text
stringlengths
4
267
በመሆኑም ዘባህ እና ጻልሙና “ዹሰው ማንነት ዚሚለካው በኃይሉ ስለሆነ አንተው ራስህ ተነስና ግደለን” አሉት። በመሆኑም ጌድዮን ተነስቶ ዘባህን እና ጻልሙናን ገደላ቞ውፀ በግመሎቻ቞ው አንገት ላይ ዚነበሩትንም ዚሩብ ጹሹቃ ቅርጜ ያላ቞ው ጌጣጌጊቜ ወሰደ።
ኹጊዜ በኋላም ዚእስራኀል ሰዎቜ ጌድዮንን “ኚምድያማውያን እጅ ስለታደግኚን አንተ፣ ልጆቜህና ዹልጅ ልጆቜህ ግዙን” አሉት።
ጌድዮን ግን “እኔ አልገዛቜሁምፀ ልጄም ቢሆን አይገዛቜሁም። ዚሚገዛቜሁ ይሖዋ ነው” አላ቞ው።
ኚዚያም ጌድዮን “አንድ ነገር ልጠይቃቜሁፊ እያንዳንዳቜሁ በምርኮ ካገኛቜሁት ላይ ዚአፍንጫ ሎቲዎቜን ስጡኝ” አላ቞ው። (ምክንያቱም ድል ዚሆኑት ሕዝቊቜ እስማኀላውያን ስለነበሩ ዹወርቅ ዚአፍንጫ ሎቲዎቜ ነበሯ቞ው።)
እነሱም “በደስታ እንሰጣለን” አሉት። ኚዚያም መጎናጞፊያ አነጠፉፀ እያንዳንዱም ሰው በምርኮ ካገኘው ውስጥ ዚአፍንጫ ሎቲውን እዚያ ላይ ጣለ።
ዚሩብ ጹሹቃ ቅርጜ ካላ቞ው ጌጣጌጊቜ፣ ኚአንገት ሐብል ማጫወቻዎቜ፣ ዚምድያም ነገሥታት ይለብሷ቞ው ኚነበሩት ቀይ ሐምራዊ ቀለም ዚተነኚሩ ዚሱፍ ልብሶቜ እንዲሁም በግመሎቹ ላይ ኚነበሩት ዚአንገት ጌጊቜ በተጚማሪ እንዲሰጡት ዹጠዹቃቾው ዹወርቅ ዚአፍንጫ ሎቲዎቜ ክብደት 1,700 ዹወርቅ ሰቅል ነበር።
ጌድዮንም በወርቁ ኀፉድ ሠራፀ ሰዎቜ እንዲያዩትም በኹተማው በኊፍራ አስቀመጠውፀ እስራኀላውያንም በሙሉ በዚያ ኚእሱ ጋር መንፈሳዊ ምንዝር ፈጞሙፀ ኀፉዱም ለጌድዮንና ለቀተሰቡ ወጥመድ ሆነ።
በዚህ መንገድ ምድያማውያን ለእስራኀላውያን ተገዙፀ ኚዚያ በኋላም ተገዳድሚዋ቞ው አያውቁምፀ በጌድዮን ዘመን ምድሪቱ ለ40 ዓመት አሚፈቜ።
ዚዮአስ ልጅ ዚሩባአልም ወደ ቀቱ ተመልሶ በዚያ መኖሩን ቀጠለ።
ጌድዮንም ብዙ ሚስቶቜ ስለነበሩት 70 ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩት።
በሎኬም ዚነበሚቜው ቁባቱም ወንድ ልጅ ወለደቜለትፀ እሱም ስሙን አቢሜሌክ አለው።
ዚዮአስ ልጅ ጌድዮንም ዕድሜ ጠግቩ ሞተፀ ዚአቢዔዜራውያን በሆነቜው በኊፍራ በሚገኘው በአባቱ በዮአስ መቃብር ተቀበሚ።
እስራኀላውያን ጌድዮን ኹሞተ ብዙም ሳይቆይ እንደገና ኚባአል ጋር መንፈሳዊ ምንዝር ፈጞሙፀ ባአልበሪትንም አምላካ቞ው አደሚጉት።
እስራኀላውያንም በዙሪያ቞ው ኚነበሩት ጠላቶቻ቞ው ሁሉ እጅ ዚታደጋ቞ውን አምላካ቞ውን ይሖዋን አላስታወሱምፀ
እንዲሁም ዚሩባአል ዚተባለው ጌድዮን ለእስራኀል ያደሚገውን ጥሩ ነገር ሁሉ አስበው ለቀተሰቡ ታማኝ ፍቅር አላሳዩም።
መሳፍንት ፍትሕን ያስፈጜሙ በነበሚበት ዘመን በምድሪቱ ላይ ሚሃብ ተኚሰተፀ አንድ ሰው ኚሚስቱና ኚሁለት ወንዶቜ ልጆቹ ጋር ዚባዕድ አገር ሰው ሆኖ ለመኖር በይሁዳ ኚምትገኘው ኚቀተልሔም ተነስቶ ወደ ሞዓብ ምድር አቀና።
ዹሰውዹው ስም ኀሊሜሌክ፣ ዚሚስቱ ስም ናኊሚ፣ ዚሁለቱ ወንዶቜ ልጆቹ ስም ደግሞ ማህሎን እና ኪሊዮን ነበር። እነሱም በይሁዳ በምትገኘው በቀተልሔም ዚሚኖሩ ኀፍራታውያን ነበሩ። ወደ ሞዓብም መጥተው በዚያ መኖር ጀመሩ።
ኹጊዜ በኋላም ዹናኩሚ ባል ኀሊሜሌክ ሞተፀ ስለሆነም ናኩሚ ኚሁለት ልጆቿ ጋር ቀሚቜ።
በኋላም ልጆቿ ሞዓባውያን ሎቶቜን አገቡፀ ዹአንደኛዋ ስም ዖርፋ፣ ዹሌላኛዋ ደግሞ ሩት ነበር። በዚያም ለአሥር ዓመት ያህል ኖሩ።
ኚዚያም ሁለቱ ወንዶቜ ልጆቿ ማህሎንና ኪሊዮን ሞቱፀ ናኩሚም ሁለት ልጆቿንና ባሏን አጥታ ብቻዋን ቀሚቜ።
እሷም በሞዓብ ምድር ሳለቜ ይሖዋ ለሕዝቡ እህል በመስጠት ፊቱን ወደ እነሱ እንደመለሰ ስለሰማቜ ኚምራቶቿ ጋር ወደ አገሯ ለመመለስ ኚሞዓብ ተነሳቜ።
ኚሁለቱ ምራቶቿም ጋር ትኖርበት ዹነበሹውን ቊታ ትታ ሄደቜ። ወደ ይሁዳ ምድር ለመመለስ ወደዚያ ዚሚወስደውን መንገድ ይዘው እዚሄዱ ሳሉም
ናኩሚ ሁለቱን ምራቶቿን እንዲህ አለቻ቞ውፊ “ሂዱ፣ ሁለታቜሁም ወደ እናቶቻቜሁ ቀት ተመለሱ። ለሞቱት ባሎቻቜሁና ለእኔ ታማኝ ፍቅር እንዳሳያቜሁ ሁሉ ይሖዋም ለእናንተ ታማኝ ፍቅር ያሳያቜሁ።
ይሖዋ በዚባላቜሁ ቀት ያለስጋት እንድትኖሩ ያድርጋቜሁ።” ኚዚያም ሳመቻ቞ውፀ እነሱም ድምፃ቞ውን ኹፍ አድርገው ማልቀስ ጀመሩ።
እንዲህም አሏትፊ “በፍጹም! ኚአንቺ ጋር ወደ ወገኖቜሜ እንሄዳለን።”
ናኩሚ ግን እንዲህ አለቻ቞ውፊ “ልጆቌ፣ ተመለሱ። ለምን ኚእኔ ጋር ትሄዳላቜሁ? ለእናንተ ባሎቜ ሊሆኑ ዚሚቜሉ ወንዶቜ ልጆቜ አሁንም ልወልድ ዚምቜል ይመስላቜኋል?
ልጆቌ፣ ተመለሱ። እኔ እንደሆነ በጣም ስላሚጀሁ ኚእንግዲህ ባል ላገባ አልቜልምፀ ስለዚህ ሂዱ። ዛሬ ማታ ባል ዚማግኘትና ልጆቜ ዚመውለድ ተስፋ ቢኖሚኝ እንኳ
እስኪያድጉ ድሚስ ትጠብቃላቜሁ? እነሱን በመጠበቅስ ባል ሳታገቡ ትቆያላቜሁ? ልጆቌ፣ ይሄማ አይሆንምፀ ዹይሖዋ እጅ በእኔ ላይ ስለተነሳ ዚእናንተን ሁኔታ ሳስብ ሕይወቮ መራራ ይሆንብኛል።”
እነሱም እንደገና ድምፃ቞ውን ኹፍ አድርገው አለቀሱፀ ኚዚያም ዖርፋ አማቷን ስማ ተሰናበተቻት። ሩት ግን ኚእሷ ላለመለዚት ዚሙጥኝ አለቜ።
ናኩሚም “ተመልኚቜ፣ መበለት ዚሆነቜው ዚባልሜ ወንድም ሚስት ወደ ወገኖቿና ወደ አማልክቷ ተመልሳለቜ። አብሚሻት ተመለሜ” አለቻት።
ሩት ግን እንዲህ አለቻትፊ “ኚአንቺ እንድለይና ትቌሜ እንድመለስ አትማጞኚኝፀ እኔ እንደሆነ ወደምትሄጂበት እሄዳለሁፀ በምታድሪበት አድራለሁ። ሕዝብሜ ሕዝቀ፣ አምላክሜም አምላኬ ይሆናል።
በምትሞቺበት እሞታለሁፀ በዚያም እቀበራለሁ። ኚሞት በቀር ኚአንቺ ዹሚለዹኝ ቢኖር ይሖዋ አንዳቜ ነገር ያምጣብኝፀ ኚዚያም ዹኹፋ ያድርግብኝ።”
ናኊሚ፣ ሩት ኚእሷ ጋር ለመሄድ እንደቆሚጠቜ ስታውቅ መወትወቷን አቆመቜ።
ኚዚያም ወደ ቀተልሔም ጉዟቾውን ቀጠሉ። ቀተልሔም እንደደሚሱም በእነሱ ምክንያት መላ ኹተማዋ ታመሰቜፀ ሎቶቹም “ይህቜ ናኩሚ አይደለቜም እንዎ?” ይሉ ነበር።
እሷም እንዲህ ትላ቞ው ነበር፩ “ናኩሚ ብላቜሁ አትጥሩኝ። ሁሉን ቻይ ዹሆነው አምላክ ሕይወቮን መራራ አድርጎታልና ማራ ብላቜሁ ጥሩኝ።
ኹዚህ ስወጣ ሙሉ ነበርኩፀ ይሖዋ ግን ባዶ እጄን እንድመለስ አደሚገኝ። ይሖዋ ተቃውሞኝና ሁሉን ዚሚቜለው አምላክ መኚራ አምጥቶብኝ ሳለ ለምን ናኩሚ ብላቜሁ ትጠሩኛላቜሁ?”
እንግዲህ ናኩሚ ምራቷ ኚሆነቜው ኚሞዓባዊቷ ሩት ጋር ኚሞዓብ ምድር ዚተመለሰቜው በዚህ ሁኔታ ነበር። ቀተልሔም ዚደሚሱትም ዚገብስ አዝመራ መሰብሰብ በጀመሚበት ወቅት ነበር።
ኚዚያም አማቷ ናኩሚ እንዲህ አለቻትፊ “ልጄ ሆይ፣ መልካም ይሆንልሜ ዘንድ ቀት ልፈልግልሜ አይገባም?
ቩዔዝ ዘመዳቜን አይደለም? አብሚሻ቞ው ዚነበርሜው ወጣት ሎቶቜ ዚእሱ ና቞ው። ዛሬ ማታ በአውድማው ላይ ገብስ ያዘራል።
ስለዚህ ተነስተሜ ተጣጠቢና ሰውነትሜን ጥሩ መዓዛ ያለው ዘይት ተቀቢፀ ኚዚያም ልብስሜን ለባብሰሜ ወደ አውድማው ውሚጂ። ሰውዹው በልቶና ጠጥቶ እስኪጚርስ ድሚስ እዚያ መኖርሜን እንዲያውቅ ማድሚግ ዚለብሜም።
ሲተኛም ዚሚተኛበትን ቊታ ልብ ብለሜ እዪፀ ኚዚያም ሄደሜ እግሩን ገልጠሜ ተኚ። እሱም ምን ማድሚግ እንዳለብሜ ይነግርሻል።”
እሷም “ያልሜኝን ሁሉ አደርጋለሁ” አለቻት።
ስለዚህ ሩት ወደ አውድማው በመውሚድ ሁሉንም ነገር ልክ አማቷ እንዳዘዘቻት አደሚገቜ።
ቩዔዝም ኹበላና ኚጠጣ በኋላ ልቡ በደስታ ተሞላ። ኚዚያም ሄዶ ዹተቆለለው እህል አጠገብ ተኛ። ሩትም በቀስታ መጥታ እግሩን ገልጣ ተኛቜ።
እኩለ ሌሊትም ሲሆን ቩዔዝ እዚተንቀጠቀጠ ኚእንቅልፉ ባነነፀ ቀና ሲልም አንዲት ሎት እግሩ ሥር ተኝታ ተመለኚተ።
እሱም “ለመሆኑ አንቺ ማን ነሜ?” አላት። እሷም መልሳ “እኔ አገልጋይህ ሩት ነኝ። መቀዠት ዚሚገባህ አንተ ስለሆንክ መጎናጞፊያህን በአገልጋይህ ላይ ጣል” አለቜው።
በዚህ ጊዜ እንዲህ አላትፊ “ልጄ ሆይ፣ ይሖዋ ይባርክሜ። ሀብታምም ሆኑ ድሃ፣ ወጣት ወንዶቜን ተኚትለሜ ባለመሄድሜ ኚበፊቱ ይልቅ አሁን ያሳዚሜው ታማኝ ፍቅር በለጠ።
ስለዚህ ዚእኔ ልጅ፣ አትፍሪ። አንቺ ምግባሚ መልካም ሎት መሆንሜን ዹኹተማው ሰው ሁሉ ስለሚያውቅ ያልሜውን ሁሉ አደርግልሻለሁ።
እኔ መቀዠት እንዳለብኝ ዚማይካድ ቢሆንም ኚእኔ ይልቅ ዚቅርብ ዘመድ ዹሆነ መቀዠት ዚሚቜል ሰው አለ።
ዛሬ እዚሁ እደሪፀ ሲነጋም ሰውዬው ዚሚቀዥሜ ኚሆነ፣ መልካም! እሱ ይቀዥሜ። ሊቀዥሜ ዹማይፈልግ ኹሆነ ግን ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ እኔው ራሎ እቀዥሻለሁ። እስኚ ማለዳ ድሚስ ግን እዚሁ ተኚ።”
በመሆኑም እስኪነጋ ድሚስ እግሩ ሥር ተኛቜፀ ኚዚያም ጎህ ቀዶ ሰውን በውል መለዚት ዚሚያስቜል ብርሃን ኚመውጣቱ በፊት ተነሳቜ። እሱም “አንዲት ሎት ወደ አውድማው መጥታ እንደነበር ማንም አይወቅ” አለ።
በተጚማሪም “ዚለበስሜውን ኩታ ዘርግተሜ ያዢው” አላት። ስትዘሚጋለትም ስድስት መስፈሪያ ገብስ ሰፈሚላትና አሞኚማትፀ በኋላም ወደ ኹተማ ሄደ።
እሷም ወደ አማቷ ሄደቜፀ አማቷም “ልጄ ሆይ፣ እንዎት ሆነልሜ?” አለቻት። ሩትም ሰውዹው ያደሚገላትን ሁሉ አንድ በአንድ ነገሚቻት።
እንዲሁም “‘ወደ አማትሜ ባዶ እጅሜን አትሂጂ’ ብሎ ይህን ስድስት መስፈሪያ ገብስ ሰጠኝ” አለቻት።
በዚህ ጊዜ ናኩሚ እንዲህ አለቻትፊ “ልጄ ሆይ፣ ኹዚህ በኋላ ቁርጡ እስኪታወቅ ድሚስ ዝም ብለሜ ተቀመጪፀ ምክንያቱም ሰውዹው ዛሬውኑ ለጉዳዩ እልባት ሳያበጅ ዝም ብሎ አይቀመጥም።”
ናኩሚ በባሏ በኩል ሀብታም ዹሆነ ዚቅርብ ዘመድ ነበራትፀ ይህ ሰው ቩዔዝ ዚሚባል ሲሆን ዚኀሊሜሌክ ቀተሰብ ነበር።
ሞዓባዊቷም ሩት ናኩሚን “እባክሜ ወደ እርሻ ቊታዎቹ ልሂድና ሞገስ ዚሚያሳዚኝ ሰው ካገኘሁ እህል ልቃርም” አለቻት። ናኩሚም “ልጄ ሆይ፣ ሂጂ” አለቻት።
ሩትም ሄደቜፀ በማሳውም ውስጥ ኚአጫጆቹ ኋላ እዚተኚተለቜ መቃሹም ጀመሚቜ። እንደ አጋጣሚ ሆኖ ዚገባቜው ዚኀሊሜሌክ ቀተሰብ ወደሆነው ወደ ቩዔዝ እርሻ ነበር።
በዚህ ጊዜ ቩዔዝ ኚቀተልሔም መጣፀ አጫጆቹንም “ይሖዋ ኚእናንተ ጋር ይሁን” አላ቞ው። እነሱም “ይሖዋ ይባርክህ” ብለው መለሱለት።
ኚዚያም ቩዔዝ ዚአጫጆቹ አለቃ ዹሆነውን ወጣት “ይህቜ ወጣት ዹማን ነቜ?” ሲል ጠዚቀው።
ዚአጫጆቹ አለቃ ዹሆነው ወጣትም እንዲህ በማለት መለሰ፩ “ወጣቷ፣ ናኩሚ ኚሞዓብ ምድር ስትመለስ አብራት ዚመጣቜ ሞዓባዊት ነቜ።
እሷም ‘እባክህ፣ ኚአጫጆቹ ኋላ እዚተኚተልኩ ዚወደቁትን ዛላዎቜ መቃሹም እቜላለሁ?’ አለቜኝ። ይኾው ወደዚህ ኚመጣቜበት ኚጠዋት አንስቶ ወደ ዳሱ ገብታ ጥቂት አሹፍ እስካለቜበት እስካሁን ድሚስ አንዮም እንኳ ቁጭ አላለቜም።”
ኚዚያም ቩዔዝ ሩትን እንዲህ አላትፊ “ልጄ ሆይ፣ ስሚኝ። ለመቃሹም ወደ ሌላ እርሻ አትሂጂፀ ዚትም አትሂጂፀ ኚወጣት ሎት ሠራተኞቌም አትራቂ።
ዚሚያጭዱበትን ማሳ እያዚሜ አብሚሻ቞ው ሂጂ። ወጣቶቹም ወንዶቜ እንዳይነኩሜ አዝዣ቞ዋለሁ። ውኃ ሲጠማሜ ወደ እንስራዎቹ ሄደሜ ወጣቶቹ ቀድተው ካስቀመጡት ጠጪ።”
እሷም መሬት ላይ በግንባሯ ተደፍታ በመስገድ “እኔ ዚባዕድ አገር ሰው ሆኜ ሳለሁ በፊትህ ሞገስ ላገኝ ዚበቃሁትና ትኩሚት ልትሰጠኝ ዚቻልኚው እንዎት ነው?” አለቜው።
ቩዔዝም እንዲህ ሲል መለሰላትፊ “ባልሜ ኹሞተ በኋላ ለአማትሜ ያደሚግሜላትን ሁሉ እንዲሁም አባትሜን፣ እናትሜንና ዘመዶቜሜ ዚሚኖሩበትን አገር ትተሜ ቀድሞ ወደማታውቂው ሕዝብ እንዎት እንደመጣሜ በሚገባ ሰምቻለሁ።
ላደሚግሜው ሁሉ ይሖዋ ብድራትሜን ይመልስልሜፀ በክንፎቹ ሥር ለመጠለል ብለሜ ወደ እሱ ዚመጣሜበት ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ሙሉ ዋጋሜን ይክፈልሜ።”
እሷም መልሳ “ጌታዬ ሆይ፣ እኔ ኚሎት አገልጋዮቜህ አንዷ ባልሆንም እንኳ ስላጜናናኞኝና እኔን አገልጋይህን በሚያበሚታታ መንገድ ስላነጋገርኚኝ ምንጊዜም በፊትህ ሞገስ ላግኝ” አለቜው።
ዚምግብ ሰዓትም ሲደርስ ቩዔዝ “ወደዚህ ቀሚብ በይፀ ዳቊ ወስደሜ ብዪፀ ዚቆሚስሜውንም ሆምጣጀ ውስጥ አጥቅሺ” አላት። በመሆኑም ኚአጫጆቹ ጋር ተቀመጠቜ። እሱም ቆሎ ዘግኖ ሰጣትፀ እሷም እስክትጠግብ ድሚስ በላቜፀ ዹተወሰነም ተሚፋት።
ለመቃሹም በተነሳቜ ጊዜም ቩዔዝ ወጣቶቹን ወንዶቜ እንዲህ ሲል አዘዛቾው፩ “ኚታጚዱት ዛላዎቜ ላይ እንኳ ሳይቀር ትቃርምፀ ምንም እንዳትበድሏት።
ኚታሰሚው ነዶ ላይም ዹተወሰኑ ዛላዎቜን እዚመዘዛቜሁ ጣሉላትና ትቃርምፀ ማንም እንዳይኚለክላት።”
እሷም እስኚ ማታ ድሚስ ስትቃርም ቆዚቜ። ዚቃሚመቜውንም ገብስ በወቃቜው ጊዜ አንድ ዚኢፍ መስፈሪያ ያህል ሆነ።
እህሉንም ይዛ ወደ ኹተማ ሄደቜፀ አማቷም ምን ያህል እንደቃሚመቜ አዚቜ። በተጚማሪም ሩት በልታ ኚጠገበቜ በኋላ አስተርፋ ያመጣቜውን ምግብ አውጥታ ለአማቷ ሰጠቻት።
በዚህ ጊዜ አማቷ “ዛሬ ዚቃሚምሜው ዚት ነው? ዚትስ ስትሠሪ ዋልሜ? ትኩሚት ዚሰጠሜ ሰው ዚተባሚኚ ይሁን” አለቻት። እሷም “ዛሬ ስሠራ ዚዋልኩት ቩዔዝ በተባለ ሰው እርሻ ውስጥ ነው” በማለት ኹማን ጋር ስትሠራ እንደዋለቜ ለአማቷ ነገሚቻት።
ናኩሚም ምራቷን “ለሕያዋንም ሆነ ለሙታን ታማኝ ፍቅሩን ኚማሳዚት ወደኋላ ዹማይለው ይሖዋ ይባርኚው” አለቻት። አክላም “ሰውዹው ዘመዳቜን ነው። ኚሚቀዡን ሰዎቜ አንዱ ነው” አለቜ።
ኚዚያም ሞዓባዊቷ ሩት “ደግሞም ‘ወጣቶቹ ሠራተኞቌ አዝመራዬን በሙሉ ሰብስበው እስኪጚርሱ ድሚስ ኚእነሱ አትራቂ’ ብሎኛል” አለቻት።
ናኩሚም ምራቷን ሩትን “ልጄ ሆይ፣ ወደ ሌላ እርሻ ብትሄጂ ሊተናኮሉሜ ስለሚቜሉ ኚእሱ ሎት ሠራተኞቜ ጋር አብሚሜ መሆን ይሻልሻል” አለቻት።
ስለዚህ ሩት ዚገብሱ አዝመራና ዚስንዎው አዝመራ ተሰብስቊ እስኪያልቅ ድሚስ ኹቩዔዝ ሎት ሠራተኞቜ ሳትርቅ ስትቃርም ቆዚቜ። ኚአማቷም ጋር መኖሯን ቀጠለቜ።
ኚዚያም ቩዔዝ ወደ ኹተማዋ በር ሄዶ በዚያ ተቀመጠ። በዚህ ጊዜ ቩዔዝ ቀደም ሲል ጠቅሶት ዹነበሹው ዚሚቀዠው ሰው በዚያ ሲያልፍ ተመለኚተ። ቊዔዝም “እገሌ፣ አንዮ ወደዚህ ናፀ እዚህ ተቀመጥ” አለው። ሰውዹውም መጥቶ ተቀመጠ።
ኚዚያም ቩዔዝ ኹኹተማዋ ሜማግሌዎቜ መካኚል አሥር ሰዎቜ አምጥቶ “እዚህ ተቀመጡ” አላ቞ው። እነሱም ተቀመጡ።
ቩዔዝም ዚሚቀዠውን ሰው እንዲህ አለው፩ “ኚሞዓብ ምድር ዚተመለሰቜው ናኩሚ ዚወንድማቜንን ዚኀሊሜሌክን ዚእርሻ ቊታ ልትሞጠው ነው።
ስለዚህ ጉዳዩን ለአንተ ላሳውቅህና እንዲህ ልልህ አሰብኩፊ ‘እዚህ በተሰበሰቡት ነዋሪዎቜና በአገሬ ሜማግሌዎቜ ፊት ግዛው። ልትቀዠው ዚምትፈልግ ኹሆነ ተቀዠው። ልትቀዠው ዚማትፈልግ ኹሆነ ግን ንገሹኝና ልወቀውፀ ምክንያቱም በቅድሚያ ዚመቀዠት መብት ያለህ አንተ ነህፀ እኔ ደግሞ ኹአንተ ቀጥሎ ነኝ።’” ሰውዹውም “ልቀዠው ፈቃደኛ ነኝ” አለ።
ኚዚያም ቩዔዝ “መሬቱን ኹናኩሚ በምትገዛበት ቀን ውርሱ በሟቹ ስም እንዲጠራ ለማድሚግ ዚሟቹ ሚስት ኚሆነቜው ኚሞዓባዊቷ ሩት ላይም መግዛት እንዳለብህ እወቅ” አለው።
ዚሚቀዠውም ሰው “ዹገዛ ርስ቎ን አደጋ ላይ ልጥል ስለምቜል ልቀዠው አልቜልም። እኔ ልቀዠው ስለማልቜል በእኔ ዚመቀዠት መብት ተጠቅመህ አንተ ለራስህ ተቀዠው” አለው።
በጥንት ዘመን በእስራኀል ውስጥ በነበሹው ልማድ መሠሚት ኚመቀዠት መብትም ሆነ ይህን መብት ለሌላ ሰው ኚማስተላለፍ ጋር በተያያዘ ማንኛውም ዓይነት ስምምነት ዚሚጞድቀው አንድ ሰው ጫማውን አውልቆ ለሌላው ወገን ሲሰጥ ነበርፀ በእስራኀል ውስጥ አንድ ውል ዹሚጾናው በዚህ መንገድ ሲኚናወን ነበር።
በመሆኑም ዚሚቀዠው ሰው ቩዔዝን “አንተ ለራስህ ግዛው” በማለት ጫማውን አወለቀ።
ኚዚያም ቩዔዝ ለሜማግሌዎቹና ለሕዝቡ ሁሉ እንዲህ አለ፩ “ዚኀሊሜሌክ ዹሆነውን ሁሉ እንዲሁም ዚኪሊዮንና ዹማህሎን ዹሆነውን ሁሉ ኹናኩሚ ለመግዛቮ ዛሬ እናንተ ምሥክሮቜ ናቜሁ።
በተጚማሪም ዚሟቹ ስም ኚወንድሞቹ መካኚል እንዲሁም ኚሚኖርባት ኹተማ በር እንዳይጠፋ ዚሟቹን ስም ዳግም በርስቱ ለማስጠራት ዹማህሎን ሚስት ዚሆነቜውን ሞዓባዊቷን ሩትን ሚስት አድርጌ ወስጃታለሁ። ለዚህም እናንተ ዛሬ ምሥክሮቜ ናቜሁ።”
በዚህ ጊዜ በኹተማዋ በር ላይ ዚነበሩት ሰዎቜ ሁሉና ሜማግሌዎቹ እንዲህ አሉ፩ “እኛ ምሥክሮቜ ነን! ይሖዋ ወደ ቀትህ ዚምትገባውን ሚስት ዚእስራኀልን ቀት እንደገነቡት እንደ ራሔልና እንደ ሊያ ያድርጋት። አንተም በኀፍራታ ዹበለጾግክ ሁንፀ በቀተልሔምም መልካም ስም አትርፍ።
እንዲሁም ይሖዋ ኚዚህቜ ወጣት ሎት በሚሰጥህ ዘር አማካኝነት ቀትህ ትዕማር ለይሁዳ እንደወለደቜለት እንደ ፋሬስ ቀት ይሁን።”
በመሆኑም ቩዔዝ ሩትን ወሰዳትፀ ሚስቱም ሆነቜ። ኚእሷም ጋር ግንኙነት ፈጞመፀ ይሖዋም እንድትፀንስ አደሚጋትፀ ወንድ ልጅም ወለደቜ።
ሎቶቹም ናኩሚን እንዲህ አሏትፊ “ዛሬ ዚሚቀዥ ሰው ያላሳጣሜ ይሖዋ ይወደስ። ስሙም በእስራኀል ይታወጅ!
ዚምትወድሜና ኚሰባት ወንዶቜ ልጆቜ ዚምትበልጥብሜ ምራትሜ ዚወለደቜው ስለሆነ እሱ ሕይወትሜን ዚሚያድስ ይሆናልፀ በእርጅናሜም ዘመን ይጊርሻል።”
ናኩሚም ልጁን ወስዳ አቀፈቜውፀ ትንኚባኚበውም ጀመር።
ኚዚያም ጎሚቀቶቿ ዹሆኑ ሎቶቜ ስም አወጡለት። እንዲሁም “ለናኩሚ ወንድ ልጅ ተወለደላት” አሉፀ ስሙንም ኢዮቀድ አሉት። እሱም ዚዳዊት አባት ዹሆነው ዚእሎይ አባት ነው።
እንግዲህ ዚፋሬስ ዚትውልድ ሐሹግ ይህ ነው፩ ፋሬስ ኀስሮንን ወለደፀ
ኀስሮንም ራምን ወለደፀ ራምም አሚናዳብን ወለደፀ
አሚናዳብም ነአሶንን ወለደፀ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደፀ
ሰልሞንም ቩዔዝን ወለደፀ ቩዔዝም ኢዮቀድን ወለደፀ
ኢዮቀድም እሎይን ወለደፀ እሎይም ዳዊትን ወለደ።