text
stringlengths
0
200
ሜርክል ይህን አስመልክተዉ ባለፈዉ ታኅሳ ወር እንዲህ ነበር ያሉት በግዳጅ ኚመመለሱ አስቀድሞ በፈቃደኝነት ዚሚመለሱትን እናበሚታታለቜ።
በተቃራኒዉ ኹጋና በርካታ ወጣቶቜ ለትምህርትም ሆነ ለሙያዊ ሥልጠና ወደ ጀርመን እንዲመጡ ሁኔታዎቜ እንዲመቻቹ እንፈልጋለን።
ሕገወጥ ስደተኝነትን መዋጋት ይኖርብናል ሆኖም በአንፃሩ ለወጣቶቜ ሕጋዊ ዕድሎቜ እንዲኚፈቱ እንፈልጋለን።
ጀርመን ዉስጥ በአሁን ወቅት ወደጋና ሊመለሱ ይቜላሉ ዚተባሉ አራት ሺህ ገደማ ተሰዳጆቜ ይኖራሉ።
ዚተመላሜ ስደተኞቜን ሁኔታ ለማመቻ቞ትም አክራ ላይ በጀርመን ትብብር አንድ ማዕኹል ተኚፍቷል።
እንዲያም ሆኖ ዹጋናዉ ፕሬዝደንት ወደጋና ይመለሳሉ ዚተባሉት ማንነት አስቀድሞ እንዲጣራ ጠይቀዋል።
መዝናኛ፩ አዝማሪ ኚያንያን ራድዮ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚቱርክ ሕዝበ ውሳኔ ውጀት ባለፈው እሁድ ቱርክ ያካሄደቜው ህዝበ ውሳኔ ዚቱርክ ፕሬዝዳንት ጠይብ ሬቌፕ ኀርዶሃን ዚሚፈልጉትን ውጀት አስገኝቷል ።
ድምጜ ለመስጠት ኚወጣው ህዝብ በመቶው በቱርክ ህገ መንግሥት ላይ ማሻሻያ እንዲደርግ ተስማምቷል።
ማሻሻያው ዚቱርክን አስተዳደር ኚፓርላሜንታዊ ወደ ፕሬዝዳንታዊ ዚመንግሥት ስርዓት ዹሚቀይር ነው ።
ፕሬዝዳንቱ ቀድሞ ያልነበሚውን ሚኒስትሮቜ ዹመሰዹም በጀት ዚማዘጋጀት እና አብዛኛዎቹን ኹፍተኛ ዳኞቜ ዚመሟም ሥልጣን ያገኛል።
በመቶ ድምፅ ሰጭዎቜ ማሻሻያው ፕሬዝዳንቱ ሥልጣኑን በሙሉ ጠቅለው እንዲይዙ ስለሚያደርግ ህገ መንግሥቱ እንዳለ ይቀጥል ሲሉ ነበር ድምጻ቞ውን ዚሰጡት ።
ኹዚህ ሌላ ህዝቡ ስለ ህዝበ ውሳኔው ምንነት አስቀድሞ በቂ መሹጃ እንዲያገኝ አልተደሹገም ሲሉም ተቜተዋል።
በህገ መንግሥታዊ ማሻሻያ ጥያቄ ላይ ዚተካሄደው ዚሚያዚያ ቱ ህዝበ ውሳኔ በተመጣጣኝ ዚመፎካኚሪያ ሜዳ ላይ አልተካሄደም ።
ድምጜ ሰጭዎቜ ስለ ማሻሻያው ቁልፍ ጉዳዮቜ ገለልተኛ ዹሆነ መሹጃ አልተሰጣ቞ውም።
በሐምሌ ኹኹሾፈው ዹመፈንቅለ መንግሥት ሙኚራ በኋላ ዹተደነገገው ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ለዎሞክራሲያዊ ሂደት ወሳኝ ዹሆኑ መሠሚታዊ ነጻነቶቜን ገድቧል።
ቱርክን ኚአውሮጳ ህብሚት ጋር ካቃቃሯት ጉዳዮቜ አንዱ ዚአውሮፓ ህብሚት አባል ለመሆን ስታካሂድ ዹነበሹው ድርድር መገታት ነው።
ህብሚቱ ሀገሪቱ ማሟላት አለባት ዹሚላቾውን በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያተኮሩ መስፈርቶቜን ለድርድሩ አለመቀጠል አንደ አንድ ምክንያት ይጠቀሳል።
ዚዶቌቬለ ዚኢስታንቡል ዘጋቢ ዶርያን ጆንስ እንዳለው ዚአውሮጳ ታዛቢዎቜ አስተያዚት እና ዚኀርዶሀን ዛቻ በድርድሩ ተስፋ ላይ ተጜእኖ ማሳደሩ አይቀርም።
ዚአውሮጳ ምክር ቀት እና ኩ ኀስ ሲ ኢ ህዝበ ውሳኔው ዚተካሄደበትን መንገድ በጥብቅ አውግዘዋል።
እናም ቱርክ ኀርዶጋን በሥልጣን ላይ እስካሉ ድሚስ ዚአውሮጳ ህብሚት ህብሚት አባል መሆን አትቜልም ዹሚለው አስተሳሰብ በአውሮፓ እንዲሰፍን አድርጓል ።
እንደሚመስለኝ ኚአውሮጳ ህብሚት ጋር ስታካሂድ ዚቆዚቜው ድርድር ወደፊት ዚመራመዱ ተስፋ አናሳ ነው ።
ዹጀርመን ጥምር መንግሥት አካል ዹሆነው ዚክርስቲያን ሶሻል ህብሚት ፓርቲ በምህፃሩ ሊቀመንበር ማንፍሬድ ቬበር ይህን ካሉት ዹጀርመን ፖለቲኚኞቜ አንዱ ና቞ው።
ቱርክ አሁን በአውሮጳ ህብሚት እይታ ዚተሳሳተ መንገድ ለመኹተል ኚመሚጠቜ ኚቱርክ ጋር ያለንን ግንኙነት እንደገና መፈተሜ አለብን ።
ያ ማለት በቱርክ ዚአውሮጳ ህብሚት አባልነት ማመልኚቻ ላይ ዚምናካሂደው ድርድር በሚዥሙ ጊዜ ሊቀጥል አይቜልም።
ለንግግር መቅሚብ ያለበት ዚሁለቱንም ወገኖቜ ጥቅም ዚሚያስጠብቅ አጋርነት ነው።
ይህን መታዘቡን ያሳወቀው ዹጀርመን መንግሥት ክፍፍሉን ለማስወገድ በቱርክፖለቲካዊ ውይይት እንዲካሄድ ጠይቋል።
ይሁንና እና ፕሬዝዳንት ኀርዶሀን ኚድሉ በኋላ ትናንት ባሰሙት ንግግር ማሳሰቢያዎቹን ኚቁብ ዚቆጠሩት አይመስልም ።
ስለ ህዝበ ውሳኔው ዹሚደሹገው ውይይትም ሆነ ውዝግቡ አብቅቷል ትቜቱም መቆም አለበት ብለዋል ።
ዹህዝበ ውሳኔው ውጀት ዚተቃወሙትንም ተመልኚቱ እንዎት ሜንፈታ቞ውን እንደሚያኚበሩ ሲሉ አሹፈውባ቞ዋል።
ምንም እንኳን ኚአንድ በመቶ በላይ በሆነ ድምጜ ቢያሞንፉም ትቜቱ መቆም አለበት ዹሚል እምነት ነው ያላ቞ው።
እናም ፕሬዝዳንቱ በተቃዋሚዎቜ ላይ ጠንኹር ያለ እርምጃ ይወስዳሉ ተብሎ ነው ዚሚጠበቀው።
ጋዜጠኛ ዲርያን እንደሚለው ኀርዶሀን ኚሁለት ዓመት በኋላ ማለትም በጎርጎሮሳዊው በቱርክ ለሚካሄደው ምርጫ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ኹአሁን መንገዱን እያመቻቹ ነው።
ፀሹ አውሮጳ ንግግራ቞ውም ሆነ ዛቻ቞ው በህዝበ ውሳኔ ያጡትን ድምጜ ለማግኘት ዚሚጠቀሙበት ዘዮም ነው ይላል።
ኚቱርክ ብሔሚተኞቜ አብዛኛዎቹ በህዝበ ውሳኔው ልደገፏቾውም ዹሚል ግምት አለ ።
በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ በሚካሄደው ምርጫ ኀርዶሀን ዚብሔሚተኞቜ ድምጜ ያስፈልጋ቞ዋል ።
እናም ዚሞት ቅጣት ተመልሶ ህጋዊ ይሁን አይሁን ዹሚለው ጉዳይ እና በአውሮጳ ህብሚት ላይ ዚሚያነሱት ጥያቄ ዚብሔሚተኞቜን ቀልብ ለመሳብ ይጠቅማቾዋል ።
ግን ጥያቄው እነዚህ ጉዳዮቜ ለህዝበ ውሳኔ ይቀርባሉ ወይ ነው ።
ኚአውሮፓ ምክር ቀትም ሆነ ኚአውሮፓ ዚሰብዓዊ መብቶቜ ምክር ቀትጋር ዚሚኖራት ግንኙነትም ጥያቄ ውስጥ ይገባል።
ስደተኞቜ ወደ አውሮጳ እንዳይገቡ ለመኹላኹል ኚህብሚቱ ጋር ዚደሚሰቜበት ውል ሁለቱን ወገኖቜ ኚሚያስተሳስሯ቞ው ጥቅሞቜ አንዱ ነው ።
ቱርክ ዚአውሮፓ ህብሚት ዋነኛ ዚንግድ አጋር መሆንዋም ሌላው ዚጋራ ጥቅማ቞ው መገለጫ ነው።
ዹነዚህ ትስስሮቜ ዚወደፊት እጣ ምን ሊሆን ይቜላል ዹሚለው አሁንም ማነጋገሩ እንደቀጠለ ነው።
ዚኢትዮጵያ መንግስት ዚቀድሞውን ዚደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት በአዲስ አበባ እንዳይተላለፉ ያገደው ባለፈው እሁድ ነበር፡፡
ዚስፖርት ዘገባ ዓለም አቀፉ ኩሎምፒክ ኮሚ቎ ሩስያን በተመለኹተ ትናንት ያስተላለፈው ውሳኔ ብዙዎቜን አስደምሟል።
ዚሩስያ መንግሥት አትሌቶቹ አበሚታቜ ንጥሚ ነገሮቜን እንዲጠቀሙ ሁኔታዎቜን ሲያመቻቜ በመክሹሙ ቡድኑ ሙሉ ለሙሉ ኚሪዮ ኩሎምፒክ ሊታገድ ይቜላል ተብሎ ነበር።
ዚቱር ደ ፍሯንስ ብስክሌት ሜቅድምድም በብሪታንያዊው ክሪስ ፍሮም ድል ተጠናቋል።
በሜዳ ቎ኒስ ዚሞንትሪያል ውድድር ሎሬና ዊሊያምስ ለሊስት ጊዜያት ያሞነፈቜበት ውድድር ላይ አትካፈልም።
ዚአውስትራሊያ ዹኩሎምፒክ ቡድን ወደ ሪዮ ዹኩሎምፒክ መንደር እንደማይገባ አስታወቋል።
በፖላንዱ ዓለም አቀፍ ዚታዳጊዎቜ አትሌቲክስ ፉክክር ኢትዮፕያ ዚሊስተኛ ደሹጃን አገኘቜ።
ዓለም አቀፉ ዹኩሎምፒክ ኮሚ቎ ሩስያ ሙሉ ለሙሉ ኚሪዮ ኩሎምፒክ ትታገድ ዹሚለውን ሐሳብ ውድቅ አድርጓል።
ሐሳቡ ዹቀሹበው በዓለም አቀፉ ጾሹ አበሚታቜ ንጥሚ ነገር ተኚታታይ ተቋም በእንግሊዝኛ ምኅጻሩ ነበር።
እያንዳንዱ አትሌት በውድድሩ ላይ መሳተፍ አለያም አለመሳተፉን በተመለኹተ ዓለም አቀፍ ፌዎሬሜኖቜ በተናጠል ሊወስኑ ይቜላሉ ብሏል።
ብዙአዚሁ ዋጋው ዹዓለም አቀፍ ዚአትሌቲክስ ፌዎሬሜኖቜ ማኅበርን ጚምሮ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ እና ዹሀገር ውስጥ መገናኛ አውታሮቜ ዘጋቢ ነው።
በሩስያ ጉዳይ ዓለም አቀፍ ዚስፖርት ተቋማቱ ወዲህ እና ወዲያ ዚማለታ቞ውን ምክንያት እንዲህ ያብራራል።
ይህን ዚተናገሩት ዚሩስያ ኩሎምፒክ ኮሚ቎ ኃላፊ አሌክሳንደር ዙኮቭ መሆናቾውን አር ስፖርት ዹዜና ምንጭ ዘግቧል ሲል ሮይተርስ አክሎ ጠቅሷል።
በፖላንድ ቢድጎቺቜ ኹተማ ለ ቀናት ዹተኹናወነው ዚታዳጊዎቜ ዹዓለም አትሌቲክስ ውድድር ትናንት ተጠናቋል።
ዕድሜያ቞ው ኹ ዓመት በታቜ ዹሆኑ አትሌቶቜ በሚሳተፉበት ውድድር ኢትዮጵያ ዹወርቅ ዚብር እና ዚነሀስ በአጠቃላይ ሜዳሊያዎቜን በማግኘት ኬንያን ተኚትላ ሊስተኛ ወጥታለቜ።
ዹወርቅ ዚብር እና ዚነሀስ በአጠቃላይ ሜዳሊያዎቜ ሰብስባ ዩናይትድ ስ቎ትስ አንደኛ ወጥታለቜ።
ስዋንሲ ሲቲ ደግሞ ዹ ዓመቱ ዊልፍሬድ ቩኒን ኚማን቞ስተር ሲቲ ሊያስፈርም እዚተነጋገሚ መሆኑን ሰንዮይ ኀክስፕሚስ ዹተሰኘው ጋዜጣ አትቷል።
቞ልሲ በቅርቡ ያስፈሚመው ንጎሎ ካን቎ በሚቀጥለው ዚጚዋታ ክፍለ ጊዜ ዚሚለብሰው ሰባት ቁጥር መለያ ሰጥቶታል።
ዚማርሎዩ ዹክንፍ ተጚዋቜ ጌኊርጌስ ኬቪን ንኮዱ ለቶትንሀም ለመፈሹም ጫፍ ላይ መድሚሱን ኢንዲፔንደት ዘግቧል።
ሊቹርፑል ለአውሮጳ ሊግ ኚስፔኑ ሎቪያ ጋር በተጫወተበት ወቅት ደጋፊዎቹ ርቜቶቜን እዚተኮሱ በመበጥበጣ቞ው ፓውንድ መቀጣቱ ተገልጧል።
ዚደጋፊዎቜ ብጥብጡ ዹተኹሰተው ኚሁለት ወራት በፊት ዚስዊዘርላንድ ባዝል ኹተማ ውስጥ ነበር።
ብስክሌት ብሪታንያዊው ክሪስ ፍሮም በቱር ደ ፍሯንስ ዚብስክሌት ሜቅድምድም ኛ እና ዚመጚሚሻ ዙር ውድድር አጠቃላይ አሾናፊ ሆነ።
ክሪስ ዘንድሮ ዚውድድሩ አጠቃላይ አሾናፊ ሲሆን ለሊስተኛ ጊዜ ነው።
አሜሪካዊው ላንስ አርምስትሮንግ ውጀቶቹን በመነጠቁ ክሪስ ፍሮም ኚስፔናዊው ሚጉዌል ኢንዱራይን ቀጥሎ ውጀቱን በማስጠበቅ ሁለተኛ ነው።
ለ ተኚታታይ ጊዜያት አሾናፊ ዹነበሹው አሜሪካዊው ላንስ አርምስትሮንግ አጠቃላይ ውጀቶቹ ዚተሰሚዙበት አበሚታቜ ንጥሚ ነገር መጠቀሙን በማመኑ ነበር።
ስፔናዊው ሚጉዌል ኢንዱራይንእንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር ኹ አንስቶ ለአምስት ተኚታታይ ዓመታት ዚቱር ደ ፍሯንስ ዚብስክሌት ሜቅድምድም አሾናፊ ጠንካራ ተወዳዳሪ ነው።
ዚዘንድሮውን ጚምሮ ለሊስት ዓመታት ባለድል ዹሆነው ዚብሪታንያው ክሪስ ፍሮሜሚጉዌል ላይ ለመድሚስ እዚገሰገሰ ነው።
ምናልባት ጥንካሬው በዚሁ ኹቀጠለ እና በተኚታታይ ካሞነፈ በ ዓመቱ ስፔናዊውን በመብለጥ ክብርወሰኑን ይሰብር ይሆናል።
ለ ዚተለያዩ ቀናት በተኹናወነው ዚቱር ደ ፍሯንስ ዚብስክሌት ሜቅድምድም አጠቃላይ ውጀት ኢትዮጵያዊው ጜጋቡ ገብሚማርያም ኹ ተወዳዳሪዎቜ ዹ ኛ ደሹጃን አግኝቷል።
ጜጋቡ ለመጀመሪያ ጊዜ በቱር ደ ፍሯንስ ያስመዘገበው ውጀት እጅግ ዚሚበሚታታ ነው።
ዚኀርትራው ናትናኀል ብርሃኔ ኛ ደሹጃን ሲያገኝ ሌላኛው ዚኀርትራ ተወዳዳሪ ዳንኀል ተክለ ሃይማኖት ኛ በመውጣት ጠንካራ ብስክሌተኛነቱን አስመስክሯል።
ሎሬና ኚውድድሩ ዚወጣቜው ትኚሻዋ ላይ በደሚሰባት ጉዳት መሆኑን ዚውድድሩ አዘጋጆቜ ገልጠዋል።
በእሁዱ ዚሐንጋሪ ግራንድ ፕሪ ሜቅድምድም ሐሚልተን ሰአት ኹ ደቂቃ ኹ ሰኚንድ በማጠናቀቅ መሪነቱን አስጠብቋል።
በፌራሪ ተሜኚርካሪው ዚሚወዳደሚው ዚፊንላንዱ አሜኚርካሪ ኪም ሬይኚነን በ ነጥቡ አራተኛ ደሹጃ ላይ ይገኛል።
አሜሪካዊቷ ሎሬና ዊሊያምስ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ዚስደተኞቜ ቡድን በኩሎምፒክ ይሳተፋል።
በስደተኞቜ ቡድን ኚታቀፉት አትሌቶቜ መካኚል ዹ ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ማራቶን ሯጭ ዮናስ ኪዳኔ ይገኝበታል።
ዮናስ ካለፉት አምስት ዓመታት አንስቶ ነዋሪነቱን በአውሮጳ ሉግዘምበርግ አድርጓል።
ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ ጀርመን ውስጥ ያደሚገውን ውድድርም ሰአት ኹ ደቂቃ በማጠናቀቅ ብርቱ ተፎካካሪ መሆኑን አሳይቷል።
ዚአውስትራሊያ ዹኩሎምፒክ ቡድን ዚብራዚሏ ሪዮ ዹኩሎምፒክ መንደር ዚጥራት ደሹጃውን ዹጠበቀ አይደለም በሚል አትሌቶቹ መንደሩ ውስጥ እንደማይቆዪ አስታወቀ።
ፍሳሜ በአግባቡ ዚማያስተላልፉ መጞዳጃ ቀቶቜ እና ዚሚያንጠባጥቡ ቧንቧዎቜ መገኘታ቞ው አውስትራሊያ ወደ ኩሎምፒክ መንደሩ ላለመሄድ ምክንያት እንደሆናት አስታውቃለቜ።
ኹ ዓመት በታቜ ዚኢትዮጵያ ፕሪሚዚር ሊግ ዚፍጻሜ እና ዹደሹጃ ውድድሮቜ ዚፊታቜን ቅዳሜ እንደሚኚናወኑ ዚኢትዮጵያ ስፖርት ፌዎሬሜን በኢሜል በላኹው መልእክት ገልጧል።
ዹጀርመን እግር ኳስ ፌዎሬሜን ዚቀድሞው ፕሬዚዳንት ቮልፍጋንግ ኒርስባኅ ኹማንኛውም ዚእግር ኳስ እንቅስቃሎ ለአንድ ዓመት ታገዱ።
ሆኖም አብዛኛዎቹ ጀርመን እንድትቀበላ቞ው ዹጠዹቁ አመልካ቟ቜ ዚመኖሪያ ፈቃድ ዚማግኘት እድላ቞ው አነስተኛ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ ዚሚኚታተሉ ባለሞያዎቜ ይናገራሉ ።
ጀርመን ውስጥ ካለ ህጋዊ ዚመኖሪያ ፈቃድ ዹሰቀቀን ህይወት በመግፋት ላይ ዹሚገኙም ጥቂት አይደሉም ።
ለዚህም ድርጅቱ በዋነኛ ምክንያትነት ያቀሚበው ዚሶሪያውን ዚርስ በርስ ጊርነት ነው ።
ኚሶሪያና ኚሌሎቜ ሃገራት ተሰደው በ በኢንዱስትሪ በበለፀጉት ሃገራት ጥገኝነት እንዲሰጣ቞ው ያመለኚቱ ስደተኞቜ ቁጥር ኹ ሺህ በላይ ነው ።
በዓመቱ ጀርመን ጥገኝነት እንዲሰጣ቞ው ያመለኚቱ ስደተኞቜ ወደ ሺህ ይጠጋሉ ።
ዩናይትድ ስ቎ትስ ሁለተኛውን ደሹጃ ስትይዝ ዚጥገኝነት ማመልኚቻ ያስገቡት ቁጥር ሺህ ነው ።
ዹጀርመን ዹተገን አሰጣጥ ሂደት ቢያንስ አንድ ዓመት ወይም ደግሞ ኚዚያ በላይ ዚሚወስድ በመሆኑ ኚአመልካ቟ቹ ምን ያህሉ ጀርመን እንደሚቆዩ አይታወቅም ።
ዚአብዛኛው ተገን ጠያቂዎቜ ምርጫ ጀርመን ዚሆነበት ምክንያት እያነጋገሚ ነው ።
አብዛኛዎቹ በሌላ ዚአውሮፓ ህብሚት አባል ሃገር ዚተመዘገቡ ናቾው ።
እዚያም አብዛኛዎቹ ተገን ጠያቂዎቜ እስኚመኖራ቞ው ዚተሚሱ በአግባቡም ያልተያዙና ዚሃገራቱ ስደተኞቜ አቀባበል ስርዓት ዹተኹተለ አይደለም ።
ኚምክንያቶቹ አንደኛው በአውሮፓ ህብሚት ህግ መሰሚት አንድ ተገን ጠያቂ ጉዳዩ መታዚት ያለበት መጀመሪያ በገባበት ሃገር መሆኑ ነው ።
ዹጀርመን ዹውጭ ዜጎቜና ዚስደተኞቜ ጉዳይ መሥሪያ ቀት ጀርመን እንድትቀበላ቞ው ዚሚያመለክቱ ተገን ጠያቂዎቜን ወደ መጡበት ለመመለስ ዚተቻለውን ሁሉ ይሞክራል ።
በተለይ ዚተሻለ አያያዝ አላቾው ተብለው ኚሚታሰቡት ሃገራት ዚሚመጡት ሰዎቜ ማመልኚዎቜ ተቀባይነት ያለማግኘት እድላ቞ው ኹፍተኛ ነው ።
በሜሶቪክ እምነት በ ጀርመን ኚደሚሷት ሺህ ዹተገን ጠያቂዎቜ ማመልኚቻዎቜ አብዛኛዎቹ በቀደመው በ ዓም ጥያቄአ቞ው ውድቅ ዚተደሚገባ቞ው ስደተኞቜ ማመልኚቻዎቜም ናቾው ።
ጥቂት ዚማይባሉም ዚፖለቲካ ጭቆና ወይም ኢሰብዓዊ ቅጣቶቜ አይፈፀሙባ቞ውም ለህይወት አስጊ አይደሉም ኚሚባሉ ዚባልካን አገራት ነው ዚመጡት ።
ዹጀርመን መንግሥት ኹነዚህ ሃገራት ዚሚሰደዱትን ሰዎቜ ማመልኚቻ቞ውን በቀላሉ ውድቅ ለማድሚግ ዚሚሚዳውን ህግ እያሚቀቀ ነው ።