text
stringlengths
0
200
አሁን ዚፌደራል ጀርመን መንግስት ኚምዕራብ ባልካን ሃገራት ዚመጡ ስደተኞቜ ላስገቧ቞ው ዚጥገኝነት ማመልኚቻዎቜ መልስ መስጠት ዚሚቜልበትን ሹቂቅ ህግ እያዘጋጀ ነው ።
ዹዚህ ህግ ዓላማ ሰርቢያ ቊስኒያና ሌሎቜ ሃገራትን ዹተሹጋጉና አስተማማኝ ኚሚባሉ ሃገራት ዝርዝር ውስጥ ማስገባት ነው ።
ይህ ኹተደሹገም ኹነዚህ ሃገራት ዚሚመጡ ዹተገን ጥያቄ ማመልኚቻዎቜን ወዲያውኑ ውድቅ ለማድሚግ ይቻላል ።
ለስደተኞቜ መብት ተቆርቃሪው ድርጅት ምክትል ሃላፊ ቀርንት ሜሶቪክ ይህ ትርጉም ዚለሜ አሰራር ነው ይላሉ ።
ጀርመን ተገን እንዲሰጣ቞ው ኚሚጠይቁት መካኚል ዚተሻለ እድል ያላ቞ው ሶሪያውያን ናቾው ።
በጥብቅ መስፈርት ተመርጠው እስካሁን ጀርመን ዚገቡት ግን ብቻ ናቾው ።
ኹዚህ በተጚማሪም በሌሎቜ መንገዶቜ ጀርመን ዚገቡ ዚሶሪያ ስደተኞቜ ጥገኝነት እንዲሰጣ቞ው አመልክተዋል ።
ዚሶሪያ ስደተኞቜ ጀርመን ኚሚገኙት ተገን ጠያቂዎቜ ኹፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ ።
ዹተገን ጠያቂዎቹ ብዛትና ጀርመን ልትቀበል ቃል ዚገባቜው ዚሶሪያ ስደተኞቜ ቁጥር ዚሚመጣጠን አይደለም ።
ሁሌም ወደነርሱ ዚምንጠቁማባ቞ው ሌሎቹ ቁጥሩ ሊታመን ዚማይቜል ስደተኛ ጫንቃ቞ው ላይ ተጭኗል ።
ኹኛ በኀኮኖሚ እጅግ ደካማ በሆኑ ጎሚቀት ሃገራ ኚሁለት ሚሊዮን ዚሚበልጡ ስደተኞቜ አሉ ።
እኛ ደግሞ ምን ማድሚግ እንቜላለን ብለን ራሳቜንን መጠዹቅ አለብን ።
አንዳንድ ጀርመናውያን አስተያዚት ሰጭዎቜ ጀርመን ስደተኞቜ በብዛት ኚተቀበለቜ ጫናው ይኚብዳታል ሲሉ ስጋታ቞ውን ይገልፃሉ ።
ሪኮቭስኪ ግን ለዚህ መልስ ዚሚሰጡት እጎአ ኹ እስኚ በተካሄደው ዚቊስኒያ ጊርነት ወቅት ጀርመን ዚተቀበለቻ቞ውን ስደተኞቜ ብዛት በማስታወስ ነው ።
በወቅቱ ጀርመን ግጭት ኚተኚሰተበት ኹዚህ አካባቢ ኹ ሺህ በላይ ስደተኞቜን ተቀብላለቜ ።
ይህ አሃዝ ሪኮቭስኪ እንዳሉት በ ጀርመን ተገን እንድትሰጣ቞ው ኚጠዚቁት ስደተኞቜ በሶስት እጥፍ ይበልጣል ።
በሌላ በኩል ጀርመን ህጋዊ ሰነድ ዹሌላቾው ሺህ ዚሚደርሱ ዹውጭ ዜጎቜ ዚሚገኙባትም ሃገር ናት ።
ኚዛሬ ነገ ወደ ሃገራቜን እንባሚራለን ኹሚል ስጋት ጋር ዚሚኖሩት እነዚህ ሰዎቜ በሃገሪቱ ምንም መበት ዹላቾውም ።
ማርያ ኚአንድ ቊታ ወደ ሌላ ስትንቀሳቀስ ጥንቃቄ ተለይቷት አያውቅም ።
ባቡር ኚተሳፈሚቜ ትክክለኛውን ቲኬት ይዛ ነው መንገድ ስታቋርጥ እንኳን መኪና ዹለም ብላ ቀይ መብራት ጥሳ አታልፍም ።
በቀን ሰዓት ወለልና መፀዳጃ ቀቶቜን በምታጞዳበት ዚስራ ቊታዋ እሚፍት አታውቅም ።
በቂ ደሞዝ ባታገኝም ሁሌም በሰዓቱ በሥራ ገቊታዋ ላይ ዚምትገኝ አንድም ቀን አመመኝ ብላ ዚማታውቅ ታታሪ ሎት ነበሚቜ ።
ዋናው ባቡር ጣቢያ ስትደርስ እንደ አጋጣሚ ፖሊሶቜ ዚሰዎቜን ህጋዊነት ለማሚጋገጥ መታወቂያ ሲጠይቁ ትደርሳለቜ ።
ማርያ ባለፉት ዓመታት ያለ ህጋዊ ሰነድ ነበርና ዚምትኖሚው ተፈላጊውን ማስሚጃ ማቅሚብ አልቻለቜም ።
በዚህ አጋጣሚ ዚተያዘቜው ዚአንዲት ልጅ እናት ማርያ ኹልጅዋ ጋር ወደ ሃገርዋ ተጠርዛ ተልካለቜ ።
ልጅዋንና ርስዋን በህክምና ይሚዱ ቩን ዹሚገኝ ዚግብሚ ሰናይ ድርጅት ባልደሚቊቜ ጀርመንን ለቃ ኚመሄዷ በፊትም ተሰናብታ቞ዋለቜ ።
ዚድርጅቱ ምክትል ሃላፊ ኡልሪሜ ኮርትማን በጀርመን ዚማርያን መሰል ህይወት ዹሚገፉ ስደተኞቜ ህይወት አስ቞ጋሪ መሆኑን ያስሚዳሉ።
ግን በድብቅ መኖር ግዎታዋ ነበር ያልተኚፈለበት ዚመጓጓዣ ቲኬት በባቡር ውስጥ ይዞ መገኘት ኹሃገር እስኚመባበሚር ዚሚያደርስ ትልቅ አደጋ አለው ።
እናም ዘወትር እያዛለሁ ወይም ተቆጣጣሪዎቜ ይደርሱብናል በሚል ስጋት ይኖራሉ ።
ለህክምና አገልግሎት ዹሚሆን ገንዘብ ዹላቾውም ጀርመን ውስጥ ያለ ገንዘብ ምንም ማድሚግ አይቻልም ።
ወይዘሮዋ እና ሌሎቜ ባልደሚቊቻ቞ው ስደተኞቹን ሊሚዷ቞ው ኹሚፈልጉ ሃኪሞቜ ጋር ያገናኟ቞ዋል ።
ዚመኖሪያ ፈቃድ ዹሌላቾውም ሰዎቜ ዹህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድሚግ እንፈልጋለን ።
ዚዛሬ ዓመታት ሲመሰሚት ይህን ያህል እድሜ ይኖሹዋል ዹሚል ግምትም አልነበሹም ።
በግብሚ ሰናዩ ድርጅት ስር በልዩ ልዩ ዹህክምና ዘርፎቜ አገልግሎት ዚሚሰጡ ዶክተሮቜ ታቅፈዋል ።
እነዚህ ሃኪሞቜ ዚጀና ኢንሹራንስ ዹሌላቾውን ሰነድ አልባ ስደተኞቜ ያክማሉ ።
ዚድርጅቱ ምክትል ሃላፊ ኡልሪሜ ኮርትማን እንደሚሉት አንዳንዎ ዚስደተኞቹ ዚጀና ቜግር ኚባድ ኹሆነ መንግስት አስተያዚት ሊያደርግላ቞ው ይቜላል ።
በተግባር እስካሁን እንደታዚው ኚባድ ህመም ያለባ቞ው ሰዎቜ ኹሃገር እንዲወጡ አይገደዱም ።
እነዚህ ስደተኞቜ በአንድ አጋጣሚ በተቆጣጣሪዎቜ እጅ ኹወደቁ ዚማርያ እጣ ሊገጥማ቞ው ይቜል ይሆናል ።
ዹ መልዕክቶቻቜሁን በ ፃፉልን ኀሚላቜን ነው በስልክ መልዕክት መተው ዚምትፈልጉ ደግሞ ቁጥራቜን ነው ።
ዓለም ኢትዮጵያውያን ሐጃጆቜ በሳዑዲ አሚቢያ ዚኢድ አል አደሐ አሹፋ በዓል በነገው ዕለት ይኚበራል።
ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ ለመላው ዚእስልምና ዕምነት ተኚታዮቜ ዚእንኳን አደሚሳቜሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ኢትዮጵያውያን ሐጃጆቜ በሳዑዲ አሚቢያ ዚኢድ አል አደሐ አሹፋ በዓል በነገው ዕለት ይኚበራል።
ሳዑዲ አሚቢያ ዹሚገኘው ነብዩ ሲራክ ደግሞ ዚዕምነት ግዎታ቞ውን ሊወጡ መንገድ ዚገቡ ሐጃጆቜን አነጋግሯል።
ዚሁለት ሀገራት ምርጫ ታሕሳስ ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሪያዉያን አቆጣጠር ነዉ ጋምቢያዎቜ ዚወደፊት ፕሬዝደንታ቞ዉን መሚጡ።
ዚምርጫዉ ሒደት ዉጀት አንድነት ተቃርኖዉ ያፍታ ዝግታቜን ትኩሚት ነዉ።
መልኹዓ ምድራዊ ካርታዋን ትኩር ብሎ ያዚ ዚብሪታንያ እና ዚፈሚንሳይ ቅኝ ገዢዎቜ ሜኩቻ ዉጀት መሆንዋን ለማወቅ ሌላ ምርምር አይጠይቀዉም።
ካርታዉን ኚባሕሩ ወደ ምድሩ ሲመለኚቱ በቀድሞዋ ዚፈሚንሳይ ቅኝ ተገዢ ሮኔጋል ላይ ያሚፈ ዚአንድ እግር ፈለግ ትመስላለቜ።
ወይም አካሉን ባሕር ዉስጥ ደብቆ መላሱን ሮኔጋል ላይ ዹጎለገለ ሰዉ ወይም እንስሳ።
ሮኔጋል ራስዋን ደሚቷ ላይ አስደግፋ እግሯን ባሕሩ ዉስጥ ነክራ ዹተቀሹ አካሏን በሁለት ክንዶቜዋ ታቅፋ ዚምታጥባት ሕፃን ትመስላለቜ።
ጋና በቆዳ ስፋትም በሐብትም በሕዝብ ብዛትም ጋምቢያን ኚአስር ጊዜ በላይ ታጥፋታለቜ።
ዚቀድሞዋ ዹወርቅ ጠሹፍ ጎልድ ኮስት ዹ ሚሊዮኖቜ ሐገር ናት።
ጋና ቀደም ጋምቢያ ኹተል ብለዉ ሁለቱም በ ዎቹ ኹቅኝ ገዢያ቞ዉ ነፃ ወጡ።
ሥለ ነፃነት ገድል ድል ታሪካ቞ዉ ሲያወሩ ጋናዎቜ ክዋሚ ንኩሩማን ይዘክራሉ።
ጋናዎቜ በመፈንቅለ መንግሥት በአመፅ ሁኚት ሲተራመሱ ጋሚቢያዎቜ በዚአምስት ዓመቱ እንዎ መሪ እና እንደራሎዎቻ቞ዉን እዚመሚጡ ቀዝቃዛዉን ጊርነት ዘመን ተሻገሩ።
በሁሉም ምርጫ ዚሚያሞንፈዉ ግን ዳዋድ ጃዋራ ዚሕዝብ ዕድገት ያሉት ፓርቲያ቞ዉ ነበር።
ዚጋምቢያ ሕዝብ በጣሙን ጩር ሐይሉ ብዙ ዘግይቶ ኹጋና እና ኚብዙዎቹ ዚአፍሪቃ ሐገራት ዹተማሹዉን ገቢር አደሚገ።
ዚመጀመሪያዉን መፈንቅለ መንግስት ዚመሩት መቶ አለቃ ያሕያ አብዱል አዚዝ ጄሙስ ጁንኩንግ ጃሜሕ ዚትሺቱ ሐገር ሁለተኛ መሪ ሆኑ።
ምክንያቱም ይሕ ኹመላዉ ዓለም በጣም ግልፅና ዹማይጭበሹበር ምርጫ ነዉ።
ምርጫ እንዲደሚግ ዹወሰነዉም ዚሚመራቜሁን ሰዉ ማንነት ዚምትወስኑት እናንት ዚጋምቢያ ሕዝብ በመሆናቜሁ ነዉ።
ተቃዋሚዬ በአንድ ድምፅ እንኳን ቢበልጠኝ ምርጫዉ ነግልፅ እስኚሆነ ድሚስ ዉጀቱን እቀበላለሁ።
ዚምርጡኝ ዘመቻዉ ዚተፎካካሪዎቜ አሰላለፍ ዚድምፅ አሰጣጡ ሒደትም ታዛቢዎቜ እንደመሰኚሩት ዚጋምቢያም ዹጋናም ተመሳሳይ ነበር።
እንደ ምርጫዉ ጊዜ ሁሉ ዉጀቱ ቀደሞ ዚታወጀዉ ግን ኚባንጁል ነበር።
ኹተሰጠዉ ድምፅ ዉን ድምፅ በማግኘት አዳማ ቊሮዉ ዚጋምቢያ ሪፐብሊክን በፕሬዝደትነት እንዲያገለግሉ መመሚጣ቞ዉን አስታዉቃለሁ።
ጃሜሕ ቀተ መንግሥት ዚገቡበትን ስምንተኛ ዓመት ሲያኚብሩ ፖለቲካ ዚማያዉቁት ዚዕድሜ አቻ቞ዉ ያሁን ተቀናቃኛቾዉ ወደ ብሪታንያ ተሰደዱ።
ዚድሮ ዚሐገራ቞ዉ ቅኝ ገዢዎቜ ያሉ ያደሚጓ቞ዉ ወይም ያደሚጉላ቞ዉ አይታወቅም።
ድላ቞ዉ ሲታወጅ ደግሞ ኚትራምፕ በላይ አስደናቂ ዉጀት እያሉ አደነቋ቞ዉ።
ዚፖለቲካ ተንታኞቜ ባሮዉን ዹ ዓመቱን አምባ ገነን ገዢ ያንበሚኚኩ ዹማይደፈሹዉን ዚደፈሩ እያሉ አወደሷ቞ዉ።
ትንሺቱ ዓመት በአምባገነን ዚብሚት ጡንቻ ስትገዛ ዚኖሚቜዉ ጋምቢያ ያስተናገደቜዉ ምርጫ በቅርቡ ዩናይትድ ስ቎ትስ ኹተደሹገዉ ምርጫም ዚበለጥ ሜግግር ነዉ ዚሚመስለዉ።
ዚምዕራባዉያንን መርሕ ባደባባይ በማጋለጥ በመዝለፍ መሳደብ ዚሚበልጥ እና በቅርቡ ዘመን ዚሚቀድማ቞ዉ ኚነበሚ።
ዚምዕራባዉያን ጃሜሕን ዹሚጠሉ ዜጎቻ቞ዉ ለዉጥ ዹፈለጉ ምናልባትም ዚአዳማ ባሮዉን ትኩሚት መሳብ ዚሚሹ ሁሉ እንጂ።
በፌስታ ፈንጠዝያዉ መሐል ጋምቢያዊዉ አንጋፋ ድምፃዊ ጃሊብ ኩያ቎ሕ ባንድ ወቅት ሐገሬን ስጠራ አፍሬ ነበር አለ።
ባንጁል ዹ ዓመት ገዢዎቜዋን አንገት አስደፍታ አሞናፊዎቜን ሥታስቊርቅ አክራ ዚምርጫ ዉጀትዋን አወጀቜ።
አሁን በሥልጣን ላይ ያሉትን ፕሬዝደንት ጆን ድራማኒ ማሐማን በኹፍተኛ ዚድምፅ ልዩነት አሞነፉ።
ዚአኩፎ አዶ ደጋፊ አድናቂዎቜ በተገኘዉ ዉጀት መፈንደቅ መቩሹቃቾዉ አልቀሚም።
ፍንደቃ ቡሚቃዉ ግን እንደ ጋምቢያዎቜ ተሾናፊዉን በማዉገዝ መዝለፍ መወሹፍ ላይ ያተኮሚ አልነበሚም።
ስለዚሕ አዲሱ መሪ በጋራ ሆነን እንድንታገል ዚሚያስተባብሚን መሆን አለበት።
ያም ሆኖ ሁሉም ተመሳሳይ መልዕክት ወይም አቋም አለዉ ማለት አይደለም።
ጋና ጋምቢያ ናጄሪያ ሆነ ኢትዮጵያ ለመጥፎ ይሁን ለጥሩ ዚአብዛኛዉን ሕዝብ አስተሳሰብ ዹሚቀርፁ ዚሚቀይሱ አቅጣጫ ዚሚያመለክቱትም አንድም መሪዎቹ ሁለትም አዋቂዎቹ ና቞ዉ።
አሞናፊነታ቞ዉ በታወጀ በሳልስቱ ዹ ዓመቱን ገዢ ያስጠነቅቁ ያሳሰቡ ለማዘዝም ይንጠራሩ ገቡ።
በሥልጣን ላይ ያለዉ መንግሥት ዚፖለቲካ እስሚኞቹን መፍታት አለበት አሉ።
ይሕን ካደሚጋቜሁ ሥልጣን ስትለቁ ጥሩ ዚንግድ ምልክት ትታቜሁ ትሔዳላቜሁ።
በስልጣን ላይ ያለዉን መንግስት ባለሥልጣናት ፍርድ ቀት እንደሚያቀርቡ ዛቱ።
ጋምቢያ በጃሜሕ ዘመን ዚገባባቻ቞ዉን ዓለም አቀፍ ዉሎቜ ዳግም እንደሚያጀኑት አስታወቁ።
ጃሜሕ አሁንም ሥልጣን ላይ መሆናቾዉን ዘነጉት መሰለኝ አሉ ዚባንጁል ነዋሪ።
ጋናዎቜ ኚተሞናፊዎቜ ጋር ሰላማዊ ዚሥልጣን ሜግግር ለማድሚግ እንደሚመክሩ ሲያስታዉቁ ዚጋምቢያ ምርጫ ዉጀት ዚወለፊንድ ባሚቀ።
ዹ ዓመቱ ገዢ ተቀናቃኛቾዉ በአንዲት ድምፅ ቢበልጣ቞ዉ እንኳን ዉጀቱን ለመቀበል ቃል ዚገቡት ጃሜሕ ዚምርጫዉን ዉጀት ዉድቅ አደሚጉት።
በተመድ ዹዹመን ዹሰላም መልክተኛ ኢስማኢል ኊልድ ቌክ ሚቡዕ ዕለት በሰጡት መግለጫ በዹመን ተቀናቃኞቜ መካኚል ያለዉ ልዩነት ዹሰፋ ነዉ።
አሳሳቢዉ ዹዹመን ሁኔታ ዳግም ለሰላም ለድርድሩ ለመቀመጥ ተስፋ አይታይም በዹመን በአዹርና በምድር ዹሚደሹገዉ ጊርነት ተባብሶ ቀጥሎአል።
በሌላ በኩል ዹዹመኑን ጊርነት አልፈዉ ወደ ስዑድ አሚብያ ዚሚገቡት ኢትዮጵያዉያን ቁጥር ጥቂት እዳልሆነ በጅዳ ዹሚገኘዉ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ገልፆልናል።
በተመድ ዹዹመን ዹሰላም መልክተኛ ኡልድ ቌክ አህመድ በዹመን በአዹርም ሆነ በመሪት ለመሪት ዉግያዉ ተጠናክሮ መቀጠሉን ትናንት በሰጡት መግለጫ አዉግዘዋል።
እንደ ኡልድ ቌክ አህመድ ኚሁለቱም ዹዹመን ተቀናቃኝ ኃይሎቜ በኩል ዚተኩስ አቁም ስምምነት ለማድሚግ ምንም ዓይነት ጥሚትም ሆነ ፍንጭ አይታይም።
ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እንደገለፀዉም ዹዹመን ሁኔታ ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚተባባሰ መጥቶአል።
በዹመን ዚዚርስ በርሱን ጊርነት አልፈዉ ወደ ርያድ ዚሚገቡ ዚኢትዮጵያዉያን ስደተኞቜ ቁጥርም ኹፍተኛ መሆኑን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ገልጟልናል።
ዹዹመንን ቀዉስ እዚተባባሰ ነው ሲሉ ዚመንግሥታቱ ድርጅት ዚሰብዓዊ ጉዳዮቜ ተጠሪ ስ቎ፈን ብሪይን በሳምንቱ መጀመርያ ላይ አስጠንቅቀዋል።
በአማራ ክልል ዚኊሮሞ ብሔሚሰብ አስተዳደር ደግሞ በዞኑ ዚተደራጀና ዚታጠቀ ኃይል ፈፅሞ ዹለም ባይ ነው።
ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በሰሜን ሾዋ ዞን አጣዚ አካባቢ በተፈጠሹው ግጭት ሰዎቜ መገደላቾውና መቁሰላቾው ተነግሯል፡፡
ዹሰሜን ሾዋ ዞን አስተዳደር አጣዚን ለማጥቃት ዹተዘጋጀ እና ዚተደራጀ ኃይል በኊሮሞ ብሔሚሰብ አስተዳደር ውስጥ አለ ይላል።
ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በሰሜን ሾዋ ዞን አጣዚ አካባቢ በተፈጠሹው ግጭት ሰዎቜ መሞታ቞ውና መቁሰላቾውን አመራሮቹ ለዶይቌ ቬለ ተናግሚዋል፡፡
አፍሪቃ አሞባብ ላይ ያነጣጠሚው ዚኬንያ በቀል ዚኬንያ መንግስት ዚዳዳብ ዚስደተኞቜ መጠለያ ጣቢያን ሊዘጋ መሆኑን ዹጀርመን ዹዜና ወኪል ዘገበ።
በጣቢያው ዹሚገኙ ኹ ሺ በላይ ዚሶማሊያ ስደተኞቜ ዚአሞባብ ታጣቂ ቡድን ወደ ማይገኝባ቞ው ዚሶማሊያ ግዛቶቜ እንዲመለሱ ይደሹጋል ተብሏል።