርዓቱ እንጂ ህዝቡ አልበደለንም፡፡ እነዛም ቢሆኑ ሁሉም ወንድሞቻችን ናቸውና ከልባችን ይቅር ብለን ፍቅር ያሸንፋል ብለን ለፍቅር እየሰራን እንገኛለን፡፡ ማህበራችንን ከመሰረትን በኀላም ደሜ ብሔር የለውም ደሜ ቋንቋ የለውም ደሜ ለወገኔ በሚል የደም ልገሳ መርኃግብር አካሂደናል፡፡ በተለያዩ ክብረ በዓላት ጊዜም ሳንከፋፈል የጽዳት ሥራዎችን ሰርተናል፡፡ የካቲት 15 ደግሞ ለፍቅር እንሩጥ በሚል ርዕስ 40000 ሰዎች የሚሳተፉበት የሩጫ መርኃግብር አዘጋጅተናል፡፡ ውድድሩን የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮች ሁሉም በጋራ ያስጀምሩታል ብለን አቅደናል፡፡ ከዛም ባለፈ በአለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ የሚመዘገብ ሰፊ እንጀራ ተጋግሮ ሁሉም የፓርቲ አመራሮች ከአንድ መአድ እንዲቋደሱ ይደረጋል። ### Response:
### Text: አስቸኳይ የሳዑዲ አረቢያ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነና ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፎ ነበር።የሳዑዲ ፀጥታ ኃይሎች በሰሩት ኦፕሬሽን ተይዘው በሹሜሲ የማቆያ ጣብያ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የውሃ የምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች እጥረት እንዳጋጠማቸው ተሰምቷል። በመሆኑም1ኛ ከ10 ቀን እስከ 3 ዓመት ዕድሜ ላላቸው ህፃናት የሚሆን ወተት 2ኛ ከ1 ቁጥር እስከ 5 ቁጥር የሆኑ የህፃናት ዳይፐርሃፋዛ3ኛ ለታዳጊ ህፃናት እና ለአዋቂዎች የሚሆኑ ደረቅ ምግቦች 4ኛ ለሴቶች እና ለሕፃናት የሚሆኑ የመፀዳጃ ቁሳቁሶች በተለይ ዋይፕ እና ሞዴስ 5ኛ የሚጠጣ ውሃ እጥረት ያጋጠመ በመሆኑ ዜጎቻችን ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል።ዕርዳታ ማድረግ የምትፈልጉ ግለሰቦች አደረጃጀቶች በጄዳ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ኮሚዩኒቲ የስራ ኃላፊነቱን ወስዶ እንቅስቃሴ የጀመረ በመሆኑ ዕርዳታችሁን በኮሚኒቲ ጽቤት ቢሮ ቁጥር 1 ማድረስ እንደሚቻል በጄዳ የሚገኘው ቆንስላ ፅቤት ዛሬ ማምሻውን ገልጿል።ይህ መልዕክት የደረሳችሁ ጅዳ አካባቢ የምትገኙ የቲክቫህ አባላት በመሉ የምትችሉትን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን። ### Response:
### Text: አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከጠሚ ዶር ዐቢይ ጋር ተነጋገሩ።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በትግራይ ክልል ስላለው እጅግ በጣም አሳሳቢ የሰብዓዊ ሁኔታ ላይ ከጠሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር መነጋገራቸውን ድርጅቱ አሳውቋል።ዋና ፀሃፊው ጠሚ ዐቢይ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያደርጉ ተቋማት በፍጥነት የማመቻቸት ስራ እንደሚሰራ ማረጋገጣቸውን እና በክልሉ መሰረታዊ አገልግሎቶች ቴሌኮሚኒኬሽን እና የኤሌክትሪክ ኃይል ጨምሮ በፍጥነት እንዲመለስ ለማድረግ ቁርጠኝነታቸውን መግለፃቸውን በደስታ ተቀብለዋል።በተጨማሪም ዋና ፀሀፊው የኢትዮጵያ መንግስት የተኩስ አቁሙን አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ ለማመቻቸት ወደ ትግራይ የሚደረግ መደበኛ የተመድ የሰብዓዊ ድጋፍ በረራን ጨምሮ ለግብርና ስራዎች ድጋፍ እንዲሆን ቃል መግባቱን እውቅና ሰጥተዋል።በመጨረሻም ዋና ጸሐፊው ሁሉም ወገኖች የሲቪሎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታቸውን እንዲወጡ፣ ፣ ያልተገደበ የሰብዓዊ ድጋፍ ተደራሽነት እንዲኖር እንዲያደርጉ እንዲሁም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕጎችን ማክበር እንዳለባቸው በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።ጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ ከአንቶኒ ጉተሬዝ ጋር ስላደረጉት የስልክ ውይይት በጠሚ ፅቤት በኩል የተባለ ነገር የለም። ### Response:
### Text: ጀርመን ፍራንክፈርት️ከክቡር የኢፌዲሪ ጠሚ ዶር አብይ አህመድ ጋር ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓም በሚደረገው የውይይት መድረክ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ወደ ጀርመን ፍራንክፈርት መግባት ጀምረዋል፡፡ኢትዮጵያውያኑና በአውሮፓ ከሚገኙ 12 ኤምባሲዎች የተወከሉ ዲፕሎማቶች ፍራንክፈርት እየደረሱ ሲሆን መድረኩ በአንድነት እንነሳ፣ ነገንም እንገንባ በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው፡፡በኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካንአያኖ የሚመራው ብሄራዊ ኮሚቴ ከበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የፍራንክፈርት የቆንስላ ጽቤት እንዲሁም የዳያስፖራ አባላት ጋር በመሆን ለስነስርዓቱ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ኮሚቴው የእስከአሁኑን ዝግጅትና አጠቃላይ ሂደት አስመልክቶ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡የፍራንክፈርቱ ዝግጅት የተሳካ እንዲሆን 200 የበጎ ፍቃድ ሠራተኛ ኢትዮጵያውያን ተሳታፊ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡በሰሜን አሜሪካ ክቡር ጠሚ ዶር አብይ አህመድ ከጥቂት ወራት በፊት ያደረጉት ጉብኝት ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው ይኸው መድረክ የአንድነትና የፍቅር ድልድይ በመገንባቱ የተፈጠረው የህብረት መንፈስ ለአገር ግንባታ ማዋል እንዲቻል ጥሪ ይቀርብበታል ተብሎይጠበቃል፡፡ምንጭ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ### Response:
### Text: የሰላም ሚኒስቴር ከተፈናቃዮች ጋር በተያያዘና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተሰጠው መግለጫ የተነሱ አንኳር ነጥቦች ተፈናቃዮች ከጌዲዮ ብቻ ሳይሆን ከምእራብና ምስራቅ ጉጂም የተፈናቀሉ ዜጎች ነበሩ፡፡ ዜጎቹን ወደ ቀያቸው በጊዜያዊነት ለመመለስ ከእርዳታ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ተሰርቷል፡፡ ለተረጂዎች የሚደርሰው የሰብአዊ እርዳታ እስካሁንም ያልተቋረጠና በቀጣይም የሚቀጥል ነው ከምስራቅ ጉጂ የተፈናቀሉ 13 ሺህ ገደማ የሚሆኑ ዜጎች ብቻ ሲቀሩ ከምእራብ ጉጂ የተፈናቀሉት በሙሉ ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል፡፡ ተፈናቃዮችን በቋሚነት የማቋቋም ስራ ለመስራት 3 አካላት ሀላፊነቱን ወስደዋል፡፡ እነሱም፡ የኦሮሚያ ክልል መንግስት፣ የደቡብ ክልል መንግስትና የፌደራል መንግስት ናቸው፡፡ ተፈናቃዮች በቋሚነት እስኪቋቋሙ ባሉበት ሆነው ሲረዱ ቆይተዋል፡፡ ትናንት በነበረው ውይይት ከተፈናቃዮች ጋር ለ8 ወራት እርዳታ አላገኘንም የተባለው ትክክል አለመሆኑን ተግባብተናል፡፡ ሚድያዎችም ሲዘግቡ በዚህ መንገድ የዘገቡት ትክክል አይደለም። በመሀል በአካባቢው የፀጥታ ችግር ስላለ የተደራጁ ቡድኖች እርዳታውን የመቀማትና ለራስ ጥቅም የማዋል ችግሮች ነበሩ። በአመራር ችግር ምክንያት መድረስ ያለበት መጠን ሳይደርስ የቀረበት ሁኔታዎች ነበሩ። ### Response:
### Text: ነቀምቴ ጥቃት ያደረሰባቸው ሰው ማንነት ገና አልታወቀም። የፀጥታ ሰዎች ግን ክትትል እያደረጉ ነው። ከሰሞኑ ጉዳይ ጋር አይገናኝም አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃኢትዮቴሌኮም የምዕራብ ሪጅን ሥራ አስኪያጅ አቶ ገመቺስ ታደሰ ትናንት ምሽት በመኖሪያ ቤታቸው መገደላቸውን የነቀምት ከተማ ኮምንኬሽን ጽህፈት ቤት ዛሬ አስታውቋል። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃ ለጀርመን ራድዮ ጣቢያ እንደተናገሩት አቶ ገመቺስ የተገደሉት ተተኩሶባቸው ነው ጥቃቱን ፈጽመዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ማንነት ለመለየትም የፀጥታ አካላት ክትትል እያደረጉ ነው። ግድያው ሰሞኑን በኦሮምያ ከተፈጠረው አመረጋጋት ጋር የተያያዘ ስለ መሆን አለመሆኑ የተጠየቁት አቶ ደሳለኝ ግድያው ከሰሞኑ ተቃውሞ ጋር የተያያዘ አይደለም ብለዋል።«ትናንት ማታ የተመቱት ግለሰብ በመሣሪያ ነው የተመቱት። በመኖሪያ ቤታቸው ነው ጥቃቱ የደረሰበት። ጥቃት ያደረሰባቸው ሰው ማንነት ገና አልታወቀም። የፀጥታ ሰዎች ግን ክትትል እያደረጉ ነው። ከሰሞኑ ጉዳይ ጋር አይገናኝም። ከዚሁ ጋር በተገናኘ የተለየ ሰልፍ የወጣ የለም። የተለየ ያሳየው ተቃውሞም የለም።» የነቀምት ከተማን ጨምሮ የወለጋ አራቱም ዞኖች ላለፉት አራት ወራት በወታደራዊ እዝ ኮማንድ ፖስት ስር ናቸው። የጀርመን ድምፅ ራድዮ ### Response:
### Text: መንግስት በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚያቀርበውን ፈሳሽ ዘይት ከውጪ ሊያስገባ ነው፡፡ ዘይቱ ወደ አገር እየተጓጓዘ መሆኑንና እስከ 15 ቀን ድረስ ገብቶ እንደሚከፋፈልም ይጠበቃል፡፡ በየወሩ 33 ሚሊየን ሊትር ፈሳሽ ዘይት እንዲያስገባና እንዲያከፋፍል የተፈቀደለት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት ኢግልድ ዘይቱ ቀደም ብሎ ሲሰራጭ የነበረው እና የረጋው ዘይት በሚከፋፈልበት ዋጋ ለህብረተሰቡ እንደሚቀርብ ለሸገር ኤፍ ኤም 1021 ተናግሯል፡፡በድርጅቱ የሽያጭ ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ደጀኑ ተክለ ማርያም እንደተናገሩት 1 455 ኮንቴነር ፈሳሽ ዘይት ከኢንዶኔዢያ ተገንዘቶ ወደ አገር እየተጓጓዘ ነው፡፡ 30 ሚሊየን ሊትሩ ከሚረጋው ዘይት በደረጃ ከፍ ያለና ፈሳሽ ሲሆን 3 ሚሊዮን ሊትሩ ደግሞ የተጣራ የሱፍ ዘይት መሆኑን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል፡፡ ዘይቱ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች እንደሚከፋፈልም ተሰምቷል፡፡መንግስት በወሰነው መሰረት በየወሩ 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት ከውጪ ተገዝቶ ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ይከፋፈላል፡፡ በቅርቡ 67 በመቶውን እንዲያስመጣና እንዲያከፋፍል የተፈቀደለት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት ፈሳሽ ዘይት ብቻ እንደሚያስገባ ለሸገር ኤፍ ኤም 1021 ተናግሯል፡፡ሸገር ኤፍ ኤም ### Response:
### Text: እንድታውቁት በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ተሳትፎ ውድድሩን በውጤት ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ይገባል፡፡ ቡድኑ በስካይ ላይት ሆቴል አርፎ ነገ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች አቀባበል ይደረግለታል።በአቀባበሉ ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይደረጋሉ ተብሏል።ቡድኑ ከስካይ ላይት ሆቴል ተነስቶ በአጅብ በቦሌ ጎዳና ፣ መስቀል አደባባይ ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፣ ሂልተን ሆቴል ፣ ፓርላማ ፣ አራት ኪሎ ፣ ራስ መኮንን ድልድይ ፣ ፒያሳ ፣ ቸርችል ጎዳና ፣ ቴዎድሮስ አደባባይ፣ ብሔራዊ ቴአትር ፣ ሜክሲኮ አደባባይ ፣ ለገሃር ፣ መስቀል አደባባይ በማድረግ መዳረሻውን ብሔራዊ ቤተመንግስት ያደርጋል፡፡ ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ ነው።የአትሌትክስ ቡድኑ በአጀብ በሚያልፍበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም ከተፈቀደላቸው ተሽከርካሪዎች በስተቀር የተጠቀሱት መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።ወደ ቦሌ አየር መንገድ የሚመጡ መንገደኞችና ሌሎች ተጠቃሚዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ ተላልፏል።መረጃው የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረኃይል ነው። ### Response:
### Text: የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ️የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተለያዩ ዘርፎች ጥፋት የሰሩ የስራ ሀላፊዎችን ለህግ ለማቅረብ የምርመራ ስራውን አበርትቶ መቀጠሉን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ተናገረ፡፡የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ለሸገር እንደተናገረው በመጭዎቹ መቶ ቀናት በተመረጡ ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ምርመራውን ለመቀጠል ውጥን ይዟል፡፡የኢኮኖሚ አሻጥር፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ ገንዘብ በህገወጥ መንገድ ከሃገር ማሸሽ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራባቸዋል ተብለው ከተመረጡ ዘርፎች መካከል ናቸው ብለዋል በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዝናቡቱኑ ፡፡ሥርዓት አልበኝነትን ለመቆጣጠርም አጥፊ የተባሉትን ለይቶም ለህግ ለማቅረብ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የምርመራ ስራውን ማበርታቱን ተናግረዋል፡፡ህገወጥ የሰዎች ዝውውርም ሌላው በ100 ቀኑ እቅድ ምርመራ ተደርጎ አጥፊዎችን ለመያዝ ከሚሰራባቸው ዘርፎች መካከል ነው ተብሏል፡፡ዘርፉ እየተለየ ምርመራ የማድረግና ተጠያቂዎችን ለህግ የማቅረቡ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የ100 ቀን እቅድ አውጥቶ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እየሰራ መሆኑን ተሰምቷል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ለመገናኛ ብዙሃን ዛሬ ዝርዝር መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ምንጭ ሸገር 1021 ### Response: